#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሰባ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ጆይስ ወረደችና ሚስተር ካርላይልን ራት ከሚበላበት አስነሥታ ይዛው መጣች
“ ማዳም ቬን ባሰባት እንዴ . . ኮርኒሊያ ? እኔን ፌለገችኝ ?
“ አዎን ልታነጋግርህ ትፈልጋለች ”
ሚስ ካርላይል እየተናገረች በሩን ከፈተችው "መጀመሪያ እሷ እንድትግባ በጁ አመለከታት “ የለም” አለችው “ ብቻህን ገብተህ ብታያት ይሻላል ”
ሊገባ ሲል ጆይስ ክንዱን ያዘችው “ ጌታዬ ተዘጋጅተው ይግቡ“ እማማ
ለምን አይነግሯቸውም ?”
ሁለቱንም ትክ ብሎ አያቸው ሁኔታቸውን ይኸ ነው ብሎ ለመናገር አልቻለም
አንግዳ ነገር ሆነበት " እንዲያውም ወደ ዕብደቱ ወሰድ ያደረጋቸው መሰለው
ፊቷ ምንም ቢሆን ተለውጦ የማያውቀው ኮርኒሊያ እንኳን ምንም ኮስተር ብላ
ብትቆምም ከንፈሮቿ ሲንቀጠቀጡ መቁጣጠር አልቻለችም " ሚስተር ካርላይል ግንባሩን ቋጥሮ ሲገባ እነሱ በሩን ዘጉበት "
በቀጥታ ወደ በሽተኛይቱ አልጋ ቀስ ብሎ ተጠጋና “በጣም አዝናለሁ ማዳም ቬን...” ብሎ የጀመረውን ሳይጨርስ ቀሪዎቹ ቃላት ምላሱ ላይ ተንከባለሉ"
ሊወጡ አልቻሉም . እሱም እንደ ጆይስ የሳቤላን መንፈስ ያየ መሰለው
ከአልጋው ትንሽ አፈገፈገ ወርዶ አንገቷ ላይ የተቆለለው ጸጉሯ የሚያምሩትና የኀዘን ዳመና የጣለባቸው 0ይኖቿ ሳይቀሩ የሳቤላ ቬንን መልክ ቁልጭ አድርገው አሳዩት
አርኪባልድ ! ” አለችው "
የሚንቀጠቀጠው እጅዋን ዘረጋችና እጁን ያዘችው " ትክ ብሎ አያት» ከሕልም የነቃ ይመስል ዙሪያውንም አስተውሎ አየ "
“ነፍሴ ያንተን ይቅርታ ሳታገኝ ከሥጋዋ መለየት አልቻለችም " አለችው
የሰራችውን በደል ስታስብ ዐይኖቿን ስብር አድርጋ “ ተው ' ፊትህን አታዙርብኝ " ለአንዳፍታ ታገሠኝ ይቅር ብየሻለሁ ብቻ በለኝና በሰላም ልሙት
“ ሳቤላ ! አንቺ ነሽ? አንቺ ነሽ ? ማዳም ቬን የነበርሽው ? " አለ የሚናገረውን አላወቀውም።
ይቅር በለኝ ማረኝ... አርኪባልድ | አልሞትኩም » የደረሰብኝ አደጋ ለወጠኝ እንጂ አልገደለኝም » ነገር ግን ማንም አላወቀም ስለዚህ ማዳም ቬን
ተብዬ ወደዚሁ መጣሁ " ተነጥዬና ርቄ መኖር አልቻልኩም » ማረኝ ... አር
ኪባልድ ማረኝ " "
የሚናገረው የሚያደርገው ቅጡ ጠፋው " አምሮው ጠሮ ነፋስ እንደ ገባበት
ተበጠበጠ ግራ ገብቶት ዝም ብሎ እንደ ቆመ ነገሯን ቀጠለች "
“ ከአንተና ከልጆቼ ተነጥዬ መኖር አልቻልኩም " ያንተ ናፍቆት ሊገድለኝ ሆነ ” አለችው " አነጋግሯ የትኩሳት ቅዠት ይመስል ነበር “ “ እንደዚያ አሳብዶኝ ካን† ከተለየሁ ወዲህ የአንዲት ቅጽበት እንኳን ሰላም አግኝቸ አላውቅም .
መላው ባይጠፋኝ ኖሮ ወዲያው ተመልሸ እመጣ ነበር ከቤት ከወጣሁ አንድ
ሰዓት እንኳን ሳልቆይ ጸጸት ያዘኝ እያደር እየከበደኝ እየጠናብኝ ሔደ ምን እንዳ
ስመሰለኝ ታየዋለህ ? እየው ተመልከተው " ብላ የሸበተው ጸጉሯን የመነመ
ነውን እጁዋን አሳየችው » አንተው ማረኝ ይቅር በለኝ !ጥፋቴ በጣም ከባድ ነው ! የተቀበልኩት ቅጣት ግን ይበልጣል " ለብዙ ዘመን ከባድ መከራ ከባድ
ሥቃይ ተቀብያለሁ " ሕይወቴ ረጅም ዘመን የፈጀ የጻዕረ ሞት ሕይወት ነበር ”
“ እንዲያው ሲጀመር ምን ሆነሽ ሔድሽ?”
“ ለምን እንዶ ሔድኩ አላወቅህም? ”
“ የለም አላውቅም " እስከ ዛሬ ምስጢር እንደ ሆነብኝ ነው ”
“ አንተን ከመውደዴ የተነሣ ነበር የሔድኩት " ከንፈሮቹን በንቀት ቀስቀስ አደረጋቸው " በጣር ላይ ሆናም የምትቀልድበት መሰለው
“ ተው እንደሱ አድርገህ አትየኝ " አቅም የለኝም " ያለው የሌለው ጉልበቴ አልቋል " ከሰውነት ወጥቻለሁ " ዐይንህ ያያል " የምነግርህ እውነት መሆኑን ተረዳልኝ ነገሬ ግልጽ ካልሆነ እንጃ በጣም እወድሀ ስለ ነበር ጠረጠርኩህ፤ እኔን አለሁልሽ ብለህ እያታለልክ ፍቅርህን ለሌላ የሰጠህብኝ መስለኝ » ስለዚህ በጥርጣሬ ቅናት እንደ ቆሰልኩ ከዚያ ክፉ ሰው ወጥመድ ገባሁ " እንድበቀልህ በጆሮዬ ሹክ ይለኝ ነበር ”
“እኔ ግን አንቺን በሐሳብም፡ በቃልም በተግባርም ለማታለል አልሞከርኩም"
ያንጊዜም ታውቂኝ ነበር " ከዚያ ወዲህም ሳታውቂኝ አልቀረሽም
“አርኪባልድ ... አብጀ ነበር " በዕብደት እንጂ በጤንነት እንደዚያ ያለውን ሥራ አልሠራውም ነበር " ስለዚህ እርሳው ' ይቅር በለኝ ”
“ መርሳት አልችልም " ይቅር ካልኩሽ ግን ቆይቻለሁ "
“ ከዚያ ሌሊት ወዲህ ያለፈውን የኀዘንና የብስጭት ጊዜ ለመርሳት ሞክር” አለችው ዕንባዋ በሁለት ጉንጮቿ እየወረደ " ሥጋው አልቆ አጥንቱ ብቻ ቀርቶ በትኩሳት የሚቃጠለውን ክንዷን ወደሱ ዘርግታ : “ በሱ ፈንታ የፍቅር ጊዜአችንን ላለመርሳት ሞክር "
አኔን በመጀመሪያ ወደ ዐወቅህበት ዘመን መልሰው " ከዚህ ቤት ሳቤላ ሼን አየተባልኩ ካባቴ ጋር ደስተኛ ልጅ የነበርኩበትን ዘመን አስታውስ ያኔ ለኔ ባትገልጽልኝም እንዴት ልትወደኝ እንደቻልክ አስታውስ" አባቴ በሞተ ጊዜ የተቸገርክልኝን በዚያች ምናምን ባልነበረኝ ሰዓት አንድ መቶ ፓውንድ የሰጠኸኝን ወደ ካሰል ማርሊንግ የመጣህ ዜ
ሐሳብህን ላንዳፍታ
ላገባህ ቃል የገባሁበትን ለመጀመሪያ ጊዜ ከንፌሬን የሳምከኝን ከተጋባን በኋላ የነበረን ደስታ ትዝ ይልሃል ? አብረን ያሳለፍናቸውን የፍቅር ዘመናት ታስታውሳቸዋለህ ? ሉሲ ስትወለድ ከሞት አፋፍ በመትረፌ የተሰማህን
ሁሉ ትዝ ይልሃል ? ”
“ ታዲያ አሁን እኔን ይህን አጠፋህ የምትይኝ አለሽ ” አላት አሳዛኝ እጅዋን
በእጁ ይዞ ።
አንተን ? በኔ ቀርቶ በአምላክ ዘንድም ጥፋት አይገኝብህም " ከልብህ
ወደከኝ ነበር " ለደኅንነቴ ባያሌ» ስትጨነቅልኝ ነበር » አንተ ደግሞ ምንህ ይወቀሳል? ምን አንደነበርክና ዛሬም እንዴት ያለህ ሰው እንደሆንክ ሳስበውና ከመለስኩልህ ውለታ ጋር ሳነጻጽረው በኃፍረትና በጸጸት መሬት ተከፍታ ብትውጠኝ እወድ ነበር ለራሴም ጥፋት የሚያበቃኝን ቅጣት ተቀብያለሁ ባንተና
በልጆችህ ያመጣሁባችሁን ውርደት ግን ማስለቀቅ አልችልም ”
“ የኔን ፈተና ግን አስበው " አለችው ድምጿ እየደከመ " እሱም እየራቀ የሔደውን ድምፅ ለመስማት ጆሮውን ጠጋ ለማድረግ ተገደደ ። “ በዚህ ቤት ውስጥ ከሚስትህ ጋር ተቀምጬ ምን ያህል እንደምታፈቅራት እኔን ትዳብስኝ እንደ ነበረው ስትዳብሳት እያየሁ ' በቅናት ስንገገብ ኖርኩ አሳልፌ ለሌላ ከስጠሁህ በኋላ ያፈቀርኩህን ያህል አፍቅሬህ አላውቅም ነበር " እስቲ ይታይህ' ዊልያም ልጄ ጉልበቱ እየመነመነ ሰውነቱ እያለቀ ሲሔድ እያየሁ ነፍሱ በምትወጣበት
ሰዓት ካንተ ጋር ብቻችንን ሆነን ስንጠብቀው እናቱ መሆኔን እንኳን ለመናገር
አለመቻሌ እንደ ሞተም ቤተሰቡ ሁሉ ሰምቶ ሲደናገጥ የኔን የወላጅ እናቱን ኀዘን ሳይሆን የስዋን ትንሽ መጠነኛ ኀዘን ነበር የምታጽናኑት " እኔ ባሁኑ ጊዜ ከዚህ ቤት ችየው የኖርኩት ፈተና የሞት ያህል መራራና አስጨናቂ ነበር "
“ለምን ተመልሰሽ መጣሽ ? ” አላት "
“ ነገርኩህ እኮ ካንተና ከልጆቼ ተለይቸ መኖር አልቻልኩም '
“ስሕተት ነበር ! ፍጹም ስሕተት ነበር የሠራሽው
፡
፡
#ክፍል_ሰባ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ጆይስ ወረደችና ሚስተር ካርላይልን ራት ከሚበላበት አስነሥታ ይዛው መጣች
“ ማዳም ቬን ባሰባት እንዴ . . ኮርኒሊያ ? እኔን ፌለገችኝ ?
“ አዎን ልታነጋግርህ ትፈልጋለች ”
ሚስ ካርላይል እየተናገረች በሩን ከፈተችው "መጀመሪያ እሷ እንድትግባ በጁ አመለከታት “ የለም” አለችው “ ብቻህን ገብተህ ብታያት ይሻላል ”
ሊገባ ሲል ጆይስ ክንዱን ያዘችው “ ጌታዬ ተዘጋጅተው ይግቡ“ እማማ
ለምን አይነግሯቸውም ?”
ሁለቱንም ትክ ብሎ አያቸው ሁኔታቸውን ይኸ ነው ብሎ ለመናገር አልቻለም
አንግዳ ነገር ሆነበት " እንዲያውም ወደ ዕብደቱ ወሰድ ያደረጋቸው መሰለው
ፊቷ ምንም ቢሆን ተለውጦ የማያውቀው ኮርኒሊያ እንኳን ምንም ኮስተር ብላ
ብትቆምም ከንፈሮቿ ሲንቀጠቀጡ መቁጣጠር አልቻለችም " ሚስተር ካርላይል ግንባሩን ቋጥሮ ሲገባ እነሱ በሩን ዘጉበት "
በቀጥታ ወደ በሽተኛይቱ አልጋ ቀስ ብሎ ተጠጋና “በጣም አዝናለሁ ማዳም ቬን...” ብሎ የጀመረውን ሳይጨርስ ቀሪዎቹ ቃላት ምላሱ ላይ ተንከባለሉ"
ሊወጡ አልቻሉም . እሱም እንደ ጆይስ የሳቤላን መንፈስ ያየ መሰለው
ከአልጋው ትንሽ አፈገፈገ ወርዶ አንገቷ ላይ የተቆለለው ጸጉሯ የሚያምሩትና የኀዘን ዳመና የጣለባቸው 0ይኖቿ ሳይቀሩ የሳቤላ ቬንን መልክ ቁልጭ አድርገው አሳዩት
አርኪባልድ ! ” አለችው "
የሚንቀጠቀጠው እጅዋን ዘረጋችና እጁን ያዘችው " ትክ ብሎ አያት» ከሕልም የነቃ ይመስል ዙሪያውንም አስተውሎ አየ "
“ነፍሴ ያንተን ይቅርታ ሳታገኝ ከሥጋዋ መለየት አልቻለችም " አለችው
የሰራችውን በደል ስታስብ ዐይኖቿን ስብር አድርጋ “ ተው ' ፊትህን አታዙርብኝ " ለአንዳፍታ ታገሠኝ ይቅር ብየሻለሁ ብቻ በለኝና በሰላም ልሙት
“ ሳቤላ ! አንቺ ነሽ? አንቺ ነሽ ? ማዳም ቬን የነበርሽው ? " አለ የሚናገረውን አላወቀውም።
ይቅር በለኝ ማረኝ... አርኪባልድ | አልሞትኩም » የደረሰብኝ አደጋ ለወጠኝ እንጂ አልገደለኝም » ነገር ግን ማንም አላወቀም ስለዚህ ማዳም ቬን
ተብዬ ወደዚሁ መጣሁ " ተነጥዬና ርቄ መኖር አልቻልኩም » ማረኝ ... አር
ኪባልድ ማረኝ " "
የሚናገረው የሚያደርገው ቅጡ ጠፋው " አምሮው ጠሮ ነፋስ እንደ ገባበት
ተበጠበጠ ግራ ገብቶት ዝም ብሎ እንደ ቆመ ነገሯን ቀጠለች "
“ ከአንተና ከልጆቼ ተነጥዬ መኖር አልቻልኩም " ያንተ ናፍቆት ሊገድለኝ ሆነ ” አለችው " አነጋግሯ የትኩሳት ቅዠት ይመስል ነበር “ “ እንደዚያ አሳብዶኝ ካን† ከተለየሁ ወዲህ የአንዲት ቅጽበት እንኳን ሰላም አግኝቸ አላውቅም .
መላው ባይጠፋኝ ኖሮ ወዲያው ተመልሸ እመጣ ነበር ከቤት ከወጣሁ አንድ
ሰዓት እንኳን ሳልቆይ ጸጸት ያዘኝ እያደር እየከበደኝ እየጠናብኝ ሔደ ምን እንዳ
ስመሰለኝ ታየዋለህ ? እየው ተመልከተው " ብላ የሸበተው ጸጉሯን የመነመ
ነውን እጁዋን አሳየችው » አንተው ማረኝ ይቅር በለኝ !ጥፋቴ በጣም ከባድ ነው ! የተቀበልኩት ቅጣት ግን ይበልጣል " ለብዙ ዘመን ከባድ መከራ ከባድ
ሥቃይ ተቀብያለሁ " ሕይወቴ ረጅም ዘመን የፈጀ የጻዕረ ሞት ሕይወት ነበር ”
“ እንዲያው ሲጀመር ምን ሆነሽ ሔድሽ?”
“ ለምን እንዶ ሔድኩ አላወቅህም? ”
“ የለም አላውቅም " እስከ ዛሬ ምስጢር እንደ ሆነብኝ ነው ”
“ አንተን ከመውደዴ የተነሣ ነበር የሔድኩት " ከንፈሮቹን በንቀት ቀስቀስ አደረጋቸው " በጣር ላይ ሆናም የምትቀልድበት መሰለው
“ ተው እንደሱ አድርገህ አትየኝ " አቅም የለኝም " ያለው የሌለው ጉልበቴ አልቋል " ከሰውነት ወጥቻለሁ " ዐይንህ ያያል " የምነግርህ እውነት መሆኑን ተረዳልኝ ነገሬ ግልጽ ካልሆነ እንጃ በጣም እወድሀ ስለ ነበር ጠረጠርኩህ፤ እኔን አለሁልሽ ብለህ እያታለልክ ፍቅርህን ለሌላ የሰጠህብኝ መስለኝ » ስለዚህ በጥርጣሬ ቅናት እንደ ቆሰልኩ ከዚያ ክፉ ሰው ወጥመድ ገባሁ " እንድበቀልህ በጆሮዬ ሹክ ይለኝ ነበር ”
“እኔ ግን አንቺን በሐሳብም፡ በቃልም በተግባርም ለማታለል አልሞከርኩም"
ያንጊዜም ታውቂኝ ነበር " ከዚያ ወዲህም ሳታውቂኝ አልቀረሽም
“አርኪባልድ ... አብጀ ነበር " በዕብደት እንጂ በጤንነት እንደዚያ ያለውን ሥራ አልሠራውም ነበር " ስለዚህ እርሳው ' ይቅር በለኝ ”
“ መርሳት አልችልም " ይቅር ካልኩሽ ግን ቆይቻለሁ "
“ ከዚያ ሌሊት ወዲህ ያለፈውን የኀዘንና የብስጭት ጊዜ ለመርሳት ሞክር” አለችው ዕንባዋ በሁለት ጉንጮቿ እየወረደ " ሥጋው አልቆ አጥንቱ ብቻ ቀርቶ በትኩሳት የሚቃጠለውን ክንዷን ወደሱ ዘርግታ : “ በሱ ፈንታ የፍቅር ጊዜአችንን ላለመርሳት ሞክር "
አኔን በመጀመሪያ ወደ ዐወቅህበት ዘመን መልሰው " ከዚህ ቤት ሳቤላ ሼን አየተባልኩ ካባቴ ጋር ደስተኛ ልጅ የነበርኩበትን ዘመን አስታውስ ያኔ ለኔ ባትገልጽልኝም እንዴት ልትወደኝ እንደቻልክ አስታውስ" አባቴ በሞተ ጊዜ የተቸገርክልኝን በዚያች ምናምን ባልነበረኝ ሰዓት አንድ መቶ ፓውንድ የሰጠኸኝን ወደ ካሰል ማርሊንግ የመጣህ ዜ
ሐሳብህን ላንዳፍታ
ላገባህ ቃል የገባሁበትን ለመጀመሪያ ጊዜ ከንፌሬን የሳምከኝን ከተጋባን በኋላ የነበረን ደስታ ትዝ ይልሃል ? አብረን ያሳለፍናቸውን የፍቅር ዘመናት ታስታውሳቸዋለህ ? ሉሲ ስትወለድ ከሞት አፋፍ በመትረፌ የተሰማህን
ሁሉ ትዝ ይልሃል ? ”
“ ታዲያ አሁን እኔን ይህን አጠፋህ የምትይኝ አለሽ ” አላት አሳዛኝ እጅዋን
በእጁ ይዞ ።
አንተን ? በኔ ቀርቶ በአምላክ ዘንድም ጥፋት አይገኝብህም " ከልብህ
ወደከኝ ነበር " ለደኅንነቴ ባያሌ» ስትጨነቅልኝ ነበር » አንተ ደግሞ ምንህ ይወቀሳል? ምን አንደነበርክና ዛሬም እንዴት ያለህ ሰው እንደሆንክ ሳስበውና ከመለስኩልህ ውለታ ጋር ሳነጻጽረው በኃፍረትና በጸጸት መሬት ተከፍታ ብትውጠኝ እወድ ነበር ለራሴም ጥፋት የሚያበቃኝን ቅጣት ተቀብያለሁ ባንተና
በልጆችህ ያመጣሁባችሁን ውርደት ግን ማስለቀቅ አልችልም ”
“ የኔን ፈተና ግን አስበው " አለችው ድምጿ እየደከመ " እሱም እየራቀ የሔደውን ድምፅ ለመስማት ጆሮውን ጠጋ ለማድረግ ተገደደ ። “ በዚህ ቤት ውስጥ ከሚስትህ ጋር ተቀምጬ ምን ያህል እንደምታፈቅራት እኔን ትዳብስኝ እንደ ነበረው ስትዳብሳት እያየሁ ' በቅናት ስንገገብ ኖርኩ አሳልፌ ለሌላ ከስጠሁህ በኋላ ያፈቀርኩህን ያህል አፍቅሬህ አላውቅም ነበር " እስቲ ይታይህ' ዊልያም ልጄ ጉልበቱ እየመነመነ ሰውነቱ እያለቀ ሲሔድ እያየሁ ነፍሱ በምትወጣበት
ሰዓት ካንተ ጋር ብቻችንን ሆነን ስንጠብቀው እናቱ መሆኔን እንኳን ለመናገር
አለመቻሌ እንደ ሞተም ቤተሰቡ ሁሉ ሰምቶ ሲደናገጥ የኔን የወላጅ እናቱን ኀዘን ሳይሆን የስዋን ትንሽ መጠነኛ ኀዘን ነበር የምታጽናኑት " እኔ ባሁኑ ጊዜ ከዚህ ቤት ችየው የኖርኩት ፈተና የሞት ያህል መራራና አስጨናቂ ነበር "
“ለምን ተመልሰሽ መጣሽ ? ” አላት "
“ ነገርኩህ እኮ ካንተና ከልጆቼ ተለይቸ መኖር አልቻልኩም '
“ስሕተት ነበር ! ፍጹም ስሕተት ነበር የሠራሽው
👍10
በጣም ስሕተት ነበር እውነትህን ነው ግን ማንነቴን እንዳይታወቅ ያዶረግሁት ጥንቃቄ እስከተሳካ ድረስ የስሕተቱን ውጤት የተቀበልኩት የቅጣቱን ጽዋ የጠጣሁት እኔ ብቻ ነኝ ሞት እናቴን እንዳደረጋት እኔንም ሳላስበው ድንገት ዘሎ አነቀኝ እንጂ እኔ እስክ ሞት ድረስ ከዚህ ቤት እቆያለሁ የሚል hሳብ አልነበረኝም "
“ እንዳልከው ፍጹም ጥፋት ነው አሁን አንተን አስጠርቸ ማነጋገሬ ራሱም ከብዙዎቹ ጥፋቶች አንዱ ነው ነገር ግን እኔ ለዚህ ዓለም ሙት ማለት ስለሆንኩ ወደዚያኛው ለማለፍ አፋፍ
ላይ በማንዣበብ ላይ ስላለሁ አዲሱን ቃል ኪዳንህን የሚነካ አይመስለኝም ግን ባሌ ነበርክ " ነበር...አርኪባልድ ስለዚህ ባለፉት ጥቂት ቀኖች ውስጥ ይቅርታህን ለመለመን በጣም ስፈልግህ ነበር "
ምነው ያለፈው ነገር ሁሉ እልም ብሎ በቀረ " ምነው የፈጸምኩት ጥፋት የተቀበልኩት መከራ ሁሉ ቅዠት ሆኖ እልም ብሎ በጠፋና እንደ ዱሮ የምትወዳት ጤነኛና ደስተኛ ሚስትህ ሁኜ በነቃሁ »
"እኔ ወደ ዊልያም እየሔድኩ ነው » ሉሲና አርኪባልድ ይቀራሉ " ራራላቸው ኋላ ለተወለዱት ልጆችህ አድልተህ ፍቅርህን እንዳትቀንስባቸው " በኔ ጥፋት እነሱን አትጥላቸው
በናታቸው ዐይን አትያቸው ”
" ይህን አደራ ሊያናግርሽ የሚችል ምልክት አየሽብኝ?ልጆቹን አሁንም ልክ አንቺን እወድሽ እንደ ነበረው ያህል አወዳቸዋለሁ "
"አርኪባልድ...ወደሚቀጥው ዓለም ለመሔድ ከደፉ ላይ ቁሜአለሁ" አልፌው ከመሔዴ በፊት አንድ የፍቅር ቃል አትተነፍስሽልዥምን ? የዛሬውን ማንነቴን ለጊዜው ከአእምሮህ አውጣውና ብትችል ስለዚያች ሚስትህ ስለአደረግሃት ጠባየ ንጽሕት ለስላሳ ልጅ ለማስብ ሞክርና ፡ አንድ መልካም ቃል ብለህ ተሰናበተኝ "
“ ሳቤላ.. መጀመሪያ ጥለሽኝ የሔድሽ ጊዜ ልቤ በኀዘን ሊፈርስልሽ ምንም
አልቀረም ነበር " ሆኖም' " እኔ አሁን አንቺን በሙሉ ልቤ ይቅር እንዳልኩሽ ሁሎ እኔንም እንደዚሁ ያድርግልኝ
“ በል ዳግመኛ እንገናኛለን አብረንም እስከ ዘለዓለም እንኖራለን ዊልያም
አናቴ ከወንዙ ዳር ትፈልገኛለች ብሎ ነበር » ነገር ግን ዊልያም ነው አሁን እኔን በመፈለግ ላይ ያለው"
ሚስተር ካርላይል ሁለት እጆቹን ይዛው ስለ ነበር አንዱን አስለቅቆ ከግንባሯ ላይ ችፍፍ ያለውን የሞት ጤዛ በገዛ መሐረቡ ጠረገላት …
“ በል አርኪባልድ ቅጣቴን ከዚሀ ጨርሻለሁ ሁላችንም ከዚያ እንገናኛለን እኛም ልጆቻችንም ለዘለዓለም እንኖራለን " ይኸውም ከዚያ ሔዶ መዳር መጋባት የለምና ኃጢአት አይሆንም " አንተ ግን ለዚያች በከንቱ ለቀረችው ላንተይቱ ሳቤላ ከልብህ ውስጥ ትንሽ የትዝታ ማዕዘን ከልለህ ያዝላት። ”
'' እሺ እሺ !” አለ በሹክሹክታ "
“ መሔድህ ነው ? ” አለች እየቃተተች"
“ በጣም እየደከመሽ ነው ' ዕርዳታ መፈለግ አለብኝ „ ”
"በል እንግዲያው ደኅና ሁን እስከ መረሻው ደኀና ሁን” አለችው በረጅሙ ተንፍሳ ዕንባዋ ሳያቋርጥ እንደ ዝናብ መውረዱን ቀጠለ “ነገሩ የሞት አንጂ የዝለት አይመስለኝም " አዬ ጉድ መለያየት ጭንቅ ነው " ደኅና ሁን...ደኅና ሁን የዱሮው ውድ ባሌ "
ደግፏት የነበረውን ትራስ ለቃ ቀና አለች » የመንፈሷ መሸበር ብርታትን ሰጣት - ከክንዱ ተጠመጠመችበትና ናፍቆት የጎዳውን ፊቱን ቀና አድርጋ አየችው ሚስተር ካርላይል ቀስ አድርጎ መልሶ አስተኛትና ከንፈሮቹን በከንፈሮቿ ላይ ማረፋቸውን ቻለ።
“ እስከ ዘለዓለም ” አለ በሹክሹክታ ።
ምልስ ብሎ ከክፍሉ እስኪወጣ ድረስ በዐይኗ ስትከተለው ቆየችና ፊቷ
ወደ ግድግዳው አዞረች “ በቃ አለቀ ” አለች "
ሚስተር ካርይል እንደ ወጣ ከደረጃው ላይ ቁሞ ከራሱ ጋር ትንሽ መከሪና ጆይስን ወደ በሽተኛይቱ እንድትሔድላት ጠቀሳት " እኀቱ ከበራፍ ቁማ ነበር
“ ኮርኒሊያ ” ብሎ ጠራትና ወደ ምግብ ቤት ተከትላው ገባች "
“ ዛሬ ከዚህ ታድሪያለሽ ? ከሷ ጋር ''
" ደግሞ ለዚህ ትጠራጠር ኖረሃል ? አሁን ወዴት ልትሔድ ነው ?” አለችው
“ሎርድ ማውንት እስቨርንን ለመጥራት ወደ ቴሌግራፍ ቤት መሔዴነው…”
“ ምነው ሌላ ሰው አትልክም? ራትህ እንደ ቀረበ ሳትቀምስለት እንዳለ
ይጠብቅሃል።
ወደ ጠረጴዛው ያለ ልቡ ዞር ብሎ አየና፡ ለኮርኒሊያም ያልተሰማ መልስ አልጎምጉሞ ወቶ ሔደ ።
ሊመለስ እኅቱ ከመተላለፊያው ጠብቃ ካጠገቧ ከነበረው አንድ ክፍል ይዛው ገባች » በሩን ዘጋች ሳቤላ ከዐሥር ደቂቃ በፊት ሕይወቷ ማለፉን ነገረችው
“ አንተ ከወጣህ አንድም ቃል አልተናገረችም አርኪባልድ " መጨረሻ
ላይ ትንፋቯ ሲዘጋ ትንሽ ተወራጨች እንጂ በሰላም ሔደች "
ሎርድ ማውንት እስቨርን በአስቸኳይ የተጠራበት ምክንያት ለምን እንደሆነ
እያሰበ ምንም ጊዜ ሳያባክን ገሥግሶ በበነጋታው ጧት ደረስ ሚስተር ካርላይል
ዝግ ሠረገላውን ይዞ ከጣቢያ ጠብቆ ተቀበለው ወደ ኢስትሊን ሲመጡ በመንገድ አረዳው ኧርሉ ነገሩ ሊገባው አልቻለም " ሲገባው ደግሞ ማመን አቃተው።
" ከቤትህ ለመሞት ነው የመጣችው ? አንተስ አስገባሃት ? እኔ ነገሩ ምንም አልገባኝም ” አለው
ሚስተር ካርላይል ሁኔታውን ጨምሮ አብራራለትና በመጨረሻ ገባው „
“ ምን የሚሉት ዕብደት ነው? እዚህ መምጣት ? ማዳም ቬን እንዴት
ሳትታወቅ ቀረች ? ”
"አልታወቀችም አለ ሚስተር ካርላይል " ማዳም ቬን ከመጀመሪያ ሚስቴ ጋር በመመሳሰሏ ገርሞኝ ነበር" ግን እሷ ትሆናለች ብዬ አልጠረጠርኩም።
መመሳሰሉም ቢሆን መመሳሰል አይባልም " ፊቷ ሁሉ ተለውጦ ነበር " ያልትለወጡት ዐይኖቿንም ያለ መነጽር ዐይቻቸው አላውቅም "
ሎርድ ማውንት እስቨርን ያተኮሰውን ፊቱን ጠረገ " መርዶውን ከምንም
አልቆጠረውም " መሞቷን ቢያውቅም በአድራጐቷ ተናደዶ ሚስዝ ካርላይል ባለመኖሯም ደስ አለው "
“ አሁን ሊያዩዋት ይፈልጋሉ ? " አለው ሚስተር ካርላይል ገና ወደ ቤት ሲገቡ "
“ አዎን"
ሚስተር ካርላይል በሩን ከፈተውና ገቡ " ጆይስና ኮርኒሊያ አስፈላጊውን
ሁሉ አድርገውላታል " ሎርድ ማውንት እስሸርን ጠጋ ብሎ መልኳን አነጻጸረና
ባየው መመሳሰል ተደነቀ
ምን ገደላት ? ” አለው "
እሷ ጎዘን ነው ትል ነበር
“በዚህ ከሆነ ገና ዱሮ ባለመሞቷም ያስደንቃል" ጎዘኗማ ምን ልክ አለው! ”
አዬ ያልታደልሺው ሳቤላ” አለ እጂዋን እየነካ » “ የገዛ ደስታሽን አበላሸሽው ካርላይል ይህ የጋብቻ ቀለበትሀ መሰለኝ "
ሚስተር ካርላይል ወደ ቀለበቱ አየት አድርጎ “ ሳይሆን አይቀርም ' አለ"
“ ምንም ሳታወልቀው መኖሯም የሚገርም ነው ” አለና ይዞት የነበረውን
የ በረዶ እጅዋን ለቀቀው “እኔ ይሀን ታሪክ ማን ይቸግረኛል "
ይኸንንእየተናገረ ከክፍሉ ወጣ " ሚስተር ካርላይል ግንባሯን በጣቶቹ እየነካ ፊቷን ለአንድ ሁለት ደቂቃ ያህል ትክ ብሎ ሲመለከታት ቆናና የገለጠውን ፊት መልሶ ሸፍኖት ወጣ "
ሎርድ ማውንት እስቨርንና ሚስተር ካርላይል ወደ ቁርስ ቤት ወረዱ ሚስ
ካርላይልን ተቀምጣ ስትጠብቃቸው አገኙዋት " " ዐይኖቻቸሁ የት ሔዶው ነው ኧረ ያላወቃችሁዋት ? ” አለ ኧርሉ "
“ የእርስዎ ዐይኖች ከሔዱበት ” አለችው ኮርኒሊያ “ እርስዎ ማዳም ቬንን እኛ እንዳየናት አድርገው አይተዋታል
እኔ ከሁለትና ከሦስት ጊዜ የበለጠ አላየኋትም " ለዚያው ቆቧንና ዐይነ ርግቧን አውጥታ አይቻት አላውቅም ። ካርላይል ግን ለምን ሳያውቃት እንደ ቀረ
ይገርማል ።
“ እንዳልከው ፍጹም ጥፋት ነው አሁን አንተን አስጠርቸ ማነጋገሬ ራሱም ከብዙዎቹ ጥፋቶች አንዱ ነው ነገር ግን እኔ ለዚህ ዓለም ሙት ማለት ስለሆንኩ ወደዚያኛው ለማለፍ አፋፍ
ላይ በማንዣበብ ላይ ስላለሁ አዲሱን ቃል ኪዳንህን የሚነካ አይመስለኝም ግን ባሌ ነበርክ " ነበር...አርኪባልድ ስለዚህ ባለፉት ጥቂት ቀኖች ውስጥ ይቅርታህን ለመለመን በጣም ስፈልግህ ነበር "
ምነው ያለፈው ነገር ሁሉ እልም ብሎ በቀረ " ምነው የፈጸምኩት ጥፋት የተቀበልኩት መከራ ሁሉ ቅዠት ሆኖ እልም ብሎ በጠፋና እንደ ዱሮ የምትወዳት ጤነኛና ደስተኛ ሚስትህ ሁኜ በነቃሁ »
"እኔ ወደ ዊልያም እየሔድኩ ነው » ሉሲና አርኪባልድ ይቀራሉ " ራራላቸው ኋላ ለተወለዱት ልጆችህ አድልተህ ፍቅርህን እንዳትቀንስባቸው " በኔ ጥፋት እነሱን አትጥላቸው
በናታቸው ዐይን አትያቸው ”
" ይህን አደራ ሊያናግርሽ የሚችል ምልክት አየሽብኝ?ልጆቹን አሁንም ልክ አንቺን እወድሽ እንደ ነበረው ያህል አወዳቸዋለሁ "
"አርኪባልድ...ወደሚቀጥው ዓለም ለመሔድ ከደፉ ላይ ቁሜአለሁ" አልፌው ከመሔዴ በፊት አንድ የፍቅር ቃል አትተነፍስሽልዥምን ? የዛሬውን ማንነቴን ለጊዜው ከአእምሮህ አውጣውና ብትችል ስለዚያች ሚስትህ ስለአደረግሃት ጠባየ ንጽሕት ለስላሳ ልጅ ለማስብ ሞክርና ፡ አንድ መልካም ቃል ብለህ ተሰናበተኝ "
“ ሳቤላ.. መጀመሪያ ጥለሽኝ የሔድሽ ጊዜ ልቤ በኀዘን ሊፈርስልሽ ምንም
አልቀረም ነበር " ሆኖም' " እኔ አሁን አንቺን በሙሉ ልቤ ይቅር እንዳልኩሽ ሁሎ እኔንም እንደዚሁ ያድርግልኝ
“ በል ዳግመኛ እንገናኛለን አብረንም እስከ ዘለዓለም እንኖራለን ዊልያም
አናቴ ከወንዙ ዳር ትፈልገኛለች ብሎ ነበር » ነገር ግን ዊልያም ነው አሁን እኔን በመፈለግ ላይ ያለው"
ሚስተር ካርላይል ሁለት እጆቹን ይዛው ስለ ነበር አንዱን አስለቅቆ ከግንባሯ ላይ ችፍፍ ያለውን የሞት ጤዛ በገዛ መሐረቡ ጠረገላት …
“ በል አርኪባልድ ቅጣቴን ከዚሀ ጨርሻለሁ ሁላችንም ከዚያ እንገናኛለን እኛም ልጆቻችንም ለዘለዓለም እንኖራለን " ይኸውም ከዚያ ሔዶ መዳር መጋባት የለምና ኃጢአት አይሆንም " አንተ ግን ለዚያች በከንቱ ለቀረችው ላንተይቱ ሳቤላ ከልብህ ውስጥ ትንሽ የትዝታ ማዕዘን ከልለህ ያዝላት። ”
'' እሺ እሺ !” አለ በሹክሹክታ "
“ መሔድህ ነው ? ” አለች እየቃተተች"
“ በጣም እየደከመሽ ነው ' ዕርዳታ መፈለግ አለብኝ „ ”
"በል እንግዲያው ደኅና ሁን እስከ መረሻው ደኀና ሁን” አለችው በረጅሙ ተንፍሳ ዕንባዋ ሳያቋርጥ እንደ ዝናብ መውረዱን ቀጠለ “ነገሩ የሞት አንጂ የዝለት አይመስለኝም " አዬ ጉድ መለያየት ጭንቅ ነው " ደኅና ሁን...ደኅና ሁን የዱሮው ውድ ባሌ "
ደግፏት የነበረውን ትራስ ለቃ ቀና አለች » የመንፈሷ መሸበር ብርታትን ሰጣት - ከክንዱ ተጠመጠመችበትና ናፍቆት የጎዳውን ፊቱን ቀና አድርጋ አየችው ሚስተር ካርላይል ቀስ አድርጎ መልሶ አስተኛትና ከንፈሮቹን በከንፈሮቿ ላይ ማረፋቸውን ቻለ።
“ እስከ ዘለዓለም ” አለ በሹክሹክታ ።
ምልስ ብሎ ከክፍሉ እስኪወጣ ድረስ በዐይኗ ስትከተለው ቆየችና ፊቷ
ወደ ግድግዳው አዞረች “ በቃ አለቀ ” አለች "
ሚስተር ካርይል እንደ ወጣ ከደረጃው ላይ ቁሞ ከራሱ ጋር ትንሽ መከሪና ጆይስን ወደ በሽተኛይቱ እንድትሔድላት ጠቀሳት " እኀቱ ከበራፍ ቁማ ነበር
“ ኮርኒሊያ ” ብሎ ጠራትና ወደ ምግብ ቤት ተከትላው ገባች "
“ ዛሬ ከዚህ ታድሪያለሽ ? ከሷ ጋር ''
" ደግሞ ለዚህ ትጠራጠር ኖረሃል ? አሁን ወዴት ልትሔድ ነው ?” አለችው
“ሎርድ ማውንት እስቨርንን ለመጥራት ወደ ቴሌግራፍ ቤት መሔዴነው…”
“ ምነው ሌላ ሰው አትልክም? ራትህ እንደ ቀረበ ሳትቀምስለት እንዳለ
ይጠብቅሃል።
ወደ ጠረጴዛው ያለ ልቡ ዞር ብሎ አየና፡ ለኮርኒሊያም ያልተሰማ መልስ አልጎምጉሞ ወቶ ሔደ ።
ሊመለስ እኅቱ ከመተላለፊያው ጠብቃ ካጠገቧ ከነበረው አንድ ክፍል ይዛው ገባች » በሩን ዘጋች ሳቤላ ከዐሥር ደቂቃ በፊት ሕይወቷ ማለፉን ነገረችው
“ አንተ ከወጣህ አንድም ቃል አልተናገረችም አርኪባልድ " መጨረሻ
ላይ ትንፋቯ ሲዘጋ ትንሽ ተወራጨች እንጂ በሰላም ሔደች "
ሎርድ ማውንት እስቨርን በአስቸኳይ የተጠራበት ምክንያት ለምን እንደሆነ
እያሰበ ምንም ጊዜ ሳያባክን ገሥግሶ በበነጋታው ጧት ደረስ ሚስተር ካርላይል
ዝግ ሠረገላውን ይዞ ከጣቢያ ጠብቆ ተቀበለው ወደ ኢስትሊን ሲመጡ በመንገድ አረዳው ኧርሉ ነገሩ ሊገባው አልቻለም " ሲገባው ደግሞ ማመን አቃተው።
" ከቤትህ ለመሞት ነው የመጣችው ? አንተስ አስገባሃት ? እኔ ነገሩ ምንም አልገባኝም ” አለው
ሚስተር ካርላይል ሁኔታውን ጨምሮ አብራራለትና በመጨረሻ ገባው „
“ ምን የሚሉት ዕብደት ነው? እዚህ መምጣት ? ማዳም ቬን እንዴት
ሳትታወቅ ቀረች ? ”
"አልታወቀችም አለ ሚስተር ካርላይል " ማዳም ቬን ከመጀመሪያ ሚስቴ ጋር በመመሳሰሏ ገርሞኝ ነበር" ግን እሷ ትሆናለች ብዬ አልጠረጠርኩም።
መመሳሰሉም ቢሆን መመሳሰል አይባልም " ፊቷ ሁሉ ተለውጦ ነበር " ያልትለወጡት ዐይኖቿንም ያለ መነጽር ዐይቻቸው አላውቅም "
ሎርድ ማውንት እስቨርን ያተኮሰውን ፊቱን ጠረገ " መርዶውን ከምንም
አልቆጠረውም " መሞቷን ቢያውቅም በአድራጐቷ ተናደዶ ሚስዝ ካርላይል ባለመኖሯም ደስ አለው "
“ አሁን ሊያዩዋት ይፈልጋሉ ? " አለው ሚስተር ካርላይል ገና ወደ ቤት ሲገቡ "
“ አዎን"
ሚስተር ካርላይል በሩን ከፈተውና ገቡ " ጆይስና ኮርኒሊያ አስፈላጊውን
ሁሉ አድርገውላታል " ሎርድ ማውንት እስሸርን ጠጋ ብሎ መልኳን አነጻጸረና
ባየው መመሳሰል ተደነቀ
ምን ገደላት ? ” አለው "
እሷ ጎዘን ነው ትል ነበር
“በዚህ ከሆነ ገና ዱሮ ባለመሞቷም ያስደንቃል" ጎዘኗማ ምን ልክ አለው! ”
አዬ ያልታደልሺው ሳቤላ” አለ እጂዋን እየነካ » “ የገዛ ደስታሽን አበላሸሽው ካርላይል ይህ የጋብቻ ቀለበትሀ መሰለኝ "
ሚስተር ካርላይል ወደ ቀለበቱ አየት አድርጎ “ ሳይሆን አይቀርም ' አለ"
“ ምንም ሳታወልቀው መኖሯም የሚገርም ነው ” አለና ይዞት የነበረውን
የ በረዶ እጅዋን ለቀቀው “እኔ ይሀን ታሪክ ማን ይቸግረኛል "
ይኸንንእየተናገረ ከክፍሉ ወጣ " ሚስተር ካርላይል ግንባሯን በጣቶቹ እየነካ ፊቷን ለአንድ ሁለት ደቂቃ ያህል ትክ ብሎ ሲመለከታት ቆናና የገለጠውን ፊት መልሶ ሸፍኖት ወጣ "
ሎርድ ማውንት እስቨርንና ሚስተር ካርላይል ወደ ቁርስ ቤት ወረዱ ሚስ
ካርላይልን ተቀምጣ ስትጠብቃቸው አገኙዋት " " ዐይኖቻቸሁ የት ሔዶው ነው ኧረ ያላወቃችሁዋት ? ” አለ ኧርሉ "
“ የእርስዎ ዐይኖች ከሔዱበት ” አለችው ኮርኒሊያ “ እርስዎ ማዳም ቬንን እኛ እንዳየናት አድርገው አይተዋታል
እኔ ከሁለትና ከሦስት ጊዜ የበለጠ አላየኋትም " ለዚያው ቆቧንና ዐይነ ርግቧን አውጥታ አይቻት አላውቅም ። ካርላይል ግን ለምን ሳያውቃት እንደ ቀረ
ይገርማል ።
👍19
“ መናገር ካስፈለገ ሐቅ ምን ጊዜም ሐቅ ነው " ከዚህ በሔደች ጊዜ ገና ወጣት ፊተ ብሩህ ንቁ ጸጉረ ጥቁርና ረጅም ቁመናዋ እንደ ቀስት ቀጥ ያለ
በጠቅላላው በጣም የምታምር ልጅ ነበረች አሁን ደግሞ ማዳም ቬን ተብላ ስትመጣ ፊቷ ገርጥቶ ጐብጣ ' አንክሳ ከእመቤት ሳቤላ አጥራ ልዩ ልዩ የማሳሳቻ ልብስ ደራርባ ተሸፋፍና ፡ ጸጉሯ ሸብቶና ከቆቡ ውስጥ ተጠቅልሎ አፏ ተለዋውጦ ፥ የፊት ጥርሶቿ ወልቀው ንግግሯ ተኮላትፎ ከፍተኛ ለውጥ ደርሶባት ነበር" ይህን ሁሉ አጠቃልለን ስንመለከተው” አለች ሚስ ካርላይል ስታጠቃልል፡
“ያቺ ከዚህ የጠፋችውን ሳቤላ ጨርሳ አትመስልም ነበር። አሁን እርስዎ ..ጌታ
በጣም የሚወዱት ጓደኛዎ በአደጋ ተሰባብሮ እንደሷ ሆኖ ተለዋውጦ ቢያዩት
በቀላሉ ሊያውቁት ይችላሉ ? ” አለችው "
አባባሏ ሎርድ ማውንት እስቨርንን አንድ ነገር አስገነዘበው አንድ በቅርብ
የሚያውቀው ሰውዬ አሠቃቂ አደጋ ደረሰበትና የድሮ መልኩ ጨርሶ ተለዋወጠ" አንደ ሳቤላ እንኳን ተጨማሪ ማሳሳቻ አላደረገም " ነገር ግን የገዛ ቤተሰቦቹም ሊያውቁት አልቻሉም " ይህ በርግጥ የደረሰ እውነተኛ ታሪክ ነው "
“የመልኳን መመሳሰል እንኳን እንደ ተባለው ለመጠርጠር ያስቸግር ይሆናል።ነገር ግን ያንን ሁሉ መሸፋፈኛ ስትደራርብ መንቃት ነበረብን” አለ ሚስተር ካርላይል
እሱንማ ገና እዚህ ቤት እንደገባች ” አለች ሚስ ኮርኒሊያ የገለጠች እንደሆን ራሷን አይኗን ፊቷን ሳይቀር እንደሚያማት ስትናገር ጊዜ ሁሉም አመናት በዚህ በኩል እንዳትጠረጠር በሩን ዘጋችው ከዚህም ሌላ እንድ
ሎርድ ማውንት እስቨርን የዱሲ ቤተሰቦችም
ጀርመን ሳለች አብረዋት ነበሩ » ግን እሷ ትሆናለች ብለው አልጠረጠሩም ሌላው መረሳት የሌለበት ነገር አለ በጣም ከፍተኛ ያሆነ መመሳሰል ብናይባትም አንሥተን አልተነጋገርንበትም " የእመቤት ሳቤላን ስም በሹክክታ እንኳን አንሥተነው አናውቅም " "
እውነት ነው ! ” አለ ሎርድ ማውንት እስቨርን " " የምትይው ሁሉ እውነት ነው።
ሚስተር ካርላይል ዓርብ የሚከተለውን ደብዳቤ ወደ ሚሲዝ ካርላይል ላከ
· የኔፍቅር እሑድ ከሰዓት በኋላ አንቺ ዘንድ እደርሳለሁ ብየሽ የነበረው የማይሳካልኝ ስለሆነ በእሑድ ሌሊት ባቡር እነሰለሁ » ስለዚህ እንዳትጠብቂኝ ሎርድ ማውንት እስቨርን ለጥቂት ቀኖች ወደዚህ መጥተው አብረውኝ አሉ”
መልካም ምኞታቸውን ያቀርቡልሻል "
“ በይ ባርባራ .. አሁን ለአንድ አስደንጋጭ ወሬ ተዘጋጂ' ማዳም ቬን ዐረፈች እኛ እንደሔድን ባንድ ጊዜ አጣድፎ ለሞት አደረሳት ብለው ነገሩኝ። ረቡዕ
ሌሊት ሞተች። ባለመኖርሽ ደስ ብሎኛል . . ምን ጊዜም ያንቺው ነኝ የኔ ፍቅር
አርኪባልድ ካርላይል”
የዌስትሊን ሕዝብ ምስጢሩ አልገባውም" የሎርድ ማውንት እስቨርንና የሚስተር ካርላይል ኀዘንተኞች ሆነው አስከሬኑን አጅበው ሊቀብሩ መምጣት የመጀመሪያው ከቤቱ ሬሳ ስለ ወጣ ሁለተኛው ደግሞ በእንግድነት እንደ ወጣ ለሚስተር ካርላይል ከበሬታ ሲል ያደረገው መስሎ ታየው ።
አስከሬኑ በሠረገላዎች ታጅቦ ክብር ባለው ሁኔታ መጥቶ ሲቀበርም አስተማሪቱ ለቀብሯ ማስፈጸሚያ በቂ ግንዘብ አጠራቅማ ስለተወች ነው ተባለ እሑድ ጧት ካባቷ ጐን ተቀበረች" ለዚሁም የዌስት ሊን ስው ምክንያት አላጣም አጋጣሚ ሆኖ ከኧርል ዊልያም ሼን መቃብር አጠግብ ባዶ ቦታ ስለ ተገኘ ነው ተባለ "
ከዚያም አስቀብረው ሲያበቁ ኧርሎና ሚስተር ካርላይል በጎዘኑ ሠረገላ ተሳፍረው ወደ ኢስት ሊን ተመለሱ "
ከመቃብሯ ላይ ሁለት ጫማ በአንድ ጫማ ተኩል የሆነ ነጭ ዕብነ በረድ
እንዲቆምላትና ሳ. ሜ . ቬ ( ሳቤላ ሜሪ ቬን ) የሚሉ ቀለሞችና ዘመንም እንዲ
ቀረፅበት ወደ ቤት በመመለስ ላይ እያሉ ከመንገድ ተስማሙ "
የቀብሩ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞ በመመለስ ላይ እንዳሉ የአንድ ሌላ ቤተክርስቲያን ደወሎች ማስተጋባት ጀመሩ " ደወሎቹ አንድ ሥርዓተ ተክሊል ሲፈጸም አብሣሪዎች ነበሩ" አፊ ሆሊጆን በሁለት ካህናትና በስድስት የሴት ሚዜዎች
ረዳትነት • ሚስዝ ጂፊን ተብላ ተሠየመች » በመጨረሻ ሚስተር ጂፊን የልቡ ደረሰ "
ኧርሉ ከሰዓት በኋላ ወደ አጀሩ ተመለሰ " ጥቂት ቆይታ ባርባራ ደረሰች
ዊልሰን እመቤቷ ከቤት እስክትገባ ለመቆየት እንኳን ቸኮለች » እንዲያውም ሕፃኒቱን ከሠረገላ ውስጥ ትታት ልትሔድ ምንም አልቀራትም ነበር ያቺ ፈረንሳዊት አስተማሪ ምን እንደ ገደላት ወሬ ለማግኘት ነበር የዊሰን ጥድፊያ ሚስተር ካርላይል ደግሞ ካስበው ጊዜ ቀድመው መምጣታቸው ድንገተኛ ነገር ሆነበት "
“ አንተ ወሬውን ከነገርከኝ በኋላ እንዴት ብዬ እስከ ሰኞ ልሰንብት አርኪባልድ ? ለመሆኑ በምን ሞተች ? መቸም ድንገተኛ ነገር መሆን አለበት 'አለችው "
“ ይመስለኛል” አላት ያለልቡ ሐሳቡ በሌላ ተይዞበት ስለ ነበር እንዴት
እንደሚገልጽላት ማንስ ቢገልጽላት አንደሚሻል ያወጣ ያወርድ ጀመር በመጨረሻ ግን ከሌላ ሰው ከምትሰማ ጊዜ ሳይወስድ ወዲያውኑ እሱ ቢነግራት መሻሉን መረጠ "
“ ግን ምን ሆንክ .. አርኪባልድ ! አመመህ እንዴ ? " አለችው የፊቱን
መለወጥ አይታ "
" አንድ የምነግርሽ ነገር አለኝ . . ባርባራ ” አላት አብረው እንደቆሙ እጂዋን ወደሱ ሳብ አድርጎ " ከሷ መልበሻ ክፍል ነበሩ : “ ረቡዕ ማታ ከቤት ገብቼ
ራት ልበላ ስል ማዳም ቬን በሞት አፋፍ መሆኗን ጆይስ ነገረችኝ "
እኔም ሔጄ መጠየቅ ይገባኛል ብዬ አሰብኩ „
እንዴታ” አለች ባርባራ“ ልክ ነህ !እንዴት ታርጋለህ?”
