አትሮኖስ
283K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
502 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ግን_አንድ_ቃል_አለ!

.እኔ በቅሎ አደለሁ

ይሄ ሁሉ ሸክም በላዬ ተጭኖ
እንደምን ልራመድ
የየለት ተግባሬ ብልጭ ብሎ መጥፋት
እሳት ሆኖ ማመድ

መኖር አለመኖር
አለመኖር መኖር

መሆን አለመሆን
አለመሆን መሆን

ጊዜ እነደሽልጦ እያገላበጠኝ
ወይ በደህና አልበስል
ዝም ብዬ እፀናለሁ እዮብን ይመስል

ዝም ብዬ
ዝም ብዬ
ይህም ያልፋል ብዬ

በጣር ያቆምኩት ቤት በንፋስ ይገፋል
በውኔ ያቀድኹት ህልም ሆኖብኝ ያልፋል

ወይ በርትቼ አልቆምም ወይ ወስኜ አሎድቅም
ዝም ብዬ እድሀለኹ እንደ ህፃን ልጅ አቅም

ዝም ብዬ
ዝም ብዬ
አንዲትን ቃል ብዬ

ላለመሞት መሞት ለመኖር መታገል
ብረት ነኝ ስል ኖሬ ሸክላ ሆንኩ እንደገል

ስብር ብር ..
. እንክት ክት
ጊዜ ሁን ያለኝን በምኔ ልመክት
ብቻ ግን ብቻ ግን አለሁ ለምልክት

ግን አንድ ቃል አለኝ
"አለት ሆኜ ወደኩ ጠጠር ሆኜ በዛው
የሚል ታሪክ አለኝ ነፍሴን የሚገዛው"
ተመስገን፡፡

🔘አስታውሰኝ ረጋሳ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍39🥰21
#ይነጋል

ታድለሻል ቢሉም፣
የ13 ወር ፀሀይ፣ የ13 ወር ፀጋ
ብርሀንሽ ተሰርቆ፣
ሲጨላልም እንጂ፣ መች አየን ሲነጋ?

ተፈጥሮ ቸር ሆና፣
ሰማይዋ ባይነጥፍ፣ ምድሯ ቢለመልም፣
ከልጆቿ ልብ ውስጥ፣
ፍቅር ሲጎድል ነው፣ ሀገር የምትጨልም!፣

"አረ ነግቷል" ቢሉ የታለ የነጋው?
አዕላፋት ተቧድነው፣ በየጎጥ በመንጋው፣
ሰው ከነገ ይልቅ፣ ዛሬን እያሰጋው የታለ የነጋው?
ታሪኩን እንዳይፅፍ፣ ትውልድ እጁ ታስሮ፣
በትላንቱ ሾተል ዛሬው ተሸንቁሮ፣
ባልኖረው ተካሶ፣ ባልሰራው ተዋቅሶ፣
ለፀብ መዶለቻ፣ ያ'ያቱን ስም ጠቅሶ፣
ላለፈው ሲናከስ ለመጪው ሳይተጋ፣
በምን ስሌት ይሆን፣
ትዉልዷ ጨልሞ ሀገር የምትነጋ?
.
የህሊና መስታወት በጥበብ ሲፀዳ፣
ማስተዋል እንዳ'አደይ ፈክቶ ሲፈነዳ፣
መገፋፋት ሲቀር ፣መደጋገፍ ነግሶ
አንዱ ማገር ሲሆን፣ ሌላኛው ምሰሶ፣
የአብሮነትን ሸማ ትዉልዱ ሲሸምን፣
ያኔ ነው ሀገሬ መንጋቷን የማምን።

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍274🔥3
#ጥበቃ

እኛን ያሳደጉን

'"ሀገር ተረካቢ" በሚሉት ሀረግ ነው፤

አድገናል እንሆ

ሀገሪቷን ስጡን እየጠበቅን ነው።

🔘በረከት ባይጨክን🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍17😱61
#የታል_ልጅነቴ?

እነ ጋሽ አበበ ሚጡዬና ቹቹ

እነ ትዬ ፀሐይ እንዲሁም ሌሎቹ

ወዴት ተሰደዱ የታሉ ሰዎቹ የሰፈሩ ሜዳ የለም ከኖረበት መንገዱም ተለምቷል ሱቅ የተላኩበት የታሉ ዛፎቹ ምሽግ መስሪያዎቹ ልጥ የላጥንባቸው ኳስ ማሰሪያዎቹ ካሬ ስድስት ቆርኪ የተጫወትኩበት የት ሄደ ደስታዬ የት ሄደ ልጅነት ሸርተቴ ያልኩበት የጭቃው ተራራ

ልጅነቴን ትቶ ፎቅ በላዩ ሠራ

መርቅ አልመርቅም የተጣላሁበት

የከድር ሱቅ የለም ፈልጌ አጣሁት

ቡልኮ ጠጅ ቤት ጉልት የሰፈሩ

ተሰደዱ መሰል እነሱም ሳይቀሩ

ከቤቴ በር ላይ ወጥቼ ቆሜአለሁ

ሰላም የሚለኝ ሰው በዓይኔ እፈልጋለሁ

በተወለድኩበት ባደኩበት ሰፈር

ሆኛለሁ ባይተዋር

የለም ልጅነቴ

ማርና ወተቴ

🔘እመቤት መንግሥቴ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍26😢116👎2
Forwarded from አትሮኖስ (◔͜͡◔ Mellos ◔͜͡◔🐾🦒)
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...

🦧| ምትሰበስቡት ነጥብ ቀጥታ ወደ ቶክን ይቀየራል
🦓| ፕሮጀክቱ ለጥቂት ግዜ የሚቆይ ስለሆነ አያሰላቻም
🐊| አጨዋወቱ እንስሶችን በተሰጣችሁ Feed መመገብና Upgrade ማድረግ ነው
🦜| ብዙ ሰው ስላልበዛበት በግዜ ብትጀምሩ ይመረጣል

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍122
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን
==========================
ዛሬ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ድክምክም ብሎኛል፡፡ብዙ ስራ እየሰራሁ ስለዋልኩ አይደለም..እንደውም በተቃራኒው ስቀመጥ ስለዋኩ ይመስለኛል ዛል እስክል የደከመኝ፡፡ ‹‹መቀመጥ መቆመጥ ነው››ትል ነበር አንድ ኑሮዋ ጠቅላላ ተረት በተረት የሆነባት ተራች አክስቴ፡፡ ሰዓቱ 12፡35….ሆኗል ፡፡ምሽቱ ደረስኩ እያለ ነው፡፡ስቀመጥ ከዋልኩበት ቢሮዬ ለሊቱን ስተኛ ወደማሳልፍበት ቤቴ ቀጥታ ማምራት ስላልፈለግኩ ለምን ትንሽ ወክ አላደርግም አልኩና ወደ ቤቴ አቅጣጫ በጣም በዝግታ ማዝገም ጀመርኩ፡፡እርምጃዬ ጽሞና የታከለበት እንዲሆን ስለፈለኩ ዋናውን የአስፓልት መንገድ ለቀቅኩና በሁለተኛው መንገድ መጓዝ ጀመርኩ.፡፡እሱም በባጃጅና በመንገደኛ ሰዎች ስለተሞላ አልተመቸኝም ወደ 3ተኛው መንገድ ተሸጋገርኩ፡፡አዎ ይሄ ይሻላል.. እሬሳን ወደ የዘላለም ማረፊያው ወደ ሆነው ቀብሩ እንደሚሸኝ ሰው ወይም በመንግስት ወታደሮች እጅ ወድቆ እጁ በሰንሰለት ወደኃላ እንደተጠፈረ አሸባሪ ተብዬ እጆቼን ወደኃላ አጣምሬ በዝግታና በፀጥታ እጓዛለሁ፡፡አካባቢው ፀጥ ያለ ነው፡፡አዕምሮዬ ግን በጫጫታ የተሞላ ነው፡፡ዝም ብሎ ህልሙንም እውኑንም ይፈተፍታል፡፡

ድንገት ከአንዱ መንገድ ተጠምዝዤ ወደ አንዱ ስገባ ዓይኔ አየ.. ምን ዓየ …..?አትሉኝም፡፡ልክ ለዘመናት እንደተራብኩት የእናቴ ጡት ዓይነት ነገር፣ልክ በፀሎት እና በእምነት አማኞች እንደሚናፍቆት ገነት ዓይነት ፣ልክ ፖለቲከኞች ለዘመናት ይመኙት እንደነበረው የቤተ መንግስት ወንበር ዓይነት… አይገርምም…፡፡ ያየሁት እኮ አሁን እንደጠቀስኩላችሁ ዓይነት ነገር ሆኖ አይደለም..እኔን ግን ውስጤን የተሰማኝ…በወቅቱ አደነዛዘዜ ፤ አደነጋገጤ እንደዛ ነው ያስመሰለብኝ፡፡ …ወፈር ደልደል ያለ ቀይ ቂጥ ነው ያየሁት..….ያየሁት ከገባሁበት መንገድ በግራ ጠርዝ በኩል በግምት 100ሜትር ርቀት ላይ የቀበሌውን ጽ/ቤት አጥር ተጠግቶ ነው፡፡እኔ ያልኳችሁ ፍም ቂጥ ብቻ አየሁ አይደል..?ግን የዘነጋሁት ወይም ያልነገርኳችሁ አንድ ነገር የቂጡንም ባለቤት ማየቴን ነው፡፡ግራ ቀኝ ስታማትር እሷም እኔን አይታኛለች፡፡ግራ የተጋባች ይመስላል፡፡የለበሰችውን ቡኒ ጅንስ ሱሪ አውልቃ ጉልበቷ ጋር አድርሳዋላች ፣በእርቃን ቂጧ እና ወልቆ ጉልበቷ ጋር በደረሰው ሱሪዋ መሀከል ሆኖ የሚዋልል ሌላ ቀይ ነገር ይታየኛል..አዎ ፓንቷ ነው ፡፡ ግራ ገብቷት ወይም የራሱ ጉዳይ ብላ መሰለኝ ችላ አለቺኝና ቁጢጥ አለች፡፡
እኔም የእራሴው እርቃን በአደባባይ እየታየብኝ ያለ ይመስል ሽምቅቅ ብዬ የ100 ሜትሩን ርቀት ወደ 70 ሜትር ካጠበብኩት በኃላ ቆምኩ፡፡..በቃ  ዝም  ብዬ  ቆምኩ፡፡ ቆሜም  ማሰላሰል  ጀመርኩ፡፡ እሷም አንዴ ወደ መሬት አንዴ ወደ እኔ እያች የኩላሊቷን ጥዝጣዜ ና የፊኛዋን ውጥረት ማስተንፈስ ቀጠለች….‹‹ሾሾ… ሾ… ዋዋ›› የሚል የሽንት ድምፅ ተሰማኝ..፡፡እርግጠኛ ግን አይደለሁም፡፡ ብቻ የሰማሁ መስሎኛል፡፡
ግን በፊት ቅምቅም አያቶቻችን ለወንድ ሱሪ ለሴት ቀሚስ የሚባል ልብስ ለምን እንዲኖር እንዳደረጉ ዛሬ ነው ፍንትው ብሎ የገባኝ.፡፡ይሄኔ እኮ ይህቺ ሚስኪን ሴት ቀሚስ ለብሳ ቢሆን ኖሮ እሷም አትጋለጥም.. እኔም አልደነግጥም ነበር፡፡ቁጭ ብላ ቀሚሷን ገለብ ታደርግና ‹ሾዋ..ዋ…ዋ› በማድርግ ከተነፈሰች በኃላ ምንም እንዳልተፈጠረ ተነስታ ትሄድ ነበር፡፡
ወይ..ሀሳቤን ሳልጨርስ ጨርሳ ቆመች፡፡ፊቷን ከእኔ በተቃራኒው  አዞረችና መጀመሪያ ቀዩን  ፓንቷን ወደ ላይ ስባ  ቀዩን ቂጧን ሸፈነችው፤  አቤት  በፓንትም  ሲታጠር  ያምራል፣ምራቄን  ገርገጭ አደረግኩ፡፡ ከዛ ሱሪዋን ወደ ላይ እየጎተተች ለበሰች፡፡ከጨረሰች በኃላ ቀጥታ ወደ እኔ አቅጣጫ መጣች፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ወደ ኃላ ልመለስ ወይስ ወደ ፊት ልቀጥል…?፡፡ከሁለቱ እግሮቼ የትኛውን ላስቀድም?፡፡ እያልኩ በሀሳብ እየተጨነቅኩ ስዋልል እሷ ቀድማኝ ስሬ ደረሰች፡፡አትኩሬ አየኋት… ቂጧም ብቻ ሳይሆን መልኳም ቀይ ነው፡፡የሆነ ክልስ ነገር ሳትሆን አትቀርም…፡፡ፈርዶብኝ ቀይ ሴቶች ልቤን በቀላሉ ብትንትን ያደርጉታል ፡፡ፍቅረኛዬ ሀይሚም እንደዚህችው ነች፡፡ ዓይኖቾ ጐላ ጐላ ያሉ ባለ ሉጫ ፀጉር ነች..፡፡አደንዛዥ ፈገግታ መግባኝ ታካኝ አልፋኝ ሄደች፡፡ እኔም ቀኝ ኃላ ዞሬ ተከተልኳት፡፡ ውሳኔዬ እሷን መከተል እንዲሆን ያስገደደኝ የቂጧ ቀይነት ይሁን የፈገግታዋ ጉዳይ አልገባኝም፡፡ደረስኩባት እና ዝም ብዬ ከጎኗ መራመድ ጀመርኩ፡፡
ግራ ገባቷት‹‹እንተዋወቃለን?››አለቺኝ፡፡

