Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
❤"የእግዚአብሔር መልአክ"❤
#በስሙ ስመ እግዚአብሔርን የተሸከመ መልአክ ማለት ነው።ሚካኤል፣ገብርኤል፣ሩፋኤል ወ.ዘ.ተ የሚሉት ስሞች ውስጥ "ኤል" የሚለው ቃል አምላክ ማለት ነውና።“ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ።”ዘጸ 23፥21
እንዲል።
#በልቡ ስብሐተ እግዚአብሔርን የያዘ በአንደበቱም
እግዚአብሔርን የሚያመሰግን መልአክ ነው።“አንዱም ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር።”(ኢሳ 6፥3) እንዳለ ነቢዩ።
#ፈቃደ እግዚአብሔርን የሚፈጽም ማለት ነው።ማር ያለውን ይምራል ፤ ቅሰፍ ያለውን ይቀስፋልና።
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”(መዝ33፥7)
“ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ።”ሐዋ12፥23
ተብሎ እንደተጻፈ።
#የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጥ መልአክ ነው።“ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።” (መዝ 18፥1) በሚለው ኃይለ ቃል ውስጥ "ሰማያት" የሚለው ቃል በምሥጢር መላእክት ማለት ነው።ይኸውም “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”
(ሉቃ2፥14) ባለው ኃይለ ቃል ውስጥ ካለው "አርያም" ከሚለው ቃል ጋር አንድ ነው።
#የእግዚአብሔርን ሕዝብ መርቶ ወደ ተዘጋጀላቸው ስፍራ የሚያገባ መልአክ ነው።“በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።”
( ዘጸ 23፥20) እንዲል።
#በእግዚአብሔር የሚታመነውን ሰው እግሩ በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቹ የሚያነሣ መልአክ ነው።"በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
(መዝ 90:11-12)
#ሰዎች ሁሉ መዳንን (መንግሥተ እግዚአብሔርን) እንዲወርሱ ለማገዝ የሚላክ፤የሚያገለግልም መልአክ ነው።“ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?”(ዕብ 1፥14) እንዳለ ሐዋርያው።
#በኃጢአተኞች መዳንም የሚደሰት መልአክ ማለት ነው።“ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።”ሉቃ15፥10
ይኸውም ሰውን እጅግ እጅግ እጅግ የሚወድድ መልአከ ምሕረት፣መልአከ ፍስሐ፣መልአከ ሰላም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነው!!!በረከቱ ይደርብን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር ሚካኤል/2017 ዓ.ም
#በስሙ ስመ እግዚአብሔርን የተሸከመ መልአክ ማለት ነው።ሚካኤል፣ገብርኤል፣ሩፋኤል ወ.ዘ.ተ የሚሉት ስሞች ውስጥ "ኤል" የሚለው ቃል አምላክ ማለት ነውና።“ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ።”ዘጸ 23፥21
እንዲል።
#በልቡ ስብሐተ እግዚአብሔርን የያዘ በአንደበቱም
እግዚአብሔርን የሚያመሰግን መልአክ ነው።“አንዱም ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር።”(ኢሳ 6፥3) እንዳለ ነቢዩ።
#ፈቃደ እግዚአብሔርን የሚፈጽም ማለት ነው።ማር ያለውን ይምራል ፤ ቅሰፍ ያለውን ይቀስፋልና።
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”(መዝ33፥7)
“ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ።”ሐዋ12፥23
ተብሎ እንደተጻፈ።
#የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጥ መልአክ ነው።“ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።” (መዝ 18፥1) በሚለው ኃይለ ቃል ውስጥ "ሰማያት" የሚለው ቃል በምሥጢር መላእክት ማለት ነው።ይኸውም “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”
(ሉቃ2፥14) ባለው ኃይለ ቃል ውስጥ ካለው "አርያም" ከሚለው ቃል ጋር አንድ ነው።
#የእግዚአብሔርን ሕዝብ መርቶ ወደ ተዘጋጀላቸው ስፍራ የሚያገባ መልአክ ነው።“በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።”
( ዘጸ 23፥20) እንዲል።
#በእግዚአብሔር የሚታመነውን ሰው እግሩ በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቹ የሚያነሣ መልአክ ነው።"በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
(መዝ 90:11-12)
#ሰዎች ሁሉ መዳንን (መንግሥተ እግዚአብሔርን) እንዲወርሱ ለማገዝ የሚላክ፤የሚያገለግልም መልአክ ነው።“ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?”(ዕብ 1፥14) እንዳለ ሐዋርያው።
#በኃጢአተኞች መዳንም የሚደሰት መልአክ ማለት ነው።“ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።”ሉቃ15፥10
ይኸውም ሰውን እጅግ እጅግ እጅግ የሚወድድ መልአከ ምሕረት፣መልአከ ፍስሐ፣መልአከ ሰላም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነው!!!በረከቱ ይደርብን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር ሚካኤል/2017 ዓ.ም
❤ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ❤ (መዝ103፥27)
#ፍጥረት ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል።ምርጫ አይደለም የህልውና ጉዳይ እንጂ።በደመነፍስ ሕያዋን ሆነው የሚኖሩት እንስሳት፣አራዊት፣አዋዕፍ፣ዓሦችና አንበሪዎች እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ ተስፋ ያደርጉታል።እርሱም ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸዋል።ከቸር እጆቹ ጠግበው ያመሰግኑታል።
#ሰውም እንደ መላእክት ሁሉ "ተስፋ" የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።ተስፋውም በሕግ ቃልኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው።“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።”(ዘፍ 2፥17) ሲል ጌታ ለሰው ማዘዙ የሰው የሕይወት ተስፋው ሕጉን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዳል።
#ኋላም በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት የተሰጠው “ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።” (ዘጸ 20፥6) የሚለው ቃል ከላይ ያነሣነውን ሐሳብ ያጠናክረዋል።
#በእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተወደደ ሰው የሚባል ፍጡር ለሕይወቱ የተሰጠውን ሕግ አፍርሶ ቢበድል እንኳን ይቅር የመባል ተስፋ አለው። ስለዚህ የሚተማመነው "በእግዚአብሔር ምሕረት" ላይ እንጂ በራሱ ሕግ የመጠበቅ ብቃት ላይ አይሆንም።
#ተስፋ ቆርጫለሁ
#የሚለው ድምፅ እዚህና እዚያ ይሰማል።ተስፋ ማለት እግዚአብሔር ከሆነ ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት እግዚአብሔርን ትቼአለሁ ማለት ይሆናል።ተስፋ ለመቁረጥ ተስፋ ማድረግ ያስፈልጋል።ሰው ተስፋ የሚያደርጋቸው ጊዜአዊ ነገሮች ከእውነተኛ ተስፋው ከእግዚአብሔር ጋር ይምታቱበትና፤ያልተሳኩ እንደሆነ
ተስፋ ቆረጥሁ ይላል።መማርን፣አንድ ቦታ ተቀጥሮ መሥራትን፣እገሌን ወይ እገሊትን ማግባትን፣ልጆች መውለድን፣ባህር ማዶ ተሻግሮ መኖርን ወ.ዘ.ተ።
#አሁንስ ደከመኝ፣ታከትኩ፣ከዚህ በላይስ አልሄድም፣
በቃኝ ... የሚሉ ንግግሮች ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች አለመሳካት የሚነገሩ ናቸው።"እናንተ ስለፈለጋችሁ የሚሆን ነገር የለም፤ሆኑ አልሆኑ የእግረ መንገድ ጉዳዮች ናቸው።እነዚህ ጉዳዮች እንደ ሕፃናት ማቆያዎች (Day cares) ናቸው።የተፈጠራችሁላቸው ዓላማዎች አይደሉም።" እያለ ሕፃንነታችንን እየነገረን ከሆነስ!? "ፈቃድህ ይሁን" ብለን በፈቃዱ ሲከለክለን ማዘን አይገባም።
#ኑሮው!!! ኧረ ውድነቱ!!! "እግዚአብሔር ሆይ ወዴት ነህ???" "አንተን በማኖር ግብር ነኝ" ይልሃላ።ወይ ግሩም እስከዛሬ ታዲያ በኑሮ ርካሽነት ነበር እንዴ የኖርነው!?በእኔ ዕድሜ ሳውቅ በየጊዜው "ኑሮ ተወደደ" ነው የሚባለው።ሲወደድ እንጂ ሲረክስ ያየሁት ነገር የለም (ከሰው(ከእኔ) በቀር 😭)።ግን በቸርነቱ አለን!!!ግሩም ነው መቼስ!!!
#ለነፍሳችን ለማደር ከኃጢአት ጋር በምናደርገው ትግልም ተመሳሳዩ ነገር ይገጥመናል።"ከዚህ በኋላ ይህንን ያህል በድለህ እግዚአብሔር ይቅር የሚልህ መሰለህ" የሚል ሐሳብ በኅሊናህ ሲመጣ "አዎን ይቅር ይለኛል" በለው።ገድለህ "አዎን"፤አመንዝረህ "አዎን"፤ዘሙተህ "አዎን"፤ሰርቀህ "አዎን"፤"ዋሽተህ" አዎን!!!
#ታዲያ የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?
