አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ስትፈጠፈጥ።” የሚል ሆድ የባሰው መካሪ… ባይሰማም ኡኡ ብሎ የሚጮህ… ቃል አንድ ቀን ሥጋ መልበሱ አይቀር። ክፉ ስጋ ለብሶ ፍልጥ ከማንሳቱ በፊት በዘመነ ፈሊጥ ቃሉን የማያቀሉ ብፁዓን ናቸው።

በዕርግጥ ይሄንን ስል ሊመክረኝ የሞከረ ትሁት ወዳጅ ነበረኝ። ምን አልኩት ? ሂድ እባክህ ..
አንተን ብሎ መካሪ ! አንተ ስለሚስቴ ፀጉር የምታውቀው አንድ ነገር የለህም ! እንደውም ራስህ በየጓዳህ የምታለቅስበትን እውነት ነው እዚህ በአደባባይ ፋራ ላለመባል የምትቃወመው! እኔ ለሚስቴ ታማኝ ነኝ ! በዚህም እኮራለሁ ! ለፌቨን ታማኝ ነኝ። እንኳን ከትዳሬ ውጭ ሌላ ሴት ልነካ፣ ለሚስቴ የምጠቀመውን የአድናቆት ቃል ብሞት ለሌላ ሴት አልጠቀምም። ስለማያምረኝ አልነበረም። አምናኝ እኔጋ የሆነች ሚስቴን ማክበር ራሴን ማክበር መሆኑን ስለማውቅ ነው። ደግሞም ደስተኛ ነበርኩ።

ፍፁም ደስተኛ።”

እያንዳንዷ ቃሌ በሚስቴ ፊት ሞገስ እንዲኖራት እፈልጋለሁ። በትዳር ውስጥ በጋራ ጉዳይ ላይ የግል አመለካከት የሚባል ነገር የለም። በሚስቴ ሰውነት ላይ ስለምትደረግ እያንዳንዷ ነገር ያገባኛል። ምክንያቱም “አንድ አካል አንድ አምሳል ሆናችኋል” ብለው ያጋቡንን ቄስ ተላልፌ ሲመቸን አንድ ላይ ሳይመቸን በየግላችን እንድንዳክር አልፈቅድም። በምንም ነገር 'ስለኔ አይመለከትህም የምትል ሴት ወይ በሽተኛ አልያም የትዳር ኃላፊነት ያልገባት መደዴ ሴት ናት። መከባበር በሌለበት ውበት
ገደል ይግባ። የስጋ ክምራ ስላማለለህ ዘለህ አልጋ ላይ ትወድቃለህ፣ ከአልጋህ ስትወርድ ምድርህ እሳት ለብሶ ይጠብቅሃል። ፍቺ በማሕበረሰብህ ጸያፍ ነገር ነውና እያስመሰልክ ትኖራለህ። ማስመሰል ደግሞ ያንገሸግሻል። ራስህን በእሳት ልምጭ መግረፍ በለው። በዚህ ዓይነቱ ኑሮ እንኳን ሚስት ተብዬዋ ያጠለቀችልህ ቀለበት፣ ቀለበት የተጠለቀበት ጣትህም ይቀፍሃል።”

“ሚስቱ ስለእርሱ ሕይወት የት ድረስ እንደሚያገባትና የት ድረስ የእርሱ ጉዳይ እንደማይመለከታት
መስመር የሚያሰምር ወንድም ድድብና ከነጓዙ የሰፈረበት ደነዝ ይመስለኛል።ይህን የምለው ወንድ
በመገሰፅ ሚዛናዊ ለመሆን አይደለም፤ የነፍስ ሐቄ፣ የኖርኩበትም መንገድ ስለነበር እንጂ። ይጠየቅ ጎረቤት። ይጠየቅ ቤተሰቤ። ኧረ ራሷ ፌቨን ትጠየቅ። ምርር ቢልም ተገደን መዋጥ ያለብን እውነት ይሄ ነው። ባልም ለሚስቱ፣ ሚስትም ለባሏ ተገዥ ናቸው። ውልፍት የለም። አንዱ ካለአንዱ ፍላጎት ስንዝር ሊራመዱ አይገባም። ሚስቴ እኔ ላይ በዚህ ምድር ካለ ማንኛውም ሰው በላይ ኃላፊ ነች። እኔ የርሷ ነኝ፣ ርሷም የእኔ ናት። ፋሽንም በለው ዘመን አመጣሽ ቅራቅንቦ በጎጆዬ ውስጥ የጥፍር ቁራጭ የሚያክል ቦታ እንዲኖራቸው አልፈልግም። ለምን መሰለህ ..ከሦስቱ ጉልቻ አንዱም ከውጭ አይመጣም፤ አንተ፣ ሚስትህና ፍቅር ብቻ ናችሁኮ ጉልቾቹ…” መካሪዬን በደም ፍላት ደንፍቼበት አመንኩበት ባልኩት ሐቅ አከላፍቼው አጠገቤ ድርሽ እንዳይል አባረርኩት።

ምን ላድርግ …. ሳሎን የተቀመጠ ስልኩ ሲጠራ ሚስቱ እንዳታነሳበት በአፉ እስኪደፋ ከሻወር ወደ ሳሎን የሚሮጥ ወንድ ልምከርህ ሲለኝ ምን ላድርግ ታዲያ። መተዋወቃችንኮ ነው ችግሩ። ሐቅ መቼስ ለራስ ነው ሰላም የሚሰጠው። እኔ እንዳይሆን የምፈልገውን ነገርም ሚስቴ ከእኔ ፍላጎት ውጭ
ልታደርግ አንዳች ስልጣን የላትም። የራሴ የምትለው ሰውነት የላትም። የዘመናችን በሽተኛ ሴታዊ አምባገነንነት፣ በሽተኛው ፌሚኒዝም' እሳቤ ውስጥ ገብተው የተነከሩ ለፋፊዎችን በአማርኛ መስማት ከትርጉሙ ሳይሆን ከመንፈሱ አቀባበል የማይነቀል ደዌ ሴቶቻችን ልብ ውስጥ ዘራ። እነሱም ያሰቡትን ( ነፃነት ላያገኙ እኛም ካንዷ ወደ ሌላዋ ያደግንበትን የወንድነት ክብር ፍለጋ ስንዘል ዘመን ጣጥሎን
እብስ ! የሴት ልጅ ክብር በፍቅር እንጂ በትጥቅ ትግልም በአደባባይ ጩኸትም አይመጣም !! በቤቱ ሚስቱ የገፋችው፣ ፍቅረኛው ያቀለለችው ወንድ ሺ ሕግ ፣ሚሊየን መመሪያ ቢወጣ ሴትን ያከብራል ማለት ዘበት ነው።

አባትና እናቱ ሲደባደቡና ባለመከባበር አፍ ሲከፈቱ እያየ ያደገ ሕፃን ባባቱ ሲወጣ እያዩ፣ ልጅ የፍቅር ገመድ ነው ይሉናል። በጥላቻና በመናናቅ ትዳር ውስጥ የበቀለ ሕፃን የፍቅር ሳይሆን የማሕበረሰቡን ሕግና ባሕል ማነቂያ ገመድ ነው ! ብዙዎቹን 'ዘመናዊነት' ፍዳቸውን የሚያበላቸውን ሴቶች ታዘብ
እስቲ ፤ መነሻቸው ፍቅሩን አሟጥጦ እየተቋሰለ የኖረ ግድ የለሽ ቤተሰብ ነው። ካልተፋቀርን ምን አወላለደን! ልጅ አሻንጉሊት አይደለም !! ቃላችንን ማፅናት ሲያቅተን፣ ሥጋ ለበስ ሐውልት ቤታችን ውስጥ ተክለንልና መልክ ይዳዳናል! “ልጅ ወለድን” ብለን አንመፃደቅ። በልጆቻችን እናት ካልተደሰትን የልጆቻችንን ግማሽ ክፍል አንወደውም ማለት ነው። እናቶቹም ቢሆኑ፣ “ለልጄ ስል እንዲህ ሆንኩ፣ ለልጄ ስል ተፈለጥኩ ተቆረጥኩ…”፤ እስቲ መጀመሪያ ለእኛ ለባሎቻቸው ሲሉ ይፈለጡ ይቆረጡ።የልጅሽ ግማሽ አካል እኛ ባሎች አይደለንም እንዴ ?! እነዚህ ኮተታም ዘፈኖችና ፊልሞች በቀጥታም በተዘዋዋሪም የወንድን ልክስክስነት ለሴቶቻችን ሲሰብኩ፣ “ታዲያ ለማን ብለሽ ነው የምትታመኝው”
እያሉ ለመደዴነት ሚስታችንን፣ እህታችንን እያዘጋጇት መሆኑን ዘግይቶ ነው የሚገባን።

እና ሚስቴ ካለፍቃዴ ፀጉሯን ተቆረጠች ስል፣ 'መብቷ ነው ቅብርጥስ' የሚለኝ መብዛቱ መልሶ እኔኑ ይገርመኛል። ትዳርም ይሁን ፍቅር ለወደዱት ሁሉን ነገር መስጠት ነው። ግማሽ መሰጠት የሚባል ነገር የለም። እዚህ አዲስ አበባ ብልጣብልጥ ነፍሶች ፍቅርን እንደሚሸቅጡት ዓይነት ማለቴ ነው።እንዳሻኝ እዘልላለሁ ማለት የፈለገ ጓዙን ጠቅልሎ እዛው ተራ ዝላዩ ላይ !! ሲጀመርም ጭብጨባው አምሮት እንጂ እንዲህ ዓይነቱ አጋር የትዳር ወኔው የለውም !! ልክ በመንፈሳዊው ዓለም፣ “አንድም
ከእግዜር አንድም ከሰይጣን” እንደሚባለው በትዳርም አንድ እግርን ትዳር ውስጥ ሌላኛውን አጉል ምኞት ውስጥ ማቆም የለም!! ጥቅልል ብሎ መሰጠት ካልሆነ ጓዝን ጠቅልሎ ወደ መሄጃው !! ከተልካሻ
አብሮነት ከጠነዛና ከደነዘዘ የሁለትዮሽ ስብሰባ ብቸኝነት በስንት ጣዕሙ።

በዚህ ሆድ በባሰው ለዛ ቢስ ጊዜ ጋብቻን የልጅ ማሽን አድርገው የሚመለከቱ ወላጆች ክፉኛ
ተበራክተዋል። ይሄ ነገር ይቆጨኛል (ሆድ እንደባሰኝ ላውራው)። የፍቅር ሰንሰለት ያላቆራኘው ልባቸውን በመውለድ ሊያጣምሩ የሚደክሙ ! ቃል ነው ማሰሪያው ልጅ አይደለም ! ቃል ነው ስጋ ለብሶ ልጅ የሚሆነው! አብርሽ ውለዱ ልጅ ቢኖር እንዲህ በትንሽበ ትልቁ አትጋጩም ይሉኛል ... !! እንኳን ካለፍቃዴ ፀጉሯን ተቆርጣ ... የአንዲት በየቤቱ መዞርን ትዳር ያደረገች ሴት ምክር ሰምታ ይቅርና … ሳስነጥስ ይማርህ አላለችኝም ብዬ መፍታት እችላለሁ !! ልጅም ምንም አያግደኝም !
“ዋናው ያልበጀ ቅራሪው ሰው ፈጀ”
ሚስቴ ካለፍቃዴ ፀጉሯን ስለተቆረጠች እፈታታለሁ ...

እንኳን ፀጉሯን መቆረጥ እኔ በማልወደው “ስታይል” ማበጠርም እንደሌለባት የጉልበት ሕግ ሳይሆን የአብሮነትና የመተሳሰብ መርህ ሊያስገድዳት ይገባል ! ይህ ካልገባት ሚስቴ ደንዝዛለች፣ የሆነ የማስተዋል ችሎታዋ ተወስዷል !መተሳሰብን እና ፍቅርን ችላ ከማለት ሕግን ችላ ብትል ይሻልሃል! 'መብቴ ነው' ይሉት ጥራዝ ነጠቅ እንቧ ከረዩ ሕጋዊ ቢሆንም ከሰብዓዊ ጥላቻ ግን አያድንም። ህግ ኑሮህን ከእንከን ይከላከላል እንጅ ራሱ ኑሮ አይሆን ። የአንድ ፍቅረኛ ትልቁ ብቃት መርታት ሳይሆን
ያፈቀረውን ሰው በፍቅር መርታት መቻሉ ላይ ነው።...

ይቀጥላል
👍28👏3👎1
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_አራት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....እኔ ፓሪስ ሄጀ ቅናት ውስጥ ስንፈላሰስ ኤክስ ውስጥ ምን ምን
ተደረገ? ከባህራም፣ ከተካና ከኒኮል የሰማሁትን ሳገጣጥመው እንደ እሚከተለው ሆነ፡-.

አንድ ማክሰኞ ከሰኣት በኋላ (ኒኮል ከፋሺስቶቹ ተደብቃ
ሰንብታ ከተመለሰች በኋላ) ባህራም የሚሰራበት ትምህርት ቤት ዲሬክተር ቢሮው አስገባውና ከስራዎ ላሰናብትዎ ነው» አለው።
ባህራም «ምነው?» ቢለው “በስራዎ በጣም ተደስቼ ነበር፤ ግን የጋርደን ከተማ የፖሊስ ሹም እንዳሰናብትዎ አዘዘኝ» አለው

«እዚህ ውስጥ የፖሊስ ሹም ምን አገባው?» አለ ባህራም

«አዩ፣ እርስዎ የውጭ አገር ዜጋ እንደመሆንዎ መጠን፣ እዚህ
አገር ስራ ለመያዝ ልዩ ፈቃድ ያስፈልግዎታል። እስካሁን ያለ
ፈቃድ ወረቀት ስለስሩ እርስዎም እኔም ልንቀጣ እንችል ነበር፡፡ ግን
የፖሊስ ሹሙ ጓደኛዬ ነው፡፡

የስራ ፈቃድ እንደሌለኝ እንዴት አወቀ?» አለ ባህራም

ሰው ነገረው:: ይመስለኛል፣ ኤክስ ውስጥ ጠላቶች አሉዎት።»
ባህራም ገባው። ፋሽስቶቹ መሆን አለባቸው

«እሺ ደመወዜን ይስጡኝ አለ። የሁለት ወር ከሶስት ሳምንት
ደመወዝ አለው። ዲሬክተሩ ገንዘቡን ከቢሮው ጠረጴዛ ኪስ አውጥቶ አቀበለው። ባህራም ገንዘቡን ቆጠረ። የተዋዋሉት ገንዘብ ሲሶ ነው።
«ሌላውስ?» አለ ባህራም
ዲሬክተሩ ከጠረጴዛው ኋላ እንደተቀመጠ፣ ቅዝቅዝ ባለ ክፉ
ድምፅ
«የምን ሌላ?» አለው
«ይሄ ሙሉ ደመወዜ አይደለም፡፡ አንድ ሶስተኛው ነው::
«ማን ነው ያለው? ደመወዝህን ሰጥቼሀለሁ፡፡ ከፈለግክ ውሰደው፣
ካልፈለግክ ተወው:: ድሮ አልጄርያ ሳለሁ አረቦቹን ከዚህ ባነሰ
ደመወዝ ነበር የምናሰራችሁ»
ባህራም ረጋ ባለ ድምፅ አረቦቹን ቅኝ ግዛት ስላደረጋችኋቸው
በካልቾ ብለው ካገራቸው አስወጧችሁ፡፡ የሆነ ሆኖ፣ እኔ አረብ አይደለሁም፡፡ የኢራን ሰው ነኝ፡፡ የኢራን ሰው ሰውን አይነካም። ግን ማንም ሰው የኢራንን ሰው አይበድልም፡፡ ስለዚህ አለና ድንገት
በጠረጴዛው ተንጠራርቶ ሰውዬውን አነቀው፡፡ ሰውየው ራሱን ለማስጣል አልሞከረም፡፡ ባህራም ሲያፈጥበት፣ በደነገጠ ድምፅ

«አይነቁኝ፡፡ አስም በሽታ አለብኝ» አለው ባህራም ለቀቀው፡፡ ሰውዬው ከጠረጴዛው ኪስ ሌላ ገንዘብ አውጥቶ ባህራም ፊት ቆጠረው። ባህራም ገንዘቡን አንስቶ ኪሱ ከተት። ሰውየውን አየው፡፡ ወምበሩ ላይ ተቀምጦ ወደ ላይ ይመለከተዋል። ባህራም አፉ ውስጥ ብዙ ምራቅ ሰበሰበ፡፡ ሰውዬው ፊት ላይ ተፋው፡፡ ሰውዬው መሀረብ ሊያወጣ እጁን ወደ ኪሱ ሲከት ባህራም ትቶት ወጣ

ከዚያ እየጨሰ ወደ ኤክስ የሚወስደውን አቶቡስ ተሳፈረ
ያን ቀን ተካን ባያገኘው ጥሩ ነበር
ተካ በበኩሉ ከአንድ ወር በላይ ሲበሳጭ ሰንብቷል። ጀርመንዋ
ልጅ እየባሰባት ሄደ። በፊት እንኳ ከዚያ ካገሯ ልጅ ጋር የምትወጣው አልፎ አልፎ ነበር፡፡ አሁን ግን ቢያንስ በሳምንት አራት ማታ ከሱ ጋር ነች። ተካ እንግዲህ ቢበዛ በሳምንት ሁለት ማታ ቢያገኛት ነው። ለዚያውም ሁለቱም ማታ የንትርክ ማታ ነው።
ሁልጊዜ ስለጀርመኑ ይጨቃጨቃሉ

«ከሱ ጋር ምን ትሰሪያለሽ?»
በራሴ ህይወት ምን አገባህ?»
አብራችሁ ትተኛላችሁ?»
«ምን አገባህ?»
በጥፊ እየመታት «ንገሪኝ! ይተኛል?» ይላታል
በንዴት «አዎን ይተኛኛል! በል ምን ትሆን!?» ትለዋለች
እንደገና አንድ ሁለት ጥፊ ያቀምሳትና፣ በግድ ታግሎ
ይተኛታል
አንድ ማታ ግን፣ ዝግ ባለ ድምፅ
«ልሰናበትህ ነው የመጣሁት» አለችው
ልቡ እየፈራ «ምነው? የት ልትሄጂ ነው?» አላት
«የትም አልሄድም፡፡ እስቲ
ዛሬ እንኳ ሳንጣላ እንደር፡፡
የመጨረሻችን ሌሊት ነው፡፡ ሄርማን ሊያገባኝ ቆርጧል፡፡ እኔም እሺ ብየዋለሁ።»

በሰላም አደሩ፡፡ ከዚያ በኋላ አነጋግራው አታውቅም
ጀርመንዋ ያስለመደችው ሲቀርበት ጊዜ ያንገበግበው ጀመር፡፡በቶሎ ሴት ማግኘት እንዳለበት ገባው:: ቢመለከት፣ ኒኮል አለች::መልኳ እጅግም ነው፡ ወንድ በብዙ ልትስብ አትችልም፡፡ ለዚህ አይደል ባህራምን በገንዘቧ 'ምታኖረው? ግን አሁን ባህራም
አብዛኛውን ጊዜ ከኤክስ ውጪ ነው:: ስለዚህ ሌላ ወንድ መፈለጓ
አይቀርም። እንድያውም ይህን ጊዜ እሱ (ተካ) ሴት ያስፈለገውን
ያህል እሷም ወንድ መፈለጓ አይቀርም፡፡ ሌላ ሴት እስኪያገኝ ማቆያ ትሆነዋለች። እሷም በበኩሏ ባህራም እስኪመጣላት ማቆያ ይሆናታል፡፡ የጋራ ጥቅም!
ማክሰኞ ከምሳ በኋላ ቤቷ ሄደ
ቡና አፈላችለትና «ዛሬስ ምን ሰማህና ልትጎበኘኝ መጣህ?»
አለችው
«እንድ ነገር አስቤ ነው» አላት
«ምን?»
«እኔንና አንቺን የሚጠቅም ሀሳብ ነው»
«ንገረኛ»
«ደስ ትዪኛለሽ፡፡ ስለዚህ ባህራም በሌለበት ጊዜ እዚህ ብመጣ
ጥሩ ይመስለኛል»
«መጥተህስ?»
«እናወራለን፤ እንጫወታለን» እያለ እጁን እጇ ላይ አስቀመጠ
እጇን እያሸሸች «ለኔ የሚሆን ጨዋታ ያለህ አይመስለኝም»
አለችው
«አለኝ»
«የለህም»
«ከባህራም በምን አንሳለሁ?»
በሁሉም ነገር»
«ሞኝ ነሽ። ይልቅ አንድ አቃጣሪ አረብ እየከፈልሽው
ከሚተኛሽ፣ እኔ ያለ ገንዘብ ብተኛሽ አይሻልሽም?» አላት
ፊቷ በቁጣ እሳት መሰለ፣ ግን ድምፅዋ አልተለወጠም
«ወንድ ከሆንክ ሂድና ባሀራምን አቃጣሪ አረብ ነህ በለው። እኔ
ወንድ ስላልሆንኩ የሚገባህን ቅጣት ልሰጥህ አልችልም። ግን ቆሻሻ ነህ፡፡ አንጎልህም ቆሻሻ ነው፣ ሰውነትህም ቆሻሻ ነው። እግርህ ይገማል፣ አፍህ ከሬሳ እኩል ይቆንሳል። አሁን ቤቴ ሳይገማ ተነስና ሂድልኝ አለችው
ተነሳ። ቁጭ እንዳለች ሳታስበው በጥፊ መታት። ከወምበሯ
ተከነበለች። ከወለሉ ላይ በፀጉሯ ጎትቶ እነሳትና እንገቷን ሳማት።
ስትፍጨረጨር እጁን ጠምዞ ወደ አልጋዋ ወሰዳት። አልጋው ላይ
ጣላትና አንድ ጡቷን ጭብጥ አርጎ ያዘ፡፡ መፍጨርጨሯን ተወች
በኣፏ ብቻ

