ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
" #ካለ_ፈጣሪ_አሟጠሽ ጋግሪ"
______________________
ስስት ንፍገት ፣ሆዳምነትን፣ ኑሮዬ ይበቃኛል አለማለትን እንዲሁም አልጠግብ ባይነትን የሚገልጽ ግሥ ነው ። (የመ.ቅዱስ መዝገበ ቃላት/ ገጽ ፹ ፭ ) በዘመናች ቋንቋ "ቋጣሪነት" ልንለው እንችላለን። በንባባችን ላይ ቋጣሪነት ወይም ስስታምነት ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ የመጣ ነገር እንጂ በሰው ተፈጥሮ ውስጥ "ስስት" ወይም "ንፍገት" የሚባል ነገር የለም ። የስስት ተቃራኒ ቸርነት ነው ። ቸር ደግሞ #እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሌሎች ቸር ቢሆኑ #ከእግዚአብሔር የተቀበሉን በመስጠት ነው እንጂ የእራሳቸው አንዳች የላቸውም ቸርነትን ለሌላው ቢያደርጉ በሥጋ የሕሊና ሰላም ፣በሃይማኖት ደግሞ ጽድቅን ፈልገውበት ነው ።

#እግዚአብሔር ቸር ቢሆን ግን እጸድቅበት አይል ነገር ጻድቅ ነው እከብርበት አይል ነገርም ክቡር ነው ስለዚህ ቸርነት ማንም ያልሰጠው ማንምም የማይነጥቀው የእግዚአብሔር የባሕሪው ገንዘቡ ነው:: “ #ከአንዱ_ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።” ሉቃ ፲ ፰ ፥፲ ፱

ይህን ያልተገነዘበው ዲያቢሎስ እሩቅ ብዕሲ (ተራ ሰው) መስሎት አርባ ቀን በገዳመ ቆሮንቶስ ጾሞ ሲወጣ መራቡን ዐይቶ ቸሩ መድኃኔዓለምን በስስት ሊፈትነው ቀረበ ። በኮሮጆም ትኩስ የሚሸት ዳቦ ይዞ "የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ ይህን ድንጋይ ዳቦ እንዲሆን እዘዝ " አለው :: #ማቴ ፬÷፫

#ቸሩ_መድኃኔ_ዓለምም ማንነቴን ላሳየው፤ ሁሉን ቻይነቴን ይወቅልኝ ሳይል ዲያቢሎስ እንዳለው ድንጋዮን ዳቦ ሳያደርግ "ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም " ተብሎ ተጽፏል ብሎ " #በትዕግስት" ድል ነሳው። #ማቴ ፬÷፬

በበርሃ የሚኖሩ መነኮሳት ፆራቸው ስስት ነው ፤ በፈለጉ ጊዜ ምግባቸውን አያገኙምና ‹‹ ያለችን ብንመፀውት ሰውን ብናበላ ያለችን ታልቅብናለች ከዚያ ምን እንበላለን›› እያሉ በስስት ብዙውን ይፈተናሉ፡፡ ስለዚህ ቸሩ ፈጣሪያቸን ይህን የስስት ፈተና እንዴት በትዕግሥት ድል ማድረግ እንደሚችሉ ሲያስተምራቸው በመነኮሳት ቦታ በበርሃ ተገኝቶ ዲያቢሎስን በትዕግስ "ሰው በእጀራ ብቻ አይኖርም" ብሎ ድል አደረገው፡፡

#በስስት የመጣብንን ፈተና በትግሥትና በቸርነት ለንሻገረው ያስፈልጋል ያ ሲባል ግን ቁጠባንና ባህሉን ለመሸርሸር ሳይሆን የመቀበል ግልብጥ ስሌት መስጠት እንደሆነ ጭምር ለማስታወስ ነው ። ሁለት ነገር ያለው ሰው ሌላ ሦስተኛ ነገር ከፈጣሪው ከፈለገ ከያዘው ሁለት ነገር ቢያንስ አንዱን እንኳ ምንም ለሌለው መስጠት ይገባዋል :: ለመቀበልምኮ መስጠት ያስፈልጋል! ሰው ሁለት እጅ የተሰጠው በአንዱ ተቀብሎ በሌላኛው እንዲያቀብል ነው እንዲሉ አበው።


“ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።” #ምሳሌ ፲ ፱ ፥፲ ፯ “ኀጥእ ቀኑን ሁሉ ምኞትን ይመኛል፤ ጻድቅ ግን ይሰጣል፥ አይሰስትም።” #ምሳሌ ፳ ፩ ፥ ፳ ፮ ስለዚህም በክርስቶስ እኖራለሁ የሚል ክርስቶስ ደግሞ እንደተመላለስ ይመላለስ ! ጸሎቱም ሁል ጊዜ “ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን።” የሚል ይሁን ! #መዝ ፻ ፲ ፰ (፻ ፲ ፱) ፥ ፴ ፮
......... ይቆየን..........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" #ካለ_ፈጣሪ_አሟጠሽ ጋግሪ"
______________________
ስስት ንፍገት ፣ሆዳምነትን፣ ኑሮዬ ይበቃኛል አለማለትን እንዲሁም አልጠግብ ባይነትን የሚገልጽ ግሥ ነው ። (የመ.ቅዱስ መዝገበ ቃላት/ ገጽ ፹ ፭ ) በዘመናች ቋንቋ "ቋጣሪነት" ልንለው እንችላለን። በንባባችን ላይ ቋጣሪነት ወይም ስስታምነት ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ የመጣ ነገር እንጂ በሰው ተፈጥሮ ውስጥ "ስስት" ወይም "ንፍገት" የሚባል ነገር የለም ። የስስት ተቃራኒ ቸርነት ነው ። ቸር ደግሞ #እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሌሎች ቸር ቢሆኑ #ከእግዚአብሔር የተቀበሉን በመስጠት ነው እንጂ የእራሳቸው አንዳች የላቸውም ቸርነትን ለሌላው ቢያደርጉ በሥጋ የሕሊና ሰላም ፣በሃይማኖት ደግሞ ጽድቅን ፈልገውበት ነው ።

#እግዚአብሔር ቸር ቢሆን ግን እጸድቅበት አይል ነገር ጻድቅ ነው እከብርበት አይል ነገርም ክቡር ነው ስለዚህ ቸርነት ማንም ያልሰጠው ማንምም የማይነጥቀው የእግዚአብሔር የባሕሪው ገንዘቡ ነው:: “ #ከአንዱ_ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።” ሉቃ ፲ ፰ ፥፲ ፱

ይህን ያልተገነዘበው ዲያቢሎስ እሩቅ ብዕሲ (ተራ ሰው) መስሎት አርባ ቀን በገዳመ ቆሮንቶስ ጾሞ ሲወጣ መራቡን ዐይቶ ቸሩ መድኃኔዓለምን በስስት ሊፈትነው ቀረበ ። በኮሮጆም ትኩስ የሚሸት ዳቦ ይዞ "የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ ይህን ድንጋይ ዳቦ እንዲሆን እዘዝ " አለው :: #ማቴ ፬÷፫

#ቸሩ_መድኃኔ_ዓለምም ማንነቴን ላሳየው፤ ሁሉን ቻይነቴን ይወቅልኝ ሳይል ዲያቢሎስ እንዳለው ድንጋዮን ዳቦ ሳያደርግ "ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም " ተብሎ ተጽፏል ብሎ " #በትዕግስት" ድል ነሳው። #ማቴ ፬÷፬

በበርሃ የሚኖሩ መነኮሳት ፆራቸው ስስት ነው ፤ በፈለጉ ጊዜ ምግባቸውን አያገኙምና ‹‹ ያለችን ብንመፀውት ሰውን ብናበላ ያለችን ታልቅብናለች ከዚያ ምን እንበላለን›› እያሉ በስስት ብዙውን ይፈተናሉ፡፡ ስለዚህ ቸሩ ፈጣሪያቸን ይህን የስስት ፈተና እንዴት በትዕግሥት ድል ማድረግ እንደሚችሉ ሲያስተምራቸው በመነኮሳት ቦታ በበርሃ ተገኝቶ ዲያቢሎስን በትዕግስ "ሰው በእጀራ ብቻ አይኖርም" ብሎ ድል አደረገው፡፡

#በስስት የመጣብንን ፈተና በትግሥትና በቸርነት ለንሻገረው ያስፈልጋል ያ ሲባል ግን ቁጠባንና ባህሉን ለመሸርሸር ሳይሆን የመቀበል ግልብጥ ስሌት መስጠት እንደሆነ ጭምር ለማስታወስ ነው ። ሁለት ነገር ያለው ሰው ሌላ ሦስተኛ ነገር ከፈጣሪው ከፈለገ ከያዘው ሁለት ነገር ቢያንስ አንዱን እንኳ ምንም ለሌለው መስጠት ይገባዋል :: ለመቀበልምኮ መስጠት ያስፈልጋል! ሰው ሁለት እጅ የተሰጠው በአንዱ ተቀብሎ በሌላኛው እንዲያቀብል ነው እንዲሉ አበው።


“ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።” #ምሳሌ ፲ ፱ ፥፲ ፯ “ኀጥእ ቀኑን ሁሉ ምኞትን ይመኛል፤ ጻድቅ ግን ይሰጣል፥ አይሰስትም።” #ምሳሌ ፳ ፩ ፥ ፳ ፮ ስለዚህም በክርስቶስ እኖራለሁ የሚል ክርስቶስ ደግሞ እንደተመላለስ ይመላለስ ! ጸሎቱም ሁል ጊዜ “ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን።” የሚል ይሁን ! #መዝ ፻ ፲ ፰ (፻ ፲ ፱) ፥ ፴ ፮
......... ይቆየን..........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም