አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

ገመዶ እኩለ ለሊት ላይ ስልኩ ጮኸ….

"ምንድን ነው ነገሩ" በማለት እየተነጫነጨ በተኛበት እጁን ዘረጋና ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አንስቶ ጆሮው ላይ ለጠፈና ‹‹ሄሎ››አለ፡፡

‹‹ኮማንደር መስማት አለብህ ብዬ ነው…ድንገተኛ ነገር ተከስቷል."ምክትሉ ነበር፡፡ ከመኝታው ተነሳና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ፡፡

"…ምንድነው የተፈጠረው?"

"ከእርባታ. ቦታው …ማለቴ የቤተሰቦችህ እርባታ ቦታ፣ከዛ ነው የተደወለልን"አለው…

ከአልጋው ወርዶ ጂንስ ሱሪውን መልበስ ጀምሮ ነበር፡፡ጭንቅላቱ የፍርሀት ቅዝቃዜ ሲፈስ ታወቀው፡፡

"ምን አይነት ድንገተኛ አደጋ ነው?"
‹‹ገና አልተረጋገጠም..ኃይል ወደእዛው ልከናል፡፡›› ያልተቆለፈ ሸሚዙን ከቆለፈ በኋላ ቆሞ ጫማውን አደረገ፡፡

‹‹በቃ ቶሎ አጣርተህ ደውልልኝ…ወደእዛው እሄዳለው፣ይሄው እየወጣሁ ነው… ››ስልኩን ዘጋና ኮቱንና ኮፍያውን አድርጎ ወደ ኮሪደሩ ሮጠ።
/////

አለም በከባድ እንቅልፍ ውስጥ ነበረች፣ ለዚህም ነው የበሯን መንኳኳት በህልሟ መስሎ የተሰማት…።ህልም ውስጥ ነበረች….በመጨረሻ ተከታታይ የሆነው የጥሪ ድምፅ ከእንቅልፏ ቀስቅሷት።

"ተነሺ እና በሩን ክፈቺ."በቁጣ እየጮኸባት ነው፣ ቁጭ አለችና አልጋው ዳር ያለውን መብራት አበራችው… መብራቱ ሲበራ …. ብርሃኑ ዓይኗን አጭበረበራት።

"ገመዶ ነኝ… ክፈቺ?" ጮኸ ። ዝም አለችው፡፡

"በአስር ሰከንድ ውስጥ ካልተነሳህሽ በሩን ሰብረዋለው››

የግድግዳውን ሰዓት ተመለከተች። ከምሽቱ ስምንት ሰዓት ገደማ ነበር።

‹‹ኩማንደሩ ወይ ሰክሯል ወይም አብዷል።››ስትል አሰበች፡፡ ያም ሆነ ይህ አሁን ባለበት ሁኔታ በሯን ልትከፍትለት አልፈለገችም።

"ምን ፈለክ?"

ከእሱ መልስ ስትጠብቅ በራፉ ላይ ፈንጅ የተጣለበት ይመስል ጎጎጎጎ አለና ተከፈተ….ተንደረደረና መኝታ ቤቷ ገባ፡፡በድንጋጤ እየተንቀጠቀጠች አልጋዋ ላይ ቆመች "ምን እየሰራህ ነው?"ብላ ጮኸችበት በቆመችበት አልጋ ልብሱን እየሰበሰበች እርቃኗን ለመሸፈን እየጣረች ነው››

"አንቺን ለማግኘት ነው የመጣሁ ‹‹
ከአልጋው ላይ ጎተተና ወለሉ ላይ አቆማት፣የተጠቀለለችበትን አልጋ ልብስ ከላዬ ላይ ገፎ ወረወረው፣እርቃኗን በፓንት ብቻ ፊት ለፊቱ ቆመች፣ምን ሊያደርጋት እንደሆነ መገመት ሁሉ አልቻለችም፡፡

"ኩማንደር በሬን ገንጥለህ መኝታ ቤቴ ለመግባትህ በቂ ምክንያት እንዳለህ ተስፋ አደርጋለሁ።"

"ማብራሪያ አለኝ።" አለና መሳቢያውን ከፈተ እና ውስጡ ያሉትን ልብሶች ማተረማመስ ጀመረ።

"ንገረኝ ምን እየፈለክ ነው?."አለችና እርቃኗን ወደእሱ ሄዳ ሚያተራምሰውን  የቁምሳጥን በራፍ በዳሌዋ ገፋችና ዘጋችበት ፡፡

"ምን ፈልገህ ነው?"ዳግመኛ ጠየቀችው፡፡
"ልብስ። እንደዚህ እርቃንሽን  መውጣት ካልመረጥሽ በስተቀር  ምትለብሺው ልብስ ያስፈልግሻል››

‹‹ወደየትም አልሄድም››

" ጂንስሽ የት ነው ያለው?›› በ ወፍራም ድምፁ ጠየቀ ። "የትም አልሄድም። ስንት ሰዓት እንደሆነ ታውቃለህ?››

ድንገት ቀና ሲል ከአልጋው አጠገብ ባለው ግድግዳ ልብሷ ተሰቅሎ አየው፡፡ ጂንሱን ከተሰቀለበት ላይ አወረደና ወረወረላት፣ መያዝ ስላልቻለች ወደ ወለሉ ወደቀ።
ከጫማዋቾ ውስጥ አንዱን መረጠና ወደእግሯቾ አቀረበላት፡፡ ዝም ብላ ፈዛ ታየው ጀመር፡፡ "እሺ.. እንዳለብስሽ ትፈልጊያለሽ?"

እሱን ለማስቆጣት ምን እንዳደረገች መገመት አልቻለችም። እርቃኗን እሱ ፊት ቆማ መከራከሩ ስለደከማት ጆንሱን አነሳችና አጠለቀች ፡፡ከላይ ሹራብ ለበሰች….ከኮመዲኖ መሳቢያ ውስጥ አንድ ካልሲ አወጣችና አራግፋ አጠለቀችና ጫማዋን አደረገች፡፡ በመጨረሻም ዞር ብላ አየችው።

"እሺ ይሄው ልብስ ለብሻለሁ …አሁን ምን እየተካሄደ እንደሆነ ንገረኝ ?"

"እየሄድን  እነግርሻለው  ››አለና  እጆቿን  በመያዝ  እየጎተተ  ይዞት  ወጣ  ፡፡በንዴት እየተንቀጠቀጠች ነበር።

‹‹እንዲህ እንድታደርገኝ ማን ነው የፈቀደልህ?››

"አንገትሽን መስበር አለብኝ…..አላደረገውም››በማለት ወደእሷ ተጠጋና ከንፈሯን ሳማት።ያለተቃውሞ ተሳመችለት፡፡ምላሱን ወደ አፏ ውስጥ አስገባ። በዚህ ጊዜ በቁጣ ስሜት መነጨቀችውና እራሷን አላቀቀች፡፡

ኮትዋን ከሳሎን በራፍ አካባቢ ካለው ማንጠልጠያ አነሳችና ያዘች፡፡ ከቤት ይዞት ወጣ " በሩስ?"ብላ ጠየቀችው ።
"የሚጠግን ሰው እልካለሁ።"

"በዚህ ለሊት?"

"በፈጣሪ … በሩን እርሺው..በአካባቢው ቤትሽን በንቃት የሚጠብቁ ፖሊሶች አሉ" ብሎ ጮኸ።

‹‹የሚጠብቁ ነው ሚሰልሉኝ?››

እጇን ጨምድዶ እንደያዛት ስትጠብቀው ወደነበረ ታክሲ ውስጥ ይዞት ገባ፡፡

"በፈጣሪ ገመዶ…ምን እየተፈጠረ ነው……?ነው ወይስ እያሰርከኝ ነው?››

‹‹እያሰርከኝ ..አንቺን……?ምነው ወንጀል ሰርተሸል እንዴ?›› ፡፡

‹‹እና ምንድነው ንገረኛ….?ወደየት እንደምሄድና ለምን እንደምሄድ የማወቅ መብት አለኝ›› ።

"የእርባታ ቦታው እየተቃጠለ ነው."

‹‹የእርባታ ቦታው.?.የነጁኒዬር?››

‹‹አዎ››

‹‹ወይ..ፈረሶችህ ተረፉ?››

ፈረሶቹን ምን ያህል ይወዳቸውና በምን ያህል መጠን ይንከባከባቸው እንደነበረ ስለምታውቅ ነው ቀድማ ስለፈረሶቹ የጠየቀችው፡፡

‹‹አላውቅም…የወደመውንና የተረፈውን ስንደርስ ነው የምናውቀው፡፡››
////
ሲደርሱ እሳቱ ከፈረሶቹ ጋጣ አካባቢ እየተንቀለቀለ ነው…በአንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሚገኘው የእንጨት ፋብሪካው ከአደጋ ውጭ ነው፡፡ቢሆንም በንፋስ ታግዞ ወይም በሆነ ምክንያት እሳቱ እዛ ቢደርስ ከፍተኛ ውድመት እንደሚያስከትል የታወቀ ነው፡፡

እንደደረሱ መኪናዋ ስትቆም ኩማንደሩ ከመኪናው ወረደና ወደእሳቱ አቅጣጫ ተንቀሳቀሰ…አለም ከኋላው ተከተለችው፡፡ከአንዱ የፈረስ ጋጣ ጭስ ሲትጎለጎል ይታያል…አለም ሆዷ ተገለባበጠባት። የእሳት አደጋ መከላከያ ሰራተኞች፣ የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው እሳቱን ለመቆጣጠር እየሞከሩ ነበር።ብዛት ያላቸው የእርባታው ሰራተኞችና የአካባቢው ኑዋሪዎች ቅጠለም አፈርም እየተጠቀሙ እሳቱ እንዳይዛመት ለመቆጣጠር እየተረባረቡ ነው፡፡
አንድ ሰው ወደኩማንደሩ ቀርቦ"በጣም ብዙ ጉዳት ከማድረሱ በፊት ደርሰውበታል" ሲል ነገረው፡፡

‹‹ሰውስ አልተጎዳም?››

‹‹አንድ የተጎዳ ሰው አለ…››የሚል ድምፅ ሰማ፡፡

"ማንው የተጎድቷል?"

‹‹በጣም አሰቃቂ ትዕይንት ነበር።ከፈረስ ተንከባካቢዎች አንዱ ነው… በቂ አየር ወደ ሳምባዋ መሳብ አልቻለችም። ፈረሶችን ለማዳን ሲሯሯት አንድ እግሩም ተሰብሯል››

በዛ ቅፅበት አንድ ፈረስ እየጮኸ ነበር፣ በግልጽ ህመም ላይ እንዳለ ያስታውቃል። አለም እስካሁን ሰምታ የማያውቀው እጅግ አሳቃቂ ድምፅ ነበር የሰማችው። ገመዶ በፍጥነት ወደእዛው አመራ…ከኃላው ተከተለችው….የአቶ ፍሰሀ ቤተሰቦች በጠቅላላ በለሊት ቢጃማቸው በአካባቢው ነበሩ ፡፡መኖሪያ ቤታቸው ከእርባታው ድርጅት ብዙም ሰላማይርቅ እንደሰሙ በእግራቸው ነው ሮጠው ወዲያው ነው የደረሱት፡፡ ሳራ እያለቀሰች ነበር። ፍሰሀ

እራሱን ተቆጣጥሮ በፅናት ቆሞ ይታያል…ጁኒዬር እናቱን አቅፎ ያፅናናል፡፡ ገመዶ ወደ ጎን ገፋቸው እና እሳቱ ጠፍቶ ጭሱ ብቻ ከሚታይበት ጋጣ ውስጥ ገባ ፡፡
48👍4🔥1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

ከኪሊንኩ ጀርባ ያለው የዶ/ር ኤሊያስ  ቢሮ ምናልባት አለም ከዚህ በፊት ካየቻቸው ቢሮዎች ሁሉ የተዝረከረከ ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡

"ዶክተር ኤሊያስ እኔን ለማየት ስለተስማማህ አመሰግናለሁ።"

"ችግር የለም …ዛሬ ብዙም ስራ አልነበረኝም " ከቀጥታ ከጠረጴዛው አጠገብ ያለውን የእንጨት ወንበር ላይ ያሉትን መጽሔቶችን አስነሳና ጠረጴዛ ላይ በማድረግ ለአለም እንድትቀመጥበት አመቻቸላት፡፡

"አንቺን ሳይሽ ብዙም አልተገረምኩም

"አላት በቅንነት ።

"ለምን?"

"ዋና አቃቢ ህጉ ደውሎ አንዳንድ ጥያቄዎችን ልትጠይቂኝ እንደምትፈልጊ ነግሮኝ ነበር።"

"ዛሬ ከከተማ ውጭ ያለ መስሎኝ ነበር."

"አይ ከቀናት በፊት ነበር ሰሞኑን ትመጣለች ቡሎ የነገረኝ ።"

"ገባኝ…ለሊት የእሳት ቃጠሎ ቦታው እንስሳቶችን ለመርዳት ስትሯሯጥ ስለነበርክ…ዛሬ እንዲህ ንቁ ሆነህ ቢሮህ አገኝሀለው ብዬ አላሰብኩም ነበር።"

በመደነቅ‹‹እንዴ እዛ እንደነበርኩ በምን አወቅሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹እኔም እንዳጋጣሚ እዛ ነበርኩ…አሁን ጊዜህን ሳልሻማብህ ቀጥታ ወደጉዳዬ ልግባ …የእናቴ የሰሎሜን ግድያን በተመለከተ መረጃዎችን እየሰበሰብኩ ነው….እባክህ አንተ በአቶ ፍሰሀ የእንስሳት እርባታ ድርጅት ውስጥ የእንስሳት ሀኪም ሆነህ እንደመስራትህ የምታውቀው ነገር ይኖር ይሆን ?" ስትል አሳዛኝ በሆነ የድምፅ ቅላፄ ጠየቀችው፡፡

"በእርግጥ እናትሽን አውቃታለው . እሷ በጣም አስደማሚ ሴት ነበረች. በእሷ ሞት ያላዘነ ሰው የለም ››

"አመሰግናለሁ፣ በዛን ወቅት በአቶ ፍሰሀ የእርባታ ድርጅት ውስጥ የእንስሳቱን ጤንነት ሚከታተሉት አባትህ እንደነበሩ ማወቅ ችያለው፡፡ "

" ልክ ነው …በዛን ወቅት አባቴ ነበር….እሱ ከሞተ በኋላ ግን ስራውን እኔ ተረክቤያለሁ." "አባትህ ስለ ሰሎሜ ግድያ ሁኔታ የሆነ ነገር ነግሮህ ይሆን?››

"በቀዶ ጥገና ቢላዋ መገደሏን በሰማ ጊዜ እንደ ሕፃን ነበር ተንሰቅስቆ ያለቀሰው››

"አባትህ እናቴ የተገደለለችበት መሳሪያ ከየት እንደመጣ አውቋል›?›

"አዎ …ያ አባቴ እንስሳቱን ለማከም የሚጠቀምበት መሳሪያ ነበር፣እናቴ ነበረች የሸለመችው የስሙ የመጀመሪያ ፊደል ተቀርፆበት ነበር ፡፡እንዴት አድርጎ ከቦርሳው እንደወደቀበት ነው ግራ የገባው፡፡››

"እንደዛ አይነት ግድ የለሽነት ከእሱ ባህሪ ጋር አይሄድም አይደል?"

