አትሮኖስ
283K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
503 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
…..በጣም ነው የምወድህ……››አለችው
‹‹እኔም እህቴ በጣም ወድሻለው…አሁን እራት እየቀረበ ነው መሰለኝ ወደቤት እንግባ…››
‹‹እሺ እንግባ››ተባባሉና ተያይዘው ወደቤት በመግባት ከቀረው ቤተሰቡ ጋር ተቀላቀሉ፡፡
//
አቶ ለሜቻና ቤተሰባቸው በአጠቃላይ ሙሉ ትኩረቱ የበሬዱ የሶስተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ ላይ ነው፡፡ይሄ ባለፈው ሁለት አመት በተመሳሳይ የመታሰቢያ ድግስ የተደገሰ ቢሆንም የዘንድሮ ግን በተለየ ሁኔታ ትኩረት ተሰጥቶታል ፡፡የዚህም ምክንያት በቤተሰቡ ውስጥ ተአምራዊ በሆነ መንገድ በፀሎት የምትባል ልጅ ስለተጨመረችና ከዛም ተያይዞ ከሞላ ጎደል የቤተሰቡ የገንዘብ ችግር ስለተሻሻለ፤ ከዚህ በፊት ከነበረው ከፍ ባለ ሁኔታ ለመደገስና በሟቾ ስም በርከት ያሉ ችግረኞችን በማብላት ነፍስ ይማር በማሰኘት የተወሰነ የመንፈስ እረካታና የአእምሮ መረጋጋት ለማግኘት ጠንክረው በጥሩ ሞራል እየደገሱ ነው፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ ኃይለልኡል ቤት በአይነቱ ለየት ያለ ድብልልቅ ያለ ድግስ እየተደገሰ ነው፡፡የእነሱ ምክንያት ደግሞ ሚያዚያ 20 ቀን የልጃቸው በፀሎት የልብ ንቅለተከላ ያደረገችበትና ሁለተኛ የመኖር እድል ያገኘችበት ስለሆነ ያንን ቀን በፌሽታና በምስጋና የማሳለፍ አላማ ያለው ነው፡፡ይሄንን ድግስ ያለፉትን ሁለት አመታት አድርገውታል፡፡ የዘንድሮው ግን በአይነትም ሆነ በመጠን ከፍ ያለ ነው፡፡ይሄም ዘንድሮ ሁኔታዎች የተለዩ

ስለሆኑ ነው፡፡ከቤታቸውም ከፊታቸውም የተሰወረችው የልጃቸው በፀሎት ከወር በኃላ ወደቤቷ ምትመለስበት ቀን ይሆናል የሚል ጉጉት ስላላቸው ልጃቸውን እጥፍ ድርብ በሆነ ፌሽታ ለመቀበል ያደረጉት ነው፡፡ከዚህም በተጨማሪ ሌላ የተለየ ምክንያት አላቸው ፡፡ባልና ሚስቶቹ ለአመታት ከገቡበት አስጠሊታ ግንኙነት እና የእርስ በርስ ጥላቻ ተገላግለው. ቀሪ ህይወታቸውን በመከባበር እና በፍቅር ለማሳለፍ ወስነውና ተስማምተው ቀሪ እንደአዲስ ለመጀመር የወሰኑበት ወቅት ስለሆነ ለእነሱም እንደ ዳግማዊ ሰርግ ነው…ለዛ ነው የተለየና እንከን አልባ ድግስ እንዲሆን እየጣሩ ያሉት…ያው እንደተለመደው የድግሱን ቅንጅት በሀላፊነት የወሰዱት ፕሮፌሽናል ባለሞያዎች ናቸው፡፡
የጭንቁ ቀን ደርሶል ፡፡አቶ ለሜቻና ወይዘሮ እልፌ ከሌሎች ጎረቤቶች ጋር በለሊት ነው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው ቅዳሴ የገቡት…በጸሎትን ጨምሮ ሌሎቹ ልጆች ግን ወደ ቤተክርስቲያን የሚወሰደውን ምግብና መጠጥ ሲያዘጋጁ ከቆዩ በኃላ አንድ ሰዓት ተኩል ሲል ዳቦ፤ እንጃራና ጠላውን በፒካፕ መኪና እስጭነው ቤተክርስቲያን በመውሰድ ለቄሶቹ የተዘጋጀውን ወደሰንበቴ ቤት አስገብተው ሌላውን ውጭ አስቀምጠው ቅዳሴው እስኪገባደድ መጠበቅ ጀመሩ ፡፡ልክ ቅዳሴው ተጠናቆ ሁሉም እንደወጣ አቶ ለሜቻና ወይዘሮ እልፌ ከቄሶቹ ጋር ወደሰንበቴ ቤት ቄሶቹንና ሌሎች ምዕመናንን ለማሰተናገድ ሲገቡ፡፡ በፀሎትና እና ለሊሴ ደግሞ ከሌሎች የሰፈር ወጣቶች ጋር በመሆን ቤተክርስቲያኑ የውጭ አጥር ጋር ተኮልኩለው ለሚገኙ የእኔ ቢጤዎችና፤ ምፅዋት ጠያቂዎች አንድ እንጀራ በወጥ ፤አንድ ጉማጅ ዳቦና አንድ ሀይ ላንድ ጠላ ለእያንዳንዱ እያደሉና ነፍስ ይማር እያስባሉ ካጠናቀቁ በኃላ ዕቃቸውን ሰብስበው እነአቶ ለሜቻ ከሰንበቴ ቤት እስኪወጡ መጠበቅ ጀመሩ…ሁሉ ነገር ከተጠናቀቀ በኃላ ቤተሰቡ ወደቤታቸው ከመመለሳቸው በፊት ቀጥታ ተያይዘው ወደበሬዱ መቃብር ነው የሄዱት፡፡የእሷ ምስል ያለበት ጥቁር ቲሸርት የለበሱት አስራ ምናምን ሰዎች የሀውልቱን ዙሪያ ገባ ከበው በዝምታ ሲፀልዩና አንዳንዱም ሲያነባ ከቀዩ በኃላ ሁሉም ቀስ በቀስ ስፍራውን እየለቀቁ ሄዱ…በመጨረሻ የቀሩት በፀሎት አቶ ለሜቻና ወ.ሮ እልፍነሽ ነበሩ፡፡
በፀሎት ይሄንን የልጅቷን ሀውልት ስታይ በጣም ትልቅ የሆነ ሀዘን ነው የተሰማት…‹‹በእሷ ምትክ..እኔ ነበርኩ እዚህ ስፍራ ከዚህ ሀውልት ስር መተኛት የሚገባኝ››ብላ ስታስበው እራሱ ዝግንን አላት…ልክ እንደሁል ጊዜውም የሌላን ሰው ህይወት ሰርቃ እየኖረች እንዳለች አይነት ስሜት ነው እተሰማት ያለው….የሚቀፍ አይነት ስሜት…›

አቶ ለሜቻ በዝምታ ሲያስተውሏት ስለቆዩ ያመማት መሰላቸው…‹‹ለማታውቃት ልጅ ይሄን ያህል ሀዘን ከየት የመጣ ነው?››በውስጣቸው ያብሰሰሉት ሀሳብ ነበር፡፡ በዝምታ ወደእሷ መጥተው ትከሻዋን በመያዝ…‹‹ልጄ በቃ እንሂድ ይበቃል››ሲሏት ከገባችበት ጥልቅ የመደንዘዝ ስሜት ባነነችና ቀና ብላ አየቻቸው…ትከሻዋን አቅፈው በፍቅር እየተመለከቷት ነው፡፡በሶስት ሜትር ርቀት ፈንጠር ብለው ወ.ሮ እልፍነሽ እያነቡ ይታዬታል…የአቶ ለሜቻን እጅ ያዘችና ‹‹አባዬ ና..››ብላ ወስዳ ከባለቤታቸው ጎን አቆመቻቸውና…ሁለቱም እግር ስር ድፍት ብላ አንድ አንድ እግራቸውን በመያዝ…‹‹አባዬ እማዬ እኔን ይቅር በሉኝ….በበሬዱ ይዣችኃለው ይቅር በሉኝ….ይቅር ካላላችሁኝ መኖር አልችልም….የእውነቴን ነው የምላችሁ ይቅርታችሁን ካላገኘው ሞታለው፡፡››ስትል ሁለቱም በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ…ምንም እየገባቸው አይደለም….‹‹ምን አጥፍታ ነው…?ምንስ ብታጠፋ ይቅርታ መጠየቂያው ቦታና ጊዜው ትክክል ነው?፡፡››በውስጣቸው የተፈጠረ ጥያቄ ነበር…ሁለቱም ግራና ቀኝ ትከሻዋን ይዘዘው ቀና ሊያደርጎት ሞከሩ ..ግን እልቻሉም፡፡
‹‹ይቅርታ ካላደረጋችሁልኝ አልነሳም››
‹‹ምን አጥፍተሸ ነው? ምንም አልገባንም እኮ››አቶ ለሜቻ ጠየቋት፡፡
‹‹አጭበርብሬችኃለው ..ዋሽቼያችኃለው..እኔ እናንተ ጋር የመጣሁት ከእንጀራ አባቴ ጠፍቼ አይደለም….››
‹‹እና ምን ሆነሽ ነው?፡፡››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ ማለት …የልጃችሁን ልብ በውስጤ ተሸክሜ የምዞር..በእሷ ምክንያት እየተነፈስኩ ያለው ልጅ ነኝ…..፡፡››
ሁለቱም የሚሰሙትን ለማመን አልቻሉም ..አቶ ለሜቻ ቀስ ብለው ትከሻዋን ይዘው አስነሷት…ፊቷን የተሻፋፈነችበትን ሻርፕ ቀስ ብለው ከላዮ ገፈፉና ጣሉት.. ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ ፊቷን ተመለከቱት‹‹አዎ እራሷ ነች››ትከሻዋን ያዙና ደረታቸው ላይ ለጠፏት…ግንባሯን፤ ጉንጮን፤ ፀጉሯን እየደጋገሙ ሳሟት‹‹….ልጄ አዎ አውቄው ነበር..አንቺ ወደቤቴ ያለምክንያት እንዳልመጣሽ ታውቆኝ ነበር….ከዛሬ ነገ ጥላኝ ትሄዳለች በሚል ስጋት ስሳቀቅ ነበር..አሁን ግን የራሴው ልጅ ነሽ የትም አትሄጂም..አዎ የራሴው ልጅ ነሽ››ተንሰፈሰፉላት….ፍፁም ያልጠበቀችውን ምላሽ ነው ያገኘችው፡፡

‹‹አዎ አባዬ ያንተው ልጅ ነኝ…ዘላለም ካአንተ መለየት አልችልም…እማዬ እኔ ልጅሽ ነኝ››ሶስቱም አንድ ላይ አርስ በርስ ተቃቅፈው ለበርካታ ደቂቃ ተላቀሱ ..በመከራ ነበር አካባቢውን የለቀቁት…ሁሉም የቤተክርስቲያኑ በራፍ ላይ ተሰብስበው እየጠበቋቸው ነበር….ግን በፊት ከነበሩት በተጨማሪ የበፀሎት እናትና አባት ልዩ አይነት ባስ መኪና አጠገብ ቆመው በራፍ ላይ ሲጠብቋቸው ነበር..ይሄ ደግሞ እነአቶ ለሜቻን ብቻ ሳይሆን በፀሎትንም ጭምር ነበር ያስደነቃት…እርስ በርስ ተቀራርበው ሰላምታ ከተለዋወጡ በኃላ ሁሉም በመኪና ውስጥ እንዲገቡ ተደረገ…በመኪና ውስጥ ጠቅላላ 25 የሚሆኑ ሰዎች ገቡ…ሹፌሩ መኪናውን ወደእነ አቶ ለሜቻ ቤት አቅጣጫ መንዳት ጀመረ…ቤታቸው ለመድረስ ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ሲቀረው ግን ወደግራ ተጠመዘዘና አንድ ግቢው ውስጥ ገባ..ሁሉም ግራ ተጋባ….አቶ ኃይለልኡል መኪናው እንደቆመ በራፈ ከመከፈቱ በፊት ከተቀመጡበት ተነሱና መናገር ጀመሩ‹‹ ..ይቅርታ የማታውቁኝ ካላችሁ ኃይለልኡል እባላለሁ…የበፀሎት አባት ነኝ…በዛሬው ቀን በደም የተጣመሩ ሁለት ቤተሰቦች እዚህ ይገኛሉ ..የእኛና የአቶ ለሜቻ ቤተሰብ፡፡ይሄ ሁለት ቤተሰብ የተሳሰረው ዛሬ
👍707👎1
አብራን በሌለችው በበሬዱና አጠገባችን ባለችው በፀሎት ነው፡፡የእኔ ልጅ ዛሬ በህይወት ያለችው ከበሬዱ በተሰጣት ልብ ነው፡፡እዚህ እነአቶ ለሜቻ ቤት ለሟች ልጃቸው የሙት አመት መታሰቢያ ሲከበር በእኛ ቤት ግን ለልጃችን ንቅለ-ተከላ ተደርጎላት ዳግም የመኖር እድል ስላገኘች ድል ያለ የምስጋና ድግስ እናዘጋጅ ነበር ..ዘንድሮ ግን በፀሎት ውሳኔ እንደዛ ማድረግ አልቻልንም…እዚህ ግቢ አንድ ላይ መታሰቢያውንም ምስጋናውንም አብረን እንድናከብር ወስነናል..አሁን ሁላችንም ወርደን የተዘጋጀውን ዝግጅት እንታደም፡፡››የሚል ንግግር ካሰሙ በኃላ በራፉ ተከፈተ …
ዛሬ እየሆነ ያለው ነገር በጠቅላላ ምንም ያልገባቸው አቶ ለሜቻና ወ.ሮ እልፍነሽ አቶ ኃይለልኡልንና ባለቤታቸውን ተከትለው ከባስ ወረዱ፡፡ይሄንን ሰፈራ የሚገኘው በገዛ ቀበሌያቸውና በሰፈራቸው ስለሆነ በደንብ ያውቁታል፡፡ግቢው ንብረትነቱ የቀበሌው ሲሆን  ባለ5 ሺ ካሬ ግዙፍ ጊቢ ነው…ከመኪና ወርደው ሲመለከቱ ግቢው በሰዎች ታጭቆል ፡፡ ሰዎቹ ደግሞ አብዛኛው ጎዳና ተዳዳሪዎች፤የኔ ቢጤዎች የደከሙና የተጎዱ አቅመ ደካሞች…..ለአይን እንኳን ተቆጥሮ የማያልቅ የእንጀራ ክምር ..በበርሜል የተደረደረ ልዩ ልዩ የወጥ አይነት…ራቅ ብሎ ደግሞ በተንጠልጣይ ብረት ላይ የተደረደረ ጥሬ ስጋ እንደተራራ የተቆለለ የታሸገ ውሀ……

በሌላ ጎን ከአዳራሹ ፊት ለፊት ግዙፍ ፖስተር ይታያል…በፖስተሩ ላይ በቀኝ የበሬዱ ፎቶ በስተግራ ደግሞ የበፀሎት ፎቶ መሀከል ላይ የበሬዱ በፀሎት የምገባ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ይላል፡፡ብዛት ያላቸው ጋዜጠኛች ከወዲህ ወዲያ እየተዘዋወሩ ፎቶ ያነሳሉ ኢንተርቪው ያደርጋሉ፡፡
ማታ በሁለት ሰዓት ዜና ላይ በኢትዮጴያ ቴሌቭዝን የቀረበው ዜና የሚከተለው ነበር….
‹‹የታዋቂ የቢዝነስ ማን አቶ ሃይለልኡል ብቸኛ ልጅ ከጠፋችበት መገኘቷ ታወቀ…በፀሎት ከሶስት አመት በፊት ልቧ መስራት አቁሞ የነበረ ሲሆን በዛን ወቅት የመኪና አደጋ ደርሶባት አብራት ለህክምና ወደ ታይላንድ የሄደችው በሬዱ ለሜቻ ህይወቷ በማለፉ አባትዬው በሰጡት ፍቃድ መሰረት ልቧን ለበፀሎት በመለገሷ የልብ ንቅለ-ተከላ ሊደረግላትና ድና ወደሀገር ልትመለስ ችላለች…ባለፈው ወር የጠፋችው በፀሎት ኃይለልኡል የተገኘችው በእነዚሁ በአቃቂ ክፍለከተማ በሚኖሩት ልብ በለገሰቻት ልጅ ቤተሰቦች ቤት መሆኑ በጣም አነጋጋሪና አስደማሚ ታሪክ ሆነዋል፡፡
በዛሬው እለት የበሬዱ የሶስተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ የነበረ ሲሆን በተመሳሳይ ሁኔታ ባለፉት ሁለት አመት እንደተደረገው በአቶ ኃይለልኡል ቤት የምስጋና ድግስ ሲደገስ የቆየ ቢሆንም..ዛሬ ግን ይሄ ቀርቶ አቶ ኃይለልኡልና ቤተሰባቸው በቤታቸው የደገሱትን ድግስ ሙሉ በሙሉ ሰርዘው በሞች በሬዱ ለሜቻ የትውልድ አካባቢ ለስሟ መታሰቢነት እንዲሆን ከዛሬ ጀምሮ በአካባቢው አቅም የሌላቸውና ችግረኞችን በቀን ሁለት ጊዜ የሚመግብ በሬዱ በፀሎት ምገባ ተቋምን ከፍተው ያስመረቁና በቦታውም ከ500 በላይ ሰዎችን በመመገብ ማስጀመራቸውን ማወቅ ተችሏል፡፡
በዚህም የሞች አባት የሆኑት አቶ ለሜቻ ስለሁኔታው ሲናገሩ‹‹በእውነት ልጄ ዛሬ ሞትን ድል ነስታ እንደተነሳች ነው የምቆጥረው..ልጄ በህይወት እያለች ለተቸገረ ሁሉ የምታዝን የዋህ ነበረች..አሁንም ከሞተች በኃላ ይሄው በስሟ ብዙዎች ጠግበው እንዲያድሩ ምክንያት ስለሆነች ኮርቼለሁ….ይሄንን እውን ያደረጉትን አቶ ኃይለልኡል እና ባለቤታቸውን አመሰግናለሁ….የእነሱ ልጅ የሆነችው በፀሎት ለእኔም ልጄ ነች….ከአሁን በኃላ በሬዱ ሞተች ብዬ አላዝንም…. ስትናፍቀኝ በፀሎትን አቅፌ አፅናናለሁ…ደግሞ እዚህ ስፍራ መጥቼ በስሟ ሰዎች ምግብ ቀምሰው ሲያድሩ ተመልክቼ ረካለው››በመላት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል…የሚል ነበር፡፡

ከድግሱ በኃላ አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ ወደቤታቸው ሲሄዱ በፀሎት ግን ለሊሴን ተከትላ ወደእነሱ ቤት ነበር የሄደችው…በማግስቱ ግን ቤተሰቡ በአጠቃላይ ተሰብስበው ወደቦሌ ሄዱ ፡፡ሲደርሱ ሰለሞንም ነበር….ይህ ዝግጅትና ግንኙነት ለሁለቱም ቤተሰብ ልክ እንደቅልቅል ነው፡፡በዚህ ደግሞ ቁጥር አንድ የፈነጠዘችው በፀሎት ነች፡፡የእሷን ደስታና ፈንጠዝያ ሲከታተል የነበረው ሰለሞን ‹‹እሺ ይህቺን ልጅ ለማግባት ልጃችሁን ስጡኝ ብዬ ሽማግሌ ምልከው ለየትኛው ቤተሰብ ነው፡፡ብሎ እራሱን ጠየቀና ፈገግ አለ፡፡‹‹ግድ የለም እሷ ትስማማ እንጂ እኔስ ሁለት የሽማግሌ ቡድን ማቋቋም አያቅተኝም፡፡›› ሲል ለራሱ መልስ ሰጠ፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ ፊራኦልም ከሰለሞን ጎን ተቀምጦ ፊት ለፊቱ በፀሎትን እየተመለከተ በውስጡ ‹‹እሺ አሁን የእህቴን ልብ ተሸክማ እህቴ ስለሆነች ልደሰት ወይስ. ፍቅሬን ተቀብላ ፍቅረኛዬ መሆን ስለማትችል ልከፋ?››በውስጡ የሚያመነዥገው ጥያቄ ነበር፡፡‹‹ፍቅሯ በዚሁ ቀጥሎ ከባሰብኝ ምንድነው የማደርገው?››በጣም ተጨነቀ፡፡

ተፈፀመ

በሌላ ስራ እስክንገናኝ ደህና ሁኑልኝ።


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
1👍11830😢16🥰9👏4
"ሁሌ ባገኝህ አይሰለቸኝም" አለችው

"እውነትሽ ነው"

"አዎ ገና መተዋወቃችን ቢሆንም ደጋግሜ ላገኝህ እፈልጋለሁ"

ዝም ተባባሉ ረጅም ሰዓት።

"እኔ ምልህ ህይወት ላንተ  ምንድነው አለችው?"

"ቀይሮ መድገም ነው" አላት

"ማለት"

"አሁን የሆነች ተራ ካፌ ቡና ትጠጪያለሽ ሲኖርሽ ሸራተን ነው ራሱን ቡና

አሁን  አንድ ክፍል ቤትሽ ውሰጥ ትተኛለሽ
ሲኖርሽ አስር ክፍል ያለው ግን አንዱ ክፍል ብቻ ራሱን እንቅልፍ ትተኛለሽ

ደሀ ሆነሽ አረቄ ነው
ሀብታም ስትሆኚ ውስኪ ነው ቀይሮ መድገም

ሰው ለምን ይመስለሻል አንድ ደብር ደጋግሞ ከመሳለም ደብር የሚቀያይረው ቦታ ቀይሮ ጸሎት ለመድገም ነው።

በፊት የሆነ ልጅ ትወጃለሽ ስትለያይ
ልጅ የሆነ ትወጃለሽ 
ያንኑ መውደድ ቀይሮ ነው መድገም ነው

የሆነ ዘፈን በሌላ ዘፈን ዘፋኝ ቀይሮ መድገም

የምታውቂውን ስብከት በሌላ ሰባኪ ወይም ቄስ ቀይሮ መድገም 

በኢኮኖሚ ክላስ መሄድ ዝነኛ ስትሆኚ እዛው ፕሌን ውስጥ ቢዝነስ ክላስ ሆኖ ወንበር ቀይሮ በረራ መድገም

ሰው ሁሉ ገንዘብ የሚፈልገው የነበረውን ነገር ቀይሮ ለመድገም ነው።"

የሆነ ነገሯ ተዛባባት።

"በቃ የዘመኑን ከቨር ሙዚቃ ታውቂያለሽ?"

"አዎ" አለችው

"የኛ ሰው ህይወት እንደዛ ነው
የህይወት ከቨር በይው።
የሆነ የሆነ ነገር ቀንጭጮቦ መምጣት ቀጣጥሎ ማዜም
ቀያይሮ መድገም..."


"የሚቀጥለው አመት እደውልልሀለሁ" አለችው


🔘ኤልያስ ሽታሁን🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍49🔥11😁42👏1
አንድ በይ

አልቸኩልም ገላ አውቃለሁ
                :
አልስምሽም ከንፈር ያው ነው::
               
ደክሜያለሁ በብዙ ሴት
ግና የለም አዲስ ሀሴት።


ሁለት በይ

ስንቱን ጣለ ወገብ ዳሌ
              :
ወንድ ይቀልጣል እንዳሞሌ።
                
በቃኝ አይሉት ደስታ ባለም
ስሜት አውሬ ጠገብኩ የለም።

ያጠምደዋል ስሜት መረብ
ለመለያየት ነው ያንዳዱ አቀራረብ።

በመጨረሻም

አንቺን ግና
እስክትስሚኝ እንዲጨንቀኝ
ተረት አውሪኝ ሴት ይናፍቀኝ።
ፍቅራችንን ነፍስ ዘርቶ እንድናየው
ደስታችንን እናቆየው።

በትንሽ እንኑር
ቶሎ አይፈጸም የጎዟችን ሜዳው
ደስታን ሲያሳድድ ነው ፍቅር የተጎዳው።


🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
🥰22👍20👏32🔥2
#ምን_እየሆንኩ_ልጠብቅሽ?

ቅድ ሰማይ እየሰፋሁ
ራስ ዳሽን እየገፋሁ
ወይስ
እየሰራሁ የኖኅ መርከብ
ሳፈላልግ የሰው ኮከብ..
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?

እየዘመርኩ?
እየዘፈንኩ?
እያረመምኩ?
ግራ ገባኝ እኮ
ያልለየት ድል ነው ያልለየት ምርኮ።

ምን ስሆን ልጠብቅሽ?
አባይን ስጠልቀው
ኤርታሌን ስሞቀው
ቆዳዬን እንደጨርቅ ችሎ ቢተኩሰው
ተዋነይ ጋር ልሂድ ዕፁን እንዲምሰው።

ማን ጋር ልጠብቅሽ?
ከጌታዬ ግራ ከጌታዬ ቀኙ
በየት ትመጫለሽ ወይ አፍቃሪ ሞኙ።
ካብርሃም ቤት  አጋር
ወይስ
ባቢሎን ግንብ ጋር።

የት ጋር ትመጫለሽ?

በዘመን የት ዘመን?
በቦታ የት ቦታ?

ከንጉሥ የት ንጉሥ?
ከባህር ምን ባህር?

ከጫካ የት ጫካ?
ከደብር የት ደብር?
           :
ከሶላት ምን ሰዓት?

ምን እያረግኩኝ ልጠብቅሽ?
ከመላእክት ጋር ስገለፍጥ
የዛፍ ቆዳ ስልጥ...

ግዙፍ ሆኜ ወይ ረቂቅ
ንፋስ ሆኜ ወይስ ደቂቅ....

ወንዝ ሆኜ ወይስ አምባ
ደስታ ሆኜ ወይስ ዕምባ...

ፀሀይ ግርጌ ወይ ጨረቃ
ግጥም ሆኜ ወይ ሙዚቃ...

ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
🥰29👍247
#ምኑ_ነው_ስህተቴ'

ተሳሳትሽ አትበለኝ የቱ ነው ስህተቴ፤
ጥበብ ነው ማርከሻ የብዕር ጥይቴ።
አዎ መንጋማ አለ ከጥንት መሰረቱ፤
እየሱስን አስረው በርባንን ሲያስፈቱ።

ዛሬም በኔ ዘመን
የመንጋ ፍርድ ነው ሀገሬን የፈታት፤
አዋቂ ዝም ብሎ መንጋ እየፈተታት።
በድንጋይ በርሚል ውስጥ ሽ ድንጋይ ቢቀቀል፤
ሽ ዘመን ተጥዶ እልፍ አመት አይበስል።

አገር ተረክቦ በሰፈረ የኮራ፤
የመንጋ ፍርድ አይደል ያበቃን ለተራ።
የቱ ጋ ነው የሳትኩ አርመኝ መምህሩ፤
ምላስክን አጥፈኽው ሞክር በብዕሩ።
ዘመን የሰጠው ቅል ድንጋይ ቢሰብር ጣሪያ፤
ማዕዘን ተደርጎ አይሆን ለቤት መስሪያ።
ሰውነት ነው ልኩ የሰው ሚዛን ፍርዱ፣
አዋቂ እንዲበይን መንጋዎች ይውረዱ።

አሁንም እላለው
በመንጋ ተፈጭቶ በመንጋ ተጋግሮ፤
እልፍ ጾም አዳሪ ወና ነው ጉረሮ።
ቤት መምታት ቤት መድፋት ስንኝ መቋጠሩ
ጥበቡ ቢያቅተው፤
ቤት እያፈረሰ ህዝብ እያስደደ
አገሩን አመሰው።
እኔ ይሄንን ሰው፣
ሌላ ምን ልበለው፣
መንጋነትም ሲያንሰው።

በባዶነት ሙሌት በዘር እብሪት ታስሮ፣
ከጥበብ ጓዳ ውስጥ ከሰውነት አጥሮ።
አበውን ሲያሰደድ ሲያርድ ሲያጎሳቁል፣
አንተም መንጋ ካልሆንክ መቼም ሰው ነው አትል።

እና ምኑ ላይ ነው ብዕሬ የሳተች፣
ብሔር የነቀፈች ህዝብን ያዋረደች።
"ንገረኝ በሞቴ የመንጋው ጠበቃ
አንተም ሰው ሁንና መንጋነትህ ይብቃ"

🔘ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍30🔥21
#ሳትመጪ_ነይ

የጀመርሽው መንገድ ፥ ጉዞሽ እንዲቃና
በስሌት ተራመጅ ፥ ስሜቱን ተይና፣
ከልካይ የለም ብለሽ ፥ አቲጅ በመደዳው
ፈንጂ ወረዳ ነው ፥ የጨዋታ ሜዳው፣
ይልቅ ኳሷን ላኪያት ፥ ትሂድ ቃልሽን ሰምታ
ገላሽ ሳይሸራረፍ ፥ ህልምሽ ግቡን ይምታ።

🔘በርናባስ ከበደ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍185
#እንደነገርኩሽ_ነው 
         
        አፍሽም ለብቻው - ስሙን እያወጣ ፣
        ጆሮሽም ለብቻው - ስሙን እያወጣ ፣
        ወየው ! ወየው ! እንጂ … ወዬ ! የሚል ታጣ

እግዜሩም! እንደ ሰው!
         ባለመስጠት ሞላ ፣ ከመስጠት ጎደለ ፤
         ብጠራው? ብጠራው? 'አቤት' አልል አለ ።
ማለትሽን ሰምቼ
… እኔ ምልሽ...
ምስኪን እግዜርሽን!
         ካመልሽ አዛምደሽ ፣ ከምትጠረጥሪው ፣
         እስቲ ቅፅሉን ተይና  በዋና ስም ጥሪው ።

ሰሚን ሲደልሉ !
ጠሪን ሲበድሉ !
ለግዜሩም! 'ቅፅል-ስም' አወጡለት አሉ ።

እናልሽ  . . .
በልጥፍጥፍ መአት ዋናው ገጽ ፈረሰ ፤
ስም አውጪው ቢበዛ አቤት ባይ አነሰ ።

ደግሞ . . .
አመሌን ! አመልሽን ! ለማያውቁ ሁሉ ፣
"ጠርቼው አልመጣም" ትይኛለሽ አሉ ።

         እሷ የስም ሀብታም !
         ትጠራው አታጣ ! ትሸኘው አታጣ !
እኔ ባለ አንድ ስም ― ምን ሰምቼ ልምጣ ?

         እሷ የስም ሀብታም !
         ስትገዛ በደርዘን ! ስትሸጥ በደርዘን !
ይኸው ከስረን ቀረን ― አንድ አንድ ስም ይዘን።

         ሰሚን ሲያጣጥሉ ― ጠሪን ሲያቃልሉ ፤
         ስም አምራቾች ሞሉት ― ጉራንጉሩን ሁሉ ።

      ]  የላክሽው ፎቶ አንሺ  [
በጥላሽ ከልሎ ፣ ባንቺ ብርሃን ኩሎ ፤
ፎቶ ነስቶኝ ሄደ ― ፎቶ አነሳሁ ብሎ ።

        ፓ!  ፓ¡  ፓ!  ካሜራ ¿  ...  ኧረረ ! !  ካሜራ ¡ ¡
                     በሌሉበት ሁሉ ማንሳት የማይራራ ¡
                     ሊያውም በክት ልብስ ጥለት አዛንቄ …
                     ሊያውም በጀግና ልብስ በኒሻን ደምቄ …

             ... … እያገላበጠ … …

     'ተዟዟርር' እያለ ― ሲያነሳኝ ሰንብቶ ፣
              በትኖልኝ ሄደ ― ልብስ የሌለው ፎቶ ።
                      ካሜራሽ ስልጡኑ ¡ ካንቺ እኩል ያወቀ ¡
                                  ፎቶ ያጥባል ! አሉኝ … ልብስ እያወለቀ ።

እንደነገርኩሽ ነው ።

              የማንም ያልሆነን ― ያንተ ነው ተብዬ ፣
              በምስልሽ ፈንታ ― ፍሬምሽን ሰቅዬ …
                       … ግራ የገባው ዓይኔ …
               በከልካይ መነፅር ከቧልት ይፋጠጣል!
                       … ካሽሙር ይፋጠጣል …
                   የጀግና ፎቶዬ ከሱቅሽ ይሸጣል ።
.
                 አንቺ የመልክ ሀብታም ፤ ቀለም የተረፈሽ ፣
                 አንቺ የመልክ ሀብታም ፤ መስመር የተረፈሽ ፣
                 የተኩላዎች ክፋት ― በበጎች ስም ፅፈሽ ፤
                 መጥቀሻል ይሉኛል ― በምኞት መሠላል ።
       … ግድየለም ምጠቂ …
                 ቅዠት ሲደጋገም ― ከህልም ይመሳሰላል ።