#ቅዱስ ዳዊት “መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም።”(መዝ 76፥19) ሲል የእግዚአብሔር አሠረ ፍትሑ (የፍርዱ መንገድ) እንደማይታወቅ ተናግሯል።ቅዱስ ጳውሎስም “የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።”(ሮሜ 11 ፥ 33) በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ አይመረመሬነት ገልጧል።ስለዚህ "የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "በራሱ ዘንድ ነው" የሚል ነው።
#ይህንን ሁሉ አጥፈተህማ እግዚአብሔር ሳይቀጣህ አይቀርም" የሚል ድምፅ ኅሊናህ ውስጥ ሲመላለስ፤"እግዚአብሔር ደግ አባቴ ነውና በደንብ ይቅጣኝ፤አንዴ አይደለም መቶ ጊዜ ይቅጣኝ።ብቻ ለአንተ ለከይሲው አሳልፎ አይሰጠኝ።እንኳን የእኔ የአንዱ በደል ከአዳም ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚሠራው ኃጢአት የደጉ አባቴን የእግዚአብሔርን አንዲቱን የምሕረት ጠብታ አያህልም!!!" በለው። እንዲህ ብለን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እግዚአብሔር ደስ ይለዋል።ቁጣውን ሁሉ ይተወዋል።ሰው ራሱ ላይ ከልቡ ሲፈርድ እግዚአብሔር ፍርዱን ይተውለታል!!!
“እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ ጽድቅንም ይወድዳል፤ ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።”(መዝ 11፥7) እንዳለ መዝሙረኛው በጽድቅ ራሳችን ላይ ፈርደን፤በልብ ቅንነት ራሳችንን ጻድቅ ለሆነ እግዚአብሔር ስንሰጥ፤እግዚአብሔር ደግሞ የምሕረት ፊቱን ያሳየናል።ይህንንም በልባችን በሚመላብን ፍጹም ሰላምና ደስታ እናውቃለን!!!
"#ሳለ #መድኃኔዓለም" የምወዳት የእናቶቼ ብሂል ናት።እውነትም "#ሳለ #መድኃኔዓለም" #አምላከ #ተክለሃይማኖት!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 13/2017 ዓ.ም
#ፍጥረት ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል።ምርጫ አይደለም የህልውና ጉዳይ እንጂ።በደመነፍስ ሕያዋን ሆነው የሚኖሩት እንስሳት፣አራዊት፣አዋዕፍ፣ዓሦችና አንበሪዎች እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ ተስፋ ያደርጉታል።እርሱም ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸዋል።ከቸር እጆቹ ጠግበው ያመሰግኑታል።
#ሰውም እንደ መላእክት ሁሉ "ተስፋ" የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።ተስፋውም በሕግ ቃልኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው።“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።”(ዘፍ 2፥17) ሲል ጌታ ለሰው ማዘዙ የሰው የሕይወት ተስፋው ሕጉን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዳል።
#ኋላም በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት የተሰጠው “ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።” (ዘጸ 20፥6) የሚለው ቃል ከላይ ያነሣነውን ሐሳብ ያጠናክረዋል።
#በእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተወደደ ሰው የሚባል ፍጡር ለሕይወቱ የተሰጠውን ሕግ አፍርሶ ቢበድል እንኳን ይቅር የመባል ተስፋ አለው። ስለዚህ የሚተማመነው "በእግዚአብሔር ምሕረት" ላይ እንጂ በራሱ ሕግ የመጠበቅ ብቃት ላይ አይሆንም።
#ተስፋ ቆርጫለሁ
#የሚለው ድምፅ እዚህና እዚያ ይሰማል።ተስፋ ማለት እግዚአብሔር ከሆነ ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት እግዚአብሔርን ትቼአለሁ ማለት ይሆናል።ተስፋ ለመቁረጥ ተስፋ ማድረግ ያስፈልጋል።ሰው ተስፋ የሚያደርጋቸው ጊዜአዊ ነገሮች ከእውነተኛ ተስፋው ከእግዚአብሔር ጋር ይምታቱበትና፤ያልተሳኩ እንደሆነ
ተስፋ ቆረጥሁ ይላል።መማርን፣አንድ ቦታ ተቀጥሮ መሥራትን፣እገሌን ወይ እገሊትን ማግባትን፣ልጆች መውለድን፣ባህር ማዶ ተሻግሮ መኖርን ወ.ዘ.ተ።
#አሁንስ ደከመኝ፣ታከትኩ፣ከዚህ በላይስ አልሄድም፣
በቃኝ ... የሚሉ ንግግሮች ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች አለመሳካት የሚነገሩ ናቸው።"እናንተ ስለፈለጋችሁ የሚሆን ነገር የለም፤ሆኑ አልሆኑ የእግረ መንገድ ጉዳዮች ናቸው።እነዚህ ጉዳዮች እንደ ሕፃናት ማቆያዎች (Day cares) ናቸው።የተፈጠራችሁላቸው ዓላማዎች አይደሉም።" እያለ ሕፃንነታችንን እየነገረን ከሆነስ!? "ፈቃድህ ይሁን" ብለን በፈቃዱ ሲከለክለን ማዘን አይገባም።
#ኑሮው!!! ኧረ ውድነቱ!!! "እግዚአብሔር ሆይ ወዴት ነህ???" "አንተን በማኖር ግብር ነኝ" ይልሃላ።ወይ ግሩም እስከዛሬ ታዲያ በኑሮ ርካሽነት ነበር እንዴ የኖርነው!?በእኔ ዕድሜ ሳውቅ በየጊዜው "ኑሮ ተወደደ" ነው የሚባለው።ሲወደድ እንጂ ሲረክስ ያየሁት ነገር የለም (ከሰው(ከእኔ) በቀር 😭)።ግን በቸርነቱ አለን!!!ግሩም ነው መቼስ!!!