"ትክክል ነሽ….አባዬ ለህክምና እቃዎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያደርግ አይነት ሰው ነው
…በቆዳ በተለበጠ የእንጨት ሣጥን ውስጥ ነበር የሚያስቀምጣቸው…ያ ስለት ከሳጥኑ እንዴት እንደወደቀ ፈጽሞ ማወቅ አልቻለም ነበር, ››

"እናቴ በሞተችበት ቀን አንተ እዚያ ነበርክ?"

"ይህን ቀድመሽ ታውቂያለሽ ብዬ አስባለሁ። አባዬን ለመርዳት ትምህርት ከሌለኝ በስተቀር እዛ እገኝ ነበር …በዛም ቀን  አብሬው ሄጄ ነበር።››

"ገመዶ እዚያ ነበር?"

"በእርግጥ ኩማንደር እዚያም ነበረ።››

"ለሊቱን ሙሉ."

‹‹እሱን እርግጠኛ አይደለሁም…በመሀል አቋርጦ የሄደ ይመስለኛል››

"አባትህ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን የሆነ ቦታ አስቀምጦ ዞር ብሎ ያውቃል?" ኤሊያስ ማሰላሰል ጀመረ … መልስ መስጠት እንደማይፈልግ ነገራት፡፡

‹‹ በዚያ ቀን በዛ አካባቢ ሌላ ማን ነበር?"ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

ለማስታወስ ሲጥር ተመለከተች‹‹‹ጁኒየር፣ ገመዶ፣ ጋሽ ፍሰሀ….እናትሽ….ስርጉት."

‹‹ ማን… ስርጉት ነበረች? ››

‹‹አዎ ነበረች …ከዛ ወደ ቤት መሄድ እንዳለባት ተናገረች እና አካባቢውን ለቃ ሄደች፡፡

‹‹ከግቢው ወጥታ ስትሄድ አይተሃታል….››

‹‹አይ መሄድ አለብኝ ብላ ስታወራ እንጂ ወጥታ ስትሄድ አላየኋትም….›› " ስለ ሊቁ ምን ማለት ይቻላል? እሱ በአካባቢው ነበር?"

‹‹እሱ ሁሌ  በሁሉም ቦታ የሚዞር..በሄድሽበት ቦታ የማታጪው አይነት ንክ ነበር ፣እውነቱን ንገረኝ ካልሺን ግን በዛን ቀን እሱን እዛ ቦታ እንዳየሁት አላስታውስም››

"እርሱን ካላየኸው በሰሎሜ ደም በተሸፈነ ልብሱ በቁጥጥ ስር ሲውል አልተገረምክም?"

‹‹በእርግጥ አልተገረምኩም…. ምን አልባት እኔ ሳላየው ጊቢ ውስጥ ሲዞዞር ከአባዬ ቦርሳ የወደቀውን ቢላዋ እንዳገኘው ገምታለው፣ ከዛ እናትሽን ገድሏታል ብዬ አስባለው.››

‹‹ነገር ግን ከዛ ሁሉ የአባትህ የህክምና መሳሪያዎች መካከል አንድ ቢላዋ ብቻ ሾልኮ መውደቁ ግራ መጋባት ውስጥ አይከትም… ?››

ዝም አላት…..፡፡

ይህ ዶ.ር የሶስቱም ተጠርጣሪዎች ጓደኛ ነው። በዛ ላይ በቋሚነት ለአቶ ፍሰሀ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው ነው፡፡የሚያውቀው ነገር እንኳን ቢኖር በምንም አይነት ተአምር አሳልፎ ሊሰጣቸው እንደማይፈቅድ አወቀች፡፡ከዚህ በላይ ጊዜዋን ማባከን ፋይዳ እንደሌለው ስላመነች ከመቀመጫዋ ተነሳችና አመስግናው ወደ ሁለተኛ ጉዳዮ አመራች፡፡
///
የእርባታ ድርጅት የእንቅስቃሴ አልባ ሆኗል ። የጽዳት ሠራተኞች ከቃጠሎ የተረፈውን ፍርስራሹን እና አመዱን እየሰበሰቡ እና እየጠረጉ በአካባቢው የቆመው መኪና ላይ እየጫኑ ነው። ኩማንደሩ በአካባቢው ወዲህ ወዲያ እየለ የሚሰራውን እየተመለከተ ነው፡፡ አለም ከመኪናዋ ስትወርድ አይቶታል፣ ነገር ግን እሷን ለማናገር ሲሞክር በአካባቢው የነበረው የእሳት አደጋ ተቆጣጣሪ ሰለጠራው ወደእዛ ለመሄድ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ሀሳቡን ቀይሮ ቆሞ ጠበቃት፡፡ ደረሰችበት…ሰላም ይለኛል ብላ ስትጠብቅ

"እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?"ብሎ ጠየቃት፡፡

‹ከሳራ ጋር ሻይ ልጠጣ ነው የመጣሁት።››

በመደነቅ አፍጥጦ ተመለከታ‹‹ከእሷ ጋር ደግሞ ከመቼ ወዲህ ነው ጓደኛ የሆናችሁት?››

“ሃሳብ የእኔ ሳይሆን የእሷ ነበር” አለችው።

"እሺ ተዝናኑ" አለና ፊቱን አዙሮ ሲጠራው ወደ ነበረው ሰውዬ ሄደ፡፡

እሷም ወደማረፊያ ቤቱ ተራመደች..አቶ ፍሰሀ  በቤቱ በረንዳ ላይ ቆሞ ነበር፣ ስትጠጋ ፍርሃቷ እንዳይታይ ለማድረግ ሞክራለች።

"እንዴት ነህ … ጋሽ ፍሰሀ?"

"  ሰዓት  አክባሪነትሽ  የሚደነቅ  ነው…እናትሽም  ልክ  እንደዚህ  ነበረች››አላት፡፡ለምን እንደመጣች እንደሚያውቅ ተረዳች

‹‹አመሰግናለው››አለችው፡፡

‹‹ምንም አይደል››

"ኩማንደሩ እሳቱን ያስነሳውን ሰው  በቁጥጥር ስር እንደሚያውለው  ተስፋ አደርጋለሁ። እኔም ተገቢን ፍትህ እንድታገኙ አስፈላጊውን ሁሉ አደርጋለሁ።"ስትል ቃሏን ሰጠችው፡፡

"አዎ፣ እኔም ተስፋ አደርጋለው… ሁሉንም ነገር ችላ ማለት እችላለሁ። ነገር ግን ያን የመሰለ ተወዳጁን የገመዶን ፈረስ እንዲሞት ያደረገውን ሰው ግን ይቅር አልለውም።ያን ፈረስ በማሳደግና በመንከባከቡ ይሰማው የነበረውን ኩራት እኔ ነበርኩ የማውቀው።"

በዚህ ጊዜ ጁኒዬር ከውስጥ ወጣ…በውብ ፈገግታ ተሞልቶ የሞቀ ሰላምታ ሰጣት፡፡ አለም"ወደ ውስጥ ብገባ ይሻለኛል… እናትህን ብዙ አላስጠብቃት" አለቸው ።
ጁኒየር እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነና "እናቴ የትላንት ማታውን ጥፋቷን ማረም ትፈልጋለች። ግብዣዋን ስለተቀበልሽ በጣም ተደስታ ነበር። አንቺን ለማየት በጉጉት እየጠበቀችሽ ነው።››አላት

‹‹ጥሩ››ብላ ወደ ውስጥ ገባች፡፡
አገልጋይዋ በራፉ ድረስ መጥታ ተቀበለቻት።‹‹ግቢ።››ብላ ወደ ውስጠኛው ክፍል እየመራች ወሰደቻትና ከሳራ ጋር አገናኘቻት፡፡

ከሳራ ጋር ተጨባበጡና ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙ፡፡
አለም የክፍሉን ዙሪያ ገባ እየተመለከተች"እንዴት የሚያምር ክፍል ነው?!"

"ወደድሽው?።"

‹‹በጣም እንጂ…››
43👍7👏2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///

"ምንድነው የነገረችሽ?"

"እኔ ዲቃላ መሆኔን ."

የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።

"እውነት ነው አይደል?"
ጁኒየር እጆቹን ዘረጋና እቅፉ ውስጥ አስገባት… እንባዋ በመጨረሻ የዐይን ሽፋኖቿን ሞልተው ያለከልካይ ፈሰሰ።

"ሰሎሜ ከኮፈሌ ተመልሳ መጣች። ከገመዶ ጋር ለመታረቅ ተዘጋጅታ ነበር።ፍቅራቸውን ለማደስ ተስማምተው ነበር …የመጋባት እድል ሁሉ ነበራቸው…በመሀል ግን ለማንኛችንም ሳትነግረን መልሳ ጠፋች….በኋላ ነው አንቺን ማረገዟን ስላወቀች እንደጠፋች ያወቅነው፡፡››ሲል አስረዳት፡፡

በእፍረት ፊቷን በእጆቿ ሸፈነች።
" ኦ አምላኬ በጣም ቢጠላኝ አይገርምም።››

ጁኒየር እጆቿን ከፊቷ ላይ አንስቶ በቅን ልቦና የሚወዳቸውን ጥቆቁር አይኖችን እየተመለከተ።

"ገመዶ አንቺን አይጠላሽም አሌክስ። ማናችንም ብንሆን አንጠላሽም…ያ ከአመታት በፊት ተጋፍጠን በይቅርታ ያለፍነው ጉዳይ ነው››

በንግግሩ በምሬት ሳቀች።‹‹ለምን አያቴ ሁሌ እኔ ላይ ጥብቅ እንደምትሆን እያሰብኩ እበሳጭ ነበር …በስንት ሰዓት ከቤት እንደወጣው? በስንት ሰዓት እንደተመለስኩ..?ከማን ጋር እንደነበርኩ ከአግባቡ ያለፈ ቁጥጥር ታደርግብኝ ነበር…ምክንያቷ አሁን ነው የገባኝ
…ለካ እናቴን ያጋጠማት ነገር እንዳያጋጥመኝ ፈርታ ነው፡፡አሁን ነው የገባኝ፡››

"ይሄ ከሃያ አምስት አመታት በፊት የሆነ ድርጊት ነው ፣ አሌክስ አሁን ስለዛ ማሰብ አቁሚ "

"አያቴ በእውነት እኔን ለምን እንደማትወደኝ የሚያብራራልኝ ታሪክ ነው… የሰሎሜን ህይወት አበላሽቻዋለሁ…እና ለዛ ፈጽሞ ይቅር ሳትለኝ ነው የሞተችው…. ሰሎሜ ገመዶን አጥታለች …ፍቅራቸው እንዳይሆን ሆኖ ተሰባብሯል … እና ሁሉም የሆነው በእኔ ምክንያት ነው››.

‹‹ኦህ፣በእግዚአብሔር !ተረጋጊ እንጂ!"
አለም ከእቅፉ ወጣችና ወደ መኪናዋ ሮጠች…መኪና ውስጥ በመግባት አስነሳችና አካባቢውን ለቀቀች።

."ምንድነው ነገሩ?" አለም ወደ መኪናዋ አቅጣጫ ስትሮጥ ያያት አቶ ፍሰሀ ጠየቀው።

"ሁለታችሁም እሷን ተዋት" ሳራ ከውስጥ እየወጣች ለባሏ መለሰች፡፡

ጁኒየር ወደ እናቱ ዞረና።

"እማዬ እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ? እንዴት ልጅቷን እንዲህ ትጎጂያታለሽ?"

"ልጎዳት አስቤ አይደለም የነገርኳት፡፡››

"ምን ነግራት ነው?" አቶ ፍሰሀ ጠየቀ ፡፡

ጁኒየር “በእርግጥ ጎድተሻታል። ደግሞ አቅደሽበት ነው ያደረግሽው… ለምን ነገርሻት?"

‹‹ምክንያቱም እሷ ማወቅ ስላለባት። አለምን የምትጎዳት እራሱ አለም ብቻ ነች። ሸቅዠቷን እያሳደደች ነው። የምትፈልጋት አይነት ቅድስት የሆነች እናት በሰሎሜ ውስጥ አልነበረችም። ሰሎሜ ምትባል ድንቅ እናት እንደነበረቻት በማይረባ ጭንቅላቷ ደምድማለች። እናቷ ምን ያህል ተንኮለኛ እና ሀጥያተኛ እንደሆነች ልጅቷ ማወቅ አለባት.. እናቷ ስትማግጥ እሷን ዲቃላ እንዳረገዘቻት የማወቅ መብት አላት››

" አንቺ እኮ ጤነኛ አይደለሽም!" አቶ ፍሰሀ ተበሳጨባት፡፡

አቶ ፍሰሀ በጸጥታ ወደ መኝታ ቤት ገባና ከኋላው በሩን ዘጋው፡፡ሳራ በአልጋዋ ላይ ያሉትን ትራስ ደራርባ ተደግፋ መፅሃፏን እያነበበች ነበር…እሱን ስታይ መፅሀፉን ከደነችና አጠገቧ ያለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠች ።

ወደአልጋው ቀረበና " ላናግርሸ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡

"ስለ ምን?"

‹‹ዛሬ ከሰአት በኋላ ስለተፈጠረው ነገር።››
"ራስ ምታት እየፈለጠኝ ነው…ለእራት ወደታች ያልመጣሁትም ለዛ ነው"

‹‹የሆነ መድሀኒት አልወሰድሺበትም?"

