ዐውደ ምሕረት
3.66K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ስለ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ የሚባሉ ተአማኚነት ያላቸው ይትባህሎች

፩. #አስታራቂነት ፡-ነብርና አንበሳ አይስማሙም፤ በአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሥዕል ሥር ግን ነብርና አንበሳ ተስማምተው ይታያሉ፡፡ በዚህ የተነሣ ለመታረቅ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለማስታረቅ የሚሄዱ ሽማግሌዎች ‹አቦን ሆነን መጥተናል› ይላሉ፡፡

፪. #የአቦ_ጠበል ፡- አንድ ሰው እየተመገበ ቢያንቀው ‹የአቦ ጠበል› እያልክ ውኃን ሦስት ጊዜ ጠጣው ይባላል፡፡
፫. #የአቦ_ብቅል ፡- አንድ ሰው ከማያውቀው ቦታ ስሙ ቢጠራና በአካባቢው የሚያውቀውን ሰው ቢያጣ የጠራው ሰይጣን ሊሆን ስለሚችል ‹‹የአቦን ብቅል እፈጫለሁ› በል ይባላል፡፡

፬. #የአቦ_መገበሪያ ፡- አንድ ሰው አንድን ነገር አጥፍቶ ተሠውሮ እንደማይቀመጥ ለመግለጥ ‹‹የአቦን መገበሪያ የበላ ሲለፈልፍ ይውላል›› ይባላል፡፡

፭. #አቦ_ሰጥ ፡- አንድ ሰው የማያውቀውን ነገር በግምት ሲናገር ‹አቦ ሰጥ› ይባላል፡፡

፮. # በአቦ_ይዤሃለሁ ፡- አራዊት የቤት እንስሳትን እንዳይበሉባቸው ገበሬዎች ‹በአቦ ይዤሃለሁ› ብለው ይገዝቷቸዋል፡፡

፯. #የአቦ_መንገድ ፡- በሰሜን ሸዋ መራኛ አካባቢ ባሉ ሕዝቦች ዘንድ ‹የአቦ መንገድ› የሚባል ብሂል አለ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሚዳ ከሚገኘው የአቡነ መልከ ጼዴቅ ገዳም ጥቂት ጊዜ ቆይተዋል ይባላል፡፡ በኋላ ከዚያ ገዳም ሲወጡ አቡነ መልከ ጼዴቅ ‹‹የት ሊሄዱ ነው›› ብለው ቢጠይቋቸው ‹እርሱ ወደ መራኝ›› ብለው መለሱላቸው፡፡
ከተማው ‹‹መራኛ›. የተባለው በዚህ ምክንያት ነው ይባላል፡፡ ታድያ በዚህ ምክንያት አንድ ሰው መድረሻውን በውል ሳያውቀው መንገድ ሲጀምር መንገዱ ‹የአቦ መንገድ› ይባላል፡፡

፰. #የአቦ_ቁራ ፡- ሰይጣን በቁራ ተመስሎ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ዓይናቸውን ሊያወጣ ስለመጣ በጎ ነገር የያዘ መስሎ የሚመጣ ክፉ ሰው ‹የአቦ ቁራ› ይባላል፡፡

፱. #በአቦ_በሥላሴ ፡- በሕዝቡ ብሂል ውስጥ ከሥላሴ ጋር ተያይዘው ብዙ ጊዜ የሚጠሩት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ‹በአቦ በሥላሴ› ሲባል አጥብቆ መለመን ነው፡፡ በሕዝባዊ መዝሙሮችም ውስጥ ‹በአምስት አቦ ናቸው በሰባት ሥላሴ› የሚል ሐረግ በተደጋጋሚ ይሰማል፡፡
ስለ አቡዬ  ሌሎች የሚያውቋቸው ይት ባህሎች ካሉ ይጨምሩበት!

#የጻድቁ እረድኤት አይለየን...አሜን!