#ለነፍሳችን ለማደር ከኃጢአት ጋር በምናደርገው ትግልም ተመሳሳዩ ነገር ይገጥመናል።"ከዚህ በኋላ ይህንን ያህል በድለህ እግዚአብሔር ይቅር የሚልህ መሰለህ" የሚል ሐሳብ በኅሊናህ ሲመጣ "አዎን ይቅር ይለኛል" በለው።ገድለህ "አዎን"፤አመንዝረህ "አዎን"፤ዘሙተህ "አዎን"፤ሰርቀህ "አዎን"፤"ዋሽተህ" አዎን!!!
#ታዲያ የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?
#ቅዱስ ዳዊት “መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም።”(መዝ 76፥19) ሲል የእግዚአብሔር አሠረ ፍትሑ (የፍርዱ መንገድ) እንደማይታወቅ ተናግሯል።ቅዱስ ጳውሎስም “የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።”(ሮሜ 11 ፥ 33) በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ አይመረመሬነት ገልጧል።ስለዚህ "የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "በራሱ ዘንድ ነው" የሚል ነው።
#ይህንን ሁሉ አጥፈተህማ እግዚአብሔር ሳይቀጣህ አይቀርም" የሚል ድምፅ ኅሊናህ ውስጥ ሲመላለስ፤"እግዚአብሔር ደግ አባቴ ነውና በደንብ ይቅጣኝ፤አንዴ አይደለም መቶ ጊዜ ይቅጣኝ።ብቻ ለአንተ ለከይሲው አሳልፎ አይሰጠኝ።እንኳን የእኔ የአንዱ በደል ከአዳም ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚሠራው ኃጢአት የደጉ አባቴን የእግዚአብሔርን አንዲቱን የምሕረት ጠብታ አያህልም!!!" በለው። እንዲህ ብለን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እግዚአብሔር ደስ ይለዋል።ቁጣውን ሁሉ ይተወዋል።ሰው ራሱ ላይ ከልቡ ሲፈርድ እግዚአብሔር ፍርዱን ይተውለታል!!!
“እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ ጽድቅንም ይወድዳል፤ ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።”(መዝ 11፥7) እንዳለ መዝሙረኛው በጽድቅ ራሳችን ላይ ፈርደን፤በልብ ቅንነት ራሳችንን ጻድቅ ለሆነ እግዚአብሔር ስንሰጥ፤እግዚአብሔር ደግሞ የምሕረት ፊቱን ያሳየናል።ይህንንም በልባችን በሚመላብን ፍጹም ሰላምና ደስታ እናውቃለን!!!
"#ሳለ #መድኃኔዓለም" የምወዳት የእናቶቼ ብሂል ናት።እውነትም "#ሳለ #መድኃኔዓለም" #አምላከ #ተክለሃይማኖት!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 13/2017 ዓ.ም
#ተስፋ ነቢያት ክርስቶስ
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
#ተስፋ ነቢያት ክርስቶስ
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
❤ሥላሴ❤
#ከቸርነትህ እጅግ እጅግ እጅግ ጥቂቱን ልበል ፦
#ሥላሴ ጌታዬ አምላኬም❤
#ሥላሴ አባቴ እናቴም❤
#ሥላሴ የጠላትን ጦር መመከቻ ጋሻዬ❤
#ሥላሴ ጠላትን ማጥቂያ ጦሬ❤
#ሥላሴ ከኃዘኔ መጽናኛ ደስታዬ❤
#ሥላሴ በድካሜ ጊዜ ጉልበቴና ኃይሌ❤
#ሥላሴ የተቆረጠውን የምትቀጥል ተስፋዬ❤
#ሥላሴ ሳዝን ሲከፋኝ ማልቀሻዬ❤
#ሥላሴ ሩኅሩኅ የጽድቅ ዳኛዬ❤
#ሥላሴ ሃይማኖቴ ማዕተቤም❤
+ኃይልየ #ሥላሴ ወጸወንየ #ሥላሴ
+በስመ #ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ
+ ሁሉ #ከሥላሴ #በሥላሴ #ለሥላሴ ሆነ !!!