እንደነገርኩሽ ነው
      ቧልተኛው ዶክተርሽ በስላቁ ፈዞ ፣
             'አከምኩህ' ይለኛል ¡¿
      የራሱን መዳኒት ለመምተኛው አዞ ።

የመምተኛሽ ደግሞ …
       ካኪምሽም ብሶ ሁለቴ ገደለኝ ፤
               ተመረመርኩልህ ይቺን ዋጣት አለኝ።
                       በታመመ ልኩ ― ጤና ሲሰፍርልኝ …
                                በሽተኛ ልጅሽ ― ተመረመረልኝ ።
.
መድሃኒት ከሰረ
      ጤና ተቃወሰ በሽታ ተስፋፋ
              ግብረ ገብ ጎደለ ስነ ምግባር ጠፋ
                             ወዘተ . . . ወዘተ . . .
                  ጉባኤ ሰብስበው ሰበብ ሲያዳምቁ
                              እኔን የገደለኝ ከበሽታው ይልቅ
                                        በሽተኛው በውል አለመታወቁ ።

ያንቺማ ዓይነቱ
ማድማቱን ደብቆ ፣ መድማቱን ለብቻ እያስመረመረ ፤
             ፈውስ በስም ብቻ ተድበስብሶ ቀረ ።

በኔ"ና አንቺ ዓለም … ከማዘን ! ― ማሳዘን !
       ከመሳት ! ማሳሳት ! ― ከደም ማነስ ! ደም ማሳነስ !
               ከመርሳት ! ማስረሳት ! በእጥፍ ይቀድማል ፤
                       ከበሽታው ይልቅ … በሽተኛው ያማል ።
.
ኧረ ያንቺስ ሞያ
       ትንሽ እየሰፋ ― ብዙ መቅደድ ያውቃል ፤
       ክርሽ ስራ ፈትቶ ― መርፌሽ ብቻ ያልቃል ።
ኧረ ያንቺስ አራጅ ቅርጫሽን ሳንበላው …
" ያልቅብሻል " አሉ! ሞረድ እና ቢላው ።
.
... እንደነገርኩሽ ነው …

                        ጎዳናው ሳይጠበን አመል እያጋፋን !
                        እንኳን አካሄዱ ― አቋቋሙ ጠፋን ።

🔘በረከት በላይነህ🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍5511👏6🥰1
#ትርጉም !
..
"አስቀያሚ፣
አሰጠሊታ ፣
መልከ  ጥፉ፤
እንደ ደሀ  ቀዬ መስቦችህ የረገፉ!

የማትባል  እዚህ ግባ ፣
የሰው ፍራሽ  ፣ ማማር አልባ!

ፊተ መአት ፣ ያመድ ክምር!
የጭራቅ ሳቅ  ያይጥ ፞ ድምር
              ባትታይም የማታምር! !!"

እረ !  ሌላም፣ ሌላም፣
ትልሀለች ብለው የነገሩኝ ለታ ፤
አቤት ሀሴት ፣ አቤት ደስታ!

ለምን ብትይ?

መልኬ ከሸለመሽ  የማይሽር ጥላቻ ፤
ደስታ  አሰከረኝ 'ስላየሺኝ' ብቻ

🔘በረከት በላይነህ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍238🎉1
#መራራቅ
:
:
ቅዠታም አዳሩን ጨፍጋጋ ዉሎዉን
ዝብርቅርቅ ተስፋዉን ደረቅ ትዝታዉን
በይሉኝታ ከፈን እየጠቀለለ ከጥርሱ ሲጥለዉ
ተቀባይ ይሻማል ሳቅ እየመሰለዉ።

🔘በረከት በላይነህ🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍352
#ግን_አንድ_ቃል_አለ!

.እኔ በቅሎ አደለሁ

ይሄ ሁሉ ሸክም በላዬ ተጭኖ
እንደምን ልራመድ
የየለት ተግባሬ ብልጭ ብሎ መጥፋት
እሳት ሆኖ ማመድ

መኖር አለመኖር
አለመኖር መኖር

መሆን አለመሆን
አለመሆን መሆን

ጊዜ እነደሽልጦ እያገላበጠኝ
ወይ በደህና አልበስል
ዝም ብዬ እፀናለሁ እዮብን ይመስል

ዝም ብዬ
ዝም ብዬ
ይህም ያልፋል ብዬ

በጣር ያቆምኩት ቤት በንፋስ ይገፋል
በውኔ ያቀድኹት ህልም ሆኖብኝ ያልፋል

ወይ በርትቼ አልቆምም ወይ ወስኜ አሎድቅም
ዝም ብዬ እድሀለኹ እንደ ህፃን ልጅ አቅም

ዝም ብዬ
ዝም ብዬ
አንዲትን ቃል ብዬ

ላለመሞት መሞት ለመኖር መታገል
ብረት ነኝ ስል ኖሬ ሸክላ ሆንኩ እንደገል

ስብር ብር ..
. እንክት ክት
ጊዜ ሁን ያለኝን በምኔ ልመክት
ብቻ ግን ብቻ ግን አለሁ ለምልክት

ግን አንድ ቃል አለኝ
"አለት ሆኜ ወደኩ ጠጠር ሆኜ በዛው
የሚል ታሪክ አለኝ ነፍሴን የሚገዛው"
ተመስገን፡፡

🔘አስታውሰኝ ረጋሳ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍39🥰21
#ይነጋል

ታድለሻል ቢሉም፣
የ13 ወር ፀሀይ፣ የ13 ወር ፀጋ
ብርሀንሽ ተሰርቆ፣
ሲጨላልም እንጂ፣ መች አየን ሲነጋ?

ተፈጥሮ ቸር ሆና፣
ሰማይዋ ባይነጥፍ፣ ምድሯ ቢለመልም፣
ከልጆቿ ልብ ውስጥ፣
ፍቅር ሲጎድል ነው፣ ሀገር የምትጨልም!፣

"አረ ነግቷል" ቢሉ የታለ የነጋው?
አዕላፋት ተቧድነው፣ በየጎጥ በመንጋው፣
ሰው ከነገ ይልቅ፣ ዛሬን እያሰጋው የታለ የነጋው?
ታሪኩን እንዳይፅፍ፣ ትውልድ እጁ ታስሮ፣
በትላንቱ ሾተል ዛሬው ተሸንቁሮ፣
ባልኖረው ተካሶ፣ ባልሰራው ተዋቅሶ፣
ለፀብ መዶለቻ፣ ያ'ያቱን ስም ጠቅሶ፣
ላለፈው ሲናከስ ለመጪው ሳይተጋ፣
በምን ስሌት ይሆን፣
ትዉልዷ ጨልሞ ሀገር የምትነጋ?
.
የህሊና መስታወት በጥበብ ሲፀዳ፣
ማስተዋል እንዳ'አደይ ፈክቶ ሲፈነዳ፣
መገፋፋት ሲቀር ፣መደጋገፍ ነግሶ
አንዱ ማገር ሲሆን፣ ሌላኛው ምሰሶ፣
የአብሮነትን ሸማ ትዉልዱ ሲሸምን፣
ያኔ ነው ሀገሬ መንጋቷን የማምን።

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍274🔥3
#ጥበቃ

እኛን ያሳደጉን

'"ሀገር ተረካቢ" በሚሉት ሀረግ ነው፤

አድገናል እንሆ

ሀገሪቷን ስጡን እየጠበቅን ነው።

🔘በረከት ባይጨክን🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍17😱61
#የታል_ልጅነቴ?

እነ ጋሽ አበበ ሚጡዬና ቹቹ

እነ ትዬ ፀሐይ እንዲሁም ሌሎቹ

ወዴት ተሰደዱ የታሉ ሰዎቹ የሰፈሩ ሜዳ የለም ከኖረበት መንገዱም ተለምቷል ሱቅ የተላኩበት የታሉ ዛፎቹ ምሽግ መስሪያዎቹ ልጥ የላጥንባቸው ኳስ ማሰሪያዎቹ ካሬ ስድስት ቆርኪ የተጫወትኩበት የት ሄደ ደስታዬ የት ሄደ ልጅነት ሸርተቴ ያልኩበት የጭቃው ተራራ

ልጅነቴን ትቶ ፎቅ በላዩ ሠራ

መርቅ አልመርቅም የተጣላሁበት

የከድር ሱቅ የለም ፈልጌ አጣሁት

ቡልኮ ጠጅ ቤት ጉልት የሰፈሩ

ተሰደዱ መሰል እነሱም ሳይቀሩ

ከቤቴ በር ላይ ወጥቼ ቆሜአለሁ

ሰላም የሚለኝ ሰው በዓይኔ እፈልጋለሁ

በተወለድኩበት ባደኩበት ሰፈር

ሆኛለሁ ባይተዋር

የለም ልጅነቴ

ማርና ወተቴ

🔘እመቤት መንግሥቴ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍26😢116👎2
Forwarded from አትሮኖስ (◔͜͡◔ Mellos ◔͜͡◔🐾🦒)
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...

