ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም የዛሬን አያድርገውና ኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1

አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።

" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"

ምን አልሽ አንቺ ??

#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል

አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።

#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው

ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።

የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
#የአድዋ_ተራሮች ትዝብት
_____

ቲሺ ምናለ ከዚህ ንበር ትንሽ ቀቅ ብዬ በተፈጠርኩ ካድማሱ ባሻገር እንደ ሰንሰለት ከተያያዙት ከአድዋ ተራሮች በመጠኑ ተለቅ የሚለው የአንዱ ተራራ የምሬት ንግግር ነበር

#እንዴ ይህ እኮ እኛ የተፈጠርንበትን የነጻነት ጀንበር የተፈነጠቀበት የኢትዮጱያ መሬት ነው ይህን መሬት ስንቱ ተራራ ሊፈጠርበት እንደሚመኝ እረስተህው ነው ።

ሌላኛው ከግራ ያለው ተራራ ቀበል አርጎ የዓለምና የአፍሪካ ስመ ጥር ተራሮች ኤቨረስትና ኪሊማንጃሮ እራሳቸው ረጃጅሞች ስመ ጥር ተራራሮች ሆነው ከሚታወቁ ይልቅ እዚህ ቦታ ተፈጥረው የጥቁር ሕዝብ ድልን የሰውልጅ እኩልነት የነጻነት ቀንዲል መለኮሰን ዕብሪተኝነት አንገት ሲደፈ ጨዋነት ሲረታ ቢያዮና የጀግኞች የዐይን መስክር ቢሆኑ የበለጠ ደስተኛ ይሆኑ ነበር። አንተ እዚህ በመፈጠረህ ታማርራለህ

#ግዙፉ ተራራ ከመካከላቸው ሆኖ ዐይ የልጅ ነገር እሱ መቼ ጠፋኝ " ለቀባሪው አረዱት አሉ " እናንተ በዚህች ምድር ከመፈጠራችሁ በፊት እኔ ቀድሜ ነበርኩ አድዋ ጦርነት እራሱ ከእናንተ የተሻለ ቁመናና ርዝመት ያለኝ በመሆኔ ከናንተ በተሻለ የጦርነቱን ሙሉ እንቅስቃሴ ለማየት ታድያለው የአባ ነብሶ ድፍረት መድፉን ለብቻ ሲያጓራው ፣የገበየው ደረት ደልብጦ መግባት ፣የጣይቱ ብልሐት፣ የምኒልክ ጽናት የሰማዕቱ እርዳታ ሁለም እንደ ትላንትና ሆኖ በሐይኔ ሕሊናዬ ተሰሎ ተቀምጧል መቼም ልረሳው አልችልም ያቺ የኃላ ደጀን የነበረች አዝማሪ ጻድቄ እራሱ ሳትቀር ከነ ግጥሞቿና ከነ አበረታች መሰንቆዋ የዕለት ለዕለት ትዝታዬ ነች እንዲያውም አንድ ጊዜ ጠላት በአድዋ ሥላሴ በኩል ገፍቶ ሲያይል "የአድዋን ሥላሴ ጠላት አረከሰው ገበየው በሞቴ ግባና ቀድሰው " ብላ ገጥማ ነበር።
ታድያ ይህን ያክል የምታስታውሰው ከሆነ ምን ቢመር ነው ከዚህች የነጻነት ድንበር ውጪ መፈጠርን የፈለክ? ሆ ሰው እንዴት ሰው አልኩ እንዴ ተራራ እንዴት በተመረጠ መሬት በነፃነት ሀገር ተፈጥሮ ሲያበቃ ለምን በዚህ የነፃነት ሀገር ተፈጠርኩ ብሎእንዴት በከንቱ ያማርራል?
#በከንቱ_አይደለም ማማረሬ እውነት ይዤ እንጂ ። በግራና በቀኝ ያሉት በመጠናቸው አነስ የሚሉት ተራሮች በተመሳሳይ ሰዓትና ቃል ማለት አልገባንም? አሉ።

