ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
ቅድ ሰማይ እየሰፋሁ ራስ ዳሽንን እየገፋሁ
ወይስ እየሰራሁ የኖኅ መርከብ
ሳፈላልግ የሰው ኮከብ..
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
እየዘመርኩ?
እየዘፈንኩ?
እያረመምኩ?
ግራ ገባኝ እኮ ያልለየት ድል ነው ያልለየት ምርኮ።
ምን ስሆን ልጠብቅሽ?
አባይን ስጠልቀው
ኤርታሌን ስሞቀው
ቆዳዬን እንደጨርቅ ችሎ ቢተኩሰው ተዋነይ ጋር ልሂድ ዕፁን እንዲምሰው።
ማን ጋር ልጠብቅሽ?
ከጌታዬ ግራ ከጌታዬ ቀኙ በየት ትመጫለሽ ወይ አፍቃሪ ሞኙ።
ካብርሃም ቤት አጋርወይስ
ባቢሎን ግንብ ጋር።
የት ጋር ትመጫለሽ?
በዘመን የት ዘመን? በቦታ የት ቦታ?
ከንጉሥ የት ንጉሥ? ከባህር ምን ባህር? ከጫካ የት ጫካ? ከደብር ምን ደብር?
ከሶላት ምን ሰዓት?
ምን እያረግኩኝ ልጠብቅሽ? ከመላእክት ጋር ስገለፍጥ የዛፍ ቆዳ ስልጥ...
ግዙፍ ሆኜ ወይ ረቂቅ ንፋስ ሆኜ ወይስ ደቂቅ....
ወንዝ ሆኜ ወይስ አምባ ደስታ ሆኜ ወይስ ዕምባ...
ፀሀይ ግርጌ ወይ ጨረቃ
ግጥም ሆኜ ወይ ሙዚቃ...
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
ቅድ ሰማይ እየሰፋሁ ራስ ዳሽንን እየገፋሁ
ወይስ እየሰራሁ የኖኅ መርከብ
ሳፈላልግ የሰው ኮከብ..
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
እየዘመርኩ?
እየዘፈንኩ?
እያረመምኩ?
ግራ ገባኝ እኮ ያልለየት ድል ነው ያልለየት ምርኮ።
ምን ስሆን ልጠብቅሽ?
አባይን ስጠልቀው
ኤርታሌን ስሞቀው
ቆዳዬን እንደጨርቅ ችሎ ቢተኩሰው ተዋነይ ጋር ልሂድ ዕፁን እንዲምሰው።
ማን ጋር ልጠብቅሽ?
ከጌታዬ ግራ ከጌታዬ ቀኙ በየት ትመጫለሽ ወይ አፍቃሪ ሞኙ።
ካብርሃም ቤት አጋርወይስ
ባቢሎን ግንብ ጋር።
የት ጋር ትመጫለሽ?
በዘመን የት ዘመን? በቦታ የት ቦታ?
ከንጉሥ የት ንጉሥ? ከባህር ምን ባህር? ከጫካ የት ጫካ? ከደብር ምን ደብር?
ከሶላት ምን ሰዓት?
ምን እያረግኩኝ ልጠብቅሽ? ከመላእክት ጋር ስገለፍጥ የዛፍ ቆዳ ስልጥ...
ግዙፍ ሆኜ ወይ ረቂቅ ንፋስ ሆኜ ወይስ ደቂቅ....
ወንዝ ሆኜ ወይስ አምባ ደስታ ሆኜ ወይስ ዕምባ...
ፀሀይ ግርጌ ወይ ጨረቃ
ግጥም ሆኜ ወይ ሙዚቃ...
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
❤27👏8👍3
ፈጣሪን ለማን ያሙታል
ቤተ መንግሥቱ ጀርባ ያለው ቅዱስ ገብርዔል ቤተክርስትያን አንዳንዴ አመሻሻ ላይ አርምሞውን፣ ድባቡን፣ የዛፎቹን ሽውታ ስለምወደው ጎራ እላለሁ።
ይሄ ምዕመን ጸሎቱ አድርገልህልኛል እና ተመስገን ነው፤ ይኼኛው አሳካልኝ ተማጽኖ ነው እያልኩ የምዕመናኑን ጸሎት ከሁኔታቸው አንጻር እገምታለሁ፡፡
እዚ የቤተክርስትያን ቅፅር : ግቢ ስገባ ነፍሴ እርጋታ ይሰፍንባታል።
ዛሬ...
ሁልጊዜ ስመጣ የምቀመጥበት ደረጃው ላይ ቁጭ ባልኩበት እማማ ጀማነሽ መጡ። ልጃቸው ከሞተባቸው አራት ቀን ሆኗቸዋል፡፡
እማማ ጀማነሽ ብቻቸውን ሲያወሩ፣ ሳንቲም ሲለምኑ፣ ትክዝ ኩርምት ብለው መሬት ሲጭሩ፣ ማንን እንደሆነ እንጃ ሲሳደቡ ብዙ ቀን አይቻቸዋለሁ፡፡ ሳንቲም ሙዳዬ ምጽዋት ውስጥ ሲከቱም ተመልክቼ አውቃለሁ።
ይለምናሉ። ካሏቸው ሦስት ልጆች ሁለቱ ልጆቻቸው ትንሽ አእምሯቸውን እንደሚያምባቸው አውቃለሁ፡፡
የልጃቸው ቀብር ቀን አይናቸው ላይ ትኩስ እንባ እንዳልታየ በትዝብት የልጃቸውን ስርዓተ ቀብር ቆመው ካለ ዋይታ፣ ካለ እንባ አንጀት የሚበላ ፊት እየታየባቸው እንዳስፈጸሙ ሰምቻለው።
እማማ ጀማነሽ ትንሽ ብቻ ራቅ ብለው አጠገቤ መጥተው ቁጭ አሉ። ሰውነታቸው ደልደል ያለ፣ ፊታቸው ጥብስብስ ያለ፣ ጸጉራቸው በሙሉ የሸበተ፣ ጉስቁልና እያንዳንዱ ዳናቸው ላይ ያረፈባቸው፣ አሮጌ ያደፈ ሙሉ ቀሚስ የለበሱ፣
ሰማያዊ እንደነበረ የሚያስታውቅ የመነቸከ ሻርፕ አድርገው፣ ባዶ እግራቸውን ሆነው መከራ ራሱን መስለዋል።
እማማ ጀማነሽ ትንሽ ቁጭ እንዳሉ አንጋጠው ወደ ሰማይእያዩ፦
“ልጄን ወሰድክ አይደል?! ክፋት ካልሆነ በቀር የሚያምብኝን እዮብን ወይ ሚኪን አትወስድም?!” አሉ።
"ክፉ ሆነህ እንጂ!! አቅም የሌለው ፍጡር ላይ እንዲህ ይጨከናል?! የፈጣሪስ ባሕሪ ነው? ስንት ሰው ለመዳን እየለመነህ እኔ ግደለኝ ስል እምቢ ትል ነበር?
ምግብ የቆለፈውን፣ ሲጮህ የሚውለውን ልጄን ትተህ ሁለት ቀን ያልታመመውን ልጄን ትቀማኛለህ? ለፍቶ፣ ሮጦ በፌስታል እህል የሚያመጣልንን ልጄን፣ አንድ ምርኩዛችንን መቀማት ምን ይባላል?!
እ?!
ፍጡርን ማምለጫ ማሳጣት ምን የሚሉት ጥበብ ነው? እንኳን በሕልውናህ የሚያምን ቀርቶ የካደህስ ቢሆን እንዲህ ይደረጋል?
ይደረጋል ወይ? ክፉ ሆነህ አንጂ!!! እንኳንስ ፈጣሪ በዚህ መጠን ፍጡርስ የወደቀን ለመጣል ይታገላል?!
ለማርያምስ ስንቴ ነገርኳት፤ ሕመሜን፣ እጦቴን እሷ ናት የሚገባት ብዬ ተሳልኩ፣ ለመንኩ፣ ምንም የለም?
በድዬም እንደ ሆነ ይቅር እንድትለኝ ለመንኩህ! ተማጸንኩህ!
መልስ የለም።
ደግሞስ ልበድል! ላጥፋ እኔ ብቻ ነኝ ኃጥያተኛ? ሌላው በሕግህ ስለሄደ ነው ብቻዬን የምሰቀለው?
አንተ ግን ማሰቃየት፣ ምርኩዜን መስበር አይደክምህም ?!"
ከዚህ በላይ የሚናገሩትን ቁጭ ብሎ ለመስማት ፈጣሪን ራሱን መሆን ሳያስፈልግ አይቀርም።
ጌታዬ፣ አንተ ግን እኔ እንደሰማኋቸው ስትሰማቸው ምን ብለህ ይሆን??
🔘አድኀኖም ምትኩ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ቤተ መንግሥቱ ጀርባ ያለው ቅዱስ ገብርዔል ቤተክርስትያን አንዳንዴ አመሻሻ ላይ አርምሞውን፣ ድባቡን፣ የዛፎቹን ሽውታ ስለምወደው ጎራ እላለሁ።
ይሄ ምዕመን ጸሎቱ አድርገልህልኛል እና ተመስገን ነው፤ ይኼኛው አሳካልኝ ተማጽኖ ነው እያልኩ የምዕመናኑን ጸሎት ከሁኔታቸው አንጻር እገምታለሁ፡፡
እዚ የቤተክርስትያን ቅፅር : ግቢ ስገባ ነፍሴ እርጋታ ይሰፍንባታል።
ዛሬ...
ሁልጊዜ ስመጣ የምቀመጥበት ደረጃው ላይ ቁጭ ባልኩበት እማማ ጀማነሽ መጡ። ልጃቸው ከሞተባቸው አራት ቀን ሆኗቸዋል፡፡
እማማ ጀማነሽ ብቻቸውን ሲያወሩ፣ ሳንቲም ሲለምኑ፣ ትክዝ ኩርምት ብለው መሬት ሲጭሩ፣ ማንን እንደሆነ እንጃ ሲሳደቡ ብዙ ቀን አይቻቸዋለሁ፡፡ ሳንቲም ሙዳዬ ምጽዋት ውስጥ ሲከቱም ተመልክቼ አውቃለሁ።
ይለምናሉ። ካሏቸው ሦስት ልጆች ሁለቱ ልጆቻቸው ትንሽ አእምሯቸውን እንደሚያምባቸው አውቃለሁ፡፡
የልጃቸው ቀብር ቀን አይናቸው ላይ ትኩስ እንባ እንዳልታየ በትዝብት የልጃቸውን ስርዓተ ቀብር ቆመው ካለ ዋይታ፣ ካለ እንባ አንጀት የሚበላ ፊት እየታየባቸው እንዳስፈጸሙ ሰምቻለው።
እማማ ጀማነሽ ትንሽ ብቻ ራቅ ብለው አጠገቤ መጥተው ቁጭ አሉ። ሰውነታቸው ደልደል ያለ፣ ፊታቸው ጥብስብስ ያለ፣ ጸጉራቸው በሙሉ የሸበተ፣ ጉስቁልና እያንዳንዱ ዳናቸው ላይ ያረፈባቸው፣ አሮጌ ያደፈ ሙሉ ቀሚስ የለበሱ፣
ሰማያዊ እንደነበረ የሚያስታውቅ የመነቸከ ሻርፕ አድርገው፣ ባዶ እግራቸውን ሆነው መከራ ራሱን መስለዋል።
እማማ ጀማነሽ ትንሽ ቁጭ እንዳሉ አንጋጠው ወደ ሰማይእያዩ፦
“ልጄን ወሰድክ አይደል?! ክፋት ካልሆነ በቀር የሚያምብኝን እዮብን ወይ ሚኪን አትወስድም?!” አሉ።
"ክፉ ሆነህ እንጂ!! አቅም የሌለው ፍጡር ላይ እንዲህ ይጨከናል?! የፈጣሪስ ባሕሪ ነው? ስንት ሰው ለመዳን እየለመነህ እኔ ግደለኝ ስል እምቢ ትል ነበር?
ምግብ የቆለፈውን፣ ሲጮህ የሚውለውን ልጄን ትተህ ሁለት ቀን ያልታመመውን ልጄን ትቀማኛለህ? ለፍቶ፣ ሮጦ በፌስታል እህል የሚያመጣልንን ልጄን፣ አንድ ምርኩዛችንን መቀማት ምን ይባላል?!
እ?!
ፍጡርን ማምለጫ ማሳጣት ምን የሚሉት ጥበብ ነው? እንኳን በሕልውናህ የሚያምን ቀርቶ የካደህስ ቢሆን እንዲህ ይደረጋል?
ይደረጋል ወይ? ክፉ ሆነህ አንጂ!!! እንኳንስ ፈጣሪ በዚህ መጠን ፍጡርስ የወደቀን ለመጣል ይታገላል?!
ለማርያምስ ስንቴ ነገርኳት፤ ሕመሜን፣ እጦቴን እሷ ናት የሚገባት ብዬ ተሳልኩ፣ ለመንኩ፣ ምንም የለም?
በድዬም እንደ ሆነ ይቅር እንድትለኝ ለመንኩህ! ተማጸንኩህ!
መልስ የለም።
ደግሞስ ልበድል! ላጥፋ እኔ ብቻ ነኝ ኃጥያተኛ? ሌላው በሕግህ ስለሄደ ነው ብቻዬን የምሰቀለው?
አንተ ግን ማሰቃየት፣ ምርኩዜን መስበር አይደክምህም ?!"
ከዚህ በላይ የሚናገሩትን ቁጭ ብሎ ለመስማት ፈጣሪን ራሱን መሆን ሳያስፈልግ አይቀርም።
ጌታዬ፣ አንተ ግን እኔ እንደሰማኋቸው ስትሰማቸው ምን ብለህ ይሆን??
🔘አድኀኖም ምትኩ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢27❤8
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹በተሰቀለው…አሁን ምንድነው የምናደርገው?››
‹‹አላውቅም…ለአባትህ ደውልለትና በአስቸኳይ ይምጣ…እዛ ይርጋጨፌ ምንም አያደርግም››
‹‹ደውዬለታለው… እየመጣነው››ሲል መለሰ ጁኑየር
‹‹ዳኛውም እየደወለልኝ ነበር››
‹‹እሱን ተወው ባክህ..ከአሁኑ በልብ ድካም እስከወዲያኛው ማንቀላፋቱ አይቀርም..ለማንኛውም እዚህ ምንም አንሰራም ..ወደቤት እንሄድ›› ተባባሉና ሁለቱም ወደ መኪናቸው በመግባት ተከታትለው ወደእነ ጁኒዬር ቤት መጓዝ ጀመሩ፡፡
በማግስቱ ጥዋት አንድ ሰዓት በሶሌ ኢንተርፕራይዝ ህንፃ የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እየተወያዩ ነው፡፡
‹‹ያሰማራናቸውን ሰዎች ምንም ፍንጭ አላገኙም››አቶ ፍሰሀ ናቸው ጠያቂው፡፡
‹‹እዚህ ከተማ ውስጥ ያለች አይመስለኝም….እያንዳንዱን ሆቴል እና ፔንሲዬን አሳስሼለው….የለችም፡፡››ገመዶ መለሰ፡፡
‹‹ወደ አዲስአበባ ተመልሳ ሊሆን ይችላል?››
‹‹ወደዛም ሰው ልኬለው…..እንግዲህ የሚሆነውን እናያለን፡፡››
‹‹ጥሩ …ዩቲዬብ ባለቤትስ ማግኘት ችለናል…..?››አቶ ፍሰሀ ናቸው ሌላ ጥያቄ የጠየቁት፡፡
‹‹አዎ አናግሬው ነበር…የፈለገውን ያህል ብር እንደምንከፍለውና ቀጣዩን ስራ እንዳይለቅ ጠይቄው ነበር…››
‹‹እና?››
‹‹እናማ…ቀጣዩን አልሰጠችኝም…እራሷ ቀርፃ ነው የምትልክልኝ ….››የሚል መልስ ነው የሰጠኝ፡፡
እንደዛ ከሆነ እኮ አሪፍ ነው…ለልጁ ደህና ብር ስጡትና ቀጣዩን ታሪክ ልታስረክበው ስትቀጥረው ይደውልልን እና እናገኛታለን ማለት ነው››ዳኛው በአዲስ ተስፋ ተሞልተው ተናገሩት፡፡
ኩማንደር ፈገግ አለና‹‹ክቡር ዳኛ….ይሄንን ማሰብ የሚያቅተኝ ይመስልሀል?››
‹‹አይ በፍጹም እንደዛ አላልኩም….ውይይት ላይ ስለሆን የተሰማኝን በግልፅ ነው የተናገርኩት››
‹‹ጥሩ…ለልጁ ይሄንን ሀሳብ አቅርቤለት ነበር….ወዲያው ይሄንን መልእክት አሳየኝ፡፡››
‹‹ምንድነው?››
በዩቲዬብ የተለቀቀውን የወንጀል ታሪካችሁን መንደርደሪያ ስትሰሙ መጀመሪያ ምታደርጉት ወደእዚህ ዩቲዩበሩ ልጅ ጋር ሄዳችሁ በገንዘብም በማስፈራራትም ቀጣዩን እንዳይለቀውና በእሱ አማካይነት እኔን ለመያዝ እንደምትሞክሩ አውቃለው….ለዛም ነው ቀድሜ ይሄንን መልዕክት ልጁ ጋር የተውኩት፡፡አንደኛ ከአሁን በኃላ ቀጥታ ልጁን አላገኘውም .. የተቀረፀውን በሌላ መንገድ ነው ምልክለት፡፡ሁለተኛ ልጅን የምታቆሙት ከሆነ እየተቆራረጠ በአምስት ክፍል ይለቀቅ የነበረውን ለሌላ ዩቲዬበር አንዴ ሰጥቼው በአንዴ እንዲለቀቅና ነገሮች ፍርጥርጥ እንዲሉ አደርጋለው ….ያ ማለት ደግሞ ለማሰቢያ እና የተሻለውን መንገድ መምረጫ ጊዜ ያሳጣችኋላ..እንግዲህ ምርጫው የእናንተ ነው፡፡››ይላል፡፡
‹‹ምን አይነት ጉድ ልጅ ነች?››አቶ ፍሰሀ ነው የተናገረው፡፡
‹‹ብዬችሁ ነበር..አልሰማ ብላችሁ ሁላችንንም መቀመቅ ውስጥ ከተታችሁኝ….በጊዜ ትወገድ ብያችሁ ነበር፡፡››ዳኛው ተወራጩ፡፡
‹‹አንተ ቀበተት ሽማግሌ…በዚህ እድሜህ አንድ ፍሬ ልጅ ትገደል ስትል ትንሽ አይቀፍህም?››አቶ ፍሰሀ በንዴት መለሰ፡፡
‹‹አሁንማ እንድትገደል ብንስማማስ የት እናገኛታለን?በዚህ ሁሉ እድሜዬ አንተንና ኩማንደሩን በእንደዚህ አይነት ጫወታ የበለጠች ብቸኛዋ ሴት እሷ ብቻ ነች፡፡በጣም ብጠላትም በጣም የምትደነቅ ጀግና የሆነች ልጅ ነች››ሲል ዳኛው ተናገረ፡፡
በዚህ ሰዓት ድንገት የኩማንደሩ ስልክ ጠራ ..ከኪሱ አወጣና አየው…..የማያውቀው ቁጥር ነው፡፡አነሳው‹‹ውዴ በጣም ናፍቀኸኛል››
በስልኩ በእግር በፈረስ የሚፈልጋትን የአለም ድምፅ እየሰማ መሆኑን ማመን አልቻለም
‹‹አንቺ…የትነሽ ያለሽው?››
‹‹ቅርብህ ነኝ….ጁኒዬርም አብሮህ ነው አይደል?››
‹‹ምን እያወራሽ ነው?››
‹‹ሁለችሁም ናፍቃችሁኛል?››
‹‹ቀለድሽብን ማለት ነው?››
‹‹አይደለም…መቼስ ሁለታችሁንም እንደምወዳችሁ አትጠራጠሩም አይደል..?ልክ እንደእናቴ… እኔም አፈቅራኋላው፡፡››
ሁሉም አፍጥጠው ይመለከቱት ነበር‹‹እና ምንድነው የምትፈልጊው?፡፡››
‹‹ምፈልገውንማ መጀመሪያ ከተገናኘንበት ቀን አንስቶ መች ደብቄችሁ አውቃለው››
‹‹እና አሁን ምን ይሁን ነው የምትይው?››
‹‹ምንም ….እኔ አሁን እየፈለኩት ስላላው ፍትህ ወይም በቀል ላወራችሁ አይደለም የደወልኩት ..ድምፃችሁን ልሰማ ነው..እባክህ ስልኩን ለጁኒዬር ትሰጠዋለህ፣በጣም ነፍቆኛል…››
‹‹ገደል ግቢ››አለና ስልኩን ጠረቀመው፡፡
‹‹ምንድነው ..ስልኩን ለምን ዘጋህባት?››ጁኒዬር በንዴት ጠየቀው፡፡
‹‹እሷ ኮመዲ እየሰራችብን ነው..እንደናፈቅካት ተናግራ ካንተ እንዳገናኛት ነው የምትፈልገው››
‹‹ታዲያ ለምን ሳታገኛኘን?››
‹‹ምነው ?አንተም ናፍቃሀለች እንዴ?››
‹‹ተረጋጉ…ሁላችም ወደመቀመጫችሁ ተመለሱ››አቶ ፍሰሀ በመሀከል ጣልቃ ገብተው ሁሉም ወደቀልባቸው እንዲመለሱ አደረጉ፡፡
‹‹ልጆች አይታያችሁም እንዴ..?ይሄ እኮ የበቀሏአንዱ አካል ነው፡፡››
‹‹ማለት..?››ገመዶም ሆነ ጁኒዬር በአንድነት አቶ ፍሰሀ ላይ አፈጠጡ፡፡
‹‹በሁለታችሁ መካከል ቅሬታ በመፍጠር ኃይላችንን ለመበታተን እየጣረች ነው….›› ጁኒዬር ባለማመን ‹‹እንደዛ አስባ ይመስልሀል?፡፡››ሲል በጥርጣሬ ጠየቀ፡፡
‹‹ታዲያ ያንተን ስልክ እያወቀች ለምን ብላ ነው ለገመዶ ደውላ ከጁኒዬር ጋር አገናኘኝ ናፍቆኝ ነው የምትለው?››
‹‹አባዬ እውነትህን ነው….››
///
በተሰጣቸው ሶስት ቀን ውስጥ እሷን አድነው መያዝ አልቻሉም…እሷንም ቀጣዩን ክፍል በተመሳሳይ በዩቲዩብ ገፅ እንዳትለቅ ማድረግ አልቻሉም…ይሄ ሁለተኛው ግን ከመጀመሪያው በበለጠ ጫና ውስጥ ከተታቸው፡፡የከተማው የገዢው ፓርቲ ፅህፈት ቤትም ጁኒዬርን አስጠርቶ በሶሻል ሚዲያው ስለሚዘዋወረው ነገር ማብራሪያ እንዲያቀርብና በአፋጣኝ እየተሰነዘረበት ካለው ክስ ራሱ ነፃ እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው፡፡
‹‹አባዬ..ይህ ምርጫ ለምን አይቀርብኝም?››
‹‹ለምን እንደዛ አልክ?››
‹‹የፓርቲው ሰዎች እኮ ቁም ስቅሌን እያሳዩኝ ነው፡፡በአንድ ሳምንት ውስጥ በእኔና በቤተሰቦቼ ላይ እየተነዛ ያለውን ሀሚት ማጥራት ካልቻልኩ በእኔ ጉዳይ ላይ አቋም እንደሚወስዱ ነግረውኛል››
‹‹ምን አይነት አቋም››
‹‹ይመስለኛል..እጩ መቀየር የሚችሉት እስከዚህ ወር መጨረሻ ድረስ ነው፡፡እዚህ ከተማ ላይ በተቃዋሚዎች መሸነፍ አይፈልጉም ..ስለዚህ በሌላ እጩ ሊተኩኝ እያሰቡ ይመስለኛል፡፡››
‹‹ወይ ነዶ..ያን ሁሉ ብር ከስክሰን እንደዚህ ጉድ እንሁን…የክልል ወዳጆቻችንም ለእኔ ደጋግመው እየደወሉልኝ ነው፡፡ልጅቷን መያዝ ካልቻላችሁ እኛ እናግዛችሁ እያሉ ነው፡፡››
‹‹እንዴት አድርገው ነው የሚያግዙን››ጁኒዬር ጠየቀ፡፡
‹‹በአካባቢው ያሉትን የከተማ የፀጥታ አካላት በማነጋገር ፍላጋው ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ ነዋ››
‹‹ታዲያ አሪፍ እድል አይደል?››
‹‹አሪፍ እድል ነው..ግን ደግሞ እገዛቸውን አልተቀበልኩም››
‹‹ለምን?››
‹‹ምክንያቱም እሷን በማደኑ ላይ የመንግስት የፀጥታ አካላት ከገቡበት ድንገት ባልታሰበ ሁኔታ ልትጎዳ ትችላለች…ያንን ሪስክ መውሰድ አልችልም››
‹‹አባዬ..እዚህች ልጅ ላይ የምታሳየው የርህራሄ ስሜት ከእለት ወደእለት እያስደመመኝ ነው፡፡የተለየ ምክንያት አለህ እንዴ?››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹በተሰቀለው…አሁን ምንድነው የምናደርገው?››
‹‹አላውቅም…ለአባትህ ደውልለትና በአስቸኳይ ይምጣ…እዛ ይርጋጨፌ ምንም አያደርግም››
‹‹ደውዬለታለው… እየመጣነው››ሲል መለሰ ጁኑየር
‹‹ዳኛውም እየደወለልኝ ነበር››
‹‹እሱን ተወው ባክህ..ከአሁኑ በልብ ድካም እስከወዲያኛው ማንቀላፋቱ አይቀርም..ለማንኛውም እዚህ ምንም አንሰራም ..ወደቤት እንሄድ›› ተባባሉና ሁለቱም ወደ መኪናቸው በመግባት ተከታትለው ወደእነ ጁኒዬር ቤት መጓዝ ጀመሩ፡፡
በማግስቱ ጥዋት አንድ ሰዓት በሶሌ ኢንተርፕራይዝ ህንፃ የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እየተወያዩ ነው፡፡
‹‹ያሰማራናቸውን ሰዎች ምንም ፍንጭ አላገኙም››አቶ ፍሰሀ ናቸው ጠያቂው፡፡
‹‹እዚህ ከተማ ውስጥ ያለች አይመስለኝም….እያንዳንዱን ሆቴል እና ፔንሲዬን አሳስሼለው….የለችም፡፡››ገመዶ መለሰ፡፡
‹‹ወደ አዲስአበባ ተመልሳ ሊሆን ይችላል?››
‹‹ወደዛም ሰው ልኬለው…..እንግዲህ የሚሆነውን እናያለን፡፡››
‹‹ጥሩ …ዩቲዬብ ባለቤትስ ማግኘት ችለናል…..?››አቶ ፍሰሀ ናቸው ሌላ ጥያቄ የጠየቁት፡፡
‹‹አዎ አናግሬው ነበር…የፈለገውን ያህል ብር እንደምንከፍለውና ቀጣዩን ስራ እንዳይለቅ ጠይቄው ነበር…››
‹‹እና?››
‹‹እናማ…ቀጣዩን አልሰጠችኝም…እራሷ ቀርፃ ነው የምትልክልኝ ….››የሚል መልስ ነው የሰጠኝ፡፡
እንደዛ ከሆነ እኮ አሪፍ ነው…ለልጁ ደህና ብር ስጡትና ቀጣዩን ታሪክ ልታስረክበው ስትቀጥረው ይደውልልን እና እናገኛታለን ማለት ነው››ዳኛው በአዲስ ተስፋ ተሞልተው ተናገሩት፡፡
ኩማንደር ፈገግ አለና‹‹ክቡር ዳኛ….ይሄንን ማሰብ የሚያቅተኝ ይመስልሀል?››
‹‹አይ በፍጹም እንደዛ አላልኩም….ውይይት ላይ ስለሆን የተሰማኝን በግልፅ ነው የተናገርኩት››
‹‹ጥሩ…ለልጁ ይሄንን ሀሳብ አቅርቤለት ነበር….ወዲያው ይሄንን መልእክት አሳየኝ፡፡››
‹‹ምንድነው?››
በዩቲዬብ የተለቀቀውን የወንጀል ታሪካችሁን መንደርደሪያ ስትሰሙ መጀመሪያ ምታደርጉት ወደእዚህ ዩቲዩበሩ ልጅ ጋር ሄዳችሁ በገንዘብም በማስፈራራትም ቀጣዩን እንዳይለቀውና በእሱ አማካይነት እኔን ለመያዝ እንደምትሞክሩ አውቃለው….ለዛም ነው ቀድሜ ይሄንን መልዕክት ልጁ ጋር የተውኩት፡፡አንደኛ ከአሁን በኃላ ቀጥታ ልጁን አላገኘውም .. የተቀረፀውን በሌላ መንገድ ነው ምልክለት፡፡ሁለተኛ ልጅን የምታቆሙት ከሆነ እየተቆራረጠ በአምስት ክፍል ይለቀቅ የነበረውን ለሌላ ዩቲዬበር አንዴ ሰጥቼው በአንዴ እንዲለቀቅና ነገሮች ፍርጥርጥ እንዲሉ አደርጋለው ….ያ ማለት ደግሞ ለማሰቢያ እና የተሻለውን መንገድ መምረጫ ጊዜ ያሳጣችኋላ..እንግዲህ ምርጫው የእናንተ ነው፡፡››ይላል፡፡
‹‹ምን አይነት ጉድ ልጅ ነች?››አቶ ፍሰሀ ነው የተናገረው፡፡
‹‹ብዬችሁ ነበር..አልሰማ ብላችሁ ሁላችንንም መቀመቅ ውስጥ ከተታችሁኝ….በጊዜ ትወገድ ብያችሁ ነበር፡፡››ዳኛው ተወራጩ፡፡
‹‹አንተ ቀበተት ሽማግሌ…በዚህ እድሜህ አንድ ፍሬ ልጅ ትገደል ስትል ትንሽ አይቀፍህም?››አቶ ፍሰሀ በንዴት መለሰ፡፡
‹‹አሁንማ እንድትገደል ብንስማማስ የት እናገኛታለን?በዚህ ሁሉ እድሜዬ አንተንና ኩማንደሩን በእንደዚህ አይነት ጫወታ የበለጠች ብቸኛዋ ሴት እሷ ብቻ ነች፡፡በጣም ብጠላትም በጣም የምትደነቅ ጀግና የሆነች ልጅ ነች››ሲል ዳኛው ተናገረ፡፡
በዚህ ሰዓት ድንገት የኩማንደሩ ስልክ ጠራ ..ከኪሱ አወጣና አየው…..የማያውቀው ቁጥር ነው፡፡አነሳው‹‹ውዴ በጣም ናፍቀኸኛል››
በስልኩ በእግር በፈረስ የሚፈልጋትን የአለም ድምፅ እየሰማ መሆኑን ማመን አልቻለም
‹‹አንቺ…የትነሽ ያለሽው?››
‹‹ቅርብህ ነኝ….ጁኒዬርም አብሮህ ነው አይደል?››
‹‹ምን እያወራሽ ነው?››
‹‹ሁለችሁም ናፍቃችሁኛል?››
‹‹ቀለድሽብን ማለት ነው?››
‹‹አይደለም…መቼስ ሁለታችሁንም እንደምወዳችሁ አትጠራጠሩም አይደል..?ልክ እንደእናቴ… እኔም አፈቅራኋላው፡፡››
ሁሉም አፍጥጠው ይመለከቱት ነበር‹‹እና ምንድነው የምትፈልጊው?፡፡››
‹‹ምፈልገውንማ መጀመሪያ ከተገናኘንበት ቀን አንስቶ መች ደብቄችሁ አውቃለው››
‹‹እና አሁን ምን ይሁን ነው የምትይው?››
‹‹ምንም ….እኔ አሁን እየፈለኩት ስላላው ፍትህ ወይም በቀል ላወራችሁ አይደለም የደወልኩት ..ድምፃችሁን ልሰማ ነው..እባክህ ስልኩን ለጁኒዬር ትሰጠዋለህ፣በጣም ነፍቆኛል…››
‹‹ገደል ግቢ››አለና ስልኩን ጠረቀመው፡፡
‹‹ምንድነው ..ስልኩን ለምን ዘጋህባት?››ጁኒዬር በንዴት ጠየቀው፡፡
‹‹እሷ ኮመዲ እየሰራችብን ነው..እንደናፈቅካት ተናግራ ካንተ እንዳገናኛት ነው የምትፈልገው››
‹‹ታዲያ ለምን ሳታገኛኘን?››
‹‹ምነው ?አንተም ናፍቃሀለች እንዴ?››
‹‹ተረጋጉ…ሁላችም ወደመቀመጫችሁ ተመለሱ››አቶ ፍሰሀ በመሀከል ጣልቃ ገብተው ሁሉም ወደቀልባቸው እንዲመለሱ አደረጉ፡፡
‹‹ልጆች አይታያችሁም እንዴ..?ይሄ እኮ የበቀሏአንዱ አካል ነው፡፡››
‹‹ማለት..?››ገመዶም ሆነ ጁኒዬር በአንድነት አቶ ፍሰሀ ላይ አፈጠጡ፡፡
‹‹በሁለታችሁ መካከል ቅሬታ በመፍጠር ኃይላችንን ለመበታተን እየጣረች ነው….›› ጁኒዬር ባለማመን ‹‹እንደዛ አስባ ይመስልሀል?፡፡››ሲል በጥርጣሬ ጠየቀ፡፡
‹‹ታዲያ ያንተን ስልክ እያወቀች ለምን ብላ ነው ለገመዶ ደውላ ከጁኒዬር ጋር አገናኘኝ ናፍቆኝ ነው የምትለው?››
‹‹አባዬ እውነትህን ነው….››
///
በተሰጣቸው ሶስት ቀን ውስጥ እሷን አድነው መያዝ አልቻሉም…እሷንም ቀጣዩን ክፍል በተመሳሳይ በዩቲዩብ ገፅ እንዳትለቅ ማድረግ አልቻሉም…ይሄ ሁለተኛው ግን ከመጀመሪያው በበለጠ ጫና ውስጥ ከተታቸው፡፡የከተማው የገዢው ፓርቲ ፅህፈት ቤትም ጁኒዬርን አስጠርቶ በሶሻል ሚዲያው ስለሚዘዋወረው ነገር ማብራሪያ እንዲያቀርብና በአፋጣኝ እየተሰነዘረበት ካለው ክስ ራሱ ነፃ እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው፡፡
‹‹አባዬ..ይህ ምርጫ ለምን አይቀርብኝም?››
‹‹ለምን እንደዛ አልክ?››
‹‹የፓርቲው ሰዎች እኮ ቁም ስቅሌን እያሳዩኝ ነው፡፡በአንድ ሳምንት ውስጥ በእኔና በቤተሰቦቼ ላይ እየተነዛ ያለውን ሀሚት ማጥራት ካልቻልኩ በእኔ ጉዳይ ላይ አቋም እንደሚወስዱ ነግረውኛል››
‹‹ምን አይነት አቋም››
‹‹ይመስለኛል..እጩ መቀየር የሚችሉት እስከዚህ ወር መጨረሻ ድረስ ነው፡፡እዚህ ከተማ ላይ በተቃዋሚዎች መሸነፍ አይፈልጉም ..ስለዚህ በሌላ እጩ ሊተኩኝ እያሰቡ ይመስለኛል፡፡››
‹‹ወይ ነዶ..ያን ሁሉ ብር ከስክሰን እንደዚህ ጉድ እንሁን…የክልል ወዳጆቻችንም ለእኔ ደጋግመው እየደወሉልኝ ነው፡፡ልጅቷን መያዝ ካልቻላችሁ እኛ እናግዛችሁ እያሉ ነው፡፡››
‹‹እንዴት አድርገው ነው የሚያግዙን››ጁኒዬር ጠየቀ፡፡
‹‹በአካባቢው ያሉትን የከተማ የፀጥታ አካላት በማነጋገር ፍላጋው ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ ነዋ››
‹‹ታዲያ አሪፍ እድል አይደል?››
‹‹አሪፍ እድል ነው..ግን ደግሞ እገዛቸውን አልተቀበልኩም››
‹‹ለምን?››
‹‹ምክንያቱም እሷን በማደኑ ላይ የመንግስት የፀጥታ አካላት ከገቡበት ድንገት ባልታሰበ ሁኔታ ልትጎዳ ትችላለች…ያንን ሪስክ መውሰድ አልችልም››
‹‹አባዬ..እዚህች ልጅ ላይ የምታሳየው የርህራሄ ስሜት ከእለት ወደእለት እያስደመመኝ ነው፡፡የተለየ ምክንያት አለህ እንዴ?››
❤51👍7😁1
‹‹ለእሷ ደህንነት ለመጨነቅ ምን የተለየ ምክንያት ያስፈልጋል…..አንዴ ስህተት ሰርተን እናቷን በጨቅላ እድሜዋ አሳጥተናታል….አሁን ደግሞ መልሰን እሷን ብንጎዳት ይቅር የሚባል ድርጊት አይሆንም..››
‹‹እና ምን ትላለህ…?.የሰራሁት ስህተት የምከፍልበት ጊዜ ደርሷል ..ከዚህ በላይ ቤተሰቤንም ሆነ በዙሪያዬ ያሉ ሰዎች ሲረበሹና ሲጎዱ ቁጭ ብዬ ማየት አልችልም፡፡››
‹‹ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው…?ምን ለማድረግ አስበህ ነው?፡፡››
‹‹በመጀመሪያ ነገ ጥዋት የፓርቲው ፅ/ቤት ሄጂ ከእጩነት እንዲያነሱኝና በእኔ ምትክ ሌላ ሰው እንዲተኩ ማመልከቻዬን አስገባለው፡፡ከዛ ቀጣዩን ደግሞ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አስብበታለው..ሶስተኛው ቪዲዬ ከመልቀቋ በፊት አንድ ሰው ኃላፊነቱን መውሰድና እሷንም ማቆም መቻል አለብን፡፡››
‹‹ልጄ ..እንዳልከው ከእጩነት እራስህን የማግለሉን ውሳኔ እኔም እቀበለዋለው…ከዛ ውጭ ግን በራስህ ምንም ነገር አታደርግም..እዚህ ጉዳይ ላይ ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ ሁላችንም አብረን ነበርን..አሁንም አብረን ነን … መደረግ ያለበትን ሁሉ ተነጋግረንና ተስማምተን ነው የምንወስነው፡፡››
‹‹አባዬ ለዛ የሚሆን ጊዜ እኮ የለንም››
‹‹አውቃለው…አታስብ ዛሬና ነገን የሆነ ነገር እናደርጋለን..በል አሁን ወደ ቤት ልሄድ ነው፡፡››
‹‹እሺ አባዬ እኔም የተወሰነ መስራት ያለብኝ ስራ አለ…ማታ እቤት መጣለው….››
‹‹ጥሩ ››አለና….ቢሮውን ለቆ በመውጣት ካለወትሮው መኪናውን እራሱ እያሽከረከረ ወደቤቱ ጉዞ ጀመረ፡፡
አቶ ፍሰሀ ቤቱ ከመድረሱ በፊት በጣም ተጨናነቀ … ወደአንድ ግሮሰሪ ጎራ አለና የሚፈልገውን መጠጥ አዞ እየተጎነጨ ይሄንን ከአልም ጋር ያለውን ችግር በምን ዘዴ ሊፈታው እንደሚችል ማሰላሰል ጀመረ..
….////
አለም እዛው ሻሸመኔ ከተማ በተከራየችው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ሆና ጥግ ግድግዳ ታካ በተነጠፈች አንድ ሜትር ፍራሽ ላይ ጋደም ብላ በቀጣይ ማድረግ ስላለባት ነገር እያሰላሰለች ነው፡፡አሁን የመጀመሪያ በቀሏን ባሰበችው መንገድ አሳካታለች…ጁኒዬር ከተማዋን ወክሎ ለፌዴራል ህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት ለመግባት የነበረውን ሀሳብ ሰርዞ ከእጩነት እራሱን እንዲያገል ማድረግ ችላለች፡፡
በቀጣይ ደግሞ የበቀሏ ጅራፍ የሚለመጥጠው ኩማንደሩን ነው..እሱም ቢያንስ ስልጣኑን እንዲለቅና ከስራውም እንዲታገድ ማድረግ ነው የምትፈልገው…ከዚያም እንዲረዳት በቀጣይ እያዘጋጀች ያለችው በዩቲዬብ የሚለቀቀውን ሶስተኛ ቪዲዬ በእሱ ወንጀሎች ዙሪያ እንዲያጠነጥን እያደረገች ነው፡ሶሌ ኢንተርፕራይዝ ውስጥ ያለው ሚስጥራዊ የአክሲዬን ድርሻ ፤ እና ይሄንን ኢንተርፕራይዝ ለማሳደግ እድገትና ደህንት ለመጠበቅ ስልጣኑንና የመንግስትን ንብረት እንዴት አላግባብ ሲጠቀም እንደኖረ መረጃዎችን እያጠናከረችና እያደራጀች ነው፡፡
በቀጣይ ደግሞ ዳኛው ላይ ትዘምታለች..እሱም ለክብር ጡረታ ሳይበቃ ቀጥታ ከወንበሩ በውርደት ተሸቀንጥሮ ወደወህኒ እንዲወረወር ነው የምትፈልገው፡፡በመጨረሻ የአቶ ፍሰሀ ተራ ይሆናል፡፡ሁሉንም ቀስ በቀስ ክንፋቸውን በየተራ እየነቃቀለች በማድቀቅ መብረር የማይችሉ ተራ ሰው ታደርጋቸዋለች..አዎ እቅዷ እንደዛ ነው፡፡ሴቶቹን ለማጥፋት ጉልበቷን አታባክንም….ወንዶቹ ሲከስሙ እነሱም መደብዘዛቸው እና መንኮታኮታቸው አይቀርም…ከዛ በኃላ ምን አልባት ከተማውንም ሆነ ሀገሪቱን ለቃ ትሰደድ ይሆናል!!እዚህ ሀገር እንድትኖር የሚያበረታታ ምን ተዝታና ምን አይነት ተስፋ ይቀራታል?
ድንገት ብልጭ አለባትና ከተኛችበት ተነስታ ቻርጀር ላይ የነበረውን ስልኳን አነሳችና ክፍል ውስጥ ከነበረችው አንድና ብቸኛ አነስተኛ ጠረጴዛ ላይ ካሉ ከስምንት ከሚበልጡ ሲም ካርዶች መካከል አንዱን አነሳችና ስልኳ ውስጥ ከጨመረች በኃላ መደወል የምትፍገውን ቁጥር ፈለገችና ደወለች….ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ…ማን ልበል?››
‹‹እኔ ነኝ ..ጋሽ ፍሰሀ››
‹‹ይቅርታ የእኔ እመቤት …አላወቅኩሽም››
‹‹እንደው ብትረሳ ብትረሳ ይሄን ድምፅ ትረሳለህ..እርግጠኛ ነኝ ከመደወሌ በፊት እራሱ ስለእኔ ነበር እያሰብክ ያለሀው››
‹‹አለም ነሽ እንዴ?››
‹‹በትክክል ተመልሷል››
‹‹እንዴት ነሽ…?የት ነሽ?››
‹‹ተው እንጂ ጋሽ ፍሰሀ… አሁን እዚህ ቦታ ነኝ ብዬ የምገኝበትን ቦታ የምነግርህ ይመስልሀል?ባይሆን አንተ የት ነህ…?መኪና እየነዳህ ይመስላል?፡፡››
‹‹አዎ …ምንም እልተሳሳትሽም..ስለአንቺ እያሰብኩ እየነዳው ቤቴን አልፌ ከተማውንም ለቅቄ ወደ ባሌ ጎባ የሚወስደውን መንገድ ይዤ እየነዳው ነው፡፡››
‹‹በዚህ ማታ… ሁለት ሰዓት እኮ ሆኗል….››
‹‹አላስተዋልኩም ነበር..አሁን እማ እዚህ ሶሌ መድረሴ ካልቀረ ወደ ደን ማሳዬ እየገባው ነው….እዚሁ አድሬ ጥዋት እመለሳለው..ደኑ ውስጥ ማረፊያ ጎጆ አለን››
‹‹አይ ጥሩ ነው…እንደውም እኔን እንዴት በቀላሉ አጥምደህ በእጅህ ማስገባት እንደምትችል የሆነ ሀሳብ ብልጭ ሊልልህ ይችላል…እንደዛ አይነት በደን የተሸፈነ ፀጥ ያለ ቦታ ለማሰብ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቼለው››
‹‹ጥሩ እየተዝናናሽብን ነው አይደል?››
‹‹አረ ምን በወጣኝ››
‹‹እሺ..አሁን ለምን ፈልግሺኝ››
‹‹እንዲሁ ናፍቀኸኝ….››
‹‹ምን አልሽ…?ቆይ ወይኔ አውሬ ገባብኝ…አውሬ….››የመርበትበት ድምጹን ተከትሎ ከፍተኛ የመንጓጓትና የፍንዳታ ድምፅ ተሳማ…በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤት
ውስጥ እየተዟዟረች ስልኩን ብትሞክር ይጠራል አይነሳም…..ምታደርገው ግራኝ ገባት
..ቀጥታ ቦርሳዋን ይዛ ከቤት ወጣች…ታክሲ ያዘችና መሄድ ወደማታስብበት ወደቀድሞ ቤቷ አመራች …እንደደረሰች ታክሲውን አሰናበተች እና ቀጥታ ወደግቢው ውስጥ ነው የገባችው…ምን አልባት የሆነ ከለላ ስር ተደብቆ የእሷን መምጣጥ የሚጠብቅ ሰላይ ሊኖር እንደሚችል ትገምታለች..ቢሆንም ግድ አልሰጣትም፡፡ቀጥታ ግቢ ውስጥ ወደቆመችው መኪናዋ ነው ያመራችው …ውስጥ ገባችና ሞተሩን አስነስታ እየነዳች ከግቢው ይዛ ወጣች
..ቀጥታ አቶ ፍሰሀ ወደነገራት አቅጣጫ መንዳት ጀመረች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹እና ምን ትላለህ…?.የሰራሁት ስህተት የምከፍልበት ጊዜ ደርሷል ..ከዚህ በላይ ቤተሰቤንም ሆነ በዙሪያዬ ያሉ ሰዎች ሲረበሹና ሲጎዱ ቁጭ ብዬ ማየት አልችልም፡፡››
‹‹ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው…?ምን ለማድረግ አስበህ ነው?፡፡››
‹‹በመጀመሪያ ነገ ጥዋት የፓርቲው ፅ/ቤት ሄጂ ከእጩነት እንዲያነሱኝና በእኔ ምትክ ሌላ ሰው እንዲተኩ ማመልከቻዬን አስገባለው፡፡ከዛ ቀጣዩን ደግሞ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አስብበታለው..ሶስተኛው ቪዲዬ ከመልቀቋ በፊት አንድ ሰው ኃላፊነቱን መውሰድና እሷንም ማቆም መቻል አለብን፡፡››
‹‹ልጄ ..እንዳልከው ከእጩነት እራስህን የማግለሉን ውሳኔ እኔም እቀበለዋለው…ከዛ ውጭ ግን በራስህ ምንም ነገር አታደርግም..እዚህ ጉዳይ ላይ ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ ሁላችንም አብረን ነበርን..አሁንም አብረን ነን … መደረግ ያለበትን ሁሉ ተነጋግረንና ተስማምተን ነው የምንወስነው፡፡››
‹‹አባዬ ለዛ የሚሆን ጊዜ እኮ የለንም››
‹‹አውቃለው…አታስብ ዛሬና ነገን የሆነ ነገር እናደርጋለን..በል አሁን ወደ ቤት ልሄድ ነው፡፡››
‹‹እሺ አባዬ እኔም የተወሰነ መስራት ያለብኝ ስራ አለ…ማታ እቤት መጣለው….››
‹‹ጥሩ ››አለና….ቢሮውን ለቆ በመውጣት ካለወትሮው መኪናውን እራሱ እያሽከረከረ ወደቤቱ ጉዞ ጀመረ፡፡
አቶ ፍሰሀ ቤቱ ከመድረሱ በፊት በጣም ተጨናነቀ … ወደአንድ ግሮሰሪ ጎራ አለና የሚፈልገውን መጠጥ አዞ እየተጎነጨ ይሄንን ከአልም ጋር ያለውን ችግር በምን ዘዴ ሊፈታው እንደሚችል ማሰላሰል ጀመረ..
….////
አለም እዛው ሻሸመኔ ከተማ በተከራየችው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ሆና ጥግ ግድግዳ ታካ በተነጠፈች አንድ ሜትር ፍራሽ ላይ ጋደም ብላ በቀጣይ ማድረግ ስላለባት ነገር እያሰላሰለች ነው፡፡አሁን የመጀመሪያ በቀሏን ባሰበችው መንገድ አሳካታለች…ጁኒዬር ከተማዋን ወክሎ ለፌዴራል ህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት ለመግባት የነበረውን ሀሳብ ሰርዞ ከእጩነት እራሱን እንዲያገል ማድረግ ችላለች፡፡
በቀጣይ ደግሞ የበቀሏ ጅራፍ የሚለመጥጠው ኩማንደሩን ነው..እሱም ቢያንስ ስልጣኑን እንዲለቅና ከስራውም እንዲታገድ ማድረግ ነው የምትፈልገው…ከዚያም እንዲረዳት በቀጣይ እያዘጋጀች ያለችው በዩቲዬብ የሚለቀቀውን ሶስተኛ ቪዲዬ በእሱ ወንጀሎች ዙሪያ እንዲያጠነጥን እያደረገች ነው፡ሶሌ ኢንተርፕራይዝ ውስጥ ያለው ሚስጥራዊ የአክሲዬን ድርሻ ፤ እና ይሄንን ኢንተርፕራይዝ ለማሳደግ እድገትና ደህንት ለመጠበቅ ስልጣኑንና የመንግስትን ንብረት እንዴት አላግባብ ሲጠቀም እንደኖረ መረጃዎችን እያጠናከረችና እያደራጀች ነው፡፡
በቀጣይ ደግሞ ዳኛው ላይ ትዘምታለች..እሱም ለክብር ጡረታ ሳይበቃ ቀጥታ ከወንበሩ በውርደት ተሸቀንጥሮ ወደወህኒ እንዲወረወር ነው የምትፈልገው፡፡በመጨረሻ የአቶ ፍሰሀ ተራ ይሆናል፡፡ሁሉንም ቀስ በቀስ ክንፋቸውን በየተራ እየነቃቀለች በማድቀቅ መብረር የማይችሉ ተራ ሰው ታደርጋቸዋለች..አዎ እቅዷ እንደዛ ነው፡፡ሴቶቹን ለማጥፋት ጉልበቷን አታባክንም….ወንዶቹ ሲከስሙ እነሱም መደብዘዛቸው እና መንኮታኮታቸው አይቀርም…ከዛ በኃላ ምን አልባት ከተማውንም ሆነ ሀገሪቱን ለቃ ትሰደድ ይሆናል!!እዚህ ሀገር እንድትኖር የሚያበረታታ ምን ተዝታና ምን አይነት ተስፋ ይቀራታል?
ድንገት ብልጭ አለባትና ከተኛችበት ተነስታ ቻርጀር ላይ የነበረውን ስልኳን አነሳችና ክፍል ውስጥ ከነበረችው አንድና ብቸኛ አነስተኛ ጠረጴዛ ላይ ካሉ ከስምንት ከሚበልጡ ሲም ካርዶች መካከል አንዱን አነሳችና ስልኳ ውስጥ ከጨመረች በኃላ መደወል የምትፍገውን ቁጥር ፈለገችና ደወለች….ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ…ማን ልበል?››
‹‹እኔ ነኝ ..ጋሽ ፍሰሀ››
‹‹ይቅርታ የእኔ እመቤት …አላወቅኩሽም››
‹‹እንደው ብትረሳ ብትረሳ ይሄን ድምፅ ትረሳለህ..እርግጠኛ ነኝ ከመደወሌ በፊት እራሱ ስለእኔ ነበር እያሰብክ ያለሀው››
‹‹አለም ነሽ እንዴ?››
‹‹በትክክል ተመልሷል››
‹‹እንዴት ነሽ…?የት ነሽ?››
‹‹ተው እንጂ ጋሽ ፍሰሀ… አሁን እዚህ ቦታ ነኝ ብዬ የምገኝበትን ቦታ የምነግርህ ይመስልሀል?ባይሆን አንተ የት ነህ…?መኪና እየነዳህ ይመስላል?፡፡››
‹‹አዎ …ምንም እልተሳሳትሽም..ስለአንቺ እያሰብኩ እየነዳው ቤቴን አልፌ ከተማውንም ለቅቄ ወደ ባሌ ጎባ የሚወስደውን መንገድ ይዤ እየነዳው ነው፡፡››
‹‹በዚህ ማታ… ሁለት ሰዓት እኮ ሆኗል….››
‹‹አላስተዋልኩም ነበር..አሁን እማ እዚህ ሶሌ መድረሴ ካልቀረ ወደ ደን ማሳዬ እየገባው ነው….እዚሁ አድሬ ጥዋት እመለሳለው..ደኑ ውስጥ ማረፊያ ጎጆ አለን››
‹‹አይ ጥሩ ነው…እንደውም እኔን እንዴት በቀላሉ አጥምደህ በእጅህ ማስገባት እንደምትችል የሆነ ሀሳብ ብልጭ ሊልልህ ይችላል…እንደዛ አይነት በደን የተሸፈነ ፀጥ ያለ ቦታ ለማሰብ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቼለው››
‹‹ጥሩ እየተዝናናሽብን ነው አይደል?››
‹‹አረ ምን በወጣኝ››
‹‹እሺ..አሁን ለምን ፈልግሺኝ››
‹‹እንዲሁ ናፍቀኸኝ….››
‹‹ምን አልሽ…?ቆይ ወይኔ አውሬ ገባብኝ…አውሬ….››የመርበትበት ድምጹን ተከትሎ ከፍተኛ የመንጓጓትና የፍንዳታ ድምፅ ተሳማ…በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤት
ውስጥ እየተዟዟረች ስልኩን ብትሞክር ይጠራል አይነሳም…..ምታደርገው ግራኝ ገባት
..ቀጥታ ቦርሳዋን ይዛ ከቤት ወጣች…ታክሲ ያዘችና መሄድ ወደማታስብበት ወደቀድሞ ቤቷ አመራች …እንደደረሰች ታክሲውን አሰናበተች እና ቀጥታ ወደግቢው ውስጥ ነው የገባችው…ምን አልባት የሆነ ከለላ ስር ተደብቆ የእሷን መምጣጥ የሚጠብቅ ሰላይ ሊኖር እንደሚችል ትገምታለች..ቢሆንም ግድ አልሰጣትም፡፡ቀጥታ ግቢ ውስጥ ወደቆመችው መኪናዋ ነው ያመራችው …ውስጥ ገባችና ሞተሩን አስነስታ እየነዳች ከግቢው ይዛ ወጣች
..ቀጥታ አቶ ፍሰሀ ወደነገራት አቅጣጫ መንዳት ጀመረች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤56👍11🤩1
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
እሷ እንደጠረጠረችው…ልክ ግቢዋን ከፍታ እንደገባች በተጠንቀቅ ሲጠብቃት የነበረው ኩማንደር ያስቀመጠው ሰው ወዲያው ነበር ያያት…ስልኩን አንስቶ ኩማንደሩ ጋር ለመደወል ያባከነው ደቂቃ አልነበረም….
ኩማንደሩ ስልኩ ሲደወልለት ዳኛው ቤት ቁጭ ብሎ ማድረግ ስለሚገባቸው አንዳንድ ነገሮች እየተወያዩ ነበር….
‹‹በቃ ታክሲ ያዝና ተከታተላት..ከእይታህ እንዳትሰወር…ያለህበት ድረስ እመጣለው››የሚል ትዕዛዝ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ ለዳኛው አለም እንደተገኘች ሲነግራቸው ዳግመኛ እንደተወለዱ አይነት እፎይታ ነው የተሰማቸው…
‹‹.እንዲከተሏት አድርጌያለው…አሁን መሄድ አለብኝ….. ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡
‹‹ለምን ሪስክ ትወስዳለህ..?ወዲያው እንዲይዞት ማድረግ ነበረብህ››ሲሉ አካሄዱ ላይ ያላቸውን ተቃውሟ አሰሙ፡፡
‹‹ይዘናትስ….?ምንም የሰራችው ወንጀል የለም እኮ…ዝም ብለን አንጠልጥለን ልናስራት አንችልም››
‹‹እስከዛሬ የምታስሯቸውን ሰዎች ሁሉ ወንጀል ሰርተው ነው?››ዳኛው ስትሰሩ የኖራችሁትን ማላውቅ መሰላችሁ የሚል ቃና ባለው ንግግር ታቃወሙ፡፡
‹‹ልጅቷ እኮ የዞኑ ምክትል አቃቢ ህግ የነበረች የህግ ባለሞያ ነች….ሌላ ሰው ላይ የምናደርገውን ሁሉ እሷ ላይ በቀላሉ ማድረግ አንችልም…በዛ ላይ መከተላችን…የትነው የምትሄደው…?አጋዥ አላት ወይስ ብቻዋን ነች?››የሚለውን ለማጥናት ይረዳናል….ምን
አልባት ከሌሎች ጠላቶቻችን ጋር ህብረት ፈጥራ የምትንቀሳቀስ ከሆነም እሷን ብቻ ነጥለን መያዝ ከምንም አያተርፈንም…..››
‹‹ጥሩ አስበሀል ..እንግዲያው እኔም አብሬህ መሆን ፈልጋለው….››
‹‹አረ በዚህ ምሽት ይቅርብህ…ባይሆን ሁኔታውን በየጊዜው እየደወልኩ አሳውቅሀለው…››
‹‹አረ እኔም ከእናንት ጋር እሄዳለው››
ፎቅ ላይ ሆና ንግግሯቸውን ስታዳምጥ የነበረችው ስርጉት የአለምን መገኘት ዜና ስትሰማ በደስታ ጃኬቷን ደርባ አምርራ የምትጠላትን ሴት መያዝ በቀጥታ በአይኗ ለመከታተል ዝግጁ ሆና ወደእነሱ ስትመጣ ተመለከተ…ብዙ ቢከራከራቸውም ሁለቱም ለመቅረት ፍላጎት ስላላሳዩ ምን አገባኝ በሚል መንፈስ አብረውት እንዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡በኩማንደሩ ሹፌርነት አባትና ልጅ ከኋላ ሆነው አለምን ለመከታል ወጡ ..አለምን የሚከታተላትን ታክሲ አዲሱ መነኸሪያ ካለፈ በኃላ ነበር የደረሱበት…ከዛ የአለምን መኪና ካሳያቸው በኃላ እሱ እንዲመለስ ነገረውና አነሱ የአለምን መኪና መከታተሉን ቀጠሉ..እሷ ቀጥታ ለዛ ምሽት ፈጣን በሚባል አነዳድ የቦሌን የአስፓልት መንገድ ይዛ እየነዳችው ነው፡፡
‹‹ልጅቷ ወደየት እየሄደች ነው?፡፡››ስርጉት ግራ በመጋባት ውስጥ ሆና ጠየቀች፡፡
‹‹ይመስለኛል…ግብረ አበሮቾ ጋር የምትገናኘው ከከተማው ውጭ ነው፡፡››አባቷ የመሰላቸውን ተናገሩ፡፡
‹‹አይመስለኝም››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡
‹‹ማለት…ምን አሰብክ?››
‹‹ትዝ ይላችኃላ እናቷ ኮፈሌ ዘመዶች ነበሯት…የአባቷም ዘመዶች እዛው ናቸው..እኛ በማናውቅበት መንገድ ከዘመዶቾ ጋር መገናኘት ጀምራ ነበር ማለት ነው..እና አሁን እነሱን ለማግኘት እየሄደች ያለ ይመስለኛል..››ሲል መላምቱን አስቀመጠ፡፡
‹‹እና ኮፈሌ ድረስ ልንከተላት ነው ማለት ነው?፡፡››
‹‹እንግዲህ ቀድሞውንም አትከተሉኝ ያልኩት ለዚህ ነው…እኔ እንኳን እዚህች ኮፈሌ ድረስ ይቅርና ሱማሌም ድረስ ከነዳችው ከመከተል ወደኃላ አልልም››ሲል ፍርጥም ያለ ውሳኔውን ነገራቸው፡፡
//
አለም መኪናዋን በፍጥነት እያበረረች እንኳን ደጋግማ አቶ ፍሰሀ ስልክ ላይ ከመደወል አልታቀበችም…ግን አሁንም ስልኩ ይጠራል እንጂ አይነሳም…‹‹ይሄ ማለት ሰውዬው ከባድ አደጋ ደርሶበታል ማለት ነው..?››ስትል አሰበችና ዝግንን አላት….በእሱ ላይ በሚደርስ አደጋ እንደዚህ አይነት ሽብር ውስጥ እገባለሁ ብላ አስባ አታውቅም ነበር….እርግጥ እንዲህ በድሎኛል ብላ አንድም ቀን አካላዊ ጉዳቱን ወይም ሞቱን ተመኝታለት አታውቅም
…ቢሆንም ደህንነቱ በዚህ መጠን እንዲህ ያሳስበኛል ብላም ግምቱ አልነበራትም፡፡እና የራሷ ሁኔታ በጣም ነው ያስገረማት፡፡
‹‹ፈጣሪ ሆይ እባክህ..ህይወቱን ጠብቃት››ከልቧ ፀለየች፡፡ለቤተሰቦቹ መሳወቅ እንዳለባት ትዝ ያላት ወደባሌ የሚያመራውን የአስፓልት መንገድ ለቃ ወደቀኝ በመታጠፋ ወደ ሶሌ ደን የሚወስደውን ጥርጊያ መንገድ ከያዘች በኃላ ነበር፡፡የጂኒዬርን ቁጥር ፈለገችና ደወችለት፡፡
‹‹ሄሎ ጁኒዬር…. አለም ነኝ››
‹‹አለም ..ደህና ነሽ…?የት ነሽ….?እንዴት ነሽ?››የእሷን ድምፅ ሲሰማ የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋበት፡፡ስልኩ ሲደወልለት ቤት ከእናቱ ጋር ሳሎን ቁጭ ብሎ እየተጫወተ ነበር፡፡እሷ ለእሱ መርበትበት ቁብም ሳትሰጥ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ጂኒዬር ልብ ብለህ አድምጠኝ…ከ30 ደቂቃ በፊት ከአባትህ ጋር በስልክ እያወራሁ ነበር…መኪና እየነዳ ሳያስበው ከከተማ እንደወጣ እና ወደሶሌ ደን እየተቃረበ መሆኑንና ከአሁን በኃላ ስለመሸ ወደከተማ እንደማይመለስና ማረፊያ ጎጆ ስላለው እዛው እንደሚያድር እየነገረኝ ነበር፡፡›
‹‹አዎ እዛ አልፎ አልፎ የምናርፍበት ጎጆ አለን….››
‹‹እና..ምን መሰለህ?››
‹‹እያስደነገጥሺኝ ነው..ስለምን ነበር እያወራችሁ የነበረው?››
‹‹እሱ ምን ይሰራልሀል…ለማንኛውም ንግግራችንን ሳንጨርስ አውሬ ገባብኝ የሚል ድምፅ እና ከፈተኛ ፍንዳታ የመሰለ ነገር ሰማው..እና ስልኩ ተቋረጠ.. መልሼ ደጋግሜ ብደውል ስልኩ ይጠራል… አይነሳም..፡፡››
‹‹ወይኔ ፈጣሪ…ምን እያልሺኝ ነው?››አጠገቡ የነበረችው እናቱ ሳራ የልጇ ጭንቀት በእሷም ላይ ተጋብቶባት…ስሩ ቆማ ትንቆራጠጥ ጀመር፡፡.
‹‹ለምንኛውም አሁን ቦታው ላይ እየደረስኩ ነው.. እንዳገኘሁትና ሁኔታውን እንዳየው እደውልልሀለው…ምን አልባት አንብላንስ ያስፈልግ ይሆናል››ስልኩ ተቋረጠ
‹‹ምንድ ነው ልጄ..?ፍሰሀ ምን ሆነ?››ሳራ ጠየቀች፡፡
‹‹አባዬ አደጋ ደርሶበታል መሰለኝ..ሶሌ ያለው ደን ውስጥ ነው…መሄዴ ነው››
‹‹እኔም አብሬህ እሔዳለው››
‹‹እማዬ አንቺ እዚሁ ሆነሽ ጠብቂ….››
‹‹እሔደለው..አልኩህ እሔዳው›› አጉረጠረጠችበት፡፡ምንም አላለም…በክርክር ጊዜ ማባከን ስላልፈለገ ቀጥታ ወደሳሎኑ መውጫ መራመድ ጀመረ… እናቱም ከኃላው ተከተለችው… መኪና ውስጥ ገቡ ..ወደባሌ ጎባ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ይዘው ወደ ሶሌ ጉዞ ጀመሩ
///
አቶ ፍሰሀ አውሬውን አድናለው ብሎ መሪውን ሲጠመዝ ሙሉ በሙሉ ከመንገዱ ወጥቶ በግራ በኩል ባለው ገደል መሰል ጉድጓድ ውስጥ ነበር ጎማው ተንሸራቷ የገባው…ከዛ ፍሬኑን ለመያዝ ቢሞክርም የመኪናዋን ፍጥነትም ሆነ ባላንስ መቆጣጠር አቅቶት አንድ ዙር ተገለበጠና አንድ የብሳና ዛፍ ተደግፎ ቆመ….ለአምስት ደቂቃ ራሱን አያውቅም ነበር፡፡ከገባበት መደንዘዝ ሲወጣ ወንበሩ ስር ተወሽቆ ነው ራሱን ያገኘው…እንደምንም ታግሎ ቀበቶውን ከአንገቱ አወጣና በራፍን በእግሮቹ ገፍቶ ለመክፈት ሞከር..ቀላል ስራ እልሆነለትም፡፡እግሮቹ ምን እንደነካቸው ባያውቅም የሚያሰበውን ያህል ጥንካሬ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
እሷ እንደጠረጠረችው…ልክ ግቢዋን ከፍታ እንደገባች በተጠንቀቅ ሲጠብቃት የነበረው ኩማንደር ያስቀመጠው ሰው ወዲያው ነበር ያያት…ስልኩን አንስቶ ኩማንደሩ ጋር ለመደወል ያባከነው ደቂቃ አልነበረም….
ኩማንደሩ ስልኩ ሲደወልለት ዳኛው ቤት ቁጭ ብሎ ማድረግ ስለሚገባቸው አንዳንድ ነገሮች እየተወያዩ ነበር….
‹‹በቃ ታክሲ ያዝና ተከታተላት..ከእይታህ እንዳትሰወር…ያለህበት ድረስ እመጣለው››የሚል ትዕዛዝ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ ለዳኛው አለም እንደተገኘች ሲነግራቸው ዳግመኛ እንደተወለዱ አይነት እፎይታ ነው የተሰማቸው…
‹‹.እንዲከተሏት አድርጌያለው…አሁን መሄድ አለብኝ….. ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡
‹‹ለምን ሪስክ ትወስዳለህ..?ወዲያው እንዲይዞት ማድረግ ነበረብህ››ሲሉ አካሄዱ ላይ ያላቸውን ተቃውሟ አሰሙ፡፡
‹‹ይዘናትስ….?ምንም የሰራችው ወንጀል የለም እኮ…ዝም ብለን አንጠልጥለን ልናስራት አንችልም››
‹‹እስከዛሬ የምታስሯቸውን ሰዎች ሁሉ ወንጀል ሰርተው ነው?››ዳኛው ስትሰሩ የኖራችሁትን ማላውቅ መሰላችሁ የሚል ቃና ባለው ንግግር ታቃወሙ፡፡
‹‹ልጅቷ እኮ የዞኑ ምክትል አቃቢ ህግ የነበረች የህግ ባለሞያ ነች….ሌላ ሰው ላይ የምናደርገውን ሁሉ እሷ ላይ በቀላሉ ማድረግ አንችልም…በዛ ላይ መከተላችን…የትነው የምትሄደው…?አጋዥ አላት ወይስ ብቻዋን ነች?››የሚለውን ለማጥናት ይረዳናል….ምን
አልባት ከሌሎች ጠላቶቻችን ጋር ህብረት ፈጥራ የምትንቀሳቀስ ከሆነም እሷን ብቻ ነጥለን መያዝ ከምንም አያተርፈንም…..››
‹‹ጥሩ አስበሀል ..እንግዲያው እኔም አብሬህ መሆን ፈልጋለው….››
‹‹አረ በዚህ ምሽት ይቅርብህ…ባይሆን ሁኔታውን በየጊዜው እየደወልኩ አሳውቅሀለው…››
‹‹አረ እኔም ከእናንት ጋር እሄዳለው››
ፎቅ ላይ ሆና ንግግሯቸውን ስታዳምጥ የነበረችው ስርጉት የአለምን መገኘት ዜና ስትሰማ በደስታ ጃኬቷን ደርባ አምርራ የምትጠላትን ሴት መያዝ በቀጥታ በአይኗ ለመከታተል ዝግጁ ሆና ወደእነሱ ስትመጣ ተመለከተ…ብዙ ቢከራከራቸውም ሁለቱም ለመቅረት ፍላጎት ስላላሳዩ ምን አገባኝ በሚል መንፈስ አብረውት እንዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡በኩማንደሩ ሹፌርነት አባትና ልጅ ከኋላ ሆነው አለምን ለመከታል ወጡ ..አለምን የሚከታተላትን ታክሲ አዲሱ መነኸሪያ ካለፈ በኃላ ነበር የደረሱበት…ከዛ የአለምን መኪና ካሳያቸው በኃላ እሱ እንዲመለስ ነገረውና አነሱ የአለምን መኪና መከታተሉን ቀጠሉ..እሷ ቀጥታ ለዛ ምሽት ፈጣን በሚባል አነዳድ የቦሌን የአስፓልት መንገድ ይዛ እየነዳችው ነው፡፡
‹‹ልጅቷ ወደየት እየሄደች ነው?፡፡››ስርጉት ግራ በመጋባት ውስጥ ሆና ጠየቀች፡፡
‹‹ይመስለኛል…ግብረ አበሮቾ ጋር የምትገናኘው ከከተማው ውጭ ነው፡፡››አባቷ የመሰላቸውን ተናገሩ፡፡
‹‹አይመስለኝም››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡
‹‹ማለት…ምን አሰብክ?››
‹‹ትዝ ይላችኃላ እናቷ ኮፈሌ ዘመዶች ነበሯት…የአባቷም ዘመዶች እዛው ናቸው..እኛ በማናውቅበት መንገድ ከዘመዶቾ ጋር መገናኘት ጀምራ ነበር ማለት ነው..እና አሁን እነሱን ለማግኘት እየሄደች ያለ ይመስለኛል..››ሲል መላምቱን አስቀመጠ፡፡
‹‹እና ኮፈሌ ድረስ ልንከተላት ነው ማለት ነው?፡፡››
‹‹እንግዲህ ቀድሞውንም አትከተሉኝ ያልኩት ለዚህ ነው…እኔ እንኳን እዚህች ኮፈሌ ድረስ ይቅርና ሱማሌም ድረስ ከነዳችው ከመከተል ወደኃላ አልልም››ሲል ፍርጥም ያለ ውሳኔውን ነገራቸው፡፡
//
አለም መኪናዋን በፍጥነት እያበረረች እንኳን ደጋግማ አቶ ፍሰሀ ስልክ ላይ ከመደወል አልታቀበችም…ግን አሁንም ስልኩ ይጠራል እንጂ አይነሳም…‹‹ይሄ ማለት ሰውዬው ከባድ አደጋ ደርሶበታል ማለት ነው..?››ስትል አሰበችና ዝግንን አላት….በእሱ ላይ በሚደርስ አደጋ እንደዚህ አይነት ሽብር ውስጥ እገባለሁ ብላ አስባ አታውቅም ነበር….እርግጥ እንዲህ በድሎኛል ብላ አንድም ቀን አካላዊ ጉዳቱን ወይም ሞቱን ተመኝታለት አታውቅም
…ቢሆንም ደህንነቱ በዚህ መጠን እንዲህ ያሳስበኛል ብላም ግምቱ አልነበራትም፡፡እና የራሷ ሁኔታ በጣም ነው ያስገረማት፡፡
‹‹ፈጣሪ ሆይ እባክህ..ህይወቱን ጠብቃት››ከልቧ ፀለየች፡፡ለቤተሰቦቹ መሳወቅ እንዳለባት ትዝ ያላት ወደባሌ የሚያመራውን የአስፓልት መንገድ ለቃ ወደቀኝ በመታጠፋ ወደ ሶሌ ደን የሚወስደውን ጥርጊያ መንገድ ከያዘች በኃላ ነበር፡፡የጂኒዬርን ቁጥር ፈለገችና ደወችለት፡፡
‹‹ሄሎ ጁኒዬር…. አለም ነኝ››
‹‹አለም ..ደህና ነሽ…?የት ነሽ….?እንዴት ነሽ?››የእሷን ድምፅ ሲሰማ የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋበት፡፡ስልኩ ሲደወልለት ቤት ከእናቱ ጋር ሳሎን ቁጭ ብሎ እየተጫወተ ነበር፡፡እሷ ለእሱ መርበትበት ቁብም ሳትሰጥ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ጂኒዬር ልብ ብለህ አድምጠኝ…ከ30 ደቂቃ በፊት ከአባትህ ጋር በስልክ እያወራሁ ነበር…መኪና እየነዳ ሳያስበው ከከተማ እንደወጣ እና ወደሶሌ ደን እየተቃረበ መሆኑንና ከአሁን በኃላ ስለመሸ ወደከተማ እንደማይመለስና ማረፊያ ጎጆ ስላለው እዛው እንደሚያድር እየነገረኝ ነበር፡፡›
‹‹አዎ እዛ አልፎ አልፎ የምናርፍበት ጎጆ አለን….››
‹‹እና..ምን መሰለህ?››
‹‹እያስደነገጥሺኝ ነው..ስለምን ነበር እያወራችሁ የነበረው?››
‹‹እሱ ምን ይሰራልሀል…ለማንኛውም ንግግራችንን ሳንጨርስ አውሬ ገባብኝ የሚል ድምፅ እና ከፈተኛ ፍንዳታ የመሰለ ነገር ሰማው..እና ስልኩ ተቋረጠ.. መልሼ ደጋግሜ ብደውል ስልኩ ይጠራል… አይነሳም..፡፡››
‹‹ወይኔ ፈጣሪ…ምን እያልሺኝ ነው?››አጠገቡ የነበረችው እናቱ ሳራ የልጇ ጭንቀት በእሷም ላይ ተጋብቶባት…ስሩ ቆማ ትንቆራጠጥ ጀመር፡፡.
‹‹ለምንኛውም አሁን ቦታው ላይ እየደረስኩ ነው.. እንዳገኘሁትና ሁኔታውን እንዳየው እደውልልሀለው…ምን አልባት አንብላንስ ያስፈልግ ይሆናል››ስልኩ ተቋረጠ
‹‹ምንድ ነው ልጄ..?ፍሰሀ ምን ሆነ?››ሳራ ጠየቀች፡፡
‹‹አባዬ አደጋ ደርሶበታል መሰለኝ..ሶሌ ያለው ደን ውስጥ ነው…መሄዴ ነው››
‹‹እኔም አብሬህ እሔዳለው››
‹‹እማዬ አንቺ እዚሁ ሆነሽ ጠብቂ….››
‹‹እሔደለው..አልኩህ እሔዳው›› አጉረጠረጠችበት፡፡ምንም አላለም…በክርክር ጊዜ ማባከን ስላልፈለገ ቀጥታ ወደሳሎኑ መውጫ መራመድ ጀመረ… እናቱም ከኃላው ተከተለችው… መኪና ውስጥ ገቡ ..ወደባሌ ጎባ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ይዘው ወደ ሶሌ ጉዞ ጀመሩ
///
አቶ ፍሰሀ አውሬውን አድናለው ብሎ መሪውን ሲጠመዝ ሙሉ በሙሉ ከመንገዱ ወጥቶ በግራ በኩል ባለው ገደል መሰል ጉድጓድ ውስጥ ነበር ጎማው ተንሸራቷ የገባው…ከዛ ፍሬኑን ለመያዝ ቢሞክርም የመኪናዋን ፍጥነትም ሆነ ባላንስ መቆጣጠር አቅቶት አንድ ዙር ተገለበጠና አንድ የብሳና ዛፍ ተደግፎ ቆመ….ለአምስት ደቂቃ ራሱን አያውቅም ነበር፡፡ከገባበት መደንዘዝ ሲወጣ ወንበሩ ስር ተወሽቆ ነው ራሱን ያገኘው…እንደምንም ታግሎ ቀበቶውን ከአንገቱ አወጣና በራፍን በእግሮቹ ገፍቶ ለመክፈት ሞከር..ቀላል ስራ እልሆነለትም፡፡እግሮቹ ምን እንደነካቸው ባያውቅም የሚያሰበውን ያህል ጥንካሬ
❤37👍4
የላቸውም፡፡ከ10 ደቂቃ ትግል በኃላ በራፉ ተከፈተለት….እንደምንም እራሱን ጎትቶ ወጣና መሬት ላይ ተዘረረ….ከግንባሩ የሚንጠባጠብ ደም ተመለከተ…እጆቹ ሁለት ቦታዎች በመስታወት ስብርባሪ ተቆርጠዋል…እንደምንም ራሱን አጠናክሮ ተነስቶ ቆመ …በሰማዩ ላይ ጨረቃዋ በግማሽ ወጥታ የተወሰነ ብርሀን እየረጨች ስለሆነ ሙሉ በሙሉ ድቅድቅ ጨለማ አይደለም…ከቦታው ተንቀሳቀሰ እና ወደጫካው ውስጥ ገብቶ በግምት 20 ደቂቃ ያህል ወደሚያስኬደው አቋራጭ ጠባብ የእግር መንገድ ገባና ወደ ጎጆው መራመድ ጀመረ…፡፡
በሰላሙ ጊዜ እድሜውን ሙሉ ሲወጣ ሲወርድበት የኖረበት ጥቅጥቅ ጫካ ቢሆንም በዚህ ጊዜ ሁሉም ነገር የተለመደ እና አሰልቺ የሆነበት ይመስላል፡፡ በጫካው ውስጥ የሚገኙትን ግዙፍ የጥድ ዛፎች መቶ ዓመት ያስቆጠሩ ሊሆኑ ይችላል፣ እና እነዚህ በተለያዩ ቁጥቆጦዎች የተሸፈኑ ጥንታዊ ዛፎች ግንዶቻቸው በውስጣቸው የበሰበሱ ነበሩ። አንዳንድ ዛፎች ወድቀው ግዙፍና አስቀያሚ ሥሮቻቸውን ወደ ላይ ተፈንቅለው ይታዩ ነበር፣ እና የስሮቹ ቅርፃች በዛ ጭለማ ድንገት ላያቸው አስፈሪ ጭራቆች ስለሚመስሉ ቅፅበታዊ ፍራቻ በሰው ደም ውስጥ ይረጫሉ፡፡ አብዛኛው ደን ግን በለምለም የባህር ዛው ዛፎች ተጠቅጥቆ የተሞላ ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ በጫካው ውስጥ የሚንሾሹትን ዛፎቹ እያቋረጠ እና የረገፉ ቅጠሎች በእግሮቹ እያንኮሻኮሸ ሰሞኑን aስላጋጠሙት ችግሮች እያሰላሰለ ጉዞውን ቀጥሏል። እንደዛም ቢሆን በውስጡ የነገሰው መጨነቅ፤ውዝግቦች፣ ብስጭቶች እና ጭንቀቶች በጫካው ታላቅነትና ጥንታዊ ኃይል የተዳከሙ ይመስሉ ነበር። ከወራት በፊት እሱ ልክ እንደብረት ጠንካራ እና ጤናማ ሰው ነበር፡፡ያቺ ሴት ወደእዚህ ከተማ መጥታ ፊት ለፊቱ ከተጋገረጠችበት ቀን አንስቶ ግን እንደቀድሞ ብርቱ ሆኖ መቀጠል አልቻለም…በሙሉ አቅም ሊፋለሟት የማይችሉት ጠላት ነው የሆነችበት፡፡ ሰሞኑን ስለእሱና ስለቤተሰቦቹ በዩቲዩብ የለቀቀችው ሁለት ተከታታይ ቪዲዬ ቅስሙን ሰብረውታል…ከቀናት በኃላ በቀጣዩ ቨዲዬ በሚለቀቁ መረጃዎች ሙሉ በሙሉ ከቁጥጥር ውጭ ከመውጣታቸው በፊት ማስቆም ባለመቻሉ ነበር ተስፋ የቆረጠው።
‹‹ይሄ ምልክት ነው ››ሲል አሰበ…
‹‹ከደቂቃዎች በፊት ሞት ፊት ለፊቴ ቆሜ ነበር…ከእነ ሚስጥሬ እና ከነ ሀጥያቴ ሞቼ ነበር…አምላክ አሳይቶ የማረኝ ነገሮችን በትክክለኛው መንገድ እንዳስተካክል ነው››ሲል አሰበ….ነገሮችን በትክክለኛው መንገድ ለማስተካከል ግን የግድ በውስጡ ለአመታት የቀበረውን ሚስጥር ለመላ ቤተሰቡ በግልፅ መናገር አለበት….ያንን ማድረግ ደግሞ ምን አልባት ብዙ ነገር ሊያሳጣው ይችላል፡፡በዚህ የመጨረሻ የእድሜ ዘመኑ የሚያፈቅራት ሚስቱ ሳራ ልትፈታው ትችለች…ልጁ ጁኒዬርም መቼም ይቅር ላይለው ይችላል….‹‹ቢሆንም ይሄ ሁሉ ቅጣት ይገባኛል››ሲል ነገሩን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ወሰነ፡፡እንደዚህ በመወሰኑ የሰውነት ቅጥቅጥ ጥዝጣዜ ነፍሱን ጭምር እያነሰፈሰፈው ቢሆንም ከብዙ ወራቶች ቁዘማ በኃላ እየተረጋጋ ሲሄድ ተሰማው ..ከዚህ ውሳኔ በኃላ ነው ድንገት ከጅቡ ጋር በትንሽ ርቀት ተፋጦ ራሱን ያገኘው፡፡ አውሬው ጋር ፊት ለፊት እየተያዩ ቆሙ። በአቶ ፍሰሀ ሰውነት የፍርሀት ቅዝቃዜ ፈሰሰ። ‹‹እንዴ አምላኬ የሰጠኸኝን የንሰሀ ጊዜ መልሰህ ልትነጥቀኝ ነው እንዴ?…አረ አታድርገው››ከአመታት በኃላ እውነተኛ ፀሎት ፀለየ፡፡
‹‹ ምን ማድረግ አለብኝ?››እራሱን ጠየቀ፡፡ድንገት ጎኑን ሲዳብስ ሽጉጡ መኖሩን ተመለከተ፡፡ቶሎ ብሎ አወጣውና በእጁ አስተካክሎ ያዘው፡፡ተኩሶ ለመግደል አልፈለገም፡፡ እሱ ራሱ ከደቂቃ በፊት ነፍሱ ከሞት በተአምር ተርፏል.. ምንም እንኳን እንስሳ ቢሆንም አሁን መልሶ ሌላ ነፍስ አያጠፋም…ወሰነ‹‹እግዜር ያተረፈኝ ነፍስ እንዳጠፋ አይደለም››
‹‹ዞር ብዬ መሮጥ አለብኝ?››ሲል ራሱን ጠየቀ.. በዚህ ዕድሜው በዛ ላይ እንዲህ ሰውነቷ ደቆ በጫካ ውስጥ ህይወቱን ለማዳን ሲሮጥ በአይነ ህሊናው ሳለው፡፡
‹‹ፍሰሀ በጭራሽ አትሮጥም፡፡›› ለራሱ ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ቀስ ብሎ ወደኃላው ማፈግፈግ ጀመረ…‹‹እውነት ነው፣ ጠላት ካንተ ሲበረታ አቅምን አውቆ ማፈግፈግ ብልህነት ነው። እና አንዳንዴ በጦርነት ጊዜ ሞኞች መንገድን ሲጠረቅሙት በብልጠት ከመንገድ ዞር ማለት ያስፈልጋል።››አለ፡፡
በራሳቸው የሚንከራተቱ ጅቦች በመንገዳቸው ላይ ያጋጠማቸውን ማንኛውንም ፍጥረት ሊያጠቁ እንደሚችሉ ከልምድ ያውቃል፡፡ በተለይ እንደተበደሉ ከተሰማቸው ቂመኞች እና ቁጡዎች ናቸው..አሁን ፊት ለፊቱ የተጋረጠው በጣም ወጣት ጅብ አይመስልም። እንስሳው ፍሰሀን በትኩረት ተመለከተው፣ ፍጹም የማይንቀሳቀስ ሆኖ ቆመ፣ አንድም ጊዜ እንቅስቃሴ አላደረገም።የሚንቀሳቀሰው ጅራቱ ብቻ ነው ። ለጥቃት ወይም ለማፈግፈግ በተከፋፈለ ልብ ተጨንቆ የነበረ ይመስላል?የሰው ልጅ ለመረዳት ቀላል ነበር፣ እና ሳያውቁ ጥቃት ካልደረሰበት እና ድንገት ከኋላው ቢላዋ ካልተሰካበት በስተቀር ራስን ለመከላከል ቀላል ነበር። ድንገተኛ ጥቃት ከሁሉ የከፋው ነበር ፡፡
‹‹እስከመቼ እንደዚህ ተፋጠን እንቆያለን?››መላሽ ባይኖርም ጠየቀ፡፡
እንስሳው ማጥቃት ሊጀምር መሰለ.. እና ዓይኖቹ ተጨፍነዋል…እና ሰውነቱ ሁሉ ሲወጣጠር በፊት ከነበረው የበለጠ ግዙፍ ሆኖ ታየ .፣ ዓላማው ገዳይ ለመሆን እቅድ ያለው አይመስልም ።ምናልባት ታሞ ይሆናል? እነዚህን የሩቅ ቁጥቋጦች ላይ በብቸኝነት ለመዝመት ፈልጎ ይሆን?
አቶ ፍሰሀ‹‹ በእውነት ወደ እዚህ ስፍራ የመጣኸው ለመሞት ከሆነ ንገረኝ ?››ሲል በውስጡ እንስሳው ላይ አጉረመረመ ፡፡
‹‹ተረድቼሀለው እና እውነቱን ማወቅ ከፈለግክ እኔ በአንተ በጣም በጣም እንደምቀና ልንግርህ ፈልጋለው። እኔም መሞት እፈልጋለሁ። አዎ እዚህ ጫካ ውስጥ. በፀጥታ ብሞት በጣም ደስተኛ ነኝ …ግን የሰራሁትን ከባድ ስህተት ማስተካከል አለብኝ፣ለዛ ደግሞ ጥቂትም ቢሆን ተጨማሪ ጊዜ እፈልጋለው። ››
በቅጽበታዊ ውሳኔ ሽጉጡን ወደሰማይ ከፍ አደረገና ቃታውን ተጫነና ሁለት ጥይቶች አከታትሎ ተኮሰ…. እንስሳው በሸኮናው መሬቱን በንዴት ቧጠጠ እና ራሱን ወደጫካው ወረወረ፣ ።አቶ ፍሰሀ በራሱ ብልህነት መገረሙን ማቆም አልቻለም። በአቅራቢያው ካለው ዛፍ ጀርባ ተወረወረ…ከዚያም ሸጉጡን እንደያዘ በጥድ በተሟላ ጥሻ ውስጥ ዘልቆ ገባና ተሸሸገ።በመጨረሻ ቆም ብሎ ሲያዳምጥ መንጋው ሆነው ወደእሱ እየመጡ መሰለው፡፡ የሰማው ነገር የመንጋ የእግር ኮቴ ሳይሆን የገዛ የልቡ ምቱ መሆኑን ለመረዳት ብዙ ጊዜ ወስዶበት ነበር። ደሙ ወደ ጭንቅላቱ ሽቅብ እየሮጠ ከመሆኑም በላይ በጆሮው አስፈሪ ጩኸት ይሰማው ጀመር….በአካባቢው ምንም አይነት የድሩ እንስሳት ድምጽ የለም። አውሬው አሁንም በመቶ ሜትር ርቀት ላይ ተሸሽጎ እየተነፈሰ ነው።አቶ ፍሰሀ መንገዱን አሳብሮ ተንቀሳቀሰ..አውሬው ሊከተለው አልደፈረም….ወዲያው የባትሪ መብራት በላዩ ላይ ሲወነጨፍ ተመለከተ….‹‹ማነው…?እባካችሁ እርዱኝ›› ድምጽ አውጥቶ ተማፀነ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronosen
በሰላሙ ጊዜ እድሜውን ሙሉ ሲወጣ ሲወርድበት የኖረበት ጥቅጥቅ ጫካ ቢሆንም በዚህ ጊዜ ሁሉም ነገር የተለመደ እና አሰልቺ የሆነበት ይመስላል፡፡ በጫካው ውስጥ የሚገኙትን ግዙፍ የጥድ ዛፎች መቶ ዓመት ያስቆጠሩ ሊሆኑ ይችላል፣ እና እነዚህ በተለያዩ ቁጥቆጦዎች የተሸፈኑ ጥንታዊ ዛፎች ግንዶቻቸው በውስጣቸው የበሰበሱ ነበሩ። አንዳንድ ዛፎች ወድቀው ግዙፍና አስቀያሚ ሥሮቻቸውን ወደ ላይ ተፈንቅለው ይታዩ ነበር፣ እና የስሮቹ ቅርፃች በዛ ጭለማ ድንገት ላያቸው አስፈሪ ጭራቆች ስለሚመስሉ ቅፅበታዊ ፍራቻ በሰው ደም ውስጥ ይረጫሉ፡፡ አብዛኛው ደን ግን በለምለም የባህር ዛው ዛፎች ተጠቅጥቆ የተሞላ ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ በጫካው ውስጥ የሚንሾሹትን ዛፎቹ እያቋረጠ እና የረገፉ ቅጠሎች በእግሮቹ እያንኮሻኮሸ ሰሞኑን aስላጋጠሙት ችግሮች እያሰላሰለ ጉዞውን ቀጥሏል። እንደዛም ቢሆን በውስጡ የነገሰው መጨነቅ፤ውዝግቦች፣ ብስጭቶች እና ጭንቀቶች በጫካው ታላቅነትና ጥንታዊ ኃይል የተዳከሙ ይመስሉ ነበር። ከወራት በፊት እሱ ልክ እንደብረት ጠንካራ እና ጤናማ ሰው ነበር፡፡ያቺ ሴት ወደእዚህ ከተማ መጥታ ፊት ለፊቱ ከተጋገረጠችበት ቀን አንስቶ ግን እንደቀድሞ ብርቱ ሆኖ መቀጠል አልቻለም…በሙሉ አቅም ሊፋለሟት የማይችሉት ጠላት ነው የሆነችበት፡፡ ሰሞኑን ስለእሱና ስለቤተሰቦቹ በዩቲዩብ የለቀቀችው ሁለት ተከታታይ ቪዲዬ ቅስሙን ሰብረውታል…ከቀናት በኃላ በቀጣዩ ቨዲዬ በሚለቀቁ መረጃዎች ሙሉ በሙሉ ከቁጥጥር ውጭ ከመውጣታቸው በፊት ማስቆም ባለመቻሉ ነበር ተስፋ የቆረጠው።
‹‹ይሄ ምልክት ነው ››ሲል አሰበ…
‹‹ከደቂቃዎች በፊት ሞት ፊት ለፊቴ ቆሜ ነበር…ከእነ ሚስጥሬ እና ከነ ሀጥያቴ ሞቼ ነበር…አምላክ አሳይቶ የማረኝ ነገሮችን በትክክለኛው መንገድ እንዳስተካክል ነው››ሲል አሰበ….ነገሮችን በትክክለኛው መንገድ ለማስተካከል ግን የግድ በውስጡ ለአመታት የቀበረውን ሚስጥር ለመላ ቤተሰቡ በግልፅ መናገር አለበት….ያንን ማድረግ ደግሞ ምን አልባት ብዙ ነገር ሊያሳጣው ይችላል፡፡በዚህ የመጨረሻ የእድሜ ዘመኑ የሚያፈቅራት ሚስቱ ሳራ ልትፈታው ትችለች…ልጁ ጁኒዬርም መቼም ይቅር ላይለው ይችላል….‹‹ቢሆንም ይሄ ሁሉ ቅጣት ይገባኛል››ሲል ነገሩን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ወሰነ፡፡እንደዚህ በመወሰኑ የሰውነት ቅጥቅጥ ጥዝጣዜ ነፍሱን ጭምር እያነሰፈሰፈው ቢሆንም ከብዙ ወራቶች ቁዘማ በኃላ እየተረጋጋ ሲሄድ ተሰማው ..ከዚህ ውሳኔ በኃላ ነው ድንገት ከጅቡ ጋር በትንሽ ርቀት ተፋጦ ራሱን ያገኘው፡፡ አውሬው ጋር ፊት ለፊት እየተያዩ ቆሙ። በአቶ ፍሰሀ ሰውነት የፍርሀት ቅዝቃዜ ፈሰሰ። ‹‹እንዴ አምላኬ የሰጠኸኝን የንሰሀ ጊዜ መልሰህ ልትነጥቀኝ ነው እንዴ?…አረ አታድርገው››ከአመታት በኃላ እውነተኛ ፀሎት ፀለየ፡፡
‹‹ ምን ማድረግ አለብኝ?››እራሱን ጠየቀ፡፡ድንገት ጎኑን ሲዳብስ ሽጉጡ መኖሩን ተመለከተ፡፡ቶሎ ብሎ አወጣውና በእጁ አስተካክሎ ያዘው፡፡ተኩሶ ለመግደል አልፈለገም፡፡ እሱ ራሱ ከደቂቃ በፊት ነፍሱ ከሞት በተአምር ተርፏል.. ምንም እንኳን እንስሳ ቢሆንም አሁን መልሶ ሌላ ነፍስ አያጠፋም…ወሰነ‹‹እግዜር ያተረፈኝ ነፍስ እንዳጠፋ አይደለም››
‹‹ዞር ብዬ መሮጥ አለብኝ?››ሲል ራሱን ጠየቀ.. በዚህ ዕድሜው በዛ ላይ እንዲህ ሰውነቷ ደቆ በጫካ ውስጥ ህይወቱን ለማዳን ሲሮጥ በአይነ ህሊናው ሳለው፡፡
‹‹ፍሰሀ በጭራሽ አትሮጥም፡፡›› ለራሱ ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ቀስ ብሎ ወደኃላው ማፈግፈግ ጀመረ…‹‹እውነት ነው፣ ጠላት ካንተ ሲበረታ አቅምን አውቆ ማፈግፈግ ብልህነት ነው። እና አንዳንዴ በጦርነት ጊዜ ሞኞች መንገድን ሲጠረቅሙት በብልጠት ከመንገድ ዞር ማለት ያስፈልጋል።››አለ፡፡
በራሳቸው የሚንከራተቱ ጅቦች በመንገዳቸው ላይ ያጋጠማቸውን ማንኛውንም ፍጥረት ሊያጠቁ እንደሚችሉ ከልምድ ያውቃል፡፡ በተለይ እንደተበደሉ ከተሰማቸው ቂመኞች እና ቁጡዎች ናቸው..አሁን ፊት ለፊቱ የተጋረጠው በጣም ወጣት ጅብ አይመስልም። እንስሳው ፍሰሀን በትኩረት ተመለከተው፣ ፍጹም የማይንቀሳቀስ ሆኖ ቆመ፣ አንድም ጊዜ እንቅስቃሴ አላደረገም።የሚንቀሳቀሰው ጅራቱ ብቻ ነው ። ለጥቃት ወይም ለማፈግፈግ በተከፋፈለ ልብ ተጨንቆ የነበረ ይመስላል?የሰው ልጅ ለመረዳት ቀላል ነበር፣ እና ሳያውቁ ጥቃት ካልደረሰበት እና ድንገት ከኋላው ቢላዋ ካልተሰካበት በስተቀር ራስን ለመከላከል ቀላል ነበር። ድንገተኛ ጥቃት ከሁሉ የከፋው ነበር ፡፡
‹‹እስከመቼ እንደዚህ ተፋጠን እንቆያለን?››መላሽ ባይኖርም ጠየቀ፡፡
እንስሳው ማጥቃት ሊጀምር መሰለ.. እና ዓይኖቹ ተጨፍነዋል…እና ሰውነቱ ሁሉ ሲወጣጠር በፊት ከነበረው የበለጠ ግዙፍ ሆኖ ታየ .፣ ዓላማው ገዳይ ለመሆን እቅድ ያለው አይመስልም ።ምናልባት ታሞ ይሆናል? እነዚህን የሩቅ ቁጥቋጦች ላይ በብቸኝነት ለመዝመት ፈልጎ ይሆን?
አቶ ፍሰሀ‹‹ በእውነት ወደ እዚህ ስፍራ የመጣኸው ለመሞት ከሆነ ንገረኝ ?››ሲል በውስጡ እንስሳው ላይ አጉረመረመ ፡፡
‹‹ተረድቼሀለው እና እውነቱን ማወቅ ከፈለግክ እኔ በአንተ በጣም በጣም እንደምቀና ልንግርህ ፈልጋለው። እኔም መሞት እፈልጋለሁ። አዎ እዚህ ጫካ ውስጥ. በፀጥታ ብሞት በጣም ደስተኛ ነኝ …ግን የሰራሁትን ከባድ ስህተት ማስተካከል አለብኝ፣ለዛ ደግሞ ጥቂትም ቢሆን ተጨማሪ ጊዜ እፈልጋለው። ››
በቅጽበታዊ ውሳኔ ሽጉጡን ወደሰማይ ከፍ አደረገና ቃታውን ተጫነና ሁለት ጥይቶች አከታትሎ ተኮሰ…. እንስሳው በሸኮናው መሬቱን በንዴት ቧጠጠ እና ራሱን ወደጫካው ወረወረ፣ ።አቶ ፍሰሀ በራሱ ብልህነት መገረሙን ማቆም አልቻለም። በአቅራቢያው ካለው ዛፍ ጀርባ ተወረወረ…ከዚያም ሸጉጡን እንደያዘ በጥድ በተሟላ ጥሻ ውስጥ ዘልቆ ገባና ተሸሸገ።በመጨረሻ ቆም ብሎ ሲያዳምጥ መንጋው ሆነው ወደእሱ እየመጡ መሰለው፡፡ የሰማው ነገር የመንጋ የእግር ኮቴ ሳይሆን የገዛ የልቡ ምቱ መሆኑን ለመረዳት ብዙ ጊዜ ወስዶበት ነበር። ደሙ ወደ ጭንቅላቱ ሽቅብ እየሮጠ ከመሆኑም በላይ በጆሮው አስፈሪ ጩኸት ይሰማው ጀመር….በአካባቢው ምንም አይነት የድሩ እንስሳት ድምጽ የለም። አውሬው አሁንም በመቶ ሜትር ርቀት ላይ ተሸሽጎ እየተነፈሰ ነው።አቶ ፍሰሀ መንገዱን አሳብሮ ተንቀሳቀሰ..አውሬው ሊከተለው አልደፈረም….ወዲያው የባትሪ መብራት በላዩ ላይ ሲወነጨፍ ተመለከተ….‹‹ማነው…?እባካችሁ እርዱኝ›› ድምጽ አውጥቶ ተማፀነ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronosen
👍50❤27🤔4
#እኛኮ_ተለያይተናል
አብረን ሆነን በቃሽ በቃህ ተባብለናል አብረን ሆነን እንዴት ቆምን በዚህ ርቀት አለን ስንል ምን ዳረገን ለዚህ ውድቀት?
ስር ስሩን በልቶን ጥላቻ እየሳቅን የምንታይ ለተመልካች አይን ብቻ ፍቅራችንን ዳባ አልብሰን አቅም እስኪያጥረን ለአቤት የተፋታን ግን በአንድ ቤት
ለህመማችን መዳኛ መድሀኔት መፈለግ ትተን ምን ይሉን የሚያቃትተን እኛኮ አልኖርንም ለኛ እኛኮ አልቆምንም ለኛ ቤታችን ሲፈርስ እንዳናይ ጀርባ ለጀርባ ስንተኛ
ምን ሆነን ነው?
ምን ነክቶን ነው?
"ምን እናድርግ" ማለት ትተን ይኸው አለን በአንድ ላይ በአንድ ቤት ተለያይተን
ይቅርታ...
እኛኮ ተለያይተናል አብረን ሆነን በቃሽ በቃህ ተባብለናል አብረን ሆነን እንዴት ቆምን በዚህ ርቀት አለን ስንል ምን ዳረገን ለዚህ ውድቀት?
ስር ስሩን በልቶን ጥላቻ እየሳቅን የምንታይ ለተመልካች አይን ብቻ ፍቅራችንን ዳባ አልብሰን አቅም እስኪያጥረን ለአቤት የተፋታን ግን በአንድ ቤት
ለህመማችን መዳኛ መድሀኔት መፈለግ ትተን ምን ይሉን የሚያቃትተን እኛኮ አልኖርንም ለኛ እኛኮ አልቆምንም ለኛ ቤታችን ሲፈርስ እንዳናይ ጀርባ ለጀርባ ስንተኛ
ምን ሆነን ነው?
ምን ነክቶን ነው?
"ምን እናድርግ" ማለት ትተን ይኸው አለን በአንድ ላይ በአንድ ቤት ተለያይተን
ይቅርታ...
"ይቅርታ" ምትለውን ቃል ማን ደፍሮ ከአፉ ይትፋት ማን አምኖ ቀድሞ ይፃፋት?
እኔ ከአንቺ ይምጣ እያልኩኝ አንቺ ደሞ ስትይ ከኔ ኩራት ይሁን ወይም እልህ አልያ ደግሞ አጉል ወኔ በአንድ የቃል እርቀት ከሁለት ጥግ እንደቆምን ይኸው ዘመናት አለፈ አልሸነፍም ስላልን የኛ ፍቅር ተሸነፈ ለአለም ይበቃል ያልነው ከጥላቻ እንኳን ኮሰሰ እንደ ነውር እንደ ሀጥያት በየሰዉ አፍ ታመሰ
አብረን ሆነን በቃሽ በቃህ ተባብለናል አብረን ሆነን እንዴት ቆምን በዚህ ርቀት አለን ስንል ምን ዳረገን ለዚህ ውድቀት?
ስር ስሩን በልቶን ጥላቻ እየሳቅን የምንታይ ለተመልካች አይን ብቻ ፍቅራችንን ዳባ አልብሰን አቅም እስኪያጥረን ለአቤት የተፋታን ግን በአንድ ቤት
ለህመማችን መዳኛ መድሀኔት መፈለግ ትተን ምን ይሉን የሚያቃትተን እኛኮ አልኖርንም ለኛ እኛኮ አልቆምንም ለኛ ቤታችን ሲፈርስ እንዳናይ ጀርባ ለጀርባ ስንተኛ
ምን ሆነን ነው?
ምን ነክቶን ነው?
"ምን እናድርግ" ማለት ትተን ይኸው አለን በአንድ ላይ በአንድ ቤት ተለያይተን
ይቅርታ...
እኛኮ ተለያይተናል አብረን ሆነን በቃሽ በቃህ ተባብለናል አብረን ሆነን እንዴት ቆምን በዚህ ርቀት አለን ስንል ምን ዳረገን ለዚህ ውድቀት?
ስር ስሩን በልቶን ጥላቻ እየሳቅን የምንታይ ለተመልካች አይን ብቻ ፍቅራችንን ዳባ አልብሰን አቅም እስኪያጥረን ለአቤት የተፋታን ግን በአንድ ቤት
ለህመማችን መዳኛ መድሀኔት መፈለግ ትተን ምን ይሉን የሚያቃትተን እኛኮ አልኖርንም ለኛ እኛኮ አልቆምንም ለኛ ቤታችን ሲፈርስ እንዳናይ ጀርባ ለጀርባ ስንተኛ
ምን ሆነን ነው?
ምን ነክቶን ነው?
"ምን እናድርግ" ማለት ትተን ይኸው አለን በአንድ ላይ በአንድ ቤት ተለያይተን
ይቅርታ...
"ይቅርታ" ምትለውን ቃል ማን ደፍሮ ከአፉ ይትፋት ማን አምኖ ቀድሞ ይፃፋት?
እኔ ከአንቺ ይምጣ እያልኩኝ አንቺ ደሞ ስትይ ከኔ ኩራት ይሁን ወይም እልህ አልያ ደግሞ አጉል ወኔ በአንድ የቃል እርቀት ከሁለት ጥግ እንደቆምን ይኸው ዘመናት አለፈ አልሸነፍም ስላልን የኛ ፍቅር ተሸነፈ ለአለም ይበቃል ያልነው ከጥላቻ እንኳን ኮሰሰ እንደ ነውር እንደ ሀጥያት በየሰዉ አፍ ታመሰ
❤14👍3🔥1
ኩራታችን ጎን ሞልቶ ላያሳድር አመቻችቶ መውደዳችን ወድቆ ሲቀር ኋላ ኋላ ሊፀፅተን ከአፈር አፍሶ ለማንሳት ጎምበስ የሚል ደረት አተን ይቅር ቃሉ ያሻፈረን አለን ይኸው በአንድ ላይ በአንድ ቤት ተለያይተን ክብርን መውደድ ላይ ደንቅረን
እና ባክሽ እንታረቅ እንደበፊታችን ነይ እንተሳሰርፍቅራችንን ተይው ስንት የለፋንበት ፀባችን አይክሰር
ያ ሁሉ መኳረፍ ያ ሁሉ መጣላት አይሁን ለጠላችው ወይ ደሞ ለጠላት ያፈሰስሺው እምባ ያለቀስሽው በኔ ተይ አይቅር በከንቱ እንታረቅ ባክሽ ናፍቀሺኛል እኔ
እንደ ልጅነቱ የማርያም ጣትሽን ዘርጊልኝ አንድ አፍታ ስንቱን ላሳለፈው ለምስኪን ፍቅራችን ይበዛል ይቅርታ?
አይበዛም... አይበዛም... ነይ ባክሽ ታረቂኝ ከመኖር ላስታርቅሽ ከህይወት አስታርቂኝ
እንዲያ ያኳረፈን... እንዲያ ያዛለፈን በረባው ባረባው እሾህ ቢመስለንም ጥለን የማንሄደው የኛ ነው አበባው
እና ለምን ብለን? ፍቅራችንን ወዲያ ጥለን በሁለት መንገድ እንሄዳለን እኔና አንቺኮ ቢከፋም ቢለማም ትልቅ ታሪክ አለን
ባክሽ እንታረቅ
🔘ዘዉድ አክሊል🔘
እና ባክሽ እንታረቅ እንደበፊታችን ነይ እንተሳሰርፍቅራችንን ተይው ስንት የለፋንበት ፀባችን አይክሰር
ያ ሁሉ መኳረፍ ያ ሁሉ መጣላት አይሁን ለጠላችው ወይ ደሞ ለጠላት ያፈሰስሺው እምባ ያለቀስሽው በኔ ተይ አይቅር በከንቱ እንታረቅ ባክሽ ናፍቀሺኛል እኔ
እንደ ልጅነቱ የማርያም ጣትሽን ዘርጊልኝ አንድ አፍታ ስንቱን ላሳለፈው ለምስኪን ፍቅራችን ይበዛል ይቅርታ?
አይበዛም... አይበዛም... ነይ ባክሽ ታረቂኝ ከመኖር ላስታርቅሽ ከህይወት አስታርቂኝ
እንዲያ ያኳረፈን... እንዲያ ያዛለፈን በረባው ባረባው እሾህ ቢመስለንም ጥለን የማንሄደው የኛ ነው አበባው
እና ለምን ብለን? ፍቅራችንን ወዲያ ጥለን በሁለት መንገድ እንሄዳለን እኔና አንቺኮ ቢከፋም ቢለማም ትልቅ ታሪክ አለን
ባክሽ እንታረቅ
🔘ዘዉድ አክሊል🔘
❤8👍4🔥1
#ባለመኖር_ስጋት
አብሬሽ እስካለሁ ''ፈልገሽ አትጪኝ''
ከሚል ምኞት በቀር ሌላ ሐቅ አላውቅም፣ በተፈለጉበት አለመኖር እንጂ
የሚፈልጉትን ማጣት ብዙ አይጨንቅም፡፡
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አብሬሽ እስካለሁ ''ፈልገሽ አትጪኝ''
ከሚል ምኞት በቀር ሌላ ሐቅ አላውቅም፣ በተፈለጉበት አለመኖር እንጂ
የሚፈልጉትን ማጣት ብዙ አይጨንቅም፡፡
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
👍6❤2
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
‹‹ጋሽ ፍሰሀ..አንተ ነህ…?››
‹‹አዎ አለም…እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?››አውሬው ካስደነገጠው በላይ የእሷ በዚህ ሰዓት እዚህ አካባቢ መገኘት አስደነገጠው፡፡
‹‹እንዴ ስልክ እያወራን ነበር እኮ የተቆረጠው….መኪናህ እንደተገለበጠች እርግጠኛ ስለነበርኩ ወዲያውኑ ወደእዚህ የመጣሁት…መኪናህን ቀድሜ ባገኛትም ውስጡ የለህም..ግን የሚንጠባጠበውን ደም እየተከተልኩ ደረስኩብህ››
‹‹ስሩ ደርሳ ደገፈችው››
‹‹አብሮሽ ማን አለ?››
‹‹አረ ማንም የለ….መንገድ ላይ ሆኜ ለጁኒዬር ደውዬለታለው..ይሄኔ እየመጡ ይሆናል፡››
‹‹ይገርማል..የሆነ ነገር ቢያጋጥምሽስ?››
‹‹ሀሳቤ ሁሉ ያንተን ደህንነት ማረጋገጥ ላይ ስለነበር እሱን አላሳብኩትም ነበር…እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ ግን አሁን በፍራቻ እየተንቀጠቀጥኩ ነው፡፡››
‹‹በጣም ነው ያስገረምሺኝ..አይዞሽ አሁን አምስት ደቂቃ ነው ደርሰናል….እንደውም እዛ መብራት ጭልጭል የሚልበት ቦታ ይታይሻል …?እዛ ነው ጎጆው…በአቅራቢያው የእኔ ሰራተኞች ቤትም አለ…››
‹‹ በአንድ እጇ ደግፋው በሌላ እጇ ደግሞ የስልኳን ባትሪ ከፊት ለፊት እያበራች ወደፊት በዝግታ መራመዳቸውን ቀጠሉ፡፡
አቶ ፍሰሀ ከአውሬው ጋር የነበረው መፋጠጥ አሁንም ከምናብ ሊደበዝዝ አልቻለም… ልቡ ለምን እንዲህ ከመጠን በላይ መታ? ጉዳዩ ምን ነበር? የዱር አውሬው በጣም አስፈርቶት ነው? አይደለም፡፡ እሱ ስለእነሱ አላሰበም። በህይወቱ የበለጠ አስፈሪ ነገሮችን አሳልፎ ያውቃል። ወዲያው ከኃላቸው እየተንሾካሾኩ የሚመጣ የእግር ኮቴ ሰሙ…መንገዱን ለቀቁና ጢሻውን ተከልለው ቆሙ..ሲጠጎቸው ማንነታቸውን በድምፅ ለዩ…‹‹ገመዶ››
ባትሪውን ሲያበራባት ፈጽሞ እዚህ አገኘዋለሁ ብሎ ያላሰበውን አቶ ፍሰሀን በአለም ተደግፋፎ ልክ እንደተወዳጅ ልጁ ስሩ ተሸጉጣ ሲያይ አይኑን ማመን አልቻለም፡፡
ሁሉም ተንደርድረው ከበቧቸው‹‹ጋሼ ምን እየተካሄደ ነው?››
‹‹አይዞችሁ አትደንግጡ… ተርፌለው››
‹‹ተርፌለው ማለት?››ኩማንደሩ በመገረም ጠየቀ፡፡
‹‹የመኪና አደጋ እንደደረሰብኝ ሰምታችሁ አይደለም እንዴ የመጣችሁት?››
‹‹አረ በፈጣሪ..ተርፍክ ታዲያ…?እኛ አልሰማንም..እሷን ከከተማ ስትወጣ አይተን ተከትለናት ነው የመጣናው…ከጠላቶቻችን ጋር ልትገናኝ መስሎን ነበር››
‹‹አይ እሷ እኔን ለማትረፍ ነው የመጣችው››
‹‹እንዴት ከእኛ ቀድማ ልትሰማ ቻለች?..ነው ወይስ በአደጋው ላይ የእሷ እጅ አለበት?››
‹‹እሱን ጎጆው ጋር ደርሰን ትንሽ ካረፈ በኃላ ብትጠይቀው አይሻልም?››አለችው አለም በንዴት፡፡
‹‹ለምን ወደጎጆ እንሄዳለን? መኪናችንን እኮ በቅርብ ርቀት ላይ ነው ያቆምናት..እዚሁ ጠብቁኝና ይዣት ልምጣ..ቀጥታ ወደከተማ ሄደህ ህክምና ማግኘት አለብህ››
‹‹አይ ደህና ነኝ..አሁን ማረፍ ነው የምፈለገው..ወደጎጆ ውሰዱኝ››
‹‹ተው እንጂ ፍሰሀ ..ሀኪም ሊያይህ ይገባል››ዳኛው ጣልቃ ገብተው ለኩማንደሩ ድጋፋቸውን ሰጡ፡፡
‹‹የበለጠ እያደከማችሁኝ መሆኑን ልብ አላላችሁም እንዴ..?ወደጎጆ መሄድ ነው የምፈልገው›› በማለት የማይቀየር አቋማቸውን አሰሙ፡፡
‹‹ይቅርታ ጋሼ..አንተ ካልክ እሺ ወደጎጆ እንወስድሀለን….እነ ጁኒዬርም አሁን ደውለውልኝ ነበር …መገንጠያው ጋር ደርሰዋል….ከደቂቃዎች በኃላ ይደርሳሉ..››አለና ሄዶ በሌላ ጎኑ አቶ ፍሰሀን ደገፈ….ከ5 ደቂቃ በኃላ ጎጆዋ ደረሱ፡፡ፋኖስ አበሩ፣ መኝታው ተስተካክሎ እንዲተኛ ተደረገና በቅርብ ርቀት ያሉ ሌላ የሳር ቤት ውስጥ ወደሚኖሩት የእነሱ ሰራተኞች ተቀስቅሰው መጡ..እሳት እንዲቃጣጠል ተደረገ…ጁኒዬርና ሳራ የመጀመሪያ ለእረዳታ መስጫ የሚያለግሉ ቁሳቁሶች ይዘው እያለከለኩ ደረሱ…ለተወሰነ ጊዜ ለቅሶና ግርግር በጠባቧ ጎጆ ነገሰ..ከዛ ቀስ በቀስ ወደመረጋጋት ቢመጣም በሰው ብዛት በታፈነችው ጎጆ ውጥረትና ጭንቀት ነግሶ ነበር፡፡
‹‹ቆይ እኔ ያልገባኝ…ምንድነው የሚያስጠብቀን..?ለምንድነው ወደከተማ ይዘነው ሔደን ሀኪማ የማያየው?››ሳራ ነች ግራ በመጋባት ተመሳሳይ አይነት ጥያቄ ለሶስተኛ ጊዜ ያነሳችው፡፡
‹‹ጋሼ አልፈልግም ስላለ እኮ ነው…ጋሼ አሁን ትንሽ አርፈሀል፣ብንሄድ ምን ይመስልሀል?››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡
‹‹አይ ዛሬ ማንም ከዚህ አይሄድም…አሁን ሰዎቹን ሸኞቸውና የምንነጋገረው ነገር አለ››ሲል ሁሉም በቀጣይ ምን ሊፈጠር ነው በሚል እርስ በርስ ተያዩ፡፡
ጁኒዬር ከጎረቤት ጎጆ የመጡትን ባልና ሚስቶች ከነልጆቻቸው አመስግኖ ወደቤታቸው እንዲሄዱ ካደረገ በኃላ የጎጆዋ ቤት ተዘጋ፡፡አሁን ስድስት ሰዎች ፊት ለፊት ተፋጠጡ …ሁለቱ ሴቶች እና አዛውንቱ ዳኛ አቶ ፍሰሀ ጎን የተቀመጠችውን አለምን በከፍተኛ ጥላቻን መጠየፍ ነበር የሚመለከቷት፡፡
አቶ ፍሰሀ ከትራሱ ቀና አደረገና አስተካክሎ በመደገፍ መናገር ጀመረ‹‹ዛሬ እየሆነ ያለው ሁሉ ነገር ተአምር ነው…እኔ እቅዴ እንደማንኛውም ቀን ስራ ውዬ ወደቤቴ መግባት ነበር….ነገር ግን የሰሞኑን ውጣ ውረድ እያሰላሰልኩ ሳላስበው ከከተማ ወጣሁና እራሴን እዚህ ሶሌ ደን አካባቢ አገኘሁት..እንዴት እዚህ ልደርስ ቻልኩ? ብዬ እየተገረምኩ ሳለ ያልጠበቅኳት አለም ደወለችልኝ..ከእሷ ጋር እያወራው ሳለ ድንገት ሳላስበው አውሬ ገባብኝና እሱን አድናለው ስል መኪናዬ መንገድ ስታ ተገለበጥኩ…እንደአደጋው መሞት ነበረብኝ..ግን ከተወሰነ ጭረት በስተቀር ምንም አልሆንኩም…እግዜር አሳይቶ ከሞት ደጃፍ መለሰኝ..ከመኪናው ወጥቼ በጫካው እያሳበርኩ ወደእዚህ እየመጣው ሳለ ከጅብ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጥኩ…እሱንም ወደሰማይ ተኩሼ አስበረገግኩትና ሁለተኛውን ፈተና አለፍኩ..ከዛ ወዲያው አለምን ከፊት ለፊቴ አገኘኃት..ወዲያው እነ ገመዶና መጡ…ጎጆው እንደደረስን ደግሞ ልጄና ባለቤቴ መጡ …እኔ ለማናችሁም አደጋ ደረሰብኝ ብዬ አልደወልኩም..በአደጋው ጊዜ ስልኬ ወደየት እንደጠፋም አላውቅም..ግን ሁላችሁም እዚህ ተገኝታችኃላ..ሁላችንን እዚህ ያለነው ለምክንያት ነው፡፡ከአለም ጋር የጀመርነው ድብብቆሽ እዚህ ጋ ማብቃት መቻል አለበት፡፡
‹‹አዎ ማብቃት አለበት …ይህቼ ሴት ከዚህ በፊት ንብረቴ እንዲቃጠል አደረገች… ዛሬ ባለቤቴን ገድላብኝ ነበር….››ሳራ ተንዘረዘረች…ዳኛውና ስርጉት አይናቸውን በማጉረጥረጥ እና በመገላመጥ ለሳራ ያላቸውን እገዛ አሳዩ ፡፡
‹‹ሳራ ተይ ..ዛሬ የምንበሳጭበትና ራሳችንን ሀጥያት ለመሸፈን ሌላ ስው በሀሰት የምንወቅስበት ቀን አይደለም..እኔ አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከሁለት ሞት ነው የዳንኩት…ይሄ ያለምክንያት አይደለም..ይህቺን ልጅ ሁላችንም በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ በድለናታል…ሁላችንም ለእሷ መናዘዝ መቻል አለብን..እውነቱን ልንነግራት ይገባል..ከዛ አመዛዝና ከፈለገች ትበቀለን… ከፈለገች ደግሞ ወደፍትህ አደባባይ ወስዳ ታሰቅለን፡፡
የአቶ ፍሰሀን ንግግር የሰሙት ዳኛው ጫንቃቸውን አላባቸው፡፡ይሄ ሰውዬ በተገበጠበት ወቅት ጭንቅላቱን ተመቶ ማሰቢያው ላልቶ ይሆን እንዴ?››ሲል አሰበና አይኑን ገመዶና ጁኒዬር ላይ አንከራተተ…የሆነ ነገር ብለው የጀመረውን ቅዠት የመሰል ድርጊት እንዲያስቆሙት ነው ፍላጎቱ.