ተወኝ! ብትተወኝ ይሻልሀል!» እያለች ትፎክራለች እጁን ሰደደና ሙታንቲዋን ሊያወልቅ ሲል እንደገና መፍጨርጨር ጀመረች፡፡ ጡቷን የባሰውን በሀይል ዉበጠው:: ፀጥ አለች፡፡ ሙታንቲዋን አወለቀው። እምባዎ ይወርድ ጀመር፡፡ ቁጣዋ
ወደ ልመና ተለወጠ
እባክህ ተወኝ፡፡ ምን አረግኩህ?»
ልመናዋን ከምንም አልቆጠረውም። ጡቷን ጨብጦ እንደያዘ የሱሪውን ቀበቶ ፈታ
አሁንም እምባዋ እየወረዳ «እባክህን ተወኝ፡፡ እርጉዝ ነኝ፡፡
የሁለት ወር ነብሰ ጡር ነኝ» አለችው

የሱሪውን ቁልፍ ይፈታ የነበረው እጁ ባለበት ደረቀ። ጡቷን ይዞ የነበረው እጁ ለቀቃት፡፡ ሱሪውን መልሶ ቆለፈ፡፡ ትቷት ወጣ

አልጋዋ ላይ ተደፍታ ስታለቅስ ባህራም ደረሰ፡፡ ከጋርደን
እያበሽቀ መምጣቱ ነበር። በጥፊ ተመትቶ የቀላውን ፊቷን አየ፡፡
እያለቀሰች የሆነውን ሁሉ ነገረችው
ተናዶ ተካን ፍለጋ ወጣ፡፡ ኒኮል ተከተለችው። ምናልባት
ኣደገኛ ነገር እንዳይስራ ፈርታለች። እሱ በረዥሙ ሲራመድ እሷ
አልደርስበት ብላ ከኋላው ከሩቅ ሱክ ሱክ ስትል፤ ኤክስን አቋርጠው ሲቴ አጠገብ ሲደርሱ ባህራም ተካን አየው፡፡ ጠራው፡፡ ተካ ቆመ፡፡አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ነበር። ባህራም ደረሰና ቃል ሳይናገር በጥፊ መታው። ተካ ቡጢ ሰነዘረበት። ባህራም ጎምበስ ብሎ አመለጠና፡
በፍጥነት የተካን እጅ ይዞ ጠምዞ በሀይል ወረወረው: ከዛፉ ጋር
አጋጨው። ከዚያ በኋላ ተካ ሊካላከል አልቻለም፤ አንጎሉ ዞሮበታል፡ ባህራም እጅ ውስጥ እንደ ህፃን ሆነ። ባህራም ጭንቅላቱን ይዞ ፊቱን
ከዛፉ ጋር ደጋግሞ ደጋግሞ አጋጨው። የተካ ፊት በደም ተበከለ።ኒኮል ደርሳ ባታስጥለው ኖሮ ምናልባት ይገድለው ነበር
👍211
ተካ አልሞተም፡፡ ብቻ ሳየው ግራ እጁ በፋሻ ተጠምጥሞ፣ ደረቱ ላይ ታጥፎ፣ ከአንገቱ በፋሻ ተንጠልጥሏል። ፈገግ ሲል አንዱ
የላይኛ የፊት ጥርሱ ወልቋል
ከሁለት ሳምንት በኋላ ወርቅ ጥርስ አስተከለ ባህራምን «እውነት ኒኮል አርግዛለች?» አልኩት
«አዎን አለኝ «እንግዲህ ታሰርኩ ማለት ነው፡፡
ዝም አልኩ፡፡ ምን ልበል?
ያ ሁሉ የሬቮሉሽን ወሬ ከንቱ ቀረ። ኒኮል ካረገዘች ሁለት
ወር አለፈ። ታሰርኩ፡፡»
«ለምን አላስወረዳችሁትም?»
«እንዴት እርገን ልጃችንን እንገድላለን?» አለኝ
ለዚህ መልስ አልነበረኝም፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ማን ያውቃል?
ምናልባት የተረገዘው ልጅ የባህራም አማንዳ ወሬውን ስትሰማ አብሬያት ነበርኩ። ሆቴል ክፍሏ ውስጥ ቁጭ ብለን ስናወራ ስንስቅ በሩ ተንኳኳ
“Corne in... I mean Entrez!” አለች እየሳቀች
ተካ እጁን እንደጠመጠመ ገባ፡፡ አየነው
«ሰምተሀል?» አለኝ በአማርኛ። ሸራፋው ክፍት ክድን ይላል
«ምን?» አልኩት
“ሞንቴ ካርሎ ሆቴል ውስጥ ጀምሺድና ያገራችን ልጅ ሞተው ተገኙ።»
“What is it? What is it?” አለች አማንዳ
«እርግጠኛ ነህ?» አልኩት
“What is it?”
«እርግጠኛ ነኝ። ፖሊሶቹ እንደሚሉት፣ ጀምሺድ መጀመርያ
የኛን ልጅ በሽጉጥ ግምባሩን ብሉ ገደለውና -»
"What is it?"
ቀጥሉ የራሱን አንጎል ብትንትን አደረገ፡፡ አሁን
ሬሳዎቻው ወደየአገራቸው ሊላኩ ነው::»
አማንዳ ተነሳችና (እኔ ለካ ሳይታወቀኝ ተነስቻለሁ) ትከሻዬን
እየነቀነቀች፡ በእንግሊዝኛ
«እባክህን ንገረኝ። ምንድነው?» አለችኝ
«አዝናለሁ» አልኳት
«ሉ ነው?» አለች። በሀይል ፈርታለች «ንገረኝ፣ ሉ ነው?»
በጭንቅላቴ አዎን አልኳት
ምን ሆነ? ምን ሆነ? ንገረኝ!» አለችኝ
«ልታገኚው ባትሞክሪ ይሻላል። ወደ ፓሪስ ተመለሺ፡፡»
«ለምን? ለምን? ምን ሆኗል?»
«ልታገኚው አትችይም»
በሀይል እየነቀነቀችኝ፤ በጠንካራ ድምፅ
«ንገረኝ!» አለችኝ
“ከንግዲህ ማንም ሊያገኘው አይችልም» አልኳት
በሹክሹክታ መሳይ ድምፅ፤ «ሞቷል?» አለችኝ
ዝም አልኳት፡፡ ወደ ተካ ዞረችና፣ በተዘረጋ እጇ በሩን እያመለከተች
«Get Out!" ብላ ጮኸችበት
ባማርኛ «ቂንጥራም!» ብሏት ወጣ፡፡ በሩን ዘጋ፡፡
ረጋ ባለ ሁኔታ ቦርሳዋን ከሶፋው ላይ አነሳች፣ ወደ በሩ
መራመድ ጀመረች። ዘልዬ ቀደምኳትና በሩጋ ቆምኩ፡፡
አሳልፈኝ» አለችኝ፡፡ አታለቅስም፡፡ ያዘነችም አትመስልም፡፡
አይኖቿ ፍዝዝ ብለው፣ በህልም ውስጥ ያለች ትመስላለች
«የት ትሂጂ?» አልኳት
«ሄጄ ሉን አየዋለሁ።
ሁለት እጄን ትከሻዋ ላይ ጫንኩና
«እንድታዪው አይፈልግም፡፡ እንደድሮው ሲስቅ ሲጫወት
እንድታስታውሺው ነው የሚፈልገው» አልኳት
«ሲስቅ ሲጫወት! ሲስቅ ሲጫወት!» አለችና ስቅስቅ ብላ
ማልቀስ ጀመረች። ትከሻዋ ላይ፧ ባሉት እጆቼ ወደኔ ሳብ
አደረግኳት። ራሷን ደረቴ ላይ አንተራሰችና ለቅሶዋን ቀጠለች
አልቅሳ ስትጨርስ ሀኪም ጠራሁላት፡፡ የሚያስተኛ መርፌ
ወጋትና ሄደ
«አጠገብሽ ብሆን እወድ ነበር» አልኳት
ክፍሉ ውስጥ አንድ ትንሽ አልጋ አስነጠፈችልኝ፡፡ ተኛች።
ሲመሽ ወጣ ብዬ እራት በልቼ ተመለስኩ፡፡ ተኝታለች። ልብወለድ
መፅሀፍ ሳነብ አምሽቼ ተኛሁ።
ጧት ተነሳች። ገላዋን ታጠበች። ረዥም ስስ ሀምራዊ የሌሊት
ልብሷ ላይ ከፎጣ የተሰራ ወይን ጠጅ የቤት ካፖርት ደርባለች።
ብርሀን መሳይ ፀጉሯ በሚያስደስት አኳኋን ተሞነጫጭሯል። አብረን
ቁርስ በላን። ሉልስገድን እንዳናነሳ ፈርተን ስለሆሊውድ ማውራት
ጀመርን ቁርስ በልተን ስናበቃ፣ እኔ ሶፋው ላይ ቁጭ እንዳልኩ
ተነሳችና ከፊቴ ቆመች። በዝግታ የፎጣ ካፖርቷን መቀነት ፈታች።
ካፖርቱን አውልቃ ለቀቀችው። ምንጠፉ ላይ እግሮቿ ዙርያ ተጠቀለለ፡፡ ሀምራዊ ስስ የሌሊት ልብሷ ድምብሼ ገላዋን እንደ ደመና ከቦታል እንጂ አልሸፈነውም፡፡ጡት
መያዣና ሙታንቲ አላደረገችም፡፡ አቤት ወርቃማ ጭገሯ ማማሩ! እጇን ዘርግታ ፊቴን ዳሰሰች። ትርጉሙ የማይታወቅ ፈገግታ
ፊቷ ላይ ሰፍሯል።
ከተቀመጥኩበት ወደፊት ጎንበስ በማለት ምንጣፉ ላይ ተምበረከክሁ።
ፊቴን ለስላሳ ሆዷ ላይ አሳረፍኩ፡ እጆቼን ወፍራም ዳሌዋ ዙርያ
ጠመጠምኩ፡፡ ራሴን እቅፍ አደረገችኝ። እንደዚህ ሆነን ረዥም ጊዜ ቆየን። ምን እንደፈለገች ስላልገባኝ፡ ምንም ባላደርግ ይሻላል በማለት ባለሁበት ረጋሁ። በኋላ፤ ከተምበረከክሁበት አስነሳችኝ። ወደ አልጋዋ ወሰደችኝ። መኖሩን ሰምቼው የማላውቅ አዲስ የግብረ ስጋ
አገር አሳየችኝ ይሄ ሁሉ ሲሆን፣ ያ ትርጉሙ የማይታወቅ ፈገግታ ፊቷ ላይ ብቅ ጥፍት ይል ነበር። ምሳ ከበላን በኋላ ሻንጣዋን መኪናዋ ኋላ ወምበር ላይ አስቀመጥኩት። አብሬያት ከኤክስ ወጣሁ። ወደ
አቪኞን የሚወስደውን መንገድ እንደያዘች መኪናዋን አቆመች።
አየችኝ። ሰማያዊ አይኖቿ እምባ አቀረሩ። አንገቴን ስባ አፈ ላይ
ሳመችኝ። መሀረቤን እያቀበልኳት

«አሁን የት ነው የምትሄጂው?» አልኳት

«እኔ እንጃ። ብቻ ከ'ንግዲህ ኤከስን ማየት አልፈልግም» አለች
እንባዋን እየጠረገች ከአጭር ዝምታ በኋላ «አንድ ነገር ልጠይቅሽ እፈልግ ነበር»
አልኳት። ግን አመነታሁ፡፡
«ገብቶኛል» አለችኝ «ጧት ለምን እንደዚያ እንደሆንኩ ልትጠ
ይቀኝ ነው የምትፈልገው?»
«አዎን»
ሳቅ እያለች «አንተስ ለምን እሺ አልከኝ?» አለችኝ
«እኔማ ሻንዜሊዚ ካየሁሽና ሌላ ሴት እየመሰልሽኝ ከተዋወቅን
ጀምሮ "አምረሽኝ ነበር።»
«እንደሱ ቢሆን ኖሮ ፓሪስ የተገናኘን ጊዜ በጣም ይመች
አልነበረም? ይልቅ እውነቱን ንገረኝ፡፡»
«እኔ ለራሴ በጣም ደስ እንዳለኝ አውቃለሁ እንጂ፣ ምኑም
አልገባኝም፡፡ አንቺ ንገሪኝ እስቲ»

ያ ምስጢራዊ ፈገግታ ፊቷ ላይ ብቅ አለ

«እውነቱን ለመናገር የሚበቃ ቃላት የለኝም» አለችኝ ግን
እንዲህ ልበልህ፡፡ ሞት መጥቶ በግድ ካልወሰደኝ በስተቀር፣ እውስጤ ገብቶ ስፍራ እንዲይዝ አልፈቅድለትም፡፡ መቸም ቢሆን፥ ጥልቅ ሀዘን ውስጥም ብሆን፡ ህይወት ሞትን ድል እንዲነሳው እፈልጋለሁ፡፡ ጧት ሳይታወቅህ፣ እውስጤ ገብተህ ሞትን እንዳባርረው አግዘኸኛል።
ምነው በመገረም ታየኛለህ? ተለውጫለሁ አላልኩህም እንዴ?»
«አሁንማ ገባኝ፡፡ ውስጥሽ ከፀጉርሽ ይበልጥ ውብ ሆኗል»
አይኖቿ እንደገና እምባ ሞሉ። እንደገና በአንገቴ ስባ በረዥሙ
ሳመችኝ
«ተጠንቅቀሽ 'ንጂ፡ እሺ?» አልኳት
ሳቅ አለች «አትስጋ። አገርህ ከመሄድህ በፊት ፓሪስ ብቅ ብለህ
ታየኝ የለ?»
«እመጣለሁ፡፡ እስከዚያ አድራሻሽን ላኪልኝ፡፡»
«ትፅፍልኛለህ?»
«በሳምንት በሳምንት፡፡»
«ጥሩ ልጅ ነህ፡፡ በጣም ጥሩ ልጅ ነህ፡፡»
«ላንቺ ብዬ አይደለም፡፡ ለራሴ ብዬ ነው። እንዳንቺ ያለች
ብርቱ ውብ ሴት ካየሁ አያስችለኝም፡፡»
እንደገና በአንገቴ ስባ አፌ ላይ በሀይል ሳመችኝ። ከመኪናዋ
ወረድኩ፡፡ ሞተሩን ቀሰቀሰች። ጭልጥ አለች። እስክትጠመዘዝ
በአይኔ ተከተልኳት። ጥልቅ ሀዘን ተሰማኝ። የሄደችበትን መንገድ
ሳይ የቆየሁበት አይኔ ብዥ አለብኝ። አይኔን በሀይል ጨፈንኩ።እምባው ጉንጩ ላይ መውረድ ጀመረ። እጄን ኪሴ ከተትኩ።
መሀረቤ የለም፡፡ እማንዳ ይዛው ሄዳለች
ፊቴን ወደ ከተማው መለስኩ፡፡ ኤክስ ራቅ ብላ ትታየኛለች።
ከበላይዋ ንፁህ ሰማይ ተዘርግቷል። የአማንዳን አይኖች ይመስላል....

💫ይቀጥላል 💫
👍20
#ተነሳና_ተነስ

ቀልደኛ ገበሬ ሳይቀልድ
በሰኔ ወር እየሞተ
ሰኔና ሰኞ ገጥሞበት
ሀገሬው እያቃሰተ
እያየህ በየጎዳናው
እያየህ ባደባባይ ላይ
ከምድር አረንቋ በዝቶ
ከሰማይ ተከፍቶ ቀላይ
ባትፈረጅ ምን አለበት
ባትባልስ ክፉ ብቃይ
አትነስ እንዳነሱቱ
ለፍቶ አዳሪውን አታብግን
በተንኮል ከዘሩት ማሳ
ከሰዎች ጭዳ ሳትዘግን
ከራስህ ትንሽ ቀንሰህ
ላገርህ በብዙ ወግን
ልጅ እያለህ በጨቅላነትህ
ከመላእክት ስታወጋ
ፈገግ ብለህ ባደክበት
በእናት ባባትህ አልጋ
በእስተርጅና ጭንቀት ሳይሆን
ምሽታቸዉ እንዲነጋ
አትቅበዝበዝ ሰከን በል
ከቀልብህ ሁን ትንሽ እርጋ
ግድ የለህም እንኳን ለሞት
ለእርጅና እንኳን ይጠብቋል
” እደግ" ብሎ ” እንትፍ” ያለም
ለነፍስ ይማር ይመርቋል
የጭብጨባ ጎርፍ አይዋጥህ
ላልባሌ ጆሮህን ድፈን
ብቻህን ብትሆን ቢበርድህ
ቢያቆራምድህ የኑሮ ቆፈን
በማሕበር አትመራ
ዙርያህን እያየህ መርምር
” የማይሆን” ቢሆንስ? ብለህ
አንዳንዴ በልብህ ጠርጥር
የሰጡህ ጭምብል አይሆንም
ፊትህ ላይ እንዳታጠልቀው
እምነትህን በታማኝነት
ደግመህ ደጋግመህ አጥብቀው
ላብህ ነው ጥሪት የሚሆን
ሳትጠረጥር እወቀው
ያርባ ቀን እጣህን ይዘህ
የሌሎችን ግን ልቀቀው
ሞትን እየሞትክ ሳይሆን
በሕይወት ሆነህ ጠብቀው

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍63
#ሚስቴን_አከሸፏት


#አምስት (መጨረሻው)


#በአሌክስ_አብርሃም

...ፌቨን ከዛ ቀን በኋለ የፀጉሩ ነገር እንዳበቃለት ሲገባት ያማልለኛል ያለችውን ነገር ሁሉ እያሳየች የተንኮታኮተ ፍቅሬን ልትመልሰው ተፍገመገመች። አንዴ አጭር ቀሚስ ለብሳ እግሯን እስከታፋዋ ታሳየኛለች፤ (እግርሽ ያምራል እላት ነበር ድሮ እንደዛሬው እያንቀዠቀዠ አልባሌ ቦታ ሳይወስዳት በፊት) የእጇን ጣቶች ብታወናጭፍ፣ ዓይኗን ብታፈጥ፣ከንፈሯን ብታሞጠሙጥ... ውሉን ቆርጣ ጥላ ትርፍራፊ ውበቷን ብታግተለትል ወይ ፍንክች። እንደውም የባሰ አስጠላችኝ። አይናገረውም እንጂ ሁሉም አፍቃሪ ለዘላለሙ የሚያመልከው የሚያፈቅረው ሰው ላይ በየቀኑ ዓይኑ የሚፈልገው የውበት አማካይ ቦታ አለው። ሌላው ሁሉ ካለዚህ ነጥብ ባዶ ነው። ለእኔ የፌቨን አማካይ የውበት ቦታ ፀጉሯ ነበር። ፌቨንን እንደከተማ ብመለከታት መሐል አደባባይዋ ፈርሷል። አንጋፋ ፍቅር አዲስ ከተማ ላይ መኖር ያንገሸግሸዋል።

የዘመናዊው ፋሽን ትልቅ ችግር የሴቶችን ፀጉር የሚያደንቅ ተፈጥሯችንን በግድ ጠምዝዞ ሴቶች ዳሌ ላይ ለማሳረፍ መጣሩ ነው። ሴቶች እግር ላይ ሴቶች ጡት ላይ ዓይናችንን በግድ ማስተከል። እንቢ ማየት
አንፈልግም ስንል ውበት የማይገባን ገገማዎች መሆናችንን በማሳመን ስልጡን አይደላችሁም ይለናል ሞላ ያለች ሴት እይታችንን ትስበው ይሆናል። ፋሽን ተብዬው ግን የትከሻዋ አጥንት ካልተሰረጎደ
ሴት ምኑን ሴት ሆነች ብሎ ሊያሳምነን ይጥራል። ፋሽን ጉልበተኛ ነው። በተለይ ሴቶች ላይ ክንዱ ይበረታል። ዛሬ ፋሽን ለመከተል ፀጉሯን የቆረጠች ሴት ነገ የላይኛውን የፊት ጥርስ አስነቅሎ በባዶ ድድ መገልፈጥ ያምርብሻል ብትባል ጥርሷን ከማራገፍ አትመለስም፡፡ የተጋነነ ይመስላል እንጂ ባለፉት
አስር ዓመታት በአገራችን አይሆኑም ያልናቸው ጉዳዮች ዛሬ ላይ ለትውልዱ ተራ ጉዳዮች ሆነዋል።ደግሞ ፍጥነታችን

የፌቨንን ፀጉር መቆረጥ ከሴት ልጅ ግርዛት ለይቼ አላየውም። ልዩነቱ የሴት ልጅ ግርዛት በሴቷ ስሚት ላይ መቀለድ ሲሆን ይሄንኛው በእኔ ፍላጎትና ስሜት ላይ መጫወት መሆኑ ነው። እናም ፌቨንን እፈታታለሁ !! እሷን ብሎ ሚስት። የፍርድ ቤት ቀጠሮዬ ነገ ነው። ፌቨን እናቷ ጋር ከሄደች ሃያ ቀናቶች አልፈዋል፡፡ አልናፈቀችኝም። እንደውም የተሰማኝ ሰላም ልክ አልነበረውም። ትንሽ የተሰማኝ ፌቨንንም ሆነ እናቷን በገንዘብ የምረዳቸው እኔ ነበርኩ በዚህኛው ወር ግን ምንም አልሰጠኋቸውም። ከፌሽን
ጋር ስለተጣላሁ ሳይሆን ብሩን ብልክላቸው ፌቨንን የመፈለግ ስሜት ያደረብኝ እንዳይመስላቸው
በማሰብ ብቻ ነው….

ከፌቨን ጋር ከተለያየን በኋላ ብዙዎች እንዳሰቡት ስትናፍቀኝ “ማሪኝ” ብዬ ቤቷም አልሄድኩ።
ስልክም አልደወልኩም። እንደውም አንዳንዶች፣ “ሚስቴ ቤቱን ጥላልኝ ስትሄድ ቤቱ ሊበላኝ ደረሰ፣ ጭር አለ ኦና ሆነ” ምናምን የሚሉት ነገር ለምን እንደሚባል ገረመኝ። በጣም ነው ቤቱ የተስማማኝ ገነት ነው የሆነብኝ ! ምግብ ራሴ አበስላለሁ፣ ቤቴን በደንብ አፀዳለሁ፣ አነባለሁ፣ ፊልም አያለሁ
(እንደውም ከዚያ ፌቨን ከምትከፍተው አሰልቺ የቴሌቪዥን ድራማ ተገላገልኩ) እና ደግሞ ሰላም ሆንኩ!! እንደውም ባልና ሚስት የፈለገ ቢፋቀሩ፣ ትንሽ መለያየት፣ ራሳቸውን የሚያደምጡባት
“ሱባዔ” መሰል ብቸኝነት ታስፈልጋቸዋለች ብዬ አሰብኩ።

ፌቨንን ለራሴ እንኳን ስሟን በውስጤ መጥራት ይቀፈኛል። በቃ በተፈጥሮዬ ወግ አጥባቂ ነገር ነኝ ማለት ነው ብዬ አሰብኩ። እና እንዴት ይሄን ሁሉ ዓመት አብራኝ የኖረች ሴት ያውም በፍቅር ተነስታ ስትሄድ ምንም ሳይመስለኝ ቀረ። ለደቂቃ መኝታ ቤታችን ውስጥ ስትበር የነበረች ትንኝ
እንኳ በሆነ ሽንቁር ስትወጣ የሚናፍቅ ነገር አላት። አይ ጤነኛ አይደለሁም ማለት ነው። ወይስ የሆነ ውስጣችን ሳያውቀው የሚሰለቸው አብሮነት አለ ... ምክንያት ፈልጎ የሚፈነዳ ... ፌቨንን ሳላስበው ውስጤ ሰልችቷት ይሆን ? ዓይቷት የማይቋምጥ ወንድ የለም … ቁንጅናዋ እንግዳ ነገር ነው ..
መኝታ ቤት ገብታ ወደ ሳሎን ስትመለስ እንኳ አዲስ ቆንጆ ሴት እንዳየ ጎረምሳ ልቤ ይደነግጥላት
ነበር ... እና እንዴት ነው ነገሩ ... እንዲህ ልክ የሌለው ግዴለሽነት የሞላኝ ወይስ እየቆየ እንደተዳፈነ
እሳት ሊያንገበግበኝ ይሆን ...

ለነገሩ ቆንጆ ሴቶች ቶሎ ነው የሚሰለቹት ይባላል። በጥናት ባይረጋገጥም የሆነ እውነት እንዳለው በብዙ ቆንጆ ፍቅረኛ ባላቸው ጓደኞቼ ታዝቤያለሁ። በተለይ ከተጋቡ በኋላ ቆንጆ ሚስቶች ለውጭ ተመልካች እንጂ ለባሎቻቸው ያን ያህል አስገራሚም አስደሳችም ነገር የላቸውም እየተባለ ከፉኛ
ይታማል ሚስቶቹም ራሳቸው ይሄ ነገር ግራ ይገባቸዋል አንድ ጓደኛዬ እንዳለኝ ከሆነ እንደውም
ቃል በቃል፣ ለዛ ቢስ ናቸው !!” ነበር ያለው እንግዲህ ከሰፊ የብሶት ምክሩ የተወሰነውን ሳስታውስ (ያኔ እንኳ ችላ ብዬው ነበር) ቁንጅናቸው ይስብሃል፣ ቁንጅናቸውን ትፈልጋለህ፣ ታገኘዋለህ፣ ቁንጅናቸው መጋረጃ ሆኖ ስለሚጋርድህ ከማግኘት ቀጥሎ ያለውን ሕይወት አታስበውም። መጋረጃውን ስታልፍ ግን ጭው ያለ በረሃ ይጠብቀሃል.. ሰሐራ ! ምንም አይኖርም ወላ ሃንቲ !! ሁሉም ነገራቸው ወዲያው ነው
የሚሰለችህ... እንደውም እነሱን ለማግኘት የደከምከው ድካም ከንቱ ሆኖ ስለሚታይህ ነጭናጫ
ትሆናለህ ድሮ ይቺን ሚስትህን አፍቅረህ ስትንከራተት ፊት የነሳሃት በፍቅር ዓይን ስትስለመለምልህ
የነበረች ጎራዳ ሽቦ ፀጉር ልጅ ሁሉ ትናፍቅሃለች ! ለዛ ነው ብዙውን ጊዜ “ልዕልት የመሰለች ሚስት
አስቀምጦ ሰራተኛው ጋር…” ምናምን ሲባል የምትሰማው እንጅማ ሚስትህ ልዕልት ባትመስልም ሌላ ሴት ጋር ሂድ የሚል ፍርድ የለም መቼስ።” የጓደኛዬ ምክር ይከሰትልኝ ይጀምራል። የበላኝን
እንደሚያክልኝ ሁሉ ንግግሩን የራሱ ልምድና አመለካከት አድርጌ ከማድመጥ በላይ ዓለምአቀፍ
የሴቶች ባህሪ አድርጌ ልቀበለው ይዳዳኛል። ማንም ሰው በጋራ ብሶት ውስጥ ሲኖር በአዕምሮው ልክ ሳይሆን በብሶቱ ልክ ያስባልና።

“ሴትን ልጅ ለማየት ይሄ ደካማ ሥጋዊ ዓይን በቂ አይደለም ድፍን የስሜት ሕዋሳቶችህ፣ በአካባቢህ ያለው እውነታ፣ ታሪክ፣ ፍልስፍና፣ ኃይማኖት፣ አስተዳደግህ፣ የትምሕርት ደረጃህ ሁሉ “ተቀናጅቶ” መሥራት ይኖርበታል። በደመ ነፍስ ዘለህ ከገባህ በደም ግፊት ዘለህ መቃብር ጉድጓድህ ውስጥ ነው
የምትገባው ያውም በጭንቅላትህ። ፍቅር ላይ ያለህ ነገር ከተበላሸ በምድር ላይ ያለህ ማንኛውም ነገር እንደተበላሸ ቁጠረው። ሌላው ቢቀር እየቆየ የሚያገረሽ የተበላሸ ትዝታ ይኖርሃል። ልብህን ለፍቅር
ስትሰጥ ወሲብ ያዞረው ናላህን አሽቀንጥረህ መጣል አለብህ። እሱ ነው እንደጋሪ ፈረስ ሸብቦ አንድ ነገር ብቻ እንድታይ የሚነዳህ። ለምን እቅጩን አልነግርህም ያኔ አንድ ቤት የሁለትዮሽ ስብሰባ ላይ ስትገናኝ
ተረከዝ አይመስጥህ፣ ዳሌ አያማልልህ፣ ከንፈር አያስጎመዥህ፣ ስርቅርቅ ድምፅ ቀልብ አያሳጣህ፣ ጉችም ይበል
ዝርግፍም ይበል ጡት ከመጤፍ አይቆጠር ሃቂቃዋ የፍቅር ዘርልብህ ውስጥ ከሌለች
አለቀልህ !”
👍453👏3👎1
“የተንዛዛ እና የሚያዛጋ የሕይወት ድራማ ውስጥ ራስህን ታገኘዋለህ አቤት ሲያስጠላ። አንድ
የማይመሽና የማይነጋ ረዥም ቀን ላይ ያለህ ነው የሚመስልህ። ሁልጊዜ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት የሚመስል የሆነ ጠራራ ሕይወት ! በቲቪ፣ በመጽሔት ምናምን ታዋቂ ሰዎች፣ “ሚስቴን እወዳታለሁ፣ ባሌን እወደዋለሁ” ሲሉ ሰምተህ ታውቃለህ አይደል ? እስቲ ዝም ብለህ አስበው ሚስቱን ካልወደደ
ማንን ሊወድ ነበር ታዲያ። እሷስ “ባሌን እወደዋለሁ” … ፓ ተናግራ ሞታለች እና ምን ይጠበስ::
ባልን መውደድ የተለየ ብቃት የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲያስመስሉ ይገርመኛል። መዋደድ ያንተም የሚስትህም ብቃት አይደለም። (ሰምተኃል) ፍቅር ለሁለታችሁም ያደላችሁ ፀጋ ብቻ ነው ! ፍቅር የተጠራ ሞተበት የውሻሸት አብሮነት የተሸከመ ጎጆ ሁለት ያልተመቻቸው ሬሳዎች ያቀፈ የአስክሬን ሳጥን ነው !! ለስንቱ በነጭ ቬሎ ስር ጥቁር የውስጥ ልብስ ለለበሰ ትዳር ሃይሎጋ ብለናል !”

“እና በዚች ምድር በጥልቀት ማሰብ ያለብህ ነገር ፍቅርህን ማን ላይ እንደምትጥል ነው። መጽሐፉ
የከበረውን እንቁ አሳሞች እግር ስር አትጣሉ ሲልህ ቀልድ መስሎህ ችላ እንዳትል። ይሄ ለሴትም ይሰራል። ስንቷ መሰለችህ ያላትን ማንነት አራግፋ ለአንዱ አሳማ አፍቃሪ ሰጥታ አፍንጫሽን ላሽ ስትባል እድሜ ልኳን ከራማዋ እንደተገፈፈ የውሻሸት ኖራ ያለፈች ! ካላመንክ እዚሁ አዲስ አበባ አንዷን ኑሮ
የተመቻት የምትመስል ቆንጆ ጠጋ በልና “እህ” ብለህ አድምጣት። ከእድሜዋ በላይ ብሶት ትዘረግፍልሃለች። ብሶት የሌላት ለአቅመ ሔዋን የደረሰች ሴት ካገኘህ ወይ እድሜዋ ለአቅመ
ብሶት አልደረሰም አልያም ከባቄላ ፍላት ያመለጠች ጥሬ ባቄላ አጋጥሞሃልና ፈጣሪህን አመስግን። ሆድ ይፍጀው ብሎ እየተሽቀረቀረ ነው እንጂ ከተማው ሁሉ በፍቅር ቁስለኛ የተሞላ ማገገሚያ ሆስፒታል እኮ ነው። ሁሉም አንድ ቀን ባንድ ላይ የብሶቱን ያህል ስቅስቅ ብሎ እስኪወጣለት ቢያለቅስ አዲስ
አበባ ላይ ብቻ ትልልቁን ሕንፃ ሁሉ እንደጀልባ የሚያንሳፍፍ የእንባ ባሕር ይፈጠር ነበር !”

ደግሞ አንተ ቀለል አድርገህ የምታየው ነገር ለሴቶች እንዴት ትልቅ ታሪክ መሰለህ አድዋ ነው!
እውነቴን ነው። በቅርቡ የተዋወቅካትን ፍቅረኛህን ያለፈ ሕይወት ብትጠይቅ (ባትጠይቅም ትነግርሃለች …ችግሩ የምትነግርህ መናገር ያለባትን ሳይሆን የርሷን ታማኝነት፣ ታጋሽነት፣አፍቃሪነት፣የካዳትን ፍቅረኛዋን ርኩስነት፣ አርዮስነት ያሳያል ብላ ያሰበችውን ተረት ብቻ ነው) ለምሳሌ እያወራችሁ እያለ ትክዝ ብላ እንዲህ ልትልህ ትችላለች፤

“ዘነበ የሚባል ፍቅረኛ ነበረኝ። ስምን መልዓክ ያወጣዋል። በያገኘበት የሚዘንብ። እና አንድ ቀን እዚህ ቶታሉጋ አበራሽ ሥጋ ቤት ከራሴ ጓደኛ ጋር ... ማንትስ ድርጅት ሴክሬቴሪዋ ...ከእሷ ጋር እየተጎራረሱ ቅቅል ሲበሉ በዓይኔ በብረቱ አየኋቸው .. ድሮም ወንድ ማመን” ብላ እንባዋ በዓይኗ ግጥም። አንተ ታዲያ፣ቅቅል መብላት ምን ይገርማል.. ብለህ ካሰብክ አለቀልህ። ቅቅል' ቅኔም ሊሆን ይችላል፤ አንተ ጠበስኳት ስትል እሷ ትልቅ የተረት ብረት ድስት ውስጥ እየቀቀለችህ !”

ወይኔ ጉዴ ብቻዬን ባዶ ቤት ተቀምጩ በሐሳብ ስባዝን ማበዴ ነው መሰል። ፌቨን እያለችኮ ማሰብ አልችልም ነበር። ትንሽ ዝም ካልኩ፡ ምን ሆንክ የኔ ማር ... መሥሪያ ቤት ተጋጨህ አመመህ
ራስህ…” በቃ ንዝንዝ ነው። አሁን እስከ ነገ ወዲያ ባስብ ማን ከልካይ አለብኝ ሃሌ ሉያ !!

እና ከሚስቴ ፌቨን ጋር ልፋታ የመጨረሻው የፍርድ ቤት ቀጠሮዬ እንደነገ ሆኖ እንደዛሬ ማታ አንድ ጥግ ላይ ኩርምት ብዬ እንዲህ የባጥ የቆጡን ሳስብ ሌሊቱ ተጋመሰ። “አብርሽ እስካሁን አልተኛህም”የሚል ድምጽ ሰምቼ ቀጥ ብል ማንም በቤቱ የለም … ግን የሆነ አናቱ ላይ እሳት የመሰለ ወርቃማ ፀጉር
የሚንቀለቀልበት ፍጡር ውልብ ሲል ያየሁ መስሎኝ ነበር። በስመዓብ (የማርያምን ብቅል ፈጭቻለሁ አንቺ። በራሴ አባባል በደረቅ ሌሊት ከት ብዬ ሳቅኩ። እስቲ አሁን ምን አሳቀኝ። አይይይይይ ያ እኛ ሰፈር የነበረው ጃንቦ የሚባለው ሰውዬ ልክ የዛሬ ሃያ አመት መወፈፍ ሲጀምር ከሌሊቱ ስምንት ስዓት እንዲህ እንደኔ ከትከት ብሎ ስቆ ነበር አሉ። ማበዱንስ ልበድ …. ግን እንዴት ፋሽኑ ያለፈበት አስተባለድ አብዳለሁ…

ለነገሩ የሳቅኩት ነገ ዳኛዋ ስታፋታን ምን እንደምንል አስቤ ነው። ቆይ ሰው ሲጋባ በሐዘን ቢሆን በደስታ፣ በጤና ቢሆን በሕመም አብሬያት ... አብሬው ልሆን ምናምን ተብሎ ቃል ይገባል። ባልና ሚስት ሲፋቱ ምን ይሆን የሚሉት። ሰው ሲፋታ አይቼ ስለማላውቅ ግራ ገብቶኛል ...

በመንገድ ቢሆን በሥራ ቦታ፣ በፒያሳ ቢሆን በመርካቶ፣ የደረሰችበት ላልደርስ …. ሃሃሃሃ

እኔና ፌቨን ስንጋባ ያጋቡን የእናቴ ንስሃ አባት መምሬ አምሳሉ ነበሩ። እሳቸው የሚሉትን እየተከተልኩ
እንድል አዝዘውኝ ነበር። በነገራችን ላይ መምሬ እኔን ስለማያምኑኝ ቶሎ ቃልገብቼ በቀለበት ስታሰር
ለማየት ቸኩለው ነበር። እናቴንም ብለዋታል፣አዬ አብርሃም ላገባ ነው ሲልሽ አምነሽ በሬ አስገዛሽ፣ እንጀራ ጋገርሽ፣ ዳስ አስጣልሽ…”
እና ሲያጋቡኝ መስተዋቱ በተሰነጠቀ መነፅራቸው አናት በጥርጣሬ እያዩኝ ነበር ቃል ያስገቡኝ፣
“በጥጋብ ቢሆን በርሃብ ከጎኗ ልሆን ቃል እገባለሁ!” አሉ።
“ብጠግብም ባልጠግብም ቃል እገባለሁ!” አልኩ ተቀብዬ፤ እኔ አሳጠርኩ ብዬ ነው።
አብርሃም … ተው በሰርግህ ቀን እንኳን ያላዘዙህን አታውራ” በማለት ሰርገኛው ሳይሰማ ወደእኔ ጠጋ ብለው አንሾካሾኩ። ፌቨን በሳቅ ፍርስስስስ !ፌቨን ያሳቃት ገብቶኛል። ብዙ ጊዜ ትለኛለች፣ “አብርሽ አንተኮ አንዳንዴ ወሬ ስትጀምር ከጉዳዩ ጋር የማይያያዘውንም፣ የሚያያዘውንም ትቀላቅለዋለህ” አባ ስለደገሙላት ነው የሳቀችው። መምሬ ግን በፌቨንም ሳቅ ተቆጡ፣

“ኤዲያ አንቺ ደሞ እስቲ ለሰርግሽ ቀን እንኳ በልኩ ሳቂ…” ብለው የሆነ ነገር በግዕዝ ተናገሩና በአማርኛ ተረጎሙት፣ “ባልና ሚስት ከአንድ ወንዝ ይቀዳሉ።” መምሬ የሚሉትን እኔና ፌቨን ተከትለን ቃል ገባን። ምነው የዛን ጊዜ፣ “ባሌ ሳይፈቅድ ቅንጣት ፀጉር ላልቆረጥ” የሚል ቃል ጨምረውልኝ በነበረ

ፍርድ ቤት ስደርስ ግቢው ውስጥ የፌቨን እናት፣ ወንድሟ፣ ፌቨንና ያች ማሜ የምትባል ተደርድረው
ተቀምጠዋል። በቀጥታ ሄጄ ማዘርን ሰላም አልኳቸው። “
አብርዬ” ብለው በሁለት እጃቸው ሰላም አሉኝ። ልክ እንደሆነ ባለሥልጣን ነበር ያከበሩኝ። ውስጤ የሆነ ሕመም ተሰማው። የባሰ ያዘንኩት ደግሞ ወንድሟ በስርዓት ሰላም ሲለኝ …. ኮሌታው ንትብ ያለ ሸሚዝ ለብሷል። አያለሁ፣ አያለሁ ዓይኔ
እየተስገበገበ እያንዳንዷን ነገር ያያል። እየቀፈፈኝ ማሜ የምትባለውን የፌቨንን ጓደኛ ሰላም አልኳት። በስርዓት ሰላም አለችኝ። ዛሬ ሰዉን ሁሉ ምን ነካው ብዬ ተገረምኩ። ችሎቱ እስከሚጀመር አብረን ተቀመጥን። ፌቨን በፍርሃት አልፎ አልፎ ቀጥ እያለች ታየኛለች። ፀጉሯን በጥቁር ሻሽ አስራዋለች።

ዳኛዋ አንዴ አየት አድርጋኝ ገባች ..

