አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
481 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
የሚያሳድዱኝን እንዴት መውደድ እንዳለብኝ - ቤተሰቤን ያረዱትንም ሁሉ እንዴት እንደምምር ዕውቀት የቀሰምኩበት ነው፡፡
ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ይህ በታሪክ ብዙ ሕዝብ ካለቀባቸው ጭፍጨፋዎች በአንዱ እግዚአብሔር እንዴት እንደተገለጠልኝ የሚያሳይ ታሪክ ነው።
=======

ይሄን ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ ታሪክ ዘወትር ከሰኞ አስከ ቅዳሜ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ በ #አትሮኖስ ቻናል ብቻ ያገኙታል እንድትከታተሉ ስጋብዛቹ በደስታ ነው ከናንተ ከውድ የቻናሉ አባላቶች የምጠብቀው #MUTE ያደረገችሁን #UNMUTE እንድታደርጉንና ዘወትር ማንበብን ነው ያበረታናል እና Like 👍 እንድታደርጉልንም ነው።
ማታ #አንድሰአት እንገናኝ

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ።
እንዴት ናቹ #የአትሮኖስ ቻናል ቤተሰቦች እንደሚታወቀው #ሁቱትሲ የተሰኘው ድርሰት በትላንትናው እለት ተጠናቋል ያላችሁንም አስተያየት በውስጥ መስመር እየገለፃችሁልኝ ነው ለዚህም ከብዛቱ የተነሳ ለሁሉም መልስ መስጠት ስላልቻልኩ ይቅርታ እየጠየኩ ባጠቃላይ ግን ሁላችሁንም ከልቤ ማመስገን እፈልጋለሁ። 🙏

ሌላው በቅርብ ቀን ልንጀምረው ያሰብነው
ረጅም ታሪክ አለ ከነዚህም ውስጥ ለጊዜው 3 አሉ ከነዚህ ውስጥ አንዱን መርጦ ለመጀመር የናተ ከፍተኛ ትብብር ያስፈልጋል

መጀመርያ ከታች ከማስቀምጣቻው ምርጫዎች ውስጥ በናተ በከፍተኛ መጠን የተመረጠውን ቅድምያ አቀርባለው

ሌላው #MUTE አድርጋችሁ የምትጠቀሙ የቻናሉ ቤተሰቦች ፅሁፍ ማዘጋጀት በጣም ከባድ ነው አንዳንድ ቻናሎች ላይ እንደምታዩት ሌላ ቻናል ላይ ያሉትን ታሪኮች Cope paste አደለም የማደርገው በተቻለ መጠን አዳዲስ ታሪኮችን ይዤ ለመምጣት እሞክራለሁ ለዚህም ደሞ ለናተ በሚመች መልኩ ለማቅረብ ከፍተኛ ልፋት አለው እንዲህ የተዘጋጀውን ደሞ እናተ ካላያችሁት ልፋት ብቻ ነው የሚሆነው እናም እባካችሁ #UNMUTE አድርጋችሁ ተጠቀሙ እኔም ሳልሰለች ለናተ ምርጥ ምርጥ ታሪኮችን ይዤ እመጣለሁ

ከታች ካሉት ምርጫዎች ቅድምያ ይቅረብ የምትሉትን በመምረጥ ተሳተፉ

💚 #ፍቅር_እስከ_መቃብር

💛 #ሮዛ

❤️ #የአና_ማስታወሻ
የደረሱ ይመስላሉ፡፡ ቢዝነስ ቅድሚያ መከፈል እንዳለበት ስነግረው ሁለት መቶ ዶላር ሰጠኝ፡፡ የመጠጡን ሒሳብ ዘግቶ ወደ መኝታ ክፍሉ አመራን፡፡ በምንጠጣበት
ወቅት፣ በየጨዋታችን መሃል ራስታው እኔ ከአጠገቡ መኖሬን የረሳ እስኪመስለኝ ድረስ በሐሳብ የሆነ ቦታ ደርሶ ይመለስ እንደነበር አስተውያለሁ፡፡

የመኝታ ክፍሉ ውስጥ እንደገባን ከነ ልብሱና ጫማው አልጋው ላይ በጀርባው ተዘረረ፡፡ ምንም ዓይነት ጥድፊያ አላየሁበትም፡፡ ይደባብሰኛል ብዬ ስጠብቅ እንደ ለመደው በሐሳብ ወደ ሌላ ቦታ ነጎደ፡፡
ቀዩ ሚኒስከርቴን እንደለበስኩ ከአጠገቡ ተኝቻለሁ፡፡ ሳዋራው አይመልስልኝም፡፡ በሐሳቡ ተመስጧል፡፡
መደባበሱና ማሻሸቱን ራሱ እስኪጀምር ድረስ ምንም ላለማድረግ ወሰንኩ፡፡ በቶሎ ከሐሳቡ አልተመለሰም፤
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ፊቱን ወደኔ አዞረ፡፡ ሁለት መቶ ዶላር ከባለ ብዙ ኪስ ሚሊተሪ ጃኬቱ እውጥቶ ሰጠኝ፡፡ አመሰገንኩት፡፡ መኸሲ ቦኩ!

ያሻሽኝ ጀመር፣ ጡቶቼን ፣ጭኔንና የብልቴን አካባቢ መነካካት ጀመረ፡፡ ብልቱ በሱሪው ውስጥ ድንኳን
ሲሰራ ተመለከትኩ፡፡የጀርባ ዚፔን ከፍቶ ሚኒስከርቴን አወለቀ፡፡ የሸሚዙን ቁልፎች ከፋፍቼ ሸሚዙን አወለቅኩለት፡፡ በጀርባው እንደተኛ አይኑን ጨፈነ፡፡ ብልቱ ቆሟል፡፡ ኮንዶም ካጠለኩለት በኋላ ላይ ሆኜ መወሰብ ጀመርኩ፡፡ አይኑ ቡዝዝ ከማለቱ እየወሰብኩት ሰባተኛ ሰማይ የደረሰ መሰለኝ፡፡ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ገልብጦኝ ከላይ ሆኖ መወሰብ ጀመረ፡፡ በዚያ ሁኔታ የተወሰነ ከቆየ በኋላ በጉልበት እንድዞርለትና የኋሊት እንድሰጠው አመቻቸኝ፡፡ ምንም ሊረጋጋ አልቻለም፤በስሜት እያለከለከ ይቅበዘበዛል፤አለቅጥ ይጣደፋል፡፡ እንደገና ደግሞ ልቡ የቆመች ይመስል ስልብ ይላል

በሐሳብ፡፡ ከኋላ እየበዳኝ ጥቂት እንደተንቀሳቀሰ በከፍተኛ ድምጽ መጮህ ጀመረ!
(serpent serpent serpent! Aide moi Serpent!

