አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በጥላሁን

ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭን መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"

ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዋ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰማኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••ኀ
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በአሌክስ_አብርሃም

"ልጄን! ልጄን እያለች እናቴ ወደ እኔ
ስትሮጥ ይሰማኛል …ቀለል አለኝ !
።።።።
ለድፍን አንድ ሳምንት ከቤቴ ሳልወጣ አሳለፍኩ፤ ከእሁድ እስከ እሁድ፡፡ ምን እኔ ብቻ፣ ከዚያች ምሽት ጀምሮ እናቴ እንቅልፍ አልነበራትም፣ ለወትሮው ጧት ጧት ሳታዛንፍ የምትስመውን ቤተክርስቲያን ርግፍ አድርጋ ትታ፣ የእኔው ጠባቂ ሆና አብራኝ ታሰረች፡፡ እንኳን ከቤት ርቄ ልሄድ፣ ለሽንት እንኳን ከቤታችን ኋላ ወዳለው መፀዳጃ ቤት ደረስ ብዬ ለመመለስ አታምነኝም፡፡ ተከትላኝ ወጥታ በር ላይ ትቆማለች፡፡ ተጨንቃ ነበር፡፡
እውነት ነበራት ደግሞ፤ ድፍን ከተማው ሌላ ወሬ አልነበረውም፡፡ “የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛው የአቶ ዝናቡ ልጅ እቤታቸው ያስጠጓትን ምስኪን ሕፃን ልጅ ደፈረ…”

እግዚኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦ! ስምንተኛው ሺ!”

ጎረቤቱ ከላይ እስከታች በአንድ ጊዜ የነመሐሪን ቤተሰቦች ረጋሚ እና ዘላፊ ሆኖ ነበር፡፡
ይኼ ዘለፋ ታዲያ ባለፍ ገደም ወደኔም እንጥፍጣፊው መድረሱ አልቀረም፡፡ ያስገረመኝ የዚህ የጥላቻ ዘመቻ ዋና አራጋቢዎች ሰፈር ውስጥ ትምህርት እምቢ ያላቸው ልጆች መሆናቸው! እነሱም ብሎ ጎበዝ ተማሪም ይላሉ፡፡ መቼም መሐሪ ሲነሳ “እነሱ” ከተባለ
ያው አንዱ እኔው ነኝ፡፡ እስቲ አሁን ጉብዝናችን ላይ ምን ወስዶ አንጠላጠላቸው? በዚህ ሰበብ ጉብዝናችንን ካዱትም አልካዱትም ትምህርት ሚኒስተር መጽዋች ስለሆነ አይደለም አራት ነጥብ የሰጠን፡፡ ምን ያገናኘዋል? ሲያጨበጭቡልን እየተበሳጩ ነበር እንዴ ሰፈራችንን አስጠራችሁት ያሉት፣ ሰበብ አግኝተው እንደ ኦሪት መስዋዕት ከሰፈር አውጥተው ሊያቃጥሉን ነበር እንዴ? ግን ከተፈጠረው ነገር ይልቅ፣ የተበለጡትን መከረኛ ትምህርት እያነሱ፣ መሐሪንም እኔንም ሲያንቋሽሹ ነበር ውለው የሚያድሩት፡፡
አብሯቸው የኖረ የበታችነት እና የመብለጥ ስሜት፣ ሳሌም የምትባል መርፌ ስትወጋው እንደባሉን እየተነፈሰ ነበር ፡፡

አባባ እንደ ማንኛውም ቀን ፣ምንም እንዳልተፈጠረ፣ በነጠላ እራፊ የተጠመጠመ እግሩን በተደራረበ ትራስ ላይ አሳርፎ፣ (አስር ጊዜ ትራሱን አስተካክልልኝ እያለ)ስለእቁብ
ሲያወራ ይውላል፡፡ ይኼ ነገሩ ትንሽ ቢያሳዝነኝም፣ ከእናቴ ጭንቀት ይልቅ የእርሱ ግድ የለሽነት የተሻለ ያረጋጋኝ ስለነበር፣ ብዙውን ጊዜ የማሳልፈው ከአባባ ጋ በማውራት ነበር፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን የሆነ ነገር እንዲለኝ ፈልጌ ነበር፡፡ ቢያንስ አይዞህ እንዲለኝ፡፡
አይዞህ ብቻ፡፡ ምንም ቢያወራ ነገሬ ብዬ ከማልሰማው አባባ፣ አንድ ቃል ናፈቀኝ፡፡
አባትነት ልጅ በመውለድ ብቻ የሚመጣ ነገር እንዳልሆነ የገባኝ ያኔ ነው እየወደድኩት ውስጤ ያዝን ነበር፡፡ ነፍሱ ውስጥ እኔ የለሁም እላለሁ፡፡ ሩቅ
ሐገር ተፈጽሞ በዜና ቢሰማ እንኳን ስሜትን የሚረብሽ ነገር እዚህ አፍንጫው ሥር፣ ያውም ከወንድምም በሚቀርብ የልጁ ጓደኛ ተፈጽሞ ፣ ጎረቤቱ ሁሉ እየዛተና እየፎከረ - “ድሮውንም አንገት
ደፊ” በሚል ገደምዳሞሽ አሽሙር፣ በሌለሁበት እኔንም ጨምሮ እየቀጣኝ ምንም ስሜት ያልሰጠው አባት፣ እንዴት ዓይነት ተፈጥሮ ቢኖረው ነው!? እያልኩ እገረማለሁ፡፡

ለእኔ ብቻ ሳይሆን፣ የእናቴን ጭንቀት ትንሽ እንኳ ቢካፈላት፣ ሌት ተቀን ልጇን ሊነጥቋት እንደከበቧት አራስ ነብር፣ ቁጣና ስጋት ከቧት ስትንቆራጠጥ፡ ኮሽ ባለ ቁጥር ብርክ ሲይዛትና፣ በበር ሽንቁር ወደውጭ እያጨነቆረች ስትመለከት፣ እይዞሽ ቢላት ምናለበት፣ እያልኩ አስባለሁ፡፡ ተኚ እኔ አለሁ ለምን አይላትም? እልናገረውም ግን
አስባለሁ፡፡ ምንም ይሁን አባት፣ ፈርጣማ ክንድ ባይኖረው እንኳ፣ ተስፋና ማጽናናት
እንዴት ይነጥፍበታል፡፡ “እንድ ሰው የልጄን ስም ያነሳና፣ ውርድ ከራሴ፣ እሱ ምን
ያርጋችሁ? እዚህ እንደ እንሽላሊት በየጥጋጥጉ እየሄዳችሁ የምታሽሟጥጡት” ቢል ምን
ይሆናል አንድ ቤት የምንኖር ሳይሆን፣ ታክሲ ፌርማታ ላይ ድንገት ተገናኝተን፣ ታክሲ እስከሚመጣ የምንጠብቅ መንገደኞች የሆንን እስኪመስለኝ ምንም የምንጋራው ስሜት አልነበረም፡፡ ቸልተኛ ነበር፤ እሽ ይሁን፡ ቸልተኝነቱን ትንሽ ወደ ምክር ቢለውጠው እና አይደል፤ አትስማቸው '' ችላ ብሎ ማለፍ ነው" ቢል፡፡

ገና እቤት መዋል በጀመርኩ በሦስተኛው ቀን፡ እናቴን እንዲህ እላት፡፡ “በመንደሩ ያለው ሰው የዝናቡ ልጅ ብቻ ነው እንዴ?…ይውጣና ኮመንደሩ ልጆች ጋር ንፋስ ተቀብሎ ይምጣ፤ እንግዲህ አንዴ የሆነው ሁኗል፡ የፈሰሰ ውሃ እይታፈስ!”፡፡ እንዴ የሆነው ሁኗል ማለት ምን ማለት ነው? እንዳትደግመው እንጂ የሆነው ሆኗል ነበር የሚመስለው አነጋገሩ፡፡ ከዚያ በፊት ችላ ብየው፣ አልያም ሳላስተውለው ቆይቼ የገረመኝ ነገር ደግሞ፣አባቴ መሐሪን በስሙ ጠርቶትም ሆነ ጓደኛህ” ብሎ አያቅም፡፡ “የዝናቡ ልጅ” ነው የሚለው፡፡ ለነገሩ አባባ፣ መሐሪን ብቻ ሳይሆን፣ ሕፃንም ይሁን ወጣት በስም
አይጠራም፡፡ የእከሌ ልጅ ነው የሚለው፡፡ ሴቶችን ሳይቀር “ይች የእከሌ ሚስት” ነው የሚለው፡፡

