#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ወደ መኪናዬ ሽምጥ እየሮጥሁ ሳለ ነበር፣ የንስሐ አባቴን እንኳን
እንዳልተሰናበትኋቸዉ ያወቅሁት፡፡ እንደ ልማዴ በጥድፊያ ወደ ሲራክ፯ አሽከረከርኩ። መቼም ከባልቻ የተደበቀ ነገር የለም፡፡ እሱን አግኝቼ እስከማማክረዉ ድረስ ትንፋሼን እንኳን ወደ ዉስጥ መሳብ አልሆነልኝም፡፡ ቸኩያለሁ። አይደርሱት የለም ደረስሁና ቢሮዉን በርግጄ ስገባ፣ ባልቻ በወንበሩ ላይ ለጠጥ ብሎ እንቅልፍ አሸልቦት አገኘሁት።
በተለይም የሲራክ ፯ ዋና ኃላፊ ከሆነ በኋላ የግል መኖሪያ ቤቱን አይቶት የሚያዉቅ አይመስለኝም። ዉሎዉም አዳሩም እዚሁ ሆኗል። እዚሁ ምግብ ያስመጣል፣ እዚሁ ወንበሩ ላይ ትንሽ ዕረፍት ያደርጋል። ከስንት አንድ ወደ ዉጪ ቢወጣ እንኳን ምክንያቱ ለዚሁ ለሲራክ ጉዳይ ብቻ
ነዉ፡፡
“ባልቻ!” ብዬ ስጮህበት፣ ብርግግ ብሎ ብድግ አለልኝ።
“ዉብርስት?” አለ ተጨናብሶ፣ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ፡፡
“እሰይ! ‹ዉብርስት?” አልሁት፣ ልጃለሜ የሚለዉ ቁልምጫዉ
መቅረቱ ከንክኖኝ፡፡ እኔ ደግሞ ከእሱ ብቻ ሳይሆን ከማንም ቁልምጫ የለመድሁ ሰዉ ነኝ። ቁልምጫዉን ሳይቀር እንደገና በሚያቆላምጥ ቤተሰብ መሀል ነዉ ያደግሁት። ያዉም ዉብዬዋ፣ ‹ዉቤዋ፣ የኔ ዉብ፣ ዓለሜዋ፣ ‹ልጃለሜ› እየተባልሁ። ባልቻ እንዲሁ እንደ ወረደ በስሜ ጠርቶኝ ካለማወቁ የተነሳ፣ ስሜን ሁሉ የሚያዉቀዉ አይመስለኝም
ነበር። ትዝ ሲለኝ እኔ ራሴ ባልቻ ብዬ ነዉ የጠራሁት ለካ። «አባታለም» የሚለዉ ቁልምጫዬስ? የት ተዉሁት?
“ይኸዉ መጣሽ። በስንት ጊዜሽ? ስደዉል ሳታነሺ፣ ሳስጠራሽ ሳትመጪ፣ ስፈልግሽ ሳትገኘ፤ ዛሬ ምን አመጣሽ በይ?”
“እሸቴ ጠፍቷል”
“ጠፋ? ማን እፍ ብሎት ይሆን በናትሽ? ቀድሞስ በርቶ ኖሯል እንዴi” ሲል አላገጠብኝ፡፡
“ማላገጥህ ነዉ?”
“ራስሽ ከመሀል ጀመርሽዋ! እኔና አንቺ እኮ ገና እንደገና መተዋወቅ
አለብን። ቆይ የት አዉቅሻለሁ? አንቺ ታዉቂኛለሽ?”
“በማርያም አባታለም? ፈርቻለሁ። እሽቴ በመንግሥት ደኅንነቶች እጅ
ወድቆ እንዳይሆን ልቤ ሰግቷል”
“እና ምናገባኝ እኔን?”
“ኧረ ባዛኝቱ? እንዴት ነዉ የማያገባህ፤ እሽቴ እኮ ነዉ!”
"የሆነስ እንደሆነ!”
“አዉቃለሁ አሳዝኜሃለሁ። ለዚያም እንዴ ት ይቅርታ መጠየቅ እንዳለብኝ አላዉቅም። ቢሆንም ግን በዚህ መሀል እሸቴ በጨካኞች እጅ ወድቆ
ከሆነ አያሳዝንህም?”
“ያሳዝነኛል”
“እኮ አንድ ነገር አድርጋ”
“ምን ላድርግ?”
“የማታስፈልገዉ?”
“እሺ። አስፈልጌ ሳገኘዉስ?”
“ያንተን አላዉቅም። እኔ ግን ተንበርክኬ ይቅርታ እለምነዋለሁ”
“ለምን?”
“ስለሚገባዉ”
“እሺ። መጀመሪያ ግን እንስማማ”
“ንገረኝ በምን?”
“ተንበርክከሽ የምትጠብቀዉ ከሆነና፣ ተሳክቶልኝ ካገኘሁት ደግሞ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ቃል ከገባሽልኝ.…”
“ይኼዉ!” ብዬ ጉልበቴ ግዉ እስከሚል ድረስ ወድቄ ተንበረከክሁ፡፡
“ብቻ አንተ እሺ በለኝ። እገባለሁ። እሄዳለሁ፤ አሁኑኑ ፈልግልኝ!”
“ዉዉዉ-ዉቤ?” የሚል ድምፅ ከኋላዬ ሰማሁ። ማን በተብታባ ድምፁ እንደ ጠራኝ ለማጣራት ዞሬ ማየት ያስፈልገኝ ኖሯል? ኧረ በጭራሽ በጠረኑ ብቻ አዉቀዋለሁ፡፡ እሸቴ ነዉ፡፡ ወይ ባልቻ! ምን ዓይነት ልብ
ነዉ የታደለዉ ግን? መቼም ጨክኖ ማኩረፉን አያውቅበት! ሆነ ብሎ ኖሯል ለካ እሸቴን ከሁላችንም እይታ እንዲጠፋ ያደረገዉ፡፡ እኔ እንደሆነ
እንዳልሞተ ሰዉ የማራክስዉ ነገር የለኝም፡፡ ጊዜ እንኳን ዉድ
የሚሆንብኝ ካለፈ በኋላ ዞሬ ሳየዉ ብቻ ነዉ። እቃም ቢሆን ከእጅ አምልጦ ካልተሰበረ ወይ ደግሞ ካልተሰረቀ በቀር ዉድነቱ አይታወቀኝም።እሸቴንም ባላጣዉ ኖሮ አልፈልገዉም ነበር። ለዚህ ይመስለኛል ባልቻም
እሸቴን ከዓይኔ እንዲጠፋ ያደረገብኝ። የእሽቴን ዉድነት እንዳምን፣ ከዓይኔ ሠወረብኝ፡፡ እንኳንም ሠወረብኝ፣ እንኳንም ናፈቅሁት፣ እንኳንም
አገኘሁት። ተሳክቶለታል።
ባልቻን በስስትም በኩራትም እያየሁት ሳለ፣ እሸቴ ከፊት ለፊቴ መጥቶ እንደኔዉ በጉልበቱ ወደቀ። ጥዉልግ ብሏል። ከንፈሩ ሳይቀር ኩችር ብሎ ደርቆ ታየኝ፡፡
“እሽቴ?”
“ጨጨጨ ጨከንሽብኝ እኮ
ዉቤ”
“ኹለተኛ አላደርገዉም”
“አአአ አአ አለሽልኝ ግን?”
“አለሁልህ። አለህልኝ?”
የባልቻን መኖር ሁሉ ረስተን፣ አንገት ለአንገት ተቆላልፈን ቆየን፡፡
እንደዚሁ እንዳለን፣ ልክ እሸቴን እንዳገኘልኝ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ የገባሁት ቃል ትዝ አለኝ። እስከሚነጋ ቸኮልሁ።
ከአምስት ወር በላይ በሆዴ ፅንስ ይዤ፣ ያዉም እኔ ራሴ የሕክምና
ባለሙያ ሆኜ ፤ እስከ አሁን ግን የሕክምና ክትትል አለመጀመሬ ለግድ የለሽነቱ ወደር የማይገኝልኝ ሴት መሆኔን መስክሮብኛል፡፡ ይኼንን ማንም ሳይነግረኝ አዉቄዋለሁ። ሲሆን ሲሆን እርግዝና ከመፈጠሩ ከዓመት ወይ
ከወራት ቀደም ሲል ጀምሬ ዝግጅት ማድረግ ነበረብኝ፡፡ እንደኔ እንኳን እርግዝናዉ በድንገት ለተፈጠረበትም ቢሆን፣ ከመጀመሪያዉ ጀምሮ
ሙሉ ምርመራ እና ክትትል ማድረግ የግድ ነዉ። እኔ ግን ቢያንስ ቅሪት መሆኔን ያወቅሁት ቶሎ ቢሆንም፣ ይኼዉ 22ኛ ሳምንቴን ጭልጥ አድርጌ ነዉ ገና ነገርዮዉን እንኳን በበጎነቱ የተቀበልሁት።
ዛሬ ነዉ ወደ ሆስፒታል ለመምጣት የወሰንሁት። ዛሬ ገና።
ዛሬ ግን ቆርጬ መጥቻለሁ።
በእናቶች እና ሕጻናት ሕክምና ዝነኛ ወደ ሆነዉ ሐሚያሉ ሆስፒታል ገብቼ ካርድ አወጣሁና ወደ ተጠቆምሁት የዶክተር ክፍል አመራሁ። ብዙም ሳልቆይ ወረፋዬ ደረሰኝና፣ መለስ ያለዉን በር ገፍቼ ወደ ዉስጥ ገባሁ። ሆስፒታሉን በበጎ ስሙ መረጥሁት እንጂ፣ የተለየ የሐኪም ምርጫ አላደረግሁም ነበር። ሆኖም ከዉስጥ የጠበቀችኝን ሐኪም ካየሁ በኋላ፤ ሕይወት የአጋጣሚዎች ጋን መሆኗን አመንሁ።
ሐኪሟ ስንቱን አብራኝ ያሳለፈች፣ የቀድሞ ጓደኛዬ ሆና እርፍ!
“ሸዊት!” አልኋት፣ ለረዥም ደቂቃ እጄን አፌ ላይ ጭኜ ስደነቅ ከቆየሁ በኋላ።
"የፈጣሪ ያለህ! ዉብዬ ?” አለች እሷም፣ አሁንም አሁንም ዓይኖቿን
ጨፍና እየገለጠቻቸዉ። ከመልኬ እኩል በሆዴ ያለዉን አስተዉላለች፡፡ ከነጭራሹ የምንገናኝ፣ ያዉም እንዲህ ሆኜ፣ አልጠበቀችኝም ነበር። ለነገሩማ እኔስ እንዴት ብዬ እጠብቃለሁ? በጎንደር ዩኒቨርስቲ የሕክምና
ዶክትሬት ዲግሪያችንን አብረን በተማርንበት ወቅት የነበረንን ጓደኝነት አይቶ ትንሽ ትልቁ እንደዚያ ከዓይን ያዉጣችሁ እንዳላለን ሁሉ፣ እንደዚህ በአንድ ከተማ መኖራችንን እንኳን እስካለመተዋወቅ ድረስ
መራራቃችን ዋዛ ነዉ፡፡ ምን ሆነን ነዉ ግን? ምንም፡፡ ለነገሩ ዩኒቨርስቲ ካስተዋወቀኝ ወዳጆቼ ማንን አግኝቼ አዉቃለሁ? ከስንት አንድ በአጋጣሚ ካልሆነ በቀር፣ አብዛኞቹ የት እንዳሉ እንኳን አላዉቅም፡፡
“ዋዉ!” አለችኝ፣ እንደ ታቦት እየዞረችኝ፡፡
“እሩ እስኪ ሰላም በዪኝ መጀመሪያ”
“እንኳን ለዚህ አበቃሽ ዉብዬ” ብላ መጥታ አንገቴ ሥር ሰረገች፡፡
እንደገና ሆድ ሆዴን ትኩር ብላ አየችኝና፣ ጭምጭም አድርጋ ሳመችኝ፡፡የምር ደስ ብሏታል። እንባዋ ሳይቀር ጠይም ጉንጮቿን እያራሰ በብርቅዬ አንገቷ በኩል ፈሰሰ።
ሀገር ዉስጥ ነዉ የምትኖሪዉ? ጭራሽ እዚሁ አዲስ አበባ?” አልኋት፣
ደስታዋ እንዲጋባብኝ ልቤን እየደቃሁት።
“አይ፤ ቅርብ ጊዜ ነዉ የመጣሁት። ጀርመን ነበርሁ፣ ትምህርት ላይ”
“ተዪ እንጂ? ጀርመን፤ ምን ስፔሻላይዝ አደረግሽ ታዲያ?”
“ይኸዉ እያየሽኝ? ለእር ግዝና ክትትል አይደል እንዴ እኔ ጋ
የመጣሽዉ?”
“አይ አጅሪት! እንዲያ ነዉ እንጂ የኔ እህት! ደግሞ ጥሩ ምርጫ ነዉ”
“አንቺስ ምን አጠናሽ?”
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ወደ መኪናዬ ሽምጥ እየሮጥሁ ሳለ ነበር፣ የንስሐ አባቴን እንኳን
እንዳልተሰናበትኋቸዉ ያወቅሁት፡፡ እንደ ልማዴ በጥድፊያ ወደ ሲራክ፯ አሽከረከርኩ። መቼም ከባልቻ የተደበቀ ነገር የለም፡፡ እሱን አግኝቼ እስከማማክረዉ ድረስ ትንፋሼን እንኳን ወደ ዉስጥ መሳብ አልሆነልኝም፡፡ ቸኩያለሁ። አይደርሱት የለም ደረስሁና ቢሮዉን በርግጄ ስገባ፣ ባልቻ በወንበሩ ላይ ለጠጥ ብሎ እንቅልፍ አሸልቦት አገኘሁት።
በተለይም የሲራክ ፯ ዋና ኃላፊ ከሆነ በኋላ የግል መኖሪያ ቤቱን አይቶት የሚያዉቅ አይመስለኝም። ዉሎዉም አዳሩም እዚሁ ሆኗል። እዚሁ ምግብ ያስመጣል፣ እዚሁ ወንበሩ ላይ ትንሽ ዕረፍት ያደርጋል። ከስንት አንድ ወደ ዉጪ ቢወጣ እንኳን ምክንያቱ ለዚሁ ለሲራክ ጉዳይ ብቻ
ነዉ፡፡
“ባልቻ!” ብዬ ስጮህበት፣ ብርግግ ብሎ ብድግ አለልኝ።
“ዉብርስት?” አለ ተጨናብሶ፣ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ፡፡
“እሰይ! ‹ዉብርስት?” አልሁት፣ ልጃለሜ የሚለዉ ቁልምጫዉ
መቅረቱ ከንክኖኝ፡፡ እኔ ደግሞ ከእሱ ብቻ ሳይሆን ከማንም ቁልምጫ የለመድሁ ሰዉ ነኝ። ቁልምጫዉን ሳይቀር እንደገና በሚያቆላምጥ ቤተሰብ መሀል ነዉ ያደግሁት። ያዉም ዉብዬዋ፣ ‹ዉቤዋ፣ የኔ ዉብ፣ ዓለሜዋ፣ ‹ልጃለሜ› እየተባልሁ። ባልቻ እንዲሁ እንደ ወረደ በስሜ ጠርቶኝ ካለማወቁ የተነሳ፣ ስሜን ሁሉ የሚያዉቀዉ አይመስለኝም
ነበር። ትዝ ሲለኝ እኔ ራሴ ባልቻ ብዬ ነዉ የጠራሁት ለካ። «አባታለም» የሚለዉ ቁልምጫዬስ? የት ተዉሁት?
“ይኸዉ መጣሽ። በስንት ጊዜሽ? ስደዉል ሳታነሺ፣ ሳስጠራሽ ሳትመጪ፣ ስፈልግሽ ሳትገኘ፤ ዛሬ ምን አመጣሽ በይ?”
“እሸቴ ጠፍቷል”
“ጠፋ? ማን እፍ ብሎት ይሆን በናትሽ? ቀድሞስ በርቶ ኖሯል እንዴi” ሲል አላገጠብኝ፡፡
“ማላገጥህ ነዉ?”
“ራስሽ ከመሀል ጀመርሽዋ! እኔና አንቺ እኮ ገና እንደገና መተዋወቅ
አለብን። ቆይ የት አዉቅሻለሁ? አንቺ ታዉቂኛለሽ?”
“በማርያም አባታለም? ፈርቻለሁ። እሽቴ በመንግሥት ደኅንነቶች እጅ
ወድቆ እንዳይሆን ልቤ ሰግቷል”
“እና ምናገባኝ እኔን?”
“ኧረ ባዛኝቱ? እንዴት ነዉ የማያገባህ፤ እሽቴ እኮ ነዉ!”
"የሆነስ እንደሆነ!”
“አዉቃለሁ አሳዝኜሃለሁ። ለዚያም እንዴ ት ይቅርታ መጠየቅ እንዳለብኝ አላዉቅም። ቢሆንም ግን በዚህ መሀል እሸቴ በጨካኞች እጅ ወድቆ
ከሆነ አያሳዝንህም?”
“ያሳዝነኛል”
“እኮ አንድ ነገር አድርጋ”
“ምን ላድርግ?”
“የማታስፈልገዉ?”
“እሺ። አስፈልጌ ሳገኘዉስ?”
“ያንተን አላዉቅም። እኔ ግን ተንበርክኬ ይቅርታ እለምነዋለሁ”
“ለምን?”
“ስለሚገባዉ”
“እሺ። መጀመሪያ ግን እንስማማ”
“ንገረኝ በምን?”
“ተንበርክከሽ የምትጠብቀዉ ከሆነና፣ ተሳክቶልኝ ካገኘሁት ደግሞ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ቃል ከገባሽልኝ.…”
“ይኼዉ!” ብዬ ጉልበቴ ግዉ እስከሚል ድረስ ወድቄ ተንበረከክሁ፡፡
“ብቻ አንተ እሺ በለኝ። እገባለሁ። እሄዳለሁ፤ አሁኑኑ ፈልግልኝ!”
“ዉዉዉ-ዉቤ?” የሚል ድምፅ ከኋላዬ ሰማሁ። ማን በተብታባ ድምፁ እንደ ጠራኝ ለማጣራት ዞሬ ማየት ያስፈልገኝ ኖሯል? ኧረ በጭራሽ በጠረኑ ብቻ አዉቀዋለሁ፡፡ እሸቴ ነዉ፡፡ ወይ ባልቻ! ምን ዓይነት ልብ
ነዉ የታደለዉ ግን? መቼም ጨክኖ ማኩረፉን አያውቅበት! ሆነ ብሎ ኖሯል ለካ እሸቴን ከሁላችንም እይታ እንዲጠፋ ያደረገዉ፡፡ እኔ እንደሆነ
እንዳልሞተ ሰዉ የማራክስዉ ነገር የለኝም፡፡ ጊዜ እንኳን ዉድ
የሚሆንብኝ ካለፈ በኋላ ዞሬ ሳየዉ ብቻ ነዉ። እቃም ቢሆን ከእጅ አምልጦ ካልተሰበረ ወይ ደግሞ ካልተሰረቀ በቀር ዉድነቱ አይታወቀኝም።እሸቴንም ባላጣዉ ኖሮ አልፈልገዉም ነበር። ለዚህ ይመስለኛል ባልቻም
እሸቴን ከዓይኔ እንዲጠፋ ያደረገብኝ። የእሽቴን ዉድነት እንዳምን፣ ከዓይኔ ሠወረብኝ፡፡ እንኳንም ሠወረብኝ፣ እንኳንም ናፈቅሁት፣ እንኳንም
አገኘሁት። ተሳክቶለታል።
ባልቻን በስስትም በኩራትም እያየሁት ሳለ፣ እሸቴ ከፊት ለፊቴ መጥቶ እንደኔዉ በጉልበቱ ወደቀ። ጥዉልግ ብሏል። ከንፈሩ ሳይቀር ኩችር ብሎ ደርቆ ታየኝ፡፡
“እሽቴ?”
“ጨጨጨ ጨከንሽብኝ እኮ
ዉቤ”
“ኹለተኛ አላደርገዉም”
“አአአ አአ አለሽልኝ ግን?”
“አለሁልህ። አለህልኝ?”
የባልቻን መኖር ሁሉ ረስተን፣ አንገት ለአንገት ተቆላልፈን ቆየን፡፡
እንደዚሁ እንዳለን፣ ልክ እሸቴን እንዳገኘልኝ ወደ ሆስፒታል ለመሄድ የገባሁት ቃል ትዝ አለኝ። እስከሚነጋ ቸኮልሁ።
ከአምስት ወር በላይ በሆዴ ፅንስ ይዤ፣ ያዉም እኔ ራሴ የሕክምና
ባለሙያ ሆኜ ፤ እስከ አሁን ግን የሕክምና ክትትል አለመጀመሬ ለግድ የለሽነቱ ወደር የማይገኝልኝ ሴት መሆኔን መስክሮብኛል፡፡ ይኼንን ማንም ሳይነግረኝ አዉቄዋለሁ። ሲሆን ሲሆን እርግዝና ከመፈጠሩ ከዓመት ወይ
ከወራት ቀደም ሲል ጀምሬ ዝግጅት ማድረግ ነበረብኝ፡፡ እንደኔ እንኳን እርግዝናዉ በድንገት ለተፈጠረበትም ቢሆን፣ ከመጀመሪያዉ ጀምሮ
ሙሉ ምርመራ እና ክትትል ማድረግ የግድ ነዉ። እኔ ግን ቢያንስ ቅሪት መሆኔን ያወቅሁት ቶሎ ቢሆንም፣ ይኼዉ 22ኛ ሳምንቴን ጭልጥ አድርጌ ነዉ ገና ነገርዮዉን እንኳን በበጎነቱ የተቀበልሁት።
ዛሬ ነዉ ወደ ሆስፒታል ለመምጣት የወሰንሁት። ዛሬ ገና።
ዛሬ ግን ቆርጬ መጥቻለሁ።
በእናቶች እና ሕጻናት ሕክምና ዝነኛ ወደ ሆነዉ ሐሚያሉ ሆስፒታል ገብቼ ካርድ አወጣሁና ወደ ተጠቆምሁት የዶክተር ክፍል አመራሁ። ብዙም ሳልቆይ ወረፋዬ ደረሰኝና፣ መለስ ያለዉን በር ገፍቼ ወደ ዉስጥ ገባሁ። ሆስፒታሉን በበጎ ስሙ መረጥሁት እንጂ፣ የተለየ የሐኪም ምርጫ አላደረግሁም ነበር። ሆኖም ከዉስጥ የጠበቀችኝን ሐኪም ካየሁ በኋላ፤ ሕይወት የአጋጣሚዎች ጋን መሆኗን አመንሁ።
ሐኪሟ ስንቱን አብራኝ ያሳለፈች፣ የቀድሞ ጓደኛዬ ሆና እርፍ!
“ሸዊት!” አልኋት፣ ለረዥም ደቂቃ እጄን አፌ ላይ ጭኜ ስደነቅ ከቆየሁ በኋላ።
"የፈጣሪ ያለህ! ዉብዬ ?” አለች እሷም፣ አሁንም አሁንም ዓይኖቿን
ጨፍና እየገለጠቻቸዉ። ከመልኬ እኩል በሆዴ ያለዉን አስተዉላለች፡፡ ከነጭራሹ የምንገናኝ፣ ያዉም እንዲህ ሆኜ፣ አልጠበቀችኝም ነበር። ለነገሩማ እኔስ እንዴት ብዬ እጠብቃለሁ? በጎንደር ዩኒቨርስቲ የሕክምና
ዶክትሬት ዲግሪያችንን አብረን በተማርንበት ወቅት የነበረንን ጓደኝነት አይቶ ትንሽ ትልቁ እንደዚያ ከዓይን ያዉጣችሁ እንዳላለን ሁሉ፣ እንደዚህ በአንድ ከተማ መኖራችንን እንኳን እስካለመተዋወቅ ድረስ
መራራቃችን ዋዛ ነዉ፡፡ ምን ሆነን ነዉ ግን? ምንም፡፡ ለነገሩ ዩኒቨርስቲ ካስተዋወቀኝ ወዳጆቼ ማንን አግኝቼ አዉቃለሁ? ከስንት አንድ በአጋጣሚ ካልሆነ በቀር፣ አብዛኞቹ የት እንዳሉ እንኳን አላዉቅም፡፡
“ዋዉ!” አለችኝ፣ እንደ ታቦት እየዞረችኝ፡፡
“እሩ እስኪ ሰላም በዪኝ መጀመሪያ”
“እንኳን ለዚህ አበቃሽ ዉብዬ” ብላ መጥታ አንገቴ ሥር ሰረገች፡፡
እንደገና ሆድ ሆዴን ትኩር ብላ አየችኝና፣ ጭምጭም አድርጋ ሳመችኝ፡፡የምር ደስ ብሏታል። እንባዋ ሳይቀር ጠይም ጉንጮቿን እያራሰ በብርቅዬ አንገቷ በኩል ፈሰሰ።
ሀገር ዉስጥ ነዉ የምትኖሪዉ? ጭራሽ እዚሁ አዲስ አበባ?” አልኋት፣
ደስታዋ እንዲጋባብኝ ልቤን እየደቃሁት።
“አይ፤ ቅርብ ጊዜ ነዉ የመጣሁት። ጀርመን ነበርሁ፣ ትምህርት ላይ”
“ተዪ እንጂ? ጀርመን፤ ምን ስፔሻላይዝ አደረግሽ ታዲያ?”
“ይኸዉ እያየሽኝ? ለእር ግዝና ክትትል አይደል እንዴ እኔ ጋ
የመጣሽዉ?”
“አይ አጅሪት! እንዲያ ነዉ እንጂ የኔ እህት! ደግሞ ጥሩ ምርጫ ነዉ”
“አንቺስ ምን አጠናሽ?”
👍48❤1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...“በይ እሺ፡፡ በይ ደርሰሽ ነይ”
የምርመራ ማዘዣዎችን ተቀብያት ስወጣ፣ ለአልትራሳውንድ ምርመራዉ ጨመር ያለ ዉሃ መጠጣቱ እንደሚጠቅመኝ ስለማዉቅ፣ ወደ ሆስፒታል
ስመጣ ጀምሬዉ ያጋመስሁትን ኹለት ሊትር ዉሃ እየተጎነጨሁለት
ወደ ቤተ ሙከራዉ ተመለስሁ። እንደ ፈራሁት ስዓቱ ሰዉ የማይበዛበት ሰዓት ሆኖ ይመስለኛል፣ የሚያማርር ወረፋ አልገጠመኝም። በመሆኑም፣
ደሜን ጨምሮ የሚያስፈልጉ ዋና ዋና ናሙናዎችን ሰጥቼ በግማሽ ሰዓት ዉስጥ ዉጤት ደረስልኝ። ዉጤቴን ይዤ እንደገና ወደ ቀድሞዋ የልቤ ሰዉ፣ የአሁኗ ደግሞ ሐኪሜ ቢሮ ወጥሮ የያዘኝን ሽንቴን እንደ
ቆነጠጥሁ ተመለስሁ። ገለጥ አድርጌ እንኳን ወረቀቱን የማየት ሐሳብ ብልጭ አላለልኝም።
ሆስፒታላችሁ ብርሃናዊ አይደል እንዴ አንቺ፣ ፍጥነቱ!”
“ዉጤቱ ደረሰልን?”