ምን እንደሚል ስላልገባኝ እኔም አብሬው እሪታዬን አስነካሁት፡፡ እንዳልተረዳሁት ሲገባው snake snake help help...እባብ! እባብ እባብ በቂጥሽ ላይ እየሔደ ነው በሩን ለመከፈት መታገል ጀመረ ፡፡ጩኸቱ ጣራ ይሰነጥቃል፡፡ የሆቴሉ አስተናጋጆች፣ አሳላፊዎቹና ጎረቤት ክፍሎች ውስጥ የነበሩት ጥንዶች በራችንን በኃይል ማንኳኳት ጀመሩ፤

"Mr Patrice! Open the door please! We are here to help you!"

የሆቴሉ አስተናጋጆች በሩ እንዲከፈትላቸው ተማጸኑ፡፡ ፓትሪስ በፈረንሳይኛ እየጮኸ በሩን ከፈተላቸው።

“በቂጧ ላይ የሚንቀሳቀሰው እባብ ሊነድፈኝ ነው!help help serpent serpent”

በብርድ ልብሱ ተከናንቤ ተሸፍኛለሁ፡፡ አልጋ አከራዩ ፓትሪስን በፈረንሳይኛ ማናገር ጀመረ፡፡ እባቡ የታለ?”

ሁለቱ አስተናጋጆች ከፍሉን ከጥግ እስከ ጥግ መቃኘት ጀመሩ “ቂጧ ላይ ነው ሲንቀሳቀስ ያየሁት”
እኔ ጣልቃ ገባሁ፡፡ አንሶላውን ብቻ ለብሼ ተነሣሁ ፤
“ቀኝ ቂጤ ላይ የእባብ ንቅሳት አለ፡፡ ቅድም በሃሺሽ ሲጦዝ ስለነበር sex ስናደርግ በጡዘት እባቡ የእውነት
ሲንቀሳቀስ ታይቶት ነው”

ሁለቱ አስተናጋጆች ይኼን እየተናገርኩም አልጋውንና የአልጋውን ስር ጎንበስ ብለው መቃኘታቸውን አላቆሙም፡፡ ብዙዎቹ በሳቅ እየተንከተከቱ ወደየከፍሎቻቸው ሔዱ፡፡ እኔ ግን ዘበኞቹ ቂጤን ስላዩብኝ
ተናደድኩ፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ይሄ ቻናል እንደምታዩት ከ 90,000 በላይ ተከታዬች አሉት ግን በሚያሳዝን ሁኔታ የምለጥፈውን ከ 3000 ሰው በላይ አያየውም ይሄ ደሞ እንዴት ሞራል እንደሚሰበር ብታውቁት አዲስ ነገር ለማዘጋጀት ይቅርና የጀመርኩትንም ለመቀጠል ሞራል ያሳጣል እናም እባካችሁ #MUTE ያረጋችሁ #UNMUTE አድርጉ ያነበባችሁትን ሌላም ያነበው ዘንድ SHARE አድርጉ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍132
ከሰል እና ፌሮ ተሸካሚ ልወድ አልችልም፤ሰፈራቸው ደብተራ ይበዛል?

"ወንድ ሁሉ ውሻ ነው፤ሮዝ ሙች፤ሰራተኛዬ እኮ የሆነ መጋጫ ነገር ነች፤መልከ ጥፉ አይገልጻትም፤ ግራ
ቂጤ ከሷ ፊት ይነጻል፡፡ ከኔ በምን ተሸላ ነው ከሷ ጋር የሚባልገው?

ፍቅርተ በአሹ የተነሳ ህዝበ አዳምን አምርራ ጠላች፤ለመበቀልም ዛተች፤ለአሹ ስትል የከሰከሰችው
ሀብትና ንብረት የእግር እሳት ሆኖ ያቃጠላት፤ከብስጭቷ ለመገላገል ከዚህ ቀደም የሌለባትን አመል እመጣች፤ አልኮል አብዝታ መጠጣት ጀመረች፤ማርቲ እንደነገረችኝ ፍቅርተ ስትጠጣ
አያምርባትም፤ከሁሉም ጋር ትላተማለች፡በተለይ ከሆቴሉ ደምበኞች ጋር ወንዶችን በስድብ ዶፍ ታጥረገርጋቸዋለች፡በዚሁ ተናካሽ ጸባይዋ ብዙ ጊዜ ከሆቴሉ ደምበኖች ዱላ ተቃጥቶባት ገላጋዮች
አትርፈዋታል፡፡ይኸው ክፉ አመልዋ ለአመታት ተከትሏት ከትላንት በስቲያ ለቀመሰቸው የሞት ጽዋመንስኤ ሆነ፡፡

ትዳር ሁለት፣የፍቅርተ ገዳይ

ፍቅርተ በደበበ ተክሌ ለአመት ያህል ከሰራች በኋላ እንደገና ፍቅር አገረሽባት፤አሁን ግን ፍቅር የጀመረችው እንደ አሹ ካለ መናጢ ጋር አልነበረም፣ይሄኛው ሀብታም ነው፤የክፍለ ሀገር ሀብታም፡፡ በተደጋሜ ጎበዝ
ገበሬ ተብሎ በቲቪ ሲሸለም ታይቷል፡፡ ከአንድም ሁለት አይሱዞዎች አሉት፡፡ አንድ ቅጥቅጥ ካቻማሊ አለው፡፡ መንግስት ስለሚወደው ገጠር ብዙ መሬት ሰጥቶታል፡፡ የኢህአዴግ አባል ስለሆነ ጉዳይ ቶሎ ይፈጸምለታል፡፡ በስራው ታታሪ ነው፣ እረፍት አያውቅም፡፡ ጎልማሳ ነው፤ፍቅርተ እንደነገረችኝ በአስራ
አራት አመት ይበልጣታል፡፡ሸሌነቱን አስትቷት በትዳር ጠቀለላት፡፡ፍቅርተ ከኛም ራቀች፡፡ከዘጠኝ ወራት በኋላ ደውላ ከማርታ ጋር አገኘችን፣ከምሳ ጀምሮ አብረን ዋልን፤ነፍሰጡር ናት፡፡

በዚያን ወቅት በትዳር ህይወቷ መማረር ጀምራ ነበር፤ባልዋ ከነመኖራ ረስቷታል፣እንደሷ አባባል ወሲብ
ከፈጸሙ ወራት ተቆጥረዋል፣ እሱ ሁልጊዜ ለመሸለም እና በቲቪ ለመታየት ነው የሚሰራው፡፡ እኔን ረስቶኛል እያለች ታማራለች፡፡

ከባሌ ጋር በአንድ ቤት እየኖርን ከተፋታን ቆይተናል፤ትዳር አትበሉት!ቀን ስለ ቢዝነሱ ሲብሰለሰል እና የፓርቲ ስብሰባ ሲመራ ይውላል፤ማታ በአልኮል ድንብዝ ብሎ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ይመጣና ጀርባው
ሰጥቶኝ ይተኛል"