+ክብር #ለሥላሴ በሰማይ በምድር!!! +በባሕርና በጥልቆች ሁሉ ይሁን አሜን!!!
ታኅሣሥ #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ከቸርነትህ እጅግ እጅግ እጅግ ጥቂቱን ልበል ፦
#ሥላሴ ጌታዬ አምላኬም❤
#ሥላሴ አባቴ እናቴም❤
#ሥላሴ የጠላትን ጦር መመከቻ ጋሻዬ❤
#ሥላሴ ጠላትን ማጥቂያ ጦሬ❤
#ሥላሴ ከኃዘኔ መጽናኛ ደስታዬ❤
#ሥላሴ በድካሜ ጊዜ ጉልበቴና ኃይሌ❤
#ሥላሴ የተቆረጠውን የምትቀጥል ተስፋዬ❤
#ሥላሴ ሳዝን ሲከፋኝ ማልቀሻዬ❤
#ሥላሴ ሩኅሩኅ የጽድቅ ዳኛዬ❤
#ሥላሴ ሃይማኖቴ ማዕተቤም❤
+ኃይልየ #ሥላሴ ወጸወንየ #ሥላሴ
+በስመ #ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ
+ ሁሉ #ከሥላሴ #በሥላሴ #ለሥላሴ ሆነ !!!
+ክብር #ለሥላሴ በሰማይ በምድር!!! +በባሕርና በጥልቆች ሁሉ ይሁን አሜን!!!
ታኅሣሥ #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶቼ በተጠቀሱት የሒሳብ ቁጥሮች የአቅማችንን ( ቢያንስ የአንድ ነጠላ እና ማዕተብ) አስተዋጽኦ በማበርከት የዚህ ታሪክ ተካፋይ እንሁን፤ ለአንዲት ነፍስ የክርስትና አባት/እናት እንሁን።
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴ከተጠሩት መሐል እንዳልሄድ ኮብልዬ በ1987ዓ.ም የተዘመረ#Ethiopian Orthodox Tewabido Old Mezmur
መጥቅዕ ሚዲያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ዶግማ ቀኖና ትውፊት እና ሥርዓት የጠበቁ የቅዱስ ያሬድ መዐዛ ያላቸውን ዝማሬዎችን አውደ ስብከቶችን የበጎ አድራጎት ክንውኖችን በመንፈሳዊ ህይወት እንዲጠነክሩ የሚያስችል ተግባራዊ የህይወት ተሞክሮዎችን ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ክንውኖችን እና ሌሎች መሰል ጉዳዮች የሚቀርቡበት ነው፤
ማኅቶት ቲዩብ, ኢቲአርት ሚዲያ, ታቦር ቲዩብ, ንቁ የጸሎትና…
ማኅቶት ቲዩብ, ኢቲአርት ሚዲያ, ታቦር ቲዩብ, ንቁ የጸሎትና…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
የዩቲዩብ ቻናሌን subscribe ያድርጉ ቤተሰቦች 🙏🙏🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
http://www.youtube.com/@ZemariDawitkibru2405
Youtube channel - Zemari Dawit kibru | Official ዘማሪ ዳዊት ክብሩ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የማይቀርበት መርሐግብር
ቀን - ታኅሳስ 20/2017 ዓ.ም እሑድ በሰንበተ ክርስቲያን
ሰዓት - ከ7:00 ጀምሮ
አድራሻ - ኮተቤ ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ኮተቤ 02 ሐና ማርያም ቤ/ክ ከፍ ብሎ እንዳይቀሩ 🙏🙏🙏
ቀን - ታኅሳስ 20/2017 ዓ.ም እሑድ በሰንበተ ክርስቲያን
ሰዓት - ከ7:00 ጀምሮ
አድራሻ - ኮተቤ ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ኮተቤ 02 ሐና ማርያም ቤ/ክ ከፍ ብሎ እንዳይቀሩ 🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
Ethiopia : #ዲያቆን ዘላለም ታዬ #ወደ ድኅነት የሚያመራ ድንቅ ስብከት #የኃጢኣትን በር ጥልቀት አሳየን #eotc #Dn Zelalem Taye #sibket
Ethiopia : #ዲያቆን ዘላለም ታዬ #ወደ ድኅነት የሚያመራ ድንቅ ስብከት #የኃጢኣትን በር ጥልቀት አሳየን #eotc #Dn Zelalem Taye #sibket
#sibket
#Mezmur
#ኆኅተ ብርሃን
#habesha
#eotcmk
#ኃጢአት
|ንስሐ
Sibket 2024, Ethiopia News, Habesha, Dr Abiy, Jawar Mohamed, Amharic Movie, Ethiopia music, Abel…
#sibket
#Mezmur
#ኆኅተ ብርሃን
#habesha
#eotcmk
#ኃጢአት
|ንስሐ
Sibket 2024, Ethiopia News, Habesha, Dr Abiy, Jawar Mohamed, Amharic Movie, Ethiopia music, Abel…
#ደስ ይበልሽ#
-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።
-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።
- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።
- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።
"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)
- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።
-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"
-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።
#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!