“ይኼዉ” አልኋት፣ ጠረጴዛዋ ላይ እንደ ከባድ እቃ በኹለት እጄ
እያስቀመጥሁላት።
“ደፈንሽዉ ኣ?” አለችኝ፣ ትኩረቷን አድርጋበት ከነበረዉ ኮምፒዉተሯ
ወደ ዉጤት ወረቀቴ እያመጣችዉ።
“እረ እኔ ምኑንም አላየሁት”
ለመጨረሻ ጊዜ ሆዴን ሰረቅ አድርጋ አየችዉና ወረቀቱን ገለጠችዉ፡፡ድንገት ፊቷ እብጥ አለብኝ። ዉጤቱ ላይ ደስ የማይል ነገር እንዳገኘች ጠረጠርሁ። ቢሆንም ግን ራሷ እስከምትነግረኝ ድረስ ብጠብቅ ይሻላል ብዬ ያላየኋት መሰልሁ። እሷም ያልደነገጠች ለመምሰል የሆነ ያልሆነዉን ቀበጣጠረች፡፡ እንደገና በሚያደናግር ትኩረት አስተዋለችዉና ወደ አልትራሳዉንድ ክፍሉ እንድከተላት ነገረችኝ፡፡ ስንገባ ያገኘነዉን ራዲዮሎጂስት እንኳን በቅጡ ሰላም አላለችዉም። ቶሎ ብዬ ሆዴን ገልጬ አልጋዉ ላይ እንድንጋለል አዘዘችኝ፡፡ ለወትሮዉ በልዩነት የተማረዉ ባለሙያ ያለበትን አልትራሳዉንድ ይቅርና ተራ ነገርም ቢሆን
ሐኪም ያለሙያዉ ገብቶ አይፈተፍትም፡፡ እሷ ግን እጅግ ከመቻኮሏ የተነሳ እሱን ጨምራ በጥድፊያ ከፍ ዝቅ አደረገችዉ። የእዉር ድንብሯ ወጥቷል። ሌላዉ ቀርቶ ገና በመመርመሪያዉ (ultrasound probe)
እንኳን ሳይዳብሰኝ ነበር ዓይኖቿን ወደ ምስል መከሰቻዉ የተከለቻቸዉ።
ችኮላዋን በበጎ የተረዳት የክፍሉ ባለሙያ፣ ሳይቀየማት የሚደረገዉን ሁሉ አድርጎ የፅንሱን ጥላማ ገጽ ፊት ለፊታችን ባለዉ ዝርግ መከሰቻ አመጣልን። ይኼ ሁሉ ሲሆን የእሷን አድራጎት ብቻ ነበር የምከታተለዉ።
እስኪበቃት ድረስ እያጎላች እና እያሳነሰች ስትመለከተዉ ቆየች። እኔንም እንዳየዉ ጋበዘችኝ፡፡
አየሁት።
ችግር አለ። ከባድ ችግር!
“አይ፤ ያን ያህል እንኳን አንገት የሚያስደፋ አይደለም” አለችኝ፣
ከአልጋዉ ላይ እንድነሳ እየደገፈችኝ። ድንገት ሰዉነቴ እየከዳኝ፣ የበለጠ ድጋፍ እየፈለግሁ መጣሁ። ደግነቷ፣ እጇን አልከለከለችኝም።
“በእርግጥ የማልደብቅሽ ነገር ቢኖር፤ እኔም ልክ የላብራቶሪ ዉጤትሽን ሳየዉ ደንግጫለሁ። በዚያም ላይ ከእኔ ባልተናነስ ስለ ሁኔታዉ ልታወቂ እንደምትችይ ስለማዉቅ በማይመስልሽ ቃል አንቺን አልሸነግልሽም።እንኳንስ የሕክምና ሥነ ምግባር ለማገባት ላንቺ ለጓደኛዬ ይቅርና፣
ለታካሚዎቼ ሁሉ የሆነዉን በግልጽነት የማስረዳት ኃላፊነት አለብኝ። የምልሽ ይገባሻል መቼስ”
ጓደኛዬም ሐኪሜም በሆነችዋ ሸዊት ፊት፣ ግብኔ ብቻ ያልቀረ ለመምሰል ተጣጣርሁ። ጠንካራ ለመምሰል እየሞከርሁ የዉጤት ወረቀቱን እንድትመልስልኝ እና የሆነዉን ሁሉ በራሴ ዓይን እንዳየዉ እጄን ዘረጋሁላት። ሐኪሜ ለምን እንደዚያ እንደሆነች ገባኝ፡፡ ምክንያቱም የፎሊክ አሲድ መጠኑ ከሚጠበቀዉ መጠን እጅግ የወረደ ኖሯል።
እንደዚህ ሲሆን ደግሞ በፅንሱ ላይ የነርቭ ክፍተት የማስከተል ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን እንኳንስ ሥራዬ ብላ ያጠናችዉ እሷ ትቅርና፣ እኔ ዉብርስትም አዉቀዋለሁ። የፎሊክ አሲድ እጥረት ከተከሰተ፣ የነርቭ
ዘንግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ በወቅቱ እንዳይዘጋ ያደርገዋል። በመሆኑም፣ የፎሊክ አሲድ እጥረት እንዳያጋጥም፣ እርግዝና ከመፈጠሩ አስቀድሞ ወይ ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ ከተመረጡ ምግቦች፣ ወይ ደግሞ ሰዉ ሰራሽ እንክብሎችን መዉሰድ ያስፈልጋል። ያለበለዚያ ይኼዉ በእኔ የምርመራ ዉጤት ላይ እንደ ታየዉ፣ ልክ ያልሆነ ነገር በፅንሱ ላይ ይፈጠራል።
ምን ዋጋ አለኝ? አርፍጃለኋ!
“በእርግጥ ሌሎችም መነሻዎች ስላሉት፣ የፎሊክ አሲድ እጥረቱ ነዉ ይኼን ያመጣዉ ብሎ አፍን ሞልቶ መደምደም አይቻልም። ሆኖም እኔን ደጋግመዉ ከገጠሙኝ ዐሥር የፎሊክ አሲድ እጥረት ያየሁባቸዉ ነፍሰ
ጡሮች፣ ቢያንስ የስድስቱ ወደ ነርቭ ክፍተት ያደርሳል። የነርቭ ክፍተት ስልሽ የተለመዱትን፣ በተለይም ስፓይናቢፊዳ(አከርካሪው ላይ ያለው ነርቭ ወደ ውጭ መውጣት) ማለቴ ነዉ። ይኼ ደግሞ ያልሰለጠነ ሀገር በሽታ እየሆነ መጥቷል። ምክንያቱም የበለጸጉት ሀገራት ምግባቸዉን በጠቅላላ በፎሊክ እንዲበለጽግ ስላደረጉት፣ ብዙም አያጋጥማቸዉም። የእኛን ሀገር ግን አታንሺዉ”
“በናትሽ መፍትሔ አለዉ በዪኝ”
“ደግሞ በኛ ዘመን መፍትሔ የሌለዉ ነገር ምናለና ዉቤ”
“እኮ ምን?”
“በተአምር ታምኛለሽ?”
የጭንቅ ዝልዝል የተንጠለጠለበትን ፊቴን መለስሁላት።
“ተአምር?”
“አሁን አንዴ ፅንሱ ቅርጽ ይዟል። ተአምር ካልተፈጠረ በቀር፣ ሕጻኗ... በነገራችን ላይ ጾታዋን አልነገርሁሽም አይደል ቅድም? ሴት ናት። እና፤ከላብራቶሪም ሆነ ከአልትራሳዉንድ ባገኘነዉ ዉጤት መሠረት፣ በወሊድ ጊዜ ሊገጥሙን የሚችሉ የነርቭ ዘንግ ክፍተቶች ይኖራሉ፡፡ በተለይ
ስፓ ይናባይፊዳ የሚባለዉ ለብቻዉ ወይም ደግሞ ሀይድሮሴፋለስ(ጭንቅላት ውስጥ ውሃ መቋጠር) ጭምር
ሊሆኑ ይችላሉ። ግን እንዳልሁሽ ነዉ፤ ተወልዳ በዓይናችን እስከምናያት ድረስ መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆን አንችልም”
“እንዲያዉ አይበልብኝና ይኼ ነገር እዉነት የሚሆን ከሆነ ምንድነዉ
የሚሆነዉ ግን?”
“እንደምታዉቂዉ፤ ለሐቅ የቀረበ ግምት እንጂ ፍጹም የሚባል ያለቀ
የደቀቀ ሐቅ የለም በሳይንስ፡፡ አንቺም ሐሳቤን የምትጋሪዉ ይመስለኛል።ሆኖም አብዛኛዎቹ የዚህ ክፍተት ተጠቂዎች የታወቁ ጉዳቶች ይገጥሟቸዋል። ለምሳሌ ሽንትና ሰገራ ያለመቆጣጠር፣ የእግርና የእጅ ሽባነት፣ የዓይን መንሸዋረር ወይ መጥፋት እና ሌሎችም ጭምር።እንዲያዉም አልፎ አልፎ የከፋዉ ሲመጣ፣ እነዚህ ያልሁሽ ሁሉም አንድ
ላይ የሚከሰቱበት አጋጣሚ ሁሉ አለ። ታዲያ እንዳልሁሽ፣ በኛ ዘመን
መፍትሔ የሌለዉ ችግር የለም። ቢፈጠርም እንኳን ሕክምና አለዉ”
“አለዉ?” አልሁኝ፣ ለእፎይታ ራሴን እያመቻቸሁ። አንደኛዬን ግልብ
ሆኜ የለ አሁንማ? አሁን መሳቅ አሁን ማልቀስ፣ አሁን ማመን አሁን
መካድ። ስስ ሆኛለሁ።
“አዎ። ቀዶ ጥገናም እኮ አለዉ። አንቺን መምከር ሳይገባኝም፣ ከዚህ በላይ መጨነቅ ግን አይኖርብሽም። ጭንቀት ራሱ ሌላ ጣጣ ስላለዉ፣ እዉነታዉን የምነግርሽ እንድትጨነቂበት ሳይሆን ለግልጽነት ብዬ ነዉ።
በዚያ ላይ አንቺ ጠንካራ ሰዉ መሆንሽን ለእኔ ለጓደኛሽ እንዲነግሩኝ አልጠብቅም። አዉቅሻለኋ!”
ቀዝቃዛ ትንፋሽ ተነፈስሁ። ገና ዛሬ፣ አሁን ገና የእግዚአብሔርን ይቅር ባይነት ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠራጠርሁት። ወይ ስለ ንስሐ ምንም አላዉቅም፣ ወይ ደግሞ እግዚአብሔር ቂመኛ ነዉ
ስል አሰብሁ። እኔ የተማርሁት ሰዉ ፍጹም ተጸጽቶ ንስሐ ከገባ
ኃጢአቱ ሁሉ ፍጹም ይሰረይለታል የሚለዉን ነበር። ከእግዚአብሔር
ጋር የሚያደረገዉም እርቅ ፍጹም ይሆንለታል ሲባል አዉቃለሁ። ታዲያ እኔ ፍጹም የሆነ ጸጸት ተጸጽቼ ንስሐ አልገባሁም? ቀኖናዬንስ በሚገባ ወይስ እግዚአብሔር ፍጹም አምላክ መሆኑን አላመንሁም?
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...“በይ እሺ፡፡ በይ ደርሰሽ ነይ”
የምርመራ ማዘዣዎችን ተቀብያት ስወጣ፣ ለአልትራሳውንድ ምርመራዉ ጨመር ያለ ዉሃ መጠጣቱ እንደሚጠቅመኝ ስለማዉቅ፣ ወደ ሆስፒታል
ስመጣ ጀምሬዉ ያጋመስሁትን ኹለት ሊትር ዉሃ እየተጎነጨሁለት
ወደ ቤተ ሙከራዉ ተመለስሁ። እንደ ፈራሁት ስዓቱ ሰዉ የማይበዛበት ሰዓት ሆኖ ይመስለኛል፣ የሚያማርር ወረፋ አልገጠመኝም። በመሆኑም፣
ደሜን ጨምሮ የሚያስፈልጉ ዋና ዋና ናሙናዎችን ሰጥቼ በግማሽ ሰዓት ዉስጥ ዉጤት ደረስልኝ። ዉጤቴን ይዤ እንደገና ወደ ቀድሞዋ የልቤ ሰዉ፣ የአሁኗ ደግሞ ሐኪሜ ቢሮ ወጥሮ የያዘኝን ሽንቴን እንደ
ቆነጠጥሁ ተመለስሁ። ገለጥ አድርጌ እንኳን ወረቀቱን የማየት ሐሳብ ብልጭ አላለልኝም።
ሆስፒታላችሁ ብርሃናዊ አይደል እንዴ አንቺ፣ ፍጥነቱ!”
“ዉጤቱ ደረሰልን?”
“ይኼዉ” አልኋት፣ ጠረጴዛዋ ላይ እንደ ከባድ እቃ በኹለት እጄ
እያስቀመጥሁላት።
“ደፈንሽዉ ኣ?” አለችኝ፣ ትኩረቷን አድርጋበት ከነበረዉ ኮምፒዉተሯ
ወደ ዉጤት ወረቀቴ እያመጣችዉ።
“እረ እኔ ምኑንም አላየሁት”
ለመጨረሻ ጊዜ ሆዴን ሰረቅ አድርጋ አየችዉና ወረቀቱን ገለጠችዉ፡፡ድንገት ፊቷ እብጥ አለብኝ። ዉጤቱ ላይ ደስ የማይል ነገር እንዳገኘች ጠረጠርሁ። ቢሆንም ግን ራሷ እስከምትነግረኝ ድረስ ብጠብቅ ይሻላል ብዬ ያላየኋት መሰልሁ። እሷም ያልደነገጠች ለመምሰል የሆነ ያልሆነዉን ቀበጣጠረች፡፡ እንደገና በሚያደናግር ትኩረት አስተዋለችዉና ወደ አልትራሳዉንድ ክፍሉ እንድከተላት ነገረችኝ፡፡ ስንገባ ያገኘነዉን ራዲዮሎጂስት እንኳን በቅጡ ሰላም አላለችዉም። ቶሎ ብዬ ሆዴን ገልጬ አልጋዉ ላይ እንድንጋለል አዘዘችኝ፡፡ ለወትሮዉ በልዩነት የተማረዉ ባለሙያ ያለበትን አልትራሳዉንድ ይቅርና ተራ ነገርም ቢሆን
ሐኪም ያለሙያዉ ገብቶ አይፈተፍትም፡፡ እሷ ግን እጅግ ከመቻኮሏ የተነሳ እሱን ጨምራ በጥድፊያ ከፍ ዝቅ አደረገችዉ። የእዉር ድንብሯ ወጥቷል። ሌላዉ ቀርቶ ገና በመመርመሪያዉ (ultrasound probe)
እንኳን ሳይዳብሰኝ ነበር ዓይኖቿን ወደ ምስል መከሰቻዉ የተከለቻቸዉ።
ችኮላዋን በበጎ የተረዳት የክፍሉ ባለሙያ፣ ሳይቀየማት የሚደረገዉን ሁሉ አድርጎ የፅንሱን ጥላማ ገጽ ፊት ለፊታችን ባለዉ ዝርግ መከሰቻ አመጣልን። ይኼ ሁሉ ሲሆን የእሷን አድራጎት ብቻ ነበር የምከታተለዉ።
እስኪበቃት ድረስ እያጎላች እና እያሳነሰች ስትመለከተዉ ቆየች። እኔንም እንዳየዉ ጋበዘችኝ፡፡
አየሁት።
ችግር አለ። ከባድ ችግር!
“አይ፤ ያን ያህል እንኳን አንገት የሚያስደፋ አይደለም” አለችኝ፣
ከአልጋዉ ላይ እንድነሳ እየደገፈችኝ። ድንገት ሰዉነቴ እየከዳኝ፣ የበለጠ ድጋፍ እየፈለግሁ መጣሁ። ደግነቷ፣ እጇን አልከለከለችኝም።
“በእርግጥ የማልደብቅሽ ነገር ቢኖር፤ እኔም ልክ የላብራቶሪ ዉጤትሽን ሳየዉ ደንግጫለሁ። በዚያም ላይ ከእኔ ባልተናነስ ስለ ሁኔታዉ ልታወቂ እንደምትችይ ስለማዉቅ በማይመስልሽ ቃል አንቺን አልሸነግልሽም።እንኳንስ የሕክምና ሥነ ምግባር ለማገባት ላንቺ ለጓደኛዬ ይቅርና፣
ለታካሚዎቼ ሁሉ የሆነዉን በግልጽነት የማስረዳት ኃላፊነት አለብኝ። የምልሽ ይገባሻል መቼስ”
ጓደኛዬም ሐኪሜም በሆነችዋ ሸዊት ፊት፣ ግብኔ ብቻ ያልቀረ ለመምሰል ተጣጣርሁ። ጠንካራ ለመምሰል እየሞከርሁ የዉጤት ወረቀቱን እንድትመልስልኝ እና የሆነዉን ሁሉ በራሴ ዓይን እንዳየዉ እጄን ዘረጋሁላት። ሐኪሜ ለምን እንደዚያ እንደሆነች ገባኝ፡፡ ምክንያቱም የፎሊክ አሲድ መጠኑ ከሚጠበቀዉ መጠን እጅግ የወረደ ኖሯል።
እንደዚህ ሲሆን ደግሞ በፅንሱ ላይ የነርቭ ክፍተት የማስከተል ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን እንኳንስ ሥራዬ ብላ ያጠናችዉ እሷ ትቅርና፣ እኔ ዉብርስትም አዉቀዋለሁ። የፎሊክ አሲድ እጥረት ከተከሰተ፣ የነርቭ
ዘንግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ በወቅቱ እንዳይዘጋ ያደርገዋል። በመሆኑም፣ የፎሊክ አሲድ እጥረት እንዳያጋጥም፣ እርግዝና ከመፈጠሩ አስቀድሞ ወይ ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ ከተመረጡ ምግቦች፣ ወይ ደግሞ ሰዉ ሰራሽ እንክብሎችን መዉሰድ ያስፈልጋል። ያለበለዚያ ይኼዉ በእኔ የምርመራ ዉጤት ላይ እንደ ታየዉ፣ ልክ ያልሆነ ነገር በፅንሱ ላይ ይፈጠራል።
ምን ዋጋ አለኝ? አርፍጃለኋ!
“በእርግጥ ሌሎችም መነሻዎች ስላሉት፣ የፎሊክ አሲድ እጥረቱ ነዉ ይኼን ያመጣዉ ብሎ አፍን ሞልቶ መደምደም አይቻልም። ሆኖም እኔን ደጋግመዉ ከገጠሙኝ ዐሥር የፎሊክ አሲድ እጥረት ያየሁባቸዉ ነፍሰ
ጡሮች፣ ቢያንስ የስድስቱ ወደ ነርቭ ክፍተት ያደርሳል። የነርቭ ክፍተት ስልሽ የተለመዱትን፣ በተለይም ስፓይናቢፊዳ(አከርካሪው ላይ ያለው ነርቭ ወደ ውጭ መውጣት) ማለቴ ነዉ። ይኼ ደግሞ ያልሰለጠነ ሀገር በሽታ እየሆነ መጥቷል። ምክንያቱም የበለጸጉት ሀገራት ምግባቸዉን በጠቅላላ በፎሊክ እንዲበለጽግ ስላደረጉት፣ ብዙም አያጋጥማቸዉም። የእኛን ሀገር ግን አታንሺዉ”
“በናትሽ መፍትሔ አለዉ በዪኝ”
“ደግሞ በኛ ዘመን መፍትሔ የሌለዉ ነገር ምናለና ዉቤ”
“እኮ ምን?”
“በተአምር ታምኛለሽ?”
የጭንቅ ዝልዝል የተንጠለጠለበትን ፊቴን መለስሁላት።
“ተአምር?”
“አሁን አንዴ ፅንሱ ቅርጽ ይዟል። ተአምር ካልተፈጠረ በቀር፣ ሕጻኗ... በነገራችን ላይ ጾታዋን አልነገርሁሽም አይደል ቅድም? ሴት ናት። እና፤ከላብራቶሪም ሆነ ከአልትራሳዉንድ ባገኘነዉ ዉጤት መሠረት፣ በወሊድ ጊዜ ሊገጥሙን የሚችሉ የነርቭ ዘንግ ክፍተቶች ይኖራሉ፡፡ በተለይ
ስፓ ይናባይፊዳ የሚባለዉ ለብቻዉ ወይም ደግሞ ሀይድሮሴፋለስ(ጭንቅላት ውስጥ ውሃ መቋጠር) ጭምር
ሊሆኑ ይችላሉ። ግን እንዳልሁሽ ነዉ፤ ተወልዳ በዓይናችን እስከምናያት ድረስ መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆን አንችልም”
“እንዲያዉ አይበልብኝና ይኼ ነገር እዉነት የሚሆን ከሆነ ምንድነዉ
የሚሆነዉ ግን?”
“እንደምታዉቂዉ፤ ለሐቅ የቀረበ ግምት እንጂ ፍጹም የሚባል ያለቀ
የደቀቀ ሐቅ የለም በሳይንስ፡፡ አንቺም ሐሳቤን የምትጋሪዉ ይመስለኛል።ሆኖም አብዛኛዎቹ የዚህ ክፍተት ተጠቂዎች የታወቁ ጉዳቶች ይገጥሟቸዋል። ለምሳሌ ሽንትና ሰገራ ያለመቆጣጠር፣ የእግርና የእጅ ሽባነት፣ የዓይን መንሸዋረር ወይ መጥፋት እና ሌሎችም ጭምር።እንዲያዉም አልፎ አልፎ የከፋዉ ሲመጣ፣ እነዚህ ያልሁሽ ሁሉም አንድ
ላይ የሚከሰቱበት አጋጣሚ ሁሉ አለ። ታዲያ እንዳልሁሽ፣ በኛ ዘመን
መፍትሔ የሌለዉ ችግር የለም። ቢፈጠርም እንኳን ሕክምና አለዉ”
“አለዉ?” አልሁኝ፣ ለእፎይታ ራሴን እያመቻቸሁ። አንደኛዬን ግልብ
ሆኜ የለ አሁንማ? አሁን መሳቅ አሁን ማልቀስ፣ አሁን ማመን አሁን
መካድ። ስስ ሆኛለሁ።
“አዎ። ቀዶ ጥገናም እኮ አለዉ። አንቺን መምከር ሳይገባኝም፣ ከዚህ በላይ መጨነቅ ግን አይኖርብሽም። ጭንቀት ራሱ ሌላ ጣጣ ስላለዉ፣ እዉነታዉን የምነግርሽ እንድትጨነቂበት ሳይሆን ለግልጽነት ብዬ ነዉ።
በዚያ ላይ አንቺ ጠንካራ ሰዉ መሆንሽን ለእኔ ለጓደኛሽ እንዲነግሩኝ አልጠብቅም። አዉቅሻለኋ!”
ቀዝቃዛ ትንፋሽ ተነፈስሁ። ገና ዛሬ፣ አሁን ገና የእግዚአብሔርን ይቅር ባይነት ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠራጠርሁት። ወይ ስለ ንስሐ ምንም አላዉቅም፣ ወይ ደግሞ እግዚአብሔር ቂመኛ ነዉ
ስል አሰብሁ። እኔ የተማርሁት ሰዉ ፍጹም ተጸጽቶ ንስሐ ከገባ
ኃጢአቱ ሁሉ ፍጹም ይሰረይለታል የሚለዉን ነበር። ከእግዚአብሔር
ጋር የሚያደረገዉም እርቅ ፍጹም ይሆንለታል ሲባል አዉቃለሁ። ታዲያ እኔ ፍጹም የሆነ ጸጸት ተጸጽቼ ንስሐ አልገባሁም? ቀኖናዬንስ በሚገባ ወይስ እግዚአብሔር ፍጹም አምላክ መሆኑን አላመንሁም?
👍39❤1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ክፉ ያሳሰበኝን መንፈስ እከድከ ሰይጣን እያልሁ በልቤ ደጋግሜ ጸልዬ አስታገስሁት። ቀጥዬም ሰላም ለኪን ደገምሁበት እና ከሆስፒታል ወጣሁ። እንደ ወጣሁ የሆነብኝን ሁሉ የምነግረዉ ስፈልግ ከሁሉ ቀድሞ
ሐሳቤ ላይ የገባልኝ ሰዉ ባልቻ ነበር፡ እመዋን አቆይቼ ማለቴ ነዉ።ለእሷስ ያለፈዉ ይበቃታል፡ የሆስፒታሉንም ነግሬ ዳግመኛ ቅስሟን ልሰብረዉ አልፈልግም።
በእርግጥ እህትና ወንድሞቼም ነበሩልኝ። ጓደኞቼ ሁሉ አሉ። እሽቴም ቢሆን እኮ አለ የኖረዉ ቢኖርም፣ በተለይ አሁን ስላንጨዋለለኝ ፈታኝ ጉዳይ ለማማከር ግን፣ ከምድር ማንም እንደ ባልቻ የሚሆንልኝ ሰዉ
አይታየኝም: እሱ ብቻ ነዉ የጭንቄን መጠን ልክ እንደ ነገርሁት፣ እንዲያዉም ከነገርሁት አልፎ የሚገነዘብልኝ። ለማባበል
አይሸነግለኝም። ማባበል ከፈለገም እንደ'ሱ የሚያዉቅበት የለም። ጆሮዉ የተለየ ነዉ። ጭጭ ብሎ ሲያዳምጥ ብቻ ከጭንቅ ይፈዉሳል። እኔ ራሴ
እንኳን ስለ ራሴ የማላዉቀዉን ከእመዋ ቀጥሎ የሚያውቅልኝ ሌላ ሰዉ አላዉቅም: ባልቻ ብቻ:: እንዲያ ቢሆንም ግን፣ እሸቴም መስማት ስላለበት ኹለቱንም ወደማላጣበት ወደ ሲራክ-፯ ማዕከል ሄድሁ።
“አባትዮ” አልሁት፣ ወደ ትልቁ የማኅበሩ ሕንጻ እየተቃረብሁ ሳለ ወደ ባልቻ ስልክ ደዉዬለት።
“አቤት ልጅየዋ”
“ለአንድ አፍታ ፈልጌህ ነበር”
“መቼ”
“አሁን”
“ዉይ፣ አሁን እንኳ አንዲት የጀመርኋት ሥራ አለችብኝ: ባይሆን ይቺን እንደ ጨረስሁ ልደዉልልሽ?”
“በማርያም! አሁኑኑ ነዉ የምፈልግህ፤ ይልቅ ቶሎ ናና ጉዴን ስማልኝ'
“እህ፤ እየነገርሁሽ?”
“ስሞትልህ! ከእሸቴ ጋር እዚሁ አንደኛ ፎቅ ባለዉ ምግብ ቤት
ብትመጡልኝ፣ የምጋብዛችሁ አታዉቁትም: አንተስ ምናለ ለአንዳንዴስ እንኳን ንፋስ ቢያገኝህ? ሁልጊዜ እዚያ ዉስጥ ተቀብረህ” አልሁት፣ ለግብዣዬ ያለዉን ከበሬታ ዘንግቶ ላለመምጣት ሲያቅማማ በዚያም ላይ ሰዓቱ የምሳ ስለሆነ ሦስታችን አብረን የምንበላበት የመጀመሪያ አጋጣሚ ይሆንልናል። እንዳሰብሁት፣ ብዙም ሳያስጠብቁኝ ከእሸቴ ጋር ፊት እና
ኋላ ሆነዉ መጡልኝ፡
“አንቺ፤ ብለሽ ብለሽ ደግሞ እንዴት እንዴት ነዉ ያናገርሽኝ? እንደ ልጅ ና ከረሜላ ልግዛልህ ማለት እኮ ነዉ የቀረሽ አሁንማ አሁንማ” አለኝ በጨዋታ፣ ወንበር ስቦ ከአጠገቤ እየተቀመጠ፡ መልስ ከለከልሁት
“አንቺ? ምንድነዉ ደግሞ ለንቦጭሽ የታላቁን ንጉሥ አወዳደቅ ወድቋልሳ: ገና ለገና እርምሽን ልትጋብዥን ብትይ፣ ከአሁኑ ማኩረፍሽ ነዉ? አየህልኝ እሽቴ? ገና ከአሁኑ እንዲህ ከሆነች፣ ሂሳቡን ስትከፍልማ
እንደ ጨዉ ሟሙታ ወደ መሬት መስረጓ ነዉ በለኛ”
ወድጄ አይደለም ዝም ያልኋቸዉ ሆስፒታል የጀመሩኝ ክፉ ክፉ የሚባሉ ሐሳቦች ሁሉ አሁንም አሁንም ወደ ልቡናዬ እየመጡ ግብግብ ገጥመዉኛል፡ እንደ ምንም ጥርሴን ለመፈልቀቅ ሞከርሁ። የዉጤቱን ወሬ ከምሳ በኋላ መንገሩን ስለመረጥሁ፣ በግድ ፈገግ ለማለት እየታገልሁ
ነዉ፡ ብቻ የሆነ ያልሆነዉን እየቀላቀልሁ የጨዋታ ወሬ ለማምጣት ተዉሸለሸልሁ
“ምንድነዉ ልጄ?” አለ ባልቻ አዉቆብኝ ያልፈሰሰ እንባዬን እያበሰልኝ “ አሃ፤ ዛሬ ከነጋ አላየሁሽም ለካ? የት ዋልሽ?”
አስተናጋጁ እየተሸቆጠቆጠ መጥቶ የምንፈልገዉን ሊታዘዘን አጎበደደ፡ እሰይ! ገላገለኝ። በባዶ ሆዳቸዉ ሐቲታቸዉን ከምበላዉ፣
ምሳችንን በሰላም ብንበላ ለእነሱም ይሻላቸዋል። የቤቱን
የአገልግል ምግብ ከተጨማሪ ሱፍ ፍትፍት ጋር እንዲያመጣልን አዘዝን ሱፍ ፍትፍት የባልቻ የምንጊዜም ምርጫ መሆኑን
ከእሱ ጋር ለአንዴም
ቢሆን ማዕድ የተጋሩ ሁሉ ያዉቁለታል። የሚበላም የሚጣጠም ሲጠየቅ
ቀድሞ የሚመጣለት ነገር ሱፍ ነዉ። በሀገር ዉስጥ ምግብ ቤቶች ብቻም ሳይሆን፣ አንዴ ሩስያ አብረን የሄድን ጊዜ ሁሉ ቀዝቀዝ ያለ ሱፍ ፍትፍት ይኖራችኋል? ብሎ ሩስያዊቷን አስተናጋጅ ሲጠይቃት
ሰምቼዉ፣ የሳቅሁትን ሳቅ ሞቼም መርሳቴን እንጃልኝ! እስከ አሁን ትዝ ባለኝ ቁጥር ስቄ አይወጣልኝም: ሱፍ አዝዞ የለም ከተባለ፣ ለሆቴሉ የሚኖረዉ ግምት ሁሉ ወርዶ እንዴት እንደሚያደርገዉ አያድርስ ነዉ።
ይኼ ደግሞ ሆቴል ነዉ? ሱፍ ፍትፍት እንኳን የሌለበት ቤት! ብሎ
ሲያጣጥል ብዙ ጊዜ ሰምቼዋለሁ። ለእኔ ግን የሚበላ ይሁን እንጂ ምንም ቢሆን ያን ያህል አላማርጥም: በተለይ አሁን በኃይል ሞርሙሮኛል። ለወትሮዉ እንዲህ ድባቴ ዉስጥ ስሆን እንኳንስ ሊርበኝ ይቅርና የምግብ
ሽታ ሁሉ አይደርስብኝም ነበር አሁን ግን ምራቄ ኩችር ብሎ፣
ትንፋሼም ሳይቀር ሽታዉ እንደ ተለወጠ ለእኔም ታዉቆኛል።
“ችግር አለ እንዴ ዉቤ?” አለ እሸቴ፣ ከበላን በኋላ ከሁላችን በኋላ እጁን ታጥቦ ከመመለሱ፡
“ፊትሽ በፍጹም ልክ አይደለም” አለ፣ ባልቻም ተደርቦ፡
“ሆስፒታል ሄጄ ነበር''
“እ?” አሉ ኹለቱም፣ እኩል። የሆነዉን እና በሐኪሟ የተባልሁትን ሁሉ አንድም ሳላስቀር ነገርኋቸዉ። በየመሀሉ በድንጋጤ ከአሁን አሁን
ራሳቸዉን ይስታሉ ብዬ ስጠባበቅ፣ እነሱ ከመጤፍ ሳይቆጥሩት ቀሩብኝ ጭራሽ ባልቻማ ሊስቅብኝ ምንም አልቀረዉ፡ እሸቴም ቢሆን የምጠብቅበትን ያህል ጸጸት ቀርቶ ሐዘኔታ እንኳን አላሳየኝም፡
“ለዚህ ነዉ እንዴ ፊትሽን እንዲህ የክረምት ሰማይ ያስመሰልሽዉ?
“ከዚህ በላይ ምን አለና አባታለም?”
“ኧረ ዝም በይ! ደም አርግቶ የፈጠረንን አምላክ ለምናመልክ ለኛ፤ ይኼንን ጉዳይ ብለሽ … ምን እና ምኑ ተገናኝቶ፣ ሰዉ ሆነን እንደ
ተፈጠርን ጠፍቶሽ ነዉ? ልጄ ሙች! ካንቺ ይኼን አልጠብቅም”
ድንገት የእጅ ስልኩ ጮኸ፡ ወዲያዉ ፈገግታዉንም ተግሳጹንም አቋርጦ ስልኩን አነሳና፣ ለቅጽበት ያህል ከወዲያ በኩል አዳመጠ። ወዲያዉም
የምግቡን ሂሳብ ለመክፈል ኪሱን መፈታተሽ ሲጀምር አስቸኳይ ሁኔታ እንደ ተፈጠረ ገባኝ። ቀድሜዉ ሦስት ድፍን ድፍን መቶ ብሮች ጠረጴዛዉ ላይ አስቀመጥሁ።
“ምን ተፈጠረ?” አለ እሸቴ፣ እሱም እንደኔ ጥድፊያዉን በጥሞና እየተከታተለዉ ቆይቶ።
“ዕረፍት ያስፈልግሽ ነበር እዴ ዉቤ? አንድ መጥፎ ወሬ ደርሶኛል”
“ምነዉ ምን ተፈጠረ? ከየት ነዉ?”
“መስጊድ ላይ እሳት ተነስቷል ነዉ የሚሉኝ”
“የ..ት?” አለ እሸቴ፣ ልለዉ የነበረዉን ከአፌ ነጥቆኝ።
“ተከተሉኝ” ብሎ ከምግብ ቤቱ የመሮጥ ያህል ተራምዶ ወጣ፡ በእሱ ፍጥነት እግር በእግር ተከትለነዉ አሳንሠሩ ዉስጥ ገባንና ቁልፉን ተጭነን ወደ ላይኛዉ ፎቅ ጋለብን፡ በጠመዝማዛዉ መንገድ ገብተን
የለመድናቸዉን የደኅንነት ኬላዎች ሁሉ አልፈን በዚሁ ሕንጻ ወደ
ተሠወረዉ የሲራክ ፯ ማዕከል ስንደርስ፣ ሁሉም በየጥፍራቸዉ ቆመዉ አገኘናቸዉ እንኳንስ የጭንቅ ወሬ ተሰምቶበት፣ እንዲያዉም የዕረፍት
አልባዎች ቤት ነዉ ማዕከሉ
“እስኪ የታለ?” አለ ባልቻ፣ ከወገብ በላይ በግድግዳዉ ዙሪያ ወደ ተንጣለለዉ ዝርግ መከሰቻ ዓይኑን እያነጣጠረ፡
ደዉሎ የጠራዉ ልጅ የባልቻ ጥያቄ ስለገባዉ፣ የሚነካዉን ነካክቶ በርከት ያሉ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በሰፊዉ መከሰቻ ከዳር እስከ ዳር ደረደረልን እስከ ሚናራዉ ድረስ በኃይለኛ እሳት ሲንቀለቀል የሚያሳዩ
የመስጊድ ምስሎች ናቸዉ። ወላፈኑ እዚህ ያለንበት ድረስ በሚለበልብ እሳት ሲነድ ይታያል። ብዙ ሰዎችም እሳቱን ለማጥፋት ዙሪያዉን ሲዋደቁ ይታያሉ እንደ እሳቱ አያያዝ ግን መስጊዱን ማትረፍ የሚቻል አይመስለኝም:: ባይሆን ዙሪያዉን ባልተዛመተ እና በአካባቢዉ ተጨማሪ ዉድመት ባልደረሰ ስል በልቤ ጸለይሁ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ክፉ ያሳሰበኝን መንፈስ እከድከ ሰይጣን እያልሁ በልቤ ደጋግሜ ጸልዬ አስታገስሁት። ቀጥዬም ሰላም ለኪን ደገምሁበት እና ከሆስፒታል ወጣሁ። እንደ ወጣሁ የሆነብኝን ሁሉ የምነግረዉ ስፈልግ ከሁሉ ቀድሞ
ሐሳቤ ላይ የገባልኝ ሰዉ ባልቻ ነበር፡ እመዋን አቆይቼ ማለቴ ነዉ።ለእሷስ ያለፈዉ ይበቃታል፡ የሆስፒታሉንም ነግሬ ዳግመኛ ቅስሟን ልሰብረዉ አልፈልግም።
በእርግጥ እህትና ወንድሞቼም ነበሩልኝ። ጓደኞቼ ሁሉ አሉ። እሽቴም ቢሆን እኮ አለ የኖረዉ ቢኖርም፣ በተለይ አሁን ስላንጨዋለለኝ ፈታኝ ጉዳይ ለማማከር ግን፣ ከምድር ማንም እንደ ባልቻ የሚሆንልኝ ሰዉ
አይታየኝም: እሱ ብቻ ነዉ የጭንቄን መጠን ልክ እንደ ነገርሁት፣ እንዲያዉም ከነገርሁት አልፎ የሚገነዘብልኝ። ለማባበል
አይሸነግለኝም። ማባበል ከፈለገም እንደ'ሱ የሚያዉቅበት የለም። ጆሮዉ የተለየ ነዉ። ጭጭ ብሎ ሲያዳምጥ ብቻ ከጭንቅ ይፈዉሳል። እኔ ራሴ
እንኳን ስለ ራሴ የማላዉቀዉን ከእመዋ ቀጥሎ የሚያውቅልኝ ሌላ ሰዉ አላዉቅም: ባልቻ ብቻ:: እንዲያ ቢሆንም ግን፣ እሸቴም መስማት ስላለበት ኹለቱንም ወደማላጣበት ወደ ሲራክ-፯ ማዕከል ሄድሁ።
“አባትዮ” አልሁት፣ ወደ ትልቁ የማኅበሩ ሕንጻ እየተቃረብሁ ሳለ ወደ ባልቻ ስልክ ደዉዬለት።
“አቤት ልጅየዋ”
“ለአንድ አፍታ ፈልጌህ ነበር”
“መቼ”
“አሁን”
“ዉይ፣ አሁን እንኳ አንዲት የጀመርኋት ሥራ አለችብኝ: ባይሆን ይቺን እንደ ጨረስሁ ልደዉልልሽ?”
“በማርያም! አሁኑኑ ነዉ የምፈልግህ፤ ይልቅ ቶሎ ናና ጉዴን ስማልኝ'
“እህ፤ እየነገርሁሽ?”
“ስሞትልህ! ከእሸቴ ጋር እዚሁ አንደኛ ፎቅ ባለዉ ምግብ ቤት
ብትመጡልኝ፣ የምጋብዛችሁ አታዉቁትም: አንተስ ምናለ ለአንዳንዴስ እንኳን ንፋስ ቢያገኝህ? ሁልጊዜ እዚያ ዉስጥ ተቀብረህ” አልሁት፣ ለግብዣዬ ያለዉን ከበሬታ ዘንግቶ ላለመምጣት ሲያቅማማ በዚያም ላይ ሰዓቱ የምሳ ስለሆነ ሦስታችን አብረን የምንበላበት የመጀመሪያ አጋጣሚ ይሆንልናል። እንዳሰብሁት፣ ብዙም ሳያስጠብቁኝ ከእሸቴ ጋር ፊት እና
ኋላ ሆነዉ መጡልኝ፡
“አንቺ፤ ብለሽ ብለሽ ደግሞ እንዴት እንዴት ነዉ ያናገርሽኝ? እንደ ልጅ ና ከረሜላ ልግዛልህ ማለት እኮ ነዉ የቀረሽ አሁንማ አሁንማ” አለኝ በጨዋታ፣ ወንበር ስቦ ከአጠገቤ እየተቀመጠ፡ መልስ ከለከልሁት
“አንቺ? ምንድነዉ ደግሞ ለንቦጭሽ የታላቁን ንጉሥ አወዳደቅ ወድቋልሳ: ገና ለገና እርምሽን ልትጋብዥን ብትይ፣ ከአሁኑ ማኩረፍሽ ነዉ? አየህልኝ እሽቴ? ገና ከአሁኑ እንዲህ ከሆነች፣ ሂሳቡን ስትከፍልማ
እንደ ጨዉ ሟሙታ ወደ መሬት መስረጓ ነዉ በለኛ”
ወድጄ አይደለም ዝም ያልኋቸዉ ሆስፒታል የጀመሩኝ ክፉ ክፉ የሚባሉ ሐሳቦች ሁሉ አሁንም አሁንም ወደ ልቡናዬ እየመጡ ግብግብ ገጥመዉኛል፡ እንደ ምንም ጥርሴን ለመፈልቀቅ ሞከርሁ። የዉጤቱን ወሬ ከምሳ በኋላ መንገሩን ስለመረጥሁ፣ በግድ ፈገግ ለማለት እየታገልሁ
ነዉ፡ ብቻ የሆነ ያልሆነዉን እየቀላቀልሁ የጨዋታ ወሬ ለማምጣት ተዉሸለሸልሁ
“ምንድነዉ ልጄ?” አለ ባልቻ አዉቆብኝ ያልፈሰሰ እንባዬን እያበሰልኝ “ አሃ፤ ዛሬ ከነጋ አላየሁሽም ለካ? የት ዋልሽ?”
አስተናጋጁ እየተሸቆጠቆጠ መጥቶ የምንፈልገዉን ሊታዘዘን አጎበደደ፡ እሰይ! ገላገለኝ። በባዶ ሆዳቸዉ ሐቲታቸዉን ከምበላዉ፣
ምሳችንን በሰላም ብንበላ ለእነሱም ይሻላቸዋል። የቤቱን
የአገልግል ምግብ ከተጨማሪ ሱፍ ፍትፍት ጋር እንዲያመጣልን አዘዝን ሱፍ ፍትፍት የባልቻ የምንጊዜም ምርጫ መሆኑን
ከእሱ ጋር ለአንዴም
ቢሆን ማዕድ የተጋሩ ሁሉ ያዉቁለታል። የሚበላም የሚጣጠም ሲጠየቅ
ቀድሞ የሚመጣለት ነገር ሱፍ ነዉ። በሀገር ዉስጥ ምግብ ቤቶች ብቻም ሳይሆን፣ አንዴ ሩስያ አብረን የሄድን ጊዜ ሁሉ ቀዝቀዝ ያለ ሱፍ ፍትፍት ይኖራችኋል? ብሎ ሩስያዊቷን አስተናጋጅ ሲጠይቃት
ሰምቼዉ፣ የሳቅሁትን ሳቅ ሞቼም መርሳቴን እንጃልኝ! እስከ አሁን ትዝ ባለኝ ቁጥር ስቄ አይወጣልኝም: ሱፍ አዝዞ የለም ከተባለ፣ ለሆቴሉ የሚኖረዉ ግምት ሁሉ ወርዶ እንዴት እንደሚያደርገዉ አያድርስ ነዉ።
ይኼ ደግሞ ሆቴል ነዉ? ሱፍ ፍትፍት እንኳን የሌለበት ቤት! ብሎ
ሲያጣጥል ብዙ ጊዜ ሰምቼዋለሁ። ለእኔ ግን የሚበላ ይሁን እንጂ ምንም ቢሆን ያን ያህል አላማርጥም: በተለይ አሁን በኃይል ሞርሙሮኛል። ለወትሮዉ እንዲህ ድባቴ ዉስጥ ስሆን እንኳንስ ሊርበኝ ይቅርና የምግብ
ሽታ ሁሉ አይደርስብኝም ነበር አሁን ግን ምራቄ ኩችር ብሎ፣
ትንፋሼም ሳይቀር ሽታዉ እንደ ተለወጠ ለእኔም ታዉቆኛል።
“ችግር አለ እንዴ ዉቤ?” አለ እሸቴ፣ ከበላን በኋላ ከሁላችን በኋላ እጁን ታጥቦ ከመመለሱ፡
“ፊትሽ በፍጹም ልክ አይደለም” አለ፣ ባልቻም ተደርቦ፡
“ሆስፒታል ሄጄ ነበር''
“እ?” አሉ ኹለቱም፣ እኩል። የሆነዉን እና በሐኪሟ የተባልሁትን ሁሉ አንድም ሳላስቀር ነገርኋቸዉ። በየመሀሉ በድንጋጤ ከአሁን አሁን
ራሳቸዉን ይስታሉ ብዬ ስጠባበቅ፣ እነሱ ከመጤፍ ሳይቆጥሩት ቀሩብኝ ጭራሽ ባልቻማ ሊስቅብኝ ምንም አልቀረዉ፡ እሸቴም ቢሆን የምጠብቅበትን ያህል ጸጸት ቀርቶ ሐዘኔታ እንኳን አላሳየኝም፡
“ለዚህ ነዉ እንዴ ፊትሽን እንዲህ የክረምት ሰማይ ያስመሰልሽዉ?
“ከዚህ በላይ ምን አለና አባታለም?”
“ኧረ ዝም በይ! ደም አርግቶ የፈጠረንን አምላክ ለምናመልክ ለኛ፤ ይኼንን ጉዳይ ብለሽ … ምን እና ምኑ ተገናኝቶ፣ ሰዉ ሆነን እንደ
ተፈጠርን ጠፍቶሽ ነዉ? ልጄ ሙች! ካንቺ ይኼን አልጠብቅም”
ድንገት የእጅ ስልኩ ጮኸ፡ ወዲያዉ ፈገግታዉንም ተግሳጹንም አቋርጦ ስልኩን አነሳና፣ ለቅጽበት ያህል ከወዲያ በኩል አዳመጠ። ወዲያዉም
የምግቡን ሂሳብ ለመክፈል ኪሱን መፈታተሽ ሲጀምር አስቸኳይ ሁኔታ እንደ ተፈጠረ ገባኝ። ቀድሜዉ ሦስት ድፍን ድፍን መቶ ብሮች ጠረጴዛዉ ላይ አስቀመጥሁ።
“ምን ተፈጠረ?” አለ እሸቴ፣ እሱም እንደኔ ጥድፊያዉን በጥሞና እየተከታተለዉ ቆይቶ።
“ዕረፍት ያስፈልግሽ ነበር እዴ ዉቤ? አንድ መጥፎ ወሬ ደርሶኛል”
“ምነዉ ምን ተፈጠረ? ከየት ነዉ?”
“መስጊድ ላይ እሳት ተነስቷል ነዉ የሚሉኝ”
“የ..ት?” አለ እሸቴ፣ ልለዉ የነበረዉን ከአፌ ነጥቆኝ።
“ተከተሉኝ” ብሎ ከምግብ ቤቱ የመሮጥ ያህል ተራምዶ ወጣ፡ በእሱ ፍጥነት እግር በእግር ተከትለነዉ አሳንሠሩ ዉስጥ ገባንና ቁልፉን ተጭነን ወደ ላይኛዉ ፎቅ ጋለብን፡ በጠመዝማዛዉ መንገድ ገብተን
የለመድናቸዉን የደኅንነት ኬላዎች ሁሉ አልፈን በዚሁ ሕንጻ ወደ
ተሠወረዉ የሲራክ ፯ ማዕከል ስንደርስ፣ ሁሉም በየጥፍራቸዉ ቆመዉ አገኘናቸዉ እንኳንስ የጭንቅ ወሬ ተሰምቶበት፣ እንዲያዉም የዕረፍት
አልባዎች ቤት ነዉ ማዕከሉ
“እስኪ የታለ?” አለ ባልቻ፣ ከወገብ በላይ በግድግዳዉ ዙሪያ ወደ ተንጣለለዉ ዝርግ መከሰቻ ዓይኑን እያነጣጠረ፡
ደዉሎ የጠራዉ ልጅ የባልቻ ጥያቄ ስለገባዉ፣ የሚነካዉን ነካክቶ በርከት ያሉ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በሰፊዉ መከሰቻ ከዳር እስከ ዳር ደረደረልን እስከ ሚናራዉ ድረስ በኃይለኛ እሳት ሲንቀለቀል የሚያሳዩ
የመስጊድ ምስሎች ናቸዉ። ወላፈኑ እዚህ ያለንበት ድረስ በሚለበልብ እሳት ሲነድ ይታያል። ብዙ ሰዎችም እሳቱን ለማጥፋት ዙሪያዉን ሲዋደቁ ይታያሉ እንደ እሳቱ አያያዝ ግን መስጊዱን ማትረፍ የሚቻል አይመስለኝም:: ባይሆን ዙሪያዉን ባልተዛመተ እና በአካባቢዉ ተጨማሪ ዉድመት ባልደረሰ ስል በልቤ ጸለይሁ
👍35❤2👎1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ባለ ዲጂኖዉ ትንፋሹ ሳይቀር የሚሰማበት ቅርበት ላይ ከአጠገቤ ደርሷል። ምኔን ቢወጋኝ አንድ ምት እንደሚበቃኝ እያማረጠ ይመስለኛል ትንሽ ፋታ ስጠኝ። ዓይኔን ጨፍኜ ብቻ ስንቱን እንዳሰብሁት በዚች ቅጽበት! ሞት እንዲህ አብሮኝ ኖሯል ለካ። “ቁልቁል ወደ ምድር
ለመዉረድ የፈጀነዉን ያህል፣ የሩብ ሩቡን እንኳን ሽቅብ ወደ ሰማይ ለመዉጣት አንፈጀዉም” ትላለች እመዋ። እዉነቷን አይደል? እንዲያዉ ማርያም ብላዉ የምጡ ጭንቅ ቀለል ያለ ቢሆን እንኳን፣ ለመወለድ ቢያንስ ቢያንስ ለዘጠኝ ወራት በማሕጸን ዉስጥ መክረም የግድ ነዉ።ለመሞት ግን ይኸዉ አንዲት ቅጽበት እና ዲጂኖ ያለዉ ገዳይ በቂ የሚሆኑበት ጊዜ አለ።
ግንባሬን ይለኛል ጸጥ እላለሁ። አበቃልኝ።
እንደ ዛሬ ሞትን ቀርቤ፣ ትንፋሽ ለትንፋሽ ተሻትቼዉ አላዉቅም: በዓይነ ኅሊናዬ የመጡልኝን ሁሉ በልቤ ተሰናብቼ ራሴን ለሞት አደላደልሁ።እመዋ፣ ባልቻ እና እሸቴ ነበሩ ቀድመዉ ትዝ ያሉኝ፡ በእርግጥ በየመሀሉ
የመጡልኝን ሌሎች ማኅበርተኞቼን እና ጓደኞቼን ሁሉ አዳርሻለሁ።በመጨረሻም፣ በሆዴ ወደ ተሸከምሁት ፅንስ እጆቼን ሰድጄ ደባበስሁት፡ እህ? ለካንስ ሐኪሟ ፅንሱ የሴት ነዉ ብላኛለች፡ ሴት ከሆነች ደግሞ እመዋ ስም አዉጥታላታለች: ማን ብላ? ቱናት። ቱናትን በዳሰሳ ተሰናበትኋት፡ ፀእንዲያዉ ነዉ የተሰናበትኂት እንጂ፣ መቼስ እኔ ሞቼ
ቱናት አትተርፍ፡ አብረን ወደ ሞት ተጓዦች ነን
“ዉብርስት?” የሚል ቃል ድንገት አጠገቤ ሰማሁ ገዳዬ አይደል? እንደ ምንም የአንድ ዓይኔን ሽፋሽፍት ፈልቅቄ ስገልጥ፣ ገዳዬ ቆሞበት በነበረ ሥፍራ ቢራራ ቆሞበታል እንደገና ጨፈንሁና ብገልጥም፣ ከቢራራ በቀር ማንም በፊቴ የለም፡፡
“የት ገባ?”
“ማ ?”
“ባለ ዲጂኖዉ?”
ፍርስ ብሎ የንቀት ሳቁን ለቀቀብኝ፡ “ለካ ስ እንዲህ ፈሪ ነሽና” እያለ
እንደ መሽኮርመም እያደረገዉም ጭምር አሁንም አሁንም አሽካካብኝ::እዉነትም ገና ድንጋጤዬ አለቀቀኝም: ድንገት እርም እርም የሚል የብዙ
ሰዉ ሆታ ሰማሁና፣ ዞር ስል ሰዎች ወደ ቤተልሔሙ እና ወደ ግምጃ
ቤቱ ይሯሯጣሉ፡ አንዳንዱ አፈር፣ አንዳንዱ ዉሃ፣ አንዳንዱ ደግሞ
ቅጠል እየያዘ ይራወጣል ያ ይባስ ያ ይቅደም ያን ተወዉ. እዚህ
ጋ አምጣዉ የሚል የተለያየ ሰዉ ድምፅ ተሰማኝ፡
እሳቱ! አሁን ገና ወደ ልቡናዬ ተመለስሁ፡
“እሳቱ! ወይኔ ወይኔ! ቤተልሔሙን ፈጀዉ” ስል ጮኹኩ፣ በሚርገበገብ ድምፅ ብሞትስ ቆይ!? ደግሞ እኮ ለሰማዕትነት ዝግጁ ነኝ እያልሁ ስመጻደቅ ነበር እንደ ደህና ሰዉ በቤተ ክርስቲያን ከመጡብኝ እንኳንስ
ሌላ፣ ሞትንም አልፈራ ባይ ነበርሁ ሐሰት ይኼዋ ልኬን አወቅሁት መስዋእትነቱም ይቅርና፣ ከራሴ ቀድሜ የማተርፈዉ ምንም ነገር
አለመኖሩን ነዉ ያየሁት ቢሆንም ግን ቀደም ብዬ የደወልሁት ደወል
የጠራቸዉ ምዕመናን እንደ ደራሽ ጎርፈዉ፣ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ እሳቱን በአጭር አስቀረተዉታል። ቢራራም አጠገቤ ቆሞ በእኔ የሚስቀዉ፣ የእሳቱን መጥፋት ካረጋገጠ በኋላ እንደሆነ ገባኝ፡
ሰአሊ ለነ!
“ቆይ ግን ገዳዬ የት ተሰለበ? አሁን እኮ እንዲህ ብሎ ቆሞ ነበር''
አልሁት ቢራራን፣ እጄን ጦር እንደሚወረዉር አዳኝ አድርጌ እያሳየሁት እሺ እሳቱስ ከምኔዉ ጠፋ? ይኼ ሁሉ ሲሆን እንዴት እንደሆነ የማስታዉሰዉ ምንም ነገር የለኝም:: የሚደንቀዉ ደግሞ አሁንም ገና ድንጋጤዉ ጨርሶ አልለቀቀኝም: ቆመች ቆመች እንደሚባልላት ጨቅላ
የሚያደርገዉን የጉልበቴን መንቀጥቀጥ ማንም እንዳያይብኝ ተሳቀቅሁ፡ቢራራ ከፊቴ እስከሚሄድልኝ ድረስ በዝምታ ብጠባበቀዉም አልሄድልሽ
አለኝ፡ ባለሁበት ቁጢጥ አልሁና ወደ ልቡናዬ ለመመለስ፣ መድኃኒቴ የሆነችዋን ጸሎቴን በለሆሳስ አደረስሁ: ከቅድሙ አንጻር ልቤም የሚመታበት ፍጥነቱ በረድ ቢልም፣ ጨርሶ ግን ልክ ሊሆንልኝ አልቻለም
"እና ፈርቼ ነዉ?” አልሁት ቢራራን፣ ፈቀቅ ብሎ ወዳለዉ የእንጨት
መቀመጫ እየጎተትሁት።
“እንክት!” አለኝ፣ በእርግጠኝነት
“በእርግጥ ፈተና ባይኖር ሁሉ ተማሪ፣ ጠያቂ ባይኖር ሁሉ አስተማሪ መባሉን አዉቃለሁ: ግን እንደዚያ ነበርሁ ወይ እኔ? ተሞክሬ ባላዉቅ ነዉ
እዉነት? በጅቦች መካከል፣ በጨለማ አካፋይ ሞትን ተፋጥጬዉ አላዉቅም? ሌላዉ ሌላዉ ቢቀር፣ ሲራክን ከተቀላቀልሁ እንኳ ን
ይኼዉ ኹለተኛ ዓመቴን ጨልጫለሁ: እስከ አሁንም ድረስ ሐሞቴን የሚፈትኑ ስትና ስጓት ተልእኮዎች በየዕለቱ ከማዕከሉ እቀበላለሁ:: እንዲያዉ ምን ብረሳ ብረሳ በታላቁ ቤተ መንግሥት የገጠመኝን እረሳዋለሁ? እዉነት አተስ ያን ጀብዱ ሳትሰማ ቀርተህ ነዉ?” አልሁት፣ ቤተ መንግሥቱን መጥቀሴ ክፋት እንደ ሌላዉ በማስተዋል እኔ አሁን ጀብዱ ስለምለዉ ነገሬ ላይሰማ ቢችልም፣ ማዕከላችን ሲራክ ፯ በቤተ መንግሥት ምስጢር እንዳለዉ ያወቅነዉ ግን አብረን ነበር
“ሳትሰማ ቀርተህ ነዉ እዉነት ቢራራ?” አልሁት፣ ባለማመን። ይኼ ታሪክ ከተፈጸመ በኋላ፣ እንደኔ ላሉ የሲራክ ፯ መረጃ ሰብሳቢዎች በነበረዉ ወቅታዊ ስልጠና ጭምር ለምሳሌነት ተጠቅሶ እንደ ነበር
በማስታወስ፡
“በታላቁ ቤተ መ ግሥት?”
“ታዲያስ!”
“እንደምታዉቀዉ፣መአከላችን ሲራክ ዋና ዋና በሚባል
የመንግሥት…ብዬ ጀመርሁለት። እዉነትም አልሰማም ኖሯል
እየተቁነጠነጠ አዳመጠኝ።
እንደምታዉቀዉ፣ ማዕከላች ሲራክ ዋና ዋና በሚባሉ የመንግሥት እና ዓለም አቀፍ ዋና በሚባሉ የመንግሥት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ዉስጥም እጅግ ቁልፍ ሥራ ያላቸዉን ዳሳሾች (Sensors) እና ካሜራዎች በሥዉር አስቀምጧል: አንዳንዶቹ ድምፅ፣ አንዳንዶቹ ምስል፣ አንዳዶቹ ደግሞ እንቅስቃሴ በድብቅ እየዳሰሱ እና እየቀዱ ወደ ማዕከላችን የመረጃ ቋት
በቀጥታ የሚልኩ ናቸዉ:: ስለሆነም እነዚህ መሣሪያዎች በተሸሸጉበት አካባቢ ሁሉ የተፈሳችም ሆነ የተተነፈሰች ነገር ሲራክን አምልጣ ?
አታዉቅም: ምንም እንኳን መተዳደሪያ ሥነ ሥርዓቱ ስለማይፈቅድልኝ በየትኛዉ ቦታ ስንት ዳሳሽ መሣሪያ እንደ ተተከለ የማዉቅበት ደረጃ ላይ ባልሆንም፣ ከዐሥር ሺ ያላነሱ ዘመናዊ ዳሳሾች በተለያዩ ቦታዎች
እንደሚኖሩ እገምታለሁ: ለግምቴ ደግሞ በቂ ምክንያት አለኝ” አልሁት፣ የማዳመጥ ጉጉቱን ቀና ብዬ እያስተዋልሁበት ቋምጧል።
“ሰኞ ይሁን ማክሰኞ ቀኑን ዘነጋሁት እንጂ…”
ሰኞ ይሁን ማክሰኞ ቀኑን ዘነጋሁት እንጂ፣ የዛሬ ሰባት ወር ገደማ
ለአንድ ተልእኮ እንድዘጋጅ በራሱ በቀድሞዉ የሲራክ ፯ ኃላፊ ታዘዝሁ። “ ስለ ምንነቱ በዝርዝር ከመንገሩ በፊት፣ ስለ አደገኛነቱ አጥብቆ ሊያስረዳኝ ከሞከረ፡ እኔም ተልእኮዉ ምን ይሁን የት ይሁን ገና ሳላዉቀዉ፤ ምንም
ሥጋት እንዳይገባዉ በልበ ሙሉነት ገለጽሁለት።
“የለም የለም፣ የገባሽ አልመሰለኝም” አለኝ እንደገና፣ ጉዳዩን ማቃለሌ ገርሞት ባላስተዋልኋቸዉ ነገሮችም ሳይታዘበኝ የቀረ አይመስለኝም።
እንዲሁ ላይ ላዩን ፍርጥም አለብኝ፡ እዉነትም ከእሱ ጋር ቃል እየተመላለስሁ መሆኑን ራሱ ያስተዋልሁት ዘግይቼ ነበር
“ለወትሮዉ ማንኛዉንም ተልእኮ የምቀበለዉም ሆነ ተልዕኮዬን በተመለከተ የምነጋገረዉ ከቅርብ ኃላፊዬ ጋር ብቻ ነዉ። ሲጀመር የቀድሞዉን ዋና “ ኃላፊ ለመጀመሪያ ጊዜ በቅርበት ያየሁት ራሱ፣ በዚሁ ዕለት ባልቻ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ባለ ዲጂኖዉ ትንፋሹ ሳይቀር የሚሰማበት ቅርበት ላይ ከአጠገቤ ደርሷል። ምኔን ቢወጋኝ አንድ ምት እንደሚበቃኝ እያማረጠ ይመስለኛል ትንሽ ፋታ ስጠኝ። ዓይኔን ጨፍኜ ብቻ ስንቱን እንዳሰብሁት በዚች ቅጽበት! ሞት እንዲህ አብሮኝ ኖሯል ለካ። “ቁልቁል ወደ ምድር
ለመዉረድ የፈጀነዉን ያህል፣ የሩብ ሩቡን እንኳን ሽቅብ ወደ ሰማይ ለመዉጣት አንፈጀዉም” ትላለች እመዋ። እዉነቷን አይደል? እንዲያዉ ማርያም ብላዉ የምጡ ጭንቅ ቀለል ያለ ቢሆን እንኳን፣ ለመወለድ ቢያንስ ቢያንስ ለዘጠኝ ወራት በማሕጸን ዉስጥ መክረም የግድ ነዉ።ለመሞት ግን ይኸዉ አንዲት ቅጽበት እና ዲጂኖ ያለዉ ገዳይ በቂ የሚሆኑበት ጊዜ አለ።
ግንባሬን ይለኛል ጸጥ እላለሁ። አበቃልኝ።
እንደ ዛሬ ሞትን ቀርቤ፣ ትንፋሽ ለትንፋሽ ተሻትቼዉ አላዉቅም: በዓይነ ኅሊናዬ የመጡልኝን ሁሉ በልቤ ተሰናብቼ ራሴን ለሞት አደላደልሁ።እመዋ፣ ባልቻ እና እሸቴ ነበሩ ቀድመዉ ትዝ ያሉኝ፡ በእርግጥ በየመሀሉ
የመጡልኝን ሌሎች ማኅበርተኞቼን እና ጓደኞቼን ሁሉ አዳርሻለሁ።በመጨረሻም፣ በሆዴ ወደ ተሸከምሁት ፅንስ እጆቼን ሰድጄ ደባበስሁት፡ እህ? ለካንስ ሐኪሟ ፅንሱ የሴት ነዉ ብላኛለች፡ ሴት ከሆነች ደግሞ እመዋ ስም አዉጥታላታለች: ማን ብላ? ቱናት። ቱናትን በዳሰሳ ተሰናበትኋት፡ ፀእንዲያዉ ነዉ የተሰናበትኂት እንጂ፣ መቼስ እኔ ሞቼ
ቱናት አትተርፍ፡ አብረን ወደ ሞት ተጓዦች ነን
“ዉብርስት?” የሚል ቃል ድንገት አጠገቤ ሰማሁ ገዳዬ አይደል? እንደ ምንም የአንድ ዓይኔን ሽፋሽፍት ፈልቅቄ ስገልጥ፣ ገዳዬ ቆሞበት በነበረ ሥፍራ ቢራራ ቆሞበታል እንደገና ጨፈንሁና ብገልጥም፣ ከቢራራ በቀር ማንም በፊቴ የለም፡፡
“የት ገባ?”
“ማ ?”
“ባለ ዲጂኖዉ?”
ፍርስ ብሎ የንቀት ሳቁን ለቀቀብኝ፡ “ለካ ስ እንዲህ ፈሪ ነሽና” እያለ
እንደ መሽኮርመም እያደረገዉም ጭምር አሁንም አሁንም አሽካካብኝ::እዉነትም ገና ድንጋጤዬ አለቀቀኝም: ድንገት እርም እርም የሚል የብዙ
ሰዉ ሆታ ሰማሁና፣ ዞር ስል ሰዎች ወደ ቤተልሔሙ እና ወደ ግምጃ
ቤቱ ይሯሯጣሉ፡ አንዳንዱ አፈር፣ አንዳንዱ ዉሃ፣ አንዳንዱ ደግሞ
ቅጠል እየያዘ ይራወጣል ያ ይባስ ያ ይቅደም ያን ተወዉ. እዚህ
ጋ አምጣዉ የሚል የተለያየ ሰዉ ድምፅ ተሰማኝ፡
እሳቱ! አሁን ገና ወደ ልቡናዬ ተመለስሁ፡
“እሳቱ! ወይኔ ወይኔ! ቤተልሔሙን ፈጀዉ” ስል ጮኹኩ፣ በሚርገበገብ ድምፅ ብሞትስ ቆይ!? ደግሞ እኮ ለሰማዕትነት ዝግጁ ነኝ እያልሁ ስመጻደቅ ነበር እንደ ደህና ሰዉ በቤተ ክርስቲያን ከመጡብኝ እንኳንስ
ሌላ፣ ሞትንም አልፈራ ባይ ነበርሁ ሐሰት ይኼዋ ልኬን አወቅሁት መስዋእትነቱም ይቅርና፣ ከራሴ ቀድሜ የማተርፈዉ ምንም ነገር
አለመኖሩን ነዉ ያየሁት ቢሆንም ግን ቀደም ብዬ የደወልሁት ደወል
የጠራቸዉ ምዕመናን እንደ ደራሽ ጎርፈዉ፣ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ እሳቱን በአጭር አስቀረተዉታል። ቢራራም አጠገቤ ቆሞ በእኔ የሚስቀዉ፣ የእሳቱን መጥፋት ካረጋገጠ በኋላ እንደሆነ ገባኝ፡
ሰአሊ ለነ!
“ቆይ ግን ገዳዬ የት ተሰለበ? አሁን እኮ እንዲህ ብሎ ቆሞ ነበር''
አልሁት ቢራራን፣ እጄን ጦር እንደሚወረዉር አዳኝ አድርጌ እያሳየሁት እሺ እሳቱስ ከምኔዉ ጠፋ? ይኼ ሁሉ ሲሆን እንዴት እንደሆነ የማስታዉሰዉ ምንም ነገር የለኝም:: የሚደንቀዉ ደግሞ አሁንም ገና ድንጋጤዉ ጨርሶ አልለቀቀኝም: ቆመች ቆመች እንደሚባልላት ጨቅላ
የሚያደርገዉን የጉልበቴን መንቀጥቀጥ ማንም እንዳያይብኝ ተሳቀቅሁ፡ቢራራ ከፊቴ እስከሚሄድልኝ ድረስ በዝምታ ብጠባበቀዉም አልሄድልሽ
አለኝ፡ ባለሁበት ቁጢጥ አልሁና ወደ ልቡናዬ ለመመለስ፣ መድኃኒቴ የሆነችዋን ጸሎቴን በለሆሳስ አደረስሁ: ከቅድሙ አንጻር ልቤም የሚመታበት ፍጥነቱ በረድ ቢልም፣ ጨርሶ ግን ልክ ሊሆንልኝ አልቻለም
"እና ፈርቼ ነዉ?” አልሁት ቢራራን፣ ፈቀቅ ብሎ ወዳለዉ የእንጨት
መቀመጫ እየጎተትሁት።
“እንክት!” አለኝ፣ በእርግጠኝነት
“በእርግጥ ፈተና ባይኖር ሁሉ ተማሪ፣ ጠያቂ ባይኖር ሁሉ አስተማሪ መባሉን አዉቃለሁ: ግን እንደዚያ ነበርሁ ወይ እኔ? ተሞክሬ ባላዉቅ ነዉ
እዉነት? በጅቦች መካከል፣ በጨለማ አካፋይ ሞትን ተፋጥጬዉ አላዉቅም? ሌላዉ ሌላዉ ቢቀር፣ ሲራክን ከተቀላቀልሁ እንኳ ን
ይኼዉ ኹለተኛ ዓመቴን ጨልጫለሁ: እስከ አሁንም ድረስ ሐሞቴን የሚፈትኑ ስትና ስጓት ተልእኮዎች በየዕለቱ ከማዕከሉ እቀበላለሁ:: እንዲያዉ ምን ብረሳ ብረሳ በታላቁ ቤተ መንግሥት የገጠመኝን እረሳዋለሁ? እዉነት አተስ ያን ጀብዱ ሳትሰማ ቀርተህ ነዉ?” አልሁት፣ ቤተ መንግሥቱን መጥቀሴ ክፋት እንደ ሌላዉ በማስተዋል እኔ አሁን ጀብዱ ስለምለዉ ነገሬ ላይሰማ ቢችልም፣ ማዕከላችን ሲራክ ፯ በቤተ መንግሥት ምስጢር እንዳለዉ ያወቅነዉ ግን አብረን ነበር
“ሳትሰማ ቀርተህ ነዉ እዉነት ቢራራ?” አልሁት፣ ባለማመን። ይኼ ታሪክ ከተፈጸመ በኋላ፣ እንደኔ ላሉ የሲራክ ፯ መረጃ ሰብሳቢዎች በነበረዉ ወቅታዊ ስልጠና ጭምር ለምሳሌነት ተጠቅሶ እንደ ነበር
በማስታወስ፡
“በታላቁ ቤተ መ ግሥት?”
“ታዲያስ!”
“እንደምታዉቀዉ፣መአከላችን ሲራክ ዋና ዋና በሚባል
የመንግሥት…ብዬ ጀመርሁለት። እዉነትም አልሰማም ኖሯል
እየተቁነጠነጠ አዳመጠኝ።
እንደምታዉቀዉ፣ ማዕከላች ሲራክ ዋና ዋና በሚባሉ የመንግሥት እና ዓለም አቀፍ ዋና በሚባሉ የመንግሥት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ዉስጥም እጅግ ቁልፍ ሥራ ያላቸዉን ዳሳሾች (Sensors) እና ካሜራዎች በሥዉር አስቀምጧል: አንዳንዶቹ ድምፅ፣ አንዳንዶቹ ምስል፣ አንዳዶቹ ደግሞ እንቅስቃሴ በድብቅ እየዳሰሱ እና እየቀዱ ወደ ማዕከላችን የመረጃ ቋት
በቀጥታ የሚልኩ ናቸዉ:: ስለሆነም እነዚህ መሣሪያዎች በተሸሸጉበት አካባቢ ሁሉ የተፈሳችም ሆነ የተተነፈሰች ነገር ሲራክን አምልጣ ?
አታዉቅም: ምንም እንኳን መተዳደሪያ ሥነ ሥርዓቱ ስለማይፈቅድልኝ በየትኛዉ ቦታ ስንት ዳሳሽ መሣሪያ እንደ ተተከለ የማዉቅበት ደረጃ ላይ ባልሆንም፣ ከዐሥር ሺ ያላነሱ ዘመናዊ ዳሳሾች በተለያዩ ቦታዎች
እንደሚኖሩ እገምታለሁ: ለግምቴ ደግሞ በቂ ምክንያት አለኝ” አልሁት፣ የማዳመጥ ጉጉቱን ቀና ብዬ እያስተዋልሁበት ቋምጧል።
“ሰኞ ይሁን ማክሰኞ ቀኑን ዘነጋሁት እንጂ…”
ሰኞ ይሁን ማክሰኞ ቀኑን ዘነጋሁት እንጂ፣ የዛሬ ሰባት ወር ገደማ
ለአንድ ተልእኮ እንድዘጋጅ በራሱ በቀድሞዉ የሲራክ ፯ ኃላፊ ታዘዝሁ። “ ስለ ምንነቱ በዝርዝር ከመንገሩ በፊት፣ ስለ አደገኛነቱ አጥብቆ ሊያስረዳኝ ከሞከረ፡ እኔም ተልእኮዉ ምን ይሁን የት ይሁን ገና ሳላዉቀዉ፤ ምንም
ሥጋት እንዳይገባዉ በልበ ሙሉነት ገለጽሁለት።
“የለም የለም፣ የገባሽ አልመሰለኝም” አለኝ እንደገና፣ ጉዳዩን ማቃለሌ ገርሞት ባላስተዋልኋቸዉ ነገሮችም ሳይታዘበኝ የቀረ አይመስለኝም።
እንዲሁ ላይ ላዩን ፍርጥም አለብኝ፡ እዉነትም ከእሱ ጋር ቃል እየተመላለስሁ መሆኑን ራሱ ያስተዋልሁት ዘግይቼ ነበር
“ለወትሮዉ ማንኛዉንም ተልእኮ የምቀበለዉም ሆነ ተልዕኮዬን በተመለከተ የምነጋገረዉ ከቅርብ ኃላፊዬ ጋር ብቻ ነዉ። ሲጀመር የቀድሞዉን ዋና “ ኃላፊ ለመጀመሪያ ጊዜ በቅርበት ያየሁት ራሱ፣ በዚሁ ዕለት ባልቻ
👍38❤5🥰1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
ዉሃ ሆንሁ፣ የመጨረሻዉን ድንጋጤ ደነገጥሁ።
ከነበርሁበት የምድር በታቹ የሲራክ ፯ ማዕከል ወጥቼ በቅርበት ወደሚገኘዉ የድንግል ማርያም ገዳም ለጸሎት ገባሁ አንድ ያለኝ አቅም ጸሎት ነዉና፣ አሳፍሮኝ የማያዉቀዉን አምላክ በእናትህ እርዳኝ አልሁት ተንበርክኬ ከተንበረከክሁበት ተነስቼ በምሥራቅ በኩል ባለዉ የቅጽሩ
በር ልወጣ እየተራመድሁ ልክ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ላይ ስደርስ፣ ደስ የሚያሰኝ የሕጻናት መዝሙር በጆሮዬ ጥልቅ አለ በክፍቱ መስኮት አስግጌ ወደ ዉስጥ ስመለከት፣ ሰልፍና ልብሳቸዉን ያሳመሩ ሕጻናት “ሀገሪትነ” የሚለዉን ነባር ዝማሬ በኅብረት ያጠናሉ። ለአጭር
አፍታ ከዝማሬያቸዉ ቀምሼ መንገዴን ልቀጥል እግሬን ሳነሳ አንድ በየት
በኩል እንደ መጣ ያላየሁት፤ 'ቤ መ' የሚል ኮድ ያለዉ ታርጋ የለጠፈ
መኪና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በር ጥሩንባዉን ነፋና ሲጢጥ ብሎ ቆመ። የታርጋዉ ኮድ ትኩረቴን ስለ ሳበዉ፣ በአዳራሹ እና በግቢዉ አጥር መካከል ወዳለዉ ሰዋራ ሥፍራ ተሰዉሬ የሚሆነዉን ሁሉ በሥርቆሽ መከታተሌን ጀመርሁ: አፍታም ሳትቆይ፣ ሕጻናቱን
እያስጠናች የነበረችዋ ወጣት ወደ በሩ ብቅ ብላ አየችዉና ልጆቹን
እንዲወጡ ጠራቻቸዉ። ሕጻናቱም በደስታ እየፈነደቁ ተሯሩጠዉ ወጥተዉ የመኪናዉ በር እስከሚከፈትላቸዉ ድረስ ተቁነጠነጡ።
“ኧረ ክፈቱልን” ይላል አንደኛዉ ሕጻን፣ አላዳርስ ብሎት በሩን ራሱ
ለመክፈት እየታገለ
“ስሚ ለማን እንደምዘምር አዉቀሻል ግን? ለመንግሥት እኮ ነዉ” ትላለች ሌላኘዋ ጓደኛዋን ለማስቀናት በሚመስል አኳኋን አንገቷን እየወዘወዘች።
“ለመግሥት? ኧረ አይባልም!” ብላ አረመቻት ያቺኛዋ፣ በሳቅ ቡፍ
እያለችባት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም ጠርታ፣ መንግሥት ያለችዋን ልጅ አላገጠችባት።
አሁን ነዉ እንግዲህ መፍጠን አልሁት ለራሴ፡ ዕድሎች ከስንት አንድ
ከላይ ይወርዱልናል፣ አብዛኞቻችን ግን ራሳችን ነን የፈጠርናቸዉ› ሲባል
ሰምቼ ነበር በማዕከላችን በሲራክ ፯ ከስንት አንድ ከሚወርዱት ዕድሎች
አንደኛዉ ይኼዉ የዓይኔ ብረቱ ሥር ወርዶልኛል።
እንዴት ብጠቀመዉ ይሻላል?
ሁሉም ሕጻናት ከወጡ በኋላ መዝሙሩን ያስጠናችዋ ወጣት መብራቱን
አጠፋፍታ ነጠላዋንም በቅጡ እያጣፋች መጣች፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ሾፌሩ
አልወረደም አለመዉረዱ ሲገርመኝ፤ በሩንም ራሷ እንድትከፍትላቸዉ
ጠበቃት እሷ ደርሳ ስትከፍትላቸዉ ልጆቹ እሽቅድምድም ፈጥረዉ አይገቡ የለም እርስ በእርስ እየተጣጣሉ ገቡ፡ አሁን መኪናዉ ፊቱን አዙሮ ይሄዳል ብዬ ስጠባበቅ፣ ምን እንደ ረሳች እንጃላት፣ አስጠኛቸዉ ወረደችና ተመልሳ ወደ አዳራሹ ሮጣ ገባች። ይኸኔ ጥግ ለጥግ
ተሹለኩልኬ የአዳራሹን የኋላ በር በኃይል አንኳኳሁባት። ያለ ምንም ፋታ ደጋግሜ ሳንጓጓባት ብልጭ ብሎባት በእልህ ከፈተችልኝ።
“እ! ምንድነዉ?” አለች፣ በሩን በጥድፊያ ስትከፍተዉ እኔ በድንግዝግዙ
ዉስጥ ብቁለጨለጭባት የተመለሰችዉ ከበሮዉን ረስታዉ ኖሯል ለካ፣
በቀኝ ትከሻዋ አንግታዋለች ለኹለት ሰዓታት ሰመመን ዉስጥ የሚከተዉን ቅባት የረጨሁባቸዉ መዳፎቼን እያፋተግሁ ትንሽ የመዘናጊያ ፋታ ከሰጠኋት በኋላ ዘልዬ አፏን አፈንሁት፡ በቅጽበት መዝለፍለፍ ስትጀመርልኝ፤ ከበሮዉን በአንድ እጄ፣ እሷን ደግሞ
በሌላኛዉ እጄ ለመደገፍ ሞከርሁ፡ ሽርተት ብላ መሬት ያዘችልኝ፡ ዝቅ ብዬ እጄን በመሬቱ አሽቼ ቅባቱን ካረከስሁት በኋላ፣ ነጠላዋን ልክ እሷ ተከናንባዉ እንደነበር አድርጌ አጣፋሁትና ከበሮዉን አንስቼ አነገትሁት ክራሬንም በግራ እጄ አንጠለጠልሁትና መብራቱን አጠፋፋሁ፡፡
መኪናዉም ፊቱን አዙሮ ለመሄድ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቀኝ፡ ከሾፌሩ ይልቅ ሕጻናቱ እንዳይለዩኝ የባሰ ስለ ሰጋሁ፣ ከበሮዉን ከኋላ ጭኜ፣ ጋቢና ገባሁ ብቻ የፈራሁትን ያህል ሳልቸገር፣ ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት ገባሁ የመኪና ማቆሚያዉ ላይ ስንደርስ፣ ሌላ ሰዉ ተቀብሎን ወደ
ግብዣዉ አዳራሽ ወሰደን በዚያ ስንደርስ ደግሞ አንዲት ባህላዊ ቀሚስ
የለበስች ሴት ተቀብላ ከመድረኩ ጀርባ ካሉት ክፍሎች ወደ አንደኛዉ
አስገባችን ክፍሉን ሳየዉ ጠበብ ያለ ቢመስለኝም፣ ስንገባበት ግን ጠብ
እንኳን አላልንበትም ሌላ ብዙ ሰዉ ቢጨመር ሁሉ አይጠብም፡ በዚያም
ላይ የመድረኩን ትዕይንት በቀጥታ የሚያስተላልፍልን ዘመናዊ
ቴሌቪዥን ግድግዳዉ ላይ ተሰቅሎበታል
አሁን ነዉ ጉዱ ከሕጻናቱ ጋር በደማቅ ብርሃን ልፋጠጥ ነዉ፡ መቼም ጥያቄ
መጠየቃቸዉ አይቀር፣ ወይ ደግሞ እንድናገር የሚያደርጉበት አንድ ነገር
አያጡም: ያስጠናቻቸዉ ወጣት እንዳልሆንሁ ሲያዉቁ ምን ያደርጉ
ይሆን? በተቻለኝ መጠን አንገቴን አቀርቅሬ ወዲያ ወዲህ እያልሁ ራሴን ባተሌ አደረግሁባቸዉ። ዓይናቸዉ ዉስጥ ላለመግባት ብዙ ተፍተለተልሁ መቆያ ክፍል የሰጠችን ደርባባ ሴት ተመልሳ መጣችና የመርሐ ግብሩ ቅደም ተከተል የሰፈረበት ወረቀት ሰጠችኝ፡ አስከትላም፣
የኛ ተራ እስከሚደርስ ድረስ የመጨረሻ ልምምድ ማድረግ ከፈለግን፣
ያለንበት ክፍል ድምፅ ወደ ዉጪ ስለማያስወጣ እዚሁ መለማመድ
እንደምንችል አሳወቀችኝ፡ ስለዚያ ገና ሳላመሰግናት፣ መቆያ ምግብ
እንድናዝዝ ጎንበስ ብላ ጠየቀችን፡ እንዲህ ያለችዋ ሽቁጥቁጥ ሴት ለሕጻናቱ ከተመደበች፣ ለዋናዎቹ እንግዶችማ እንዴት ያለ ሰዉ ሊመደብ እንደሚችል ገመትሁ። መቼም ትሕትናዋ ወደር አይገኝለትም: ምንም እንኳን ሕጻናቱ ምርጫቸዉን እየለዋወጡ ረዥም ሰዓት ቢወስዱባትም፣ከበሬታዋ ግን አልቀነስም፡ እኔም እንዲሁ ወዳፌ የመጣልኝን የባቄላ
ሾርባ አዘዝሁ።
የሕጻናቱን መዝሙር ተከትሎ መንዙማ የሚያቀርቡ ሙስሊም ሕጻናትም መኖራቸዉን ያወቅሁት ወረቀቱ ላይ የሰፈረዉን ዝርዝር መርሐ ግብር ከተመለከትሁ በኋላ ነበር ሰዓቴን ስመለhት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ይላል። በዕቅዱ መሠረት መዝሙር ለሚቀርብበት ተራ፣ ሃያ ደቂቃዎች ይቀራሉ ማለት ነዉ: ከፊቴ የተሰቀለዉ ቴሌቪዥን፣
የአዳራሹን ትዕይንት ቀጥታ እያመጣ ስለሚያሳየኝ፣ የተጠቀሱት መርሐ
ግብራት ያለ ምንም መጓተት በየተራቸዉ እየቀረቡ መሆኑን አዉቄያለሁ:
ሲንሾካሾኩ ሰምቼ በቀስታ ዞር ብል ሁሉም ሕጻናት አፍጥጠዉብኛል ዝምታየ ሽሽቴ፣ አድራጎቴ ሁሉ ገርሟቸዉ! ወዲያ ስልም ወዲህም ስል በዓይናቸዉ ይከታተሉኛል። የመጣዉ ይምጣ ብዬ ክንብንቤን ገለጥ
አደረግሁና፤ ማንነቴን በከፊል ነገርኋቸዉ።
“እንዴ?” ተባባሉ
“አላልኋችሁም? እግዚሐርያ አይደለችም” አለ አንደኛዉ ሕጻን፣ዉርርዱን በማሸነፍ።
“እሷስ?”
“እግዚሐርያስ?”