“እና ሐሳብህን አልቀየርክም አብርሃም” ንግግሯ ተለሳልሷል።
👍201
“አልቀየርኩም። ዳኛዋ እንደማሰብ አለች እናም ያለምንም ውጣ ውረድ ከሰዓት ቀጠረችን።
ልታፋታን። ከችሎቱ ስወጣ ፌቨን እንደ ጆቢራ ድንገት ፊቴ ተገተረች። ሁሉም ነገር ስልችት እንዳላት ታስታውቃለች። እናም አየችኝ፣ በጣም አየችኝ። ዓይኖቿ በእንባ ተሞሉ። ከንፈሯ ይንቀጠቀጣል፤ ልታብድ መስሎኝ ነበር።
“አትረባም አብርሽ አትረባም” ብላኝ ልትሄድ መንገድ ከጀመረች በኋላ ተመልሳ እጇን ስትዘረጋ
በጥፊ አጮለችኝ ብዬ ዓይኔን አጨናበስኩ። ፌቨን ግን ምን እንዳደረገች ታውቃላችሁ። ፀጉሬ ላይ ያየችውን የሆነ ነቁጥ ነገር አንስታልኝ ቀስ እያለች በርቀት ወደሚጠብቋት ቤተሰቦቿ አዘገመች። ምን ማለት ነው። ማንም ይሄ ምን ማለት እንደሆነ መግለፅ አይችልም። ደግሞ ልታስመስል አልነበረም
አውቃታለሁ ፌቨንን።
ፈዝዤ አንዱ ጥግ እንደቆምኩ ማሜ የምትባለው ደንቃራ ሴትዮ ፊት ለፊቴ እየተውረገረገች መጣች። የለበሰችው አጭር ቀሚስ ለመራመድ አስቸግሯታል። ያደረገችው ጫማ ረዥም ቁመቷን የባሰ ብቅል አውራጅ አድርጎታል። ሁሉም ሰው እየተገላመጠ ያያታል። ቅላቷ የሚያንቦገቦግ ነገር ነው።አጠገቤ ስትደርስ የዙሪያዬ ዓየር በሽቶ ጠረን ተሞላ የሚያፍን ነገር።እንደወትሮው አላሽካካችም፣ አልጮኸችም፣ በታፈነ ግን በሚያስፈራ ጠንካራ ድምፅ እንዲህ አለችኝ፣

አብርሃም እንደማትወደኝ አውቃለሁ። የራስህ ጉዳይ ነው፤ ወደድክ አልወደድክ ምን ልትቀንስብኝ። ደግሞም ማንም እንዲወደኝ አልፈልግም ለየትኛው እድሜ” አለችኝ። አነጋገሯ በታሪክ ከሷ ይወጣል ብዬ አስቤው አላውቅም። ኧረ መኮሳተር !ቀጠለች፣ ፌቨን ላንተ ብላ ሥራ እንዳቋረጠች እያወቅከ፣
ከነቤተሰቧ በርሃብ እየቀጣሃት ነው። ብትጠላኝም እኔ አከብርሃለሁ። እንዲህ ዓይነት ተራ ሥራ ትሰራለህ ብዬ አላስብም። ፌቨን እየተራበች ነው ..ይገባሃል አብርሽ”። በቃ ይሄን ተናግራ ተመልሳ ሄደች መርዝ ! በሰከንድ አዕምሮዬን ገለባበጠችው። ርሃብ አልወድም። በተለይ የሴት ልጅን ርሃብ አልወድም። ካፌ ገብቼ እንኳን ሴት ልጅ ቶሎ ቶሎ ስትበላ ካየሁ ታሳዝነኛለች። ርሃብ አልወድም። ርሃብ ማለት ምግብ አለመብላት ብቻ አይደለም። በምድር ላይ በጣም ትንሹን ነገር የዕለት ጉርስን የሚሰጠን ሰው ማጣት ማለት ነው ለኔ ... ርሃብ አልወድም !
ፌቨን ራበኝ ካለችኝ ምንም ልሥራ ምን እርግፍ አድርጌ ትቼ ወደ ምግብ !!ፌቨን እኮ ስትራብ ስታሳዝን በእግዚአብሔር ! እነዛ የሚያማምሩ ጣቶቿ ሳይቀሩ እቃ ማንሳት አይችሉም። በቃ በተፈጥሮዋ ረሃብ አትችልም። ቆይ ግን ስንት ቀን ተርባ ይሆን ..የኔ ተራ ኩርፊያ ስንት ቀን አንድን ቤተሰብ አስርቦ ይሆን
እግዚኦ እንዴት ዓይነት ድድብና ውስጥ ነኝ ! የፌቨን እናት ማለትኮ አገር ያወቃቸው የተራበ ሁሉ
ቤታቸው ገብቶ ጠግቦ የሚወጣ ደግ እናት ነበሩ። ዛሬ ጊዜ ጥሏቸው የአንድ ጭንጋፍ እጅ ጠባቂ ሆነው እኔም ወጉ ደርሶኝ አንድ ቤተሰብ አስርባለሁ። ትላንት የበላሁት ፒዛ ግማሹን ነካክቼ የመለስኩት፣ ዛሬ ጠዋት የበላሁት ቋንጣ ፍርፍር ትዝ አለኝ ሆዳም ነኝ ! ደደብ !!

ምሳ መብላት አልቻልኩም። ቀጠሮው እስኪደርስ ውኃ አዝዤ እዛው አካባቢ ያለ ካፌ ቁጭ አልኩ።

ከሰዓት ፍርድ ቤቱ ስደርስ ወደነ ፌቨን ሄድኩ።

"ፌቨፕ” አልኳት፡፡ ቀጥ ብላ አየችኝ እና መጣች ወደኔ።

“ላናግርሽ ነበር…”

በጓሮ በኩል ወዳለ ቦታ ሄድን። እኔ ከመናገሬ በፊት የፌቨን እንባ ተዘረገፈ። በእንባዋ ውስጥ እያየችኝ እንዲህ አለች፣

“አብርሽ ይቅርታ፣ ሁሉም ነገር ይቅር በማርያም አትለየኝ እወድሃለሁ” አሁን እኔ እንዲህ የሚለመን ምን ነገር አለኝ፤ ምንም። ራሴ አስጠላኝ ከምር። ቀስ እያልን ወደ ዋናው በር አዘገምን። ማለት ፌቨን
አንድም ቃል ባትናገር ደስታዬ ... የእሳት አለንጋ ... ነገሮች ሁሉ አንዳንዴ ይገለባበጣሉ። ዝም ብለን ወደ ውጭ፤ ከኋላዬ ምን ሰማሁ፣

“አቶ አብረሃም ዓለምሰገድ እና ወ/ሮ ፌቨን…” የችሎት ተራችን ደርሶ ሥማችን እየተጠራ ነበር።
(እንዳልሰማ ከግቢው ውልቅ፣ ሁሉንም እዛው ጥለናቸው) አንድ የምንወደው ሬስቶራንት ነበር እኔና
ፌቨን የምንሄድበት። እዛ ተገኘን። ፊት ለፊቴ ተቀምጣ ፌቨን ታየኛለች። እናም በሚንቀጠቀጡ እጆቿ እጄን ያዘችኝ።

“ተሳስቻለሁ”። ስትገርም፤ ይሄን ሁሉ የምታደርገው አንድ ተራ ወንድ መለማመጥ ፈልጋ እንዳልሆነ አውቃለሁ። ፌቨን ምንጊዜም ከሴትነቷ ሰው መሆኗ የሚቀድምባት ልጅ ስለሆነች እንጂ።እና ሳላስበው
መለፍለፍ ጀመርኩ ያውም ሳላባራ። ፌቨን ዓይን ዓይኔን እያየች እንዲወጣልኝ ታዳምጠኛለች።

“አራት ኪሎ ፈርሶ ውብ ሕንፃ ተገነባበት። ትዝታው አብሮ ፈረሰ። ኧረ ትዝታችን ሲባል ፀረ
ልማት ተባልን። ከዛ ጭርንቁስ የጭቃ ቤት ይሄንኛው ውብ ሕንፃ መሻሉን ሳናውቅ ቀርተን ነው ?
አይደለም ፌቪ ... ሰው ከስጋና ከደም ብቻ አይደለም የሚሰራው። ማንነቱን ደግፎ የያዘው የትዝታ
አፅም የመላመድ አጥንት በውስጡ አለ ! እሱን ነው ያፈራረሱት ! መቼም የማይለማ ማንነታችንን ነው ያወደሙት። አሁንም ፀጉርሽ ትዝታችን ነበር . ትዝታችን ሲፈራርስ ….ፋራ የሴቶች እኩልነት ያልገባው ምናምን ይሉኛል ፌቪ . ያኔ በፍቅረኝነት ዘመናችን የቀጠርሽኝ ቦታ ስትመጪ እዛ ማነው
ስሙ ኪዎስክ ጋር ስትደርሽ ፀጉርሽን ንፋስ ሲበትነው … ከሩቅ ጥቁር ፀጉርሽ ንፋስ ሲያራውጠው
በእጅሽ መለስ እያደረግሽው ወደ እኔ ስትመጪ … ፀጉርሽ የፍቅር ባንዲራ ነበር የሚመስለኝ -
ባንዲራዬን ነው የቆረጡብኝ ፌቪ” ፌቨን እጆቼን እያሻሸች ዝም ብላ ታየኛለች። አውራ ጣቴን ይዛ
የምታስለፈልፈኝ ነበር የሚመስለው

“ለሚታየው እና ለሚዳሰሰው ማንነታችን ስንት የማይታዩ ጥቃቅን ማንነቶች አሉ
እነዚያን እየቀፈቀፍን ባዶ ግንዱ የቀረ እንጨት በመብት ስም እንድናቅፍ ለምን ይገፋፉናል አልፈልግም
! ባንዲራዬን መሬት ጥላ ቆሻሻ አድርጋዋለች ብዬ አዝኜብሻለሁ። ከጥራጊ ጋር ያን ውብ ፀጉሯን ወደ
ገንዳ እንዲወረውሩ ፈቀደችላቸው ብዬ አዝኜብሻለሁ ፌቪ … አራት ኪሎን ሲያፈርሱት ቦታው የኛ
ስላልሆነ ዝም ብለናል ... ሚስቴ ግን የኔ ነች … የጋራችንን ትዝታ ስታፈራርስ እንደ መንገደኛ መቼስ
ምን ይደረግ ብዬ ዝም አልልም። የእጇ ልስላሴ፣ የከንፈሯ ጣዕም፣ ፈገግታዋ ሁሉ ሕዝብን ነው
የሚወከለው በፀጉሯ ባንዲራ ... ይሄን ፀጉር መቁረጥ ድንበር ከመገንጠል ለይቼ አላየውም ብዬ
በቻዬን ተማርሬብሻለሁ ፌቪ” ፌቨን እንባዋ ጉንጫ ላይ እየፈሰሰ ዝም ብላ ታየኛለች..

ፌቪ አስጠልተሽኛል፣ አበሳጭተሽኛል፣ የናቅሽኝ የገፋሽኝ መስሎ ተሰምቶኛል። እኔን ከሕይወትሽ ገፍትረሽ ሌላ ሰው ከሰውም ሰው ማሜ የምትባል ሴትዮ የኔን ቦታ የሰጠሻት መስሎኛል። እና
አፈቅርሻለሁ !”

ፌቨን ትንፋሽ እስኪያጥረኝ ከንፈሬን

ቅድም ሊያፋታን የነበረው ሕግ በአደባባይ ከንፈር ለከንፈር መሳሳም ወንጀል ነው ይላል አሉ! ይበላ

የፌቨን እንባ ይፋጃል !!


አለቀ
22👍13👏2
አትሮኖስ pinned «#ሚስቴን_አከሸፏት ፡ ፡ #አምስት (መጨረሻው) ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም ...ፌቨን ከዛ ቀን በኋለ የፀጉሩ ነገር እንዳበቃለት ሲገባት ያማልለኛል ያለችውን ነገር ሁሉ እያሳየች የተንኮታኮተ ፍቅሬን ልትመልሰው ተፍገመገመች። አንዴ አጭር ቀሚስ ለብሳ እግሯን እስከታፋዋ ታሳየኛለች፤ (እግርሽ ያምራል እላት ነበር ድሮ እንደዛሬው እያንቀዠቀዠ አልባሌ ቦታ ሳይወስዳት በፊት) የእጇን ጣቶች ብታወናጭፍ፣ ዓይኗን…»
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


የቀይ ኮከብ ጥሪ
ባህራም

ባህራም እየተለወጠ ሄደ፡፡ እነ ማኦ ትዜ ቱንግ የደረሱዋቸውን
መፃህፍት ማንበብ ተወ:: ስለኮሙኒዝም ማውራት ተወ፡፡ ክፍል መግባት ተወ:: እኔንም ይሽሸኝ ጀመር። እንደቀስተ ደመና ውብ የነበረውን የሬቮሉሽን ተስፋውን በብዙ የእሳት ቃላት ይነግረኝ ስለነበረ' አሁን ቀስተ ደመናው ተሰባብሮ ወድቆ ከበሰበሰ በኋላ፣ እንደገና
ሊያነጋግረኝ አልፈቀደም፡፡ ኒኮልም ፊት ነሳችኝ፡፡የባህራምን ክንፍ እንደሰበረችው ስላወቅኩ ፊት ነሳችኝ

የኤክስን ሰማይ የሉልሰገድና የጀምሺድ መቀሰፍ አላስደነገጠውም፡ የአማንዳ ጉብዝና አላስደነቀውም፡ የኒኮል ማርገዝ አላናደደውም፡ የባህራም መታሰር አላሳዘነውም፡፡ የኤክስ ሰማይ ለዚህ ሁሉ ደንታ የለውም
የኤክስ ሰማይ አብዛኛውን ጊዜ እንደ አማንዳ አይን ብሩህ
ሰማያዊ ነው፡ አንዳንድ ጊዜ እንደ ኒኮል አይን ውሀ አረንጓዴ
ይሆናል፡ ወደ ማታ ጊዜ እንደ ሲልቪ ጉንጭ ይቀላል
የኤክስ ሰማይ ደመና አይለብስም፤ ሁልጊዜ ራቁቱን ነው! ሁልጊዜ ውብ ነው፡ ሁልጊዜ ሰላማዊ ነው። ሌሊት የአልማዝ
ከዋክብትና የሰላም ፀጥታ ለብሶ ያድራል

የኤክስ የፀደይ ፀሀይ እየበረታች ሄደች። ንፁህ ብርሀኗ ቀስ
እያለ ወደ ብጫ ሀሩር ተለወጠ፡ ለስላሳውን የፀደይ ንፋስ
አደከመው፡ የሚወብቅ የአየር ባህር አደረገው፡፡ በጋ መጥቶ ኤክስ ውስጥ እንደ ሰፊ ድካም ተንሳፈፈ። አሮጊቶቹና ሽማግሌዎቹ ጥላ ውስጥ ቁጭ ብለው በዝግታ እያለከለኩ፣ የሞትን ምህረት የሚጠብቁ
ይመስሉ ጀመር

እንዳንድ ጊዚ ባህራምንና ኒኮልን ምግብ ቤቱ ሲገቡ ወይም
ሰወጡ አያቸዋለሁ። ባህራም ከስቷል፡ አይስቅም፣ በፍጥነት
አይራመድም። ሽበቱም የበዛ መሰለኝ፡፡ ኒኮል ግን ወፈር ብላ፣
እርግዝናዋ በጣም አምሮባታል፡ በዝግታ ስትራመድ ታስጎመጃለች
ቀስ በቀስ ምግብ ቤት መምጣቱን ተዉት ተካ የኒኮልን ማርገዝ ለመሸሸግ ያሉት ነው» አለኝ፡፡ ሌላ
ነገር ነገረኝ ባህራም ማታ ማታ ኒኮልን ቤቷ ትቷት ይወጣና
ሲኒማ ይገባል ከሲኒማ ወጥቶ ካፌ 'ሰንትራ' ይሄዳል፡ እዚያው
ያድራል፤ ሲነጋ ወደ ኒኮል ቤት ይኳትናል፡ ተኝቶ ይውላል

አንድ ማታ ወደ ስድስት ሰአት ላይ ከሲኒማ ወጥቼ ወደ ቤቴ
በኩል ስራመድ፡ ከኋላዬ እንደ ፈጣን እርምጃ ሲከተለኝ ተሰማኝ።
እንዳልሰሙ መንገዴን ቀጠልኩ። ደረሰብኝ፡፡ ባህራም፡፡ ወደ ካፌ
ሰንትራ ሄደን ቢራ ካዘዝን በኋላ
ቁጭ ብለን ካወራን ብዙ ጊዜ ሆነን አለኝ፡፡ አይኖቹ እንደ
መድከም ብሏቸዋል፡ ፊቱ ላይ የአምስት አመት ያህል እድሜ
ተጨምሯል
"አንተ አትገኝም አልኩት"
በገዛ ራሴ ጥፋት በታሰርኩ' አንተ ጋ መጥቼ ባለቅስብህ ተገቢ
ማስሉ አልተሰማኝም

ጥሩ እድል አጋጥሞህ ቢሆን ኖሮ ግን መጥተህ ታጫውተኝ
ነብር፡ ደስታህን ታካፍለኝ ነበር»
አዎን። ይኸውልህ፡ ልክ ከፓሪስ እንደተመለስክ እንድንጋገርበት አቅጄ ነበር፡፡ ግን ገና ሳትመለስ ጣጣ ውስጥ ገባሁ። ስትመጣ ታድያ፤ መንፈሴ ተሸንፎ ስለነበረ ያቀድኩትን ችላ አልኩት፡፡ አሁን ፈቃደኛ ከሆንክ ብንነጋገርበት ጥሩ ይመስለኛል።»
"ጥሩ"
መጀመር አስቸገረው። ሲጋራ አቀጣጠለ።
ስለሰልቪ ጉዳይ ነው። ነግርሀለች?»
«አዎን፡፡
«ምን አለችህ?»
የነገረችኝን ባጭሩ አጫወትኩት። ዝም ብሎ ሰማኝ። ስጨርስ
«ውሸቷን ነው» አለኝ
«እንዴት?
«እኔ ነኝ የለመንኳት፡፡ እሷ እምቢ ብላኝ ነበር። ለብዙ
ተለማመጥኳት። 'አሁን አሁን ከሞት ጋር ስታገል ነበር፡ ውስጤ
በፍርሀት ተሞልቷል፡ ብቻየን ነኝ፡ የሰው ሙቀት ያስፈልገኛል፣
በጣም ያስፈልገኛል አልኳት። እሺ አለችኝ። ግን እሺ ያለችኝ ብዙ
ከተለማመጥኳት በኋላ ነው»
«ማንኛችሁን ልመን?»
«እኔን
«ለምን?»
«ውሸት አልነግርህማ»
«እሷስ ለምን ውሽት ትነግረኛለች?»
«እንዳንጣላ ብላ»
ዝም አልኩ። ንዴቱ ውስጤ ሲጠራቀም ይሰማኛል
«ከፈለግክም አገጣጥመን» አለኝ፡፡ ቁጣዬን ለመግታት ስል
መዋሽት ጀመርኩ
«ግድ የለም ይቅር። አሁን ስላንተ ንገረኝ አልኩት። ድምፁ
እንደተለወጠ ተሰማኝ
«ይቅርታ አርገህልኛል ማለት ነው?» አለኝ
«እንርሳው» አልኩት
«እፍረት ይሰማኛል። አይንህ ውስጥ ንቀት ይታየኛል»
«ንቀት አይደለም» አልኩት
«ታድያ ምንድነው?»
«ስሜቴን ልግለፅልህ?»
«አዎን»
እኔ ሳላውቀው የተጨበጠ ቀኝ እጄ በፍጥነት ሄዶ አገጩን
መታው:: ከነወምበሩ ወደኋላ ተገለበጠ። እጆቼን እንደ ጨበጥኩ ከበላዩ ቆምኩ፡፡ የተገለበጠው ወምበር አጠገብ እንደተጋደመ ወደ ላይ ያየኛል። ማንኛችንም አልተንቀሳቀስንም። ወደ ላይ እያየኝ ቀስ ብሎ መሀረቡን ከኪሱ አወጣ፡፡ መሀረቡ ውስጥ ተፋ። ደም፡ ቀና
ብሉ ቀይ ፈገግታ ሰጠኝ፡፡ እጁን ዘረጋልኝ። ጨበጥኩት፣ ወደ ላይ
ሳብኩት። በየቦታችን ተመልሰን ተቀመጥን