-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።
-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።
- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።
- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።
"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)
- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።
-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"
-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።
#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!
-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
❤ከዕለቱ #መዝሙር❤
#መዝሙረ ዳዊት 69
አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።
እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!
#ታኅሣሥ 23/2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#መዝሙረ ዳዊት 69
አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።
እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!
#ታኅሣሥ 23/2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
እንዳይቀሩ ተጋብዘዋል !🙏🙏🙏
" #ደስታ_ተክለ_ሃይማኖት_ተወለደ"
#የሚገቡት
እንኳን ማርያም ማረችሽ ፣
አሜን!
እንኳን ማርያም ሁለት አረገችሽ
አሜን!
#የሚወጡት
ማርያም ጭንሽን ታሙቀው
አሜን!
ማርያም በሽልም ታውጣሽ.......ይሏታል
የእመጫቷ መልስ አሜን !አሜን! የሚል ብቻ ነው። ይህ የእግዚእኃረያ ቤት ነው። ባሏ ፀጋ ዘአብ ደስታውን መቋቋም አቅቶታል ቤቷ በወዳጆቻቸው እና በጠያቂዎቻቸው እንዲሁም ባለ መውለዳቸው እንደ ኃጢያተኛ ቆጥሮ ይጠቋቆሙባቸው በነበሩ ሰዎች ተጨናንቃለች መካን ሚስቱ ወንድ ልጅን ወልዳለችና ። ለሁሉም እንደ ማዕረጋቸው ምሳ አደረጉላቸው ማጋረጃ ገልጠው እናቲቱንና ልጇን ቅቤ እስኪቀቡ የቸኮሉ ሳይኖሩ አይቀሩም ሌላው ግን ስለ አወላለዷ ለመረዳት ሰሀናቸውን ይዘው የወላዲቱ አልጋ አጠገብ ጠጋ ብለው የተቀመጡም አልጠፋም ።
#እርሷም_የእግዚአብሔርን ቸርነት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየመሰከረች ከሞተለሚ ምርኮ እንዴት ባለ ተአምር እደዳነች እያወራች ከባሏ ከፀጋ ዘአብም ጋርም ወንድ ልጅ ስለ መውለዷ አስቀድመው ዕራይን እንዳዮ እየነገረቻቸው ቀኑን በደስታ አሳለፈች ደስታ የሆነ ልጅ ወልዳለችና ።
*ስሙንስ ማን አላችሁት ?
ፍስሐ ጽዮን ( የጽዮን ደስታዋ) ብለነዋል ። ነገር ግን መላእኩ እንደነገረን ስሙ ሌላ ነው ከእናንተም የተሰወረ በልበ ሥላሴ የተጻፈ አዲስ ስም ይወጣለታል ብሎናል። "ተክለ ሃይማኖት"! ሕጻናት እንደሚያለቅሱም አያለቅስም ነበር "ቅኖች ሰዎች ሁል ጊዜ ደስ ይላቸዋል" እንደሚል
"ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለእራስህ አዘጋጀህ " አንደተባለም ሕጻኑ ፍስሐ ጽዮን በተወለደ ገና በሦስተኛው ቀን ከእናቱ እቅፍ ወርዶ "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ ሥላሴን በአንድነት በሦስትነት አመስግነ:: መዝ 9÷2
#ልጆች_የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው የእግዚአብሔር ስጦታ ሁሉ ደግሞ ደስ ያሰኛል ። ይልቁኑ እግዚአብሔር በእነርሱ አድሮ ድንቅ ሥራውን ይሰራባቸው ዘንድ ያዘጋጃቸው የቅዱሳን ሰዎች ልደታቸው ብቻ ሳይሆን እነርሱ እራሳቸው ደስታ ናቸው :: " በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ተድላና ደስታም ይሆንልሃል" ዮሐ1፥14 ተብሎ እንደተጻፈ እውነት ነው በመወለዱ ብዙዎች ደስ ብሎናል በሉቃስ ወንጌል ላይ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል በመጥምቀ መለኮት በቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ እንደሚሰኙ አስረግጦ ነግሮናል።
እነሆ ዛሬ ደግሞ እንደ ዮሐንስ በድንግልና የኖረ እንደ መጥምቁ ካህን ያውም ሰማያዊ የሆነ እንደ አዋጅ ነጋሪው በምድረ ኢትየጵያን ሁሉ እየዞረ ወንጌልን የሰበከ ለእናትና ለአባቱ እንዲሁም ለብዝዎቻችን የደስታ ምንጭ የሆነ የጽዮን ደስታዋ የተባለ ፍስሐ ጽዮን ተወለደ እነሆ እኛም እንደ ተስፋው ቃል ዳግማዊው ዮሐንስ ተወልዶልናልና ደስ አለን::
#መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰለሞን" ጻድቃን በበዙ ቁጥር ሕዝብ ደስ ይለዋል" እንዳለ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በተወለዱ ሰዓት ክርስቲያኖች ደስ ብሏቸዋል ምክንያቱም ጻድቁ ሕሙማነ ነፍስን በትምህርታቸው ሕሙማነ ሥጋን በተአምራታቸው እያዳኑና እየፈወሱ ለሕዝብ ደስታ ምንጭ ሆነዋል ያን ጊዜ ብቻም ሳይሆን ዛሬም በአፀደ ነፍስ ሳሉ ለኛ ለክርስቲያኖች የደስታችን ምንጭ ናቸው " የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለችና " ስለኛ የጽድቅ ሕይወት የሰላም እጦት የሃይማኖት ጉለት የምግባር ዝቅጠት ዕለት ዕለት ወደ ፈጣሪ እየጸለዮ ያማልዱናልና ነው #ያዕቆ 5÷16
በጻድቃን መወለድ ሕዝብ ደስ የሚለው በተወለዱበት ዘመን እና ወር ብቻ አይደለም አንዴ ጻድቃን ከተወለዱ በኃላ ሕዝብ ለዘለአለሙ ደስ ይለዋል ጻድቃን በአፀደ ሥጋም በአፀደ ነፍስም በምልጃቸው ደስ ያሰኛሉና ..... .. ልክ እንደዛሬው......
" #እኔ ግን ለዘለዓለሙ ደስ ይለኛል
ለያዕቆብ( #ለተክለ_ሃይማኖት )
አምላክም ዝማሬን አቀርባለው" #መዝ76÷9
...........ይቆየን........
የጻድቁ አባታችን የተክለ ሃይማኖት እረድኤትና በረከት በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ሁሉ ለዘለዓለሙ ቀንቶ ይኑር ....!!!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
በድጋሚ የተለጠፈ ጥንተ ጽሕፈቱ
ታህሳስ 22/2013ዓ/ም
#የሚገቡት
እንኳን ማርያም ማረችሽ ፣
አሜን!
እንኳን ማርያም ሁለት አረገችሽ
አሜን!
#የሚወጡት
ማርያም ጭንሽን ታሙቀው
አሜን!
ማርያም በሽልም ታውጣሽ.......ይሏታል
የእመጫቷ መልስ አሜን !አሜን! የሚል ብቻ ነው። ይህ የእግዚእኃረያ ቤት ነው። ባሏ ፀጋ ዘአብ ደስታውን መቋቋም አቅቶታል ቤቷ በወዳጆቻቸው እና በጠያቂዎቻቸው እንዲሁም ባለ መውለዳቸው እንደ ኃጢያተኛ ቆጥሮ ይጠቋቆሙባቸው በነበሩ ሰዎች ተጨናንቃለች መካን ሚስቱ ወንድ ልጅን ወልዳለችና ። ለሁሉም እንደ ማዕረጋቸው ምሳ አደረጉላቸው ማጋረጃ ገልጠው እናቲቱንና ልጇን ቅቤ እስኪቀቡ የቸኮሉ ሳይኖሩ አይቀሩም ሌላው ግን ስለ አወላለዷ ለመረዳት ሰሀናቸውን ይዘው የወላዲቱ አልጋ አጠገብ ጠጋ ብለው የተቀመጡም አልጠፋም ።
#እርሷም_የእግዚአብሔርን ቸርነት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየመሰከረች ከሞተለሚ ምርኮ እንዴት ባለ ተአምር እደዳነች እያወራች ከባሏ ከፀጋ ዘአብም ጋርም ወንድ ልጅ ስለ መውለዷ አስቀድመው ዕራይን እንዳዮ እየነገረቻቸው ቀኑን በደስታ አሳለፈች ደስታ የሆነ ልጅ ወልዳለችና ።
*ስሙንስ ማን አላችሁት ?
ፍስሐ ጽዮን ( የጽዮን ደስታዋ) ብለነዋል ። ነገር ግን መላእኩ እንደነገረን ስሙ ሌላ ነው ከእናንተም የተሰወረ በልበ ሥላሴ የተጻፈ አዲስ ስም ይወጣለታል ብሎናል። "ተክለ ሃይማኖት"! ሕጻናት እንደሚያለቅሱም አያለቅስም ነበር "ቅኖች ሰዎች ሁል ጊዜ ደስ ይላቸዋል" እንደሚል
"ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለእራስህ አዘጋጀህ " አንደተባለም ሕጻኑ ፍስሐ ጽዮን በተወለደ ገና በሦስተኛው ቀን ከእናቱ እቅፍ ወርዶ "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ ሥላሴን በአንድነት በሦስትነት አመስግነ:: መዝ 9÷2
#ልጆች_የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው የእግዚአብሔር ስጦታ ሁሉ ደግሞ ደስ ያሰኛል ። ይልቁኑ እግዚአብሔር በእነርሱ አድሮ ድንቅ ሥራውን ይሰራባቸው ዘንድ ያዘጋጃቸው የቅዱሳን ሰዎች ልደታቸው ብቻ ሳይሆን እነርሱ እራሳቸው ደስታ ናቸው :: " በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ተድላና ደስታም ይሆንልሃል" ዮሐ1፥14 ተብሎ እንደተጻፈ እውነት ነው በመወለዱ ብዙዎች ደስ ብሎናል በሉቃስ ወንጌል ላይ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል በመጥምቀ መለኮት በቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ እንደሚሰኙ አስረግጦ ነግሮናል።
እነሆ ዛሬ ደግሞ እንደ ዮሐንስ በድንግልና የኖረ እንደ መጥምቁ ካህን ያውም ሰማያዊ የሆነ እንደ አዋጅ ነጋሪው በምድረ ኢትየጵያን ሁሉ እየዞረ ወንጌልን የሰበከ ለእናትና ለአባቱ እንዲሁም ለብዝዎቻችን የደስታ ምንጭ የሆነ የጽዮን ደስታዋ የተባለ ፍስሐ ጽዮን ተወለደ እነሆ እኛም እንደ ተስፋው ቃል ዳግማዊው ዮሐንስ ተወልዶልናልና ደስ አለን::
#መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰለሞን" ጻድቃን በበዙ ቁጥር ሕዝብ ደስ ይለዋል" እንዳለ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በተወለዱ ሰዓት ክርስቲያኖች ደስ ብሏቸዋል ምክንያቱም ጻድቁ ሕሙማነ ነፍስን በትምህርታቸው ሕሙማነ ሥጋን በተአምራታቸው እያዳኑና እየፈወሱ ለሕዝብ ደስታ ምንጭ ሆነዋል ያን ጊዜ ብቻም ሳይሆን ዛሬም በአፀደ ነፍስ ሳሉ ለኛ ለክርስቲያኖች የደስታችን ምንጭ ናቸው " የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለችና " ስለኛ የጽድቅ ሕይወት የሰላም እጦት የሃይማኖት ጉለት የምግባር ዝቅጠት ዕለት ዕለት ወደ ፈጣሪ እየጸለዮ ያማልዱናልና ነው #ያዕቆ 5÷16
በጻድቃን መወለድ ሕዝብ ደስ የሚለው በተወለዱበት ዘመን እና ወር ብቻ አይደለም አንዴ ጻድቃን ከተወለዱ በኃላ ሕዝብ ለዘለአለሙ ደስ ይለዋል ጻድቃን በአፀደ ሥጋም በአፀደ ነፍስም በምልጃቸው ደስ ያሰኛሉና ..... .. ልክ እንደዛሬው......
" #እኔ ግን ለዘለዓለሙ ደስ ይለኛል
ለያዕቆብ( #ለተክለ_ሃይማኖት )
አምላክም ዝማሬን አቀርባለው" #መዝ76÷9
...........ይቆየን........
የጻድቁ አባታችን የተክለ ሃይማኖት እረድኤትና በረከት በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ሁሉ ለዘለዓለሙ ቀንቶ ይኑር ....!!!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
በድጋሚ የተለጠፈ ጥንተ ጽሕፈቱ
ታህሳስ 22/2013ዓ/ም