ማርቲ በፍቅርተ ሀዘን በግና ነበር፤

ታዲያ ምን እየጠበቅሽ ነው?ለምን አትፈቺውም?ገንዘቡ ለምን ጥንቅር ብሎ አይቀርም! ፍቅርተ ከሺሻው
አንዴ ከማገችለት በኋላ ማርቲን በአትኩሮት ተመለከተቻት፤
“ማርቲ!ወንዶች ሲባሉ አንድ ናቸው፤በቁጥጥራቸው ውስጥ እስከትወድቂ ነው የሚንከባከቡሽ የእነሱ
እንደሆንሽ ሲያረጋግጡ ይረሱሻል፤ መጀመሪያ ከኔ ፍቅርና ወሲብን ይፈልግ ነበር፤አሁን በሆዴ ያለውን ልጅ ብቻ ነው የሚፈልገው፤እኔም ልጄን እስከገላገል ነው የምታገሰው፣"

ሆኖም ፍቅርተ ያለችውን አላረገችም፤ ወልዳ ወራት እና አመታት ከተቆጠሩ በኋላም ከሱ ጋር ኑሮዋን ቀጠለች፣ እንደበፊቱ ግን ነጻነቷን አልገታችም፣ ፍቅርተ እንደገና ፈነዳች፡ከኛ ጋር በየቀኑ መገናኘት ጀመረች፤ምሳ ከበላን በኋላ እየቃምንና እየጠጣን እንውላለን፤ማታ ከባልዋ ጋር ሁለቱም በስካር ቅኝት ላይ
ሆነው ይሰዳደባሉ፡፡
ፍቅርተ ሰከረች

ማርታ እንዳጫውተኝ የፍቅርተ ባል ቢሰከርም የመሳደብ ልማድ አልነበረውም፡የፍቅርተን ባህሪ
የወረሰው ከአንድ አጋጣሚ በኋላ ነበር፡፡ባል ሊጠጣ ሲፈልግ ፒያሳ ከሚገኛው እና ከሃያ በላይ ሸሌዎች በአይነት በአይነቱ ከሚርመሰመሱበት ናሽናል ሆቴል ይገባል፣ያዘዘውን መጠጥ እየጠበቀ አይኑን ሲያማትር
ፍቅርተን ከአንድ ወንድ ጋር እየጠጣች ያያታል፤በመጀመሪያ አይኑን ተጠራጠረ ህልም ይሁን እወን ግራ ተጋብቷል፡እሷ አይታው ፈግግ ስትል በብርሀን ፍጥነት ከተቀመጠበት ተነስቶ አንገቷን አንቆ ከሆቴሉ አስወጣት፣መኪናው ውስጥ ወርውሯት ነጎደ፡፡

“ጥፋተኛው እኔ ነኝ!ሸርሙጣ ሁሌም ሸርሙጣ ናት!ደሞ እዚህ ቤት ምን ልትሰሪ መጣሽ?"

"ደበበ ተከሌ ሆቴል አብረውኝ ይሰሩ የነበሩት ማርቲና ዝናሽ እዚህ ስለገቡ ላገኛቸው ነው የመጣሁት፤በጣም
ናፍቀውኛል' ባል አላመናትም፤
አንቺ ደደብ ሸርሙጣ ደድበሽ እንደ ደደብ አትመልከቺን እኔ የተከበርኩ ሰው ነኝ፡፡ እንኳን አንቺ መንግስት ያከበረኝ ሰው ነኝ፡፡ ያገኘሁሽ እኮ ከምትያቸው ሴቶች ጋር አይደለም ከወንድ ጋር እየጠጣሽ
ስትገለፍጪ ነው ያገኘሁሽ!"

"የድሮ ደምበኛዬ ነው!በአጋጣሚ ነው እዚህ ቤት ያገኘሁት!ከመጫወት ውጪ ያደረግነው ነገር የለም

ቀጣፊ ሸርሙጣ ስለሆንሽ አላምንሽም..ጓደኞቼን ምክር አልሰማ ብዬ ነው ያገባሁሽ.ሰው ላደርግሽ
ነበር

ፍቅርተ እሳት ለበሰች፤ በሞቅታ መለሰችለት፤

ታዲያ አንተም ልትሸረሙጥ ስለመጣህ ምኑ ያስገርማል…?”

በማግስቱ ማርቲ የፍቅርተን ፊት አባብጦና በላልዞ አገኘችው፤ባል ከፉኛ ደበደባት፡፡

በሽማግሌዎች ተታርቀው የትዳር ጥምረታቸውን ቀጠሉ፤ሁለቱም ሰከረው እየመጡ መሰዳደባቸው ግን
ቀጠለ፤በዚህ ሁኔታ ወራት አለፉ…

ፍቅርተ በመጨረሻዋ ሰአት

ለቀስተኛው ስለ ፍቅርተ አሟሟት ብዙ ሲያወራ ሰምቼያለሁ፤ሁሉም ጎረቤቶቿ ገዳዩ እጁን ለፖሊስ ሲሰጥ እየጮኸ በተደጋጋሚ የተናገረውን በደንብ ሰምተዋል፡፡
ከትናንት በስቲያ ምሽት ባል ምንም ሳይጠጣ ገብቶ ልጁን ያጫውታል፡፡4፡30 አካባቢ ፍቅርተ ሰክራ ገባች፤አቅሏን እስክትስት ጠጥታለች፣ባል ላይ የተለመደ የስድብ ናዳዋን ታወርደው ጀመር፡፡ባል ሆደ ሰፊ ሆኖ በሰላም ክፍሏ ገብታ እንድትተኛ በተደጋጋሚ ተማጸነ፡፡ፍቅርተ በስድቧ ቀጠለችበት፡፡በስካር
እንደምታወራ የተገነዘበው ባል ምንም መልስ አልሰጣትም፡፡ቢጨንቀው ለልጇ ስትል መኝታ ከፍሏ ገብታ
እንድትተኛ ጠየቀ፤

እባክሽ ፍቅርተ፡ባንቺ ሁኔታ ልጃችን ይረበሻል፤ምናለ ገብተሸ ብትተኚ!"

የተከተለው የፍቅርተ መልስ ባልን በንዴት ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ ሽጉጡን እንዲመዝ አስገደደው፡፡

እንዴት አፍህን ሞልተህ ልጃችን ትላለህ?ያንተ ልጅ እንደሆነ በምን እርግጠኛ ሆንከ?”

💫ይቀጥላል💫

Like 👍 Share እያደረጋችሁ #MUTE ያደረጋችሁ #UNMUTE አድርጉ እባካችሁ ሁሌ የምለጥፈውን ለመከታተል ቻናሉን #Favorites ውስጥ አስገቡት #አመሰግናለው

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍81
#ሮዛ-2

#ብጥስጣሽ_የእለት_ማስታወሳዎች

#ከባለታሪኳ_ግርድፍ_ማስታወሻዎች #የተዋቀረ

#መግብያ

መግቢያ ጥሩ ነው። ያግባባል። ብዥታን ያጠራል። መግቢያ እንኳን ለመጽሐፍ ለ“ሾርት”ም ያስፈልጋል። እነ ሮዚ
ለምሳሌ ወንድ አቻኩሎ ወደ መኝታ ሲነዳቸው ይከፋቸዋል። ጋብዞ፣ አግባብቶ፣ አጫውቶ፣ አቅፎና ደግፎ
ሲሆን ግን ቅልል ይላቸዋል። ለዚህ መጽሐፍ አጭር መግቢያ እንዲኖር የፈለኩትም ለዚሁ ነው።
ሮዚን እስኪ በሞቴ ትንሽ መግቢያ ነገር ጻፊያ ብላት፤ እኔ መዉጫ እንጂ መግቢያ አላውቅልህም”ትለኛለች።አንባቢ እንደሚረዳው “መዉጫ” ማለት ሮዚና ባልደረቦቿ ከሚሠሩበት ቡና ቤት ለአዳር ሲወጡ የሚከፍሉት የኮቴ ግብር ነው። ታዲያ እሷን ከማስቸግር ለምን ራሴ አልሞከረውም?