ካፌው ውስጥ ሌሎች ሰዎች እንዳሉና እንደሚያዩን ገና አሁን
ታወቀኝ። አፈርኩ፡፡ ግምባሬን አላበኝ፡፡ መሀረቤን አውጥቼ
ጠረግኩት። ባህራም እንደገና መሀረቡ ውስጥ ተፋ፡፡ ሳቅ እያለ
«እንደሱ እንኳ ይሻላል» አለኝ
አንድ ነገር አስታወስኩ፡፡ ባህራም ቢፈልግ ነብሴ እስኪመጣ
ሊደበድበኝ ይችል ነበር! እንደገና አላበኝ። በመሀረቤ ጠረግኩት
ከዚህ በኋላ ከባህራም ጋር እንደ ድሮው ማውራት ጀመርን።
የደረሰበትን እጫወተኝ። ኒኮል ማርገዟን ስታውቅ መበሳጨት
ጀመረች፡፡ ባህራም ከስራ ሲወጣ ብስጭቷ እየባሰባት ሄደ።
ሉልሰገድና ጀምሺድ ከሞቱ በኋላ፣ ብስጭቱ ወደ እምባ ተለወጠ፡፡
ማታ ማታ ታለቅሳለች። ባህራም ያባብላት፣ በስጋ ይገናኛትና
ያስተኛታል እሷ ስትተኛ እሱ ሲጋራ አቀጣጥሎ በጨለማው ስለ ኢራን
ያስባል። ከንቱ! ያ ሁሉ ዝግጅት ከንቱ ቀረ፡፡ ያ ሁሉ አመታት
በከንቱ አለፈ፡፡ ማኑ ያ ኢራን ሳሉ የ«ፍሬ አለቃው የነበረ
ስለአምባጓሮ ያስተማረው ውድ ጓደኛው ማኑ በሱ ቦታ ቢሆን
አሁን ምን ባደረገ ነበር? ለመሆኑ፣ ማኑ የት ይሆን? እዚያው
እንግሊዝ አገር ይሆን?
«ይገርምሀል” አለ ባህራም ሲነግረኝ አንድ አስር ቀን ያህል
በተርታ፣ ማታ ማታ ስለማኑ ብዙ ብዙ አሰብኩ። እና አንድ ቀን
ከሱ ደብዳቤ መጣልኝ። አይገርምህም? አድራሻዬን እንዴት እንዳገኘ

«ደብዳቤው ምን ይላል?» አልኩት፡፡

ከኪሱ ሁለት በአረብ ፊደላት የተፃፉ ደብዳቤዎች አውጥቶ
አንዱን ተረጎመልኝ

«ብዙ ብዙ የምነግርህ አለኝ፡፡ ግን በደብዳቤ አይሆንም።ስንገናኝ ነው። እዚህ ለንደን ውስጥ ሶስት ሚልዮን ፓውንድና ኣንድ
ዘመናዊ ማተሚያ ቤት አለን፡፡ ገንዘቡ ከቻይና፣ ከሶቭየት ህብረትና ከሌሎች ወዳጆች የተሰጠን ነው፡፡ ብዙ ሌላ እርዳታም ተሰጥቶናል፡፡
አስራ አምስት ሺ ካላሽኒኮቭ ጭምር! እንግዲህ ጊዜው ደረሰ፡፡
ፎቶግራፍህን ላክልኝና ፓስፖርት ይዤልህ እመጣለሁ። እኔና አንተ
አገራችን እንገባለን፡፡ እዚያ ብዙ ብዙ ስራ ይጠብቀናል። ዝግጁ ነህ?እንዲያው ነው የምጠይቅህ እንጂ ዝግጁ እንደሆንክ እርግጠኛ ነኝ፡፡ይህን ሁለት አመት የት የት ነበርኩ መሰለህ? ፒኪንግ፣ ሞስኮ፣ፕራግ፣ ቡዳፔስት ብቻ ስንገናኝ እነግርሀለሁ። ቶሎ ፎቶህን ላክልኝ»

ባህራም ደብዳቤውን እጥፎ ኪሱ ከተተ። ረዥም ዝምታ ሰዎቹ ካፌው ውስጥ ያወራሉ። አንዷ ኮረዳ ከሽንት ቤት ወጥታ
👍181
ሶስት ጎረምሶች መካከል ተቀመጠች።
«ፎቶህን ላክለት?»
«የለም»
«ምነው?»
«ከሱ ጋር ልሄድ አልችልማ»
«ለደብዳቤው መልስ ፃፍክለት?»
«አዎን። 'ካንተ ጋር ልመጣ አልችልም፡፡ ሀሳቤን ለውጫለሁ'
አልኩት
«መቼ ነበር ይሄ የሆነው?»
«ከአስራ አምስት ቀን በፊት። ዛሬ ሌላ ደብዳቤ ደረሰኝ።
'ሀሳቤን ለውጫለሁ ብትለኝ አላምንህም። ይልቅ ምን እንደሆንክ
ንገረኝ ይላል።»
«ትነግረዋለህ?» አልኩት
«እኔ እንጃ
ዝም ብለን ብዙ ጊዜ ቆየን
ደብዳቤው ከደረሰህ በኋላ ነው እዚህ 'ሰንትራ' ማደር
የጀመርከውን
«እዎን።»
ከኒኮል ጋር ማደር አልቻልኩም፡፡ ለቅሶዋ ሊያሳብደኝ ነው።»
አሁንማ ስትዘጋጅበት፣ ስትጓጓለት የነበረው ስኬት ሲመጣልህ
እኔ ከለከልኩህ፡ ገደልኩህ፣ እኔ አንተን ገደልኩህ!» እያለች ነው
የምታለቅሰው፡፡ አልቻልኩትም፡፡ ባንድ በኩል ቁጭት፣ ባንድ በኩል
የሷ ለቅሶ፡፡ በዛብኝ፡፡»

ካንድ አመት ተኩል በፊት፣ በክረምት፣ ቤቱ ማሞቂያ
ስላልነበረውና የክረምቱ ብርድ ስለበረታበት፣ ካፌ «ሴንትራ» ያድር
ነበር፡፡ አሁን ደሞ የኒኮል እምባ እያባረረው ካፈ ሰንትራ» ያድራል። ሲጋራ እያጨሰ ሲተክዝ ያድራል፡፡ ስለ ኢራን ሲያሰላስል ያድራል። ከንቱ ሀሳብ ሲያወጣ ከንቱ ሀሳብ ሲያወርድ ከንቱ ሌሊቶችን ያነጋል...

💫ይቀጥላል💫
👍92
በሣቅሽልኝ ቁጥር ፣ ወደደችኝ ያልከት፣
ሣቅሽን በፍቅር ፣ እየተረጎምኩት፣
የምወቃቀሰው፣
የምቀዋውሰው፣
እስኪታዘበኝ ሰው።
ጅል አይደለሁ? መቼም
በሣቅሽልኝ ቁጥር ፣ ልቤን ስታሞኒ
ወንድ አይደለሁ? መቼም
ቀልዴን ጨረስኩብሽ ፣ ቤቴ ሳትኾኚ፤
ቀልዱን ለጨረሰ ፣ በወደድሽኝ ተስፋ
በእንባ ላይበተን ፣ከሳቅ የተሰፋ
ቆይ ምን ምን ሆኜ ጃል
በሴት ሣቅ ሞጃጃል?
የጥርስሽ ዘብ ሆኜ ፣ ሞቴ ተወጠነ፤
ቀልዴን መጨረሴሞ ፣ ራሱ ቀልድ ሆነ፤
ቀልድ የጠፋው አዳም፣
ቀልድ ያለቀበት ወንድ፣
ከታዘብሽ ከሰማሽ ፣ ወርደትን ሸክፎ
አትፍረጅ ግድ የለም
ለሴት ጨርሶት ነው ፣ በጥርሷ ተለክፎ፤


🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍19🥰9👏41
#የፍርምባ_ጦርነት


#በአሌክስ_አብርሃም


በንቃት ድንበር እየጠበቅኩ ነው ፤ ጠላት ፊት ለፊቴ አፍጥጧል፡፡ በማንኛውም ሰዓት ወደ እኔ
ሊንደረደር ይችላል፡፡ በመጠኑ ያደፈች ጅንስ ቁምጣዬን ከጉርድ ቀይ ካኒቴራ ጋር ለብሼ ነጠላ
ጫማዬ ከእግሬ ላይ ትበር ይመስል በእግሮቼ ጣቶች በመንከስ ከቤታችን በር ላይ ነው ያለሁት በእጄ ከአቅሜ በላይ የሆነ ብትር ይዣለሁ…የአያቴ የተሰበረ መቋሚያ ነው…መቋሚያውም
የተሰበረው እዚሁ በዓይነ ቁራኛ የምጠብቀው ጠላት ጀርባ ላይ ነበር :: አባቶቻችን ያወረሱንን
ጠላት አያቶቻችን ባወረሱን ሰባራ መቋሚያ እየተከላከልሁ ነው፡፡
ነገ በዓል ነው፡፡ ቤታችን ትንሽ ጠቦት ታርዶ ቤቱ ስጋ ስጋ ይሸታል፡፡ እናቴ ቤቱን እና ስጋውን
እንድጠብቅ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥታኝ ገበያ ሄዳለች፡፡ በዋናነት የተሰጠኝ ተልዕኮ፣

1. ዶሮዎች የተሰጣውን የሽሮ ክክ እንዳይበትኑ

2. ሌባ ወደቤታችን እንዳይገባ

3ኛው እና ዋናው…“ገንባው እዚህች ግድም ድርሽ እንዳይል…” ነው፡፡ (እዚህች ግድም ድርሽ
እንዳይል ? ማን ? ገንባው !!)

ዶሮዎች ስጡ አካባቢ መለቃቀም ይችላሉ፡፡ ስጡን መብላትም ሆነ መበተን ግን የለባቸውም፣…
ሌባ በአጥራችን ጥግ መሄድ ይችላል፣ “ደህና አደራችሁ” ብሎም ማለፍ አይከለከልም፡፡ ሰላምታ የእግዜር ነው ትላለች እናቴ….ዕርግጥ ሲደጋግሙባት ሦስት ጊዜ እንዴት አደራችሁ አንዱ ለነገር ነው ትልና የእግዜር ሰላምታ መደጋገም ባለቤትነቱ የሰይጣን ሊሆን እንደሚችል በተዘዋዋሪ
ትናገራለች፡፡ እና ሌባው እስካልደጋገመ ድረስ ሰላም ብሎ ማለፍ ይችላል፡፡ ገንባው ግን
እዚህች ግድም ድርሽ ማለት የለበትም :: መላ ሰላም ማለት ሁሉ አይችልም፡፡ ሰላምታውን
ደገመም አልደገመም ፤ በቃ የበላይ ትዕዛዝ ነው !!
ገንባው በመንደራችን የሚኖር ባለቤት የሌለው ትልቅ ድመት ነው :: የበግ ግልገል የሚያክል
ዥጉርጕር ድመት ! እኔ ከተቀመጥኩበት አንድ አስራ አምስት ሜትር ራቅ ብሎ ከኋላው ሸብረክ በማለት ሁለት የፊት እግሮቹን ቀጥ አድርጎና ደረቱን ነፍቶ ጉርድ ፎቶ ሊነሳ ፎቶ አንሽ ፊት የተቀጠ ጎረምሳ መስሎ ቁሟል ፡፡

ተራ ድመት እንዳይመስላችሁ.. በሰፈራችን ውስጥ ያልገለበጠው ድስት፣ ያልከፈተው መሶብ፣
የመንጠቅ ሙከራ ያላደረገበት የስጋ ዘር የለም፡፡ መንደራችን ውስጥ ዶሮም ይሁን በግ ሲታረድ
ገንባውን ጠባቂ ቃፊር ማቆም ቸል የማይባል ጉዳይ ነው፡፡ “ገንባው ሲመቸው ቆሞ ከሚሄድ
በግ ሳንባ ይመነትፋል” ይሉታል..ሞኝ ሰፈርተኞች!! ታሪክ የሚተነፍሱበትን፣ የተዓማኝነት
ሳንባቸውን በቁማቸው እንደመነተፉቸው ማን በነገራቸው::

ገንባው ግዙፍ ቢሆንም የተጎሳቆለና በእድሜ የገፋ ድመት ነው:: ትንሽ ያነክሳል፡፡ በዛ ላይ
ዓንድ አይን የለውም፡፡ ጅራቱም ቆራጣ ነው፡፡ ሲጮኸ ድምፁ ያስፈራራል፡፡ እማማ ብርዘገን
ለፋሲካ የገነጣጠሏትን ዶሮ ላጥ አድርጎባቸው ሲሮጥ ጉሮሮውን በቢለዋ ወግተውት ነው ድምፁ
ተበላሽቶ የቀረው፡፡ የዛሬን አያድርገውና "ሚያውውውው" ሲል የአይጥ ሰራዊትን የሚያርድ፣
ሴት ድመቶችን የሚያማልል ድምፀ መረዋ ድመት ነበር ::

ድሮ የጋሽ ታምሩ ድመት ነበረ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ፍርምባ የሚባል ነገር ሰረቀ ብለው አባ ታምሩ በአንካሴ ወጉት፡፡ ከዛ በኋላ እሳቸው ቤት መኖር አቆመ፡፡ ጨካኝ ናቸው:: ፍርምባ
ለምታክል ስጋ ብለው…ተወልዶ ካደገበት ቤት አባረሩት ፣ ያውም በአንካሴ ወግተው፡፡ እሳቸው
ግን፣ “ድመቱን ለፍርምባ ብዬ አልወጋሁትም” ብለው ዋሹ፡፡ ትልቅ ሰው ይዋሻል ? ደግሞ
እኮ ያኔ የሆነውን ሁሉ በዓይኔ በብረቱ አይቻለሁ…ማሪያምን አይቻለሁ !

ድመቱ ፍርምባውን በአፉ እንጠልጥሎ መሬት ለመሬት እየጎተተ እኛ ቤት ፊት ለፊት ወዳለው የውሃ መውረጃ ቱቦ ሲሮጥ አባ ታምሩ ልክ እንደኦሎምፒክ ተወዳዳሪ ግራ እጃቸውን ወደፊት ቀስረውና ጦር የጨበጠ ቀኝ እጃቸውን እስከቻሉት ድረስ ወደኋላ ለጥጠው በሰፋፊ ርምጃዎች
ተንደረደሩ 1..…2..3..ጦሩን ዥው ...አደረጉት፡፡ ድመቱ ሲሮጥ ጦሩ ሲከተለው፣ ጦሩ ህይወት ያለው ይመስል ነበር፡፡ ልክ ቱቦው ጫፍ ላይ ሲደርስ የድመቱ የኋላ እግር ታፋ ላይ ጦሩ ተቀበቀበ…አቤት ገንባው እንዴት አሰቃቂ ጩኽት እንደጮኸ ..እንዳንቡላንስ
ነው የጮኸው ሚያያያያያያያያያያያያያ…! ሲጮህ በአፉ የያዘው ፍርምሳ ወደቀ፡፡ አንድ ነጭ ያልቆሰለም ያልተወጋም ድመት ቀልቦት ወደቱቦው ውስጥ ጥልቅ አለ…!!

ጎረቤቱ ሁሉ፣ “አቤት አጨካከን እናትዬ የእግዜር ፍጡር ነው…ምን በደለ ?” እያለ ሲያጉረመርም
አባ ታምሩ ታሪክ ፈጠሩ፡፡ “የልጅ ልጄን ዓይኗን ሊያወጣት ነበር እኮ፣ ግዴላችሁም ይሄ ድመት
አውሬ ሆኗል...” በማለት የፍርምባውን ፀብ ትውልድ ለማዳን የተደረገ ጦርነት አስመሰሉት፡፡

የሚገርመኝ ታዲያ የመንደሩ ሰው ነው፡፡ በወሬ ወሬ “ ይሄ ድመት ምን ሆኖ ነው የሚያነክሰው?
ሲባል ፤ ..."ይሄ አውሬ ነው ጋሽ ታምሩን የልጅ ልጅ ዓይኗን ሊያወጣ ሲል አያቷ ሃይሌ
በአንካሴ ወጉት” ይላል :: ጭራሽ አይጦቻቸውን እያሳደደ እንዳልፈጀላቸው አውሬ የሚል
ስም ሰጡት ለዚህ ሚስኪን ገንባው !!

ትልልቆቹ ሰዎች ሁሉ፣ ፀጉራቸው የሸበተው አስተማሪው ሰውዬ (ትልቁ ግቢ ቤት ውስጥ የሚኖሩት
ሳይቀሩ ይሄን የፈጠራ ታሪክ ያወራሉ፡፡ታዲያ ስለ አገር ታሪክ እናውራ ሊሉ አላምናቸውም
ትላንት አፍንጫቸው ስር ያውም በጠራራ ፀሐይ የተፈፀመ የድመት ታሪክ ወጊው በፈለጉበት መንገድ
የተረኩ ሁሉ ስለአገሬ ታሪክ
እናውራህ ሲሉኝ እንዴት ልመናቸው? በመደራቸው
የድመት ታሪክ ያልታመኑ ሁሉ ስለአገራቸው አንበሶች ጀብዱ ሲደሰኩሩ እንዴት ልቤ እሺ ብሎ
ይቀበል ?ታሪክ ማውራት ታሪክ ከመስራት እኩል ጀግንነት እንደሚጠይቅ የገባኝ ያኔ ነው

ከዛን ቀን ጀምሮ ጦርነቶች ሁሉ የአደባባይ ምክንያታቸው ምንም ይሁን ምን ከኋላቸው ፍርምባ
የሚባል ስጋ ያለ ይመስለኛል፡፡ ገንባው አውሬ አይደለም፡፡ ገንባው የከለከሉትን የዕለት እንጀራ ነጥቆ “ተመስገን” የሚል ሚስኪን ድመት ነው፡፡ የዕለት እንጀራውን ቢነጥቃቸው የዘላለም
ስሙን ነጠቁት፡፡ “ያኔ ባንካሴ ሳንወጋው ኖሮ ትውልዱ ሁሉ እውር በሆነ እያሉ ከድመት
ጥፍር በባሰ የውሸት ጥፍራም ታሪከ ጭፍን ትውልድ ይፈጥራሉ፡፡

በሀሳብ ካቀረቀርኩበት ቀና ስል ገንባው የለም፡፡ “በስማም የት ሄደ ሰባራ መቋሚያዬን ወድሬ ወደ ጓዳ ሮጥኩ፡፡ መስኮቱ ገርበብ ብሏል፡፡ የጠቦቱ ታፋም ተሰቅሎ በነበረበት ቦታ የለም፡፡ .…ወይኔ ጉዴ ዛሬ እናቴ ገደለችኝ በቃ::

ሮጬ ወደ ውጭ ስወጣ ገንባው ታፋውን እየጎተተ ወደ ቱቦው ጥልቅ ሲል አየሁት፡፡

“ወይኔ አንካሴ ኖሮኝ በነበር..ይሄን አውሬ አልለቀውም ነበር" አልኩ ለራሴ፡፡


አለቀ
👍32👏4
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....ካንድ አመት ተኩል በፊት፣ በክረምት፣ ቤቱ ማሞቂያ
ስላልነበረውና የክረምቱ ብርድ ስለበረታበት፣ ካፌ «ሴንትራ» ያድር
ነበር፡፡ አሁን ደሞ የኒኮል እምባ እያባረረው ካፈ «ሴንትራ»
ያድራል። ሲጋራ እያጨሰ ሲተክዝ ያድራል፡፡ ስለ ኢራን ሲያሰላስል
ያድራል። ከንቱ ሀሳብ ሲያወጣ ከንቱ ሀሳብ ሲያወርድ ከንቱ
ሌሊቶችን ያነጋል