ከመካከላቸው መሆኑ እንደፈለጉ ጥያቄ እየጠየቁ እንደ ገና ዳቦ በጥያቄ ሊጠብሱት የተዘጋጁ አስመስሏቸዋል። ከዛ አንደኛው ተራራ ከአድመኝነት መንፈስ ወጣ ለማለት ብሎ ሀሳቡን ለመረዳት ትንሽ ፋታ ከወሰደ በኋላ እስቲ በል ንገረን ምንድነው ይህን ያክል ቁጭት አሳድሮ የተፈጠርክበትን የነፃነት ምድር ለመጸየፍ ያበቃህ? ሲል በእርጋታ ጠየቀው
እሳት አመድ ወልዶ ሳይ እንዴት የቁጭት ቆፈን አይውረሰኝ? በዕድሜ አንጋፈ አዛውንት የሚመስለው ተራራ ሳግ እየተናነቀው እንዳይታወቅበት ጉረሮውን እያጸዳ ቀስ ብሎ ቁጭቱን ሊያስረዳቸው ጀመር።
#በዚህ ቦታ በኖርኩበት በእስኳሁኑ ዕድሜ እንዲህ ዐይነት ውርደትና መሸማቀቅ ደርሶብኝ አያውቅም ። ጥንት ኢትዮጵያዊያን አርበኞች ጠላትን በዚህ ሥፈራ ድል ሲነሱ ለ ሀገር ለድንበር ለሃይማኖት ለአንድነት ለአንድ ሕዝብ ብለው ዋጋ ፍለው ደም አፍስሰው ሥጋ ቆርሰው አጥንት ገብረው ባለፉበት በዚሁ ሥፍራ በገደሉበት ሥፍራ ሲገዳደሉ ነጻ በወጡበት ሰፈር ምርኮ ሲገቡ ድል በነሱበት ሀገር ድል ሲነሳሱ ከማየት ሌላ ምን ውርደት አለ? የዘንድሮስ አድዋ ፋሽሽት ኢጣሊያንን ወይስ የእናት ልጅ ወንድምን ድን የነሳንበት በዓል ነው ብለው ሊያከብሩት ነው ?

የጀግኖች ደም ዋጋ ቢስ ሲሆን ከማየት ሌላ ምን አስቆጪ ነገርስ ይኖራል ? እነሱስ አንዴ ለሀገር ለድንበር ለነፃነትና ለሃይማኖት የሚገባቸውን ዋጋ ከፍለው በክብር አርፈዋል ይብላኝ እንጂ ለኔ ሞት ወስዶ ለማይገላግለኝ ግዑዝ ነው ይሉኛል ምንም የማይሰማኝ ንግግሬን ማድመጥ ያልቻሉ እነሱ መሆናቸው ማን በነሱ ቋንቋ በነገረልኝ

#ያኔ ቋንቋ ብሔር ዘር ሳይለያቸው እንደ አንድ ልብ መካሪ አንደ አንድ ቃል ተናጋረ ሆነው ጠላትን ያስጨነቁ ዛሬ ብሔሬ ቋንቋዬ ተባብለው ሲተላለቁ በዚሁ ሥፍራ ሳይ ለምን አልበግን

ደሞኮ ቋንቋውም ቢሆን በቅጡ የአባቶቻቸውን ቋንቋ አቀላጥፈው አያውቁትም ሁሉም ባለ ቋንቋ ነኝ ባይ ከእንግሊዘኛ ሳያዳቅል ማን በቅጡ የሚናገራቸው አለ እስቲ ቆንጆ ኦሮምኛ ተናጋሪ አምጡልኝ እስቲ ንጹሑ አማርኛ አንደበት ያለው ፈልጉልኝ እስቲ ትግርኛን አቀላጥፎ የሚያወራ የሰሜን ሰው ፈልጉልን የለም አታገኙም ። ለመጠፋፋትና ለመገዳደል ሲሆን ግን ብሔሬ ቋንቋዬ ይባልልኛል አስቀድመህ በቅጡ ውረስወ እስቲ ።