“ ተነሳሁና ብሔድ እውነትም ደክማ አገኘኋት ግን የጠበቀኝ ሌላ ነገር ነበር ባርባራ ሴትዮይቱ ማዳም ቬን አልነበረችም "
“ማዳም ቬን አልነበረችም ? " አለች ባርባራ ድንግጥ ብላ።
" የድሮዋ ሚስቴ ነበረች ሳቤላ ቬን ”
የባርባራ ፊት መጀመሪያ ደም መሰለ። ቀጠለና ነጭ ዕብነ በረድ መስሎነጣ "
ይዞት የነበረው እጂዋን አስለቀቀችና ስበሰበች ሆኖም የታየባትን መለዋወጥና ያደረገችውን መቁነጥነጥ ልብ ብሎ ያስተዋለ አልመሰለም " ክርኑን ከአሳት መሞቂያው ምድጃ ላይ አስደግፎ ባጭሩ ማብራራቱን ቀጠለ።
“ ከልጆቹ ተለይታ መኖር ስላልቻለች ፈረንሳይ ሳለች የደረሰባት የባቡር አደጋ በጣም ስለ ለወጣትና በተጨማሪም ከጸጉሯ ሽበት ሌላ መነጽሯንና ያለባበሷን
ሁኔታ ቀያይራ እንደማትታወቅ በማመን ማዳም ቬን ተብላ መጣች አለመታወቋን ሳስበው ይገርመኛል እንደዚህ ያለ ታሪክ ከሌላ ብሰማው በጭራሽ አላምንም ነበር «
" አንተስ ጠርጥረህ ነበር ? ” አለችው ብዙ ከተጨነቀች በኋላ "
ባርባራ!ብጠረጥር ኖሮ መቸ ዝም እል ነበር?እሷ ግን ስለ ዐለፈው ድርጊቷና እንደገናም ተመልሳ ስለ መምጣቷ ይቅርታ ለመነችኝ እኔም ከልቤ አልኳት። ለማውንት እስቨርን ቴሌግራፍ ለማድረግ ዌስት ሊን ሔጄ ስመለስ ሙታ
ቆየችኝ " ኀዘን ነው የገደለኝ አለችኝ ግን ባርባራ...በዚህ አንደነቅም "
ሚስተር ካርላይል ዝም አለ። ሚስቱ ፊቷን እንዳያይባት ስትዞር አያት እሱ ግን አሷ ሳታስተውለው ቀስ ብሎ አስተውሉ ተመለከታት አውነትም የመታወክ ምልክት አየባት "
አጆቹን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ቀና ብላ እንድታየው አደረገ "
“ የኔ ፍቅር . . ምንድነው ? "
አርኪባልድ !” አለች ዕንባዋን እያወረደች “እና'ይህ ነር ፍቅርህን
ወስዶብኝ ይሆን ?
ሁለቱን እጆን በአንድ እጁ ይዞ ሌላዉን እጁን ሽንጧ ላይ ጠምጥሞ ከፊቱ
ይዟት ቆመ » አንድም ነገር ሳይናገር ዝም ብሎ ዐይን ዐይኗን ሲያያት ቆየና በመጨረሻ“ እኔስ ሚስቴ በሙሉ ልቧ የምታምነኝ ይመስለኝ ነበር ” አላት።
በጠቅላላው በጣም የምታምር ልጅ ነበረች አሁን ደግሞ ማዳም ቬን ተብላ ስትመጣ ፊቷ ገርጥቶ ጐብጣ ' አንክሳ ከእመቤት ሳቤላ አጥራ ልዩ ልዩ የማሳሳቻ ልብስ ደራርባ ተሸፋፍና ፡ ጸጉሯ ሸብቶና ከቆቡ ውስጥ ተጠቅልሎ አፏ ተለዋውጦ ፥ የፊት ጥርሶቿ ወልቀው ንግግሯ ተኮላትፎ ከፍተኛ ለውጥ ደርሶባት ነበር" ይህን ሁሉ አጠቃልለን ስንመለከተው” አለች ሚስ ካርላይል ስታጠቃልል፡
“ያቺ ከዚህ የጠፋችውን ሳቤላ ጨርሳ አትመስልም ነበር። አሁን እርስዎ ..ጌታ
በጣም የሚወዱት ጓደኛዎ በአደጋ ተሰባብሮ እንደሷ ሆኖ ተለዋውጦ ቢያዩት
በቀላሉ ሊያውቁት ይችላሉ ? ” አለችው "
አባባሏ ሎርድ ማውንት እስቨርንን አንድ ነገር አስገነዘበው አንድ በቅርብ
የሚያውቀው ሰውዬ አሠቃቂ አደጋ ደረሰበትና የድሮ መልኩ ጨርሶ ተለዋወጠ" አንደ ሳቤላ እንኳን ተጨማሪ ማሳሳቻ አላደረገም " ነገር ግን የገዛ ቤተሰቦቹም ሊያውቁት አልቻሉም " ይህ በርግጥ የደረሰ እውነተኛ ታሪክ ነው "
“የመልኳን መመሳሰል እንኳን እንደ ተባለው ለመጠርጠር ያስቸግር ይሆናል።ነገር ግን ያንን ሁሉ መሸፋፈኛ ስትደራርብ መንቃት ነበረብን” አለ ሚስተር ካርላይል
እሱንማ ገና እዚህ ቤት እንደገባች ” አለች ሚስ ኮርኒሊያ የገለጠች እንደሆን ራሷን አይኗን ፊቷን ሳይቀር እንደሚያማት ስትናገር ጊዜ ሁሉም አመናት በዚህ በኩል እንዳትጠረጠር በሩን ዘጋችው ከዚህም ሌላ እንድ
ሎርድ ማውንት እስቨርን የዱሲ ቤተሰቦችም
ጀርመን ሳለች አብረዋት ነበሩ » ግን እሷ ትሆናለች ብለው አልጠረጠሩም ሌላው መረሳት የሌለበት ነገር አለ በጣም ከፍተኛ ያሆነ መመሳሰል ብናይባትም አንሥተን አልተነጋገርንበትም " የእመቤት ሳቤላን ስም በሹክክታ እንኳን አንሥተነው አናውቅም " "
እውነት ነው ! ” አለ ሎርድ ማውንት እስቨርን " " የምትይው ሁሉ እውነት ነው።
ሚስተር ካርላይል ዓርብ የሚከተለውን ደብዳቤ ወደ ሚሲዝ ካርላይል ላከ
· የኔፍቅር እሑድ ከሰዓት በኋላ አንቺ ዘንድ እደርሳለሁ ብየሽ የነበረው የማይሳካልኝ ስለሆነ በእሑድ ሌሊት ባቡር እነሰለሁ » ስለዚህ እንዳትጠብቂኝ ሎርድ ማውንት እስቨርን ለጥቂት ቀኖች ወደዚህ መጥተው አብረውኝ አሉ”
መልካም ምኞታቸውን ያቀርቡልሻል "
“ በይ ባርባራ .. አሁን ለአንድ አስደንጋጭ ወሬ ተዘጋጂ' ማዳም ቬን ዐረፈች እኛ እንደሔድን ባንድ ጊዜ አጣድፎ ለሞት አደረሳት ብለው ነገሩኝ። ረቡዕ
ሌሊት ሞተች። ባለመኖርሽ ደስ ብሎኛል . . ምን ጊዜም ያንቺው ነኝ የኔ ፍቅር
አርኪባልድ ካርላይል”
የዌስትሊን ሕዝብ ምስጢሩ አልገባውም" የሎርድ ማውንት እስቨርንና የሚስተር ካርላይል ኀዘንተኞች ሆነው አስከሬኑን አጅበው ሊቀብሩ መምጣት የመጀመሪያው ከቤቱ ሬሳ ስለ ወጣ ሁለተኛው ደግሞ በእንግድነት እንደ ወጣ ለሚስተር ካርላይል ከበሬታ ሲል ያደረገው መስሎ ታየው ።
አስከሬኑ በሠረገላዎች ታጅቦ ክብር ባለው ሁኔታ መጥቶ ሲቀበርም አስተማሪቱ ለቀብሯ ማስፈጸሚያ በቂ ግንዘብ አጠራቅማ ስለተወች ነው ተባለ እሑድ ጧት ካባቷ ጐን ተቀበረች" ለዚሁም የዌስት ሊን ስው ምክንያት አላጣም አጋጣሚ ሆኖ ከኧርል ዊልያም ሼን መቃብር አጠግብ ባዶ ቦታ ስለ ተገኘ ነው ተባለ "
ከዚያም አስቀብረው ሲያበቁ ኧርሎና ሚስተር ካርላይል በጎዘኑ ሠረገላ ተሳፍረው ወደ ኢስት ሊን ተመለሱ "
ከመቃብሯ ላይ ሁለት ጫማ በአንድ ጫማ ተኩል የሆነ ነጭ ዕብነ በረድ
እንዲቆምላትና ሳ. ሜ . ቬ ( ሳቤላ ሜሪ ቬን ) የሚሉ ቀለሞችና ዘመንም እንዲ
ቀረፅበት ወደ ቤት በመመለስ ላይ እያሉ ከመንገድ ተስማሙ "
የቀብሩ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞ በመመለስ ላይ እንዳሉ የአንድ ሌላ ቤተክርስቲያን ደወሎች ማስተጋባት ጀመሩ " ደወሎቹ አንድ ሥርዓተ ተክሊል ሲፈጸም አብሣሪዎች ነበሩ" አፊ ሆሊጆን በሁለት ካህናትና በስድስት የሴት ሚዜዎች
ረዳትነት • ሚስዝ ጂፊን ተብላ ተሠየመች » በመጨረሻ ሚስተር ጂፊን የልቡ ደረሰ "
ኧርሉ ከሰዓት በኋላ ወደ አጀሩ ተመለሰ " ጥቂት ቆይታ ባርባራ ደረሰች
ዊልሰን እመቤቷ ከቤት እስክትገባ ለመቆየት እንኳን ቸኮለች » እንዲያውም ሕፃኒቱን ከሠረገላ ውስጥ ትታት ልትሔድ ምንም አልቀራትም ነበር ያቺ ፈረንሳዊት አስተማሪ ምን እንደ ገደላት ወሬ ለማግኘት ነበር የዊሰን ጥድፊያ ሚስተር ካርላይል ደግሞ ካስበው ጊዜ ቀድመው መምጣታቸው ድንገተኛ ነገር ሆነበት "
“ አንተ ወሬውን ከነገርከኝ በኋላ እንዴት ብዬ እስከ ሰኞ ልሰንብት አርኪባልድ ? ለመሆኑ በምን ሞተች ? መቸም ድንገተኛ ነገር መሆን አለበት 'አለችው "
“ ይመስለኛል” አላት ያለልቡ ሐሳቡ በሌላ ተይዞበት ስለ ነበር እንዴት
እንደሚገልጽላት ማንስ ቢገልጽላት አንደሚሻል ያወጣ ያወርድ ጀመር በመጨረሻ ግን ከሌላ ሰው ከምትሰማ ጊዜ ሳይወስድ ወዲያውኑ እሱ ቢነግራት መሻሉን መረጠ "
“ ግን ምን ሆንክ .. አርኪባልድ ! አመመህ እንዴ ? " አለችው የፊቱን
መለወጥ አይታ "
" አንድ የምነግርሽ ነገር አለኝ . . ባርባራ ” አላት አብረው እንደቆሙ እጂዋን ወደሱ ሳብ አድርጎ " ከሷ መልበሻ ክፍል ነበሩ : “ ረቡዕ ማታ ከቤት ገብቼ
ራት ልበላ ስል ማዳም ቬን በሞት አፋፍ መሆኗን ጆይስ ነገረችኝ "
እኔም ሔጄ መጠየቅ ይገባኛል ብዬ አሰብኩ „
እንዴታ” አለች ባርባራ“ ልክ ነህ !እንዴት ታርጋለህ?”
“ ተነሳሁና ብሔድ እውነትም ደክማ አገኘኋት ግን የጠበቀኝ ሌላ ነገር ነበር ባርባራ ሴትዮይቱ ማዳም ቬን አልነበረችም "
“ማዳም ቬን አልነበረችም ? " አለች ባርባራ ድንግጥ ብላ።
" የድሮዋ ሚስቴ ነበረች ሳቤላ ቬን ”
የባርባራ ፊት መጀመሪያ ደም መሰለ። ቀጠለና ነጭ ዕብነ በረድ መስሎነጣ "
ይዞት የነበረው እጂዋን አስለቀቀችና ስበሰበች ሆኖም የታየባትን መለዋወጥና ያደረገችውን መቁነጥነጥ ልብ ብሎ ያስተዋለ አልመሰለም " ክርኑን ከአሳት መሞቂያው ምድጃ ላይ አስደግፎ ባጭሩ ማብራራቱን ቀጠለ።
“ ከልጆቹ ተለይታ መኖር ስላልቻለች ፈረንሳይ ሳለች የደረሰባት የባቡር አደጋ በጣም ስለ ለወጣትና በተጨማሪም ከጸጉሯ ሽበት ሌላ መነጽሯንና ያለባበሷን
ሁኔታ ቀያይራ እንደማትታወቅ በማመን ማዳም ቬን ተብላ መጣች አለመታወቋን ሳስበው ይገርመኛል እንደዚህ ያለ ታሪክ ከሌላ ብሰማው በጭራሽ አላምንም ነበር «
" አንተስ ጠርጥረህ ነበር ? ” አለችው ብዙ ከተጨነቀች በኋላ "
ባርባራ!ብጠረጥር ኖሮ መቸ ዝም እል ነበር?እሷ ግን ስለ ዐለፈው ድርጊቷና እንደገናም ተመልሳ ስለ መምጣቷ ይቅርታ ለመነችኝ እኔም ከልቤ አልኳት። ለማውንት እስቨርን ቴሌግራፍ ለማድረግ ዌስት ሊን ሔጄ ስመለስ ሙታ
ቆየችኝ " ኀዘን ነው የገደለኝ አለችኝ ግን ባርባራ...በዚህ አንደነቅም "
ሚስተር ካርላይል ዝም አለ። ሚስቱ ፊቷን እንዳያይባት ስትዞር አያት እሱ ግን አሷ ሳታስተውለው ቀስ ብሎ አስተውሉ ተመለከታት አውነትም የመታወክ ምልክት አየባት "
አጆቹን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ቀና ብላ እንድታየው አደረገ "
“ የኔ ፍቅር . . ምንድነው ? "
አርኪባልድ !” አለች ዕንባዋን እያወረደች “እና'ይህ ነር ፍቅርህን
ወስዶብኝ ይሆን ?
ሁለቱን እጆን በአንድ እጁ ይዞ ሌላዉን እጁን ሽንጧ ላይ ጠምጥሞ ከፊቱ
ይዟት ቆመ » አንድም ነገር ሳይናገር ዝም ብሎ ዐይን ዐይኗን ሲያያት ቆየና በመጨረሻ“ እኔስ ሚስቴ በሙሉ ልቧ የምታምነኝ ይመስለኝ ነበር ” አላት።
👍12
አዎን አምንሃለሁ እንደማምንህ አንተም ታቃለህ . . አርኪባልድ”
ይቅርታ አድርግልኝ ” ብላ ከደረቱ ተደግፋ ቀስ ብላ አለቃቀስችና ቀና ብላ አየችው።
“ የኔ ሚስት " የኔ ፍቅር • አሁንም ሁልጊዜም "
“ ልቤን በዚህ በማሻከሬ አዝናለሁ የማይረባ አስተሳሰብ ነው. .
አርኪባልድ አሁን ግን ዐለፈ
" እንደዚህ ያለ ስሜት ዳግመኛ እንዳይመጣ
... ባርባራ “ ስሟም ሁለተኛ በመኻላችን መነሣት ኢያስፈልገውም እስከ ዛሬም እንዳይወሳ የተከለከለ ነበር " እንግዲህም ቢሆን አይነሣም "
" አንተ ያልከው ሁሉ ይሁን " ዋናው ምኞቴ አንተን በማስደስት ለፍቅርህና
ለአክብሮትህ ብቁ ሁኘ ለመገኘት ነው አርኪባልድ . . .በልጆችህ እንኳን ዐይነት ስሜት አድሮብኝ ነበር ገባህ አስተሳሰቤ ምን ያህል የተሳሳተ እንደ ነበር አውቄዋለሁ » ለማረም ከልቤ ጥሬአለሁ ። በሚገባ ሞክሬአለሁ " አሁን
ጨርሶ ሊለወጥ ምንም አልቀረውም " ልክ እንደ ልጆቼ ልወዳቸው ' ልንከባከባቸው ' እንዲረዳኝ ሁልጊዜ እጸልያለሁ " "
እንድናገኘው ከልባችን የምንመኘውና የምንታገልለት መልካም ነገር ሁሉ ጊዜውን ጠብቆ ይደርሳል” አለ ሚስተር ካርላይል ” ሰማሽ ባርባራ . .ምንም ቢሆን መርሳት የማይገባሽ አንድ ነገር አለ " በመጨረሻ የተረጋገጠ ሰላም ለማግኘት ሳይስገበገቡ መልካም ሥራ ለመሥራት ያለ ማቋረጥ መታገል ማስፈለጉን አትርሺ።
💫ተ..ፈ..ፀ..መ💫
አሰተያየታችሁን እጠብቃለሁ።
ይቅርታ አድርግልኝ ” ብላ ከደረቱ ተደግፋ ቀስ ብላ አለቃቀስችና ቀና ብላ አየችው።
“ የኔ ሚስት " የኔ ፍቅር • አሁንም ሁልጊዜም "
“ ልቤን በዚህ በማሻከሬ አዝናለሁ የማይረባ አስተሳሰብ ነው. .
አርኪባልድ አሁን ግን ዐለፈ
" እንደዚህ ያለ ስሜት ዳግመኛ እንዳይመጣ
... ባርባራ “ ስሟም ሁለተኛ በመኻላችን መነሣት ኢያስፈልገውም እስከ ዛሬም እንዳይወሳ የተከለከለ ነበር " እንግዲህም ቢሆን አይነሣም "
" አንተ ያልከው ሁሉ ይሁን " ዋናው ምኞቴ አንተን በማስደስት ለፍቅርህና
ለአክብሮትህ ብቁ ሁኘ ለመገኘት ነው አርኪባልድ . . .በልጆችህ እንኳን ዐይነት ስሜት አድሮብኝ ነበር ገባህ አስተሳሰቤ ምን ያህል የተሳሳተ እንደ ነበር አውቄዋለሁ » ለማረም ከልቤ ጥሬአለሁ ። በሚገባ ሞክሬአለሁ " አሁን
ጨርሶ ሊለወጥ ምንም አልቀረውም " ልክ እንደ ልጆቼ ልወዳቸው ' ልንከባከባቸው ' እንዲረዳኝ ሁልጊዜ እጸልያለሁ " "
እንድናገኘው ከልባችን የምንመኘውና የምንታገልለት መልካም ነገር ሁሉ ጊዜውን ጠብቆ ይደርሳል” አለ ሚስተር ካርላይል ” ሰማሽ ባርባራ . .ምንም ቢሆን መርሳት የማይገባሽ አንድ ነገር አለ " በመጨረሻ የተረጋገጠ ሰላም ለማግኘት ሳይስገበገቡ መልካም ሥራ ለመሥራት ያለ ማቋረጥ መታገል ማስፈለጉን አትርሺ።
💫ተ..ፈ..ፀ..መ💫
አሰተያየታችሁን እጠብቃለሁ።
👏23👍20🔥2😁2😢1
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ከመሐል አትላንቲክ ወደ ቦትውድ (ካናዳ)
ዳያና ላቭሴይ ባሏ ፎየንስ ላይ አይሮፕላኑን መሳፈሩ በእጅጉ አስቆጥቷታል፡ በመጀመሪያ ዱካዋን እግር በእግር ተከታትሎ በመምጣት መሳቂያ መሳለቂያ ስላደረጋት አፍረት ውስጥ ከቷታል፡ ባሏ እቤታችን እንሂድ ቢላትም ሀሳቧን መለወጥ አትፈልግም ከማርክ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሄድ የወሰነች ብትሆንም መርቪን ግን የመጨረሻ ውሳኔዋ ነው ብሎ መቀበል አልቻለም፡፡ ይሄ ደግሞ በቁርጠኝነቷ ላይ ጥላ አጥልቶበታል፡፡እሱም ውሳኔዋን እንደገና እንድታጤነው ደጋግሞ ስላሳሰባት ውሳኔዋን
በተደጋጋሚ ገልጻለታለች፡፡ በመጨረሻ ግን የአየር ጉዞዋ የሰጣትን ደስታ
ነጥቋታል፡፡
በህይወት አንዴ ብቻ የሚገጥም ከፍቅረኛ ጋር የሚደረግ ጉዞ፡፡
ከሳውዝ ሃምፕተን ሲነሱ የነበረው የነጻነትና የደስታ ስሜት አሁን የለም: መርቪን ከመጣ ወዲህ ምቹው አይሮፕላን፣ ከተለያዩ ተሳፋሪዎች ጋር መቀላቀሉና እጅ የሚያስቆረጥመው ምግብ ደስታ እየሰጣት አይደለም፡መርቪን ባጋጣሚ ሲያልፍ ያየኛል ብላ ስለፈራች ከማርክ ጋር መላፋት፣መተሻሸትና መሳሳም አልቻለችም፡፡ መርቪን የት እንደተቀመጠ አታውቅም፡፡ካሁን አሁን ይመጣ ይሆን እያለች ትበረግጋለች። ማርክ ካሊፎርኒያ ስለሚጠብቃቸው ኑሮ በተስፋ ሲያወራና ሲቀልድ ቆይቶ ጣውንቱ ከሰማይ
እንደወደቀ ሁሉ ድንገት አይሮፕላኑ ውስጥ ጥልቅ ካለ ወዲህ ግን ቀልቡ
ግፍፍ ብሏል፡ አሁን የተነፈሰ ፊኛ መስሏል፡፡ ዳያና አጠገብ ቁጭ ብሎ
አንድም ቃል ሳያነብ የመጽሔቱን ገጾች ያገላብጣል፡፡ ስሜቱ መጎዳቱን ዳያና አይታለች፡፡ አንድ ወቅት ላይ ይዟት እንዲጠፋ ከቆረጠች በኋላ ሃሳቧን ለውጣ ነበር፡፡ አሁን ባሏ ስለመጣ ከእሱ ጋር እሄዳለሁ ብላ ሃሳቧን
የማትለውጥ መሆኗን እርግጠኛ መሆን አልቻለም፡፡
የአየሩ ሁኔታ እየከፋ መምጣቱ ደግሞ ሌላ ራስ ምታት ሆኖባታል
አይሮፕላኑ ልክ ኮረኮንች ላይ እንደሚሄድ መኪና ይንገጫገጫል፡፡ በየሰዉ
ፊት ላይ ፍርሃት ይነበባል፡፡ ተሳፋሪው ሁሉ የሚያወራው ይህንኑ ነው፡
ዳያና ባሏ የት እንደተቀመጠ ማወቅ ፈለገች፡፡ እግረ መንገዴን ባየው እየተዘዋወረች ብትቃኝም መርቪንን የበላው ጅብ አልጮህ አለ፡፡ በመጨረሻ የቀራት ክፍል የሙሽሮቹ ክፍል ብቻ ነው፡፡
የሴቶች መዋቢያ ክፍል ገባች። ክፍሉ ውስጥ ሁለት ወምበሮች ያሉ ሲሆን አንዱ ወንበር ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ ትኳኳላለች፡፡ ዳያና በሩን ልትዘጋ ስትል አይሮፕላኑ ዘጭ ሲል ሚዛኗን ስታ ልትወድቅ ምንም አልቀራትም፡፡ እንደምንም ተንገዳግዳ ሄዳ ባዶው ወምበር ላይ ዘፍ አለች።
‹‹ተረፍሽ?›› ስትል ጠየቀች ሴትየዋ፡፡
‹‹አዎ፣ አመሰግናለሁ›› አለች ዳያና ‹‹አይሮፕላን እንዲህ ሲሆን አልወድም››
‹‹እኔም አልወድም፡ ከዚህ በኋላ ጉዟችን የከፋ እንደሚሆን አንድ ሰው
ነግሮኛል፡ ዶፍ ዝናብ ይጠብቀናል›› አለች፡፡
የአይሮፕላኑ ውዝዋዜ ጋብ ሲል ዳያና ጸጉሯን ማበጠር ጀመረች።
‹‹ሚስስ ላቭሴይ ነሽ አይደለም?›› ስትል ጠየቀች
‹‹አዎ ዳያና በይኝ››
‹‹እኔ ናንሲ ሌኔሃን እባላለሁ:: ፎየንስ ላይ ነው የተሳፈርኩት”
ከሊቨርፑል ካንቺ. . . ከሚስተር ላቭሴይ ጋር ነው የመጣሁት››
‹‹ኦ!›› ዳያና ይህን ስትሰማ ፊቷ በእፍረት ቲማቲም መሰለ፡፡ ‹‹ጓደኛ እንዳገኘ አላወቅሁም ነበር›› አለች በምጸት፡፡
‹‹ይህን አይሮፕላን ለመሳፈር ወደ ሳውዝ ሃምፕተን ለመሄድ ፈልጌ
ሊቨርፑል ላይ መውጫ አጥቼ ስጨነቅ ባለቤትሽን አየር ማረፊያ ላይ
አገኘሁትና እንዲወስደኝ ለመንኩት››
‹‹እንኳን ቀናሽ›› አለች ዳያና፡፡ ‹‹የእሱ መምጣት እኔን እፍረት ውስጥ
ከቶኛል፡፡››
‹‹ማፈር የለብሽም፡፡ ሁለት ወንዶችን በፍቅር ማጥመድሽ ደስ የሚል
ነገር ነው፡፡ እኔ አንድ እንኳን ፍቅረኛ የለኝም፡፡››
ዳያና ናንሲን በመስታወት አየቻት፡፡ ሴትየዋ ቆንጆ ባትባልም የደስ ደስ አላት፡ ጸጉረ ጥቁር ስትሆን ከሰውነቷ ጋር የሚሄድ ልብስ ለብሳለች።
ስትታይ በራሷ የምትተማመን ትመስላለች፡ መርቪን ሊፍት ቢሰጥሽ
አያስገርምም፡ እሱ እንዳንቺ ያለች ሴት ነው የሚፈልገው አለች ዳያና በሆዷ፡፡
‹‹እንዴት ነው ያሳየሽ ባህሪ ጥሩ ነበር?›› ስትል ጠየቀቻት ናንሲን፡፡
‹‹ብዙም ጥሩ አልነበረም›› አለች በቅሬታ ፈገግታ፡
‹‹አዝናለሁ፡ ይህ ባህሪው ነው የሚያስጠቃው›› አለችና ሊፒስቲኳን ጨረገች
‹‹ሆኖም በችግሬ ጊዜ ስለደረሰልኝ ባለውለታዬ ነው›› አለችና ናንሲ
ተናፈጠች፡ ናንሲ ቀለበት ማሰሯን ዳያና አጤነች፡፡ ‹‹ትህትና ባይኖረውም
ጥሩ ሰው ይመስላል፡፡ ራትም ጋብዞኛል፡ ጨዋታ ያውቃል፡፡ የሴት ልጅን
ልብ የሚሰርቅ ቁመናና መልክ አለው›› አለች፡፡
ጥሩ ሰው ቢሆንም….... አለች ዳያና ‹‹ሰው ይንቃል፡፡ ትዕግስትም የሚባል ነገር ፈጽሞ አልፈጠረበትም፡፡››
ናንሲ ጥቁር ጥቅጥቅ ያለውን ጸጉሯን ታበጥራለች ሽበቷን ለመደበቅ ቀለም ትቀባ ይሆን?› አለች ዳያና በሆዷ።
አንቺን መልሶ በእጁ ለማስገባት ሲል የሚደርስበትን መከራ ለመቀበል ቆርጧል››
‹‹አይደለም ክብሩ ስለተነካ ነው›› አለች ዳያና ‹‹ሌላ ወንድ ስለወሰደኝ ነው ያንጨረጨረው፡፡ ተጋፊ ስለመጣበት ነው ተከትሎኝ የመጣው፡ ጥዬው
እህቴ ቤት ሄጄ ቢሆን ኖሮ እኔን ለመፈለግ እግሩን አያነሳም ነበር››
ናንሲ ሳቀችና ‹‹እንዳነጋገርሽ አንቺን ለማስመለስ ተስፋ ያለው
አይመስልም›› አለች፡፡
‹‹ምንም ተስፋ የለውም›› አለች ዳያና፡፡ ዳያና ድንገት ስሜቷ ስለተረበሸ ከናንሲ ጋር ከዚህ በላይ ማውራት አልፈለገችም፡፡ ሜክአፕና ማበጠሪያዋን ቦርሳዋ ውስጥ ከታታ ለናንሲ ያላት ጥላቻ እንዳይታወቅባት የውሽት ፈገግታ አሳየቻትና ‹‹ወደ ቦታዬ ልሂድ›› ብላ ተነሳች፡፡
‹‹መልካም ዕድል!››
ከሴቶች መዋቢያ ክፍል ስትወጣ ሉሉ ቤልንና ልዕልት ላቪኒያ የመዋቢያ ዕቃዎቻቸውን ያጨቁበትን ቦርሳዎቻቸውን አንጠልጥለው ገቡ፡፡
ወደ ቦታዋ ስትመለስ አስተናጋጁ ዴቭ መቀመጫቸውን ወደ ታጣፊ አልጋ ሲቀይር አየች፡፡ ዳያና አንድ ተራ ሶፋ እንዴት ወደ ተደራራቢ አልጋ ሊቀየር
እንደሚችል ገርሟታል። ዴቭ ከወምበሩ ስር አንሶላና ብርድ ልብስ አወጣና
አነጠፈ፡፡
ተደራራቢ አልጋዎቹ ምቹ ቢሆኑም ከሰው እይታ ውጭ ባለመሆናቸው
ዴቭ መጋረጃ አመጣና ጋረዳቸው፡ ከዚያም በአልጋዎቹ ጎን ትንሽ ታጣፊ
መሰላል አያያዘባቸው፡፡ ዴቭ ይህን የሰራው በሚያስደንቅ ቅልጥፍና ነው፡፡
ዴቭ ወደ ዳያናና ማርክ ዞሮ ፈገግታ ሳይለየው መኝታችሁ እንዲዘጋጅላችሁ ከፈለጋችሁ ንገሩኝና አዘጋጅላችኋለሁ›› አላቸው፡፡
‹‹ተደራራቢ አልጋዎቹ ውስጥ ሲተኙ ሰዎች አይታፈኑም?››
‹‹እያንዳንዱ አልጋ የራሱ አየር ማስገቢያ አለው›› ሲል መለሰ ‹ቀና ብለሽ ብታዪ ያንቺ አልጋ አየር ማስገቢያ አለው፡›› ዳያና ቀና ስትል መስቀያና መዝጊያና መክፈቻ ያለው በብረት ፍርግርግ የተሰራ አየር ማስገቢያ አየች:: "ከዚህ በተጨማሪ›› ሲል ቀጠለ ዴቭ ‹‹የራስሽ መስኮት፣ መብራት፣ የልብስ መስቀያና የመፀሐፍ ማስቀመጫ አለሽ።ከዚህ በተረፈ የምትፈልጊው ነገር
እንዲመጣልሽ ስትፈልጊረመ ይህን ቁልፍ ብትጫኚው ከተፍ እልልሻለሁ›› አላት።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ከመሐል አትላንቲክ ወደ ቦትውድ (ካናዳ)
ዳያና ላቭሴይ ባሏ ፎየንስ ላይ አይሮፕላኑን መሳፈሩ በእጅጉ አስቆጥቷታል፡ በመጀመሪያ ዱካዋን እግር በእግር ተከታትሎ በመምጣት መሳቂያ መሳለቂያ ስላደረጋት አፍረት ውስጥ ከቷታል፡ ባሏ እቤታችን እንሂድ ቢላትም ሀሳቧን መለወጥ አትፈልግም ከማርክ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሄድ የወሰነች ብትሆንም መርቪን ግን የመጨረሻ ውሳኔዋ ነው ብሎ መቀበል አልቻለም፡፡ ይሄ ደግሞ በቁርጠኝነቷ ላይ ጥላ አጥልቶበታል፡፡እሱም ውሳኔዋን እንደገና እንድታጤነው ደጋግሞ ስላሳሰባት ውሳኔዋን
በተደጋጋሚ ገልጻለታለች፡፡ በመጨረሻ ግን የአየር ጉዞዋ የሰጣትን ደስታ
ነጥቋታል፡፡
በህይወት አንዴ ብቻ የሚገጥም ከፍቅረኛ ጋር የሚደረግ ጉዞ፡፡
ከሳውዝ ሃምፕተን ሲነሱ የነበረው የነጻነትና የደስታ ስሜት አሁን የለም: መርቪን ከመጣ ወዲህ ምቹው አይሮፕላን፣ ከተለያዩ ተሳፋሪዎች ጋር መቀላቀሉና እጅ የሚያስቆረጥመው ምግብ ደስታ እየሰጣት አይደለም፡መርቪን ባጋጣሚ ሲያልፍ ያየኛል ብላ ስለፈራች ከማርክ ጋር መላፋት፣መተሻሸትና መሳሳም አልቻለችም፡፡ መርቪን የት እንደተቀመጠ አታውቅም፡፡ካሁን አሁን ይመጣ ይሆን እያለች ትበረግጋለች። ማርክ ካሊፎርኒያ ስለሚጠብቃቸው ኑሮ በተስፋ ሲያወራና ሲቀልድ ቆይቶ ጣውንቱ ከሰማይ
እንደወደቀ ሁሉ ድንገት አይሮፕላኑ ውስጥ ጥልቅ ካለ ወዲህ ግን ቀልቡ
ግፍፍ ብሏል፡ አሁን የተነፈሰ ፊኛ መስሏል፡፡ ዳያና አጠገብ ቁጭ ብሎ
አንድም ቃል ሳያነብ የመጽሔቱን ገጾች ያገላብጣል፡፡ ስሜቱ መጎዳቱን ዳያና አይታለች፡፡ አንድ ወቅት ላይ ይዟት እንዲጠፋ ከቆረጠች በኋላ ሃሳቧን ለውጣ ነበር፡፡ አሁን ባሏ ስለመጣ ከእሱ ጋር እሄዳለሁ ብላ ሃሳቧን
የማትለውጥ መሆኗን እርግጠኛ መሆን አልቻለም፡፡
የአየሩ ሁኔታ እየከፋ መምጣቱ ደግሞ ሌላ ራስ ምታት ሆኖባታል
አይሮፕላኑ ልክ ኮረኮንች ላይ እንደሚሄድ መኪና ይንገጫገጫል፡፡ በየሰዉ
ፊት ላይ ፍርሃት ይነበባል፡፡ ተሳፋሪው ሁሉ የሚያወራው ይህንኑ ነው፡
ዳያና ባሏ የት እንደተቀመጠ ማወቅ ፈለገች፡፡ እግረ መንገዴን ባየው እየተዘዋወረች ብትቃኝም መርቪንን የበላው ጅብ አልጮህ አለ፡፡ በመጨረሻ የቀራት ክፍል የሙሽሮቹ ክፍል ብቻ ነው፡፡
የሴቶች መዋቢያ ክፍል ገባች። ክፍሉ ውስጥ ሁለት ወምበሮች ያሉ ሲሆን አንዱ ወንበር ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ ትኳኳላለች፡፡ ዳያና በሩን ልትዘጋ ስትል አይሮፕላኑ ዘጭ ሲል ሚዛኗን ስታ ልትወድቅ ምንም አልቀራትም፡፡ እንደምንም ተንገዳግዳ ሄዳ ባዶው ወምበር ላይ ዘፍ አለች።
‹‹ተረፍሽ?›› ስትል ጠየቀች ሴትየዋ፡፡
‹‹አዎ፣ አመሰግናለሁ›› አለች ዳያና ‹‹አይሮፕላን እንዲህ ሲሆን አልወድም››
‹‹እኔም አልወድም፡ ከዚህ በኋላ ጉዟችን የከፋ እንደሚሆን አንድ ሰው
ነግሮኛል፡ ዶፍ ዝናብ ይጠብቀናል›› አለች፡፡
የአይሮፕላኑ ውዝዋዜ ጋብ ሲል ዳያና ጸጉሯን ማበጠር ጀመረች።
‹‹ሚስስ ላቭሴይ ነሽ አይደለም?›› ስትል ጠየቀች
‹‹አዎ ዳያና በይኝ››
‹‹እኔ ናንሲ ሌኔሃን እባላለሁ:: ፎየንስ ላይ ነው የተሳፈርኩት”
ከሊቨርፑል ካንቺ. . . ከሚስተር ላቭሴይ ጋር ነው የመጣሁት››
‹‹ኦ!›› ዳያና ይህን ስትሰማ ፊቷ በእፍረት ቲማቲም መሰለ፡፡ ‹‹ጓደኛ እንዳገኘ አላወቅሁም ነበር›› አለች በምጸት፡፡
‹‹ይህን አይሮፕላን ለመሳፈር ወደ ሳውዝ ሃምፕተን ለመሄድ ፈልጌ
ሊቨርፑል ላይ መውጫ አጥቼ ስጨነቅ ባለቤትሽን አየር ማረፊያ ላይ
አገኘሁትና እንዲወስደኝ ለመንኩት››
‹‹እንኳን ቀናሽ›› አለች ዳያና፡፡ ‹‹የእሱ መምጣት እኔን እፍረት ውስጥ
ከቶኛል፡፡››
‹‹ማፈር የለብሽም፡፡ ሁለት ወንዶችን በፍቅር ማጥመድሽ ደስ የሚል
ነገር ነው፡፡ እኔ አንድ እንኳን ፍቅረኛ የለኝም፡፡››
ዳያና ናንሲን በመስታወት አየቻት፡፡ ሴትየዋ ቆንጆ ባትባልም የደስ ደስ አላት፡ ጸጉረ ጥቁር ስትሆን ከሰውነቷ ጋር የሚሄድ ልብስ ለብሳለች።
ስትታይ በራሷ የምትተማመን ትመስላለች፡ መርቪን ሊፍት ቢሰጥሽ
አያስገርምም፡ እሱ እንዳንቺ ያለች ሴት ነው የሚፈልገው አለች ዳያና በሆዷ፡፡
‹‹እንዴት ነው ያሳየሽ ባህሪ ጥሩ ነበር?›› ስትል ጠየቀቻት ናንሲን፡፡
‹‹ብዙም ጥሩ አልነበረም›› አለች በቅሬታ ፈገግታ፡
‹‹አዝናለሁ፡ ይህ ባህሪው ነው የሚያስጠቃው›› አለችና ሊፒስቲኳን ጨረገች
‹‹ሆኖም በችግሬ ጊዜ ስለደረሰልኝ ባለውለታዬ ነው›› አለችና ናንሲ
ተናፈጠች፡ ናንሲ ቀለበት ማሰሯን ዳያና አጤነች፡፡ ‹‹ትህትና ባይኖረውም
ጥሩ ሰው ይመስላል፡፡ ራትም ጋብዞኛል፡ ጨዋታ ያውቃል፡፡ የሴት ልጅን
ልብ የሚሰርቅ ቁመናና መልክ አለው›› አለች፡፡
ጥሩ ሰው ቢሆንም….... አለች ዳያና ‹‹ሰው ይንቃል፡፡ ትዕግስትም የሚባል ነገር ፈጽሞ አልፈጠረበትም፡፡››
ናንሲ ጥቁር ጥቅጥቅ ያለውን ጸጉሯን ታበጥራለች ሽበቷን ለመደበቅ ቀለም ትቀባ ይሆን?› አለች ዳያና በሆዷ።
አንቺን መልሶ በእጁ ለማስገባት ሲል የሚደርስበትን መከራ ለመቀበል ቆርጧል››