ያን ሰሞን የሲልቪ መፅህፍ ለሶስተኛ ጊዜ እምቢ አለ።
ለሶስተኛ ጊዜ አባረረችኝ። እኔም መፃፍ አቃተኝ፡፡ እንዴትስ ላያቅተኝ ይችላል? ሲልቪ በጉልህ ሰማያዊ አይኖቿ ብርሀን ካላየችኝ፡
በውብ ሰፊ አፏ ሙቀት ካልሳመችኝ፣ ሰለስላሳ ገላዋ ካላቀፈችኝ እንዴት ልስራ እችላለሁ? መስራቱን ተውኩት
ዩኒቨርሲቲው አጠገብ ያለው መናፈሻ ውስጥ የኤክስ አዛውንት
በስጋው አቧራ ውስጥ “boule” ሲጫወቱ፡ በኮሚክ የደቡብ
ፈረንሳይኛቸው እየፎከሩ አንዷን የብረት ኳስ በሌላ እያነጣጠሩ
ወርውረው እየገጩ እየተሳደቡ ወይም እየተሳሳቁ ሲንጫጩ አያለሁ
ከዚያ ወደ ኩር ሚራቦ ሄጄ Monoprix የተባለው ትልቅ ሱቅ
ፊት ለፊት ከአንዱ ሽማግሌ ወይም ከአንዷ አሮጊት አጠገብ
አግድም ወምበር ላይ እቀመጥና፣ የኤክስ ሚስቶችና እናቶች
ከመንገዱ ወደ ሱቁ እየገቡ፣ ከውስጥ “Monoprix የሚል
የታተመባቸው የሞሉ ቡኒ የወረቀት ከረጢቶች ይዘው ወደ መንገዱ ሲጎርፉ አያለሁ፡፡ አስተያየታቸውም ሆነ አለባበሳቸው ወይም
አረማመዳቸው የጎረምሳ አይን አይስብም፡፡ ድሮ የጎረምሳ አይን
ስበው፣ ፍቅረኛ ይዘው፣ አግብተው ወልደው በቅቷቸዋል። አሁን
ወይም አርጅተዋል፣ ወይም ወፍረዋል ወይም ተዝረክርከዋል
ኮረዳዎቹ ጡታቸውን አሹለው! ዳሌያቸውን አሳብጠው፤
አይናቸውን ተኩለው፣ ፀጉራቸውን ተሰርተው ሽቶ አርከፍክፈው
እጅጌ የሌለው የበጋ ልብስ እየለበሱ፣ የብብታቸውን የተለያየ ከለር ፀጉር እያሳዩ፣ በጎረምሳ ታጅበው እየሳቁ እያወሩ በኩር ሚራቦ ይመላለሳሉ፡፡ ወይም ካፌዎቹ በር አጠገብ መንገዱ ላይ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው ግማሽ ጭናቸውን እያሳዩ ልዩ ልዩ ቀዝቃዛ
እየጠጡ ያወራሉ

አሮጊቶቹና ሽማግሌዎቹ አግድም ወምበር ላይ ፈዘው ቁጭ
ብለው ፀሀይ ይሞቃሉ። እኔም ቁጭ ብዬ ስለሲልቪ ስለባህራም፣ስለኒኮል፣ ስለሉልሰገድ፣ ስለአማንዳ እያሰብኩ አላፊ አግዳሚውን
እመለከታለህ
ሲልቪ መቼ መጥታ ወደ እቅፏ ትጠራኝ ይሆን? ጊዜው አላልፍልህ ይለኛል። ወደ ዘጠኝ ሰአት ላይ ሲኒማ " እገባለሁ።
ከሲኒማ ወጥቼ አንዱ ካፌ እሄድና ኣንድ ቢራ ጠጣለሁ

አንድ ቀን ወደ አስራ ሁለት ሰአት ላይ ነበር። ሰማዩ ቀልቶ፣
ፀሀይዋ እንደ ቀይ ብርቱካን ከምእራባዊው አድማስ በላይ
ተንጠልጥላለች፡ ግን ገና አትጠልቅም፡ እስከ ሁለት ሰአት ተንጠልጥላ ኤክስን ታስውባታለች
አየሩ የሚለሰልስበት ጊዜ፣ ብቸኝነት የሚፈለግበት ሰአት ነው፡
የትዝታ የትካዜ ሰአት
ካፈ ኒኮል ሄድኩና በረንዳው ላይ ፊቴን ወደ ፀሀይዋ አድርጌ ቁጭ ብዬ ቡና አይነቱን ቢራ አዘዝኩ፡፡ አሮጊቷ ቢራውን እያቀረቡልኝ
"Ça fait longtemps qu'on vous a pas vu monsieur" አሉኝ ብዙ ጊዜ ሆነን ካየኖዎት)
Oui, madame." አልኳቸው
ጓደኛዎትስ ደህና ናቸው?»
ደህና ነው። አገሩ ገብቷል
ትምህርታቸውን ጨረሱ?»
"Il était tres gentil, votre ami“ (በጣም ጥሩ ሰው ነበር ጓደኞት")
"Oui, madame"
አሮጊቷ ሄዱ፡፡ ብቻየን ቀረሁ፡፡ ከቀይዋ ፀሀይ ጋር፣ ከቡናማው
ቢራ ጋር። ከሉልሰገድ ትዝታ ጋር መንግስተ ሰማያት ማለት
ሴት በየዛፉ ስር፣ በየግድግዳው ጥግ የሚበቅልበት ማለት ነው
አየህ፣ የኒኮል ጡት እንደ ነጭ ውብ ሰማይ ነው፡፡ ሰማዩ መሀል ላይ በሮዝ ቀለም የተከበበች ወይን ጠጅ ጨረቃ አለች እኔ 'ምልህ! ከኒኮል ጋር አልጋ ላይ የወጣህ ጊዜ' በቅዱስ ብልግናዋ ትባርክሀለች
አይ አንተ ባላገር መባዳት ቁላን እምስ ውስጥ መክተት ይመስልሀል። ስንት ሳይንስና ስንት አርት እንዳለው ባወቅክ! ኒኮልን
በቀመስክ!.....
ፀሀይዋን ከለለኝ፡ ከሉልሰገድ ነጠለኝ፡፡ ቀና ብዬ አየሁት፡፡
ባህራም። አጠገቡ አንድ ቀጭን ባለመነፅር ሰውዬ ቆሟል። ቁመቱ
ከባህራም ትንሽ ይበልጣል። ያገሩ ልጅ ይመስላል ብድግ አልኩ፡፡ ሰውዬው ፈገግ አለ። ፈገግታው ደስ ይላል። የልጅ ፈገግታ ይመስላል። እጁን እየዘረጋ፣ በጣም ወፍራም በሆነ
ድምፅ በእንግሊዝኛ ከለንደን መምጣቴ ነው አለኝ
ጨበጥኩት፡፡ አጨባበጡ ልዩ ሆኖ ተሰማኝ። እጁ አይመችም።
በኋላ ሳየው መሀል ጣቱ ወደ አንድ በኩል ተጣሟል አይታጠፍም።ሌሎቹ ጣቶቼ ረዣዥም ቀጭን ቆንጆ ናቸው
እንኳን ደህና መጣህ!» አልኩት። ቁጭ አልን፡፡ባህራም ግን አልተቀመጠም። እኔን «ይሄ ማኑ ነው።የፈለግከውን ልትነግረው ትችላለህ» አለኝና ወደ ካፌው ውስጥ ገባ የማኑ ግምባር በጣም ጠባብ ነው: ወደኋላ የተበጠረው ፀጉሩ ከቅንድቦቹ ጋር ሊገናኝ ምን ያህል አይቀረው
ሳቅ አለ፡፡ የላይኛ የፊት ጥርሱ ሁለቱ የራሱ አለመሆኑን አስተዋልኩ ሰው ሰራሽ የአጥንት ጥርስ ነው። ጥያቄው አመለጠኝና

ጥርሶችህ የት ሄዱ?» አልኩት። የልጅ ሳቁን እየሳቀ ሰባራ
መሀል ጣቱን በግራ እጁ እያሻሸ
“አገሬ ትቻቸው መጣሁ:: እስር ቤት ውስጥ ኣለኝ፡፡ ወፍራም
ድምፁ ውስጥ መመረር አያሰማም፡፡ ሲስቅ ከመነፅሩ ኋላ አይኖቹ ጥፍት ይላሉ

«አህ! » አልኩት፡፡ ምን ማለቴ እንደሆነ እንጃ

«አሁን ጥርሶቼን ፍለጋ አገሬ መመለስ አለብኝ፡፡ ባህራም
ቢያፋልገኝ ቶሉ አገኛቸው ነበር። እሱ ግን ኣላግዝህም አለኝ»

«የጥርስ ኣዳኝ መሆን አልፈልግም አለ? »

“እህስ! ያውም የኔን የጓደኛውን ጥርሶች! አይገርምህም?»
በጣም እንጂ» ይሄ ምን አይነት ንግግር ነው? የሚል ሀሳብ
ጨረፈኝ

“ካንተ ጋር ብተዋወቅና በሰፊው ባወራ ደስ ይለኝ ነበር። ግን
እቸገራለሁ። ጥርሶቼ ናፍቀውኛል» አለ። ይስቃል
«ይገባኛል» አልኩት እየሳቅኩ
ባሀራም እንደሚያስፈልገኝስ ይገባሀል?»
“አዎን"
ሳቁ ከፊቱ ጠፋ፡፡ ጉንጮቹ ወደ ውስጥ የጎደጎዱ ናቸው፡፡ በብዙ
የሚመገብ አይመስልም። ቆንጆ ጣቶቹን አየሁዋቸው፤ ንፁህ ናቸው፤ የሲጋራ ልማድ አልተለጠፈባቸውም

አሮጊቷ ሲመጡ ማኑ ቀዝቃዛ ወተት አዘዘ፡፡ አንዲት ኮረዳ
ባጠገባችን ስታልፍ ሽቶዋ አንድ ጊዜ አወደን፡፡ ነጭ ሸሚዝና
ሰማያዊ ቁምጣ የለበሰው ቅርፅዋ አይን ይማርካል፡ የሚወዛወዝ ዳሌዋ ያስጎመጃል፡፡ ማኑ አይኑን ጣል አረገባት፡ ያኔውኑ ረሳት፡ ወደ
ካፌው ውስጥ እስክትገባ በአይኑ አልተከተላትም። ለምግብም፤
ለሲጋራም፣ ለመጠጥም፡ ለሴትም ጊዜ ያለው አይመስልም። ጊዜውን
በሙሉ ለሬቮሉሽኑ መድቧል? ስራውም፤ ጨዋታውም፣ እረፍቱም
ያው ሬቮሉሽን ይሆን?
እንዲህ አይነቶቹ ታጥቀው ሲነሱ፤ በሁለት አመት ውስጥ ሞስኮ፤ ፒኪንግ፣ ቡዳፔስት ወዘተርፈ እየዞሩ ሶስት ሚልዮን
ፓውንድና አስራ አምስት ሺ መትረየስ የሚያከማቹ ጎልማሶች
ታጥቀው ሲነሱ፡ እስር ቤት ውስጥ ጣታቸው ተሰብሮ ጥርሳቸው
የተሽረፈ ሰዎች ታጥቀው ሲነሱ፣ ለሴትም ለመጠጥም ጊዜ የሌላቸው ጎረምሶች ታጥቀው ሲነሱ፡ የኢራን ሻህ ለምን ያህል ጊዜ ዙፋኑ ላይ ሊቆይ ይችል ይሆን?

ማኑ እንዲህ አለኝ
👍311
«ባህራም እዚህ አገር ውስጥ ደምበኛ ስራ ለመያዝ የሚያበቃ
ትምህርት ወይም የሙያ ችሎታ የለውም፡፡ ግፋ ቢል አንድ ፋብሪካ
ውስጥ ይቀጠራል፡፡ ሲሰራ ውሉ ማታ ሲጠጣ ያመሻል። እኔ
ወደምሄድበት አብሮኝ ለመምጣት አለመቻሉ እየቆጨው ይሄዳል።
ከሁለት አመት በኋላ ዋና ሰካራም ይወጣዋል' ራሱን አይጠብቅም'
ማንንም አይጠቅም፡፡ ልጅቱም . ኒኮል ነው ስሟ? እሷም
ሲበላሽ እያየች ትንቀዋለች፡፡ አበላሸሁት ብላ ፀፀት ውስጥ መኖር ትጀምራለች። ትንሽ ቆይታ ፍታኝ ትለዋለች። ኑሮው በሙሉ ፈሩን ሳተ ማለት ነው

«ከኔ ጋር የመጣ እንደሆነ ግን »

«ይህን ሁሉ አውቃለሁ'ኮ» አልኩት

«እንግዲያው አግዘኛ! እሱንም እግዘው። በዚያውም በሀያ
ሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ታግዛለህ»
ላግዝህ መቻሌን እንዴት ታውቃለህ?» አልኩት
«ማወቁንማ አላውቅም፡፡ ምናልባት ብትችል ብዬ ነው " እንጂ።
አየህ! ባህራም ያስፈልገናል። በጣም ያስፈልገናል። ለሱም የኛ
አይነት ኑሮ ያስፈልገዋል»

«ላግዝህ የምችል አይመስለኝም። ግን አንድ እኔ የማውቀው
ነገር አለ። ምናልባት ሊረዳህ ይችል ይሆናል»
«ንገረኝ»
ግን እኔ ማወቄን ባህራም እንዳያውቅ»

«ግድ የለህም»

ስለኒኮል ስለሉልሰገድና ስለጀምሺድ የማውቀውን
አጫወትኩት። ጭንቅላቱን አስር ጊዜ ወደ ላይ ወደ ታች እየነቀነቀ
በፀጥታ አዳምጠኝ፡፡ ነግሬው ስጨርስ፡
“ገባኝ። እንኳን አንተን እገኘሁህ!> አለኝና ተነሳ። እኔም ተነሳሁ፡፡ ባህራም ከካፈው ውስጥ መጣ። ማኑ እየጨበጠኝ
(የተጣመመች ጣቱ እየቆረቆረችኝ
ልታግዘኝ ባለመቻልህ አዝናለሁ። ደህና ሁን አለኝ
ከባህራም ጋር ጎን ለጎን እየተራመዱ ከኔ ራቁ። ማኑ ትንሽ
ትንሽ ያነከሳል። ከበላያቸው ሰማዩ ደም ለብሷል ቅድም ወደ ካፌው የገባችው ባለቁምጣ ልጅ ወጣች።
ስትራመድ የውብ ቂጧን ከፍ ዝቅ በአይኔ ተከተልኩ። አይቼው
የማላውቀው የኒኮል ቂጥ ትዝ አለኝ። አየህ የኒኮል ቂጥ
እንድያው ለመቀመጫ የተፈጠረ ቂጥ እይደለም፡ የውበት ክምር
ነው። አንዳንዴ አልጋው ላይ በሆዷ እስተኛትና ያንን ቂጧን
አየዋለሁ' አየዋለሁ' አየዋለሁ! አይቼ አልጠግበውም፡፡ እያየሁት
በእጀ እንዲህ፣ እንዲህ' እያደረግኩ እዳብሰዋለሁ፡፡ ጎምበስ ብዬ
እንደ ቤተ ክርስትያን እስመዋለሁ። አይተህልኛል የኒኮልን
አይኖች? አረንጓዴ የውበት ሀይቆች የሀዘን ሀይቆች። አቤት
አይኖቿ ውስጥ ያለው ሀዘን ሲያምር. , ,

የኒኮል ውበት ለባህራምም እንዲህ ጎልቶ ይታየው ይሆን?
እግዲህ ከኒኮልና ከማኑ ማን ያሸንፍ ይሆን?

ለመሆኑ የዚህ የማኑ አለም ውስጡ እንዴት ያለ ይሆን?
የመጠጥ ሙቀትና የኮረዳ ትኩሳት የሌለበት አለም አይቀዘቅዝም?
ወይስ ቀዩ የሬቮሉሽን ኮከብ ዘለአለማዊው የሳጥናኤል ኮከብ ንፁህ ሙቀትና ውብ ትኩሳት ይሰጠው ይሆን? እነካስትሮ እነሆቺሚን እነማኦ በወጣትነታቸው እንደማኑ ነበሩ? ወይስ እንደ ባህራም ነበሩ?
፣ እንደ ባህራም ቢሆኑ ኖሮ እንደ ኒኮል ያለች ውብ ኮረዳ
ግማሽ መንገድ ላይ አታስቀራቸውም ነበር? ወይስ ግርማዊው
የሳጥናኤል ኮከብ በቀይ ብርሀኑ ከሩቅ ሲጠራህ፣ ከለስላሳ የሴት ልጅ ጭን ሙቀት ወጥተህም ቢሆን ጥሪውን ማክበርህ አይቀርም ይሆን? እስቲ እናያለን