ይኼው አሁንም “የዝናቡ ልጅ ብቻ ነው ወይ በመንደሩ ያለው? ይለኛል፡፡እና በመንደሩ ማን አለ? …ከመሐሪ ሌላ ማን አለ? …መሐሪ ከሰፈር ልጆች እንዱ አልነበረምኮ መሐሪ ጓደኛ ብቻ አልነበረምኮ ከመኖር ብዛት የራሳችንን ቋንቋ የፈጠርን፣ ሁለት ሰዎች ውስጥ የተቀመጠች አንዲት ውብ ነፍስ የተጋራን ፍጥረቶች ነበርን፡፡ ቃል ሳንተነፍስ
ልባችን ውስጥ ያለውን ሐሳብ በአንድ የዓይን ጥቅሻ የምንካፈል፡፡ ትንሽ ዓለሜ
የቆመችው፣ ሁለት ምሰሶዎች ላይ ነበር፡፡ አንዱ እኔ ራሴ፣ አንዱ መሐሪ! ግማሽ እኔ እስር ቤት ውስጥ ነኝ ሚዛኗን ስታ እየተንገዳገደች ያለች ሚጢጢ ዓለሜን፣ ወደፊት መራመዱ ቢቀር፣ ቀጥ ብላ እንድትቆም እየታገልኩ ነበር፡፡ ለድጋፍ እጁን የሚሰጥ ሰው እንጂ፣ ግዴለም በአንድ እግርህ ውጣና፣ ሌላ እግር ፈልግ የሚል ሰው አልነበረም ፍላጎቴ! “ከሰፈር ልጆች ጋር ነፋስ ተቀበል” ይለኛል፡፡ እንኳን አብሬው ነፋስ የምቀበለው የሰፈር ልጅ፣ በመንደሩ ውስጥ ነፋስ አለ ወይ?… መንደሩስ ራሱ አለወይ … እቤቴ ቁጭ
ያልኩት (ምን ቁጭ ያልኩት የተደበኩት) እንደ ሕፃን ልጅ የራሴን ዓይን ስጨፍን
ከዓለም ሁሉ የተደበቅሁ መስሎ እየተሰማኝ፣ ለአፍታም ቢሆን እፎይታ ስለሚሰማኝ ነበር፡፡ በሆነው ሁሉ ከማፈሬ ብዛት የሰው ዓይን ፈርቼ ነበር፡፡
መሐሪ ሁለት ቀን ፖሊስ ጣቢያ ቆይቶ በሦስተኛው ቀን ፍርድ ቤት ቀረበ ተባለ፡፡ የዚያኑ ቀን ከሰዓት በኋላ፣ ወደ ትልቁ ማረሚያ ቤት እንደተወሰደ ሰማሁ፡፡ ይኼን ሲነግሩኝ፣ ያ አሮጌ የብረት በር እየተንሳጠጠ ከኋለው ሲከረቸምበት ታየኝ፡፡ ውስጤ ሂድ ሂድ ይለኛል፡፡ከስንት ዓመታት በፊት ያየሁት ማረሚያ ቤት ሲታወሰኝ፣ዘገነነኝ፡፡ የማቅለሽለሽ
ስሜትም ተሰማኝ፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ ዝም ብሎ የማቅለሽለሽ ስሜት ቶሎ ቶሎ
ይሰማኛል፡፡ሳምንቱን ሙሉ እንደ ነፍሰጡር ምግብ ሲሸተኝ፣ ጧት ስነሳ ያቅለሸልሽኝ ነበር፡፡

ግንኮ እስከ ዛሬ ብዙ ነገር ይስተካከል ይሆናል” ብዬ እራሴን ለማጽናናት ሞከርኩ፡፡ለምሳሌ ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ዘመናዊ የመዋኛ ገንዳ ተሠርቶ ሊሆን ይችላል (መሐሪ ዋኝቶ አያውቅም እንጂ ዋና ይወዳል፡፡ ስናድግ እቤቱ የመዋኛ ገንዳ ሊያስገባ ሐሳብ ነበረው) ምናልባት ምሳቸው በባልዲ የተቀዳ ወጥ ሳይሆን፣ ነጫጭ ልብስ በለበሱ ጠረጴዛዎች ላይ፣ በቆንጆ አስተናጋጆች በሸክላ ሰሀን የሚቀርብ ብዙ ዓይነት ምግብ ሊሆን ይችላል፡፡ በቅመም ያበደ ሻይም ከምሳ በኋላ ይቀርብላቸው ይሆናል። (መሐሪ
ከምሳ በኋላ እንደዚያ ዓይነት ሻይ ይወዳል) ከዚህ ሁሉ
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሶስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን
ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን ሰላምታ ከተሰጣጣን በኋላ ጁማህን መፈለግ
ጀመርን። ፊቱን ወደ ጫካው ያዞረ ጡብ ቤት ደጃፍ ላይ ዥዋዥዌ ላይ ተቀምጦ ነበር። ከጎኑ መሳሪያ ነበር። ቀስ ብለን ወደ እሱ ስንጠጋ ፊቱን አዞሮ አየን።

ከባድ መሳሪያ ይዘህ ነው ምትዞረው ማለት ነው?” ብሎ አል ሃጂ ቀለደ።

“እንግዲህ ምን ታረገዋለህ! ከ AK ከፍ እያልኩ ነው” ብሎ መለሰ።ሁላችንም ሳቅን።

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እንደምንመለስ ነግረነው ጥይት እና ምግብ ልንጭን ወደ መጋዝን ሄድን።መጋዝን እያለን አዛዣችን፥ መቶ አለቃ “ዛሬን ከዚህ እደሩ፤ እራት ተዘጋጅቷል” እንዳለ ነገረን፡፡ አልራበኝም፡ ስለዚህ ኬን እና አል ሃጂ ወደ እራት
ሲሄድ እኔ ተለይቼ ወደ ጁማህ ተመልሼ ሄድኩ። ማውራት ከመጀመሩ በፊት ለደቂቃዎች ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡

ነገ በጥዋት ለውጊያ ስለምወጣ ከመሄዳችሁ በፊት አላይህም” ብሎ ዝም አለ እና መሳሪያውን እየነካካ ቀጠለ:
የዚህን መሳሪያ ባለቤት ገደልኩት።
ብዙዎቻችንን ከገደለ በኋላ ነበር የደረስኩበት። ከዛ በኋላ ነበር እኔ የያዝኩት ”ብሎ ፈገግ አለ፡፡ እጃችንን አጋጨንና ሳቅን።ወዲያውኑ እንድንሰበሰብ ተጠራን:: ተሰባስቦ መጫወቻ እና
የአዛዦችን መተዋወቂያ ማህበራዊ ፕሮግራም ነበር። ጁማህ መሳሪያውን በአንድ እጁ ከያዘ በኋላ በሌላ እጁ ጫንቃየ ላይ አድርጎ አቅፎኝ ወደ መሰብሰቢያው ሜዳ ሄድን።ኬን እና አል
ሃጂ ከዛው እያጨሱ ነበሩ። መቶ አለቃም በቦታው ነበር። ትንሽ ፈንጠዝያ ነበር። የመቶ አለቃ ጓደኞች አብዛኞቹ ማለትም ሃምሳ አለቃ ማንሳራይ እና አስር አለቃ ጋዳፊ ሙተዋል። እሱ እንዴት
እንደተረፈ አይታወቅም። በተዕምር ምኑም ሳይነካ የለአንዳች ጠባሳ ተርፎ ሌሎች ሃይለኛ እና ታዛዥ ጓዶችን በሞቱ ጓደኞቹ ምትክ ለማፍራት በቅቷል።መቶ አለቃ ጋር ስለ ሼክስፔየር ማውራት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን እሱ በማስተባበር ፤ ሰላም በመስጠት ተጠምዶ ነበር። በመጨረሻ እኔ ፊት ለ ፊት ሲደርስ
እጄን ጥብቅ አርጎ ያዘና “ማክቤዝ አይበገርም፧ ታላቁ የብሪያም ጫካ ዶንከን ኮረብታ እስኪደርስ ድረስ ማክቤዝ እጅ አይሰጥም አለ።

ጮክ ብሎ ”ልለያችሁ ነው ጓዶች” አለ። እጅ ከነሳን በኋላ እጁን እያውለለበ ሄደ። እኛም መሳሪያችን ከፍ አድርገን በጩኸት
ሰላምታችን ገለጸን። መቶ አለቃ ከሄደ በኋላ የሴራሊዮንን ብሄራዊ መዝሙር መዘመር ጀመርን። “ከፍ አድርገን
እናከብርሻለን፤ የነጻ ህዝቦች ሃገር፤ ጥልቅ ነው ለአንቺ ያለን ፍቅር” ለሊቱን ሙሉ ስንጫወት ስናወራ አሳለፍን።
ከመንጋቱ በፊት ጁማህ እና የተወሰኑ ወታደሮች ለውጊያ ሄዱ። አል ሃጂ፣ ኬን እና እኔ በሚቀጥለው ጥየቃ ብዙ
እንደምንጫወት ቃል ገብተን ተሰናበትነው:: ጁማህ ፈገግታ ካሳየን በኋላ መሳሪያውን ጠበቅ አድርጎ ከያዘ በኋላ ወደ ጫካው ገባ፡፡