‹‹አሁን ተዋወቅን አይደል እንዴ?››መለስኩላት፡፡

‹‹አሁን የት ?››

‹‹እዛ ነዋ.. እኔ ፈዝዤ ተገትሬ አንቺ ቁጢጥ ብለሽ፡፡››

ከት ብላ ሳቀች… ሳቋ ያምራል‹‹…ጉደኛ ነህ!!! ትንሽ እንኳን አታፍርም እንዴ..?እኔስ ተጨንቄ ነው አንተ ምን አለ ዞር ብትልልኝ  ኖሮ?››

‹‹ወዴት ዞር ልበል..?ከተጠጋሁሽ እኮ ይበልጥ አይሻለሁ ብዬ ነው  የቆምኩት፡፡››

‹‹ዞረህ በሌላ መንገድ አትሄድም እንዴ?››

‹‹አኸ እንደዛም ይቻል ነበር ለካ..?እሱ እንኳን ትዝ አላለኝም፡፡››

‹‹ደንዝዘህ እንዴት ትዝ ይልሀል..?ወይ ወንዶች ስትባሉ!!!›› አለችኝ፡፡ይህቺን‹ ወይ ወንዶች ስትባሉ!!! › ቢያንስ ከ100 ሴቶች ሰምቼያታለሁ ፡፡ግን ወንዶች ስንባል እንዴት ነን..? ያው እንደዛ የሚሉን ሴቶች እራሳቸው ይመልሱት ፡፡

‹‹ግን ያምራል›› አልኳት፡፡

የድንጋጤም የእፍረትም ሳቅ እየሳቀች‹‹ምኑ?›› አለችኝ፡፡

‹‹ያየሁት ››አልኳት… አኔም በተራዬ እንደማፈር ብዬ፡፡

‹‹የትኛውን አይተህ የትኛውን እንደዘለልክ በምን አውቃለሁ?›››

‹‹ከወርቃማዋ ሸለቆሽ በስተቀር ሁሉንም አይቼያለሁ››

አቤት የሳቀችው ሳቅ… እንባዋ እስኪንጠባጠብ ነው ተንፈራፍራ የሳቀችልኝ፤ሴት  ልጅ  እንደዚህ  ስትስቅልኝ  ለመጀመሪያ  ጊዜ ይመስለኛል፡፡ ባይገርማችሁ ከቤቴ መንገድ በተቃራኒው ይህቺን ባለ ቀይ ቂጥ ሴትዬ ተከትዬ ለ24 ደቂቃ ተጉዤያለሁ፡፡

‹‹ምትገርም ልጅ ነህ ..ለማንኛውም የምሄድበት ቦታ ደርሼያለሁ በዚህ ነው የምጠመዘዘው፡፡ ››

‹‹እንዴ!!! እኔስ?›› አልኳት ደንግጬ፡፡

‹‹አንተ ምን..?ወደምትሄድበት ሂዳ፡፡››

‹‹የምሄደውማ ወደ ቤቴ ነበር …ቅድም እሄድበት በነበረው አቅጣጫ፡፡››

‹‹በል እንግዲህ የቂጥ አምላክን እየረገምክ ቀኝ ኃላ ዙርና ንካው›› አለችኝ፡፡

‹‹ስልክ ቁጥርሽን ስጪኛ?››

‹‹ምን ልታደርገው?››

‹‹በቃ እንዲሁ፡፡››

‹‹ባለትዳር ብሆንስ?››የማልመልሰውን ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ሁኚያ..እኔ እንዲሁ ነው የፈለኩት አልኩሽ እኮ፡፡›› እንዲሁ መፈለግ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ብትጠይቀኝ ግን መልስ አልነበረኝም፡፡

‹‹ሁላችሁም ወንዶች በመጀመሪያ እንዲሁ ነው የምትፈልጉት በኃላ እንጂ ነገር የምታመጡት፡፡››

‹‹ኸረ እንዲሁ ነው ስጪኝ፡፡››በአሳዛኝ ሁኔታ ተለማመጥኳት፡፡

እያጉረመረመች ሰጠችኝ፡፡ተሰናበተኳትና እንዳለቺኝ ቀኝ ኃላ ዞሬ ወደቤቴ ነካሁት፡፡
ለሊቱን ሙሉ የቂጧ ምስል በህልሜ ሲመላለስ እና ሲያሰቃየኝ አደረ፡፡ ምን ነካኝ ግን ?ፍቅር ሊይዘኝ ይሆን እንዴ? ኸረ አይደረግም…፡፡ ቢያንስ በ10 ዓመት እኮ ትበልጠኛለች፡፡ ግን ይሄ ምን ችግር አለው? ከስድስት ወር በፊት የጠበስኳት ቀሚ ፍቅረኛዬ የሆነችውን ሀይሚን በ10 ዓመት እበልጣት የለ?አንዷን እበልጣታለሁ አንዷ ደግሞ ትበልጠኛለች..በቃ ማቻቻል ማለት እንዲህ ነው፡፡
👍79😁258🔥1🥰1
ደግነቱ በማግስቱ ቅዳሜ ነው፡፡ ቅዳሜ ደግሞ ሀይሚ እቤቴ እንደምትመጣ ቃል ገብታልኛለች፡፡መቼስ እንዲህ ስላችሁ ታድለህ ሁል ጊዜ በሳምንቱ መጨረሻ የረፍት ቀንህን እየጠበቀች ፍቅረኛህ እቤትህ ስለምትመጣልህ በደስታ አለምህን ትቀጫለህ ብላችሁ አስባችሁ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን በጣም..በጣም ተሳስታችኋል ፡፡ አይደለም በሳምንት ልትመጣ በስድስት ወር የፍቅረኝነት ጉዞችን ካፌ እንኳን አስቀምጬ ለመጋበዝ ከእሷ ፍቃድ ያገኘሁት ከ3 ቀን   ለማይበልጡ ቃናቶች ብቻ ነው፡፡… በቃ ፍቅራችን በአብዛኛው በስልክ ነው…. በሚሴጅ እና በቻት….ቀላል ሞዛዛ መሰለቻችሁ..፡፡

..ይሄ የእሷ ባህሪ ግን አንድ ወሳኝ ጥቅም አለው መሰለኝ፡፡ ወጪ በመቆጠብ… ፡፡የእኔ ጓደኞች በሳምንት አንድ ቀን ፍቅረኛቻቸውን ለመጋበዝ በሳምንት 3 ቀን ምሳ እንደሚዘሉ አውቃለሁ፡፡ ካለ በለዚያማ ያቺ ሚጢጢዬ ከመንግስት ሚወረውርላቸው ደሞዝ ተብዬ ክፍያ እንዴት ትበቃቸዋለች..?ውይ እረስቼው፡፡እኔም ለካ ሀይሚን በመጋበዝ ምንም የማወጣው ወጪ ባይኖርብኝም በወር አንድ ቀን ደሞዝ በምቀበልበት ሰሞን እንትን ስለሚያምረኝ..ሀይሚም እሺ ብላ ስለማትሰጠኝ ግዢ ወጣለው፡፡
የዛን ቀን ታዲያ የደሞዜን ግማሽ አስረክቤ እመለሳለው፡፡ ይሄኔ አመንዝራ..ባለጌ …ፍቅረኛ እያለህ.. ኃጥያት አይደለም? ብላችሁ በሆዳችሁ አምታችሁኝ ይሆናል? ታዲያ ምን እንዳደርግ ትጠብቃላችሁ ?ፍቅረኛ ቢኖረኝ እምቢኝ ካለችኝ በግድ አልደፍራት፡፡ሀይሚ እኮ ማለት ምግብ ቤት ግድግዳ ላይ ተለጥፎ የሚታይ የፍራፍሬ ፖስተር ማለት ነች፡፡ለማስጐምዠት አገልግሎት ብቻ የተፈጠረች፡፡ አስገድጄ …ብፈልግስ የት አግኝቼት… ?መንገድ ላይ አላደርገው፡፡ እሷ እንደሆነ ከእኔ ጋር በባዶ ቤት ላለመገናኘት የምታደርገው ጥረት ልነግራችሁ አልችልም፡፡ጥሩነቱ የእሷም ሰበብ እንደአለማለቁ የእኔም ትዕግስት አያልቅም.፡፡.እወዳታለሁ…፡፡ በጣም ነው የማፈቅራት፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose


የጣት ቁስልድርሰት #በአብርሃም_ቃሉ በቀጣይ የማቀርበው ድርሰት ይሄ አሁን የጀመርነው አጭር ታሪክ ሲያልቅ መልካም ምሽት



ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍608😱2
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_ሁለት


#ድርስት_በዘሪሁን
==========================
ቢሆንም ቅንዝሬ ያው ቅንዝር ነውና ጆሮው የተደፈነ ነው፤የእኔ እና የእሷን ምክንያት አያዳምጥም ፡፡ስለዚህ እመክረው እመክረውና…ከዛም ደግሞ እለምነው እለምነው እና በቃ ከአቅሜ በላይ ሲሆን  እንደነርኳችሁ በወር አንዴ በደሞዝ ሰሞን ወደ አብረቅራቂ መብራት ወደሚንቦገባግባቸው የለሊት ቤቶች ጐራ እላለሁ ፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን ልቤ ለሀይሚ እንዳላዘነ ነው፡፡ዛሬ ግን እፎይ ልገላገል ነው ፡፡ሀይሚ እቤት ለመምጣት ከስድስት አታካች ወራቶች ጭቅጭቅ በኋላ ተስማምታለች፡፡ከቀኑ 8 ሰዓት ነው የምትመጣው፡፡እኔ ግን ከእንቅልፍ የባነንኩት ከለሊቱ 8 ሰዓት ነው፡፡ለዝግጅት፡፡እውነቴን ነው እኮ ፡፡ገና እቤት ማዘጋጀት አለ፣ዕቃ ማጣጠብ አለ፣አልጋ በስርአት ማንጠፍ አለ፣ለፍቅራችን ማጀቢያ ሙዚቃ መምረጥ አለ፣ደግሞ እኔም እንድደፍራት እሷም እንድትደፈርልኝ የሚያግዝ መጠጥ ማዘጋጀት አለ፣አረ ስንቱ….፡፡