‹‹አይደለም ክብሩ ስለተነካ ነው›› አለች ዳያና ‹‹ሌላ ወንድ ስለወሰደኝ ነው ያንጨረጨረው፡፡ ተጋፊ ስለመጣበት ነው ተከትሎኝ የመጣው፡ ጥዬው
እህቴ ቤት ሄጄ ቢሆን ኖሮ እኔን ለመፈለግ እግሩን አያነሳም ነበር››
ናንሲ ሳቀችና ‹‹እንዳነጋገርሽ አንቺን ለማስመለስ ተስፋ ያለው
አይመስልም›› አለች፡፡
‹‹ምንም ተስፋ የለውም›› አለች ዳያና፡፡ ዳያና ድንገት ስሜቷ ስለተረበሸ ከናንሲ ጋር ከዚህ በላይ ማውራት አልፈለገችም፡፡ ሜክአፕና ማበጠሪያዋን ቦርሳዋ ውስጥ ከታታ ለናንሲ ያላት ጥላቻ እንዳይታወቅባት የውሽት ፈገግታ አሳየቻትና ‹‹ወደ ቦታዬ ልሂድ›› ብላ ተነሳች፡፡
‹‹መልካም ዕድል!››
ከሴቶች መዋቢያ ክፍል ስትወጣ ሉሉ ቤልንና ልዕልት ላቪኒያ የመዋቢያ ዕቃዎቻቸውን ያጨቁበትን ቦርሳዎቻቸውን አንጠልጥለው ገቡ፡፡
ወደ ቦታዋ ስትመለስ አስተናጋጁ ዴቭ መቀመጫቸውን ወደ ታጣፊ አልጋ ሲቀይር አየች፡፡ ዳያና አንድ ተራ ሶፋ እንዴት ወደ ተደራራቢ አልጋ ሊቀየር
እንደሚችል ገርሟታል። ዴቭ ከወምበሩ ስር አንሶላና ብርድ ልብስ አወጣና
አነጠፈ፡፡
ተደራራቢ አልጋዎቹ ምቹ ቢሆኑም ከሰው እይታ ውጭ ባለመሆናቸው
ዴቭ መጋረጃ አመጣና ጋረዳቸው፡ ከዚያም በአልጋዎቹ ጎን ትንሽ ታጣፊ
መሰላል አያያዘባቸው፡፡ ዴቭ ይህን የሰራው በሚያስደንቅ ቅልጥፍና ነው፡፡
ዴቭ ወደ ዳያናና ማርክ ዞሮ ፈገግታ ሳይለየው መኝታችሁ እንዲዘጋጅላችሁ ከፈለጋችሁ ንገሩኝና አዘጋጅላችኋለሁ›› አላቸው፡፡
‹‹ተደራራቢ አልጋዎቹ ውስጥ ሲተኙ ሰዎች አይታፈኑም?››
‹‹እያንዳንዱ አልጋ የራሱ አየር ማስገቢያ አለው›› ሲል መለሰ ‹ቀና ብለሽ ብታዪ ያንቺ አልጋ አየር ማስገቢያ አለው፡›› ዳያና ቀና ስትል መስቀያና መዝጊያና መክፈቻ ያለው በብረት ፍርግርግ የተሰራ አየር ማስገቢያ አየች:: "ከዚህ በተጨማሪ›› ሲል ቀጠለ ዴቭ ‹‹የራስሽ መስኮት፣ መብራት፣ የልብስ መስቀያና የመፀሐፍ ማስቀመጫ አለሽ።ከዚህ በተረፈ የምትፈልጊው ነገር
እንዲመጣልሽ ስትፈልጊረመ ይህን ቁልፍ ብትጫኚው ከተፍ እልልሻለሁ›› አላት።
👍10
ዴቭ ፍራንክ ጎርደንና ራስ በራው ኦሊስ ፊልድ ወደ መታጠቢያ ቤት ሲሄዱ አየና የእነሱንም መኝታ ማበጃት ጀመረ።
።።።።።።።።።።።።
ልዕልት ላቪኒያ መሬት የሚጠርግ ፒጃማ ለብሰውና ከእሱ ጋር
የሚሄድ ሻሽ ራሳቸው ላይ ጠምጥመው ከመታጠቢያ ቤት ተመለሱ።
በፒጃማ ሰው ፊት መታየታቸው ምቾት የነሳቸው በመሆኑ ፊታቸውን
ክረምት አስመስለውና ተጀንነው ተኮፍሰዋል። ድፍን የአይሮፕላኑን ሰው በፍርሃት ነው የሚያዩት:
‹‹እዚህ እፍግፍግ ያለ ቦታ ተቀምጬ መሞቴ
ነው›› ሲሉ አማረሩ። ነገር ግን ነገሬ ያላቸው ሰው የለም። ነጠላ ጫማቸውን
አወለቁና ታችኛው አልጋ ላይ ወጡ አጠገባቸው ያሉትን ሰዎች ደህና እደሩ
እንኳን ሳይሉ መጋረጃቸውን ዘጉና ብርድ ልብስ ውስጥ ገብተው ጥቅልል አሉ።
ብዙም ሳይቆዩ ሉሉ ቤል ገላዋን ወለል አድርጎ የሚያሳይ የመኝታ
ልብስ ለብሳ እየተውረገረገች ብቅ አለች: ከፎየንስ ከተሳፈሩ ወዲህ ከዳያናና ከማርክ ጋር የነበራትን መቀራረብ በድርበቡ አድርጋ ከቆየች በኋላ ማርክና ዳያና አጠገብ ቁጭ ብላ ወግ መጠረቅ ጀመረች።
‹‹አጠገባችን ስላሉት ተሳፋሪዎች አንድ ወሬ አግኝቻለሁ›› አለች ወደ
ፊልድና ጎርደን ቦታ እያመለከተች።
ማርክ በፍርሃት ወደ ዳያና አማተረና ‹‹ምን ሰማሽ ሉሉ?›› ሲል ጠየቀ፡
‹‹ሚስተር ፊልድ የኤፍ.ቢ.አይ አባል ነው››
ይሄ ታዲያ ምን ያስደንቃል የኤፍቢ.አይ አባል እኮ ፖሊስ ነው አለች ዳያና በሆዷ።
ሉሉ ወሬዋን ቀጠለች ‹‹ሌላው ጉዳይ ደግሞ ፍራንክ ጎርደን እስረኛ
ነው»
ማርክም ቀጠለና ‹‹ማን ነገረሽ?›› ሊል ጠየቃት፡
‹‹መታጠቢያ ቤት ሁሉም የሚያወራው ይህንኑ ነው››
‹‹ታዲያ ሁሉም ስላወራው እውነት ይሆናል?›› አለ ማርክ።
‹‹እንደማታምኑኝ እኮ አውቃለሁ›› አለች ሉሉ ያ ትንሹ ልጅ ካፒቴኑና ፊልድ ሲጨቃጨቁ ሰምቷል፡ ኤፍ.ቢ.አይ የፓን አሜሪካንን አየር መንገድ ሳያሳውቅ አደገኛ ወንጀለኛ አይሮፕላኑ ላይ ማሳፈሩ ካፒቴኑን እብድ
አድርጎታል፡ በኋላ የፊልድን ትጥቅ የአይሮፕላኑ ሰራተኞች አስፈቱት…››
ዳያና ፊልድ የጎርደን አንጋች መስሏት ነበር፡ ‹‹ጎርደን ጥፋቱ ምንድነው?›› ስትል ጠየቀች፡:
‹‹ማፊያ ነው፡፡ አንድ ሰው ገድሎ፣ አንዲት ሴት አስገድዶ ደፍሮ የምሽት ክበብ በእሳት አጋይቷል፡››
ዳያና የሉሉ ቤልን ወሬ አምና መቀበል ተቸገረች፡ ወጣቱን ሰው ራሷ
አናግራው ነበር፡፡ በእርግጥ ንግግሩ ብዙም የታረመ አይደለም፡፡ ይሄ እውነት
ነው: መልከ መልካምና አለባበሱ ያማረ ነው፡፡ አንድ ጊዜ ልትዳራው ሞክራ
ነበር፡ ምናልባት አጭበርባሪ ይሆናል ወይም በህገወጥ ቁማር ጨዋታ ተይዞ ይሆናል፡ ነገር ግን ሰው ገድሏል የተባለው ሊታመን አይችልም› አለች በሀሳቧ ሉሉ ደግሞ ትልቁንም ትንሹንም ታምናለች፡
‹‹ማመን ያስቸግራል›› አለ ማርክ፡፡
‹‹በሉ ፍቅረኞች›› አለች ሉሉ እጇን በንዴት አወናጭፋ ‹‹ልተኛ ነው፡፡ጎርደን ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍር ከሆነ ቀስቅሱኝ›› አለችና ላይኛው አልጋ ላይ በመሰላል ወጣች፡ መጋረጃውን ከፈተችና ዳያናን ‹‹የኔ ማር አየርላንድ ውስጥ ለምን እንደተናደድሽብኝ ገብቶኛል፡ አውጥቼ አውርጄ ተገልጾልኛል ማርክ ላይ ስላንዣበብኩኝ ነው፡ ከፍቅረኛሽ ጋር እንዳትጫወቺ በወሬ
ጠምጄው አቆይቼዋለሁ፡ ነገር ቶሎ የማይገባኝ ሰው ነኝ፡ ጥፋቴን አርማለሁ፡ አንቺም ቂም አትያዥብኝ፡ ደህና እደሩ›› አለች።
የሉሉ ቤል ንግግር ይቅርታ እንደመጠየቅ ይቆጠራል፡ ዳያናም ይቅር ላለማለት ምክንያት አላገኘችም፡፡ ‹‹ደህና እደሪ ሉሉ›› አለች ዳያና፡፡
ሉሉም መጋረጃዋን ዘጋች፡፡
‹‹እሷ ብቻ አይደለችም፡ እኔም ጥፋተኛ ነኝ፡፡ እኔንም ይቅር በይኝ፡፡ የኔ ፍቅር›› አላት ማርክ፡፡
ዳያና መልስ የመስጠት ያህል ከንፈሩን መጠጠችው፡
ከዚያማ ምን ይወራል! ቀለል እያላት ሲመጣ መላ ሰውነቷ ዘና አለ፡፡
እየሳመችው ወንበሩን ተደገፈች፡፡ እየሳመችው ጡቷ ደረቱን ሲታከክ
ተሰማት፡ እንደገና ገላ ለገላ መተሻሸት መቻሏ ደስታ ፈጥሮላታል፡ በከንፈሩ
ጫፍ ከንፈሯን ሲዳስስ ስሜት ውስጥ ገብታ አፏን ከፍታ ተቀበለችው፡፡ ጫን
ጫን መተንፈስ ጀመረች፡ በእርግጥ የሚያደርጉት ነገር መረን የለቀቀ
መሆኑ ታውቋታል፡ ዓይኗን ስትከፍት መርቪንን አየችው:
በመጀመሪያ እያለፈ ስለነበር አላስተዋላትም ነበር፡ ድንገት ወዳለችበት
ፊቱን ዞር ሲያደርግ ያየው ነገር ከእርምጃው ገታው፡ እሷም ስታየው ፊቷ
በድንጋጤ አመድ ለበሰ፡፡....
✨ይቀጥላል✨
።።።።።።።።።።።።
ልዕልት ላቪኒያ መሬት የሚጠርግ ፒጃማ ለብሰውና ከእሱ ጋር
የሚሄድ ሻሽ ራሳቸው ላይ ጠምጥመው ከመታጠቢያ ቤት ተመለሱ።
በፒጃማ ሰው ፊት መታየታቸው ምቾት የነሳቸው በመሆኑ ፊታቸውን
ክረምት አስመስለውና ተጀንነው ተኮፍሰዋል። ድፍን የአይሮፕላኑን ሰው በፍርሃት ነው የሚያዩት:
‹‹እዚህ እፍግፍግ ያለ ቦታ ተቀምጬ መሞቴ
ነው›› ሲሉ አማረሩ። ነገር ግን ነገሬ ያላቸው ሰው የለም። ነጠላ ጫማቸውን
አወለቁና ታችኛው አልጋ ላይ ወጡ አጠገባቸው ያሉትን ሰዎች ደህና እደሩ
እንኳን ሳይሉ መጋረጃቸውን ዘጉና ብርድ ልብስ ውስጥ ገብተው ጥቅልል አሉ።
ብዙም ሳይቆዩ ሉሉ ቤል ገላዋን ወለል አድርጎ የሚያሳይ የመኝታ
ልብስ ለብሳ እየተውረገረገች ብቅ አለች: ከፎየንስ ከተሳፈሩ ወዲህ ከዳያናና ከማርክ ጋር የነበራትን መቀራረብ በድርበቡ አድርጋ ከቆየች በኋላ ማርክና ዳያና አጠገብ ቁጭ ብላ ወግ መጠረቅ ጀመረች።
‹‹አጠገባችን ስላሉት ተሳፋሪዎች አንድ ወሬ አግኝቻለሁ›› አለች ወደ
ፊልድና ጎርደን ቦታ እያመለከተች።
ማርክ በፍርሃት ወደ ዳያና አማተረና ‹‹ምን ሰማሽ ሉሉ?›› ሲል ጠየቀ፡
‹‹ሚስተር ፊልድ የኤፍ.ቢ.አይ አባል ነው››
ይሄ ታዲያ ምን ያስደንቃል የኤፍቢ.አይ አባል እኮ ፖሊስ ነው አለች ዳያና በሆዷ።
ሉሉ ወሬዋን ቀጠለች ‹‹ሌላው ጉዳይ ደግሞ ፍራንክ ጎርደን እስረኛ
ነው»
ማርክም ቀጠለና ‹‹ማን ነገረሽ?›› ሊል ጠየቃት፡
‹‹መታጠቢያ ቤት ሁሉም የሚያወራው ይህንኑ ነው››
‹‹ታዲያ ሁሉም ስላወራው እውነት ይሆናል?›› አለ ማርክ።
‹‹እንደማታምኑኝ እኮ አውቃለሁ›› አለች ሉሉ ያ ትንሹ ልጅ ካፒቴኑና ፊልድ ሲጨቃጨቁ ሰምቷል፡ ኤፍ.ቢ.አይ የፓን አሜሪካንን አየር መንገድ ሳያሳውቅ አደገኛ ወንጀለኛ አይሮፕላኑ ላይ ማሳፈሩ ካፒቴኑን እብድ
አድርጎታል፡ በኋላ የፊልድን ትጥቅ የአይሮፕላኑ ሰራተኞች አስፈቱት…››
ዳያና ፊልድ የጎርደን አንጋች መስሏት ነበር፡ ‹‹ጎርደን ጥፋቱ ምንድነው?›› ስትል ጠየቀች፡:
‹‹ማፊያ ነው፡፡ አንድ ሰው ገድሎ፣ አንዲት ሴት አስገድዶ ደፍሮ የምሽት ክበብ በእሳት አጋይቷል፡››
ዳያና የሉሉ ቤልን ወሬ አምና መቀበል ተቸገረች፡ ወጣቱን ሰው ራሷ
አናግራው ነበር፡፡ በእርግጥ ንግግሩ ብዙም የታረመ አይደለም፡፡ ይሄ እውነት
ነው: መልከ መልካምና አለባበሱ ያማረ ነው፡፡ አንድ ጊዜ ልትዳራው ሞክራ
ነበር፡ ምናልባት አጭበርባሪ ይሆናል ወይም በህገወጥ ቁማር ጨዋታ ተይዞ ይሆናል፡ ነገር ግን ሰው ገድሏል የተባለው ሊታመን አይችልም› አለች በሀሳቧ ሉሉ ደግሞ ትልቁንም ትንሹንም ታምናለች፡
‹‹ማመን ያስቸግራል›› አለ ማርክ፡፡
‹‹በሉ ፍቅረኞች›› አለች ሉሉ እጇን በንዴት አወናጭፋ ‹‹ልተኛ ነው፡፡ጎርደን ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍር ከሆነ ቀስቅሱኝ›› አለችና ላይኛው አልጋ ላይ በመሰላል ወጣች፡ መጋረጃውን ከፈተችና ዳያናን ‹‹የኔ ማር አየርላንድ ውስጥ ለምን እንደተናደድሽብኝ ገብቶኛል፡ አውጥቼ አውርጄ ተገልጾልኛል ማርክ ላይ ስላንዣበብኩኝ ነው፡ ከፍቅረኛሽ ጋር እንዳትጫወቺ በወሬ
ጠምጄው አቆይቼዋለሁ፡ ነገር ቶሎ የማይገባኝ ሰው ነኝ፡ ጥፋቴን አርማለሁ፡ አንቺም ቂም አትያዥብኝ፡ ደህና እደሩ›› አለች።
የሉሉ ቤል ንግግር ይቅርታ እንደመጠየቅ ይቆጠራል፡ ዳያናም ይቅር ላለማለት ምክንያት አላገኘችም፡፡ ‹‹ደህና እደሪ ሉሉ›› አለች ዳያና፡፡
ሉሉም መጋረጃዋን ዘጋች፡፡
‹‹እሷ ብቻ አይደለችም፡ እኔም ጥፋተኛ ነኝ፡፡ እኔንም ይቅር በይኝ፡፡ የኔ ፍቅር›› አላት ማርክ፡፡
ዳያና መልስ የመስጠት ያህል ከንፈሩን መጠጠችው፡
ከዚያማ ምን ይወራል! ቀለል እያላት ሲመጣ መላ ሰውነቷ ዘና አለ፡፡
እየሳመችው ወንበሩን ተደገፈች፡፡ እየሳመችው ጡቷ ደረቱን ሲታከክ
ተሰማት፡ እንደገና ገላ ለገላ መተሻሸት መቻሏ ደስታ ፈጥሮላታል፡ በከንፈሩ
ጫፍ ከንፈሯን ሲዳስስ ስሜት ውስጥ ገብታ አፏን ከፍታ ተቀበለችው፡፡ ጫን
ጫን መተንፈስ ጀመረች፡ በእርግጥ የሚያደርጉት ነገር መረን የለቀቀ
መሆኑ ታውቋታል፡ ዓይኗን ስትከፍት መርቪንን አየችው:
በመጀመሪያ እያለፈ ስለነበር አላስተዋላትም ነበር፡ ድንገት ወዳለችበት
ፊቱን ዞር ሲያደርግ ያየው ነገር ከእርምጃው ገታው፡ እሷም ስታየው ፊቷ
በድንጋጤ አመድ ለበሰ፡፡....
✨ይቀጥላል✨
👍17
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሀያ ስምንት (28)
እንደሚያፈቅራት ብትፈቅድለትና ፍቅራቸውን ለመካፈል ቢችሉ ደስ እንደሚለው ደጋግሞ ገልጾላታል ። ግን እሷ ልቧን ትጠራጠረዋለች ። በይመስለኛል ስሜት ተገፋፍታ ሳይሆንላት ቢቀር ፒተርን ማስቀየም
ይሆናል ። ይህንን ደግሞ ፈፅሞ አትፈልገውም ። ስለዚህ የፒተር ጥያቄ የኣሺታም የእምቢታም መልስ ሳያገኝ በውዝፍ ዶሴ ተይዞ ቀርቷል ። መዋደዳቸው ፤ መተሳሰባቸው ፤ ጓደኝነታቸው ግን አሌ የሚባል ነገር አይደለም ። «በጣም ናፍቀኸኝ ኖሯል ፒተር» አለች ሜሪ ። ይህን ብላ ህክምና በሚደረግላት ጊዜ እምትቀመጥበት ወንበር ላይ ተቀምጣ ሥራውን እንዲቀጥል ዝግጁ ሆነች ። ዓይኗን ገርበብ አደረገች ። ከወንበሩ ላይ ተነስቶ ትንሽ ከተመለከታት በኋላ « ዛሬ ደግሞ ለመታከም ጥድፊያ በጥድፈያ ሆነሻል » አላት በተለመደው ብርጩማው ላይ ፊት ለፊቷ ተቀመጠ፡፡ « ሁለት ዓመት ሙሉ በፋሻ ስትሸፈን ፤ ፋሻ ሲላጥልክ ብታሳልፍና የመጨረሻው ቀን ቢመጣ አንተ ራስህስ ብትሆን ያንለት ለመገላገል መቻኮልህ ይቀር ነበር ? »
«አይቀርም ፤ እንዲሁ ለማለት ያህል አልኩ እንጂ ነገሩስ ይገባኛል ። ... በደንብ ይገባኛል የኔ መቤት» እግንባሯ ላይ ያለውን ፋሻ ካነሳላት በኋላ ፤ «አሁን አይንሽን መግለጥና ፊትሽን በመስታወት ማየት ትችያለሽ ፣ ሜሪ» አለ ። ሜሪ ግን ካለችበት ላይ ንቅንቅ አላለችም ። ብዙ ዓለም አይታ መጥታለች ። ሆኖም የአዲስ እሷን ፊት ሙሉውን አታውቀውም ። አንደኛው ጐን ቢገለጥ ሌላኛው ወይ በፋሻ ተሸፍኖ ወይ ፕላስተር ተለጥፎበት ወይም ተደርቶ ነበር የምታየው። «በያ ብድግ በይና ወደ መስታወቱ ቅረቢ» አለ ፒተር ያን አዲስ ፊት ፤ ያን ናንሲ ማክአሊስተር የነበረችውን የቀድሞ እሷን ሳይሆን ሜሪ አዳምሰን የተባለችውን አዲስ እሷን ለማየት ፍርሃት ተጫናት ። ምን ያለ የማይረባ ፍርሃት ነው አለች በሐሳቧ። ፍርሃቷን እሸንፋ ተነሳች ። ፊቷን በመስታወቱ ውስጥ ስታይ ፊቷ በሳቅ ቧ ብሎ ተከፈተ ። በጉንጯ ላይ ግን እንባዋ ይጐርፍ ነበር ። ይህ የስሜት ግንፈላ ተግ እስኪልላት ድረስ አልተጠጋትም ። አላነገራትም ። ያ ጊዜ የግሏ የሆነ ማንም ሊጋራት የማይገባ ጊዜ እንደሆነ በመገንዘብ ። «ፒተር ፤ እረ የፈጣሪ ያለህ ! እንዴት ቆንጆ ነው አለች ። «አይ አንቺ ቂል ፍጡር» አለ ፒተር በለሆሳስ እየሳቀ «እንዴት ቆንጆ ነው ሳይሆን እንዴት ቆንጆ ነኝ በይ… ያቺ የምታያት ሌላ ሰው ወይ ሌላ ነገር አይደለችም ። አንቺ ነሽ ራስሽ ነሽ›› ዞራ አየችው ። የተናገረው ትክክል እንደሆነ በቃላት መግለጽ አቃታት ። ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች ። ልክ ነው ። ሙሉ በሙሉ ተቀይራለች ። ከምታውቀው መልኳ የቀረ ቅንጣት ምልክት የለም ። አሁን ያላንዳች ማወላወል ሜሪ አዳምሰን ነኝ ስትል አመነች
«ፒተር !...» አለች ውለታ በበዛበት ድምጽ ። ሄዳ ተጠመጠመችበት ። ተቃቅፈው ብዙ ጊዜ ቆዩ ። በመጨረሻ ፊቷን ለማየት እስኪችል ድረስ በክንዶቿ ይዞ ራቅ አደረጋት ። ፈቷ በእንባ ርሷል ። በጣቶቹ ጠረገላት ። «ፒተር. . . አየህ እንባየ እንኳ ፊቱን አላሟሟውም ! » አለች ። «ያ ብቻ ሳይሆን በትንሽ በትንሹ ይሁን እንጂ ፀሐይም መሞቅ ትችያለሽ» አላት ። ከዚያ በኋላ ግን ዕድሜሽን በሙሉ የፈለግሽውን ነገር ማድረግ ትችያለሽ ። ደስ ያለሽን ብትሆኝ ምንም አደጋ አይኖርም ። በነገራችን ላይ ምን ለማድረግ ነው እቅድሽ ? »
ይህን ብላ እተሽከርካሪው ወንበር ላይ ተቀምጣ ፤ እግሯ ጉንጯን ነክቶ ከራሷ በላይ እስኪሆን ሽቅብ አንስታ ከወንበሩ ጋር መሽከርከር ጀመፎች ። «አምላኬ እስቲ ይኸን ምን ትለዋለህ ? ሴትዮዋ እቢሮዬ ውስጥ ገብታ አንድ አካሏ ቢጐድል ሰው ምን ይለኛል ። አበጀህ እንኳን ይለኝ ይሆን ?»
«አትፍራ እኔ እንደሆነ ዛሬ የመጣው ቢመጣ ጥርሴ እረገፈ ፤ እግሬ ተሰበረ ... ካሣ ምናምን እንደማልል ይግባህ ።የማከብረው እንጂ የምጨቃጨቅበት ቀን አይደለም»
«እንዲያም ከሆነ መልካም ። ይህ ቀን ዓመት ባልሽ መሆኑን መስማቴ ደሞ በጣም ደስ አስኝቶኛል » ፒተር ብቻ ሳይሆን ፍሬድም (ውሻው) በሆነው ነገር ደስ ያለው ይመስላል ። ይዘላል ፤ ይቧርቃል ፤ ጭራውን ይቆላል። የተናገርኩት ስለገባው ነው አለች ውሻውን እያሰበች ። ከዚያም ጨብጠኝ እንደማለት እጅዋን እየዘረጋችለት ፣ «አላወክም ነበር ማለት ነው ጅሎ !. ይህን ዕለት ለማክበር ለራሳችን ጢን ያለ የምሳ ግብዣ እናደርጋለን ፒተር›› አለች ። ስሙን ከጠራችው በኋላ ሙሉ በሙሉ እያየችው «ፒተር ውለታህን ልከፍልህ የምችል አይመስለኝም ። ግን ደግሞ እስከመቃብር ከልቤ አትጠፋም ። መቼም ቢሆን የትም ቢሆን አስታውስሃለሁ ። በበድን አካሌ ነፍስ የዘራህባት አንተ ነህ» አለች ።
«አ…እ… እኔ ሳልሆን ሌላ ሰው ነው» አለ ፒተር ። አዎ ማሪዮን ሂልያርድ ፤ የማይክል እናት ናት ፤ ይህ ሁሉ እንዲሆን ያደረገችው። ግን ደግሞ ሜሪ ማሪዮንን ምን ያህል እንደምትጠላት ስለሚያውቅ ስሟን ሊጠራ አልፈላገም ። ሌላ ሰው ብሎ ጠራት ።
ቀጥሎም...
«እኔ. .. እኔ በበኩሌ ግን ሜሪ… ያደረግኩልሽን ሁሉ ስላደረኩልሽ ደስ ይለኛል ። ለወደፊቱም ላደርግልሽ የምትፈልጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ» አለ ። «ነው?... ቀልድ መስሎሃል ፤ አደል ? እንዲያውም ከዛሬ እንጀምራለን ፤ ዛሬ በስድስት ሰዓት ተኩል ተገናኝተን ምሳዬን እንድታጐርሰኝ እፈልጋለሁ ። እሺ?»
«ደስ ይለኛል»
«የት እንገናኝ ? » አንድ በቅርብ የተከፈተ ምግብ ቤት ጠቀሰላትና ታውቀው እንደሆነ ጠየቃት ።
«በሚገባ !» አለች ።
«ይስማማሻል ?››
«አሳምሮ ። እንዲያውም ካሁን ጀምሬ ወደዚያው አካባቢ ሄጂ ሰዓቱ እስኪደርስ ፎቶግራፍ ሳነሳ እቆያለሁ፡፡ አይን የሚገባ ነገር ከተገኘ»
«አሁን የልቤን ምኞት ነገርሺኝ ። ገበያ ሄጄ አዲስ ልብስ ስመርጥ ወይም ሌላ ብትይኝ ኖር ይከፋኝ ነበር» ተሰነባብተው ተለያዩ ፤ እስከምሳ ሰዓት ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በምሳ ሰዓት ሲገናኙ ልብሷን ቀይራ ሽክ ብላ አገኛት ። «በእውነት ይቺ ሴት አንቺው ራስሽ ነሽ ?»
«ባለወርቅ ጫማዋ ልዕልት እነሆኝ ፡። እንዴት ነው ፤ አምሮብኛል ?»
«አምሮብኛል !? እንደ ቅዱሳን አንፀባርቀሻል እንጂ ፤ ምንማማር ብቻ! ... እንደፈራሁት ፎቶ ግራፍ ማነሳሳቱን ትተሽ ቀሚስ መረጣ ላይ ዋልሽ ልበል?»
«ምን ይደረግ ትላለህ ። ሳስበው ለካ ይህ ቀን የሚከበር ፌስታ የሚደረግበት እንጂ የሚሠራበት አይደለም» ድንገት አቅፈህ ሳማት የሚል ሐሳብ መጣበት ፤ እምግብ ቤቱ ውስጥ ያ ሁሉ ሰው እያዬ ። ሐሳቡን ገታና እጅዋን ጥብቅ አድርጐ ያዛት ። «ውዴ ይህን ያህል ደስ ብሎሽ ስላየሁ እኔንም እጅግ ደስ አለኝ» ኣለ ። «ፒተር በጣም ደስ ብሎኛል ። የዛሬዋ ቀን ለኔ ልዩ ናት። ስለገጽታዬ ብቻ አይምሰልህ ። የዛሬ ቀን. . . ነገ የፎቶግራፍ ተርኢት የማቀርብበት ፤ ኤግዚቢሽኔ የሚከፈትበት ቀንም ስለሆነ... አዲስ ሕይወት መጀመሬም ነው።... አንተም አጠገቤ እንዳለህና ድንቅ እንደሆንክ ስለማውቅ»
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሀያ ስምንት (28)
እንደሚያፈቅራት ብትፈቅድለትና ፍቅራቸውን ለመካፈል ቢችሉ ደስ እንደሚለው ደጋግሞ ገልጾላታል ። ግን እሷ ልቧን ትጠራጠረዋለች ። በይመስለኛል ስሜት ተገፋፍታ ሳይሆንላት ቢቀር ፒተርን ማስቀየም
ይሆናል ። ይህንን ደግሞ ፈፅሞ አትፈልገውም ። ስለዚህ የፒተር ጥያቄ የኣሺታም የእምቢታም መልስ ሳያገኝ በውዝፍ ዶሴ ተይዞ ቀርቷል ። መዋደዳቸው ፤ መተሳሰባቸው ፤ ጓደኝነታቸው ግን አሌ የሚባል ነገር አይደለም ። «በጣም ናፍቀኸኝ ኖሯል ፒተር» አለች ሜሪ ። ይህን ብላ ህክምና በሚደረግላት ጊዜ እምትቀመጥበት ወንበር ላይ ተቀምጣ ሥራውን እንዲቀጥል ዝግጁ ሆነች ። ዓይኗን ገርበብ አደረገች ። ከወንበሩ ላይ ተነስቶ ትንሽ ከተመለከታት በኋላ « ዛሬ ደግሞ ለመታከም ጥድፊያ በጥድፈያ ሆነሻል » አላት በተለመደው ብርጩማው ላይ ፊት ለፊቷ ተቀመጠ፡፡ « ሁለት ዓመት ሙሉ በፋሻ ስትሸፈን ፤ ፋሻ ሲላጥልክ ብታሳልፍና የመጨረሻው ቀን ቢመጣ አንተ ራስህስ ብትሆን ያንለት ለመገላገል መቻኮልህ ይቀር ነበር ? »
«አይቀርም ፤ እንዲሁ ለማለት ያህል አልኩ እንጂ ነገሩስ ይገባኛል ። ... በደንብ ይገባኛል የኔ መቤት» እግንባሯ ላይ ያለውን ፋሻ ካነሳላት በኋላ ፤ «አሁን አይንሽን መግለጥና ፊትሽን በመስታወት ማየት ትችያለሽ ፣ ሜሪ» አለ ። ሜሪ ግን ካለችበት ላይ ንቅንቅ አላለችም ። ብዙ ዓለም አይታ መጥታለች ። ሆኖም የአዲስ እሷን ፊት ሙሉውን አታውቀውም ። አንደኛው ጐን ቢገለጥ ሌላኛው ወይ በፋሻ ተሸፍኖ ወይ ፕላስተር ተለጥፎበት ወይም ተደርቶ ነበር የምታየው። «በያ ብድግ በይና ወደ መስታወቱ ቅረቢ» አለ ፒተር ያን አዲስ ፊት ፤ ያን ናንሲ ማክአሊስተር የነበረችውን የቀድሞ እሷን ሳይሆን ሜሪ አዳምሰን የተባለችውን አዲስ እሷን ለማየት ፍርሃት ተጫናት ። ምን ያለ የማይረባ ፍርሃት ነው አለች በሐሳቧ። ፍርሃቷን እሸንፋ ተነሳች ። ፊቷን በመስታወቱ ውስጥ ስታይ ፊቷ በሳቅ ቧ ብሎ ተከፈተ ። በጉንጯ ላይ ግን እንባዋ ይጐርፍ ነበር ። ይህ የስሜት ግንፈላ ተግ እስኪልላት ድረስ አልተጠጋትም ። አላነገራትም ። ያ ጊዜ የግሏ የሆነ ማንም ሊጋራት የማይገባ ጊዜ እንደሆነ በመገንዘብ ። «ፒተር ፤ እረ የፈጣሪ ያለህ ! እንዴት ቆንጆ ነው አለች ። «አይ አንቺ ቂል ፍጡር» አለ ፒተር በለሆሳስ እየሳቀ «እንዴት ቆንጆ ነው ሳይሆን እንዴት ቆንጆ ነኝ በይ… ያቺ የምታያት ሌላ ሰው ወይ ሌላ ነገር አይደለችም ። አንቺ ነሽ ራስሽ ነሽ›› ዞራ አየችው ። የተናገረው ትክክል እንደሆነ በቃላት መግለጽ አቃታት ። ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች ። ልክ ነው ። ሙሉ በሙሉ ተቀይራለች ። ከምታውቀው መልኳ የቀረ ቅንጣት ምልክት የለም ። አሁን ያላንዳች ማወላወል ሜሪ አዳምሰን ነኝ ስትል አመነች
«ፒተር !...» አለች ውለታ በበዛበት ድምጽ ። ሄዳ ተጠመጠመችበት ። ተቃቅፈው ብዙ ጊዜ ቆዩ ። በመጨረሻ ፊቷን ለማየት እስኪችል ድረስ በክንዶቿ ይዞ ራቅ አደረጋት ። ፈቷ በእንባ ርሷል ። በጣቶቹ ጠረገላት ። «ፒተር. . . አየህ እንባየ እንኳ ፊቱን አላሟሟውም ! » አለች ። «ያ ብቻ ሳይሆን በትንሽ በትንሹ ይሁን እንጂ ፀሐይም መሞቅ ትችያለሽ» አላት ። ከዚያ በኋላ ግን ዕድሜሽን በሙሉ የፈለግሽውን ነገር ማድረግ ትችያለሽ ። ደስ ያለሽን ብትሆኝ ምንም አደጋ አይኖርም ። በነገራችን ላይ ምን ለማድረግ ነው እቅድሽ ? »
ይህን ብላ እተሽከርካሪው ወንበር ላይ ተቀምጣ ፤ እግሯ ጉንጯን ነክቶ ከራሷ በላይ እስኪሆን ሽቅብ አንስታ ከወንበሩ ጋር መሽከርከር ጀመፎች ። «አምላኬ እስቲ ይኸን ምን ትለዋለህ ? ሴትዮዋ እቢሮዬ ውስጥ ገብታ አንድ አካሏ ቢጐድል ሰው ምን ይለኛል ። አበጀህ እንኳን ይለኝ ይሆን ?»
«አትፍራ እኔ እንደሆነ ዛሬ የመጣው ቢመጣ ጥርሴ እረገፈ ፤ እግሬ ተሰበረ ... ካሣ ምናምን እንደማልል ይግባህ ።የማከብረው እንጂ የምጨቃጨቅበት ቀን አይደለም»
«እንዲያም ከሆነ መልካም ። ይህ ቀን ዓመት ባልሽ መሆኑን መስማቴ ደሞ በጣም ደስ አስኝቶኛል » ፒተር ብቻ ሳይሆን ፍሬድም (ውሻው) በሆነው ነገር ደስ ያለው ይመስላል ። ይዘላል ፤ ይቧርቃል ፤ ጭራውን ይቆላል። የተናገርኩት ስለገባው ነው አለች ውሻውን እያሰበች ። ከዚያም ጨብጠኝ እንደማለት እጅዋን እየዘረጋችለት ፣ «አላወክም ነበር ማለት ነው ጅሎ !. ይህን ዕለት ለማክበር ለራሳችን ጢን ያለ የምሳ ግብዣ እናደርጋለን ፒተር›› አለች ። ስሙን ከጠራችው በኋላ ሙሉ በሙሉ እያየችው «ፒተር ውለታህን ልከፍልህ የምችል አይመስለኝም ። ግን ደግሞ እስከመቃብር ከልቤ አትጠፋም ። መቼም ቢሆን የትም ቢሆን አስታውስሃለሁ ። በበድን አካሌ ነፍስ የዘራህባት አንተ ነህ» አለች ።
«አ…እ… እኔ ሳልሆን ሌላ ሰው ነው» አለ ፒተር ። አዎ ማሪዮን ሂልያርድ ፤ የማይክል እናት ናት ፤ ይህ ሁሉ እንዲሆን ያደረገችው። ግን ደግሞ ሜሪ ማሪዮንን ምን ያህል እንደምትጠላት ስለሚያውቅ ስሟን ሊጠራ አልፈላገም ። ሌላ ሰው ብሎ ጠራት ።
ቀጥሎም...
«እኔ. .. እኔ በበኩሌ ግን ሜሪ… ያደረግኩልሽን ሁሉ ስላደረኩልሽ ደስ ይለኛል ። ለወደፊቱም ላደርግልሽ የምትፈልጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ» አለ ። «ነው?... ቀልድ መስሎሃል ፤ አደል ? እንዲያውም ከዛሬ እንጀምራለን ፤ ዛሬ በስድስት ሰዓት ተኩል ተገናኝተን ምሳዬን እንድታጐርሰኝ እፈልጋለሁ ። እሺ?»
«ደስ ይለኛል»
«የት እንገናኝ ? » አንድ በቅርብ የተከፈተ ምግብ ቤት ጠቀሰላትና ታውቀው እንደሆነ ጠየቃት ።
«በሚገባ !» አለች ።
«ይስማማሻል ?››
«አሳምሮ ። እንዲያውም ካሁን ጀምሬ ወደዚያው አካባቢ ሄጂ ሰዓቱ እስኪደርስ ፎቶግራፍ ሳነሳ እቆያለሁ፡፡ አይን የሚገባ ነገር ከተገኘ»
«አሁን የልቤን ምኞት ነገርሺኝ ። ገበያ ሄጄ አዲስ ልብስ ስመርጥ ወይም ሌላ ብትይኝ ኖር ይከፋኝ ነበር» ተሰነባብተው ተለያዩ ፤ እስከምሳ ሰዓት ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በምሳ ሰዓት ሲገናኙ ልብሷን ቀይራ ሽክ ብላ አገኛት ። «በእውነት ይቺ ሴት አንቺው ራስሽ ነሽ ?»
«ባለወርቅ ጫማዋ ልዕልት እነሆኝ ፡። እንዴት ነው ፤ አምሮብኛል ?»
«አምሮብኛል !? እንደ ቅዱሳን አንፀባርቀሻል እንጂ ፤ ምንማማር ብቻ! ... እንደፈራሁት ፎቶ ግራፍ ማነሳሳቱን ትተሽ ቀሚስ መረጣ ላይ ዋልሽ ልበል?»
«ምን ይደረግ ትላለህ ። ሳስበው ለካ ይህ ቀን የሚከበር ፌስታ የሚደረግበት እንጂ የሚሠራበት አይደለም» ድንገት አቅፈህ ሳማት የሚል ሐሳብ መጣበት ፤ እምግብ ቤቱ ውስጥ ያ ሁሉ ሰው እያዬ ። ሐሳቡን ገታና እጅዋን ጥብቅ አድርጐ ያዛት ። «ውዴ ይህን ያህል ደስ ብሎሽ ስላየሁ እኔንም እጅግ ደስ አለኝ» ኣለ ። «ፒተር በጣም ደስ ብሎኛል ። የዛሬዋ ቀን ለኔ ልዩ ናት። ስለገጽታዬ ብቻ አይምሰልህ ። የዛሬ ቀን. . . ነገ የፎቶግራፍ ተርኢት የማቀርብበት ፤ ኤግዚቢሽኔ የሚከፈትበት ቀንም ስለሆነ... አዲስ ሕይወት መጀመሬም ነው።... አንተም አጠገቤ እንዳለህና ድንቅ እንደሆንክ ስለማውቅ»
👍14❤1
ያንተ መኖር የምትለዋ ነገር ልቡን አፈካችው ። የሰማውን አምኖ መቀበል ከበደው ። በዛበት ። ስለዚህ እንዲህ ሲል ቀለል ሊያደርገው ሞከረ ። «ይገርምሻል ። ኤግዚቢሽን ፤ አዲስ ሕይወት... ከዚያ ሁሉ ነገር በታች እኔ ! የእኔስ ይሁን ፍሬድሳ ምን ያህል ነው አስፈላጊነቱ ? » ቀልድ ነበርና ሁለቱም ከልባቸው ይስቁ ጀመር ። የምግብ ቤቱ አሳላፊ መጥቶ ምን እንደሚጠጡ ሲጠይቃቸው ፣ ሁለት ዊስኪ እንዲያመጣ ፒተር አዘዘው ፤ወዲያው ሀሳቡን ቀየረና «የለም ሻፓኝ አድርገው » አለ ። «ሻፓኝ ? !» አለች ሜሪ ። «ነዋ! እለቱን በፌስታ እናሳልፈው ብለን የለምን? ! ለፌስታ ሻፓኝ ። በዚያ ላይ ከሰዓት በኋላ ለራሴ ፈቃድ ሰጥቻለሁ ። ሥራ አልገባም »
« እውነተኛ ፌስታ ሆነ በለኛ »
«መሆን አለበት ።. . . ምናልባት. . . ማለት አንቺ ሌላ ጉዳይ ከሌለሽ »
«የምን ሌላ ጉዳይ በል ?»
«ሥራ . . . ምናልባት »
«በዛሬው ቀን!?» ጊዜውን አብረው አሳለፉ ። በዚያ የክረምት ወራት ባህርዳር መዝናናት ያልተለመደ መሆኑ ፒተርን ቢያስገርመውም ይህን ሀሳብ ለሜሪ ሊገልጽላት ቢሞክርም ባቀረበችው ሀሳብ መሠረት ወደዚያው ሔደው ቆዩ ። እዚያም እስከዚያ ሰዓት ደብቃ ያቆየችውን ስጦታ አበረከተችለት ።የፎቶ ግራፍ ስጦታ ። ፒተር እጅግ ተደሰተ ። የሜሪ መኖሪያ አፓርታማ እንደደረሱ ፤ «ለጥቂት ጊዜ አብረን እንቆይ ተጋብዘኃል » አለች የቀረኝ ስጦታ አለ ። ጊዜ ካለህ እንግባ »
« እውነትሽን ነው ? »
‹‹ አትጠራጠር »
እሳሎን እንደደረሱ የስዕል መሳያ አትሮኖሷን ገጽ ወደ ፒተር አዞረችና መብራት አበራች ። አየው ሥዕሉን ። እዛፍ ላይ የተንጠለጠለና በዛፍ ቅርንጫፍ በመጠኑም የተከለለው ልጅ ያለበት የገፀ ምድር ምስል ሥዕሏ ነበር ። «ይህን ሥዕል ሳበረክትልህ ደስ ይለኛል ። . . . ከጀመርኩት ረጂም ጊዜ አልፏል... የጨረስኩት ግን በቅርብ ነው ። . ልጨርሰው የቻልኩት ለአንተ ለመስጠት ስለወሰንኩ ነው ። »
«ይህን ያህል. . . ?» አለ እውነት ሊሆን አይችልም በሚል ድምፅ ። በአድናቆት ተመለከታት ፡ በፍቅር አያት ። «የለም ይህ የማይሆን ነገር ነው» አለ ። « ብዙ ብዙ ነገር ሰጥተሺኛል ፡ ይበዛብኛል»
«ፒተር እስከ ዛሬ ፎቶ ግራፍ ብቻ ነው የሰጠሁህ ። ይኸኛው ይለያል ፤ ፒተር ። ይኽውም የዳግም ልደቴ ማብሰሪያ ነው ። ሌላ ሰው ከሆንኩ በኋላ ቡሩሽና ቀለም እጄን የነካው ይህን ሥዕል ለመጨረስ ስል ነው ። . . . ፒተር ይህ ሥዕል ለኔ ምን ያህል እንደነበር ልነግርሀ አልችልም ። ስለዚህ ነው ለአንተ ልሰጥህ የወሰንኩት እባክህ ተቀበለኝ » አይኗ እንባ አቆረዘዘ . . . ጠጋ አላትና አቀፋት «እንዴት ደስ የሚል ቀን ነው ። እንዴት ዋጋ የማይተመንለት ስጦታ ነው ። ምን ብዬ ላመሰግንሽ እንደምችል አላውቅም ። ደግነትሽ እጅግ ከበደኝ »
«ምንም ነገር ማለት አይሻህ ። ዝም ብትልም ይገባኛል» አለች እውጭ የጨለማው ጥላ እየከበደ ሲሄድ ይታያት ነበር ።
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
« እውነተኛ ፌስታ ሆነ በለኛ »
«መሆን አለበት ።. . . ምናልባት. . . ማለት አንቺ ሌላ ጉዳይ ከሌለሽ »
«የምን ሌላ ጉዳይ በል ?»
«ሥራ . . . ምናልባት »
«በዛሬው ቀን!?» ጊዜውን አብረው አሳለፉ ። በዚያ የክረምት ወራት ባህርዳር መዝናናት ያልተለመደ መሆኑ ፒተርን ቢያስገርመውም ይህን ሀሳብ ለሜሪ ሊገልጽላት ቢሞክርም ባቀረበችው ሀሳብ መሠረት ወደዚያው ሔደው ቆዩ ። እዚያም እስከዚያ ሰዓት ደብቃ ያቆየችውን ስጦታ አበረከተችለት ።የፎቶ ግራፍ ስጦታ ። ፒተር እጅግ ተደሰተ ። የሜሪ መኖሪያ አፓርታማ እንደደረሱ ፤ «ለጥቂት ጊዜ አብረን እንቆይ ተጋብዘኃል » አለች የቀረኝ ስጦታ አለ ። ጊዜ ካለህ እንግባ »
« እውነትሽን ነው ? »
‹‹ አትጠራጠር »
እሳሎን እንደደረሱ የስዕል መሳያ አትሮኖሷን ገጽ ወደ ፒተር አዞረችና መብራት አበራች ። አየው ሥዕሉን ። እዛፍ ላይ የተንጠለጠለና በዛፍ ቅርንጫፍ በመጠኑም የተከለለው ልጅ ያለበት የገፀ ምድር ምስል ሥዕሏ ነበር ። «ይህን ሥዕል ሳበረክትልህ ደስ ይለኛል ። . . . ከጀመርኩት ረጂም ጊዜ አልፏል... የጨረስኩት ግን በቅርብ ነው ። . ልጨርሰው የቻልኩት ለአንተ ለመስጠት ስለወሰንኩ ነው ። »
«ይህን ያህል. . . ?» አለ እውነት ሊሆን አይችልም በሚል ድምፅ ። በአድናቆት ተመለከታት ፡ በፍቅር አያት ። «የለም ይህ የማይሆን ነገር ነው» አለ ። « ብዙ ብዙ ነገር ሰጥተሺኛል ፡ ይበዛብኛል»
«ፒተር እስከ ዛሬ ፎቶ ግራፍ ብቻ ነው የሰጠሁህ ። ይኸኛው ይለያል ፤ ፒተር ። ይኽውም የዳግም ልደቴ ማብሰሪያ ነው ። ሌላ ሰው ከሆንኩ በኋላ ቡሩሽና ቀለም እጄን የነካው ይህን ሥዕል ለመጨረስ ስል ነው ። . . . ፒተር ይህ ሥዕል ለኔ ምን ያህል እንደነበር ልነግርሀ አልችልም ። ስለዚህ ነው ለአንተ ልሰጥህ የወሰንኩት እባክህ ተቀበለኝ » አይኗ እንባ አቆረዘዘ . . . ጠጋ አላትና አቀፋት «እንዴት ደስ የሚል ቀን ነው ። እንዴት ዋጋ የማይተመንለት ስጦታ ነው ። ምን ብዬ ላመሰግንሽ እንደምችል አላውቅም ። ደግነትሽ እጅግ ከበደኝ »
«ምንም ነገር ማለት አይሻህ ። ዝም ብትልም ይገባኛል» አለች እውጭ የጨለማው ጥላ እየከበደ ሲሄድ ይታያት ነበር ።
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
❤7🥰5👍2
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ባኞ ቤቱ ውስጥ ጠብ ጠብ ከሚለው የውኃ ድምፅ በተጨማሪ ላይ ላይ የምትተነፍስ ሴት ድምፅ ይሰማል" የመታጠቢያ ገንዳው ውኃ እስከ ወገቡ የደረሰ ሲሆን ካርለት ውኃው ውስጥ ጋደም ብላ
ቀኝ እግሯን ገንዳው ከንፈር ላይ በማስቀመጥ ከግርጌዋ ያለውን የውኃ ማሞቂያ በተመስጦ ትመለከታለች" ከውኃ ገንዳው በስተቀኝ የእጅ መታጠቢያው ከፍ ብሎ ደግሞ በክፍሉ ሙቀት ሳቢያ የሚያዠው መስተዋት አለ የመታጠቢያ ክፍሉ ጠበብ ያለ ቢሆንም ንጹሕና ዘመናዊ ነው ከመግቢያው በር በስተግራ ካለው የቆሻሻ ልብስ ማጠራቀሚያ ቅርጫት ካኔተራ፣ ሱሪና ጃኬት ተቀምጧል። ከሱ በላይ ሰፋና ረዘም ያለ በነጭና ሐምራዊ ቀለም የተዥጎረጎረ ፎጣ
ተንጠልጥሏል።
ካርለት የገንዳውን ውኃ ቀይራ ሰውነቷን በንጹሕ ውኃ ከተለቃለቀች በኋላ ከገንዳው ውስጥ ወጥታ በጥቁርና ነጭ ቀለም
የአጥር ሥዕል ከተሣለበት ጸጕራማ ምንጣፍ ላይ ቆመች" እርጥቡ ጸጕሯ ትከሻዋና ደረቷ ላይ ተለጥፏል" ከጸጕሯ ወደ ግንባሯ እየተንኳለለ የሚወርደው ውኃ በቅንድቧ ሥር እየሰረገ ተለቅና
ሰርጐድ ያለውን ዓይኗን ያራጥባል” በደረትና ትከሻዋ አካባቢ ቁጥር ቁጥር ያለ የውኃ እንክብል ከመታየቱም ባሻገር ከሴት ብልቷ ላይ ካለው ስስ ጸጕር ላይ ደግሞ በውርጭ ሰሞን ሳር ላይ የሚታየውን የመሰለ ትንንሽ የውኃ ነጠብጣብ ይታያል"
ካርለት ወደ መስተዋቱ ቀረብ እንዳለች ገፅታዋ ከሚያዠው መስተዋት ውስጥ ተከፋፍሎ ታያት። መስተዋቱን ተወት አድርጋ
በእጆቿ ጡቶቿን ጨበጥ ጨበጥ አደረገቻቸው" ቀኝ እጇ ቀኝ ጡቷ ላይ ሲቀር ግራ እጇ ግን ወደ ታች እየተንከላወሰ ጕዞ ጀመረ ወደ ሴት ብልቷ" እጇ የደረሰበትን በዓይኗ ተመለከተችው
ከሰፊው የመስተዋት መስኮትና ላዩ ላይ ከተንጠለጠለው ነጭና
ቡና ዓይነት መጋረጃ አልፎ አልፎ ዧ ብሎ የሚያልፍ የመኪና ድምፅ ይሰማል" ክፍሉ ውስጥ ካሉት ሁለት አልጋዎች መካከል አንድ
ኮመዲኖ አለ። ኮመዲኖው ላይ «ሶኒ» የሚል ምልክት ካለበት ሬዲዮ ካሴት ውስጥ ከዛሬ ሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በፊት በሞዛርት የተቀነባበረው ፒያኖ ሶናታ የሙዚቃ ስልት ድምፁን ሰለምለም
ሞቅ ሞቅ ሰለምለም...እያደረገ ይንቆረቆራል ከመስኮቱ ጠርዝ አካባቢ ሁለት ሶፋና አንድ ጠረጴዛ ያለ ሲሆን ጠረጴዛው ላይ ከግማሽ
በላይ የተጠጣለት የማር አረቄ ይታያል"
ስቲቭ ማርቲን የአደረው «የዞረ ድምር» ዓይኖቹን ከርቸም ያለ እንቅልፍ አጋድሞታል በአዲስ አበባው ሒልተን ሆቴል
በተዘጋጀው የቡፌ ግብዣ ላይ ሦስት ወንበር እንዲያዝላቸው በማዘዝ ሁለቱ የፍቅር ጓደኛሞች ከከሎ ሆራ ጋር በመሆን ምሽቱን ከምግብ ጕዝጓዙ በኋላ መጎንጨቱንና በአፍሪቃውያን ሙዚቃ መውረግረጉን
እስከ እኩለ ሌሊት ሲያስኬዱት ቆይተው ነው ሁለቱ ፍቅረኛሞችና
ከሎ ሆራ «መሥመርህን ለይ» የተባባሉት"
ካርለት እና ስቲቭ የሥራ ቦታቸው በጣም የተራራቀና
የትራንስፖርትም ችግር ያለበት በመሆኑ ተመልሶ ለመገናኘት ቢያንስ የሦስት ወር ጊዜ ያስፈልጋቸዋል" በፍቅር አባዜ ለተያዙት ለእነዚህ ወጣቶች ደግሞ ጊዜው የትየለሌ ነው ሩቅ። ስለ መለያየታቸው እንጂ ስለ መገናኘታቸው የማይተማመኑት ፍቅረኛሞች በወሲብና በፍቅር ጨዋታ ሰዓታቸውን በሚገባ ለመጠቀም በአንድ ወጥ ስሜት ጥረዋል" ድብቅነት በሌለው ንጹሕ የፍቅር ጨዋታ ልባቸውን
ስልትና ቃናው በሚጣፍጥ ቅላፄ እያስጨፈሩ ራሳቸውን በመሆን በፍቅር ባሕር ከመዋኘት አልፈው ዘቅጠውበት አድረዋል።
ካርለት እንደምንም በድኗን ከስቲቭ እቅፍ መንጭቃ ተነሥታ ወደ ባኞ ክፍሉ በመሄድ ገላዋን ተጣጥባ ስትጨርስና በፎጣ ገላዋን
ስታደራርቅ ከስቲቭ ረዘም ላለ ጊዜ የመለየቷን፣ የፍቅርና ወሲብ ጥመኛ የመሆኗን ትርዒት በእዝነ ልቦናዋ ስትቃኝ ፍርሃትና ጭንቀት መንፈሷን ሰንገው ያዙት ተፈጥሯዊ ስሜቷ መኪና አይቶ እንደማያውቅ ፈረስ አእምሮዋን ጥሎ በረገገባት"
አንገቷን ዘንበል በማድረግ መጀመሪያ ጡቶቿን ከዚያም
እምብርቷንና ሰርጓዳ ወገቧን፣ ለስላሳ ጭኖቿን ስትመለከት ስሜቷን
በአእምሮዋ ለመቆጣጠር ተሳናት" ካርለት ስሜቷን ልትጫነው ስላልፈለገች በግዴለሽነት የመታጠቢያ ከፍሉን በር በርግዳ ስትወጣ ስቲቭ ቀኝ እግሩን አጠፍ አድርጎ ጭኖቹን በመበርገድ ተንጋሎ ተኝቷል።
ካርለት ስቲቭን ስታየው የሆነ ስሜት በመላ አካሏ ቅጽበታዊ መተረማመስ ፈጠረና ፍቅር አመንጭ ሕዋሳቶቿ ተከፋፍተው ወደ ፊት ገፈተሯት አእምሮዋም በስቲቭ አካል ላይ ቀስቱን ደገነ የልግጠም፣ ይውጋኝ ፍልሚያ። «ግንኮ የስቲቭ ስሜት እንደኔ ላይሆን ይችላል? ስሜቴን መቆጣጠር መቻል አለብኝ" ሊደከመውም እኮ ይችላል!» ብላ አሰበች" ታስብ እንጂ መንቀሳቀሷን አላቆመችም የሚገፋፋት ስሜት ወደፊት አዳፋት ተጠጋችው» ካርለት ያሰቡትን ለማድረግ መወሰን የሚሳንበት ወቅት መሆኑ ገብቷታል"
«ስቲቭ» አለች የእጅ ጣቶቿን ወደ ቡናማው ጸጕሩ እየሰገሰገች።
ቦንብ ቢፈነዳ እንኳን የሚነቃ የማይስለው ፍቅረኛዋ የእሷን ውብ ድምፅ ሰምቶ ዓይኖቹን ሲገልጥ የሚወደው ምስል እርቃነ ሥጋውን ከአጠገቡ ቆሞ ሲያይ፣ «ኦ...» ብሎ ዓይኖቹን ገለጠ።
«ፍቅር የሚጣፍጠው ሲልሱት ሳይሆን ሲግጡት፣ ኩርሽምሽም አድርገው ሲውጡት፣ ከአካል ጋር ሲዋሐድ፣ የተፈጥሮ ቦታውን
ሲይዝ፣ ደባቂና ተደባቂ ሲሆን እንጂ በቃላት ድርደራ አይደለም»ብላ የምታምነው ካርለት ለስቲቭ፣ «ና» የሚል ምልክት በእጇ አሳየችው ያ እጇ ሁሌም ከሚያስደስተው አካሏና ውስጣዊ እሷነቷ
እንደሚያደርሰው ያውቃልና ተከተለው።
በጣም ደክሞታል፤ ከካርለት እጆችና የፈገግታ ኃይል ግን ራሱን ሊለይ አልተቻለውም። ስለዚህ ወደ ተጠራበት አቅጣጫ ተጓዘ ጒዞው ራቀበት ከተጠራበት አካል ቶሎ ደርሶ ለመደሰት በጣም ጓጕቷል ካርለት ባኞ ቤት ውስጥ እንደገቡ ገፍትራ ለብ ካለው ውኃ
ውስጥ ከተተችው ሣቀ ሣቀች ሁለመናቸው ተሣሣቀ
ጭኖቿን ተመርኵዞ አንጋጦ ሲያይ የገነትን በር ያየ መሰለው ታዲያ የዚያን ውብ ስፍራ በር ከፍቶ የማይገባ ማን አለ? በየጅማቱ ሥር ተበታትኖ የነበረው ኃይል ዘቅዝቆ ወደ ብልቱ ሲንዶለዶል
ተሰማው" ያ የተበታተነ ኃይል እንኳን የተፈቀደለትን፣ ሌላ ጠንካራ በር እንኳ ጥሶ የሚያስገባ ኃይል እንዳለው አመነ።
«እወድሃለሁI ፍቅርህን አልጠግብምI ስግብግብ ነኝ እንድትለቀኝ አልፈልግም...» የሚል ድምፅ የሰማ መሰለው
የቃላት ምልልስ ወቅቱ አለመሆኑን በመረዳቱ ግን እግሮቿን እየዳሰሰ
ተነሣ ሁለቱ አካሎች ተዋሐዱ ፍጡር ካለ ክንፍ ወደሚንሳፈፍበት ወደ ሰማየ ሰማያት ተነጥቆ የገነትን ውበት ወደሚጎበኝበት ማራኪ መዓዛ ውብና እንከን የለሽ ተፈጥሮ ወደሚታይበት፣
እውነተኛ የፍቅርና የደስታ ዜማ ወደሚዜምበት ዓለም ተያይዘው ነጐዱI በሩ ተከፍቶ ተዘጋ።
።።።።።።።።።።።
ካርለት አልፈርድ በኦhስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በሶስዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘች በኋላ በዩኒቨርሲቲው የአንትሮፖሎጂ
ዲፓርትመንት አባል በመሆን በወቅቱ ታዋቂ በነበሩት አንትሮ ፖሎጂስቶች የተዘጋጁትን ጽሑፎችና ዲስኩሮች ተከታትላለች።
ከአሥራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን በተለይም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ከፍተኛ እመርታን ካሳየበት ከዛሬ መቶ ሃምሳ ዓመት ወዲህ እየተዋጡ
የመጡት ቅርሶች፣ የተናቁት ባህሎችና ለከፍተኛ ውጤት ሊያበቁ የሚችሉት የአርኪዮሎጂና የሌሎችም ጥናቶች የምሁራኑን አእምሮ ይበልጥ በመሳባቸው እንደ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ አሜሪካና ጃፓን የመሳሰሉት ምሁራን ትኵረት እንደ ሰጡት እንግሊዛውያንም ምሁራንም በመስኩ እጅግ ተስበው ነበር"
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ባኞ ቤቱ ውስጥ ጠብ ጠብ ከሚለው የውኃ ድምፅ በተጨማሪ ላይ ላይ የምትተነፍስ ሴት ድምፅ ይሰማል" የመታጠቢያ ገንዳው ውኃ እስከ ወገቡ የደረሰ ሲሆን ካርለት ውኃው ውስጥ ጋደም ብላ
ቀኝ እግሯን ገንዳው ከንፈር ላይ በማስቀመጥ ከግርጌዋ ያለውን የውኃ ማሞቂያ በተመስጦ ትመለከታለች" ከውኃ ገንዳው በስተቀኝ የእጅ መታጠቢያው ከፍ ብሎ ደግሞ በክፍሉ ሙቀት ሳቢያ የሚያዠው መስተዋት አለ የመታጠቢያ ክፍሉ ጠበብ ያለ ቢሆንም ንጹሕና ዘመናዊ ነው ከመግቢያው በር በስተግራ ካለው የቆሻሻ ልብስ ማጠራቀሚያ ቅርጫት ካኔተራ፣ ሱሪና ጃኬት ተቀምጧል። ከሱ በላይ ሰፋና ረዘም ያለ በነጭና ሐምራዊ ቀለም የተዥጎረጎረ ፎጣ
ተንጠልጥሏል።
ካርለት የገንዳውን ውኃ ቀይራ ሰውነቷን በንጹሕ ውኃ ከተለቃለቀች በኋላ ከገንዳው ውስጥ ወጥታ በጥቁርና ነጭ ቀለም
የአጥር ሥዕል ከተሣለበት ጸጕራማ ምንጣፍ ላይ ቆመች" እርጥቡ ጸጕሯ ትከሻዋና ደረቷ ላይ ተለጥፏል" ከጸጕሯ ወደ ግንባሯ እየተንኳለለ የሚወርደው ውኃ በቅንድቧ ሥር እየሰረገ ተለቅና
ሰርጐድ ያለውን ዓይኗን ያራጥባል” በደረትና ትከሻዋ አካባቢ ቁጥር ቁጥር ያለ የውኃ እንክብል ከመታየቱም ባሻገር ከሴት ብልቷ ላይ ካለው ስስ ጸጕር ላይ ደግሞ በውርጭ ሰሞን ሳር ላይ የሚታየውን የመሰለ ትንንሽ የውኃ ነጠብጣብ ይታያል"
ካርለት ወደ መስተዋቱ ቀረብ እንዳለች ገፅታዋ ከሚያዠው መስተዋት ውስጥ ተከፋፍሎ ታያት። መስተዋቱን ተወት አድርጋ
በእጆቿ ጡቶቿን ጨበጥ ጨበጥ አደረገቻቸው" ቀኝ እጇ ቀኝ ጡቷ ላይ ሲቀር ግራ እጇ ግን ወደ ታች እየተንከላወሰ ጕዞ ጀመረ ወደ ሴት ብልቷ" እጇ የደረሰበትን በዓይኗ ተመለከተችው
ከሰፊው የመስተዋት መስኮትና ላዩ ላይ ከተንጠለጠለው ነጭና
ቡና ዓይነት መጋረጃ አልፎ አልፎ ዧ ብሎ የሚያልፍ የመኪና ድምፅ ይሰማል" ክፍሉ ውስጥ ካሉት ሁለት አልጋዎች መካከል አንድ
ኮመዲኖ አለ። ኮመዲኖው ላይ «ሶኒ» የሚል ምልክት ካለበት ሬዲዮ ካሴት ውስጥ ከዛሬ ሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በፊት በሞዛርት የተቀነባበረው ፒያኖ ሶናታ የሙዚቃ ስልት ድምፁን ሰለምለም
ሞቅ ሞቅ ሰለምለም...እያደረገ ይንቆረቆራል ከመስኮቱ ጠርዝ አካባቢ ሁለት ሶፋና አንድ ጠረጴዛ ያለ ሲሆን ጠረጴዛው ላይ ከግማሽ
በላይ የተጠጣለት የማር አረቄ ይታያል"
ስቲቭ ማርቲን የአደረው «የዞረ ድምር» ዓይኖቹን ከርቸም ያለ እንቅልፍ አጋድሞታል በአዲስ አበባው ሒልተን ሆቴል
በተዘጋጀው የቡፌ ግብዣ ላይ ሦስት ወንበር እንዲያዝላቸው በማዘዝ ሁለቱ የፍቅር ጓደኛሞች ከከሎ ሆራ ጋር በመሆን ምሽቱን ከምግብ ጕዝጓዙ በኋላ መጎንጨቱንና በአፍሪቃውያን ሙዚቃ መውረግረጉን
እስከ እኩለ ሌሊት ሲያስኬዱት ቆይተው ነው ሁለቱ ፍቅረኛሞችና
ከሎ ሆራ «መሥመርህን ለይ» የተባባሉት"
ካርለት እና ስቲቭ የሥራ ቦታቸው በጣም የተራራቀና
የትራንስፖርትም ችግር ያለበት በመሆኑ ተመልሶ ለመገናኘት ቢያንስ የሦስት ወር ጊዜ ያስፈልጋቸዋል" በፍቅር አባዜ ለተያዙት ለእነዚህ ወጣቶች ደግሞ ጊዜው የትየለሌ ነው ሩቅ። ስለ መለያየታቸው እንጂ ስለ መገናኘታቸው የማይተማመኑት ፍቅረኛሞች በወሲብና በፍቅር ጨዋታ ሰዓታቸውን በሚገባ ለመጠቀም በአንድ ወጥ ስሜት ጥረዋል" ድብቅነት በሌለው ንጹሕ የፍቅር ጨዋታ ልባቸውን
ስልትና ቃናው በሚጣፍጥ ቅላፄ እያስጨፈሩ ራሳቸውን በመሆን በፍቅር ባሕር ከመዋኘት አልፈው ዘቅጠውበት አድረዋል።
ካርለት እንደምንም በድኗን ከስቲቭ እቅፍ መንጭቃ ተነሥታ ወደ ባኞ ክፍሉ በመሄድ ገላዋን ተጣጥባ ስትጨርስና በፎጣ ገላዋን
ስታደራርቅ ከስቲቭ ረዘም ላለ ጊዜ የመለየቷን፣ የፍቅርና ወሲብ ጥመኛ የመሆኗን ትርዒት በእዝነ ልቦናዋ ስትቃኝ ፍርሃትና ጭንቀት መንፈሷን ሰንገው ያዙት ተፈጥሯዊ ስሜቷ መኪና አይቶ እንደማያውቅ ፈረስ አእምሮዋን ጥሎ በረገገባት"
አንገቷን ዘንበል በማድረግ መጀመሪያ ጡቶቿን ከዚያም
እምብርቷንና ሰርጓዳ ወገቧን፣ ለስላሳ ጭኖቿን ስትመለከት ስሜቷን
በአእምሮዋ ለመቆጣጠር ተሳናት" ካርለት ስሜቷን ልትጫነው ስላልፈለገች በግዴለሽነት የመታጠቢያ ከፍሉን በር በርግዳ ስትወጣ ስቲቭ ቀኝ እግሩን አጠፍ አድርጎ ጭኖቹን በመበርገድ ተንጋሎ ተኝቷል።
ካርለት ስቲቭን ስታየው የሆነ ስሜት በመላ አካሏ ቅጽበታዊ መተረማመስ ፈጠረና ፍቅር አመንጭ ሕዋሳቶቿ ተከፋፍተው ወደ ፊት ገፈተሯት አእምሮዋም በስቲቭ አካል ላይ ቀስቱን ደገነ የልግጠም፣ ይውጋኝ ፍልሚያ። «ግንኮ የስቲቭ ስሜት እንደኔ ላይሆን ይችላል? ስሜቴን መቆጣጠር መቻል አለብኝ" ሊደከመውም እኮ ይችላል!» ብላ አሰበች" ታስብ እንጂ መንቀሳቀሷን አላቆመችም የሚገፋፋት ስሜት ወደፊት አዳፋት ተጠጋችው» ካርለት ያሰቡትን ለማድረግ መወሰን የሚሳንበት ወቅት መሆኑ ገብቷታል"
«ስቲቭ» አለች የእጅ ጣቶቿን ወደ ቡናማው ጸጕሩ እየሰገሰገች።
ቦንብ ቢፈነዳ እንኳን የሚነቃ የማይስለው ፍቅረኛዋ የእሷን ውብ ድምፅ ሰምቶ ዓይኖቹን ሲገልጥ የሚወደው ምስል እርቃነ ሥጋውን ከአጠገቡ ቆሞ ሲያይ፣ «ኦ...» ብሎ ዓይኖቹን ገለጠ።
«ፍቅር የሚጣፍጠው ሲልሱት ሳይሆን ሲግጡት፣ ኩርሽምሽም አድርገው ሲውጡት፣ ከአካል ጋር ሲዋሐድ፣ የተፈጥሮ ቦታውን
ሲይዝ፣ ደባቂና ተደባቂ ሲሆን እንጂ በቃላት ድርደራ አይደለም»ብላ የምታምነው ካርለት ለስቲቭ፣ «ና» የሚል ምልክት በእጇ አሳየችው ያ እጇ ሁሌም ከሚያስደስተው አካሏና ውስጣዊ እሷነቷ
እንደሚያደርሰው ያውቃልና ተከተለው።
በጣም ደክሞታል፤ ከካርለት እጆችና የፈገግታ ኃይል ግን ራሱን ሊለይ አልተቻለውም። ስለዚህ ወደ ተጠራበት አቅጣጫ ተጓዘ ጒዞው ራቀበት ከተጠራበት አካል ቶሎ ደርሶ ለመደሰት በጣም ጓጕቷል ካርለት ባኞ ቤት ውስጥ እንደገቡ ገፍትራ ለብ ካለው ውኃ
ውስጥ ከተተችው ሣቀ ሣቀች ሁለመናቸው ተሣሣቀ
ጭኖቿን ተመርኵዞ አንጋጦ ሲያይ የገነትን በር ያየ መሰለው ታዲያ የዚያን ውብ ስፍራ በር ከፍቶ የማይገባ ማን አለ? በየጅማቱ ሥር ተበታትኖ የነበረው ኃይል ዘቅዝቆ ወደ ብልቱ ሲንዶለዶል
ተሰማው" ያ የተበታተነ ኃይል እንኳን የተፈቀደለትን፣ ሌላ ጠንካራ በር እንኳ ጥሶ የሚያስገባ ኃይል እንዳለው አመነ።
«እወድሃለሁI ፍቅርህን አልጠግብምI ስግብግብ ነኝ እንድትለቀኝ አልፈልግም...» የሚል ድምፅ የሰማ መሰለው
የቃላት ምልልስ ወቅቱ አለመሆኑን በመረዳቱ ግን እግሮቿን እየዳሰሰ
ተነሣ ሁለቱ አካሎች ተዋሐዱ ፍጡር ካለ ክንፍ ወደሚንሳፈፍበት ወደ ሰማየ ሰማያት ተነጥቆ የገነትን ውበት ወደሚጎበኝበት ማራኪ መዓዛ ውብና እንከን የለሽ ተፈጥሮ ወደሚታይበት፣
እውነተኛ የፍቅርና የደስታ ዜማ ወደሚዜምበት ዓለም ተያይዘው ነጐዱI በሩ ተከፍቶ ተዘጋ።
።።።።።።።።።።።
ካርለት አልፈርድ በኦhስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በሶስዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ካገኘች በኋላ በዩኒቨርሲቲው የአንትሮፖሎጂ
ዲፓርትመንት አባል በመሆን በወቅቱ ታዋቂ በነበሩት አንትሮ ፖሎጂስቶች የተዘጋጁትን ጽሑፎችና ዲስኩሮች ተከታትላለች።
ከአሥራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን በተለይም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ከፍተኛ እመርታን ካሳየበት ከዛሬ መቶ ሃምሳ ዓመት ወዲህ እየተዋጡ
የመጡት ቅርሶች፣ የተናቁት ባህሎችና ለከፍተኛ ውጤት ሊያበቁ የሚችሉት የአርኪዮሎጂና የሌሎችም ጥናቶች የምሁራኑን አእምሮ ይበልጥ በመሳባቸው እንደ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ አሜሪካና ጃፓን የመሳሰሉት ምሁራን ትኵረት እንደ ሰጡት እንግሊዛውያንም ምሁራንም በመስኩ እጅግ ተስበው ነበር"
👍46
በእርግጥ፣ የአንትሮፖሎጂ ጥናት የማይዳስሰው የሕይወት ክፍል እንዳለመኖሩ ሁሉ ጥናቱና ምርምሩ ችግርና ሰቆቃ የበዛበት በመሆኑ ብዙዎቹን ቢያስደነግጥም፣ ጥቂት በሙያው የተመሰጡና እራሳቸውን መሥዋዕት ያደረጉት ግን ከራሳቸው የሕሊና እርካታ በተጨሪ ለሰው ልጆች ደኅንነትና ጥቅም ያደረጉት አስተዋፅኦና ለዓለማችን ይበልጥ መቀራረብ የተጫወቱት ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው"
ካርለትም በወባ በሽታ ተይዘው የሞቱትን፣ የአውሬ ሲሳይ የሆኑትን፣ በነፍሰ ገዳይ የተገደሉትን ስትሰማ፣ በዚህ ውጣ ውረድ በበዛው የሙያ መስክ ለመሰማራት ማሰቧ እራሷን ለመከራና ችግር መዳረግ ይሆናል ብላ በመገመቷ የተሳሳተ የሕይወት መሥመር
የተከተለች መስሏት ሰግታ ነበር" እንዳጋጣሚ ሆኖ ግን፣ እርቃ ሳትሄድ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ጽሑፎችን ስታነብና
ከተመራማሪዎች አንደበት የሚወጣውን ንግግር ስታዳምጥ፣የነበራትን ጥላቻ ለመመርመር ተገደደች።
መኖርና መሞት የሰው ልጅ አይቀሬ ዕጣ ፈንታ ቢሆንም ዓላማ ያላቸው ሰዎች አለመሞታቸውን የሚያረጋግጡት በእስትንፋሳቸው
መኖር ሳይሆን ለሕብረተሰቡ በሚያበረክቱት መልካም የሥራ ውጤት መሆኑን ስለምታምን፣እሷም በሕይወት መኖሯን
የማስመከር፣ በተለይም ሰው ሠራሽ ጾታዊ ግድቡን የማፍረስ ተልዕኮ
እንዳላት ገባት።
ካርለት ዕድሜዋ አሥራ ሁለት ዓመት ሲሆን፣ አባቷ ቻርልስ አልፈርድ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛ መምህር በመሆን እ.ኤ.አ እስh 1955 ዓ.ም ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ስለ ደቡብ አፍሪካ የነጮችና ጥቁሮች ቋንቋና ኢትኖግራፊ ጥናት በማካሄድ በርካታ ጽሑፎችን ያቀረቡና ለንደን በሚገኘው የአንትሮፖሎጂስቶች
መዕከል ፕሮፌሰር የነበሩ ናቸው።
ካርለት በወርቃማው የወጣትነት ዘመኗ እንደማንኛውም የታላቋ
ብሪታንያ ወጣት ሁሉ ብርቅዬ በሆኑ አልባሳት አጊጣ ከአገሯ አልፋ
ፈረንሳይን፣ ጀርመንን፣ እስፓኝን ካናዳን...በማካለል ተዝናንታለች" ካርለት በእናቷ ትብብር ፒያኖና ቫዮለን የሙዚቃ መሣሪያዎች አጨዋወት የተማረች ቢሆንም ከሙዚቃው ይልቅ
ስሜቷ ወደ ፎቶግራፍ ማንሣት ጥበብ ስላጋደለ የፎቶግራፍ ጥበቡን
ጀመረችI ሆኖም በዚህም ብዙ ሳትገፋ ተወችው።
ካርለት ምርጫዋን ለማስተካከል ተስኗት ከፊል ጊዜዋን በመዝናናት ስታሳልፍ አባቷ ቻርልስ ዘመኑ ያቀረበላትን ማዕድ
ባርከው ሲለግሷት፣ በወቅታዊው እፍ እፍ ስሜቷ ውስጥ ጣልቃ ባይገቡም እንኳን ሕሊናቸው በወደፊት የልጃቸው ዕጣ ሕይወት
መባዘኑ አልቀረም። ሜዲትራኒያንንና የሰሃራ በረሃን አቋርጠው በመጓዝ ስላዩት ተፈጥሮ፣ ባህልና ይዘው ስለተመለሱት የጥናትናዐምርምር ውጤት ሲያወጓት፣ «እባክህ አባዬ የወሬ ርዕስህን ቀይርና
ይልቁንስ ሽርሽር ይዘኸኝ ውጣ...» ስትላቸው፣ ምንም እንኳን ስሜታቸውን በገጽታቸው ባይገልጹትም ውስጥ ውስጡን ያማቸው
ነበር" ያም ሆኖ ግን ልጃቸውን ጥናታቸውን ወደ አከናወኑበት ደቡብ
አፍሪካ ሲወስዷት እግረ መንገዳቸውን በተፈጥሮ ሀብታቸውና ቅርሳቸው የሚያደንቋቸውን አገሮች ኢትዮጵያን፣ ኬንያንና
ዝንቧቡዌን አስጐበኟት
እ.ኤ.አ በ1970 ዓ.ም ፕሮፌሰር ቻርልስ በአደረባቸው የልብ
ካንሰር ሕመም ምከንያት ፒጃማ ለብሰው ቤት መዋል ከጀመሩና እልፈተ ሕይወታቸው በግል ሐኪማቸው ከተረጋገጠ ማግስት ጀምሮ ስለ አባቷ የተጻፉ አስተያየቶችና አድናቆቶች የገዛ አባቷን
ገድል እንደምትመረምር ጋበዟት"
ካርለት ለመጀመሪያ ጊዜ ካሸለበችበት በመንቃት የአባቷን ወርቃማ ሥራዎች ለመረዳት ተጣጣረች ጥረቷ የዘገየና ፀሐይ ከጠለቀ በኋላ በመሆኑ ግራ ብትጋባም፣ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ዓላማቸውንና ያደረጉትንም አስተዋፅኦ ተገነዘበች" ያ ወቅት
በእርግጥ የወጣትነት ቡረቃዋን ገትታ፣ ዘላቂውን የሕይወት ድርሻዋን፣ የምትከተለውን ዓላማ ያጤነችበት፣ የረጋው ፍላጎቷ
ማዕበሉ ተጠናክሮ የዋዠቀችበትና በመጨረሻም መልሕቋን
በመወርወር ለውሳኔ የበቃችበት ወቅት ሆነ።
ወርቃማው ጸጕሯ፣ ድሎት ያወረዛው ፊቷና መካከለኛው ቁመናዋ በጅምናስቲክ በተገነባው ቅርፅዋ እየተረዱ የብዙ ወንዶችን ልብ ያሸፈቱ ቢሆኑም፣ ተባባሪ የውበት አለኝታዎቿ አቅመ ቢስ
ሆነውባት እሷም በፍቅር ቡጢ ጥርሷ እስኪነቃነቅና እንባዋ እስኪጐርፍ ድረስ አፍቅራ ተመናቅራለች እንዲያውም ይህ ልምዷ
የተመኙትን ሁሉ ማግኘት አለመቻሉን፣ ፈላጊና ተፈላጊ መተላለፍ የሚያበዙ መሆናቸውንና የፈለጋት እንዲያገኛት በተቻለ መጠን
መገኘት የሚያስችላትን ቦታ ፈልጋ እንድታገኝ ረዳት
ካርለት፣ በሕይወቷ ሽንፈት ደጋግሞ እንደሚያጋጥማት
ታምናለች የምትፅናናበት ግን በፍላጎቷ ወደ ውድድር መድረክ መቅረቧና ከማን ከማን ጋር እንደምትወዳደር ማወቋ ነው «ከተወዳዳሪዎቹ ሁሉ ጅሉ ሰው በውድድሩ ተካፍሎ ለማሸነፍ በመጣጣር
አልሳካልህ ብሎ የተሸነፈው ሳይሆን፣ መወዳደሩንና ተወዳዳሪዎቹን ሳያውቅ ለድል የበቃው ነው» ማለት ታዘወትራለች።
ካርለት የማንችስተር ዩኒቨርሲቲ የአንትሮፖሉጂ ዲፓርትመንት አባል ሆና የማስተር ዲግሪዋን ካገኘች በኋላ፣ ለቀረው ጥናቷ ቀደም ሲል አባቷ ካሳይዋት አገሮች ኢትዮጵያን መረጠች በማከታ ተልም ኢትዮጵያ ነከ የሆኑ የጽሑፍ፣ የፊልምና የስላይድ መረጃዎችን
በየጕራንጕሩ ሁሉ እያነፈነፈች ከተመለከተች፣ በተለይም ስለ ኢትዮጵያ ዕውቀት ካላቸው አማካሪዋ ከፕሮፌሰር ጆን ፒደርሰን ጋራ በወደፊት የጥናት ቦታዋ ላይ በስፋት ከተመካhሩ በኋላ በእንግሊዝ የምሥራቅ አፍሪካ አንትሮፖሎጂስቶች የጥናት ድርጅት አባል
ሆነች ከዚያም በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ማኅበረሰቦች ውስጥ በሐመር ማኅበረሰብ ባህል ላይ ጥናቷን ለመጀመር ከአማካሪዋ ጋር ተስማሙ። ልታከናውን ላሰበችው ጥናትም የእርዳታ ሐሳብ
ለድርጅቱ አቀረበች ድርጅቱም የጠየቀችውን በጀት አጸደቀላት።ካርልት፣ በዚህ በጀት ብቻም ሳትወሰን ለዓለም የሴቶች ኮሚቴም ተጨማሪ በጀት እንዲሰጣት ጠየቀች.....