ቀዩ ሰማይ እየጠቆረ ሄደ፡፡ ካፌው ውስጥ መብራት በራ። ሌላ
ቢራ ኣዘዝኩ፡፡ ስለኒኮል ማሰብ ጀመርኩ፡፡ በጭለማው ኣልጋ ውስጥ ተቃቅፈን፣ እጄን ሙታንቲዋ ጠርዝ ላይ ሳሳርፍ ትዝ አለኝ።የፍትወት ትኩሳት ጀመረኝ። ያን ሰሞን እርግዝናዋ አፋፍቷት፣
ከመቸም የበለጠ ታምራለች። በበጋው ሙቀት በዝግታ ስትራመድ የግብረ ስጋ እመቤት ትመስላለች፡፡ ባየኋት ቁጥር ፍትወት ያቁነጠንጠኛል። ለመሆኑ፣ ማኑን ስለነሉልሰገድ ያጫወትኩት ለምን ኖሯል? ባህራም ሄዶ የሚወደውን ሬቮሉሽን እንዲቆሰቁስ ነበር?
ወይስ ባህራም ሄዶልኝ እኔ ኒኮልን እንድቆሰቁስ ነበር? ወይስ
ሁለቱም ነበር?
ማታ አምስት ተኩል ላይ ከሲኒማ ስወጣ፣ ሲልቪን በሩ ላይ
አገኘሁዋት። ሳያት ከመጠን በላይ ደስ አለኝ፡፡ ፈራሁ። እቺን ልጅ
እንዴት አድርጌ ልለያት እችላለሁ? ፈገግታዋ ልቤን አሞቀው።
የተዘረጋ ቀኝ እጂን በግራ እጄ ተቀብዬ እያሻሽ እንዴት ታምሪያለሽ!» አልኳት
«ዛሬ ከኔ ጋር ማደር ትፈልጋለህ?»
«በጣም! ታድያ ግን እንቅልፍ አልፈልግም»
«ካልክስ እኔም አልፈልግም
መኪናዋ ጋራዥ ገብታ ስለነበረ፣ ወደ ቤቷ ስንራመድ፣
ትከሻዋን እያቀፍኩ
«እንዴት አገኘሽኝ?» አልኳት
እየሳቀች ሲቲ ሄጄ ኣጣሁህ፡፡ ስለዚህ ሲኒማ ቤት ሳይሆን
አይቀርም አልኩ፡፡ የኢጣልያ ፊልም የሚታይበት መሆን አለበት
አልኩ፡፡»
“A la Sherlock Holmes, quoi!” አልኳት (በሸርሎክ ሆምዝ ዘዴ ነዋ)
እየተራመድን፣ ዳሌዋ በአንዱ እርምጃ እየተጠጋኝ በሌላው
እየራቀኝ፡ እየራቀኝ እየተጠጋኝ እየራቀኝ፣ የጫማዋ ኳኳ
እየተሰማኝ
«ደስ ይለኛል» አለችኝ «እየሄድን እጅህን ራሴ ላይ ስታሳርፈው
በሀይል ደስ ይለኛል። እጅህ ከክፉ የሚከልለኝ ይመስለኛል፡
የሚባርከኝ ይመስለኛል፡፡ ካንተ ጋር ባልሆንኩ ጊዜ ሳስብህ፣
መጀመሪያ ትዝ የሚለኝ እጅህ ራሴ ላይ ሲያርፍ ነው»
እየተራመድን እጇን ሳምኩት
«አሁን የሳምከው የተራ ሰው እጅ እንዳይመስልህ» አለችኝ፣
ደራሲ እጅ ነው»
የውብ ደራሲ እጅ ነዋ ያውም!» አልኳት
«እውነቴን'ኮ ነው። ዛሬ ከኤዲስዮን ግራሴ (Editions Grasset) ደብዳቤ ደረሰኝ። አስራ ሶስቱ አንተ የመረጥካቸው አጫጭር ልቦለዶቼ Treize de Sylvie ተብለው ሊታተሙ ነው።»
«ውሽትሽን ነው!»
«መፅሀፉ ለሚመጣው ፀደይ ይወጣል»
«ማርሰይ እንሂድ?» አልኳት
«ለምን?»
«ይህን ግሩም ቀን ማክበር አለብን። ይገባሻል? እንግዲህ'ኮ
ስምሽ ከነፍራንስዋዝ ሳጋን፣ ከነኮሌት ጋር ሊጠራ ነው:: ቀስ ብሎ ከነፍሉብር፣ ከነፕሩስት፣ ከነማልሮ ጋር ይጠራል»
«ይመስልሀል?»
«እርግጠኛ ነኝ»
«እንዴት ጥሩ ነው!»
«ብቻ እንዳልኩሽ ነው:: የመሰለሽን ሁሉ ሳትፈሪ ፃፊ»
«አልፈራም። በጭራሽ አልፈራም»
«እንደሱ ነው! አሁን ማርሰይ እንሂድ?»
«የለም። ቤት እንሂድና በሩን ቆልፈን ራቁታችንን ወጥተን
እንዳንድ ቀኑ እንሰሳዎች እንሁን። በሀይል ናፍቀኸኛል።
«እኔም በሀይል ናፍቀሽኛል»
"Parole d'honneur?"
“Parole d'honneur! እጅሽን አምጪ እስቲ። አይታወቅሽም?»
«ይታወቀኛል። ለኔ ነው እንዲህ እሚዘለው?»
«ላንቺ አይደለም፡፡ ለእንትንሽ ነው»
ሳቀች፡ ቅንዝረኛ የጉሮሮ ሳቋን ሳቀች
ከኤክስ ወጣ እንዳልን
«ባህራም ሰውየውን የገደለው እዚችጋ ነበር» አለች። ትንሽ ሄድ
ካልን በኋላ «እኔ እዚችጋ ነበርኩ»
«ከዚያ ቤትሽ ወሰድሽው»
እየተጠጋችኝ «አዎን» አለች
«ከዚያስ?»
«ከዚያማ የሆነውን ነግሬህ የለ?»
«የነገርሽኝ በሙሉ እውነት ነበር?»
«አዎን»
«ባህራም ግን እኔ ነኝ በብዙ ተለማምጭ እሺ ያሰኘኋት እንጂ
እሷስ እምቢ ብላኝ ነበር» አለኝ
«ውሸቱን ነው»
«ለምን ይዋሻል?» አልኳት
«እንዳያጣላን ፈርቶ፡፡
«አንቺ አለመዋሸትሽን በምን አውቃለሁ?»
«እኔ ለምን እዋሻለሁ? ታውቀኝ የለ? ስንትና ስንት ጉድ
አውጥቼ ነግሬህ፣ እዚች ላይ ውሸት እነግርሀለሁ? ይመስልሀል?»
👍23
«ከዚያ በኋላ ተገናኝታችሁ ታውቃላችሁ?»
«የለም»
“ምነው? እምቢ አልሽው ወይስ እምቢ አለሽ?»
ሁለታችንም ተውነው»
«ለምን?»
«እሱ ላንተ ሲል ይመስለኛል»
«አንቺስ?»
“እኔም ላንተ ስል ይመስለኛል። ግን እርግጠኛ አይደለሁም፡፡»
«እንዴት?»
«ተለውጫለሁ መሰለኝ። ለምሳሌ ከፓሪስ ከተመለስን ካንተ ሌላ
ማንም ወንድ አልሄድኩም፡፡ በፈት ግን ካንተ ሌላ በሳምንት ቢያንስ
አንድ ወንድ ካልቀመስኩ አይሆንልኝም ነበር። ፓሪስ ሆነን ሌሎቹ ጋ እየሳክከኝ የራስህ የብቻህ አደረግከኝ መሰለኝ
«ሌሉቹ ጋ እየሳክኩሽ የብቻዬ አደረግኩሽ?»
«አትሳቅ፡፡ እኔ የምሬን ነው:: በፊት፣ ሌላ ወንድ እያሰብኩ
እንዳቅፍህ ስለፈቀድክልኝ እንደ ልቤ አደረግኩትና ጠገብኩት።
አሁን ማንንም ሳቅፍ ሌላ ሰው ማሰብ የለብኝም፡፡ ድኛለሁ። ሙሉ
ነፃነት ስለሰጠኸኝ ነገሩን ጠገብኩትና ወጣልኝ፡፡ አሁንም እንደሱ አርገህል መሰለኝ።»
«እንዴት ማለት?»
«ፓሪስ ሆነን እንደ ልቤ ወንድ እንዳሳድድ ፈቀድክልኝ፡፡ ወንድ
እያቀያየርኩ እስኪደክሙኝ ተደስቼ ስመለስ፣ በሙሉ ልብህ
ተቀበልከኝ። ስትቀበለኝ ጊዚ ወንድ መለዋወጡ ክልክል መሆኑ ቀረ።
ስለዚህ ሰለቸኝ፣ ጠገብኩት፡፡ ተውኩት ይመስለኛል።»

«እርግጠኛ ነሽ?»

“እርግጠኛ ለመሆንማ ጊዜ ያስፈልገኛል። ግን የሚገርም ነገር
ነው። ሙሉ ነፃነት ስለሰጠኸኝ ታሰርኩ፡፡ አይታይህም?»
«መታሰርሽን ገና አላወቅነውም» አልኳት ለመቀለድ እየሞከርኩ
«እኔ አውቄዋለሁ፡፡ ለምሳሌ፡ ከዚህ በፊት መፅሀፌ " እምቢ
ሲለኝ፣ አንተን አባርሬ ምን ነበር የማረገው መሰለህ?»....

💫ይቀጥላል💫
👍221
#ተሸከመናታል !!


#በአሌክስ_አብርሃም


እናቴ ሁልጊዜ እንድናጠና ስትመክረን እንዲህ ትላለች፡-

እናንተ ልጆች አጥኑ፣ ተማሩ እባካችሁ ! ..እኔ ባለሙማሬ ነው ጉዴን ተሸክሜ የዋልኩት፤”
ማንበብም መፃፍም ስለማትችል ንግግሯ በቁጭት ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ይሄ ተሸክማ የዋለችው ጉድ ምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቼ ጠየቅኳት፣
“ማሚ የምን ጉድ ነው ተሽከመሽ የዋልሽው ?”
አወራችኝ…


በደርግ ጊዜ መስከረም ሁለት ቀን ሕዝቡ በግድም ሆነ በውድ የድጋፍ ሰልፍ ይወጣ ነበር፡፡
መስከረም ሁለት ደርግ ንጉሱን ገልብጦ ሥልጣን የያዘበት ቀን ነው፡፡ በአጭር አገላለፅ መስከረም ሁለት የደርግ ግንቦት ሃያ ነበር፡፡ ያሁኑ እንኳን መቼ እንደሆነ እኔንጃ ካወቃቹ ንገሩኝ ታዲያ እናቴ በወቅቱ የነበረውን የግዳጅ ውትድርና በመፍራት
የመጀመሪያ ልጇን ወታደር ቤት እንዳይወስዱባት ከከተማው ወጣ ያለ አክስታችን ቤት ደብቃ፣
ሁለተኛ ልጇንም ገጠር እናቷ ጋር ልካ፣ ሦስተኛውን ልጇን አልጋ ስር አስቀምጣ፣ አባቴንም
“ታምሜያለሁ በል!' ብላው፣ እሷ ግን ነጭ ልብስ ለብሳ ሰልፍ ወጣች፡፡ ግዴታ ነዋ!

ቀበሌ ስትደርስ ሴት ወንዱ ያለውን ለብሶ ተሽቀርቅሮ፣ ቀበሌውም በተለያዩ መፈክሮችና በባለ ቀለም
መብራቶች አጊጦ ጠበቃት፡፡ የቀበሌው የኢሴማ ኃላፊ የነበረች ሴት በባለእጀታ የጣውላ ሰሌዳ ላይ ተፅፈው የተዘጋጁ በመቶ የሚቆጠሩ መፈክሮችን ለእናቴ እያሳየቻት፣“ምረጭና አንዱን ያዥ” አለቻት፡፡

እናቴ ቀለል ያለችና በደማቅ ቀይ ቀለም የተሽሞነሞነች መፈከር መርጣ አነሳችና ወደ ሰልፉ
ተቀላቀለች፡፡ ከለበሰችው የሚያምር የአበሻ ቀሚስ እና ከራሷም ቁንጅና ጋር ተዳምሮ የኦሎምፒክ መከፈቻ ላይ ኢትዮጵያ የሚል ምልክት ይዛ ሰልፉን የምትመራ ቆንጆ የአበሻ ሴት ትመስል ነበር፡፡

በዕለቱ መስቀል አደባባይ ላይ እናቴን በርካታ ሰዎች በግርምትና በአድናቆት ሲመለከቷት ዋሉ፡፡
ታዲያ በዚያ ሰሞን ማታ በቴሌቪዥን ደጋግመው እናቴን ከነመፈክሯ ያሳይዋት ጀመረ፡፡ ምን ይሄ ብቻ፣ ዓመቱን ሙሉ ፎከረውም እናቴን ማሳየት፣ ኢህአፓ ብለውም እናቴን፣ መኢሶን ብለውም እናቴን፣ ቀይ ሽብር ብለውም እናቴን፣ ጓድ ሊቀመንበር ተናግረው ሲያበቁም እናቴን ማሳየት፡፡

ጭራሽ ብሔራዊ ውትድርና ተብሎ ምድረ ወጣት ሲጋፈ ፣ የብሔራዊ ውትድርና አገር አቀፍ ዓርማ የእናቴ ፎቶ ሆኖ በየቦታው ተለጠፈ፡፡ በነጭ ልብስ ተውባ መፈክር ይዛ የቆመች እናቴ የብሔራዊ ውትድርና አገር አቅፍ አርማ ሆነች፡፡አንድ ጋዜጣ ላይ የእናቴ ፎቶ ስር እንዲህ የሚል ጽሑፍ ሰፍሮ ነበር፤

“አብዮታዊት ሶሻሊስት ኢትዮጵያ ነጭ ቀሚስ ለብሳ”

እናቴ ታዲያ መጀመሪያ አካባቢ በቴሌቪዥን በታየች ቁጥር በቁንጅናዋ የተመረጠች መስሏት
አባቴ ላይ በኩራት ትነሰነስበት ነበር፣ “ጓዳ ለጓዳ ስውል ቀላል ሰው አድርገኸኝ፣ እግሬ ወጣ ካለ አገር ነው የሚሰግድልኝ!” ትለዋለች ኮራ ብላ፡፡ አባቴ አፉን ሸርመም አድርጎ፣ “እዩኝ እዩኝ ማለት ደብቁኝ ደብቁኝ ያመጣል ” ይላታል::

“የቅናት ወሬ ነው ይሄ” ትልና ሆነ ብላ ለማበሳጨት በቴሌቪዥን ደጋግሞ የሚታየውን
ምስሏን አተኩራ እየተመለከተች፣
“አንዲት ፍሬ ልጅ እኮ ነኝ” ትላለች፡፡ አባባ ታዲያ “ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…” ብሎ በረዥሙ ይሰቅና “ሰልፍ ላይማ መንግስትም አንድ ፍሬ ነኝ ነው የሚለው” ይላል፡፡
“ኤዲያ እንግዲህ ቦለቲካህን ልትጀምር ነው…” ብላ ወደ ጓዳዋ ትገባለች፡፡
ይሁንና እናቴ እየቆየች በቴሌቪዥን መታየቱ እና ስለ እርሷ መወራቱም ሲደጋገምባት ፈራች፡፡
በተለይም ጓድ መንግስቱ ኃይለማሪያም መስቀል አደባባይ በትልቁ የተሰቀለውን የእናቴን ፎቶ
ለተሰበሰበው ሕዝብ እያሳዩ በደም ፍላት፣
“እንደነዚህ ዓይነት ጀግና እናቶች ያሉባት አገር በማንም ወመኔ ከሃዲ ስትወረር እንዴት
ወንዶቿ አልጋ ስር ይደበቃሉ? እነዚህን ቦቅቧቃ ወንዳገረዶች ቂጣቸውን በሳንጃ…” እያሉ
ንግግር ካደረጉ በኋላ እናቴ ስጋቷ ከፍ አለ፡፡

ስጋቷን ለማስታገስ፣ “ኧረ ይሄ መፈክር ምንድን ነው የሚለው?” ብላ የተማረ ሰው ጠየቀች፡፡
መስከረም ሁለት ሰልፍ ላይ ይዛ ስለወጣችው መፈክር ተሸክማው ስለነበረው ጽሑፍ ሚያዚያ
ላይ “ምንድን ነው?” ብላ ጠየቀች፡፡ ሲነበብላት አመዷ ቡን አለ ፤ ብርክ ያዛት፡፡ መፈከሩ እንዲህ ነበር የሚለው

“የአብዮት ጠላቶችን ለማደባየት እኛ እናቶች ልጆቻችንን፣ ካስፈለገም ባሎቻችንን በደስታ እናዘምታለን!”

አለቀ
👍36😁189👏2
አትሮኖስ pinned «#ተሸከመናታል !! ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም እናቴ ሁልጊዜ እንድናጠና ስትመክረን እንዲህ ትላለች፡- እናንተ ልጆች አጥኑ፣ ተማሩ እባካችሁ ! ..እኔ ባለሙማሬ ነው ጉዴን ተሸክሜ የዋልኩት፤” ማንበብም መፃፍም ስለማትችል ንግግሯ በቁጭት ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ይሄ ተሸክማ የዋለችው ጉድ ምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቼ ጠየቅኳት፣ “ማሚ የምን ጉድ ነው ተሽከመሽ የዋልሽው ?” አወራችኝ… በደርግ ጊዜ…»
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


....ከዚህ በፊት መፅሀፌ " እምቢ
ሲለኝ፣ አንተን አባርሬ ምን ነበር የማረገው መሰለህ?»

«ከመፅሀፍሽ ጋር የምትታገዪ ነበር የሚመስለኝ»

ተሳስተሀል። በየቀኑ ከምሳ በኋላ ማርሰይ እወርድና፡ ከሰአት
በኋላውን፣ ማታውን፣ አንድ አራት አምስት ወንድ ተኝቶኝ፣ ወደ
እኩለ ሌሊት ላይ ድክም ብሎኝ ወደ ኤክስ እመለሳለሁ:: በቀን
በቀኑ ይህን አረጋለሁ። አንድ ቀን ልሄድ ስዘጋጅ ፃፊ ፃፊ ይለኛል፡፡
መፃፍ እጀምራለሁ፡፡ ወንዶቹ በቁኝ ማለት ነው። በፊት እንዲህ ነበር
የማረገው

«አሁንስ?»

“አሁንም ላደርገው ተነሳሁ። ማርሰይ ወረድኩ። ግን ምንም
ሳላረግ ተመለስኩ።
«ወንዶችሽ እምቢ አሉሽ?»
በጉሮሮዋ ውስጥ ቅንዝረኛ ሳቋን እየሳቀች
“ትቀልዳለህ?» አለችኝ ተለውጬ ነው እንጂ። ወንድ መሄድ
ሱስ መሆኑ ቀረ»
«ሱስ መሆኑ ቀረ እንጂ መደረጉ ግን አልቀረም፣ እ?»
«መደረጉማ ለምን ይቀራል? የስሜት ደስታ አይደለም እንዴ?»
ይህን ጊዜ ቤቷ ልንደርስ አንድ መቶ ሜትር ያህል ቀርቶናል፡፡
ታሻሽው የነበረውን እጄን ለቀቀችና
ማን ይቅደም?» ብላ ትታኝ ሮጠች፡፡ እንዳልቀድማት ብዬ
ጫማዬን በሀይል እያስጮህኩ ተከተልኳት። እሷ እየጮኸች፣ እኔ
እየሳቅኩ ቤቷ ጋ ስንደርስ፣ በሩን ቀድማኝ በእጇ ነካችው
ቀደምኩህ!» አለችና በሩን ተደግፋ ቁና ቁና ስትተነፍስ፣
ጉንጮቿን በእጆቼ ይዤ ግምባሯን ሳምኳት እንደዚህ ለዋውጠኸኝ፣ በኋላ ያላንተ እንዳት ልሆን ነው?»
አለችኝ፡፡ በሀይል አሳዘነችኝ፡፡ ሆዴ ሽምቅቅ አለ፡፡ ወደኔ አስጠግቼ
ራሷን እየደባበስኩ ውይ የኔ ቆንጆ! እንድተውሽ አትፈልጊም እንዴ?» አልኳት
«አልፈልግም አልፈልግም አልፈልግም!» እያለች በጣም
ተጠጋችኝ፡ ራሷን አንገቴ ውስጥ ሸሸገች፡፡ እምባዋ አንገቴን ነካኝ
«እኔም ልተውሽ አልፈልግም፣ የኔ ቆንጆ፣ አልተውሽም፡፡
እስከመቼም አልተውሽም፡፡ ምንም ቢመጣ አልተውሽም» አልኳት
«እፈራለሁ፡፡ ካንት መለየቱን ሳስበው እፈራለሁ፡፡ አንተ አገርህ
ትሄድና፣ ከዚያ በኋላ አንገናኝም። እስከመቸም አላይህም፡፡ በቃ
ለዘለአለም?! ውይ! እቀፈኝ! እቀፈኝ!. . . መኖር እንዴት አስቸጋሪ
ነው!»
«አይዞሽ አንለያይም፣ የኔ ሲልቪ»
«አንለያይም?»
«አንለያይም። አይዞሽ አታስቢ። አሁን እንግባ»
አልጋ ውስጥ ላዬ ላይ አደረግኳትና፣ ጀርባዋንና አንገቷን
ጭንቅላቷን እየደባበስኩ ብዙ ጊዜ ከቆየን በኋላ፤
«አሁን ተለያይተን በወድያኛው ህይወት የምንገናኝ እንኳ
ቢሆን፣ ምናልባት እችለው ነበር» አለችኝ ግን መለያየቱ ለዘለአለም
ቢሆን፡ አንድ ጊዜ አይህና ከዚያ በኋላ ለዘለአለም ለዘለአለም
እስከመቸም የማንተያይ ስንሆን፣ በጣም ያስፈራኛል!» ብላ ተጠመጠመችብኝ

«አይዞሽ እንለያይም»
«አንለያይም?»
በሩ ተንኳኳ። ድንግጥ አለች
«አይዞሽ አይዞሽ»
በሩ እንደገና ተንኳኳ
«ማነው በይ» አልኳት
«ማነው?» አለች ጮክ ብላ
«ባህራም!»
ድንጋጤዋ ወደ ብሽቀት ተለወጠ። እየተነጫነጨች ተነስታ የሌሊት ካፖርቷን ራቁት ገላዋ ላይ ጣል አርጋመቀነቱን እየታጠ
ቀች ሄዳ በሩን ከፈተች
ባህራም «ይቅርታ በዚህ ሰአት ስላስቸገርኩ» እያለ ገባ። ጥቁር
ሙሉ ሱፍ ልብስ፣ ውሀ ሰማያዊ ሸሚዝ፣ ደማቅ ሰማያዊ ክራቫት::
ፂሙን ተላጭቶ፣ ፀጉሩን ወደ ኋላ አበጥሯል፡፡ ከጎንና ከጎን የበቀለው
ሽበት' የእርጅና ምልክት መሆኑ ቀርቶ ልዩ ጌጥ መስሏል፡፡ የድል
አድራጊነት ፈገግታ የሚጨፍርበት ፊቱ ወጣትነት ተላብሷል መጥቶ የተጋደምኩበት አልጋ አጠገብ ወምበር ላይ ሲቀመጥ
«እንዲህ ዘንጠህ የት ልትሄድ ነው? » አልኩት
ሲልቪ መጥታ ከጎኔ አልጋው ውስጥ ገባች
«እገሬ መግባቴ ነው» ከለ
“ልሰናበታችሁ ነው የመጣሁት»
«መሄድህ ነው በቃ?» አለችው ሲልቪ
“አዎን"
«ቆይ ዊስኪ ላምጣልህ» ብላ፣ ከአልጋው ወጥታ ወደ ወጥ ቤት
ሄደች፡፡ ቶሎ ከኪሱ አንድ ወረቀት አውጥቶ፣ ወምበር ላይ
የተሰቀለው ኮቴ ኪስ ውስጥ ከተተና፣ በሹክሹክታ
«ለብቻህ አንብበህ ቅደደው » አለኝ
"ላንተም ላምጣልህ? » አለች ከወጥ ቤቱ
«ለኔም ላንቺም አምጪ» አልኳት
ይዛ መጣች። ከልጋ ውስጥ ገባች። ዊስኪውን አነሳሁና ባሀራምን
«መልካም ጉዞ!» አልኩት
ፉት አልን
«ከመሄዴ በፊት ጥቂት ልነግርህ የሚገባኝ ነገር አለ» አለኝ።
ሲልቪ ትታን ልትሄድ ስትል «ካንቺ የሚደበቅ ያለበት አይደለም»
አላት
«እሺ» አልኩት
ብዙ ልነግርሀ በፈቀድኩ። ግን አብዛኛው የኢራን ኮሙኒስት
ፓርቲ ምስጢር ነው፡፡ አንተን አምንሀለሁ፡፡ ግን ፓርቲው
እንድነግርህ አይፈቅድልኝም»
«ይገባኛል፡፡ ምንም መናገር የለብህም»
«አውቃለሁ፡፡ ሁለት ነገር ብቻ በጠቅላላ ባጭሩ ልንገርህን
«ሁለት አመት ሙሉ በይሩት ነበርኩ፡፡ ግን ዩኒቨርሲቲው
ውስጥ የህክምና ትምህርት አልተማርኩም፡፡ ሌላ ስራ ነበረኝ። በቅርብ ምስራቅ ውስጥ ያሉትን የኢራን ኮሙኒስቶች ሳደራጅ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደሞ ከሻህ ሰላዮችና ከሲ.አይ.ኤ ጋር ረዥም ጦርነት ስናካሂድ ነበር። ሲ.አይ.ኤ ሊገድለኝ ሲሆን ጊዜ፣ ቱዴህ (የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ) እንድሸሽ አዘዘኝ። ወደ ኤክስ መጣሁ። እውነተኛ ስሜን
ልነግርህ አልችልም፡ ግን ባህራም አይደለም። ባሀራም ከፍሻር
በይሩት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ህክምና ይማር ነበር። በሱ ስም የውሽት ፓስፖርት አውጥቼ ነው፡፡