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
‹‹ጋሽ ፍሰሀ..አንተ ነህ…?››
‹‹አዎ አለም…እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?››አውሬው ካስደነገጠው በላይ የእሷ በዚህ ሰዓት እዚህ አካባቢ መገኘት አስደነገጠው፡፡
‹‹እንዴ ስልክ እያወራን ነበር እኮ የተቆረጠው….መኪናህ እንደተገለበጠች እርግጠኛ ስለነበርኩ ወዲያውኑ ወደእዚህ የመጣሁት…መኪናህን ቀድሜ ባገኛትም ውስጡ የለህም..ግን የሚንጠባጠበውን ደም እየተከተልኩ ደረስኩብህ››
‹‹ስሩ ደርሳ ደገፈችው››
‹‹አብሮሽ ማን አለ?››
‹‹አረ ማንም የለ….መንገድ ላይ ሆኜ ለጁኒዬር ደውዬለታለው..ይሄኔ እየመጡ ይሆናል፡››
‹‹ይገርማል..የሆነ ነገር ቢያጋጥምሽስ?››
‹‹ሀሳቤ ሁሉ ያንተን ደህንነት ማረጋገጥ ላይ ስለነበር እሱን አላሳብኩትም ነበር…እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ ግን አሁን በፍራቻ እየተንቀጠቀጥኩ ነው፡፡››
‹‹በጣም ነው ያስገረምሺኝ..አይዞሽ አሁን አምስት ደቂቃ ነው ደርሰናል….እንደውም እዛ መብራት ጭልጭል የሚልበት ቦታ ይታይሻል …?እዛ ነው ጎጆው…በአቅራቢያው የእኔ ሰራተኞች ቤትም አለ…››
‹‹ በአንድ እጇ ደግፋው በሌላ እጇ ደግሞ የስልኳን ባትሪ ከፊት ለፊት እያበራች ወደፊት በዝግታ መራመዳቸውን ቀጠሉ፡፡
አቶ ፍሰሀ ከአውሬው ጋር የነበረው መፋጠጥ አሁንም ከምናብ ሊደበዝዝ አልቻለም… ልቡ ለምን እንዲህ ከመጠን በላይ መታ? ጉዳዩ ምን ነበር? የዱር አውሬው በጣም አስፈርቶት ነው? አይደለም፡፡ እሱ ስለእነሱ አላሰበም። በህይወቱ የበለጠ አስፈሪ ነገሮችን አሳልፎ ያውቃል። ወዲያው ከኃላቸው እየተንሾካሾኩ የሚመጣ የእግር ኮቴ ሰሙ…መንገዱን ለቀቁና ጢሻውን ተከልለው ቆሙ..ሲጠጎቸው ማንነታቸውን በድምፅ ለዩ…‹‹ገመዶ››
ባትሪውን ሲያበራባት ፈጽሞ እዚህ አገኘዋለሁ ብሎ ያላሰበውን አቶ ፍሰሀን በአለም ተደግፋፎ ልክ እንደተወዳጅ ልጁ ስሩ ተሸጉጣ ሲያይ አይኑን ማመን አልቻለም፡፡
ሁሉም ተንደርድረው ከበቧቸው‹‹ጋሼ ምን እየተካሄደ ነው?››
‹‹አይዞችሁ አትደንግጡ… ተርፌለው››
‹‹ተርፌለው ማለት?››ኩማንደሩ በመገረም ጠየቀ፡፡
‹‹የመኪና አደጋ እንደደረሰብኝ ሰምታችሁ አይደለም እንዴ የመጣችሁት?››
‹‹አረ በፈጣሪ..ተርፍክ ታዲያ…?እኛ አልሰማንም..እሷን ከከተማ ስትወጣ አይተን ተከትለናት ነው የመጣናው…ከጠላቶቻችን ጋር ልትገናኝ መስሎን ነበር››
‹‹አይ እሷ እኔን ለማትረፍ ነው የመጣችው››
‹‹እንዴት ከእኛ ቀድማ ልትሰማ ቻለች?..ነው ወይስ በአደጋው ላይ የእሷ እጅ አለበት?››
‹‹እሱን ጎጆው ጋር ደርሰን ትንሽ ካረፈ በኃላ ብትጠይቀው አይሻልም?››አለችው አለም በንዴት፡፡
‹‹ለምን ወደጎጆ እንሄዳለን? መኪናችንን እኮ በቅርብ ርቀት ላይ ነው ያቆምናት..እዚሁ ጠብቁኝና ይዣት ልምጣ..ቀጥታ ወደከተማ ሄደህ ህክምና ማግኘት አለብህ››
‹‹አይ ደህና ነኝ..አሁን ማረፍ ነው የምፈለገው..ወደጎጆ ውሰዱኝ››
‹‹ተው እንጂ ፍሰሀ ..ሀኪም ሊያይህ ይገባል››ዳኛው ጣልቃ ገብተው ለኩማንደሩ ድጋፋቸውን ሰጡ፡፡
‹‹የበለጠ እያደከማችሁኝ መሆኑን ልብ አላላችሁም እንዴ..?ወደጎጆ መሄድ ነው የምፈልገው›› በማለት የማይቀየር አቋማቸውን አሰሙ፡፡
‹‹ይቅርታ ጋሼ..አንተ ካልክ እሺ ወደጎጆ እንወስድሀለን….እነ ጁኒዬርም አሁን ደውለውልኝ ነበር …መገንጠያው ጋር ደርሰዋል….ከደቂቃዎች በኃላ ይደርሳሉ..››አለና ሄዶ በሌላ ጎኑ አቶ ፍሰሀን ደገፈ….ከ5 ደቂቃ በኃላ ጎጆዋ ደረሱ፡፡ፋኖስ አበሩ፣ መኝታው ተስተካክሎ እንዲተኛ ተደረገና በቅርብ ርቀት ያሉ ሌላ የሳር ቤት ውስጥ ወደሚኖሩት የእነሱ ሰራተኞች ተቀስቅሰው መጡ..እሳት እንዲቃጣጠል ተደረገ…ጁኒዬርና ሳራ የመጀመሪያ ለእረዳታ መስጫ የሚያለግሉ ቁሳቁሶች ይዘው እያለከለኩ ደረሱ…ለተወሰነ ጊዜ ለቅሶና ግርግር በጠባቧ ጎጆ ነገሰ..ከዛ ቀስ በቀስ ወደመረጋጋት ቢመጣም በሰው ብዛት በታፈነችው ጎጆ ውጥረትና ጭንቀት ነግሶ ነበር፡፡
‹‹ቆይ እኔ ያልገባኝ…ምንድነው የሚያስጠብቀን..?ለምንድነው ወደከተማ ይዘነው ሔደን ሀኪማ የማያየው?››ሳራ ነች ግራ በመጋባት ተመሳሳይ አይነት ጥያቄ ለሶስተኛ ጊዜ ያነሳችው፡፡
‹‹ጋሼ አልፈልግም ስላለ እኮ ነው…ጋሼ አሁን ትንሽ አርፈሀል፣ብንሄድ ምን ይመስልሀል?››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡
‹‹አይ ዛሬ ማንም ከዚህ አይሄድም…አሁን ሰዎቹን ሸኞቸውና የምንነጋገረው ነገር አለ››ሲል ሁሉም በቀጣይ ምን ሊፈጠር ነው በሚል እርስ በርስ ተያዩ፡፡
ጁኒዬር ከጎረቤት ጎጆ የመጡትን ባልና ሚስቶች ከነልጆቻቸው አመስግኖ ወደቤታቸው እንዲሄዱ ካደረገ በኃላ የጎጆዋ ቤት ተዘጋ፡፡አሁን ስድስት ሰዎች ፊት ለፊት ተፋጠጡ …ሁለቱ ሴቶች እና አዛውንቱ ዳኛ አቶ ፍሰሀ ጎን የተቀመጠችውን አለምን በከፍተኛ ጥላቻን መጠየፍ ነበር የሚመለከቷት፡፡
አቶ ፍሰሀ ከትራሱ ቀና አደረገና አስተካክሎ በመደገፍ መናገር ጀመረ‹‹ዛሬ እየሆነ ያለው ሁሉ ነገር ተአምር ነው…እኔ እቅዴ እንደማንኛውም ቀን ስራ ውዬ ወደቤቴ መግባት ነበር….ነገር ግን የሰሞኑን ውጣ ውረድ እያሰላሰልኩ ሳላስበው ከከተማ ወጣሁና እራሴን እዚህ ሶሌ ደን አካባቢ አገኘሁት..እንዴት እዚህ ልደርስ ቻልኩ? ብዬ እየተገረምኩ ሳለ ያልጠበቅኳት አለም ደወለችልኝ..ከእሷ ጋር እያወራው ሳለ ድንገት ሳላስበው አውሬ ገባብኝና እሱን አድናለው ስል መኪናዬ መንገድ ስታ ተገለበጥኩ…እንደአደጋው መሞት ነበረብኝ..ግን ከተወሰነ ጭረት በስተቀር ምንም አልሆንኩም…እግዜር አሳይቶ ከሞት ደጃፍ መለሰኝ..ከመኪናው ወጥቼ በጫካው እያሳበርኩ ወደእዚህ እየመጣው ሳለ ከጅብ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጥኩ…እሱንም ወደሰማይ ተኩሼ አስበረገግኩትና ሁለተኛውን ፈተና አለፍኩ..ከዛ ወዲያው አለምን ከፊት ለፊቴ አገኘኃት..ወዲያው እነ ገመዶና መጡ…ጎጆው እንደደረስን ደግሞ ልጄና ባለቤቴ መጡ …እኔ ለማናችሁም አደጋ ደረሰብኝ ብዬ አልደወልኩም..በአደጋው ጊዜ ስልኬ ወደየት እንደጠፋም አላውቅም..ግን ሁላችሁም እዚህ ተገኝታችኃላ..ሁላችንን እዚህ ያለነው ለምክንያት ነው፡፡ከአለም ጋር የጀመርነው ድብብቆሽ እዚህ ጋ ማብቃት መቻል አለበት፡፡
‹‹አዎ ማብቃት አለበት …ይህቼ ሴት ከዚህ በፊት ንብረቴ እንዲቃጠል አደረገች… ዛሬ ባለቤቴን ገድላብኝ ነበር….››ሳራ ተንዘረዘረች…ዳኛውና ስርጉት አይናቸውን በማጉረጥረጥ እና በመገላመጥ ለሳራ ያላቸውን እገዛ አሳዩ ፡፡
‹‹ሳራ ተይ ..ዛሬ የምንበሳጭበትና ራሳችንን ሀጥያት ለመሸፈን ሌላ ስው በሀሰት የምንወቅስበት ቀን አይደለም..እኔ አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከሁለት ሞት ነው የዳንኩት…ይሄ ያለምክንያት አይደለም..ይህቺን ልጅ ሁላችንም በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ በድለናታል…ሁላችንም ለእሷ መናዘዝ መቻል አለብን..እውነቱን ልንነግራት ይገባል..ከዛ አመዛዝና ከፈለገች ትበቀለን… ከፈለገች ደግሞ ወደፍትህ አደባባይ ወስዳ ታሰቅለን፡፡
የአቶ ፍሰሀን ንግግር የሰሙት ዳኛው ጫንቃቸውን አላባቸው፡፡ይሄ ሰውዬ በተገበጠበት ወቅት ጭንቅላቱን ተመቶ ማሰቢያው ላልቶ ይሆን እንዴ?››ሲል አሰበና አይኑን ገመዶና ጁኒዬር ላይ አንከራተተ…የሆነ ነገር ብለው የጀመረውን ቅዠት የመሰል ድርጊት እንዲያስቆሙት ነው ፍላጎቱ.
❤45👍4
‹‹ቆይ ….ለምንድነው የተሰወርሽው…..?እስከአሁን የት ተደብቀሽ ነበር?››ኩማንደሩ ነው ሲያስገርመው የነበረ ጥያቄ አለምን የጠየቃት፡፡
‹‹የት ነበርሽ ላልከው..እዚሁ ሻሸመኔ ውስጥ ነበርኩ፡፡ለምን ላልከው ግን ሳትቀድሙኝ ልቀድማቹሁ ነው…..ረሰሀው እንዴ አፍናችሁ ይርጋጨፌ ጫካ ውስጥ ልታኖሩኝ እየተዘጋጃችሁ ነበር እኮ››
ቤት ውስጥ ያሉት ወንዶች በአጠቃላይ እርስ በርስ ተያዩ‹‹ያንን እንዴት አወቅሽ?››
ከተቀመጠችበት ተነሳች..ወደኩማንደሩ ተጠጋች….ምን ልታደርግ ነው በሚል ሁሉም በትኩረት እየተመለከቷት ነው….እጇን ሰነዘረችና ደረት ኪሱ ውስጥ ያለውን ብዕር መዛ አወጣች…ትዝ ይልሀል…ይሄ የእኔ ብዕር ነው…ከኪስህ እንዳትለየው ስንገናኝ ትመልስልኛለህ ብዬህ ነበር…አሁን ስለተገናኘን ወስጄዋለው››
‹‹እ..አዎ የአንቺ ብዕር ነው… እና ምን ይፈጠር?››
‹‹ምን ይፈጠር ትላለህ እንዴ….ውይይታችሁን በጠቅላላ በድምፅ እየቀረፀ የሚያስተላልፍልኝ መሳሪያ ነበራ…..››አለችና በእርካታ ፈገግ ብላ ወደመቀመጫዋ ተመለሰች…ኩማንደሩ ራሱን በመከራ ነው የተቆጣጠረው..በህይወቱ በዚህ መጠን ማንም ተጫውቶበት አያውቁም፡፡
የተወስነ ደቂቃ ሁሉም በፀጥታ ተዋጠ..ከዛ ድንገት ጁኒዬር መናገር ጀመሩ‹‹እንግዲህ እወነቱን እኔ ልንገርሽ…ምክንያቱም በእናትሽ ሞት ዋናው ተጠያቂ እኔ ነኝ..በእኔ ምክንያት ቤተሰቦቼና ወዳጆቼ ከዚህ በላይ እንዲሰቃዩ አልፈቅድም….እናትሽ ከአወቅኳት ቀን ጀምሮ እስክትሞት ቀን ድረስ ከዛም አልፎ እስከዛሬ ድረስ በጣም አፈቅራታለው..በእሷ ልክ ማንንም ሴት ማፍቀር አልችልም..››ትንፋሽ ወሰደነ በጨረፍታ ስርጉትን ተመለከታት..ይሄንን ሲል ውስጧ እንዴት ፍርስርስ እንደሚል ያውቃል..ቢሆንም ምንም ለማድረግ አይችልም..፣ዛሬ አባቱ እንዳለው ንፅሁን እውነት የሚናገርበት ቀን ነው፡፡በምራቁ ጉሮሮውን አረጠበና ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይሄንን ለአንቺም ከዚህ በፊት ደጋግሜ ነግሬሻለው፡፡በዛን ቀን ህይወቴ በማይነጥፍ ብርሀን የሚሞላ መስሎኝ ነበር…በደስታዬ መላዕክቶች የሚዘምሩበት ለሊት መስሎኝ ነበር፤ በህይወቴ ዋነኛው በረከትና የመትረፍረፍ ቀን ይሆናል የሚል ግምት ነበር የነበረኝ…እናትሽን እንድታገባኝ ለመጠየቅ የዳይመንድ ፈርጥ ያለበት ቀለበት በልዩ ትዕዛዝ አዘጋጅቼላት ነበር፡፡ቆይ እንደውም…..›› አለና የጃኬቱ ኪስ ውስጥ ገባና የገንዘብ ቦርሳውን በማውጣት ውስጡን ከፍቶ ከአንደኛው ኪስ በነጭ ጨርቅ የተጠቀለለ ነገር በማውጣት ከጨርቁ ፈልቅቆ ወደእሷ ተጠግቶ ፊቷ አስቀመጠው…‹‹ቦርሳውና የሚጠቀለልበት ጨርቅ ቢቀያየርም ይህ ቀለበት ግን ላለፉት 25 አመት ከደረት ኪሴ ተለይቶኝ አያውቅም…እና ይሄ የአልማዝ ፈርጥ ያለው ቀለበት ስላለኝ በተወሰነ መልኩ አብራኝ ያለች ይመስለኛል፡፡››ከግራ አይኑ የመነጨው እንባ በግራ ጉንጩ ላይ ሲንኳለል የተመለከተችው አለም ውስጦ በሀዘን ራደ…
‹‹እንደዛ አይነት ዝግጅት በሚኖረን ጊዜ ለዘበኞችና ለሌሎች አዳሪ ሰራተኞች እረፍት እንሰጣለን…በዛን ቀን ሰራተኞች ሁሉ ከአራት ሰአት በኃላ በየቤታቸው ሄደው ስለነበር..በግቢው ውስጥ ቤተሰብ ብቻ ነበር የቀረነው….በኃላ ቆይተን እንደተረዳነው ግን እኛ ሳናስተውል ስራ ላይ የነበሩ አንድ ሁለት ሰዎች ነበሩ..አንደኛው የእንስሳት ደክተሩ ሲሆኑ ሌለኛው ደግሞ የከብቶቹን ተንከባካቢ ጋሼ ሙስጠፋ ነበር፡፡
እና ለሊቱ ደማቅ ነበር..ዝግጅቱም ሁሉም ሰው የተገኘበት ውብ ነበር፡፡የጋብቻ ጥያቄውን ጠይቄ ቀለበቱን ላጠልቅለት ያሰብኩት ግን ሁሉም ሰው የእርባታ ግቢውን ለቀው ከሄዱ በኃላ ነበር… ቀደም ብለን እዛው ባለው ማረፊያ ቤታችን ውስጥ ለማደር ተስማምተን ስለነበረ ቤቱን በልዩ ሁኔታ እንዲሸበርቅ አድርጌ ነበር፡፡እኩለ ለሊት ትንሽ እንዳለፈ እኔ ከአባዬ ጋር እየተጫወትኩ ሳለው እሷ ከእማዬና ከስርጉት ጋር እቤት ውስጥ ሆነው እያወሩና እየተጫወቱ ነበር….እያንዳንዷን ነገር በግልፅ አስታውሳለው…ከዛ ለአባቴ ነገርኩት…ቀለበት ላጠልቅላት እንደሆነ እና በቅርብ ቀናት ውስጥ ላገባት እንደምፈልጋት እዛ እሳት ዳር ቁጭ ብለን ጨረቃዋን ወደሰማይ አንጋጠን እያየን ነገርኩት…መጀመሪያ ደነገጠ‹‹የልጅ እናት እኮ ነች ይሄ ነገር እንዴት ይሆናል?›› አለኝ?፡፡
‹‹የግድ መቻል አለበት…መንታ ልጆችም ይዛ ቢሆን እሷን እስካገኘው ድረስ ግድ የለኝም አልኩት….ከምሬ ነበረ…‹‹ትንሽ ተረጋግተህ ብታስብብበት አይሻልም ወይ?›› የሚል ሀሳብ አቀረበልኝ….
‹‹ከዚህ በላይ መጠበቅ አልችልም…በፍቅሯ ላብድ ነው›› አልኩት….‹‹እንደዛ ከሆነ ጥሩ…ለማንኛውም እኔ ከጨረቃዋ ጋር እያወራው ትንሽ መቆየት እፈልጋለው…እናትህን ወደቤት መሄድ ፈልጋለው እያለች ነበር ..ደግሞ ብርድ ነክቷት ሳሏ እንዳይነሳባት እቤት አድርሳት›› አለኝ….እሱን እዛው እሳት ዳር ተውኩትና ወደማረፊያው ቤቱ ስሄድ ሶስቱ ሴቶች ነጭ ወይን እየጠጡ በወሬ ተጠምደዋል….‹‹አባዬ ስለሚያመሽ ወደቤት ልውሰዳችሁ አልኳቸው››ሁለቱም ተስማሙ.. እናቴንና ስርጉትን በእኔ መኪና ይዤ ወደቤት ሄድኩ..እንደምታውቂው ቤታችን ከእርባታ ድርጅቱ አስር ደቂቃ ብቻ የሚርቅ ስለሆነ ብዙም አልቆየው …ወዲያው አድርሻቸው ስመለስ አባዬና እና ሰሎሜ በረንዳ ላይ ፊት ለፊት ቆመው እየተመነጫጨቁ ሲያወሩ ደረስኩ…አባዬ ያልሆነ ነገር ተናግሯት እቅዴን እንዳያሰናከልብኝ በጣም ፈራው..የእኔን መምጣት በመኪናዬ ድምፅ ሲሰሙ ድምፃቸውን ቀንሰው ሁኔታቸውን በፍጥነት አስተካከሉ… እኔ ግን ወዲያው ነበር የተረዳሁት ‹‹አባዬ ገና አራስ ሆነሽ ፤የሌላ ሰው ልጅ ይዘሽ ..እንዴት እንደዚህ በፍጥነት ልጄን ታገቢያለሽ ብሎ እያናገራት እንደነበረ እርግጠኛ ነበርኩ..፡እኔ እንደደረስኩ አባዬ ወዲያው በቅጡ እንኳን ሳይሰናበተኝ ወጥቶ ሄደ…ወደበረንዳው ተጠግቼ ሰሎሜን ሳያት በንዴት የፊቷ ስሮች ተግተርትረው በለቅሶ አይኖቾ ደፈራርሰው ሌላ ሰው መስላለች፡፡ተጠመጠምኩባትና አቅፌ ምን እንደሆነች ጠየቅኳት…እየተንሰቀሰቀች ከማልቀስ ውጭ ምንም ልትለኝ አልቻለችም…ነይ ከብርዱ ላይ ወደ ውስጥ እንግባ ብዬ ይዤት ወደውስጥ ገባውና አልጋው ላይ አስቀምጬያት ተመለስኩና በራፉንና መስኮቶቹን ዘጋጋው….፡፡
ስመለስ ስታለቅስ የነበረችው ልጅ ተንከትክታ እየሳቀች ነበር…ሳቋ ከለቅሶዋ በላይ ነበር ያስፈራኝ….‹‹.ምን ሆነሻል?››ስል ጠየቅኳት፡፡
‹‹ልታገባኝ ነው አይደል?››
‹‹አዎ..አባዬ ነገረሽ እና ሰርፕራይዜን አበላሸብኝ አይደል?››አልኳት
‹‹አዎ…..ቀለበቱ የታል?››ስትል ጠየቀችኝ፡፡አውጥቼ ሰጣዋት፡፡ አገላብጣ አየችው..እጣቷ ላይ አድርጋ ተመለከተችው…ተንከትክታ ሳቀች…..ከዛ ቀለበቱን አወጣችና መልሳ በእጄ አስጨበጠችኝ..በጣም ደነገጥኩ..‹‹ምነው..አልወደድሽውም እንዴ?››ስል በፍርሀት ጠየቅኳት፡፡
‹‹ይሄን መሰለ ውብ ቀለበት እንዴት ላልወደው እችላለው?››ስትል መለሰችልኝ፡፡
‹‹እና እኔን ነው የማትወጂኝ?››
‹‹አንተንም በጣም ነው ምወድህ…ቤተሰቦችህን ግን ….››አለችና ከተቀመጠችበት ተስፈንጥራ በመነሳት ፊት ለፊት ግድግዳ ላይ ከነበረ የቁም መስታወት ላይ በግንባሯ ተላተመች፡፡ የመስታወት መፈረካከስና ፍንጥርጣሪ በመላ ክፍሉ ተበተነ…ከእሷ ግንባር የሚፈሰው ደም በአካባቢው ተረጨ…የምገባበት ጠፋኝ…ዘልዬ ያዝኮትና ወደአልጋው መልሼ ላስቀምጣት ስሞክር… ከእኔ ለማምለጥ ስትንፈራገጥ እኔ አንሸራተተኝና ይዣት ወደቅኩ..ማለቴ ስንወድቅ እሷ ከስር ነበረች..ከዛ እንቅስቃሴዋ እየቀነሰ ፣ድምጻም እየጠፋ ሲሄድ ምን እንደተፈጠረ ግራ ገባኝና ለቅቄት ገለበጥኳትና ሳያት..
‹‹የት ነበርሽ ላልከው..እዚሁ ሻሸመኔ ውስጥ ነበርኩ፡፡ለምን ላልከው ግን ሳትቀድሙኝ ልቀድማቹሁ ነው…..ረሰሀው እንዴ አፍናችሁ ይርጋጨፌ ጫካ ውስጥ ልታኖሩኝ እየተዘጋጃችሁ ነበር እኮ››
ቤት ውስጥ ያሉት ወንዶች በአጠቃላይ እርስ በርስ ተያዩ‹‹ያንን እንዴት አወቅሽ?››
ከተቀመጠችበት ተነሳች..ወደኩማንደሩ ተጠጋች….ምን ልታደርግ ነው በሚል ሁሉም በትኩረት እየተመለከቷት ነው….እጇን ሰነዘረችና ደረት ኪሱ ውስጥ ያለውን ብዕር መዛ አወጣች…ትዝ ይልሀል…ይሄ የእኔ ብዕር ነው…ከኪስህ እንዳትለየው ስንገናኝ ትመልስልኛለህ ብዬህ ነበር…አሁን ስለተገናኘን ወስጄዋለው››
‹‹እ..አዎ የአንቺ ብዕር ነው… እና ምን ይፈጠር?››
‹‹ምን ይፈጠር ትላለህ እንዴ….ውይይታችሁን በጠቅላላ በድምፅ እየቀረፀ የሚያስተላልፍልኝ መሳሪያ ነበራ…..››አለችና በእርካታ ፈገግ ብላ ወደመቀመጫዋ ተመለሰች…ኩማንደሩ ራሱን በመከራ ነው የተቆጣጠረው..በህይወቱ በዚህ መጠን ማንም ተጫውቶበት አያውቁም፡፡
የተወስነ ደቂቃ ሁሉም በፀጥታ ተዋጠ..ከዛ ድንገት ጁኒዬር መናገር ጀመሩ‹‹እንግዲህ እወነቱን እኔ ልንገርሽ…ምክንያቱም በእናትሽ ሞት ዋናው ተጠያቂ እኔ ነኝ..በእኔ ምክንያት ቤተሰቦቼና ወዳጆቼ ከዚህ በላይ እንዲሰቃዩ አልፈቅድም….እናትሽ ከአወቅኳት ቀን ጀምሮ እስክትሞት ቀን ድረስ ከዛም አልፎ እስከዛሬ ድረስ በጣም አፈቅራታለው..በእሷ ልክ ማንንም ሴት ማፍቀር አልችልም..››ትንፋሽ ወሰደነ በጨረፍታ ስርጉትን ተመለከታት..ይሄንን ሲል ውስጧ እንዴት ፍርስርስ እንደሚል ያውቃል..ቢሆንም ምንም ለማድረግ አይችልም..፣ዛሬ አባቱ እንዳለው ንፅሁን እውነት የሚናገርበት ቀን ነው፡፡በምራቁ ጉሮሮውን አረጠበና ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይሄንን ለአንቺም ከዚህ በፊት ደጋግሜ ነግሬሻለው፡፡በዛን ቀን ህይወቴ በማይነጥፍ ብርሀን የሚሞላ መስሎኝ ነበር…በደስታዬ መላዕክቶች የሚዘምሩበት ለሊት መስሎኝ ነበር፤ በህይወቴ ዋነኛው በረከትና የመትረፍረፍ ቀን ይሆናል የሚል ግምት ነበር የነበረኝ…እናትሽን እንድታገባኝ ለመጠየቅ የዳይመንድ ፈርጥ ያለበት ቀለበት በልዩ ትዕዛዝ አዘጋጅቼላት ነበር፡፡ቆይ እንደውም…..›› አለና የጃኬቱ ኪስ ውስጥ ገባና የገንዘብ ቦርሳውን በማውጣት ውስጡን ከፍቶ ከአንደኛው ኪስ በነጭ ጨርቅ የተጠቀለለ ነገር በማውጣት ከጨርቁ ፈልቅቆ ወደእሷ ተጠግቶ ፊቷ አስቀመጠው…‹‹ቦርሳውና የሚጠቀለልበት ጨርቅ ቢቀያየርም ይህ ቀለበት ግን ላለፉት 25 አመት ከደረት ኪሴ ተለይቶኝ አያውቅም…እና ይሄ የአልማዝ ፈርጥ ያለው ቀለበት ስላለኝ በተወሰነ መልኩ አብራኝ ያለች ይመስለኛል፡፡››ከግራ አይኑ የመነጨው እንባ በግራ ጉንጩ ላይ ሲንኳለል የተመለከተችው አለም ውስጦ በሀዘን ራደ…
‹‹እንደዛ አይነት ዝግጅት በሚኖረን ጊዜ ለዘበኞችና ለሌሎች አዳሪ ሰራተኞች እረፍት እንሰጣለን…በዛን ቀን ሰራተኞች ሁሉ ከአራት ሰአት በኃላ በየቤታቸው ሄደው ስለነበር..በግቢው ውስጥ ቤተሰብ ብቻ ነበር የቀረነው….በኃላ ቆይተን እንደተረዳነው ግን እኛ ሳናስተውል ስራ ላይ የነበሩ አንድ ሁለት ሰዎች ነበሩ..አንደኛው የእንስሳት ደክተሩ ሲሆኑ ሌለኛው ደግሞ የከብቶቹን ተንከባካቢ ጋሼ ሙስጠፋ ነበር፡፡
እና ለሊቱ ደማቅ ነበር..ዝግጅቱም ሁሉም ሰው የተገኘበት ውብ ነበር፡፡የጋብቻ ጥያቄውን ጠይቄ ቀለበቱን ላጠልቅለት ያሰብኩት ግን ሁሉም ሰው የእርባታ ግቢውን ለቀው ከሄዱ በኃላ ነበር… ቀደም ብለን እዛው ባለው ማረፊያ ቤታችን ውስጥ ለማደር ተስማምተን ስለነበረ ቤቱን በልዩ ሁኔታ እንዲሸበርቅ አድርጌ ነበር፡፡እኩለ ለሊት ትንሽ እንዳለፈ እኔ ከአባዬ ጋር እየተጫወትኩ ሳለው እሷ ከእማዬና ከስርጉት ጋር እቤት ውስጥ ሆነው እያወሩና እየተጫወቱ ነበር….እያንዳንዷን ነገር በግልፅ አስታውሳለው…ከዛ ለአባቴ ነገርኩት…ቀለበት ላጠልቅላት እንደሆነ እና በቅርብ ቀናት ውስጥ ላገባት እንደምፈልጋት እዛ እሳት ዳር ቁጭ ብለን ጨረቃዋን ወደሰማይ አንጋጠን እያየን ነገርኩት…መጀመሪያ ደነገጠ‹‹የልጅ እናት እኮ ነች ይሄ ነገር እንዴት ይሆናል?›› አለኝ?፡፡
‹‹የግድ መቻል አለበት…መንታ ልጆችም ይዛ ቢሆን እሷን እስካገኘው ድረስ ግድ የለኝም አልኩት….ከምሬ ነበረ…‹‹ትንሽ ተረጋግተህ ብታስብብበት አይሻልም ወይ?›› የሚል ሀሳብ አቀረበልኝ….
‹‹ከዚህ በላይ መጠበቅ አልችልም…በፍቅሯ ላብድ ነው›› አልኩት….‹‹እንደዛ ከሆነ ጥሩ…ለማንኛውም እኔ ከጨረቃዋ ጋር እያወራው ትንሽ መቆየት እፈልጋለው…እናትህን ወደቤት መሄድ ፈልጋለው እያለች ነበር ..ደግሞ ብርድ ነክቷት ሳሏ እንዳይነሳባት እቤት አድርሳት›› አለኝ….እሱን እዛው እሳት ዳር ተውኩትና ወደማረፊያው ቤቱ ስሄድ ሶስቱ ሴቶች ነጭ ወይን እየጠጡ በወሬ ተጠምደዋል….‹‹አባዬ ስለሚያመሽ ወደቤት ልውሰዳችሁ አልኳቸው››ሁለቱም ተስማሙ.. እናቴንና ስርጉትን በእኔ መኪና ይዤ ወደቤት ሄድኩ..እንደምታውቂው ቤታችን ከእርባታ ድርጅቱ አስር ደቂቃ ብቻ የሚርቅ ስለሆነ ብዙም አልቆየው …ወዲያው አድርሻቸው ስመለስ አባዬና እና ሰሎሜ በረንዳ ላይ ፊት ለፊት ቆመው እየተመነጫጨቁ ሲያወሩ ደረስኩ…አባዬ ያልሆነ ነገር ተናግሯት እቅዴን እንዳያሰናከልብኝ በጣም ፈራው..የእኔን መምጣት በመኪናዬ ድምፅ ሲሰሙ ድምፃቸውን ቀንሰው ሁኔታቸውን በፍጥነት አስተካከሉ… እኔ ግን ወዲያው ነበር የተረዳሁት ‹‹አባዬ ገና አራስ ሆነሽ ፤የሌላ ሰው ልጅ ይዘሽ ..እንዴት እንደዚህ በፍጥነት ልጄን ታገቢያለሽ ብሎ እያናገራት እንደነበረ እርግጠኛ ነበርኩ..፡እኔ እንደደረስኩ አባዬ ወዲያው በቅጡ እንኳን ሳይሰናበተኝ ወጥቶ ሄደ…ወደበረንዳው ተጠግቼ ሰሎሜን ሳያት በንዴት የፊቷ ስሮች ተግተርትረው በለቅሶ አይኖቾ ደፈራርሰው ሌላ ሰው መስላለች፡፡ተጠመጠምኩባትና አቅፌ ምን እንደሆነች ጠየቅኳት…እየተንሰቀሰቀች ከማልቀስ ውጭ ምንም ልትለኝ አልቻለችም…ነይ ከብርዱ ላይ ወደ ውስጥ እንግባ ብዬ ይዤት ወደውስጥ ገባውና አልጋው ላይ አስቀምጬያት ተመለስኩና በራፉንና መስኮቶቹን ዘጋጋው….፡፡
ስመለስ ስታለቅስ የነበረችው ልጅ ተንከትክታ እየሳቀች ነበር…ሳቋ ከለቅሶዋ በላይ ነበር ያስፈራኝ….‹‹.ምን ሆነሻል?››ስል ጠየቅኳት፡፡
‹‹ልታገባኝ ነው አይደል?››
‹‹አዎ..አባዬ ነገረሽ እና ሰርፕራይዜን አበላሸብኝ አይደል?››አልኳት
‹‹አዎ…..ቀለበቱ የታል?››ስትል ጠየቀችኝ፡፡አውጥቼ ሰጣዋት፡፡ አገላብጣ አየችው..እጣቷ ላይ አድርጋ ተመለከተችው…ተንከትክታ ሳቀች…..ከዛ ቀለበቱን አወጣችና መልሳ በእጄ አስጨበጠችኝ..በጣም ደነገጥኩ..‹‹ምነው..አልወደድሽውም እንዴ?››ስል በፍርሀት ጠየቅኳት፡፡
‹‹ይሄን መሰለ ውብ ቀለበት እንዴት ላልወደው እችላለው?››ስትል መለሰችልኝ፡፡
‹‹እና እኔን ነው የማትወጂኝ?››
‹‹አንተንም በጣም ነው ምወድህ…ቤተሰቦችህን ግን ….››አለችና ከተቀመጠችበት ተስፈንጥራ በመነሳት ፊት ለፊት ግድግዳ ላይ ከነበረ የቁም መስታወት ላይ በግንባሯ ተላተመች፡፡ የመስታወት መፈረካከስና ፍንጥርጣሪ በመላ ክፍሉ ተበተነ…ከእሷ ግንባር የሚፈሰው ደም በአካባቢው ተረጨ…የምገባበት ጠፋኝ…ዘልዬ ያዝኮትና ወደአልጋው መልሼ ላስቀምጣት ስሞክር… ከእኔ ለማምለጥ ስትንፈራገጥ እኔ አንሸራተተኝና ይዣት ወደቅኩ..ማለቴ ስንወድቅ እሷ ከስር ነበረች..ከዛ እንቅስቃሴዋ እየቀነሰ ፣ድምጻም እየጠፋ ሲሄድ ምን እንደተፈጠረ ግራ ገባኝና ለቅቄት ገለበጥኳትና ሳያት..