💫ይቀጥላል💫
ካርለትም በወባ በሽታ ተይዘው የሞቱትን፣ የአውሬ ሲሳይ የሆኑትን፣ በነፍሰ ገዳይ የተገደሉትን ስትሰማ፣ በዚህ ውጣ ውረድ በበዛው የሙያ መስክ ለመሰማራት ማሰቧ እራሷን ለመከራና ችግር መዳረግ ይሆናል ብላ በመገመቷ የተሳሳተ የሕይወት መሥመር
የተከተለች መስሏት ሰግታ ነበር" እንዳጋጣሚ ሆኖ ግን፣ እርቃ ሳትሄድ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ጽሑፎችን ስታነብና
ከተመራማሪዎች አንደበት የሚወጣውን ንግግር ስታዳምጥ፣የነበራትን ጥላቻ ለመመርመር ተገደደች።
መኖርና መሞት የሰው ልጅ አይቀሬ ዕጣ ፈንታ ቢሆንም ዓላማ ያላቸው ሰዎች አለመሞታቸውን የሚያረጋግጡት በእስትንፋሳቸው
መኖር ሳይሆን ለሕብረተሰቡ በሚያበረክቱት መልካም የሥራ ውጤት መሆኑን ስለምታምን፣እሷም በሕይወት መኖሯን
የማስመከር፣ በተለይም ሰው ሠራሽ ጾታዊ ግድቡን የማፍረስ ተልዕኮ
እንዳላት ገባት።
ካርለት ዕድሜዋ አሥራ ሁለት ዓመት ሲሆን፣ አባቷ ቻርልስ አልፈርድ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛ መምህር በመሆን እ.ኤ.አ እስh 1955 ዓ.ም ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ስለ ደቡብ አፍሪካ የነጮችና ጥቁሮች ቋንቋና ኢትኖግራፊ ጥናት በማካሄድ በርካታ ጽሑፎችን ያቀረቡና ለንደን በሚገኘው የአንትሮፖሎጂስቶች
መዕከል ፕሮፌሰር የነበሩ ናቸው።
ካርለት በወርቃማው የወጣትነት ዘመኗ እንደማንኛውም የታላቋ
ብሪታንያ ወጣት ሁሉ ብርቅዬ በሆኑ አልባሳት አጊጣ ከአገሯ አልፋ
ፈረንሳይን፣ ጀርመንን፣ እስፓኝን ካናዳን...በማካለል ተዝናንታለች" ካርለት በእናቷ ትብብር ፒያኖና ቫዮለን የሙዚቃ መሣሪያዎች አጨዋወት የተማረች ቢሆንም ከሙዚቃው ይልቅ
ስሜቷ ወደ ፎቶግራፍ ማንሣት ጥበብ ስላጋደለ የፎቶግራፍ ጥበቡን
ጀመረችI ሆኖም በዚህም ብዙ ሳትገፋ ተወችው።
ካርለት ምርጫዋን ለማስተካከል ተስኗት ከፊል ጊዜዋን በመዝናናት ስታሳልፍ አባቷ ቻርልስ ዘመኑ ያቀረበላትን ማዕድ
ባርከው ሲለግሷት፣ በወቅታዊው እፍ እፍ ስሜቷ ውስጥ ጣልቃ ባይገቡም እንኳን ሕሊናቸው በወደፊት የልጃቸው ዕጣ ሕይወት
መባዘኑ አልቀረም። ሜዲትራኒያንንና የሰሃራ በረሃን አቋርጠው በመጓዝ ስላዩት ተፈጥሮ፣ ባህልና ይዘው ስለተመለሱት የጥናትናዐምርምር ውጤት ሲያወጓት፣ «እባክህ አባዬ የወሬ ርዕስህን ቀይርና
ይልቁንስ ሽርሽር ይዘኸኝ ውጣ...» ስትላቸው፣ ምንም እንኳን ስሜታቸውን በገጽታቸው ባይገልጹትም ውስጥ ውስጡን ያማቸው
ነበር" ያም ሆኖ ግን ልጃቸውን ጥናታቸውን ወደ አከናወኑበት ደቡብ
አፍሪካ ሲወስዷት እግረ መንገዳቸውን በተፈጥሮ ሀብታቸውና ቅርሳቸው የሚያደንቋቸውን አገሮች ኢትዮጵያን፣ ኬንያንና
ዝንቧቡዌን አስጐበኟት
እ.ኤ.አ በ1970 ዓ.ም ፕሮፌሰር ቻርልስ በአደረባቸው የልብ
ካንሰር ሕመም ምከንያት ፒጃማ ለብሰው ቤት መዋል ከጀመሩና እልፈተ ሕይወታቸው በግል ሐኪማቸው ከተረጋገጠ ማግስት ጀምሮ ስለ አባቷ የተጻፉ አስተያየቶችና አድናቆቶች የገዛ አባቷን
ገድል እንደምትመረምር ጋበዟት"
ካርለት ለመጀመሪያ ጊዜ ካሸለበችበት በመንቃት የአባቷን ወርቃማ ሥራዎች ለመረዳት ተጣጣረች ጥረቷ የዘገየና ፀሐይ ከጠለቀ በኋላ በመሆኑ ግራ ብትጋባም፣ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ዓላማቸውንና ያደረጉትንም አስተዋፅኦ ተገነዘበች" ያ ወቅት
በእርግጥ የወጣትነት ቡረቃዋን ገትታ፣ ዘላቂውን የሕይወት ድርሻዋን፣ የምትከተለውን ዓላማ ያጤነችበት፣ የረጋው ፍላጎቷ
ማዕበሉ ተጠናክሮ የዋዠቀችበትና በመጨረሻም መልሕቋን
በመወርወር ለውሳኔ የበቃችበት ወቅት ሆነ።
ወርቃማው ጸጕሯ፣ ድሎት ያወረዛው ፊቷና መካከለኛው ቁመናዋ በጅምናስቲክ በተገነባው ቅርፅዋ እየተረዱ የብዙ ወንዶችን ልብ ያሸፈቱ ቢሆኑም፣ ተባባሪ የውበት አለኝታዎቿ አቅመ ቢስ
ሆነውባት እሷም በፍቅር ቡጢ ጥርሷ እስኪነቃነቅና እንባዋ እስኪጐርፍ ድረስ አፍቅራ ተመናቅራለች እንዲያውም ይህ ልምዷ
የተመኙትን ሁሉ ማግኘት አለመቻሉን፣ ፈላጊና ተፈላጊ መተላለፍ የሚያበዙ መሆናቸውንና የፈለጋት እንዲያገኛት በተቻለ መጠን
መገኘት የሚያስችላትን ቦታ ፈልጋ እንድታገኝ ረዳት
ካርለት፣ በሕይወቷ ሽንፈት ደጋግሞ እንደሚያጋጥማት
ታምናለች የምትፅናናበት ግን በፍላጎቷ ወደ ውድድር መድረክ መቅረቧና ከማን ከማን ጋር እንደምትወዳደር ማወቋ ነው «ከተወዳዳሪዎቹ ሁሉ ጅሉ ሰው በውድድሩ ተካፍሎ ለማሸነፍ በመጣጣር
አልሳካልህ ብሎ የተሸነፈው ሳይሆን፣ መወዳደሩንና ተወዳዳሪዎቹን ሳያውቅ ለድል የበቃው ነው» ማለት ታዘወትራለች።
ካርለት የማንችስተር ዩኒቨርሲቲ የአንትሮፖሉጂ ዲፓርትመንት አባል ሆና የማስተር ዲግሪዋን ካገኘች በኋላ፣ ለቀረው ጥናቷ ቀደም ሲል አባቷ ካሳይዋት አገሮች ኢትዮጵያን መረጠች በማከታ ተልም ኢትዮጵያ ነከ የሆኑ የጽሑፍ፣ የፊልምና የስላይድ መረጃዎችን
በየጕራንጕሩ ሁሉ እያነፈነፈች ከተመለከተች፣ በተለይም ስለ ኢትዮጵያ ዕውቀት ካላቸው አማካሪዋ ከፕሮፌሰር ጆን ፒደርሰን ጋራ በወደፊት የጥናት ቦታዋ ላይ በስፋት ከተመካhሩ በኋላ በእንግሊዝ የምሥራቅ አፍሪካ አንትሮፖሎጂስቶች የጥናት ድርጅት አባል
ሆነች ከዚያም በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ማኅበረሰቦች ውስጥ በሐመር ማኅበረሰብ ባህል ላይ ጥናቷን ለመጀመር ከአማካሪዋ ጋር ተስማሙ። ልታከናውን ላሰበችው ጥናትም የእርዳታ ሐሳብ
ለድርጅቱ አቀረበች ድርጅቱም የጠየቀችውን በጀት አጸደቀላት።ካርልት፣ በዚህ በጀት ብቻም ሳትወሰን ለዓለም የሴቶች ኮሚቴም ተጨማሪ በጀት እንዲሰጣት ጠየቀች.....
💫ይቀጥላል💫
👍35🥰1
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሀያ ዘጠኝ (29)
«ውዴ . . . እስኪ ዚፔን ዝጋልኝ » ብላ ውብ ጀርባዋን አዞረችለት « እኔ እንኳ ደስ የሚለኝ… ብከፍተው ነበር››
«ፒተር ! . . . እንዲህ ያለ ወሬ… » አለች በማስጠንቀቅ መልክ ተገላምጣ እያያችው ። ሁለቱም ሳቁ ። አለባበሷን ሲመለከት ፣ ውበቷን ሲያይ በአድናቆት ተዋጠ ። «በኋላ ምን ብሎ ነበር ብለሽ ናቂኝ አንድ ሰው ፎቶግራፍሽን ቢያይ ከምላሴ ጠጉር »
« ለምን?»
«የተመልካች ዓይን አንቺው ላይ ያርፋል ። እዚያ ተተክሎ ይቀራል። በቃ !»
« ያን ያህል ?» ይህን ስትል ያለውን ነገር ፈጽሞ እንዳላመነች ገባው ። ጥርጣሬዋ የመገረም ሳቅ አሳቀው ። እሱም በኤግዚብሽን መክፈቻ ላይ ሽክ ብሎ ለብሷል ። ቢጋቡ የሚያስቀኑ ባልና ሚስት ይሆናሉ። «እንዴት ነው ? ፎቶ ግራፎቹን እንደምትፈልጊው አድርገው ሰቀሉልሽ ? ጊዜው ጠፋና ይህን እንኳ ልጠይቅሽ አልቻልኩም»
«ምንም ችግር የለም ። ያዘዝኩት ሁሉ እንዳዘዝኩት ሆኖ ተፈጽሟል ። እድሜ ላንተ ፤ ፒተር ። ይኸኔ ቅር ይላትና ዋ! ብለሀቸዋል ። ወይ አንተ ወይ ጃክ ይህን ያላችሁ ይመስለኛል » ጃክ የኤግዚብሽኑ አዳራሽ ባለቤት ሲሆን የፒተር ግሬሰ? የረጂም ጊዜ ጓደኛ ነው ። « ሁሉን ነገር ሰው ይሰራዋል ። እኔ በቃ አርቲስት ብቻ ነኝ የሚል ስሜት ይሰማኝ ጀመር››
«ሊሰማሽ የሚገባ ነው። ይሀ ትርኢት ሲያልቅ የኪነጥበብ ስራሽ ምን ያህል ዋጋ እንዳለው ያኔ ታያለሽ ።»
እንዳለውም ሆነ ። ኤግዚብሽኑ በተከፈት ማግስት በጋዜጦች ላይ የተሰጡ አስተያየቶች በአድናቆት የተሞሉ ነበሩ። ፒተርና ሜሪ ጧት ቁርሳቸውን በልተው ቡና እየጠጡ ጋዜጦችን ሲያነቡ በጣም ደስ አላቸው ። «አላልኩሽም ?» አላት ፒተር ፤ ገና የመጀመሪያውን በአድናቆት የተሞላ አስተያየት ሲያነብ « አየሽ ? ኮከብ ነሽኮ »
«አንተ ደሞ ጅል ነህ ! » አለችና ጋዜጣውን አስደገፈበት ጭኑ ላይ ዘጭ ብላ ተቀመጠችበት ። ጋዜጣው ተጨማደደ። «እስከሚቀጥሊው ሳምንት ቆይና ደሞ ሌላ ተአምር ታያለሽ ። እያንዳንዱ ፎቶግራፍ እያራባ የሚሸጥ ድርጅትና ፎቶግራፍ አሻሻጭ ከመላ ሀገሪቱ ዳር እስከዳር ስልክ እየደወለ ባያስቸግርሽ ቱ! ከምላሴ ፀጉር ! »
«በቃ አዕምሮሀን እንደመንሳት እያደረገህ ነውኮ ውዴ!» ሆኖም የፒተር ግምት ሜሪ የገመተችውን ያህል ከእውነት የራቀ አልነበረም ። በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከተለያዩ ቦታዎች ከተለያዩ ሰዎች የስልክ ጥሪዎች ይመጡ ጀመር። ሰኞ ዕለት ከሎስ አንጀለስ እና ከችካጐ የተለያዩ ጥሪዎች ደረሷት ። እያንዳንዱ ሰው ስልክ ደውሎ የሚያቀርብላት ጥያቄና አድናቆት አስደነቃትም ። አስደሰታትም ። ስለዚህም ስልክ በተደወለ ቁጥር አሁን ደግሞ ምን ይሉ ይሆን ? በሚል ጉጉት ስልኩን ታነሣለች ። ይህ ቀጠለ ፤ ቤን አቭሪ እስኪደውልላት ድረስ ።
ቤን አቭሪ የደወለው አንድ ማክሰኞ ቀን ወደ ማታ አካባቢ ነበር ። በዚያም ሰዓት ሜሪ ፊልሞችን ለማሳደግና ለማጣብ በማሰናዳት ላይ ነበረች ። ከተለያዩ ቦታዎች ፎቶግራፎቿን ለመግዛት የትእዛዝ ጐርፍ መጉረፍ ጀምሮ ስለነበር ከፎቶግራፍ ማጠቢያው ክፍል (ዳርክ ሩም) ለመውጣት እንኳ ጊዜ አነበራትም ። በሥራዋ ተመስጣ እያለች ስልኩ ተንጫረረ። ሥራዋን አቋርጣ እየተጣደፈች ወጣች ። ምክንያቱም ፒተር «በዚያ ሰዓት ስብሰባ ስላለብኝ ደውዬ የት እንደምንገናኝ እነግርሻለሁ » ብሏት ነበር ። ስልኩን አንሥታ «ሃሎ » አለች ። «ሚስ አዳምሰን» አለ አንድ የማታውቀው ድምጽ፡፡ «ነኝ» አለች ፒተር ስለመሰላት በገጽታዋ ላይ ፈክቶ የነበረው ፈገግታዋ እየጨለመ ። «አኦ.. ከዚህ በፊት ለገና በዓል የስጦታ ዕቃዎችን ስገዛ ሚስ አዳምሰን ከምትባል ሰው ጋር ተዋውቀን ነበር ። ከሞክሼሽ ጋር ይሁን ካንቺ ጋር እርግጠኛ አይደለሁም ። የጉዞ ሻንጣዎች ስገዛ ተገናኝተን... » ቤን ነው ማለት ነው ። አይደለሁም ልበለው? ለምን?
« ከኔ ጋር ሳይሆን አልቀረም » አለች…. መዋሸት የሚያስፈልግ አልመሰላትም ። «ማለቴ ...እኔ.. ነው ? ማለት የማውቃት ሚስ አዳምሰን ነሻ ? »
«ነኝ»
« ይህንን ማረጋገጡም አንድ ነገር ነው ። ማለት ተቀራርበን ለመነጋገር ባንችልም እንተዋወቃለን ። ብቻ አሁን የደወልኩልሽ እንኳ የያኔ ትውውቃችንን በሚመለከት አይደለም ። የፎቶግራፍሽን ኤግዚብሽን ስላየሁ አንዳንድ ነገር እንድንነጋገር ስለፈለኩ ነው ።. ...ግሩም የሆነ ሥራ ነው ሚስ አዳምሰን ። እኔም ጓደኛዬ ሚስ ታውንሴንድም ኤግዚብሽኑን ዓይተን የተሰማን ስሜት ከፍተኛ ነው » የጠራት ሴት ዕቃው የተገዛላት ሴት ትሆን ? የማወቅ ፍላጐት አደረባት ። ሆኖም መጠየቅና ማወቁ አስፈላጊ መስሎ አልተሰማትም ። ስለዚህም በረጂሙ ተንፍሳ…. «ደስ ስለተሰኛችሁ እኔም ደስ ብሎኛል ፤ ሚስተር አቭሪ›› አለች ።
« ስሜንም አልረሳሽም?»
«ስሞችና የመሳሰሉ ነገሮችን አልረሳም ። አንድ ዓይነት እነዚህን ነገሮች የማያስረሳ ተፈጥሮ አለኝ »
«መታደል ነው ። እኔ ደሞ የስም ነገር አይሳካልኝም ። ይኽ ደሞ ለሥራዬ ጥሩ ነገር አይደለም። አንጐሌ ወንፊት ቢጤ ሆኖ ሲፈጠር ጊዜ ምን ማድረግ ይቻለኛል ! ወደ ፍሬ ነገሩ ልመለስና ተገናኝተን ስለሥራዎችሽ ብንነጋገር በጣም ደስ ይለኝ ነበር ።»
« በምን መንገድ ? » አለች ። ምን የሚያነጋግረን ነገር ተፈጠረ ደግሞ ! አለች በሐሳቧ ። «እንዲህ ነው ሚስ አዳምሰን ። እዚህ ሳንፍራንሲስኮ ውስጥ አንድ የሕክምና ማዕከል ሕንፃ በመሥራት ላይ እንገኛለን ። በጣም ግዙፍ የሆነ ፕሮጄክት ነው ። ፕሮጀክቱን ስንቀበል ከገባናቸው ውሎች አንዱ ሕንፃውን እስከማስዋብ ያለውን ሥራ ፈጽመን ማስረከብ እንዳለብን ይገልጸል ። ያንችን ፎቶግራፎች ስመለከት ለዚህ ተግባር በጣም ሊያገለግሉን እንደሚችሉ ተረድቻለሁ ። እንዴት አድርገን በምን ሁኔታ እንደምንጠቀምባቸው ግልጽ የሆነልን ነገር የለም ። ስለዚህም ተገናኝተን ይህንን ጭምር ብንወያይበት ደህና ገቢም ይኖረዋል ። ላንቺም ቢሆን ሥራሽን ያስተዋውቅልሻል» አለ ቤን ። ይህን ሲናገር በሙሉ ልቡ እንደነበረ ድምጹ ይናገራል፡፡ «ገባኝ።. . . ግን የትኛውን ድርጅት ወክለህ እንዳነጋገርከኝ ልትነግረኝ ትፈቅዳለህ ? » አለች ። ድርጅቱ ማን ሊሆን እንዶሚችል ስለጠረጠረች ፤ ከላይ ከላይ ሊላት ያሰበውን ትንፋሷን ቁጥር አድርጋ መጠባበቅ ጀመረች ።
«ድርጅቱ» አለ ቤን ኮራ ብሎ «የኒውዮርኩ ኮተር ሂልያርድ ነው»
«ነው... ስላሰብክልኝ አመሰግናለሁ።፤ ሚስተር አቭሪ ግን አይሆነኝም »
«አይሆነኝም ? ለምን ?» አለ የመደመም በሆነ ድምጽ
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሀያ ዘጠኝ (29)
«ውዴ . . . እስኪ ዚፔን ዝጋልኝ » ብላ ውብ ጀርባዋን አዞረችለት « እኔ እንኳ ደስ የሚለኝ… ብከፍተው ነበር››
«ፒተር ! . . . እንዲህ ያለ ወሬ… » አለች በማስጠንቀቅ መልክ ተገላምጣ እያያችው ። ሁለቱም ሳቁ ። አለባበሷን ሲመለከት ፣ ውበቷን ሲያይ በአድናቆት ተዋጠ ። «በኋላ ምን ብሎ ነበር ብለሽ ናቂኝ አንድ ሰው ፎቶግራፍሽን ቢያይ ከምላሴ ጠጉር »
« ለምን?»
«የተመልካች ዓይን አንቺው ላይ ያርፋል ። እዚያ ተተክሎ ይቀራል። በቃ !»
« ያን ያህል ?» ይህን ስትል ያለውን ነገር ፈጽሞ እንዳላመነች ገባው ። ጥርጣሬዋ የመገረም ሳቅ አሳቀው ። እሱም በኤግዚብሽን መክፈቻ ላይ ሽክ ብሎ ለብሷል ። ቢጋቡ የሚያስቀኑ ባልና ሚስት ይሆናሉ። «እንዴት ነው ? ፎቶ ግራፎቹን እንደምትፈልጊው አድርገው ሰቀሉልሽ ? ጊዜው ጠፋና ይህን እንኳ ልጠይቅሽ አልቻልኩም»
«ምንም ችግር የለም ። ያዘዝኩት ሁሉ እንዳዘዝኩት ሆኖ ተፈጽሟል ። እድሜ ላንተ ፤ ፒተር ። ይኸኔ ቅር ይላትና ዋ! ብለሀቸዋል ። ወይ አንተ ወይ ጃክ ይህን ያላችሁ ይመስለኛል » ጃክ የኤግዚብሽኑ አዳራሽ ባለቤት ሲሆን የፒተር ግሬሰ? የረጂም ጊዜ ጓደኛ ነው ። « ሁሉን ነገር ሰው ይሰራዋል ። እኔ በቃ አርቲስት ብቻ ነኝ የሚል ስሜት ይሰማኝ ጀመር››
«ሊሰማሽ የሚገባ ነው። ይሀ ትርኢት ሲያልቅ የኪነጥበብ ስራሽ ምን ያህል ዋጋ እንዳለው ያኔ ታያለሽ ።»
እንዳለውም ሆነ ። ኤግዚብሽኑ በተከፈት ማግስት በጋዜጦች ላይ የተሰጡ አስተያየቶች በአድናቆት የተሞሉ ነበሩ። ፒተርና ሜሪ ጧት ቁርሳቸውን በልተው ቡና እየጠጡ ጋዜጦችን ሲያነቡ በጣም ደስ አላቸው ። «አላልኩሽም ?» አላት ፒተር ፤ ገና የመጀመሪያውን በአድናቆት የተሞላ አስተያየት ሲያነብ « አየሽ ? ኮከብ ነሽኮ »
«አንተ ደሞ ጅል ነህ ! » አለችና ጋዜጣውን አስደገፈበት ጭኑ ላይ ዘጭ ብላ ተቀመጠችበት ። ጋዜጣው ተጨማደደ። «እስከሚቀጥሊው ሳምንት ቆይና ደሞ ሌላ ተአምር ታያለሽ ። እያንዳንዱ ፎቶግራፍ እያራባ የሚሸጥ ድርጅትና ፎቶግራፍ አሻሻጭ ከመላ ሀገሪቱ ዳር እስከዳር ስልክ እየደወለ ባያስቸግርሽ ቱ! ከምላሴ ፀጉር ! »
«በቃ አዕምሮሀን እንደመንሳት እያደረገህ ነውኮ ውዴ!» ሆኖም የፒተር ግምት ሜሪ የገመተችውን ያህል ከእውነት የራቀ አልነበረም ። በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከተለያዩ ቦታዎች ከተለያዩ ሰዎች የስልክ ጥሪዎች ይመጡ ጀመር። ሰኞ ዕለት ከሎስ አንጀለስ እና ከችካጐ የተለያዩ ጥሪዎች ደረሷት ። እያንዳንዱ ሰው ስልክ ደውሎ የሚያቀርብላት ጥያቄና አድናቆት አስደነቃትም ። አስደሰታትም ። ስለዚህም ስልክ በተደወለ ቁጥር አሁን ደግሞ ምን ይሉ ይሆን ? በሚል ጉጉት ስልኩን ታነሣለች ። ይህ ቀጠለ ፤ ቤን አቭሪ እስኪደውልላት ድረስ ።
ቤን አቭሪ የደወለው አንድ ማክሰኞ ቀን ወደ ማታ አካባቢ ነበር ። በዚያም ሰዓት ሜሪ ፊልሞችን ለማሳደግና ለማጣብ በማሰናዳት ላይ ነበረች ። ከተለያዩ ቦታዎች ፎቶግራፎቿን ለመግዛት የትእዛዝ ጐርፍ መጉረፍ ጀምሮ ስለነበር ከፎቶግራፍ ማጠቢያው ክፍል (ዳርክ ሩም) ለመውጣት እንኳ ጊዜ አነበራትም ። በሥራዋ ተመስጣ እያለች ስልኩ ተንጫረረ። ሥራዋን አቋርጣ እየተጣደፈች ወጣች ። ምክንያቱም ፒተር «በዚያ ሰዓት ስብሰባ ስላለብኝ ደውዬ የት እንደምንገናኝ እነግርሻለሁ » ብሏት ነበር ። ስልኩን አንሥታ «ሃሎ » አለች ። «ሚስ አዳምሰን» አለ አንድ የማታውቀው ድምጽ፡፡ «ነኝ» አለች ፒተር ስለመሰላት በገጽታዋ ላይ ፈክቶ የነበረው ፈገግታዋ እየጨለመ ። «አኦ.. ከዚህ በፊት ለገና በዓል የስጦታ ዕቃዎችን ስገዛ ሚስ አዳምሰን ከምትባል ሰው ጋር ተዋውቀን ነበር ። ከሞክሼሽ ጋር ይሁን ካንቺ ጋር እርግጠኛ አይደለሁም ። የጉዞ ሻንጣዎች ስገዛ ተገናኝተን... » ቤን ነው ማለት ነው ። አይደለሁም ልበለው? ለምን?
« ከኔ ጋር ሳይሆን አልቀረም » አለች…. መዋሸት የሚያስፈልግ አልመሰላትም ። «ማለቴ ...እኔ.. ነው ? ማለት የማውቃት ሚስ አዳምሰን ነሻ ? »
«ነኝ»
« ይህንን ማረጋገጡም አንድ ነገር ነው ። ማለት ተቀራርበን ለመነጋገር ባንችልም እንተዋወቃለን ። ብቻ አሁን የደወልኩልሽ እንኳ የያኔ ትውውቃችንን በሚመለከት አይደለም ። የፎቶግራፍሽን ኤግዚብሽን ስላየሁ አንዳንድ ነገር እንድንነጋገር ስለፈለኩ ነው ።. ...ግሩም የሆነ ሥራ ነው ሚስ አዳምሰን ። እኔም ጓደኛዬ ሚስ ታውንሴንድም ኤግዚብሽኑን ዓይተን የተሰማን ስሜት ከፍተኛ ነው » የጠራት ሴት ዕቃው የተገዛላት ሴት ትሆን ? የማወቅ ፍላጐት አደረባት ። ሆኖም መጠየቅና ማወቁ አስፈላጊ መስሎ አልተሰማትም ። ስለዚህም በረጂሙ ተንፍሳ…. «ደስ ስለተሰኛችሁ እኔም ደስ ብሎኛል ፤ ሚስተር አቭሪ›› አለች ።
« ስሜንም አልረሳሽም?»
«ስሞችና የመሳሰሉ ነገሮችን አልረሳም ። አንድ ዓይነት እነዚህን ነገሮች የማያስረሳ ተፈጥሮ አለኝ »
«መታደል ነው ። እኔ ደሞ የስም ነገር አይሳካልኝም ። ይኽ ደሞ ለሥራዬ ጥሩ ነገር አይደለም። አንጐሌ ወንፊት ቢጤ ሆኖ ሲፈጠር ጊዜ ምን ማድረግ ይቻለኛል ! ወደ ፍሬ ነገሩ ልመለስና ተገናኝተን ስለሥራዎችሽ ብንነጋገር በጣም ደስ ይለኝ ነበር ።»
« በምን መንገድ ? » አለች ። ምን የሚያነጋግረን ነገር ተፈጠረ ደግሞ ! አለች በሐሳቧ ። «እንዲህ ነው ሚስ አዳምሰን ። እዚህ ሳንፍራንሲስኮ ውስጥ አንድ የሕክምና ማዕከል ሕንፃ በመሥራት ላይ እንገኛለን ። በጣም ግዙፍ የሆነ ፕሮጄክት ነው ። ፕሮጀክቱን ስንቀበል ከገባናቸው ውሎች አንዱ ሕንፃውን እስከማስዋብ ያለውን ሥራ ፈጽመን ማስረከብ እንዳለብን ይገልጸል ። ያንችን ፎቶግራፎች ስመለከት ለዚህ ተግባር በጣም ሊያገለግሉን እንደሚችሉ ተረድቻለሁ ። እንዴት አድርገን በምን ሁኔታ እንደምንጠቀምባቸው ግልጽ የሆነልን ነገር የለም ። ስለዚህም ተገናኝተን ይህንን ጭምር ብንወያይበት ደህና ገቢም ይኖረዋል ። ላንቺም ቢሆን ሥራሽን ያስተዋውቅልሻል» አለ ቤን ። ይህን ሲናገር በሙሉ ልቡ እንደነበረ ድምጹ ይናገራል፡፡ «ገባኝ።. . . ግን የትኛውን ድርጅት ወክለህ እንዳነጋገርከኝ ልትነግረኝ ትፈቅዳለህ ? » አለች ። ድርጅቱ ማን ሊሆን እንዶሚችል ስለጠረጠረች ፤ ከላይ ከላይ ሊላት ያሰበውን ትንፋሷን ቁጥር አድርጋ መጠባበቅ ጀመረች ።
«ድርጅቱ» አለ ቤን ኮራ ብሎ «የኒውዮርኩ ኮተር ሂልያርድ ነው»
«ነው... ስላሰብክልኝ አመሰግናለሁ።፤ ሚስተር አቭሪ ግን አይሆነኝም »
«አይሆነኝም ? ለምን ?» አለ የመደመም በሆነ ድምጽ
👍14
«የምትይው አልገባኝም?»
«በዚህ በዚህ ምክንያት ልልህ አልፈልግም ሚስተር አቭሪ ። ፍላጐቴ እንዳልሆነ ብቻ ብትረዳልኝ ይበቃል»
«ተገናኝተን ልንነጋገር ብንችል ደግ ይመስለኛል ። ማለቴ በነገሩ ላይ»
«ምንም ንግግር አያስፈልግም»
«ግን... እዪው ይህን ነገር አስቀድሜ ነግሬአለሁ... .ለ..ለ...እኔ...»
«ምንም ብትለኝ መልሴ አንድ ነው ። አይቻልም ። አመሰግናለሁ ፤ ደህና ሁን ሚስተር አቭሪ»
ይህን ብላ የስልኩን መነጋገሪያ በቀስታ ወደ ቦታው መለሰችው ። ሥራዋን ለመቀጠል ፊልም ማዘጋጃውና ፎቶግራፍ ማጠቢያው ጨለማ ክፍል ስትሄድ ፤ የለም ለዚህ ድርጅትስ አልሠራም ለማይክል ሂልያርድ አጎልግሎት ለመስጠት ?! ምን በወጣኝ አለች ። ሚስቴ ልትሆኚ አትበቂም ብሎ አይደለም የተዋት ። እሷም ቀጣሪዬ ልትሆን ብቁነት አላይብህም ፤ምኔም ምኔም ለመሆን ብቁ አይደለህም ። ልትለው ያስፈልጋል… ይህን አሰበች ።
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
«በዚህ በዚህ ምክንያት ልልህ አልፈልግም ሚስተር አቭሪ ። ፍላጐቴ እንዳልሆነ ብቻ ብትረዳልኝ ይበቃል»
«ተገናኝተን ልንነጋገር ብንችል ደግ ይመስለኛል ። ማለቴ በነገሩ ላይ»
«ምንም ንግግር አያስፈልግም»
«ግን... እዪው ይህን ነገር አስቀድሜ ነግሬአለሁ... .ለ..ለ...እኔ...»
«ምንም ብትለኝ መልሴ አንድ ነው ። አይቻልም ። አመሰግናለሁ ፤ ደህና ሁን ሚስተር አቭሪ»
ይህን ብላ የስልኩን መነጋገሪያ በቀስታ ወደ ቦታው መለሰችው ። ሥራዋን ለመቀጠል ፊልም ማዘጋጃውና ፎቶግራፍ ማጠቢያው ጨለማ ክፍል ስትሄድ ፤ የለም ለዚህ ድርጅትስ አልሠራም ለማይክል ሂልያርድ አጎልግሎት ለመስጠት ?! ምን በወጣኝ አለች ። ሚስቴ ልትሆኚ አትበቂም ብሎ አይደለም የተዋት ። እሷም ቀጣሪዬ ልትሆን ብቁነት አላይብህም ፤ምኔም ምኔም ለመሆን ብቁ አይደለህም ። ልትለው ያስፈልጋል… ይህን አሰበች ።
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍14
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከኢትዮጵያ ጥናትና ምርምርና ከሌሎች ተቋማት ለጥናቷ
አስፈላጊ የሆኑትን ውጤቶች ካነበበችና ከግለሰቦች ጋር ሐሳብ
ለሐሳብ ከተለዋወጠች በኋላ እግረ መንገዷን ሊረዳት የሚችል የክልሉ ተወላጅ አድራሻ፣ የጥናትና የጕዞ ፈቃድ አውጥታ ወደ
ጥናት ቦታዋ ከመጓዟ በፊት ምሽቱን በአዲስ አበባው ሒልተን እንግሊዝ ኤምባሲ ከሚሠራውና ለተወሰኑ ወራት በአዲስ አበባው
ቆይታዋ ጠረኑን ከለመደችው ጓደኛዋ ጋር እቅፉ ውስጥ ስትንቀሳቀስ
አድራ እንደገና ገላዋን ታጠበችና ልብሷን ለባብሳ ወጣች"
በአስተሳሰቧ፣ በግልጽነቷና በውበቷ የነሆለለው ስቲቭ
አለባበሷን፣ ከሰዓታት በፊት ፍቅር አመንጪ የነበረው አካሏ ተለውጦ ለሥራ መዘጋጀቷን ሲያይ እሱ ፍቅር ከፈጠረው የደስታ
ዓለም ከነበረበት ፈጽሞ ሳይንቀሳቀስ እሷ ግን ገስግሳ ወደ ገሐዱ
ዓለም በመመለሷ በፍጥነቷ ተደንቆ በተመስጦ ሲመለከታት ቆየና፣
«የኔ ቆንጆ አሁንም ታምሪያለሽ» አላት።
«ማማሬን እርሳው» አለችው።
«ለምን?»
«ከጥቂት ሰዓታት በፊት እኔም እረስቸዋለሁና።»
«የኔ ቆንጆ፣ ታዲያ ምን እንድልሽ ትፈልጊያለሽ?»
«የጉጉትን ዘዴ፣ የንስርን ማስተዋል፣ የአንበሳን ልብ፣ የኢዮብን ትዕግሥት፣ የአባትሽን ተስፋ አይቆርጤነትና አእምሮ ይስጥሽ በለኝ» ብላ፣ ጉንጩን ሳም አደረገችው"
ስቲቭ አስተያየቱን ጠለቅ አድርጎ ሲያስተውላት ቆየና፣ «አሁን አንችን የመሰለ ውብ ከእነዚያ ዘላኖች...» ሊናገር የፈለገውን ሳታስጨርሰው አፉን በአመልካች ጣቷ ከደነችው።
«ማፍቀር ያለብህ እኔን ብቻ ሳይሆን ፍላጎቴንም እንዲሆን እፈልጋለሁ" ትልቁ ውበት ደግሞ ሥራ መሆኑን አትዘንጋ» አለችውና ሌላ ቃል ሳይለዋወጡ ለቁርስ ክፍሉን ቆልፈው ወጡ"
።።።።።።።።።።።።።
ፈርጠም ያለ፣ የቀይ ሽንኩርት ቅርፅ መሳይ አፍንጫ ያለው! ዳጐስ ብሎ ቀላ ያለውን ከንፈሩን ሲገልጥ ነጫጭ ፍልጥ ጥርሶቹ የሚያማምሩና ከሸበላው ቁመናው ጋር የተስተካከለ አቋም ያለው
ከሎ ሆራ ለየት ያለ ባሕርይ ይታይበታል።
ቁጥብነቱን፣ ጅንንነቱን፣ ጥርጣሬውንና ብቸኝነት መውደዱን ያዩ ጓደኞቹ፣ «ነብሮ» ይሉታል የዩኒቨርሲቲ ጓደኞቹ" ቀልድ፣
ቧልት ከጀመሩለት እንደ ቆሰለ ጎሽ በንዴት ጦፎ ይፎገራል" ከሰው ጋር ደጋግሞ እንደ መጣላቱ ግን ኃይሉን ተማምኖ ተማቶ
አያውቅም" ሁለቴ ሦስቴ ቃጥቶ ቃጥቶ ማንም በማይገባው ቋንቋ
አኩተምትሞ ዘወር ይላል" ታዲያ ብዙዎቹ አዳልጧቸው ቀልድ ብጤ ጀማምረው በዚያ ፈርጣማ ጡንቻው በሰነዘረ ቁጥር ጠረመሰን
እያሉ አንዴ ከተሳቀቁ፣ «እርም» ብለው ይሸሹታል" ስለዚህ ምን እንደሚያበሽቀው ያለፈው ሕይወቱ ምን እንደሚመስል፣
ብቸኝነቱ ከመቼ ወዲህ እንደ ጀመረው ከፍቶ ማየት የሚችል ሰው አልተገኘም ግለቱ ስላላስቀረበ"
የተማሪን ቆብ አውላቂ መምህራን በለመዱት ቧልት «ጢብ ጢብ» ሊጫወቱበት ይዳዳቸውና እንደ ከለመዳሪ የሚነፋውን
ከንፈሩንና እሳት ተፊ ትናንሽ ዓይኖቹን ሲያዩ በተለይም
በአንቀሳቀሰው ቁጥር እንደ አሎሎ የሚንከባለለውን ጡንቻውን ሲመለከቱ! «በቸር አውለኝ» ብለው አቅጣጫቸውን ሲቀይሩ
ዓመታት ተቈጠሩ“
ከሎ ሆራ የአራተኛ ዓመት የሶሲዮሎጂ ትምህርቱን ሊያጠናቅቅ በተቃረበበት ወቅት በቀጭን ወገቧ ጂንስ ሱሪዋን በቀላል «ቲሸርት» አስተካክላ ለብሳ፣ የተጐነጐነ ረዥም ጸጕሯን ወገቧ ላይ እያላጋች፣ ቶሎ ቶሎ በመራመድ ጫማዋን ቀጭ ቋ ቀጭ ቋ እያደረገች የምትገሰግሰው ወጣት ከዩኒቨርሲቲው ፖስታ ቤት ወረድ ብሎ ከሚገኘው ኮሪደር ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ እግሩን እያወዛወዘ!
ጠጠር ወደሚወረውረው ጥቁር ወጣት ተጠግታ፣ «ይቅርታ ከሎ ሆራ ነህ አይደለም?» ብላ ጠየቀችው፣ በእንግሊዝኛ"
«አዎ ነኝ» አለ ከሎ፣ ከተቀመጠበት ሳይንቀሳቀስ"
«ካርለት አልፈርድ እባላለሁ" እንግሊዛዊት አንትሮፖሎጂስት
ነኝ" ስለ ሐመር ሴቶች ጥናት ለማድረግ ዓላማ አለኝ" አንተም የሐመር ተወላጅ መሆንህን ከዲፓርትመንትህ ኃላፊ ጠይቄ አረጋግጫለሁ» አለችና ንግግሯን በመግታት ትኵር ብላ ተመለከተችው
ከሎ ሆራ፣ የመርበትበት ስሜት አሳየና ከተቀመጠበት ፈጥኖ ተነሣ
ላብ ከወደግንባሩና ቅንድቡ አካባቢ ችፍፍ ችፍፍ ሲል ከንፈሩ አመድ የነሰነሱበት መሰለ።
«ሶ ለምን ፈለግሽኝ?» አላት በተቆራረጠ ድምፅ
«እንድትረዳኝ እፈልጋለሁ» አለችው፣ በዓይኗ እየመረመረችው
«እንድትረዳኝ እፈልጋለሁ?» ብሎ አባባሏን ደገመና ለትንሽ ጊዜ የመመሰጥ ሁኔታ አሳይቶ፣
«አዝናለሁ፣ ልረዳሽ አልችልም» አላት"
ካርለት፣ የከሎ ሰውነት ሲለዋወጥና ከብስጭቱ ጋር ሲታገል ያስተዋለች መሰላት ስለዚህ ወጣቱ ከሷ ያለበለዚያም ራሱ ከራሱ
ጋር ያልተግባቡት ወይንም ለእሷ ግልጽ ያልሆነላት ሌላ ምክንያት እንዳለው በመረዳቷ ተጨማሪ ጥያቄ ሳታነሣ፣ «አመሰግናለሁ“ ነገ
ግን ጊዜ ወስደህ ካሰብክበት በኋላ ሐሳብህን ከቀየርክ አይ.ኢ.ኤስ
ልታገኘኝ ትችላለህ ካለዚያም ስልክ ቁጥሬን ልሰጥህ እችላለሁ» ብላ፣ ፍጹም ልብ በሚነካ ፈገግታ የአድራሻዋን ካርድ ሰጥታው
«ደህና ሁን» እያለች፣ እጇን አውለብልባለት ሄደች"
ከሎ ሆራ ወደ መቀመጫው ሲመለስ፣ የሚሰበቀውን ወገቧንና ጀርባዋ ላይ ከብለል ከብለል የሚለውን ጉንጉን ጸጕሯን ሲመለከት
ሐሳቡ ሸፈተበት" ከዓይኑ እስክትሰወር ድረስ በመደመም ሲመለከታት ቆየና ከጥቂት ደቂቃ በፊት የነበረበትን ድንገተኛ ሁኔታ ለማስታወስ ሞከረ» «ሐመር ጥናት ውብ እንግሊዛዊት የሐሳብ
ፍጥጫ፣ የተዳፈነ እሳት ጭረት.እሳት ጫሪ አንትሮፖሎጂስት...ወጣትና ውብ...ዳሚት» አለ፣ እጆቹን ከተቀመጠበት ደረጃ
ጋር እያላተመ።
።።።።።።።።።።።።።
ልቡ የአዶከበሬ አታሞ ይመስል እየተነረተ፣ ሰውነቱ ፀሐይ እንዳቆረናው የበረሃ ባልጩት ድንጋይ እያተኮሰ፣ እንቅልፍ ሲመኝ ግን ሲነቃ፣ ዕረፍትን ሲሻ፣ ሲንጠራወዝ፣ ሲገለባበጥ፣ በሐሳብ
ሲድህና ፎቀቅ ፎቀቅ ሲል አድሮ ዋለ"
ብዙ አወጣ አወረደI ያለፈ የልጅነት መጥፎ ትዝታውንም አስታወሰ" አሁን ሊያደርግ የማይፈልገውን እንዲያደርግ ግብዣው
ቀርቦለታል" ሌላው ቀን አልፏል። ለዛሬ ሥሩ ትናንት ነው" ትናንት ደግሞ እሱ የመከራ ጽዋውን የጨለጠበት ወቅት ነው" ዳግመኛ ሬት ሊያወርድ የሚችል ጉሮሮ የለውም” ስለዚህ በትናንት ቂም ያረገዘው አእምሮው አጓርቶና ድብልቅልቁ ወጥቶ እንዲሟሟና እንዲተን
ይፈልጋል" ችግሩ እንዳሰበው ለማድረግ አቅሙ አለ ወይ ነው።
የልጅነት ጊዜው መጥፎ ትዝታ ጥርሱን አግጥጦ፣ ጥፍሩን በማሾል፣ የታባክ ይለዋል“ ይኸኔ እንደ ልጅነቱ ልጅ ይሆንና በጭንቀት እየተንቦራቸ ይርበተበታል" ሊጮህ ይፈልግና ድምፁ
አልወጣልህ ይለዋል" ትናንት ከገደል ውስጥ ወጥቷልI ዛሬ ግን ወደ
ገደል ተገፍቶ ለመግባትና ለመሞት ዝግጁ አይደለም" መሞትም አይሻም ለምን?
እንግዲህ ችግሩ ያለው በትናንትናና በዛሬ መካከል ነው" ልጅ ከነበረው ከሎና አሁን በአካልና በአእምሮ ካደገው ከሎ መካከል
አንዱ ሽሽቱን ማቆምI አለበለዚያም፣ «በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ» እንዲሉ፣ በፍርሃት ላይ የጅብን ፍርሃት እያከለ ወደ ኋላ ሳያይ የሕይወትን ሩጫ መሸምጠጥ አለበት።
ትንሹ ከሎ ማምለጥ፣ መሸሽ ይፈልጋል ከሐመር። ትልቁ ከሎ ደግሞ ልቡ ከሁለት ቦታ ተንጠልጥሎበታል" ከሎ ውሳኔው ሲከብደው ካርለት ከተወችለት ካርድ ላይ በብዕር የተጻፈውን ስልክ
ቁጥር ተመልክቶ ስልክ ደወለ" «ሔሎ ከሎ» አለችው እንደ ሕፃን
ተቁነጥንጣ።
«...ደህና ነኝ» አላት"
«ምነው ልትገልጽልኝ የምትፈልገው ጉዳይ አለ?» አለችው።
«ለመሄድ ፈቃደኛ ነኝ» አለ ከሎ።
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከኢትዮጵያ ጥናትና ምርምርና ከሌሎች ተቋማት ለጥናቷ
አስፈላጊ የሆኑትን ውጤቶች ካነበበችና ከግለሰቦች ጋር ሐሳብ
ለሐሳብ ከተለዋወጠች በኋላ እግረ መንገዷን ሊረዳት የሚችል የክልሉ ተወላጅ አድራሻ፣ የጥናትና የጕዞ ፈቃድ አውጥታ ወደ
ጥናት ቦታዋ ከመጓዟ በፊት ምሽቱን በአዲስ አበባው ሒልተን እንግሊዝ ኤምባሲ ከሚሠራውና ለተወሰኑ ወራት በአዲስ አበባው
ቆይታዋ ጠረኑን ከለመደችው ጓደኛዋ ጋር እቅፉ ውስጥ ስትንቀሳቀስ
አድራ እንደገና ገላዋን ታጠበችና ልብሷን ለባብሳ ወጣች"
በአስተሳሰቧ፣ በግልጽነቷና በውበቷ የነሆለለው ስቲቭ
አለባበሷን፣ ከሰዓታት በፊት ፍቅር አመንጪ የነበረው አካሏ ተለውጦ ለሥራ መዘጋጀቷን ሲያይ እሱ ፍቅር ከፈጠረው የደስታ
ዓለም ከነበረበት ፈጽሞ ሳይንቀሳቀስ እሷ ግን ገስግሳ ወደ ገሐዱ
ዓለም በመመለሷ በፍጥነቷ ተደንቆ በተመስጦ ሲመለከታት ቆየና፣
«የኔ ቆንጆ አሁንም ታምሪያለሽ» አላት።
«ማማሬን እርሳው» አለችው።
«ለምን?»