#ሁለቱ ተራሮች ምንም ሊመልሱለት አልቻሉም ከልብ ያልኖረ እውነት ከየት ይገለጣል።

እሱማ እውነትህን ነው በሚል በተጸጸተ አስተያየት ከግራም ከቀኝም ተመለከቱት

የላሊበላ መቅደስ ሰሪዎች እናንተ አይደላችሁም ቢሆንማ ኖሮ ሌላም አስደማሚ የኪነ ሕንጻ አብዝታችሁ ሰርታችሁ ከድኅነት አረንቋ በወጣችሁ ነበር የሚሉን የቀደመ ሥልጣኔያችንን ሊያስክዱን የሚዳዱ የነጭ እባቦች ከንፈር አደዋም የናንተ የኢትዮጵያዊያዊያን ድል አይደለም ቢሆንማ ዛሬ አንድነታችሁን ምን ፈታው መተባበራችሁን ማን ወሰደው ቢሉን ምን እንመልስ ይሆን?
በዚህ የመበላላት መንፈስ ውስጥ ሆነን የአፍሪካዊያን የነፃነት ቀንዲል የተለኮሰው ከዚህ ሀገር በነዚህ ተራሮች ሥር ነው ቢባል ማን ያምናል?

#አንዱ ወጣት እግር የሆነ ተራራ ይህማ አይሆንም እኔ አንደበት አውጥቼ እንደ ቢታንያ ድንጋይ አድዋ የኢትዮጵያዊያን ድል ነው ስል ጮክ ብዬ እመሰክራለዋ ሲል ሌላላው ቀበል አርጎ አዎ እኔም ዝም አልልም አድዋ ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ የጥቁር ሕዝበ ሁሉ ድል ነው ሲል አሳቡን ተጋራው
አንጋፈው ተራራ ግን ከሰማይ ደመናትን ሰብስቦ እንደ ጋቢ ተከናንቦ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል በሽሙጥ ተከናነበ ቀጠል አርጎም አንድነቱና ህብረቱ እንዲመጣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ካልጣረ እመሆኝ ወደፊት እኔ እንዳልኳችሁ ሳይሆን አይቀርም በርግጥ ሁሉም ነገር ከትምህት ቤት መማር አይቻልም የዕድሜ ባለ ፀጋ ሲነግራችሁ ግን እህ ብላችሁ ብሰሙ መልካም ነው ዕድሜ እዚህች ዮኒቨርስ ላይ ያልተገነባና የማይገነባ ትልቅ ዮኒቨርስቲ ነው ።