❤36😱4😢2
አንድ የመስታወት ቁራጭ ከእንብርቷ በታች ሆዷ ላይ ተሸጦባት ነበር….ትንፋሿን ሳዳምጥ ትንሽ ትንሽ ብን ብን ይላል፡፡በደመነፍስ ስልኬን አውጥቼ ለአባዬ ደወልኩለት… ከዛ በኃላ የሆነውን እኔ አላውቅም….እራሴን ስቼ ቤት ክፍሌ ውስጥ ተዘግቶብኝ በሶስተኛው ቀን ነው የነቃሁት፡፡እና አውቄም ሆነ በድንገት አደጋ እናትሽን የገደልኳት እኔ ነኝ…ነገ ጥዋት ወደከተማ እንደተመለስን አሁን ለአንቺ የነገርኩሽን ጠቅላላ ቃሌን ሰጥቼ ፍርዴን እቀበላለው..በወላጆቼና በሌሎች ሰዎች ላይ የያዝሽውን ቂም ግን በቃ አዚህ ላይ አቁሚ፡፡››አለና በረጅሙ በመተንፈስ ወደኩርሲው ተመልሶ ተቀመጠ፡፡
አለም የጂኒዬርን ኑዛዜ በጥሞና ነው ያዳመጠችው….አንድም ቃል አላሳለፈችም…. እናቷ እንዴት እንደሞተች አሁን በግልፅ አውቃለች….ግን አሁንም ታሪኩ ሙሉ አልሆነላትም…‹‹በምንም አይነት ወንጀለኛውማ ጂኒዬር ብቻ አይሆንም››ስትል በውስጧ አሰበች…እሷ የሆነ ነገር ከማለቷ በፊት….እናቱ ሳራ በድንገት መናገር ጀመረች፡፡
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››አለችው፡፡
‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››
‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አለም የጂኒዬርን ኑዛዜ በጥሞና ነው ያዳመጠችው….አንድም ቃል አላሳለፈችም…. እናቷ እንዴት እንደሞተች አሁን በግልፅ አውቃለች….ግን አሁንም ታሪኩ ሙሉ አልሆነላትም…‹‹በምንም አይነት ወንጀለኛውማ ጂኒዬር ብቻ አይሆንም››ስትል በውስጧ አሰበች…እሷ የሆነ ነገር ከማለቷ በፊት….እናቱ ሳራ በድንገት መናገር ጀመረች፡፡
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››አለችው፡፡
‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››
‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍82❤28😱23
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››
‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››
‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››ስርጉት በተቀመጠችበት ሆና አቃሰተች….ዳኛው መተንፈስ ከበዳቸው፡፡ሳራ ግን ለማናቸውም ግድ አልነበራትም..የእሷ ዋናው ትኩረት ልጇን ከእስር ማዳን ብቻ ነው..እና ንግግሯን ቀጠለች፡፡
‹‹.የዛን ቀን አንተ እኛን ወደቤታችን ከመሸኘትህ በፊት መጠጧ ውስጥ መድሀኒት ጨምረንባት ነበር..ከ30 ደቂቃ በኃላ እንደማሳበድ አድርጓት በአንድ ሰአት ውስጥ ሙሉ በሙሉ የሚገድላት መድሀኒት ነበር፡፡እሷ የተቀየረችብህና ከመስታወት ላይ ግንባሮሯን የከሰከሰችው በመድሀኒቱ ተጽዕኖ ነው…መስታወቱ ሆዷ ውስጥ ቢሻጥ እንኳን አልሞተችም ነበር…አባትህ መጥቶ ሀኪም ቤት ሊወስዳት መኪናው ውስጥ አስገብቶ መንገድ ከጀመረች በኃላ ነው እስትንፋሷ የተቋረጠው…ያም የሆነው በተወጋችው ውግ ወይም በፈሰሳት ደም ሳይሆን በጠጣችው መርዝ ምክንያት ነው፡፡
‹‹እማዬ ይሄን እንዴት እሰከዛሬ ሳላውቅ…?አባዬ አንተ እንዲህ መሆኑን ታውቃለህ?››ሲል አባቱ ላይ አፈጠጠበት፡፡
አቀርቅሮ የነበረው አቶ ፍሰሀ በከፊል ቀና አለና ‹‹ከአንተ እና ከአለም በስተቀር ይሄንን ጉዳይ እዚህ ቤት ያለው ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡››ሲል እውነቱን ፍርጥም ብሎ መለሰለት፡፡
‹‹ምን አረገቻችሁ ቆይ …?ምናችሁ ላይ ደረሰች?››አለም በእንባ ታጥባ እየነፈረቀች ሳራ ላይ አፈጠጠችባት፡፡
ሳራ እሷን ችላ ብላ ወደልጇ እየተመለከተች‹‹አንተን እንዳታገባህ እና ከስርህ እንድትርቅ ለአመታት ለመናት.. አስጠነቀቅናት፤ እሷ ግን ሌላ ሰው አግብታ ወልዳ እንኳን ልትተውህ አልቻለችም…የልጄ ህይወት በእንደዛ አይነት ሁኔታ ሲበላሽ ቆሜ ማየት አልቻልኩም፡፡እኔ ስርጉትን እንድታገባ ነበር ምፈልገው፣ከልቧ በጣም የሚታፈቅርህ ሰሎሜ ሳትሆን ስርጉት እንደሆነች በደምብ አውቃለው..››
ወዲያው ሳራ ንግግሯን እንዳገባደደች ኩማንደር ተቀበላት‹‹ያው እንግዲህ መጠኑ ይለያይ እንጂ በእናትሽ ግድያ ሁላችንን የየድርሻችንን ተወጥተናል…እኔ በእለቱ እስከእራት ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር አብሬቸው የቆየሁት…ከለሊቱ ዘጠንኝ ሰዓት ጋሽ ፍሰሀ ደወለልኝ.. ስመጣ
…እናትሽ ጋሼ መኪናው ውስጥ እጥፍጥፍ ብላና በደም ተበክላ ነበር…ጋሼ የሆነውን በአጭሩ አስረዳኝና የሚሆነውን እንዳደርግ ሀላፊነቱን ለእኔ ሰጠኝ ….ነገሩ ወደህግ ከሄደ ጁኒዬር፤ሳራም ሆነች ስርጉት ዘብጥያ መውረዳቸው አይቀርም …ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ያ ሊቁ የተባለው እብድ በዛ ውድቅት ለሊት እየለፈለፍ በእርባታ ድርጅቱ ፊት ለፊት ባለው መንገድ ሲያልፍ አየሁት..ወዲያው ሀሳብ ብልጭ አለልኝ..ሮጥኩና ይዤው ወደውስጥ ገባው..ከማታ እራት የተረፈ ምግብና መጠጥ ስለነበረ እሱን ሰጠሁትና ስለማደርገው ነገር መዘጋጀት ጀመርኩ..የምጠቀምበት እቃ ስፈልግ የእንስሳት ዶክተሩ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን በረንዳ ላይ ተቀምጦ ነበር፤አይኔ ውስጥ ገባ፣ ቶሎ አልኩና ከፈትኩት ፡፡ የቀዶ ህክምን ሚገለገሉበትን ቢላዋ አገኘሁና .. በወቅቱ በጣም ተደናግጬ ስለነበረ የማደርገውን ሁሉ የማደርገው በደመነፍስ ነበር….እና ያው ልጅ እንደገደላት እንዲመስል አደረኩና ጥዋት ለፖሊስ ተደወለ.. በኃላ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እየተጓዙ ሳለ አያትሽ ልጄን የገደላት እብዱ ሳይሆን እነሱ ናቸው… የሚል ወሬ መንዛት እና
አቤቱታ ማሰማት ጀመሩ…ከዛ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ዘንድ አንዳንድ ጥርጣሬዎች ብልጭ ማለት ጀመሩ..ሬሳው በደንብ ይመርመር የሚል ግሩፕ ተነሳ…ከዛ ከጋሼ ጋር ተማከርንና የሆስፒታሉ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍል እሳት እንዲነሳና እሬሳውም እንዲቃጠል አደረግን..በስተመጨረሻም አያትሽን ይሄንን ሀገር ለቀው ካልሄዱ አንቺን ነጥቀን እስከወዲያኛው እንዳያገኙሽ እንደምናደርግ አስፈራርተናቸው ዝም እንዲሉና ከተማውንም ለቀው እንዲሄዱ አደረግን…እናም በተጨማሪ ስለእናትሽ አሟሟት ሊነግርሽ ነበረውን ሙስጠፋንም የገደልኩት እኔ ነኝ!!የዛን ቀን እኛ ሳናየው እዛ ተደብቆ እያንዳንዱን ነገር ሲያይ ነበር….ይሄን ሁሉ ነገር ግን ፍርድ ቤት ቀርቦ ያምንልኛል ብለሽ እንዳትጠብቂ…››ሲል ንግግሩን አገባደደ፡፡
አለም ደም በለበሱ አስፈሪ አይኖቾን ኩማንደሩ ላይ አፍጥጣ‹‹ቆይ ቆይ እስኪ…ልጁ የገደላት ለማስመሰል ከሞተች በኃላ በዛ የቀዶ ጥገና ቢላዋ ደጋግመህ ወጋሀት አይደል?
…?ከዛ ደሟ ሲንፎለፎል በእጅህ እየዘቅክ እዛ ሚስኪን ልጅ ልብስ ላይ አዳረስከው …እንዳዛ አይደል ያደረከው?በቁሟ እያለች በፍቅር ልብህን ስለሰበራች ልትበቀላት ታስብ ነበር፣ግን ለማድረግ ወኔ አልነበረህም..በዛን ወቅት ግን አጋጣሚው ተመቻቸልህ..ነፍሷ ውስጧ ባይኖርም ደጋግመህ ሰጋዋን በመበሳሳት ንዴትህን ተወጣህባት….ከዛ ሬሳዋ ለምርመራ ሆስፒታል ገባ ..አንዳንድ ጥርጣሬ የሚያስነሱ ነገሮች መፈጠር ሲጀምሩ እራሳችሁን ከማንኛውም አደጋ ጥርጣሬ ለመጠበቅ አስፈላጊ ስለነበረ ጋሼ ፍሰሀ ደግሞ የሆስፒታሉ የሆነ ክፍል በእሳት እንዲያያዝ እና ሬሳዋም እንዲቃጠል እና አመድ እንዲሆነ አደረገ..ከዛ አቶ ዳኛ በዚህ ወንጀል ውስጥ ልጁ ስላለችበት ይህንን ወንጀል እንዳይጋለጥ ባለህ ስልጣን ሁሉ ተጠቅመህ ፋይሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲዘጋ አደረክ…፡፡በትክክል ተረድቼችኋለው አይደል..?እንዲህ ነው ያደረጋችሁት?
‹‹ሁሉም በመሸማቀቅ አንገታቸውን አቀርቅረው ነበር የሚሰሟት‹‹እስከአሁን እንደሰማሁት ከሆነ እኮ ጁኒዬር ብቻ አይደለም ራሱን ለህግ አሳልፎ መስጠት ያለበት …ሁላችሁም ናችሁ..እና እኔ ዳኛ ብሆን በጣም ትንሹን ፍርድ የምፈርደው በእሱ ላይ ነው….እሱ ሳያስበው…በድንገተኛ አደጋ የፈጠረው ወንጀል ነው…ሌለቻችሁ ግን አስባችሁ እና አቅድ አውጥታችሁ ደግማችሁ ደጋግማችሁ እናቴን በነፍስም በስጋም አጥፍታችኃታል….እና ነገ ወደከተማ ስንመለስ ምን እንደምታደርጉ ለማየት በጣም ጎጉቼለው….፡፡››
‹‹መቼስ ሁላችንም ሳታጠፊን እንቅልፍ አይወስድሽም አይደል…?ደስ ይበልሽ ይሄው ተሳካልሽ››አሉ ዳኛው ቅስማቸው ስብርብር ብሎ፡፡
‹‹ደስ ይበልሽ !!….ጭራሽ ደስ ይበልሽ…?.ፍርድን በአደባባይ ሲሸጦት ያዛን ጊዜ ማሰብ ነበረቦት››
‹‹አይ መሬት ያለ ሰው….በእኔ ላይ የደረሰውን ወላጅ ስትሆኚ ነው የምታውቂው….ልጄን ከእስርና ከእንግልት ለማዳን ስል ነው እዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ የገባሁት››
‹‹አይ ልጆትን ከእስር ለማትረፍ ብቻ አይደለም….ከሶሌ ኢንተርፕራይዝም የ10 ፐርሰንት የአክሲዬን ድርሻ በልጆት ስም ማግኘት ችለዋል፡፡››
‹‹ይህ ፍፁም እውነት አይደለም…ያንን አክሲዬን የገዛሁት በራሴ ብር ነው….ከወላጆቼ በውርስ ያገኘሁትን ንብረት በጠቅላላ ሸጬ ነው የገዛሁት…ያንንም ፈልጌው ሳይሆን ኩማንደሩ እና ፍሰሀ አስገድደውኝ ነው፡፡በልጄ አስፈራርተውኝ ነው››
ዳኛው የሚናገሩትን ባለማመን ቀና አለችና ኩማንደሩ ላይ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹አዎ..እውነቱን ነው፡፡ይሄንን ወንጀል ዛላለም በመሀከላችን እንደተቀበረ እንዲቆይ እርስ በርስ የበለጠ መተሳሰር አለብን ብለን አሰብን…ከዛ ከጁኒዬር እና ከሳራ ድርሻ ላይ ተቀንሶ በስርጉት ስም አክሲዬን እንዲገዙ አደረግን….ባይሆን እኔ ቀጥታ ጠይቄ ባይሆንም ከእናትሽ ሞት በኃላ የአክሲዬን ድርሻዬ ወደ30 ፐርሰንት እንዲያድግ ሆኗል….››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››
‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››
‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››ስርጉት በተቀመጠችበት ሆና አቃሰተች….ዳኛው መተንፈስ ከበዳቸው፡፡ሳራ ግን ለማናቸውም ግድ አልነበራትም..የእሷ ዋናው ትኩረት ልጇን ከእስር ማዳን ብቻ ነው..እና ንግግሯን ቀጠለች፡፡
‹‹.የዛን ቀን አንተ እኛን ወደቤታችን ከመሸኘትህ በፊት መጠጧ ውስጥ መድሀኒት ጨምረንባት ነበር..ከ30 ደቂቃ በኃላ እንደማሳበድ አድርጓት በአንድ ሰአት ውስጥ ሙሉ በሙሉ የሚገድላት መድሀኒት ነበር፡፡እሷ የተቀየረችብህና ከመስታወት ላይ ግንባሮሯን የከሰከሰችው በመድሀኒቱ ተጽዕኖ ነው…መስታወቱ ሆዷ ውስጥ ቢሻጥ እንኳን አልሞተችም ነበር…አባትህ መጥቶ ሀኪም ቤት ሊወስዳት መኪናው ውስጥ አስገብቶ መንገድ ከጀመረች በኃላ ነው እስትንፋሷ የተቋረጠው…ያም የሆነው በተወጋችው ውግ ወይም በፈሰሳት ደም ሳይሆን በጠጣችው መርዝ ምክንያት ነው፡፡
‹‹እማዬ ይሄን እንዴት እሰከዛሬ ሳላውቅ…?አባዬ አንተ እንዲህ መሆኑን ታውቃለህ?››ሲል አባቱ ላይ አፈጠጠበት፡፡
አቀርቅሮ የነበረው አቶ ፍሰሀ በከፊል ቀና አለና ‹‹ከአንተ እና ከአለም በስተቀር ይሄንን ጉዳይ እዚህ ቤት ያለው ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡››ሲል እውነቱን ፍርጥም ብሎ መለሰለት፡፡
‹‹ምን አረገቻችሁ ቆይ …?ምናችሁ ላይ ደረሰች?››አለም በእንባ ታጥባ እየነፈረቀች ሳራ ላይ አፈጠጠችባት፡፡
ሳራ እሷን ችላ ብላ ወደልጇ እየተመለከተች‹‹አንተን እንዳታገባህ እና ከስርህ እንድትርቅ ለአመታት ለመናት.. አስጠነቀቅናት፤ እሷ ግን ሌላ ሰው አግብታ ወልዳ እንኳን ልትተውህ አልቻለችም…የልጄ ህይወት በእንደዛ አይነት ሁኔታ ሲበላሽ ቆሜ ማየት አልቻልኩም፡፡እኔ ስርጉትን እንድታገባ ነበር ምፈልገው፣ከልቧ በጣም የሚታፈቅርህ ሰሎሜ ሳትሆን ስርጉት እንደሆነች በደምብ አውቃለው..››
ወዲያው ሳራ ንግግሯን እንዳገባደደች ኩማንደር ተቀበላት‹‹ያው እንግዲህ መጠኑ ይለያይ እንጂ በእናትሽ ግድያ ሁላችንን የየድርሻችንን ተወጥተናል…እኔ በእለቱ እስከእራት ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር አብሬቸው የቆየሁት…ከለሊቱ ዘጠንኝ ሰዓት ጋሽ ፍሰሀ ደወለልኝ.. ስመጣ
…እናትሽ ጋሼ መኪናው ውስጥ እጥፍጥፍ ብላና በደም ተበክላ ነበር…ጋሼ የሆነውን በአጭሩ አስረዳኝና የሚሆነውን እንዳደርግ ሀላፊነቱን ለእኔ ሰጠኝ ….ነገሩ ወደህግ ከሄደ ጁኒዬር፤ሳራም ሆነች ስርጉት ዘብጥያ መውረዳቸው አይቀርም …ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ያ ሊቁ የተባለው እብድ በዛ ውድቅት ለሊት እየለፈለፍ በእርባታ ድርጅቱ ፊት ለፊት ባለው መንገድ ሲያልፍ አየሁት..ወዲያው ሀሳብ ብልጭ አለልኝ..ሮጥኩና ይዤው ወደውስጥ ገባው..ከማታ እራት የተረፈ ምግብና መጠጥ ስለነበረ እሱን ሰጠሁትና ስለማደርገው ነገር መዘጋጀት ጀመርኩ..የምጠቀምበት እቃ ስፈልግ የእንስሳት ዶክተሩ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን በረንዳ ላይ ተቀምጦ ነበር፤አይኔ ውስጥ ገባ፣ ቶሎ አልኩና ከፈትኩት ፡፡ የቀዶ ህክምን ሚገለገሉበትን ቢላዋ አገኘሁና .. በወቅቱ በጣም ተደናግጬ ስለነበረ የማደርገውን ሁሉ የማደርገው በደመነፍስ ነበር….እና ያው ልጅ እንደገደላት እንዲመስል አደረኩና ጥዋት ለፖሊስ ተደወለ.. በኃላ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እየተጓዙ ሳለ አያትሽ ልጄን የገደላት እብዱ ሳይሆን እነሱ ናቸው… የሚል ወሬ መንዛት እና
አቤቱታ ማሰማት ጀመሩ…ከዛ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ዘንድ አንዳንድ ጥርጣሬዎች ብልጭ ማለት ጀመሩ..ሬሳው በደንብ ይመርመር የሚል ግሩፕ ተነሳ…ከዛ ከጋሼ ጋር ተማከርንና የሆስፒታሉ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍል እሳት እንዲነሳና እሬሳውም እንዲቃጠል አደረግን..በስተመጨረሻም አያትሽን ይሄንን ሀገር ለቀው ካልሄዱ አንቺን ነጥቀን እስከወዲያኛው እንዳያገኙሽ እንደምናደርግ አስፈራርተናቸው ዝም እንዲሉና ከተማውንም ለቀው እንዲሄዱ አደረግን…እናም በተጨማሪ ስለእናትሽ አሟሟት ሊነግርሽ ነበረውን ሙስጠፋንም የገደልኩት እኔ ነኝ!!የዛን ቀን እኛ ሳናየው እዛ ተደብቆ እያንዳንዱን ነገር ሲያይ ነበር….ይሄን ሁሉ ነገር ግን ፍርድ ቤት ቀርቦ ያምንልኛል ብለሽ እንዳትጠብቂ…››ሲል ንግግሩን አገባደደ፡፡
አለም ደም በለበሱ አስፈሪ አይኖቾን ኩማንደሩ ላይ አፍጥጣ‹‹ቆይ ቆይ እስኪ…ልጁ የገደላት ለማስመሰል ከሞተች በኃላ በዛ የቀዶ ጥገና ቢላዋ ደጋግመህ ወጋሀት አይደል?
…?ከዛ ደሟ ሲንፎለፎል በእጅህ እየዘቅክ እዛ ሚስኪን ልጅ ልብስ ላይ አዳረስከው …እንዳዛ አይደል ያደረከው?በቁሟ እያለች በፍቅር ልብህን ስለሰበራች ልትበቀላት ታስብ ነበር፣ግን ለማድረግ ወኔ አልነበረህም..በዛን ወቅት ግን አጋጣሚው ተመቻቸልህ..ነፍሷ ውስጧ ባይኖርም ደጋግመህ ሰጋዋን በመበሳሳት ንዴትህን ተወጣህባት….ከዛ ሬሳዋ ለምርመራ ሆስፒታል ገባ ..አንዳንድ ጥርጣሬ የሚያስነሱ ነገሮች መፈጠር ሲጀምሩ እራሳችሁን ከማንኛውም አደጋ ጥርጣሬ ለመጠበቅ አስፈላጊ ስለነበረ ጋሼ ፍሰሀ ደግሞ የሆስፒታሉ የሆነ ክፍል በእሳት እንዲያያዝ እና ሬሳዋም እንዲቃጠል እና አመድ እንዲሆነ አደረገ..ከዛ አቶ ዳኛ በዚህ ወንጀል ውስጥ ልጁ ስላለችበት ይህንን ወንጀል እንዳይጋለጥ ባለህ ስልጣን ሁሉ ተጠቅመህ ፋይሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲዘጋ አደረክ…፡፡በትክክል ተረድቼችኋለው አይደል..?እንዲህ ነው ያደረጋችሁት?
‹‹ሁሉም በመሸማቀቅ አንገታቸውን አቀርቅረው ነበር የሚሰሟት‹‹እስከአሁን እንደሰማሁት ከሆነ እኮ ጁኒዬር ብቻ አይደለም ራሱን ለህግ አሳልፎ መስጠት ያለበት …ሁላችሁም ናችሁ..እና እኔ ዳኛ ብሆን በጣም ትንሹን ፍርድ የምፈርደው በእሱ ላይ ነው….እሱ ሳያስበው…በድንገተኛ አደጋ የፈጠረው ወንጀል ነው…ሌለቻችሁ ግን አስባችሁ እና አቅድ አውጥታችሁ ደግማችሁ ደጋግማችሁ እናቴን በነፍስም በስጋም አጥፍታችኃታል….እና ነገ ወደከተማ ስንመለስ ምን እንደምታደርጉ ለማየት በጣም ጎጉቼለው….፡፡››
‹‹መቼስ ሁላችንም ሳታጠፊን እንቅልፍ አይወስድሽም አይደል…?ደስ ይበልሽ ይሄው ተሳካልሽ››አሉ ዳኛው ቅስማቸው ስብርብር ብሎ፡፡
‹‹ደስ ይበልሽ !!….ጭራሽ ደስ ይበልሽ…?.ፍርድን በአደባባይ ሲሸጦት ያዛን ጊዜ ማሰብ ነበረቦት››
‹‹አይ መሬት ያለ ሰው….በእኔ ላይ የደረሰውን ወላጅ ስትሆኚ ነው የምታውቂው….ልጄን ከእስርና ከእንግልት ለማዳን ስል ነው እዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ የገባሁት››
‹‹አይ ልጆትን ከእስር ለማትረፍ ብቻ አይደለም….ከሶሌ ኢንተርፕራይዝም የ10 ፐርሰንት የአክሲዬን ድርሻ በልጆት ስም ማግኘት ችለዋል፡፡››
‹‹ይህ ፍፁም እውነት አይደለም…ያንን አክሲዬን የገዛሁት በራሴ ብር ነው….ከወላጆቼ በውርስ ያገኘሁትን ንብረት በጠቅላላ ሸጬ ነው የገዛሁት…ያንንም ፈልጌው ሳይሆን ኩማንደሩ እና ፍሰሀ አስገድደውኝ ነው፡፡በልጄ አስፈራርተውኝ ነው››
ዳኛው የሚናገሩትን ባለማመን ቀና አለችና ኩማንደሩ ላይ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹አዎ..እውነቱን ነው፡፡ይሄንን ወንጀል ዛላለም በመሀከላችን እንደተቀበረ እንዲቆይ እርስ በርስ የበለጠ መተሳሰር አለብን ብለን አሰብን…ከዛ ከጁኒዬር እና ከሳራ ድርሻ ላይ ተቀንሶ በስርጉት ስም አክሲዬን እንዲገዙ አደረግን….ባይሆን እኔ ቀጥታ ጠይቄ ባይሆንም ከእናትሽ ሞት በኃላ የአክሲዬን ድርሻዬ ወደ30 ፐርሰንት እንዲያድግ ሆኗል….››
❤46👍5😱2
ጁኒዬር ከተቀመጠበት ተነሳ፣ ወደኩማንደሩ ቀረበና እየተንዘረዘረ ማውራት ጀመር‹‹ከዛ እኔ ጅሉን አባቷ የሰራሀውን ወንጀል እንዲደብቅልህ እና ወደእስር ቤት እንዳትገባ ልጁን ማግባትና መዛመድ አለብህ ብላችሁ አስፋፈራራችሁኝና..በሰሎሜ ሞት ከደረሰብኝ ሀዘን እንኳን በቅጡ ሳላገግም አግለብልባችሁ ስርጉትን እንዳገባት አደረጋችሁ››ብሎ አፈጠጠበት፡፡
ኩማንደሩ አንገቱን ከማቀርቀር ውጭ ምንም አልመለሰለትም፡፡
‹‹ምን አይነት ጅል ኖሬያለው…አባቴና የልብ ጓደኛዬ እድሜዬን ሙሉ እንደጅል ሲጫወቱብኝ የማላውቅ ሞኝ ››ተንሰቅስቆ አለቀሰ…እናትዬው ከተቀመጠችበት ተነሳችና አቅፋ እያባበለች ወደመቀመጫው መለሰችው፡፡
ከተወሰነ የውጥረት ዝምታ በኃላ‹‹አንድ የመጨረሻ ነገር አለ…››አለ አቶ ፍሰሀ፡፡ የሁሉም አይኖች ወደእሱ ዞረ..
‹‹ከዚህ በላይ ምን ቀረ? አለቀ እኮ… ለመስማት ሳልመው የነበረውን ነገር ሁሉ በዝርዝር አስረዳችሁኝ፡፡››
‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው..ልጄ ጁኒዬር በዛን ቀን እናትህንና ስርጉትን ሸኝተህ ስትመጣ ከሰሎሜ ጋር ስናወራ እና ስንጨቃጨቅ የነበረው. ልጄን አታገቢውማ
..አገባዋለው በሚለው ጉዳይ አይደለም››
‹‹እና ታዲያ በምንድነው?››ጁኒዬር በመገረም ጠየቀ፡፡
‹‹ይሄንን እውነት ስነግራችሁ ሁላችሁም ከህይወታችሁ አንቅራችሁ እንደምትተፉኝ አውቃለው …ይሁን እንጂ በዚህ ለሊት እግዚያብሄር ሁለቴ ከሞት ደጃፍ አድርሶ የመለሰኝ እውነቱን ተናግሬ ንሰሀ እንድገባ ነው….ስለዚህ ነግራችኃላው…የሚያምም ቢሆን ስሙኝ፡፡አለም አንቺ የጎበና ልጅ አይደለሽም…››በቤቱ ሌላ ድንጋጤ..ተበተነ፡፡
‹‹ከዚህ በፊት ዲቃላ ነሽ አላችሁኝ ..አሁን ደግሞ ያንኑ ዲቃላነቴን ልትነጥቁኝ ነው?ይሄስ ምን ማለት ነው?››
‹‹ገመዶ ትዝ ይልህ እንደሆነ አንጃ እሷ በዛን ክረምት ለአንተም ሆነ ለማንም ሳትናገር ወደኮፈሌ ድንገት ብን ብላ ነው የሄደችው…ምክያቱም በማታውቀው ሰው ተደፍራ ነበር፡፡››
‹‹ምን? ማለት?››ዜናው ቤቱ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉ የሚያደነዝዝ ነበር፡፡
‹‹አዎ እኛ ቤት የጁኒዬር የ19 ዓመት የልደት በዓል ዝግጅት ነበር…ትልቅ ድግስ ነበር…ወጣቶች ሲጠጡና ሲጨፍሩ ውለው ሲጨፍሩ ነበር ያመሹት…..እሷ ቤታችን እቤቷ ስለሆነ ጓዲያ ጎድጓዳውን ታውቀዋለች…ለሊት ሰባት ሰዓት አካባቢ ሁኔታው እንዴት እንደሆነ እና የለማና አየጠፋ ነገር እንዳለ ለማየት ከመኝታ ቤቴ ወጣሁና ሳሎን ሄጂ ነገሮችን ተመልክቼ ስመለስ ከእንግዳ ክፍሎች መካከል አንዱን ገርበብ ብሎ ተከፍቷል
..የሆነ ነገር ትኩረቴን ሳበውና ተጠግቼ ገፋ ሳደርገው ተከፈተ፡፡ አልጋው ላይ ከላይ ሰሎሜ ተዘርራ ተኝታ ነበር…በጣም እንደሰከረች ከሁኔታዋ ማየት ይቻላል..ቀሚሷ ወደላይ ተገልቦ ጭኗ ክፉኛ ተጋልጧል…፡፡መልሼ በራፉን ዘጋሁና ወደመኝታ ቤቴ ሄድኩ .የዛን ጊዜ ሳራ ያማት ስለነበረ ለብቻዋ ነበር የምትተኛው፡፡ከዛ የተጋለጠ ጭኖ ከህሊናዬ ሊጠፋ አልቻለም…ስጋለበጥ ከቆየው በኃላ ተመልሼ ሄድኩና ሰው በኮሪደር ላይ አለመኖሩን አረጋግጬ ወደክፍሉ ገባው፣ ከውስጥ ቀረቀርኩት መብራቱን አጠፋው… ከዛ በኃላ
ያለውን ዝርዝሩል ልነግራችሁ አልችልም…ብቻ ማን እንደደፈራት ባታውቅም መደፈራን ግን አውቃ ስለነበረ በብስጭትና በእፍረት በማግስቱ ከተማውን ለቃ ወደኮፈሌ እንደሄደች ሰማው…በእውነቱ ከፊቴ ዞር ስላለች እፎይ ነበር ያልኩት….ከሁለት ነው ከሶስት ወር በኃላ መልሳ መጣች….አሁንም ትንሽ ቆይታ መሄዷን ሳማው..ከዛ ማርገዞን እና ልታገባ መሆኑን ተወራ…ቀኑ ተጠብቆ አንቺ ተወለድሽ ..ቀኑን እስልቼ ስቆጥረው ትክክል ነበር ..የእኔ ልጅ መሆንሽን ባውቅም ለማንም መናገር የምችለው ነገር አልነበረም፡፡የዛን ቀን ልጄ ቀለበት ሊያስርላት መሆኑን ሲነግረኝ ግድ እሷን ከዛ ጋብቻ ላስቆም ብዬ የልጅሽ አባት ጎባና እንዳልሆነ ታውቂያለሽ አይደል?››ስላት
‹‹እኔስ አዎ እናት ስለሆንኩ አውቃለው..አንተ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?›› አለችኝ፡፡
‹‹እኔም አባት ስለሆንኩ ነው ላውቅ የቻልኩት ብዬ ታሪኩን በዝርዝር ስነግራት አበደች…በዛ እየተጨቃጨቅን እያለ ጁኒዬር ተመልሶ መጣ ..እንግዲህ ከጠጣችው መርዝ ጋር ከእኔ የሰማችው ዜና ምን ያህል አእምሮዋን እንደሚያስታት መገመት ቀላል ነው…እና እዚህ ዋናው ወንጀለኛ እኔ ነኝ…››
‹‹እና አንተ ..አባቴ…››አለም በተጎተተ ቃላት ከአደበቷ በግድ አወጣች፡፡
‹‹አዎ እኔ አባትሽ….ይሄንንም አሁን ወደእዚህ ከመጣሽ በኃላ በሚስጥር ሳታውቂ እኛ ቤት መጥተሸ የጠጣሽበትን ብርጭቆ በመውሰድ ዲኤንኤ በማሰራት አረጋግጬለው፡፡ እና…››ብሎ ሊቀጥል ሲል አለም ዥው ብላ በተቀመጠችበት እራሷን ስታ ወደኃላዋ ተዘረረች፡፡
‹‹ወይኔ ልጄን..አቶ ፍሰሀ ተስፈንጥሮ ስሯ ደርሶ ደገፋት….ጁኒዬር ተከተለው፡፡ገመዶ ግን ከአቶ ፍሰሀ በሰማው ነገር ደንዝዞ ሰውነቱ ሁሉ እየተንቀጠቀጠበት ነው…‹‹እጅህን ወደጎንህ ላክና ሽጉጥህን መዥረጥ አድርገህ ከአለም በስተቀር እዚህ ቤት ያሉትን ሀጥያተኞች ሁሉ ግንባር ግንባራቸውን በልና ከዛ ራስህንም ገላግለህ ለዚህች ሚስኪን ልጅ ፍትህ አስገኝላት›› የሚል ስሜት ይታናነቀው ነበር፡፡ወዲያው ከጎኑ የነበረችው ሳራ ልክ እንደአለም የሰማችውን ዜና መቋቋም አቅቷት እራሷን በመሳት ከመቀመጫዋ ተንሸራተተችና እላዩ ላይ ተዘረገፈችበት፡፡
✨ተፈፀመ✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ኩማንደሩ አንገቱን ከማቀርቀር ውጭ ምንም አልመለሰለትም፡፡
‹‹ምን አይነት ጅል ኖሬያለው…አባቴና የልብ ጓደኛዬ እድሜዬን ሙሉ እንደጅል ሲጫወቱብኝ የማላውቅ ሞኝ ››ተንሰቅስቆ አለቀሰ…እናትዬው ከተቀመጠችበት ተነሳችና አቅፋ እያባበለች ወደመቀመጫው መለሰችው፡፡
ከተወሰነ የውጥረት ዝምታ በኃላ‹‹አንድ የመጨረሻ ነገር አለ…››አለ አቶ ፍሰሀ፡፡ የሁሉም አይኖች ወደእሱ ዞረ..
‹‹ከዚህ በላይ ምን ቀረ? አለቀ እኮ… ለመስማት ሳልመው የነበረውን ነገር ሁሉ በዝርዝር አስረዳችሁኝ፡፡››
‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው..ልጄ ጁኒዬር በዛን ቀን እናትህንና ስርጉትን ሸኝተህ ስትመጣ ከሰሎሜ ጋር ስናወራ እና ስንጨቃጨቅ የነበረው. ልጄን አታገቢውማ
..አገባዋለው በሚለው ጉዳይ አይደለም››
‹‹እና ታዲያ በምንድነው?››ጁኒዬር በመገረም ጠየቀ፡፡
‹‹ይሄንን እውነት ስነግራችሁ ሁላችሁም ከህይወታችሁ አንቅራችሁ እንደምትተፉኝ አውቃለው …ይሁን እንጂ በዚህ ለሊት እግዚያብሄር ሁለቴ ከሞት ደጃፍ አድርሶ የመለሰኝ እውነቱን ተናግሬ ንሰሀ እንድገባ ነው….ስለዚህ ነግራችኃላው…የሚያምም ቢሆን ስሙኝ፡፡አለም አንቺ የጎበና ልጅ አይደለሽም…››በቤቱ ሌላ ድንጋጤ..ተበተነ፡፡
‹‹ከዚህ በፊት ዲቃላ ነሽ አላችሁኝ ..አሁን ደግሞ ያንኑ ዲቃላነቴን ልትነጥቁኝ ነው?ይሄስ ምን ማለት ነው?››
‹‹ገመዶ ትዝ ይልህ እንደሆነ አንጃ እሷ በዛን ክረምት ለአንተም ሆነ ለማንም ሳትናገር ወደኮፈሌ ድንገት ብን ብላ ነው የሄደችው…ምክያቱም በማታውቀው ሰው ተደፍራ ነበር፡፡››
‹‹ምን? ማለት?››ዜናው ቤቱ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉ የሚያደነዝዝ ነበር፡፡
‹‹አዎ እኛ ቤት የጁኒዬር የ19 ዓመት የልደት በዓል ዝግጅት ነበር…ትልቅ ድግስ ነበር…ወጣቶች ሲጠጡና ሲጨፍሩ ውለው ሲጨፍሩ ነበር ያመሹት…..እሷ ቤታችን እቤቷ ስለሆነ ጓዲያ ጎድጓዳውን ታውቀዋለች…ለሊት ሰባት ሰዓት አካባቢ ሁኔታው እንዴት እንደሆነ እና የለማና አየጠፋ ነገር እንዳለ ለማየት ከመኝታ ቤቴ ወጣሁና ሳሎን ሄጂ ነገሮችን ተመልክቼ ስመለስ ከእንግዳ ክፍሎች መካከል አንዱን ገርበብ ብሎ ተከፍቷል
..የሆነ ነገር ትኩረቴን ሳበውና ተጠግቼ ገፋ ሳደርገው ተከፈተ፡፡ አልጋው ላይ ከላይ ሰሎሜ ተዘርራ ተኝታ ነበር…በጣም እንደሰከረች ከሁኔታዋ ማየት ይቻላል..ቀሚሷ ወደላይ ተገልቦ ጭኗ ክፉኛ ተጋልጧል…፡፡መልሼ በራፉን ዘጋሁና ወደመኝታ ቤቴ ሄድኩ .የዛን ጊዜ ሳራ ያማት ስለነበረ ለብቻዋ ነበር የምትተኛው፡፡ከዛ የተጋለጠ ጭኖ ከህሊናዬ ሊጠፋ አልቻለም…ስጋለበጥ ከቆየው በኃላ ተመልሼ ሄድኩና ሰው በኮሪደር ላይ አለመኖሩን አረጋግጬ ወደክፍሉ ገባው፣ ከውስጥ ቀረቀርኩት መብራቱን አጠፋው… ከዛ በኃላ
ያለውን ዝርዝሩል ልነግራችሁ አልችልም…ብቻ ማን እንደደፈራት ባታውቅም መደፈራን ግን አውቃ ስለነበረ በብስጭትና በእፍረት በማግስቱ ከተማውን ለቃ ወደኮፈሌ እንደሄደች ሰማው…በእውነቱ ከፊቴ ዞር ስላለች እፎይ ነበር ያልኩት….ከሁለት ነው ከሶስት ወር በኃላ መልሳ መጣች….አሁንም ትንሽ ቆይታ መሄዷን ሳማው..ከዛ ማርገዞን እና ልታገባ መሆኑን ተወራ…ቀኑ ተጠብቆ አንቺ ተወለድሽ ..ቀኑን እስልቼ ስቆጥረው ትክክል ነበር ..የእኔ ልጅ መሆንሽን ባውቅም ለማንም መናገር የምችለው ነገር አልነበረም፡፡የዛን ቀን ልጄ ቀለበት ሊያስርላት መሆኑን ሲነግረኝ ግድ እሷን ከዛ ጋብቻ ላስቆም ብዬ የልጅሽ አባት ጎባና እንዳልሆነ ታውቂያለሽ አይደል?››ስላት
‹‹እኔስ አዎ እናት ስለሆንኩ አውቃለው..አንተ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?›› አለችኝ፡፡
‹‹እኔም አባት ስለሆንኩ ነው ላውቅ የቻልኩት ብዬ ታሪኩን በዝርዝር ስነግራት አበደች…በዛ እየተጨቃጨቅን እያለ ጁኒዬር ተመልሶ መጣ ..እንግዲህ ከጠጣችው መርዝ ጋር ከእኔ የሰማችው ዜና ምን ያህል አእምሮዋን እንደሚያስታት መገመት ቀላል ነው…እና እዚህ ዋናው ወንጀለኛ እኔ ነኝ…››
‹‹እና አንተ ..አባቴ…››አለም በተጎተተ ቃላት ከአደበቷ በግድ አወጣች፡፡
‹‹አዎ እኔ አባትሽ….ይሄንንም አሁን ወደእዚህ ከመጣሽ በኃላ በሚስጥር ሳታውቂ እኛ ቤት መጥተሸ የጠጣሽበትን ብርጭቆ በመውሰድ ዲኤንኤ በማሰራት አረጋግጬለው፡፡ እና…››ብሎ ሊቀጥል ሲል አለም ዥው ብላ በተቀመጠችበት እራሷን ስታ ወደኃላዋ ተዘረረች፡፡
‹‹ወይኔ ልጄን..አቶ ፍሰሀ ተስፈንጥሮ ስሯ ደርሶ ደገፋት….ጁኒዬር ተከተለው፡፡ገመዶ ግን ከአቶ ፍሰሀ በሰማው ነገር ደንዝዞ ሰውነቱ ሁሉ እየተንቀጠቀጠበት ነው…‹‹እጅህን ወደጎንህ ላክና ሽጉጥህን መዥረጥ አድርገህ ከአለም በስተቀር እዚህ ቤት ያሉትን ሀጥያተኞች ሁሉ ግንባር ግንባራቸውን በልና ከዛ ራስህንም ገላግለህ ለዚህች ሚስኪን ልጅ ፍትህ አስገኝላት›› የሚል ስሜት ይታናነቀው ነበር፡፡ወዲያው ከጎኑ የነበረችው ሳራ ልክ እንደአለም የሰማችውን ዜና መቋቋም አቅቷት እራሷን በመሳት ከመቀመጫዋ ተንሸራተተችና እላዩ ላይ ተዘረገፈችበት፡፡
✨ተፈፀመ✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤58👎27🤔11👍9🔥1
ካቲካላ የለም ፤ ከዛሬ ጀምሮ!
ለምን?
መለኪያ ተሰብሮ።
ብለሽ
ደሞ መሸጥ ቀጠልሽ
ጥያቄ...
መለኪያሽ ነው እንጂ የተሰባበረው፣ ካቲካላሽማ... በርሜሉን ሙሉ ነው።
ይሄንን ስትሰሚ
እንዳትገረሚ።
መኮመሪያ ቤትሽ መስፈሪያ የጣለ
ባገኘው ይለካል ያገኘውን ኹሉ ልኬት ነው እያለ፡፡
እረ ያንቺስ እውነት ፣ ልኩን ያሳጣሽው፣
በምን ለክተሽ ነው...
አንድ አረቄ እያሉ ፣ በርሜል የጨረሽው?
መለኪያሽን ዐየሽ ፣ ንቀሽው ተሰብሮ፤
በዋጋ ያጣላል ፤ ልክ የሌለው ኑሮ።
ለዋጋሽ መለኪያ፤
ለስካር መለኪያ፤
ለማወቅ መለኪያ፤ ጠፍቶሽ እንዳሰምጪ፤
አረቄሽን ዘግተሽ ፣ መለኪያሽን አውጪ።
ተይ በልክ ቅጂ
ተይ በልክ ቅጂ
ተይ በልክ ቅጂ...
ቀጥ ብለው እየገቡ ፣ ሲወጡ በዳዴ፣
በምን ሰጠሻቸው ፣ ሰከሩልሽ ባንዴ።
የአረቄሽ ሞገስ.…
ሰው እየመሰለው ፣ ዐይኑ ደም ሲቀላ፣
ገዳም ናት ይልሻል ፤ ሰው ቤትሽ ሲሞላ።
ገድሽ መለኪያሽ ነው! የተሰበረልሽ፤
አትሰሰትም ብሎ ፣ ሰው የሚያመጣልሽ።
ሀገሬው ሀገርሽ ፣ስስት ከመለካት ተደበላልቆበት፣
የሚለካን ኹሉ ስስታም የሚል ስም ወስዶ ለጠፈበት።
ተይ በልክ ቅጂ
ተይ በልክ ቅጂ...
ማይለካ አረቄ ፣ እያደልሽው በገፍ፣
ሀገር ሰከረልሽ ፤ በምኑ ይደገፍ?
ተይ በልክ ቅጂ፣
ጤነኛውስ ይኹን ፤ እብድ አታስብጂ።
ተይ በልክ ቅጂ!!!
🔘ኤልያስ ሽታሁን🔘
ለምን?
መለኪያ ተሰብሮ።
ብለሽ
ደሞ መሸጥ ቀጠልሽ
ጥያቄ...
መለኪያሽ ነው እንጂ የተሰባበረው፣ ካቲካላሽማ... በርሜሉን ሙሉ ነው።
ይሄንን ስትሰሚ
እንዳትገረሚ።
መኮመሪያ ቤትሽ መስፈሪያ የጣለ
ባገኘው ይለካል ያገኘውን ኹሉ ልኬት ነው እያለ፡፡
እረ ያንቺስ እውነት ፣ ልኩን ያሳጣሽው፣
በምን ለክተሽ ነው...
አንድ አረቄ እያሉ ፣ በርሜል የጨረሽው?
መለኪያሽን ዐየሽ ፣ ንቀሽው ተሰብሮ፤
በዋጋ ያጣላል ፤ ልክ የሌለው ኑሮ።
ለዋጋሽ መለኪያ፤
ለስካር መለኪያ፤
ለማወቅ መለኪያ፤ ጠፍቶሽ እንዳሰምጪ፤
አረቄሽን ዘግተሽ ፣ መለኪያሽን አውጪ።
ተይ በልክ ቅጂ
ተይ በልክ ቅጂ
ተይ በልክ ቅጂ...
ቀጥ ብለው እየገቡ ፣ ሲወጡ በዳዴ፣
በምን ሰጠሻቸው ፣ ሰከሩልሽ ባንዴ።
የአረቄሽ ሞገስ.…
ሰው እየመሰለው ፣ ዐይኑ ደም ሲቀላ፣
ገዳም ናት ይልሻል ፤ ሰው ቤትሽ ሲሞላ።
ገድሽ መለኪያሽ ነው! የተሰበረልሽ፤
አትሰሰትም ብሎ ፣ ሰው የሚያመጣልሽ።
ሀገሬው ሀገርሽ ፣ስስት ከመለካት ተደበላልቆበት፣
የሚለካን ኹሉ ስስታም የሚል ስም ወስዶ ለጠፈበት።
ተይ በልክ ቅጂ
ተይ በልክ ቅጂ...
ማይለካ አረቄ ፣ እያደልሽው በገፍ፣
ሀገር ሰከረልሽ ፤ በምኑ ይደገፍ?
ተይ በልክ ቅጂ፣
ጤነኛውስ ይኹን ፤ እብድ አታስብጂ።
ተይ በልክ ቅጂ!!!
🔘ኤልያስ ሽታሁን🔘
❤25👏2
#ማበድ_ይሻላል
አእምሮዋን ያማታል፤ ሃና ትባላለች። በኮሮኮንቹ፣ በአቋራጭ፣ በድልድዩ በኩል አልፋ ቤታችን ትመጣለች፤ ስትመጣ ሰዓት አትመርጥም። የአቅሜን ለማንም ሳልናገር እንድትድን ጥሬያለሁ፤ አልተሳካልኝም እንጂ። መዳኗ በእኔ እንዲሆን አልተመረጠም ወይም ከነጭራሹ እንድትድን አልተፈቀደም።
አንዳንድ ቀን መጥታ በሩን በኃይል ስታንኳኳ ልጄ ከእንቅልፉ ይባንናል። በር የሚከፍት ሲጠፋ በጓሮ ያለውን መስኮት
በድንጋይ ስታንኳኳ መሰለኝ አራት ያህል ጊዜ ሰብራዋለች። በሃኒቾ አልናደድም፤ ይልቅ ይበልጥ ታሳዝነኛለች። ባለቤቴ ግን በእሷ ጉዳይ ሆደ ሰፊነቴ ይገርማታል።
አንድ ዕለት ከእኛ የተረፈ ምግብ ልትሰጣት ስትል ገላምጬ አዲስ ያልተነካካ ምግብ እንድትሰጣት ስነግራት፣ አገለማመጤ ከዚህ በፊት ያላየችው ዓይነት ስለነበር ቅሬታ ልቧ ውስጥ ለሳምንት ያህል ተቀርቅሮባት እንደነበርአስታውሳለሁ።
አንዳንዴ ትክ ብላ ስታየኝ "ሃኒቾ ደህና ነሽ?" ስላት አንገቷን በአዎንታ ትነቀንቃለች። አይኗ ያሳዝናል። አይኗ ሁሉ ነገሯን የሚናገርባት ፍጡር ናት፤ አይኗ ስሜቷን ማንጸባረቂያ መስታወቷ ነውና ሁሉን ከአይኗ አገኘዋለሁ። ሃኒቾን አይቻት ከራባት ቃል ባታወጣ እንኳ አውቃለሁ።
አንድም በልጅነቴ ረሃብን የታናሽ የወንድሜን ያህል በቅርበት ስለማውቀው የራበውን ሰው ትክ ብዬ ማየት አልችልም፤ አጎነብሳለሁ፤ ክፉ ትዝታዬን ይቀሰቅስብኛል። ክፉ ትውስታችንን የሚያስታውሰውን የአእምሮ ክፍል በሆነ ጥበብ ማደንዝዝ ቢቻለን ብዬ አንዳንዴ እመኛለሁ።
ሁለተኛ ሃኒቾን አውቃታለሁና መራቧን አይቻት ባውቅ አይገርምም።
መንገድ ሳገኛት አሊያም ቤታችን ስትመጣ
"ደህና ነህ እዩ”
“ደህና ነኝ”
“አንቺ እንዴት ነሽ?” ስላት ጭንቅላቷን ደህና ነኝ ለማለት ትነቀንቃለች፤ ከዛ ውጪ ሌላ ምንም አትልም።
ባለቤቴ ሰፈሩን፣ ቤታችንን ጠላችው። በእሷ ጉዳይ ከእኔ ጋ ተያይዞ የሚነዛው ወሬ አወካት፤ በሌሊት እየመጣች እዩ ምግብ ስጠኝ የምትለው፤ በር የሚከፍት ሲጠፋ በጀርባ መስኮት የምትሰብረው ነገር ታከታትና ባልተለመደ ሁኔታ ልትቀና ይቃጣት ጀመር። ባመመው የቀና ሰው ካመመው ሰው በምን ይሻላል እላለሁ በልቤ። ከሚስቴ ጋር በሃኒቾ ጉዳይ ተጎረባበጥን፤ በር በኃይል ስታንኳኳ የልጄን መበርገግ መልመድ አልቻልንም።
አንድ ጠማማ ቀን
ድብርት እንደ ነጭናጫ ሕፃን ልጅ ሱሪዬን ይዞ ሙጭጭያለበትን ውሎ አሳልፌ ቤቴ ገባሁ። ልጄ ባለመተኛቱ መግባቴን እንዳየ አባ እያለ ደስታ ፊቱ ላይ ተጥለቀለቀ። አንድ ቀን እንደ ዘላለም በሆነበት የትግል መንደር ለመውደቅ ጥንጥ ቀርቶኝ እቤት ስደርስ አባ... አባ የሚለኝ የልጄ ቃል ነው እጅ የማያሰጠኝ። የልጄን ጉንጩን፣ ግንባሩን፣ አንገቱን፤ የሚስቴን ጉንጭ ስሜ እራት እንደማልበላ ለሚስቴ ነግሬ ወደ መኝታ በቴ ሳመራ ባለቤቴ ገጼን እያየች “ውሎ እንዴት ነበር?" ስትለኝ ማለት የቻልኩት አድካሚ ነበር ብቻ ነው።
David Darybyshire Bad Day
It's seems on some days
The whole world is against you You feel really down, in a haze
How long do have to feel blue
እንዲል... አንዳንድ ቀን ይደብራል። አውጥተን፣ አውርደን ያቀድነው ይከሽፋል፤ ተስፋ ያደረግነው ይዘምማል። ዕድለኛ ያልመሆን ስሜት ውስጣችን ይርመሰምሳል፤ ኋላ የመቅረት ስሜት ይላፋናል፤ በአጠቃላይ ዛሬ ጥሩ የሚባል ቀን አላሳለፍኩም።
ሹልክ ብዩ አልጋዬ ላይ ጋደም እንዳልኩ በስንት መገላበጥ እንቅልፍ ሸለብ እንዳደረገኝ፤ በሩ ከዚህ ቀደም ተደብድቦ ከሚያውቀው በላይ በኃይል ተደበደበ። ባንኜ፣ ተንደርድሬ
ሃኒቾ ነች፤ አመድማ፣ ግራ የገባው ፊት እንዳየሁ ፍንትው ብሎልኛል።
በሩን እንደከፈትኩት እያጉረጠረጥኩ ፊቴን አጠይፌ እ ምንድን ነው ሕይወቴን የምታከብጂው? እንዴ......!!!! ካለ እኔስ ሰው አታውቂም? ሁለተኛ እዚህ ቤት እንዳትመጪ..... አልኳት። የሌባ ጣቴን ፊቷ ላይ ደቅኜ እያውለበለብኩባት… ተናግርያለሁ!! እንዳልኩ አስታውሳለሁ።
ትክ ብላ አይታኝ በዝግታ አጎነበሰች። ቀና ብላ አየችኝ፤ ቀና ብላ ስታየኝ አይኖቿ እንባ አርግዘው ነበር። ቀስ ብላ አንገቷን ወደ መሬት ቀብራ፣ መሬት መሬት እያየች በዝግታ ትንሽ ወደፊት እንደተራመደች እሳት ለብሼ ፊቴን አጨፍግጌ ባለቤቴ ከኋላዬ እንደቆመች ዞራ ተመለከተችን አይኗ ያረገዘውን እንባ እያፈሰሰ ነበር።
አስተያየቷ፣ እንባዋ፣ አዟዟሯ ቢያሳዝነኝም ማዘኔን ፊት ነስቼ ፊቴን አዙሬ ወደ ቤቴ ገባሁ። ቀጥታ ወደ አልጋዬ ሄጄ ተመልሼ ተንጋለልኩ። እንደቅድሙ ማሸለብ አልቻልኩም እንጂ። እንባዋ፣ አስተያየቷ፣ አጎነባበሷ አንጀቴን በላው። አንሶላ ውስጥ ገብቼ እንደበደለ ሳይሆን እንደተበደለ፤ እንደጮኸ ሳይሆን እንደተጮኸበት፤ እንዳባረረ ሳይሆን እንደተባረረ ሆኜ አለቀስኩ።
ሃኒቾ ለእኔ ምን እንደሆነች የነበረንን ቁርኝትም የሰፈሩ ሰው ሁሉ በደንብ ያውቃል። ሚስቴ ይሄን ስለምታውቅ ነው እንደልቧ የማትናገረው፤ ይሄን ስለምታውቅ ነው ሐዘኔታዬ ላይ ቅናት የሚጣባት።
ሃኒቾ ታሪኬ ናት። ዋናው ታሪኬ እሷ ጋ ነው ያለው፡፡ እጮኛሞቾች ነበርን። አንድ ሸበጥ ለሁለት አድርገናል፤ ቤተሰብ አብሮነታችንን ጠልቶ ሊለያየን ሞክሮ አልሳካ ብሎት ያውቃል፤ በክፉ ካያት ጋ ለእሷ ተቆርቁሬ ተጣልቼላት አውቃለሁ፤ ጎድሎብኝ ሰርቃ ሞልታልኛለች፤ ለምና ተቀብላ ሰጥታኝ ታውቃለች፤ ኪሴ ኪሷ፣ ኪሷ ኪሴ ነበር።
ከእሷ የበለጠ ችስታ ስለነበርኩ ከእኔ በላይ እሷ ለእኔ ሆናልኛለች። ከሁሉ ሰው በላይ ስለምወዳት መንሰፍሰፌን በኩራት ነበር በየአጋጣሚው የምለፍፈው። እሷ ጋ ስሆን ቁጥብነቴ በስሱ ይተናል፤ ፍላጎት እና ገጠመኜን ከሌላው በተለየ እተነፍሳለሁ።
ትዝብት እና ፍርሃቴን አጋራታለሁ፤ እሷ ጋ ሆኜ ስደሰት ፈንጠዝያዬ ማንም እንደሌለ ዓይነት ነበር። ገመናዬን
ነግሬያታለሁ፤ ገመናዋን ነግራኛለች፤
ገበናችንን ተገላልጠናል፤ መተዋወቃችን ነው የሚያገማምተን። አንድ ዕለት አበሳጭታኝ ሁለተኛ አጠገቤ እንዳትደርሺ ስላት ፈገግ እያለች
“በኋላ ስታስሰኝ ትውላለህ“
“አታውቂኝም!!"
በእርግጥ እንዳለችው በቶሎ የዛኑ ቀን አላሰስኳትም፤ ከሁለት ቀን በላይ ግን : መሻገር አልተቻለኝም፤ ትዕቢት ተናነቀኝ። ፍቅሬ ከትዕቢቴ ስለሚበልጥ አይኔን በጨው አጥቤ አገኝቻታለሁ፤ ፍቅራችን አይናችን ውስጥ ይጮህ ነበር። እሷን ባለማግኘቴ ምክንያት ተጭኖኝ የነበረው ድብርት በነነ፤ ልትመጣ ስትል እንደመጣሁ መደበቅ አልተቻላትም::
ሃኒቾ ቶሎ ቶሎ ታኮርፍ ነበር፤ እኔ መኳረፍ ጭንቅ የሚለኝ ሰው ነኝ። መለማመጥ ስለማልወድ እንድታዋራኝ ቀልብ ገዝቶ ኩርፊያዋን ለማርገፍ ድራማ ፈጥሬ እተውናለሁ፤ ማኩረፏን ረስታ ቀልቧን ትሰጠኛለች፤ መቅደድ እንጀምራለን።
ደግሞ ትቀና ነበር፤ መቅናቷን በሁኔታዋ ነው የምትገልጸው፤ ትገባኛለች። ሳትጠይቀኝ የቀናችበት የመሰለኝን ጉዳይ አብራራላታለሁ፤ ቀስ ብላ ፍትት ትላለች፤ ፈገግ ስል
“ምን ያስቃሃል?" ትላለች።
ሰውነቷን ለልፊያ እያዘጋጀች የበለጠ አፌን ከፍቼ ስስቅ ትላፋኛለች፤ እላፋታለሁ።
ስስ ነበረች። እሷ በቶሎ ስለምትከፋ እኔም በትንሽ እንዳልከፋባት ይደብረዋል የምትለውን ነገር ላለማድረግ ትጥራለች።
ትንሽ ነገር ይረብሻታል፤ ሲጨንቃት አቅፋታለሁ፤ እጄን ጸጉሯ ላይ እያንሸረሸርኩ ሁሉም ነገር ይስተካከላል፣ ከባድ አይደለም፤ ደግሞ አምላክ ይረዳናል እላታለሁ፤ እርጋታ ሲያጥለቀልቃት ይሰማኛል።
አእምሮዋን ያማታል፤ ሃና ትባላለች። በኮሮኮንቹ፣ በአቋራጭ፣ በድልድዩ በኩል አልፋ ቤታችን ትመጣለች፤ ስትመጣ ሰዓት አትመርጥም። የአቅሜን ለማንም ሳልናገር እንድትድን ጥሬያለሁ፤ አልተሳካልኝም እንጂ። መዳኗ በእኔ እንዲሆን አልተመረጠም ወይም ከነጭራሹ እንድትድን አልተፈቀደም።
አንዳንድ ቀን መጥታ በሩን በኃይል ስታንኳኳ ልጄ ከእንቅልፉ ይባንናል። በር የሚከፍት ሲጠፋ በጓሮ ያለውን መስኮት
በድንጋይ ስታንኳኳ መሰለኝ አራት ያህል ጊዜ ሰብራዋለች። በሃኒቾ አልናደድም፤ ይልቅ ይበልጥ ታሳዝነኛለች። ባለቤቴ ግን በእሷ ጉዳይ ሆደ ሰፊነቴ ይገርማታል።
አንድ ዕለት ከእኛ የተረፈ ምግብ ልትሰጣት ስትል ገላምጬ አዲስ ያልተነካካ ምግብ እንድትሰጣት ስነግራት፣ አገለማመጤ ከዚህ በፊት ያላየችው ዓይነት ስለነበር ቅሬታ ልቧ ውስጥ ለሳምንት ያህል ተቀርቅሮባት እንደነበርአስታውሳለሁ።
አንዳንዴ ትክ ብላ ስታየኝ "ሃኒቾ ደህና ነሽ?" ስላት አንገቷን በአዎንታ ትነቀንቃለች። አይኗ ያሳዝናል። አይኗ ሁሉ ነገሯን የሚናገርባት ፍጡር ናት፤ አይኗ ስሜቷን ማንጸባረቂያ መስታወቷ ነውና ሁሉን ከአይኗ አገኘዋለሁ። ሃኒቾን አይቻት ከራባት ቃል ባታወጣ እንኳ አውቃለሁ።
አንድም በልጅነቴ ረሃብን የታናሽ የወንድሜን ያህል በቅርበት ስለማውቀው የራበውን ሰው ትክ ብዬ ማየት አልችልም፤ አጎነብሳለሁ፤ ክፉ ትዝታዬን ይቀሰቅስብኛል። ክፉ ትውስታችንን የሚያስታውሰውን የአእምሮ ክፍል በሆነ ጥበብ ማደንዝዝ ቢቻለን ብዬ አንዳንዴ እመኛለሁ።
ሁለተኛ ሃኒቾን አውቃታለሁና መራቧን አይቻት ባውቅ አይገርምም።
መንገድ ሳገኛት አሊያም ቤታችን ስትመጣ
"ደህና ነህ እዩ”
“ደህና ነኝ”
“አንቺ እንዴት ነሽ?” ስላት ጭንቅላቷን ደህና ነኝ ለማለት ትነቀንቃለች፤ ከዛ ውጪ ሌላ ምንም አትልም።
ባለቤቴ ሰፈሩን፣ ቤታችንን ጠላችው። በእሷ ጉዳይ ከእኔ ጋ ተያይዞ የሚነዛው ወሬ አወካት፤ በሌሊት እየመጣች እዩ ምግብ ስጠኝ የምትለው፤ በር የሚከፍት ሲጠፋ በጀርባ መስኮት የምትሰብረው ነገር ታከታትና ባልተለመደ ሁኔታ ልትቀና ይቃጣት ጀመር። ባመመው የቀና ሰው ካመመው ሰው በምን ይሻላል እላለሁ በልቤ። ከሚስቴ ጋር በሃኒቾ ጉዳይ ተጎረባበጥን፤ በር በኃይል ስታንኳኳ የልጄን መበርገግ መልመድ አልቻልንም።
አንድ ጠማማ ቀን
ድብርት እንደ ነጭናጫ ሕፃን ልጅ ሱሪዬን ይዞ ሙጭጭያለበትን ውሎ አሳልፌ ቤቴ ገባሁ። ልጄ ባለመተኛቱ መግባቴን እንዳየ አባ እያለ ደስታ ፊቱ ላይ ተጥለቀለቀ። አንድ ቀን እንደ ዘላለም በሆነበት የትግል መንደር ለመውደቅ ጥንጥ ቀርቶኝ እቤት ስደርስ አባ... አባ የሚለኝ የልጄ ቃል ነው እጅ የማያሰጠኝ። የልጄን ጉንጩን፣ ግንባሩን፣ አንገቱን፤ የሚስቴን ጉንጭ ስሜ እራት እንደማልበላ ለሚስቴ ነግሬ ወደ መኝታ በቴ ሳመራ ባለቤቴ ገጼን እያየች “ውሎ እንዴት ነበር?" ስትለኝ ማለት የቻልኩት አድካሚ ነበር ብቻ ነው።
David Darybyshire Bad Day
It's seems on some days
The whole world is against you You feel really down, in a haze
How long do have to feel blue
እንዲል... አንዳንድ ቀን ይደብራል። አውጥተን፣ አውርደን ያቀድነው ይከሽፋል፤ ተስፋ ያደረግነው ይዘምማል። ዕድለኛ ያልመሆን ስሜት ውስጣችን ይርመሰምሳል፤ ኋላ የመቅረት ስሜት ይላፋናል፤ በአጠቃላይ ዛሬ ጥሩ የሚባል ቀን አላሳለፍኩም።
ሹልክ ብዩ አልጋዬ ላይ ጋደም እንዳልኩ በስንት መገላበጥ እንቅልፍ ሸለብ እንዳደረገኝ፤ በሩ ከዚህ ቀደም ተደብድቦ ከሚያውቀው በላይ በኃይል ተደበደበ። ባንኜ፣ ተንደርድሬ
ሃኒቾ ነች፤ አመድማ፣ ግራ የገባው ፊት እንዳየሁ ፍንትው ብሎልኛል።
በሩን እንደከፈትኩት እያጉረጠረጥኩ ፊቴን አጠይፌ እ ምንድን ነው ሕይወቴን የምታከብጂው? እንዴ......!!!! ካለ እኔስ ሰው አታውቂም? ሁለተኛ እዚህ ቤት እንዳትመጪ..... አልኳት። የሌባ ጣቴን ፊቷ ላይ ደቅኜ እያውለበለብኩባት… ተናግርያለሁ!! እንዳልኩ አስታውሳለሁ።
ትክ ብላ አይታኝ በዝግታ አጎነበሰች። ቀና ብላ አየችኝ፤ ቀና ብላ ስታየኝ አይኖቿ እንባ አርግዘው ነበር። ቀስ ብላ አንገቷን ወደ መሬት ቀብራ፣ መሬት መሬት እያየች በዝግታ ትንሽ ወደፊት እንደተራመደች እሳት ለብሼ ፊቴን አጨፍግጌ ባለቤቴ ከኋላዬ እንደቆመች ዞራ ተመለከተችን አይኗ ያረገዘውን እንባ እያፈሰሰ ነበር።
አስተያየቷ፣ እንባዋ፣ አዟዟሯ ቢያሳዝነኝም ማዘኔን ፊት ነስቼ ፊቴን አዙሬ ወደ ቤቴ ገባሁ። ቀጥታ ወደ አልጋዬ ሄጄ ተመልሼ ተንጋለልኩ። እንደቅድሙ ማሸለብ አልቻልኩም እንጂ። እንባዋ፣ አስተያየቷ፣ አጎነባበሷ አንጀቴን በላው። አንሶላ ውስጥ ገብቼ እንደበደለ ሳይሆን እንደተበደለ፤ እንደጮኸ ሳይሆን እንደተጮኸበት፤ እንዳባረረ ሳይሆን እንደተባረረ ሆኜ አለቀስኩ።
ሃኒቾ ለእኔ ምን እንደሆነች የነበረንን ቁርኝትም የሰፈሩ ሰው ሁሉ በደንብ ያውቃል። ሚስቴ ይሄን ስለምታውቅ ነው እንደልቧ የማትናገረው፤ ይሄን ስለምታውቅ ነው ሐዘኔታዬ ላይ ቅናት የሚጣባት።
ሃኒቾ ታሪኬ ናት። ዋናው ታሪኬ እሷ ጋ ነው ያለው፡፡ እጮኛሞቾች ነበርን። አንድ ሸበጥ ለሁለት አድርገናል፤ ቤተሰብ አብሮነታችንን ጠልቶ ሊለያየን ሞክሮ አልሳካ ብሎት ያውቃል፤ በክፉ ካያት ጋ ለእሷ ተቆርቁሬ ተጣልቼላት አውቃለሁ፤ ጎድሎብኝ ሰርቃ ሞልታልኛለች፤ ለምና ተቀብላ ሰጥታኝ ታውቃለች፤ ኪሴ ኪሷ፣ ኪሷ ኪሴ ነበር።
ከእሷ የበለጠ ችስታ ስለነበርኩ ከእኔ በላይ እሷ ለእኔ ሆናልኛለች። ከሁሉ ሰው በላይ ስለምወዳት መንሰፍሰፌን በኩራት ነበር በየአጋጣሚው የምለፍፈው። እሷ ጋ ስሆን ቁጥብነቴ በስሱ ይተናል፤ ፍላጎት እና ገጠመኜን ከሌላው በተለየ እተነፍሳለሁ።
ትዝብት እና ፍርሃቴን አጋራታለሁ፤ እሷ ጋ ሆኜ ስደሰት ፈንጠዝያዬ ማንም እንደሌለ ዓይነት ነበር። ገመናዬን
ነግሬያታለሁ፤ ገመናዋን ነግራኛለች፤
ገበናችንን ተገላልጠናል፤ መተዋወቃችን ነው የሚያገማምተን። አንድ ዕለት አበሳጭታኝ ሁለተኛ አጠገቤ እንዳትደርሺ ስላት ፈገግ እያለች
“በኋላ ስታስሰኝ ትውላለህ“
“አታውቂኝም!!"