ደግሞ አይገርማችሁም ዛሬ ሀይሚ ቤት ልትመጣ ትናንትና ቂጣሟን ማግኘቴ….፡፡ ማግኘቴ ብቻ ሳይሆን እቤቷ ድረስ መከተሌ..ከዛም አልፎ ስልክ ቁጥሯን መቀበሌ..፡፡አሁን ልደውልላት እንዴ….? የሚል ሀሳብ መጣብኝ ፡፡መልሼ ሀሳቤን ውድቅ አደረግኩት ::ለሀይሚ ያለኝን ታማኝነት ዝቅ ማድረግ ነው:: አይደለም መደወል …ቢቻል በምናቤ ተንጠልጥሎ አልወርድ ያለኝን የቂጧን ምስል አሽቀንጥሬ መጣል ብችል ደስ ይለኝ ነበር፡፡እንደቀጠሯችን ምንም ሳታረፍድ ከቀኑ 9 ሰዓት ሀይሚ መጣች..ያው አንድ ሰዓት ዘገየች ማለት አረፈደች ተብሎ መደምደም የለባትም ብዬ ነው፡፡ አለባበሷን ልግለጽላችሁ፣ቡትስ ጫማ፣ጥብቅ ያለ ጅንስ ሱሪ፣በሱሪው ላይ ቁርጭምጭሚቷ ጋር የሚጠጋ ቀሚስ፣በቀሚሱ ውስጥ ደግሞ ሱሪዋ በቀበቶ የተጠፈረ መሆኑን በሚታየው የቀበቶ ቅርፅ ማወቅ ይቻላል፣ከላይ ደግሞ ግብዳ ሹራብ ደርባለች፡፡
ጉንጯን እያገላበጥኩ እየሳምኩ ቢሆንም አይኖቼን ግን ሰማዩ ላይ አንጋጥጬ እያንከራተትኩ ነው፡፡ሀሞቴ ፍስስ ነው ያለው፡፡አሁን እሺ ብላ እንድናደርግ ፍቃዱን ብትሰጠኝ ..ይሄን ጫማዋን ፈትቼ እስካወልቅ አንድ ሰዓት፣ሱሪዋን እስካወልቅ ሌላ አንድ ሰዓት፣ምን አልባት ከሱሪዋ ስር ታይት፣ከታይቱ ስር ደግሞ ሁለት ወይም ሶስት ፓንት ታጥቃ ሊሆን ይችላል..? ታዲያ መሽቶ ነጋ ማለት አይደል?፡፡

ወደ ቤት ዘልቃ ቁጭ አለች፡፡ቁጭ አባባሏ እራሱ ሲያበሳጭ፡፡ ከጓዲያ ወጥቶ ማጅራቷን አንቆ የሚውጣት ዳይኖሰር ያለ ይመስል በራፉ ጥግ የሚገኝ ኩርሲ ላይ ተቀመጠች፡፡ፈርጥጣ ለመውጣት እንዲያመቻት ይመስለኛል፡፡ ደግሞ እሷ ብቻ ሳትሆን እኔም አበሳጫለሁ ፤ ምን አለበት ከመምጣቷ በፊት እቤቴ ያሉትን መቀመጫቸው ሁሉ ሰብስቤ ጓዲያ አስገብቼ ቢሆን ኖሮ ምርጫ ስታጣ አልጋ ላይ መቀመጧ አይቀርም ነበር፡፡

‹‹ሀይሚ ..ምነው በራፍ ላይ….. ?አልጋው አይሻልሽም…?››

‹‹አይ መጣለሁ  ብዬህ እንዳልቀር ነው እንጂ …እሄዳለሁ፡፡››

‹‹ወዴት?››

‹‹ወደቤት ነዋ…እናቴ ስራ አዛኝ ነበር ….ተደብቄ ነው የመጣሁት››ብላኝ እርፍ፡፡

ይታያችሁ ሰው አሁን ይህቺን ያፈቅራል...?ከለሊቱ 8 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ፍዳዬን ስበላ ቆይቼ እሷ ግን ገና መጥታ ሳትጨርስ ልሄድ ነው ትላለች፡፡ቀኑን ሙሉ እሷን እያሰበ ሲወጣጠር የዋለውን እንትኔ ወዲያው ልፍስፍስ ብሎ ሲሸበለል ይታወቀኛል፡፡ችላ አልኳት እና ወደ ጓዲያ ገብቼ የሰራሁትን ምግብ በማምጣት ጠረጴዛ ላይ ደረደርኩት፡፡ ወይኑንም አወጣሁ..አሁን የምግብ ጠረጰዛው አልጋውን ተጠግቶ ስለሚገኝ ምርጫ የላትም መጥታ አልጋው ላይ ከጐኔ መቀመጧ አይቀርም ፡፡

‹‹ሀይሚ ነይ ምሳ እንብላ ፣እርቦኛል..እስከአሁን እኮ አንቺን ስጠብቅ አልበላሁም፡፡››

‹‹እኔ እኮ በልቼያለሁ፡፡››አቤት ወሽመጥ ስትቆርጥ፡፡

‹‹ባክሽ አታበሳጪኝ..በስንት ጣጣ  መጥተሸ ደግሞ..?›› ተኮሳተርኩ፡፡ እንደመደንገጥ አለችና መጣች፡፡ እንዴት መጣች አትሉኝም…? ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት ከአልጋው ራቅ ብላ ተቀመጠች፡፡ ምርጫ አልነበረኝም፤ እጇን አስታጠብኳት ፤ወይኑን ስቀዳ‹‹ለእኔ እንዳትቀዳልኝ››አለችኝ እየተንዘረዘረች፡፡ መርዝ ልቀዳላት የተዘጋጀው አስመሰለችው፡፡

‹‹አንድ ብርጭቆ ብቻ››ተለማመጥኳት፡፡
‹‹አንድ መለኪያም አልጠጣም..እንድበላ ከፈለክ በውሃ ቀይርልኝ…›› ለወራት ተጨንቆ የቀየሰው የጦርነት እስትራቴጂ ፍርክስክሱ እንደወጣበት የጦር ጄኔራል ሞራሌ ድቅቅ አለበኝ፡፡ለንቦጬን ጣልኩ …ያለችውን አደርግኩ፡፡

እየተጐራረስን በፀጥታ በልተን ጨረስን፡፡እኔ የእሷንም ፋንታ የምጠጣ ይመስል እንደውሃ እጋተው ጀመር ፡፡ እንደጨረስን የተበላበትን ዕቃ አነሳሳሁ..እጇን አስታጠብኳት እና እኔም ታጥቤ  ወደ ቦታዬ ተመለስኩ፡፡

ልክ ምሳዋን ለመብላት የመጣች ይመስል…‹‹ልሂድ በቃ፡፡›› አለችኝ፡፡

‹‹ቆይ ማውራት አለብን፡፡››

‹‹ምንድነው የምናወራው?››

‹‹ስለፍቅራችን ነዋ፡፡ ››

እንደመደንገጥ ብላ‹‹ፍቅራችን ምን ሆነ ?››አለችኝ፡፡

‹‹እስከአሁን ምንም አልሆነ …ካላወራንበት እና መፍትሄ ካላበጀንለት ግን መሆኑ አይቀርም.››ወይኑን በደረቁ እየለጋሁት ስለሆነ በድፍረት የመናገር ወኔዬ ሙሉ ነው፡፡

‹‹እሺ ፈጠን በልና እናውራበት››

‹‹ታፈቅሪኛለሽ?››

ግራ በመጋባት‹‹ምን ማለት ነው?››

‹‹ታፈቅሪኛለሽ ወይ?››ደግሜ ጠየቅኳት፡፡  

‹‹በጣም አፈቅርሀለሁ፡፡››
  ‹‹ካፈቀርሺኝ …ዛሬ ፍቅር እንድንሰራ እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹ፍቅር እየሰራን አይደል እንዴ?››

‹‹እንደ እሱ አይደለም..ልብስሽን አወላልቀሽ..እኔም ልብሴን አውልቄ… እዚህ አልጋ ላይ ወጥተን ምናምን ማለቴ ነው… በጣም አምሮኛል…ስንት ወር ነው የምሰቃየው…?››ብሶቴን ተረተርኩት፡፡

‹‹እሱማ አይሆንም፡፡››

‹‹ለምን አይሆንም?››

‹‹አፈቅርሀለሁ… ግን ጊዜው አሁን አይደለም…ገና 18 ዓመት እኮ አልሞላኝም፡፡ በዛ ላይ የሃይእስኩል ትምህርቴንም አልጨረስኩም፡፡››

‹‹ስንት ዓመትሽ ነው?››

‹‹17 ዓመት ከ11 ወር…››

‹‹እና ታዲያ ሰው ለሚወደው እንኳን አንድ ወር ይቅርና አንድ ዓመትስ ቢያጭበረብር ምን አለበት?››

‹‹እንደ እናቴ መሆን አልፈልግም፡፡››

‹‹እንዴት እንደ እናትሽ?››

‹‹እሷም 10ኛ ክፍል እያለች ነው እኔን ያረገዘችው፡፡በዛ የተነሳ ትምህርቷን አቋርጣ ብዙ ስቃይ ተሰቃይታለች፡፡ ብዙ ብዙ መከራ ካሳለፍን በኋላ ነው በቅርቡ ህይወታችን የተስተካከለው፡፡››

‹‹እኔ እኮ ብታረግዢም አፈቅርሻለሁ..ማለቴ አገባሻለሁ፡፡››

‹‹አባቴም እሷን እንደዛ ነበር የሚላት…፡፡የእውነት እንዳረገዘች ስትነግረው ግን የራስሽ ጉዳይ ነበር ያላት፡፡››

‹‹እሺ በቃ በኮንዶም እንጠቀም..ህይወት ትረስት፣ሴንሴሽን፣ሜምበርስ ኦንሊ… የፈለግሽው አይነት አለ፡፡››

‹‹እንዴ ዲኬት ነው እንዴ የምትሰራው…? ይሄ ሁሉ ኮንደም ምን ልታደርግ ሰበሰብከው…?››ያላሰብኩትን መስቀለኛ ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ባክሽ አንድ ዲኬት የሚሰራ ጓደኛዬ ነው አምጥቶ ለማንኛውም እያለ ቤቴ የሚያስቀምጠው፡፡››

‹‹ጥሩ…. ግን ድንግል ነኝ… ድንግልናዬን ደግሞ በኮንደም አላስወስደውም፡፡››

‹‹እኔ እኮ ድንግልናውን አልፈልገውም..፡፡››
‹‹……እና አውልቄ ላስቀምጠውና ተጠቅመህ ከጨረስክ በኃላ መልሼ ላጥልቀው?››ንግግሯ ከማበሳጨትም አልፎ አሳቀኝ፡፡

‹‹እና ምንድነው መፍትሄው?››

‹‹ምታፈቅርኝ ከሆነ ጠብቀኝ?››
‹‹እሱማ አፈቅርሻለሁ፡፡››
👍865👏2👎1
‹‹ጐሽ ስለዚህ ትጠብቀኛለህ ማለት ነው…?›› ብላ ከመቀመጫዋ ተነስታ በስሱ እና በስስት ከንፈሬን ስማ እንድሸኛት ጠየቀችኝ፡፡እኔም እንዳለቺኝ አደረግኩ፡፡በቃ ተመለስ እስክትለኝ ድረስ ሸኘኋት…፡፡ተመለስኩና የቀረውን ወይን በንዴት መጠጥኩት..ምጥጥ አድርጌ ሳጠናቅቅ 12 ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡አልጠገብኩም… ፡፡ቤቴን ዘግቼ ወጣሁና ሰፈራችን ከሚገኘው ግሮሰሪው ተሰየምኩ፡፡ቢራ አዘዝኩ ፡፡ሁለት ሰዓት ሲሆን ጥግብ አልኩ..ጥግብ አልኩና ስልኬን በማውጣት ደወልኩ.. ባለቀይ ቂጥ   ባለቤቷ ጋር፡፡

‹‹ሄሎ፡፡››

‹‹ሄሎ ማን ልበል?››

‹‹የምን ማን ልበል ነው… ? ምንድነው ምትረብሺኝ፡፡››አንቧረቅኩባት፡፡

‹‹ይቅርታ የተሳሳትክ መሰለኝ፡፡››

‹‹አልተሳሳትኩም ባክሽ፡፡››

‹‹እና አላወቅኩህማ፡፡››

‹‹እኔም እኮ አላውቅሽም..ቂጥሽን ግን… ወይ ቂጥ›› 

ሳቋን አንጣረረችው‹‹አንተ ጉደኛ..አንተው ነህ?››

‹‹አዎ እኔው ነኝ..ፈፅሞ ልረሳው እኮ አልቻልኩም፡፡››

‹‹እሱማ እኔም ደግመህ እያየኸኝ እየመሰለኝ አስሬ እየተገላመጥኩ  ኃላ ኃላዬን ሳይ ነው የዋልኩት.. አሳቀቅከኝ፡፡››
‹‹አትይኝም..ታዲያ ደግመሽ ለምን አታሳይኝም?››

‹‹ኸረ ባክህ!!! ደግመህ ማየትም ያምርሀል..?በትክክል ድጋሚ ማየት ፈልገህ ቢሆን ኖሮማ ቀን ትደውልልኝ ነበር፡፡›› አለችኝ፡፡ ምን ታድርግ… ቀኑን በእንዴት አይነት መከራ ውስጥ እንዳሳለፍኩ አታውቅም….ሀይሚን በእጄ ይዤ እንዴት እሷ ጋር ልደውል አቅም ይኖረኝል፡፡ አሁንም ሀይሚ የጋተችኝ ንዴት እና በገዛ እጄ የተጋትኩት መጠጥ ናቸው ተባብረው ድፍረቱን የሰጡኝ፡፡ አይገርምም ግን ሀይሚና ይህቺ ባለቀይ ቂጧ ያላቸው  ልዩነት..ፍጹም ተቃራኒ ናቸው፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose



ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
😁27👍206👎2
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን

====================
‹‹ካሰብሽበት አሁንም ቀን ነው፡፡››
‹‹አንተ ቤተሰብ ያለኝ ሰው እኮ ነኝ፡፡››
‹‹አንቺ እሺ ይኑርሽ.. ያደነዘዘኝን ቂጥሽን ግን ላኪልኝ፡፡››መቼስ የምላሴ ፍሬኔ ብጥስጥስ ብሎብኛል፡፡
‹‹ናና ውሰደዋ፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ፡፡››
‹‹እውነትህን ነው?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው..ትናንት የተለያየንበት ቦታ ስደርስ ደውልልሻለሁ››
‹‹ያ እኮ ሰፈሬ አይደለም ብላ …የእሷን ትክክለኛ ሰፈር በምልክት ነገረችኝ.. ሂሳብ እንዴት እንደከፈልኩ.. እንዴት ተንደርድሬ ሰፈሯ እንደደረስኩ አላውቅም..ግን ስደውልላት ባሏ ተከትሏት ቢወጣስ..?የራሱ ጉዳይ ‹‹የቆመበት የቆመ ነገር አያይም››ይባል የለ፡፡ ደወልኩላት… ከአምስት ደቂቃ በኃላ መጣች፡፡ጨለማ ውስጥ ሆኜ ያለሁበትን ቦታ በእጅ ምልክት ጠቆምኳት..መጣች፡፡
‹‹አንተ ጉደኛ!!!››
በቃላት መልስ ከመመለሴ በፊት ጐተትኩና ከሰውነቴ አጣብቄያት ከንፈሯን ገመጥኳት ፡፡የሀይሚን እልክ በእሷ እየተወጣሁ ያለው መሰለኝ፤ በግድ ነው ያስለቀቀቺኝ‹‹አንተ ሰፈሬ እኮ ነው ያለሁት…ሰው ቢያየኝስ?››አለችኝ፡፡ ንግግሯ ደስ አሰኘኝ…ሰፈሯ ባይሆን ኖሮ በመሳሟ ደስተኛ ነች ማለት ነው፡፡
‹‹ባክሽ ጭለማ ውስጥ ነው ያለነው..ማንም አያይሽም፡፡››
‹‹ወይኔ ጉዴ!!!››አለች ድንገት ራሷን ይዛ እየተርበተበተች፡፡
‹‹ምነው….?ምን ሆንሽ…?›.
‹‹ባሌ መጣ …ባሌ፡፡››
በድንጋጤ ተሸቀንጥሬ ጨለማ ውስጥ ተሸገጥኩ፤እሷ በቆመችበት ሆና በሳቅ ፍርስ አለች‹‹ሲያዩህ ጀግና ትመስላለህ››
ከተወሸቅኩበት ወጣሁና ወደ እሷ በእርጋታ እየቀረብኩ ‹‹ጀግናማ ጀግና ነኝ ላንቺ ደህንነት አስቤ አስጂ..፡፡››
‹‹እሱን እንኳን ተወው..ጀግና አናውቅም እንዴ?››
‹‹ግን ባልሽ እቤት ነው?››
‹‹ባሌ እቤት ቢኖር..እንዲህ አጥር ስር አስደግፌህ አዋራሀለው፡፡››
‹‹ጥሩ አጋጣሚ ነው ፊልድ ሄዶል ማለት ነው››..አንገቷን ወደ መሬት ደፍታ ዝም አለች፡፡ግራ ገባኝ‹‹ምነው ያልኩሽን ሰምተሸል?››
‹‹አዎ ባሌ የሞተብኝ በቅርብ ነው፡፡ ሰሞኑን ነው ጥቁሩን የሀዘን ልብሴን ያወለቅኩት ››ደነገጥኩ፡፡የተደፈነ ልብ ሸሽቼ ስመጣ የተሸነቆረ ልብ ገጠመኝ እንዴ..?
‹‹ይቅርታ›› ብዬ ዳግመኛ ወደ ሰውነቴ አጣበቅኳትና ከንፈሯ ላይ ተጣበቅኩ፡፡እጄ ትናንትና ያደነዘዘኝ ቂጦ ላይ አርፎል… ቃተተች፡፡ እንደምንም ተላቀቀቺኝና ‹‹እዚሁ ብትንትኔን አወጣኸው እኮ..በዛ ላይ ረሀብተኛ ነኝ፡፡››
‹‹እኔም ጠኔ ሊጥለኝ ትንሽ ነው የቀረኝ፡፡በቃ ይዘሺኝ ወደ ቤት ግቢያ..››
‹‹ወዴት?››
‹‹ወዳንቺ ቤት ነዋ፡፡››
‹‹እንዴ ልጄ እኮ አለች..በዛ ላይ ሰራተኛዋም….››
‹‹እሺ የሆነ ሰበብ ፍጠሪና ወደ እኔ ቤት ወይም ወደፈለግሽበት ሌላ  ቦታ ይዤሽ ልሂድ፡፡››
‹‹እሱማ አይቻልም..ውጭ ለማደር ምንም የምሰጠው ምክንያት የለኝም..ይልቅ ደፋር ከሆንክ አንድ ሀሳብ አለኝ፡፡››
‹‹ኸረ አፄ ቴዎድሮስ አጐቴ ነው… ጀግንነቱ ከደማችን ነው ሚንጠባጠበው፡፡››
‹‹ከ3-4 ሰዓት ባለው ጊዜ ይተኛሉ ..መኝታ ቤቴ ለብቻዬ ስለሆነ ስደውልልህ ትመጣና ትገባለህ..ታዲያ ለሊት 11 ሰዓት ወጥተህ ለመሄድ ከተስማማህ ነው ?››
ጥብቅ ብዬባት ሳምኳት እና ‹‹ቂጥሽ ብቻ ሳይሆን ልብሽም ቀይ ነው..ተስማምቼያለሁ፡፡››
‹‹ታዲያ እስከዛ የት ትቆያለህ?››
‹‹ችግር የለውም..ወደኃላ ተመልሼ በቅርብ የሚገኝ አንዱ ቡና ቤት አመሻለሁ… ስለ እሱ አታስቢ አንቺ ብቻ እንዳልሺው አድርጊ፡፡››
‹‹ችግር የለውም …አሁን ግን ሱቅ ዕቃ ልግዛ ብዬ ስለወጣሁ  መመለስ አለብኝ፡፡››
‹‹ታዲያ የገዛሽው ዕቃ የታል?››
‹‹አጣኋ…ባለሱቆቹ የለንም ጨርሰናል አሉኝ፡፡›› ብላ ጉንጬን በስሱ ስማኝ እየፈገገች ወደ ግቢዋ ተመልሳ ገባች፡፡››
አቤት የሰው ልጅ ልዩነት ድሮም ከህፃን ጋር መከራዬን ሳይ መኖሬ እንዲህ ትናንት ተዋውቆ ለዛሬ ብን ማለት እያለ ስድስት ወር ሙሉ  ስዳክር መኖሬ..አምኜ ወደ ኃላ ልመለስ አልቻልኩም፡፡እንዴ የሆነ ነገር ቢያጋጥመኝስ..? ድንገት ሳልሰማ ጉልበተኛው መንግስታችን ሰዓት እላፊ አውጆ ቢሆንስ…?ድንገት ዘራፊዎች ሞባይሌን ቢመነትፉኝስ በምን ደውዬ አገኛታለሁ…?ኸረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን እንጂ በእንደዚህ አይነቱ ቀን ድንገት የሚፈጠር ስንት አደናቃፊ ነገር አለ መሰላችሁ፡፡ለሀይሚ ተብዬዋ እንኳን ያን ሁሉ ሰዓት በባዷ አባክኜ የለ…ያደረግኩት አንድ ነገር ቢኖር እዛው ፊት ለፊቴ ካለች አንድ ትንሽ ኪወክስ ሄጄ ጭንብል መሸመት ነው፡፡ሶስት እሽግ ህይወት ትርስት..ሶስት እሽግ ሰንሴሽን ሸመትኩና በእያንዳንዱ ኪሴ ሁለት ሁለት በታትኜ ከተትኩ፡፡
አንድ ወንዳ ወንድ የሆነች የሱቁ ሻጭ‹‹ምነው የወር ቀለብ ነው እንዴ?›› አለቺኝ፡፡
‹‹ምነው ችግር አለው?››
‹‹ለምን ችግር የለውም ፡፡ ሆነ ብለህ ምርትን ከተገቢው በላይ በማከማቸት የዋጋ ንረት ለመፍጠር አስበህ ቢሆንስ?››
‹‹አይዞሽ አትስጊ ከተረፈኝ ጥዋት መልስልሻለው ›› አልኳት እና መልሼ ጨለማዬ ውስጥ ተወሸቅኩ፡፡3፤15 ሲሆን ተደወለ.. ባለቂጧ መስላኝ ተንደርድሬ አፈፍ አድርጌ አነሳሁና‹‹እሺ ተኙልሽ››
‹‹አዎ ልተኛ ነው››አለችኝ፡፡አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ.. ከራማዬ ነው ቡን ያለው፡፡ ሀይሚ ነበረች ደዋዮ፡፡አሁን በዚህ አሳሳች ሰዓት  ማን ደውይ አላት?
‹‹ሄሎ ምነው ዝም አልከኝ፤አኩርፈኸል እንዴ?››
‹‹አይ ለምን አኮርፍሻለሁ?››
‹‹ደግሞ ውጭ ነው እንዴ ያለኸው...፡፡ንፋስ ነገር ይሰማኛል›› ብላኝ ቁጭ፡፡ሁሉም ሴቶች ከጥንቆላ መንፈስ የተገነባ ስድስተኛ የስሜት ህዋሳት አላቸው…፡፡ይሄ ጉዳይ ሁሌ ይገርመኛል፡፡ከሆነች ሴት ጋር አፍ ለአፍ ገጥመህ ስታወራ…ወይንም የሆነች ሴት ልትስም አፍህን አሞጥሙጠህ ወደ ፊት መጓዝ ስትጀምር..ወይ ለአንዴ ልስረቅ ብለህ ሱሪህን በማውለቅ ላይ ሳለህ…ስልካቸው ጭርርርርርር ይልብህና ያሳቅቅሀል፡፡
‹‹ባክሽ ደብሮኝ እቤቴ በረንዳ ላይ ቁጭ ብዬ ከዋክብት እየቆጠርኩ ነው››
‹‹አውቄያለሁ ደብሮሀል ማለት ነው..?ግን ለቀኑ ነገር ተረድተኸኛል አይደል…?››ለዚህ ጥያቄዋ መልስ ከመመለሴ በፊት ሌላ ስልክ ዌይቲንግ ገባብኝ..ቂጣሟ ነች፡፡
‹‹በጣም ነው የተረዳሁሽ የእኔ ፍቅር፡፡አሁን ግን ሀለቃዬ እየደወለልኝ ነው..ላናግረውና መልሼ ደውልልሻለሁ፡፡››
‹‹አይ አያስፈልግም ፍቅር ..ልተኛ ስለሆነ ደህና እደር… ነገ ትደውልልኛለህ..ደግሞ አፈቅርሀለው እሺ፡፡››አለችኘ፡፡
‹‹እኔም አፈቅርሻለሁ፡፡›› አልኩና ዘጋሁት ..አያችሁልኝ አይደል፡፡‹‹አፈቅርሀለሁ፡፡››ብላኝ እኮ አታውቅም፡፡ሁልጊዜ ከስልክ ልውጥ  በኃላ ‹‹አፈቅርሻለሁ›› ስላት ‹‹እኔም›› ብላ ነው ምታሳርገው፡፡ ዛሬ ግን እኔን ለማሳቀቅ እና በአእምሮዬ ፀፀት ለመርጨት ሆነ ብላ አቅዳ እና አልማ ‹‹አፈቅርሀለሁ›› አለችኝ፡፡..ሞኟን ትፈልግ …በዚህ ሰዓት ለእሷ ንግግርም ሆነ ለአዕምሮዬ ፊት አልሰጣቸውም፡፡….
የቂጣሟን ስልክ አነሳውት…..‹‹ሄሎ››
‹‹ና በቃ … በራፍ ላይ ስትደርስ ደውልልኝ››
‹‹በመጀመሪያውስ ከበራፍሽ መች ተንቀሳቀስኩ››
‹‹እስከአሁን እዛው ነኝ እንዳትለኝ?››
‹‹አልኩሽ..ከስልክ እንጨቱ ጋር ተጣብቄልሻለሁ፡፡››
‹‹እውነትም ቀንዝሮብሀል..እሺ መጣሁ ››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡የውጩ በራፍ ተከፈተ፤ ጐትታ ወደ ውስጥ አስገባችና መልሳ ዘጋችው፡፡በግቢው ሆነ በቤታቸው ምንም አይነት መብራት አይታይም፡፡‹‹ምነው መብራ ተቆርጦባችሁ ነው?››በሹክሹክታ ጠየቅኳት፡፡
👍778😁2
‹‹አንተን ለማስገባት እራሴው ነኝ የቆረጥኩት…እቤቱ ጋ እንደተጠጋሁ ወደ ሳሎኑ በረንዳ ሳቀና..‹‹ኸረ ባክህ እንደ አባወራ በፊት ለፊት በር መግባት ያምርሀል? ››ብላ በመጐተት ወደ ጓሮ ይዛኝ ሄደችና አንድ መስኮት ጋር ስንደርስ ቆመች ፡፡መስኮቱ በቁመት ከፍ ያለ ነው፤ግን ዘዴኛ ነች መሰላል አገድማበታለች፡፡ትከሻዬን ተደግፋ በመሰላሉ እየተራመደች ቀድማኝ ገባች፤ ተከተልኳት.. መስኮቱን ዘጋችው፡፡
‹‹ አልጋው ላይ ተቀመጥ፡፡›› አለችኝ..ባትለኝስ እኔ ሀይሚን አይደለው ኩርሲ ላይ የምቀመጥ ፡፡ፍልስስ ብዬ አልጋው ላይ ተቀመጥኩ፡፡ክፍሉ በሻማ ብርሀን ደምቋል
‹‹መብራቱ የእውነት የለም?››
‹‹ባክህ ከቆጣሪው አጥፍቼው ነው..ምን ይታወቃል የሆነ ነገር ፈልጋ ልጄ ወደ መኝታ ክፍሌ ብትመጣ እንኳን አንተን መደበቅ እንድችል  ብዬ ነው፡፡››
‹‹አንድ ልጅ ነው ያልሺኝ?››
‹‹አዎ በልጅነቴ የወለድኳት ልጄም ጓደኛዬም ነች፡፡››
‹‹ትልቅ ነቻ?››
‹‹አስራ ስምንት እየተጠጋት ነው፡፡››
‹‹አስራ ስምንት?››
‹‹አዎ-ምነው?››