እናንተ ይህ ትላላችሁ አክሱም፣ ጀጎል፣ አባይ ፣ጣና ሁሉ ሳይቀር ከሀገር ሊወጡ ሲሉ አገኘዋቸውና ስለምን ይህችን ምድር ለቃችሁ ትወጣላችሁ ስል ሞገትኳቸው ሲሉ የነበሩ ኢትዮጵያ አብጠርጥረው ያውቋታል የሚባሉ ለምድ የከበዱ ሰዎች እንኳ ሳይቀሩ ዛሬ መሀመድ ግራኝ ወራሪአይደለም ሲሉ እየተደመጡ ነው ተደምጠዋል ምን ያርጉ ሥልጣን ወደ ሐሰት ዘወረቻቸው ። ታድያ ግራኝ ወራሪ ካልሆነ አርበኛ ነውንን? አምባ ሳደር ነውን? ወይ ብሔራዊ ጀግናችን ነው? በዚህ ዓይነትኮ ወደፊት ዐውልት ይቁምለት መንገድ ይሰየምለት መባሉ አይቀሬ ነው ። በዕድሜ የምታንሱኝ ልጆቼና ወንድሞቼ ይህ አበክራችሁ ስሙኝ በልባችሁም ጽላት ጽፋችሁ አኑሩት እውነት ሁል ጊዜም እውነት ነች ለማቻቻልና ሚዛን ለመጠበቅ አልያም ዲሞክራት ለመሆን ብለህ ልትሸፉፍናት መልኳን አጥፍተህ ልታጠይማት አትችልም ። መሀመድ ግራኝ ሀገር ያፈረሰ ሃይማኖት ያጠፈ ወራሪ ነው። ግራኝ ወራሪ አይደለም ካልን 11 ሚሊየን አይሁዳዊያንን በዘራቸው ምክንያት የጨፈጨፋቸው ኢትለር ቅዱስ ነው ሀገሩም ከደጋጎቹ ሀገር ከመንግሥተ ሠማይ ነው ማለት ነው
በዚህ ዘመን ዶሮ መሆን በራሱ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መታደል ነው።
#እንዴት?
በውድ ነዋ የምትሸጪው !
#በውድ ተሸጭክም ፤ በርካሽ ያው መታረድህ አይቀር
ቢሆንም በክብር ተሽጦ ክብርን በሚመጥን መንገድ መሞት ሰማዕትነት ነው ።
#በርኳሽ ስትሸጥ መቆየትህ ቁጭት አሳድሮብሃል ማለት ነው?
እንዴታ ለምን አያሳድርብኝም ? አታስታውሺም ፈንግል የተባለ በርድ ፍሎ የወፍ ጉንፋን በሽታ የመጣ ጊዜ ሁለት ዶሮ በ1ብር የተሸጠበትን የቅርብ ጊዜ ታሪክ? ይህው ዛሬ የሰው ጉንፋን covid 19 መጣና ሰው ረክሶ እኛ ተወደድን ለነገሩ የ ዛሬን አያድርገውና ከጅምሩ እኛኮ እኛ የነ አይደፈሩ የነ ዳይኖንሰር ዘር እኮነን ። ዶሮ የዳይነንሰር የመጨረሻ ዝርያው ነው ያሉትን የሳይንቲስቶች ምርምር አልሰማሽምን?
#ዶሮን ሲያታልሏት ዳይኖሰር ነሽ አሏት ኩኩኩኩኩኩኩ
ምን ያስካካሻል ውሸት ነው ልትይ ነው ዳይኖንሰርም ዶሮም ተመሳሳይ አቆም እንዳላቸው እራስሽ ማረጋገጥ ትቺያለሽ
#እንዴት አረጊ?
ላባው የተራገፈ አንድ ዶሮና አንድ ዳይኖንሰር በአምሮሽ ሳይ በሁለት እግራቸው የቆሙ
ሁለት እጃቸው አጠር ብሎ ወደ ደረታቸው የተጠጋ በመጠን ብቻ የሚለያዮ ተመሳሳይ ፍጥረት ይመጣልሻል።
#አስብኩት..... በእውነቱ እውነት ይመስላል ። ቆይ ግን አንተ መታረድህ ነው ወይስ የነ ዳይኖንሰር ዘር ሆኜ እንዴት በርኳሽ ተሽጬ እታረዳለሁ የሚለው ነው የሚያሳስብህ ?
ሁለቱም ያሳስቡኛል ክብሬም ሕይወቴም
#ወገኛ የቱ ክብርህ የክብር ባለቤት እንኳ በሰላሳ ዲናር ተሽጦ ያለ እርራዬ መታረዱን አትዘንጋ።
ዛሬ ጥሬ ስትለቅሚ የነበረው ከ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ነበር እንዴ?
#እንዴ አዎ ለምን ጠየከኝ?
ሰባኪ መሰልሽኛ!
#እእእእ_በነገራችን ላይ ላስተዋለው ሁሉም ፍጥረት በራሱ ሰባኪ ነው “ሰማያት #የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ” እንዳለ መጻሕፉ መዝ 19፥1