"አዎ ወስጄለሁ…አሁን በመጠኑ እየተሻለኝ ነው ።"የሳራ የራስ ምታት በትዳራቸው ልክ አብሯት የቆየ ህመም ስለሆነ የተለመደ ነው፡፡

በአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠ እና አቀርቅሮ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡

" ምንድነው ፍሰሀ ?አሁንም የሚያሰጋን ችግር አለ እንዴ?››ጠየቀች፡፡

"አይ..ሁሉም ነገር ሰላም ነው።"

"ታዲያ ለምን ታስባለህ…?እግዚአብሔር ይመስገን ብቸኛው የሞተው ፈረስ የገመዶ ነው
።››
አቶ ፍሰሀ ምንም አስተያየት መስጠት አልፈለገም ። ሳራ ጆ ለገመዶ ያላት ስሜት ፈጽሞ አይለወጥም፤በዚህ ጉዳይ ከእሷ ጋር መነጋገር ጥቅም አልባ እንደሆነ እርግጠኛ ነው፡፡ከእሷ ጋር ሊወያይ የመጣው ስስ ስለሆነ ጉዳይ ነው። ቃላቱን በጥንቃቄ ለመምረጥ ትንሽ ጊዜ ወሰደበት.

"ሳራ ዛሬ ከሰአት በኋላ -……" "በጣም ተበሳጭቼ ነበር" አለችው፣ ፡፡

" ተበሳጭተሽ ነበር?" ፍሰሀ ትዕግሥተኛ ሆኖ ጠየቃት፡፡ወደ ድምዳሜው ከመዝለሉ በፊት ከእሷ ወገን ያለውን የታሪኩን ገጽታ መስማት ፍልጓል።

"የአለምን ስሜትስ የጎዳሽ አይመስልሽም…?"

"ዲቃላ መሆኗን ስላወቀች ብቻ አይደለም የተናደደችው….እሷ በተፈጥሮዋም ብስጩ ነች:: "

"እኔ በእሷ ቦታ ብሆን አይገርመኝም… ወላጆቼ የጋብቻ ሰርተፊኬት እንዳላቸው በጭራሽ አጣርቼ አላውቅም.., እና ባይኖራቸውም ምንም አይመስለኝም ነበር.››

" ሁሉም ሰው ለነገሮች ያለው ምላሽ የተለያየ ነው››

‹‹ አለም ግን ስሜታዊነት የሚያጠቃት ወጣት ሴት ነች።"

"እሷ ይሄን ታሪክ ለመቀበል የሚያስችል ጥንካሬ እንዳላት አምናለው."ስትል መለሰችለት

"በእርግጥ የምትይውን ያህል ጥንካሬ እንዳላት እርግጠኛ አይደለሁም።በረንዳ ላይ ቆሜ እያየችኝ እኔን እንኳን ሀሳትሰናበተኝ ነው ገፍትራኝ ሮጣ የሄደችው፡፡››

የሳራ ፈገግታ ተሰበረ። "ስለነገርኳት ትወቅሰኛለህ? ስህተት የሰራው  ይመስልሃል?"ስትል ጠየቀችው፡፡

በዛ ልብን በሚሰረስር የግሏ የሆነ ልዩ እይታ ስታየው፣ ልቡ ቀለጠ። ሁል ጊዜም የዚህ አይነት አስተያየት ስታየው የሚሆነው እንደዚሁ ነው። ፍሰሀ በስሱ ይዳብሳት ጀመር፡፡

‹‹ውዴ ስለነገርሻት አልወቅስሽም። ግን የነገርሽበት መንገድ እንደዚህ ባይሆን ጥሩ ነበር፡፡ እንደዛ ከማድረግሽ በፊት ከጁኒዬር እና ከእኔ ጋር መመካከር ነበረብሽ…በህይወቷ ሙሉ ባታውቀው የሚሻል ታሪክ ነበር፡፡››

"አልስማማም" ስትል ሳራ ተከራከረች።
አቶ ፍሰሀም "እናቷ እና አባቷ አብረው ከተኙ በኃላ አለመጋባታቸው ወይ መጋባታቸው በእሷ ልጅነት ላይ አሁን ምን ለውጥ ያመጣል? ይህ በቡዙ ወጣት ሴቶች ህይወት ላይ የሚያጋጥም በጣም የተለመደ ነገር ነው..››አላት፡፡

"ልጅቷ ስለ ሰሎሜ ያላት አመለካከት ላይ ግን ለውጥ ያመጣል። ››

‹‹እንዴት?››

‹‹ሰሎሜ ልጅቷ የምታስባትን አይነት ቅድስት ሴት አይደለችም…ይሄን ማወቋ የእሷን የግድያ ጉዳይ ለማወቅ የምታደርገውን ልፋትና ጥረት ቆም ብላ እንድታይ ያግዛት ይሆናል….ይልቅ ከአሁን በኃላ ሁላችሁም ከአለም ጋር መገናኘቱን እና መወያየቱን ማቆም አለባችሁ፡፡››

"ለምን?"ግራ ገብቶት ጠየቀው፡፡

"ለምን? ምክንያቱም እሷ እኛን ለማጥፋት እየሞከረች ነው…ለዚህ ነው. እሷን ለመፋለም የወሰንኩ…. ያለኝን ጥይት ነው የተጠቀምኩት….አንተን እና ጁኒየርን ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነበር."

በእውነቱ፣ ፍሰሀ እንደ አለም ያለ በራስ መተማመን የነበራትን ሴትን ለመጋፈጥ ለሣራ ትልቅ ድፍረት እንደሆነ አሰበ። ያደረገችው ስህተት ቢሆንም ሳራ ያደረገችውን ነገር ያደረገችው ቤተሰቧን ልትጠብቅ እንደሆነ ተረድቷታል። የጀግንነት ጥረቷ ከትችት የተሻለ ነገር ይገባዋል ብሎ አሰበ እና ጎንበስ ብሎ ግንባሯን ሳመ።

ለስለስ ባለ ንግግር" የትግል መንፈስሽን አደንቃለሁ… ግን ማናችንም ያንቺን ጥበቃ አንፈልግም ።"አላት፡፡
46👍3
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
ስርጉት እኩለ ለሊት ቢያልፍም ኪችን ውስጥ ስራ እየሰራች ስለነበር አልተኛችም..ድንገት ግን የውጭ በራፍ ሲንጎጎ ስትሰማ እጇ ላይ የነበረውን የሸክላ ሰሀን ለቀቀችውን ወለል ላይ አርፎ ፍርክስክስ ብሎ ተሰበረባት፡፡የበሩ መንኳኳት እንደቀጠለ ነው..ቶሎ ብላ ኪችኑን ለቃ ወጣችና ወደሳሎን ሄደች ...

" በፈጣሪ ማን ነው ?" ጠየቀች፡፡

"ስርጉት… እኔ ነኝ ..ክፈቺ."

የሰማችውን ድምፅ ልታምን አልቻለችም  ….ለማሰብ ጥቂት ሰከንድ እንኳን ሳታቅማማ
ተንደርድራ ወደበሩ ሄደችና ከፈተችው፡፡

በረንዳው ላይ ተገትሯል…ለደቂቃዎች በራፉን አንደያዘች በትኩረት ተመለከተች፣

‹‹በሰላም ነው ጁኒዬር?››

‹‹ሰላም ነው››መለሰላት፡፡

‹‹ግባ …››አለችና ከበራፉ ዞር አለችለት..ሰተት ብሎ ገባ፡፡

"እዚህ ምን እየሰራህ ነው?"

"አንቺ ጋር መጥቼ ነዋ…ክብር ዳኛ ተኝቶ እንደሚሆን እገምታለው››

"አዎ አባዬ በጊዜ ነው የተኛው።››

የቀድሞ ባለቤቷ በዚህ እኩለ ለሊት እሷን ብሎ የሚመጣበት አንድም አሳማኝ ምክንያት ሊመጣላት አልቻለም፡፡ ቢሆንም ግን….ግድ አልነበራትም። እዚህ መገኘቱ በቂ ነበር። አባቷ ካገመሰው ቦድካ በብርጭቆ ቀዳችና ሰጠችው፡፡ተቀበላትና በቆመበት አንዴ ተጎነጨለት፡፡

"ይህ የሌሊቱ የመጀመሪያ መጠጥህ አይደለም አይደል?"

"አይ..አይደለም." ድምፁን ዝቅ አድርጎ መለሰላት ፡፡

"ወደእኔ እንድትመጣ ለወራት ስጠብቅ ነበር ። ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ አሁን ወደእኔ ስትመጣ ደግሞ ለምን የሚል ጥያቄ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ነው፡፡››አለችው፡፡

" ፈልጌ ነበር." አላት፡፡

ለጁኒየር አእምሮ ያ በቂ ምክንያት እንደሆነ ታውቃለች። ሶፋው ላይ ተቀመጠና ጎትቶ ከጎኑ አስቀመጣት።ከበርካታ ደቂቃ ፀጥታ በኋላ " በእርባታ ድርጅቱ ውስጥ ስለተፈጠረው ችግር ሰምቻለሁ" አለችው.

"አሁን ሁሉ ነገር ሰላም ሆኗል….እሳቱ በጊዜው ነው የተደረሰበት…በጣም የከፋ ሊሆን ይችል ነበር."

እያመነታች እጇን እጁ ላይ አሳረፈች፡፡
‹‹አንተ ግን ራስህን ጠብቅ…ንብረታችሁን ለማቃጠል የደፈረ ጠላት በእናንተም ላይ ቀጥታ ጥቃት ከመፈፀም ወደኃላ ላይል ይችላል፡፡››

"አሁንም ለደህንነቴ ትጨነቂያለሽ?"

"ሁልጊዜ።"አለችው፡፡

‹‹ሰሎሜ እንዳንቺ ጣፋጭ ሆኖልኝ አታውቅም። ››

"የደከመህ እና የተቸገርክ ትመስላለህ?።"

"አዎ ደክሞኛል!!።"

ሶፋው ላይ ሙሉ በሙሉ ወጣና ትራሱን ተንተርሶ አረፈ። "በሰሎሜ ግድያ ላይ ያለው ውዥንብር እየበጠበጠን ነው።ሁሉም ነገር እንደ ገሃነም ተስፋ አስቆራጭ ነው።››አላት፡፡ከትራሱ ቀና አለና እሷ ትከሻ ላይ ተንተራሰ"እህ…ጥሩ መዓዛ አለሽ…ይህ ሽታ ናፍቆኝ ነበር. በጣም ንጹህ. ነው፡፡

"ስለዚህ ምርመራ በጣም የሚያስጨንቅህ ምንድን ነው?"

"ምንም የተለየ ነገር የለም። አለም ነች ። እሷ እና እናቴ ዛሬ ተፋጠው ነበር። እናቴ ስለሰሎሜ አንዳንድ መጥፎ ነገሮችን ነገረቻትና በጣም እንድታዝን አደረገቻት… ያ ጥሩ ትእይንት አልነበረም።››

ክንዱ በወገቧ ዙሪያ ላከውና አቀፋት ..እጇን አነሳች እና ጭንቅላቱ ላይ አሳርፋ እንደህፃን ልጅ ታሻሸው ጀመር፡፡

"ዋሻተኋታል እንዴ?"

"የማጣት ፍርሀት የወለደው ውሸት"ጁኒየር ፍላጎት በማጣት አጉተመተመ።

"እናቷ በተገደለችበት ቀን በረንዳ ላይ እንደነበርኩ አልነገርኳትም።ለምን እንደዛ አደረክ ?"

" በተከታታይ ጥያቄዎች እንድታጣድፈኝ አልፈለኩም።አንዳንድ መመለስ የማልችላቸውን ጥያቄዎች ብትጠይቀኝ እንዴት አደርጋለው?›››

‹‹ ጁኒየር ዳግመኛ ችግር ስለፈጠረችብህ ጠላኋት።"

"አለም ሁኔታውን ልትረዳ አትችልም….ያም የእሷ ጥፋት አይደለም.››

ጁኒየር ስለ ሶለሜ ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነገር ተናግሮ ነበር። የቱንም ያህል ብታበሳጨውም ስለእሷ ጠንከር ያለ ቃል ተናግሮ አያውቅም።ስርጉት በሹክሹክታ

‹‹ይህችን የሰሎሜን ልጅ ልክ እንደእናቷ በጣም እጠላታለሁ››ስትል አንሾካሾከች፡፡

"አሁን ስለዛ አታስቢ። ይህ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ አያደርግም" አላት፡

እጁን አነሳና እርጥበታማ ከንፈሯ ላይ አሳርፉ ዳበሳት …ከለበሰችው ጋወን ያፈነገጡ ጡቶቾን ተመለከተ።እጁን ከከንፈሯ አነሳና ጡቷ ላይ አስቀመጠ…

‹‹እንደዚህ ሳደርግ ሁል ጊዜ ደስ ይልሽ ነበር ።››

"አሁንም አድርገው።››

‹‹እውነት? ››

"ጡቷን ወደ አፉ አቀረበችለት…ጎረሰው…. እጁን በጭኖቿ መካከል ሰነቀረው፡፡እርጥበት ያለውን ፀጉር እየዳበሰ ወደውስጥ መጓዙን ቀጠለ … ስሙን እየጠራች አቃሰተች።

‹‹ካልፈለግሽ ይገባኛል››አላት

"አይ" አለች በፍጥነት "እፈልጋለው እባክህ።›››ተማፀነችው፡፡፡

"ስርጉቴ ያንቺ በርህራሄ የበለጸገ ፍቅራዊ እንክብካቤ ዛሬ ማታ ያስፈልገኛል። ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ሁልጊዜም በአንቺ ልተማመንብሽ እችላለሁ።››ሲል ተናዘዘላት፡፡

ጎንበስ አለችና ከንፈሩን ሳመችው፡፡

"ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት እንዴሰማኝ እንደጣርሽ ነው…አይደል እንዴ?" ብሎ ጠየቃት፡፡

"አዎ ።"አለችና አጎንብሳ ተመለከተችው። ልክ እንደ መልአክ ፈገግ አለላት ። እንደዚያ ሲያያት ምንም ልትከለክለው አቅም አይኖራትም በጭራሽ።
///
"ወ/ሪት አለም…ወ.ሪት አለም?አለሽ እንዴ?››

አለም ድክምክም ብላ ተኝታ ነበር። ጥገና የተደረገላት በሯን በተደጋጋሚ ሲንኳኳ ነው ከእንቅልፎ የነቃችው፡፡ ስትነቃ… ደንዛዛ እና ቀዝቃዛ ነበር።ከመተኟቷ በፊት ለረጅም ሰዓት ከማልቀሷ የተነሳ ዓይኖቿ አብጠው ነበር።

"ምን ፈለክ?" ድምጿ ለጩኸት የቀረበ ነበር።

" ክፈቺልኝ እትዬ…መልዕክት አለሽ?።"
እንደምንም ከአልጋው ወረደችና ጋወኗን ለብሳ ወደሳሎን በመሄድ በራፉን ከፈተች፡፡የተከራየችበት አፓርታማ ዘበኛ ነው

"እትዬ ስልክሽ ከአገልግሎት መስጫ ውጭ ነው ይላል?"

