አትሮኖስ
280K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
477 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን
==========================
ዛሬ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ድክምክም ብሎኛል፡፡ብዙ ስራ እየሰራሁ ስለዋልኩ አይደለም..እንደውም በተቃራኒው ስቀመጥ ስለዋኩ ይመስለኛል ዛል እስክል የደከመኝ፡፡ ‹‹መቀመጥ መቆመጥ ነው››ትል ነበር አንድ ኑሮዋ ጠቅላላ ተረት በተረት የሆነባት ተራች አክስቴ፡፡ ሰዓቱ 12፡35….ሆኗል ፡፡ምሽቱ ደረስኩ እያለ ነው፡፡ስቀመጥ ከዋልኩበት ቢሮዬ ለሊቱን ስተኛ ወደማሳልፍበት ቤቴ ቀጥታ ማምራት ስላልፈለግኩ ለምን ትንሽ ወክ አላደርግም አልኩና ወደ ቤቴ አቅጣጫ በጣም በዝግታ ማዝገም ጀመርኩ፡፡እርምጃዬ ጽሞና የታከለበት እንዲሆን ስለፈለኩ ዋናውን የአስፓልት መንገድ ለቀቅኩና በሁለተኛው መንገድ መጓዝ ጀመርኩ.፡፡እሱም በባጃጅና በመንገደኛ ሰዎች ስለተሞላ አልተመቸኝም ወደ 3ተኛው መንገድ ተሸጋገርኩ፡፡አዎ ይሄ ይሻላል.. እሬሳን ወደ የዘላለም ማረፊያው ወደ ሆነው ቀብሩ እንደሚሸኝ ሰው ወይም በመንግስት ወታደሮች እጅ ወድቆ እጁ በሰንሰለት ወደኃላ እንደተጠፈረ አሸባሪ ተብዬ እጆቼን ወደኃላ አጣምሬ በዝግታና በፀጥታ እጓዛለሁ፡፡አካባቢው ፀጥ ያለ ነው፡፡አዕምሮዬ ግን በጫጫታ የተሞላ ነው፡፡ዝም ብሎ ህልሙንም እውኑንም ይፈተፍታል፡፡