‹‹አይ 18 ዓመት ልጅ ያለሽ ሳይሆን አንቺ እራስሽ የአስራ ስምንት ዓመት ልጃገረድ ነው የምትመስይው፡፡››
‹‹ፎገርከኝ ማለት ነው…?አይዞህ አግባኝ አልልህም.. ቂጤን ደግመህ ለማየት እንጂ የትዳር ጥያቄ ልታቀርብልኝ እንዳልመጣህ አውቃለሁ?››
‹‹ከተመቸሺኝ የት ይቀራል..ግን ብዙ ዓመት በትዳር አሳልፈሻል ማለት ነው?››
‹‹አይ 6 ዓመት ብቻ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ ከመጋባታችሁ በፊት ነው የወለዳችሁት ማለት ነው?››
‹‹አይደለም ለሟቹ መውለድ አልቻልኩም…›› ይሄንን ስትናገር ልብሷን አውልቃ ዕርቃኗን ቆማ ነበር..፡፡ በደብዛዛው ብርሀን ተያየን፡፡ ተንደርድሬ ከአልጋው ላይ በመነሳት ተለጠፍኩባት ፡፡ከዛ በኃላ ምን ልበላችሁ ሁለት ረሀብተኞች ተገናኝተው የሚፈጠረውን መገመት አይከብዳችሁም፡፡ሀይሚ ይብላኝልሽ ላንቺ እንጂ እኔስ የቅንዝር አምላክ በነፍስ ደረሰልኝ፡፡ስንት ሰዓት ፍትጊያው ተጠናቆ እንቅልፍ እንደወሰደን ትዝ አይለኝም፡፡ሁለታችንም በሌላ ቀን ተገናኝተን ስለመድገማችን እርግጠኞች ስላልነበርን ይመስለኛል ውልቅልቃችን እስኪወጣ ነው ስንጋልብ ያደርነው ፤የባነነው በራሳችን ጊዜ ነቅተን ሳይሆን በበር መንኳኳት ነበር
‹‹እማ..እማ ረፈደብኝ …ትምህርት ቤት ሄጄያለሁ›› በሰመመን ነው የሰማሁት፡፡ ብቻ ሁለታችንም በርግገን በድንጋጤ ከተኛንበት በመፈናጠር ወዲህ ማዶ እና ወዲያ ማዶ ካልጋው ወርደን ቆምን፡፡..እርቃናችንን ነን..ሁሉ ነገሯን እስክጠግብ በግልፅ አየኋት፡፡
‹‹አንተ ወይኔ ቅሌቴ!!! ››እያለች ወለሉ ላይ የተጣለውን ፓንቷን ከወደቀበት አንስታ ወደ ቁም ሳጥኑ ሄደች፡፡..ያ አደንዛዥ ቂጧ ሰንበር በሰንበር ሆኗል፡፡ጥፍሮቼን አየኋቸው…  አድገዋል፡፡እኔም  ከወለሉ ላይ ልብሶቼን ተራ በተራ በመለቃቀምና በማራገፍ መልበስ ጀመርኩ፡፡ ሁለታችንም እኩል ጨረስን፡፡
‹‹በይ ቸው መስኮቱን ክፈቺልኝ ››አልኳት፡፡
‹‹እሱማ ጊዜው አለፈ ..አሁን አይሆንም፡፡››
‹‹ታዲያ ታግቼ መዋሌ ነዋ?››
‹‹እዚሁ ቆየኝ… ሰራተኛዋን ሱቅ ልኬያት ልምጣና በፊት ለፊት በር ትወጣለህ፡፡››ብላኝ የመኝታ ቤቱን በራፍ ከፍታ ወጣችና በላዬ ላይ ጠርቅማብኝ ሄደች፡፡ እኔም አልጋው ጠርዝ ላይ አረፍ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ‹‹አቤት ይህቺን ሴትማ መደጋገም አለብኝ..እርግጥ አሁንም ስሜቴ ያለው እዛችው ግትሯ ሀይሚ ጋር ነው… ቢሆንም ግን…፡፡››
በራፉ ተከፈተ‹‹ያው ውጣ››አለችኝ ፡፡ወጣሁ.. ተከትያት ሳሎን ገባሁ…. ወደ መውጫው በር ሳመራ‹‹ቁጭ በል እንጂ …ያልጋ መውረጃ ቁርስ በልተህ ትሄዳለህ፡፡››
‹‹ሰራተኛሽ ተመልሳ ብትመጣብኝስ?››
‹‹ትምጣ..አሁን ነው የመጣሀው..የሟች ባሌ ጓደኛ የነበርክ…አሁን ልትጠይቀኝ የመጣህ እንግዳ ነህ..በቃ ምን ችግር አለው?››
‹‹እሱስ ችግር የለውም፡፡››
ወደ ጓዲያ ሄደች..ቁጭ አልኩ፡፡ ሳሎናቸው ሰፊ ነው የሟች ባሏ ፎቶ ፊት ለፊት ግድግዳ ላይ ተንጠልጥሏል፡፡ የሚያምር ደልዳላ ሰው ነበር፡፡ኸረ ሌላም ፎቶ አየሁ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳሁና ተጠጋሁት ፡፡ባየው ባየው ያልገባኝ ፎቶ ‹‹ምነው?››አለችኝ በአንድ እጇ ትኩስ እንቁላል ፍርፍራ በሌላው ሁለት ብርጭቆ ሻይ በሰርቢስ ይዛ‹‹ይህቺ ልጅ….?››
‹‹አዎ ልጄ ነች፡፡››
‹‹ሀይማኖት ልጅሽ ነች?››
‹‹ሀይማኖት…!!! ታውቃታለህ?››ቀይ የነበረችው ሴትዬ በሽርፍራፊ    ሰከንድ ጭላሼት ለበሰች፡፡
‹‹እኔ እንጃ፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃ?››
‹‹የእሷ ጓደኛ የጓደኛዬ እህት ነች ….እዛ ቤት አብረው ሲመጡ        አውቃታለሁ፡፡››
‹‹ሁፍፍፍ..እንዴት አስደነገጥከኝ መሰለህ፡፡››
‹‹ለምን ደነገጥሽ?››
‹‹እንዴ ምን ይታወቃል…የዛሬ ልጆች እኮ የት እና ከማን ጋር          እንደሚውሉ መገመት ከባድ ነው…፡፡››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው.. እኔም ጉድ ሆኜያለሁ፡፡››
‹‹እንዴት ?››
‹‹ያንቺን  ቂጥ  አፍቅሬ  ነዋ፡፡››በማለት  አስቀየስኩ፤ 
‹‹የአንቺን  ልጅ አፍቅሬ፡፡›› ለማለት ነበር የፈለግኩት፡፡
ቁርሴን በላሁና ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ ፤ ቀጥታ ወደቤት ነው የሄድኩት፡፡ ሰውነቴ ድክምክም ውስጤም እርብሽብሽ ብሎብኛል፡፡አሁን እንዴት ነው የማደርገው..? የእኔ እና የሀይሚ ጉዳይ አበቃለት ማለት ነው ? ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ … ኪሱ ቆረቆረኝ … እጄን ስሰድ ያልተከፈት ሁለት እሽግ ኮንደም፡፡ልቤ ትርትር አለ፡፡ሌላኛው ኪሴ ገባሁ፡፡ አዛም እንደታሸገ፡፡ ማታ ማሰቢያ ጭንቅላቴን እቤት ነበር እንዴ ረስቼው የሄድኩት….? እንዴት ኮንደም በኪሴ እንዳለና መጠቀም እንዳለብኝ ለማስታወስ ሚሆን ሜሞሪ አጣለሁ.... ? ወይ ንዴት!!!ወይ ስካር!!! ወይ መስገብገብ!!! ውጤቱ እንዲህ ይሁን?
ወይ እኔ…!!!ወይ ሀይሚ..!!!ወይ ቂጣሟ…!!!

ተጠናቀቀ

ነገ በአዲስ ታሪክ እንገናኛለን

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose


ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍72😁193👎3🥰1😱1
#የጣት_ቁስል


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ

አማላጅ

ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም   አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡

መጣራታቸውን ትተው "ደህና አደራችሁ መልካሙ" ? አሉ፡፡ ቄስ አሻግሬ ፤

አቀርቅረው ከሚያነቡት መፅሃፍ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው "እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደሩ" ? አሉ ፡፡ ቄስ መልካሙ፡፡ ንስሃ አባታቸው ያለወትሯቸው በጥዋት በመምጣታቸው የመደናገጥ ምልክት እየታየባቸው ፡፡ ፀበል ሊረጩን ይሆን ? ሳንነግራቸውና ሳንዘጋጅ ፤ እነሱም ሳይነግሩን ፤ በሰላም ይሆን የመጡት? ከራሳቸው ሃሳብ ሳይወጡ የተናገሩት ነበር

"አንተን ፈልጌ ነበር የመጣሁት"፡፡ እደጅ ላግኝህ አሉ ቄስ አሻግሬ ፡፡ ለስለስ ባለ አነጋገር ፡፡

"ለምን እንደተፈለጉ ባያውቁም "ምነው ደህና አይደሉም እንዴ"?

አይ ደህና ነኝ ፡፡ ለጉዳይ ፈልጌህ ነበር አሉ
ከየት መጀመር እንዳለባቸው ግራ ቢገባቸውም "አቶ ለማ ልጅህን ለልጄ እንዲሰጡኝ አማላጅ ሂድልኝ ብሎኝ ነው የመጣሁት"፡፡ ብለው ሃሳባቸውን ሳያቋርጡ በመቀጠል አቶ ለማ ሽፈራው ጥሩ ሰው ናቸው፡፡ ዘራቸውም ቢሆንም ምንም አይወጣለትም ፡፡ ልጁም የተባረከ ፤ የተመሰገነ ፤ ጨዋ ፤ ድምፁም የማይሰማ ማለፊያ ገበሬ ነው" አሉ፡፡

ቄስ መልካሙ ያልጠበቁትና ያላሰቡት ነገር ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው ምን ማለት እንዳለባቸው አብሰለሰሉ፡፡ የማይሆን ነገር ነው፡፡ አሁን እድላዊትን አግቢ ብላት ትምህርቷን ትታ የምታገባ አይመስለኝም፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር እየተሟገቱ ከቆዩ በኋላ "እንግዲህ
ከቤተሰብና ዘመድ ጋር መክረን መልስ ብንሰጥ ይሻላል፡፡ አሁን እኔ ለብቻየ የምወስነው ነገር የለም" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመባባት እያለም ቢሆን፡፡

"ታዲያ ቀነ ቀጠሮው ለመቼ ይሁን" ? አሉ፡፡ መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል የአገሩ ባህልና የተለመደ መሆኑን ስለሚያውቁ ፡ተመልሰው የሚመጡበትን ቀን በጉጉት ለመስማት እየጠበቁ ፡፡

"ዛሬ ቀኑ ሮዕብ አይደለም፡፡ የዛሬ አስራ አምስት ቀን ይመለሱ፡፡ እኛም እስከዛ ብንመካከርበት ይሻላል" በማለት መልስ ሰጧቸው፡፡

ይሁን መልካም ነው፡፡ ብለው የተሰጣቸውን ቀነ ቀጠሮ ተቀብለው ከቄስ መልካሙ ጋር ተሰነባብተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡

ንሰሃ አባታቸውን ከሸኙ በኋላ ፤ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ በመጨጊያቸው ላይ ተቀመጡ፡፡ አገጫቸውን በቀኝ እጃቸው ደገፍ አደረጉ፡፡ ትክዝ ባለ አንደበት ስለልጃቸው እድላዊት በውስጣቸው ማብሰልሰል ተያያዙት፡፡

ወ/ሮ አሰገደች ከማድቤት ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤት እየሄዱ ባለቤታቸው ከወትሯቸው በተለየ ተክዘው ተመለከቷቸው፡፡ እርምጃቸውን ገታ አድርገው "ምነው ቄስ አሻግሬ አመጣጣቸው በደህና አይደለም እንዴ"? አሉ ፤ ለባለቤታቸው ፡፡

"አይ ደህና" ናቸው ፤ አሉ፡፡ ሃዘን ይሁን ትካዜ በተቀላቀለበት ንግግር፡፡

ወ/ሮ አሰገደች የንሰሃ አባታቸው ዛሬ በጥዋት አመጣጣቸው ለምን እንደሆነ ባያውቁም የባለቤታቸው መተከዝ አስጨንቋቸዋል፡፡ "በሰላምማ አልመሰለኝም" አሉ፡፡ ወደ ባለቤታቸው እየተጠጉ፡፡

"የመጡትስ በሰላም ቢሆንም አቶ ለማ ሽፈራው አማላጅ ልከዋቸው ነው የመጡት" አሉ፡፡ የባለቤታቸውን ሁኔታ እየተመለከቱ፡፡

"የምን አማላጅ ነው?" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመርበትበት እያለ፡፡ የምን አማላጅነት እንደሆነ ለመስማት በመቸኮል፡፡

የአቶ ለማን ልጅ ታውቂዋለሽ ?"፡፡

"ትንሹን ነው ትልቁን?፡፡

"አይ! ትንሹን ይሁን ትልቁን አለየሁትም፡፡ አበበ የሚባለውን፡፡

ምን እንደሆነ ሳያውቁ "በሞትኩት ምን ነካው ያምስኪን ልጅ ከሰው ተጣላ" እንዴ ?፡፡

"እሱስ አልተጣላም፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው እድላዊትን ለአበበ ስጡኝ ብሎ ነው፡፡ ቄስ አሻግሬን አማላጅ ተልከው የመጡት"፡፡

ወ/ሮ አሰገደች ለመስማት የጓጉትና ልባቸው ተንጠልጥሎ ሲጠብቁት የነበረው ምን እንደ ሆነ ባያውቁም ከባለቤታቸው የሰሙት ያልጠበቁትና ያላሰቡት ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው መርዶ እንደ ተነገራቸው ያህል በዝምታ ተዋጡ፡፡ በሃሳባቸው ልጄን እማ አልሰጥም አስተምራለሁ፡፡ ትምህርቷን ሳትጨርስ አልድራትም፡፡ እሷም እሽ አትልም በዛ ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተባለች አገር የመሰከረላት ነች ፡፡ የልጃቸውን ሃሳብ እያወጡና እያወረዱ ከሔዱበት የሃሳብ ሰመመን ሳይመለሱ..

እና "አሁን ምን ይሻላል ትያለሽ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡ ከነጎዱበት የሃሳብ ሰመመን መለስ ብለው "እኔ ምን እላለሁ አንተ ምን አልካቸው?፡፡

"እኔማ ለዛሬ አስራምስት ቀን ተመልሰው እንዲመጡ ቀጥሪያቸዋለሁ፡፡ እኛም መመካከርና የእድላዊትን ፈቃድ ማወቅ ስላለብን ብየ ነው፡፡ ቀኑን ያስረዘምኩት፡፡ ለመሆኑ የሚሳካ ይመስልሻል ?፡፡

"እኔ እድላዊት ለማግባት እሽ የምትል አይመስለኝም፡፡በዛ ላይ ለትምህርቷ ያላት ፍላጎት ጎበዝ ተማሪ እንደሆነች ማንም ያውቃታል፡፡ እንደ እኔ ሃሳብ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ፤ ብታገባ ይሻላል፡፡ ትዳር ይደረሳል፡፡ የት እንዳትሔድ ነው፡፡ ብለው አሁን አንተ ምን ወሰንክ አሉ?፡፡

"ማድረግ ያለብንማ ሁለታችንም ተመካክረን መወሰን ነው፡፡ እንደ እኔ እድላዊት እሷ እንኳን ባትፈቅድም ማግባት አለባት፡፡ ለትዳር ደርሳለች፡፡ ትምህርቷም ይበቃታል፡፡ ከአሁን በኋላ፤ ከትምህርቷ ቀርታ የቤት ሙያ መልመድ አለባት" አሉ፡፡

እድላዊት እንደ እናቷ የጠይም ቆንጆ ሰለክለክ ያለች ፤ ቁመናዋ እና ጥርሶቿ ልክ እንደ አባቷ ከሩቅ የሚያማልል ነው፡፡ ታዲያ የጠይም መልከመልካሟን ቆንጆ እንድላዊትን የሚያያት ሁሉ ሳይጎመዣት
አያልፍም ነበር ፡፡

አበበ ለማ እድላዊትን ሊያገባት አማላጅ የላከው በአጋጣሚ ከወንድሟ ከተመስገን ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ባያት ማግስት ነበር፡፡ለቤተሰቦቹ ነግሮ አማላጅ እንዲላክለት ያደረገው፡፡

ወ/ሮ አሰገደች እድላዊትን አልድርም ፤ አስተምራለሁ ፤ እያሉ በሃሳባቸውም ሲፎክሩ የነበሩት በባለቤታቸው ቁጣ ያዘለ ንግግር ተቀየሩ፡፡

አንተ ከወሰንህ ታዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እኔም ማግባት አለባት ባይ ነኝ፡፡ ማግባቷ ለእኔም ትጠቅመኛለች፡፡ ብታመም እንኳን ጠያቂ ዘመድ በቅርብ የለኝ፡፡ የምታገባበት ቦታ ቅርብም በመሆኑ እየመጣች ትጠይቀኛለች፡፡ በፍራትም ቢሆን ከባለቤታቸው ሃሳብ ላለመውጣት የተናገሩት ነበር፡፡

ቄስ መልካሙ የባለቤታቸውን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ አንድ ላይ ካሰባሰቡ በኋላ፤ እድላዊትን አሁን የተባባልነውን ሁሉ ከትምህርቷ ስትመጣ ንገሪያትና ከትምህርት ቀርታ የቤት ውስጥ ስራ እንድትለምድ አድርጊያት አሉ፡፡ ቁርጥና ኮስተር ባለ ንግግር፡፡

"እሽ ነግሬያት እንድትቀር አደርጋለሁ ፡፡

እድላዊትና ተመስገን

የጥዋት ተማሪ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እድላዊት ከወትሮው በተለየ ምክንያቱ በምን እንደሆነ አላወቀችውም፡፡ ግራ ተጋብታለች ፤ ሰውነቷ ይርበተበታል፡፡ ወደ ፊት መሔዷን ተወት አድርጋ አንዳንዴ ቆም በማለት ራሷን ለማረጋጋት ትሞክራለች፡፡

ተመስገንም በእህቱ መለዋወጥና ዝምታ ግራ ገብቶታል፡፡ ከአሁን አሁን ትነግረኛለች ብሎ ቢያስብም እድላዊት ግን የሆነችውን ለራሷ አላወቀችም፡፡ ምን እንደሆነችም ልትነግረው አልቻለችም ነበር፡፡

"ምን ሆነሽ ነው አሞሻል እንዴ?፡፡

"አላመመኝም ውስጤን ግን ፍራት ፍራት ይለኛል፡፡

"ምነው በሰላም ?፡፡
👍8911🥰1😱1🎉1
"እንጃ ውስጤ ሰላም አይሰማኝም፡፡ ዛሬ ደግሞ ሲያቃዠኝ ነው ያደረው"፡፡

ተመስገን ቅዠት ይሁን ህልም መፍታት ባይችልም ፤ ለመስማት ስለፈለገ ብቻ "ምንድ ነው ያቃዠሽ ንገሪኝ" አላት፡፡

"ቅዠት ይሁን ህልም ባላቀውም የሆነ ሰው ይመስለኛል ፤ ሲያባርረኝ እየሮጥሁ ከእሱ ለማምለጥ ስል ገደል ገባሁ፡፡ ከዚያ ብንን ስል ያለሁት መኝታየ ላይ ነው" አለች፡፡ አሁንም የፍራትና የጭንቀት ምልክት እየተሰማት፡፡

ተመስገን በግምትም ቢሆን ገደል መግባቷ መጥፎ ህልም ሳይሆን አይቀርም ብሎ በውስጡ አሰበ፡፡

እድላዊት የነገረችውን ህልም ከአሁን አሁን ፈቶ ይነግረኛል ብላ ብትጠብቅም ሳይፈታላትና ሳይመልስላት ትምህርት ቤት ደረሱ፡፡

"ታመመሽ አስፈቅደን እንመለሳለን" አላትና ሁለቱም የሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ቢሆኑም ክላሳቸው ስለሚለያይ ተጨባብጠው ወደዬ ክላሳቸው ገቡ፡፡

እድላዊት ለትምህርት ያላት ፍላጎት ወደር የለውም ነበር፡፡ ዛሬ ግን በተፈጠረባት የጭንቀት ስሜት የምትወደው ትምህርት አስጠልቷታል፡፡ እንደ ነብር ዘሎ የሚውጣት መስሎም ታይቷታል፡፡

መድረስ አይቀርም ሰዓት ደርሶ ተማሪ ተለቀቀ፡፡ እድላዊት ትምህርት ቤት ይሁን የፀሎት ቦታ ያለችበት ተዘንግቷታል፡፡ የመለቀቂያ ሰዓት ደርሶ ውጡ ሲባል እንኳን አላመነችም ነበር፡፡ ከተማሪዎች ቀድማ ወጣች፡፡ ወንድሟን መንገድ ላይ ስትጠብቅ ቆይታ ሲመጣ አብረው ጉዟቸውን ወደ ቤት ቀጠሉ፡፡

"አሁንም አልተሻለሽም እንዴ? ብሎ እጇን ጨበጥ አደረጋት፡፡

"ከጥዋቱ አሁን ተሸሎኛል" አለች፡፡ የሆዷ መረበሽና ጭንቀት እየባሰባት ቢመጣም ወንድሟ ላለማስጨነቅ ብላ፡፡

ተመስገንም አይዞሽ፡፡ እያለ እያፅናናት እቤት ደረሱ፡፡

እናታቸው ወ/ሮ አሰገደች "መጣችሁ አሉ፡፡

"አዎ ፤ መጥተናል" አለች እድላዊት፡፡

በይ! ምሳችሁን ብሉና ተመስገን ከብቶቹን ውሃ ያጠጣ፡፡ አንች ስራ ትረጅኛለሽ ብለው ወደ ማድቤት ገቡ፡፡ እንጀራ ለመጋገር የገለባ ማገዷቸውን ማቀጣጠል ጀመሩ፡፡

እድላዊት ምሳዋን ተመግባ እንደደበራት እናቷን ለማገዝ ወደ ማድቤት ገባች፡፡ "ምን ልርዳሽ ? አለች፡፡ ወደ እናቷ እየተጠጋች፡፡

"አንች ወጡን ስሪ ፤ እኔ እንጀራውን ቶሎ ቶሎ ልጋግር፡፡ አባትሽም ከቤተክርስቲያን መምጫው ሰዓት ደርሷል"አሏት፡፡

እሽ ብላ መስራት ጀመረች፡፡ እናትና ልጅ የተኮራረፉ ይመስላል፡፡ ሁለቱም በዝምታ ተውጠው ስራ ስራቸውን ይላሉ፡፡

ወ/ሮ አሰገደች የእድላዊት ዝምታ ከምን የመጣ እንደሆነ ግራ ገብቷቸዋል፡፡ ዝም በማለቷ ተጠራጠሩ ፤ ሰምታ ይሆን እንዴ? ባል እንደመጣላት ; ማንስ ይነግራታል? ለነገሩ የዛሬ ወሬ አይደበቅም፡፡ ንፋስ የሚያወራው ይመስል ውሎ ሳያድር አገሩን ያዳርሰዋል፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሲከራከሩ ከቆዩ በኋላ፤ "ምን ሆነሽ ነው ዛሬ ያለወትሮሽ ዝም ያልሽው?

አሞሻል እንዴ? አሉ፡፡ ቁጣ የተቀላቀለበት በሚመስል ንግግር፡፡

"አላመመኝም" አለች እድላዊት፡፡

"እና ምን ሆነሽ ነው? አሏት፡፡ አሁንም ቁጣ ቁጣ በሚል ንግግራቸው፡፡

እድላዊት የእናቷ ቁጣ የተቀላቀለበት ንግግር አልገባትም፡፡ "ከትምህርት ስለመጣሁ ደከሞኝ ይሆናል፡፡ ሌላ ምንም አልሆንኩም" አለች፡፡ አቀርቅራ የወጥ መስሪያ ሽንኩርቷን እየላጠች፡፡

አይ! ድካም ከሆነ ምንም ማለት አይደለም፡፡ የሰማሽው ወሬ እንዳለ ብየ ነው አሉ፡፡ የልጃቸው መልስ ባይዋጥላቸውም፡፡

እድላዊት ግን የሆነችውንና የተሰማትን ለመናገር አልፈለገችም፡፡ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ "የምን ወሬ ነው የምሰማው? አለች እንደ መደንገጥ ብላ፡፡

ወ/ሮ አሰገደች ገና ሳይነግሯት የልብ ትርታቸው ጨመረ፡፡ እየፈሩ ብነግራት ምን ትል ይሆን? ብትደነግጥስ ምን ትሆናለች? በማለት እራሳቸውን አፅናኑ፡፡ ለመናገር ወሰኑ፡፡ ስልታዊ አነጋገር እንኳን አልተጠቀሙም፡፡ በቀጥታ "ካልሰማሽማ እኔው ልንገርሽ ባል መቶልሻል፡፡ ከነገ ጀምረሽ ትምህርት ቤት አትሔጅም፡፡ ትምህርቱን ትተሸ የቤት ውስጥ ሙያ ትለምጃለሽ አሏት፡፡

ታዲያ ወ/ሮ አሰገደች ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረው በመናገራቸው ለራሳቸው ቢቀላቸውም ለልጃቸው ግን ከሰማይ የመጣ ዱብዳ ሆኖባታል፡፡

እድላዊት በሰማችው ነገር ደነገጠች፡፡ በተቀመጠችበት ጉጉት ሆና ቀረች፡፡ አትናገር አትጋገር ፍጥጥ ብላ
እናቷን ታያለች፡፡

‹‹የአፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽ ሆነና ነገሩ›› ወ/ሮ አሰገደች በልጃቸው ሁኔታ ተደናግጠው ምነው ባልነገርኳት፡፡ እያወኩ ፣ ሆዴ እየፈራ ፣ እየተርበተበቱ ራሳቸውን መውቀስ ጀመሩ፡፡

እድላዊት እናቷ የተናገሯትን ማመን አቃታት፡፡ መልስም አልሰጠችም፡፡ ቀኑ ሁሉ ሲጨንቃት የነበረውና ሲያምሳት የዋለው ይሔ የወደፊት አላማዋንና ሃሳቧን ከግብ አይደለም ከማሃል እንኳን ሳይደርስ ወሽመጧን የሚቆርጥ መርዶ ሊያሰማት መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ ከሔደችበት የሀሳብ ሰመመን አልተመለሰችም፡፡ ባል! ባል! ባል! እኮ ባል መጥቶልሻል ታገቢያለሽ አለች እናቴ፡፡ በቃ ወስነዋል ማለት ነው?፡፡ የእኔ መጨረሻ ይሔ ሆነ?፡፡ በውስጧ እልህና ቁጭት አደረባት፡፡ ከወሰዳት የድንጋጤ መንፈስ መለስ አለች፡፡ ከየት መጣ ሳይባል እንባዋ ግራና ቀኝ በጉንጮቿ ላይ መውረዱን ተያያዙት፡፡

ቄስ መልካሙ ከቤተክርስቲያን ተመልሰው መጡ፡፡ እድላዊት እያለቀሰች ደረሱ፡፡ ምን ሆና ነው የምታለቅሰው ነገርሻት እንዴ? ባል እንደመጣላት" አሉ ለባቤታቸው፡፡

አዎ"ነግሬያት ነበር፡፡

"እና እሷስ ምንም አላለችሽም"?፡

"ምንም አላለችም፡፡ ይኸው እንደምታያት ዝም ብላ ትነፋረቃለች፡፡ እስኪ አንተን የምሰማህ ከሆነ ዝም እንድትል አድርጋት''

የባለቤታቸው መርበትበትና መረበሽን የተካፈሉት ይመስላል፡፡ እድላዊትን ለማናገር ሆዳቸው ፈራ ተባ አለ፡፡ "ምን ሆነሽ ነው? የምትነፋረቂው" አሏት፡፡ በፊታቸው ላይ የቁጣ ምልክት በማሳየት፡፡

እድላዊት የባሰ አባቷን ስታይ እንባዋን መቆጣጠር አቃታት፡፡ መልስ ለመስጠት ተርበተበተች፡፡ እልህ ተናነቃት፡፡ "ምን ሆነሽ ነው ትለኛለህ ? ስራህን ሰርተህ ከጨረስህ በኋላ!፡፡ ግን የማገባ ይመስልሃል ትምህርቴን ሳልጨርስ አላገባም፡፡ ቆሜ እቀራለሁ እንጅ ብላ እልህና ንዴት በተቀላቀለበት ንግግር አባቷን ከአሁን በፊት ደፍራ ተናግራቸው የማታውቀውን ተናገረቻቸው፡፡

ቄስ መልካሙ ከልጃቸው የሰሙት ንዴት የተቀላቀለበት ንግግር አስከፊና መመለሻ የሌለው መስሎ ታያቸው፡፡ ልጃቸውን ተቆጥተውና አስፈራርተው መናገር ስላለባቸው "ታገቢያለሽ"፡፡ ስለ ማግባትሽ ደግሞ አንች ሳትሆኝ የምትወስኝው እኔ አባትሽ ነኝ፡፡ አሁን ተነስተሸ ወደ ቤት ግቢ መነፋረቁን ትተሸ" አሉ፡፡ በዱላ የመምታት ያህል በሚሰማ ንግግራቸው፡፡

እድላዊት በአባቷ ቁጣ ብትደነግጥም እንባዋ ግን መውረዱን ቀጥሏል፡፡ እንባዋን ሳያቋርጥ እያለቀሰች ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ እራሷን አሟት ስለነበር መኝታዋን ሳታነጥፍ ጋደም እንዳለች እንቅልፍ ሸለብ አደረጋት፡፡

ተመስገን እቤት ሲገባ የሰማውንና ያየውን ትርኢት ማመን አቃተው፡፡ በሰማው ነገር ግራ ተጋባ፡፡ ሃዘንም ተሰማው፡፡ ሆዱ ተረበሸ፡፡ አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ በማይል የማይለካ እሩቅ የመድረስ አላማና ተስፋው ፍሬ ሳያፈራ አይደለም እንቡጥ እንኳን ሳይዝ መቀጨቱ ታወቀው፡፡ የእህቴ ምኞትና ተስፋ የእኔም ነበር፡፡ አሁን ግን አበቃለት ፤ አከተመለት፡፡ በሃዘን በተሞላ እና እንባ በተናነቀው አንደበቱ ሰው ሳይሰማው ለራሱ እየተጨናነቀና እያማረረ የተናገረው ነበር፡፡
👍7412
ቤተሰቦቹንም ሆነ እህቱን ሳያነጋግር ወደ መኝታው ሄደ፡፡ ጭንቀቱና መረበሹ የሚቀልለት መስሎት እራት እንኳን ሳይበላ መኝታው ላይ ጋደም አለ፡፡ መረበሹና ጭንቀቱን ሊያስታግስለት ግን አልቻለም፡፡ እንቅልፍ የሚባል አልወስድ ብሎታል፡፡ መኝታው የቆረቆረው ይመስል እየተገላበጠ ሌሊቱን ሁሉ አሳልፎ
ሳይወስደው ያደረው እንቅልፍ ሊነጋጋ አካባቢ መጥቶ ሸለብ አደረገው፡፡

ቄስ መልካሙ የተፈጠረው ነገር ሁሉ አሳስቧቸዋል፡፡ እድላዊትን በመቆጣታቸው እና በማስፈራራታቸው ተፀፅተዋል፡፡ ምነው? ባልተቆጣኋት፤ ቀስ ብየ ብመክራት ይሻል ነበር፡፡ አሁን ከሆነ ወዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እንግዲህ ነገ የተሻላት እንደሆነ ቀስብየ እመክራታለሁ፡፡ በስጋ ከባለቤታቸው ጋር ቢሆኑም በመንፈስ ግን የት እንደደረሱ ባይታወቃቸውም እራሳቸውን ለማረጋጋት ያወሩት ነበር፡፡

ወ/ሮ አሰገደች እንደ ባለቤታቸው በሃሳብ ፈረስ ነጉደው ሲመለሱ "የተመስገን ደግሞ ተደርቦ ማኩረፍ ምን ይሉታል?" አሉ ፤ ከባለቤታቸው መልስ የሚያገኙ መስሏቸው፡፡

ተመስገንና እድላዊት በተፈጠረው ነገር ከእናት አባታቸው ጋር አለማምሽታቸው ቤቱን በሃዘን የተዋጠ አስመስሎታል፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose



ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍622
አትሮኖስ pinned «#የጣት_ቁስል ፡ ፡ #ክፍል_አንድ ፡ ፡ #ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ አማላጅ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም   አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡ መጣራታቸውን ትተው "ደህና…»
#የጣት_ቁስል


#ክፍል_ሁለት


#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ

ቄስ አሻግሬ

ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡

ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡

ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡

አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡

"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡

"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡

"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡

"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::

"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡

አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡

"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡

"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡

ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡

አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡

እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?

ተመስገን

ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡

እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡

ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡

ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡

ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡

የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡

ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡

ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡

ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡

ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡

የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ

"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡

እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡

ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
👍735👏3
ተመስገን እህቱን ፍለጋ እንደወጣ ቶሎ አልተመለሰም፡፡ እየተንከራተተ አንዴ እራራቲ ፤ አንዴ ዶፋ ፤ አንዴ ብቻሽ እና በየቤተክርስቲያኑ እየዞረ ቢጠይቅም ቢያጠያይቅም ፤ ቢያስስም ፣ ቢያሳስስም እድላዊትን ግን ሊያገኛት አልቻለም ነበር፡፡ ተንከራቶ እህቱን ባለማግኘቱ በጣም አዘነ፡፡ የተፈጠረበት ቀን እስከ ሚያስጠላው ድረስ አምርሮ ረገመ፡፡ እያለቀሰ ቢውልና ቢያድርም የሱን እንባ እድላዊት ልትሰማለት አልቻለችም፡፡

እድላዊት እና ተመስገን ትምህርት ቤት እንኳን ሲሔዱ አንድ ቀንም ተለያይተው አያውቁም ነበር፡፡ በጣም ሲዋደዱ እና ፍቅራቸውን ላየ የሚያስቀኑም ልጆች ነበሩ፡፡

ተመስገን እህቱን ፍለጋ ሲወጣ በቅርብ የሚመለስ መስሎት ስንቅ እንኳን አልያዘም፡፡ እርሃብ ሲብስበት እና ሲጠናበት ከሰው ቤት እዳይለምን እፍረት እየያዘው ሳይጠይቅ ሲርበው ውሎ ሲርበው ያድራል፡፡ ለማደር ሲፈልግ ፀበለተኛ መስሎ ሲመሽበት ወደ አገኘው ቤተክርስቲያን ይሄዳል፡፡ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና ፀበለተኞች ከያዙት ስንቅ አካፍለውት በልቶ ሳይሆን ቀምሶ ያድር ነበር፡፡

ታዲያ የሚያውቀውንም ፣ የማያውቀውንም ፣ አገር አካሎ ከመድከም ውጭ ምንም ባለ ማግኘቱ ሲንከራተት ከርሞ ወደ ቤቱ ለመመለስ ሲያስብ የእናት አባቱን አይን ለማየት አስጠልቶት እኔም እንደ እድላዊት ብን ብየ በዚሁ ልጥፋ ወይስ ገደል እና ውሃ ውስጥ ገብቼ ብሞት ይሻላል፡፡ በውስጡ የተሰማውን ተናግሮ ሳይጨርስ ልቡ በሌላ ሃሳብ ይቀየርበታል፡፡ እህቴን ሳላያት ከምሞት ከቤት ከወጣሁ ቆይቻለሁ፡፡ ምን አልባት ተመልሳ እቤት መጥታ ሊሆን ይችላል፡፡ ብሎ በማሰብ ከራሱ ሃሳብ ጋር ሲሟገት እና ሲከራከር ቆይቶ ወደ ቤቱ ለመሔድ ወሰነ ።

ተመስገን ጉዞ ላይም እያለ በሃሳቡ ስለ እህቱ ማብሰልሰሉን ይሁን መጨነቁን አላቋረጠም፡፡ ምነው ያን እለት ማታ ባናግራት፡የምትሔድበትን እንኳን ትነግረኝ ነበር፡፡ ለእኔ አትደብቀኝም ነበር፡፡ ይሔ ሁሉ ስቃይና መንከራተትም አይደርስብኝም ነበር፡፡ ያለፈው እያናደደው ሲጓዝ መድረስ አይቀርም እቤቱ ደረሰ፡፡

እናት እና ልጅ ለብዙ ቀን ተለያይተው እንዳልቆዩ አብረው እንደከረሙ እና አብረው እንዳደሩ ሰላም እንኳን አልተባባሉም፡፡ በቀጥታ እድላዊት አልመጣችም እንዴ?" አላቸው፡፡ እልህ እና ንዴት በተቀላቀለበት አንደበት፡፡

"አይ! ልጄ ከየት ትመጣለች፡፡ እሳት የገባ ቅቤ ይታፈሳል እንዴ? እግዚአብሔር ባያድለኝ ነው እንጅ፡፡ ምነው እንዳሁኑስ የነገርኳት እለት ሞቴን ቢያደርግልኝ ይሻል ነበር"፡፡ እስካሁን በሔድህበት ቦታ እና አካባቢ ምንም ወሬዋን አልሰማህም ? አየኋት ፣ አልፋለች የሚል ሰው ጠፋ ልጄ? "አሉት፡፡ የአይናቸውን እንባ እየጠራረጉ ፡፡

ተመስገን ከእናቱ የሰማው መልስ ተስፋ አስቆረጠው፡፡ እድላዊት ወደ ቤት መታ እቤት አገኛታለሁ ያለው ሃሳብ አልተሳካለትም፡፡ መጓጓቱ እና ማሰቡ ከንቱ ሆነ፡፡ እንዳትገኝ አድርጋችሁ ከሸኛችኋት በኋላ፤ ማንስ አየሁ ይለኛል ? የትስ አገኛታለሁ?"፡፡

ወደ ቤት ሲመጣ እመንገድ ላይ እህል አምጣ እያለ እንደ አዲስ መሬት ያስቸገረው ሆዱ እቤት ሲገባ እድላዊትን ባለማግኝቱ በንዴት እና በብስጭት የራበው ሁሉ ጠፋ፡፡

ወ/ሮ አሰገደች የልጃቸው ብሶትና ብስጭት ተሰማቸው፡፡ ሳይታወቃቸው በግራና በቀኝ ጉንጫቸው ላይ እንባቸው እንደ ሃምሌ ዝናብ መውረዱን ተያያዘው፡፡ ታዲያ እንባቸው ሲወርድ ላየው ሰው ወላድ መሆን አይደለም ሰው መሆንም ያስጠላ ነበር፡፡ ደግመው ለመናገር እንባ ተናነቃቸው፡፡ መናገር አልቻሉም፡፡ አንደበታቸው ተሳሰረ፡፡ ከተቀመጡበት ተነሱ፡፡ እንባቸውን በቀሚሳቸው እየጠራረጉ ወደ ጓዳ ሊገቡ ሲሉ ራሳቸውን አዞራቸው ፤ ከቤቱ ግድግዳ ጋር ተላተሙ፡፡

ተመስገን እናቱ በልጇ መጥፋት ሆድ እንደባሳቸውና በሃዘን እንደ ተጎዱ ታወቀው የእድላዊት መጥፋት ሳያንሰው የእናቱ እንደዚህ መሆን የባሰ ስቅስቅ አድርጎ አስለቀሰው፡፡

ከተላተሙበት የቤት ግድግዳ ተመለሱ፡፡ እንደገና አዙሯቸው የቤቱ ወለል ላይ ወደቁ፡፡ ከወደቁበት ሳይነሱ

ጆሮ ግንዳቸውን በቀኝ እጃቸው ደግፈው አቀረቀሩ፡፡ ምን ነክቷቸው ከግድግዳ እንደተላተሙ ለማስታወስ እየሞከሩ ፤ ካቀረቀሩበት ቀና ሲሉ ልጃቸው እያለቀሰ አዩት፡፡ ማፅናናታቸውን ትተው ያቋረጡት ለቅሶ ተያያዙት፡፡

ቄስ መልካሙ ከስራ ቆይተው ሲመለሱ ቤቱ በሃዘን እና በለቅሶ ተሞልቷል፡፡ "ምንድነው ለቅሶው ; ልጄ መሞቷ ተሰማ እንዴ ? ምን ተፈጥሮ ነው "አሉ፡፡ አይኖቻቸው ላይ የእንባ ብዥታ እየታየባቸው፡፡

"የልጄን መሞት እማ ብሰማ አንዴ አልቅሼ እና እርሜን አውጥቸ አርፍ ነበር"፡፡ የገባችበትን እና የበላትን ጅብ አለመጮሁ ነው እንጅ ፤ የሚያስለቅሰኝ" አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡

ተመስገን አባቱ ሲመጡ ማልቀሱን ባያቋርጥም እያለቀሰ በአባቱ ፊት መቆየት አልፈለገም፡፡ እረስቷት ወደ ሰነበተው የመኝታ ቤቱ ተነስቶ ሄደ፡፡

"ተመስገን ምን አለሽ ? እንዴው ወሬዋን እንኳን የሰማ ሰው አላገኘም ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ ለባለቤታቸው ፡፡

"ያየ አይደለም ሰማሁ የሚልም አላገኘም፡፡ እሱም እንዴው ሲንከራተት ከርሞ ይሔው ሰውነቱ አልቆ መጣ፡፡ እኔ ደግሞ ሲሰነብት ጊዜ በዛው ሔደ ብየ ፈርቼ ነበር፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ፊቱን ወደ ቤት መለሰልኝ" እንጅ ፡፡ቄስ መልካሙ ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረውን እንባ በጋቢያቸው ጠራርገው መለሱት፡፡

"ምን እናደርጋለን ታዲያ እንግዴህ አንዴ ሲፈጥረን ተሰቃዩ ብሎን የለ፡፡ የእኔ መሞቻ የቀረው እናት አባቴን ያጣሁ ዕለት ነበር"፡፡ ምነው ያኔ ከነሱ ጋር ሞቴን ብታደርግልኝ፡፡ ምን አለ ፈጣሪየ ፣ ምን በደልኩህ ; ምንስ አልኩህ ? የአንተ አገልጋይ እንኳን ነበርኩ፡፡ ስቃየን እነደዚህ ባታበዛብኝ ምን ? አለ"፡፡

መጀመሪያ ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረውን እንባ በጋቢያቸው ጠርገው ቢመልሱትም አሁን ግን ገፍቶ መጥቷል፡፡ ሊመልሱት አልቻሉም፡፡ የተናነቃቸውን እንባ ዘረገፉት፡፡

ቄስ መልካሙ በምንጃር አውራጃ ውስጥ ጉራንባ ማርያም በሚባል ጎጥ ተወልደው ባደጉበት አካባቢ የድቁና ትምህርታቸውን በጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን እየተከታተሉ ባሉበት ሰዓት ነበር፡፡ እናት አባታቸውን በመብረቅ አደጋ በሞት የተነጠቁት፡፡ ለእናት አባታቸው አንድ ልጅ ብቻ ነበሩ፡፡ እናት አባታቸው ከሞቱባቸው በኋላ ፤ ያላሳዳጊ ብቻቸውን በባዶ ቤት ሲሰቃዩ ቆይተው ከአራት አመት እንግልት በኋላ፤ ነበር፡፡ ወ/ሮ አሰገደችን አግብተው ተመስገንን እና እድላዊትን ማፍራት የቻሉት፡፡

ታዲያ ተመስገን የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን እድላዊት ሁለተኛ ልጃቸውም ነበረች፡፡

"በቃህ! አይበቃህም ወይ! ለቅሶ አልነው ፤ አልነው፡፡ እድላዊት በለቅሶ የምትመጣ ቢሆን እስካሁን ባልቆየች ነበር፡፡ የባሰ ስታለቅስ አይንህን እንዳታጣና በንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዳይሆን፡፡ እንግዴህ እግዚአብሔር ከፈቀደ ልቧን አራርቶት ተመልሳ ልትመጣ ትችላለች፡፡ አይታወቅም፡፡ ሰጭውም ነሽውም እሱ አንድ አምላክ እስከሆነ ድረስ አደራውን ለሱ መስጠት ነው አሉ ፤ ወ/ ሮ አሰገደች፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose



ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍983
አትሮኖስ pinned «#የጣት_ቁስል ፡ ፡ #ክፍል_ሁለት ፡ ፡ #ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ ቄስ አሻግሬ ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው…»
#የጣት_ቁስል


#ክፍል_ሶስት


#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ

እድላዊት

ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡

የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡

መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡

ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡

መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡

እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት  ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡

ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡

ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡

እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡

እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡

እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡

ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡

"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡

እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡

እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡

አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?

እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;

እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡

እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡

ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡

እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡

ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡

እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡

አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
👍867🔥1👏1
እረኞቹ እድላዊትን ለቀው እግሬ አውጭኝ እያሉ ተበታተኑ፡፡ አቶ አርምዴ እረኞቹን ትቶ በደምና በአቧራ ተለውሳ ወደ ወደቀችው እድላዊት ተጠጋ፡፡ ጥልቅ ሃዘን ተሰማው፡፡ አይኖቹ እንባ ቋጠሩ፡፡
ከወደቀችበት አነሳት፡፡ አይዞሽ አይዞሽ አላት፡፡ ደፈሩሽ እንዴ ብሎ ጠየቃት፡፡ እድላዊት የዋለባት ውሃ ጥም ሳያንሳት ተጨማሪ በደረሰባት ጉዳት የድረሱልኝ ጩኸት ስትጮህበት የቆየችው ድምጿ ለመናገር ተሳነው፡፡ የሞት ሞቷን አልደፈሩኝም አለች፡፡

"ደብድበውሻል እንዴ" አላት፡፡ እድላዊት ግን መናገር አቃታት፡፡ መልስ አልሰጠችውም፡፡
እሱም ከእድላዊት መልስ አልጠበቀም፡፡ እረኞቹ ሲጎትቷት ደምቶ የነበረው ጉልበቷን የለበሰውን ሸሚዝ ቀዶ ደሟን ጠራርጎላት፡፡ በቀረው ጨርቅ ቁስሏን አሰረላት፡፡ እድላዊት እራሷን ችላ መሄድ አልቻለችም፡፡ የያዘውን መሳሪያ በፊት ደረቱ አንግቶ…..

ተመስገን

ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡

ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡

ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡

ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡

ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡

ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡

ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡

"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡

"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡

ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡

ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡

ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose


ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍10513