አንዳንድ የተኖረ ሕይወት ለልቦለድነት የቀረበ ነው። ለምሳሌ የሮዚ ዓይነት ሕይወት። ለዚህም ነው ይህን
መጽሐፍ እውነተኛ ታሪክ” በሚል ሼልፍ ላይ ማስቀመጥ የሚጎረብጠው። “ኩሽተኛ ታሪክ” ቢባል ደግሞ
ትክክል አይሆንም። ደግሞ ልቦለድም አይደለም፣ ባይሆን የተቀባባ፣ በልቦለድኛ የተለወሰ፣ ግን ደግሞ ድብን
ተደርጎ የተኖረ ታሪክ ብንለው ይቀላል።
ስንትና ስንት ግሩም ድንቅ ታሪኮች በጥሩ ሁኔታ ስላልተጻፉ ብቻ ከአንባቢ ሳይደርሱ በትነት መልክ
ይጠፋሉ! እነዚህን ታሪኮች አርታኢ አደምኖ ወደ ሕዝብ ካላዘነባቸው ማን አላቸው!? የሴተኛ አዳሪ ታሪኮች
ደግሞ ጥሎባቸው በአግራሞት የተሞሉ ናቸው። ለመሆኑ እንደነሱ ሕይወትን እስከነንፍጧ የሚያሳየን ሌላ
ፍጥረት አለ? ለዚህ ይመስለኛል ብዙ ሰዎች ለእንዲህ አይነት ታሪኮች ቶሎ የሚሳቡት።

ይህንን መጽሐፍ ትውልድ እንዲማርበት ነው በዚህ መልክ ያዘጋጀሁት እያልኩ መታበይ አልፈልግም። መጽሐፉ
ትውልድ የማነጽም ሆነ ትውልድ የማባለግ ግብ ይዞ አልተነሳም። ነገር ግን ለጥንቃቄ ሲባል ከታዳጊዎች ይልቅ
አዋቂዎች ቢያነቡት ደስ ይለኛል። አዋቂዎችም ቢኾኑ "ሳማት ሳመችው”፣“አወቃት-አወቀችው፣ •
ተኛችው” ከሚሉት ትዕይንቶች ባሻገር ያሉ ሕይወቶች ላይ ቢያሰላስሉ ይበልጥ ደስ ይለኛል። ጨዋነትም ሆነ
ራስን መጠበቅ በማፈር ላይ ሳይሆን በማወቅ ላይ፣ በመሸፋፈን ሳይሆን በመገላለጥ ላይ፣ በድብቅነት ሳይሆነ
በግልጽነት ላይ፣ መሬት ላይ ያለን ተጨባጭ ሀቅ በማበል ሳይሆን እውነታን በመቀበል ላይ፣ በማስመሰል ላይ .
ሳይሆን በመሆን ላይ ሲመሰረት ቶሎ አይናድም።
ገና ወደፊት በስልጣኔ መስኮት ሾልከው ከሚገቡ ስንትና ስንት ጣጣዎች ጋ እንደምንላተም ሳስብ ካሁኑ ይደክመኛል።

ድሮ የሞራል አስተማሪዎቼን ማታ መስመር ላይ ሳገኛቸው ከነርሱ በላይ እኔ በሐፍረት እከሳ ነበር። ከነ ሮዚ ጋር
እየዋልኩ እያደርኩ ብዙ ጉድ የሚያሰኙ ታሪኮችን ስሰማ መገረም ማቆም እንዳለብኝ ተሰማኝ።ብዙ ሰው ግን አሁንም መገረም አላቆመም መሰለኝ።

ባለታሪኳን የማውቃት አገር ቤት ሳለሁ ነው፤መስቀል ፍላወር በአንድ ተራ ሺሻዊ” አጋጣሚ ይህ የባለስልጣን ፊርማ የመሰለ ሕይወቷን የቸከቸከችበት የማስታወሻ ደብተር እጄ ውስጥ ገባ። አነበብኩት። በጊዜው በነበራት
ብሩህ አእምሮ ተደመምኩ። ያኔ ኮሌጅ የበጠሰ ሸሌ ለኔ ብርቅ ነበር። የመስቀል ፍላወር ጓደኞቼ እንትን ስጪኝ እያሉ ደጅ ሲጠኗት እኔ ደግሞ በተቃራኒው”ዳያሪሽን ስጪኝ እያልኩ አስጨነቅኳት።ተሳካልኝ
ከብዙ ወራት በኋላ ደግሞ በተራዋ

“ዳያሪዬን መልስልኝ!” እያለች ጨቀጨቀችኝ።

ጭቅጭቋ ሰለቸኝ። በኋላ በአንድ የስካር ሞቅታ ተገናኘንና እንዳትጨቀጭቀኝ ፈርቼ አፌ እንዳመጣልኝ
“መጽሐፍ አደርገዋለሁ! ስላት ሳቀችብኝ። ሮዚ ስትስቅ እንዴት ታምር እንደነበር! አልነግራችሁም።

እነሆ ከስንትና ስንት ዓመት በኋላ በቃሌ ስገኝ።

ፍጹም ብርሃኔ አራጌ (አርታኢ)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ያው እንግዲህ የ #አትሮኖስ ቻናል ተከታታዮች ቃል በገባሁትና በናንተም ምርጫ መሰረት #ሮዛ-ቀጥር-2 ይዤላችሁ መጥቻለው #ሮዛ-ቁጥር-1 ለመጀመርያ ጊዜ በኛ ቻናል አቅሪቤላችሁ(ማለቴ ታሪኩ በኛ ከቀረበ በኋላ በብዙ ቻናሎች ላይ copy paste ተደርጎ ስለምታገኙት ማለቴ ነው) እንደተመቻቹ በቃላቱም ወጣ ማለት ደንገጥ ብላችሁ አስተያየት የሰጣችሁኝ ብዙ ተከታዎቼ አላችሁ ለሁሉም መልስ ግን ከላይ #መግቢያው ላይ ያለውን እኔም እጋራዋለሁ።

ዛሬ በተለመደው ሰዓት #ሮዛ-ቁጥር-2ትን ይዤላችሁ እቀርባለው እናንተም ወድያው እንዲደርሳቹ ቻናሉን #MUTE ያደረጋችሁ #UNMUTE በማድረግ ተባበሩን አብሮነተችሁን #Like 👍 በማድረግ አሳውቁን።
👍141
ቅምጥ ቀምጠዋል አልያም በቅቻቸዋለሁ
የሚያወጡትን ገንዘብ ከምሰጣቸው ጊዜ ጋር እያነፃፀሩ ማስላት ይጀምራሉ፡፡