"አዎ…ዝግ ነው….ለምን ፈለከኝ?" ግራ በመጋባት ጠየቀችው፡፡

‹‹እኔ አይደለውም…አቶ ግርማ የሚባሉ ሰውዬ መጥተው ነበር›› ደነገጠች‹‹የት ነው..?አሁን አለ?››

‹‹አይ ሄደዋል …መልዕክት ንገርልኝ ብለዋል….ነገ ጥቃት ዝዋይ ስብሰባ ስላለ እንድትገኚ ብለዋል››

‹‹ዝዋይ..?የምን ስብሰባ?››

‹‹አላውቅም እትዬ …ሰውዬው ናቸው ያሉት››

‹‹ማለት ተሳስተህ እንዳይሆን?››

‹‹አይ  ይሄው  ማስታወሻ  ላይ  አስፍሬዋለው…››ብሎ  በተወለጋገደ  ፅሁፍ  የተፃፈውን ማስታወሻ አሳያት፡፡

‹‹እሺ በቃ አመሰግናው››ብላ ሸኘችውና ወደ መኝታ ቤቷ ተመለሰች፡፡ከዛ ስልኳን ፈለግችና አበራችው…ዋናው አቃቢ ህጉ ጋር ደወለች….ስልኩ አይሰራም፡፡፡ስልኳን አስቀመጠችና ጋወኗን አውልቃ ቢጃማ መልበስ ጀመረች፡፡እንደጨረሰች ከእንደገና ስልኳን አነሳችና ደወለች፡፡

"ፖሊስ መምሪያ ነው…ምን እንርዳዎት?."

"እባክህ ኩማንደር ገመዶን ፈልጌ ነበር፡፡"

"እሱ የለም። ሌላ የሚረዳሽ ሰው ጋር እናገናኝሽ?"

"አይ፣ አመሰግናለሁ፣ በቀጥታ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብኝ…ምክትል አቃቢ ህግ አለም ጎበና ነኝ።"

‹‹ክብርት አቃቢ ህግ እንዴት ነሽ….አሁን የት ነሽ?፧"

"እቤቴ ነኝ …ለምን ጠየቅከኝ?"

"ኩማንደር ወደአንቺ እየመጣ ነው….እስከአሁን ይደርሳል››

‹‹ምነው በሰላም…..?››መልሱን ሳይመልስላት በራፏ ሲንኳኳ ሰማች‹‹ እሺ …በል ደህና ሁን…ደርሶል መሰለኝ ››አለችና ስልኩን በመዝጋት ወደሳሎን ሄዳ በራፉን ከፈተችለት፡፡

‹‹እሺ ኩማንደር ?››

‹‹ዞር በይልኝ እንጂ ልግባ።››

‹‹መግባትህ አስፈላጊ ነው?››እያለች በራፉን ለቀቀችለት፡፡
83👍15
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ከሰፍል_ሀያ_አምስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
የዝዋዩን ስብሰባ ተሳትፈው በተመለሱ በማግስት ዋና አቃቢ ህጉና አለም በቢሮቸው ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡

እሱ እጁ ላይ አንድ ደብዳቤ በትኩረት እየተመለከተ ትካዜ ውስጥ ገብቷል …

‹‹ክብሩ አቃቢ ህግ…ምነው ችግር አለ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹ወደስራ ስትመጪ ከተማው ውስጥ የታዘብሽው ነገር የለም?››

‹‹ምንን በተመለከተ…?››

‹‹የምታሳድጃቸውን ሰዎች በተመለከተ፡፡››
‹‹እ..የጁኒዬር ፍሰሀ ምስል የያዘ የምርጫ ቅስቀሳ ፖስተር ከተማውን ሞልቶታል፡፡ገዢውን ፓርቲ ወክሎ ለተወካዬች ምክር ቤት መወዳደሩ እርግጥ ሆኗል….ያንን ነው የታዘብኩት›››

‹‹አዎ…የዚህ ትርጉም ገብቶሻል ብዬ አስባለው….ጠላቶችሽ ከቀን ወደቀን የማይነኩ አይነት ኃያል እየሆኑ ነው፡፡››

"ምንም ሆነ ምንም …እኔ የጀመርኩትን ወደፊት ከመቀጠል አያስቆመኝም››
‹‹አይ የግድ ለማቆም ትገደጂያለሽ…..››

‹‹ለምን ተብሎ››

እጁ ላይ ያለውን ደብዳቤ ወረወረላት፤ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ ተቀበችውና አነበበች..ማመን ነው ያቃታት….ከመቀመጫዋ ተነሳች…ተወራጨች…

‹‹ምንድነው ይሄ…››

‹‹ታላቅ እድል ነው….እንደኦሮሚያ ይህንን እድል ካገኙ ሁለት የህግ ባለሞያዎች መከካል አንዷ አንቺ ነሽ…ቀጣዩን ስድስት ወር ቻይና ሄደሽ ይህንን ስልጠና ትወስጂያለሽ…ከዛ ስትመለሺ እርግጠኛ ነኝ….ወይ እዛው ክልል ዋናው ቢሮ ካለበለዚያም ሌላ ዞን በዋና አቃቢ ህግነት ትመደቢያለሽ››

‹‹እኔ መች ፈለኩና…?በምን መስፈርት ነው እኔ የተመረጥኩት….?››

‹‹እሱን እኔ አላውቅም..››

‹‹አወቅክም አላወቅክም ..ይህ እኔን ከእዚህ ገለል ለማድረግ የተሸረበ ሴራ ነው..ለስድስት ወር ከሀገር ወጣሁ ማለት… እስከዛ ጁኒዬር ምርጫውን አሸንፎ ምክርቤት ይገባል…ስመለስም ወደእዚህ ከተማ ስለማይልኩኝ የእናቴ ገዳይ ነፃ እንደሆነ ይቀጥላል ማለት ነው…ይህን መቀበል አልችልም፡፡››

‹‹መቀበልማ የግድ ነው….በዚህ ስራ ላይ ለመቆየት ያለሽ እድል ከ15ቀን አይበልጥም……እሱም ምን አልባት ነው፡፡ደብዳቤውን አንብበሻል አይደል?ይሄ ደብዳቤ ከደረሰት ቀን አንስቶ እጇት ላይ ያለውን ስራና የመንግስት ንብረት ለተተኪው ሰው አስረክበው ለጉዞው ይዘጋጁ ነው የሚለው፡፡››

በንዴት ተንዘረዘረች‹‹አየህ የሰዎቹን ተንኮል….ይህንን ያቀናጁት አቶ ፍሰሀ እና ገመዶ እናም ዳኛው እንደሆኑ እርግጠኛ ነኝ…በዘዴ እኔን ለማስወገድ የሄዱበትን ርቀት የማይታመን ነው››

‹‹አይ የእነሱ እጅ የለበትም ብዬ ልከራከርሽ አልፈልግም….እንደውም ሁኔታውን በደንብ አንድትረጂ ነው የምፈልገው…የሰዎች አቅምና ኃይል ክልል እና ፌዴራል ድረስ ምን ያህል የተዘረጋ እና ስር የሰደደ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡አንቺ በማትጎጂበት መንገድ ከጀመርሽው መንገድ ዞር ለማድረግ የቀየሱት ጥበብ የተሞላበት ዘዴ ነው፡፡ያ ማለት እኔ እፈራው እንደነበር ቀጥታ አንቺ ላይ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሊያደርሱብሽ ፍላጎቱም ሆነ እቅዱ የላቸውም ማለት ነው….ይሄንን በማወቄ አፎይታ ተሰምቶኛል፡፡››

"አንተም እንድሄድ ነው የምትፈልገው?"

"አዎ፣ ሳስበው ለአንቺም የሚበጅሽ እንደዛ ማድረጉ ነው።" በለሆሳስ መለሰላት፡፡
ዋና አቃቢ ህጉ ለእሷ ከአለቃ ይልቅ እንደ ጓደኛ ነው። ስለዚህ እሷ ደህነንት ያሳስበዋል፡፡ " እንደምንም አንድ ወር በስራዬ ላይ እንድቆይ አድርግ"ተማፀነችው፡፡

" እንደዛማድረግ አልችልም.. አልፈልግም."
‹‹እባክህ››

"አንድ ሳምንት አለሽ…ልክ የዛሬ ሳምንት የቢሮሽን ቁልፍ አስረክበሽ ወደ አዲስ አበባሽ ጉዞ ትጀምሪያለሽ።"

" አታስበው…የመጣሁበትን ከግብ ሳላደርስ ከዚህች ከተማ ንቅንቅ አልልም››

‹‹እንዳዛ ከሆነ ስራሽን ታጪያለሽ››

‹‹ስራውን በስራነቱ እንደማልፈልገው ታውቃለህ….የእናቴን ገዳይ እንዳገኝ ካረዳኝ ስራው ምን ያደርግልኛል?››

‹‹የውጭ እድሉም ይቃጥልብሻል››

‹‹አልፈልገውም …ለሌላ ሰው ስጡት፡፡››

‹‹ይሄንን ስራ ከለቀቅሽ…በራስሽ ብቻሽን ነው የምትቆሚው…የቢሮው እገዛና ጥበቃ አይኖርሽም::እንደአንድ ተራ ግለሰብ እነሱን መጋፈጥ እትችይም….››

‹‹ያንን ስሞክር ነው የማውቀው››

"በእግዚያብሄር ስም …ምን አይነት ግትር ሴት ነሽ?"

‹‹ይህ ግትርነት አይደለም…እዚ ከተማ ስመጣ አሁን እናቴን ገድለዋት ይሆናሉ ብዬ የምጠረጥራቸው ሶስት ሰዎች ነበሩ ..ወደዚህ መጥቼ ምርመራዬን ከጀመርኩ በኃላ ተጠርጣሪዎች ወደአምስት አድገዋል፡፡››

‹‹ጭራሽ ተጠርጣሪዎችሽን ቁጥር እያጠበብሽ መሄድ ሲገባሽ እያንዛዛሽው መጣሽ ማለት ነው…ለመሆኑ እነማን ናቸው የተካተቱበት?››

‹‹የአቶ ፍሰሀ ባለቤት ሳራ እና የጁኒዬር የቀድሞ ባለቤት ስርጉት››

ሲጋራውን ከፓኮው አወጣና ለኮሰ ፣ አንዴ ማገና ጭሱን በአየሩ ላይ በተነው ‹‹እንሱ ደግሞ ለምን ብለው ነው እናትሽን የሚገድሏት?››ሲል ከመገረም ውስጥ ሳይወጣ ጠየቃት፡፡

እንደውም ከወንዶቹ በተሻለ እናቴን ለመግደል በቂ ምክንያት እና ጥላቻ ያላቸው ሴቶቹ ናቸው፡፡ወ.ሮ ሳራ ልጇ ጁኒዬር እናቴን እዳያገባ ስትጥር ነበር ቆየችው....በዚህ ጉዳይ ከአያቴ ጋር ሁሉ እንተጨቃጨቁ በገዛ አንደበቷ ነው የነገረቺኝ፡፡በእሷ እምነት እናቴ በሁሉም መስፈርት ለአንድዬና ብቸኛ ልጇ ሚስት ለመሆን እንደማትመጥን ነው የምታስበው፡፡እና ልጇም ተመሳሳዪን እንዲያስብ ብዙ ጊዜ ሞክራ እንዳልተሳካላት ነግራኛለች..ይታይህ ታዲያ ድንገት እኔን ወልዳ አራስ የሆነችውን እናቴን ሊያገባ እየተዘጋጀ ነው ብለው ሲነግሯት እሷን አስወግዳ ልጇን ነፃ ለማውጣት ብትሞክር ምን ይገርማል…?በሌላ በኩል የዳኛው ልጅ የሆነችው ስርጉት ደግሞ ጁኒዬርን ለአመታት ስታፈቅረው እና የራሷ እንዲሆን ስትመኘው የነበረ ሰው ነው….እሱን የራሷ እንዳታደርገው እንቅፋት የሆነቻት እናቴ ነች..ይባስ ብሎ ከአንድ ዲቃላ ልጇ ጋር ሊያገባት እንደሆነ ስትሰማ ምንድነው የሚሰማት….?ደግሞ እናቴን እንዴት አምርራ ትጠላት እንደነበረና መሞቷን እንደግልግል እንደወሰደችው እዛ ድግስ ላይ
የተገናኘን ቀን ምንም ሳትደብቅ ነግራኛለች፡፡እና በአጠቃላይ ከእናቴ ሞት ይበልጥ ተጠቃሚ የሆነው ማን ነው? ብለን ሰንጠይቅ ለጊዜው ሁለቱ ሴቶች የሚል መልስ ነው ምናገኘው…ሳራም ልጇ የማትፈልጋትን ሴት ከማግባት ተገላገለ..ስርጉትም እናቴ ሞታ ብዙም ሳይቆይ ለአመታት ስታፈቅረው የነበረውን ሰው አሳምና ማግባት ቻለች….ምንም እንኳን ጋብቻው ረጅም እድሜ መቆየት ባይችልም ለጊዜው ግን ተጠቃሚ ነበረች፡፡››
በጥሞና ሲያዳምጣት የቆየው አቃቢ ህግ ጭንቅላቱን እየነቀነቀ‹‹ጥሩ መላ ምት ነው››አላት
፡፡
"በዚህ ጉዳይ እኔን የገረመኝን አንድ ነገር ታውቃለህ? ዳኛው። የእናቴን ግድያ በተመለከተ ተጠርጣሪዎች በጠቅላላ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ከእሱ ጋር ትስስር ያላቸው ናቸው..ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው ትክክለኛውን ፍርድ ሊፈርድ የሚችለው?።"

በማግስቱ የአለም የመጀመሪ ስራ የዋና አቃቢ ህጉን ቢሮ ማንኳኳት ነበር፡፡ ባልተሟሸ የጥዋት ሻካራ ድምፅ፡፡‹‹ይግቡ››አላት፡፡
በራፉን ገፋ አድርጋ ገባች

‹‹የመጀመሪያ ባለጉዳይ አንቺ ትሆኜያለሽ ብዬ አልጠበቅኩም ነበር››
ለቀልዱ ምንም መልስ ለመስጠት ፍላጎት አልነበራትም…ጠረጴዛውን ተጠጋች እና ከቦርሰዋ ውስጥ አንድ ወረቀት አውጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት፡፡ጠቅላላ አቃቢ ህጉ በሁኔታዋ ግራ ተጋብቶ‹‹ምንድነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹ስራ መልቀቂያ ነው››