#ምንጭ :- ከሙሃዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ጽሁፍ የተቀነጨበ
የብዙ ቅዱሳን ማረፊያና መፍለቂያ #የቅዱሳን_ወደብ_ሀገረ_እግዚአብሔር_ኢትዮጵያ

#ልዮ ልዮ ወደቦቻችንን አተናል የቅዱሳን ማደሪያ ወደብ መሆናችንን ካጣን ግን ከቀድሞ ይልቅ አሁን ይብስብናል።

#ኢትዮጵያ_የብዙ_ቅዱሳን_ወደብና_የክርስቲያኖች_ደሴት_ናት !
ከተራ #ዘኢትዮጵያ
_______
#ሳቢ ያልቅ ይ እንጂ ሐሳብ አያልቅም! ስለዚህ ሀሳብ ቦይ እስካገኘ ድረስ ፈሶ
የማያልቅ ወንዝ ነው ። ይልቁኑ መነሻቸው በምድር የማይታወቁ ገነታዊ የሆኑ ወንዞች ለዚህ
ጥሩ ማሳያዎች ናቸው።
ሀገራችን ሁል ጊዜ የጥምቀት በዓልን ምክንያት አድርጋ ዋዜማውን ማለትም ጥር 10 ቀንን
" ከተራ " ብላ ታቦት ከመንበሩ አንስታ ድንኳን ወደ ተተከለበት የታቆረ ፣የተከተረ፣የተገደበ
ውኃ ወዳለበት ሥፍራ ይዛ በመሄድ በልልታና በግርግርታ በድምቀት ከምዕመኞቿ ጋር
ታከብረዋለች ። ኢያሱ 3÷3
#ይህንንም ማድረጓ አምላካችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እራሱ መጥቶ
ያጥምቀኝ ሳይል ወደ ባሪያው ወደ ዮሐንስ በትሕትና ሄዶ መጠመቁን ለማሰብ ነው።
የትሕትና አባት ! ይህን በማድረግ ባያስተምረን ኖሮ ዛሬ ካህናቱ ቤታችን መጥተው
ያጥምቁን ባልን ነበር። ከተራ የቃሉ ትርጉም መገደብ ፣ በአንድ ቦታ መርጋት (ለፈሳሽ
ነገር)፣ መታቆር ፣መቆም ወይም ማቆም የሚል ነው።
ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ " እነሆ ውኃ ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድነው? " ብላ
ከተጠመቀችበት ጊዜ አንስቶ ይህው ዛሬ ድረስ ምሥጢረ ጥምቀትን በሚገባ ለልጆቿ
ስታስተምርና ሥርዓቱንም ስትፈጽም ኖራለች ። ወደ ፊትም ትኖራለች። # ሐዋ 8÷36
#ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የጥምቀትን በዓል ማክበር የጀመረችሁ በኩረ ጳጳሳት ዘኢትዮጲያ
የሚባሉት " ፍሬ ምናጦስ" ወይም ሕዝቡ ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ ፊደል ቀርጾ ንባብ አደላድሎ
የድንቁርናን ጽልመት ገፏልናልና ብለው " አቡነ ሠላማ ከሳቴ ብርሃን " /የሠላም አባት
ብርሃንን የሚገልጥ / እያሉ ይጠሯቸው በነበሩት በመጀመሪያው ታላቅ ጳጳሳችን ትዕዛዝና
መመሪያ ነበር።
ከዛ በመቀጠል እነ አፄ ገብረ መስቀል፣ እነ አፄ ናዖድ እና አፄ ዘርዓ ያዕቆብ የመሳሰሉት
ቅዱሳን ነገሥታት ይህ ደገኛ የጥምቀት በዓል በአደባባይ እንዲከበር አድርገውታል።
ዛሬ ዛሬ እነዚህን የመሰሉ ቅድስናን ከንግሥና አስተባብረው የያዙ መሪዎችን በማጣቷ
ባህሏን ፣ወጓን፣ ሃይማኖቷን ፣ትውፊቷ ፣ሥርዓቷን በአደባባይ ወጥታ እንዳታከብር ጫና
እያሳደሩባት ትገኛለች።
#እርሷ ግን ተስፋዋ እግዚአብሔር ነውና ዛሬም ወደ ዮርዳኖስን መውረዷን አላቆመችም ።
አንድነት ይዛለች ፣ ፍቅር ከትራለች ፣ ሠላም ጸንሳለች መለያት እንዳያጨነግፋት፣ አጥንት
ቆጣሪነት እንዳይበትናት እንጠንቀቅላት።
ይህ ሀገራዊ ከተራ ከመንፈሳዊ ክትረት ምሳሌነት አልፎ በየ ቤታችን መብራትና እራት ሆኖ
የሚመጣ የብልጥግናችን ቀንዲል ነው። ከተራውን ከተራ ነገሮች ሁሉ ወጥተን በአንድነት
የምንረጨው ጥሩ ውኃ ያድርግልን። # ሕዝ 36÷25
"ሃይማኖት፣ ብሔር፣ዘር የማይለኝ ሰናይ ከተራ... #ዓባይ !"
ኃ/ማርያም
አ.አ ኢትዮጵያ
10/2013ዓ.ም
ዐውደ ምሕረት
Photo
#የአምላካችሁን_የእግዚአብሔርን_ቃል_ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት።”
#ኢያሱ 3፥3
ዐውደ ምሕረት
Photo
#አስተርዮ_ማርያም
______