ከትንሽ ስዓታት በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ወደ መንደር መጣ፡፡ ዩኒሴፍ UNICEF የሚል ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ የለበሱ
አራት ሰዎች ከመኪናው ወርደው ወደ እኛ መጡ። አንድ ነጭ እና ቆዳዋ ነጣ ያለ ምንአልባት የሊባኖስ ሰው እና ሌሎቹ የሃገሩ ሰዎች ሴራሊዎናውያን ናቸው:: ጦርነቱን ያዩ አይመስሉም የተመቻቸው ነበሩ። ወደ መቶ አለቃ ተልከው የመጡ ይመስላሉ። እሱም ሲጠብቃቸው ነበር፡፡ ቤት ደጃፍ ተቀምጠው ሲያወሩ ከማንጎ ዛፍ ስር ተቀምጠን መሳሪያችንን
እየወለወልን እናያቸው ነበር። በኋላ መቶ አለቃ ከሁለቱ የውጭ ሃገር ሰዎች ጋር እጅ ተጨባበጠ፡፡ ጠባቂው ወደ እኛ መጣ እና እንድንሰለፍ ነገረን። ሰፈሩን እየዞረ ከ “ መቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው!” ትዕዛዝ መቀበል እና የታዘዝ ነውን መፈፀም ለምደናል። ወደ ጎን መስመር ሰርተን መጠበቅ ጀመርን።

መቶ አለቃ ከፊታችን ቁሞ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠን፡፡ ሌላ ግዳጅ እየጠበቅን ነበር፡፡ “አሳርፍ” ብሎ ቀስ ብሎ መራመድ
መቃኘት ጀመረ፡፡ እንግዶቹ ከጀርባ ነበሩ።
“ስጠቁም ወደ ጠባቂየ በመሄድ ትሰለፋላችሁ ገብቷችሃል።”ሲል “አዎ! አለቃ” ብለን ጮህን፡፡

“አንተ፣ አንተ.....” መቶ አለቃ እየመረጠ እስከ ሰልፉ መጨረሻ ደረሰ፡፡ መቶ አለቃ እኔን ሲመርጠኝ አትኩሬ ተመለከትኩት።
እሱ ግን አላየኝም:: አል ሃጂም ተመረጠ። ኬን ግን ትልቅ ስለሆነ አልተመረጠም:: “መሳሪያችሁን የጥይት ካዝና አወላልቃችሁ መሬት ላይ አስቀምጡ” የሚል ትዕዛዝ ከመቶ አለቃ ሰጠ፡፡ መሳሪያችንን አወላልቀን መሬት ላይ አስቀመጥን።መቶ አለቃን ተከትለን እንግዶች ወደ የመጡበት ገልባጭ መኪና ሄድን። መቶ አለቃ ፊቱን ወደ እኛ ሲያዞር ቆምን “ ጎበዝ ጀግና
ወታደር ነበራችሁ! ታውቃላችሁ የዚህ ወንድማማችነት እና ሃገርን የማዳን ጥሪ አካል እንደነበራችሁ። ከእናንተ ጋር ሃገሬን
በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል። ኮርቼባችዋለሁ። አሁን ስራችሁ
እዚህ ጋ ያበቃል። ልለቃችሁ ይገባል። እነዚህ ሰዎች ትምህርት ቤት ያስገቧችኋል፤ ሌላ መልካም ህይወት እንዲኖሩዋችሁ ይረድዋችኋል።” ይሄን ብቻ ነበር ተናግሮ ትቶን ሄደ:: ቀጥሎ
ፍተሻ ነበር። ሰንጢ እና ቦምብ ይዤ ስለነበር መፈተሽ አልፈለኩም፡ ፈታሹን ብትነካኝ እገልሃለሁ ብየ ዛትኩበት። ከእኔ
ጎን ወደ አለው ቀጠለ።

ምን እየሆነ እንዳለ አልገባኝም? መቶ አለቃ ለእነዚህ ሰዎች ለምን አሳልፎ ሊሰጠን እንደወሰነ አልገባኝም። ጦርነቱ እስኪበቃ ድረስ የምንቀጥል መስሎን ነበር፡፡ ግን ያለምንም ማብራሪያ
ተወሰድን፡፡

መኪና ውስጥ የደንብ ልብሳቸው ንጹህ እና መሳሪያቸው አዲስ የሆነ ሶስት ፖሊሶች ነበሩ። ፖሊሶቹ ከገልባጩ ወርደው እኛ እንድንወጣ ጠቆሙን። ወጥተን ሁለት አግድም ወንበሮች
ላይ ፊት ለ ፊት ተቀመጥን። ፖሊሶች መውረጃው ላይ ተቀመጥን።

አል ሃጂ እና እኔ በመገረም በብስጭት ተያየን። የት እንደሚወስዱን እንኳ አናውቅም። ለስዓታት ተጓዝን። ያለምንም ስራ ቁጭ ብሎ መጓዙ አድካሚም
አሰልቺም ነበር፡፡ መኪናውን ጠልፎ ወደ ባውያ ለመመለስ አሰብኩ። መሳሪያውን ለመንጠቅ ስዘጋጅ መኪናው ለፍተሻ
ፍጥነቱን ቀንሶ ፖሊሶቹ ወረዱ።
መቀመጥ ስላልቻልኩ በጉዞ በሙሉ እረፍት አልነበረኝም ያቁነጠንጠኝ ነበር። የፍተሻ ጣቢያዎች ስንደርስ ትንሽ ፈታ እል ነበር። በመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያ ያገኘናቸው ወታደሮች የሚያምር ደንብ ልብስ የለበሱ መሳርያቸው አዲስ ነበር።

በኮሮኮንች መንገድ የመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያውን አልፈን እንደሄድን የተጨናነቀ የአስፓልት መንገድ ደረስን። ዙሪያውን
መኪኖች በተለያየ አቅጣጫ ሲጓዙ አየሁ፡፡ በህይወቴ የዚህን ያህል ብዙ መኪኖች አይቼ አላውቅም፡፡ መርሰዲሶች፣ቶዮታዎች፣ማዝዳዎች፣ቼርቮያለ ትዕግስት ሲያጮሁ ሙዚቃ ሲያጫውቱ ነበር፡፡ የት እንደምንሄድ አሁንም አላውቅም ነገር ግን Freetown ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ እንዳለን
አውቂያለሁ።ለምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም፡፡

ውጩ እየጨለመ ነው። መኪናችን በዝግታ ወደ ተጨናነቀው መንገድ ሲገባ የመንገድ መብራቶች ተራ በተራ
እንደፍንጣቂ ነገር ቦግ ቦግ እያሉ መብራት ጀመሩ። የሱቆች እና
የመጠጥ ቤት መብራቶች ሳይቆጠር ብዙ መንገድ መብራቶች ከተማዋን አንቆጥቁጠዋታል። የከተማዋ ፎቆቹም በብዙ ብርሃን የተንቆጠቆጡ ናቸው። ለተወሰኑ ደቂቃዎች በፍጥነት
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...“ይቺ በመቀጨጭ ላይ ያለችዋ ” አሉ ዮናታን' ወደ ቆርቆሮው ውስጥ በጣታቸው እያመለከቱ።

“ እም ፡ አዎ ከእንግዲህ የምታድግ አትመስልም ”አሉ ዶክተር አጥናፉ ፥ ብዙም ባልተደነቀ ስሜት ።

“ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፡ ዐይናቸውን ወደ እስጉብኝው እያሸጋገሩ ።

“ አካባቢው ኣልተስማማት ይሆናላ ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ ፡ በቀልድ ዐይነት ! “ ወይም ደግሞ ፍሬዋ ከጓደኞቿ ተለይታ በተለየ ዐፈር ውስጥ መብቀል ፈልጋ ይሆናል ። ”

ከት ብሎም ባይስቅ እስጐብኝው ፈገግ አለ ። ዮናታን ግን የተቋጠረው ግንባራቸው አልተፈታም " ይብሱን ነገሩን
አጠንክረው
“ የአካባቢም ተጽፏኖ ሆና የዐፈሩ አለመማማት ፥ወይም ሌላ ችግር ፡ የስንዴዋ መቀጨጭ ከአያያዝ ግድየለሽ
ነት የመጣ ነው ። ገና ከእንጭጭነት ችግሯን አስተውሉ አካባቢዋን ወይም አፈሯን መለወጥ ቢቻል ኖሮ ለዚህ አት
ደርስም ነበር ። ግን አንድ ነች ። አንድ ነገር አንድ ነውና አብዛኛውን ጊዜ አናስብበትም ። አናስተውሰውም ። ጣሳው ሙሉ ተክል ሊበላሽ ቢሆን ኖሮ ግን ወዲያው መፍትሔ በተ ፈለገለት ነበር

አስጐብኝው በድንጋጤ ክው ብሎ ቀረ አምርረዋል ወይሰ ይቀልዳሉ ? ” አለ በልቡ እሱም ። አማካሪው ዶክተር ኤጥናፉ ቸል ያሉትን ነገር ዮናታን አምርረው መያዛቸው ምክንያቱ አልገባህ አለው ። “ ምነው ባልጋበዝኳችው ! ” አለ በልቡ ፡ አነጋገራቸው ዶክተር አጥናፉን
ይላውጥብኛል ብሎ ስለፈራ ዮናታንን በጥላቻ እያያቸው