‹‹ማለት ?አልገባኝም››
44👍6👎1👏1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///
እሱ በራፉን ለመክፈት ሲሄድ አለም ቶሎ ብላ ቦርሳዋ ውስጥ ገባች እና በጣም የሚያምር ውድና ጌጠኛ ብእር አወጣችና ወደቤቱ በራፉ ፊት ለፊት በመወርወር ወደፊት ራመድ ብላ እስኪመለሱ መጠበቅ ጀመረች፡፡

‹‹እ..ሰላም ነው..?ስልክህ አይነሳም፡፡››አቶ ፍሰሀ ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹ውስጥ ቻርጅ ላይ እርጌው አላየሁትም…ግባ››ኩማንደሩ መለሰለት፡፡ ወደውስጥ ሲገባ አለምን ስላያት ነገሩ ገባው፡፡

‹‹እንዴት ነህ አቶ ፍሰሀ?››

‹‹ሰላም ነኝ…አንቺስ?››

‹‹አለሁ..››አላችና ‹‹በሉ እንግዲህ መሄዴ ነው››ስትል አከለችበት፡፡

‹‹ምነው ..እኔ ስመጣ ነው እንዴ ምትሄጂው?››

‹‹አይ መጀመሪያውኑም ለመሄድ ስል ነው የመጣሀው…ጉዳዬን ጨርሼለው..ተራውን ለአንተ ልልቀቅ፡፡››አለችና ሁለቱንም ተሰናብታ ወጣች፡፡

ገመዶ እና አቶ ፍሰሀን አስከትሎ ወደውስጥ ለመግባት ሲራመድ በራፉ ጋር ሲደርሱ አቶ ፍሰሀ ጎንበስ አለና አይኑ የገባውን ብዕር አነሳ፡፡

‹‹ይሄን የመሰለ ብዕር ትጥላልህ እንዴ?››ብሎ ወደ ኩማንደሩ ዘረጋለት፡፡ኩማንደሩ ተቀብሎ አገላብጦ ተመለከተውና‹‹ወይ የእኔ አይደለም…የአለም መሰለኝ›››አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለላት፡፡

‹‹ሄሎ››

‹‹ ምነው ከአሁኑ ናፈቅኩህ እንዴ?››
‹‹ባክሽ ሌላ ቦታ ጥዬዋለው ብለሽ እንዳትፈልጊ ነው…አንድ ብዕር ጥለሽ ሄደሻል..ካልራቅሽ ተመለሺና ውሰጂው››

‹‹ወይ  እንዴት  ጣልኩት…?ለማንኛውም  በጣም  ከምወደው  ሰው  የተሰጠኝ  ስጦታ ነው…ከኪስህ እንዳይወጣ …ስንናኝ ትሰጠኛለህ››አለቸው፡፡

‹‹እሺ ቻው››አለና ስልኩን በመዝጋት ብእሩን ደረት ኪሱ ውስጥ ሻጠውና ከአቶ ፍሰሀ ጋር ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ….

‹‹ቢራ ልክፈትልህ››

‹‹በጣም ደስ ይለኛል››

ለሁለቱም ቢራ ከፈተና ፊት ለፊት ተቀመጠ፡፡

‹‹መጥፎ ሰዓት ነው እንዴ የመጣሁት?››አቶ ፍሰሐ ጠየቀ፡፡

‹‹አይ እንደውም በተቃራኒው ጥሩ ሰዓት ላይ ነው የመጣሀው..በጣም አደጋ ላይ ነን››

‹‹ማለት››

‹‹ይህቺ ልጅ ከጠበቅኳት በላይ አደገኛ ነች…ሳታጠፋን አርፋ አትቀመጥም….››

‹‹ማለት….አንተ እንዲህ ካልክ ነገሮች ከባድ ናቸው ማለት ነው››

‹‹አዎ…ስለእያንንድ  የሶሌ  ኢንተርፕራይዝ  የአክሲዬን  ድርሻ…ማን  ስንት  ፐርሰንት እንዳለው…አክሲዬኑ መቼ እንዳገኘነው….ዝርዝር መረጀ አላት፡፡››
አቶ ፍሰሀ ልብ ምቱ በደቂቃ ውስጥ ሲጨምር ታወቀው….

‹‹ምን እያልከኝ ነው?››

‹‹አዎ….የእናቴን ሞት ተከትሎ የአንዳችሁ አክሲዬን ተቀንሶ ለሌሎቻችሁ የተጨመረው ለምንድነው ብላ ጠየቀችኝ…?፡፡››

‹‹ይሄ እኮ ወደእውነት እየቀረበች መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡››

‹‹አዎ…አንድ ውሳኔ መወሰን አለብን፡፡››
አቶ ፍሰሀ ወዲያው ስልኩን አወጣ…መጀመሪያ ዳኛ ዋልልኝ ጋር ደወል…አሁኑኑ ወደቤት እንዲመጣ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ መልሶ ልጁ ጁኒዬር ጋር ደወለ..ቤት እንደሆነ ነገረው…ሳይወጣ እንዲጠብቀው ነግሮ ዘጋውና‹‹በል ተነስ እንሂድ….አሁኑኑ ተነጋግረን አንድ ነገር ማድረግ አለብን፡፡››
///
ከምሽቱ አራት ሰዓት አራቱ ሰዎች ምድር ቤት በሚገኘው የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ፊት ለፊት ተፋጠዋል…በጠረጴዛው መሀከል ሙሉ የውስኪ ጠርሙስ ሲኖር በመሀከላቸው ግማሽ ድረስ የተሞላ ብርጭቆ አለ….

‹‹እኔ  ከመጀመሪያውም  ነግሬችሁ  ነበር..ይህቺን  ሴት  አንድ  ነገር  አድርጓት  ስላችሁ ነበር››ዳኛው በንዴት ደነፉ፡፡

‹‹አሁን ያለፈውን ገር እያነሳን ልንወቃቀስ አይደለም የተገናኘው…አሁን እንዴት አድርገን እናሳቁማት የሚለው ነው ወሳኙ ነገር፡፡››

‹‹ለምን ሁችንም ባለንበት አግኝተናት ይሄንን ጉዳይ እንድታቆም ለመጨረሻ ጊዜ አናሳጠነቅቃትም››አለ ጁኒዬር፡፡

‹‹ትቀልዳለህ እንዴ….መቼስ ልጅቷን ግትርነት ከአንተ በላይ የሚያውቅ ያለ አይመስለኝም፡፡ እኔ በበክሌ እዚህ እግሯ ከረገጠበት ቀን አንስቶ በሰላምም በማስፈራራትም ይህንን ጉዳይ እንዳታቆም ያልጠየቅኳት ቀን የለም…አንድም ቀን ሽብርክ ስትል አልሰማዋትም…ዛሬም የነገረችኝ ጉዳዩን ከማቆም መሞትን እንደምትመርጥ ነው፡፡››ሲል አስተያየቱን ያቀረበው ኩማንደሩ ነበር፡፡

‹‹እሱማ ትክክል ነህ …እኔም ያልሞከርኩበት ቀን የለም…›አለ ጁኒዬር፡፡

‹‹አዎ…ይሄ ጉዳይ አይሰራም፡፡››
ዳኛው ትእግስት አልባ በሆነ ንግግራቸው‹‹በቃ በንግግር ማስቆሙ ካልሰራ …አስወግዷታ

…መቼስ ይሄንን ስታደርጉ የመጀመሪያችሁ አይደለም››አለ ፡፡

በገመዶና በጂኒዬር ላይ የተከሰተው ድንጋጤ የተለየ ነበር…..እርስ በእርስ ተያዩ….ከዛ ሁለቱም በእኩል ጊዜ ወደአቶ ፍሰሀ ዞሩ….አቶ ፍሰሀ አይናቸው ተጉረጥርጧል…ለመናገር እየፈለጉ እየተናነቃቸው ነው፡፡ከአንደበታቸው ቃል ማውጣት የከበዳቸው መሆኑን ያስታውቃል…ከዛ እንደምንም አሉና መናገር ጀመሩ፡፡

‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው…ለሁላችሁም….እዚህች ልጅ ላይ የመግደል ሀሳብ አይደለም አንዲት ፀጉሯን ለመንቀል ብታስቡ ቀጥታ ፀባችሁ ከእኔ ጋር ነው፡፡ማንም እጣቱን በእሷ ላይ ሊያነሳ አይችልም፡፡››

ዳኛው አይናቸውን አጉረጠረጡ‹‹ለምን ተብሎ..ለአንድ ዲቃላ ልጅ ሲባል የእኛ ህይወት መመሰቃቀል አለበት፡፡.እናንተ ማድረግ ካልፈለጋችሁ እኔ አደርገዋለው፡፡››

አቶ ፍሰሀ ልክ እንደጎረምሳ ከተቀመጡበት ተስፈንጥረው ተነሳና ከወገቡ ያለውን ሽጉጥ መዞ ሽማግሌው ዳኛ መላጣ ጭንቅላት ላይ ደቀነው፡፡

ገመዶና ጁኒዬር በርግገው ከተቀመጡበት ተነሱ‹‹እንዴ አባዬ ….!ምን እያደረክ ነው?››

‹‹አንተ ፈርሳም ሽማግሌ….ከዛሬ ጀምሮ እንደውም ለልጅቷ ጠባቂ ቀጥረህ እንቅፋት እንኳን እንዳይነካት ብታስጠብቃት ይሻልሀል….በማንም ሆነ በማን አንድ ነገር ገጠማት ሲባል ብሰማ ይሄንን ምላጭ በአንተ ጭንቅላት ላይ ለመሳብ ለሰከንድ እንኳን አላቅማማም፡፡››

‹‹ጋሼ በቃ…..ወደመቀመጫህ ተመለስ..ተረጋጋ…››አለ ገመዶ፡፡

አቶ ፍሰሀ የደቀነውን ሽጉጥ መልሶ ወደ ወገብ ሻጠው እና መደመቀመጫው ተመለሰ

…..ሁሉም በፀጥታ ማሰላሰል ውስጥ ገባ…ገመዶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደመስኮቱ ተጠግቶ ሲጋራውን ለኮሰና እያጬሰ ማሰብ ጀመረ፡፡ሲጋራውን እንደጨረሰ ወደመቀመጫው ተመለሰና ከውስኪው አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨ በኃላ ‹‹እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ››ሲል የሁሉንም ቀልብ ሳበ፡፡

‹‹ምንድነው እንስማው››ሁሉም ተነቃቁና ኩማንደሩ የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ሆነ፡፡

‹‹የሚቀጥሉት ስድስት ወራት ወሳኝ ጊዜዎች ናቸው..ማለቴ ከጂኒዬር የምርጫ ጉዳይ ጋር ተያይዞ ይሄ የክስ ጉዳይ ወደፊት ከገፋና እንዲህ አይነት ወሬዎች ህዝቡና ሚዲያው ጆሮ መግባት ከጀመሩ ነገሮች ድብልቅልቃቸው ነው ሚወጣው፡፡እንደእኔ ለተወሰነ ጊዜ ወደሆነ ቦት ዞር አድርገን ብናስቀምጣት፡፡››

‹‹ዞር አድርገን ስትል….?ግልፅ አድርገው?፡፡››

‹‹በቃ ከሰው እያታ ውጭ የሆነ ቤት ወሰድን እዛ ሁሉ ነገር እንዲሞላላት እድርገን ግን ደግሞ ከማንም የማትገናኝበትን ሁኔታ ብናመቻች ጥሩ ይመስለኛል፡፡››

‹‹ጥሩ…እኔም እስከዛ ጡረታ ወጣና ከዚህ ከተማ ዞር እላለሁ››በማለት ዳኛው ቅድሚያ ተስማማ፡፡

አቶ ፍሰሀ ‹‹ጥሩ ሀሳብ ይመስላል….እንደውም ይርጋ ጨፌ የቡና እርሻችን ያለበት ቦታ ብንወስዳት ማንም ሊያገኛት አይችልም……እዛ ሁሉን ነገር እናሟላላታለን…እኛም በየተራ እየሄድን እንጠይቃታለን..መጥፎ ሰዎች እንዳልሆን እንድታምን እናደርጋለን፡፡
51👍8😱2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ



///
‹‹በተሰቀለው…አሁን ምንድነው የምናደርገው?››

‹‹አላውቅም…ለአባትህ  ደውልለትና  በአስቸኳይ  ይምጣ…እዛ  ይርጋጨፌ  ምንም አያደርግም››

‹‹ደውዬለታለው… እየመጣነው››ሲል መለሰ ጁኑየር

‹‹ዳኛውም እየደወለልኝ ነበር››

‹‹እሱን ተወው ባክህ..ከአሁኑ በልብ ድካም እስከወዲያኛው ማንቀላፋቱ አይቀርም..ለማንኛውም እዚህ ምንም አንሰራም ..ወደቤት እንሄድ›› ተባባሉና ሁለቱም ወደ መኪናቸው በመግባት ተከታትለው ወደእነ ጁኒዬር ቤት መጓዝ ጀመሩ፡፡

በማግስቱ ጥዋት  አንድ ሰዓት በሶሌ ኢንተርፕራይዝ ህንፃ የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እየተወያዩ ነው፡፡

‹‹ያሰማራናቸውን ሰዎች ምንም ፍንጭ አላገኙም››አቶ ፍሰሀ ናቸው ጠያቂው፡፡

‹‹እዚህ  ከተማ  ውስጥ  ያለች  አይመስለኝም….እያንዳንዱን  ሆቴል  እና  ፔንሲዬን አሳስሼለው….የለችም፡፡››ገመዶ መለሰ፡፡

‹‹ወደ አዲስአበባ ተመልሳ ሊሆን ይችላል?››

‹‹ወደዛም ሰው ልኬለው…..እንግዲህ የሚሆነውን እናያለን፡፡››

‹‹ጥሩ …ዩቲዬብ ባለቤትስ ማግኘት ችለናል…..?››አቶ ፍሰሀ ናቸው ሌላ ጥያቄ የጠየቁት፡፡

‹‹አዎ አናግሬው ነበር…የፈለገውን ያህል ብር እንደምንከፍለውና ቀጣዩን ስራ እንዳይለቅ ጠይቄው ነበር…››

‹‹እና?››

‹‹እናማ…ቀጣዩን አልሰጠችኝም…እራሷ ቀርፃ ነው የምትልክልኝ ….››የሚል መልስ ነው የሰጠኝ፡፡

እንደዛ ከሆነ እኮ አሪፍ ነው…ለልጁ ደህና ብር ስጡትና ቀጣዩን ታሪክ ልታስረክበው ስትቀጥረው ይደውልልን እና እናገኛታለን ማለት ነው››ዳኛው በአዲስ ተስፋ ተሞልተው ተናገሩት፡፡

ኩማንደር ፈገግ አለና‹‹ክቡር ዳኛ….ይሄንን ማሰብ የሚያቅተኝ ይመስልሀል?››

‹‹አይ በፍጹም እንደዛ አላልኩም….ውይይት ላይ ስለሆን የተሰማኝን በግልፅ ነው የተናገርኩት››

‹‹ጥሩ…ለልጁ ይሄንን ሀሳብ አቅርቤለት ነበር….ወዲያው ይሄንን መልእክት አሳየኝ፡፡››

‹‹ምንድነው?››

በዩቲዬብ የተለቀቀውን የወንጀል ታሪካችሁን መንደርደሪያ ስትሰሙ መጀመሪያ ምታደርጉት ወደእዚህ ዩቲዩበሩ ልጅ ጋር ሄዳችሁ በገንዘብም በማስፈራራትም ቀጣዩን እንዳይለቀውና በእሱ አማካይነት እኔን ለመያዝ እንደምትሞክሩ አውቃለው….ለዛም ነው ቀድሜ ይሄንን መልዕክት ልጁ ጋር የተውኩት፡፡አንደኛ ከአሁን በኃላ ቀጥታ ልጁን አላገኘውም .. የተቀረፀውን በሌላ መንገድ ነው ምልክለት፡፡ሁለተኛ ልጅን የምታቆሙት ከሆነ እየተቆራረጠ በአምስት ክፍል ይለቀቅ የነበረውን ለሌላ ዩቲዬበር አንዴ ሰጥቼው በአንዴ እንዲለቀቅና ነገሮች ፍርጥርጥ እንዲሉ አደርጋለው ….ያ ማለት ደግሞ ለማሰቢያ እና የተሻለውን መንገድ መምረጫ ጊዜ ያሳጣችኋላ..እንግዲህ ምርጫው የእናንተ ነው፡፡››ይላል፡፡

‹‹ምን አይነት ጉድ ልጅ ነች?››አቶ ፍሰሀ ነው የተናገረው፡፡

‹‹ብዬችሁ  ነበር..አልሰማ  ብላችሁ  ሁላችንንም  መቀመቅ  ውስጥ  ከተታችሁኝ….በጊዜ ትወገድ ብያችሁ ነበር፡፡››ዳኛው ተወራጩ፡፡

‹‹አንተ  ቀበተት  ሽማግሌ…በዚህ  እድሜህ  አንድ  ፍሬ  ልጅ  ትገደል  ስትል  ትንሽ አይቀፍህም?››አቶ ፍሰሀ በንዴት መለሰ፡፡

‹‹አሁንማ እንድትገደል ብንስማማስ የት እናገኛታለን?በዚህ ሁሉ እድሜዬ አንተንና ኩማንደሩን በእንደዚህ አይነት ጫወታ የበለጠች ብቸኛዋ ሴት እሷ ብቻ ነች፡፡በጣም ብጠላትም በጣም የምትደነቅ ጀግና የሆነች ልጅ ነች››ሲል ዳኛው ተናገረ፡፡

በዚህ ሰዓት ድንገት የኩማንደሩ ስልክ ጠራ ..ከኪሱ አወጣና አየው…..የማያውቀው ቁጥር ነው፡፡አነሳው‹‹ውዴ በጣም ናፍቀኸኛል››
በስልኩ በእግር በፈረስ የሚፈልጋትን የአለም ድምፅ እየሰማ መሆኑን ማመን አልቻለም

‹‹አንቺ…የትነሽ ያለሽው?››

‹‹ቅርብህ ነኝ….ጁኒዬርም አብሮህ ነው አይደል?››

‹‹ምን እያወራሽ ነው?››

‹‹ሁለችሁም ናፍቃችሁኛል?››

‹‹ቀለድሽብን ማለት ነው?››

‹‹አይደለም…መቼስ ሁለታችሁንም እንደምወዳችሁ አትጠራጠሩም አይደል..?ልክ እንደእናቴ… እኔም አፈቅራኋላው፡፡››
ሁሉም አፍጥጠው ይመለከቱት ነበር‹‹እና ምንድነው የምትፈልጊው?፡፡››

‹‹ምፈልገውንማ መጀመሪያ ከተገናኘንበት ቀን አንስቶ መች ደብቄችሁ አውቃለው››

‹‹እና አሁን ምን ይሁን ነው የምትይው?››

‹‹ምንም ….እኔ አሁን እየፈለኩት ስላላው ፍትህ ወይም በቀል ላወራችሁ አይደለም የደወልኩት ..ድምፃችሁን ልሰማ ነው..እባክህ ስልኩን ለጁኒዬር ትሰጠዋለህ፣በጣም ነፍቆኛል…››

‹‹ገደል ግቢ››አለና ስልኩን ጠረቀመው፡፡
‹‹ምንድነው ..ስልኩን ለምን ዘጋህባት?››ጁኒዬር በንዴት ጠየቀው፡፡

‹‹እሷ  ኮመዲ  እየሰራችብን  ነው..እንደናፈቅካት  ተናግራ  ካንተ  እንዳገናኛት  ነው የምትፈልገው››

‹‹ታዲያ ለምን ሳታገኛኘን?››

‹‹ምነው ?አንተም ናፍቃሀለች እንዴ?››

‹‹ተረጋጉ…ሁላችም ወደመቀመጫችሁ ተመለሱ››አቶ ፍሰሀ በመሀከል ጣልቃ ገብተው ሁሉም ወደቀልባቸው እንዲመለሱ አደረጉ፡፡

‹‹ልጆች አይታያችሁም እንዴ..?ይሄ እኮ የበቀሏአንዱ አካል ነው፡፡››

‹‹ማለት..?››ገመዶም ሆነ ጁኒዬር በአንድነት አቶ ፍሰሀ ላይ አፈጠጡ፡፡

‹‹በሁለታችሁ መካከል ቅሬታ በመፍጠር ኃይላችንን ለመበታተን እየጣረች ነው….›› ጁኒዬር ባለማመን ‹‹እንደዛ አስባ ይመስልሀል?፡፡››ሲል በጥርጣሬ ጠየቀ፡፡
‹‹ታዲያ ያንተን ስልክ እያወቀች ለምን ብላ ነው ለገመዶ ደውላ ከጁኒዬር ጋር አገናኘኝ ናፍቆኝ ነው የምትለው?››
‹‹አባዬ እውነትህን ነው….››
///
በተሰጣቸው ሶስት ቀን ውስጥ እሷን አድነው መያዝ አልቻሉም…እሷንም ቀጣዩን ክፍል በተመሳሳይ በዩቲዩብ ገፅ እንዳትለቅ ማድረግ አልቻሉም…ይሄ ሁለተኛው ግን ከመጀመሪያው በበለጠ ጫና ውስጥ ከተታቸው፡፡የከተማው የገዢው ፓርቲ ፅህፈት ቤትም ጁኒዬርን አስጠርቶ በሶሻል ሚዲያው ስለሚዘዋወረው ነገር ማብራሪያ እንዲያቀርብና በአፋጣኝ እየተሰነዘረበት ካለው ክስ ራሱ ነፃ እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው፡፡

‹‹አባዬ..ይህ ምርጫ ለምን አይቀርብኝም?››

‹‹ለምን እንደዛ አልክ?››

‹‹የፓርቲው ሰዎች እኮ ቁም ስቅሌን እያሳዩኝ ነው፡፡በአንድ ሳምንት ውስጥ በእኔና በቤተሰቦቼ ላይ እየተነዛ ያለውን ሀሚት ማጥራት ካልቻልኩ በእኔ ጉዳይ ላይ አቋም እንደሚወስዱ ነግረውኛል››

‹‹ምን አይነት አቋም››

‹‹ይመስለኛል..እጩ መቀየር የሚችሉት እስከዚህ ወር መጨረሻ ድረስ ነው፡፡እዚህ ከተማ ላይ በተቃዋሚዎች መሸነፍ አይፈልጉም ..ስለዚህ በሌላ እጩ ሊተኩኝ እያሰቡ ይመስለኛል፡፡››

‹‹ወይ ነዶ..ያን ሁሉ ብር ከስክሰን እንደዚህ ጉድ እንሁን…የክልል ወዳጆቻችንም ለእኔ ደጋግመው እየደወሉልኝ ነው፡፡ልጅቷን መያዝ ካልቻላችሁ እኛ እናግዛችሁ እያሉ ነው፡፡››

‹‹እንዴት አድርገው ነው የሚያግዙን››ጁኒዬር ጠየቀ፡፡

‹‹በአካባቢው ያሉትን የከተማ የፀጥታ አካላት በማነጋገር ፍላጋው ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ ነዋ››

‹‹ታዲያ አሪፍ እድል አይደል?››

‹‹አሪፍ እድል ነው..ግን ደግሞ እገዛቸውን አልተቀበልኩም››

‹‹ለምን?››

‹‹ምክንያቱም እሷን በማደኑ ላይ የመንግስት የፀጥታ አካላት ከገቡበት ድንገት ባልታሰበ ሁኔታ ልትጎዳ ትችላለች…ያንን ሪስክ መውሰድ አልችልም››

‹‹አባዬ..እዚህች ልጅ ላይ የምታሳየው የርህራሄ ስሜት ከእለት ወደእለት እያስደመመኝ ነው፡፡የተለየ ምክንያት አለህ እንዴ?››
51👍7😁1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
እሷ እንደጠረጠረችው…ልክ ግቢዋን ከፍታ እንደገባች በተጠንቀቅ ሲጠብቃት የነበረው ኩማንደር ያስቀመጠው ሰው ወዲያው ነበር ያያት…ስልኩን አንስቶ ኩማንደሩ ጋር ለመደወል ያባከነው ደቂቃ አልነበረም….

ኩማንደሩ ስልኩ ሲደወልለት ዳኛው ቤት ቁጭ ብሎ ማድረግ ስለሚገባቸው አንዳንድ ነገሮች እየተወያዩ ነበር….

‹‹በቃ ታክሲ ያዝና ተከታተላት..ከእይታህ እንዳትሰወር…ያለህበት ድረስ እመጣለው››የሚል ትዕዛዝ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ ለዳኛው አለም እንደተገኘች ሲነግራቸው ዳግመኛ እንደተወለዱ አይነት እፎይታ ነው የተሰማቸው…

‹‹.እንዲከተሏት አድርጌያለው…አሁን መሄድ አለብኝ….. ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡

‹‹ለምን ሪስክ ትወስዳለህ..?ወዲያው እንዲይዞት ማድረግ ነበረብህ››ሲሉ አካሄዱ ላይ ያላቸውን ተቃውሟ አሰሙ፡፡

‹‹ይዘናትስ….?ምንም የሰራችው ወንጀል የለም እኮ…ዝም ብለን አንጠልጥለን ልናስራት አንችልም››

‹‹እስከዛሬ የምታስሯቸውን ሰዎች ሁሉ ወንጀል ሰርተው ነው?››ዳኛው ስትሰሩ የኖራችሁትን ማላውቅ መሰላችሁ የሚል ቃና ባለው ንግግር ታቃወሙ፡፡
‹‹ልጅቷ እኮ የዞኑ ምክትል አቃቢ ህግ የነበረች የህግ ባለሞያ ነች….ሌላ ሰው ላይ የምናደርገውን ሁሉ እሷ ላይ በቀላሉ ማድረግ አንችልም…በዛ ላይ መከተላችን…የትነው የምትሄደው…?አጋዥ አላት ወይስ ብቻዋን ነች?››የሚለውን ለማጥናት ይረዳናል….ምን
አልባት ከሌሎች ጠላቶቻችን ጋር ህብረት ፈጥራ የምትንቀሳቀስ ከሆነም እሷን ብቻ ነጥለን መያዝ ከምንም አያተርፈንም…..››

‹‹ጥሩ አስበሀል ..እንግዲያው እኔም አብሬህ መሆን ፈልጋለው….››

‹‹አረ በዚህ ምሽት ይቅርብህ…ባይሆን ሁኔታውን በየጊዜው እየደወልኩ አሳውቅሀለው…››

‹‹አረ እኔም ከእናንት ጋር እሄዳለው››

ፎቅ ላይ ሆና ንግግሯቸውን ስታዳምጥ የነበረችው ስርጉት የአለምን መገኘት ዜና ስትሰማ በደስታ ጃኬቷን ደርባ አምርራ የምትጠላትን ሴት መያዝ በቀጥታ በአይኗ ለመከታተል ዝግጁ ሆና ወደእነሱ ስትመጣ ተመለከተ…ብዙ ቢከራከራቸውም ሁለቱም ለመቅረት ፍላጎት ስላላሳዩ ምን አገባኝ በሚል መንፈስ አብረውት እንዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡በኩማንደሩ ሹፌርነት አባትና ልጅ ከኋላ ሆነው አለምን ለመከታል ወጡ ..አለምን የሚከታተላትን ታክሲ አዲሱ መነኸሪያ ካለፈ በኃላ ነበር የደረሱበት…ከዛ የአለምን መኪና ካሳያቸው በኃላ እሱ እንዲመለስ ነገረውና አነሱ የአለምን መኪና መከታተሉን ቀጠሉ..እሷ ቀጥታ ለዛ ምሽት ፈጣን በሚባል አነዳድ የቦሌን የአስፓልት መንገድ ይዛ እየነዳችው ነው፡፡

‹‹ልጅቷ ወደየት እየሄደች ነው?፡፡››ስርጉት ግራ በመጋባት ውስጥ ሆና ጠየቀች፡፡
‹‹ይመስለኛል…ግብረ አበሮቾ ጋር የምትገናኘው ከከተማው ውጭ ነው፡፡››አባቷ የመሰላቸውን ተናገሩ፡፡

‹‹አይመስለኝም››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹ማለት…ምን አሰብክ?››

‹‹ትዝ ይላችኃላ እናቷ ኮፈሌ ዘመዶች ነበሯት…የአባቷም ዘመዶች እዛው ናቸው..እኛ በማናውቅበት መንገድ ከዘመዶቾ ጋር መገናኘት ጀምራ ነበር ማለት ነው..እና አሁን እነሱን ለማግኘት እየሄደች ያለ ይመስለኛል..››ሲል መላምቱን አስቀመጠ፡፡