«ከጥቂት ሰዓታት በፊት እኔም እረስቸዋለሁና።»
«የኔ ቆንጆ፣ ታዲያ ምን እንድልሽ ትፈልጊያለሽ?»
«የጉጉትን ዘዴ፣ የንስርን ማስተዋል፣ የአንበሳን ልብ፣ የኢዮብን ትዕግሥት፣ የአባትሽን ተስፋ አይቆርጤነትና አእምሮ ይስጥሽ በለኝ» ብላ፣ ጉንጩን ሳም አደረገችው"
ስቲቭ አስተያየቱን ጠለቅ አድርጎ ሲያስተውላት ቆየና፣ «አሁን አንችን የመሰለ ውብ ከእነዚያ ዘላኖች...» ሊናገር የፈለገውን ሳታስጨርሰው አፉን በአመልካች ጣቷ ከደነችው።
«ማፍቀር ያለብህ እኔን ብቻ ሳይሆን ፍላጎቴንም እንዲሆን እፈልጋለሁ" ትልቁ ውበት ደግሞ ሥራ መሆኑን አትዘንጋ» አለችውና ሌላ ቃል ሳይለዋወጡ ለቁርስ ክፍሉን ቆልፈው ወጡ"
።።።።።።።።።።።።።
ፈርጠም ያለ፣ የቀይ ሽንኩርት ቅርፅ መሳይ አፍንጫ ያለው! ዳጐስ ብሎ ቀላ ያለውን ከንፈሩን ሲገልጥ ነጫጭ ፍልጥ ጥርሶቹ የሚያማምሩና ከሸበላው ቁመናው ጋር የተስተካከለ አቋም ያለው
ከሎ ሆራ ለየት ያለ ባሕርይ ይታይበታል።
ቁጥብነቱን፣ ጅንንነቱን፣ ጥርጣሬውንና ብቸኝነት መውደዱን ያዩ ጓደኞቹ፣ «ነብሮ» ይሉታል የዩኒቨርሲቲ ጓደኞቹ" ቀልድ፣
ቧልት ከጀመሩለት እንደ ቆሰለ ጎሽ በንዴት ጦፎ ይፎገራል" ከሰው ጋር ደጋግሞ እንደ መጣላቱ ግን ኃይሉን ተማምኖ ተማቶ
አያውቅም" ሁለቴ ሦስቴ ቃጥቶ ቃጥቶ ማንም በማይገባው ቋንቋ
አኩተምትሞ ዘወር ይላል" ታዲያ ብዙዎቹ አዳልጧቸው ቀልድ ብጤ ጀማምረው በዚያ ፈርጣማ ጡንቻው በሰነዘረ ቁጥር ጠረመሰን
እያሉ አንዴ ከተሳቀቁ፣ «እርም» ብለው ይሸሹታል" ስለዚህ ምን እንደሚያበሽቀው ያለፈው ሕይወቱ ምን እንደሚመስል፣
ብቸኝነቱ ከመቼ ወዲህ እንደ ጀመረው ከፍቶ ማየት የሚችል ሰው አልተገኘም ግለቱ ስላላስቀረበ"
የተማሪን ቆብ አውላቂ መምህራን በለመዱት ቧልት «ጢብ ጢብ» ሊጫወቱበት ይዳዳቸውና እንደ ከለመዳሪ የሚነፋውን
ከንፈሩንና እሳት ተፊ ትናንሽ ዓይኖቹን ሲያዩ በተለይም
በአንቀሳቀሰው ቁጥር እንደ አሎሎ የሚንከባለለውን ጡንቻውን ሲመለከቱ! «በቸር አውለኝ» ብለው አቅጣጫቸውን ሲቀይሩ
ዓመታት ተቈጠሩ“
ከሎ ሆራ የአራተኛ ዓመት የሶሲዮሎጂ ትምህርቱን ሊያጠናቅቅ በተቃረበበት ወቅት በቀጭን ወገቧ ጂንስ ሱሪዋን በቀላል «ቲሸርት» አስተካክላ ለብሳ፣ የተጐነጐነ ረዥም ጸጕሯን ወገቧ ላይ እያላጋች፣ ቶሎ ቶሎ በመራመድ ጫማዋን ቀጭ ቋ ቀጭ ቋ እያደረገች የምትገሰግሰው ወጣት ከዩኒቨርሲቲው ፖስታ ቤት ወረድ ብሎ ከሚገኘው ኮሪደር ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ እግሩን እያወዛወዘ!
ጠጠር ወደሚወረውረው ጥቁር ወጣት ተጠግታ፣ «ይቅርታ ከሎ ሆራ ነህ አይደለም?» ብላ ጠየቀችው፣ በእንግሊዝኛ"
«አዎ ነኝ» አለ ከሎ፣ ከተቀመጠበት ሳይንቀሳቀስ"
«ካርለት አልፈርድ እባላለሁ" እንግሊዛዊት አንትሮፖሎጂስት
ነኝ" ስለ ሐመር ሴቶች ጥናት ለማድረግ ዓላማ አለኝ" አንተም የሐመር ተወላጅ መሆንህን ከዲፓርትመንትህ ኃላፊ ጠይቄ አረጋግጫለሁ» አለችና ንግግሯን በመግታት ትኵር ብላ ተመለከተችው
ከሎ ሆራ፣ የመርበትበት ስሜት አሳየና ከተቀመጠበት ፈጥኖ ተነሣ
ላብ ከወደግንባሩና ቅንድቡ አካባቢ ችፍፍ ችፍፍ ሲል ከንፈሩ አመድ የነሰነሱበት መሰለ።
«ሶ ለምን ፈለግሽኝ?» አላት በተቆራረጠ ድምፅ
«እንድትረዳኝ እፈልጋለሁ» አለችው፣ በዓይኗ እየመረመረችው
«እንድትረዳኝ እፈልጋለሁ?» ብሎ አባባሏን ደገመና ለትንሽ ጊዜ የመመሰጥ ሁኔታ አሳይቶ፣
«አዝናለሁ፣ ልረዳሽ አልችልም» አላት"
ካርለት፣ የከሎ ሰውነት ሲለዋወጥና ከብስጭቱ ጋር ሲታገል ያስተዋለች መሰላት ስለዚህ ወጣቱ ከሷ ያለበለዚያም ራሱ ከራሱ
ጋር ያልተግባቡት ወይንም ለእሷ ግልጽ ያልሆነላት ሌላ ምክንያት እንዳለው በመረዳቷ ተጨማሪ ጥያቄ ሳታነሣ፣ «አመሰግናለሁ“ ነገ
ግን ጊዜ ወስደህ ካሰብክበት በኋላ ሐሳብህን ከቀየርክ አይ.ኢ.ኤስ
ልታገኘኝ ትችላለህ ካለዚያም ስልክ ቁጥሬን ልሰጥህ እችላለሁ» ብላ፣ ፍጹም ልብ በሚነካ ፈገግታ የአድራሻዋን ካርድ ሰጥታው
«ደህና ሁን» እያለች፣ እጇን አውለብልባለት ሄደች"
ከሎ ሆራ ወደ መቀመጫው ሲመለስ፣ የሚሰበቀውን ወገቧንና ጀርባዋ ላይ ከብለል ከብለል የሚለውን ጉንጉን ጸጕሯን ሲመለከት
ሐሳቡ ሸፈተበት" ከዓይኑ እስክትሰወር ድረስ በመደመም ሲመለከታት ቆየና ከጥቂት ደቂቃ በፊት የነበረበትን ድንገተኛ ሁኔታ ለማስታወስ ሞከረ» «ሐመር ጥናት ውብ እንግሊዛዊት የሐሳብ
ፍጥጫ፣ የተዳፈነ እሳት ጭረት.እሳት ጫሪ አንትሮፖሎጂስት...ወጣትና ውብ...ዳሚት» አለ፣ እጆቹን ከተቀመጠበት ደረጃ
ጋር እያላተመ።
።።።።።።።።።።።።።
ልቡ የአዶከበሬ አታሞ ይመስል እየተነረተ፣ ሰውነቱ ፀሐይ እንዳቆረናው የበረሃ ባልጩት ድንጋይ እያተኮሰ፣ እንቅልፍ ሲመኝ ግን ሲነቃ፣ ዕረፍትን ሲሻ፣ ሲንጠራወዝ፣ ሲገለባበጥ፣ በሐሳብ
ሲድህና ፎቀቅ ፎቀቅ ሲል አድሮ ዋለ"
ብዙ አወጣ አወረደI ያለፈ የልጅነት መጥፎ ትዝታውንም አስታወሰ" አሁን ሊያደርግ የማይፈልገውን እንዲያደርግ ግብዣው
ቀርቦለታል" ሌላው ቀን አልፏል። ለዛሬ ሥሩ ትናንት ነው" ትናንት ደግሞ እሱ የመከራ ጽዋውን የጨለጠበት ወቅት ነው" ዳግመኛ ሬት ሊያወርድ የሚችል ጉሮሮ የለውም” ስለዚህ በትናንት ቂም ያረገዘው አእምሮው አጓርቶና ድብልቅልቁ ወጥቶ እንዲሟሟና እንዲተን
ይፈልጋል" ችግሩ እንዳሰበው ለማድረግ አቅሙ አለ ወይ ነው።
የልጅነት ጊዜው መጥፎ ትዝታ ጥርሱን አግጥጦ፣ ጥፍሩን በማሾል፣ የታባክ ይለዋል“ ይኸኔ እንደ ልጅነቱ ልጅ ይሆንና በጭንቀት እየተንቦራቸ ይርበተበታል" ሊጮህ ይፈልግና ድምፁ
አልወጣልህ ይለዋል" ትናንት ከገደል ውስጥ ወጥቷልI ዛሬ ግን ወደ
ገደል ተገፍቶ ለመግባትና ለመሞት ዝግጁ አይደለም" መሞትም አይሻም ለምን?
እንግዲህ ችግሩ ያለው በትናንትናና በዛሬ መካከል ነው" ልጅ ከነበረው ከሎና አሁን በአካልና በአእምሮ ካደገው ከሎ መካከል
አንዱ ሽሽቱን ማቆምI አለበለዚያም፣ «በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ» እንዲሉ፣ በፍርሃት ላይ የጅብን ፍርሃት እያከለ ወደ ኋላ ሳያይ የሕይወትን ሩጫ መሸምጠጥ አለበት።
ትንሹ ከሎ ማምለጥ፣ መሸሽ ይፈልጋል ከሐመር። ትልቁ ከሎ ደግሞ ልቡ ከሁለት ቦታ ተንጠልጥሎበታል" ከሎ ውሳኔው ሲከብደው ካርለት ከተወችለት ካርድ ላይ በብዕር የተጻፈውን ስልክ
ቁጥር ተመልክቶ ስልክ ደወለ" «ሔሎ ከሎ» አለችው እንደ ሕፃን
ተቁነጥንጣ።
«...ደህና ነኝ» አላት"
«ምነው ልትገልጽልኝ የምትፈልገው ጉዳይ አለ?» አለችው።
«ለመሄድ ፈቃደኛ ነኝ» አለ ከሎ።
👍29
በእርግጥ በአካልና በአእምሮ ያደገው ከሎ ከዚያ የግፍ ጽዋ
ከጨለጠው እንቦቀቅላ እሱነቱ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ይፈልጋል
ማን ያውቃል ይህ የቀረበለት ግብዣ ሰበብ ሊሆን ይችላል" በሌላ ጐኑ ደግሞ ትምህርቱን ከልምድ ጋር ማቆራኘት ያስችለዋል"
ማንም የሚያውቃት ትንሿ ሣር አዋዝታ፥ ሰርስራ ፈርጣማ ጡንቻ ብቻውን የማይችለውን ድንጋይ ሰንጥቃ ብቅ ትላለች፣ ታድጋለች" ሊታመን በማይችል ሁኔታ ትንሿ ሣር ድንጋይ በስታ ሕያው
ስትሆን አይቷል" ችግሩ ግን እንዴት የሚለው ጥያቄ ነው" ይህ የሕሊና ጥያቄ ደግሞ መመለስ እንዳለበት ያምናል"
ከሁሉም በላይ ደግሞ የዚያች የሥነ ስብእ ተመራማሪ ሶምሶማ
ረጋጭ ዳሌ ቀልቡን ገፍቶታል" ስለዚህ ይህ ዕድል እንዳያመልጠው
«ዊዝድሮዋል» ለመጠየቅ ቢወስንም በስልክ በሰጠው የመሄድ ፈቃደኝነት ግን መደንገጡ አልቀረም"
«በጣም አመሰግናለሁ” ይህ ለኔ ትልቅ ዜና ነው። ግን...» ከሎ ሐሳቧን ሳያስጨርሳት፣ «ለጊዜው እንድታነሽብኝ አልፈልግም።
ሐመር አካባቢ ሄጄ ልረዳሽ ግን ፈቃደኛ ነኝ» አላት ቀጥሎ ያኩተመተመውን ግን አልተረዳችውም" የመከፋት ስሜቱን ግን በድጋሚ አጤነች።
ካርለት የስልኩን እጀታ እንደ ያዘች በሐሳቧ፣ «ጥሩ፥ የጓዳው ሲደርስ ይከፈታልI ዋናው ፈቃደኛ መሆኑ ነው» አለችና፣ «ታንኪው ...ኦ... አመሰግናለሁ...» አለች ፍንድቅድቅ ብላ፣ «ኢ ህ» ብሎ አጸፋውን መለሰላት" የሱ የልብ ፈገግታ የመጨረሻው ኮታ ይኸው ነው።
ካርለት፣ ደስታዋን እየተቆጣጠረች ስትመጣ ለከሎ ሆራ ቀጠሮ
ከመስጠቷ በፊት ስልክ እንደምትደውል ገልጻለት ለተወሰነ ጊዜ እንዲጠብቃት ከይቅርታ ጋር ጠየቀችው ከትንሽ ደቂቃ በኋላም
ሒልተን ሆቴል ልትጋብዘው እንደምትፈልግና የሴት ጓደኛውንም ይዞ ከምሽቱ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ሆቴል እንዲመጣ
ነገረችው።
ከሎ የስልኩን እጀታ ካስቀመጠ በኋላ፣ «የእኔ ተፈጥሯዊ ግለት
የበርደው...የምን ሴት ጓደኛ? እንኳን የሴት፣ ለወንዱስ ጓደኛ መቼ እኔ ያሰብኩት...እሳት ጫሪ አንትሮፖሎጂስት... ዳሚት»
ብሎ አኩተመተመ።
ከሎ ከሶሲዮሎጂ ይልቅ የሳይኮሎጂ ትምህርት እጅግ ይመስጠዋል" በተለይ የሲግመንድ ፍሮይድ፣ «ሰው በተፈጥሮው
«ወሲባዊና ሞገደኛ ነው» የሚለው እምነቱ፣ ብዙውን የሕይወት ክስተቶች ቁልጭ አድርጎ ያሳየዋል"
የሰው ልጅ ባህላዊ ግዴታዎች ባይኖሩበት ኖሮ በወደዳቸው ሴቶች ላይ ጎብኚውን ሳያፍር ዘሎ ከተጓዳኙ ጀርባ ላይ እንደሚወጣ
የዘዙ ጎሬላ ዝንጀሮ ወይንም ጭንቅላት ነክሶ እንስቷ ጀርባ እንደሚኮፈስ አውራ ዶሮ ይሆን ነበር" ሆኖም አንደበት በባህላዊ
ዚፕ ተሸብቦ፣ ልብ እየዘለለ ሲፈርጥ፣ ውጫዊ አካል ግን አገር ሰላም ነው እያለ ጥሩንባውን ይነፋል" ስለዚህ ስሜት ውሃ ይከለስበትና እንዲከስል ካለያም እንዲሸጎርበት ይደረጋል"
ከሎ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢም ሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ልቡ የከጀላትን ሴት ለማግኘት እንዳይሞከር የባህል ተጽዕኖ
እንደተቀየደች በቅሎ ኮድኩዶታልI በስጨት ብሎ ኃይል እንዳይጠቀም ደግሞ ባህልና ሕግ እጁን ጠፍሮታል" ስለዚህ
ተፈጥሮን በተፈጥሮ ሕግ እንዲገዛ ከማድረግ ይልቅ ከትውልድ ትውልድ በሚተላለፍ የባህል ገመድ ተጠፍሮ እርካታ አልባ ሆኗል
የሚፈልገውን ሳያጣ" ከሎ ወደደም ጠላ በዚህ ባህላዊ ክርን እየተደቆሰ ነው።
ከሎ ሆራ ሒልተን ሆቴል ለመሄድ ከካርለት ጋር ከተቀጣጠረበት
ኢትዬጵያ ሆቴል ሲገባ ከበስተግራ በኩል ካለው ተንቀሳቃሽ የብረት
አጥር ላይ እየተጠላለፈ ከወጣው ሐረግ ስር አሾልኮ ሲያይ ካርለት ፈገግ ብላ እሱን ለመቀበል ከመቀመጫዋ ስትነሣ ከጎኗ ሙሉ ቡላ ሱፍ፣ በነጭ ሸሚዝ ላይ ቀይ ክራቫት ያሰረ የውጭ ዜጋ አብሯት
ሲነሣ ተመለከተ» ካርለት ከሎን ከጨበጠችው በኋላ ከጎኗ ወደ ቆመው ሰው እያመለከተች ጓደኛዬን ላስተዋውቅህ አለችው
ዜጋው «ስቲቭ» ብሎ አንገቱን በማወዛወዝ እጁን ዘረጋለት። ከሎ
በልቡ «ዳሚት» ብሎ፣ የፈረንጁን ጣቶች ጨፍልቆ ያዘ" ያኔ ስቲቭ፣ «ኦ» ብሎ ቀኝ እግሩን አነሣ ይቅርታ መጠየቅ ያለመደው ከሎ ግን ለቆት ወደ ካርለት ዞረ።
ካርለት በተለይ ከሎን እንዲቀመጥ ጋብዛ፣ «ምን ትጠጣለህ?» አለች" ከሎ ተፈጥሮ ባሕርይው ሆነና ሲጠየቅ ቶሎ መመለስ
አይወድም ስለዚህ ሶፋው ላይ በመቀመጥ ዝም ብሎ ዓይን ዓይኗን ተመለከታት «አምላኬ!» አለችና ጥርሷን ሳታሳይ ፈገግ አለች።
«ለስላሳ»አለ ከሎ ጥቂት ከጠበቀችው በኋላ" ስቲቭ እጆቹን ትከሻዋ ላይ አድርጎ ከኢንግላንድ ስለ ደረሰው ደብዳቤ ያወራታል
እሷ ግን የከሎ ዝምታና የስቲቭ ቅብጥብጥነት አልስማማሽ አላት"
የመድረክ ተዋናይ የመሰለችው ወጣት ሁለት ባሕርያቸው !
«አራምባና ቆቦ» የሆኑ ሰዎች ማስተናገድ በሁለት መሰላል የመውጣት ያህል ከበዳት።
ሒልተን ሆቴል ከሄዱም በኋላ ስቲቭ እቅፉ ውስጥ ሸጎጥ አድርጎ ሲደባብሳት ከሎ ለንቦጩን ይነፋባታል" ስቲቭ ያየውን ሁሉ
ሲያደንቅ፣ ከሎ ያየውን ሁሉ ዳሚት ይላል" ሰው ሁሉ ለዳንስ መድረኩ መሃል ሲገባ፣ ከሎ ቁጭ ብሎ ቢራውን ያንቆረቁራል
ሌላው ዕረፍት ሲወስድ ደግሞ እሱ በመደነሻው መሃል ቆሞ ሲያኩተመትም ሌሊቱ ተጋምሶ ወደሚያድርበት ሰፈር ሲያደርሱት ምንም ሰላምታ ሳይሰጣቸው ወጥቶ ጕዞ ጀመረ። ካርለት ከስቲቭ
«ቢ.ኤም.ደብሊው» መኪና ወርዳ ስትሰናበተው ዘወር ብሎ አይቶ፣
«ኢ ህ» ብሏት ሄደ" ሁለቱ ፍቅረኛሞችም እርስ በእርሳቸው በአድናቆት ተያይተው ቀሪው የሌሊት ትዕይንት ወደሚታይበት
የመኝታ ክፍላቸው ከነፉ።....
💫ይቀጥላል💫
ከጨለጠው እንቦቀቅላ እሱነቱ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ይፈልጋል
ማን ያውቃል ይህ የቀረበለት ግብዣ ሰበብ ሊሆን ይችላል" በሌላ ጐኑ ደግሞ ትምህርቱን ከልምድ ጋር ማቆራኘት ያስችለዋል"
ማንም የሚያውቃት ትንሿ ሣር አዋዝታ፥ ሰርስራ ፈርጣማ ጡንቻ ብቻውን የማይችለውን ድንጋይ ሰንጥቃ ብቅ ትላለች፣ ታድጋለች" ሊታመን በማይችል ሁኔታ ትንሿ ሣር ድንጋይ በስታ ሕያው
ስትሆን አይቷል" ችግሩ ግን እንዴት የሚለው ጥያቄ ነው" ይህ የሕሊና ጥያቄ ደግሞ መመለስ እንዳለበት ያምናል"
ከሁሉም በላይ ደግሞ የዚያች የሥነ ስብእ ተመራማሪ ሶምሶማ
ረጋጭ ዳሌ ቀልቡን ገፍቶታል" ስለዚህ ይህ ዕድል እንዳያመልጠው
«ዊዝድሮዋል» ለመጠየቅ ቢወስንም በስልክ በሰጠው የመሄድ ፈቃደኝነት ግን መደንገጡ አልቀረም"
«በጣም አመሰግናለሁ” ይህ ለኔ ትልቅ ዜና ነው። ግን...» ከሎ ሐሳቧን ሳያስጨርሳት፣ «ለጊዜው እንድታነሽብኝ አልፈልግም።
ሐመር አካባቢ ሄጄ ልረዳሽ ግን ፈቃደኛ ነኝ» አላት ቀጥሎ ያኩተመተመውን ግን አልተረዳችውም" የመከፋት ስሜቱን ግን በድጋሚ አጤነች።
ካርለት የስልኩን እጀታ እንደ ያዘች በሐሳቧ፣ «ጥሩ፥ የጓዳው ሲደርስ ይከፈታልI ዋናው ፈቃደኛ መሆኑ ነው» አለችና፣ «ታንኪው ...ኦ... አመሰግናለሁ...» አለች ፍንድቅድቅ ብላ፣ «ኢ ህ» ብሎ አጸፋውን መለሰላት" የሱ የልብ ፈገግታ የመጨረሻው ኮታ ይኸው ነው።
ካርለት፣ ደስታዋን እየተቆጣጠረች ስትመጣ ለከሎ ሆራ ቀጠሮ
ከመስጠቷ በፊት ስልክ እንደምትደውል ገልጻለት ለተወሰነ ጊዜ እንዲጠብቃት ከይቅርታ ጋር ጠየቀችው ከትንሽ ደቂቃ በኋላም
ሒልተን ሆቴል ልትጋብዘው እንደምትፈልግና የሴት ጓደኛውንም ይዞ ከምሽቱ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ሆቴል እንዲመጣ
ነገረችው።
ከሎ የስልኩን እጀታ ካስቀመጠ በኋላ፣ «የእኔ ተፈጥሯዊ ግለት
የበርደው...የምን ሴት ጓደኛ? እንኳን የሴት፣ ለወንዱስ ጓደኛ መቼ እኔ ያሰብኩት...እሳት ጫሪ አንትሮፖሎጂስት... ዳሚት»
ብሎ አኩተመተመ።
ከሎ ከሶሲዮሎጂ ይልቅ የሳይኮሎጂ ትምህርት እጅግ ይመስጠዋል" በተለይ የሲግመንድ ፍሮይድ፣ «ሰው በተፈጥሮው
«ወሲባዊና ሞገደኛ ነው» የሚለው እምነቱ፣ ብዙውን የሕይወት ክስተቶች ቁልጭ አድርጎ ያሳየዋል"
የሰው ልጅ ባህላዊ ግዴታዎች ባይኖሩበት ኖሮ በወደዳቸው ሴቶች ላይ ጎብኚውን ሳያፍር ዘሎ ከተጓዳኙ ጀርባ ላይ እንደሚወጣ
የዘዙ ጎሬላ ዝንጀሮ ወይንም ጭንቅላት ነክሶ እንስቷ ጀርባ እንደሚኮፈስ አውራ ዶሮ ይሆን ነበር" ሆኖም አንደበት በባህላዊ
ዚፕ ተሸብቦ፣ ልብ እየዘለለ ሲፈርጥ፣ ውጫዊ አካል ግን አገር ሰላም ነው እያለ ጥሩንባውን ይነፋል" ስለዚህ ስሜት ውሃ ይከለስበትና እንዲከስል ካለያም እንዲሸጎርበት ይደረጋል"
ከሎ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢም ሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ልቡ የከጀላትን ሴት ለማግኘት እንዳይሞከር የባህል ተጽዕኖ
እንደተቀየደች በቅሎ ኮድኩዶታልI በስጨት ብሎ ኃይል እንዳይጠቀም ደግሞ ባህልና ሕግ እጁን ጠፍሮታል" ስለዚህ
ተፈጥሮን በተፈጥሮ ሕግ እንዲገዛ ከማድረግ ይልቅ ከትውልድ ትውልድ በሚተላለፍ የባህል ገመድ ተጠፍሮ እርካታ አልባ ሆኗል
የሚፈልገውን ሳያጣ" ከሎ ወደደም ጠላ በዚህ ባህላዊ ክርን እየተደቆሰ ነው።
ከሎ ሆራ ሒልተን ሆቴል ለመሄድ ከካርለት ጋር ከተቀጣጠረበት
ኢትዬጵያ ሆቴል ሲገባ ከበስተግራ በኩል ካለው ተንቀሳቃሽ የብረት
አጥር ላይ እየተጠላለፈ ከወጣው ሐረግ ስር አሾልኮ ሲያይ ካርለት ፈገግ ብላ እሱን ለመቀበል ከመቀመጫዋ ስትነሣ ከጎኗ ሙሉ ቡላ ሱፍ፣ በነጭ ሸሚዝ ላይ ቀይ ክራቫት ያሰረ የውጭ ዜጋ አብሯት
ሲነሣ ተመለከተ» ካርለት ከሎን ከጨበጠችው በኋላ ከጎኗ ወደ ቆመው ሰው እያመለከተች ጓደኛዬን ላስተዋውቅህ አለችው
ዜጋው «ስቲቭ» ብሎ አንገቱን በማወዛወዝ እጁን ዘረጋለት። ከሎ
በልቡ «ዳሚት» ብሎ፣ የፈረንጁን ጣቶች ጨፍልቆ ያዘ" ያኔ ስቲቭ፣ «ኦ» ብሎ ቀኝ እግሩን አነሣ ይቅርታ መጠየቅ ያለመደው ከሎ ግን ለቆት ወደ ካርለት ዞረ።
ካርለት በተለይ ከሎን እንዲቀመጥ ጋብዛ፣ «ምን ትጠጣለህ?» አለች" ከሎ ተፈጥሮ ባሕርይው ሆነና ሲጠየቅ ቶሎ መመለስ
አይወድም ስለዚህ ሶፋው ላይ በመቀመጥ ዝም ብሎ ዓይን ዓይኗን ተመለከታት «አምላኬ!» አለችና ጥርሷን ሳታሳይ ፈገግ አለች።
«ለስላሳ»አለ ከሎ ጥቂት ከጠበቀችው በኋላ" ስቲቭ እጆቹን ትከሻዋ ላይ አድርጎ ከኢንግላንድ ስለ ደረሰው ደብዳቤ ያወራታል
እሷ ግን የከሎ ዝምታና የስቲቭ ቅብጥብጥነት አልስማማሽ አላት"
የመድረክ ተዋናይ የመሰለችው ወጣት ሁለት ባሕርያቸው !
«አራምባና ቆቦ» የሆኑ ሰዎች ማስተናገድ በሁለት መሰላል የመውጣት ያህል ከበዳት።
ሒልተን ሆቴል ከሄዱም በኋላ ስቲቭ እቅፉ ውስጥ ሸጎጥ አድርጎ ሲደባብሳት ከሎ ለንቦጩን ይነፋባታል" ስቲቭ ያየውን ሁሉ
ሲያደንቅ፣ ከሎ ያየውን ሁሉ ዳሚት ይላል" ሰው ሁሉ ለዳንስ መድረኩ መሃል ሲገባ፣ ከሎ ቁጭ ብሎ ቢራውን ያንቆረቁራል
ሌላው ዕረፍት ሲወስድ ደግሞ እሱ በመደነሻው መሃል ቆሞ ሲያኩተመትም ሌሊቱ ተጋምሶ ወደሚያድርበት ሰፈር ሲያደርሱት ምንም ሰላምታ ሳይሰጣቸው ወጥቶ ጕዞ ጀመረ። ካርለት ከስቲቭ
«ቢ.ኤም.ደብሊው» መኪና ወርዳ ስትሰናበተው ዘወር ብሎ አይቶ፣
«ኢ ህ» ብሏት ሄደ" ሁለቱ ፍቅረኛሞችም እርስ በእርሳቸው በአድናቆት ተያይተው ቀሪው የሌሊት ትዕይንት ወደሚታይበት
የመኝታ ክፍላቸው ከነፉ።....
💫ይቀጥላል💫
👍24🤔3❤1
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ዳያና መልስ የመስጠት ያህል ከንፈሩን መጠጠችው፡
ከዚያማ ምን ይወራል! ቀለል እያላት ሲመጣ መላ ሰውነቷ ዘና አለ፡፡
እየሳመችው ወንበሩን ተደገፈች፡፡ እየሳመችው ጡቷ ደረቱን ሲታከክ
ተሰማት፡ እንደገና ገላ ለገላ መተሻሸት መቻሏ ደስታ ፈጥሮላታል፡ በከንፈሩ
ጫፍ ከንፈሯን ሲዳስስ ስሜት ውስጥ ገብታ አፏን ከፍታ ተቀበለችው፡፡ ጫን
ጫን መተንፈስ ጀመረች፡ በእርግጥ የሚያደርጉት ነገር መረን የለቀቀ
መሆኑ ታውቋታል፡ ዓይኗን ስትከፍት መርቪንን አየችው:
በመጀመሪያ እያለፈ ስለነበር አላስተዋላትም ነበር፡ ድንገት ወዳለችበት
ፊቱን ዞር ሲያደርግ ያየው ነገር ከእርምጃው ገታው፡ እሷም ስታየው ፊቷ
በድንጋጤ አመድ ለበሰ፡፡
ዳያና ባሏን በሚገባ ስለምታውቀው ምን ሊሰማው እንደሚችል
አልጠፋትም ምንም እንኳ ከማርክ ጋር በፍቅር መክነፏን ሰዎች ቢነግሩትም እውነትነቱን ለመቀበል ከብዶታል፡፡ ከወንድ ጋር ስትሳሳም በዓይኑ በብረቱ ሲያይ በድንጋጤ ክው አለ፡፡
መርቪን በንዴት ግምባሩን ከሰከሰ፡፡ ዳያና ባሏ በቀጥታ ጠብ ይጀምራል
ብላ ፈርታ ነበር፡፡ ሆኖም ቃል ሳይተነፍስ ዞረና መንገዱን ቀጠለ፡፡
ማርክ ‹‹ምንድነው ነገሩ?›› ሲል ጠየቃት፡፡ ዳያናን ይዞ እየጨመጨመ
ስለነበር መርቪንን አላየውም ነበር፡፡
መንገር ስለፈራች ‹‹ሰው ሊያየን ይችላል ይበቃናል›› አለችው:
ማርክም ከዳያና መላቀቁን ቢጠላም መሳሙን አቆመ::
ዳያና የመርቪን አድራጎት አናደዳት፡፡ መርቪን የዓለምን ግማሽ ርቀት እግር በእግር ተከትሏት መምጣቱ ሳያንስ ከማርክ ጋር በተላፋች ቁጥር ሊያፈጥባት መብት የለውም፡፡ ትዳር ባርነት አይደለም፡፡ ጥላው መሄዷን
መቀበል አለበት፡ ማርክም በንዴት ሲጋራ ለኮሰ፡፡ ዳያና ባሏን ፊት ለፊ ልትገጥመው ፈልጋለች፡ በቃ አልፈልግህም ልትለው ተዘጋጅታለች
ተነሳችና ‹‹መዝናኛው ክፍል ምን እንዳለ ለማየት ልሄድ ነው›› አለች
‹‹አንተ እዚህ ቁጭ ብለህ ሲጋራህን ማግ›› አለችውና ከማርክ መልስ ሳትጠብቅ እብስ አለች፡
መርቪን የት እንደተቀመጠ ባታውቅም ፍለጋዋን ቀጠለች፡፡ አሁን የአይሮፕላኑ መናወጥ የቀነሰ በመሆኑ ምንም ነገር ሳትይዝ መራመድ ችላለች፡፡ በመዝናኛ ክፍሉ ውስጥ ሰዎች ካርታ ለመጫወት ጉድ ጉድ እያሉ ሲሆን ክፍሉ
በሲጋራ ታፍኗል፡፡ ፊታቸው የመጠጥ ጠርሙሶች
ተኮልኩለዋል፡፡ ሌላ ክፍል ዘው ስትል የኦክሰንፎርድን ቤተሰብ አገኘች፡:ሎርድ ኦክሰንፎርድ ሳይንቲስቱን ካርል ሃርትማንን ከፍ ዝቅ አድርገው ሲሳደቡ መርቪን ላቭሴይ ሰምቶ እሱ እንደተነካ ተቆርቁሮ ሎርዱን
ለመደብደብ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ተሳፋሪው አይቶታል፡ መርቪን አንዳንዴ እውነት አለው፡፡ እሷም ይህን አትክድም፡፡
ከዚያም ወደ ኩሽና ሄደች፡፡ እዚያም ድብልብሉ ኒኪ ሰሃን ሲያጥብ አገኘችው::
ፎቁን ወጣችና ፓይለቶቹ ክፍል ሄደች፡፡ ሁሉም በስራ የተጠመዱ ስለሆነ ወዲያው አላይዋትም፡፡ በኋላ አንዱ አያትና ‹‹ሌላ ጊዜ እያዞርን ሁሉንም ቦታ እናሳይሻለን፡፡ ነገር ግን አሁን እውጭ ያለው የአየር ሁኔታ
መጥፎ ስለሆነ ቦታሽ ሄደሽ እንድትቀመጪ ቀበቶሽን እንድታስሪ እንጠይቃለን›› አላት፡፡
ደረጃውን ወርዳ ስትጨርስ ከማርክ ጋር ፊት ለፊት ግጥም አለች፡ሁኔታው ቢያስደነግጣትም ‹‹እዚህ ምን ልታደርግ መጣህ?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ራስሽ እዚህ ምን ልታደርጊ መጣሽ?›› አላት፡፡ ካነጋገሩ የተናደደ መሆኑ ያስታውቃል
ዞር ዞር እያልኩ እያየሁ ነው፡፡››
መርቪንን ነው የምትፈልጊው?›› አላት፡
‹‹ማርክ ለምንድነው እንደዚህ የምትሆነው?›› አለች ዳያና፡፡
‹‹ምክንያቱም ባልሽን ለማየት ሹክክ ብለሽ በመሄድሽ››
ኒክ ድንገት መጣና ጭቅጭቃቸውን አቋረጣቸው ወደ
መቀመጫችሁ ተመለሱ፡፡ አሁን በረራው ጥሩ ቢመስልም ትንሽ ቆይቶ
አይሮፕላኑ መወዛወዙ አይቀርም›› አላቸው፡፡
ማርክና ዳያና ወደ ቦታቸው ተመለሱ፡፡ ዳያና ያደረገችው የጅል ስራ መሆኑን ተገንዝባለች፡፡ መርቪንን ስትከታተል መርቪን ደግሞ እሷን ተከታትሎ የምትሰራውን አየባት፡፡
ቦታቸው ቁጭ ብለው ጭቅጭቃቸውን ሊቀጥሉ ሲሉ ኦሊስ ፊልድና
ፍራንክ ጎርደን መጡ፡፡ ጎርደን ነጠላ ጫማውን አወለቀና ላይኛው አልጋ ላይ በመሰላል ወጣ፡፡
ከዚያም ፊልድ ከፒጃማው ውስጥ እጀ ሙቅ ሲያወጣ ዳያና አይታ ደነገጠች፡ ፊልድ ፍራንክ ጎርደንን በጆሮው አንድ ነገር ሲለው ፍራንክ ተቃውሞውን ቢገልጽም ፊልድ ፈርጠም ብሎ የታዘዘውን እንዲፈጽም ሲነግረው አንድ እጁን ሰጠ፡፡ ፊልድ የፍራንክን እጅ በእጀ ሙቁ ከአልጋው ብረት ጋር አሰረና መጋረጃውን ፊቱ ላይ ጋረደበት፡
‹‹ፍራንክ እስረኛ መሆኑ እውነት ሆነ›› አለ ማርክ፡፡
‹‹እኔ ግን ነፍሰ ገዳይ ነው የተባለውን ማመን አቅቶኛል›› አለች ዳያና፡፡
‹‹እኔ ደግሞ ሳይሆን አይቀርም ብዬ ነው የምገምተው›› አለ ማርክ፡
‹‹ሃምሳ ዶላር ከፍለን በመርከብ ከምድረ ምስኪን ጋር ብንሄድ ይሻለን ነበር››
‹‹ፊልድ እጀ ሙቁን ቢፈታለት ጥሩ ነበር፡፡ ልጁ ካልጋው ጋር ተጠፍሮ
እንዴት ሊተኛ እንደሚችል አይገባኝም፡፡ መገላበጥ እንኳን አይችልም፡፡››
‹‹አንቺ ሩህሩህ ነሽ›› አለ ማርክ እቅፉ ውስጥ እየጣላት፡ ‹‹ሰውየው
እኮ ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍር ሰው ነው፡፡ አንቺ ደግሞ እንዴት ሆኖ
ሊተኛ ነው ብለሽ ታዝኛለሽ፡፡››
ዳያና ራሷን ማርክ ትከሻ ላይ አስደገፈች፡ ማርክ ጸጉሯን ይደባብሳል፡፡
ከጥቂት ጊዜ በፊት አናዳው ኤሌክትሪክ ሊጨብጥ ምንም አልቀረውም ነበር፡፡
አሁን ግን ንዴቱ በርዷል፡
ማርክዬ አለች ዳያና ይሄ አልጋ ለሁለት ሰው ይበቃል?›› ስትል
ጠየቀች፡፡
‹‹ፈራሽ የኔ ማር?››
‹‹አይ አልፈራሁም፡፡››
በመጀመሪያ ያለችው ግር ብሎት ነበር፡፡ በኋላ ሃሳቧ ገባውና ፈገግ አለ፡፡ ‹‹ሁለት ሰው ሊያስተኛ ይችላል፡፡ ነገር ግን ጎን ለጎን አይደለም፡፡አንዳችን አንዳችን ላይ መውጣት ይኖርብናል፡፡ አንቺ እላዬ ላይ መውጣት ትፈልጊያለሽ?››
‹‹አዎ እወጣለሁ›› አለች ዳያና እየሳቀች።
‹‹እስቲ ላስብበት›› አላት ኮስተር ብሎ በቀልድ ‹‹ስንት ነው ኪሎሽ?››
‹‹ብዙም አልከብድህም››
‹‹የቀን ልብሳችንን እንለውጥ›› አላት፡፡
ዳያና ባርኔጣዋን አውልቃ ወምበሩ ላይ አስቀመጠች፡፡ ማርክ
የሁለቱንም ቦርሳ ከወምበሩ ስር አወጣ፡፡
ዳያና ወደ መታጠቢያ ቤት መሄድ እንደምትፈልግ ስትነግረው ‹‹ቶሎ በይ›› አለና ደረቱ ላይ ለጥፎ ሳማት፡፡ እቅፍቅፍ ሲሉ የብልቱ መቆም