ያቢሎስን ሥራ ያፈርስ ዘንድ #የእግዚአብሔር_ልጅ የተገለጠባት ምክንያተ ድኂን #ወላዲተ_አምላክ_ቅድስት_ድንግል_ማርያም 1 ዮሐ 3÷8-9

" #ቃል_ከአብ ያለ ድካም ወጣ #ከድንግልም ያለ ሕማም ተወለደ"
_ #ቅዱስ_ኤፍሬም ሶሪያዊ __
#የአድዋ_ተራሮች ትዝብት
_____

ቲሺ ምናለ ከዚህ ንበር ትንሽ ቀቅ ብዬ በተፈጠርኩ ካድማሱ ባሻገር እንደ ሰንሰለት ከተያያዙት ከአድዋ ተራሮች በመጠኑ ተለቅ የሚለው የአንዱ ተራራ የምሬት ንግግር ነበር

#እንዴ ይህ እኮ እኛ የተፈጠርንበትን የነጻነት ጀንበር የተፈነጠቀበት የኢትዮጱያ መሬት ነው ይህን መሬት ስንቱ ተራራ ሊፈጠርበት እንደሚመኝ እረስተህው ነው ።

ሌላኛው ከግራ ያለው ተራራ ቀበል አርጎ የዓለምና የአፍሪካ ስመ ጥር ተራሮች ኤቨረስትና ኪሊማንጃሮ እራሳቸው ረጃጅሞች ስመ ጥር ተራራሮች ሆነው ከሚታወቁ ይልቅ እዚህ ቦታ ተፈጥረው የጥቁር ሕዝብ ድልን የሰውልጅ እኩልነት የነጻነት ቀንዲል መለኮሰን ዕብሪተኝነት አንገት ሲደፈ ጨዋነት ሲረታ ቢያዮና የጀግኞች የዐይን መስክር ቢሆኑ የበለጠ ደስተኛ ይሆኑ ነበር። አንተ እዚህ በመፈጠረህ ታማርራለህ

#ግዙፉ ተራራ ከመካከላቸው ሆኖ ዐይ የልጅ ነገር እሱ መቼ ጠፋኝ " ለቀባሪው አረዱት አሉ " እናንተ በዚህች ምድር ከመፈጠራችሁ በፊት እኔ ቀድሜ ነበርኩ አድዋ ጦርነት እራሱ ከእናንተ የተሻለ ቁመናና ርዝመት ያለኝ በመሆኔ ከናንተ በተሻለ የጦርነቱን ሙሉ እንቅስቃሴ ለማየት ታድያለው የአባ ነብሶ ድፍረት መድፉን ለብቻ ሲያጓራው ፣የገበየው ደረት ደልብጦ መግባት ፣የጣይቱ ብልሐት፣ የምኒልክ ጽናት የሰማዕቱ እርዳታ ሁለም እንደ ትላንትና ሆኖ በሐይኔ ሕሊናዬ ተሰሎ ተቀምጧል መቼም ልረሳው አልችልም ያቺ የኃላ ደጀን የነበረች አዝማሪ ጻድቄ እራሱ ሳትቀር ከነ ግጥሞቿና ከነ አበረታች መሰንቆዋ የዕለት ለዕለት ትዝታዬ ነች እንዲያውም አንድ ጊዜ ጠላት በአድዋ ሥላሴ በኩል ገፍቶ ሲያይል "የአድዋን ሥላሴ ጠላት አረከሰው ገበየው በሞቴ ግባና ቀድሰው " ብላ ገጥማ ነበር።
ታድያ ይህን ያክል የምታስታውሰው ከሆነ ምን ቢመር ነው ከዚህች የነጻነት ድንበር ውጪ መፈጠርን የፈለክ? ሆ ሰው እንዴት ሰው አልኩ እንዴ ተራራ እንዴት በተመረጠ መሬት በነፃነት ሀገር ተፈጥሮ ሲያበቃ ለምን በዚህ የነፃነት ሀገር ተፈጠርኩ ብሎእንዴት በከንቱ ያማርራል?
#በከንቱ_አይደለም ማማረሬ እውነት ይዤ እንጂ ። በግራና በቀኝ ያሉት በመጠናቸው አነስ የሚሉት ተራሮች በተመሳሳይ ሰዓትና ቃል ማለት አልገባንም? አሉ።