“ ይህ እኮ አብዛኛውን ጊዜ ሊደርስ የሚችል አጋጣሚ ነው ። ደግሞስ የአንዱ መቀጨጭ ምን ያህል ይጎዳል ብለህ
ነው ? የዐፈሩ ተጽዕኖ በአብዛኛው ስንዴ ዕድገት ሲለካ ይችላል ዶክተር ፡ አሁንም ለነጎሩ ክብዶት ሳይሰጠት ።

“ ይጐዳል እንጂ እንዴት አይጐዳም ?” አሉ ዮናታን አምርረው ። “ የቆርቆሮው ተክል እኮ ስምንት የምታሰኘው
ይህቺ አንዷ ስትጨርስ ነበር ስትጐድል ግን ሰባት ታረገዋለች።አንድ ሳንቲም “ ዋጋ የለውም” እንላለን ። ግን “ ዋጋ
እንዳልው የምንረዳው አራት ሳንቲም ይዘን ስንቀር ነው ”

አስጐብኝው የባሰውን በጥላቻ ገላመጣቸው ። እሳቸው ግን ልብ አላሉትም ። እሱን መጉዳታቸውም አልታወቃችውም ። ዶክተር አጥናፉ ራሳቸው፣ “ሰውዬው አበደ እንዴ?”
በማለት ዐይነት በሆዳቸው እየሣቁ ፥ ምንም ሊጠይቁ ወይም ሊናገሩ ስላልቻሉ ዝም አሉ ።

ከጥቂት ዝምታ በኋላ ዮናታን ልምጭጭ ፈገግታ እያሳዩ' በምጸታዊ አነጋገር “ አየህ የአቤልም ነገር እንዲሁ ነው ” አሏቸው ።

ዶክተር አጥናፉ የዮናታን ውስጣዊ ስሜት እንዲህ የተለዋወጠበት ምክንያት ያው ገባቸው ። ስለ አቤል ጉዳይ ደጋግመው አነጋግረዋቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ለጉዳዩ ብዙም ክብደት ወይም አትኩሮት ባለመስጠት ቸል ብለውት ስለቆዩ
አሁን ጥያቄም ይሁን መልስ ማንሣት አልፈለጉም። ሐሳባቸውን ሁሉ ወደ ተክሉ በመሰብሰብ ዐይነት ከአስጐብኝው
ጋር ሐሳብ በመለዋወጥ ዮናታን የተነሡበትን ሐሳብ ለማዘናጋት ሞከሩ ። ይሁን እንጂ ፥ ዮናታን ውስጥ የሚንቦገቦገው ሐሳብ በቀላሉ የሚበርድ አልነበረም። ጉብኝቱን ጨርሰው
ከተክሉ ቤት ሲወጡ እንደ ገና አነሡባቸው ።

“ ሁላችሁም የዚህን ልጅ ጉዳይ ቸል ማለታችሁ ነው ? ያቤልን?እንዴትነው? አሁንም አልተሻለው?” አሉ ዶክተር
አጥናፉ ሸሽተው የማያመልጡት ነገር መሆኑን ገምተው ።

ይሻለዋል ? ጉንፋን ” ኮ አይደለም ያመመው ።ይህኛው አነጋገራቸው ቁጣ ብቻ ሳይሆን ተስፋ መቁረጥም
ነበረበት ።

የዮናታን አነጋገር ዶክተር አጥናፉን አላስቆጣቸውም ።የቅርብ ጓደኝነት ስላላቸው አንዳቸው የአንዳቸውን ጸባይ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡ዮናታን ከውስጥ ሥቀው ከላይ ጥርሳቸውን ማሳየት አይችሉም ። የተማረሩበትን ወይም የበሽቁበትን ነገር ማንም ፊት ይሁን ከማንም ጋር ፊትለፊት በቁጣ ተናግረው ነው የሚወጡት ። ከዚያ ንዴቱ ቢበርድላቸው ያው ሰው አክባሪነታችው ፍቅር የተሞላበት ሰላምታችሙ
ዮናታንነታቸው ይመለሳል ። ነገር ግን የዚህ ልጅጉዳይ ይህን ያህል ለምን እንዳንገበገባቸው ዶክተር አጥናፉ ጥርት ብሎ ሊታያቸው አልቻለም ።

“ ችግሩ ኮ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፥ የዮናታንን ቁጣ ማስታገሥ በሚችል ለዘብ ያለ አነጋገር ። “ ችግሩ የሁሉም አለመተባበር ነው ። ከአሁን በፊት በዩኒቨርስቲው ውስጥ እንዲህ ዐይነት ጉዳይ ትልቅ አትኩሮት ተሰጥቶት
ስላልተሠራ አሁንም ...

ዮናታን አላስጨረሳቸውም ።

“ እኔም እኮ የምለው ይህንኑ ነው ። ለምን አትኩሮት አይሰጠውም ? በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ካሉት ችግሮች አንዱ
አይደለም ወይ? አየህ ! ፍቅር ሲሠምር ፥ ሲገኝ ሲያብብ ደስታ ፍሥሐ ነው ። ከመገኘቱ በፊት ወይም ተግኝቶ ሲጠፋ ኃይለኛ ጥማት ፡ ሥቃይ ሕመም ነው ፥ ” አሉና፡ ነገሩን ከውሉጋር እንደማያያዝ ትንሽ ካሰቡ በኋላ ፥ “ አዎ ! እና ፥ ምንም
ይሁን ምን የ ግለሰብን ከዓላማው ወይም ከግቡ የሚያዘናጋ ወይም ራሱን የሚያስጠላ ሁኔታ እስከሆነ ድረስ መድኃኒቱ መፈለግ አለበት አሁን አቤል በዚህ ሁኔታ ተጨናግፎ ትምህርቱን ቢያቋርጥ ወይም ተደባብሶ ቢመረቅ ፡ ሁለተኛ ወደ ትምህርትና ምርምር ዓለም ፊቱን እንደማይመልስ አታውቅም ? ”

“ እሱ እንኳን በጤናቸው የሚመረቁትም የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ጸባይ ነው ። ሺ አስመርቀናል ፤ ነገር ግን
ምንም ተአምር የሠራ አላየንም አሉ ዶክተር አጥናፉ በንቀትና ተስፋ በቆረጠ ስሜት ።

ይህ የሚሆነው ለምን ይመስልሃል ? ! በእኔ ግምት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቶቻቸውን በፍቅር እንዲጀምሩ
ስለማናደርጋቸው ነው ።ሳያስቡት ዶክተር አጥናፉ ቢሮ ስለ ደረሱ ። በሩን ለመ
ክፈት ቁልፉን እየጠመዘዙ አሁንም በተሰላቸና ነገሩን ቶሎ ለመቁረጥ በዳዳ ስሜት • “ ብቻ ሁሉም ነገሩን እንዳንተ
ቢያስብበት ምናልባት ውጤት ያገኝ ይሆናል ። ግን እንዳየሁት ይህን ጉዳይ ብሎ ኮሚቴ ላይ አቅርቦ መፍትሔ ለመ
ፈለግ የሚሻ ሰው እንጂ ”

“ ይህ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፥ ተከትለዋቸው ወደ ቢሮ ውስጥ እየገቡ ፤ ይህ ራሱ ምሁርነታችን የሚያስከትልብን በሽታ ራሳችንን በጣም ከፍ አድርገን ስለምንግምት ከኛ በኋላ ሰው የሚፈጠር አይመስለንም ። ዐይናችንን ገልጠን ከተማሪዎቻችን መሐል ታላላቅ ሰዎች ሊበቅሉ እንደሚችሉ ማየትና መገመት አለብን ።
ይህ ስሜት ሲኖረን ብቻ ነው ተማሪዎቻችን እንቅፋት እንዳይመታቸው ልንጠነቀቅላቸው የምንችለው ”

“ ስደበና! ” አሉና ዶክተር አጥናፉ በቀልድ ፡ “ ለማንኛውም እስኪ ቁጭ በል” ሲሉ ዮናታንን ጋበዟቸው ።

“ አልቀመጥም ” አሉ ዮናታን ሰዓታቸውን እየተመለከቱ። “ ኦ! እንዲያውም ሰዓት አሳለፍን ። በአሥር ሰዓት አንድ ተማሪ ቀጥሬ ነበር።

“ እሺ እስቲ እንግዲህ በሚቻለን መንገድ እንታግሳለና ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ " ጉዳዩ ከውስጥ ባይፈነቅላቸውም ዮናታንን ለማስደስት ያህል "

“ በውነት እንዲያው በሚቻለን መንገድ ይህንን ልጅ መርዳት አለብን ። እባክህ ቸል አትበል ” አሉ ዮናታንም ረጋ ባለ አንደበትና ረዳት በሚፈልግ ስሜት ወደ
ከዚያ ፥
ወዲያው ወጥተው በመኪናቸው ወደ ስድስት ኪሎ በረሩ ። ከቢሮአቸው ሲደርሱ እስክንድር መዝጊያን
ተደግፎ ቆሞ አገኙት።

““ ሶሪ ዘግየሁብህ አይደለም ? ” አሉት በሩን ለመክፈት እየተቻኮሉ ። ዐሥር ደቂቃ አሳልፈውበት ነበር ።ጠዋት ገለጻ ክፍላቸው ውስጥ ክፍለ ጊዜኣቸውን ጨርሰው ሲወጡ ነበር በዚህ ሰዓት እንዲያገኛቸው የቀጠሩት ። የፈለጉት ለአቤል ጉዳይ መሆኑን ፈጽሞ አልተጠራ
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....“ወ/ሮ ሮበርትስ ባለቤትሽ ከሞተ በኋላ ለምን ያህል ጊዜ ነው ሥራ ፈተሽ የተቀመጥሽው?” ብሎ ጠየቃት መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን፡፡

ኒኪ በመመርመሪያ ክፍሉ ውስጥ ባለው ጠረጴዛ ሥር የሚገኘው መዳፏን በጥፍሯ እየወጋች ከአንድ እስከ አሥር ቆጥራ ጨረሰች፡፡በውስጧም ይሄ ሰው እንዲያናድደኝ እና ስሜታዊ ሆኜ እንድናገር እንዲያደርግ ልፈቅድለት አይገባም፡፡ በቃ የንዴት ስሜቴን እንዲያነሳሳብኝ በፍፁም ልፈቅድላት አይገባም፡፡ በፍፁም እሱ የሚፈልገውን ነገር ልሰጠው አይገባኝም አለች በውስጧ፡፡
“ይቅርታ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን ዶ/ር ሮበርትስ ነኝ” ብላ ድምጿን ለስለስ በማድረግ ስሟን ከሙያ ማዕረጓ ጋር እንዳልጠራት እና አስተካክሎ ስሟን እንዲጠራት ለማሳሰብ ብላ “ይህንን የዶር ማዕረጌን አስተካክለህ እና አስታውሰህ ለመጥራት ያስቸገረህ ይመስለኛል፡፡ ሁሌ እንደዚህ አይነት የማስታወስ ችግር አለብህ? ወይንስ ከዕድሜ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የመርሳት ችግር ነው ያለብህ?” ብላ ጠየቀችው፡፡

የዶ/ር ኒኪ ሮበርትስን መልስ የሰማው ጆንሰን ፊት በንዴት በጣም ከመቅላቱም በላይ መንጋጋውንም በንዴት ነክሶ ዶክተሯን ያያት ጀመር: አብሮት ያለው ባልደረባው ጉድማንም በኒኪ መልስ እና በጆንሰን ሁኔታ የመጣበትን ሳቅ
ውጦ አስቀረው። ዶ/ር ሮበርትስ ጥያቄዎችን የምትመልስለት ስሜቷን ተቆጣጥራ ሲሆን ጆንሰን ደግሞ በተቃራኒው ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ በንዴት ስሜት ነበር የሚመለከታት፡፡

“እኔ ምንም አይነት የማስታወስ ችግር ኖሮብኝ አያውቅም ሴትዮ ያንቺን ሙያ የማሞካሽበት የማዕረግ ስምሽ ለእኔ ምኔም አይደለም። በዚያ ላይ ደግሞ ሁለታችንም ትክክለኛ ዶክተር እንዳልሆንሽ በደንብ እናውቃለን።
አላት በንዴት እየጦፈ፡፡

ሚክ በንዴት ሊፈነዳ የደረሰ በጣም የበሰለ ቋሊማ ሆኗል። ባልደረባው
ሚክ ጆንሰን ከሴቶች ጋር ያለው ግንኙነት ጥሩ እንዳልሆነ ባልደረባውዐጉድማን ያውቃል። በተለይ ደግሞ እሱ በማያውቀው አንድ ምክንያት በዚህች
ሴት ላይ ያለው ጥላቻ ሥር የሰደደ መሆኑን ጉድማን ለመታዘብ ችሏል።
ይሄ ግን ለምን እንደሆነ ሊገባው አልቻለም:: በእሱ አመለካከት ዶ/ር
ሮበርትስ ዛሬ ይበልጥ ውብ ሆና ነው የመጣችው። የእርሳስ ቀለም ያለው
ጉርድ ቀሚስ እና ከቀሚሷ ጋር የሚስማማ የሀር ሸሚዝም አድርጋለች።
ሰውነቷ ጥብቅ ያለ መሆኑንም በአይኑ እያየው ነው። በዚያ ላይ ደግሞ
እርጋታዋ እና ሁሉንም ስሜቶቿን መቆጣጠር መቻሏ ይበልጥ የምትስብ
አድርጓታል፡፡ በሉው ጉድማን አይን ደግሞ እንደዚህ ራሳቸውን እና ስሜታቸውን የሚገዙ ሰዎች ይበልጥ አይንን የሚስቡ ቆንጆ ሴቶች እንደሆኑ ይገምታል፡፡

“ጥያቄውን ብቻ መልሺ! ለምን ያህል ጊዜ ነበር ሥራ ፈትተሽ የተቀመጥሽው?” ብሎ ጆን በቁጣ ድምፅ ጠየቃት፡፡

“ወደ ስድስት ሳምንት ገደማ ያህል።” ብላ ኒኪ መለሰችላት፡፡

“ረጅም ጊዜ ይመስላል?”

“ብለህ ነው?” ብላ ኒኪ በአጭር ሀሳቡን ቆረጠችበት፡፡

“አዎ ረዥም ጊዜ ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ለመኖር ሁላችንም መሥራት ይጠበቅብናል። እኛ እንደ አንቺ አይደለንም፤ ያለ ሥራ ለብዙ ጊዜ መቆየት
አንችልም እና ጉራሽን ባትቸረችሪብን ደስ ይለናል ወ/ሮ ሮበርትስ። ምናልባት የሞተው ባልሽ ብዙ ሀብቶችን ስለተወልሽ አሁን ላይ ሀብታም ሴት ለመሆን ችለሻል” አላት፡፡

ኒኪም መርማሪው ስለ እሷ ሀብታምነት እንደዚህ መዘርዘሩ እና የነገሩ አካሄድ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም::

“ዶውግም በህይወት እያለ ቢሆን እኮ እኔ የገንዘብ ችግር የሌለብኝ ሰው ነበርኩኝ አቶ ጆንሰን። ስለዚህም የእሱ መሞት በእኔ ገቢ ላይ ምንም አይነት ለውጥ አያመጣብኝም።” አለች።

“ህምም” ብሎ ጆንሰን አጉረመረመ እና በመቀጠልም “ከመቼ ጀምሮ ነው
ትሬይ ትሬቮን አንቺ ጋር ተቀጥሮ መስራት የጀመረው?” ብሎም ጠየቃት።
ኒኪም በሀዘን ስሜት ውስጥ ሆና በረዥሙ ተነፈሰች። የትሬይን መሞት
እስከ አሁን ድረስ አምና መቀበል አልቻለችም:: የእሱን ህይወት አስመልክቶ
ለዚህ ደነዝ ፖሊስ ምንም አይነት ነገር መናገር አትፈልግም።

“እኔ እንጃ መቼ እንደሆነ በእርግጠኝነት አላስታውስም።”

“እሺ ወደ ሥራ ከተመለስሽ በኋላ ነው ወይንስ ባልሽ በአደጋ ከሞተ
በኋላ?”

“እሱ ከሞተ በኋላ ነው” ብላ ኒኪ መለሰችለት እና ወደ ጉድማንም
በመዞር “እነዚህ ጥያቄዎች ከግድያው ጋር ያላቸውን ግንኙነት አልተረዳሁም፡፡ ከዚህ ይልቅ ግን ከዚህ ክፍል በመውጣት ሊዛ እና ትሬይን ማን እንደገደላቸው ማወቅ እና መያዝ አይገባችሁም? ማለቴ ከእኔ ጋር የሚሰሩ ሰዎችን የቅጥር ጊዜ መጠየቁ መፍትሄ አለው ብላችሁ
ታስባላችሁ?”

አሁንም እኮ እያደረግን ያለነው አንቺ የምትናገሪውን ነገር ነው?” ብሎ
ጆንሰን በቁጣ ድምፅ በመቀጠልም “በሁለቱ ግድያዎች መካከል ያሉትን
ግንኙነቶች ለማየት ሞክረን ነበር። ገምቺ እስቲ... ሁለቱ ሟቾች በጋራ የሚያውቁት አንድ ሰው አለ፡፡” ብሎ ወንበሩ ላይ ከተለጠጠ በኋላም በጠቋሚ
ጣቱ ወደ ኒኪ ቀስሮ “አንቺ ነሽ ዶክተር ሮበርትስ?” አላት።
“እኔ ሊዛን እና ትሬይን እንደገደልኳቸው ታስባለችሁ?” ብላም ሁለቱን መርማሪ ፖሊሶች ጠየቀቻቸው፡፡ ጥያቄዋን ስታቀርብ ፊቷን ወደ ጆንሰን
አዙራ ስለነበር የጠየቀችው ጆንሰን መልስ ለመስጠት ወፍራም ከንፈሩን
ከፍቶ ሊመልስ ሲል ጉድማን ከወንበሩ ላይ ዘሎ ተነሳ እና “ እንደዛ ማለታችን አይደለም” ብሎ በማስከተል “አንቺ ሁለቱም ሟቾች የሚያውቁሽ ሰው ነሽ፡፡ ስለዚህ ምናልባት ነፍሰ ገዳዩ ከአንቺ ጋር የሆነ ግንኙነት ሊኖረው ይችላል ብለን እንድናስብ እንገደዳለን። አለ አይደል የቀድሞ ታካሚሽ ሊሆን ይችላል። የአሁን ላይ ታካሚሽም ሊሆን ይችላል፤ በአንቺ የሥራ ሁኔታ ደግሞ በጣም የተረበሹ ሰዎች ገጥመውሽ ሊሆን ይችላል። ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ በአንቺ እና በአንቺ ዙሪያ ከሚገኙ ሰዎች ጋር የከረረ ግንኙነት ሊኖረው ይችላል። ምናልባትም ይሄ አደገኛ ግለሰብ ሊሆን ይችላል ግድያውን የፈፀመው ብለን እናስባለን።”