ተሰማትና አህ!› አለች የእሷም ስሜት ተነሳስቶ፡፡ ስትመለስ እሱም ሊሄድ
ተነሳ፡፡ ‹‹ከመታጠቢያ ቤት ስትመለስ እንደቆመ መምጣት አለብህ››
አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ አትስጊ፤ እንደገና እንዴት እንደምታቆሚው አሳይሻለሁ›› አላት፡፡
‹‹እስክትመለስ በቅንዝር መሞቴ ነው›› ስትል በጆሮው አንሾካሾከች፡
ማርክ ቦርሳውን አንጠልጥሎ ወደ መታጠቢያ ክፍሉ ሄደ፡ መርቪን ከተቃራኒ አቅጣጫ እየመጣ ነው፡፡ ሲተላለፉ ልክ አጥር ላጥር እንደሚተያዩ ድመቶች ቢፋጠጡም ቃል አልተለዋወጡም።
ዳያና መርቫን የለበሰውን ቢጃማ አይታ ‹‹ምንድነው እናትህ የለበስከው?›› ስትል ሳቀችበት፡፡
‹‹ሳቂ እስኪበቃሽ›› አለ፡፡ ‹‹ፎየንስ ላይ ላገኝ የቻልኩት ፒጃማ ይሄ ብቻ ነው›› አላት ‹‹የዚህ አገር ሰዎች ከሃር የተሰራ ፒጃማ መኖሩን እንኳን ሰምተው አያውቁም፡፡ ስጠይቃቸው እብድ ነው ሳይሉ አይቀርም››
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ዳያና መልስ የመስጠት ያህል ከንፈሩን መጠጠችው፡
ከዚያማ ምን ይወራል! ቀለል እያላት ሲመጣ መላ ሰውነቷ ዘና አለ፡፡
እየሳመችው ወንበሩን ተደገፈች፡፡ እየሳመችው ጡቷ ደረቱን ሲታከክ
ተሰማት፡ እንደገና ገላ ለገላ መተሻሸት መቻሏ ደስታ ፈጥሮላታል፡ በከንፈሩ
ጫፍ ከንፈሯን ሲዳስስ ስሜት ውስጥ ገብታ አፏን ከፍታ ተቀበለችው፡፡ ጫን
ጫን መተንፈስ ጀመረች፡ በእርግጥ የሚያደርጉት ነገር መረን የለቀቀ
መሆኑ ታውቋታል፡ ዓይኗን ስትከፍት መርቪንን አየችው:
በመጀመሪያ እያለፈ ስለነበር አላስተዋላትም ነበር፡ ድንገት ወዳለችበት
ፊቱን ዞር ሲያደርግ ያየው ነገር ከእርምጃው ገታው፡ እሷም ስታየው ፊቷ
በድንጋጤ አመድ ለበሰ፡፡
ዳያና ባሏን በሚገባ ስለምታውቀው ምን ሊሰማው እንደሚችል
አልጠፋትም ምንም እንኳ ከማርክ ጋር በፍቅር መክነፏን ሰዎች ቢነግሩትም እውነትነቱን ለመቀበል ከብዶታል፡፡ ከወንድ ጋር ስትሳሳም በዓይኑ በብረቱ ሲያይ በድንጋጤ ክው አለ፡፡
መርቪን በንዴት ግምባሩን ከሰከሰ፡፡ ዳያና ባሏ በቀጥታ ጠብ ይጀምራል
ብላ ፈርታ ነበር፡፡ ሆኖም ቃል ሳይተነፍስ ዞረና መንገዱን ቀጠለ፡፡
ማርክ ‹‹ምንድነው ነገሩ?›› ሲል ጠየቃት፡፡ ዳያናን ይዞ እየጨመጨመ
ስለነበር መርቪንን አላየውም ነበር፡፡
መንገር ስለፈራች ‹‹ሰው ሊያየን ይችላል ይበቃናል›› አለችው:
ማርክም ከዳያና መላቀቁን ቢጠላም መሳሙን አቆመ::
ዳያና የመርቪን አድራጎት አናደዳት፡፡ መርቪን የዓለምን ግማሽ ርቀት እግር በእግር ተከትሏት መምጣቱ ሳያንስ ከማርክ ጋር በተላፋች ቁጥር ሊያፈጥባት መብት የለውም፡፡ ትዳር ባርነት አይደለም፡፡ ጥላው መሄዷን
መቀበል አለበት፡ ማርክም በንዴት ሲጋራ ለኮሰ፡፡ ዳያና ባሏን ፊት ለፊ ልትገጥመው ፈልጋለች፡ በቃ አልፈልግህም ልትለው ተዘጋጅታለች
ተነሳችና ‹‹መዝናኛው ክፍል ምን እንዳለ ለማየት ልሄድ ነው›› አለች
‹‹አንተ እዚህ ቁጭ ብለህ ሲጋራህን ማግ›› አለችውና ከማርክ መልስ ሳትጠብቅ እብስ አለች፡
መርቪን የት እንደተቀመጠ ባታውቅም ፍለጋዋን ቀጠለች፡፡ አሁን የአይሮፕላኑ መናወጥ የቀነሰ በመሆኑ ምንም ነገር ሳትይዝ መራመድ ችላለች፡፡ በመዝናኛ ክፍሉ ውስጥ ሰዎች ካርታ ለመጫወት ጉድ ጉድ እያሉ ሲሆን ክፍሉ
በሲጋራ ታፍኗል፡፡ ፊታቸው የመጠጥ ጠርሙሶች
ተኮልኩለዋል፡፡ ሌላ ክፍል ዘው ስትል የኦክሰንፎርድን ቤተሰብ አገኘች፡:ሎርድ ኦክሰንፎርድ ሳይንቲስቱን ካርል ሃርትማንን ከፍ ዝቅ አድርገው ሲሳደቡ መርቪን ላቭሴይ ሰምቶ እሱ እንደተነካ ተቆርቁሮ ሎርዱን
ለመደብደብ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ተሳፋሪው አይቶታል፡ መርቪን አንዳንዴ እውነት አለው፡፡ እሷም ይህን አትክድም፡፡
ከዚያም ወደ ኩሽና ሄደች፡፡ እዚያም ድብልብሉ ኒኪ ሰሃን ሲያጥብ አገኘችው::
ፎቁን ወጣችና ፓይለቶቹ ክፍል ሄደች፡፡ ሁሉም በስራ የተጠመዱ ስለሆነ ወዲያው አላይዋትም፡፡ በኋላ አንዱ አያትና ‹‹ሌላ ጊዜ እያዞርን ሁሉንም ቦታ እናሳይሻለን፡፡ ነገር ግን አሁን እውጭ ያለው የአየር ሁኔታ
መጥፎ ስለሆነ ቦታሽ ሄደሽ እንድትቀመጪ ቀበቶሽን እንድታስሪ እንጠይቃለን›› አላት፡፡
ደረጃውን ወርዳ ስትጨርስ ከማርክ ጋር ፊት ለፊት ግጥም አለች፡ሁኔታው ቢያስደነግጣትም ‹‹እዚህ ምን ልታደርግ መጣህ?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ራስሽ እዚህ ምን ልታደርጊ መጣሽ?›› አላት፡፡ ካነጋገሩ የተናደደ መሆኑ ያስታውቃል
ዞር ዞር እያልኩ እያየሁ ነው፡፡››
መርቪንን ነው የምትፈልጊው?›› አላት፡
‹‹ማርክ ለምንድነው እንደዚህ የምትሆነው?›› አለች ዳያና፡፡
‹‹ምክንያቱም ባልሽን ለማየት ሹክክ ብለሽ በመሄድሽ››
ኒክ ድንገት መጣና ጭቅጭቃቸውን አቋረጣቸው ወደ
መቀመጫችሁ ተመለሱ፡፡ አሁን በረራው ጥሩ ቢመስልም ትንሽ ቆይቶ
አይሮፕላኑ መወዛወዙ አይቀርም›› አላቸው፡፡
ማርክና ዳያና ወደ ቦታቸው ተመለሱ፡፡ ዳያና ያደረገችው የጅል ስራ መሆኑን ተገንዝባለች፡፡ መርቪንን ስትከታተል መርቪን ደግሞ እሷን ተከታትሎ የምትሰራውን አየባት፡፡
ቦታቸው ቁጭ ብለው ጭቅጭቃቸውን ሊቀጥሉ ሲሉ ኦሊስ ፊልድና
ፍራንክ ጎርደን መጡ፡፡ ጎርደን ነጠላ ጫማውን አወለቀና ላይኛው አልጋ ላይ በመሰላል ወጣ፡፡
ከዚያም ፊልድ ከፒጃማው ውስጥ እጀ ሙቅ ሲያወጣ ዳያና አይታ ደነገጠች፡ ፊልድ ፍራንክ ጎርደንን በጆሮው አንድ ነገር ሲለው ፍራንክ ተቃውሞውን ቢገልጽም ፊልድ ፈርጠም ብሎ የታዘዘውን እንዲፈጽም ሲነግረው አንድ እጁን ሰጠ፡፡ ፊልድ የፍራንክን እጅ በእጀ ሙቁ ከአልጋው ብረት ጋር አሰረና መጋረጃውን ፊቱ ላይ ጋረደበት፡
‹‹ፍራንክ እስረኛ መሆኑ እውነት ሆነ›› አለ ማርክ፡፡
‹‹እኔ ግን ነፍሰ ገዳይ ነው የተባለውን ማመን አቅቶኛል›› አለች ዳያና፡፡
‹‹እኔ ደግሞ ሳይሆን አይቀርም ብዬ ነው የምገምተው›› አለ ማርክ፡
‹‹ሃምሳ ዶላር ከፍለን በመርከብ ከምድረ ምስኪን ጋር ብንሄድ ይሻለን ነበር››
‹‹ፊልድ እጀ ሙቁን ቢፈታለት ጥሩ ነበር፡፡ ልጁ ካልጋው ጋር ተጠፍሮ
እንዴት ሊተኛ እንደሚችል አይገባኝም፡፡ መገላበጥ እንኳን አይችልም፡፡››
‹‹አንቺ ሩህሩህ ነሽ›› አለ ማርክ እቅፉ ውስጥ እየጣላት፡ ‹‹ሰውየው
እኮ ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍር ሰው ነው፡፡ አንቺ ደግሞ እንዴት ሆኖ
ሊተኛ ነው ብለሽ ታዝኛለሽ፡፡››
ዳያና ራሷን ማርክ ትከሻ ላይ አስደገፈች፡ ማርክ ጸጉሯን ይደባብሳል፡፡
ከጥቂት ጊዜ በፊት አናዳው ኤሌክትሪክ ሊጨብጥ ምንም አልቀረውም ነበር፡፡
አሁን ግን ንዴቱ በርዷል፡
ማርክዬ አለች ዳያና ይሄ አልጋ ለሁለት ሰው ይበቃል?›› ስትል
ጠየቀች፡፡
‹‹ፈራሽ የኔ ማር?››
‹‹አይ አልፈራሁም፡፡››
በመጀመሪያ ያለችው ግር ብሎት ነበር፡፡ በኋላ ሃሳቧ ገባውና ፈገግ አለ፡፡ ‹‹ሁለት ሰው ሊያስተኛ ይችላል፡፡ ነገር ግን ጎን ለጎን አይደለም፡፡አንዳችን አንዳችን ላይ መውጣት ይኖርብናል፡፡ አንቺ እላዬ ላይ መውጣት ትፈልጊያለሽ?››
‹‹አዎ እወጣለሁ›› አለች ዳያና እየሳቀች።
‹‹እስቲ ላስብበት›› አላት ኮስተር ብሎ በቀልድ ‹‹ስንት ነው ኪሎሽ?››
‹‹ብዙም አልከብድህም››
‹‹የቀን ልብሳችንን እንለውጥ›› አላት፡፡
ዳያና ባርኔጣዋን አውልቃ ወምበሩ ላይ አስቀመጠች፡፡ ማርክ
የሁለቱንም ቦርሳ ከወምበሩ ስር አወጣ፡፡
ዳያና ወደ መታጠቢያ ቤት መሄድ እንደምትፈልግ ስትነግረው ‹‹ቶሎ በይ›› አለና ደረቱ ላይ ለጥፎ ሳማት፡፡ እቅፍቅፍ ሲሉ የብልቱ መቆም
ተሰማትና አህ!› አለች የእሷም ስሜት ተነሳስቶ፡፡ ስትመለስ እሱም ሊሄድ
ተነሳ፡፡ ‹‹ከመታጠቢያ ቤት ስትመለስ እንደቆመ መምጣት አለብህ››
አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ አትስጊ፤ እንደገና እንዴት እንደምታቆሚው አሳይሻለሁ›› አላት፡፡
‹‹እስክትመለስ በቅንዝር መሞቴ ነው›› ስትል በጆሮው አንሾካሾከች፡
ማርክ ቦርሳውን አንጠልጥሎ ወደ መታጠቢያ ክፍሉ ሄደ፡ መርቪን ከተቃራኒ አቅጣጫ እየመጣ ነው፡፡ ሲተላለፉ ልክ አጥር ላጥር እንደሚተያዩ ድመቶች ቢፋጠጡም ቃል አልተለዋወጡም።
ዳያና መርቫን የለበሰውን ቢጃማ አይታ ‹‹ምንድነው እናትህ የለበስከው?›› ስትል ሳቀችበት፡፡
‹‹ሳቂ እስኪበቃሽ›› አለ፡፡ ‹‹ፎየንስ ላይ ላገኝ የቻልኩት ፒጃማ ይሄ ብቻ ነው›› አላት ‹‹የዚህ አገር ሰዎች ከሃር የተሰራ ፒጃማ መኖሩን እንኳን ሰምተው አያውቁም፡፡ ስጠይቃቸው እብድ ነው ሳይሉ አይቀርም››
👍12🥰1
‹‹ጓደኛህ ሚስስ ሌኔሃን ይህን አለባበስህን የምትወደው አይመስለኝም››
አለችው፡፡ ወዲያው ግን ለምን እንዲህ አልኩት› ብላ ተገረመች፡
መርቪን ጥሏት ሄደ፡
አስተናጋጁ ሲመጣ ‹‹ዴቪ አሁን አልጋችንን አዘጋጅልን›› አለች ዳያና፡፡
‹‹እሺ እመቤቴ››
‹‹አመሰግናለሁ›› አለችና ቦርሳዋን አንጠልጥላ ሄደች፡፡
ወደ መታጠቢያው ክፍል ስትሄድ ባሉት የአይሮፕላን ክፍሎች ሁሉ መርቪን አይታይም፡ ምናልባት በሙሽሮቹ ክፍል ውስጥ ሳይሆን አይቀርም ስትል አሰበች፡፡ ናንሲም የት እንዳለች ማወቅ አልቻለችም፡፡
መርቪንና ናንሲ የሙሽሮቹን ክፍል ሳይጋሩ አይቀርም ብላ ስታስብ እጅግ
በቅናት ተንጨረጨረች።
አየር መንገዱ ሙሽራ ያልሆኑ ሁለት ሰዎችን በሙሽሮች ክፍል
እንዲተኙ መፍቀድ የለበትም፡፡ ምናልባት ሌኔሃን በመጋረጃ በተጋረደው
አልጋ ውስጥ ተኝታ ይሆናል፡፡
ዳያና እውነቱን ማወቅ ፈለገች፡፡
የሙሽሮቹ ክፍል በር ላይ ስትደርስ ለመክፈት ፈራች፡፡ ከዚያም እንደምንም አለችና የበሩን እጀታ ስታዞረው በሩ ተከፈተ፡፡
በሙሽሮቹ ክፍል ውስጥ አንድ ጥግ ላይ ሁለት አልጋ የሚታይ ሲሆን በሌላ ጥግ ደግሞ ትንሽ ሶፋ፣ ጠረጴዛ፣ወንበርና የመዋቢያ ጠረጴዛ
እንዲሁም መስታወት ይታያል፡፡
መርቪን ድንገት ሚስቱ ከተፍ በማለቷ ደነገጠ፡፡ ናንሲ ባትኖርም ኮቷ
ሶፏው ላይ ተቀምጧል፡፡
ዳያና በሩን ዘጋችና ‹‹እንዴት እኔ ላይ እንዲህ ያለ ክህደት
ትፈጽማለህ?›› ስትል አፈጠጠችበት፡፡
‹‹ምን አደረግሁ?››
ጥሩ ጥያቄ ነው አለች በሃሳቧ፡፡ ምንድነው ግን እንዲህ ያናደዳት።
ተሳፋሪው ሁሉ ናንሲ ከእሷ ባል ጋር አንድ ክፍል እንደተጋሩ ያውቃል
‹‹ምርጫ አልነበረኝም፡፡ ሌላ ቦታ አልነበረም›› ሲል መለሰ፡፡
‹‹ሰዎች እንደሚስቁብን አታውቅም? እኔን መከተልህ ሳያንስ!››
‹‹ታዲያ ቢስቁ ምን ቸገረኝ? ሚስቱ ከወንድ ጋር ኮብልላለች ብለው
ነው የሚስቁት››
‹‹ተከትለኸኝ መምጣትህ ነው ደግሞ የባሰው፡፡
እውነታውን ተቀብለህ
አርፈህ እቤትህ መቀመጥ ነበረብህ››
‹‹ታውቂኛለሽ!››
‹‹አውቅሃለሁ፡ ለዚህ ነው ተከትለኸኝ እንዳትመጣ ለማድረግ የሞከርኩት››
ትከሻውን ነቀነቀና ‹‹አልሆነልሽም፡፡ ብልህነት ስለሚጎድልሽ ከእኔ
ማምለጥ አትችይም፡፡››
‹‹ሴትየዋ ለመሆኑ ምን አይነት ሸርሙጣ ብትሆን ነው ካገባ ሰው ጋር
ይሄ ሁሉ ወፈ ሰማይ ባለበት የምትማግጠው? አግብታለች፡፡ ቀለበቷን
አይቻለሁ!››
“ባሏ ሞቷል፡፡ አንቺስ ብትሆኚ ከሷ በምን ትሻያለሽ? አንቺስ ባለትዳር
ሆነሽ ከማንም ውርጋጥ ጋር እየማገጥሽ አይደለም እንዴ?››
‹ባይሆን እኛ እንደናንተ በሙሽሮች ክፍል ውስጥ አይዘጋብንም፡ እንደማንኛውም ተሳፋሪ የተለያየ አልጋ ላይ ነው የምንተኛው›› አለች ከማርክ ጋር እንዴት እንደምትተኛ ያቀደችው እየከነከናት::
‹‹እኔ እኮ ናንሲን ውሽምነት አልያዝኩም፡፡ ያለፉትን ወራት በሙሉ እግርሽን እያነሳሽ ለዚህ ሰው ስትሰጪ የነበርሽው እኮ አንቺ ነሽ፡፡ ይህን ትክጂያለሽ?››
‹‹እንዲህማ ባለጌ አትሁን፡፡ ለአፍህ ለከት ይኑረው።›› ያለው ልክ ነው
አለች በሆዷ፡ ስታደርግ የነበረው እንደዚያ ነው፡፡ እውነትም ገና ማርክጋ
እንደደረሰች ፓንቷን አሽቀንጥራ ነው የምትጥለው፡፡
‹‹ማድረጉ ነው ብልግና ከመናገሩ!›› አለ መርቪን ፈርጠም ብሎ፡
‹‹እኔ ሰው እያየኝ አገር እያወቀ ቀን በቀን አይደለም ያደረግኩት በድብቅ ነው፡፡ እንድታፍር ወይም ሰው እንዲስቅብህ አላደረኩም››
‹‹ለእሱ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ምናልባትም ድፍን ማንቺስተር የሚያውቀውን ነውርሽን የማላውቅ እኔ ብቻ ሳልሆን አልቀርም፡ ማጋጣዎች
የሚሰሩትን ስራ ማንም የሚያውቅ አይመስላቸውም››
‹‹ማጋጣ አትበለኝ!›› ስትል አምባረቀች፡ አባባሏ መልሶ አሳፈራት: ማጋጣ አይደለሁም ልትል የምትችልበትን አቅም አጣች፡:
‹‹ለምንድነው የማልልሽ? ማጋጣ አይደለሽም?››
‹‹አባባልህ አጸያፊ ነው›› አለች ዓይኑን ላለማየት ፊቷን እያዞረች
‹‹በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን እንደተደረገው በዚህ ድርጊትሽ በድንጋይ
ባለመወገርሽ እንደውም አምላክሽን ልታመሰግኚ ይገባሻል፡››
‹‹በጣም አስቀያሚ አባባል ነው››
‹‹ከንግግሩ ይልቅ ድርጊቱ ነው በሃፍረት ሊያሸማቅቅሽ ይገባ የነበረው››
‹‹አንተ ሁልዜ ራስህን ትክክለኛ አድርገህ ትቆጥራለህ›› አለች በክርክሩ ተሰላችታ ‹‹አንተስ አጥፍተህ አታውቅም?››
‹‹አንቺን በተመለከተ ያደረግሁት ሁሉ ትክክል ነው›› አለ በቁጣ፡፡
አሁን በጣም እያናደዳት መጣ፡፡ ‹‹ከኔ በፊት ሁለት ሚስቶችህ ጥለውህ
ሄደዋል፤ አንተ ግን ሁልጊዜ ራስህን ትክክለኛ አድርገህ ትቆጥራለህ፤ ኧረ
ለመሆኑ ከዚህ ቀደም ተሳስተህ እንደምታውቅ በአዕምሮህ መጥቶ
ያውቃል?›› አለችው
አሁን ንዴቱን መቆጣጠር አቃተው፡ እንቅ አድርጎ አንጠልጥሎ ይዞ
ወዘወዛትና የምትፈልጊውን ሁሉ አላደረኩልሽም? አላት በንዴት ገንፍሎ፡
‹‹አንተ ለኔ ግድ ኖሮህ አያውቅም›› ስትል ጮኸች ‹‹እንደ ዕቃ ነበር
የምትቆጥረኝ፤ ለዚህ ነው ትቼህ የሄድኩት፡፡››
እጇን ደረቱ ላይ ቀስራ ይዛ ራሷን ለማላቀቅ እየገፋችው ሳለች በሩ ተhፈተና ማርክ ገባ፡፡
ማርክ ባልና ሚስቱ ላይ እያፈጠጠ ‹‹ዳያና ምንድነው እሱ? በሙሽሮች
ክፍል ውስጥ ልታድሪ ነው እንዴ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
መርቪን ስትገፋው ለቀቃት ‹‹እዚህ አላድርም›› አለችው ማርክን ‹‹ይሄ የናንሲ ክፍል ነው፡፡ መርቪን በዚህ ክፍል በደባልነት ያድራል፡፡››
ማርክ የፌዝ ሳቅ ሳቀና ‹‹የሚገርም ነው!›› አለ፡፡
‹‹ምንም የሚያስቅ ነገር የለም›› ስትል አባባሉን አጣጣለች፡፡
‹‹ያስቃል እንጂ!›› አለ፧ ‹‹ይሄ ሰውዬ ሚስቱን እንደ እብድ እያሳደደ ባለበት ወቅት መንገዱ ላይ ካገኛት ሴት ጋር ተቆላልፎ ተገኘ!››
ዳያና የማርክ አነጋገር አበገናትና ባልዋ ያለጥፋቱ እንዳይወቀስ
‹አልተቆላለፉም›› አለች፤ ‹‹አይሮፕላኑ ውስጥ ያልተያዘው ቦታ ይሄ ብቻ
በመሆኑ ነው አንድ ላይ ለመሆን የተገደዱት››
ታዲያ እኮ ይሄ ሊያስደስትሽ በተገባ ነበር›› አለ ማርክ ‹‹ባልሽ ከእሷ ፍቅር ከያዘው አንቺን ማሳደዱን ያቆማል››
‹‹አሁን መበሳጨቴ አይታይህም ማለት ነው?››
‹‹እርግጥ ነው ተበሳጭተሻል፤ ነገር ግን ለምን እንደተበሳጨሽ ነው
ያልገባኝ›› አለ፡፡ ‹‹መርቪንን እኮ አትወጂውም፧ አንዳንዴ ለአይንሽ እንዳስጠላሽ ትናገሪያለሽ፤ ጥለሽው ሄደሻል፤ ታዲያ ከማንስ ጋር ቢተኛ አንቺ ምን ቤት ነሽ?››
‹‹አላውቅም፤ ያገባኛል! ስራው ያገር መሳቂያ ነው ያደረገኝ፡፡››
ማርክ ያለችው ነገር ሆዱን ምንም አላራራውም፡፡ ‹‹በቀደም መርቪን ጋ
ተመልሼ እሄዳለሁ ብለሽ ያዙኝ ልቀቁኝ ስትይ ነበር፧ስላናደደሽ ግን
ሃሳብሽን ለወጥሽ፤ አሁን ደግሞ ከሌላ ሴት ጋር ተኛ ብለሽ ኤሌክትሪክ
ልትጨብጪ ምንም አልቀረሽም፡፡ አንቺ ሴት ነገርሽ አልገባኝም››
‹‹እኔ ከናንሲ ጋር አልተኛሁም›› አለ መርቪን የማርክን ንግግር
አቋርጦ::ማርክ ለመርቪን መልስ ሳይሰጥ ‹‹ለመርቪን ያለሽ ፍቅር ያበቃ ለመሆኑ እርግጠኛ ነሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ያለ ክፉ ነገር ትናገረኛለህ?››
አውቃለሁ ንግግሬ ክፉ እንደሆነ ታዲያ ያልኩት እውነት አይደለም?››
‹‹አይደለም፡፡ እንዲህ ብለህ በመናገርህ አስጠልተኸኛል›› አለችና ጧ
ብላ አለቀሰች
‹‹እንግዲህ እውነት አለመሆኑን አረጋግጪልኛ! አሁን ተይውና እኔጋ ነይ ከማንም ጋር ቢተኛ ግድ እንደሌለሽ በተግባር አሳይ!››
‹‹እኔ ምንጊዜም ፈተና አልፌ አላውቅም›› ስትል ጮኸች ‹‹ሎጂክህን ተወኝ ይሄ የክርክር መድረክ አይደለም››
አለችው፡፡ ወዲያው ግን ለምን እንዲህ አልኩት› ብላ ተገረመች፡
መርቪን ጥሏት ሄደ፡
አስተናጋጁ ሲመጣ ‹‹ዴቪ አሁን አልጋችንን አዘጋጅልን›› አለች ዳያና፡፡
‹‹እሺ እመቤቴ››
‹‹አመሰግናለሁ›› አለችና ቦርሳዋን አንጠልጥላ ሄደች፡፡
ወደ መታጠቢያው ክፍል ስትሄድ ባሉት የአይሮፕላን ክፍሎች ሁሉ መርቪን አይታይም፡ ምናልባት በሙሽሮቹ ክፍል ውስጥ ሳይሆን አይቀርም ስትል አሰበች፡፡ ናንሲም የት እንዳለች ማወቅ አልቻለችም፡፡
መርቪንና ናንሲ የሙሽሮቹን ክፍል ሳይጋሩ አይቀርም ብላ ስታስብ እጅግ
በቅናት ተንጨረጨረች።
አየር መንገዱ ሙሽራ ያልሆኑ ሁለት ሰዎችን በሙሽሮች ክፍል
እንዲተኙ መፍቀድ የለበትም፡፡ ምናልባት ሌኔሃን በመጋረጃ በተጋረደው
አልጋ ውስጥ ተኝታ ይሆናል፡፡
ዳያና እውነቱን ማወቅ ፈለገች፡፡
የሙሽሮቹ ክፍል በር ላይ ስትደርስ ለመክፈት ፈራች፡፡ ከዚያም እንደምንም አለችና የበሩን እጀታ ስታዞረው በሩ ተከፈተ፡፡
በሙሽሮቹ ክፍል ውስጥ አንድ ጥግ ላይ ሁለት አልጋ የሚታይ ሲሆን በሌላ ጥግ ደግሞ ትንሽ ሶፋ፣ ጠረጴዛ፣ወንበርና የመዋቢያ ጠረጴዛ
እንዲሁም መስታወት ይታያል፡፡
መርቪን ድንገት ሚስቱ ከተፍ በማለቷ ደነገጠ፡፡ ናንሲ ባትኖርም ኮቷ
ሶፏው ላይ ተቀምጧል፡፡
ዳያና በሩን ዘጋችና ‹‹እንዴት እኔ ላይ እንዲህ ያለ ክህደት
ትፈጽማለህ?›› ስትል አፈጠጠችበት፡፡
‹‹ምን አደረግሁ?››
ጥሩ ጥያቄ ነው አለች በሃሳቧ፡፡ ምንድነው ግን እንዲህ ያናደዳት።
ተሳፋሪው ሁሉ ናንሲ ከእሷ ባል ጋር አንድ ክፍል እንደተጋሩ ያውቃል
‹‹ምርጫ አልነበረኝም፡፡ ሌላ ቦታ አልነበረም›› ሲል መለሰ፡፡
‹‹ሰዎች እንደሚስቁብን አታውቅም? እኔን መከተልህ ሳያንስ!››
‹‹ታዲያ ቢስቁ ምን ቸገረኝ? ሚስቱ ከወንድ ጋር ኮብልላለች ብለው
ነው የሚስቁት››
‹‹ተከትለኸኝ መምጣትህ ነው ደግሞ የባሰው፡፡
እውነታውን ተቀብለህ
አርፈህ እቤትህ መቀመጥ ነበረብህ››
‹‹ታውቂኛለሽ!››
‹‹አውቅሃለሁ፡ ለዚህ ነው ተከትለኸኝ እንዳትመጣ ለማድረግ የሞከርኩት››
ትከሻውን ነቀነቀና ‹‹አልሆነልሽም፡፡ ብልህነት ስለሚጎድልሽ ከእኔ
ማምለጥ አትችይም፡፡››
‹‹ሴትየዋ ለመሆኑ ምን አይነት ሸርሙጣ ብትሆን ነው ካገባ ሰው ጋር
ይሄ ሁሉ ወፈ ሰማይ ባለበት የምትማግጠው? አግብታለች፡፡ ቀለበቷን
አይቻለሁ!››
“ባሏ ሞቷል፡፡ አንቺስ ብትሆኚ ከሷ በምን ትሻያለሽ? አንቺስ ባለትዳር
ሆነሽ ከማንም ውርጋጥ ጋር እየማገጥሽ አይደለም እንዴ?››
‹ባይሆን እኛ እንደናንተ በሙሽሮች ክፍል ውስጥ አይዘጋብንም፡ እንደማንኛውም ተሳፋሪ የተለያየ አልጋ ላይ ነው የምንተኛው›› አለች ከማርክ ጋር እንዴት እንደምትተኛ ያቀደችው እየከነከናት::
‹‹እኔ እኮ ናንሲን ውሽምነት አልያዝኩም፡፡ ያለፉትን ወራት በሙሉ እግርሽን እያነሳሽ ለዚህ ሰው ስትሰጪ የነበርሽው እኮ አንቺ ነሽ፡፡ ይህን ትክጂያለሽ?››
‹‹እንዲህማ ባለጌ አትሁን፡፡ ለአፍህ ለከት ይኑረው።›› ያለው ልክ ነው
አለች በሆዷ፡ ስታደርግ የነበረው እንደዚያ ነው፡፡ እውነትም ገና ማርክጋ
እንደደረሰች ፓንቷን አሽቀንጥራ ነው የምትጥለው፡፡
‹‹ማድረጉ ነው ብልግና ከመናገሩ!›› አለ መርቪን ፈርጠም ብሎ፡
‹‹እኔ ሰው እያየኝ አገር እያወቀ ቀን በቀን አይደለም ያደረግኩት በድብቅ ነው፡፡ እንድታፍር ወይም ሰው እንዲስቅብህ አላደረኩም››
‹‹ለእሱ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ምናልባትም ድፍን ማንቺስተር የሚያውቀውን ነውርሽን የማላውቅ እኔ ብቻ ሳልሆን አልቀርም፡ ማጋጣዎች
የሚሰሩትን ስራ ማንም የሚያውቅ አይመስላቸውም››
‹‹ማጋጣ አትበለኝ!›› ስትል አምባረቀች፡ አባባሏ መልሶ አሳፈራት: ማጋጣ አይደለሁም ልትል የምትችልበትን አቅም አጣች፡:
‹‹ለምንድነው የማልልሽ? ማጋጣ አይደለሽም?››
‹‹አባባልህ አጸያፊ ነው›› አለች ዓይኑን ላለማየት ፊቷን እያዞረች
‹‹በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን እንደተደረገው በዚህ ድርጊትሽ በድንጋይ
ባለመወገርሽ እንደውም አምላክሽን ልታመሰግኚ ይገባሻል፡››
‹‹በጣም አስቀያሚ አባባል ነው››
‹‹ከንግግሩ ይልቅ ድርጊቱ ነው በሃፍረት ሊያሸማቅቅሽ ይገባ የነበረው››
‹‹አንተ ሁልዜ ራስህን ትክክለኛ አድርገህ ትቆጥራለህ›› አለች በክርክሩ ተሰላችታ ‹‹አንተስ አጥፍተህ አታውቅም?››
‹‹አንቺን በተመለከተ ያደረግሁት ሁሉ ትክክል ነው›› አለ በቁጣ፡፡
አሁን በጣም እያናደዳት መጣ፡፡ ‹‹ከኔ በፊት ሁለት ሚስቶችህ ጥለውህ
ሄደዋል፤ አንተ ግን ሁልጊዜ ራስህን ትክክለኛ አድርገህ ትቆጥራለህ፤ ኧረ
ለመሆኑ ከዚህ ቀደም ተሳስተህ እንደምታውቅ በአዕምሮህ መጥቶ
ያውቃል?›› አለችው
አሁን ንዴቱን መቆጣጠር አቃተው፡ እንቅ አድርጎ አንጠልጥሎ ይዞ
ወዘወዛትና የምትፈልጊውን ሁሉ አላደረኩልሽም? አላት በንዴት ገንፍሎ፡
‹‹አንተ ለኔ ግድ ኖሮህ አያውቅም›› ስትል ጮኸች ‹‹እንደ ዕቃ ነበር
የምትቆጥረኝ፤ ለዚህ ነው ትቼህ የሄድኩት፡፡››
እጇን ደረቱ ላይ ቀስራ ይዛ ራሷን ለማላቀቅ እየገፋችው ሳለች በሩ ተhፈተና ማርክ ገባ፡፡
ማርክ ባልና ሚስቱ ላይ እያፈጠጠ ‹‹ዳያና ምንድነው እሱ? በሙሽሮች
ክፍል ውስጥ ልታድሪ ነው እንዴ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
መርቪን ስትገፋው ለቀቃት ‹‹እዚህ አላድርም›› አለችው ማርክን ‹‹ይሄ የናንሲ ክፍል ነው፡፡ መርቪን በዚህ ክፍል በደባልነት ያድራል፡፡››
ማርክ የፌዝ ሳቅ ሳቀና ‹‹የሚገርም ነው!›› አለ፡፡
‹‹ምንም የሚያስቅ ነገር የለም›› ስትል አባባሉን አጣጣለች፡፡
‹‹ያስቃል እንጂ!›› አለ፧ ‹‹ይሄ ሰውዬ ሚስቱን እንደ እብድ እያሳደደ ባለበት ወቅት መንገዱ ላይ ካገኛት ሴት ጋር ተቆላልፎ ተገኘ!››
ዳያና የማርክ አነጋገር አበገናትና ባልዋ ያለጥፋቱ እንዳይወቀስ
‹አልተቆላለፉም›› አለች፤ ‹‹አይሮፕላኑ ውስጥ ያልተያዘው ቦታ ይሄ ብቻ
በመሆኑ ነው አንድ ላይ ለመሆን የተገደዱት››
ታዲያ እኮ ይሄ ሊያስደስትሽ በተገባ ነበር›› አለ ማርክ ‹‹ባልሽ ከእሷ ፍቅር ከያዘው አንቺን ማሳደዱን ያቆማል››
‹‹አሁን መበሳጨቴ አይታይህም ማለት ነው?››
‹‹እርግጥ ነው ተበሳጭተሻል፤ ነገር ግን ለምን እንደተበሳጨሽ ነው
ያልገባኝ›› አለ፡፡ ‹‹መርቪንን እኮ አትወጂውም፧ አንዳንዴ ለአይንሽ እንዳስጠላሽ ትናገሪያለሽ፤ ጥለሽው ሄደሻል፤ ታዲያ ከማንስ ጋር ቢተኛ አንቺ ምን ቤት ነሽ?››
‹‹አላውቅም፤ ያገባኛል! ስራው ያገር መሳቂያ ነው ያደረገኝ፡፡››
ማርክ ያለችው ነገር ሆዱን ምንም አላራራውም፡፡ ‹‹በቀደም መርቪን ጋ
ተመልሼ እሄዳለሁ ብለሽ ያዙኝ ልቀቁኝ ስትይ ነበር፧ስላናደደሽ ግን
ሃሳብሽን ለወጥሽ፤ አሁን ደግሞ ከሌላ ሴት ጋር ተኛ ብለሽ ኤሌክትሪክ
ልትጨብጪ ምንም አልቀረሽም፡፡ አንቺ ሴት ነገርሽ አልገባኝም››
‹‹እኔ ከናንሲ ጋር አልተኛሁም›› አለ መርቪን የማርክን ንግግር
አቋርጦ::ማርክ ለመርቪን መልስ ሳይሰጥ ‹‹ለመርቪን ያለሽ ፍቅር ያበቃ ለመሆኑ እርግጠኛ ነሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ያለ ክፉ ነገር ትናገረኛለህ?››
አውቃለሁ ንግግሬ ክፉ እንደሆነ ታዲያ ያልኩት እውነት አይደለም?››
‹‹አይደለም፡፡ እንዲህ ብለህ በመናገርህ አስጠልተኸኛል›› አለችና ጧ
ብላ አለቀሰች
‹‹እንግዲህ እውነት አለመሆኑን አረጋግጪልኛ! አሁን ተይውና እኔጋ ነይ ከማንም ጋር ቢተኛ ግድ እንደሌለሽ በተግባር አሳይ!››
‹‹እኔ ምንጊዜም ፈተና አልፌ አላውቅም›› ስትል ጮኸች ‹‹ሎጂክህን ተወኝ ይሄ የክርክር መድረክ አይደለም››
👍12🥰1
‹‹እውነት ነው የክርክር መድረክ አይደለም›› አለ ሌላ ድምጽ፤ ሶስቱ
ሰዎች ድምጹን ወደሰሙበት አቅጣጫ ሲዞሩ ናንሲ ሌኔሃን በመኝታ ልብሷ
አምራና ደምቃ በሩጋ ቆማለች፡ ‹‹እንደ እውነቱ ከሆነ›› አለች ንግግሯን
በመቀጠል ‹‹ይሄ የኔ ክፍል ነው በዚህ ክፍል ውስጥ እየተካሄደ ያለው
ነገር ምን እንደሆነ ብትነግሩኝ?››.....
✨ይቀጥላል✨
ሰዎች ድምጹን ወደሰሙበት አቅጣጫ ሲዞሩ ናንሲ ሌኔሃን በመኝታ ልብሷ
አምራና ደምቃ በሩጋ ቆማለች፡ ‹‹እንደ እውነቱ ከሆነ›› አለች ንግግሯን
በመቀጠል ‹‹ይሄ የኔ ክፍል ነው በዚህ ክፍል ውስጥ እየተካሄደ ያለው
ነገር ምን እንደሆነ ብትነግሩኝ?››.....