ከመካከላቸው መሆኑ እንደፈለጉ ጥያቄ እየጠየቁ እንደ ገና ዳቦ በጥያቄ ሊጠብሱት የተዘጋጁ አስመስሏቸዋል። ከዛ አንደኛው ተራራ ከአድመኝነት መንፈስ ወጣ ለማለት ብሎ ሀሳቡን ለመረዳት ትንሽ ፋታ ከወሰደ በኋላ እስቲ በል ንገረን ምንድነው ይህን ያክል ቁጭት አሳድሮ የተፈጠርክበትን የነፃነት ምድር ለመጸየፍ ያበቃህ? ሲል በእርጋታ ጠየቀው
እሳት አመድ ወልዶ ሳይ እንዴት የቁጭት ቆፈን አይውረሰኝ? በዕድሜ አንጋፈ አዛውንት የሚመስለው ተራራ ሳግ እየተናነቀው እንዳይታወቅበት ጉረሮውን እያጸዳ ቀስ ብሎ ቁጭቱን ሊያስረዳቸው ጀመር።
#በዚህ ቦታ በኖርኩበት በእስኳሁኑ ዕድሜ እንዲህ ዐይነት ውርደትና መሸማቀቅ ደርሶብኝ አያውቅም ። ጥንት ኢትዮጵያዊያን አርበኞች ጠላትን በዚህ ሥፈራ ድል ሲነሱ ለ ሀገር ለድንበር ለሃይማኖት ለአንድነት ለአንድ ሕዝብ ብለው ዋጋ ፍለው ደም አፍስሰው ሥጋ ቆርሰው አጥንት ገብረው ባለፉበት በዚሁ ሥፍራ በገደሉበት ሥፍራ ሲገዳደሉ ነጻ በወጡበት ሰፈር ምርኮ ሲገቡ ድል በነሱበት ሀገር ድል ሲነሳሱ ከማየት ሌላ ምን ውርደት አለ? የዘንድሮስ አድዋ ፋሽሽት ኢጣሊያንን ወይስ የእናት ልጅ ወንድምን ድን የነሳንበት በዓል ነው ብለው ሊያከብሩት ነው ?

የጀግኖች ደም ዋጋ ቢስ ሲሆን ከማየት ሌላ ምን አስቆጪ ነገርስ ይኖራል ? እነሱስ አንዴ ለሀገር ለድንበር ለነፃነትና ለሃይማኖት የሚገባቸውን ዋጋ ከፍለው በክብር አርፈዋል ይብላኝ እንጂ ለኔ ሞት ወስዶ ለማይገላግለኝ ግዑዝ ነው ይሉኛል ምንም የማይሰማኝ ንግግሬን ማድመጥ ያልቻሉ እነሱ መሆናቸው ማን በነሱ ቋንቋ በነገረልኝ

#ያኔ ቋንቋ ብሔር ዘር ሳይለያቸው እንደ አንድ ልብ መካሪ አንደ አንድ ቃል ተናጋረ ሆነው ጠላትን ያስጨነቁ ዛሬ ብሔሬ ቋንቋዬ ተባብለው ሲተላለቁ በዚሁ ሥፍራ ሳይ ለምን አልበግን