"በጥያቄ አካለቡኝ"
“እግዚሐርያ እኮ ድገት አሟት ተተኪልኝ ብላኝ ነዉ” አልኋቸዉ፣ መዝሙሩን ያስጠናቻቸዉ ልጅ እግዚሐርያ መባሏን ከራሳቸዉ አፍ ስላወቅሁ ስሟን መጥራቴ ለአመኔታ እንደሚያግዘኝ በማሰብ
“ኧረ ቅድም ደህና አልነበረች? ከምኔዉ አመማት?” አለ፣ ከመካከላቸዉ
ቅድም ጀምሮ ቀደም ቀደም የሚለዉ ልጅ።
“ግድየለምቆይ፤ በኋላ በስልክ አገናኛችኋለሁ: አሁን መዝሙሩን
ለመጨረሻ ጊዜ እንለማመደዉ? የማቅረቢያ ሰዓታችን እየደረሰ ነዉ። በሉ
ተነሱ። ተነሷ” አልሁ በመለማመጥም በማጣደፍም ጭምር፣ ከዚህ በላይ
እንዳይከራከሩኝ በልቤ እየጸልይሁ፡ ክራሬን እየቃኘሁ “በሉ እሺ፤
መዝሙሩን ለመዘመር፣ በአብ በወልድ በመፈስ ቅዱስ ስም…”አልኋቸዉ፣ ፋታ ላለመስጠት እዉነትም አላሳፈሩኝም፤ ብድግ ብድግ አሉልኝ፡ ከመካከላቸዉ ትንሽ ከፍ የምትለዋ ልጅ ከበሮዉን አነሳች፡ እኔም መዝሙሩን በቅጡ የምችለዉ ስለሆነ፣ እምብዛም
ሳልደነቃቀፍባቸዉ ጥሩ አድርገን አብረን ወጣነዉ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
ዉሃ ሆንሁ፣ የመጨረሻዉን ድንጋጤ ደነገጥሁ።
ከነበርሁበት የምድር በታቹ የሲራክ ፯ ማዕከል ወጥቼ በቅርበት ወደሚገኘዉ የድንግል ማርያም ገዳም ለጸሎት ገባሁ አንድ ያለኝ አቅም ጸሎት ነዉና፣ አሳፍሮኝ የማያዉቀዉን አምላክ በእናትህ እርዳኝ አልሁት ተንበርክኬ ከተንበረከክሁበት ተነስቼ በምሥራቅ በኩል ባለዉ የቅጽሩ
በር ልወጣ እየተራመድሁ ልክ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ላይ ስደርስ፣ ደስ የሚያሰኝ የሕጻናት መዝሙር በጆሮዬ ጥልቅ አለ በክፍቱ መስኮት አስግጌ ወደ ዉስጥ ስመለከት፣ ሰልፍና ልብሳቸዉን ያሳመሩ ሕጻናት “ሀገሪትነ” የሚለዉን ነባር ዝማሬ በኅብረት ያጠናሉ። ለአጭር
አፍታ ከዝማሬያቸዉ ቀምሼ መንገዴን ልቀጥል እግሬን ሳነሳ አንድ በየት
በኩል እንደ መጣ ያላየሁት፤ 'ቤ መ' የሚል ኮድ ያለዉ ታርጋ የለጠፈ
መኪና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በር ጥሩንባዉን ነፋና ሲጢጥ ብሎ ቆመ። የታርጋዉ ኮድ ትኩረቴን ስለ ሳበዉ፣ በአዳራሹ እና በግቢዉ አጥር መካከል ወዳለዉ ሰዋራ ሥፍራ ተሰዉሬ የሚሆነዉን ሁሉ በሥርቆሽ መከታተሌን ጀመርሁ: አፍታም ሳትቆይ፣ ሕጻናቱን
እያስጠናች የነበረችዋ ወጣት ወደ በሩ ብቅ ብላ አየችዉና ልጆቹን
እንዲወጡ ጠራቻቸዉ። ሕጻናቱም በደስታ እየፈነደቁ ተሯሩጠዉ ወጥተዉ የመኪናዉ በር እስከሚከፈትላቸዉ ድረስ ተቁነጠነጡ።
“ኧረ ክፈቱልን” ይላል አንደኛዉ ሕጻን፣ አላዳርስ ብሎት በሩን ራሱ
ለመክፈት እየታገለ
“ስሚ ለማን እንደምዘምር አዉቀሻል ግን? ለመንግሥት እኮ ነዉ” ትላለች ሌላኘዋ ጓደኛዋን ለማስቀናት በሚመስል አኳኋን አንገቷን እየወዘወዘች።
“ለመግሥት? ኧረ አይባልም!” ብላ አረመቻት ያቺኛዋ፣ በሳቅ ቡፍ
እያለችባት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም ጠርታ፣ መንግሥት ያለችዋን ልጅ አላገጠችባት።
አሁን ነዉ እንግዲህ መፍጠን አልሁት ለራሴ፡ ዕድሎች ከስንት አንድ
ከላይ ይወርዱልናል፣ አብዛኞቻችን ግን ራሳችን ነን የፈጠርናቸዉ› ሲባል
ሰምቼ ነበር በማዕከላችን በሲራክ ፯ ከስንት አንድ ከሚወርዱት ዕድሎች
አንደኛዉ ይኼዉ የዓይኔ ብረቱ ሥር ወርዶልኛል።
እንዴት ብጠቀመዉ ይሻላል?
ሁሉም ሕጻናት ከወጡ በኋላ መዝሙሩን ያስጠናችዋ ወጣት መብራቱን
አጠፋፍታ ነጠላዋንም በቅጡ እያጣፋች መጣች፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ሾፌሩ
አልወረደም አለመዉረዱ ሲገርመኝ፤ በሩንም ራሷ እንድትከፍትላቸዉ
ጠበቃት እሷ ደርሳ ስትከፍትላቸዉ ልጆቹ እሽቅድምድም ፈጥረዉ አይገቡ የለም እርስ በእርስ እየተጣጣሉ ገቡ፡ አሁን መኪናዉ ፊቱን አዙሮ ይሄዳል ብዬ ስጠባበቅ፣ ምን እንደ ረሳች እንጃላት፣ አስጠኛቸዉ ወረደችና ተመልሳ ወደ አዳራሹ ሮጣ ገባች። ይኸኔ ጥግ ለጥግ
ተሹለኩልኬ የአዳራሹን የኋላ በር በኃይል አንኳኳሁባት። ያለ ምንም ፋታ ደጋግሜ ሳንጓጓባት ብልጭ ብሎባት በእልህ ከፈተችልኝ።
“እ! ምንድነዉ?” አለች፣ በሩን በጥድፊያ ስትከፍተዉ እኔ በድንግዝግዙ
ዉስጥ ብቁለጨለጭባት የተመለሰችዉ ከበሮዉን ረስታዉ ኖሯል ለካ፣
በቀኝ ትከሻዋ አንግታዋለች ለኹለት ሰዓታት ሰመመን ዉስጥ የሚከተዉን ቅባት የረጨሁባቸዉ መዳፎቼን እያፋተግሁ ትንሽ የመዘናጊያ ፋታ ከሰጠኋት በኋላ ዘልዬ አፏን አፈንሁት፡ በቅጽበት መዝለፍለፍ ስትጀመርልኝ፤ ከበሮዉን በአንድ እጄ፣ እሷን ደግሞ
በሌላኛዉ እጄ ለመደገፍ ሞከርሁ፡ ሽርተት ብላ መሬት ያዘችልኝ፡ ዝቅ ብዬ እጄን በመሬቱ አሽቼ ቅባቱን ካረከስሁት በኋላ፣ ነጠላዋን ልክ እሷ ተከናንባዉ እንደነበር አድርጌ አጣፋሁትና ከበሮዉን አንስቼ አነገትሁት ክራሬንም በግራ እጄ አንጠለጠልሁትና መብራቱን አጠፋፋሁ፡፡
መኪናዉም ፊቱን አዙሮ ለመሄድ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቀኝ፡ ከሾፌሩ ይልቅ ሕጻናቱ እንዳይለዩኝ የባሰ ስለ ሰጋሁ፣ ከበሮዉን ከኋላ ጭኜ፣ ጋቢና ገባሁ ብቻ የፈራሁትን ያህል ሳልቸገር፣ ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት ገባሁ የመኪና ማቆሚያዉ ላይ ስንደርስ፣ ሌላ ሰዉ ተቀብሎን ወደ
ግብዣዉ አዳራሽ ወሰደን በዚያ ስንደርስ ደግሞ አንዲት ባህላዊ ቀሚስ
የለበስች ሴት ተቀብላ ከመድረኩ ጀርባ ካሉት ክፍሎች ወደ አንደኛዉ
አስገባችን ክፍሉን ሳየዉ ጠበብ ያለ ቢመስለኝም፣ ስንገባበት ግን ጠብ
እንኳን አላልንበትም ሌላ ብዙ ሰዉ ቢጨመር ሁሉ አይጠብም፡ በዚያም
ላይ የመድረኩን ትዕይንት በቀጥታ የሚያስተላልፍልን ዘመናዊ
ቴሌቪዥን ግድግዳዉ ላይ ተሰቅሎበታል
አሁን ነዉ ጉዱ ከሕጻናቱ ጋር በደማቅ ብርሃን ልፋጠጥ ነዉ፡ መቼም ጥያቄ
መጠየቃቸዉ አይቀር፣ ወይ ደግሞ እንድናገር የሚያደርጉበት አንድ ነገር
አያጡም: ያስጠናቻቸዉ ወጣት እንዳልሆንሁ ሲያዉቁ ምን ያደርጉ
ይሆን? በተቻለኝ መጠን አንገቴን አቀርቅሬ ወዲያ ወዲህ እያልሁ ራሴን ባተሌ አደረግሁባቸዉ። ዓይናቸዉ ዉስጥ ላለመግባት ብዙ ተፍተለተልሁ መቆያ ክፍል የሰጠችን ደርባባ ሴት ተመልሳ መጣችና የመርሐ ግብሩ ቅደም ተከተል የሰፈረበት ወረቀት ሰጠችኝ፡ አስከትላም፣
የኛ ተራ እስከሚደርስ ድረስ የመጨረሻ ልምምድ ማድረግ ከፈለግን፣
ያለንበት ክፍል ድምፅ ወደ ዉጪ ስለማያስወጣ እዚሁ መለማመድ
እንደምንችል አሳወቀችኝ፡ ስለዚያ ገና ሳላመሰግናት፣ መቆያ ምግብ
እንድናዝዝ ጎንበስ ብላ ጠየቀችን፡ እንዲህ ያለችዋ ሽቁጥቁጥ ሴት ለሕጻናቱ ከተመደበች፣ ለዋናዎቹ እንግዶችማ እንዴት ያለ ሰዉ ሊመደብ እንደሚችል ገመትሁ። መቼም ትሕትናዋ ወደር አይገኝለትም: ምንም እንኳን ሕጻናቱ ምርጫቸዉን እየለዋወጡ ረዥም ሰዓት ቢወስዱባትም፣ከበሬታዋ ግን አልቀነስም፡ እኔም እንዲሁ ወዳፌ የመጣልኝን የባቄላ
ሾርባ አዘዝሁ።
የሕጻናቱን መዝሙር ተከትሎ መንዙማ የሚያቀርቡ ሙስሊም ሕጻናትም መኖራቸዉን ያወቅሁት ወረቀቱ ላይ የሰፈረዉን ዝርዝር መርሐ ግብር ከተመለከትሁ በኋላ ነበር ሰዓቴን ስመለhት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ይላል። በዕቅዱ መሠረት መዝሙር ለሚቀርብበት ተራ፣ ሃያ ደቂቃዎች ይቀራሉ ማለት ነዉ: ከፊቴ የተሰቀለዉ ቴሌቪዥን፣
የአዳራሹን ትዕይንት ቀጥታ እያመጣ ስለሚያሳየኝ፣ የተጠቀሱት መርሐ
ግብራት ያለ ምንም መጓተት በየተራቸዉ እየቀረቡ መሆኑን አዉቄያለሁ:
ሲንሾካሾኩ ሰምቼ በቀስታ ዞር ብል ሁሉም ሕጻናት አፍጥጠዉብኛል ዝምታየ ሽሽቴ፣ አድራጎቴ ሁሉ ገርሟቸዉ! ወዲያ ስልም ወዲህም ስል በዓይናቸዉ ይከታተሉኛል። የመጣዉ ይምጣ ብዬ ክንብንቤን ገለጥ
አደረግሁና፤ ማንነቴን በከፊል ነገርኋቸዉ።
“እንዴ?” ተባባሉ
“አላልኋችሁም? እግዚሐርያ አይደለችም” አለ አንደኛዉ ሕጻን፣ዉርርዱን በማሸነፍ።
“እሷስ?”
“እግዚሐርያስ?”
"በጥያቄ አካለቡኝ"
“እግዚሐርያ እኮ ድገት አሟት ተተኪልኝ ብላኝ ነዉ” አልኋቸዉ፣ መዝሙሩን ያስጠናቻቸዉ ልጅ እግዚሐርያ መባሏን ከራሳቸዉ አፍ ስላወቅሁ ስሟን መጥራቴ ለአመኔታ እንደሚያግዘኝ በማሰብ
“ኧረ ቅድም ደህና አልነበረች? ከምኔዉ አመማት?” አለ፣ ከመካከላቸዉ
ቅድም ጀምሮ ቀደም ቀደም የሚለዉ ልጅ።
“ግድየለምቆይ፤ በኋላ በስልክ አገናኛችኋለሁ: አሁን መዝሙሩን
ለመጨረሻ ጊዜ እንለማመደዉ? የማቅረቢያ ሰዓታችን እየደረሰ ነዉ። በሉ
ተነሱ። ተነሷ” አልሁ በመለማመጥም በማጣደፍም ጭምር፣ ከዚህ በላይ
እንዳይከራከሩኝ በልቤ እየጸልይሁ፡ ክራሬን እየቃኘሁ “በሉ እሺ፤
መዝሙሩን ለመዘመር፣ በአብ በወልድ በመፈስ ቅዱስ ስም…”አልኋቸዉ፣ ፋታ ላለመስጠት እዉነትም አላሳፈሩኝም፤ ብድግ ብድግ አሉልኝ፡ ከመካከላቸዉ ትንሽ ከፍ የምትለዋ ልጅ ከበሮዉን አነሳች፡ እኔም መዝሙሩን በቅጡ የምችለዉ ስለሆነ፣ እምብዛም
ሳልደነቃቀፍባቸዉ ጥሩ አድርገን አብረን ወጣነዉ
👍39
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ረቂቋን የጆሮ ማዳመጫ አዉቆብኝ ኖሯል፤ መንጭቆ አወጣብኝ፡፡
ማደመጫዉን የያዘበትን እጁን ሳይ ተገለጠልኝ ባልቻ በአንድ ወቅት
ከፍተኛ የመንግሥት ደኅንነት ሹሞችን አጠቃላይ መገለጫቸዉን ለጥቂት
የሲራክ፯ አባላት በገለጸልን ጊዜ፣ ስለዚህ ሰዉ ልዩ ምልክት የነገረን አስታዉሼ ይኼን ሰዉ ገመትሁት አወቅሁት የቀለበት ጣቱ ከስሯ ጀምራ የለችም: በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ሰው
እጅ መግባቴን፣ አሁን አወቅሁ ሰዉዬዉ የሀገር ዉስጥ ደንነት ዋና መምሪያ ሹም መሆኑን አሁን ገና፣ ነገሮች ሁሉ ከተጨመላለቀ በኋላ ተረዳሁ። አጠመድሁ ስል እንደ ተጠመድሁ ያወቅሁት፣ አሁን ገና ሁለት እጆቹ ካነቁኝ፣ ድፍርስ ዓይኑ ካፈጠጠብኝ፣ ድርብርብ ጥርሱ ካገጠጠብኝ በኋላ ነበር። መጠርጠር አልነበረብኝም? ነበረብኝ።
«ላም ሆይ ላም ሆይ ሞኟ ላም ሆይ
ሣሩን አየሽና ገደሉን ሳታይ
እልም ካለው ገደል ወደቅሽብን ወይ
እያልሁ፣ መስኮት ቀርቶ ስንጥቅ እንኳን በሌለዉ አመዳም ግድግዳ ላይ
አፍጥጬ በራሴ አላገጥሁበት።
“ጥሩ” አለ የተገለበጠችዋን ወንበር አቃንቶ ራሱ እየተቀመጠባት
“እንተዋወቃ… ማን ብዬ ልጥራሽ?”
ባፍንጫዬ አናፍቼ ብቻ ጭጭ አልሁበት።
“ኦ..ይቅርታ፤ መጀመሪያ ራሴን ማስተዋወቅ ይገባኛል ለካ። ኮሎኔል…"
ብሎ ስለራሱ ሊነግረኝ ሲጀምር ጆሮዬን ያዝሁበት ስሙን እንዲጠራብኝ
አልፈለግሁም አዉቄዋለኋ!
“ማ..ነ..ሽ?” አለኝ በዝግታ፣ በዚያች ኦና ቤት ዉስጥ ብቻ ለብቻ ሲከበኝ
ቆይቶ በዓይኔ እንኳን እንዳልላወስ ከግድግዳዉ ጋር እያጣበቀኝ
ወዲያዉኑ ጆሮዉን ወደ ከንፈሮቼ አምጥቶ ለረዥም አፍታ መልሴን መጠባበቅ ቢጀምርም፣ ትንፋሼን ሳይቀር ዋጥሁበት እንኳንስ ለኮሎኔ ይቅርና፣ ለገዛ እናቴ እንኳን እንዲህ ነዉ ብዬ የማፍረጠርጠዉ ማንነት የለኝ እኔ፡ ዉብርስት እባላለሁ የሲራክ አባል ነኝ የምል መስሎታል? አያዉቀኝማ! አ ያ ዉ ቀ ን ም! ሲራክ.፯ን ጨርሶ አያዉቀንም ማለት ነዉ። የሆነዉ ሁሉ ሆኖም፣ ኮሎኔሉ ከዚህ በላይ
ትዕግሥት የሚኖረዉ አይመስለኝም: ቀጣዩን ጥያቄዉንም እንደዚሁ
ተለሳልሶ እንደማይጠይቀኝ ቁልጭ ብሎ ታይቶኛል።
ስለዚህ አእምሮዬን ማሠራት አለብኝ፡
እኔ ስለማደርገዉ ሳወጣ ሳወርድ፤ እሱ ቀድሞኝ ጆሮዉን ከከንፈሮቼ አንስቶ ከንፈሮቹን ወደ ጆሮዬ አመጣብኝ፡ ይህም ሳያንስ የጥምቀትን ዉርጭ የሚያስመሰግን ቀዝቃዛ ትንፋሹን ለቀቀብኝ ፡ ከዚያ ምላሱን እና
የላይኛዉን ትናጋዉን በማጋጨት መሰለኝ፣ ሦስት ሰቅጣጭ ድምፆች
አከታትሎ አጮኸብኝ በምላስም ማጨብጨብ ይቻላል እንዴ?
“ጣ! ጣ! ጣ!”
ጣዉላ እና ጣዉላ ቢጋጭ ራሱ እንደዚህ መጮሁን እኔ እንጃ በቅጽበት አንድ ጎረምሳ እንደ ሳምሶናይት ያለ ትልቅ ቦርሳ ተሸክሞ ከተፍ አለለት የመጨረሻ ዕድል ሰጥቼሻለሁ፣ የምትነግሪኝ አለ? ማነሽ ለማለት በሚመስል ሁኔታ በጥልቀት ሲያስተዉለኝ ቆይቶ ወደ በሩ አመራ።
በሩን ከፍቶ እንደ መዉጣት ካለ በኋላ፦
“ቶሎ!” የሚል ትእዛዝ ሰጠዉ
“እሺ፤ እንደ ተለመደዉ” ሲል መለሰለት፣ ባለ ሳምሶናይቱ አናዛዥ። እኔና አናዛዡ ብቻ ቀረን፡ በሩን ቀጭ አድርጎ ቆለፈና መክፈቻዉን በኪሱ ወሽቆ ሳምሶናይቱን እዚያች ደረቅ ወንበር ላይ አስቀመጠ። እስኪከፍተዉ ድረስ እሱም ዓይኑን ከዓይኔ፣ እኔም ዓይኔን ከእጁ ላይ አልነቀልንም አንደኛዉን ኪስ ከፍቶ ዘረገፈዉ፡ ሰአሊ ለነ! ያላመጣዉ ምንም የስለት መሣሪያ የለም፡ ትንሿ የብረት መጋዝ ሳትቀር መጥታለች፡ ከሳምሶናይቱ
ሌላኛዉ ኪስም እንዲሁ መርፌዎች እና መርዝ የተሞሉ አራት ብልቃጦች ዘረገፈ፡ ይኼ ሁሉ ለኔ እንዳይሆን ብቻ! ነዉ?
“ቶሎ ምረጭ፣ የቱ ላስቀድምልሽ?”
“እ?” አልሁት፣ ድምፄን ቢከዳኝ በቅንድብ ምልክት፡
“‹ለሞኝ ጉድኋድ አያሳዩትም፣ ቤት ነው ብሎ ራሱ ይገባበታል› ተብሎ ሲተረት ብሰማም፤ የቆንጆም ሞኝ እንዳለዉ ግን አቺን አሁን ገና አየሁ ገና በገዛ'ጅሽ ሰተት ብለሽ እንጦሮጦስ ትወርጃለሽ? ጅል!”
ደም የጠማዉ ነፍሱን በጥርሱ በኩል አሳየኝ፡፡ በኹለቱም ጎኗ ስለት ያላትን ቢለዋ እና ፒንሳ እያጋጨ ወደኔ መጣ፡ ሥራዉ የሰዎችን አካል እያፈረሰ የሚያናዝዝ ሰዉ መሆኑ ያስታዉቃል ለእንደ'ሱ ዓይነት ሰዎች ደግሞ ጥፍር መንቀል፣ የዉሃ ጥም እንደ መቁረጥ ያለ እርካታ ያመጣላቸዋል እንጂ እንዲች ብሎ አይስቀጥጣቸዉም፡ ለምደዉታል:
ርኅራኄ የሚባለዉን ነገር ከዉስጣቸዉ ጨልጠዉ ደፍተዉታል እንዲያዉም ብዙ ጊዜ የሚመረመረዉ ሰዉ ለሐቅም ሆነ ራሱን ለማትረፍ ሲል፣ ገና ሳይነኩት ቶሎ የተናዘዘ እንደሆነ በኃይል ይናደዳሉ ይባላል።
“ጅል ነሽ እንዴ ? ”
እንደ ቅድሙ ባፍንጫዬ አናፍቼ ብቻ ጸጥ አልሁት።
ቁልቁል እያየኝ ከአጠገቤ ቆሞ ነበር። ወደ ኋላ የሚመለስ መስሎ፣ ከመሬቱ ጋር ደባለቀኝ፡ ምኔን በምኑ እንደ መታኝ እንኳን አላየሁትም። ብቻ ብዥ ጭልም ብሎብኝ ቆየሁ።
ነፍሴ ስትመለስ ብልቃጧን ሲያነሳ አየሁት በብልቃጧ ላይ የሰፈረዉን
ስም አሻግሬ ሳነበዉ ሪማሾ-ሚር (Himacio-mir) የሚባለዉ የሰመመን
መርዝ መሆኑን አወቅሁ። ከሚያስቃዠዉ ሰመመን በፊት ጡንቻ የሚያኮማትር እና ሽቅብ ሽቅብ የሚያስብል ንጥረ ነገሮችም አብረዉ እንደ ተቀበመሙበት አዉቃለሁ እሱን የተወጋ ሰዉ ታዲያ እንባ እንደ ዝናብ
እስኪወርደዉ ድረስ ያምጣል እንጂ ወጥቶለት የሚገላገለዉ ነገር
አይኖረዉም፡ ለማስመለስ ጫፍ ይደርስና ይመለሳል። ስለሆነም ጭንቁ አያድርስ ነዉ በጠባብ ጫማ ከመዋልም፣ ሽንት አቋርጦ ከመቋጠርም፣ ሚስማር ላይ ከመቀመጥም ሁሉ ይብሳል
መርፌዉን ተክሎ ሲሪንጁ እስኪሞላ ድረስ ብልቃጧን ምጥጥ አደረጋት።
ሲሪንጁ ጢቅ አለለት: ይኸኔ ጡንቻዎቼን ማነቃቃት ጀመርሁ። ከቀደመኝ አበቃልኝ፡ ልክ እጁን አንከርፍፎ ሲመጣ፣ የፈራሁ መስዬ አንድ ዓይኔን በእጆቼ ጨፈንሁ: ወደ ማጅራቴ መርፌዉን ሲሰድ እጁን
ለቀም አድርጌ ያዝሁትና፣ ፋታ ሳልሰጠዉ ጠምዝዤ ደረቱ ላይ ስካሁለት ዓይኔን እንኳን እስከማርገበግብ አልዘገየም፣ ትዉኪያ ሲያጣድፈዉ ልክ የገማ ጣት እንደ ጎረሰ ሰዉ፣ እንባዉ ዱብ እስኪል ድረስ ሽቅብ ቢለዉም ምንም አይወጣዉ። “ህእእእ!” ይላል በየቅጽበቱ፣ ስቃይ ብቻ! በዚያ ላይ የሠራ አካላቱ እየዛለበት መጣና፣ እንደ አሮጌ ጨርቅ እጥፍጥፍ ብሏል ጊዜ ኖሮኝ ባዘንሁለትማ ደስታዬ ነበረ ግን ለሐዘኔታ የሚሆነዉን ጊዜ የት ልዉለድለት? ይልቅ አሁኑኑ ማምለጥ አለብኝ፡፡ ባይሆን
እያመለጥሁ አዝንለታሁ
ያዉም ከቻልሁ ከኪሱ ባወጣሁት ቁልፍ በሩን ቀስ አድርጌ ከፍቼ አንገቴን ሳሰግግ
በአካባቢዉ ማንም የለም:: ቢሆንም ግን እርግጠኛ መሆን አልቻልሁም:
ያለሁት ዋነኛዉ ቤተ መንግሥት ዉስጥ ነዉ፡ ቤተ መንግሥትን ያህል ግቢ፣ በሚታዩና በሚዳሰሱ ወታደሮች ብቻ ይጠበቃል ማለት ጅልነት
ነዉ። በየሥርቻዉ ካሜራ፣ በየቦታዉ ረቂቅ ዳሳሾች መኖራቸዉ አያጠራጥርም።
“ህእእእ. አህክ እትፍ! ህእእእ አህክ እትፍ!” ይላል አሁንም፣አንጀቱ ከጉሮሮዉ ጫፍ እስኪደርስበት እየሳበዉ፡ ደም ከሚያስንቅ እንባ በቀር ሌላ ምንም ጠብ አይለዉም: መጨከን አለብኝ እንጂ፣ ሁኔታዉ አንጀት ይበላል ያሳዝናል። የሐፍረተ ሥጋዉን መሸፈኛ ብቻ ትቼለት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ረቂቋን የጆሮ ማዳመጫ አዉቆብኝ ኖሯል፤ መንጭቆ አወጣብኝ፡፡
ማደመጫዉን የያዘበትን እጁን ሳይ ተገለጠልኝ ባልቻ በአንድ ወቅት
ከፍተኛ የመንግሥት ደኅንነት ሹሞችን አጠቃላይ መገለጫቸዉን ለጥቂት
የሲራክ፯ አባላት በገለጸልን ጊዜ፣ ስለዚህ ሰዉ ልዩ ምልክት የነገረን አስታዉሼ ይኼን ሰዉ ገመትሁት አወቅሁት የቀለበት ጣቱ ከስሯ ጀምራ የለችም: በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ሰው
እጅ መግባቴን፣ አሁን አወቅሁ ሰዉዬዉ የሀገር ዉስጥ ደንነት ዋና መምሪያ ሹም መሆኑን አሁን ገና፣ ነገሮች ሁሉ ከተጨመላለቀ በኋላ ተረዳሁ። አጠመድሁ ስል እንደ ተጠመድሁ ያወቅሁት፣ አሁን ገና ሁለት እጆቹ ካነቁኝ፣ ድፍርስ ዓይኑ ካፈጠጠብኝ፣ ድርብርብ ጥርሱ ካገጠጠብኝ በኋላ ነበር። መጠርጠር አልነበረብኝም? ነበረብኝ።
«ላም ሆይ ላም ሆይ ሞኟ ላም ሆይ
ሣሩን አየሽና ገደሉን ሳታይ
እልም ካለው ገደል ወደቅሽብን ወይ
እያልሁ፣ መስኮት ቀርቶ ስንጥቅ እንኳን በሌለዉ አመዳም ግድግዳ ላይ
አፍጥጬ በራሴ አላገጥሁበት።
“ጥሩ” አለ የተገለበጠችዋን ወንበር አቃንቶ ራሱ እየተቀመጠባት
“እንተዋወቃ… ማን ብዬ ልጥራሽ?”