✨ይቀጥላል✨
👍6🥰3
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሁለት ሳምንት አለፈው ካርለትና ከሎ የየራሳቸውን የጕዞ ዝግጅት ሲያደርጉ ሰነበቱ። ከሎ ሐመር ሲሄድ የሚያነባቸው ልብወለድና
ታሪክ ነክ የአማርኛ መጻሕፍት፣ መጽሔቶች፣ በእንግሊዝኛ የተጻፉ
ልብወለድና የሳይንስ መጻሕፍትን እየገዛ ከፊሉንም እየተዋሰ
አዘጋጀ"
በተለይም ካርለት ኮተቷ በዛ" በማስታወሻዋ በዝርዝር ከያዘችው
አስፈላጊ የምግብ ዓይነቶች የታሸገ የዓሣ፣ የአሳማ፣ የከብት ሥጋ የድንች የዱባ፣ ያጃ ሾርባI የፓፓያ፣ የብርቱካን፣ የአናናስ
ጭማቂ ኃይል ሰጪ ንጥረ ነገር የበዛበት ብስኩት ደረቅ ብስኩት የቆርቆሮ ቢራ ወዘተ ከመድኃኒ ዓይነትም ክሎሮኪን፣ ፓልዱሪን፣ ኒቫኩይን ለወባ መከላከያI ሌሎች፣ «አንቲባዮቲክስ» መድኃኒቶችንና የመጀመሪያ ሕክምና ኪት ኮዳክ ፊልሞችI ባትሪ
ድንጋዮችI ሶፍቶች ወዘተ. በአራት የፕላስቲh ሣጥኖች ደረደረች" ካኖንና ፔንታክስ ካሜራዋንና የተለያየ መጠን ያላቸውን ሌንሶች
በእጅ በሚንጠለጠለው ቦርሳዋ ካኪ ሱሪዎች፣ ካኔትራ፣ ውስጥ
ሱሪ ፎጣ፣ ጡት ማስያዣ፣ ስሊፒንግ ባግ፣ ግራጫ መልክ ያለው ሹራብ በአየር የሚሞላና ሌላ ተጣጣፊ ፍራሽ፣ ሳሙና፣ ኦሞ፣
ከሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በፊት በሞዛርት የተቀነባበሩ የፒያኖ ሶናታና የፒያኖ ኮንቸቶ የቤቶቪን ሲንፎኒ ከሦስት ጊዜ በላይ
የወርቅ ዲስክ አሸናፊው ድምፃዊ የቢሊ ጆይል፤ ከሦስት መቶ ዓመት
በፊት የነበረውና የሲንፎኒ አባቱ የሃይደን እንዲሁም ሌሎቹን የባሮክ
ክላሲካል፣ ሮማንቲክና ዘመናዊ የሙዚቃ ካሴቶችን፣ ማስታወሻ፣
ብዕር መጻሕፍትና መጽሔቶች በአራት ማዕዘኑ የብረት ሣጥን
ውስጥ ከተተች" ለሽፍን ላንድ ክሩሰር ቶዮታ መኪናዋም በሁለቱም
ታንከር ነዳጅ ሞላች“ አምስት ጀሪካን ናፍጣም ለመጠባበቂያ ያዘች
ካርለት ለሦስት ወራት የሚያስፈልጋትን ቁሳቁስ ካሟላች በኋላ
ቀሪውን ዕቃዋንና ገንዘቧን ስቲቭ በሰጣት ክፍል ውስጥ
አስቀመጠች» ለአንዳንድ ወጪ ብላ የያዘችውን ሦስት ሺህ አምስት
መቶ የኢትዮጵያ ብርም በሹራቧ ውስጥ በሰፋችው ስውር ኪስ፣
አንገቷ ላይ በምታንጠለጥለው የጨርቅ ቦርሳና ብረት ሣጥኑ ውስጥ
አhፋፍላ ያዘች
ሰኞ ጠዋት ልክ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ አራት ኪሎ ሞቢሉ
ጎን ካለው ሱቅ በር ላይ በቀጠሯቸው ተገናኙu ካርለት ልጥፍ የኋላ
ኪስ ያለው ካኪ ሱሪ፣ ተረከዙ ፕላስቲክ የሆነ ሽፍን ባለማሰሪያ
ማ፣ ቡና ዓይነት ቲ–ሸርት ለብሳ፣ አንገቷ ላይ አነስ ያለ ነጭ ፎጣ
ጣል አድርጋ፣ ከመኪናው በመውረድ የከሎን «ዩኤስኤ» የሚል
ወስፋት የነፋው የሕፃን ሆድ መስሎ የተወጠረ ቦርሳ የኋላ በሩን ከፍታ
በዕቃ ከሞላው መኪና ውስጥ በአንድ በኩል ባለው ክፍት ቦታ
አስገባችና ወደ መኪናው ውስጥ ገቡ" ካርለት የውኃ ኮዳዋን፣ ዳቦ
የያዘ ላስቲኳን አቀረበችና ከከሎና እሷ መካከል ካለው የካሴት ሣጥን
የሞዛርትን ፒያኖ ሶናታ ወደ መኪናው ቴፕ አስገብታ ማስታወሻዋን
በማውጣት የተነሡበትን ሰዓት መዘገበች" ከዚያም ፈገግ ብላ
«መሄድ እንችላለን?» አለችው።
«ኢ ህ» አላት ከሎ፣ ዝግጁ መሆኑን አንገቱን በማወዛወዝ እየገለጸ። ካርለት፣ ቀኝ እጇን ማርሹ ላይ በማስቀመጥ፣ በግራ እግሯ ፍሪሲዮኑን እረግጣ፣ የመኪናውን መስተዋት አየትየት በማድረግ
በአራት ኪሎው የድል ሐውልት ወደ ቀኝ ታጥፈው፣ በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት አድርገው ቁልቁል ወደ መስቀል አደባባይ ወረዱ።
ከዚያም በደብረ ዘይት መንገድ ወደ ቃሊቲ፣ አቃቂ፣ዱከም ተጕዘው ደብረ ዘይት ከተማ ሲደርሱ ወደ ግራ ታጥፈው ሁለት ኪሎ ሜትር በመጓዝ ዠመኪናዋን ሆራ ሆቴል አቁመው ለቁርስ ወደ ውስጥ ገቡ" በስተጀርባ፣ ከሐይቁ ትይዩ የመርከብ ላይ መናፈሻ ከሚመስለው ስፍራ ሆነው የተለያዩና ቱር ቱር እያሉ በመዘመር
የሚበሩ አዕዋፍን እያዩ ቁርሳቸውን ተመግበው ወጡ" ካርለትና ከሎ
ሆራ በሞጆ ታጥፈው፣ ወደ ሻሸመኔ ጕዟቸውን ተያያዙ“ ካርለት፣በመንገዱ ግራና ቀኝ የግራር፣ የጥድ፣ የኮሶ፣ የዝግባ...ዛፎችንና
የተለያዩ ቀለም ያላቸውን እፅዋት እያየች፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ከሚኙት ከሃያ በላይ አዕዋፋት ውስጥ የምታያቸውን በመልክና
በቅርፃቸው ለማወቅ በጆን ጂ ዊሊያምስና በኖርማን አርሎት የተጻፈውን የአዕዋፍ ምስል፣ ቀለም ባሕርይና የሚገኙበትን አካባቢ እያየች ተጓዙና ለምሳ በስምጥ ሸለቆ ካሉት ሐይቆችና የመናፈሻ ቦታዎች አንዱ ወደሆነው ወደ ላንጋኖ ከመንገዱ ወደ ግራ ታጥፈው ገቡ"
ላንጋኖ ሆቴል ምግብ ቤት ብዙ የውጪ ሀገር ዜጎች፣ አፍሪቃውያንና ኢትዮጵያውያን ክብ እየሠሩ በመጫወት ይመገባሉ። ከሆቴሉ ውጪ በቀላል ድንኳን ጥግ፣ በዋና ውስጥ ሱሪና ጡት ማስያዣ
ሆነው የፀሐይ ክሬም ሰውነታቸውን የሚቀቡና ሐይቁ ዳር ለዳር
የሚዋኙ ሴትና ወንዶች ይታያሉ" ጥቁርና ነጭ ሕፃናትም በመዋኛ
ፕላስቲክ ውኃውን በማንቦራጨቅ እየተንጫጩ ይጫወታሉ ከሎና ካርለት ከምግብ ቤቱ ትይዩ የፀሐይ ጃንጥላው ውስጥ
ተቀምጠው ቡናቸውን ሲጎነጩ ቆዩና ካርለት የሐይቁን ዳር ትርምስ
አሸጋግራ ስትቃኝ ቆይታ፣ «ሐይቅ ዳር ስሆን እረካለሁI አገሬ ውስጥ ከጓደኞቼና ቤተሰቦቼ ጋር ያለሁ ስለሚመስለኝ የደስታ ስሜት ይሰማኛል" በአውሮፓ፣ ብዙዎች መዝናኛዎች የሚገኙት ባሕር ዳርቻ ነው" ብቻ...» ካርለት ከሎ ሆራን በጎን ተመለከተችው“
«ኢ ህ» አላት እግሮቹን ወደፊት በመዘርጋት ሰውነቱን ለጥጦ" ካርለት የከሎ ሆራ ጠባይ ደንቋታል ግን አልከፋትም" በቀላሉ ከምትግባባቸው ሰዎች ይልቅ አስቸጋሪ ባሕርይ ያላቸውን ታከብራለች" ሁሉም ሰው ሊረዳው የሚችል ባሕርይ ያላቸው ሰዎች ለሷ አያረኳትም" እረቀቅ ያለ ባሕርይ ያላቸውን ግን አእምሮዋን
አስደንሳ መላ ፈጥራ፣ የተለያየ ስልት በመጠቀም እንደ ግል ሬዲዮና መከፈት መዝጋት እንደ መቻል
የምትረካበት ነገር የለም።
ለዚህም ካርለት «ዘመናችን የሚርጠው ልዩና ውስብስብ አስተሳሰብ ያላቸውን ነው" ምክንያቱም የነገው ፈጠራና ብሩህ
ሕልም ህላዊነት በመዳፋቸው መሃል ያለው ከእነዚህ ዓይነት ግራ
አጋቢ ባሕርይ ካላቸው ሰዎች ነው» ብላ ታምናለች።
ከሎ ቅንና ተባባሪ ሰው መሆኑን፣ ነገር ግን ይህን ባሕሪውን የሚገልጽ የቃላት ድርደራ ችሎታ የሚጎድለው መሆኑን ተገንዝባለች" ካርለት ከሎን የተለያዩ ነገሮችን እያወራች
እየጠየቀች የቱ እንደሚያስደስተው፣ የቱ አፍንጫውን እንደሚ
ያስነፋውና ጥንካሬውን ከደካማ ጎኑ ለመለየት ምርምሯን ስለ ቀጠለች
አንድ ወጥ በሆነው የሥውር ባሕርይው ዋሻ ለመግባት ትልቁ
የድንጋይ መዝጊያ ማንቀሳቀስ ጀምራለች።
«አዎ የከሎ ባሕርይ ራሱ መጠናት የሚገባው ነው" እሱን ለማጥናት ግን አስፈላጊውን ቁልፍ ማዘጋጀት አለብኝ» አለች
ካርለት፣ ከሻሸመኔ ከተማ ወጥታ የአርባ ምንጭን መንገድ ስትይዝ"
ከሻሸመኔ ትንሽ ራቅ ብለው የአስፋልቱ ጐዳና አልቆ ኮረኮንቹን መንገድ ሲጀምሩ ግን መኪናዋ እየተገጨች ስትንሰጠሰጥና ከፊት
ለፊቷ ያሉትን መኪናዎች ስታልፍና ከእሷ ተቃራኒ የሚያልፉት መኪናዎች የሚያነሡት አቧራ መኪናዋ ውስጥ እየገባ ማፈን
ሲጀምር፣ ካርለት መኪናዋን አቁማ፣ ጸጕሯን በመሸብለል፣ ቆብ
ደፋችበትና መኪናዋን በማንቀሳቀስ ከመሪው ጋር መታገል ጀመረች"
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሁለት ሳምንት አለፈው ካርለትና ከሎ የየራሳቸውን የጕዞ ዝግጅት ሲያደርጉ ሰነበቱ። ከሎ ሐመር ሲሄድ የሚያነባቸው ልብወለድና
ታሪክ ነክ የአማርኛ መጻሕፍት፣ መጽሔቶች፣ በእንግሊዝኛ የተጻፉ
ልብወለድና የሳይንስ መጻሕፍትን እየገዛ ከፊሉንም እየተዋሰ
አዘጋጀ"
በተለይም ካርለት ኮተቷ በዛ" በማስታወሻዋ በዝርዝር ከያዘችው
አስፈላጊ የምግብ ዓይነቶች የታሸገ የዓሣ፣ የአሳማ፣ የከብት ሥጋ የድንች የዱባ፣ ያጃ ሾርባI የፓፓያ፣ የብርቱካን፣ የአናናስ
ጭማቂ ኃይል ሰጪ ንጥረ ነገር የበዛበት ብስኩት ደረቅ ብስኩት የቆርቆሮ ቢራ ወዘተ ከመድኃኒ ዓይነትም ክሎሮኪን፣ ፓልዱሪን፣ ኒቫኩይን ለወባ መከላከያI ሌሎች፣ «አንቲባዮቲክስ» መድኃኒቶችንና የመጀመሪያ ሕክምና ኪት ኮዳክ ፊልሞችI ባትሪ
ድንጋዮችI ሶፍቶች ወዘተ. በአራት የፕላስቲh ሣጥኖች ደረደረች" ካኖንና ፔንታክስ ካሜራዋንና የተለያየ መጠን ያላቸውን ሌንሶች
በእጅ በሚንጠለጠለው ቦርሳዋ ካኪ ሱሪዎች፣ ካኔትራ፣ ውስጥ
ሱሪ ፎጣ፣ ጡት ማስያዣ፣ ስሊፒንግ ባግ፣ ግራጫ መልክ ያለው ሹራብ በአየር የሚሞላና ሌላ ተጣጣፊ ፍራሽ፣ ሳሙና፣ ኦሞ፣
ከሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በፊት በሞዛርት የተቀነባበሩ የፒያኖ ሶናታና የፒያኖ ኮንቸቶ የቤቶቪን ሲንፎኒ ከሦስት ጊዜ በላይ
የወርቅ ዲስክ አሸናፊው ድምፃዊ የቢሊ ጆይል፤ ከሦስት መቶ ዓመት
በፊት የነበረውና የሲንፎኒ አባቱ የሃይደን እንዲሁም ሌሎቹን የባሮክ
ክላሲካል፣ ሮማንቲክና ዘመናዊ የሙዚቃ ካሴቶችን፣ ማስታወሻ፣
ብዕር መጻሕፍትና መጽሔቶች በአራት ማዕዘኑ የብረት ሣጥን
ውስጥ ከተተች" ለሽፍን ላንድ ክሩሰር ቶዮታ መኪናዋም በሁለቱም
ታንከር ነዳጅ ሞላች“ አምስት ጀሪካን ናፍጣም ለመጠባበቂያ ያዘች
ካርለት ለሦስት ወራት የሚያስፈልጋትን ቁሳቁስ ካሟላች በኋላ
ቀሪውን ዕቃዋንና ገንዘቧን ስቲቭ በሰጣት ክፍል ውስጥ
አስቀመጠች» ለአንዳንድ ወጪ ብላ የያዘችውን ሦስት ሺህ አምስት
መቶ የኢትዮጵያ ብርም በሹራቧ ውስጥ በሰፋችው ስውር ኪስ፣
አንገቷ ላይ በምታንጠለጥለው የጨርቅ ቦርሳና ብረት ሣጥኑ ውስጥ
አhፋፍላ ያዘች
ሰኞ ጠዋት ልክ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ አራት ኪሎ ሞቢሉ
ጎን ካለው ሱቅ በር ላይ በቀጠሯቸው ተገናኙu ካርለት ልጥፍ የኋላ
ኪስ ያለው ካኪ ሱሪ፣ ተረከዙ ፕላስቲክ የሆነ ሽፍን ባለማሰሪያ
ማ፣ ቡና ዓይነት ቲ–ሸርት ለብሳ፣ አንገቷ ላይ አነስ ያለ ነጭ ፎጣ
ጣል አድርጋ፣ ከመኪናው በመውረድ የከሎን «ዩኤስኤ» የሚል
ወስፋት የነፋው የሕፃን ሆድ መስሎ የተወጠረ ቦርሳ የኋላ በሩን ከፍታ
በዕቃ ከሞላው መኪና ውስጥ በአንድ በኩል ባለው ክፍት ቦታ
አስገባችና ወደ መኪናው ውስጥ ገቡ" ካርለት የውኃ ኮዳዋን፣ ዳቦ
የያዘ ላስቲኳን አቀረበችና ከከሎና እሷ መካከል ካለው የካሴት ሣጥን
የሞዛርትን ፒያኖ ሶናታ ወደ መኪናው ቴፕ አስገብታ ማስታወሻዋን
በማውጣት የተነሡበትን ሰዓት መዘገበች" ከዚያም ፈገግ ብላ
«መሄድ እንችላለን?» አለችው።
«ኢ ህ» አላት ከሎ፣ ዝግጁ መሆኑን አንገቱን በማወዛወዝ እየገለጸ። ካርለት፣ ቀኝ እጇን ማርሹ ላይ በማስቀመጥ፣ በግራ እግሯ ፍሪሲዮኑን እረግጣ፣ የመኪናውን መስተዋት አየትየት በማድረግ
በአራት ኪሎው የድል ሐውልት ወደ ቀኝ ታጥፈው፣ በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት አድርገው ቁልቁል ወደ መስቀል አደባባይ ወረዱ።
ከዚያም በደብረ ዘይት መንገድ ወደ ቃሊቲ፣ አቃቂ፣ዱከም ተጕዘው ደብረ ዘይት ከተማ ሲደርሱ ወደ ግራ ታጥፈው ሁለት ኪሎ ሜትር በመጓዝ ዠመኪናዋን ሆራ ሆቴል አቁመው ለቁርስ ወደ ውስጥ ገቡ" በስተጀርባ፣ ከሐይቁ ትይዩ የመርከብ ላይ መናፈሻ ከሚመስለው ስፍራ ሆነው የተለያዩና ቱር ቱር እያሉ በመዘመር
የሚበሩ አዕዋፍን እያዩ ቁርሳቸውን ተመግበው ወጡ" ካርለትና ከሎ
ሆራ በሞጆ ታጥፈው፣ ወደ ሻሸመኔ ጕዟቸውን ተያያዙ“ ካርለት፣በመንገዱ ግራና ቀኝ የግራር፣ የጥድ፣ የኮሶ፣ የዝግባ...ዛፎችንና
የተለያዩ ቀለም ያላቸውን እፅዋት እያየች፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ከሚኙት ከሃያ በላይ አዕዋፋት ውስጥ የምታያቸውን በመልክና
በቅርፃቸው ለማወቅ በጆን ጂ ዊሊያምስና በኖርማን አርሎት የተጻፈውን የአዕዋፍ ምስል፣ ቀለም ባሕርይና የሚገኙበትን አካባቢ እያየች ተጓዙና ለምሳ በስምጥ ሸለቆ ካሉት ሐይቆችና የመናፈሻ ቦታዎች አንዱ ወደሆነው ወደ ላንጋኖ ከመንገዱ ወደ ግራ ታጥፈው ገቡ"
ላንጋኖ ሆቴል ምግብ ቤት ብዙ የውጪ ሀገር ዜጎች፣ አፍሪቃውያንና ኢትዮጵያውያን ክብ እየሠሩ በመጫወት ይመገባሉ። ከሆቴሉ ውጪ በቀላል ድንኳን ጥግ፣ በዋና ውስጥ ሱሪና ጡት ማስያዣ
ሆነው የፀሐይ ክሬም ሰውነታቸውን የሚቀቡና ሐይቁ ዳር ለዳር
የሚዋኙ ሴትና ወንዶች ይታያሉ" ጥቁርና ነጭ ሕፃናትም በመዋኛ
ፕላስቲክ ውኃውን በማንቦራጨቅ እየተንጫጩ ይጫወታሉ ከሎና ካርለት ከምግብ ቤቱ ትይዩ የፀሐይ ጃንጥላው ውስጥ
ተቀምጠው ቡናቸውን ሲጎነጩ ቆዩና ካርለት የሐይቁን ዳር ትርምስ
አሸጋግራ ስትቃኝ ቆይታ፣ «ሐይቅ ዳር ስሆን እረካለሁI አገሬ ውስጥ ከጓደኞቼና ቤተሰቦቼ ጋር ያለሁ ስለሚመስለኝ የደስታ ስሜት ይሰማኛል" በአውሮፓ፣ ብዙዎች መዝናኛዎች የሚገኙት ባሕር ዳርቻ ነው" ብቻ...» ካርለት ከሎ ሆራን በጎን ተመለከተችው“
«ኢ ህ» አላት እግሮቹን ወደፊት በመዘርጋት ሰውነቱን ለጥጦ" ካርለት የከሎ ሆራ ጠባይ ደንቋታል ግን አልከፋትም" በቀላሉ ከምትግባባቸው ሰዎች ይልቅ አስቸጋሪ ባሕርይ ያላቸውን ታከብራለች" ሁሉም ሰው ሊረዳው የሚችል ባሕርይ ያላቸው ሰዎች ለሷ አያረኳትም" እረቀቅ ያለ ባሕርይ ያላቸውን ግን አእምሮዋን
አስደንሳ መላ ፈጥራ፣ የተለያየ ስልት በመጠቀም እንደ ግል ሬዲዮና መከፈት መዝጋት እንደ መቻል
የምትረካበት ነገር የለም።
ለዚህም ካርለት «ዘመናችን የሚርጠው ልዩና ውስብስብ አስተሳሰብ ያላቸውን ነው" ምክንያቱም የነገው ፈጠራና ብሩህ
ሕልም ህላዊነት በመዳፋቸው መሃል ያለው ከእነዚህ ዓይነት ግራ
አጋቢ ባሕርይ ካላቸው ሰዎች ነው» ብላ ታምናለች።
ከሎ ቅንና ተባባሪ ሰው መሆኑን፣ ነገር ግን ይህን ባሕሪውን የሚገልጽ የቃላት ድርደራ ችሎታ የሚጎድለው መሆኑን ተገንዝባለች" ካርለት ከሎን የተለያዩ ነገሮችን እያወራች
እየጠየቀች የቱ እንደሚያስደስተው፣ የቱ አፍንጫውን እንደሚ
ያስነፋውና ጥንካሬውን ከደካማ ጎኑ ለመለየት ምርምሯን ስለ ቀጠለች
አንድ ወጥ በሆነው የሥውር ባሕርይው ዋሻ ለመግባት ትልቁ
የድንጋይ መዝጊያ ማንቀሳቀስ ጀምራለች።
«አዎ የከሎ ባሕርይ ራሱ መጠናት የሚገባው ነው" እሱን ለማጥናት ግን አስፈላጊውን ቁልፍ ማዘጋጀት አለብኝ» አለች
ካርለት፣ ከሻሸመኔ ከተማ ወጥታ የአርባ ምንጭን መንገድ ስትይዝ"
ከሻሸመኔ ትንሽ ራቅ ብለው የአስፋልቱ ጐዳና አልቆ ኮረኮንቹን መንገድ ሲጀምሩ ግን መኪናዋ እየተገጨች ስትንሰጠሰጥና ከፊት
ለፊቷ ያሉትን መኪናዎች ስታልፍና ከእሷ ተቃራኒ የሚያልፉት መኪናዎች የሚያነሡት አቧራ መኪናዋ ውስጥ እየገባ ማፈን
ሲጀምር፣ ካርለት መኪናዋን አቁማ፣ ጸጕሯን በመሸብለል፣ ቆብ
ደፋችበትና መኪናዋን በማንቀሳቀስ ከመሪው ጋር መታገል ጀመረች"
👍20🔥1
ካርለት፣ መኪናዋን በሰዓት ከሥልሳ እስከ ሰማንያ ኪሎ ሜትር በሚደርስ አማካኝ ፍጥነት እያሽከረhረች እንደተጓዙ ከፊት
ለፊታቸው አንድ እስከ አናቱ ድረስ የታረሰና የተለያዩ እፅዋት ያሉበት ተራራ ተመለከቱ" ከተራራው ግርጌ ራቅራቅ ያሉ
መንደሮች ሲኖሩ፣ በየመንገዱ አካባቢ ሙዝ፣ እንሰት፣ ጥድና ባሕር
ዛፍ ይታያል" ከመንደሮች ራስጌና ግርጌ እንዲሁም ግራና ቀኝ የበቆሎ፣ የጤፍ.አዝርእት ተመለከቱ" ካርለት የአካባቢው
ልምላሜና በኮርቻ ፈረስ በሶምሶማ ግልቢያ የምታያቸው ሰዎች
ስላስደነቋት «ኦ! ልምላሜ የተላበሰ ማራኪ ነው" ምን የሚባለው አካባቢ ነው?» ብላ ከሎን ጠየቀችው
«ወላይታ» አጭር መልስ መለሰላት።
«ወይታ» አለች መጥራቱ ከብዷት።
«ወላይታ”ወ.ላ.ይ..ታ» አላት ፊደሉን እየቆጠረ ከዚያም
ስለ ማኅበረሰቡ ቋንቋ ባህል ጠየቀችው ካርለት በከተማው ስታልፍ
እንደተለመደው አዋቂ ወንዶችና ሴቶች እጃቸውን አውለበለቡላት ሕፃናት፣ «ፈረንጅ» እያሉ ጨፈሩላት" መኪናዋን ስታቆም
ከበቧት፣ እጇን ለመያዝም ተሯሯጡ"
ካርለትና ከሎ ወላይታን ካለፉ በኋላ ምዕራብ አባያ ላይ በቅርጫት የተከመረ ፓፓያ፣ ገና ያልቀላ አረንጓዴ ሙዝ ከነመያዣው፣ ሎሚው ተደርድሮ ተመለከተች" በተለይ አርባ ምንጭ
ሊደርሱ ጥቂት ሲቀራቸው ባገኟት ላንቴ ከተማ ያዩት ሙዝ አንዱ ለሦስት የሚበቃ ሆኖ አገኘችው" መኪናዋን ስታቆም፣ «ሙዝ፣
ፓፓያ፣ ሎሚ» እያሉ የመኪናውን መስኮት ከበቡ።
ካርለት አንዱን ቁና ሙዝ ተቀብላ ዋጋውን ጠየቀች" አንድ ብር የሚሸጠውን ሁለት ብር አሏት፤ አንዱን ቅርጫት ፓፓያ ጠየቀች
ሦስት ብር አሏት" «አምላኬ!» አለች የነገሯት ዋጋ ትክክለኛ ስለ
መሆኑ ከሎን ጠይቃ ካረጋገጠች በኋላ።
በዓለም ላይ ተበልቶ ተጠጥቶ ከአንድ ዶላር በታች የሚጠየቅባት
አገር እሷ እስከምታውቀው ድረስ ኢትዮጵያ ብቻ ናት" ክምር ሙዝና ፓፓያ ዋጋቸው አንድ ዶላር እንኳ አይሞላም" ኢትዮጵያ
ውስጥ ተበልቶ፣ ተጠጥቶ የሚከፈለው አገሯ ለወንበር ተብሎ ከሚከፈለው ያነሰ ነው። አውሮፓ ውስጥ ትኩስ ፓፓያና ሙዝ
ዋጋቸው የዋዛ ስላልሆነ፣ ለማግኘት ከባድ ነው። እንዲያውም አንድ ጃፓናዊ ጓደኛዋ ጃፓን አገር ትኩስ ፓፓያ መብላት የሚችሉት
ሚሊየነሮች ናቸው ብሏታል" ይህን ስታስብ፤ «ኢትዮጵያ ውስጥ ፍራፍሬ ይሸጣል ከማለት ይልቅ፣ ይታደላል ቢባል እውነትነት ይኖረዋል» አለች"
ካርለትና ከሎ ወደ አርባ ምንጭ ጥቅጥቅ ባለው የግራር፣ የጥድ፣ የብርብራ ዛፍና ሌሎችም እፅዋትና በሰፊው የጥጥ እርሻ መካከል አልፈው ሲደርሱ አምስት መቶ ኪሎ ሜትር መጓዛቸውን የሚገልጽ
በነጭ ላይ ጥቁር የተጻፈበት የቆመ ድንጋይ ተመለከቱ። የአርባ
ምንጭ ከተማ የአባያንና ጫሞን ሐይቅ እግሩ ስር አድርጎ የተከተመ ከተማ ሲሆን መንገዶቹ አስፋልት ቢሆኑ ውበቱ ይጐላ ነበር።
ካርለትና ከሎ ከአዲስ አበባ አርባ ምንጭ አሥራ አንድ ሰዓት ተጕዘው ደረሱ" ከዚያም በከሎ መሪነት በቀለ ሞላ ሆቴል ሁለት
አልጋ ከያዙ በኋላ ካርለት ልብሷን ለማውለቅ እንኳ ሰንፋ ከነልብሷ ሻወር ቤት ገባች" ከሎ ሆራ ምናልባት መኪና ማሽከርከር ቢችል
ኖሮ እሷ የደከመችበትን ጒዞ ሳያርፍ ሦስቴ ሊያመላልስ የሚችል
ኃይል እንዳለው አምናለች"
ምሽት ላይ ካርለትና ከሎ ከሆቴሉ በስተጀርባ ካለው መዝናኛ ቦታ ቁጭ ብለው ከአርባ አራት ምንጭ በላይ አለው የአንበሳ መኖሪያ ነው የሚባለው ጥቅጥቅ ያለ የአበሻ ጥድ፣ ግራር፣ ዋንዛ
ሾላ፣ አጋምና ሌሎችን እፅዋት ይዞ ከወዲህ ተራራውን ተለጥፎ፣
ከወዲያ የኦሞ ሐይቅን ከጎንና ጎን ተመርኩዞ፣ ከርቀት ሰንሰለታማውን የጉጂ ተራራ ዘብ አቁሞ ሲታይ የተፈጥሮ ውበት የሚደነቅበት ሞዴል ሆኖ የጐብኚውን የተሰላቸ አእምሮ ያድሳል" ይሀን
የተፈጥሮ ውበት ሲያዩ እንኳን ካርለት ከሎም የእርካታ ስሜት አሳየ
የተፈጥሮ ውበት ሕሊናን አበረታችና ፈዋሽ ነዋ!
ካርለት ከሐይቆች ለሚነፍሰው ነፋስና ዓይኗ ለሚቃኘው ውበት
አእምሮዋን በርግዳ ከፍታ አካሏን ካዝናናች በኋላ ከሎን፣ «አንተ ቀዝቃዛ ቢራ እየተጎነጨህ ልትዝናና ትችላለህ" እኔ ግን ማረፍ
እፈልጋለሁ» በማለት ቀያይ ብር አስቀምጣለት ሄደች በእርግጥ ካርለት ከመኝታው ይልቅ መናፈሱንና ቀዝቃዛ ቢራውን መጎንጪት አሰኝቷት ነበር“ ይሁን እንጂ ከሎ በእሷ ላይ ያለውን ስሜት በትክክል
ማረጋገጥ አልቻለችም። ለነገሩ ጨዋታውን ለዓይነት ያህል ወስዳ ከሎን ማዝናናት ትችል ይሆናል፤ ፍርሃቷ ግን ለጥናቷ እንቅፋት መፍጠር ወይም እንዲፈጠር ማመቻቸት አትፈልግም። ከሉ ሆራም
ለማያገኘው ነገር ጕሮሮውን በማጮህ የስሜት ችግር ውስጥ እንዲገባ
ስላልፈለገች ወደ መኝታ ክፍሏ ሄደች።
ከሎም ያንን ስብቅብቅ ወገብና ዳንኪራ ረጋጭ ዳሌ የማግኘት
ሕልሙ እንደማይሳካ በማሰብ፣ «ዳሚት» እያለ ሲቆዝም ቆየና ቢራውን ደጋግሞ ጨልጦ፣ ወደ መኝታ ክፍሉ ሄደ"
ማክሰኞ ዕለት በእንቅስቃሴ አልባው የጫሞ ሐይቅ ዳር ጥርሱን ያገጠጠ አዞ ሲንሳፈፍ፣ ከላይ ጥፍሩን ያሾለ አሞራ ዓሣ ለማጥመድ ሲያሽቆለቁል፣ በተራራው አናት የፈነጠቀው የፀሐይ ብርሃን ውጋገን
ከውኃው ነጸብራቅ ጋር ተዋሕዶ የዓሣ ሽታ፣ የእፅዋት መዓዛ፣
ከአዕዋፍ ዝማሬ ጋር ቅንብሩ እንደተዋጣ ሙዚቃ መንፈስን በሚሰርቅበት ወቅት «ስቴሽን ዋገን» መኪና ጥግጥጉን የከብት ሽንት በመሰለው ጠመዝማዛ መንገድ እየተሹለከለከ ከነፈ።
ዘመን አመጣሹን የግብርና ዘዴ በተፈጥሯዊ ጥበብ ተጠቅሞ የአፈርን የእሸሻለሁ አትሸሽም የእርከን ሥራ ውጤት ካርለት ስታይ መሰጣት። ስለ ኮንሶ የእርከን ሥራ ባህልና የረጅም ዘመን የመጠቀም ችሎታቸው መጻሕፍት አንብባለች" ተራራማው አካባቢ ላይ የሚኖረው የኮንሶ ሕዝብ በእርከን ሥራ ዘዴ አፈርን በመንከባከብ የረጅም
ጊዜ ተጠቃሚ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ከዚህም በተጨማሪ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የሸማ ሥራ ጥበብ የተጀመረበት
መሆኑን ተረድታለች።
በቆሎ፣ ማሽላ፣ ለመድኃኒትና ለውኃ ማጣሪያ ለክልሉ ሕዝብ
የሚያገለግለው የአለኮ ዛፍና ሌሎችም አዝርዕቶች፣ ችፍግ ብለው
አዝመራውንና እፅዋቱን ሊያሳይ በሚችል መንገድ ቋጥኝ ጥግ የተሠራው መንደር እንግዶችን እይታቸውን ቶሎ መንቀል አያስችላቸውም።
አልፎ አልፎም ከመንገዱ ግራና ቀኝ ከእንጨት የተሠሩ የሰው ምስሎች ከመቃብር ላይ ተተክለው የሚታዩ ሲሆን ይህም ዘመን አመጣሹ የመቃብር ሐውልት ከመምጣቱ በፊት ኮንሶዎች የእንጨት
ምስል ቀርፀው መትከላቸው ቀድመው የሠለጠኑ እንደነበሩ ዓይነተኛ
ምስክር ሲሆን፥ ከዚህም በተጨማሪ ሥራ ወዳድነትና ጥረት ለኮንሶ ሕዝብ እንደ ቋንቋው ከልጅነቱ ጀምሮ የሚማረው ነው።
ካርለት ኮንሶንና አካባቢውን በቀስታና በአፅንኦት እየቃኘች ከተማው ደረሱ ካርለትና ከሎ ከመንገዱ በስተቀኝና በስተግራ ፊት
ለፊት ካሉት ብቸኛ ምግብ ቤቶች በግራ በኩል ወዳለው ለምሳ ገቡ።
ካርለት አርባ ምንጭ ሆቴል በተለይ ጫካ ውስጥ ያሉት የመኝታ ክፍሎችና የጽዳት ሁኔታቸው አሳቋታል። የምግብ ዝርዝሩም አነስተኛና የለመደችው ባለመሆኑ ግራ ተጋብታ ነበር የኮንሶው የምግብ ዝርዝር ግን ለእሷ እንግዳ ነው። አማራጭ ብሎ ነገር የለውም ያለው አንድ
ለፊታቸው አንድ እስከ አናቱ ድረስ የታረሰና የተለያዩ እፅዋት ያሉበት ተራራ ተመለከቱ" ከተራራው ግርጌ ራቅራቅ ያሉ
መንደሮች ሲኖሩ፣ በየመንገዱ አካባቢ ሙዝ፣ እንሰት፣ ጥድና ባሕር
ዛፍ ይታያል" ከመንደሮች ራስጌና ግርጌ እንዲሁም ግራና ቀኝ የበቆሎ፣ የጤፍ.አዝርእት ተመለከቱ" ካርለት የአካባቢው
ልምላሜና በኮርቻ ፈረስ በሶምሶማ ግልቢያ የምታያቸው ሰዎች
ስላስደነቋት «ኦ! ልምላሜ የተላበሰ ማራኪ ነው" ምን የሚባለው አካባቢ ነው?» ብላ ከሎን ጠየቀችው
«ወላይታ» አጭር መልስ መለሰላት።
«ወይታ» አለች መጥራቱ ከብዷት።
«ወላይታ”ወ.ላ.ይ..ታ» አላት ፊደሉን እየቆጠረ ከዚያም
ስለ ማኅበረሰቡ ቋንቋ ባህል ጠየቀችው ካርለት በከተማው ስታልፍ
እንደተለመደው አዋቂ ወንዶችና ሴቶች እጃቸውን አውለበለቡላት ሕፃናት፣ «ፈረንጅ» እያሉ ጨፈሩላት" መኪናዋን ስታቆም
ከበቧት፣ እጇን ለመያዝም ተሯሯጡ"
ካርለትና ከሎ ወላይታን ካለፉ በኋላ ምዕራብ አባያ ላይ በቅርጫት የተከመረ ፓፓያ፣ ገና ያልቀላ አረንጓዴ ሙዝ ከነመያዣው፣ ሎሚው ተደርድሮ ተመለከተች" በተለይ አርባ ምንጭ
ሊደርሱ ጥቂት ሲቀራቸው ባገኟት ላንቴ ከተማ ያዩት ሙዝ አንዱ ለሦስት የሚበቃ ሆኖ አገኘችው" መኪናዋን ስታቆም፣ «ሙዝ፣
ፓፓያ፣ ሎሚ» እያሉ የመኪናውን መስኮት ከበቡ።
ካርለት አንዱን ቁና ሙዝ ተቀብላ ዋጋውን ጠየቀች" አንድ ብር የሚሸጠውን ሁለት ብር አሏት፤ አንዱን ቅርጫት ፓፓያ ጠየቀች
ሦስት ብር አሏት" «አምላኬ!» አለች የነገሯት ዋጋ ትክክለኛ ስለ
መሆኑ ከሎን ጠይቃ ካረጋገጠች በኋላ።
በዓለም ላይ ተበልቶ ተጠጥቶ ከአንድ ዶላር በታች የሚጠየቅባት
አገር እሷ እስከምታውቀው ድረስ ኢትዮጵያ ብቻ ናት" ክምር ሙዝና ፓፓያ ዋጋቸው አንድ ዶላር እንኳ አይሞላም" ኢትዮጵያ
ውስጥ ተበልቶ፣ ተጠጥቶ የሚከፈለው አገሯ ለወንበር ተብሎ ከሚከፈለው ያነሰ ነው። አውሮፓ ውስጥ ትኩስ ፓፓያና ሙዝ
ዋጋቸው የዋዛ ስላልሆነ፣ ለማግኘት ከባድ ነው። እንዲያውም አንድ ጃፓናዊ ጓደኛዋ ጃፓን አገር ትኩስ ፓፓያ መብላት የሚችሉት
ሚሊየነሮች ናቸው ብሏታል" ይህን ስታስብ፤ «ኢትዮጵያ ውስጥ ፍራፍሬ ይሸጣል ከማለት ይልቅ፣ ይታደላል ቢባል እውነትነት ይኖረዋል» አለች"
ካርለትና ከሎ ወደ አርባ ምንጭ ጥቅጥቅ ባለው የግራር፣ የጥድ፣ የብርብራ ዛፍና ሌሎችም እፅዋትና በሰፊው የጥጥ እርሻ መካከል አልፈው ሲደርሱ አምስት መቶ ኪሎ ሜትር መጓዛቸውን የሚገልጽ
በነጭ ላይ ጥቁር የተጻፈበት የቆመ ድንጋይ ተመለከቱ። የአርባ
ምንጭ ከተማ የአባያንና ጫሞን ሐይቅ እግሩ ስር አድርጎ የተከተመ ከተማ ሲሆን መንገዶቹ አስፋልት ቢሆኑ ውበቱ ይጐላ ነበር።
ካርለትና ከሎ ከአዲስ አበባ አርባ ምንጭ አሥራ አንድ ሰዓት ተጕዘው ደረሱ" ከዚያም በከሎ መሪነት በቀለ ሞላ ሆቴል ሁለት
አልጋ ከያዙ በኋላ ካርለት ልብሷን ለማውለቅ እንኳ ሰንፋ ከነልብሷ ሻወር ቤት ገባች" ከሎ ሆራ ምናልባት መኪና ማሽከርከር ቢችል
ኖሮ እሷ የደከመችበትን ጒዞ ሳያርፍ ሦስቴ ሊያመላልስ የሚችል
ኃይል እንዳለው አምናለች"
ምሽት ላይ ካርለትና ከሎ ከሆቴሉ በስተጀርባ ካለው መዝናኛ ቦታ ቁጭ ብለው ከአርባ አራት ምንጭ በላይ አለው የአንበሳ መኖሪያ ነው የሚባለው ጥቅጥቅ ያለ የአበሻ ጥድ፣ ግራር፣ ዋንዛ
ሾላ፣ አጋምና ሌሎችን እፅዋት ይዞ ከወዲህ ተራራውን ተለጥፎ፣
ከወዲያ የኦሞ ሐይቅን ከጎንና ጎን ተመርኩዞ፣ ከርቀት ሰንሰለታማውን የጉጂ ተራራ ዘብ አቁሞ ሲታይ የተፈጥሮ ውበት የሚደነቅበት ሞዴል ሆኖ የጐብኚውን የተሰላቸ አእምሮ ያድሳል" ይሀን
የተፈጥሮ ውበት ሲያዩ እንኳን ካርለት ከሎም የእርካታ ስሜት አሳየ
የተፈጥሮ ውበት ሕሊናን አበረታችና ፈዋሽ ነዋ!
ካርለት ከሐይቆች ለሚነፍሰው ነፋስና ዓይኗ ለሚቃኘው ውበት
አእምሮዋን በርግዳ ከፍታ አካሏን ካዝናናች በኋላ ከሎን፣ «አንተ ቀዝቃዛ ቢራ እየተጎነጨህ ልትዝናና ትችላለህ" እኔ ግን ማረፍ
እፈልጋለሁ» በማለት ቀያይ ብር አስቀምጣለት ሄደች በእርግጥ ካርለት ከመኝታው ይልቅ መናፈሱንና ቀዝቃዛ ቢራውን መጎንጪት አሰኝቷት ነበር“ ይሁን እንጂ ከሎ በእሷ ላይ ያለውን ስሜት በትክክል
ማረጋገጥ አልቻለችም። ለነገሩ ጨዋታውን ለዓይነት ያህል ወስዳ ከሎን ማዝናናት ትችል ይሆናል፤ ፍርሃቷ ግን ለጥናቷ እንቅፋት መፍጠር ወይም እንዲፈጠር ማመቻቸት አትፈልግም። ከሉ ሆራም
ለማያገኘው ነገር ጕሮሮውን በማጮህ የስሜት ችግር ውስጥ እንዲገባ
ስላልፈለገች ወደ መኝታ ክፍሏ ሄደች።
ከሎም ያንን ስብቅብቅ ወገብና ዳንኪራ ረጋጭ ዳሌ የማግኘት
ሕልሙ እንደማይሳካ በማሰብ፣ «ዳሚት» እያለ ሲቆዝም ቆየና ቢራውን ደጋግሞ ጨልጦ፣ ወደ መኝታ ክፍሉ ሄደ"
ማክሰኞ ዕለት በእንቅስቃሴ አልባው የጫሞ ሐይቅ ዳር ጥርሱን ያገጠጠ አዞ ሲንሳፈፍ፣ ከላይ ጥፍሩን ያሾለ አሞራ ዓሣ ለማጥመድ ሲያሽቆለቁል፣ በተራራው አናት የፈነጠቀው የፀሐይ ብርሃን ውጋገን
ከውኃው ነጸብራቅ ጋር ተዋሕዶ የዓሣ ሽታ፣ የእፅዋት መዓዛ፣
ከአዕዋፍ ዝማሬ ጋር ቅንብሩ እንደተዋጣ ሙዚቃ መንፈስን በሚሰርቅበት ወቅት «ስቴሽን ዋገን» መኪና ጥግጥጉን የከብት ሽንት በመሰለው ጠመዝማዛ መንገድ እየተሹለከለከ ከነፈ።
ዘመን አመጣሹን የግብርና ዘዴ በተፈጥሯዊ ጥበብ ተጠቅሞ የአፈርን የእሸሻለሁ አትሸሽም የእርከን ሥራ ውጤት ካርለት ስታይ መሰጣት። ስለ ኮንሶ የእርከን ሥራ ባህልና የረጅም ዘመን የመጠቀም ችሎታቸው መጻሕፍት አንብባለች" ተራራማው አካባቢ ላይ የሚኖረው የኮንሶ ሕዝብ በእርከን ሥራ ዘዴ አፈርን በመንከባከብ የረጅም
ጊዜ ተጠቃሚ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ከዚህም በተጨማሪ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የሸማ ሥራ ጥበብ የተጀመረበት
መሆኑን ተረድታለች።
በቆሎ፣ ማሽላ፣ ለመድኃኒትና ለውኃ ማጣሪያ ለክልሉ ሕዝብ
የሚያገለግለው የአለኮ ዛፍና ሌሎችም አዝርዕቶች፣ ችፍግ ብለው
አዝመራውንና እፅዋቱን ሊያሳይ በሚችል መንገድ ቋጥኝ ጥግ የተሠራው መንደር እንግዶችን እይታቸውን ቶሎ መንቀል አያስችላቸውም።
አልፎ አልፎም ከመንገዱ ግራና ቀኝ ከእንጨት የተሠሩ የሰው ምስሎች ከመቃብር ላይ ተተክለው የሚታዩ ሲሆን ይህም ዘመን አመጣሹ የመቃብር ሐውልት ከመምጣቱ በፊት ኮንሶዎች የእንጨት
ምስል ቀርፀው መትከላቸው ቀድመው የሠለጠኑ እንደነበሩ ዓይነተኛ
ምስክር ሲሆን፥ ከዚህም በተጨማሪ ሥራ ወዳድነትና ጥረት ለኮንሶ ሕዝብ እንደ ቋንቋው ከልጅነቱ ጀምሮ የሚማረው ነው።
ካርለት ኮንሶንና አካባቢውን በቀስታና በአፅንኦት እየቃኘች ከተማው ደረሱ ካርለትና ከሎ ከመንገዱ በስተቀኝና በስተግራ ፊት
ለፊት ካሉት ብቸኛ ምግብ ቤቶች በግራ በኩል ወዳለው ለምሳ ገቡ።
ካርለት አርባ ምንጭ ሆቴል በተለይ ጫካ ውስጥ ያሉት የመኝታ ክፍሎችና የጽዳት ሁኔታቸው አሳቋታል። የምግብ ዝርዝሩም አነስተኛና የለመደችው ባለመሆኑ ግራ ተጋብታ ነበር የኮንሶው የምግብ ዝርዝር ግን ለእሷ እንግዳ ነው። አማራጭ ብሎ ነገር የለውም ያለው አንድ
👍16
ዓይነት ምግብ ሲሆን እሱም ሚስቶ ብቻ ነው አበቃ
ካርለት፣ «አምላኬ!» ብላ ተደንቃ ለመብላት ተጣጣረች" ሆኖም
ግን ከጉሮሮዋ አልወርድልሽ አላት ስለዚህ ባልቀዘቀዘ ኮካ ወደ ውስጥ
ለማስገባት ሞከረች ከሎ ግን ደስ ብሎት ጥርግ አድርጎ በላ ከከተማው ወጥተው አቀበት፣ ቁልቁለቱን ወርደው ሲጓዙ
አሁንም ካርለት በተፈጥሮ ውበት እየተደነቀች ከመኪና መሪ ጋር ስትታገል ቆየችና፣ «ከሎ ይህች ሀገር ልምላሜ፣ ውበትና ጥሬ ሀብቱ ሳያንሳት፣ ቀድማ ነቅታ ምነው ተመልሳ ተኛች" የእንቅልፍ
(መድኃኒት) ማን አዋጣት? የውስጥ ይሆን የውጭ ሐኪም?» አለችው ምስጥ ብላ ከሎ በሳንባው የታመቀውን አየር ወደ ውጭ እያንቦለቦለ፣ ፊቱን ቅጭም አድርጎ፣ «ሁለቱም ሁለቱም ሐኪም
ነው ካርለት» አላት" መኪናዋም አቀበቱን ለመውጣት ድምጽዋን
ቀይራ ማቃሰት ጀመረች" በመሪው በኩል ያለው ጎማ ግን ፍትጊያውን መቋቋም ስላቃተው ተነፈሰ" ከዚያም «ስኮርት» ጎማ ቀይረው ጥቂት እንደሄዱ ደግሞ በጭቃ ተያዙ"
ሰማዩ ጎሽቶ፣ ብርቅርቅታው እንደ ርችት እየተንጣጣ፣ ዶፍ ዝናቡ መዝነብ በመጀመሩ እንኳን መኪናዋን ከተያዘችበት ጭቃ ለማውጣት መሞhር ቀርቶ በሩን ለመhፈት እንኳን ተሳናቸው"
ዝናቡ አካባቢውን ሲወቃው ቆይቶ ቁልቁል ወደ በረሃው
በመውረዱ እየቆየ እየቆየ አካባቢው ሲገልጥ ወርደው መኪናውን ሲመለከቱ የመኪናው ደረትና መሬቱ ተቃቅፈዋል" መኪናውን
ለማንቀሳቀስ መሬቱ መቆፈር፣ ድንጋይ መጨመርና በሰው ኃይል
ወደ ላይ ማንሣት ያስፈልግ ስለነበር ካርለትና ከሎ ለሁለት ሊወጡት
የማይችሉት ችግር በመሆኑ አድረው የአካባቢውን ሰው ትብብር ለመጠየቅ ተስማምተው ድንኳኖቻቸውን መንገድ ዳር ተከሉ"።
💫ይቀጥላል💫
ካርለት፣ «አምላኬ!» ብላ ተደንቃ ለመብላት ተጣጣረች" ሆኖም
ግን ከጉሮሮዋ አልወርድልሽ አላት ስለዚህ ባልቀዘቀዘ ኮካ ወደ ውስጥ
ለማስገባት ሞከረች ከሎ ግን ደስ ብሎት ጥርግ አድርጎ በላ ከከተማው ወጥተው አቀበት፣ ቁልቁለቱን ወርደው ሲጓዙ
አሁንም ካርለት በተፈጥሮ ውበት እየተደነቀች ከመኪና መሪ ጋር ስትታገል ቆየችና፣ «ከሎ ይህች ሀገር ልምላሜ፣ ውበትና ጥሬ ሀብቱ ሳያንሳት፣ ቀድማ ነቅታ ምነው ተመልሳ ተኛች" የእንቅልፍ
(መድኃኒት) ማን አዋጣት? የውስጥ ይሆን የውጭ ሐኪም?» አለችው ምስጥ ብላ ከሎ በሳንባው የታመቀውን አየር ወደ ውጭ እያንቦለቦለ፣ ፊቱን ቅጭም አድርጎ፣ «ሁለቱም ሁለቱም ሐኪም
ነው ካርለት» አላት" መኪናዋም አቀበቱን ለመውጣት ድምጽዋን
ቀይራ ማቃሰት ጀመረች" በመሪው በኩል ያለው ጎማ ግን ፍትጊያውን መቋቋም ስላቃተው ተነፈሰ" ከዚያም «ስኮርት» ጎማ ቀይረው ጥቂት እንደሄዱ ደግሞ በጭቃ ተያዙ"
ሰማዩ ጎሽቶ፣ ብርቅርቅታው እንደ ርችት እየተንጣጣ፣ ዶፍ ዝናቡ መዝነብ በመጀመሩ እንኳን መኪናዋን ከተያዘችበት ጭቃ ለማውጣት መሞhር ቀርቶ በሩን ለመhፈት እንኳን ተሳናቸው"
ዝናቡ አካባቢውን ሲወቃው ቆይቶ ቁልቁል ወደ በረሃው
በመውረዱ እየቆየ እየቆየ አካባቢው ሲገልጥ ወርደው መኪናውን ሲመለከቱ የመኪናው ደረትና መሬቱ ተቃቅፈዋል" መኪናውን
ለማንቀሳቀስ መሬቱ መቆፈር፣ ድንጋይ መጨመርና በሰው ኃይል
ወደ ላይ ማንሣት ያስፈልግ ስለነበር ካርለትና ከሎ ለሁለት ሊወጡት
የማይችሉት ችግር በመሆኑ አድረው የአካባቢውን ሰው ትብብር ለመጠየቅ ተስማምተው ድንኳኖቻቸውን መንገድ ዳር ተከሉ"።
💫ይቀጥላል💫
👍14