ኒኪ ጉድማን የነገራትን ነገር አሰላሰለች። ግን በአዕምሮዋ ውስጥ ይህንን
ሊያደርግ የሚችል ሰው ሊመጣላት አልቻለም። በእሷ ሥራ ላይ እንደሚገኙት ባልደረቦቿ እሷ አንድም ቀን ቢሆን በታካሚዎቿ ጥቃት ደርሶባት አያውቅም። አንዳቸውም ቢሆኑ ከእሷ ጋር ያልተገቡ የፍቅር ስሜቶችን አስተናግደው አያውቁም። እርግጥ ነው አንድ ታካሚ ከቴራፒስቱ ጋር የቀቢፀ ተስፋ እሳቤ ሊኖረው ይችላል። ግን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ ሁለት ሰዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሊግድላቸው አይችልም።

“ስለዚህ የበፊት እና የአሁን ታካሚዎችሽ የግለሰብ መዝገቦችን ማየት እንፈልጋለን፡፡” ብሎ አስረዳት፡፡

“መልካም” ብላ ኒኪ በሀሳብ ጭልጥ ብላ ጠፋች።

“የሁሉንም ታካሚዎችን መዝገብ ነው የምንፈልገው።” ብሎ ጆንስን ጮህባት
እና “ግን ምንም አይነት አርትዖት ሳታደርጊባቸው እና ምንም አይነት የሀኪም እና ታካሚ ሚስጥር መጠበቅ የሚባል ነገርን ሳታደርጊ ነው” አላት ጆንሰን፡፡ “ምናልባት እኮ ነፍሰ ገዳዩ ከአንቺ ታካሚዎች መሀከል ሊሆን አይገባውም” ብሎ በባልደረባው እና በተመርማሪዋ መሀከል ያለውን ውጥረት ከዚህ በላይ እንዳይከር በማሰብ “የምታስታውሻቸው ጠላቶች አሉሽ ዶክተር? የሆነ ሰው አንቺን እና በአንቺ ዙሪያ የሚገኙ ሰዎችን ሁሉ ሊጎዳ የሚችል ሰው ይኖራል ብለሽ ታስቢያለሽ?”

“እረ የለም!” ብላ ኒኪ በመዳፏ አይኗን አሸች፡፡ “የሉም እንዲያውም እንደዚህ ያለ ሰውን አላስታውስም፡፡ ምን አይነት ጠላቶች ናቸው?”
👍2
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_ሶስት

#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

"አላሁ አክበር....አላሁ አክበር“አለ ኢማሙ የዕለተለን የማለዳ እስላማዊ ፀሎት ሊያደርስ
አስቻለው ዛሬ መንገደኛ ስለሆነ ከእንቅልፉ ያነቃው ዘንድ ሲጠብቀው የነበረ ድምፅ ነው
ልክ እንደነቃ ከአንገቱ ቀና ብሎ ነቅነቅ ሲል አልቀለለውም ከሰውነቱ ልጥፍ ብላ የተኛች ደሴት አለች ሔዋን ተስፋዬ።

በወርሃ የካቲት ሁልታኛ ሳምንት ላይ ሽዋዬ ዲላ ውስጥ አልነበረችም፡፡ለአንድ ሳምንት የሚቆይ አጭር የስራ ላይ ስልጠና ልትካፈል ወደ አዲስ አበባን ሄዳለች። በዚያው ሳምንት በዕለተ ሐሙስ አስቻለው ወደ አዲስ አበበ ሊሄድ ተነስቷል ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዋና መስርያ ቤት የዝውውር ጥያቄ ሊያቀርብ።

በአስገዳጅ ሁኔታ ግንኙነታቸውን ለጊዜው ለማቋረጥ ወስነው የነበሩት አስቻለውና ሔዋን ለዚያች እለት የጋራ ቃላቸውን በጋራ አፍርሰዋል የሸዋዬን አለመኖር አጋጣሚ ተጠቅመው አብረው ለማደር።በዚሁ መሰረት ትላንት ምሽት ላይ አስቻለውና በልሁ ከቤቷ አምጥተዋት ሔዋን በአስቻለው ቤት አስቻለው
አልጋ ላይ ከአስቻለው ገር አድራለች::

አስቻለው መብራት አብርቶ የሔዋንን አስተኛኘት አየት ሲያደርገው አሳዘነችው:: አንድ እግሯን ከጭኖቹ መሀል አስገብታ፤ በግራ እጇ አንገቱን አቅፋ በቀኝ
እጇ ደግሞ ወገቡ ላይ ጥምጥም ብላ ተኝታለች፡፡ ከአንገቱ፡ ቀና ብሎ ለአፍታ ያህል ቁልቁል ሲያያት ቆየና ግንባሯ ላይ ሳም አደረጋት
ምናልባት በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆና የእስቻለው እንቅስቃሴ ተሰምቷት ሳይሆን አይቀርም ሔዋን አይኗን ገለጥ ስታደረግ ሁለቱም ተያዩ

«ነጋ እንዴ አስቹ?» ስትል ጠየከቸው
«እረፍዶ!!»
ሔዋን ከአንገቷ ቀና ብላ ወደ መስኮት አየት ስታደርግ የውጭ ብርሃን የለም:: ዋሽህ' ብላ ተመልሳ ተኛች::
«ለኔ ማለቴ እኮ ነው መንገደኛ አይደለሁ!»
«ህልም እያ'የሁ ነበር አስቹ፣»
«ጥሩ ወይስ መጥፎ?»
«የት እንዳለሁ አይታወቀኝም፣ ግን እናትህ ይመስሉኛል። እፊቴ ቆመው ልጄን ከምታመጭበተ አምጪ! የት ነው የደበቅሽው? ኋላ አንድ ነገር ቢሆን ነገ ከአንቺ ራስ ላይ አልወርድም" ይሉኛል::
«ምን አልሻት ታዲያ? አላት አስቻለው እንደ መሳቅ እያለ፡፡»
ምንም! ዝም ብዬ ሳያቸው ከእንቅልፌ ነቃሁ::
«አትዋሺ! አለና አስቻለው አሁንም በቀልድ ዓይነት «ይኼኔ ልጄን
አምጪ ስትልሽ አልሰጥም የት ነው የደበቅሽው ስትልሽ ልቤ ውስጥ ኋላ ልጁ አንድ ነገር ቢሆን» ስትልሽ ደግሞ የግድ የለዎትም እኔ ጋር የተቀመጠ ነገር
አይበላሽም ብለሻት ይሆናል::» አለና ለራሱ እየሳቀ ሔዋንንም አሳቃት፡፡