ባፍንጫዬ አናፍቼ ብቻ ጭጭ አልሁበት።
“ኦ..ይቅርታ፤ መጀመሪያ ራሴን ማስተዋወቅ ይገባኛል ለካ። ኮሎኔል…"
ብሎ ስለራሱ ሊነግረኝ ሲጀምር ጆሮዬን ያዝሁበት ስሙን እንዲጠራብኝ
አልፈለግሁም አዉቄዋለኋ!
“ማ..ነ..ሽ?” አለኝ በዝግታ፣ በዚያች ኦና ቤት ዉስጥ ብቻ ለብቻ ሲከበኝ
ቆይቶ በዓይኔ እንኳን እንዳልላወስ ከግድግዳዉ ጋር እያጣበቀኝ
ወዲያዉኑ ጆሮዉን ወደ ከንፈሮቼ አምጥቶ ለረዥም አፍታ መልሴን መጠባበቅ ቢጀምርም፣ ትንፋሼን ሳይቀር ዋጥሁበት እንኳንስ ለኮሎኔ ይቅርና፣ ለገዛ እናቴ እንኳን እንዲህ ነዉ ብዬ የማፍረጠርጠዉ ማንነት የለኝ እኔ፡ ዉብርስት እባላለሁ የሲራክ አባል ነኝ የምል መስሎታል? አያዉቀኝማ! አ ያ ዉ ቀ ን ም! ሲራክ.፯ን ጨርሶ አያዉቀንም ማለት ነዉ። የሆነዉ ሁሉ ሆኖም፣ ኮሎኔሉ ከዚህ በላይ
ትዕግሥት የሚኖረዉ አይመስለኝም: ቀጣዩን ጥያቄዉንም እንደዚሁ
ተለሳልሶ እንደማይጠይቀኝ ቁልጭ ብሎ ታይቶኛል።
ስለዚህ አእምሮዬን ማሠራት አለብኝ፡
እኔ ስለማደርገዉ ሳወጣ ሳወርድ፤ እሱ ቀድሞኝ ጆሮዉን ከከንፈሮቼ አንስቶ ከንፈሮቹን ወደ ጆሮዬ አመጣብኝ፡ ይህም ሳያንስ የጥምቀትን ዉርጭ የሚያስመሰግን ቀዝቃዛ ትንፋሹን ለቀቀብኝ ፡ ከዚያ ምላሱን እና
የላይኛዉን ትናጋዉን በማጋጨት መሰለኝ፣ ሦስት ሰቅጣጭ ድምፆች
አከታትሎ አጮኸብኝ በምላስም ማጨብጨብ ይቻላል እንዴ?
“ጣ! ጣ! ጣ!”
ጣዉላ እና ጣዉላ ቢጋጭ ራሱ እንደዚህ መጮሁን እኔ እንጃ በቅጽበት አንድ ጎረምሳ እንደ ሳምሶናይት ያለ ትልቅ ቦርሳ ተሸክሞ ከተፍ አለለት የመጨረሻ ዕድል ሰጥቼሻለሁ፣ የምትነግሪኝ አለ? ማነሽ ለማለት በሚመስል ሁኔታ በጥልቀት ሲያስተዉለኝ ቆይቶ ወደ በሩ አመራ።
በሩን ከፍቶ እንደ መዉጣት ካለ በኋላ፦
“ቶሎ!” የሚል ትእዛዝ ሰጠዉ
“እሺ፤ እንደ ተለመደዉ” ሲል መለሰለት፣ ባለ ሳምሶናይቱ አናዛዥ። እኔና አናዛዡ ብቻ ቀረን፡ በሩን ቀጭ አድርጎ ቆለፈና መክፈቻዉን በኪሱ ወሽቆ ሳምሶናይቱን እዚያች ደረቅ ወንበር ላይ አስቀመጠ። እስኪከፍተዉ ድረስ እሱም ዓይኑን ከዓይኔ፣ እኔም ዓይኔን ከእጁ ላይ አልነቀልንም አንደኛዉን ኪስ ከፍቶ ዘረገፈዉ፡ ሰአሊ ለነ! ያላመጣዉ ምንም የስለት መሣሪያ የለም፡ ትንሿ የብረት መጋዝ ሳትቀር መጥታለች፡ ከሳምሶናይቱ
ሌላኛዉ ኪስም እንዲሁ መርፌዎች እና መርዝ የተሞሉ አራት ብልቃጦች ዘረገፈ፡ ይኼ ሁሉ ለኔ እንዳይሆን ብቻ! ነዉ?
“ቶሎ ምረጭ፣ የቱ ላስቀድምልሽ?”
“እ?” አልሁት፣ ድምፄን ቢከዳኝ በቅንድብ ምልክት፡
“‹ለሞኝ ጉድኋድ አያሳዩትም፣ ቤት ነው ብሎ ራሱ ይገባበታል› ተብሎ ሲተረት ብሰማም፤ የቆንጆም ሞኝ እንዳለዉ ግን አቺን አሁን ገና አየሁ ገና በገዛ'ጅሽ ሰተት ብለሽ እንጦሮጦስ ትወርጃለሽ? ጅል!”
ደም የጠማዉ ነፍሱን በጥርሱ በኩል አሳየኝ፡፡ በኹለቱም ጎኗ ስለት ያላትን ቢለዋ እና ፒንሳ እያጋጨ ወደኔ መጣ፡ ሥራዉ የሰዎችን አካል እያፈረሰ የሚያናዝዝ ሰዉ መሆኑ ያስታዉቃል ለእንደ'ሱ ዓይነት ሰዎች ደግሞ ጥፍር መንቀል፣ የዉሃ ጥም እንደ መቁረጥ ያለ እርካታ ያመጣላቸዋል እንጂ እንዲች ብሎ አይስቀጥጣቸዉም፡ ለምደዉታል:
ርኅራኄ የሚባለዉን ነገር ከዉስጣቸዉ ጨልጠዉ ደፍተዉታል እንዲያዉም ብዙ ጊዜ የሚመረመረዉ ሰዉ ለሐቅም ሆነ ራሱን ለማትረፍ ሲል፣ ገና ሳይነኩት ቶሎ የተናዘዘ እንደሆነ በኃይል ይናደዳሉ ይባላል።
“ጅል ነሽ እንዴ ? ”
እንደ ቅድሙ ባፍንጫዬ አናፍቼ ብቻ ጸጥ አልሁት።
ቁልቁል እያየኝ ከአጠገቤ ቆሞ ነበር። ወደ ኋላ የሚመለስ መስሎ፣ ከመሬቱ ጋር ደባለቀኝ፡ ምኔን በምኑ እንደ መታኝ እንኳን አላየሁትም። ብቻ ብዥ ጭልም ብሎብኝ ቆየሁ።
ነፍሴ ስትመለስ ብልቃጧን ሲያነሳ አየሁት በብልቃጧ ላይ የሰፈረዉን
ስም አሻግሬ ሳነበዉ ሪማሾ-ሚር (Himacio-mir) የሚባለዉ የሰመመን
መርዝ መሆኑን አወቅሁ። ከሚያስቃዠዉ ሰመመን በፊት ጡንቻ የሚያኮማትር እና ሽቅብ ሽቅብ የሚያስብል ንጥረ ነገሮችም አብረዉ እንደ ተቀበመሙበት አዉቃለሁ እሱን የተወጋ ሰዉ ታዲያ እንባ እንደ ዝናብ
እስኪወርደዉ ድረስ ያምጣል እንጂ ወጥቶለት የሚገላገለዉ ነገር
አይኖረዉም፡ ለማስመለስ ጫፍ ይደርስና ይመለሳል። ስለሆነም ጭንቁ አያድርስ ነዉ በጠባብ ጫማ ከመዋልም፣ ሽንት አቋርጦ ከመቋጠርም፣ ሚስማር ላይ ከመቀመጥም ሁሉ ይብሳል
መርፌዉን ተክሎ ሲሪንጁ እስኪሞላ ድረስ ብልቃጧን ምጥጥ አደረጋት።
ሲሪንጁ ጢቅ አለለት: ይኸኔ ጡንቻዎቼን ማነቃቃት ጀመርሁ። ከቀደመኝ አበቃልኝ፡ ልክ እጁን አንከርፍፎ ሲመጣ፣ የፈራሁ መስዬ አንድ ዓይኔን በእጆቼ ጨፈንሁ: ወደ ማጅራቴ መርፌዉን ሲሰድ እጁን
ለቀም አድርጌ ያዝሁትና፣ ፋታ ሳልሰጠዉ ጠምዝዤ ደረቱ ላይ ስካሁለት ዓይኔን እንኳን እስከማርገበግብ አልዘገየም፣ ትዉኪያ ሲያጣድፈዉ ልክ የገማ ጣት እንደ ጎረሰ ሰዉ፣ እንባዉ ዱብ እስኪል ድረስ ሽቅብ ቢለዉም ምንም አይወጣዉ። “ህእእእ!” ይላል በየቅጽበቱ፣ ስቃይ ብቻ! በዚያ ላይ የሠራ አካላቱ እየዛለበት መጣና፣ እንደ አሮጌ ጨርቅ እጥፍጥፍ ብሏል ጊዜ ኖሮኝ ባዘንሁለትማ ደስታዬ ነበረ ግን ለሐዘኔታ የሚሆነዉን ጊዜ የት ልዉለድለት? ይልቅ አሁኑኑ ማምለጥ አለብኝ፡፡ ባይሆን
እያመለጥሁ አዝንለታሁ
ያዉም ከቻልሁ ከኪሱ ባወጣሁት ቁልፍ በሩን ቀስ አድርጌ ከፍቼ አንገቴን ሳሰግግ
በአካባቢዉ ማንም የለም:: ቢሆንም ግን እርግጠኛ መሆን አልቻልሁም:
ያለሁት ዋነኛዉ ቤተ መንግሥት ዉስጥ ነዉ፡ ቤተ መንግሥትን ያህል ግቢ፣ በሚታዩና በሚዳሰሱ ወታደሮች ብቻ ይጠበቃል ማለት ጅልነት
ነዉ። በየሥርቻዉ ካሜራ፣ በየቦታዉ ረቂቅ ዳሳሾች መኖራቸዉ አያጠራጥርም።
“ህእእእ. አህክ እትፍ! ህእእእ አህክ እትፍ!” ይላል አሁንም፣አንጀቱ ከጉሮሮዉ ጫፍ እስኪደርስበት እየሳበዉ፡ ደም ከሚያስንቅ እንባ በቀር ሌላ ምንም ጠብ አይለዉም: መጨከን አለብኝ እንጂ፣ ሁኔታዉ አንጀት ይበላል ያሳዝናል። የሐፍረተ ሥጋዉን መሸፈኛ ብቻ ትቼለት
👍33🥰2
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
....“ራስህ ነህ፤ አዎ: ግን እንዴት?” አልሁት መኪናዉን የቤተመንግሥት ታርጋ እንዳየሁበት አስታዉሼ። ለነገሩ ባልቻ የማያልፍበት ምን የመርፌ ቀዳዳ አለና ነዉ? ልክ ወደ መዉጫዉ በር ስንቃረብ፣
መኪናዉን ድንገት ሲጢጥ አድርጎ አቆመዉ።
"አይሆንም በዚህ መልኩ መዉጣት አንችልም። ይኸኔእኮ በሩ ተከርችሞ ወታደሮችም በጥፍሮቻቸዉ ቆመዉ እየጠበቁሽ ይሆናል: ኮሎኔሉ ሳይቀር መሬቱን እየጠለዘ በመንቆራጠጥ ላይ ነዉ የሚሆነዉ።ምክንያቱም ከግብጽ ትሆኚ ከኤርትራ፣ አሸባሪ ትሆኚ ተገዳዳሪ፤ ምንነትሽን እንኳ ን በቅጡ ያላወቁሽ አንቺ ከእጃቸዉ ስላመለጥሽባቸዉ እታሰስሽ ነዉ የምትሆኝዉ: ስለዚህ በየትኛዉም በር መዉጣት አንችልም ደኅነት እና ወታደር ሁሉ ተነስንሶ እያፈላለገሽ ከሆነ ደግሞ አስቢዉ፣ግቢም ደግሞ መቆየት አንችልም: አጣብቂኝ ዉስጥ ነን”
አለኝ፣ እንደ መረታት ብሎ።
“እንዲህ ብናደርግስ?” አልሁት፣ ሰዓቱን እንዲመለከት እየጠቆምሁት።
“በመርሐ ግብሩ መሠረት፣ በአዳራሽ የነበሩት እንግዶች መዉጫቸዉ ነዉ: በእርግጥ አልፏል: የፈለገ በየሰበቡ አንዛዝተዉ ቢያቆዩአቸዉ
እንኳን፣ መዉጣታቸዉ ግን አይቀርም: መቼሰ እዚሁ አያሳድሯቸዉ።ይወጣሉ። እነሱ እስከሚወጡ ድረስ ጠብቀን በየመኪናቸዉ ተከታትለዉ
ሲወጡ እኛም ተደባልቀን መዉጣት እንችላለ”
“ፍተሻዉ ቀላል ይሆናል ብለሽ ነዉ?” አለ የመኪናዉን መብራቶች
አጠፋፍቶ በዝግታ ወደ ተነሳንበት ቦታ ወደ ኋላ እያሽከረከረ ወደ ሰፊዉ የመኪና ማቆሚያ ተመልሰን ልክ ከመቆማችን፣ የጋቢናዉ በር ተንኳኳ።
ስአሊ ለነ! መኪና ማቆሚያዉ ጠባቂ እንዳለዉ እንዴት አልገመትንም?እንኳንስ የቤተ መንግሥቱ ተራ የመንገድ ዳር መኪኖችስ ጠባቂ አላቸዉ
አይደል እንዴ? ቀሽሞች ነን! የኔስ እሺ፣ ባልቻ እንዴት ልብ አላለዉም
ይኼን?
ጋቢናዉ በድጋሚ ተንኳኳ
“አቤት?” አለ ባልቻ እኔን ወንበር ሥር እንድደበቅ በዳበሳ ምልክት
ከሰጠኝ በኋላ፣ መስታዎቱን ዝቅ አድርጎ፡
“ችግር አለ?” አለ ጠባቂዉ፣ በትሕትና
“እህህ” ብሎ የማስመሰል ሳቅ አስቀደመ፣ ባልቻ። “እህህ… ያዉ
ታዉቀዉ የለ የኛን ሥራ? አለቆቼ አድ ቦታ ላኩኝና እየወጣሁ ሳለ ደግሞ እንደገና እንድተወዉ ደዉለዉልኝ ነዉ እንጂ ችግር የለም: የማደርሳቸዉ እንግዶች ሳይኖሩ አይቀርም”
“አይደል? ተደዉሎልህ?” አለ ሰዉዬዉ ልብ በሚወጋ ስላቅ።
ወዲያዉኑ በአቅራቢያ የሚያልፉ ኹለት ወታደሮችን አፏጨላቸዉ።
እየበረሩ እንደ መጡ ኮቴያቸዉ ነግሮኛል።
“ይቅርታ ጌቶቼ፣ የሚያጠራጥር ነገር ካለ አሳዉቅ ተብዬ ነበር። መቼም ሰዉ ያለ ምክንያት መብራት አጥፍቶ ወደ ኋላ አይነዳም: ምናልባት
የምትፈልጉት ዓይነት ሰዉ እንደሆነ ብዬ ነዉ” አላቸዉ፣ ወደ ባልቻ እየጠቆመ። መሣሪያቸዉን አነጣጥረዉ ከመኪናዉ በቀስታ እንዲወርድ አዘዙት።
“እንዳትሳሳቱ፣ እኔ ተራ ሹፌር ነኝ: ከዚህ ሁሉ ለምን ጉቦዳን
አትጠይቁትም?”
ምን አስቦ እንደሆነ ባይገባኝም፣ አመላለሱ ግን ሆነ ብሎ ጥርጣሬያቸዉን የሚያጎላ ነዉ ምክንያቱም ገና አንድ ጥያቄ እንኳን ሳይጠይቁት፣
በዉስብስብ ጥያቄዎች እንዳስመረሩት ሁሉ መቀለማመዱ ከባልቻ የሚጠበቅ አይደለም: እንዲያዉም እሱ ራሱ “ጅል ለስለላ ሄዶ ምግብ
ቢያቀርቡለት ስለላ ላይ ነኝ ብሎአረፈዉ” ብሎ በተልካሻ የመረጃ አነፍናፊዎች ሲስቅ ሰምቼዋለሁ። የእሱ የተቻኮለ መልስ ግን ከጅሉ በላይ
ቢብስ እንጂ አይተናነስም
“ጉቦዳን ጠይቁት”
“ማነዉ ደግሞ ጉቦዳ?”
“ጉቦዳ የመኪና ስምሪት ኃላፊዉ ነዋ: አታዉቁትም? ጉቦዳ ?”
“ና ቅደም እስኪ ለማንኛዉም” ብለዉ ወሰዱት እርስ በእርስ ትንሽ
ከተመካከሩ በኋላ።
እኔን ማንም ሳያየኝ መኪና ዉስጥ ቀረሁ አሁን ሐሳቡ የገባኝ መሰለኝ፡ ኹለታችንም ከምንያዝ፣ እኔን አትርፎ ራሱን ማጋለጡ ነዉ። ባልቻ አይደል ሰዉዬዉ? መhራዬን መዉሰድ ያዉቅበት የለ? መንገድ አብረን እየሄድን ድንገት ጋሬጣ ሲያደናቅፈኝ ‹እኔን ባዩ ሰዉ! ለማለቱማ ማንም ሰዉ ይለኝ ይሆናል፣ ከልቡ መሆኑን ግን ከእሱ በቀር የማምነዉ ማን
አለኝ? ከእናቴ ቀጥሎ ከሰዉ ማንም እንደሱ የለም ባልቻ ብቻ!
ባልቻን በወሰዱበት መንገድ አፍጥጬ እንባ እያፈሰስሁ ለደቂቃዎች በድንዛዜ ቆየሁ ከዚያ እንደ ምንም እንባዬን ጠራርጌ ዓይነ ልቡናዬን እንዲያበራልኝ አጭር ጸሎት ማድረስ ስጀምር፣ በርከት ያለ ድምፅ ሰማሁ። እንግዶች መዉጣት ጀምረዋል። አሁን የዕቅድ ለዉጥ አድርጌም
ቢሆን ከዚህ ግቢ ቶሎ ማምለጥ አለብኝ፡ እንዴት? መቼም እንግዶቹ
ሲወጡ በር ላይ ጠበቅ ያለ ፍተሻ መኖሩ የማይቀር ነዉ። ያን ጊዜ
ትኩረቱ ሁሉ ወደ በሩ ይሆናል ማለት ነዉ፡ እንደዚያ ከሆነ ደግሞ እኔ በአጥር መዝለል እችላለሁ፡ በእርግጥ እንኳንስ በአጥሩ መዝለል ይቅርና፣ አጥሩ አጠገብ መድረሱ በራሱ ዋዛ እንደማይሆንልኝ አልጠፋኝም: ነገር ግን ከጥበቃ ማማዎች ወደሚቀርበኝ ቃኚ ወታደር መስዬ እያዘናጋሁ እቀርበዉና ያቺን የሰመመን መርዝ ጠቅ አደርግበታለሁ። ይወድቅልኝ
የለ? ያን ጊዜ ከራሱ ማማ እመር ብዬ ወደ ዉጪ እዘላለሁ፡ ምናልባት በግራና በቀኝ በኩል ባሉ ማማዎች ያሉ ወታደሮች ቢተኩሱብኝ ነዉ ቢሆንም ግን የመጨረሻዉ ቀላል ማምለጫ ይኼ ብቻ ነዉ ሌላ አልታየኝም:
ያቀድሁት ሁሉ ሰምሮልኝ ዘልዬ ወደ ዉጪ ከመዉደቄ እንደ ጠበቅሁት የተኩስ እሩምታ ይዘንብብኝ ጀመር። እየተንከባለልሁ ወደ ዋናዉ ጎዳና
ስወርድ፣ ማንነቱ የማይታይ ሰዉ አንዲት ሚኒባስ ታክሲ እያበረረ
አጠገቤ አድርሶ በሯን ከፈተልኝ፡ የሲራክ፯ አባላትን የምታግባባዋን
የመኪና ጥሩምባ ቀድሞ ስለነፋልኝ፣ ለእኔ የመጣ መሆኑን አወቅሁና ሳላቅማማ ተወርዉሬ ገባሁባት ነዳጁን ረግጦ ከግቢ ገብርኤል በታች ወዳለዉ የመንደር መንገድ ወሰደኝ።
አመለጥሁ።
ከቤተ መንግሥቱ መራቃችንን ሲያዉቅ፣ ሹፌሩ የመኪናዉን የዉስጥ መብራት አብርቶ በድል አድራጊነት አየኝ፡ አየሁት።
“አ-ባ-ቴ?!” ብዬ በጩኸት አቀለጥሁት ባልቻ ነዉ። በምን ተአምር እንዳመለጠ ልጠይቀዉ ወይስ ዝም ብዬ ከአንበሳ ጉሮሮም ቢሆን የሚያተርፈንን አምላክ ላመስግን? ቸገረኝ እኮ፡ ሰአሊ ለነ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ባልቻ ነዋ ሰዉዬዉ! እንዴት አያመልጥ?” ሲል አቋረጠኝ፣ ቢራራ እኔም ልክ አሁን የሆነ ያህል ነበር በስሜት ያጫወትሁት።
በዚህ እና ከዚህ በባሱ መዐት ሞቶች መካከል አልፌ የማዉቀዋ እኔ፣ ዛሬ ግን ፈራሁ። እዉነትስ ፈተና ባይኖር ሁሉ ተማሪ፣ ጠያቂ ባይኖር ሁሉ አስተማሪ የሚለዉ አባባል ይመለከተኛል? በጭራሽ! በጅቦች መካከል፣ በጨለማ አካፋይ ሞትን ተፋጥጬዉ አልፏል።
“እንግዲያዉ ለምን ፈራሁ አሁን? አንተ እስክትሳለቅብኝ ድረስ ለምን
ተንቀጠቀጥሁ?”
“ይኼን ስትነግሪኝ ምን እንደመጣብኝ ታዉቂያለሽ?ስለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጴጥሮስ ያነበብሁት አንድ ምዕራፍ” አለ፣ በሞባይሉ መጽሐፍ ቅዱስ እየከፈተ። የሚፈልገዉን ምዕራፍ ሲያገኘዉ፤ “ከዚህ ጀምረሽ
አንብቢዉማ” ብሎ ሞባይሉን አቀበለኝ። ታሪኩ ጌታችን ኹለት ዓሣ እና አምስት እንጀራ አበርክቶ ሕጻናቱንና ሴቶቹን ሳይጨምር አምስት ሺ ወንዶችን ያጠገበ ዕለት፤ ሌሊቱን የሆነ ነዉ።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
....“ራስህ ነህ፤ አዎ: ግን እንዴት?” አልሁት መኪናዉን የቤተመንግሥት ታርጋ እንዳየሁበት አስታዉሼ። ለነገሩ ባልቻ የማያልፍበት ምን የመርፌ ቀዳዳ አለና ነዉ? ልክ ወደ መዉጫዉ በር ስንቃረብ፣
መኪናዉን ድንገት ሲጢጥ አድርጎ አቆመዉ።
"አይሆንም በዚህ መልኩ መዉጣት አንችልም። ይኸኔእኮ በሩ ተከርችሞ ወታደሮችም በጥፍሮቻቸዉ ቆመዉ እየጠበቁሽ ይሆናል: ኮሎኔሉ ሳይቀር መሬቱን እየጠለዘ በመንቆራጠጥ ላይ ነዉ የሚሆነዉ።ምክንያቱም ከግብጽ ትሆኚ ከኤርትራ፣ አሸባሪ ትሆኚ ተገዳዳሪ፤ ምንነትሽን እንኳ ን በቅጡ ያላወቁሽ አንቺ ከእጃቸዉ ስላመለጥሽባቸዉ እታሰስሽ ነዉ የምትሆኝዉ: ስለዚህ በየትኛዉም በር መዉጣት አንችልም ደኅነት እና ወታደር ሁሉ ተነስንሶ እያፈላለገሽ ከሆነ ደግሞ አስቢዉ፣ግቢም ደግሞ መቆየት አንችልም: አጣብቂኝ ዉስጥ ነን”
አለኝ፣ እንደ መረታት ብሎ።
“እንዲህ ብናደርግስ?” አልሁት፣ ሰዓቱን እንዲመለከት እየጠቆምሁት።
“በመርሐ ግብሩ መሠረት፣ በአዳራሽ የነበሩት እንግዶች መዉጫቸዉ ነዉ: በእርግጥ አልፏል: የፈለገ በየሰበቡ አንዛዝተዉ ቢያቆዩአቸዉ
እንኳን፣ መዉጣታቸዉ ግን አይቀርም: መቼሰ እዚሁ አያሳድሯቸዉ።ይወጣሉ። እነሱ እስከሚወጡ ድረስ ጠብቀን በየመኪናቸዉ ተከታትለዉ
ሲወጡ እኛም ተደባልቀን መዉጣት እንችላለ”
“ፍተሻዉ ቀላል ይሆናል ብለሽ ነዉ?” አለ የመኪናዉን መብራቶች
አጠፋፍቶ በዝግታ ወደ ተነሳንበት ቦታ ወደ ኋላ እያሽከረከረ ወደ ሰፊዉ የመኪና ማቆሚያ ተመልሰን ልክ ከመቆማችን፣ የጋቢናዉ በር ተንኳኳ።
ስአሊ ለነ! መኪና ማቆሚያዉ ጠባቂ እንዳለዉ እንዴት አልገመትንም?እንኳንስ የቤተ መንግሥቱ ተራ የመንገድ ዳር መኪኖችስ ጠባቂ አላቸዉ
አይደል እንዴ? ቀሽሞች ነን! የኔስ እሺ፣ ባልቻ እንዴት ልብ አላለዉም
ይኼን?
ጋቢናዉ በድጋሚ ተንኳኳ
“አቤት?” አለ ባልቻ እኔን ወንበር ሥር እንድደበቅ በዳበሳ ምልክት
ከሰጠኝ በኋላ፣ መስታዎቱን ዝቅ አድርጎ፡
“ችግር አለ?” አለ ጠባቂዉ፣ በትሕትና
“እህህ” ብሎ የማስመሰል ሳቅ አስቀደመ፣ ባልቻ። “እህህ… ያዉ
ታዉቀዉ የለ የኛን ሥራ? አለቆቼ አድ ቦታ ላኩኝና እየወጣሁ ሳለ ደግሞ እንደገና እንድተወዉ ደዉለዉልኝ ነዉ እንጂ ችግር የለም: የማደርሳቸዉ እንግዶች ሳይኖሩ አይቀርም”
“አይደል? ተደዉሎልህ?” አለ ሰዉዬዉ ልብ በሚወጋ ስላቅ።
ወዲያዉኑ በአቅራቢያ የሚያልፉ ኹለት ወታደሮችን አፏጨላቸዉ።
እየበረሩ እንደ መጡ ኮቴያቸዉ ነግሮኛል።
“ይቅርታ ጌቶቼ፣ የሚያጠራጥር ነገር ካለ አሳዉቅ ተብዬ ነበር። መቼም ሰዉ ያለ ምክንያት መብራት አጥፍቶ ወደ ኋላ አይነዳም: ምናልባት
የምትፈልጉት ዓይነት ሰዉ እንደሆነ ብዬ ነዉ” አላቸዉ፣ ወደ ባልቻ እየጠቆመ። መሣሪያቸዉን አነጣጥረዉ ከመኪናዉ በቀስታ እንዲወርድ አዘዙት።
“እንዳትሳሳቱ፣ እኔ ተራ ሹፌር ነኝ: ከዚህ ሁሉ ለምን ጉቦዳን
አትጠይቁትም?”
ምን አስቦ እንደሆነ ባይገባኝም፣ አመላለሱ ግን ሆነ ብሎ ጥርጣሬያቸዉን የሚያጎላ ነዉ ምክንያቱም ገና አንድ ጥያቄ እንኳን ሳይጠይቁት፣
በዉስብስብ ጥያቄዎች እንዳስመረሩት ሁሉ መቀለማመዱ ከባልቻ የሚጠበቅ አይደለም: እንዲያዉም እሱ ራሱ “ጅል ለስለላ ሄዶ ምግብ
ቢያቀርቡለት ስለላ ላይ ነኝ ብሎአረፈዉ” ብሎ በተልካሻ የመረጃ አነፍናፊዎች ሲስቅ ሰምቼዋለሁ። የእሱ የተቻኮለ መልስ ግን ከጅሉ በላይ
ቢብስ እንጂ አይተናነስም
“ጉቦዳን ጠይቁት”
“ማነዉ ደግሞ ጉቦዳ?”
“ጉቦዳ የመኪና ስምሪት ኃላፊዉ ነዋ: አታዉቁትም? ጉቦዳ ?”
“ና ቅደም እስኪ ለማንኛዉም” ብለዉ ወሰዱት እርስ በእርስ ትንሽ
ከተመካከሩ በኋላ።
እኔን ማንም ሳያየኝ መኪና ዉስጥ ቀረሁ አሁን ሐሳቡ የገባኝ መሰለኝ፡ ኹለታችንም ከምንያዝ፣ እኔን አትርፎ ራሱን ማጋለጡ ነዉ። ባልቻ አይደል ሰዉዬዉ? መhራዬን መዉሰድ ያዉቅበት የለ? መንገድ አብረን እየሄድን ድንገት ጋሬጣ ሲያደናቅፈኝ ‹እኔን ባዩ ሰዉ! ለማለቱማ ማንም ሰዉ ይለኝ ይሆናል፣ ከልቡ መሆኑን ግን ከእሱ በቀር የማምነዉ ማን
አለኝ? ከእናቴ ቀጥሎ ከሰዉ ማንም እንደሱ የለም ባልቻ ብቻ!
ባልቻን በወሰዱበት መንገድ አፍጥጬ እንባ እያፈሰስሁ ለደቂቃዎች በድንዛዜ ቆየሁ ከዚያ እንደ ምንም እንባዬን ጠራርጌ ዓይነ ልቡናዬን እንዲያበራልኝ አጭር ጸሎት ማድረስ ስጀምር፣ በርከት ያለ ድምፅ ሰማሁ። እንግዶች መዉጣት ጀምረዋል። አሁን የዕቅድ ለዉጥ አድርጌም
ቢሆን ከዚህ ግቢ ቶሎ ማምለጥ አለብኝ፡ እንዴት? መቼም እንግዶቹ
ሲወጡ በር ላይ ጠበቅ ያለ ፍተሻ መኖሩ የማይቀር ነዉ። ያን ጊዜ
ትኩረቱ ሁሉ ወደ በሩ ይሆናል ማለት ነዉ፡ እንደዚያ ከሆነ ደግሞ እኔ በአጥር መዝለል እችላለሁ፡ በእርግጥ እንኳንስ በአጥሩ መዝለል ይቅርና፣ አጥሩ አጠገብ መድረሱ በራሱ ዋዛ እንደማይሆንልኝ አልጠፋኝም: ነገር ግን ከጥበቃ ማማዎች ወደሚቀርበኝ ቃኚ ወታደር መስዬ እያዘናጋሁ እቀርበዉና ያቺን የሰመመን መርዝ ጠቅ አደርግበታለሁ። ይወድቅልኝ
የለ? ያን ጊዜ ከራሱ ማማ እመር ብዬ ወደ ዉጪ እዘላለሁ፡ ምናልባት በግራና በቀኝ በኩል ባሉ ማማዎች ያሉ ወታደሮች ቢተኩሱብኝ ነዉ ቢሆንም ግን የመጨረሻዉ ቀላል ማምለጫ ይኼ ብቻ ነዉ ሌላ አልታየኝም:
ያቀድሁት ሁሉ ሰምሮልኝ ዘልዬ ወደ ዉጪ ከመዉደቄ እንደ ጠበቅሁት የተኩስ እሩምታ ይዘንብብኝ ጀመር። እየተንከባለልሁ ወደ ዋናዉ ጎዳና
ስወርድ፣ ማንነቱ የማይታይ ሰዉ አንዲት ሚኒባስ ታክሲ እያበረረ
አጠገቤ አድርሶ በሯን ከፈተልኝ፡ የሲራክ፯ አባላትን የምታግባባዋን
የመኪና ጥሩምባ ቀድሞ ስለነፋልኝ፣ ለእኔ የመጣ መሆኑን አወቅሁና ሳላቅማማ ተወርዉሬ ገባሁባት ነዳጁን ረግጦ ከግቢ ገብርኤል በታች ወዳለዉ የመንደር መንገድ ወሰደኝ።
አመለጥሁ።
ከቤተ መንግሥቱ መራቃችንን ሲያዉቅ፣ ሹፌሩ የመኪናዉን የዉስጥ መብራት አብርቶ በድል አድራጊነት አየኝ፡ አየሁት።
“አ-ባ-ቴ?!” ብዬ በጩኸት አቀለጥሁት ባልቻ ነዉ። በምን ተአምር እንዳመለጠ ልጠይቀዉ ወይስ ዝም ብዬ ከአንበሳ ጉሮሮም ቢሆን የሚያተርፈንን አምላክ ላመስግን? ቸገረኝ እኮ፡ ሰአሊ ለነ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ባልቻ ነዋ ሰዉዬዉ! እንዴት አያመልጥ?” ሲል አቋረጠኝ፣ ቢራራ እኔም ልክ አሁን የሆነ ያህል ነበር በስሜት ያጫወትሁት።
በዚህ እና ከዚህ በባሱ መዐት ሞቶች መካከል አልፌ የማዉቀዋ እኔ፣ ዛሬ ግን ፈራሁ። እዉነትስ ፈተና ባይኖር ሁሉ ተማሪ፣ ጠያቂ ባይኖር ሁሉ አስተማሪ የሚለዉ አባባል ይመለከተኛል? በጭራሽ! በጅቦች መካከል፣ በጨለማ አካፋይ ሞትን ተፋጥጬዉ አልፏል።
“እንግዲያዉ ለምን ፈራሁ አሁን? አንተ እስክትሳለቅብኝ ድረስ ለምን
ተንቀጠቀጥሁ?”
“ይኼን ስትነግሪኝ ምን እንደመጣብኝ ታዉቂያለሽ?ስለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጴጥሮስ ያነበብሁት አንድ ምዕራፍ” አለ፣ በሞባይሉ መጽሐፍ ቅዱስ እየከፈተ። የሚፈልገዉን ምዕራፍ ሲያገኘዉ፤ “ከዚህ ጀምረሽ
አንብቢዉማ” ብሎ ሞባይሉን አቀበለኝ። ታሪኩ ጌታችን ኹለት ዓሣ እና አምስት እንጀራ አበርክቶ ሕጻናቱንና ሴቶቹን ሳይጨምር አምስት ሺ ወንዶችን ያጠገበ ዕለት፤ ሌሊቱን የሆነ ነዉ።
👍30😁2🔥1👏1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
....“አንድ ጊዜ ከባልቻ ጋር እዚህ መጥታችሁ ነበር አይደል?” አለችኝ እንደ ዋዛ፣ ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት በቅንድቧ እየጠቆመችኝ፡
“አዎ” አልኋት፣ እኔም እንደ ዋዛ፡ “እ?” አልኋት ወዲያዉ፣ ዉሃ ሆኜ ምን ምን? ያለችዉን ነገር እኮ ገና አሁን ነዉ ልብ ያደረግሁበት::
ከማን ጋር ምንድነዉ ያለችኝ? ባልቻ? እርፍ! እንዴት እንዴት ነዉ ነገሩ? በድንጋጤ ተዝለፍልፌ አለመዉደቄ፣ ለራሴ ደነቀኝ፡ መሬቱን ይዤ አረፍ ማለትም አሰብሁ፡ ቢሆንም ግን ቸኩሎ መደናገጥን የሲራክ ፯ ማንነቴ
ስለማይፈቅድልኝ ማስጨረስ አለብኝ፡ ጥርሴን ነክሼ እንደ ምንም ተበራታሁ።
“በዚህ በኩል” አለችኝ፣ ወደ ታዕካ ነገሥት ቤተ መዘክር እያስገባችኝ
ወደ ቤተ መዘክሩ ስመጣ የመጀመሪያዬ ስላልሆነ ብርቅ አልሆነብኝም እንጂ፣ እንደዚህ ማንኛዉንም ሰዉ መንፈሳዊ የሚያደርግ ወደረኛ ቦታ
አለ ቢሉኝ አላምንም ሲጀመር በከተማ ዉስጥ ካሉ ገዳማት እንደዚህ የጸጥታ እና የአርምሞ ገዳም አላዉቅም። በበርሐ ካሉትም የሚስተካከል
ትክክለኛ የገዳም ይዞታ ያለዉ ግቢ ነዉ፡ ዕድሜ በጠገቡ እና ራሳቸዉ ታሪክ በሠሩ ጽዶች የተሞላ ስለሆነ፣ እዚህ ግቢ የገባ ሰዉ ዉጣ ዉጣ አይለዉም እንኳንስ ለአማኝ እና ለተማጻኝ ይቅርና፣ ለማንኛዉም ሰዉ
መረጋጋትን የሚሰጥ ገራሚ ሥፍራ ነዉ።
ቤተ መዘክሩ ዐሥር ብር የከፈለ ማንኛዉም ታሪክ ወዳጅ የሚጎበኘዉ ሕዝባዊ ቤት ቢሆንም፣ የሚገኘዉ ግን በዋናዉ የገዳሙ ሕንጻ ምድር ቤት ነዉ፡ ስለዚህ ወደ ቤተ መዘክሩ ለመግባት የግድ ጫማ አዉል
በቅኔ ማኅሌቱ በኩል ማለፍ ይጠይቃል። በዋናነት የዳግማዊ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል፣ የእቴጌ ዘዉዲቱ፣ የአቡነ ማቴዎስ
ግብጻዊ የልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ ዐጽሞች በየራሳቸዉ ወርቃማ ሳጥን ዉስጥ ተከብረዉ የተቀመጡበት ሲሆን፣ ዓይነተ ብዙ የካህናት እና የነገሥታት ቅርሳ ቅርሶችም አሉበት ከነዚህም መካከል ሮማዊዉ ሊቀ ጳጳስ ለአፄ ምኒልክ የላኩላቸዉ የሚካኤል አንጀሎን ትክክለኛ የእጅ ሥዕል ጨምሮ ብዙ የሚነገርላቸዉ ከሩስያ ከግሪክ ከጣልያን እና ከተለያዩ ሀገራት መንግሥታትን የተበረከቱ ቅርሶች
ሞልተዉ ተትረፍርፈዉበታል። እንዲሁም ንግሥተ ነገሥታት ዘዉዲቱ ለጸሎት ይጠቀሙበት የነበረ ወንበር፣ የእጅ ጽሑፋቸዉ ያለበት ዉዳሴ ማርያም እና ሌሎች የብራና መጻሕፍት እና ለእሳቸዉ የተሰጡ ታሪዊ ስጦታዎች ጭምር አሉበት። ለአድዋ ዘመቻ ሲታወጅ የተጎሰመዉ ነጋሪት፣ አድዋ
ድረስ የዘመተችዋ ድል አድራጊዋ የጃንሆይ መቀመጫ ወንበር ሁሉ
የሚገኙት በሌላ አይደለም፡ እዚሁ ታዕካ ነገሥት ቤተ መዘክር ዉስጥ
ነዉ።
ያም ሆኖ ግን ቤተ መዘክሩን የሚጎበኘዉ ሰዉ በታሪኩ ልክ ብዙ ነዉ ማለት አይቻልም እስከዚህም ነዉ ያን ያህል ንጉሥ ንጉሥም፣ ካህን ካህንም የሚሸት እና ቢናገሩለት የማያልቅ የቅርስ ክምችት እንዳልሞላበት
ሁሉ፣ ጎብኚ ግን ከስንት አንድ ነዉ ብቅ የሚልበት። ያዉም የዉጪ
ሀገር ሰዉ፡ ዛሬ ደግሞ ይባስ ብሎ ከነጭራሹ ማንንም አላየሁበትም። አስጎብኚዎቹም እንኳን በአካባቢዉ የሉም
“እና፣ ወደ ቤተ መንግሥቱ ያመጣችሁን ጉዳይ እንደሚሆን እንደሚሆን ከዉናችሁት ልትወጡ ስትሉ ተይዛችሁ ነበር አሉ?” አለችኝ እመዋ፣ በዚያ የዉድ ዉድ እቃዎች ክምር መካከል ለብቻችን ስንዋኝ።
ዝም ብዬ ባዳምጣት ይሻለኛል ምን ልል እችላለሁ? ጭጭ እርጭ ብዬ አዳመጥኋት። ጭራሽ ተዪዛችሁ ነዉ ያለችዉ? በስመ አብ!
“ከዚያ ባልቻ አቺን ደብቆ ራሱን አጋለጠ። አንቺ ይኸኔ የእሱ መጨረሻ እያሳሰበሽ እንደ ምንም ከቤተ መንግሥቱ ጠባቂዎች ስታመልጪ ቀድሞሽ ውጪ አገኘሽዉ በምን ተአምር ከእነሱ እጅ እንዳመለጠ ግን እስከ
አሁንም ድረስ ባሰብሽዉ ቁጥር ይገርምሻል አይደለም? በእርግጥም ግን እኮ ይገርማል። የመንግሥት ደኅነቶች ለመያዝ ዘገምተኞች ናቸዉ እንጂ ከያዙ እኮ አይለቁም ይባላል”
እመዋን አላዉቃትም ለካ በእርግጥ ግን ይቺ ሰዉ እመዋ ራሷ ናት ከንግግሩ አነጋገሯ ከአነጋገሯ ሁኔታዋ! እሷ ማለት ለኔ የስልሳ አራት ዓመት አሮጊት፣ ከጾምና ከምሕላ ሌላ የምታዉቀዉ የሌላት ምስኪን
ሃይማኖተኛ ናት፡ እንዲያዉ አዳሯ በገዛ ቤቷ ከመሆኑ በቀር፣ ሙሉ
ሕይወቷ ከመናኝ አይተናነስም፡ በቤተ መንግሥት ዙሪያዉን ባሉ ገዳማት እና አብያተ ክርስቲያናት፣ ለትንሽ ለትልቁ የምትታዘዝ ገዳማዊት ብቻ ናት። በጭራሽ እናቴን አላዉቃትም በቃ።
“በዚህ በኩል” አለችኝ፣ ከሩስያዉ የመጨረሻ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ኒኮላስ ለኢትዮጵያዉ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ የተላh መሆኑን የሚያመላክት ጽሑፍ በግርጌ ወደ ሰፈረበት ጽዋዕ እየወሰደችኝ
ከዚህ ቀደም ቤተ መዘክሩን በጎበኘሁ ጊዜ አስጎብኚዉ ስለ ጽዋዉ ያብራራልኝን አልረሳሁትም ከጽዋዉም አልፎ ጽዋዉን ስለላከዉ የሩስያ ንጉሥ ጭምር ገልጾልኛል። ለሃያ ሦስት ዓመታት ገደማ በሩስያ መንገሡን፣ የሩስያ ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ድረስ በቅዱስነቱ እንደምታወሳዉ፣ ዝነኛዉ የሀገሩ አብዮት ዘመኑን እንደ ቀጨበት
ያብራራልኝን ከነፊቱ ገጽ አስታዉሰዋለሁ። ስለ ንጉሡ ያልነገረኝ አልነበረም።
ይኼ ሩስያዊ ንጉሥ ለሐበሻዉ ንጉሥ የላከዉ ጽዋዕ አጠገብ ስትደርስ፣እመዋ ፈገግ ብላ አየችኝ። ደግሞ ምን ልትለኝ ይሆን?
“ነይ ነይ እምዬ ማርያም
ነይ ነይ ቤዛዊት ዓለም”
ስትል በፊቴ አንጎራጎረች፣ የሩስያዉ ንጉሥ ለአፄ ምኒልክ የላከዉ ጽዋዕ አጠገብ ቆማ ፊቷ የፈገግታ ብርሃን እንደ ፈነጠቀበት
“ዳዊት እደግማለሁ ቆሜ ገረገራ
እመቤቴ ማር ያም ኢትዮጵያን አደራ
ነይ ነይ እምዬ ማርያም”
ከመሬት ተነስታ እንዳልዘመረችዉ ይገባኛል። ምንም እንኳን መዝሙሩ ነባር እና ሕዝባዊ መዝሙር ቢሆንም፣ የእሷን ምክንያት ግን አግኝቼዋለሁ በሲራክ ፯ ማዕከል ዉስጥ ሥራዎቻችንን ጨርሰን ትንሽ
ፋታ ያገኘን እንደሆነ፣ አባላቱ ሁሉ ከበዉ የሚያዘምሩኝ እኔም እንደ
ጸሎት የምቆጥረዉ መዝሙር ነዉ። ከዚህ በላይ፣ ራሷ አፍ አዉጥታ የሲራክ ፯ አባል ነኝ እስከምትለኝ ልጠብቅ ካላልሁ በቀር፣ እናቴ ግን እንደማስባት ዓይነት ሰዉ ብቻ አለመሆኗን በተግባር ጭምር
አሳይታኛለች፡
“ተከተዪኝ” አለችኝ ጽዋዉን ትኩር ብላ ስታይ ቆይታ፣ ዘወር ብሎ
ወዳለዉ ሥዕል ደግሞ እየተራመደች። ልክ ከፊት ለፊቱ ስትቆም፣ ነፋስ የነካዉ ያህል ሥዕሉ መወዛወዝ አመጣ፡ ዓይኔን ተክዬ የሚሆነዉን ሁሉ
ተጠባበቅሁ: አፍታ ያህል ሲወዛወዝ ከቆየ በኋላ፣ የድምፅ ፍጥነትን በሚስተካከል ፍጥነት ተገልብጦ የፊቱ ወደ ጀርባ፣ የጀርባዉ ወደ ፊት ተለወጠ። ሥዕሉ ግን አሁንም ያዉ የቅድሙ ዓይነት ነዉ።
የሆነዉ ሆኖ ሥዕሉ ሥዕል ብቻ፣ እመዋም እመዋ ብቻ እንዳልሆነች
ገብቶኛል።
“አሁን ባልቻ እንዴት እንዳመለጠ ሳይገባሽ አልቀረም” አለችኝ
በፈገግታ።
ወደ ቤተ መንግሥቱ ግቢ የሚዘልቅ የዋሻ መንገድ አለ ማለት ነዉ?አፌን ከፍቼ፣ ዓይኔን በልጥጬ እንዳፈጠጥሁባት ቀረሁ እየቆየ የባሰ እየደነቀኝ፣ ሁሉም ነገር ቅዠት እየመሰለኝ መጣ፡ ጭንቅላቴ በጥያቄ
መዐት ተጠቃ። ሚሊዮን ጥያቄ በዉስጤ እየተዥጎደጎደ፣ አንደኛዉ ከሌላኛዉ ተሽቀዳደመብኝ፡ የሲራክ ፯ አባል ነሽ? እሺ አባል ከሆንሽ ምን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
....“አንድ ጊዜ ከባልቻ ጋር እዚህ መጥታችሁ ነበር አይደል?” አለችኝ እንደ ዋዛ፣ ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት በቅንድቧ እየጠቆመችኝ፡
“አዎ” አልኋት፣ እኔም እንደ ዋዛ፡ “እ?” አልኋት ወዲያዉ፣ ዉሃ ሆኜ ምን ምን? ያለችዉን ነገር እኮ ገና አሁን ነዉ ልብ ያደረግሁበት::
ከማን ጋር ምንድነዉ ያለችኝ? ባልቻ? እርፍ! እንዴት እንዴት ነዉ ነገሩ? በድንጋጤ ተዝለፍልፌ አለመዉደቄ፣ ለራሴ ደነቀኝ፡ መሬቱን ይዤ አረፍ ማለትም አሰብሁ፡ ቢሆንም ግን ቸኩሎ መደናገጥን የሲራክ ፯ ማንነቴ
ስለማይፈቅድልኝ ማስጨረስ አለብኝ፡ ጥርሴን ነክሼ እንደ ምንም ተበራታሁ።
“በዚህ በኩል” አለችኝ፣ ወደ ታዕካ ነገሥት ቤተ መዘክር እያስገባችኝ
ወደ ቤተ መዘክሩ ስመጣ የመጀመሪያዬ ስላልሆነ ብርቅ አልሆነብኝም እንጂ፣ እንደዚህ ማንኛዉንም ሰዉ መንፈሳዊ የሚያደርግ ወደረኛ ቦታ
አለ ቢሉኝ አላምንም ሲጀመር በከተማ ዉስጥ ካሉ ገዳማት እንደዚህ የጸጥታ እና የአርምሞ ገዳም አላዉቅም። በበርሐ ካሉትም የሚስተካከል
ትክክለኛ የገዳም ይዞታ ያለዉ ግቢ ነዉ፡ ዕድሜ በጠገቡ እና ራሳቸዉ ታሪክ በሠሩ ጽዶች የተሞላ ስለሆነ፣ እዚህ ግቢ የገባ ሰዉ ዉጣ ዉጣ አይለዉም እንኳንስ ለአማኝ እና ለተማጻኝ ይቅርና፣ ለማንኛዉም ሰዉ
መረጋጋትን የሚሰጥ ገራሚ ሥፍራ ነዉ።
ቤተ መዘክሩ ዐሥር ብር የከፈለ ማንኛዉም ታሪክ ወዳጅ የሚጎበኘዉ ሕዝባዊ ቤት ቢሆንም፣ የሚገኘዉ ግን በዋናዉ የገዳሙ ሕንጻ ምድር ቤት ነዉ፡ ስለዚህ ወደ ቤተ መዘክሩ ለመግባት የግድ ጫማ አዉል
በቅኔ ማኅሌቱ በኩል ማለፍ ይጠይቃል። በዋናነት የዳግማዊ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል፣ የእቴጌ ዘዉዲቱ፣ የአቡነ ማቴዎስ
ግብጻዊ የልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ ዐጽሞች በየራሳቸዉ ወርቃማ ሳጥን ዉስጥ ተከብረዉ የተቀመጡበት ሲሆን፣ ዓይነተ ብዙ የካህናት እና የነገሥታት ቅርሳ ቅርሶችም አሉበት ከነዚህም መካከል ሮማዊዉ ሊቀ ጳጳስ ለአፄ ምኒልክ የላኩላቸዉ የሚካኤል አንጀሎን ትክክለኛ የእጅ ሥዕል ጨምሮ ብዙ የሚነገርላቸዉ ከሩስያ ከግሪክ ከጣልያን እና ከተለያዩ ሀገራት መንግሥታትን የተበረከቱ ቅርሶች
ሞልተዉ ተትረፍርፈዉበታል። እንዲሁም ንግሥተ ነገሥታት ዘዉዲቱ ለጸሎት ይጠቀሙበት የነበረ ወንበር፣ የእጅ ጽሑፋቸዉ ያለበት ዉዳሴ ማርያም እና ሌሎች የብራና መጻሕፍት እና ለእሳቸዉ የተሰጡ ታሪዊ ስጦታዎች ጭምር አሉበት። ለአድዋ ዘመቻ ሲታወጅ የተጎሰመዉ ነጋሪት፣ አድዋ
ድረስ የዘመተችዋ ድል አድራጊዋ የጃንሆይ መቀመጫ ወንበር ሁሉ
የሚገኙት በሌላ አይደለም፡ እዚሁ ታዕካ ነገሥት ቤተ መዘክር ዉስጥ
ነዉ።
ያም ሆኖ ግን ቤተ መዘክሩን የሚጎበኘዉ ሰዉ በታሪኩ ልክ ብዙ ነዉ ማለት አይቻልም እስከዚህም ነዉ ያን ያህል ንጉሥ ንጉሥም፣ ካህን ካህንም የሚሸት እና ቢናገሩለት የማያልቅ የቅርስ ክምችት እንዳልሞላበት
ሁሉ፣ ጎብኚ ግን ከስንት አንድ ነዉ ብቅ የሚልበት። ያዉም የዉጪ
ሀገር ሰዉ፡ ዛሬ ደግሞ ይባስ ብሎ ከነጭራሹ ማንንም አላየሁበትም። አስጎብኚዎቹም እንኳን በአካባቢዉ የሉም
“እና፣ ወደ ቤተ መንግሥቱ ያመጣችሁን ጉዳይ እንደሚሆን እንደሚሆን ከዉናችሁት ልትወጡ ስትሉ ተይዛችሁ ነበር አሉ?” አለችኝ እመዋ፣ በዚያ የዉድ ዉድ እቃዎች ክምር መካከል ለብቻችን ስንዋኝ።
ዝም ብዬ ባዳምጣት ይሻለኛል ምን ልል እችላለሁ? ጭጭ እርጭ ብዬ አዳመጥኋት። ጭራሽ ተዪዛችሁ ነዉ ያለችዉ? በስመ አብ!
“ከዚያ ባልቻ አቺን ደብቆ ራሱን አጋለጠ። አንቺ ይኸኔ የእሱ መጨረሻ እያሳሰበሽ እንደ ምንም ከቤተ መንግሥቱ ጠባቂዎች ስታመልጪ ቀድሞሽ ውጪ አገኘሽዉ በምን ተአምር ከእነሱ እጅ እንዳመለጠ ግን እስከ
አሁንም ድረስ ባሰብሽዉ ቁጥር ይገርምሻል አይደለም? በእርግጥም ግን እኮ ይገርማል። የመንግሥት ደኅነቶች ለመያዝ ዘገምተኞች ናቸዉ እንጂ ከያዙ እኮ አይለቁም ይባላል”
እመዋን አላዉቃትም ለካ በእርግጥ ግን ይቺ ሰዉ እመዋ ራሷ ናት ከንግግሩ አነጋገሯ ከአነጋገሯ ሁኔታዋ! እሷ ማለት ለኔ የስልሳ አራት ዓመት አሮጊት፣ ከጾምና ከምሕላ ሌላ የምታዉቀዉ የሌላት ምስኪን
ሃይማኖተኛ ናት፡ እንዲያዉ አዳሯ በገዛ ቤቷ ከመሆኑ በቀር፣ ሙሉ
ሕይወቷ ከመናኝ አይተናነስም፡ በቤተ መንግሥት ዙሪያዉን ባሉ ገዳማት እና አብያተ ክርስቲያናት፣ ለትንሽ ለትልቁ የምትታዘዝ ገዳማዊት ብቻ ናት። በጭራሽ እናቴን አላዉቃትም በቃ።
“በዚህ በኩል” አለችኝ፣ ከሩስያዉ የመጨረሻ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ኒኮላስ ለኢትዮጵያዉ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ የተላh መሆኑን የሚያመላክት ጽሑፍ በግርጌ ወደ ሰፈረበት ጽዋዕ እየወሰደችኝ
ከዚህ ቀደም ቤተ መዘክሩን በጎበኘሁ ጊዜ አስጎብኚዉ ስለ ጽዋዉ ያብራራልኝን አልረሳሁትም ከጽዋዉም አልፎ ጽዋዉን ስለላከዉ የሩስያ ንጉሥ ጭምር ገልጾልኛል። ለሃያ ሦስት ዓመታት ገደማ በሩስያ መንገሡን፣ የሩስያ ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ድረስ በቅዱስነቱ እንደምታወሳዉ፣ ዝነኛዉ የሀገሩ አብዮት ዘመኑን እንደ ቀጨበት
ያብራራልኝን ከነፊቱ ገጽ አስታዉሰዋለሁ። ስለ ንጉሡ ያልነገረኝ አልነበረም።
ይኼ ሩስያዊ ንጉሥ ለሐበሻዉ ንጉሥ የላከዉ ጽዋዕ አጠገብ ስትደርስ፣እመዋ ፈገግ ብላ አየችኝ። ደግሞ ምን ልትለኝ ይሆን?