‹‹እና ኮፈሌ ድረስ ልንከተላት ነው ማለት ነው?፡፡››

‹‹እንግዲህ ቀድሞውንም አትከተሉኝ ያልኩት ለዚህ ነው…እኔ እንኳን እዚህች ኮፈሌ ድረስ ይቅርና ሱማሌም ድረስ ከነዳችው ከመከተል ወደኃላ አልልም››ሲል ፍርጥም ያለ ውሳኔውን ነገራቸው፡፡
//

አለም መኪናዋን በፍጥነት እያበረረች እንኳን ደጋግማ አቶ ፍሰሀ ስልክ ላይ ከመደወል አልታቀበችም…ግን አሁንም ስልኩ ይጠራል እንጂ አይነሳም…‹‹ይሄ ማለት ሰውዬው ከባድ አደጋ ደርሶበታል ማለት ነው..?››ስትል አሰበችና ዝግንን አላት….በእሱ ላይ በሚደርስ አደጋ እንደዚህ አይነት ሽብር ውስጥ እገባለሁ ብላ አስባ አታውቅም ነበር….እርግጥ እንዲህ በድሎኛል ብላ አንድም ቀን አካላዊ ጉዳቱን ወይም ሞቱን ተመኝታለት አታውቅም
…ቢሆንም ደህንነቱ በዚህ መጠን እንዲህ ያሳስበኛል ብላም ግምቱ አልነበራትም፡፡እና የራሷ ሁኔታ በጣም ነው ያስገረማት፡፡

‹‹ፈጣሪ ሆይ እባክህ..ህይወቱን ጠብቃት››ከልቧ ፀለየች፡፡ለቤተሰቦቹ መሳወቅ እንዳለባት ትዝ ያላት ወደባሌ የሚያመራውን የአስፓልት መንገድ ለቃ ወደቀኝ በመታጠፋ ወደ  ሶሌ ደን የሚወስደውን ጥርጊያ መንገድ ከያዘች በኃላ ነበር፡፡የጂኒዬርን ቁጥር ፈለገችና ደወችለት፡፡

‹‹ሄሎ ጁኒዬር…. አለም ነኝ››

‹‹አለም ..ደህና ነሽ…?የት ነሽ….?እንዴት ነሽ?››የእሷን ድምፅ ሲሰማ የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋበት፡፡ስልኩ ሲደወልለት ቤት ከእናቱ ጋር ሳሎን ቁጭ ብሎ እየተጫወተ ነበር፡፡እሷ ለእሱ መርበትበት ቁብም ሳትሰጥ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ጂኒዬር ልብ ብለህ አድምጠኝ…ከ30 ደቂቃ በፊት ከአባትህ ጋር በስልክ እያወራሁ ነበር…መኪና እየነዳ ሳያስበው ከከተማ እንደወጣ እና ወደሶሌ ደን እየተቃረበ መሆኑንና ከአሁን በኃላ ስለመሸ ወደከተማ እንደማይመለስና ማረፊያ ጎጆ ስላለው እዛው እንደሚያድር እየነገረኝ ነበር፡፡›

‹‹አዎ እዛ አልፎ አልፎ የምናርፍበት ጎጆ አለን….››

‹‹እና..ምን መሰለህ?››

‹‹እያስደነገጥሺኝ ነው..ስለምን ነበር እያወራችሁ የነበረው?››

‹‹እሱ ምን ይሰራልሀል…ለማንኛውም ንግግራችንን ሳንጨርስ አውሬ ገባብኝ የሚል ድምፅ እና ከፈተኛ ፍንዳታ የመሰለ ነገር ሰማው..እና ስልኩ ተቋረጠ.. መልሼ ደጋግሜ ብደውል ስልኩ ይጠራል… አይነሳም..፡፡››

‹‹ወይኔ ፈጣሪ…ምን እያልሺኝ ነው?››አጠገቡ የነበረችው እናቱ ሳራ የልጇ ጭንቀት በእሷም ላይ ተጋብቶባት…ስሩ ቆማ ትንቆራጠጥ ጀመር፡፡.

‹‹ለምንኛውም አሁን ቦታው ላይ እየደረስኩ ነው.. እንዳገኘሁትና ሁኔታውን እንዳየው እደውልልሀለው…ምን አልባት አንብላንስ ያስፈልግ ይሆናል››ስልኩ ተቋረጠ
‹‹ምንድ ነው ልጄ..?ፍሰሀ ምን ሆነ?››ሳራ ጠየቀች፡፡

‹‹አባዬ አደጋ ደርሶበታል መሰለኝ..ሶሌ ያለው ደን ውስጥ ነው…መሄዴ ነው››

‹‹እኔም አብሬህ እሔዳለው››

‹‹እማዬ አንቺ እዚሁ ሆነሽ ጠብቂ….››

‹‹እሔደለው..አልኩህ እሔዳው›› አጉረጠረጠችበት፡፡ምንም አላለም…በክርክር ጊዜ ማባከን ስላልፈለገ ቀጥታ ወደሳሎኑ መውጫ መራመድ ጀመረ… እናቱም ከኃላው ተከተለችው… መኪና ውስጥ ገቡ ..ወደባሌ ጎባ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ይዘው ወደ ሶሌ ጉዞ ጀመሩ
///
አቶ ፍሰሀ አውሬውን አድናለው ብሎ መሪውን ሲጠመዝ ሙሉ በሙሉ ከመንገዱ ወጥቶ በግራ በኩል ባለው ገደል መሰል ጉድጓድ ውስጥ ነበር ጎማው ተንሸራቷ የገባው…ከዛ ፍሬኑን ለመያዝ ቢሞክርም የመኪናዋን ፍጥነትም ሆነ ባላንስ መቆጣጠር አቅቶት አንድ ዙር ተገለበጠና አንድ የብሳና ዛፍ ተደግፎ ቆመ….ለአምስት ደቂቃ ራሱን አያውቅም ነበር፡፡ከገባበት መደንዘዝ ሲወጣ ወንበሩ ስር ተወሽቆ ነው ራሱን ያገኘው…እንደምንም ታግሎ ቀበቶውን ከአንገቱ አወጣና በራፍን በእግሮቹ ገፍቶ ለመክፈት ሞከር..ቀላል ስራ እልሆነለትም፡፡እግሮቹ  ምን  እንደነካቸው  ባያውቅም  የሚያሰበውን  ያህል  ጥንካሬ
37👍4
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
‹‹ጋሽ ፍሰሀ..አንተ ነህ…?››

‹‹አዎ አለም…እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?››አውሬው ካስደነገጠው በላይ የእሷ በዚህ ሰዓት እዚህ አካባቢ መገኘት አስደነገጠው፡፡

‹‹እንዴ ስልክ እያወራን ነበር እኮ የተቆረጠው….መኪናህ እንደተገለበጠች እርግጠኛ ስለነበርኩ ወዲያውኑ ወደእዚህ የመጣሁት…መኪናህን ቀድሜ ባገኛትም ውስጡ የለህም..ግን የሚንጠባጠበውን ደም እየተከተልኩ ደረስኩብህ››

‹‹ስሩ ደርሳ ደገፈችው››

‹‹አብሮሽ ማን አለ?››

‹‹አረ ማንም የለ….መንገድ ላይ ሆኜ ለጁኒዬር ደውዬለታለው..ይሄኔ እየመጡ ይሆናል፡››

‹‹ይገርማል..የሆነ ነገር ቢያጋጥምሽስ?››

‹‹ሀሳቤ ሁሉ ያንተን ደህንነት ማረጋገጥ ላይ ስለነበር እሱን አላሳብኩትም ነበር…እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ ግን አሁን በፍራቻ እየተንቀጠቀጥኩ ነው፡፡››

‹‹በጣም ነው ያስገረምሺኝ..አይዞሽ አሁን አምስት ደቂቃ ነው ደርሰናል….እንደውም እዛ መብራት ጭልጭል የሚልበት ቦታ ይታይሻል …?እዛ ነው ጎጆው…በአቅራቢያው የእኔ ሰራተኞች ቤትም አለ…››

‹‹ በአንድ እጇ ደግፋው በሌላ እጇ ደግሞ የስልኳን ባትሪ ከፊት ለፊት እያበራች ወደፊት በዝግታ መራመዳቸውን ቀጠሉ፡፡
አቶ ፍሰሀ ከአውሬው ጋር የነበረው መፋጠጥ አሁንም ከምናብ ሊደበዝዝ አልቻለም… ልቡ ለምን እንዲህ ከመጠን በላይ መታ? ጉዳዩ ምን ነበር? የዱር አውሬው በጣም አስፈርቶት ነው? አይደለም፡፡ እሱ ስለእነሱ አላሰበም። በህይወቱ የበለጠ አስፈሪ ነገሮችን አሳልፎ ያውቃል። ወዲያው ከኃላቸው እየተንሾካሾኩ የሚመጣ የእግር ኮቴ ሰሙ…መንገዱን ለቀቁና ጢሻውን ተከልለው ቆሙ..ሲጠጎቸው ማንነታቸውን በድምፅ ለዩ…‹‹ገመዶ››
ባትሪውን ሲያበራባት ፈጽሞ እዚህ አገኘዋለሁ ብሎ ያላሰበውን አቶ ፍሰሀን በአለም ተደግፋፎ ልክ እንደተወዳጅ ልጁ ስሩ ተሸጉጣ ሲያይ አይኑን ማመን አልቻለም፡፡

ሁሉም ተንደርድረው ከበቧቸው‹‹ጋሼ ምን እየተካሄደ ነው?››

‹‹አይዞችሁ አትደንግጡ… ተርፌለው››

‹‹ተርፌለው ማለት?››ኩማንደሩ በመገረም ጠየቀ፡፡

‹‹የመኪና አደጋ እንደደረሰብኝ ሰምታችሁ አይደለም እንዴ የመጣችሁት?››

‹‹አረ በፈጣሪ..ተርፍክ ታዲያ…?እኛ አልሰማንም..እሷን ከከተማ ስትወጣ አይተን ተከትለናት ነው የመጣናው…ከጠላቶቻችን ጋር ልትገናኝ መስሎን ነበር››

‹‹አይ እሷ እኔን ለማትረፍ ነው የመጣችው››

‹‹እንዴት ከእኛ ቀድማ ልትሰማ ቻለች?..ነው ወይስ በአደጋው ላይ የእሷ እጅ አለበት?››

‹‹እሱን ጎጆው ጋር  ደርሰን ትንሽ ካረፈ በኃላ ብትጠይቀው አይሻልም?››አለችው አለም በንዴት፡፡

‹‹ለምን ወደጎጆ እንሄዳለን? መኪናችንን እኮ በቅርብ ርቀት ላይ ነው ያቆምናት..እዚሁ ጠብቁኝና ይዣት ልምጣ..ቀጥታ ወደከተማ ሄደህ ህክምና ማግኘት አለብህ››

‹‹አይ ደህና ነኝ..አሁን ማረፍ ነው የምፈለገው..ወደጎጆ ውሰዱኝ››

‹‹ተው  እንጂ  ፍሰሀ  ..ሀኪም  ሊያይህ  ይገባል››ዳኛው  ጣልቃ  ገብተው  ለኩማንደሩ ድጋፋቸውን ሰጡ፡፡

‹‹የበለጠ  እያደከማችሁኝ  መሆኑን  ልብ  አላላችሁም  እንዴ..?ወደጎጆ  መሄድ  ነው የምፈልገው›› በማለት የማይቀየር አቋማቸውን አሰሙ፡፡

‹‹ይቅርታ ጋሼ..አንተ ካልክ እሺ ወደጎጆ እንወስድሀለን….እነ ጁኒዬርም አሁን ደውለውልኝ ነበር …መገንጠያው ጋር ደርሰዋል….ከደቂቃዎች በኃላ ይደርሳሉ..››አለና ሄዶ በሌላ ጎኑ አቶ ፍሰሀን ደገፈ….ከ5 ደቂቃ በኃላ ጎጆዋ ደረሱ፡፡ፋኖስ አበሩ፣ መኝታው ተስተካክሎ እንዲተኛ ተደረገና በቅርብ ርቀት ያሉ ሌላ የሳር ቤት ውስጥ ወደሚኖሩት የእነሱ ሰራተኞች ተቀስቅሰው መጡ..እሳት እንዲቃጣጠል ተደረገ…ጁኒዬርና ሳራ የመጀመሪያ ለእረዳታ መስጫ የሚያለግሉ ቁሳቁሶች ይዘው እያለከለኩ ደረሱ…ለተወሰነ ጊዜ ለቅሶና ግርግር በጠባቧ ጎጆ ነገሰ..ከዛ ቀስ በቀስ ወደመረጋጋት ቢመጣም በሰው ብዛት በታፈነችው ጎጆ ውጥረትና ጭንቀት ነግሶ ነበር፡፡

‹‹ቆይ እኔ ያልገባኝ…ምንድነው የሚያስጠብቀን..?ለምንድነው ወደከተማ ይዘነው ሔደን ሀኪማ የማያየው?››ሳራ ነች ግራ በመጋባት ተመሳሳይ አይነት ጥያቄ ለሶስተኛ ጊዜ ያነሳችው፡፡

‹‹ጋሼ አልፈልግም ስላለ እኮ ነው…ጋሼ አሁን ትንሽ አርፈሀል፣ብንሄድ ምን ይመስልሀል?››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹አይ ዛሬ ማንም ከዚህ አይሄድም…አሁን ሰዎቹን ሸኞቸውና የምንነጋገረው ነገር አለ››ሲል ሁሉም በቀጣይ ምን ሊፈጠር ነው በሚል እርስ በርስ ተያዩ፡፡

ጁኒዬር ከጎረቤት ጎጆ የመጡትን ባልና ሚስቶች ከነልጆቻቸው አመስግኖ ወደቤታቸው እንዲሄዱ ካደረገ በኃላ የጎጆዋ ቤት ተዘጋ፡፡አሁን ስድስት ሰዎች ፊት ለፊት ተፋጠጡ …ሁለቱ ሴቶች እና አዛውንቱ ዳኛ አቶ ፍሰሀ ጎን የተቀመጠችውን አለምን በከፍተኛ ጥላቻን መጠየፍ ነበር የሚመለከቷት፡፡

አቶ ፍሰሀ ከትራሱ ቀና አደረገና አስተካክሎ በመደገፍ መናገር ጀመረ‹‹ዛሬ እየሆነ ያለው ሁሉ ነገር ተአምር ነው…እኔ እቅዴ እንደማንኛውም ቀን ስራ ውዬ ወደቤቴ መግባት ነበር….ነገር ግን የሰሞኑን ውጣ ውረድ እያሰላሰልኩ ሳላስበው ከከተማ ወጣሁና እራሴን እዚህ ሶሌ ደን አካባቢ አገኘሁት..እንዴት እዚህ ልደርስ ቻልኩ? ብዬ እየተገረምኩ ሳለ ያልጠበቅኳት አለም ደወለችልኝ..ከእሷ ጋር እያወራው ሳለ ድንገት ሳላስበው አውሬ ገባብኝና እሱን አድናለው ስል መኪናዬ መንገድ ስታ ተገለበጥኩ…እንደአደጋው መሞት ነበረብኝ..ግን ከተወሰነ ጭረት በስተቀር ምንም አልሆንኩም…እግዜር አሳይቶ ከሞት ደጃፍ መለሰኝ..ከመኪናው ወጥቼ በጫካው እያሳበርኩ ወደእዚህ እየመጣው ሳለ ከጅብ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጥኩ…እሱንም ወደሰማይ ተኩሼ አስበረገግኩትና ሁለተኛውን ፈተና አለፍኩ..ከዛ ወዲያው አለምን ከፊት ለፊቴ አገኘኃት..ወዲያው እነ ገመዶና መጡ…ጎጆው እንደደረስን ደግሞ ልጄና ባለቤቴ መጡ …እኔ ለማናችሁም አደጋ ደረሰብኝ ብዬ አልደወልኩም..በአደጋው ጊዜ ስልኬ ወደየት እንደጠፋም አላውቅም..ግን ሁላችሁም እዚህ ተገኝታችኃላ..ሁላችንን እዚህ ያለነው ለምክንያት ነው፡፡ከአለም ጋር የጀመርነው ድብብቆሽ እዚህ ጋ ማብቃት መቻል አለበት፡፡

‹‹አዎ ማብቃት አለበት …ይህቼ ሴት ከዚህ በፊት ንብረቴ እንዲቃጠል አደረገች… ዛሬ ባለቤቴን ገድላብኝ ነበር….››ሳራ ተንዘረዘረች…ዳኛውና ስርጉት አይናቸውን በማጉረጥረጥ እና በመገላመጥ ለሳራ ያላቸውን እገዛ አሳዩ ፡፡

‹‹ሳራ ተይ ..ዛሬ የምንበሳጭበትና ራሳችንን ሀጥያት ለመሸፈን ሌላ ስው በሀሰት የምንወቅስበት ቀን አይደለም..እኔ አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከሁለት ሞት ነው የዳንኩት…ይሄ ያለምክንያት አይደለም..ይህቺን ልጅ ሁላችንም በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ በድለናታል…ሁላችንም ለእሷ መናዘዝ መቻል አለብን..እውነቱን ልንነግራት ይገባል..ከዛ አመዛዝና ከፈለገች ትበቀለን… ከፈለገች ደግሞ ወደፍትህ አደባባይ ወስዳ ታሰቅለን፡፡

የአቶ ፍሰሀን ንግግር የሰሙት ዳኛው ጫንቃቸውን አላባቸው፡፡ይሄ ሰውዬ በተገበጠበት ወቅት ጭንቅላቱን ተመቶ ማሰቢያው ላልቶ ይሆን እንዴ?››ሲል አሰበና አይኑን ገመዶና ጁኒዬር ላይ አንከራተተ…የሆነ ነገር ብለው የጀመረውን ቅዠት የመሰል ድርጊት እንዲያስቆሙት ነው ፍላጎቱ.
45👍4
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››

‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››

‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››ስርጉት በተቀመጠችበት ሆና አቃሰተች….ዳኛው መተንፈስ ከበዳቸው፡፡ሳራ ግን ለማናቸውም ግድ አልነበራትም..የእሷ ዋናው ትኩረት ልጇን ከእስር ማዳን ብቻ ነው..እና ንግግሯን ቀጠለች፡፡

‹‹.የዛን ቀን አንተ እኛን ወደቤታችን ከመሸኘትህ በፊት መጠጧ ውስጥ መድሀኒት ጨምረንባት ነበር..ከ30 ደቂቃ በኃላ እንደማሳበድ አድርጓት በአንድ ሰአት ውስጥ ሙሉ በሙሉ የሚገድላት መድሀኒት ነበር፡፡እሷ  የተቀየረችብህና ከመስታወት ላይ ግንባሮሯን የከሰከሰችው በመድሀኒቱ ተጽዕኖ ነው…መስታወቱ ሆዷ ውስጥ ቢሻጥ እንኳን  አልሞተችም ነበር…አባትህ መጥቶ ሀኪም ቤት ሊወስዳት መኪናው ውስጥ አስገብቶ መንገድ ከጀመረች በኃላ ነው እስትንፋሷ የተቋረጠው…ያም የሆነው በተወጋችው ውግ ወይም በፈሰሳት ደም ሳይሆን በጠጣችው መርዝ ምክንያት ነው፡፡

‹‹እማዬ ይሄን እንዴት እሰከዛሬ ሳላውቅ…?አባዬ አንተ እንዲህ መሆኑን ታውቃለህ?››ሲል አባቱ ላይ አፈጠጠበት፡፡
አቀርቅሮ የነበረው አቶ ፍሰሀ በከፊል ቀና አለና ‹‹ከአንተ እና ከአለም በስተቀር ይሄንን ጉዳይ እዚህ ቤት ያለው ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡››ሲል እውነቱን ፍርጥም ብሎ መለሰለት፡፡

‹‹ምን አረገቻችሁ ቆይ …?ምናችሁ ላይ ደረሰች?››አለም በእንባ ታጥባ እየነፈረቀች ሳራ ላይ አፈጠጠችባት፡፡

ሳራ እሷን ችላ ብላ ወደልጇ እየተመለከተች‹‹አንተን እንዳታገባህ እና ከስርህ እንድትርቅ ለአመታት ለመናት.. አስጠነቀቅናት፤ እሷ ግን ሌላ ሰው አግብታ ወልዳ እንኳን ልትተውህ አልቻለችም…የልጄ ህይወት በእንደዛ አይነት ሁኔታ ሲበላሽ ቆሜ ማየት አልቻልኩም፡፡እኔ ስርጉትን እንድታገባ ነበር ምፈልገው፣ከልቧ በጣም የሚታፈቅርህ ሰሎሜ ሳትሆን ስርጉት እንደሆነች በደምብ አውቃለው..››
ወዲያው ሳራ ንግግሯን እንዳገባደደች ኩማንደር ተቀበላት‹‹ያው እንግዲህ መጠኑ ይለያይ እንጂ በእናትሽ ግድያ ሁላችንን የየድርሻችንን ተወጥተናል…እኔ በእለቱ እስከእራት ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር አብሬቸው የቆየሁት…ከለሊቱ ዘጠንኝ ሰዓት ጋሽ ፍሰሀ ደወለልኝ.. ስመጣ
…እናትሽ ጋሼ መኪናው ውስጥ እጥፍጥፍ ብላና በደም ተበክላ ነበር…ጋሼ የሆነውን በአጭሩ አስረዳኝና የሚሆነውን እንዳደርግ ሀላፊነቱን ለእኔ ሰጠኝ ….ነገሩ ወደህግ ከሄደ ጁኒዬር፤ሳራም ሆነች ስርጉት ዘብጥያ መውረዳቸው አይቀርም …ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ያ ሊቁ የተባለው እብድ በዛ ውድቅት ለሊት እየለፈለፍ በእርባታ ድርጅቱ ፊት ለፊት ባለው መንገድ ሲያልፍ አየሁት..ወዲያው ሀሳብ ብልጭ አለልኝ..ሮጥኩና ይዤው ወደውስጥ ገባው..ከማታ እራት የተረፈ ምግብና መጠጥ ስለነበረ እሱን ሰጠሁትና ስለማደርገው ነገር መዘጋጀት ጀመርኩ..የምጠቀምበት እቃ ስፈልግ የእንስሳት ዶክተሩ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን በረንዳ ላይ ተቀምጦ ነበር፤አይኔ ውስጥ ገባ፣ ቶሎ አልኩና ከፈትኩት ፡፡ የቀዶ ህክምን ሚገለገሉበትን ቢላዋ አገኘሁና .. በወቅቱ በጣም ተደናግጬ ስለነበረ የማደርገውን ሁሉ የማደርገው በደመነፍስ ነበር….እና ያው ልጅ እንደገደላት እንዲመስል አደረኩና ጥዋት ለፖሊስ ተደወለ.. በኃላ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እየተጓዙ ሳለ አያትሽ ልጄን የገደላት እብዱ ሳይሆን እነሱ ናቸው… የሚል ወሬ መንዛት እና
አቤቱታ ማሰማት ጀመሩ…ከዛ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ዘንድ አንዳንድ ጥርጣሬዎች ብልጭ ማለት ጀመሩ..ሬሳው በደንብ ይመርመር የሚል ግሩፕ ተነሳ…ከዛ ከጋሼ ጋር ተማከርንና የሆስፒታሉ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍል እሳት እንዲነሳና እሬሳውም እንዲቃጠል አደረግን..በስተመጨረሻም አያትሽን ይሄንን ሀገር ለቀው ካልሄዱ አንቺን ነጥቀን እስከወዲያኛው እንዳያገኙሽ እንደምናደርግ አስፈራርተናቸው ዝም እንዲሉና ከተማውንም ለቀው እንዲሄዱ አደረግን…እናም በተጨማሪ ስለእናትሽ አሟሟት ሊነግርሽ ነበረውን ሙስጠፋንም የገደልኩት እኔ ነኝ!!የዛን ቀን እኛ ሳናየው እዛ ተደብቆ እያንዳንዱን ነገር ሲያይ ነበር….ይሄን ሁሉ ነገር ግን ፍርድ ቤት ቀርቦ ያምንልኛል ብለሽ እንዳትጠብቂ…››ሲል ንግግሩን አገባደደ፡፡

አለም ደም በለበሱ አስፈሪ አይኖቾን ኩማንደሩ ላይ አፍጥጣ‹‹ቆይ ቆይ እስኪ…ልጁ የገደላት ለማስመሰል ከሞተች በኃላ በዛ የቀዶ ጥገና ቢላዋ ደጋግመህ ወጋሀት አይደል?
…?ከዛ ደሟ ሲንፎለፎል በእጅህ እየዘቅክ እዛ ሚስኪን ልጅ ልብስ ላይ አዳረስከው …እንዳዛ አይደል ያደረከው?በቁሟ እያለች በፍቅር ልብህን ስለሰበራች ልትበቀላት ታስብ ነበር፣ግን ለማድረግ ወኔ አልነበረህም..በዛን ወቅት ግን አጋጣሚው ተመቻቸልህ..ነፍሷ ውስጧ ባይኖርም ደጋግመህ ሰጋዋን በመበሳሳት ንዴትህን ተወጣህባት….ከዛ ሬሳዋ ለምርመራ ሆስፒታል ገባ ..አንዳንድ ጥርጣሬ የሚያስነሱ ነገሮች መፈጠር ሲጀምሩ እራሳችሁን ከማንኛውም አደጋ ጥርጣሬ ለመጠበቅ አስፈላጊ ስለነበረ ጋሼ ፍሰሀ ደግሞ የሆስፒታሉ የሆነ ክፍል በእሳት እንዲያያዝ እና ሬሳዋም እንዲቃጠል እና አመድ እንዲሆነ አደረገ..ከዛ አቶ ዳኛ በዚህ ወንጀል ውስጥ ልጁ ስላለችበት ይህንን ወንጀል እንዳይጋለጥ ባለህ ስልጣን ሁሉ ተጠቅመህ ፋይሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲዘጋ አደረክ…፡፡በትክክል ተረድቼችኋለው አይደል..?እንዲህ ነው ያደረጋችሁት?
‹‹ሁሉም በመሸማቀቅ አንገታቸውን አቀርቅረው ነበር የሚሰሟት‹‹እስከአሁን እንደሰማሁት ከሆነ እኮ ጁኒዬር ብቻ አይደለም ራሱን ለህግ አሳልፎ መስጠት ያለበት …ሁላችሁም ናችሁ..እና እኔ ዳኛ ብሆን በጣም ትንሹን ፍርድ የምፈርደው በእሱ ላይ ነው….እሱ ሳያስበው…በድንገተኛ አደጋ የፈጠረው ወንጀል ነው…ሌለቻችሁ ግን አስባችሁ እና አቅድ አውጥታችሁ ደግማችሁ ደጋግማችሁ እናቴን በነፍስም በስጋም አጥፍታችኃታል….እና ነገ ወደከተማ ስንመለስ ምን እንደምታደርጉ ለማየት በጣም ጎጉቼለው….፡፡››

‹‹መቼስ ሁላችንም ሳታጠፊን እንቅልፍ አይወስድሽም አይደል…?ደስ ይበልሽ ይሄው ተሳካልሽ››አሉ ዳኛው ቅስማቸው ስብርብር ብሎ፡፡

‹‹ደስ ይበልሽ !!….ጭራሽ ደስ ይበልሽ…?.ፍርድን በአደባባይ ሲሸጦት ያዛን ጊዜ ማሰብ ነበረቦት››

‹‹አይ መሬት ያለ ሰው….በእኔ ላይ የደረሰውን ወላጅ ስትሆኚ ነው የምታውቂው….ልጄን ከእስርና ከእንግልት ለማዳን ስል ነው እዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ የገባሁት››

‹‹አይ ልጆትን ከእስር ለማትረፍ ብቻ አይደለም….ከሶሌ ኢንተርፕራይዝም የ10 ፐርሰንት የአክሲዬን ድርሻ በልጆት ስም ማግኘት ችለዋል፡፡››

‹‹ይህ ፍፁም እውነት አይደለም…ያንን አክሲዬን የገዛሁት በራሴ ብር ነው….ከወላጆቼ በውርስ ያገኘሁትን ንብረት በጠቅላላ ሸጬ ነው የገዛሁት…ያንንም ፈልጌው ሳይሆን ኩማንደሩ እና ፍሰሀ አስገድደውኝ ነው፡፡በልጄ አስፈራርተውኝ ነው››

ዳኛው የሚናገሩትን ባለማመን ቀና አለችና ኩማንደሩ ላይ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹አዎ..እውነቱን ነው፡፡ይሄንን ወንጀል ዛላለም በመሀከላችን እንደተቀበረ እንዲቆይ እርስ በርስ የበለጠ መተሳሰር አለብን ብለን አሰብን…ከዛ ከጁኒዬር እና ከሳራ ድርሻ ላይ ተቀንሶ በስርጉት ስም አክሲዬን እንዲገዙ አደረግን….ባይሆን እኔ ቀጥታ ጠይቄ ባይሆንም ከእናትሽ ሞት በኃላ የአክሲዬን ድርሻዬ ወደ30 ፐርሰንት እንዲያድግ ሆኗል….››
46👍5😱2