ድንገት ከአንዱ መንገድ ተጠምዝዤ ወደ አንዱ ስገባ ዓይኔ አየ.. ምን ዓየ …..?አትሉኝም፡፡ልክ ለዘመናት እንደተራብኩት የእናቴ ጡት ዓይነት ነገር፣ልክ በፀሎት እና በእምነት አማኞች እንደሚናፍቆት ገነት ዓይነት ፣ልክ ፖለቲከኞች ለዘመናት ይመኙት እንደነበረው የቤተ መንግስት ወንበር ዓይነት… አይገርምም…፡፡ ያየሁት እኮ አሁን እንደጠቀስኩላችሁ ዓይነት ነገር ሆኖ አይደለም..እኔን ግን ውስጤን የተሰማኝ…በወቅቱ አደነዛዘዜ ፤ አደነጋገጤ እንደዛ ነው ያስመሰለብኝ፡፡ …ወፈር ደልደል ያለ ቀይ ቂጥ ነው ያየሁት..….ያየሁት ከገባሁበት መንገድ በግራ ጠርዝ በኩል በግምት 100ሜትር ርቀት ላይ የቀበሌውን ጽ/ቤት አጥር ተጠግቶ ነው፡፡እኔ ያልኳችሁ ፍም ቂጥ ብቻ አየሁ አይደል..?ግን የዘነጋሁት ወይም ያልነገርኳችሁ አንድ ነገር የቂጡንም ባለቤት ማየቴን ነው፡፡ግራ ቀኝ ስታማትር እሷም እኔን አይታኛለች፡፡ግራ የተጋባች ይመስላል፡፡የለበሰችውን ቡኒ ጅንስ ሱሪ አውልቃ ጉልበቷ ጋር አድርሳዋላች ፣በእርቃን ቂጧ እና ወልቆ ጉልበቷ ጋር በደረሰው ሱሪዋ መሀከል ሆኖ የሚዋልል ሌላ ቀይ ነገር ይታየኛል..አዎ ፓንቷ ነው ፡፡ ግራ ገብቷት ወይም የራሱ ጉዳይ ብላ መሰለኝ ችላ አለቺኝና ቁጢጥ አለች፡፡
እኔም የእራሴው እርቃን በአደባባይ እየታየብኝ ያለ ይመስል ሽምቅቅ ብዬ የ100 ሜትሩን ርቀት ወደ 70 ሜትር ካጠበብኩት በኃላ ቆምኩ፡፡..በቃ  ዝም  ብዬ  ቆምኩ፡፡ ቆሜም  ማሰላሰል  ጀመርኩ፡፡ እሷም አንዴ ወደ መሬት አንዴ ወደ እኔ እያች የኩላሊቷን ጥዝጣዜ ና የፊኛዋን ውጥረት ማስተንፈስ ቀጠለች….‹‹ሾሾ… ሾ… ዋዋ›› የሚል የሽንት ድምፅ ተሰማኝ..፡፡እርግጠኛ ግን አይደለሁም፡፡ ብቻ የሰማሁ መስሎኛል፡፡
ግን በፊት ቅምቅም አያቶቻችን ለወንድ ሱሪ ለሴት ቀሚስ የሚባል ልብስ ለምን እንዲኖር እንዳደረጉ ዛሬ ነው ፍንትው ብሎ የገባኝ.፡፡ይሄኔ እኮ ይህቺ ሚስኪን ሴት ቀሚስ ለብሳ ቢሆን ኖሮ እሷም አትጋለጥም.. እኔም አልደነግጥም ነበር፡፡ቁጭ ብላ ቀሚሷን ገለብ ታደርግና ‹ሾዋ..ዋ…ዋ› በማድርግ ከተነፈሰች በኃላ ምንም እንዳልተፈጠረ ተነስታ ትሄድ ነበር፡፡
ወይ..ሀሳቤን ሳልጨርስ ጨርሳ ቆመች፡፡ፊቷን ከእኔ በተቃራኒው  አዞረችና መጀመሪያ ቀዩን  ፓንቷን ወደ ላይ ስባ  ቀዩን ቂጧን ሸፈነችው፤  አቤት  በፓንትም  ሲታጠር  ያምራል፣ምራቄን  ገርገጭ አደረግኩ፡፡ ከዛ ሱሪዋን ወደ ላይ እየጎተተች ለበሰች፡፡ከጨረሰች በኃላ ቀጥታ ወደ እኔ አቅጣጫ መጣች፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ወደ ኃላ ልመለስ ወይስ ወደ ፊት ልቀጥል…?፡፡ከሁለቱ እግሮቼ የትኛውን ላስቀድም?፡፡ እያልኩ በሀሳብ እየተጨነቅኩ ስዋልል እሷ ቀድማኝ ስሬ ደረሰች፡፡አትኩሬ አየኋት… ቂጧም ብቻ ሳይሆን መልኳም ቀይ ነው፡፡የሆነ ክልስ ነገር ሳትሆን አትቀርም…፡፡ፈርዶብኝ ቀይ ሴቶች ልቤን በቀላሉ ብትንትን ያደርጉታል ፡፡ፍቅረኛዬ ሀይሚም እንደዚህችው ነች፡፡ ዓይኖቾ ጐላ ጐላ ያሉ ባለ ሉጫ ፀጉር ነች..፡፡አደንዛዥ ፈገግታ መግባኝ ታካኝ አልፋኝ ሄደች፡፡ እኔም ቀኝ ኃላ ዞሬ ተከተልኳት፡፡ ውሳኔዬ እሷን መከተል እንዲሆን ያስገደደኝ የቂጧ ቀይነት ይሁን የፈገግታዋ ጉዳይ አልገባኝም፡፡ደረስኩባት እና ዝም ብዬ ከጎኗ መራመድ ጀመርኩ፡፡
ግራ ገባቷት‹‹እንተዋወቃለን?››አለቺኝ፡፡

‹‹አሁን ተዋወቅን አይደል እንዴ?››መለስኩላት፡፡

‹‹አሁን የት ?››

‹‹እዛ ነዋ.. እኔ ፈዝዤ ተገትሬ አንቺ ቁጢጥ ብለሽ፡፡››

ከት ብላ ሳቀች… ሳቋ ያምራል‹‹…ጉደኛ ነህ!!! ትንሽ እንኳን አታፍርም እንዴ..?እኔስ ተጨንቄ ነው አንተ ምን አለ ዞር ብትልልኝ  ኖሮ?››

‹‹ወዴት ዞር ልበል..?ከተጠጋሁሽ እኮ ይበልጥ አይሻለሁ ብዬ ነው  የቆምኩት፡፡››

‹‹ዞረህ በሌላ መንገድ አትሄድም እንዴ?››

‹‹አኸ እንደዛም ይቻል ነበር ለካ..?እሱ እንኳን ትዝ አላለኝም፡፡››

‹‹ደንዝዘህ እንዴት ትዝ ይልሀል..?ወይ ወንዶች ስትባሉ!!!›› አለችኝ፡፡ይህቺን‹ ወይ ወንዶች ስትባሉ!!! › ቢያንስ ከ100 ሴቶች ሰምቼያታለሁ ፡፡ግን ወንዶች ስንባል እንዴት ነን..? ያው እንደዛ የሚሉን ሴቶች እራሳቸው ይመልሱት ፡፡

‹‹ግን ያምራል›› አልኳት፡፡

የድንጋጤም የእፍረትም ሳቅ እየሳቀች‹‹ምኑ?›› አለችኝ፡፡

‹‹ያየሁት ››አልኳት… አኔም በተራዬ እንደማፈር ብዬ፡፡

‹‹የትኛውን አይተህ የትኛውን እንደዘለልክ በምን አውቃለሁ?›››

‹‹ከወርቃማዋ ሸለቆሽ በስተቀር ሁሉንም አይቼያለሁ››

አቤት የሳቀችው ሳቅ… እንባዋ እስኪንጠባጠብ ነው ተንፈራፍራ የሳቀችልኝ፤ሴት  ልጅ  እንደዚህ  ስትስቅልኝ  ለመጀመሪያ  ጊዜ ይመስለኛል፡፡ ባይገርማችሁ ከቤቴ መንገድ በተቃራኒው ይህቺን ባለ ቀይ ቂጥ ሴትዬ ተከትዬ ለ24 ደቂቃ ተጉዤያለሁ፡፡

‹‹ምትገርም ልጅ ነህ ..ለማንኛውም የምሄድበት ቦታ ደርሼያለሁ በዚህ ነው የምጠመዘዘው፡፡ ››

‹‹እንዴ!!! እኔስ?›› አልኳት ደንግጬ፡፡

‹‹አንተ ምን..?ወደምትሄድበት ሂዳ፡፡››

‹‹የምሄደውማ ወደ ቤቴ ነበር …ቅድም እሄድበት በነበረው አቅጣጫ፡፡››

‹‹በል እንግዲህ የቂጥ አምላክን እየረገምክ ቀኝ ኃላ ዙርና ንካው›› አለችኝ፡፡

‹‹ስልክ ቁጥርሽን ስጪኛ?››

‹‹ምን ልታደርገው?››

‹‹በቃ እንዲሁ፡፡››

‹‹ባለትዳር ብሆንስ?››የማልመልሰውን ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ሁኚያ..እኔ እንዲሁ ነው የፈለኩት አልኩሽ እኮ፡፡›› እንዲሁ መፈለግ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ብትጠይቀኝ ግን መልስ አልነበረኝም፡፡

‹‹ሁላችሁም ወንዶች በመጀመሪያ እንዲሁ ነው የምትፈልጉት በኃላ እንጂ ነገር የምታመጡት፡፡››

‹‹ኸረ እንዲሁ ነው ስጪኝ፡፡››በአሳዛኝ ሁኔታ ተለማመጥኳት፡፡

እያጉረመረመች ሰጠችኝ፡፡ተሰናበተኳትና እንዳለቺኝ ቀኝ ኃላ ዞሬ ወደቤቴ ነካሁት፡፡
ለሊቱን ሙሉ የቂጧ ምስል በህልሜ ሲመላለስ እና ሲያሰቃየኝ አደረ፡፡ ምን ነካኝ ግን ?ፍቅር ሊይዘኝ ይሆን እንዴ? ኸረ አይደረግም…፡፡ ቢያንስ በ10 ዓመት እኮ ትበልጠኛለች፡፡ ግን ይሄ ምን ችግር አለው? ከስድስት ወር በፊት የጠበስኳት ቀሚ ፍቅረኛዬ የሆነችውን ሀይሚን በ10 ዓመት እበልጣት የለ?አንዷን እበልጣታለሁ አንዷ ደግሞ ትበልጠኛለች..በቃ ማቻቻል ማለት እንዲህ ነው፡፡
👍79😁258🔥1🥰1
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_ሁለት


#ድርስት_በዘሪሁን
==========================
ቢሆንም ቅንዝሬ ያው ቅንዝር ነውና ጆሮው የተደፈነ ነው፤የእኔ እና የእሷን ምክንያት አያዳምጥም ፡፡ስለዚህ እመክረው እመክረውና…ከዛም ደግሞ እለምነው እለምነው እና በቃ ከአቅሜ በላይ ሲሆን  እንደነርኳችሁ በወር አንዴ በደሞዝ ሰሞን ወደ አብረቅራቂ መብራት ወደሚንቦገባግባቸው የለሊት ቤቶች ጐራ እላለሁ ፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን ልቤ ለሀይሚ እንዳላዘነ ነው፡፡ዛሬ ግን እፎይ ልገላገል ነው ፡፡ሀይሚ እቤት ለመምጣት ከስድስት አታካች ወራቶች ጭቅጭቅ በኋላ ተስማምታለች፡፡ከቀኑ 8 ሰዓት ነው የምትመጣው፡፡እኔ ግን ከእንቅልፍ የባነንኩት ከለሊቱ 8 ሰዓት ነው፡፡ለዝግጅት፡፡እውነቴን ነው እኮ ፡፡ገና እቤት ማዘጋጀት አለ፣ዕቃ ማጣጠብ አለ፣አልጋ በስርአት ማንጠፍ አለ፣ለፍቅራችን ማጀቢያ ሙዚቃ መምረጥ አለ፣ደግሞ እኔም እንድደፍራት እሷም እንድትደፈርልኝ የሚያግዝ መጠጥ ማዘጋጀት አለ፣አረ ስንቱ….፡፡

ደግሞ አይገርማችሁም ዛሬ ሀይሚ ቤት ልትመጣ ትናንትና ቂጣሟን ማግኘቴ….፡፡ ማግኘቴ ብቻ ሳይሆን እቤቷ ድረስ መከተሌ..ከዛም አልፎ ስልክ ቁጥሯን መቀበሌ..፡፡አሁን ልደውልላት እንዴ….? የሚል ሀሳብ መጣብኝ ፡፡መልሼ ሀሳቤን ውድቅ አደረግኩት ::ለሀይሚ ያለኝን ታማኝነት ዝቅ ማድረግ ነው:: አይደለም መደወል …ቢቻል በምናቤ ተንጠልጥሎ አልወርድ ያለኝን የቂጧን ምስል አሽቀንጥሬ መጣል ብችል ደስ ይለኝ ነበር፡፡እንደቀጠሯችን ምንም ሳታረፍድ ከቀኑ 9 ሰዓት ሀይሚ መጣች..ያው አንድ ሰዓት ዘገየች ማለት አረፈደች ተብሎ መደምደም የለባትም ብዬ ነው፡፡ አለባበሷን ልግለጽላችሁ፣ቡትስ ጫማ፣ጥብቅ ያለ ጅንስ ሱሪ፣በሱሪው ላይ ቁርጭምጭሚቷ ጋር የሚጠጋ ቀሚስ፣በቀሚሱ ውስጥ ደግሞ ሱሪዋ በቀበቶ የተጠፈረ መሆኑን በሚታየው የቀበቶ ቅርፅ ማወቅ ይቻላል፣ከላይ ደግሞ ግብዳ ሹራብ ደርባለች፡፡
ጉንጯን እያገላበጥኩ እየሳምኩ ቢሆንም አይኖቼን ግን ሰማዩ ላይ አንጋጥጬ እያንከራተትኩ ነው፡፡ሀሞቴ ፍስስ ነው ያለው፡፡አሁን እሺ ብላ እንድናደርግ ፍቃዱን ብትሰጠኝ ..ይሄን ጫማዋን ፈትቼ እስካወልቅ አንድ ሰዓት፣ሱሪዋን እስካወልቅ ሌላ አንድ ሰዓት፣ምን አልባት ከሱሪዋ ስር ታይት፣ከታይቱ ስር ደግሞ ሁለት ወይም ሶስት ፓንት ታጥቃ ሊሆን ይችላል..? ታዲያ መሽቶ ነጋ ማለት አይደል?፡፡

ወደ ቤት ዘልቃ ቁጭ አለች፡፡ቁጭ አባባሏ እራሱ ሲያበሳጭ፡፡ ከጓዲያ ወጥቶ ማጅራቷን አንቆ የሚውጣት ዳይኖሰር ያለ ይመስል በራፉ ጥግ የሚገኝ ኩርሲ ላይ ተቀመጠች፡፡ፈርጥጣ ለመውጣት እንዲያመቻት ይመስለኛል፡፡ ደግሞ እሷ ብቻ ሳትሆን እኔም አበሳጫለሁ ፤ ምን አለበት ከመምጣቷ በፊት እቤቴ ያሉትን መቀመጫቸው ሁሉ ሰብስቤ ጓዲያ አስገብቼ ቢሆን ኖሮ ምርጫ ስታጣ አልጋ ላይ መቀመጧ አይቀርም ነበር፡፡

‹‹ሀይሚ ..ምነው በራፍ ላይ….. ?አልጋው አይሻልሽም…?››

‹‹አይ መጣለሁ  ብዬህ እንዳልቀር ነው እንጂ …እሄዳለሁ፡፡››

‹‹ወዴት?››

‹‹ወደቤት ነዋ…እናቴ ስራ አዛኝ ነበር ….ተደብቄ ነው የመጣሁት››ብላኝ እርፍ፡፡

ይታያችሁ ሰው አሁን ይህቺን ያፈቅራል...?ከለሊቱ 8 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ፍዳዬን ስበላ ቆይቼ እሷ ግን ገና መጥታ ሳትጨርስ ልሄድ ነው ትላለች፡፡ቀኑን ሙሉ እሷን እያሰበ ሲወጣጠር የዋለውን እንትኔ ወዲያው ልፍስፍስ ብሎ ሲሸበለል ይታወቀኛል፡፡ችላ አልኳት እና ወደ ጓዲያ ገብቼ የሰራሁትን ምግብ በማምጣት ጠረጴዛ ላይ ደረደርኩት፡፡ ወይኑንም አወጣሁ..አሁን የምግብ ጠረጰዛው አልጋውን ተጠግቶ ስለሚገኝ ምርጫ የላትም መጥታ አልጋው ላይ ከጐኔ መቀመጧ አይቀርም ፡፡

‹‹ሀይሚ ነይ ምሳ እንብላ ፣እርቦኛል..እስከአሁን እኮ አንቺን ስጠብቅ አልበላሁም፡፡››

‹‹እኔ እኮ በልቼያለሁ፡፡››አቤት ወሽመጥ ስትቆርጥ፡፡

‹‹ባክሽ አታበሳጪኝ..በስንት ጣጣ  መጥተሸ ደግሞ..?›› ተኮሳተርኩ፡፡ እንደመደንገጥ አለችና መጣች፡፡ እንዴት መጣች አትሉኝም…? ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት ከአልጋው ራቅ ብላ ተቀመጠች፡፡ ምርጫ አልነበረኝም፤ እጇን አስታጠብኳት ፤ወይኑን ስቀዳ‹‹ለእኔ እንዳትቀዳልኝ››አለችኝ እየተንዘረዘረች፡፡ መርዝ ልቀዳላት የተዘጋጀው አስመሰለችው፡፡

‹‹አንድ ብርጭቆ ብቻ››ተለማመጥኳት፡፡
‹‹አንድ መለኪያም አልጠጣም..እንድበላ ከፈለክ በውሃ ቀይርልኝ…›› ለወራት ተጨንቆ የቀየሰው የጦርነት እስትራቴጂ ፍርክስክሱ እንደወጣበት የጦር ጄኔራል ሞራሌ ድቅቅ አለበኝ፡፡ለንቦጬን ጣልኩ …ያለችውን አደርግኩ፡፡

እየተጐራረስን በፀጥታ በልተን ጨረስን፡፡እኔ የእሷንም ፋንታ የምጠጣ ይመስል እንደውሃ እጋተው ጀመር ፡፡ እንደጨረስን የተበላበትን ዕቃ አነሳሳሁ..እጇን አስታጠብኳት እና እኔም ታጥቤ  ወደ ቦታዬ ተመለስኩ፡፡

ልክ ምሳዋን ለመብላት የመጣች ይመስል…‹‹ልሂድ በቃ፡፡›› አለችኝ፡፡

‹‹ቆይ ማውራት አለብን፡፡››

‹‹ምንድነው የምናወራው?››

‹‹ስለፍቅራችን ነዋ፡፡ ››

እንደመደንገጥ ብላ‹‹ፍቅራችን ምን ሆነ ?››አለችኝ፡፡

‹‹እስከአሁን ምንም አልሆነ …ካላወራንበት እና መፍትሄ ካላበጀንለት ግን መሆኑ አይቀርም.››ወይኑን በደረቁ እየለጋሁት ስለሆነ በድፍረት የመናገር ወኔዬ ሙሉ ነው፡፡

‹‹እሺ ፈጠን በልና እናውራበት››

‹‹ታፈቅሪኛለሽ?››

ግራ በመጋባት‹‹ምን ማለት ነው?››

‹‹ታፈቅሪኛለሽ ወይ?››ደግሜ ጠየቅኳት፡፡  

‹‹በጣም አፈቅርሀለሁ፡፡››
  ‹‹ካፈቀርሺኝ …ዛሬ ፍቅር እንድንሰራ እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹ፍቅር እየሰራን አይደል እንዴ?››

‹‹እንደ እሱ አይደለም..ልብስሽን አወላልቀሽ..እኔም ልብሴን አውልቄ… እዚህ አልጋ ላይ ወጥተን ምናምን ማለቴ ነው… በጣም አምሮኛል…ስንት ወር ነው የምሰቃየው…?››ብሶቴን ተረተርኩት፡፡

‹‹እሱማ አይሆንም፡፡››

‹‹ለምን አይሆንም?››

‹‹አፈቅርሀለሁ… ግን ጊዜው አሁን አይደለም…ገና 18 ዓመት እኮ አልሞላኝም፡፡ በዛ ላይ የሃይእስኩል ትምህርቴንም አልጨረስኩም፡፡››

‹‹ስንት ዓመትሽ ነው?››

‹‹17 ዓመት ከ11 ወር…››

‹‹እና ታዲያ ሰው ለሚወደው እንኳን አንድ ወር ይቅርና አንድ ዓመትስ ቢያጭበረብር ምን አለበት?››

‹‹እንደ እናቴ መሆን አልፈልግም፡፡››

‹‹እንዴት እንደ እናትሽ?››

‹‹እሷም 10ኛ ክፍል እያለች ነው እኔን ያረገዘችው፡፡በዛ የተነሳ ትምህርቷን አቋርጣ ብዙ ስቃይ ተሰቃይታለች፡፡ ብዙ ብዙ መከራ ካሳለፍን በኋላ ነው በቅርቡ ህይወታችን የተስተካከለው፡፡››

‹‹እኔ እኮ ብታረግዢም አፈቅርሻለሁ..ማለቴ አገባሻለሁ፡፡››

‹‹አባቴም እሷን እንደዛ ነበር የሚላት…፡፡የእውነት እንዳረገዘች ስትነግረው ግን የራስሽ ጉዳይ ነበር ያላት፡፡››

‹‹እሺ በቃ በኮንዶም እንጠቀም..ህይወት ትረስት፣ሴንሴሽን፣ሜምበርስ ኦንሊ… የፈለግሽው አይነት አለ፡፡››

‹‹እንዴ ዲኬት ነው እንዴ የምትሰራው…? ይሄ ሁሉ ኮንደም ምን ልታደርግ ሰበሰብከው…?››ያላሰብኩትን መስቀለኛ ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ባክሽ አንድ ዲኬት የሚሰራ ጓደኛዬ ነው አምጥቶ ለማንኛውም እያለ ቤቴ የሚያስቀምጠው፡፡››

‹‹ጥሩ…. ግን ድንግል ነኝ… ድንግልናዬን ደግሞ በኮንደም አላስወስደውም፡፡››

‹‹እኔ እኮ ድንግልናውን አልፈልገውም..፡፡››
‹‹……እና አውልቄ ላስቀምጠውና ተጠቅመህ ከጨረስክ በኃላ መልሼ ላጥልቀው?››ንግግሯ ከማበሳጨትም አልፎ አሳቀኝ፡፡

‹‹እና ምንድነው መፍትሄው?››

‹‹ምታፈቅርኝ ከሆነ ጠብቀኝ?››
‹‹እሱማ አፈቅርሻለሁ፡፡››
👍865👏2👎1
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን

====================
‹‹ካሰብሽበት አሁንም ቀን ነው፡፡››
‹‹አንተ ቤተሰብ ያለኝ ሰው እኮ ነኝ፡፡››
‹‹አንቺ እሺ ይኑርሽ.. ያደነዘዘኝን ቂጥሽን ግን ላኪልኝ፡፡››መቼስ የምላሴ ፍሬኔ ብጥስጥስ ብሎብኛል፡፡
‹‹ናና ውሰደዋ፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ፡፡››
‹‹እውነትህን ነው?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው..ትናንት የተለያየንበት ቦታ ስደርስ ደውልልሻለሁ››
‹‹ያ እኮ ሰፈሬ አይደለም ብላ …የእሷን ትክክለኛ ሰፈር በምልክት ነገረችኝ.. ሂሳብ እንዴት እንደከፈልኩ.. እንዴት ተንደርድሬ ሰፈሯ እንደደረስኩ አላውቅም..ግን ስደውልላት ባሏ ተከትሏት ቢወጣስ..?የራሱ ጉዳይ ‹‹የቆመበት የቆመ ነገር አያይም››ይባል የለ፡፡ ደወልኩላት… ከአምስት ደቂቃ በኃላ መጣች፡፡ጨለማ ውስጥ ሆኜ ያለሁበትን ቦታ በእጅ ምልክት ጠቆምኳት..መጣች፡፡
‹‹አንተ ጉደኛ!!!››
በቃላት መልስ ከመመለሴ በፊት ጐተትኩና ከሰውነቴ አጣብቄያት ከንፈሯን ገመጥኳት ፡፡የሀይሚን እልክ በእሷ እየተወጣሁ ያለው መሰለኝ፤ በግድ ነው ያስለቀቀቺኝ‹‹አንተ ሰፈሬ እኮ ነው ያለሁት…ሰው ቢያየኝስ?››አለችኝ፡፡ ንግግሯ ደስ አሰኘኝ…ሰፈሯ ባይሆን ኖሮ በመሳሟ ደስተኛ ነች ማለት ነው፡፡
‹‹ባክሽ ጭለማ ውስጥ ነው ያለነው..ማንም አያይሽም፡፡››
‹‹ወይኔ ጉዴ!!!››አለች ድንገት ራሷን ይዛ እየተርበተበተች፡፡
‹‹ምነው….?ምን ሆንሽ…?›.
‹‹ባሌ መጣ …ባሌ፡፡››
በድንጋጤ ተሸቀንጥሬ ጨለማ ውስጥ ተሸገጥኩ፤እሷ በቆመችበት ሆና በሳቅ ፍርስ አለች‹‹ሲያዩህ ጀግና ትመስላለህ››
ከተወሸቅኩበት ወጣሁና ወደ እሷ በእርጋታ እየቀረብኩ ‹‹ጀግናማ ጀግና ነኝ ላንቺ ደህንነት አስቤ አስጂ..፡፡››
‹‹እሱን እንኳን ተወው..ጀግና አናውቅም እንዴ?››
‹‹ግን ባልሽ እቤት ነው?››
‹‹ባሌ እቤት ቢኖር..እንዲህ አጥር ስር አስደግፌህ አዋራሀለው፡፡››
‹‹ጥሩ አጋጣሚ ነው ፊልድ ሄዶል ማለት ነው››..አንገቷን ወደ መሬት ደፍታ ዝም አለች፡፡ግራ ገባኝ‹‹ምነው ያልኩሽን ሰምተሸል?››
‹‹አዎ ባሌ የሞተብኝ በቅርብ ነው፡፡ ሰሞኑን ነው ጥቁሩን የሀዘን ልብሴን ያወለቅኩት ››ደነገጥኩ፡፡የተደፈነ ልብ ሸሽቼ ስመጣ የተሸነቆረ ልብ ገጠመኝ እንዴ..?
‹‹ይቅርታ›› ብዬ ዳግመኛ ወደ ሰውነቴ አጣበቅኳትና ከንፈሯ ላይ ተጣበቅኩ፡፡እጄ ትናንትና ያደነዘዘኝ ቂጦ ላይ አርፎል… ቃተተች፡፡ እንደምንም ተላቀቀቺኝና ‹‹እዚሁ ብትንትኔን አወጣኸው እኮ..በዛ ላይ ረሀብተኛ ነኝ፡፡››
‹‹እኔም ጠኔ ሊጥለኝ ትንሽ ነው የቀረኝ፡፡በቃ ይዘሺኝ ወደ ቤት ግቢያ..››
‹‹ወዴት?››
‹‹ወዳንቺ ቤት ነዋ፡፡››
‹‹እንዴ ልጄ እኮ አለች..በዛ ላይ ሰራተኛዋም….››
‹‹እሺ የሆነ ሰበብ ፍጠሪና ወደ እኔ ቤት ወይም ወደፈለግሽበት ሌላ  ቦታ ይዤሽ ልሂድ፡፡››
‹‹እሱማ አይቻልም..ውጭ ለማደር ምንም የምሰጠው ምክንያት የለኝም..ይልቅ ደፋር ከሆንክ አንድ ሀሳብ አለኝ፡፡››
‹‹ኸረ አፄ ቴዎድሮስ አጐቴ ነው… ጀግንነቱ ከደማችን ነው ሚንጠባጠበው፡፡››
‹‹ከ3-4 ሰዓት ባለው ጊዜ ይተኛሉ ..መኝታ ቤቴ ለብቻዬ ስለሆነ ስደውልልህ ትመጣና ትገባለህ..ታዲያ ለሊት 11 ሰዓት ወጥተህ ለመሄድ ከተስማማህ ነው ?››
ጥብቅ ብዬባት ሳምኳት እና ‹‹ቂጥሽ ብቻ ሳይሆን ልብሽም ቀይ ነው..ተስማምቼያለሁ፡፡››
‹‹ታዲያ እስከዛ የት ትቆያለህ?››
‹‹ችግር የለውም..ወደኃላ ተመልሼ በቅርብ የሚገኝ አንዱ ቡና ቤት አመሻለሁ… ስለ እሱ አታስቢ አንቺ ብቻ እንዳልሺው አድርጊ፡፡››
‹‹ችግር የለውም …አሁን ግን ሱቅ ዕቃ ልግዛ ብዬ ስለወጣሁ  መመለስ አለብኝ፡፡››
‹‹ታዲያ የገዛሽው ዕቃ የታል?››
‹‹አጣኋ…ባለሱቆቹ የለንም ጨርሰናል አሉኝ፡፡›› ብላ ጉንጬን በስሱ ስማኝ እየፈገገች ወደ ግቢዋ ተመልሳ ገባች፡፡››
አቤት የሰው ልጅ ልዩነት ድሮም ከህፃን ጋር መከራዬን ሳይ መኖሬ እንዲህ ትናንት ተዋውቆ ለዛሬ ብን ማለት እያለ ስድስት ወር ሙሉ  ስዳክር መኖሬ..አምኜ ወደ ኃላ ልመለስ አልቻልኩም፡፡እንዴ የሆነ ነገር ቢያጋጥመኝስ..? ድንገት ሳልሰማ ጉልበተኛው መንግስታችን ሰዓት እላፊ አውጆ ቢሆንስ…?ድንገት ዘራፊዎች ሞባይሌን ቢመነትፉኝስ በምን ደውዬ አገኛታለሁ…?ኸረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን እንጂ በእንደዚህ አይነቱ ቀን ድንገት የሚፈጠር ስንት አደናቃፊ ነገር አለ መሰላችሁ፡፡ለሀይሚ ተብዬዋ እንኳን ያን ሁሉ ሰዓት በባዷ አባክኜ የለ…ያደረግኩት አንድ ነገር ቢኖር እዛው ፊት ለፊቴ ካለች አንድ ትንሽ ኪወክስ ሄጄ ጭንብል መሸመት ነው፡፡ሶስት እሽግ ህይወት ትርስት..ሶስት እሽግ ሰንሴሽን ሸመትኩና በእያንዳንዱ ኪሴ ሁለት ሁለት በታትኜ ከተትኩ፡፡
አንድ ወንዳ ወንድ የሆነች የሱቁ ሻጭ‹‹ምነው የወር ቀለብ ነው እንዴ?›› አለቺኝ፡፡
‹‹ምነው ችግር አለው?››
‹‹ለምን ችግር የለውም ፡፡ ሆነ ብለህ ምርትን ከተገቢው በላይ በማከማቸት የዋጋ ንረት ለመፍጠር አስበህ ቢሆንስ?››
‹‹አይዞሽ አትስጊ ከተረፈኝ ጥዋት መልስልሻለው ›› አልኳት እና መልሼ ጨለማዬ ውስጥ ተወሸቅኩ፡፡3፤15 ሲሆን ተደወለ.. ባለቂጧ መስላኝ ተንደርድሬ አፈፍ አድርጌ አነሳሁና‹‹እሺ ተኙልሽ››
‹‹አዎ ልተኛ ነው››አለችኝ፡፡አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ.. ከራማዬ ነው ቡን ያለው፡፡ ሀይሚ ነበረች ደዋዮ፡፡አሁን በዚህ አሳሳች ሰዓት  ማን ደውይ አላት?
‹‹ሄሎ ምነው ዝም አልከኝ፤አኩርፈኸል እንዴ?››
‹‹አይ ለምን አኮርፍሻለሁ?››
‹‹ደግሞ ውጭ ነው እንዴ ያለኸው...፡፡ንፋስ ነገር ይሰማኛል›› ብላኝ ቁጭ፡፡ሁሉም ሴቶች ከጥንቆላ መንፈስ የተገነባ ስድስተኛ የስሜት ህዋሳት አላቸው…፡፡ይሄ ጉዳይ ሁሌ ይገርመኛል፡፡ከሆነች ሴት ጋር አፍ ለአፍ ገጥመህ ስታወራ…ወይንም የሆነች ሴት ልትስም አፍህን አሞጥሙጠህ ወደ ፊት መጓዝ ስትጀምር..ወይ ለአንዴ ልስረቅ ብለህ ሱሪህን በማውለቅ ላይ ሳለህ…ስልካቸው ጭርርርርርር ይልብህና ያሳቅቅሀል፡፡
‹‹ባክሽ ደብሮኝ እቤቴ በረንዳ ላይ ቁጭ ብዬ ከዋክብት እየቆጠርኩ ነው››
‹‹አውቄያለሁ ደብሮሀል ማለት ነው..?ግን ለቀኑ ነገር ተረድተኸኛል አይደል…?››ለዚህ ጥያቄዋ መልስ ከመመለሴ በፊት ሌላ ስልክ ዌይቲንግ ገባብኝ..ቂጣሟ ነች፡፡
‹‹በጣም ነው የተረዳሁሽ የእኔ ፍቅር፡፡አሁን ግን ሀለቃዬ እየደወለልኝ ነው..ላናግረውና መልሼ ደውልልሻለሁ፡፡››
‹‹አይ አያስፈልግም ፍቅር ..ልተኛ ስለሆነ ደህና እደር… ነገ ትደውልልኛለህ..ደግሞ አፈቅርሀለው እሺ፡፡››አለችኘ፡፡
‹‹እኔም አፈቅርሻለሁ፡፡›› አልኩና ዘጋሁት ..አያችሁልኝ አይደል፡፡‹‹አፈቅርሀለሁ፡፡››ብላኝ እኮ አታውቅም፡፡ሁልጊዜ ከስልክ ልውጥ  በኃላ ‹‹አፈቅርሻለሁ›› ስላት ‹‹እኔም›› ብላ ነው ምታሳርገው፡፡ ዛሬ ግን እኔን ለማሳቀቅ እና በአእምሮዬ ፀፀት ለመርጨት ሆነ ብላ አቅዳ እና አልማ ‹‹አፈቅርሀለሁ›› አለችኝ፡፡..ሞኟን ትፈልግ …በዚህ ሰዓት ለእሷ ንግግርም ሆነ ለአዕምሮዬ ፊት አልሰጣቸውም፡፡….
የቂጣሟን ስልክ አነሳውት…..‹‹ሄሎ››
‹‹ና በቃ … በራፍ ላይ ስትደርስ ደውልልኝ››
‹‹በመጀመሪያውስ ከበራፍሽ መች ተንቀሳቀስኩ››
‹‹እስከአሁን እዛው ነኝ እንዳትለኝ?››
‹‹አልኩሽ..ከስልክ እንጨቱ ጋር ተጣብቄልሻለሁ፡፡››
‹‹እውነትም ቀንዝሮብሀል..እሺ መጣሁ ››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡የውጩ በራፍ ተከፈተ፤ ጐትታ ወደ ውስጥ አስገባችና መልሳ ዘጋችው፡፡በግቢው ሆነ በቤታቸው ምንም አይነት መብራት አይታይም፡፡‹‹ምነው መብራ ተቆርጦባችሁ ነው?››በሹክሹክታ ጠየቅኳት፡፡
👍778😁2