“ነይ ነይ እምዬ ማርያም
ነይ ነይ ቤዛዊት ዓለም”
ስትል በፊቴ አንጎራጎረች፣ የሩስያዉ ንጉሥ ለአፄ ምኒልክ የላከዉ ጽዋዕ አጠገብ ቆማ ፊቷ የፈገግታ ብርሃን እንደ ፈነጠቀበት
“ዳዊት እደግማለሁ ቆሜ ገረገራ
እመቤቴ ማር ያም ኢትዮጵያን አደራ
ነይ ነይ እምዬ ማርያም”
ከመሬት ተነስታ እንዳልዘመረችዉ ይገባኛል። ምንም እንኳን መዝሙሩ ነባር እና ሕዝባዊ መዝሙር ቢሆንም፣ የእሷን ምክንያት ግን አግኝቼዋለሁ በሲራክ ፯ ማዕከል ዉስጥ ሥራዎቻችንን ጨርሰን ትንሽ
ፋታ ያገኘን እንደሆነ፣ አባላቱ ሁሉ ከበዉ የሚያዘምሩኝ እኔም እንደ
ጸሎት የምቆጥረዉ መዝሙር ነዉ። ከዚህ በላይ፣ ራሷ አፍ አዉጥታ የሲራክ ፯ አባል ነኝ እስከምትለኝ ልጠብቅ ካላልሁ በቀር፣ እናቴ ግን እንደማስባት ዓይነት ሰዉ ብቻ አለመሆኗን በተግባር ጭምር
አሳይታኛለች፡
“ተከተዪኝ” አለችኝ ጽዋዉን ትኩር ብላ ስታይ ቆይታ፣ ዘወር ብሎ
ወዳለዉ ሥዕል ደግሞ እየተራመደች። ልክ ከፊት ለፊቱ ስትቆም፣ ነፋስ የነካዉ ያህል ሥዕሉ መወዛወዝ አመጣ፡ ዓይኔን ተክዬ የሚሆነዉን ሁሉ
ተጠባበቅሁ: አፍታ ያህል ሲወዛወዝ ከቆየ በኋላ፣ የድምፅ ፍጥነትን በሚስተካከል ፍጥነት ተገልብጦ የፊቱ ወደ ጀርባ፣ የጀርባዉ ወደ ፊት ተለወጠ። ሥዕሉ ግን አሁንም ያዉ የቅድሙ ዓይነት ነዉ።
የሆነዉ ሆኖ ሥዕሉ ሥዕል ብቻ፣ እመዋም እመዋ ብቻ እንዳልሆነች
ገብቶኛል።
“አሁን ባልቻ እንዴት እንዳመለጠ ሳይገባሽ አልቀረም” አለችኝ
በፈገግታ።
ወደ ቤተ መንግሥቱ ግቢ የሚዘልቅ የዋሻ መንገድ አለ ማለት ነዉ?አፌን ከፍቼ፣ ዓይኔን በልጥጬ እንዳፈጠጥሁባት ቀረሁ እየቆየ የባሰ እየደነቀኝ፣ ሁሉም ነገር ቅዠት እየመሰለኝ መጣ፡ ጭንቅላቴ በጥያቄ
መዐት ተጠቃ። ሚሊዮን ጥያቄ በዉስጤ እየተዥጎደጎደ፣ አንደኛዉ ከሌላኛዉ ተሽቀዳደመብኝ፡ የሲራክ ፯ አባል ነሽ? እሺ አባል ከሆንሽ ምን
👍21🥰3❤1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
....“ሃያ ስምጉት ሳምንት: ደህና። መቼም ዉሃ እስከሚበቃ ጠጥተሻል አይደለም?” አለችኝ፣ ኮስተር ብላ በአንዴ ከጓደኛነት ወደ ሐኪምምነት እየተሻገረች።.
"አዎ፤ ሽንቴን ለመቋጠር ስቁነጠነጥ አታዪኝም?”
“ደምሽንስ እየተከታተልሽዉ ነዉ፤ ጥሩ ነዉ?”
“እዉነቱን ለመናገ Check አድርጌዉ አላዉቅም ወሰድ መለስ ሲያደርገኝ ሰንብቼ ወደ ቀልቤ የተመለስሁት ገና ዛሬ ነዉ
አልገርምሽም? ቅድም ስንገባ ራሱ ምድር ቤት መለካት እችል ነበር።
ደርሼ ልምጣ እንዴ አሁንም?”
“አይ አይ፤ ኧረ እዚሁ እናየዋለ”
እጅጌዬን ሰበሰብሁና ጠረጴዛዉ ጠርዝ ላይ አስደግፌ ዘረጋሁላት። የደም
ግፊት መለኪያዉን አምጥታ አሰረችልኝ፡
“oK. Nice, right? 128/74 ይላል። ጥሩ ነዉ ያለሽዉ። ሌላ የተለየ
ያጋጠመሽ ነገር የለም አይደል?”
ለመናገር ዳድቼ፣ እንደ መሳቀቅ ብዬ ቀረሁባት።
“ምንድነዉ እሱ፤ አለ እንዴ? "
“አልፎ እልፎ፣ ቀለል ያለ ደም ይፈሰኛል” በዚያ ላይ ቀደም ብሎ ይሰማኝ
የነበረዉ የፅንሱ እቅስቃሴ፣ አሁን እየተሰማኝ አይደለም”
"ምን'? ታዲያ መምጣት አልነበረብሽም? የተለየ ነገር ከገጠመሽ እንድትመጪ ተስማምተን አልነበረ?”
ልክ መሆኗን ስላወቅሁ፣ ምላሽ የሚሆን አላገኘሁላትም። ዝም ብዬ
አቀርቅሬ መሬት መሬቱን አየሁ፡
“እሺ መቼ ነዉ የጀመረሽ?”
“ምኑ?”
“ደም መፍሰሱ”
“እ፤ ደም መፍሰሱ እኳን ትናንት ነዉ የጀመረኝ ገና የእሷ እንቅስቃሴ ግን
ከተሰማኝ ሰንብቷል: አንድ ሳምት አያልፍም ብለሽ ነዉ?”
አስከትላ ማንኛዉም ለእርግዝና ክትትል የመጣ ታካሚ የሚጠየቀዉን ሁሉ ጠየቀችኝ: መቼስ ከሐኪም እና ከንስሐ አባት የሚደበቅ የለም ይባል የለ? ስለ ምግብ፣ ስሜት፣ የአካል እንቅስቃሴ፣ መንፈሳዊ ብርታት እና ስለመሳሰሉት ሁኔታዎቼ ሁሉ እንደ አጠያየቋ በግልጽነት እዉነት ዉነቱን ብቻ መለስሁላት የሁሉም መልስ ግን ያዉ ነዉ በአጭሩ፣
የትኛዎቹም ላይ ግድ የለሽ እንደ ነበርሁ አመንሁላት፡ አሁን እንደ ጓደኛም እንደ ሐኪምም ብትቆጣኝ እንደሚያምርባት ስለማዉቅ ራሴን ለዚያ አመቻችቻለሁ
“ዉብዬ፣ እኔ አንቺን እንዲህ አድርጊ ወይ አታድርጊ አልልሽም" ራስሽ
ታዉቂዋለሽ” ብላ ወደ በሩ እንደ መራመድ ካለች በኋላ፣ በሩን በኃይል ቦርቀቅ አድርጋ ከፍታ አፈጠጠችብኝ
ተከትያት ልነሳ በእጄ እሸቴ ጭን ላይ ስመረኮዝ፣ ስልኩን ሰረቅ አድርጎ አሳየኝ አሁኑኑ የሚል መልእክት ከባልቻ ተልኮለት ኖሮ፣ ምን ይሻላል የሚል ፊቱን አስነበበኝ። ቃል ሳናወጣ አዉርተን፣ አሁኑኑ ወደ ሲራክ ፯ መሄድ እንዳለበት ተማከርን ተግባባን፡
ብድግ አለ
“ወዴት ነዉ እሸቴ? እዚህ እኮ ልትጠብቀን ትችላለህ” አለችዉ፣ በቢሮ መቆየቱ አሳቅቶት የተነሳ መስሏት።
“አይ አይ፤ መሄድ አለብኝ: አጉል አድርጌ የተዉኩት ሥራ ነበረብኝ
አሁኑኑ መሄድ አለብኝ”
“እንዴ! ዉቤን ለብቻዋ ጥለሃት?”
“ምን ታደርጊዋለሽ፤ የእኀጀራ ጉዳይ…”
“ይኼን ያህል? የት ነዉ ግን የምትሠራዉ?”
“እ” ተንተባተበ፡፡ እንዲያዉም እንዲያ ነሽ አሉ ተረተኞች? እንኳን እሱ
እኔም ከእሷ ያልጠበቅሁት ጥያቄ ስለነበር፣ ክዉ ብያለሁ።
“የየየየየየ መንግሥት መሥሪያ ቤት ነዉ የምሠራዉ” አለ ለፊቷ መመለሻ፣ ወዳፉ እንደ መጣለት፡ ጎበዝ አልሁት በምልክት
“ተዉ እንጂ፣ የት?”
“..እ..…ንንንን..ግድ
የኢትዮጵያ ንግድ ባክ”
“አሪፍ! ባንከሮችማ መናፈሻችሁ ሳይቀር የብር ጫካ ነዉ አላሉም?''
“ሳቅንላት፡ ተሳሳቅን፡ አጋጣሚዋን በመጠቀም፣ እሸቴ በሳቅ እያታለለ
ሹልክ ብሎ ወጣ፡ በቅጡ እንኳን አልተሰናበታትም
"አንቺስ ዉቤ?
“እ..ኔ ምን?” አልኋት፣ የእሸቴን መንተባተብ እኔም እየደገምሁት
የት እንደምትሠሪ መቼ ነገርሽኝ''
“አይ እኔ እንኳ ን ለጊዜዉ ሥራ የለኝም። ምናልባት አንቺ በሆስፒታላችሁ
ታስቀጥሪኝ እደሆነ እንጂ፣ የቤት እመቤት ነኝ”
"አግኝተነሽ ነዉ? በይ ነይ ተነሺ ይልቅ አልትራሳዉድ ክፍል ደርሰን እንምጣ” አለችኝ፣ እንድነሳ በግማሽ ዓይኗ እየደገፈችኝ።
"ውቤ! ሰዓቱን ግን ልብ ብለሽዋል? ባለሙያዉ አልትራሳዉንድ ክፍሉን
ጠርቅሞት ይኼድልሽና በብላሽ መመለስሽ ነዉ: አጅሬዉ ጠዋት ሲገባ
ማርፈዱን እንጂ፣ ከመዉጫ ሰዓቱ እንኳን ደቂቃ ማሳለፉንም አያዉቅበት። ቶሎ በይ፣ እንድረስበት”
እኔ ሆኜባት ነዉ እንጂ፣ አብራ የመዉጣት የመዉረድ ግዴታዋ ሆኖ አይደለም ለየክፍሉ የየራሱ ባለሙያ ስላለዉ፣ ሂጅ ዉጤቱን አሰርተሽ አምጪ ማለት ትችላለች እኔ ግን እኔ ሆንሁባት
እንዳለችዉም፣ ስንደርስ ባለሙያዉ ሊወጣ በር በሩን እያየ ነበር ልክ
ሲያየን ብልጭ አለበት፡ በተለይ እሷን ከፍ ዝቅ አድርጎ ጮኸባት፡ ባለፈዉ በእኔ ጉዳይ ተዋክባ እሷ እሱን በዚሁ ድምፀት ስታናግረዉ ሰማኋት ያን ያህል አልደነገጥሁም፡ ብድሩን ነዉ የመለሰባት፡
“ምን ነካሽ ዶክተር? መዉጫ ሰዓቴን ጠብቀሽ መምጣት ምን የሚሉት
ነገር ፍለጋ ነዉ? ''
“ግድየለም፣ ያን ያህል ጊዜ አልፈጅብህም” አለችዉ፣ ልክ ትርፍ ዉለታ እንደምትጠይቀዉ ሁሉ በመለማመጥ
""ቤቴ የት ሀገር እንደሆነ እያወቅሽ?”
“ነገርኩህ እኮ፤ከመዉጫ ሰዓትህ አንዲት ደቂቃ አላሳልፍብህም ካሳለፍሁብህ ደግሞ ታቋርጠኛለህ። ቶሎ በል ይልቅ አብራዉ አጠፋፍተኸዋል መሰል ደግሞ”
እኔም ጊዜ ለመቆጠብ፣ እስከምታዘዝ ድረስ ሳልጠብቅ ቀልጠፍ ብዬ
አልጋዉ ላይ ለምርመራ ተመቻችቼ የእንግላል ሆንሁላቸዉ
እየተነጫነጨም ቢሆን የፈጀዉን ጊዜ ፈጅቶ፣ ሁሉንም ነገር ዝግጁ አደረገዉ
ከዶክተር ሸዊት የወደድሁላት ጥሩ ጸባይ፣ ያለ ሙያዋ ጥልቅ አትልም ዛሬም ሆነ ባለፈዉ እንዳስተዋልኋት ከሆነ፣ ጣልቃ መግባት ቢያስፈልጋት እንኳን፣ ቢያንስ ቢያንስ ፈቃድ ትጠይቃለች፡ ዛሬም
እንዲህ ባለቀ ሰዓት ዉስጥ ሆና፣ ባለሙያዉን ጠበቀችዉ፡ ለነገሩ
ሙያዉም ያንን አይፈቅድም፡፡ በተለይ አልትራሳዉንድ በባሕሪዉ፣ ለማዳ እጅ ይፈልጋል ዉጤቱን ትክክልም ስሕተትም የሚያመጣዉ ከመሣሪያዉ ዘመናዊነት ይልቅ የባለሙያዉ (የራዲዮሎጂስቱ) ልምድ ያለው እጅ መሆኑ ነው ይባላል።
“እያየሽዉ ነዉ ዶክተ?” አለ ራዲዮሎጂስቱ፣ መከሰቻዉ ላይ ዓይኑን
ሰክቶ ልክ ያልሆነ ነገር እንዳየ አዉቂያለሁ
“እ፤ እስኪ እስኪ” አለች እሷም፣ ትንፋሿ እየተቆራረጠ፡ ባለሙያዉን
ገፈተረችዉና ራሷ ገባችበት፡ “NO! አይደረግም!” ብላ ጮኸች።
ወዲያዉ ደግሞ በፊቴ መደንገጧ ይበልጥ አስደነገጣት፡ ጀርባዋን ሰጥታኝ
ያልደነገጠች ለመምሰል ብትሞክርም፣ እንደገና ከድንጋጤዋ ለመመለስ
ብትሞክርም፣ የትኛዉም አልሆነላትም
“በቃ፣ ጨርሻለሁ። መዘጋጋት ትችላለህ” አለችዉ ግራ ቀኝ ስትንቆራራጠጥ ቆይታ፣ ከአልጋዉ ላይ ደግፋ እያስነሳችኝ፡፡
“ኧረ ችግር የለም፣ የማግዝሽ ነገር ካለ እንዲያዉም ያን ያህል የሚ ያስቸኩል ጉዳይ የለኝም” አላት፣ እንደዚያ እሳት ለብሶ የነበረዉ ሰዉዬ በአንድ ጊዜ ዉሃ እየሆነ በሐዘኔታ አየኝ፡
“ዉብዬ” አለችኝ፣ የተከሰተዉን እንድመለከተዉ በአገጯ እየጠቆመችኝ
ግብኔን ወደ ጠቆመችኝ መከሰቻ አዞርሁላት። “ያዉ፣ ባለፈዉ እንደ ጠበቅነዉ፤ እንደፈራነዉ ሳይሆን አልቀረም በእርግጥ ያን ጊዜ ምልክቶቹን ባየን ጊዜ፣መልሶ ይቀንሳል የሚል ጭላንጭ ተስፋ ነበረኝ በበኩሌ።ሆኖም ፅንሱን እንደምታይዉ
ባልተመጣጠነ የጭንቅላት የፈሳሽ መጠን የተነሳ፣ ጭንቅላቱ ከመጠን በላይ አድጓል። ይኼ እንዳለ ሆኖ፣ መጀመሪያም ምልክቱን ያየነዉ የጀርባዋ አጥት ክፍተት ደግሞ እየሰፋ መጥቷል”
ትንሽ ተያየን፡፡ ከእሷም በሆዴ ካለችዋም ጋር አጭር ቆይታ አደረግሁ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
....“ሃያ ስምጉት ሳምንት: ደህና። መቼም ዉሃ እስከሚበቃ ጠጥተሻል አይደለም?” አለችኝ፣ ኮስተር ብላ በአንዴ ከጓደኛነት ወደ ሐኪምምነት እየተሻገረች።.
"አዎ፤ ሽንቴን ለመቋጠር ስቁነጠነጥ አታዪኝም?”
“ደምሽንስ እየተከታተልሽዉ ነዉ፤ ጥሩ ነዉ?”
“እዉነቱን ለመናገ Check አድርጌዉ አላዉቅም ወሰድ መለስ ሲያደርገኝ ሰንብቼ ወደ ቀልቤ የተመለስሁት ገና ዛሬ ነዉ
አልገርምሽም? ቅድም ስንገባ ራሱ ምድር ቤት መለካት እችል ነበር።
ደርሼ ልምጣ እንዴ አሁንም?”
“አይ አይ፤ ኧረ እዚሁ እናየዋለ”
እጅጌዬን ሰበሰብሁና ጠረጴዛዉ ጠርዝ ላይ አስደግፌ ዘረጋሁላት። የደም
ግፊት መለኪያዉን አምጥታ አሰረችልኝ፡
“oK. Nice, right? 128/74 ይላል። ጥሩ ነዉ ያለሽዉ። ሌላ የተለየ
ያጋጠመሽ ነገር የለም አይደል?”
ለመናገር ዳድቼ፣ እንደ መሳቀቅ ብዬ ቀረሁባት።
“ምንድነዉ እሱ፤ አለ እንዴ? "
“አልፎ እልፎ፣ ቀለል ያለ ደም ይፈሰኛል” በዚያ ላይ ቀደም ብሎ ይሰማኝ
የነበረዉ የፅንሱ እቅስቃሴ፣ አሁን እየተሰማኝ አይደለም”
"ምን'? ታዲያ መምጣት አልነበረብሽም? የተለየ ነገር ከገጠመሽ እንድትመጪ ተስማምተን አልነበረ?”
ልክ መሆኗን ስላወቅሁ፣ ምላሽ የሚሆን አላገኘሁላትም። ዝም ብዬ
አቀርቅሬ መሬት መሬቱን አየሁ፡
“እሺ መቼ ነዉ የጀመረሽ?”
“ምኑ?”
“ደም መፍሰሱ”
“እ፤ ደም መፍሰሱ እኳን ትናንት ነዉ የጀመረኝ ገና የእሷ እንቅስቃሴ ግን
ከተሰማኝ ሰንብቷል: አንድ ሳምት አያልፍም ብለሽ ነዉ?”
አስከትላ ማንኛዉም ለእርግዝና ክትትል የመጣ ታካሚ የሚጠየቀዉን ሁሉ ጠየቀችኝ: መቼስ ከሐኪም እና ከንስሐ አባት የሚደበቅ የለም ይባል የለ? ስለ ምግብ፣ ስሜት፣ የአካል እንቅስቃሴ፣ መንፈሳዊ ብርታት እና ስለመሳሰሉት ሁኔታዎቼ ሁሉ እንደ አጠያየቋ በግልጽነት እዉነት ዉነቱን ብቻ መለስሁላት የሁሉም መልስ ግን ያዉ ነዉ በአጭሩ፣
የትኛዎቹም ላይ ግድ የለሽ እንደ ነበርሁ አመንሁላት፡ አሁን እንደ ጓደኛም እንደ ሐኪምም ብትቆጣኝ እንደሚያምርባት ስለማዉቅ ራሴን ለዚያ አመቻችቻለሁ
“ዉብዬ፣ እኔ አንቺን እንዲህ አድርጊ ወይ አታድርጊ አልልሽም" ራስሽ
ታዉቂዋለሽ” ብላ ወደ በሩ እንደ መራመድ ካለች በኋላ፣ በሩን በኃይል ቦርቀቅ አድርጋ ከፍታ አፈጠጠችብኝ
ተከትያት ልነሳ በእጄ እሸቴ ጭን ላይ ስመረኮዝ፣ ስልኩን ሰረቅ አድርጎ አሳየኝ አሁኑኑ የሚል መልእክት ከባልቻ ተልኮለት ኖሮ፣ ምን ይሻላል የሚል ፊቱን አስነበበኝ። ቃል ሳናወጣ አዉርተን፣ አሁኑኑ ወደ ሲራክ ፯ መሄድ እንዳለበት ተማከርን ተግባባን፡
ብድግ አለ
“ወዴት ነዉ እሸቴ? እዚህ እኮ ልትጠብቀን ትችላለህ” አለችዉ፣ በቢሮ መቆየቱ አሳቅቶት የተነሳ መስሏት።
“አይ አይ፤ መሄድ አለብኝ: አጉል አድርጌ የተዉኩት ሥራ ነበረብኝ
አሁኑኑ መሄድ አለብኝ”
“እንዴ! ዉቤን ለብቻዋ ጥለሃት?”
“ምን ታደርጊዋለሽ፤ የእኀጀራ ጉዳይ…”
“ይኼን ያህል? የት ነዉ ግን የምትሠራዉ?”
“እ” ተንተባተበ፡፡ እንዲያዉም እንዲያ ነሽ አሉ ተረተኞች? እንኳን እሱ
እኔም ከእሷ ያልጠበቅሁት ጥያቄ ስለነበር፣ ክዉ ብያለሁ።
“የየየየየየ መንግሥት መሥሪያ ቤት ነዉ የምሠራዉ” አለ ለፊቷ መመለሻ፣ ወዳፉ እንደ መጣለት፡ ጎበዝ አልሁት በምልክት
“ተዉ እንጂ፣ የት?”
“..እ..…ንንንን..ግድ
የኢትዮጵያ ንግድ ባክ”
“አሪፍ! ባንከሮችማ መናፈሻችሁ ሳይቀር የብር ጫካ ነዉ አላሉም?''
“ሳቅንላት፡ ተሳሳቅን፡ አጋጣሚዋን በመጠቀም፣ እሸቴ በሳቅ እያታለለ
ሹልክ ብሎ ወጣ፡ በቅጡ እንኳን አልተሰናበታትም
"አንቺስ ዉቤ?
“እ..ኔ ምን?” አልኋት፣ የእሸቴን መንተባተብ እኔም እየደገምሁት
የት እንደምትሠሪ መቼ ነገርሽኝ''
“አይ እኔ እንኳ ን ለጊዜዉ ሥራ የለኝም። ምናልባት አንቺ በሆስፒታላችሁ
ታስቀጥሪኝ እደሆነ እንጂ፣ የቤት እመቤት ነኝ”
"አግኝተነሽ ነዉ? በይ ነይ ተነሺ ይልቅ አልትራሳዉድ ክፍል ደርሰን እንምጣ” አለችኝ፣ እንድነሳ በግማሽ ዓይኗ እየደገፈችኝ።
"ውቤ! ሰዓቱን ግን ልብ ብለሽዋል? ባለሙያዉ አልትራሳዉንድ ክፍሉን
ጠርቅሞት ይኼድልሽና በብላሽ መመለስሽ ነዉ: አጅሬዉ ጠዋት ሲገባ
ማርፈዱን እንጂ፣ ከመዉጫ ሰዓቱ እንኳን ደቂቃ ማሳለፉንም አያዉቅበት። ቶሎ በይ፣ እንድረስበት”
እኔ ሆኜባት ነዉ እንጂ፣ አብራ የመዉጣት የመዉረድ ግዴታዋ ሆኖ አይደለም ለየክፍሉ የየራሱ ባለሙያ ስላለዉ፣ ሂጅ ዉጤቱን አሰርተሽ አምጪ ማለት ትችላለች እኔ ግን እኔ ሆንሁባት
እንዳለችዉም፣ ስንደርስ ባለሙያዉ ሊወጣ በር በሩን እያየ ነበር ልክ
ሲያየን ብልጭ አለበት፡ በተለይ እሷን ከፍ ዝቅ አድርጎ ጮኸባት፡ ባለፈዉ በእኔ ጉዳይ ተዋክባ እሷ እሱን በዚሁ ድምፀት ስታናግረዉ ሰማኋት ያን ያህል አልደነገጥሁም፡ ብድሩን ነዉ የመለሰባት፡
“ምን ነካሽ ዶክተር? መዉጫ ሰዓቴን ጠብቀሽ መምጣት ምን የሚሉት
ነገር ፍለጋ ነዉ? ''
“ግድየለም፣ ያን ያህል ጊዜ አልፈጅብህም” አለችዉ፣ ልክ ትርፍ ዉለታ እንደምትጠይቀዉ ሁሉ በመለማመጥ
""ቤቴ የት ሀገር እንደሆነ እያወቅሽ?”
“ነገርኩህ እኮ፤ከመዉጫ ሰዓትህ አንዲት ደቂቃ አላሳልፍብህም ካሳለፍሁብህ ደግሞ ታቋርጠኛለህ። ቶሎ በል ይልቅ አብራዉ አጠፋፍተኸዋል መሰል ደግሞ”
እኔም ጊዜ ለመቆጠብ፣ እስከምታዘዝ ድረስ ሳልጠብቅ ቀልጠፍ ብዬ
አልጋዉ ላይ ለምርመራ ተመቻችቼ የእንግላል ሆንሁላቸዉ
እየተነጫነጨም ቢሆን የፈጀዉን ጊዜ ፈጅቶ፣ ሁሉንም ነገር ዝግጁ አደረገዉ
ከዶክተር ሸዊት የወደድሁላት ጥሩ ጸባይ፣ ያለ ሙያዋ ጥልቅ አትልም ዛሬም ሆነ ባለፈዉ እንዳስተዋልኋት ከሆነ፣ ጣልቃ መግባት ቢያስፈልጋት እንኳን፣ ቢያንስ ቢያንስ ፈቃድ ትጠይቃለች፡ ዛሬም
እንዲህ ባለቀ ሰዓት ዉስጥ ሆና፣ ባለሙያዉን ጠበቀችዉ፡ ለነገሩ
ሙያዉም ያንን አይፈቅድም፡፡ በተለይ አልትራሳዉንድ በባሕሪዉ፣ ለማዳ እጅ ይፈልጋል ዉጤቱን ትክክልም ስሕተትም የሚያመጣዉ ከመሣሪያዉ ዘመናዊነት ይልቅ የባለሙያዉ (የራዲዮሎጂስቱ) ልምድ ያለው እጅ መሆኑ ነው ይባላል።
“እያየሽዉ ነዉ ዶክተ?” አለ ራዲዮሎጂስቱ፣ መከሰቻዉ ላይ ዓይኑን
ሰክቶ ልክ ያልሆነ ነገር እንዳየ አዉቂያለሁ
“እ፤ እስኪ እስኪ” አለች እሷም፣ ትንፋሿ እየተቆራረጠ፡ ባለሙያዉን
ገፈተረችዉና ራሷ ገባችበት፡ “NO! አይደረግም!” ብላ ጮኸች።
ወዲያዉ ደግሞ በፊቴ መደንገጧ ይበልጥ አስደነገጣት፡ ጀርባዋን ሰጥታኝ
ያልደነገጠች ለመምሰል ብትሞክርም፣ እንደገና ከድንጋጤዋ ለመመለስ
ብትሞክርም፣ የትኛዉም አልሆነላትም
“በቃ፣ ጨርሻለሁ። መዘጋጋት ትችላለህ” አለችዉ ግራ ቀኝ ስትንቆራራጠጥ ቆይታ፣ ከአልጋዉ ላይ ደግፋ እያስነሳችኝ፡፡
“ኧረ ችግር የለም፣ የማግዝሽ ነገር ካለ እንዲያዉም ያን ያህል የሚ ያስቸኩል ጉዳይ የለኝም” አላት፣ እንደዚያ እሳት ለብሶ የነበረዉ ሰዉዬ በአንድ ጊዜ ዉሃ እየሆነ በሐዘኔታ አየኝ፡
“ዉብዬ” አለችኝ፣ የተከሰተዉን እንድመለከተዉ በአገጯ እየጠቆመችኝ
ግብኔን ወደ ጠቆመችኝ መከሰቻ አዞርሁላት። “ያዉ፣ ባለፈዉ እንደ ጠበቅነዉ፤ እንደፈራነዉ ሳይሆን አልቀረም በእርግጥ ያን ጊዜ ምልክቶቹን ባየን ጊዜ፣መልሶ ይቀንሳል የሚል ጭላንጭ ተስፋ ነበረኝ በበኩሌ።ሆኖም ፅንሱን እንደምታይዉ
ባልተመጣጠነ የጭንቅላት የፈሳሽ መጠን የተነሳ፣ ጭንቅላቱ ከመጠን በላይ አድጓል። ይኼ እንዳለ ሆኖ፣ መጀመሪያም ምልክቱን ያየነዉ የጀርባዋ አጥት ክፍተት ደግሞ እየሰፋ መጥቷል”
ትንሽ ተያየን፡፡ ከእሷም በሆዴ ካለችዋም ጋር አጭር ቆይታ አደረግሁ
👍34