«ቤቶችህ ይህን ያውቃሉ?»
«ታላቅ ወንድሜ ያውቃል። ስም በቀየርኩ ቁጥር አዲስ ስሜን
በደብዳቤ ነግረዋለሁ፣ ከቤት ገንዘብ ሲመጣልኝ እሱ በአዲሱ ስሜ እየላከው ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድ ነገር አለኝ የምነግርህ»
ምን?»
«ደጋግመህ መልክህ የኢራንን ሻህ ይመስላል ብለኸኛል።
እውነትክን ነው:: ሻህ የስጋ ዘመዴ ነው»
አጭር ዝምታ
«ላሳየኸኝ ጓደኝነትና ለዋልክልኝ ውለታ ላመሰግንህ አልችልም፡፡
ስለዚህ ሳላመሰግንህ መሄዴ ነው» አለኝና ተነሳ፡፡ በቁሙ ዊስኪውን ጨልጦ፣ ብርጭቆውን ኮሞዲኖ ላይ አኖረው:: ልሸኘው ካልጋ ልነሳ ስል
«አትነሳ። ማኑ እዚህ ውጭ ይጠብቀኛል። አብረኸኝ ብትመጣ
ያለቅስብኛል፡፡ እሱ ሁልጊዜ እንደተጠነቀቀ ነው። ወዴት በኩል
እንደምንሄድ አንተ'ንኳ እንድታውቅ አይፈልግም» ይስቃል፡፡ ማኑን
ስለሚወደው ይስቅበታል። ከማኑ ጋር ለመሆን በመቻሉ እጅግ ደስ
ብሉታል፡፡ ወጣትነቱን እንደገና አግኝቷል። እጄን ዘረጋሁ:: ጨበጠኝ። በኔ በኩል ተንጠራርቶ ሲልቪን ሳማት። ሊሄድ ወደ በሩ በኩል ከዞረ በኋላ
«ለመሆኑ አልኩት ዞረ። ፊቱ ላይ ፈገግታ የለም፡፡ የኢራንን ሻሀ ይመስላል።አፍንጫው ትልቅ ነው
«ለመጀመሪያ ጊዜ
ሳገኝህ ሶስት አሜሪካኖች
ይዘውህ ሊደበድቡህ መጀመራቸው ነበር» አልኩት
“A bas les Yankecs!” አለኝ እየሳቀ
“A bas!" አልኩት
ሰአቱን አየ፡፡ ቸኩሏል
“ሊደበድቡህ ይዘውህ ሳለ፣ ማኑ ያስተማረሀን የመከላከል ዘዴ
ለምን አልተጠቀምክበትምን» አልኩት
«ተማሪዎች ይሁኑ ወይ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ይሁኑ እርግጠኛ አልነበርኩም። ምናልባት እኔን ፍለጋ የመጡ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ቢሆኑስ? ያን አይነት ያምባጓሮ ዘዴ ማወቄን ካወቁ ባህራም አለመሆኔን ይጠረጥራሉ። ለዚህ ነው:: በሎ ደህና ሁኑ። ማኑ ይጠብቀኛል»
👍30🥰1👏1😁1
ደህና ሁን! አልነው ሁለታችንም
“Vive Etoile Rouge!” አለኝ (ቀዩ ኮከብ ለዘላለም ይኑር!) (Et
vive l'amitie!" (ጓደኝነትም ለዘላለም ይኑር)
“Vive!" አልኩት
ቀፈጣን እርምጃው በሩጋ ደረሰ። መለስ አለ። አሁንም የድል
አድራጊነት ፈገግታ ወጣት ፊቱ ላይ እየተጫወተ
«ሳልነግራችሁ ረስቼ» አለን ያን ጊዜ ሊገድለኝ ተገዝቶ
የመጣውን ማን እንዳስመጣው ታውቃላችሁ? ማንም
ቢያስመጣው የኔ ሞት በፋሺስቶቹ ላይ መላከኩ አይቀርም ነበር።
ይልቁንም አስመጪው ቀስ ብሎ ኮሙኒስቶቹ ተማሪዎች መካከል
ይህን ወሬ የነዛ እንደሆነ። ገባችሁ? በውነቱ ግን ነብሰ ገዳዩን ገዝቶ ያስመጣው አንድ የሻህ ሰላይ ነበር። ማን ይመስላችኋል?»

ማን?» አልነው ሁለታችንም
ደስ የሚል ወጣት ሳቁን ሳቀ
«ጀምሺድ ጓደኛችን የሻህ ሰላይ ነበር

እንዲህ ተቃቅፋችሁ ደስ ስትሉ! እንግዲህ ባሰብኳችሁ ቁጥር፣
እንዲህ ሆናችሁ ነው የምትታዩኝ፡፡ እንዴት ቆንጆ ነው! መቼም
እንደማትለያዩ ተስፋ አለኝ፡፡ አቤት እናንተ የምትወልዱት ልጅ!
ይታየኛል፡፡ እንደ ካስትሮ ያለ ጀግና ነው የሚሆነው»
እጁን አወዛወዘልን። ወደኛ እያየ በሩን ከፈተ። ወጣ፡፡ በሩን
ዘጋ። ከህይወታችን ወጣ። ሁለታችንም እንወደው ነበር። ግን ሲለየን በጣም አላዘንም። ብቻውን እንዳልሆነ እናውቃለን፣ ውጪ ጨለማው ውስጥ ጓደኛው እንደሚጠብቀው እናውቃለን። ሁለቱንም ሀያ ሚሊዮን ህዝብ እንደሚጠብቃቸው እናውቃለን። ይሂዱ፡፡መንገዳቸውን የሳጥናኤል ኮከብ ያብራላቸው!

እኔና ሲልቪ ባሀራም የወጣበትን በር በፀጥታ ስንመለከት ብዙ
ጊዜ ቆየን። ካጠገቤ ብድግ አለች፡፡ ከበላዬ ቆማ የሌሊት ካፖርቷን አውልቃ ጣለችው:: ራቁቷን ቆመች። እግሯን፣ ጉልበቷን፣ ጭኗን መሳም ጀመርኩ
ቆይ አለችና፣ ከአልጋው ወርዳ፣ ሀር ፀጉሯንና ውብ ወጣት
ዳሌዋን እያወዛወዘች ወደ በሩ ሄዳ ቆለፈችው:: ወደኔ ስትራመድ
የተገተሩት ወጣት ጡቶቿ ይንቀጠቀጣሉ። አንሶላውን ወደዚያ ገፋሁት። መጥታ ላዬ ላይ ወጣች። አበባ መሳይ ጡቷን አጎረሰችኝ፡፡

እጄን ወፍራም ዳሌዋ ላይ አኖርኩት። ሌሊቱ ተጀመረ ...

💫ይቀጥላል💫
👍23
#የአባዬ_ስልክ_እና_ባዮሎጂ


#በአሌክስ_አብርሃም


እንዲህ እንደዛሬው በየሰዉ ኪስ ሳይልከሰከስ በፊት ስልክ ተዓምራዊ የሀብት መለኪያ ነበር፡፡
አቤት ስልክ እንዴት እንደሚከበር ! እንደሚፈራ.! ያኔ ኔትወርክ እንጂ ስልክ አልነበረም፡፡ዛሬ ግን ስልክ እንጂ ኔትወርክ የለም።

እንግዲህ በሰፈራችን አንድ የቤት ስልክ ብቻ ነበረ ያለው፤ ስሙ ደግሞ “የአባዬ ስልክ”፤ ብዙው የሰፈር ሰው የእኔን እናት ጨምሮ በዚህ ስልክ ነበር የሚጠቀመው፤ ደግሞ ድምፁ የትናየት እንደሚሰማ…ኪሊሊሊሊሊሊሊሊ ሲል የመንደሩ ሰው ሁሉ ሥራ ያቆማል፡፡ ወጣቶች ፍቅረኞቻቸው የደወሉ መስሏቸው የያዙትን ሥራ እርግፍ አድርገው ጆሮና ልባቸውን ያቆማሉ፣እናቶች ሊጥም እያቦኩ ከሆነ ነጭ የቦክስ ጓንት ያጠለቁ መስለው ብቅ ይላሉ፡፡ የአባዬ የስልክ ድምጽ መቼም አይረሳኝም፡፡ አሁን የመጡ ስልኮች ቢዘፍኑ ሲንቀጠቀጡ የአባዬን ስልክ ድምፅ
ከአዕምሮዬ ሊፍቁት አልቻሉም፡፡

ስልኩ ሲጮኸ ልጆቻቸው አረብ አገር ያሉ እናቶች ልባቸው ይሰቀላል…፤ እናቴ ራሷ “ አቡቹ !
እስቲ እሱን ቆርቆሮ ቀንሰው” ትላለች፤ ቴፑን ማለቷ ነው፡፡ እንግዲህ ይሄ ሁሉ ሰው እንዳቆበቆበ የአባዩ ልጅ ቡጡጡ በራቸው ላይ ትቆምና “እማማ ፋጤ ስልክ ! ከውጭ ነው ቶሎ በሉ!” ብላ ትጮሀለች፡፡ እማማ ፋጤ ወደ አባዬ ቤት ሲሮጡ ሌላው ጎረቤት ወደየስራው ይመለሳል፤ስልኩ በተደጋጋሚ የሚጮኸው ለበዓል አካባቢ ነው፤ በተለይ ለአዲስ ዓመት!

ቀላል ስልክ እንዳይመስላችሁ፤ በዚህ ስልክ ስንቱ ከውዱ ጋር አውግቷል፤ ስንቱ የውዱን
መርዶ ተረድቶ በድንጋጤ ስልኩ የተቀመጠበት ጠረንጴዛ ስር ተጠቅልሏል፤ ስንቱ ከጠፋ
ዘመዱ ተገናኝቷል፤ ስንቱስ ብር እንደተላከለት ሰምቶ ፈንጥዟል! ኧረ ስንቱ! ወደ አባዬ ቤት
ሲንደረደር እንቅፋት አንግሎት ባፍጢሙም የተተከለ፣ ጥፍሩ የተነቀለ…አለ፡፡

ለምሳሌ የአረጋሽ ጥፍር ተጣምሞ የቀረው ወደ አባዬ ቤት ስትሮጥ እንቅፋት አንግሏት ነው፡፡ አረጋሽ
ህመሙን ቻል አድርጋው ስልኳን እናገረችና ልክ ስልኩን ስትዘጋው፣ “ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ ብላ ጮኸች፡፡ መርዶ የሰማች ነበር የምትመስለው፡ በኋላ ሲጣራ ከስልኩ በፊት ለመታት
እንቅፋት ነው ያለቀሰችው፡፡ ጥፍሯ ግን ተጣምሞ ቀረ፡፡

ይሄ ስልክ ስልክ ብቻ አይደለም፣ ጩኸቱ የምስራች ነው! ጩኸቱ መርዶ ነው፡፡ ከመንደሩ
በላይ ያለው የጊዮርጊስ ቤተከርስቲያን ደውል ድምፅ የአባዬን ስልክ ጩኸት ያህል ግርማ ሞገስ የለውም
ለመንደርተኛው:: የኛን መንደር ሰዎች ወፍራም እንጀራ፣ ደንዳና ናፍቆትና ፍቅር በቀጭን የስልከ ሽቦ ውስጥ ተጉዞ የሚያርፍበት ኬላ የት ነው ሲሉን “የአባዩ ቤት እንል ነበር ።

ይህን ስልከ በጉጉት ከሚጠብቁ ቤተሰቦች መሃል የእኛ ቤተሰብ አንዱ ነበር፡፡ አባቴ ለሥራ ከእኛ
ርቆ ይኖር ስለነበር እኛ ልጆቹን የሚመከረው ለሚስቱም የሆድ የሆዱን የሚናገረው በአባዬ
ስልክ ነበር፡፡ እንደውም ግንባር ቀደሙ የእባዬ ስልክ ተጠቃሚ ቤተሰብ የእኛ ቤተሰብ ነበር
ማለት ይቻላል። ታዲያ አባቴ ለበዓል ሲመጣ ለበአል የሆነ ነገር ይዞ ስለሚመጣ ስልከ ስንጠራ
ቤተሰባዊ ቃና ባለው መንገድ ነው፡፡ “ስልክ” ብቻ አንባልም፤ “እንዳይቆጥርበት ፍጠኑ ጋሼ
ነው ? የሚል ማስጠንቀቂያም ይጨመርበታል፡፡

ለምሳሌ አባቴ ሲደውል እናቴ ከፊት፣ እህቴ ከኋላ፣ ወንድሜ ቀጥሎ፣ እኔ፣ ትንሽዋ እህቴ
ተግተልትለን እንሄዳለን፡፡ መጀመሪያ እናቴ ናት የምታናግረው፤ ድምጿን ቀንሳ ፊቷ በሃፍረት በናፍቆትና በፍቅር ተጥለቅልቆ ብዙ “አዎ” እና “አይይ!” የበዛበት ንግግር ታደርጋለች፡፡

አዎ!
አዎ!
አዎ!

አይይይይይ!

የአባዬ ስልክ ደግሞ ለክፋቱ ይጮሃል፤ በአሁኖቹ የእጅ ስልኮች ቋንቋ ላውድ ስፒከር ላይ
ያደረጉት ይመስላል፡፡
“እንደምነሽ ! …ምነው ድምፅሽ ጎረነነ ? አመመሽ እንዴ የኔ እናት ?” ይላል አባባ፤
“አይይይይ! ደህና ነኝ! " ትለለች እናቴ፤ አንዳንድ የፍቅር ነገርም ለለሚናገር ቶሎ መሰናበት
ትፈልጋለች፡፡

ቀጣይ ተረኛ ትልቅ እህቴ ናት፡፡

“ምን ልላከልሽ"

"ስኒከር ጫማ"

"እሺ"

"ነጭ"

"እሺ የኔ ማር" ድምፁ ውስጥ ናፍቆት አለ፡

"እንደባለፈው ሰፊ እንዳታመጣ ባባ"

"እሺ የኔ ቆንጆ"

ወንድሜ ይቀጥላል...

"ታኬታ ጫማ ባለ ብሉኑን"

“ባለ ቡሎን ጫማ አለ እንዴ ?" ይላል አባቴ በግርምት፡

"እንክት!"

እሽ እፈልጋለሁ ! አንተ ብቻ እናትህን እንዳታስቸግር፡ በደንብ ተማር!"

እኔ አባትህን አናግር ስባል አላናግርም፡ አብሬ ሮጬ አባዪ ቤት ድረስ ሄጄ ግን ብሞት አላናግርምፀ እናቴ ትበሳጫለች፡፡

“እሺ ምን ላምጣልህ ይልሃል" ትላለች በብስጭት፡

"ምንም!” እንባዬ ይመጣብኛል፡ አባቴን እወደዋለሁ፡ ግን በስልኮ አላናግረውም፡፡ ለምን ቢባል መልስ የለኝም፡፡ የተባለው ነገር ሁሉ ሲመጣ ግን እህቴ ያንን ሁሉ ማብራሪያ ሰጥታ ጫማዋ ይሰፋል ወይ ይጠባታል፡፡ ወንድሜ ባለብሎን ታኬታ አያመጣለትም፡ ኧረ እንዲያ የሚባል ጫማ የለም!" ይለዋል አባባ፡፡ እኔ ግን ምንም ሳልናገር ምርጥ ነገር ያመጣልኛል፡ አባቴ እኔን ራሴን እስኪመስለኝ ምርጫው ልክ ነው፡፡

እኛ ሰፈር እንዲት ሴት ጎረመሰች የምትባለው በአባዩ ስልክ ቤተሰብ ወይም ዘመድ ያልሆነ ወንድ ከደወለላት ነው፡፡ ሁሉም ሴቶች ለፍቅረኞቻቸው የአባዬን ስልክ ነው የሚሰጡት። ወንዶችም አልፎ አልፎ ይሰጣሉ ፡፡ ታዲያ አባዬ ቤት የተወራችው ነገር ስልኩ እንደ ሜጋፎን እየጮኸ ምስጢሩን ስለሚዘራው ጎረቤቱ ጋር ወዲያው ይደርሳል፡፡

“ሮማን የያዘችው ልጅ ሹፌር ነው መሰል ሁልጊዜ ከተለያየ እገር ነው የሚደውለው?

“አትይኝም!"

"ሙች!...አንዴ ከጅቡቲ፣ አንዴ ከሞያሌ፤ ቢጡ ሲያወራ ሰምታ ነው የነገረችኝ፡፡ ሲሉ የአባዬ
ልጅ ናት፡ ማን ከማን ጋር ምን አወራ የሚለውን ለመንደሩ የምታዳርሰው እሷ ናት፡፡

እንዲህ እየተባለ በቃ የተወራው የተደረገው ሁሉ ሰፈሩ ውስጥ ይናኛል፡፡ አንዲት ሴት ወይም
ወንድ በከባዬ ስልክ ካልተደወለለት ጉርምስናው እውቅና አያገኝም፡፡

አንዲት ሴት ስልክ ማናገር እና አለማናገሯ የፀባይ መለኪያ ሆኖ በመንደርተኛው ያስወቅሳታል፡፡
አልያም ያስመሰግናታል፡፡ “ውይ እሷ አንገቷን የደፋች፣ አባዩ ቤት አንድ ቀን ረግጣ አታውቅ
"ይባላል፡፡ ወይም “እች ልጅ የአባዩን ቤት አዘወተረች፤ መዘዟን እንዳትመዝ” ይባላል፡፡ ታዲያ
የአባዬን ቤት ከማይረግጡ 'ጨዋ ጎረምሶች መሃል አንዱ እኔ ነበርኩ፡፡ ስምንተኛ ክፍል ስደርስ
ግን ጨዋነቴ ተገሰሰ፡፡

የስምንተኛ ከፍል የባዮሎጂ አስተማሪያችን እትዬ መክሊት በጣም አይናፋር ሴት ነበረች፡፡
ምእራፍ ዘጠኝ የስነተዋልዶ አካላት የሚል ርእስ ላይ ስንደርስ ፊቷ ቀልቶ እያፈረች ስታስተምረን
ትዝ ይለኛል፡፡

“የስነ ተዋልዶ አካላት እንግዲህ..ያው…ወንድ እና ሴት ...ያው…” ጭንቅ ይላታል እትዬ መክሊት፣ እኛ ደግሞ ጆሮ ብቻ እንሆናለን፡፡ ስልሳ የምንሆን የእንድ ከፍል አጉል እድሜ ላይ ለምንገኝ ተማሪዎች ይሄ ጉዳይ የነፍስ ጉዳይ ነበር የምንጓጓላት፣ ለመስማት የምንሰስትለት፤ የስነተዋልዶ አካል ነገር ልባችንን ሰቅሎት፣ ትንፋሻችንን ውጠን እንቁለጨለጫለን፡፡ በክፍለ ጊዜው መርፈ ቢወድቅ ይሰማል ፀጥታው፡፡

“ውይ…ምነው ሁልጊዜ እንዲህ በትኩረት በተከታተላችሁ…! አያችሁ መማር ለራስ ነው፤ ትምህርት አገርን ይቀይራል፡፡ ያደጉት አገሮች ዝም ብለው አላደጉም፡፡ …ትምህርት…" ኤጭጭ እኛ ስለ ስነተዋልዶ አካላት ለመስማት ጓጉተን እትዬ ምክር…መክራ፣ መክራ ምከሯ ሲያልቅባት
👍35👏1