🦧| ምትሰበስቡት ነጥብ ቀጥታ ወደ ቶክን ይቀየራል
🦓| ፕሮጀክቱ ለጥቂት ግዜ የሚቆይ ስለሆነ አያሰላቻም
🐊| አጨዋወቱ እንስሶችን በተሰጣችሁ Feed መመገብና Upgrade ማድረግ ነው
🦜| ብዙ ሰው ስላልበዛበት በግዜ ብትጀምሩ ይመረጣል

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍122
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን
==========================
ዛሬ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ድክምክም ብሎኛል፡፡ብዙ ስራ እየሰራሁ ስለዋልኩ አይደለም..እንደውም በተቃራኒው ስቀመጥ ስለዋኩ ይመስለኛል ዛል እስክል የደከመኝ፡፡ ‹‹መቀመጥ መቆመጥ ነው››ትል ነበር አንድ ኑሮዋ ጠቅላላ ተረት በተረት የሆነባት ተራች አክስቴ፡፡ ሰዓቱ 12፡35….ሆኗል ፡፡ምሽቱ ደረስኩ እያለ ነው፡፡ስቀመጥ ከዋልኩበት ቢሮዬ ለሊቱን ስተኛ ወደማሳልፍበት ቤቴ ቀጥታ ማምራት ስላልፈለግኩ ለምን ትንሽ ወክ አላደርግም አልኩና ወደ ቤቴ አቅጣጫ በጣም በዝግታ ማዝገም ጀመርኩ፡፡እርምጃዬ ጽሞና የታከለበት እንዲሆን ስለፈለኩ ዋናውን የአስፓልት መንገድ ለቀቅኩና በሁለተኛው መንገድ መጓዝ ጀመርኩ.፡፡እሱም በባጃጅና በመንገደኛ ሰዎች ስለተሞላ አልተመቸኝም ወደ 3ተኛው መንገድ ተሸጋገርኩ፡፡አዎ ይሄ ይሻላል.. እሬሳን ወደ የዘላለም ማረፊያው ወደ ሆነው ቀብሩ እንደሚሸኝ ሰው ወይም በመንግስት ወታደሮች እጅ ወድቆ እጁ በሰንሰለት ወደኃላ እንደተጠፈረ አሸባሪ ተብዬ እጆቼን ወደኃላ አጣምሬ በዝግታና በፀጥታ እጓዛለሁ፡፡አካባቢው ፀጥ ያለ ነው፡፡አዕምሮዬ ግን በጫጫታ የተሞላ ነው፡፡ዝም ብሎ ህልሙንም እውኑንም ይፈተፍታል፡፡

ድንገት ከአንዱ መንገድ ተጠምዝዤ ወደ አንዱ ስገባ ዓይኔ አየ.. ምን ዓየ …..?አትሉኝም፡፡ልክ ለዘመናት እንደተራብኩት የእናቴ ጡት ዓይነት ነገር፣ልክ በፀሎት እና በእምነት አማኞች እንደሚናፍቆት ገነት ዓይነት ፣ልክ ፖለቲከኞች ለዘመናት ይመኙት እንደነበረው የቤተ መንግስት ወንበር ዓይነት… አይገርምም…፡፡ ያየሁት እኮ አሁን እንደጠቀስኩላችሁ ዓይነት ነገር ሆኖ አይደለም..እኔን ግን ውስጤን የተሰማኝ…በወቅቱ አደነዛዘዜ ፤ አደነጋገጤ እንደዛ ነው ያስመሰለብኝ፡፡ …ወፈር ደልደል ያለ ቀይ ቂጥ ነው ያየሁት..….ያየሁት ከገባሁበት መንገድ በግራ ጠርዝ በኩል በግምት 100ሜትር ርቀት ላይ የቀበሌውን ጽ/ቤት አጥር ተጠግቶ ነው፡፡እኔ ያልኳችሁ ፍም ቂጥ ብቻ አየሁ አይደል..?ግን የዘነጋሁት ወይም ያልነገርኳችሁ አንድ ነገር የቂጡንም ባለቤት ማየቴን ነው፡፡ግራ ቀኝ ስታማትር እሷም እኔን አይታኛለች፡፡ግራ የተጋባች ይመስላል፡፡የለበሰችውን ቡኒ ጅንስ ሱሪ አውልቃ ጉልበቷ ጋር አድርሳዋላች ፣በእርቃን ቂጧ እና ወልቆ ጉልበቷ ጋር በደረሰው ሱሪዋ መሀከል ሆኖ የሚዋልል ሌላ ቀይ ነገር ይታየኛል..አዎ ፓንቷ ነው ፡፡ ግራ ገብቷት ወይም የራሱ ጉዳይ ብላ መሰለኝ ችላ አለቺኝና ቁጢጥ አለች፡፡
እኔም የእራሴው እርቃን በአደባባይ እየታየብኝ ያለ ይመስል ሽምቅቅ ብዬ የ100 ሜትሩን ርቀት ወደ 70 ሜትር ካጠበብኩት በኃላ ቆምኩ፡፡..በቃ  ዝም  ብዬ  ቆምኩ፡፡ ቆሜም  ማሰላሰል  ጀመርኩ፡፡ እሷም አንዴ ወደ መሬት አንዴ ወደ እኔ እያች የኩላሊቷን ጥዝጣዜ ና የፊኛዋን ውጥረት ማስተንፈስ ቀጠለች….‹‹ሾሾ… ሾ… ዋዋ›› የሚል የሽንት ድምፅ ተሰማኝ..፡፡እርግጠኛ ግን አይደለሁም፡፡ ብቻ የሰማሁ መስሎኛል፡፡
ግን በፊት ቅምቅም አያቶቻችን ለወንድ ሱሪ ለሴት ቀሚስ የሚባል ልብስ ለምን እንዲኖር እንዳደረጉ ዛሬ ነው ፍንትው ብሎ የገባኝ.፡፡ይሄኔ እኮ ይህቺ ሚስኪን ሴት ቀሚስ ለብሳ ቢሆን ኖሮ እሷም አትጋለጥም.. እኔም አልደነግጥም ነበር፡፡ቁጭ ብላ ቀሚሷን ገለብ ታደርግና ‹ሾዋ..ዋ…ዋ› በማድርግ ከተነፈሰች በኃላ ምንም እንዳልተፈጠረ ተነስታ ትሄድ ነበር፡፡
ወይ..ሀሳቤን ሳልጨርስ ጨርሳ ቆመች፡፡ፊቷን ከእኔ በተቃራኒው  አዞረችና መጀመሪያ ቀዩን  ፓንቷን ወደ ላይ ስባ  ቀዩን ቂጧን ሸፈነችው፤  አቤት  በፓንትም  ሲታጠር  ያምራል፣ምራቄን  ገርገጭ አደረግኩ፡፡ ከዛ ሱሪዋን ወደ ላይ እየጎተተች ለበሰች፡፡ከጨረሰች በኃላ ቀጥታ ወደ እኔ አቅጣጫ መጣች፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ወደ ኃላ ልመለስ ወይስ ወደ ፊት ልቀጥል…?፡፡ከሁለቱ እግሮቼ የትኛውን ላስቀድም?፡፡ እያልኩ በሀሳብ እየተጨነቅኩ ስዋልል እሷ ቀድማኝ ስሬ ደረሰች፡፡አትኩሬ አየኋት… ቂጧም ብቻ ሳይሆን መልኳም ቀይ ነው፡፡የሆነ ክልስ ነገር ሳትሆን አትቀርም…፡፡ፈርዶብኝ ቀይ ሴቶች ልቤን በቀላሉ ብትንትን ያደርጉታል ፡፡ፍቅረኛዬ ሀይሚም እንደዚህችው ነች፡፡ ዓይኖቾ ጐላ ጐላ ያሉ ባለ ሉጫ ፀጉር ነች..፡፡አደንዛዥ ፈገግታ መግባኝ ታካኝ አልፋኝ ሄደች፡፡ እኔም ቀኝ ኃላ ዞሬ ተከተልኳት፡፡ ውሳኔዬ እሷን መከተል እንዲሆን ያስገደደኝ የቂጧ ቀይነት ይሁን የፈገግታዋ ጉዳይ አልገባኝም፡፡ደረስኩባት እና ዝም ብዬ ከጎኗ መራመድ ጀመርኩ፡፡
ግራ ገባቷት‹‹እንተዋወቃለን?››አለቺኝ፡፡

‹‹አሁን ተዋወቅን አይደል እንዴ?››መለስኩላት፡፡

‹‹አሁን የት ?››

‹‹እዛ ነዋ.. እኔ ፈዝዤ ተገትሬ አንቺ ቁጢጥ ብለሽ፡፡››

ከት ብላ ሳቀች… ሳቋ ያምራል‹‹…ጉደኛ ነህ!!! ትንሽ እንኳን አታፍርም እንዴ..?እኔስ ተጨንቄ ነው አንተ ምን አለ ዞር ብትልልኝ  ኖሮ?››

‹‹ወዴት ዞር ልበል..?ከተጠጋሁሽ እኮ ይበልጥ አይሻለሁ ብዬ ነው  የቆምኩት፡፡››

‹‹ዞረህ በሌላ መንገድ አትሄድም እንዴ?››

‹‹አኸ እንደዛም ይቻል ነበር ለካ..?እሱ እንኳን ትዝ አላለኝም፡፡››

‹‹ደንዝዘህ እንዴት ትዝ ይልሀል..?ወይ ወንዶች ስትባሉ!!!›› አለችኝ፡፡ይህቺን‹ ወይ ወንዶች ስትባሉ!!! › ቢያንስ ከ100 ሴቶች ሰምቼያታለሁ ፡፡ግን ወንዶች ስንባል እንዴት ነን..? ያው እንደዛ የሚሉን ሴቶች እራሳቸው ይመልሱት ፡፡

‹‹ግን ያምራል›› አልኳት፡፡

የድንጋጤም የእፍረትም ሳቅ እየሳቀች‹‹ምኑ?›› አለችኝ፡፡

‹‹ያየሁት ››አልኳት… አኔም በተራዬ እንደማፈር ብዬ፡፡

‹‹የትኛውን አይተህ የትኛውን እንደዘለልክ በምን አውቃለሁ?›››

‹‹ከወርቃማዋ ሸለቆሽ በስተቀር ሁሉንም አይቼያለሁ››

አቤት የሳቀችው ሳቅ… እንባዋ እስኪንጠባጠብ ነው ተንፈራፍራ የሳቀችልኝ፤ሴት  ልጅ  እንደዚህ  ስትስቅልኝ  ለመጀመሪያ  ጊዜ ይመስለኛል፡፡ ባይገርማችሁ ከቤቴ መንገድ በተቃራኒው ይህቺን ባለ ቀይ ቂጥ ሴትዬ ተከትዬ ለ24 ደቂቃ ተጉዤያለሁ፡፡

‹‹ምትገርም ልጅ ነህ ..ለማንኛውም የምሄድበት ቦታ ደርሼያለሁ በዚህ ነው የምጠመዘዘው፡፡ ››

‹‹እንዴ!!! እኔስ?›› አልኳት ደንግጬ፡፡

‹‹አንተ ምን..?ወደምትሄድበት ሂዳ፡፡››

‹‹የምሄደውማ ወደ ቤቴ ነበር …ቅድም እሄድበት በነበረው አቅጣጫ፡፡››

‹‹በል እንግዲህ የቂጥ አምላክን እየረገምክ ቀኝ ኃላ ዙርና ንካው›› አለችኝ፡፡

‹‹ስልክ ቁጥርሽን ስጪኛ?››

‹‹ምን ልታደርገው?››

‹‹በቃ እንዲሁ፡፡››

‹‹ባለትዳር ብሆንስ?››የማልመልሰውን ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ሁኚያ..እኔ እንዲሁ ነው የፈለኩት አልኩሽ እኮ፡፡›› እንዲሁ መፈለግ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ብትጠይቀኝ ግን መልስ አልነበረኝም፡፡

‹‹ሁላችሁም ወንዶች በመጀመሪያ እንዲሁ ነው የምትፈልጉት በኃላ እንጂ ነገር የምታመጡት፡፡››

‹‹ኸረ እንዲሁ ነው ስጪኝ፡፡››በአሳዛኝ ሁኔታ ተለማመጥኳት፡፡

እያጉረመረመች ሰጠችኝ፡፡ተሰናበተኳትና እንዳለቺኝ ቀኝ ኃላ ዞሬ ወደቤቴ ነካሁት፡፡
ለሊቱን ሙሉ የቂጧ ምስል በህልሜ ሲመላለስ እና ሲያሰቃየኝ አደረ፡፡ ምን ነካኝ ግን ?ፍቅር ሊይዘኝ ይሆን እንዴ? ኸረ አይደረግም…፡፡ ቢያንስ በ10 ዓመት እኮ ትበልጠኛለች፡፡ ግን ይሄ ምን ችግር አለው? ከስድስት ወር በፊት የጠበስኳት ቀሚ ፍቅረኛዬ የሆነችውን ሀይሚን በ10 ዓመት እበልጣት የለ?አንዷን እበልጣታለሁ አንዷ ደግሞ ትበልጠኛለች..በቃ ማቻቻል ማለት እንዲህ ነው፡፡
👍79😁258🔥1🥰1
ደግነቱ በማግስቱ ቅዳሜ ነው፡፡ ቅዳሜ ደግሞ ሀይሚ እቤቴ እንደምትመጣ ቃል ገብታልኛለች፡፡መቼስ እንዲህ ስላችሁ ታድለህ ሁል ጊዜ በሳምንቱ መጨረሻ የረፍት ቀንህን እየጠበቀች ፍቅረኛህ እቤትህ ስለምትመጣልህ በደስታ አለምህን ትቀጫለህ ብላችሁ አስባችሁ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን በጣም..በጣም ተሳስታችኋል ፡፡ አይደለም በሳምንት ልትመጣ በስድስት ወር የፍቅረኝነት ጉዞችን ካፌ እንኳን አስቀምጬ ለመጋበዝ ከእሷ ፍቃድ ያገኘሁት ከ3 ቀን   ለማይበልጡ ቃናቶች ብቻ ነው፡፡… በቃ ፍቅራችን በአብዛኛው በስልክ ነው…. በሚሴጅ እና በቻት….ቀላል ሞዛዛ መሰለቻችሁ..፡፡

..ይሄ የእሷ ባህሪ ግን አንድ ወሳኝ ጥቅም አለው መሰለኝ፡፡ ወጪ በመቆጠብ… ፡፡የእኔ ጓደኞች በሳምንት አንድ ቀን ፍቅረኛቻቸውን ለመጋበዝ በሳምንት 3 ቀን ምሳ እንደሚዘሉ አውቃለሁ፡፡ ካለ በለዚያማ ያቺ ሚጢጢዬ ከመንግስት ሚወረውርላቸው ደሞዝ ተብዬ ክፍያ እንዴት ትበቃቸዋለች..?ውይ እረስቼው፡፡እኔም ለካ ሀይሚን በመጋበዝ ምንም የማወጣው ወጪ ባይኖርብኝም በወር አንድ ቀን ደሞዝ በምቀበልበት ሰሞን እንትን ስለሚያምረኝ..ሀይሚም እሺ ብላ ስለማትሰጠኝ ግዢ ወጣለው፡፡
የዛን ቀን ታዲያ የደሞዜን ግማሽ አስረክቤ እመለሳለው፡፡ ይሄኔ አመንዝራ..ባለጌ …ፍቅረኛ እያለህ.. ኃጥያት አይደለም? ብላችሁ በሆዳችሁ አምታችሁኝ ይሆናል? ታዲያ ምን እንዳደርግ ትጠብቃላችሁ ?ፍቅረኛ ቢኖረኝ እምቢኝ ካለችኝ በግድ አልደፍራት፡፡ሀይሚ እኮ ማለት ምግብ ቤት ግድግዳ ላይ ተለጥፎ የሚታይ የፍራፍሬ ፖስተር ማለት ነች፡፡ለማስጐምዠት አገልግሎት ብቻ የተፈጠረች፡፡ አስገድጄ …ብፈልግስ የት አግኝቼት… ?መንገድ ላይ አላደርገው፡፡ እሷ እንደሆነ ከእኔ ጋር በባዶ ቤት ላለመገናኘት የምታደርገው ጥረት ልነግራችሁ አልችልም፡፡ጥሩነቱ የእሷም ሰበብ እንደአለማለቁ የእኔም ትዕግስት አያልቅም.፡፡.እወዳታለሁ…፡፡ በጣም ነው የማፈቅራት፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose


የጣት ቁስልድርሰት #በአብርሃም_ቃሉ በቀጣይ የማቀርበው ድርሰት ይሄ አሁን የጀመርነው አጭር ታሪክ ሲያልቅ መልካም ምሽት



ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍608😱2
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_ሁለት


#ድርስት_በዘሪሁን
==========================
ቢሆንም ቅንዝሬ ያው ቅንዝር ነውና ጆሮው የተደፈነ ነው፤የእኔ እና የእሷን ምክንያት አያዳምጥም ፡፡ስለዚህ እመክረው እመክረውና…ከዛም ደግሞ እለምነው እለምነው እና በቃ ከአቅሜ በላይ ሲሆን  እንደነርኳችሁ በወር አንዴ በደሞዝ ሰሞን ወደ አብረቅራቂ መብራት ወደሚንቦገባግባቸው የለሊት ቤቶች ጐራ እላለሁ ፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን ልቤ ለሀይሚ እንዳላዘነ ነው፡፡ዛሬ ግን እፎይ ልገላገል ነው ፡፡ሀይሚ እቤት ለመምጣት ከስድስት አታካች ወራቶች ጭቅጭቅ በኋላ ተስማምታለች፡፡ከቀኑ 8 ሰዓት ነው የምትመጣው፡፡እኔ ግን ከእንቅልፍ የባነንኩት ከለሊቱ 8 ሰዓት ነው፡፡ለዝግጅት፡፡እውነቴን ነው እኮ ፡፡ገና እቤት ማዘጋጀት አለ፣ዕቃ ማጣጠብ አለ፣አልጋ በስርአት ማንጠፍ አለ፣ለፍቅራችን ማጀቢያ ሙዚቃ መምረጥ አለ፣ደግሞ እኔም እንድደፍራት እሷም እንድትደፈርልኝ የሚያግዝ መጠጥ ማዘጋጀት አለ፣አረ ስንቱ….፡፡

ደግሞ አይገርማችሁም ዛሬ ሀይሚ ቤት ልትመጣ ትናንትና ቂጣሟን ማግኘቴ….፡፡ ማግኘቴ ብቻ ሳይሆን እቤቷ ድረስ መከተሌ..ከዛም አልፎ ስልክ ቁጥሯን መቀበሌ..፡፡አሁን ልደውልላት እንዴ….? የሚል ሀሳብ መጣብኝ ፡፡መልሼ ሀሳቤን ውድቅ አደረግኩት ::ለሀይሚ ያለኝን ታማኝነት ዝቅ ማድረግ ነው:: አይደለም መደወል …ቢቻል በምናቤ ተንጠልጥሎ አልወርድ ያለኝን የቂጧን ምስል አሽቀንጥሬ መጣል ብችል ደስ ይለኝ ነበር፡፡እንደቀጠሯችን ምንም ሳታረፍድ ከቀኑ 9 ሰዓት ሀይሚ መጣች..ያው አንድ ሰዓት ዘገየች ማለት አረፈደች ተብሎ መደምደም የለባትም ብዬ ነው፡፡ አለባበሷን ልግለጽላችሁ፣ቡትስ ጫማ፣ጥብቅ ያለ ጅንስ ሱሪ፣በሱሪው ላይ ቁርጭምጭሚቷ ጋር የሚጠጋ ቀሚስ፣በቀሚሱ ውስጥ ደግሞ ሱሪዋ በቀበቶ የተጠፈረ መሆኑን በሚታየው የቀበቶ ቅርፅ ማወቅ ይቻላል፣ከላይ ደግሞ ግብዳ ሹራብ ደርባለች፡፡
ጉንጯን እያገላበጥኩ እየሳምኩ ቢሆንም አይኖቼን ግን ሰማዩ ላይ አንጋጥጬ እያንከራተትኩ ነው፡፡ሀሞቴ ፍስስ ነው ያለው፡፡አሁን እሺ ብላ እንድናደርግ ፍቃዱን ብትሰጠኝ ..ይሄን ጫማዋን ፈትቼ እስካወልቅ አንድ ሰዓት፣ሱሪዋን እስካወልቅ ሌላ አንድ ሰዓት፣ምን አልባት ከሱሪዋ ስር ታይት፣ከታይቱ ስር ደግሞ ሁለት ወይም ሶስት ፓንት ታጥቃ ሊሆን ይችላል..? ታዲያ መሽቶ ነጋ ማለት አይደል?፡፡

ወደ ቤት ዘልቃ ቁጭ አለች፡፡ቁጭ አባባሏ እራሱ ሲያበሳጭ፡፡ ከጓዲያ ወጥቶ ማጅራቷን አንቆ የሚውጣት ዳይኖሰር ያለ ይመስል በራፉ ጥግ የሚገኝ ኩርሲ ላይ ተቀመጠች፡፡ፈርጥጣ ለመውጣት እንዲያመቻት ይመስለኛል፡፡ ደግሞ እሷ ብቻ ሳትሆን እኔም አበሳጫለሁ ፤ ምን አለበት ከመምጣቷ በፊት እቤቴ ያሉትን መቀመጫቸው ሁሉ ሰብስቤ ጓዲያ አስገብቼ ቢሆን ኖሮ ምርጫ ስታጣ አልጋ ላይ መቀመጧ አይቀርም ነበር፡፡

‹‹ሀይሚ ..ምነው በራፍ ላይ….. ?አልጋው አይሻልሽም…?››

‹‹አይ መጣለሁ  ብዬህ እንዳልቀር ነው እንጂ …እሄዳለሁ፡፡››

‹‹ወዴት?››

‹‹ወደቤት ነዋ…እናቴ ስራ አዛኝ ነበር ….ተደብቄ ነው የመጣሁት››ብላኝ እርፍ፡፡

ይታያችሁ ሰው አሁን ይህቺን ያፈቅራል...?ከለሊቱ 8 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ፍዳዬን ስበላ ቆይቼ እሷ ግን ገና መጥታ ሳትጨርስ ልሄድ ነው ትላለች፡፡ቀኑን ሙሉ እሷን እያሰበ ሲወጣጠር የዋለውን እንትኔ ወዲያው ልፍስፍስ ብሎ ሲሸበለል ይታወቀኛል፡፡ችላ አልኳት እና ወደ ጓዲያ ገብቼ የሰራሁትን ምግብ በማምጣት ጠረጴዛ ላይ ደረደርኩት፡፡ ወይኑንም አወጣሁ..አሁን የምግብ ጠረጰዛው አልጋውን ተጠግቶ ስለሚገኝ ምርጫ የላትም መጥታ አልጋው ላይ ከጐኔ መቀመጧ አይቀርም ፡፡

‹‹ሀይሚ ነይ ምሳ እንብላ ፣እርቦኛል..እስከአሁን እኮ አንቺን ስጠብቅ አልበላሁም፡፡››

‹‹እኔ እኮ በልቼያለሁ፡፡››አቤት ወሽመጥ ስትቆርጥ፡፡

‹‹ባክሽ አታበሳጪኝ..በስንት ጣጣ  መጥተሸ ደግሞ..?›› ተኮሳተርኩ፡፡ እንደመደንገጥ አለችና መጣች፡፡ እንዴት መጣች አትሉኝም…? ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት ከአልጋው ራቅ ብላ ተቀመጠች፡፡ ምርጫ አልነበረኝም፤ እጇን አስታጠብኳት ፤ወይኑን ስቀዳ‹‹ለእኔ እንዳትቀዳልኝ››አለችኝ እየተንዘረዘረች፡፡ መርዝ ልቀዳላት የተዘጋጀው አስመሰለችው፡፡

‹‹አንድ ብርጭቆ ብቻ››ተለማመጥኳት፡፡
‹‹አንድ መለኪያም አልጠጣም..እንድበላ ከፈለክ በውሃ ቀይርልኝ…›› ለወራት ተጨንቆ የቀየሰው የጦርነት እስትራቴጂ ፍርክስክሱ እንደወጣበት የጦር ጄኔራል ሞራሌ ድቅቅ አለበኝ፡፡ለንቦጬን ጣልኩ …ያለችውን አደርግኩ፡፡

እየተጐራረስን በፀጥታ በልተን ጨረስን፡፡እኔ የእሷንም ፋንታ የምጠጣ ይመስል እንደውሃ እጋተው ጀመር ፡፡ እንደጨረስን የተበላበትን ዕቃ አነሳሳሁ..እጇን አስታጠብኳት እና እኔም ታጥቤ  ወደ ቦታዬ ተመለስኩ፡፡

ልክ ምሳዋን ለመብላት የመጣች ይመስል…‹‹ልሂድ በቃ፡፡›› አለችኝ፡፡

‹‹ቆይ ማውራት አለብን፡፡››

‹‹ምንድነው የምናወራው?››

‹‹ስለፍቅራችን ነዋ፡፡ ››

እንደመደንገጥ ብላ‹‹ፍቅራችን ምን ሆነ ?››አለችኝ፡፡

‹‹እስከአሁን ምንም አልሆነ …ካላወራንበት እና መፍትሄ ካላበጀንለት ግን መሆኑ አይቀርም.››ወይኑን በደረቁ እየለጋሁት ስለሆነ በድፍረት የመናገር ወኔዬ ሙሉ ነው፡፡

‹‹እሺ ፈጠን በልና እናውራበት››

‹‹ታፈቅሪኛለሽ?››

ግራ በመጋባት‹‹ምን ማለት ነው?››

‹‹ታፈቅሪኛለሽ ወይ?››ደግሜ ጠየቅኳት፡፡  

‹‹በጣም አፈቅርሀለሁ፡፡››
  ‹‹ካፈቀርሺኝ …ዛሬ ፍቅር እንድንሰራ እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹ፍቅር እየሰራን አይደል እንዴ?››

‹‹እንደ እሱ አይደለም..ልብስሽን አወላልቀሽ..እኔም ልብሴን አውልቄ… እዚህ አልጋ ላይ ወጥተን ምናምን ማለቴ ነው… በጣም አምሮኛል…ስንት ወር ነው የምሰቃየው…?››ብሶቴን ተረተርኩት፡፡

‹‹እሱማ አይሆንም፡፡››

‹‹ለምን አይሆንም?››

‹‹አፈቅርሀለሁ… ግን ጊዜው አሁን አይደለም…ገና 18 ዓመት እኮ አልሞላኝም፡፡ በዛ ላይ የሃይእስኩል ትምህርቴንም አልጨረስኩም፡፡››

‹‹ስንት ዓመትሽ ነው?››

‹‹17 ዓመት ከ11 ወር…››

‹‹እና ታዲያ ሰው ለሚወደው እንኳን አንድ ወር ይቅርና አንድ ዓመትስ ቢያጭበረብር ምን አለበት?››

‹‹እንደ እናቴ መሆን አልፈልግም፡፡››

‹‹እንዴት እንደ እናትሽ?››

‹‹እሷም 10ኛ ክፍል እያለች ነው እኔን ያረገዘችው፡፡በዛ የተነሳ ትምህርቷን አቋርጣ ብዙ ስቃይ ተሰቃይታለች፡፡ ብዙ ብዙ መከራ ካሳለፍን በኋላ ነው በቅርቡ ህይወታችን የተስተካከለው፡፡››

‹‹እኔ እኮ ብታረግዢም አፈቅርሻለሁ..ማለቴ አገባሻለሁ፡፡››

‹‹አባቴም እሷን እንደዛ ነበር የሚላት…፡፡የእውነት እንዳረገዘች ስትነግረው ግን የራስሽ ጉዳይ ነበር ያላት፡፡››

‹‹እሺ በቃ በኮንዶም እንጠቀም..ህይወት ትረስት፣ሴንሴሽን፣ሜምበርስ ኦንሊ… የፈለግሽው አይነት አለ፡፡››

‹‹እንዴ ዲኬት ነው እንዴ የምትሰራው…? ይሄ ሁሉ ኮንደም ምን ልታደርግ ሰበሰብከው…?››ያላሰብኩትን መስቀለኛ ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ባክሽ አንድ ዲኬት የሚሰራ ጓደኛዬ ነው አምጥቶ ለማንኛውም እያለ ቤቴ የሚያስቀምጠው፡፡››

‹‹ጥሩ…. ግን ድንግል ነኝ… ድንግልናዬን ደግሞ በኮንደም አላስወስደውም፡፡››

‹‹እኔ እኮ ድንግልናውን አልፈልገውም..፡፡››
‹‹……እና አውልቄ ላስቀምጠውና ተጠቅመህ ከጨረስክ በኃላ መልሼ ላጥልቀው?››ንግግሯ ከማበሳጨትም አልፎ አሳቀኝ፡፡

‹‹እና ምንድነው መፍትሄው?››

‹‹ምታፈቅርኝ ከሆነ ጠብቀኝ?››
‹‹እሱማ አፈቅርሻለሁ፡፡››
👍865👏2👎1
‹‹ጐሽ ስለዚህ ትጠብቀኛለህ ማለት ነው…?›› ብላ ከመቀመጫዋ ተነስታ በስሱ እና በስስት ከንፈሬን ስማ እንድሸኛት ጠየቀችኝ፡፡እኔም እንዳለቺኝ አደረግኩ፡፡በቃ ተመለስ እስክትለኝ ድረስ ሸኘኋት…፡፡ተመለስኩና የቀረውን ወይን በንዴት መጠጥኩት..ምጥጥ አድርጌ ሳጠናቅቅ 12 ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡አልጠገብኩም… ፡፡ቤቴን ዘግቼ ወጣሁና ሰፈራችን ከሚገኘው ግሮሰሪው ተሰየምኩ፡፡ቢራ አዘዝኩ ፡፡ሁለት ሰዓት ሲሆን ጥግብ አልኩ..ጥግብ አልኩና ስልኬን በማውጣት ደወልኩ.. ባለቀይ ቂጥ   ባለቤቷ ጋር፡፡

‹‹ሄሎ፡፡››

‹‹ሄሎ ማን ልበል?››

‹‹የምን ማን ልበል ነው… ? ምንድነው ምትረብሺኝ፡፡››አንቧረቅኩባት፡፡

‹‹ይቅርታ የተሳሳትክ መሰለኝ፡፡››

‹‹አልተሳሳትኩም ባክሽ፡፡››

‹‹እና አላወቅኩህማ፡፡››

‹‹እኔም እኮ አላውቅሽም..ቂጥሽን ግን… ወይ ቂጥ›› 

ሳቋን አንጣረረችው‹‹አንተ ጉደኛ..አንተው ነህ?››

‹‹አዎ እኔው ነኝ..ፈፅሞ ልረሳው እኮ አልቻልኩም፡፡››

‹‹እሱማ እኔም ደግመህ እያየኸኝ እየመሰለኝ አስሬ እየተገላመጥኩ  ኃላ ኃላዬን ሳይ ነው የዋልኩት.. አሳቀቅከኝ፡፡››
‹‹አትይኝም..ታዲያ ደግመሽ ለምን አታሳይኝም?››

‹‹ኸረ ባክህ!!! ደግመህ ማየትም ያምርሀል..?በትክክል ድጋሚ ማየት ፈልገህ ቢሆን ኖሮማ ቀን ትደውልልኝ ነበር፡፡›› አለችኝ፡፡ ምን ታድርግ… ቀኑን በእንዴት አይነት መከራ ውስጥ እንዳሳለፍኩ አታውቅም….ሀይሚን በእጄ ይዤ እንዴት እሷ ጋር ልደውል አቅም ይኖረኝል፡፡ አሁንም ሀይሚ የጋተችኝ ንዴት እና በገዛ እጄ የተጋትኩት መጠጥ ናቸው ተባብረው ድፍረቱን የሰጡኝ፡፡ አይገርምም ግን ሀይሚና ይህቺ ባለቀይ ቂጧ ያላቸው  ልዩነት..ፍጹም ተቃራኒ ናቸው፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose



ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት..ይመቻቹ

ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
😁27👍206👎2
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን

====================
‹‹ካሰብሽበት አሁንም ቀን ነው፡፡››
‹‹አንተ ቤተሰብ ያለኝ ሰው እኮ ነኝ፡፡››
‹‹አንቺ እሺ ይኑርሽ.. ያደነዘዘኝን ቂጥሽን ግን ላኪልኝ፡፡››መቼስ የምላሴ ፍሬኔ ብጥስጥስ ብሎብኛል፡፡
‹‹ናና ውሰደዋ፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ፡፡››
‹‹እውነትህን ነው?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው..ትናንት የተለያየንበት ቦታ ስደርስ ደውልልሻለሁ››
‹‹ያ እኮ ሰፈሬ አይደለም ብላ …የእሷን ትክክለኛ ሰፈር በምልክት ነገረችኝ.. ሂሳብ እንዴት እንደከፈልኩ.. እንዴት ተንደርድሬ ሰፈሯ እንደደረስኩ አላውቅም..ግን ስደውልላት ባሏ ተከትሏት ቢወጣስ..?የራሱ ጉዳይ ‹‹የቆመበት የቆመ ነገር አያይም››ይባል የለ፡፡ ደወልኩላት… ከአምስት ደቂቃ በኃላ መጣች፡፡ጨለማ ውስጥ ሆኜ ያለሁበትን ቦታ በእጅ ምልክት ጠቆምኳት..መጣች፡፡
‹‹አንተ ጉደኛ!!!››
በቃላት መልስ ከመመለሴ በፊት ጐተትኩና ከሰውነቴ አጣብቄያት ከንፈሯን ገመጥኳት ፡፡የሀይሚን እልክ በእሷ እየተወጣሁ ያለው መሰለኝ፤ በግድ ነው ያስለቀቀቺኝ‹‹አንተ ሰፈሬ እኮ ነው ያለሁት…ሰው ቢያየኝስ?››አለችኝ፡፡ ንግግሯ ደስ አሰኘኝ…ሰፈሯ ባይሆን ኖሮ በመሳሟ ደስተኛ ነች ማለት ነው፡፡
‹‹ባክሽ ጭለማ ውስጥ ነው ያለነው..ማንም አያይሽም፡፡››
‹‹ወይኔ ጉዴ!!!››አለች ድንገት ራሷን ይዛ እየተርበተበተች፡፡
‹‹ምነው….?ምን ሆንሽ…?›.
‹‹ባሌ መጣ …ባሌ፡፡››
በድንጋጤ ተሸቀንጥሬ ጨለማ ውስጥ ተሸገጥኩ፤እሷ በቆመችበት ሆና በሳቅ ፍርስ አለች‹‹ሲያዩህ ጀግና ትመስላለህ››
ከተወሸቅኩበት ወጣሁና ወደ እሷ በእርጋታ እየቀረብኩ ‹‹ጀግናማ ጀግና ነኝ ላንቺ ደህንነት አስቤ አስጂ..፡፡››
‹‹እሱን እንኳን ተወው..ጀግና አናውቅም እንዴ?››
‹‹ግን ባልሽ እቤት ነው?››
‹‹ባሌ እቤት ቢኖር..እንዲህ አጥር ስር አስደግፌህ አዋራሀለው፡፡››
‹‹ጥሩ አጋጣሚ ነው ፊልድ ሄዶል ማለት ነው››..አንገቷን ወደ መሬት ደፍታ ዝም አለች፡፡ግራ ገባኝ‹‹ምነው ያልኩሽን ሰምተሸል?››
‹‹አዎ ባሌ የሞተብኝ በቅርብ ነው፡፡ ሰሞኑን ነው ጥቁሩን የሀዘን ልብሴን ያወለቅኩት ››ደነገጥኩ፡፡የተደፈነ ልብ ሸሽቼ ስመጣ የተሸነቆረ ልብ ገጠመኝ እንዴ..?
‹‹ይቅርታ›› ብዬ ዳግመኛ ወደ ሰውነቴ አጣበቅኳትና ከንፈሯ ላይ ተጣበቅኩ፡፡እጄ ትናንትና ያደነዘዘኝ ቂጦ ላይ አርፎል… ቃተተች፡፡ እንደምንም ተላቀቀቺኝና ‹‹እዚሁ ብትንትኔን አወጣኸው እኮ..በዛ ላይ ረሀብተኛ ነኝ፡፡››
‹‹እኔም ጠኔ ሊጥለኝ ትንሽ ነው የቀረኝ፡፡በቃ ይዘሺኝ ወደ ቤት ግቢያ..››
‹‹ወዴት?››
‹‹ወዳንቺ ቤት ነዋ፡፡››
‹‹እንዴ ልጄ እኮ አለች..በዛ ላይ ሰራተኛዋም….››
‹‹እሺ የሆነ ሰበብ ፍጠሪና ወደ እኔ ቤት ወይም ወደፈለግሽበት ሌላ  ቦታ ይዤሽ ልሂድ፡፡››
‹‹እሱማ አይቻልም..ውጭ ለማደር ምንም የምሰጠው ምክንያት የለኝም..ይልቅ ደፋር ከሆንክ አንድ ሀሳብ አለኝ፡፡››
‹‹ኸረ አፄ ቴዎድሮስ አጐቴ ነው… ጀግንነቱ ከደማችን ነው ሚንጠባጠበው፡፡››
‹‹ከ3-4 ሰዓት ባለው ጊዜ ይተኛሉ ..መኝታ ቤቴ ለብቻዬ ስለሆነ ስደውልልህ ትመጣና ትገባለህ..ታዲያ ለሊት 11 ሰዓት ወጥተህ ለመሄድ ከተስማማህ ነው ?››
ጥብቅ ብዬባት ሳምኳት እና ‹‹ቂጥሽ ብቻ ሳይሆን ልብሽም ቀይ ነው..ተስማምቼያለሁ፡፡››
‹‹ታዲያ እስከዛ የት ትቆያለህ?››
‹‹ችግር የለውም..ወደኃላ ተመልሼ በቅርብ የሚገኝ አንዱ ቡና ቤት አመሻለሁ… ስለ እሱ አታስቢ አንቺ ብቻ እንዳልሺው አድርጊ፡፡››
‹‹ችግር የለውም …አሁን ግን ሱቅ ዕቃ ልግዛ ብዬ ስለወጣሁ  መመለስ አለብኝ፡፡››
‹‹ታዲያ የገዛሽው ዕቃ የታል?››
‹‹አጣኋ…ባለሱቆቹ የለንም ጨርሰናል አሉኝ፡፡›› ብላ ጉንጬን በስሱ ስማኝ እየፈገገች ወደ ግቢዋ ተመልሳ ገባች፡፡››
አቤት የሰው ልጅ ልዩነት ድሮም ከህፃን ጋር መከራዬን ሳይ መኖሬ እንዲህ ትናንት ተዋውቆ ለዛሬ ብን ማለት እያለ ስድስት ወር ሙሉ  ስዳክር መኖሬ..አምኜ ወደ ኃላ ልመለስ አልቻልኩም፡፡እንዴ የሆነ ነገር ቢያጋጥመኝስ..? ድንገት ሳልሰማ ጉልበተኛው መንግስታችን ሰዓት እላፊ አውጆ ቢሆንስ…?ድንገት ዘራፊዎች ሞባይሌን ቢመነትፉኝስ በምን ደውዬ አገኛታለሁ…?ኸረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን እንጂ በእንደዚህ አይነቱ ቀን ድንገት የሚፈጠር ስንት አደናቃፊ ነገር አለ መሰላችሁ፡፡ለሀይሚ ተብዬዋ እንኳን ያን ሁሉ ሰዓት በባዷ አባክኜ የለ…ያደረግኩት አንድ ነገር ቢኖር እዛው ፊት ለፊቴ ካለች አንድ ትንሽ ኪወክስ ሄጄ ጭንብል መሸመት ነው፡፡ሶስት እሽግ ህይወት ትርስት..ሶስት እሽግ ሰንሴሽን ሸመትኩና በእያንዳንዱ ኪሴ ሁለት ሁለት በታትኜ ከተትኩ፡፡
አንድ ወንዳ ወንድ የሆነች የሱቁ ሻጭ‹‹ምነው የወር ቀለብ ነው እንዴ?›› አለቺኝ፡፡
‹‹ምነው ችግር አለው?››
‹‹ለምን ችግር የለውም ፡፡ ሆነ ብለህ ምርትን ከተገቢው በላይ በማከማቸት የዋጋ ንረት ለመፍጠር አስበህ ቢሆንስ?››
‹‹አይዞሽ አትስጊ ከተረፈኝ ጥዋት መልስልሻለው ›› አልኳት እና መልሼ ጨለማዬ ውስጥ ተወሸቅኩ፡፡3፤15 ሲሆን ተደወለ.. ባለቂጧ መስላኝ ተንደርድሬ አፈፍ አድርጌ አነሳሁና‹‹እሺ ተኙልሽ››
‹‹አዎ ልተኛ ነው››አለችኝ፡፡አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ.. ከራማዬ ነው ቡን ያለው፡፡ ሀይሚ ነበረች ደዋዮ፡፡አሁን በዚህ አሳሳች ሰዓት  ማን ደውይ አላት?
‹‹ሄሎ ምነው ዝም አልከኝ፤አኩርፈኸል እንዴ?››
‹‹አይ ለምን አኮርፍሻለሁ?››
‹‹ደግሞ ውጭ ነው እንዴ ያለኸው...፡፡ንፋስ ነገር ይሰማኛል›› ብላኝ ቁጭ፡፡ሁሉም ሴቶች ከጥንቆላ መንፈስ የተገነባ ስድስተኛ የስሜት ህዋሳት አላቸው…፡፡ይሄ ጉዳይ ሁሌ ይገርመኛል፡፡ከሆነች ሴት ጋር አፍ ለአፍ ገጥመህ ስታወራ…ወይንም የሆነች ሴት ልትስም አፍህን አሞጥሙጠህ ወደ ፊት መጓዝ ስትጀምር..ወይ ለአንዴ ልስረቅ ብለህ ሱሪህን በማውለቅ ላይ ሳለህ…ስልካቸው ጭርርርርርር ይልብህና ያሳቅቅሀል፡፡
‹‹ባክሽ ደብሮኝ እቤቴ በረንዳ ላይ ቁጭ ብዬ ከዋክብት እየቆጠርኩ ነው››
‹‹አውቄያለሁ ደብሮሀል ማለት ነው..?ግን ለቀኑ ነገር ተረድተኸኛል አይደል…?››ለዚህ ጥያቄዋ መልስ ከመመለሴ በፊት ሌላ ስልክ ዌይቲንግ ገባብኝ..ቂጣሟ ነች፡፡
‹‹በጣም ነው የተረዳሁሽ የእኔ ፍቅር፡፡አሁን ግን ሀለቃዬ እየደወለልኝ ነው..ላናግረውና መልሼ ደውልልሻለሁ፡፡››
‹‹አይ አያስፈልግም ፍቅር ..ልተኛ ስለሆነ ደህና እደር… ነገ ትደውልልኛለህ..ደግሞ አፈቅርሀለው እሺ፡፡››አለችኘ፡፡
‹‹እኔም አፈቅርሻለሁ፡፡›› አልኩና ዘጋሁት ..አያችሁልኝ አይደል፡፡‹‹አፈቅርሀለሁ፡፡››ብላኝ እኮ አታውቅም፡፡ሁልጊዜ ከስልክ ልውጥ  በኃላ ‹‹አፈቅርሻለሁ›› ስላት ‹‹እኔም›› ብላ ነው ምታሳርገው፡፡ ዛሬ ግን እኔን ለማሳቀቅ እና በአእምሮዬ ፀፀት ለመርጨት ሆነ ብላ አቅዳ እና አልማ ‹‹አፈቅርሀለሁ›› አለችኝ፡፡..ሞኟን ትፈልግ …በዚህ ሰዓት ለእሷ ንግግርም ሆነ ለአዕምሮዬ ፊት አልሰጣቸውም፡፡….
የቂጣሟን ስልክ አነሳውት…..‹‹ሄሎ››
‹‹ና በቃ … በራፍ ላይ ስትደርስ ደውልልኝ››
‹‹በመጀመሪያውስ ከበራፍሽ መች ተንቀሳቀስኩ››
‹‹እስከአሁን እዛው ነኝ እንዳትለኝ?››
‹‹አልኩሽ..ከስልክ እንጨቱ ጋር ተጣብቄልሻለሁ፡፡››
‹‹እውነትም ቀንዝሮብሀል..እሺ መጣሁ ››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡የውጩ በራፍ ተከፈተ፤ ጐትታ ወደ ውስጥ አስገባችና መልሳ ዘጋችው፡፡በግቢው ሆነ በቤታቸው ምንም አይነት መብራት አይታይም፡፡‹‹ምነው መብራ ተቆርጦባችሁ ነው?››በሹክሹክታ ጠየቅኳት፡፡
👍778😁2