ደሞኮ ቋንቋውም ቢሆን በቅጡ የአባቶቻቸውን ቋንቋ አቀላጥፈው አያውቁትም ሁሉም ባለ ቋንቋ ነኝ ባይ ከእንግሊዘኛ ሳያዳቅል ማን በቅጡ የሚናገራቸው አለ እስቲ ቆንጆ ኦሮምኛ ተናጋሪ አምጡልኝ እስቲ ንጹሑ አማርኛ አንደበት ያለው ፈልጉልኝ እስቲ ትግርኛን አቀላጥፎ የሚያወራ የሰሜን ሰው ፈልጉልን የለም አታገኙም ። ለመጠፋፋትና ለመገዳደል ሲሆን ግን ብሔሬ ቋንቋዬ ይባልልኛል አስቀድመህ በቅጡ ውረስወ እስቲ ።

#ሁለቱ ተራሮች ምንም ሊመልሱለት አልቻሉም ከልብ ያልኖረ እውነት ከየት ይገለጣል።

እሱማ እውነትህን ነው በሚል በተጸጸተ አስተያየት ከግራም ከቀኝም ተመለከቱት

የላሊበላ መቅደስ ሰሪዎች እናንተ አይደላችሁም ቢሆንማ ኖሮ ሌላም አስደማሚ የኪነ ሕንጻ አብዝታችሁ ሰርታችሁ ከድኅነት አረንቋ በወጣችሁ ነበር የሚሉን የቀደመ ሥልጣኔያችንን ሊያስክዱን የሚዳዱ የነጭ እባቦች ከንፈር አደዋም የናንተ የኢትዮጵያዊያዊያን ድል አይደለም ቢሆንማ ዛሬ አንድነታችሁን ምን ፈታው መተባበራችሁን ማን ወሰደው ቢሉን ምን እንመልስ ይሆን?
በዚህ የመበላላት መንፈስ ውስጥ ሆነን የአፍሪካዊያን የነፃነት ቀንዲል የተለኮሰው ከዚህ ሀገር በነዚህ ተራሮች ሥር ነው ቢባል ማን ያምናል?

#አንዱ ወጣት እግር የሆነ ተራራ ይህማ አይሆንም እኔ አንደበት አውጥቼ እንደ ቢታንያ ድንጋይ አድዋ የኢትዮጵያዊያን ድል ነው ስል ጮክ ብዬ እመሰክራለዋ ሲል ሌላላው ቀበል አርጎ አዎ እኔም ዝም አልልም አድዋ ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ የጥቁር ሕዝበ ሁሉ ድል ነው ሲል አሳቡን ተጋራው
አንጋፈው ተራራ ግን ከሰማይ ደመናትን ሰብስቦ እንደ ጋቢ ተከናንቦ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል በሽሙጥ ተከናነበ ቀጠል አርጎም አንድነቱና ህብረቱ እንዲመጣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ካልጣረ እመሆኝ ወደፊት እኔ እንዳልኳችሁ ሳይሆን አይቀርም በርግጥ ሁሉም ነገር ከትምህት ቤት መማር አይቻልም የዕድሜ ባለ ፀጋ ሲነግራችሁ ግን እህ ብላችሁ ብሰሙ መልካም ነው ዕድሜ እዚህች ዮኒቨርስ ላይ ያልተገነባና የማይገነባ ትልቅ ዮኒቨርስቲ ነው ።