አሁን ከካህናቱ ጋር ሰንበቴ እንደምትቀመጪ ጭምር አረጋገጥኩ። ለነገሩ እታች ሰፈር ጥሬ ፍለጋ እያልሽ ገብስማው ዶሮጋ ከምትሄዲብኝ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መሄድሽ ይሻለኛል።

" #የአውራ ዶሮ ወዳጅ መች ጠርቶ ሊጠራ
ሲወጡ ሲገቡ ሁል ጊዜ ጥርጠራ"

ምን አልሽ አንቺ ??

#አረ ጌታው ምንም አላልኩም ወዲ ነው
እኔ የምለው እስከ ዛሬ መታረዴ ሳይሆን በርኳሽ ስሸጥ መቆየቴ የግር እሳት ሆኖብኛል እያልክ ነው።
#አዎን
ለምን ይመስልሃል ግን ዋጋችን እንዲህ ውድ የሆነው?
#እኔ ምን አውቃለሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ ግን ፈጣሪ መናቃችንን አይቶ እየካሰን ይመስለኛል

አይደለም ባክህ ሰው ስለረከሰ ነው።
#አታመጪው ጉድ የለ !። ምን?
አዎ ወዳጄ ሰው ሲረክስ ለሰው የተዘጋጁት ነገረሮች ሁሉ ይወደዱበታል በስግብግብነት ሲረክስ በአቋራጭ ለመበልጸግ ሲረክስ ነገሮች ሁሉ ውድ ይሆኑበታል።

#ይልቁኑ በበዓላት ሁሉም ሲወደድ ካየህ የሰው ልጅ እረክሷል ማለት ነው

ስኳር ውስጥ ሩዝ ፣በርበሬ ውስጥ ሸክላ ፣ቅቤ ውስጥ ሙዝ ፣እንጀራ ወስጥ ጀሶ የሚጨምረው ቢረክስ አይደለምን??!
#ሊጡ ውስጥ እንኳ ጀሶ መኖሩ አሁን አሁን ሳስበው ጥሩ መሰለኝ
እንዴት?
#ያው ያ ሀገር አቆርቋዥ ጁንታ እንደልማዱ ሰርቆ ሲጠጣ አድርቆ ያስቀርልናል።

የሚገርመው እንደዚህ በዐድ ነገር ቀላቅሎ እንኳን የሚሸጭበት ዋጋ የትዬ ለሌ ነው። ይህ እጅግ በጣም መውረዱን ነው የሚያሳየው።
#የኔ_ውድ ምን አልባት እኛም የተወደድነው እንተ እንዳልከው የዳይኖሰር ዘሮች ስለሆንን ሳይሆን ከሆነ በዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ሊሆን ይችላል ። በዘርህ ማሰብህ አቁም
ምን ? ከብዐድ ነገር ጋር ቀላቅለውን ይሆናል? ለዛነው ሣር ሳይ ጋጥ ጋጥ ፣ሜዳ ሳይ ደግሞ ተደባለል ተደባለል የሚለኝ ?
#አዎን የሐበሻውን ዶሮ ከፈረንጅ ዶሮ ጋር የፈረንጁን ዶሮ ከሰጎን እዋስ ጋር መቀላቀሉ ሳይንስ ዐዋቂነት ሆኟል።
ሰው ግን ለምን እንዲህ ከፋ ?
#ያወቀ እየመሰለው አንድም ጽድቅና ኩነኔን ቢረሳ ነዋ እኛኸ ታላቅ ሰው ያሉትን የሚያስተውል መቼ ይሆን ? "ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፉት ደግነት ሳይሻል አይቀርም"
አ.አ ኢትዮጵያ
ኃ/ማርያም ተርቢኖስ ሰብስቤ
ታኅሣሥ 28 ቀን 2014 ዓ.ም