#ኑ_ይህን_ድንቅ_እዩ !
______________
#የእመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ"፭ ቀናት ያክል የመገለጥ በዓል
#ከቅዱሳን_ክብር_የማርያም_ክብር_ይበልጣል ፤ የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማሕፀንዋ ተሸከመችው። ይህች ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች ከሦስቱ አካል ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና። የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት።
#ለቅዱሳን_ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት። በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሁኗልና።
#ኑ_ይህንድንቅ_እዩ። ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፤ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፤ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት።
የማይታወቅ ተገለጠ፤ የማይታይ ታየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በርግጥ ሰው ሆነ። ትላንት የነበረው ዛሬም ያለው መቼም የሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባሕርይ ነው። #ቅድስት_ሆይ_ለምኝልን።
____ሶሪያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_የረቡዕ ውዳሴ ማርያም____
______________
#የእመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ"፭ ቀናት ያክል የመገለጥ በዓል
#ከቅዱሳን_ክብር_የማርያም_ክብር_ይበልጣል ፤ የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማሕፀንዋ ተሸከመችው። ይህች ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች ከሦስቱ አካል ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና። የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት።
#ለቅዱሳን_ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት። በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሁኗልና።
#ኑ_ይህንድንቅ_እዩ። ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፤ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፤ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት።
የማይታወቅ ተገለጠ፤ የማይታይ ታየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በርግጥ ሰው ሆነ። ትላንት የነበረው ዛሬም ያለው መቼም የሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባሕርይ ነው። #ቅድስት_ሆይ_ለምኝልን።
____ሶሪያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_የረቡዕ ውዳሴ ማርያም____
ዐውደ ምሕረት
Photo
#ኑ-ዝምታን-እንተርጉም
---------------------------------
"አቤቱ ለአፌ ጠባቂን አኑርለት
የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ"
አጥብቆ ቢደግማት የዳዊትን መዝሙር
ተቀጥሮለት መሰል ጠባቂ ከናፍር
እንጂማ
ጆሮ አልባ በሆነች ባናጋሪ ዓለም
አስችሎት ዝም የሚል ትግስተኛ የለም
እኔስ ይመስለኛል የአባቴ ዝምታ
ቃል ያለማውጣቱ የጸትታው ፋታ
በጆሮ አልባ ሀገር
በደንቆሮ መንደር
ሰሚ በሌለበት
ፊደል ማባከኑ ቃላት ማበላሸት
መረበሽ ነው እንጂ መግባባት የለበት
ብሎ ይመስለኛል
እኔስ ይመስለኛል የአባቴ አርምሞ
በማይሰሙ ሰዎች ነብሰ ሥጋው ታሞ
ሰልችቶት ይሆናል አርሞ አርሞ
እንጂማ
እንዲያ ባይሆን ኖሮ
ባልሸሸ ነበረ ካደገበት ጓሮ
እኔስ ይመስለኛል ያባቴ አርሞሞ
ለአንድ መንጋ አንድ እረኛ
ይበቃዋል ካለ እውነተኛ
ከዛ ውጪ ነው ምንደኛ
ብሎ አስቦ በትትና
እራሱን ዝቅ አረገና
ከሰማይ ቤት ደጅ ጠና
የይህን ዓለም ንቋልና
እኔስ ይመስለኛ ያባቴ ዝምታ
አንድም ቢደርስ ነው ከቅዱሳን ተርታ
የበቃ ቢሆን ነው ምግባሩ የበረታ
ግን.... ግን
በሚንጫጫ ዓለም በማይሰማ ቅዬ
እንዴት አስችሏቸው ዝም አሉ አቡዬ?
ለፍላፊ ሳይሰሙት
ኸኸ ባይ ሳይነግሩት
ጆሮ በጠፋበት
ምላስ ሰንበር በዝቶ
ሲገድፍ የሚውል አንደበት ጾም ትቶ
ድንጋዮን ያልጣለው ከአፉ አውጥቶ
እንደምን ተጠራ ዳግማዊው አጋቶ ን ???
#ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 25 /2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
---------------------------------
"አቤቱ ለአፌ ጠባቂን አኑርለት
የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ"
አጥብቆ ቢደግማት የዳዊትን መዝሙር
ተቀጥሮለት መሰል ጠባቂ ከናፍር
እንጂማ
ጆሮ አልባ በሆነች ባናጋሪ ዓለም
አስችሎት ዝም የሚል ትግስተኛ የለም
እኔስ ይመስለኛል የአባቴ ዝምታ
ቃል ያለማውጣቱ የጸትታው ፋታ
በጆሮ አልባ ሀገር
በደንቆሮ መንደር
ሰሚ በሌለበት
ፊደል ማባከኑ ቃላት ማበላሸት
መረበሽ ነው እንጂ መግባባት የለበት
ብሎ ይመስለኛል
እኔስ ይመስለኛል የአባቴ አርምሞ
በማይሰሙ ሰዎች ነብሰ ሥጋው ታሞ
ሰልችቶት ይሆናል አርሞ አርሞ
እንጂማ
እንዲያ ባይሆን ኖሮ
ባልሸሸ ነበረ ካደገበት ጓሮ
እኔስ ይመስለኛል ያባቴ አርሞሞ
ለአንድ መንጋ አንድ እረኛ
ይበቃዋል ካለ እውነተኛ
ከዛ ውጪ ነው ምንደኛ
ብሎ አስቦ በትትና
እራሱን ዝቅ አረገና
ከሰማይ ቤት ደጅ ጠና
የይህን ዓለም ንቋልና
እኔስ ይመስለኛ ያባቴ ዝምታ
አንድም ቢደርስ ነው ከቅዱሳን ተርታ
የበቃ ቢሆን ነው ምግባሩ የበረታ
ግን.... ግን
በሚንጫጫ ዓለም በማይሰማ ቅዬ
እንዴት አስችሏቸው ዝም አሉ አቡዬ?
ለፍላፊ ሳይሰሙት
ኸኸ ባይ ሳይነግሩት
ጆሮ በጠፋበት
ምላስ ሰንበር በዝቶ
ሲገድፍ የሚውል አንደበት ጾም ትቶ
ድንጋዮን ያልጣለው ከአፉ አውጥቶ
እንደምን ተጠራ ዳግማዊው አጋቶ ን ???
#ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 25 /2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