እናንተ ይህ ትላላችሁ አክሱም፣ ጀጎል፣ አባይ ፣ጣና ሁሉ ሳይቀር ከሀገር ሊወጡ ሲሉ አገኘዋቸውና ስለምን ይህችን ምድር ለቃችሁ ትወጣላችሁ ስል ሞገትኳቸው ሲሉ የነበሩ ኢትዮጵያ አብጠርጥረው ያውቋታል የሚባሉ ለምድ የከበዱ ሰዎች እንኳ ሳይቀሩ ዛሬ መሀመድ ግራኝ ወራሪአይደለም ሲሉ እየተደመጡ ነው ተደምጠዋል ምን ያርጉ ሥልጣን ወደ ሐሰት ዘወረቻቸው ። ታድያ ግራኝ ወራሪ ካልሆነ አርበኛ ነውንን? አምባ ሳደር ነውን? ወይ ብሔራዊ ጀግናችን ነው? በዚህ ዓይነትኮ ወደፊት ዐውልት ይቁምለት መንገድ ይሰየምለት መባሉ አይቀሬ ነው ። በዕድሜ የምታንሱኝ ልጆቼና ወንድሞቼ ይህ አበክራችሁ ስሙኝ በልባችሁም ጽላት ጽፋችሁ አኑሩት እውነት ሁል ጊዜም እውነት ነች ለማቻቻልና ሚዛን ለመጠበቅ አልያም ዲሞክራት ለመሆን ብለህ ልትሸፉፍናት መልኳን አጥፍተህ ልታጠይማት አትችልም ። መሀመድ ግራኝ ሀገር ያፈረሰ ሃይማኖት ያጠፈ ወራሪ ነው። ግራኝ ወራሪ አይደለም ካልን 11 ሚሊየን አይሁዳዊያንን በዘራቸው ምክንያት የጨፈጨፋቸው ኢትለር ቅዱስ ነው ሀገሩም ከደጋጎቹ ሀገር ከመንግሥተ ሠማይ ነው ማለት ነው
#ይህን ጊዜ ታናናሾቹ ተራሮች ቡፍ ቡፍ እያሉ እጆቻቸውን በአቸው ላይ ጭነው ያመለጣቸውን ሳቅ ለማፈን ሲሞክሩ አንጋፈው ተራራ ተፈነጣጣ የምራቅ ቅንጣቶችን እንዳይለቁበት በመስጋት ከቀድሞ ይበልጥ አብልጦ ፊቱን በደመና ጋቢ ተከናነበ ። ሳቃቸው የሚጋባ ሳቅ ቢሆንም ከራሱ ቁጭት አልወጣም ነበርና ሳቃቸው በራስ እንደማሾፍ ቆጠረው

ጠላትን ድል በነሳንበት ሀገር እርስ በእርስ ድል ስንነሳሳ ለከረምን ለኛ ትልቅ ውርደት እንደሆነ ባወቃችሁ ጥርሳችሁን በዘነዘና ትነቀሱት ነበር። ለነገሩ የእሳት ልጅ አመድ ነው እናንተም የዚህ ትውልድ አብራክ አይደላችሁምን? አለና በስላቅ አብሯቸው ሳቅ አለ በልቡ ግን ግን ወይ መፍለስን ወይ መፍረስን ይመኝ ነበር ሰማይና ምድር ያልፋሉ ያለውንም እያሰበ አብዝቶ ያቺን ቀን ናፈቃት ።
_ይኩን ሠላም ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ___
ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 23/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
ዜና እረፍት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አራተኛ ፓትርያሪክ ብፅእ አቡነ መርቆሪዎስ ከዚ አለም ድካም አረፉ።

በረከታቸው ይደርብን
ዐውደ ምሕረት
Photo
#ኑ-ዝምታን-እንተርጉም
---------------------------------

"አቤቱ ለአፌ ጠባቂን አኑርለት
የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ"

አጥብቆ ቢደግማት የዳዊትን መዝሙር
ተቀጥሮለት መሰል ጠባቂ ከናፍር
እንጂማ
ጆሮ አልባ በሆነች ባናጋሪ ዓለም
አስችሎት ዝም የሚል ትግስተኛ የለም

እኔስ ይመስለኛል የአባቴ ዝምታ
ቃል ያለማውጣቱ የጸትታው ፋታ
በጆሮ አልባ ሀገር
በደንቆሮ መንደር
ሰሚ በሌለበት
ፊደል ማባከኑ ቃላት ማበላሸት
መረበሽ ነው እንጂ መግባባት የለበት
ብሎ ይመስለኛል

እኔስ ይመስለኛል የአባቴ አርምሞ
በማይሰሙ ሰዎች ነብሰ ሥጋው ታሞ
ሰልችቶት ይሆናል አርሞ አርሞ
እንጂማ
እንዲያ ባይሆን ኖሮ
ባልሸሸ ነበረ ካደገበት ጓሮ

እኔስ ይመስለኛል ያባቴ አርሞሞ
ለአንድ መንጋ አንድ እረኛ
ይበቃዋል ካለ እውነተኛ
ከዛ ውጪ ነው ምንደኛ
ብሎ አስቦ በትትና
እራሱን ዝቅ አረገና
ከሰማይ ቤት ደጅ ጠና
የይህን ዓለም ንቋልና

እኔስ ይመስለኛ ያባቴ ዝምታ

አንድም ቢደርስ ነው ከቅዱሳን ተርታ
የበቃ ቢሆን ነው ምግባሩ የበረታ

ግን.... ግን
በሚንጫጫ ዓለም በማይሰማ ቅዬ
እንዴት አስችሏቸው ዝም አሉ አቡዬ?
ለፍላፊ ሳይሰሙት
ኸኸ ባይ ሳይነግሩት
ጆሮ በጠፋበት
ምላስ ሰንበር በዝቶ
ሲገድፍ የሚውል አንደበት ጾም ትቶ
ድንጋዮን ያልጣለው ከአፉ አውጥቶ
እንደምን ተጠራ ዳግማዊው አጋቶ ን ???

#ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 25 /2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" #ካለ_ፈጣሪ_አሟጠሽ ጋግሪ"
______________________
ስስት ንፍገት ፣ሆዳምነትን፣ ኑሮዬ ይበቃኛል አለማለትን እንዲሁም አልጠግብ ባይነትን የሚገልጽ ግሥ ነው ። (የመ.ቅዱስ መዝገበ ቃላት/ ገጽ ፹ ፭ ) በዘመናች ቋንቋ "ቋጣሪነት" ልንለው እንችላለን። በንባባችን ላይ ቋጣሪነት ወይም ስስታምነት ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ የመጣ ነገር እንጂ በሰው ተፈጥሮ ውስጥ "ስስት" ወይም "ንፍገት" የሚባል ነገር የለም ። የስስት ተቃራኒ ቸርነት ነው ። ቸር ደግሞ #እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሌሎች ቸር ቢሆኑ #ከእግዚአብሔር የተቀበሉን በመስጠት ነው እንጂ የእራሳቸው አንዳች የላቸውም ቸርነትን ለሌላው ቢያደርጉ በሥጋ የሕሊና ሰላም ፣በሃይማኖት ደግሞ ጽድቅን ፈልገውበት ነው ።

#እግዚአብሔር ቸር ቢሆን ግን እጸድቅበት አይል ነገር ጻድቅ ነው እከብርበት አይል ነገርም ክቡር ነው ስለዚህ ቸርነት ማንም ያልሰጠው ማንምም የማይነጥቀው የእግዚአብሔር የባሕሪው ገንዘቡ ነው:: “ #ከአንዱ_ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።” ሉቃ ፲ ፰ ፥፲ ፱

ይህን ያልተገነዘበው ዲያቢሎስ እሩቅ ብዕሲ (ተራ ሰው) መስሎት አርባ ቀን በገዳመ ቆሮንቶስ ጾሞ ሲወጣ መራቡን ዐይቶ ቸሩ መድኃኔዓለምን በስስት ሊፈትነው ቀረበ ። በኮሮጆም ትኩስ የሚሸት ዳቦ ይዞ "የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ ይህን ድንጋይ ዳቦ እንዲሆን እዘዝ " አለው :: #ማቴ ፬÷፫

#ቸሩ_መድኃኔ_ዓለምም ማንነቴን ላሳየው፤ ሁሉን ቻይነቴን ይወቅልኝ ሳይል ዲያቢሎስ እንዳለው ድንጋዮን ዳቦ ሳያደርግ "ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም " ተብሎ ተጽፏል ብሎ " #በትዕግስት" ድል ነሳው። #ማቴ ፬÷፬

በበርሃ የሚኖሩ መነኮሳት ፆራቸው ስስት ነው ፤ በፈለጉ ጊዜ ምግባቸውን አያገኙምና ‹‹ ያለችን ብንመፀውት ሰውን ብናበላ ያለችን ታልቅብናለች ከዚያ ምን እንበላለን›› እያሉ በስስት ብዙውን ይፈተናሉ፡፡ ስለዚህ ቸሩ ፈጣሪያቸን ይህን የስስት ፈተና እንዴት በትዕግሥት ድል ማድረግ እንደሚችሉ ሲያስተምራቸው በመነኮሳት ቦታ በበርሃ ተገኝቶ ዲያቢሎስን በትዕግስ "ሰው በእጀራ ብቻ አይኖርም" ብሎ ድል አደረገው፡፡