አስቻለው ሳቁን ከጨረሰ በኋላ ወደ ቁም ነገር በመመለስ ይኼኔ እናቴ በህይወት ብትኖርልኝማ ኖሮ ብዙ ችግርቼ በቀላሉ ይፈቱ ነበር፡፡ በተለይ አንቺን የመሰለች ምራት በማግኘቷ እየተደሰተች አንቺን በማለቴ ስለተፈጠረብኝ ችግርም
መላ ትፈልግልኝ ነበር፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፤ እኔም እሷም ሳንታደል ቀረንና በልጇ ሀዘን ተቃጥላ ሞተች፡፡» አላት እውነትም በመጥፎ ትዝታ ፊቱን እየከፋው።
«ልጅ ሞቶባቸው ነበር፡፡»
«ያውም የኔ ታላቅ ! እሷንም እኔንም በገንዘብ ይረዳ የነበረ እውሮች ለምን አየህ?» ብለው ገደሉት፡፡ አላት፡፡
«እውሮች!» አለች ሔዋን አባባሉ ግራ ገባ ብሏት።
«ዓይን ቢኖራቸውም "ማስተዋል የጎደላቸው ህሊና ቢሶች፡፡ እስና ያን አሰቃቂ የቀይ ሽብር ዘመን በዓይነ ህሊናወኑ ለአፍታ ያህል ዳሰስ አደረገው::
«እየነጋ ነው ሔዩ፡» አላት ከሃሳቡ መለስ ሲል፡፡
«ትሄድ አስቹ?»
«በቅድሚያ ግን የወጭ በይኝ፡፡» ብሎ ዓይኖቹን ፈዘዝ አድርጎ ሲመለከታት ምላሹን ሰጠች። አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሮቿን በነከንፈሩ ላይ ጣል አደረገቻቸው፡፡ ወሰዳት፡፡ ወስደችው:: ዓይኖቻቸው ተስለመለሙ፡፡ ሰውነታቸው ሞቀ፡፡ ገላቸው ተጣበቀ። ትንፋሻቸው በረከተ። በስሜት ባህር ወስጥ ሰጠሙ፡፡
ምድር ላይ ሆነው ገነትን ለአንድ አፍታ ተመላለሱባት፡፡ ከስሜት ገዞ መልስ እስቻለው ከእልጋ ላይ ወረደ:: ታጠበ፡፡ አበጠረ፡፡
ለባብሶ የመንገድ ሻንጣውን ትከሻው ላይ አነገተና አልጋው ስር ቆሞ ሔዋንን ቁልቁል እየተመለከተ ከአዲስ አበባ ምን ገዝቼልሽ ልምጣ ሔዩ?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ምንም አስቹ!››
«ለምን? ጫማ ልብስ' ወይም ሌላ ነገር ብገዛልሽስ»
«ማን ገዛልኝ ብዬ ልለብሰው አስቹ?» አለችው አልጋው ላይ በክንዷ ደገፍ ብላ ከእንገቷ ቀና በማለት እየተመለከታችው፡፡ አስቻለው የዘነጋው ነገር ነበር፡፡ እንደ አዲስ ትዝ ብሎት ድንገት ቅስሙ ስብር ከለና ለአፍታ ያህል በሀዘን አይን ተመለነታት፡፡
«እንተ ብቻ በሰላም ተመለስ፡፡» አለችው ሔዋን ዓይን ዓይነን እያየች።
«አሜን የኔ ፍቅር» ብሏት ሳም አድርጎ ተሰናበታት፡፡
ሰአቱ ገና ማለዳ ስለነበር ሔዋን ወዲያው አልተነሳችም፡፡ አልጋው ላይ ጋለል ብላ ጣሪያ ጣሪያ እያየች አስተዳደሯን በትዝታ ታየው ጀመር፡፡ ደስ የሚል ሌሊት ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ አስቻለው ቃሉን ማክበሩ አስደስታት:: ለግማሽ ሌሊት ያህል ከንፈሮቻቸው ሳይላቀቁ፤ በመተሻሸት ብዛት በስሜት ሲፈራገጠ ያላደሩትን
ያህል አስቻለህ ለአንዴ እንኳ ወደ ጭኖቿ መሃል ሳያመራ በማደሩ ከልቧ አደነቀችው:: ከመቸውም ጊዜ በላይ በእሱ ላይ ያላት እምነት የፀና ሆነ፡፡ ያ ሌሊት
ሔዋን ሴት እንደመሆኗ ወንድ እንደሚያስፈልጋት በውል የተረዳችበትም ነበር!
ከሆንም አስቻለው ፍስሀ ብቻ!
ሔዋን መልካም የፍቅር ተስፋ የምታይበት አዕምሮዋን ስጋትም ጠቅ ያረገው ነበር፤ ከሁሉም በላይ እህቷ ሸዋዬ በሁለቱ ፍቅር ላይ ያላት መጥፎ አመለካከት፡፡ ከዚያ ቀጥሎ ለቤተሰቦቿ የጻፈችባት ደብዳቤ፡፡ ሁለቱም እንደ ትልቅ የፍቅር እንቅፋት ያሰጓታል፡፡ ያስጨንቋታል። ለመሆኑ አስቻለው የዝውውሩ ጉዳይ ቢቀናውስ! ወደ ሄዴበት ቦታ አብራው ትሄድ ይሆን! በምን ሁኔታ ጠፍታ ወይም በቤተሰቦቿ ፈቃድ የሚታወቅ ነገር የለም። ይህም እንዱ የሀሳቧ ዘርፍ ነበር፡፡

በዚህና በመሳሰሉት የፍቅር ጉዳዮች ዙሪያ ስታወጣ ስታወርድ ሳታውቀው እረፍዶ ኖሯል፥ በግምት ወደ አንድ ሠዓት ተኩል አካባቢ ተጠግቷል። የጠዋት
ፈረቃ ተማሪ ናትና ፈጥና ተነሳች፡፡ የአስቻለውን አልጋ ስምር አድርጋ
አነጣጠፈች፡፡ ታጥባ ፀጉሯን ጎነጎነች በኮመዲኖው ላይ የተቀመጠ የአስቻለውን
ፎቶ ግራፍ ሳም ሳም አድርጋ ቤቱን ቆላልፋ ወጣች፡፡ ከዛም ወደ ቤቷ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አስቻለው ከሾፌሩ ኋላ ሦስት ሰዎችን በሚያስቀምጠው የመጀመሪያ ወንበር ላይ በሁለት ሰዎች መካከል ተቀምጦ ወደ አዲስ አበባ ይጓዛል በጎራ በኩል የመስኮት ጥግ ይዘው ዕድሜያቸው ወደ ሀምሳዎቹ የገባ የሚመስል፤ ነገር ግን በምቾት ኑሮ ፊታቸው ደንቡሽቡሽ ያለ ቀይ መልከ መልካም ሴት ተቀምጠዋል፡፡ የጥቁርና ነጭ
ቡራቡሬ ቀሚስና ባለ ጥለት ነጭ ነጠላ ለብሰዋል። እራሳቸውን
በጥቁር ሻሽ ሽክፍ አድርገው አስረዋል። ከቀኙ በኩል ደግሞ አንዲት ዕድሜዋ ከአስራ ሰባት ዓመት የማይበልጣት ጠይም ልጃገራድ ተቀምጣለች፡፡ ነጣ ያለ ጉርድ ቀሚስ በቀይ ሹራብ ለብሳለች። ስልክክ ያለች የጠይም ቆንጆ ናት። ሦስቱም እየተጨዋወቱ ይጓዛሉ።
👍1
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....ምንትዋብ ማረፊያ ክፍሏ ቆይታ ማታ ላይ ራት ከበላች በኋላ፣ በሁለት ደንገጡሮች ታጅባ ወደ አፄ ፋሲል ቤተመንግሥት አቀናች። ደረጃውን ከወጡ በኋላ፣ ሁለት ያደገደጉ ደጅ አጋፋሪዎች መግቢያው በር ላይ ቆመው ለጥ ብለው እጅ ነሥተው መግቢያው ላይ ባለው በወንዶች የግብር አዳራሽ በኩል እንዲሄዱ መሯቸው።

ምንትዋብ ቆም አለች።

የግብር አዳራሹ ወለል ከፋርስ በመጣ ምንጣፍ አሸብርቋል። በክፍሉ ዙርያ ያሉት ባለመስተዋት መስኮቶች በሐር መጋረጃዎች ተሸፍነዋል ::በፋና ወጊዎች የተለኮሱት በየማዕዘኑ የተቀመጡት ትልልቅ ጧፎች
ክፍሉን አድምቀውታል።

ምንትዋብ ባየችው ሁሉ ተማረከች።

ሴቶቹ ግብር አዳራሽ ስትገባ ተመሳሳይ ድምቀት አይታ ሦስተኛ
ደርብ ላይ ወደሚገኘው የንጉሠ ነገሥቱ መኝታ ክፍል ለመግባት ደረጃ ስትወጣ፣ ደንገጡሮቹ እጅ ነሥተዋት ከኋላዋ ተመለሱ።

ደረጃውን ወጥታ ስትጨርስ፣ አፄ በካፋ ቀን አድርገውት የነበረውን
ዘውዳቸውንና ካባቸውን አውልቀው፣ ማምሻ ክፍል ውስጥ፣ ቀይ ከፋይ የለበሰ ሰፊ ወንበር ላይ ተቀምጠዋል። ከፊት ለፊታቸው ያለ ጠረጴዛ ላይ፣ ጠጅ በብርሌ ተቀምጧል። በክፍሉ ጥግ ጥግ የቆሙ፣ ረጃጅም
መቅረዞች ላይ የተቀመጡት ማሾዎች ለክፍሉ ልዩ ውበት ሰጥተውታል።

አፄ በካፋ፣ ምንትዋብ ስትገባ፣ በፈገግታ ተቀብለዋት፣ ከጎናቸው
ያለ ወንበር ላይ እንድትቀመጥ በእጃቸው አሳይዋት። ስትፈራ ስትቸር ተቀመጠች። ዐይናቸውን ማየት አቃታት።

እሳቸው ግን በእዚያ ምትሐታዊ ውበቷ ዳግም ተማርከው ዐይናቸውን ከእሷ ላይ ማንሳት ተስኗቸዋል። ወዲያው ግን መርበትበቷን አስተውለው፣
“አይዞሽ የኔ ዐይናማ፤ ምንም ሚያስፈራ ነገር የለም እኮ” አሏት፣ እጇን እጃቸው ውስጥ አድርገው።

አቀርቅራ ዝም አለች።

“ያረግሽልኝን ሁሉ መቸም አልረሳውም። ኸኪዳነ ምሕረት ጋር አስታመሽ አዳንሽኝ። የልዥ አዋቂ። ኪዳነ ምሕረት ታክብርሽ።
እንዳው ነገሩን ሁሉ ሳጤነው... እዝጊሃር እንድንገናኝ ፈልጎ ነው እንጂ ኸናንተ ቤት ታምሜ መምጣቴ ተጎድቸ ነበር፤ ኪዳነ ምሕረትና ሩፋኤል እንዳንቺ ባለች ዐይናማ ካሱኝ” አሉ፣ በሠርጋቸው ማግስት ስለሞተችው ሚስታቸው አስበው።

ምንትዋብ እጇን እያፍተለተለች ዝም ብላ አዳመጠቻቸው።
በተናገሩት ነገር ልቧ ተነካ። እኛ እንደዛ በወርቅና በዕንቁ ተንቆጥቁጠው፣ሩቅ ይመስሉ የነበሩት ንጉሠ ነገሥት እንደ እሷው ሰው መሰሏት።

“እስቲ ያነን ሚጥም ድምጥሽን አሰሚኝ፤ ተጫወቺ እስቲ። ኸናንተ
ቤት ሳለሁ ላነጋግርሽ እየፈለግሁ ማን መሆኔ እንዳይታወቅ ብየ ዝም አልሁ። ኸኛ ኸደግ አባትሽ ጋር ስንኳ ሳልጫወት ተመለስሁ” አሏት።

የምትለው ጠፋት። በመጨረሻ፣ ቁስቋም ታክብርልኝ። ለዝኽ
ላበቁኝ ለርሶም፤ እሷው ምላሹን ትስጥዎ” አለቻቸው።
“እኔ ምን ለዝኸ አበቃሻለሁ። ሁለተኛ እንዲ ስትይ እንዳልሰማ።
ሚገባሽ ቦታ ነው የመጣሽ። እኼ ደሞ ቤትሽ ነው፤ ቀስ እያልሽ ሁሉን ትማሪያለሽ። ሚቸግርሽ ነገር ሲኖር ሳትፈሪ ንገሪኝ። ደንገጡሮችሽም አሉ። ለኔም ኸንግዲህ ኻንቺ ሌላ ሚቀርበኝ የለም” አሉና ቀስ ብለው
ተነሥተው፣ ቀኝ እጇን ይዘው፣ መኝታ ክፍል ውስጥ ይዘዋት ሲገቡ፣ በአጎበር የተሸፈነውን ተደራራቢ የእንጨትና የጠፍር አልጋ ስታይ፣ ልቧ ተንተረከከ።

ይሁን እንጂ፣ ልጅነቷ ማክተሙን ብቻ ሳይሆን፣ የዚያን ዕለት
የጀመረችው ግንኙት ሕይወቷ የሚጓዝበትን መንገድ ዳግም እንደጠረገ አላስተዋለችም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም።”

ሰኞ ጠዋት ጥላዬና አብርሃ አለቃ ሔኖክ ቤት ሲደርሱ ባለቤትየዋ
ወጥታ ተቀበለቻቸው። ውስጥ ሲገቡ ሰባዎቹ መጀመሪያ ያሉ፣
የግርማቸው፣ የብልኅነታቸውና የደግነታቸው ድባብ የሚያስተጋባ
አዛውንት መደብ ላይ ተቀምጠው ብራና ላይ የተጻፈ ጸሎት ያነባሉ።
የጥምጥማቸው ንጣት አካባቢውን ደመቅ አድርጎታል።

“የዠመሩትን እስቲጨርሱ ነው። ዐረፍ በሉ” አለቻቸው ባለቤቲቱ፣
ከአለቃ ሔኖክ ፊት ለፊት ያለ አጎዛ ጣል የተደረገበት መደብ በእጄ
እያሳየቻቸው።

ጥላዬ፣ አለቃ ሔኖክን በፈገግታ ከላይ እስከታች ተመለከታቸው።
ቀልቡ ወደዳቸው፣ ከእሳቸው ዘንድ ጉዳዩ እንደሚቃናለት አንዳች ነገር ነገረው። ከእሳቸው ሌላ ማንም ባያስተምረው ፈለገ። ቤቱን ሲቃኝ፣ ጥግ ላይ ካለው የጠፍር አልጋ በስተቀር እምብዛም ዕቃ አይታይበትም።ከአልጋው ግርጌ የቀለም ቀንዶች፣ የቀርከሀ ስንጥሮች፣ ብራናና በዕራፊ
ጨርቅ የተጠቀለሉ ዱቄት መሳይ ነገሮች ተቀምጠዋል። ይህንን
እየተመለከተ ሳለ አለቃ ሔኖክ፣ “አድራችሁ ነው ልጆት?” ሲሏቸው
ከአብርሃ እኩል ብድግ ብሎ ለሰላምታቸው የአክብሮት ዐጸፋ መለሰ።

“ምን ፈልጋችሁ ነው?” በሚል ዓይነት ሲያይዋቸው አብርሃ፣ “እሱ
ኸቋራ ነው የዘለቀ። ሥዕል መማር ፈልጋለሁ ቢለኝ ኸርሶ ዘንድ
ይዠው መጣሁ” አላቸው።

“መልካም... ሥዕል ለመሣል ቅኔ መማር አለብህ። ሞካክረኻል?”
“ወፍታ ጊዮርጊስ የንታ አምሳሉ ዘንድ ሥላሤ አድርሽ... ወዲህ
መጣሁ።”
“ሥዕል ሥለህ ታውቃለህ?” አሉት፣ ትክ ብለው እያዩት። ዞር አሉና፣ ምድጃ ላይ ድስት ጥዳ የነበረችውን ባለቤታቸውን፣ “ወርቄ እስቲ ሚቀመስ ታለ፤ ለዛሬ ዕንግዶቻችን ናቸው እኒኸ ተማሮች” አሏት።

ጥላዬ፣ ለጠየቁት ጥያቄ አዎም የለም አልሣልኩምም ማለት ፈለገና አመነታ። ዐይናቸው እሱ ላይ ተተክሎ ሲቀር፣ “ጥቂት ሞካክሬአለሁ፤ ግና ብራና ላይ ማይዶል” አላቸው።

“ዛዲያ ኸምን ላይ ሣልህ?”
ሊናገር ፈልጎ ዐፈረ። እሳቸው መልስ ፈልገው ተጠባበቁ። ያን
ችምችም ያለና ወተት የመሰለ ጥርሱን ብልጭ አደረገና፣ “ግድግዳ
ላይ” አላቸው።
“ግድግዳ ላይ? ግድግዳ ላይ እኮ ማነም ተነሥቶ አይሥልም።”
እንጀራ በድቁስና ጠላ ይዛ የመጣችው ወርቄ ከት ብላ ሳቀች። ያን ጊዜ ሁሉም፣ አለቃ ሔኖክ ጭምር ሳቁ። ጥላዬ፣ ወርቄ ጠላውን መጀመሪያ
ለአለቃ ሔኖክ ከዚያም ለእሱናኸ ለአብርሃ ቀድታ እስክታስቀምጥ
ጠበቀና፣ “ኸቤታችን ግድግዳ ላይ ነው። በእናቴ ወንፊት ዐመድ
እየነፋሁ፣ በውሃ ለቁጨ ሳበቃ ኸቤታችን ዠርባ ግድግዳ ላይ በእናቴጸ አክርማ እሥላለሁ። አባቴ ሲያዩት ይቆጣሉ። ግድግዳውን መልሰው
በጭቃ ያስመርጉታል” አለ።
ወርቄ እንደገና ከት ብላ ሳቀች፤ ሁሉም አብረዋት ሳቁ። ጥቂት
ቆይታ በድቁስ ከቀረበው እንጀራ ላይ ግማሹን ተቃምሰው መተዋቸውን ተመልክታ ለጠላው ማጣጫ በአነስተኛ ጮጮ ላይ ቆሎ ይዛ መጣች።

አለቃን አዘግናቸው እነጥላዬን፣ “እየቆረጠማችሁ” ብላ አስቀምጣላቸው ሄደችው ።
አለቃ ሔኖክ ከዘገኑት ቆሎ ላይ ቆንጠር አድርገው አፋቸው
አደረጉና፣ “ሥዕል መሣልህ ነው ወይስ ግድግዳ ላይ መሣልህ ኣባትህን ሚያስቆጣቸው?” ሲሉ ጠየቁት።

“ወታደር መሆን አለብህ እያሉኝ... ሥዕል እንድሥል አይፈልጉም።
በቅኔውም ቢሆን እንድገፋ አይፈልጉም። እሳቸው እስታሉ ድረስ አገሬ አልመለስም ብየ ጠፍቸ ወዲህ ዘለቅሁ።”

አለቃ ሔኖክ ራሳቸውን ነቀነቁ፣ መሆን የለበትም በሚል ዓይነት።
“ላባትህ መልክትም ቢሆን ላክባቸው። ያዝናሉ። እናትህም ቢሆኑ በልቅሶ ይሞታሉ። ብዙዎቻችን ለትምርት ብለን ጠፍተን ነው ኸቤት ምንወጣ ግና ኋላ እንመለሳለን። አባትህ ላንተ ሌላ ተመኙ፣ ከንተ ደሞ ሌላ ፈለግህ። ክፋት የለውም። ባባትህ ቂም እንዳትይዝ። ለማንኛውም
👍16