ጥቂቶቹ የእናቴ መቀነት አደናቀፈኝ የአባቴ ጫማ ክር ጣለኝ ዓይነት ሰበብ አላዝነው ይሄዳሉ።ጥቂቶቹ ደግሞ
የመለየቱን እርምጃ እኔ እንድራመድ ይጠብቃሉ፡፡ የተቀሩት
ደግሞ ካወቁኝ ጀምሮ ያደረጉልኝን እየቆጠሩ ያለተጨማሪ ወጪ
ጊዜዬን ሊገዙኝ ይሞክራሉ:: እዚህ ንጭንጭ ላይ ሲደርሱ ካልተለየኋቸው
ቅቤ ልጥበስልሽ ባለው አፋቸው ብልግና
ይተፉበታል።

"አውቃለሁ። ግን ቃል ገብተህልኛል!" አልኩት ከተዋወቅን አራት ወራችን ቢሆንም መሰነባበቻችን ጊዜ ሩቅ ያለመሆኑን እያሰብኩ፡፡

"አስቢልኝ እንጂ! እናትሽ የመንግስት ገንዘብ የቀረጠፈችው እኔን ተማምና ይመስልሻል ልበል?ሲወዱሽ ያበዱልሽ መሰለሽ ንግግሩ የአፉን በር ለቆ ሲወጣ ምንም የሚያበሽቅ ነገር እንዳልተናገረ ሁሉ አለስልሶት ነበር።

"መውደድ ባንተ ጭንቅላት ምን ማለት ይሆን?" ኣልኩት፡፡ስለመውደድ መደስኮሩ ገርሞኝ እንጂ ስለእናቴ እንደዛ ሲናገር
ስሰማው የክት ስድብ ፈልጌ መሞለጭ ነበር ያማረኝ፡፡

ዘብጥያ የወረደች እናትሽንና ሽባ ወንድምሽን መቀለብ ማለት“ግን አይደለም።"ሲለኝ ከዛች ደቂቃ በላይ በአንድ ጠረጴዛ ላይ ከእርሱ ጋር ለመቀመጥ የሚያበቃ ሰውነት እንደሌለው አስቤ ቦርሳዬን ይዤ ተነሳሁ፡፡ በእርግጥ ልሰድበው ፈልጌ ነበር ችግሩ
አልችልበትም፡፡ የክት የምለው ስድቤ እንኳን ለእርሱ የሽልማት ያህል ነው።

"የማትረባ! ቀሽም!" ብዬውም ለመሄድ
ከጀመርኩ በኋላ ውስጤ በንዴት ታመሰ፡፡ ማድረግ የቻልኩት ነገር የተለያየ መጠጥና ምግብ የተሸከመው ጠረጴዛ የለበሰውን ጨርቅ ከነኮተቱ አንስቶ
አስማማውን ማልበስ ነበር፡፡ እየወጣሁኝ ቀለም የበዛበት ያላዋቂ ሰዓሊ ስዕል ያስመሰለውን ቆሻሻ ሲያራግፍ አየሁት:: ከታዳሚው ገሚሱ በጥላቻ ዓይን ሲያጉረጠርጥብኝ፣ አያሌውን ጨምሮ
ጥቂቱ ሲስቅ፣የተከሰተው ያልገባው ጉዳዩን ለማጣራት ሲንሾካሸክ ከአዳራሹ ጫጫታ እየራቅኩ ሄድኩ።ንዴቴን ከማጨሰው ሲጋራ ጭስ ጋር ልተነፍሰው ስለጓጓሁ (ብዙውን ጊዜ ሲጋራ ሳጨስ የሚሰማኝ እንደዛ ነው።) ከተደረደሩት
የታዳሚዎች አንድ መኪና የፊት ኮፈን ላይ ተቀምጬ እያጨስኩ የመኪናው ጡሩንባ ጆሮዬን ሲያደነቁረው ነው መኪናው ውስጥ ሰው መኖሩ የገባኝ

"ያምሃል እንዴ?” ብዬው ተነስቼ አጠገቡ ያለ መኪና ላይ ደገፍ አልኩ
"በእርግጥ ያመኛል። ቆየሁ ካመመኝ፡፡ ሶስት ዓመት!!" በእጁ የተገባደደ የውስኪ ጠርሙስ እንደያዘ ከመኪናው ወጣ፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
አዳሜ ደሞ #Mute አድርጋቹ ነው የምታነቡት አስቲ ሁላችሁም #Unmute አድርጉት ጎሽ የሚለቀቀውን ቶሎ ለማንበብ ያመቻችኋል ስንት ምርጥ ምርጥ ድርሰት አምልጧቹኋል መሰላቹ ወደኋላም ሄድ ብላቹ አንብቡ እውነቴን ነው ይመቻችኋል ማንበብ ባትወዱ ራሱ ሞክሩት ሱሰኛ ነው የምትሆኑት።

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#ዶሮን_ቢያማት_በሬ_ተሳሉላት

አንድ ቀን ፣ በአንድ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት ለሚካሄድ ፕሮጀክት የበጅት ኤክስፐርት ሆኖ የሚሰራ ወዳጄን ፤ ሳገኘዉ ፣ያለወትሮው ተደብሮ
ነበር።

“ምን ሆነኸል? አልኩት ።

“አንጀቴ አርሮ ነው ባክሽ...”

“አጂጀትህ ማረሩ ፊትህ ላይ ተጽፏል ። ግን ምን ሆነህ ነው?”

“እንግhዝ ያለው ዋና መስርያ ቤታችን የሠራው ሥራ እርር ድብን አድርጎኛል ።"

“ምን አደረጉህ?”

“ባለፈው ኢትዮጵያ የሚገኘው ቢሮ በየወሩ አላስፈላጊ በሆኑ ነገሮች አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር እያባከነ ስለሆነ መፍትሔ ማበጀት ፈልገናል” ብለው ኢሜይል ጻፉልኝ ።

“እ... ሺ

“የሚሉትን፣ ለመስማት ሰፍ ብዬ ስጠብቅ ፣ ከትናንት ወዲያ መፍትሔ ያሉትን ሊነግሩኝ ከለንደን ድረስ ደወሉ።''

“እህስ ... ምን አሉህ?”

ባለፈው እንዳልንህ በወር የሚባክነው፣ አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር ለማዳን የሚያስችል ሲስተም የሚዘረጋ ሰው ከዚህ እንልካለን ሰውየው
በዘርፉ በዓለም የገነነ አማካሪ ነውና በደንብ ይረዳችኋል አሉኝ።እኔም በዛውም ከሰውየው ብዙ እማራለሁ ብዬ ደስ አለኝ እና እሺ አልኩ ...”

“ደስ ካለህ ታዲያ ምን አናደደህ? ” አልኩ፥ ነገሩን፣ ፈታ ለማድርግ ።

“አታሹፊ : : የምሬን ነው : : ”

“እሺ... ምን አናደደህ? ”

“በነጋታው ሰውየው ሥራውን፤ ለመሥራት የሚከፈለውንና ተያያዥ ወጪዎቹን... አለ አይደል የአውሮፕላን ቲኬት ፣የቤት ኪራይ፣ ጥበቃ ፣ ኢንሹራንስ ምናምን በጀት ሠርተው ላኩልኝ ።

"እ....?"

ይሄ ሁኑ ሲደማመር የኢትዮጵያው ቢሮ ለሰውየው አንድ መቶ ሰማንያ ሺህ ብር በየወሩ መክፈል ይጠበቅበታል ።

አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር ለማዳን አንድ መቶ ሰማንያ ሺህ ብር ማውጣት! ሃ ሃ ሃ ሃ አልኩ እየሳቅኩ ።

“እኮ...አይገርሙሽም?” ሲለኝ አሰብ አደረግኩና ፣

“ቆይ ግን... አማካሪው ለምን ያህል ጊዜ ነው የሚመጣው? ምናልባት በረጅም ጊዜ ሲሰላ ለሱ የሚወጣው ወጪ ከሚያድነው ገንዘብ ያንስ
እንደሆነ?” አልኩት ።

“የበጅት ኤክስፐርት ሆኜ ይህን አላስብም ብhሽ ነው ...? ባሀ አንድ መቶ ሰማንያ ሺህ ብር ደሞዙ ሰውዬ የሚመጣው ለአራት ወር አገልግኬት ነው
በወር አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር አባከነ የተባለው ፖሮጀክታችን ሊያልቅ የቀረው ግን ስድስት ወር ብቻ ነው" : : ብሎ መለሰልኝ።

ወይ የእኛ ነገር ፣ ትንሽ ሽንቁር ለመድፈን ሰፋ አድርጎ መሸንቆር፡ ፡
የሀገሬ ሰው ፣ #ዶሮ_ቢያማት_በሬ_ተሳሉላት ያለው ነገር ገጥሞት መሆን አለብት!

🔘ሕይወት እምሻው🔘

#MUTE ያደረጋቹ #UNMUTE እያደረጋቹ በተቻለ መጠን Post የማደርግበት ሰአት ተመሳሳይ ለማድረግ እሞክራለሁ

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አድራ ስለምትመጣ ቀን ላይ ብርሃን ልትጠይቀኝ ብቅ ስትል “ብርሃን በእናትሽ ቶሎ ቶሉ ነይ” አልኳት፤ ልመና ነበር ውስጤ!

“ደህና ነሽ?” አለችኝ ግራ ገብቷት፤ ዝም አልኩ፡፡

ይቀጥላል

Like 👍 Share እያደረጋችሁ #MUTE ያደረጋችሁ #UNMUTE አድርጉ እባካችሁ ሁሌ የምለጥፈውን ለመከታተል ቻናሉን #Favorites ውስጥ አስገቡት #አመሰግናለው

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#እንቆቅልሽ?”


ዘንድሮ ዐሥረኛ ክፍል ከሚጀምው የአጎቴ ልጅ ጋር ፣ "እንቆቅልህ? ምን አውቅልህ? ” እየተጨዋወትኩ ነበር ፡ : በእንቆቅልሽ ሕግ እንቆቅልሹን፣መፍታትና መልስ መስጠት ያልቻለው ሰው ፣ “ሀገር ስጠኝ” ይባልና መሱ
ይነገረዋል ።

ከተለመዱትና ከቀላሎቹ ጀመርን ። ጠያቂዋ እኔ ነኝ ።

“ጸጉሯን አበጥራ ገበያ የምትወጣ?”
.
“እ... አላወቀውም : : ሀገር ልስጥሽ? ።

“አትቸኩል ፤ አስብበትና ሲያቅትህ ፣ እኔ ነኝ ለመልሱ ዘገየህ ብዬ ሀገር ስጥ
የምልህ... እሺ...?

“ካላወቅኩት ሳትጠይቂኝ እኔ ራሴ ብሰጥሽስ?

ዝም ብዬ ቆየሁና ፣ እ... ...ም.. ሌላ ጥያቄ ልጠይቅህ ፤ ቢከብድህም አስብበት... ፍንጭም እሰጥሀለሁ ።

“እ..ሺ!”

“እንዲህ ቢሉ አትታይ፤ እንዲህ ቢሉ አትታይ ”

“እኔንጃ..... ሀገር ልስጥሽ ።

'ዞሮ ዞሮ መዝጊያው ጭራሮ?”

"ይሄንንም አላወቅኩትም ፤ በቃ ሀገር ልስጥሽ ።

ከዚ በኋላ ፣ እኔ ስጠቅ ፤ እሱ ፣ ፍንጭ ልስጥህና ሞክር”

እያልኩ+ ፣ አንዴ እንኳን የግምት መልስ ሳይሞክር ፣ “ሀገር ክስጥሽ” ሲለኝ ፤ ተበሳጭቼ ጨዋታውን አቆምን ።

ልክ ሲሄድ የሚከተለውን፣ አሰብኩ ፤ “እንቆቅልሽ ሲቀርብለት ጊዜ ሰጥቶና ተማክሮ ከመፍታት ይልቅ ሀገር ለመስጠት የሚቸኩለው የአጎቴ ልጅ ፣ ነገ ፓለቲከኛ ከሆነ ይህች ሀገር አለቀላት ።

🔘ሕይወት እምሻው🔘

#MUTE ያደረጋቹ ደሞ ምርጥ ምርጥ ድርሰት አምልጧቹሀል ቶሎ ብላቹ #UNMUTE አድርጉ

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍1
ትዉልድ ማን ለምን እንዳስዎነጨፈዉ ባልገባዉ የእርግማን ፍላጻ መኻል የሚኖር ነዉ!”

🔘ጨረስኩ🔘


ታሪኩን እንዴት አገኛችሁት እንደተለመደው
አስተያየት እየሰጣቹ ሌላው #በማስታወቅያ ዛግን እያላችሁኝ ነው ምን ላድርግ አባላት ለማብዛት ነው አትሰልቹብኝ እባካችሁ እናተም ለሌላው እንዲደርስ #Share ብታደርጉ እኔም ማስታወቅያውን ቀነስ አደርጋለው #MUTE ያደረጋቹ ደሞ ምርጥ ምርጥ ድርሰት አምልጧቹሀል ቶሎ ብላቹ #UNMUTE አድርጉ


ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
#በመዋጮ_መሥዋትነት_አለቅን!

እኛ ለራሳችን፣ ኑሮ ከቀን ቀን የብረት ዘነዘና ሆኖ እንደጉድ እየቀጠቀጠን፣ እያደር እንዳረጀ የእንጨት ሙቀጫ እንሰነጣጠቃለን ፣በዚህ ለይ ትንሹም ትልቁም ገንዘብ አምጡ ። አዋጡ ይለናል

ለእንትና ክርስትና መዋጮ ፣ ለእገሌ አባት ቀብር መዋጮ፣ ለእገሊት አገባች መዋጮ ፣ የእድር መዋጮ ፣ የማርያም ማኅበር መዋጮ ፣ ጸድቶ
ለማይጸዳ አካባቢ ፣ የአካባቢ ጽዳት መዋጮ፣ ከአጥር ቀለም ባለፈ አረንጓዴነቷ ዕለት በዕለት ለሚያሽቆለቁለው ከተማችን የፅዱና አረንጓዴ አዲስ አበባ መዋጮ ፣ ዛሬ ያስቀመጥነው 4ዐዐዐ ብር ወር 500 ለሚሆነውና ለአመታት ለማናየው የጡረታ መዋጮ ፣ የአባይ ግድብ መዋጮ! መዋጮ! መዋጮ!

ሚጢጢው ገቢያችን ፣ እንኳን ዙረን አክርሮ ጥሎን ለሚበረው ኑሯችን ቀርቶ ፣ በወር ለምንፈልገው መዋጮ እንኳን አልበቃ እያለ ነው ።
ከዛሬ ገቢ ቀንሶ መስጠት ማዋጣት ሳይሆን፣ መሥዋዕትነት መክፈል ነው : : መሥዋዕትነት ብል የአሳማውና የዶሮዋ ታሪክ ትዝ አለኝ : :
ነገሩ እንዲህ ነው ። አቶ አሳማና እመት ዶሮ መንገድ ይገኛውሉ : ጥቂት ካወሩ በኋላ
ዶሮዋ ፣ “ስማ አንድ ግሩም ሐሳብ አለኝ : እኔና አንተ ለምን አንድ ምግብ ቤት በጋራ አንከፍትም?” ትለዋለች ።

አሳማም ፣ “ምን የሚባል ምግብ ቤት?” ይላል።
“የአሳማ ሥጋና እንቁላል ምግብ ቤቶ ብንለውስ? ” ዶሮ ትመልሳለች። አሳማ ዝም ብኰ ሲያስብ ፣ “ "ያው አንተም በሥጋህ እኔም በእንቁላሌ"
ማለት ነው” ብካ ቀጠለች ዶሮ"
አሳማም ትንሽ አሰብ አድርጎ ፣ “ግዴለም ይቅርብኝ ፡ : ይህች ምግብ ቤት ማቅናት ላንቺ መዋጮ ነው ፣ ለኔ ግን መስዋትነት ይጠይቃል ። ብሎ መለሰላት አሉ : :

የኛም ማለቂያ አልባ መዋጮ ፣ ምስኪኖቹ ከእመት ዶሮ ይልቅ አሳማውን፤
እያስመሰለን ነውና አንድ ቢባልስ?

🔘ጨረስኩ🔘

#MUTE ያደረጋቹ ደሞ ምርጥ ምርጥ ድርሰት አምልጧቹሀል ቶሎ ብላቹ #UNMUTE አድርጉ


ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍2
እኩል ከሳቁ ጋር ወደላይ ተናጠ፤ ፈጣን እስክስታ
የሚመስል መናጥ።

“ማምሻ ሚዜ!?” አልኩ ለራሴ: የሎዛ ነገር ሁልጊዜ ግራ ቢሆንም፣ ይኼንኛው ግን ባሰ።
ይቺ ልጅ በዚህ ውዝግብ ወዳድነቷ እንዴት ነው ይኼ ትዳር…? ሐሳቤን ሳልጨርስ ተውኩት፡፡ ለምን በሰው ትዳር አሟርታለሁ? ብዬ፡፡ ፍኖት ተመልሳ ብቅ አለችና፣ ሎዛ እንድትሰማ በሚመስል ዘረኛ ድምፅ፣ አብርሽ ማሚ ትፈልግሃለች" ብላ ጮኸች፡፡

ተነስቼ ወደ ውስጥ ስገባ፤ሎዛ ከምኔው እንደደረሰች እንጃ እየተቆናጠረች ኮሪደሩ ላይ
ገፍታኝ አለፈችና፣ እናቷ ያሉበትን ክፍል በርግዳ ቀድማኝ ገባች::.......

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ

#MUTE ያደረጋቹ ደሞ ምርጥ ምርጥ ድርሰት አምልጧቹሀል ቶሎ ብላቹ #UNMUTE አድርጉ
አንድ ባለቀለም ጉርድ ፎቶግራፍ ብቻ ነበር ውስጡ ያኘሁት፤አንዲት እድሜዋ ሦስት ዓመት የሚሆናት ቆንጅዬ ሕጻን ልጅ ፎቶ፡፡ከፎቶው ጀርባ
በእንግሊዝኛና አማርኛ ቅልቅል እንዲህ የሚል ጽሁፍ ተጽፏል የሎዛ የእጅ ጽሁፍ ነው፡፡
hello,uncle! guess what ...My name is "ማምሻ ዳግማዊ!!

ሟርት ነው አልኩ ለራሴ፡፡ ግን ደግም አይገርምም፣ ሎዛ እብድ ናት እብድ ቤተሰብ
መመስረትም ትችላለች፡፡ እናም ዓለም ፈውሷን ለመቀበል የሎዛ ዓይነት ብዙ እብዶች ሳያስፈልጓት አይቀም፡፡

ጨረስን

አረ ተዉ #MUTE ያደረጋቹ #UNMUTE አድርጉ ምንም አልሰማም አላችሁ እኮ😡 ምን ይሻለኛል ወይ እስቲ ስለድርሰቱ አስተያየት ስሰጡ #UNMUTE የማታደርጉበትን ምክንያት ምንድን ነው??? እባካችሁ ንገሩኝ..Post የሚደረጉትን ብዙ ሰው የማያነበው ከሆነ ማዘጋጀቱም ይደብራል..ሌላ ድርሰት ለመጀመር ወይም ለማቆም አስተያየታችሁን (ምክንያታችሁን) እፈልጋለው...በዛሬው ቀን ብቻ እንኳን #381 ሰው ቻናሉን #MUTE አድርጓል አስተያየት ይስጡ

@atronosebot ን ይጠቀሙ
ተንተርሳ የደረቱን ጠጉር እያፍተለተለች በወጣትነት ትኩስ ገላው ውስጥ እንደ ቅቤ ለመቅለጥ... እንደ ውሃ ለመፍሰስ... በእጅጉ ጓጉታለች፡፡

ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆነ፡፡ ጌትነት በዚያ ከጥጥና ሲባጎ በተሰራ ምቹ ሶፋ ወንበር ላይ በጀርባው ተለጥጦ እየተዝናና ጠላውን መኮምኮሙን ቀጥሏል። ሸዋዬ ሁኔታውን ስትመለከት ፈነጠዘች። ጠላዋ ስራውን በሚገባ በመስራት ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አረጋገጠች። ሁሉም
ነገር በእቅዷ መሰረት እየተቀላጠፈ ነው። ሚስኪኑ ባጠመደችለት ወጥመድ ውስጥ ያለችግር ሰተት እያለ በመግባት ላይ መሆኑን እንዳወቀች ያንን ከተዳፈነበት ተቆስቁሶ እንደ ነበልባል ሲለበልባት የቆየ፣ ውስጥ ውስጡን ያሰቃያትን፣ ቀን ከለሊት እረፍት ያሳጣትን ችግሯን ለማስወገድ ቸኮላች፡፡ የወሲበ ክብሪቷን ጭራበት በዚያ እንደ ፈረሰኛ ውሃ ሽቅብ በሚጋልበው ዳሌዋ ላይ አፈናጣ እያስጋለበች በጭኖቿ መካከል አስገብታ ልቡ እስከሚጠፋ ድረስ ልታሸውና ትኩስ የወንድነት ወኔውን ጨምቃ ልታጣጥመው ተጣደፈች፡፡

“እጅህን ታጠብ ጌቱ?” ከፊት ለፊቱ ከሞላ ጎደል ዳንስ በሚመስል ሁኔታ እየተውረገረገች የእጅ ማስታጠቢያውን አስጠጋችለት። ድሮ ጌትነት ብላ ነበር የምትጠራው።ዛሬ ግን ከወዲሁ ስሜቱን ለመስረቅ ለየት ያለ ስሜት ልታሳድርበት ፈለገችና ጌቱ ብላ አቆላመጠችው። በዚያ ላይ ደግሞ አድርጋ የማታውቀውን እጁን ልታስታጥበው ተነሳች። ጌትነት ድንግር
ግር አለው፡፡ “እንዴ! ጋሼ ቶሎሳ ሳይመጣ እራት ልበላ?”በፈዘዙ ዐይኖቹ ሽቅብ እየተመለከታት ጠየቃትና ማስታጠቢያውን ከእጇ ሊቀበል ሞከረ።
“ውይ አልነገርኩህም ለካ! የነገርኩህ መስሎኝ፡፡ ስልክ ደወለልኝ እኮ! የጓደኛዬ ልጅ ሞታ ቀብር አለብኝ እያስተዛዘንኩት ነው ብሎ ደወለልኝ”
አምሽቶ ስልክ የደወለ አስመስላ ነገረችው። ጌትነት ቅር ቢለውም እጁን
ለመታጠብ የወንበሩን መደገፊያ ተመርኩዞ ብድግ ሊል ሞከረ።
“እስቲ ለዛሬ ክብሩ ይቅርብኝና ቁጭ ብለህ ታጠብ” ከመቀመጫው እንዳይነሳ በግራ ክርኗ ትከሻውን ወደ ታች ደገፍ አድርጋ አስታጠበችው። እጁን ካስታጠበች በኋላ እንጀራ የተጉዘጉዘበት ሰፊ ትሪ አመጣች። ያንን ሰፊ ትሪ ደግሞ በጥልፍ ባሸበረቀው ትልቁ ሌማት ላይ
ካስቀመጠች በኋላ ያንን በቅመምና በቅቤ ያበደ የዶሮ ወጥ ልታመጣ
ተመልሳ ወደ ጓዳ ገባች። ወጡን ይዛ ስትገባ ረሃብ የሽረሽረው ሆዱ በነጎድጓድ ድምጽ አፍ አውጥቶ ጩኽቱን አቀለጠው..!! የወጡ ሽታ መጣፈጥ
ለጉድ ነበር። ሽዋዬ ጊዜ አላጠፋችም። በፍጥነት ከዋንዛ እንጨት የተሰራውን ኩርሲ ሳብ አድርጋ ከጐኑ ልጥፍ ብላ ተቀመጠችና በአፍ በአፉ ትለቅበት ጀመር፡፡ የጉርሻዋ ክብደት አይጠየቅም፡፡ 'ፍቅርና ጉርሻ ሲያስጨንቅ ነው ባይዋ ሸዋዬ በላይ በላዩ እየጠቀለለች ባጎረሰችው ጉርሻ ሆዱ ተወጠረ። የእራት ሥነ ሥርዐት ጨዋታው በአንድ ቋሚ የጉርሻ ተቀባይና በአንድ ቋሚ አጉራሽ መካከል ሲካሄድ ከቆየ በኋላ“ወደ ማሳረጊያው ላይ ለኔስ አታጎርሰኝም እንዴ?” አለችው እንደማቀፍ እየቃጣት።

“ማጉረስ ስለማልችል እኮ ነው እትዬ ሸዋዬ?” ከመፍዘዛቸው ብዛት ያንቀላፉ የሚመስሉ ዐይኖቹን በግድ ከፍቶ ዐይን ዐይኖቿን ሽቅብ እየተመለከተ።
“ሂድ! ጉረኛ! ይሄኔ የምትወዳት ውሽማህ ብትሆን ኖሮ በጉልበትህ ተንበርክከህ አደግድገህ ነበር የምታጎርሳት” በመቀመጫዋ ጎሽም አደረገችው።

ጌትነት አፈረና አንገቱን አቀረቀረ።
“ምን አንገትህን ትደፋለህ?! አንገት ደፊ አገር አጥፊ አሉ?! እኔ እንደሆንኩ እሳት መሆንህን ያወቅኩት ገና እንዳየሁህ ነው። ነቃሁብ አይደል?” አሁንም በመቀመጫዋ ቡጢዋን ደገመችው። ጌትነት ግራ
ተጋባ፡፡ ያከብራትና ይፈራት የነበረችው ሸዋዬ መሆኗን ተጠራጠረ፡፡ ከሷ
እንደዚህ ያለውን አቀራረብና ቅብጠት ፈፅሞ ያልጠበቀው ነበር። ስሜቱ
በመጠኑ ተረበሽ፡ ወደ መጨረሻ ላይ በግድ ልታጐርሰው ስትታገለው “በቃኝ”ብሉ እጆቿን ይዞ ተማፀናት። ከሚገባው በላይ ሲሆን እህልም ዱላ
ነው። በቁንጣን እንዳይታመም ፈራ።

“ጌቱ ይህቺን ብቻ በሞቴ!!” ሄዳ አንገቱን እቅፍ አድርጋ በግድ አጎረሰችው። የመጨረሻው ጉርሻ እንኳን ሆን ብላ አንገቱን ለማቀፍ እንጂ እንደጠገበ ሳይገባት ቀርቶ አልነበረም፡፡ በአንድ ቋሚ አጉራሽና በአንድ ቋሚ ጎራሽ መካከል ሲካሄድ የቆየው ጨዋታ አብቅቶ ገበታው ሲነሳ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡
አንድ ሰዓት ሙሉ የፈጀ የእራት ሥነ
ሥርአት... ከገበታው በኋላ ሸዋዬ ለራሷም ጠላ በዋንጫ ሞላችና ኩርሲውን የበለጠ አስጠግታ ልጥፍ አለችበት።......

ይቀጥላል

እባካችሁ #MUTE አድርጋችሁ የምትጠቀሙ #UNMUTE አድርጉ በየቀኑ የሚለቀቁትን መከታተል አትችሉም
በድርሰቶቹ ላይም ያለውን አስተያየታችሁን በመወያያ ግሩፑ @dertogadaa እና @atronosebot ላይ ማስፈር ትችላላችሁ
👍1