በእርግጥ እንዳለችው በቶሎ የዛኑ ቀን አላሰስኳትም፤ ከሁለት ቀን በላይ ግን : መሻገር አልተቻለኝም፤ ትዕቢት ተናነቀኝ። ፍቅሬ ከትዕቢቴ ስለሚበልጥ አይኔን በጨው አጥቤ አገኝቻታለሁ፤ ፍቅራችን አይናችን ውስጥ ይጮህ ነበር። እሷን ባለማግኘቴ ምክንያት ተጭኖኝ የነበረው ድብርት በነነ፤ ልትመጣ ስትል እንደመጣሁ መደበቅ አልተቻላትም::
ሃኒቾ ቶሎ ቶሎ ታኮርፍ ነበር፤ እኔ መኳረፍ ጭንቅ የሚለኝ ሰው ነኝ። መለማመጥ ስለማልወድ እንድታዋራኝ ቀልብ ገዝቶ ኩርፊያዋን ለማርገፍ ድራማ ፈጥሬ እተውናለሁ፤ ማኩረፏን ረስታ ቀልቧን ትሰጠኛለች፤ መቅደድ እንጀምራለን።
ደግሞ ትቀና ነበር፤ መቅናቷን በሁኔታዋ ነው የምትገልጸው፤ ትገባኛለች። ሳትጠይቀኝ የቀናችበት የመሰለኝን ጉዳይ አብራራላታለሁ፤ ቀስ ብላ ፍትት ትላለች፤ ፈገግ ስል
“ምን ያስቃሃል?" ትላለች።
ሰውነቷን ለልፊያ እያዘጋጀች የበለጠ አፌን ከፍቼ ስስቅ ትላፋኛለች፤ እላፋታለሁ።
ስስ ነበረች። እሷ በቶሎ ስለምትከፋ እኔም በትንሽ እንዳልከፋባት ይደብረዋል የምትለውን ነገር ላለማድረግ ትጥራለች።
ትንሽ ነገር ይረብሻታል፤ ሲጨንቃት አቅፋታለሁ፤ እጄን ጸጉሯ ላይ እያንሸረሸርኩ ሁሉም ነገር ይስተካከላል፣ ከባድ አይደለም፤ ደግሞ አምላክ ይረዳናል እላታለሁ፤ እርጋታ ሲያጥለቀልቃት ይሰማኛል።
❤39👍5🔥2
እንደምትወደኝ ሁኔታዋ ሁሉ፤ እንደምትታመን እንቅስቃሴዋ ሁሉ፤ ከእኔ ጋ መሆን እንደምትፈልግ ሁሉ ነገሯ ያሳብቅባት ነበር!!!
ከነበር በኋላ ምን አለ?
ሃኒቾን የምወዳት በጠይም ቆንጆ ፊቷ አልነበረም፤ የተማረኩት በጥቁር ዞማ ጸጉሯም አልነበረም፤ ያሸነፈችኝ ; በየዋህነቷ ነው። ሃኒቾ ለመድመቅ አለመፍጨርጨሯ ነው። ተፈላጊነቷን ለማሳየት አትዳክርም፤ ያላትን ለማጉላት አትታከክም። ምንም የሌለውም ሰው እንደሚወደድ ያሳየችኝ ሃኒቾ ነበረች።
አንድ ቀን ስለ ውሎዋ ስትነግረኝ ትረካዋን ወደ ጎን ትቼ የተዘናፈለ ዞማ ጸጉሯ፣ እርጋታዋ፣ ወዛም ጠይም ፊቷ ላይ ተመስጬ ቆንጅዬ ልጅ እንደሆንሽ ታውቂያለሽ አይደል? ስላት
ዝም ብላ ፈገግ ብላ እያየችኝ ዝም ስትል
የምር አታውቂም?
“እመቤቴን አላውቅም" እመቤቴን ስትል አማማሏ፣ አይኗ ያሳዝናል
"ማልልኝ እስኪ ቆንጆ ነኝ ግን?"
እስቃለሁ። የዋህ ባትሆን ለቆንጆ ነሽ ማልልኝ ትል ነበር?
ሃኒቾ ማለት ይቺ ነበረች በቃ!!! እሷ እመቤቴን ካለች ስለማትዋሽ ሁሉም እንደዛ ነው የሚመስላት፡፡
የሁሉም መለኪያ የልቡ እውነት እና እምነቱ አይደል?
ሃኒቾ ዘመዶቿ ጋ ክፍለሀገር ስትሄድ፣ ስትመጣ፤ እኔም ክፍለሀገር የእናቴ እህት ማሚቱ ጋ ስሄድ ስመጣ አብሮነታችን እየሳሳ እየሳሳ ሌላ መልመድ ጀመርን። ሳንቆሳሰል፣ መራር ቃል ሳንነጋገር ተራራቅን። አብሮነታችን ሳስቶ በሂደት ተለያየን። ክፍለሀገር ለብዙ ጊዜ ኖሬ፣ ትዳርመስርቼ፣ ልጅ ኖሮኝ ተወልጄ ባደግኩባት ከተማ ተመልሼ ያከራየሁትን የቤተሰቦቼን ቤት አስለቅቄ መኖር ጀመርኩ።
ሃኒቾ አግብታ እንደነበር ነገር ግን ከብዙ ንትርክ፤ ከስንት ታርቆ መጣላት በኋላ፤ ከብዙ የጓደኞች፣ የዘመዶች፣ የሽማግሌዎች እና የቤተሰብ ምክር እና ሽምግልና በኋላ አብሮ መሆን አልሆን ብሏቸው እንደተፋቱ፤ ተቆጪዋ፣ መካሪዋ፣ ተቆርቋሪዋ ታላቅ ወንድሟ ሙሉጌታ ሲነዳው የነበረው አነስተኛ መኪና ከከባድ መኪና ጋ ተጋጭቶ ሕይወቱ እንዳለፈ፤ እናቷ እማማ ፀሐይ ታመው አልጋ ላይብዙ ጊዜ እንደማቀቁ፤ ካለመሰልቸት ብቻዋን ታግላ ማትረፍ ባትችልም እንዳስታመመቻቸው ከአብሮ አደጎቻችን ሰማሁ።
ሃኒቾ በሂደት ራሷን ማግለል፣ ብቻዋን መሆን፣ ራሷን አለመጠበቅ፣ ሥራ አለመሥራት፣ ብቻዋን ማውራት፣
ሲያናግሯት ምላሽ አለመስጠት፣ የተዘበራረቀ ነገር ማውራት መጀመሯንም ክፍለሀገር እያለሁ ሰምቼ ነበር።
ለመጀመሪያ ጊዜ ስንገናኝ፤ “እዩ ደህና ነህ?" ብላ እቅፍ አደረገችኝ፤ አስተቃቀፏ እንኳን መጣህልኝ ዓይነት ነበር። እንዳቀፍኳት ደህና ነኝ አንቺ ደህና ነሽ ስላት እንዳቀፈችኝ ቃል ሳታወጣ አንገቷን ነቀነቀች፤ የሆነችውን ሁሉ ብሰማም ባይኔ ስመለከታት ሰውነቴ ብርክ ያዘው...
ያቺ ፍንጣሪ ነጥብ የምታህል ቆሻሻ ልብሷ ላይ ሲያርፍ ደስ የማትሰኝ፣ ጽዳት፣ ማጠብ፣ ማስተካከል ዋነኛ መለያዋ
የነበረው ሃኒቾ ውሃ አይቷት የማያውቅ፣ የተረሳ፣ ሽበት ጣል ጣል ያለበት ጸጉር፤ ጉስቁል፣ ጥቁር ክስት ያለ ፊት፣
የመነቸከ ሽሮ ቀለም ቲሸርት፣ ብዙ እድፍ የተሸከመ ቀለሙ ይሄ ነው የማይባል ሰፊ ሱሪ ለብሳ ባዶ እግሯን አጠገቤ
ስትቆም፣ ስታቅፈኝ ከአጠገቤ ዞር እስክትል እንኳን እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም። ሁኔታዋ፣ ያሳለፍነው ትናንታችን፣
ሳቃችን፣ ገመናችን፣ መተሳሰባችን ሁሉ አንድ በአንድ ቅልብጭ ብሎ ታወሰኝ። ሕይወት እስኪያስጠላኝ ድረስ
ተደበትኩ… ሰው የመሆን ከንቱነቱ ተዳሰሰኝ!! አንዳንድ ስሜት እውነት ካልዳሰስነው አናውቀውም!!
አብሪያት መቆም ስላልቻልኩ ቻው እንገናኘለን ብዬ ጥያት ሄድኩ። አልሆነልኝም እንጂ የዚያን ሰሞን እንድትድን ያልገባሁበት አልነበረም።
በቀን ብዛት ሰውነቴ ለመዳት እና ሲያያት ማመጽም አቆመ።
ሃኒቾ ከሌሎችም ጋ በጣም ትንሽ ብታወራም፤ ከእኔ ጋ ሲሆን አንደበቷ አይታዘዝላትም መሰለኝ
“እዩ ምግብ ስጠኝ"
“እዩ ሳንቲም ስጠኝ"
"እዩ ደህና ነህ” በቀር ሌላ ቃል አትሰነዝረም።
ሃኒቾ አልፎ አልፎ ደህና ነህ ለማለት ብቻ፣ ወይም ሳንቲም ስጠኝ ለማለት ብቻ፣ ምግብ ስጠኝ ለማለት ብቻ ቤታችን ትመጣለች። ደህና ነህ ለማለት የመጣች ቀን ገንዘብም .. ምግብም ብሰጣት እሽ አትልም። በር ስታንኳኳ ከእኔ በቀር ማንም ይክፈት ማንም እዩ አለ? የመጀመሪያ ጥያቄዋ ነው።
ችግሩ በር ስታንኳኳ በኃይል ነው። እንኳን ሕፃን ልጅ ትልቅ ሰው ያስበረግጋል። በስንት መከራ ተባብሎ የተኛውን ልጄን በር በኃይል እያንኳኳች ታባንነዋለች። ቀስ ብለሽ አንኳኪ ብለን እኔም ሆነ ሚስቴ ያልገሰጽናት ጊዜ አልነበረም፤ ለግሰጻችን ምላሿ ፊቷን አመስክና ቅልስልስ እያለች በአይኗ መለመን ብቻ ነው።
ሚስቴ እሷ ስትመጣ ፈገግታዋ ይደበዝዛል።
ሰዓት እላፊ እየመጣች፤ በስንት እሹሩሩ የተኛውን ልጃችንን እያባነነች፤ ባለመኖራችን የበሩን ድብደባ ሰሚ ስታጣ የመስኮት መስታወት እየሰበረች አስመረረችን።
ያ ዱካካም ቀን ለእሷ የነበረኝን ሐዘኔታ አትንኖት እያጉረጠረጥኩ፣ እንዳትመጪ አልኳት። የመጣልኝን እየለደፍኩ
ሄደች።
ሃኒቾ የድሮው እዮብ በልቧ ስላልጠፋ፣ ተካፍለን የበላናት፣ ተበድረን የተካፈልናት፣ የሳቅነው፣ የተጨቃጨቅነው ከውስጧ ስላልጠፋ ልቧን የወጋሁት ያህል ማንባረቄ ያሳመማት ይመስለኛል። ሁሉም እንደሚያባርራት አባረርኳት፤ ሁሉም እንደሚማረርባት ተማረርኩባት።
ሃኒቾ ከቤቴ ቀረች።
መንገድ ላይ ሳገኛት አንገቷን ደፍታ ታልፈኛለች፡፡
በስሜት ተገፍተን የበደልነው ሰው አንገቱን ሲደፋ ከማየት በላይ ያለ ሕመም የትኛው ነው?
ክፋቴን ሁለመናዋ ላይ ተነቅሳው የምትዞር መሰለኝ። ክፉ እንደሆንን የሚመሰክሩብን ተንቀሳቃሽ ሥጋ ለባሽ፣ ተጨባጭ ምስክሮች እንደማየት ያለ ጥፋተኛ ስሜትን በገላችን ውስጥ የሚረጭ ሌላ ምን ዓይነት ክስተት ይኖርይሆን?
ለግንቦት ልደታ ዕለት የሰፈር ልጆች አብዲ ሱቅ ጎን ያለችው ሜዳ ጋ ተሰብስበው ቡና አስፈልተው በስፒከር ሙዚቃ እያጫወቱ፣ እየጠጡ፣ እየተተራረቡ ሲዝናኑ ሃኒቾ ከሙዚቃውም ከቡናውም ትንሽ ነጠል ብላ ብቻዋን ጽዱ ሥር ለመቀመጫነት ከተቀመጠ ድንጋይ ላይ አይኗን ቡዝዝ አድርጋ ተቀምጣ ሳለች ቀስ እያልኩ አጠገቧ ደርሼ ሃኒቾዬ አልኳት። ሰማይ ላይ ቡዝዝ አድርጋ የተከለችውን አይኗን ወደ እኔ ስታዞር ሃኒቾ አጥፍቻለሁ ይቅርታ አድርጊልኝ ብዬ በአይኔም ጭምር ለመንኳት። ሌላ ተጨማሪ ነውር
ላለመስማት ይሆን አላውቅም ብቻ የደበዘዘ ትዝብት ለበስ ደረቅ ፈገግታ አሳይታኝ በእርጋታ ተነስታ ሄደች፡፡
ብዙ ሰው ሲያባርራት፣ በር ሲዘጋባት፣ ውሃ ሲደፋበት፣ ሰላም ስትላቸው ሲዘጓት ምንም ያልመሰላት ልጅ የእኔ ሲሆን እንደዋዛ አልተወችውም። ምን አለ ብትሰድበኝ፤ ምን አለ ከአጠገቤ ሂድ ብላ ድንጋይ ለማንሳት ብትሞክር፤ ምን አለ ክፉ ቃል ተናግራ የሠራሁትን ብልግና ብታፈዘው፤ እሷ ጠቢብ ናት፣ ጠላቷን የምትበቀለው ከእብድ በማይጠበቅ ዝምታዋ ነው!!
ዝምታን የመሰለ መሣርያ አልባ መቅጫ ምን አለ?
የሆነ ቀን ጠጥታ፤ የሆነ ቀን እርቧት፤ የሆነ ቀን ልትሰድበኝ፤ የሆነ ቀን ሳንቲም ፈልጋ የምትመጣ መስሎኝ ጠበቅኋት። በራችን በኃይል ሲንኳኳ እሷ እየመሰለችኝ ስሮጥ በሩን እየከፈትኩ ጠበቅኋት። ደህና ነሽ ሃኒቾ ስላት አንገቷን ወደ ላይ እየነቀነቀች ደህና ነኝ እንድትለኝ፤ ሳገኛት አንገቷን እንዳትደፋ ጠበቅኋት፤ ካለ ቀጠሮ መጠበቅ አናዋዥ ነውና አናወዘኝ።
ከነበር በኋላ ምን አለ?
ሃኒቾን የምወዳት በጠይም ቆንጆ ፊቷ አልነበረም፤ የተማረኩት በጥቁር ዞማ ጸጉሯም አልነበረም፤ ያሸነፈችኝ ; በየዋህነቷ ነው። ሃኒቾ ለመድመቅ አለመፍጨርጨሯ ነው። ተፈላጊነቷን ለማሳየት አትዳክርም፤ ያላትን ለማጉላት አትታከክም። ምንም የሌለውም ሰው እንደሚወደድ ያሳየችኝ ሃኒቾ ነበረች።
አንድ ቀን ስለ ውሎዋ ስትነግረኝ ትረካዋን ወደ ጎን ትቼ የተዘናፈለ ዞማ ጸጉሯ፣ እርጋታዋ፣ ወዛም ጠይም ፊቷ ላይ ተመስጬ ቆንጅዬ ልጅ እንደሆንሽ ታውቂያለሽ አይደል? ስላት
ዝም ብላ ፈገግ ብላ እያየችኝ ዝም ስትል
የምር አታውቂም?
“እመቤቴን አላውቅም" እመቤቴን ስትል አማማሏ፣ አይኗ ያሳዝናል
"ማልልኝ እስኪ ቆንጆ ነኝ ግን?"
እስቃለሁ። የዋህ ባትሆን ለቆንጆ ነሽ ማልልኝ ትል ነበር?
ሃኒቾ ማለት ይቺ ነበረች በቃ!!! እሷ እመቤቴን ካለች ስለማትዋሽ ሁሉም እንደዛ ነው የሚመስላት፡፡
የሁሉም መለኪያ የልቡ እውነት እና እምነቱ አይደል?
ሃኒቾ ዘመዶቿ ጋ ክፍለሀገር ስትሄድ፣ ስትመጣ፤ እኔም ክፍለሀገር የእናቴ እህት ማሚቱ ጋ ስሄድ ስመጣ አብሮነታችን እየሳሳ እየሳሳ ሌላ መልመድ ጀመርን። ሳንቆሳሰል፣ መራር ቃል ሳንነጋገር ተራራቅን። አብሮነታችን ሳስቶ በሂደት ተለያየን። ክፍለሀገር ለብዙ ጊዜ ኖሬ፣ ትዳርመስርቼ፣ ልጅ ኖሮኝ ተወልጄ ባደግኩባት ከተማ ተመልሼ ያከራየሁትን የቤተሰቦቼን ቤት አስለቅቄ መኖር ጀመርኩ።
ሃኒቾ አግብታ እንደነበር ነገር ግን ከብዙ ንትርክ፤ ከስንት ታርቆ መጣላት በኋላ፤ ከብዙ የጓደኞች፣ የዘመዶች፣ የሽማግሌዎች እና የቤተሰብ ምክር እና ሽምግልና በኋላ አብሮ መሆን አልሆን ብሏቸው እንደተፋቱ፤ ተቆጪዋ፣ መካሪዋ፣ ተቆርቋሪዋ ታላቅ ወንድሟ ሙሉጌታ ሲነዳው የነበረው አነስተኛ መኪና ከከባድ መኪና ጋ ተጋጭቶ ሕይወቱ እንዳለፈ፤ እናቷ እማማ ፀሐይ ታመው አልጋ ላይብዙ ጊዜ እንደማቀቁ፤ ካለመሰልቸት ብቻዋን ታግላ ማትረፍ ባትችልም እንዳስታመመቻቸው ከአብሮ አደጎቻችን ሰማሁ።
ሃኒቾ በሂደት ራሷን ማግለል፣ ብቻዋን መሆን፣ ራሷን አለመጠበቅ፣ ሥራ አለመሥራት፣ ብቻዋን ማውራት፣
ሲያናግሯት ምላሽ አለመስጠት፣ የተዘበራረቀ ነገር ማውራት መጀመሯንም ክፍለሀገር እያለሁ ሰምቼ ነበር።
ለመጀመሪያ ጊዜ ስንገናኝ፤ “እዩ ደህና ነህ?" ብላ እቅፍ አደረገችኝ፤ አስተቃቀፏ እንኳን መጣህልኝ ዓይነት ነበር። እንዳቀፍኳት ደህና ነኝ አንቺ ደህና ነሽ ስላት እንዳቀፈችኝ ቃል ሳታወጣ አንገቷን ነቀነቀች፤ የሆነችውን ሁሉ ብሰማም ባይኔ ስመለከታት ሰውነቴ ብርክ ያዘው...
ያቺ ፍንጣሪ ነጥብ የምታህል ቆሻሻ ልብሷ ላይ ሲያርፍ ደስ የማትሰኝ፣ ጽዳት፣ ማጠብ፣ ማስተካከል ዋነኛ መለያዋ
የነበረው ሃኒቾ ውሃ አይቷት የማያውቅ፣ የተረሳ፣ ሽበት ጣል ጣል ያለበት ጸጉር፤ ጉስቁል፣ ጥቁር ክስት ያለ ፊት፣
የመነቸከ ሽሮ ቀለም ቲሸርት፣ ብዙ እድፍ የተሸከመ ቀለሙ ይሄ ነው የማይባል ሰፊ ሱሪ ለብሳ ባዶ እግሯን አጠገቤ
ስትቆም፣ ስታቅፈኝ ከአጠገቤ ዞር እስክትል እንኳን እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም። ሁኔታዋ፣ ያሳለፍነው ትናንታችን፣
ሳቃችን፣ ገመናችን፣ መተሳሰባችን ሁሉ አንድ በአንድ ቅልብጭ ብሎ ታወሰኝ። ሕይወት እስኪያስጠላኝ ድረስ
ተደበትኩ… ሰው የመሆን ከንቱነቱ ተዳሰሰኝ!! አንዳንድ ስሜት እውነት ካልዳሰስነው አናውቀውም!!
አብሪያት መቆም ስላልቻልኩ ቻው እንገናኘለን ብዬ ጥያት ሄድኩ። አልሆነልኝም እንጂ የዚያን ሰሞን እንድትድን ያልገባሁበት አልነበረም።
በቀን ብዛት ሰውነቴ ለመዳት እና ሲያያት ማመጽም አቆመ።
ሃኒቾ ከሌሎችም ጋ በጣም ትንሽ ብታወራም፤ ከእኔ ጋ ሲሆን አንደበቷ አይታዘዝላትም መሰለኝ
“እዩ ምግብ ስጠኝ"
“እዩ ሳንቲም ስጠኝ"
"እዩ ደህና ነህ” በቀር ሌላ ቃል አትሰነዝረም።
ሃኒቾ አልፎ አልፎ ደህና ነህ ለማለት ብቻ፣ ወይም ሳንቲም ስጠኝ ለማለት ብቻ፣ ምግብ ስጠኝ ለማለት ብቻ ቤታችን ትመጣለች። ደህና ነህ ለማለት የመጣች ቀን ገንዘብም .. ምግብም ብሰጣት እሽ አትልም። በር ስታንኳኳ ከእኔ በቀር ማንም ይክፈት ማንም እዩ አለ? የመጀመሪያ ጥያቄዋ ነው።
ችግሩ በር ስታንኳኳ በኃይል ነው። እንኳን ሕፃን ልጅ ትልቅ ሰው ያስበረግጋል። በስንት መከራ ተባብሎ የተኛውን ልጄን በር በኃይል እያንኳኳች ታባንነዋለች። ቀስ ብለሽ አንኳኪ ብለን እኔም ሆነ ሚስቴ ያልገሰጽናት ጊዜ አልነበረም፤ ለግሰጻችን ምላሿ ፊቷን አመስክና ቅልስልስ እያለች በአይኗ መለመን ብቻ ነው።
ሚስቴ እሷ ስትመጣ ፈገግታዋ ይደበዝዛል።
ሰዓት እላፊ እየመጣች፤ በስንት እሹሩሩ የተኛውን ልጃችንን እያባነነች፤ ባለመኖራችን የበሩን ድብደባ ሰሚ ስታጣ የመስኮት መስታወት እየሰበረች አስመረረችን።
ያ ዱካካም ቀን ለእሷ የነበረኝን ሐዘኔታ አትንኖት እያጉረጠረጥኩ፣ እንዳትመጪ አልኳት። የመጣልኝን እየለደፍኩ
ሄደች።
ሃኒቾ የድሮው እዮብ በልቧ ስላልጠፋ፣ ተካፍለን የበላናት፣ ተበድረን የተካፈልናት፣ የሳቅነው፣ የተጨቃጨቅነው ከውስጧ ስላልጠፋ ልቧን የወጋሁት ያህል ማንባረቄ ያሳመማት ይመስለኛል። ሁሉም እንደሚያባርራት አባረርኳት፤ ሁሉም እንደሚማረርባት ተማረርኩባት።
ሃኒቾ ከቤቴ ቀረች።
መንገድ ላይ ሳገኛት አንገቷን ደፍታ ታልፈኛለች፡፡
በስሜት ተገፍተን የበደልነው ሰው አንገቱን ሲደፋ ከማየት በላይ ያለ ሕመም የትኛው ነው?
ክፋቴን ሁለመናዋ ላይ ተነቅሳው የምትዞር መሰለኝ። ክፉ እንደሆንን የሚመሰክሩብን ተንቀሳቃሽ ሥጋ ለባሽ፣ ተጨባጭ ምስክሮች እንደማየት ያለ ጥፋተኛ ስሜትን በገላችን ውስጥ የሚረጭ ሌላ ምን ዓይነት ክስተት ይኖርይሆን?
ለግንቦት ልደታ ዕለት የሰፈር ልጆች አብዲ ሱቅ ጎን ያለችው ሜዳ ጋ ተሰብስበው ቡና አስፈልተው በስፒከር ሙዚቃ እያጫወቱ፣ እየጠጡ፣ እየተተራረቡ ሲዝናኑ ሃኒቾ ከሙዚቃውም ከቡናውም ትንሽ ነጠል ብላ ብቻዋን ጽዱ ሥር ለመቀመጫነት ከተቀመጠ ድንጋይ ላይ አይኗን ቡዝዝ አድርጋ ተቀምጣ ሳለች ቀስ እያልኩ አጠገቧ ደርሼ ሃኒቾዬ አልኳት። ሰማይ ላይ ቡዝዝ አድርጋ የተከለችውን አይኗን ወደ እኔ ስታዞር ሃኒቾ አጥፍቻለሁ ይቅርታ አድርጊልኝ ብዬ በአይኔም ጭምር ለመንኳት። ሌላ ተጨማሪ ነውር
ላለመስማት ይሆን አላውቅም ብቻ የደበዘዘ ትዝብት ለበስ ደረቅ ፈገግታ አሳይታኝ በእርጋታ ተነስታ ሄደች፡፡
ብዙ ሰው ሲያባርራት፣ በር ሲዘጋባት፣ ውሃ ሲደፋበት፣ ሰላም ስትላቸው ሲዘጓት ምንም ያልመሰላት ልጅ የእኔ ሲሆን እንደዋዛ አልተወችውም። ምን አለ ብትሰድበኝ፤ ምን አለ ከአጠገቤ ሂድ ብላ ድንጋይ ለማንሳት ብትሞክር፤ ምን አለ ክፉ ቃል ተናግራ የሠራሁትን ብልግና ብታፈዘው፤ እሷ ጠቢብ ናት፣ ጠላቷን የምትበቀለው ከእብድ በማይጠበቅ ዝምታዋ ነው!!
ዝምታን የመሰለ መሣርያ አልባ መቅጫ ምን አለ?
የሆነ ቀን ጠጥታ፤ የሆነ ቀን እርቧት፤ የሆነ ቀን ልትሰድበኝ፤ የሆነ ቀን ሳንቲም ፈልጋ የምትመጣ መስሎኝ ጠበቅኋት። በራችን በኃይል ሲንኳኳ እሷ እየመሰለችኝ ስሮጥ በሩን እየከፈትኩ ጠበቅኋት። ደህና ነሽ ሃኒቾ ስላት አንገቷን ወደ ላይ እየነቀነቀች ደህና ነኝ እንድትለኝ፤ ሳገኛት አንገቷን እንዳትደፋ ጠበቅኋት፤ ካለ ቀጠሮ መጠበቅ አናዋዥ ነውና አናወዘኝ።
❤34👍7