#በስስት የመጣብንን ፈተና በትግሥትና በቸርነት ለንሻገረው ያስፈልጋል ያ ሲባል ግን ቁጠባንና ባህሉን ለመሸርሸር ሳይሆን የመቀበል ግልብጥ ስሌት መስጠት እንደሆነ ጭምር ለማስታወስ ነው ። ሁለት ነገር ያለው ሰው ሌላ ሦስተኛ ነገር ከፈጣሪው ከፈለገ ከያዘው ሁለት ነገር ቢያንስ አንዱን እንኳ ምንም ለሌለው መስጠት ይገባዋል :: ለመቀበልምኮ መስጠት ያስፈልጋል! ሰው ሁለት እጅ የተሰጠው በአንዱ ተቀብሎ በሌላኛው እንዲያቀብል ነው እንዲሉ አበው።


“ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።” #ምሳሌ ፲ ፱ ፥፲ ፯ “ኀጥእ ቀኑን ሁሉ ምኞትን ይመኛል፤ ጻድቅ ግን ይሰጣል፥ አይሰስትም።” #ምሳሌ ፳ ፩ ፥ ፳ ፮ ስለዚህም በክርስቶስ እኖራለሁ የሚል ክርስቶስ ደግሞ እንደተመላለስ ይመላለስ ! ጸሎቱም ሁል ጊዜ “ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን።” የሚል ይሁን ! #መዝ ፻ ፲ ፰ (፻ ፲ ፱) ፥ ፴ ፮
......... ይቆየን..........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
#እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ”
________________________________
#ያዕ ፬ ፥ ፮
#፩ጴጥ ፭ ÷ ፭

ትዕቢት ከሦስቱ (አርስተ/ ርዕሰ ኃጥዐው) መካከል አንዱ ነው:: ሦስቱ ርዕሰ ኃጥዐው የሚባሉት ስስት ፣ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው።

#ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ የኃጢያት ሁሉ እራሶች ፣ አለቆች ና አውራዎች መባላቸው ኃጢያት ሁሉ ከእነዚህ ስለሚመነጭ ነው።

ዲያቢሎስ መንፈሳዊ ሰውን የሚፈትነው በሦስቱ የፈተና ዐይነቶች ነው በስስት፣ በትዕቢትና በፍቅረ ነዋይ ፤ ሌሎች የኃጢያት ዐይነቶች የነዚህ የሦስቱ ጭፍሮች ወይም ተከታዮች ናቸው።

#ለምሳሌ የትዕቢት መንፈስ የተጠናወተው አንድ ሰው እኔ ከማን አንሳለሁ የሚል የበታችነት ስሜት ውስጥ በመግባት ለግድያ ፣ለስርቆት፣ ብሎም ለዝሙት ኃጢያቶች ተጋላጭ ይሆናል።
ትዕቢት የዲያቢሎስ ልዮ መገለጫው ነው ስለሆነም ዲያቢሎስ ስለ ግብሩ ( ስለ ሥራው) ትዕቢተኛ ብቻ ሳይሆን እራሱ ትዕቢት እየተባለ ይጠራል። ለዚህ ነው ሐዋርያው እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል" ካለ በኋላ " እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ " ሲል ትዕቢተኞች ብሎ በተውላጠ ስም የጠራቸውን ዲያቢሎስና ጭፍሮቹን አስከትሎ ደግሞ "ዲያቢሎስን" ብሎ በግልጥ የተናገረው #ያዕ ፬÷፮ - ፯
#ለዚህ ትልቁ ማሳያ የገዳመ ቆሮንቶስ ሁለተኛ ፈተና ትዕቢት የተሞላበት መሆኑ ነው "ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና (ወሰደው ሲል በፍቃዱ ሄደለት ለማለት እንጂ ለዲያቢሎስስ ታዛዢ ሆኖ አይደለም) እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው። “ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል" ብሎ የትዕቢትን ፈተና በትሕትና ድል ነሳው ። የካህናት ፆራቸው ትዕቢት ነው ፤‹ ‹ እኛ አእምሮአችን ረቂቅ ማዕረጋችን ምጡቅ ›› እያሉ በትዕቢት ይፈተናሉ፡፡ ዲያብሎስ በካህናት ቦታ በቤተመቅደስ በትዕቢት ቢመጣበት በትህትና ድል አድርጎላቸዋል፡፡ #የትዕቢትን ፈተና ማሸነፍ የሚቻለው በትሕትና ብቻ ነው! #ማቴ ፬÷ ፭- ፰ .

“ከእኔም_ተማሩ_እኔ_የዋህ_በልቤም_ትሑት_ነኝና"
#ማቴ ፲ ፩ ፥ ፳ ፱

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም