አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
467 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ

ከሎ ሆራ ልቡን የሰረቀችውን የሐመር ውብ ለማግኘት ብዙ መድከሙ
አልቀረም።ካርለትም ብትሆን የሐሳቡን መናወጥ
ስላጤነችና ለጥናቷም እገዛ ይኖረዋል ከሚል እምነት በመነሣት ያችን ውብ ኮረዳ ማፈላለጉ ላይ አልሰነፈችም ሻንቆና ላላ መንደር
አለመኖሯን ግን ሁለቱም በየፊናቸው አረጋግጠዋል።

እንደ ተለመደው ከሎ ሆራና ካረለት በየመንደሩ በመዞር
ለማጠናከር ሲንቀሳቀሱ፣ ከዲመካ ከተማ ወደ አምስት ኪሎ ሜትር
እራቅ ብላ ከምትገኘው ኮረብታማ መንደር ወሮ ሄዱ"ከዚያ እንደ ደረሱ ወንዶች ወደ ወንዝ፣ ሴቶችም እርሻና ማሳ ጥበቃ ሄደው ስለነበር፣ መንደሯ ውስጥ ያገኙት የሚያላዝኑ ውሾችንና አሮጊቶች
ብቻ ነበር። መሸትሸት ሲል ግን ከብትና ኗሪው ከየውሎው ወደ
መንደሯ መጠረቃቀም ጀመረ።

ይህ ትዕይንት ለካርለት እንግዳ አልነበረምና ከመንደሯ ወጣ ብለው የአካባቢውን ውበት ሲቃኙ፣ ከሎ ደንገጥ ብሎ ዓይኑን ወደ አንድ አቀጣጫ ደገነ" አንዲት ልጃገረድ ስታርስበት የዋለችበትን ሞፈርና ቀንበር ከበሬዎች ጫንቃ ስታላቅቅ፣ ከበስተኋላ ተመለከቱ"።
እግርቿ ግጥም፣ ዳሌዎ ኮራ ከወገቧ ሰርጎድ ያለችውን ኮረዳ ሁለቱም ከበስተኋላዋ በማየት ብቻ ማንነቷን አወቁ" ልጅቷ በሬዎቹን
ፈትታ ዘወር ስትል፣ ሁለቱም ዓይናቸው እሷ ላይ ነው" ኮረዳዋ አንዳችም የመደነጋገር ሁኔታ ሳታሳይ ፈገግ ብላ በዚያ ኰራ ባለው አረማመዷ ወደነሱ ሄደች"።

ከሎ ምራቁን ቶሎ ቶሎ ከማንጐራጐጭ በስተቀር የሚመለከተው ልጅቷን ነው" ካርለት ደግሞ በተመስጦ የምትከታተለው እሱን ነው"

በልጅነቷ ወንድና ሴት ተቃቅፈው አልጋ ላይ ሲተኙ የሚያደርጉትን ለማወቅና ብዙ ጊዜ ለማየት ትጓጓ ነበር" ነፍስ ካወቀች
ጊዜ ጀምሮ የምትተኛው በግል መኝታ ቤቷ ሲሆን፣ አንድ ቀን ታዲያ የናቷ ጓደኛና ባሏ በእንግድነት እቤታቸው ይመጣሉ" እንዳጋጣሚ ሆኖ ለእንግዳ የተዘጋጀው የመኝታ ከፍል ተይዞ ስለነበር እንግዶች
ካርለት መኝታ ክፍል እንዲያድሩ ተደረጉ፣ እሷ ከወላጆቿ መኝታ ቤት ካለው ትንሽ ክፍል እንድትተኛ ይደረጋል" ካርለት ግን
እንቅልፍ ከመተኛት ይልቅ አንድ ለብዙ ጊዜ ለማወቅ ትጓጓ የነበረውን ሁኔታ ለመፈጸም አሰበች" እናም፣ የቆየ የልጅነት ፍላጎቷን ለማሟላት እንግዶች እሷ ከምትተኛበት ክፍል ገብተው ከመተኛታቸው በፊት አልጋው ሥር ገብታ ተደበቀች" ባልና ሚስቱ
በመጠጥ ኃይል ሞቅ ብሏቸው ነበርና እየተሣሣቁ ተደጋግፈው ገብተው አልጋ ላይ እንደ ወጡ ተያያዙ"

ካርለት የአልጋ ላይ ጨዋታቸውን ሁሉ ልቅም አድርጋ ሰማች"ከዚያ በኋላ ሰዎቹ ሲተኙ፣ ወላጅ እናቷ ካርለት ከተኛችበት ከፍል
ልታያት ስትገባ ድንግጥ አለች ቀስ አድርጋ እጇን ልጇ አልጋ ላይ ስትጭን ጨርቅ ብቻ ሆነባት በድንጋጤ ጮኸች። አባት፣ እንግዶች
ሳይቀሩ እየተሯሯጡ ሲመጡ የለችም ቤቱ ቢታሰስ፣ ብትፈለግ
በቀላሉ ልትገኝ አልቻለችም" በጨረሻ ግን አልጋ ስር እንደ ውሻ ተጠቅልላ ተገኘች" እና ዛሬም እንደ የዛኔው እንዲታወቅባት
ስላልፈለገች የኮረዳዋንና የከሎን ሁኔታ በጥንቃቄ መከታተል ቀጠለች።

ከሎና ካርለት ከልጅቱ ጋር ፊትና ኋላ ወደ መንደሩ እንደ ደረሱ፣ከልጅቷ መኖሪያ ቤት ትይዩ ድንኳን ለመትከል እንደ ፈለገች ለከሎ
ሆራ ሆነ ብላ አማከረችው «ኢህ» ብሎ ፈቃደኛነቱን ገለጸላት ለነገሩማ እንሂድ ብትለውስ መቼ በጄ ይል ነበር።

ከሎ፣ ስለ ብዙ ነገር እንዳላወጣ እንዳላወረደ አሁን የሚፈልገውና የሚያየው ውብ ልጅ ነው  የሐመሯን ኮረዳ" አጠገቧ
ካለው ድንኳን ውስጥ ሆኖ እሩቅ ያለች ይመስል አለማት" ከሎ ሴት
አያውቅም ለማለት አይቻልም" በተለይ በገንዘብ የሚገኘውን የስሜት እርካታ በሚገባ ያውቀዋል" የሴት ጓደኛም ለመያዝ ብዙ
ሞካሮ ነበር" ግን፣ ከሙሉ ስሜቱ እንዲህ እንደ አሁኑ ነፍሱ ምንጥቅ እስክትል ወዶ አያውቅም"

ልጃገረዷ ደግሞ በሕይወቷ እንደ ወንድ ጓደኛ ግንኙነት
የጠገበችው የለም። ከሚጠይቋት ወንዶች ውስጥ ከመረጠቻቸው ጋር
ብቻ ተዝናንታለችI ዕድሜ ለሐመር ደንና ጫካ።

እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ልጃገረዷ ወላጆቿን በሥራ በመርዳት ስታገለግል ቆይታ ለምሽት ጭፈራው መሰናዳት ጀመረች"የጐረምሶችን ጩኸት እንደ ሰማች ከጓደኞቿ ጋር ለመደነስ ስትሄድ፣እነ ከሎ ተመለከቷት" አባቷ እንዳያገኛት ተጠንቅቃ አለፈች።

ልጃገረድ በኢቫንጋዲ (የምሽት ጭፈራ) መካፈሏን ባህሉ የሚፈቅድ ቢሆንም ወደ ጭፈራ ቦታ ስትሄድ ግን አባትየው ሳያይ
ሲሆን፣ ከጐረምሳ ጋር ስትዳራ ካገኘም አባት ተኵሶ ጐረምሳውን
እስከመግደል ድረስ መብት አለው" ይህ መብት እንጂ ያደርጋል ማለት ግን አይደለም። ስለዚህ፣ ለደንቡ ያህል ጭፈራውም ሆነ
ድሪያው አባት በማያየው መንግድ እንዲሆን ልጃገረዶች የራሳቸውን
ጥናቃቄ ይወስዳሉ"
በአጋጣሚ ግን እሷ ባህሉ ያደገችበት ሆነና ብትጠነቀቅም፣ አባቷ
ግን ከሌሎች የሐመር ወንዶች ለየት ያለ ነው።
በኢቫንጋዲ ጭፈራ ልጃገረዷ ኮከብ ደናሽ ስትሆን፣ የክልሉ ጎረምሶች
በፍቅር ሲያጫውቷትና ወደ ጫካ ሄድ መለስ ስትል ከሎን ግን ለዳንስ ሳትጋብዘው ቀረች። ወደ እኩለ ሌሊት አካባቢ ሲሆን የወንዶች ድምፅ ተሰማ። በመንገድ ላይ የሚያልፉ
ገበያተኞች እግረ መንገዳቸውን ለጭፈራ ሲመጡ የተለመደ ነበርና
ጨዋታው ቀጠለ። ካርለት አሁንም ክትትሏን እንደ ቀጠለች ነው" ጭፈራው ደመቀ፣ ውዝዋዚው ጦፈ፣ ከዚያ የመጨረሻው የዳንስ
ስልት ጊዜ እነ ካርለት የሚከታተሏት ኮረዳ ከአንድ መልከ መልካም ሸበላ ጋር መርፌና ክር ሆኑ ካርለት ያ ሰው ማን እንደሆነ ለመገመት ጊዜ አልፈጀባትም። መጀመሪያ እዳልነበረ እርግጠኛ ነች። ከገበያ ከተመለሱ መንገደኞች ጋር እንደ መጣ አወቀች" ደልቲና ኮረዳዋ
ወደ ጫካው ሲሠወሩ፣ ከሎና ካርለት ተፋጠጡ።

ውቢቷ ልጃገረድ ጎይቲ አንተነህ ትባላለች። በሐመርኛ ጎይቲ ማለት መንገድ ሲሆን፣ የስሟ ትርጓሜ ከመንገደኛ የተወለደች ለማለት ነው" ካርለትና ከሎ የሐመርኛ ቋንቋ አቀላጥፎ የሚናገ
ረውንና በአኗኗሩም ሆነ በአለባበሱ ሐመር የሆነው የጎይቲ ወላጅ አባት ጠዋት ከከብቶች በረት ሲመለስ፣ እንግዶች ከቤቱ ፊት ለፊት
ድንኳን ተክለው አየ አንተነህ (ጋልታምቤ) እንግዶቹን አንዳየ በጨዋ መልክ ሰላምታ ከሰጠ በኋላ፣ ጨዋታ ቢጤ ጀማመሩ።
የመጡበትን ጉዳይና ማንነታቸውን ከገለጸለት በኋላ፣ «ሸፈሮ ቡና
እንጠጣ» ብሎ፣ ወደ ቤቱ ይዟቸው ገባ።

ቡናውን ያፈላችውና የምትቀዳው ውቧ ልጃገረድ ጎይቲ አንተነህ ከአባቷ ፊት በጣም ጨዋና ረጋ ያለች ናት ካርለትና ከሎ በጣም
ጠባብ ወደ ሆነው የጎጆው በር በየተራ ገብተው ከተነጠፈው ቁርበት
ላይ እንደ ተቀመጡ፣ ጎይቲ በሾርቃ ሞልታ ሸፈሮ ቡናውን ለካርለት
አቀበለቻት ቀጥላ ለከሎ ስትሰጠው በአጋጣሚ እሷን እሷን እያየ ነበር እሷ ደግሞ ሾርቃውን የያዘ መስሏት ስትለቅለት ከመሬት
ወርዶ ተሰበረ። ሁለቱም በጣም ደነገጡ" ካርለት ድንገተኛ ሣቅ አፈናት፤ የልጃገረዷ አባትና ሌሎች ሁለቱ ሐመሮች ግን ጸጥ ብለው ሁኔታውን አረጋጉ።

ቡናው የውኃ ጥምን ስለሚከላከል ማንኛውም ሐመር በየመንደሩ
ቡና በእንስራ ተጥዶ፣ ሁለትና ከሁለት በላይ ሾርቃ ሳይጠጣ ከመንደሩ የሚርቅ የለም" አንተነህ ይመር ጎይቲ (ሴት ልጁ) ቡናውን
አጠጥታ ስትጨርስ፣ «ረሃብ፣ ችግር ከሐመር ምድር ይራቅ ከብቶች ይጥገቡ፤ ንቦች አበባ ይቅሰሙ፤ ሰማዩ ውኃ ያውረድ ፍቅር ሰላም ለሐመር ሕዝብ ቦርጆ ያውርድ አንቺም ተባረኪ የተባረh ባልና ትዳር ይስጥሽ፤ ሁላችሁም ተባረኩ» ብሎ ሸፈሮ ቡናውን ወደ አራቱም አቅጣጫና ወደ ጎይቲ፣ «ፕስስ...» አለና አማተበ።
👍171
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሁለት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ


ሰማዩ እንባውን አንዠቅዥቆ ወጣለት: ጀንበር ግን እሷ
እየነደደች ጮራዋን እንደገና በሐመር ተራሮች አሾልካ ፈነጠቀች ዳመናዎችም እንደገና ተበታትነው ለዓመፅ ምክር ይዘዋል  በድጋሚ
ሰማዩን ለማስለቀስ ምድሯን ለማጨቅየት...

ወፎች እጅብ ይሉና ቁልቁል ደሞ ሽቅብ ይጎኑና ቀስ በቀስ ሰማዩ ውስጥ ገብተው ይጠፋሉ።

“እምቡዋ...እምቡዋ… የሚያማምሩትና
ቆዳቸው የሚያብለጨልጨው
እንበሶች ቃጭላቸውን እያቅጨለጨሉ ልብ
በሚበላ ልጅነትን በሚያስታውስ ዜማ ይጣራሉ: ጎይቲ የነሱን
ድምፅ ስትሰማ ተብረከረከች።

የተወለደችው ከጥጃ ጋጥ ጎን የተንቦራቸችው ከነሱ ፍግ ላይ የመቦረቂያ ዜማዋ የነሱ ድምፅ ጣፋጩ የልጃገረድነት ድሪያ
ከነሱ ፊት ... ያ ተመልሰው የማያገኙት የልጅነት ዘመን ያለፈው ከእነሱ ጋር... ጎይቲ ከእንስሳት ሁሉ ጥጆችን ከወንዶች ሁሉ ያን ልቧን እያዳመጠ የሚያባዝታትን ፈትሉ ፍቅር የሚያለብላትን
ነፍሷን በሐሴት የሚያንበሸብሻትን ደልቲን ይናፍቃል::

ሲያቀብጣት ከሐመር ቀዬ ከጭፍራው ቦታ ከተፈጥሮ
መኝታ ቤቷ ከምትንተራሰው የደልቲ ክንድ ርቃ የጨረቃና
ከዋክብት ውበት ከማይታይበት የዱር ፍሬ ለቅመው ከማይበሉበት
የእንስሳት ቡረቃ
ከማይታይበት እየሳቁ እየተጫወቱ
ቡና ከማይጠጣበት. አገር ቆይታ እንደ ውሃ የራባትን የአባቷን ባህል
ደልቲን ለማየት ቀን ተሌት አልማ ስትመጣ ሁሉንም እንደነበረ ስታገኘው ጀግናዋን አጣችው ያኔ የሐመር ጫካ የከስኬ አሸዋ
የቡስካ የአስሌ ተራራ ባዶ ሆነባት::

"...በሉ ተዉኝ! እኔማ ተናግሬያለሁ! ጀግና እድሜ
የለውም የጀግና ልብ ቶሎ ይቀየማል  ጀግናም ምድሪቱን ታፈቅረዋለች መከታነቱን ትፈልገዋለች'  ብዬም አልነበር!
ሳልሰናበተው አያ ደልቲ' ብዬ ስንቅ የሚሆነውን ፍቅሬን ጉያው ውስጥ ሳልወሽቅለት ፍቅሬን በአስተቃቀፌ ጥንካሬ ሳላሳየው ምርቃቱንና የፍቅር ስንቄን ሳልቀበለው ነፍሴን ባስደስታት ደረቱ
ላይ ራሴን ደገፍ ሳላደርግ! ሳብ ገፍተር በሚያደርገኝ ልቡ እንደ ቂጠማ ጎንበስ ቀና ሳልል እሱ አየሩን ሲቀዝፍ እኔ ዳሌዬን
እያሽከረከርኩ ዳንኪራ  ሳልረግጥ አምሮቴ ሳይወጣልኝ የፍቅሩ
ጣዕም ዝንተ ዓለም ከጉሮሮዬ የማይጠፋውን የፍቅሬን ጌታ  ላልሰናበተው.

ጎይቲን ሳግ ተናነቃት አይኖችዋን ከድና ስትከፍታቸው እንባዋ ቁልቁል ወረደ እንደ ምንጭ ውሃ ኮለል ብሎ የጠራ
እውነተኛ ፍቅር የተጠመቀ ንፁህ እንባዋ ጠይም ቆዳዋን እየሸረሸረው ቁልቁል ፈሰሰ

ጎይቲ እንደ ውቅያኖስ ከአድማስ አድማስ የተንጣለለው የፍቅር ዘመን መተንፈሻ አሳጥቶ እንደ ውጋት አስቃተታት: አይኗን
ብትከድን ምድር ምድር ሰማይ ሰማይ ብታይ ለውጥ የለም! ሁሉም ቦታ የሚታያት ጮርቃወ ፍቅሯና የፍቅር ጀግናዋ ነው:
ስለዚህ ጎይቲ መድረሻ ጠፋት:: አንበሳዋ ሐመርን ለቆ ጠፋ ጫካ ውስጥ ሆኖ ማግሣቱን አቆመ፡

“.ኧረ ተቃጠልሁ... ኧረ የት ሆኜ ልጥራህ... አያ ደልቲ
አንተ እኔን ብለህ ለአደን ስትሄድ እኔ በምን አቅሜ መንገዱን ይዤ ጢሻውን ጥሼ ጫካ ልግባ." ጎያቲ ወደ ሐመር ተራራ ወደ ቡስካ ፊቷን አዞራ ጮከች! አያ ደልቲ የት ነህ?... ጥቀሰኝ መፋቂያህን
እንደጎረስህ ጥራኝ... የፍቅር ጦርህን ሰብቀህ የተኛ አካሌን ወጋጋው..." ብላ ወደ ሰማይ አንጋጣ ተጣራች፡ ሰማዩ ግን ድምጿን ዋጠው ደልቲን ዋጠው ፍቅሯን ዋጠው….
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሎ ሆራ በህምታ የምትቆዝመውን ጎይቲ ሲያይ ግራ ገባውና

“ጎይቲ” አላት

"ዩ” አለችው ከንፈሯን እያሸሸች ችምችም ብለው
የሚያንፀባርቁ ጥርሶችዋን እያሳየችው።

.እውነት ይህች ፀባዬ ሸጋ ልጅ የተሸከመችው የውበት
መዓት የኔ ነው? አላት እጁን ትከሻዋ ላይ ደገፍ አድርጎ።" እሷም የእጅ ጣቶቹን በሁለት እጆችዋ እየደባበሰች ቀና ብላ የሚያንፀባርቁ
ጥርሶችዋን እያሳየችው “ይአ!  አሁንማ የሰራ አካላቴ ሁሉ የአንተ ነው የኔ ጌታ!
ከኔ በላይ የኔ ባለቤት ነህ። ከእንግዲህ ከልቤ
የማልበው የፍቅር ወተት የአንተን ጥም ቆራጭ ነው..." ብላ ሐዘን
የተቀላቀለበት ፈገግታዋን አሳየችው።

ከሎ ሆራ! “አሁንማ የስራ አካላቴ በሙሉ የአንተ ነው..." ያለችው አባባል ከነከነው፡ ጎይቲ በዚያ የነፃነት ዘመን በሐመር
ወግና ባህል የእሱ ከመሆኗ በፊት እንደ ንብ እየዘመረች በቀሰመችው የአበባ ዘመኗ በምታደርገው  ድሪያ  የፍቅር ወለላ  እየቀመመች
ጣፋጩን ስሜት በጋራ ልሣ በእርካታ የምትንበሽበሽበት ዘመን እሸቱን ፍቅሯን እያሸች ያቃመችው ስው ሌላ ነው። ከሎም ይህን
በሚገባ ያውቃል በሥልጣኔና በተፈጥሮ ህይወት መካከል
የተከፋፈለው ህሊናው ግን የትናንቱን ድርጊት እንዲሰረዝ አሊያም
እንዲደበቅ ይፈልጋል:
የፍርፋሪ ስልጣኔ ያስተማረው የሚፈልጉትን ለማግኘት ስሜትን በረጋግዶ እጅን መዘርጋት! ችግር ሲያጋጥም ደግሞ እጅን መሰብሰብ! ስሜት ሲያስቸግር መከተል፤ ስሜት እንደ እሳተ ገሞራ
ፈንድቶ ሲፈስ መፈርጠጥ መዋሸት ፊት ማዞር... ስሜትን ከህሊናው መስተጋብር ውጭ ማድረግን ነው ያስተማረው  ከሎን።

ጎይቲ ግን ከሚካል አልባውን የከስኬን ውሃ ጠጥታ ማዳበሪያ ያልነው አፈር ያበቀለውን ማሽላ በቆሎ... በልታ ያደገች
አያት ቅድመ አያቶችዋ በተጓዙበት መንገድ በልበ ሙሉነት የምትራመድ ናትና ትናንትን በትናንትነቱ ዛሬን ደግሞ በዛሬነቱ
በሐቅ መዘከር ትመርጣለች። ስለዚህ በህሊናዋ ጓዳ የተቋጠረውን ትዝታ “አካፍይን" ካሏት ካለ ይሉኝታ እየፈታች ታሳያለች:: ሆኖ ያለፈ የደስታና የሃዘን ትውስታ በውስጧ ተከማችቶ እያስደመማት
እያስቃሰታት... እንዳልሆነ እንዳልነበረ ሁሉ የትናንትን ሁሉ  የትናንትን ትውስታ በምላሷ ጫፍ ለማጥፋት መሞከር ሞቷ ነው፡፡
ቅጥፈት ነውር ነዋ! በአባቷ ባህል።

ከሎ “...አሁንማ...”ብላ የተከዘችበት ምክንያት
አልጠፋውም፡ እንደ ወይን ታሽጎ የተቀመጠና በዋለ በሰነበተ ቁጥር ጣምናው እየጨመረ የሚመጣበት የደልቲ ፍቅር እንደሆነ ያውቃል ግን እንደ አዲስ ይጠይቃታል። ያኔም

“ጎይቲ?” አላት

“ዬ!'' አለችው።

“...አሁንማ የሰራ አካላቴ በሙሉ የአንተ ነው... ያለሽኝ ድሮስ ፍቅርሽን ለማን ነበር አልበሽ የምትሰጭው?” አላት:

“ይእ! ኧረ እዩልኝ! አንተ ሰው'' ብላ ከንፈሯ እየተለጠጠ ሲሸሽ እኒያ በረዶ የመሰሉ ጥርሶችዋ ከፊት ለፊቱ ተገጠገጡና
እንደገና ተመልሰው ተሸፈኑ፡፡
አሁን ይህን እውነት አጥተኸው ነው ድሮ ፍቅርሽን የምትሰጭው?!
ያልከኝ! ድፍን ዓለም
የሚያውቀውን! የፍቅሬን እንገር በአገሬ ጫካ እንደ እንቦሳ የጋትሁት
ለአያ ደልቲ መሆኑ እውነት አሁን ጠፍቶህ ነው። እንጥፍጣፊ ሳላስቀር ፍቅሬን ሳጠባውና ጀግናዬ ግዳዩን እንደ ባልጩት ድንጋይ በለሰለሰው ጭኑ ላይ አስቀምጦኝ ሲያገሳ ነፍሴ በደስታ ትበራለች:
ከዚያ አይኑ ላይ የተሰካውን አይኔን ሳልነቅል ቁልቁል
እንሽራተታለሁ..." ብላ የጎይቲ አይኖች ቡዝዝ ሲሉ ከሉ ሆራ እሷን የራሱ ለማድረግ በሐመር ባህል መሰረት ጫካ ለጫካ ሲዞር ግራር ዛፍ ስር ደልቲና እሷ መርፌና ክር ሆነው ሲወዛወዙ ከወገቡ
በስሜት እየተናጠ ምራቁን እያንጎራጎጨ ግንድ አቅፎ የተሻሸበትን ጊዜ አስታወሰና ቅናት ውስጡን እያተራመሰው፡-

“ከተንሽራተትሽ በኋላስ?” አላት ሳያስበው፡
👍403🥰2
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_አራት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ

እድላችን ነው: አሁን መነሳት ያለበት ጥያቂ አይደለም።
መልሉ የተሰጠ ጥያቄ ጥያቂ ሊሆን አይችልም
ይልቅስ ሁሉንም በፀጋ ተቀብሎ መኖር ነው" ለምን በምን. ላይ ያተኮረ
ሃሳብ  ሃሳብ እንዳላት ሊገባው  አልቻለም  ስለዚህ ደስታው እየኮለመነ ግራ መጋባቱ እያየለ ሄደ።

“ልታነጋግሪኝ የፈለግሽው ምንድን ነው? ፈገግ ለማለት
እየሞከረ በጥሞና ጠየቃት:

“...እንደውሻ ቢያላዝኑ ሰሚ በሌለባት ምድር ለምን
ተወለድሁ! መወለዴን ሳስበው ይቆጨኛል! መሞቴም ያበሽቀኛል፤
ለምን ተወለድኩና ለምንስ ደግሞ እሞታለሁ። ስወለድም ለሞት
የምኖረውም ለሞት... አይኖችዋ ድንገት በእንባ ተጥለቀለቁና ቁልቁል ተደፋ: ያን ጊዜ ጨነቀው፡
የሚለበልበው እንባዋ
የማያውቃት ልጅ ድንገት እቤቱ መምጣቷ ብቻ አንሷት እንደበደላት ሁሉ ስታለቅስበት የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋው።

“የኔ እህት የሶራ ገልቻ ቤት የብሶት መወጫ የበደል
ማራገፊያ ነው ያለሽ ማን ነው?... ደግሞስ እንዲህ ስታለቅሺ ሰው ቢመጣ ምን ይላል? ልቅሶ ካማረሽ ብሶትሽን ማካፈል ከፈለግሽ...”ብሎ በውስጡ የተፈጠረውን ሃሳብ በአእምሮ አዘጋጅቶ ከመቋጨቱ በፊት አናጠባቸው:

“ወኔ ቢስ! ይህን ስትል አታፍርም አይደል! እልህ
ውስጥህ አይንጠውም አይደል!  እዚች ሃገር መወለዴ እድሌ መሆኑ ጠፍቶኝ የጠየቅህ ይመስልሃል?  እንዴት ያስጨነቀኝ ጥያቂ መለስህልኝ ባክህ ጅል!" ብላ በእልክ እያለቀሰች በስርዓት የተጠቀለለ ፀጉሯን ነጨችው።

“ቆይ እስኪ እንዴ
እኔ አልበደልኩሽ የኔ እህት: አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ እንዲሉ ካለበደሌ..."

ዝም በል! ደሞ አልበደልኩሽ ይላል”  በለባጣ ሳቅ ተፍለቀለቀች። ጥርሶችዋ ያምራሉ! እያለቀሰች እንኳን አይኖችዋ
ያንፀባርቃሉ በጣቶችዋ
የምትበትነውኀፀጉሯም ውበቷን አላጎደለውም:

“ጤነኛ ነሽ? ለመሆኑ ከማን ጋር ለምን እንደምትነጋገሪ
ታውቂያለሽ?" አላት ትንሽ መረር ኮስተር ብሎ።

እሷ ግን “እብድ  መሰልኩህ? እልኸኛ በመሆኔ በማስመሰያ ግብረገባዊነት በውስጤ የሚንተከተከውን ሃሳቤን ሳላፍን እንደ እሳተ ጎሞራ ፈንድቶ ሲወጣ እየለበለበኝ የሚፈሰው እንባዬን,
ስሜቴን በማካፈሌ እብድ በለኛ! ለነገሩ ማን መርምሮኝ ጤንነቴን
አውቀዋለሁ። አመመኝ ስል አውልቂ እባላለሁ... በሽታዬ ይገኛል እፈወሳለሁ ስል ጭኖቼ ተበርግደው ቆሻሻ ይደፉብኛል”  ብላ
በትዝብትና ጥላቻ አየችው።

ከሴት ልጅ የምትፈልጉት ይህን ነው አይደል?!" ቀሚሷን ወደ ላይ ገለበችው:: ፈጣን አይኑ በለስላሳ ጭኖችዋ አልፎ
በለበሰችው ስስ ፓንት ያለውን ነገር ተመለከተ:

“...ይህን እንካ ብልህ እብድ ነሽ! አትለኝም ነበር። ከሃሣቤ ይልቅ ሳያስረዱህ የምታውቀው የስሜት ለሃጭህን የምታዝረከርከው
የሴት ልጅ ጭን ስታይ ነው አይደል!... ብሽቅ! አለችውና
ጭንቅላቷን ያዘች

“..እኔ ምንህም አይደለሁም. የአንተ እህት ግን ጓደኛዬ ናት። እንደ ሎሚ ተመጣ የምትጣል! ጭኖችዋን ለስሜት ሳይሆን ለገንዘብ የምትከፍት! የማታውቀውን ጠረን የምትታጠን... ለመሆኑ ስለእሷና ስለጓደኞችዋ አስበህ አዝነህ... ታውቃለህ? እህትህ ለተጠማው ወንድ ሁሉ በገንዘብ ተገዝታ የምትጠጣ መጠጥ
ተመልሳ ደግሞ እንደ ሽንት ቆሻሻ ላይ የምትሸና ጉድፍ መሆኗን ታውቃለህ?"

እህትህ' ስትል ነደደውና
ሶራ በጥሞና ሲያዳምጣት እንዳልቆዬ ሁሉ እህትህ
“የማን እህት?... የኔ... የኔ እህት?…" አፈጠጠባት: በንቀት እያየችው ቆየችና ረጋ ብላ፦

“ጠባብ በአብራh ክፋይ የምታምን ቂል. ሸርሙጣ እህት የለኝም እያልክ ያን የበከተ እምነትህን በመግለፅ ልትኮፈስ ይሆናል።''

“የኔ እህት ልትሰድቢኝ'ኮ…"

“ዝም በል  አንተ?” ባረቀችበት።

“የተማርከው! እንደ ባንዲራ እየዘመራችሁ ወደላይ ስቀሉኝና አየሩ ላይ ልውለብለብ ንፁህ አየር ነፍሴን ያስደስታት የነዳያንን
ጩኸት ወደማልሰማበት ፉከታቸውን ወደማላይበት! ወደላይ ሽቅብ ልውጣ... ባይ ነህ አይደል! እንደ ብዙዎቹ ምስኪን ያገራችን
ምሁራን፡

“የኛ መማር ከድሃው Uዝብ በተለየ ደሴት ውስጥ ለመኖር ነው። የተማርነውን
ንድፈ ሃሳብ ኮሯጆችን ውስጥ ከተን አንጨምርበት አኝከን አንትፋው ስንውጠው አንታይ!... ብቻ
ተሸክመነው እላይ ወጥተን መውለብለብ  ንግግሯን ገታ አድርጋ አየችው አያት፡ ተያዩ ምን እንደሚላት ጠፋው: ውጭልኝ ለማለትም ወኔ አጣ: እሷ ግን ቤቱን ደግማ አማተረች:: አይኗ
ከምኝታው ራስጌ ካለው ኮመዲኖ ባለው የሚማርh ፍሬም ላይ አረፈ።

“ምንድን ነው ይሄ?” ብላ ፈገግ እያለች በንቀት አየችው:

“የቱ?” አላት ወደራስጌው እየተመለከተ

"ዲግሪ ስትቀበል የተነሳኸው ፎቶ! አለችና ሳቀችበት።

“አያምርም! አየ አስተያየት አየ መልክ... አቤት ኩራት!
አሁንም የምፀት ሣቋን ለቀቀችው።

“...ምን ሰራሁበት ብለህ ነው ከራስጌህ ያስቀመጥከው?
መካኒክ የመካኒክነት ሙያ ንድፈ ሃሳብ በመማሩ መፍቻዎቹን ደረቱ
ላይ ደርድሮ ፎቶ ቢነሳ ምንድነው ትርጉሙ?  ጉራ ብቻ! ሥራበት አዲስ ቅርፅ አዲስ ምርት አምርትበት  ጠቅመህ ተጠቀምበት
የተባለውን መፍቻ እንደሰራው ሁሉ ደረቱ ላይ ደርድሮ ፎቶውን ገጭ አድርጎ ግድግዳው ላይ ቢሰቅለው ወይንም እንዳንተ ኮሚዲኖው ላይ ቢያስቀምጠው ፍችው ምንድነው?

ሶራ ተቁነጠነጠ ቀዝቃዛ ላብ በጆሮ ግንዱ ስር ተንቆረቆረ: “...ሌሎች የፈጠሩትን ለማወቅህ  ሌሎች ያሉትን ለመስማትህ የተቀበልከውን መተማመኛ
የደረሰህን ለማዳረስ ቃለ መሃላ የፈፀምክበትን ጥቁር ጨርቅና ወረቀት ለሰራኸው ቁም ነገር ለፈፀምከው የስው ልጅ መልካም ተግባር እንደተሰጠህ ሁሉ ቀለሙ በሚጮህ ፍሬም ውስጥ ከተህ ለእይታ ዳረግኸው፡

“ማንነትህ እንዲታወቅ... ያልተማረ እንዳትባል... በሃሣብህ ጨቅላነት የናቀህ ፎቶህን አይቶ እንዲያከብርህ እንደ ፋሲካ ዶሮ አልጋህ ላይ ልታርዳት የምታመጣት ሴት ኧረ የተማረ ይግደለኝ
ብላ በንድፈ ሃሳብ ሞረድ በተሳለው ምላስህ ሳትፈራገጥ
እንድትታረድልህ... ነው አይደል! ዲግሪ የተቀበልክበትን ፎቶ ራስጌህ ያስቀመጥኸው:

“ስትሰራ ህዝቡን ስትረዳ.. የተነሳኸውማ ምን ማስታወሻ አለህ? ማረሻ የያዘና ባዶ እጁን የቆመ ሁለቱም አንዳች ሥራ
እስካልሰሩ ድረስ ምን ለውጥ አላቸው?

“ለመሆኑ ለምን እዚች አገር ተወለድሁ? ከኬንያ
ከታንዛንያ... ያነሰች ደሃ ተብላ በምትናቅ፤ እምትኮራበት ታሪክ
አንጂ ቤሳ ቤስቲኒ ስልጣኔ በሌለባት ሃገር ለምን ተፈጠርሁ ብለህ
ቀንተህ ታውቃለህ  ከርሳም ጀብ ድሮ ጅብ ሆዱ ከሞላ በየት አገር ነው የሚቀናው: ሆዱ ከሞላ ባገኘው የቀበሮ ጉድጓድ ገብቶ መጋደም ነው: ክርፋቱ አይሸተው ጥንብ ነው ብሎ አይጠየፍ ስለ ማደሪያው አያስብ…

“በእንዳንተና እኔ አይነት ግዴለሾች ግን ችግር ችግር
እየተከመረ ዋጠን በህሊናና እጆቻችን ሰርተን ከመጠቀም ይልቅ
የህይወት ከርፋት ውስጥ ተጠቅልለን ማልቀስ መጮህ... እጣ ፈንታችን ሆነ" አላችና በሐዘን አንገቷን አቀረቀረች᎓ እንባዋ ዱብ
ዱብ ሲል ታየው: የመጣችበት ጉዳይና የምትናገርበት ምክንያት
👍372
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ስድስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ

መጀመሪያ የደራረቀ እንጨትና ግንድ ቀጥላ ለጉልቻ የሚሆን ሦስት ድንጋይ አቅርባ እሳት አቀጣጠለችና ውሃ የያዘውን
ቶፋ ወደ አንደ በኩል ዘንበል አድርጋ ጣደችው ከዚያ በለሻ እንዲበላ ስታቀብለው “አንችስ ብይ እንጂ ተወተቱም ጠጭ…"
አላት ጭብጦውን እያላመጠ።

ይእ! ይልቅ አታስቀምጠው ጠጣው። የኔ በኋላ ይደርሳል“ ብላ በጨንዋዛ ቅጠል የተቋጠረውን ሽፈሮ ቡና ፈታ በሚቆለቆሰው
እሳት በመቅጃው የቅል ጭልፋ ዙሪያ ትጉልጉል የሚለውን እንፋሉት እንዳያቃጥላት ተጠንቅቃ የቡና ገለባውን ጨመረች:

ሰማዩ ላይ እንደ ጨሌና ዛጎል ከዋክብት ሆጨጭ ብለዋል። በስተ ሰሜን በኩል ደግሞ ብናኝ ዳመና አቅፎ የያቸው ከዋክብት
ብልጭ ድርግም... ይላሉ: የምሽት በራሪዎች የሌሊት ወፍ ጉጉት የማታ ተረኞች ሆነው ወዲህ ወዲያ ይበራሉ: ጅብ ይጮሃል
አንበሳው ያገሳል... ጦጣና ዝንጀሮ ፀጥ ብለዋል: ጉሬዛዎች ግን እንደ ዶሮ ሰዓት እየጠበቁ “ጉርር ጉርር. ጉርርርር..." እየተቀባበሉ ያውካኩና ጸጥ እረጭ ይላሉ።

ዳራና ደልቲ በሚነደው የሳት ወላፈን እሷ አንድ ጉልበቷን
አጥፋ መሬት ላይ አጋድማ፧ ሌላውን ጉልበቷን አጥፋ አቁማ አልፎ አልፎ እንጨቱን ቆስቆስ እያደረገች አይኖችዋን ጨለማው ውስጥ ተክላለች።

ደልቲ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ የአባቱን ከዋክብት እንደ እሳት እየተንቦገቦጉ ቁልቁል ተወርውረው የሚጠፉትን “ሚቲዎሮች”
እያየ ያስባል።

በሁለቱ መካከል ንግግር የለም:: ፀጥታ ሆኗል: በሐመር ባህል የቡና ሥነሥርዓት እርጋታና ፀጥታ የሰፈነበት ነው:: ህፃናት
እንኳን ይህን ስለሚያውቁ  ቡረቃቸውን ገተው ያደፍጣሉ። ሴቷ ወንዱ ሽማግሌው ከራሳቸው
ጋር የሚነጋገሩበት ራሳቸውን የሚመዝኑበት አደብ የሚገዙበት በጎና እኩይ ተግባራቸውን የሚፈትሹበት... ነው የቡና ሥነ ሥርዓት ለሐመሮችሽማግሌ
ትናንትን የሚያደንቅበት ዛሬን የሚያመሰግንበት ነገን በተስፋ የሚጠባበቅበት ግለሰቡ ለማህበረሰቡ ደህንነት ሰላምን፡ ጥጋብን የሚመኝበት የአባት የአያት ደንብ ወደ ልጅ የሚሸጋገርበት ጠላትና ወዳጅ ጠንቅቆ የሚታወቅበት ምላስ አጥራ ህሊና ገዝፎ መግባባት የሚመጣበት ነው የቡና ሥነ ሥርዓት። ይህ የቡና ሥነሥርዓት ለህፃን ለወጣት ለአዋቂ ለሽማግሌ ለእንግዳ ክፍት ነው። ያሻው ሁሉ ይሳተፋል እድሜና ደረጃውን ጠብቆ ይዳረሳል። የሐመር በር መዝጊያ የለውም። የሐመር ሕይወት ጓዳ የለውም፡ የሐመር ማህበረሰብ “ከሌላው ኪስ ወስደህ የኔን ኪስ ሙላ በሚል ስግብግብነት ምኞት ላይ አልተመሰረተም።

ደስታ ችግር ጦርነት... የጋራ ነው: የአንዱ ምርኩዝ ሌላው ነው: ግለሰብ ህብረተሰብን አይረሳም። ህብረተሰቡም ግለሰቡን
አይጥልም ያሳድገዋል ሃብት ያካፍለዋል ይድረዋል ለጀግንነቱም
ያሞግሰዋል...

ስሰዚህ ደልቲና ዳራ ምንም እንኳ ጫካ መሃል ብቻቸውን ቢሆኑም ህሊናቸውና አካላቸው ግን በባህላቸው ደንብና ሥርዓት
የተገነባ ነው: ፀጥታው ተጠብቆ ዝምታው ሰፍኖ እሱም ሆነ እሷ ትናንትን ቃኝተው ዛሬን አስታውሰው ነገን ሲያልሙ በሐሳብ
ተውጠው ቆዩ።

ከዚያ ዳራ ሾርቃውን ጠረግ ጠረግ አረገችና የቅል ማንኪያውን አንስታ ቶፋው ውስጥ ጨምራ ከቡናው ሁለቴ ቀድታ ሰጠችው ደልቲ ቡናውን ለማብረድ ግራና ቀኝ ጎለል አደረገና ፉት ብሎ “ፕስስ ፕስስ.." እያለ ወደ ምስራቅ ምዕራብና ወደ መሬት የሸፈሮ ቡናውን አርከፍክፎ- “የአባቴ ሰማይ ዝናብ ይጣል በሽታዎች ከሐመር ምድር ይጥፉ፤ ከብቶች  ፍየሎች በጎች
አያገሱ  በሰላም ይግቡ ይውጡ..." ብሎ መረቀና ወደ  ዳራ ዞሮ ቡናውን ፉት ብሎ “ፕስስ..” አለና ሽፈሮ ቡናውን አርከፈከፈባት፡

ዳራ ደንገጥም አፈርም ሳትል አይኗን ከወረወረችበት
ሳትመልስ በሃሣብ እንደሰመጠች
“..ተባረኪ... ዘርሽን ያብዛው የአባትሽ የሐመር ምድር የልጆችሽ መቦረቂያ ይሁን... የባልሽ ጥገት ይብዛ" ብሎ መረቃትና ቡናውን በፀጥታ መጠጣት ጀመረ።

ሰረቅ አድርጋ አየችው: በውስጧ እንደ ህፃን የሚላወሰው እሱ ነው ከፊት ለፊቷም የተቀመጠው እሱ ነው፡ ፍቅር የሰጣት የመረቃት እሱ ነው። ስለሱ ያላትን ስሜት አሁንም በእርግጠኝነት አጤነች ስለ ጀግናው የሚባለውንም አስታወሰች።

ጥጃና ፍየል ስትጠብቅ ወንዶች የድሜ ጓደኞችዋ እነሱ ጠመንጃ እያሉ እንጨት ቆርጠው እየተሸከሙ እንደ ጥይት ዳውላ እየወረወሩ ይሄ ከብት የኔ ያ እርሻ የኔ... እየተባባሉ ሲጫወቱ። እሷም የእድሜ እኩዮችዋ ከሆኑት ልጃገረዶች ጋር ከከስኬ ወንዝ
የጭሮሽ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየለቀሙ, ልጅ እያቀፉ... ሲጫወቱ
ይቆዩና ጫካው መሃል ሚስትና ባል ሲባባሉ ቆይተው ዘፈን ሲጀምሩ
ስለ ሐመር ተራራ ስለ  ሐመር ሰማይና ምድር... ስለከብቶች ሲያዜሙ ይቆዩና የሐመር ጀግኖችን ህፃናቱ ሲያወድሱ የደልቲ ስም የደልቲ ጀግንነት... ይነሳል። ወንዶች ህፃናት “እኔ ነኝ እሱ እኔ ነኝ
ሲባባሉ እሷም ከሌሎች የእድሜ ጓደኞችዋ ጋር “ደልቲን የሆነውን ወንድ እኔ ነኝ የማገባው ! እኔ ነኝ የማገባው" ሲባባሉ አንዳንዴ ሁለት አንዳንዴ ሦስት እየሆኑ ሲያገቡት የነበረው የልጅነት ዘመኗ
ታወሳት። እንዲህ ዳሌዋ ሰፍቶ ጡቶችዋ አጎጥጉጠው ሰውነቷ
አምሮ ባለበት የቡረቃ ዘመኗ ያ ስም አብሯት አደገ:: የዚያ ጀግና መግነጢሳዊ የፍቅር ሃይል በውስጧ እየተገለባበጠ  ሲያስጨንቃት ኖረ።

ገበያ ስታየው ትንፋሽዋ ቁርጥ ያለባት ሲመስላት  ስሙ ሲነሳ እንደ አውሬ  ስትደነብር  ፍትወት ሲያስቸግራት ከልቧ
አውጥታ ጉያዋ ውስጥ በሰመመን ስታስገባው፤ በፍቅሩ ወዲያ ወዲህ
ስትንገላታ ኖረች: ነገ ነገን ሲተካ የሷ አምሮትም ከቀን ወደ ቀን ሲጨምር ከስኬ ወንዝ አሸዋ ጭራ ጭሮሽ ውሃ ስትቀዳ ያ በውስጧ
አብሯት ያደገው ጀግና ድንገት ሽቅብ ወደ ቡስካ ተራራ ሲወጣ አየችው ደነገጠች! ግራ ገባት: “አያ ደልቲ! እሱ ኮ ነው…..የኔው.." ብላ ቀባጠረች። ጓደኞችዋ ሳቁባት አላየቻቸውም።
አልሰማቻቸውም እሱም የለም: ጫካው ሰወረው። እሷ ግን ታየዋለች።አካሉ ቢሄድ እሱ ልቧ አለ፡ አወጣችው አየችው ወደደችው! አቀፈችው...

ይእ!  እሰይ እሱንም ከውስጤ ያለውንም አየሁት..." ቀና ብላ ፀሐይን ሰማዩን... ቦርጆን አመሰገነች።

“እይ! እሽ ምን ልሁን! እሽ ምን ላርገው.." ጓደኞቿ እንደገና ሳቁባት። ጆሮዋ ግን አይሰማም አይኗ አያይም... ሁሉም ጀግናዋን ሊዳብሱ ሄደዋል። ውስጧ ያለው የፍቅር ሃይል ለፍንዳታ ተዘጋጀ ተቀባበለ። ሃይሉ ናጣት ወዘወዛት, አሻት... አዞራት አሽከረከራት... ዛፍ ጥላ ስር በደመ ነፍስ ሄዳ አረፈች መረጋጋት ስትጀምር ቡስካ ተራራን ቀና ብላ አየችው: ነይ" አላት። ወሰነች
ለመሄድ ጀግናዋን ጫካ መሃል ለመፈለግ  ቆረጠች። ሄደች “አቅጣጫ ያላት ጀልባ ንፋሱም ይረዳታል ይባል የለ አገኘችው::

ደልቲ ዳራ የቀዳችለትን ሸፈሮ ቡና አራት ጊዜ እየተቀበለ ጠጣና  ሾርቃውን ከፊት ለፊቱ አስቀመጠው: በሐመር ደንብ የጠጡበትን እቃ ማቀበል ጨምሩልኝ ሲሆን ማስቀመጥ ግን በቃኝ ማለት ነው:: ዳራ ለራሷ መጠጣት ጀመረች። በሐመር ባሀል ወንድ በሐመር ባሀል ወንድ
አንበሳ ነው ሴቷ አንበሳ መጀመሪያ ግዳይ ትጥላለች: ወንዱ ጎፈር
አንበሳ ግን ቀድሞ ይባርካል ይበላል፤ ይጠግባል፤ ተንጎማሉ ሄዶ
ለመከታነቱ ተዘጋጅቶ ይጋደማል። ሴቷ አንበሳና ደባሎችዋ የጎፈር
አንበሳው ግሣት ደህንነታቸው ህልውናቸው ነው... እሱ ሲጠግብ
እሱ ሲጠነክር ይረካሉ። ዳራም አንበሳዋ ከጠገበ በኋላ ጭብጦዋን በላች ቡናዋን ጠጣች ከዚያ እቃውን ሸካከፈች።
👍37👎1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰባት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ


ከአዲስ አበባ ፍልውሃ በታች ከማህተማ ጋንዲ መንገድ መስመር ከብሔራዊ ስታዲዬም ብዙም ሳይርቅ ከግዮን
ከኢትዮጵያ ከሒልተን
ሆቴል... ለሚመጡ እንግዶች አመች የሆነው የ“ጎጆ” ምግብ ቤት ግቢው በመኪና ተጣቧል።

ቢኤም ደብሊው መኪና በዘበኛው መሪነት ቦታዋን ይዛ እንደቆመች ሁለቱ እንግሊዛውያን ወደ ምግብ ቤቱ አመሩ። እሷ ቀደም እሱ ደግሞ ከኋላዋ ተከትሏት ሲገባ እንደ ቀልድ ቁመናዋን አስተዋለ: ፀጉሯ አጠር ከማለቱ ሌላ ስትሄድ የሚደንሰው ዳሌዋ አለ
'' የለም' »አስኝቶ የሚያወራርደው ወገቧ
ያው ነው።ስትጠመጠም እንደ ላስቲክ እየተሳሳበ በሰራ አካላቱ የሚስለከለከው አካሏ ለውጥ የለውም። ልክ እንደ ዛሬ ሁለት ዓመት ከስድስት ወሩ ነው ጥቁር ቲሽርት እንደ ወትሮው ሁሉ ጂንስ ሱሪ ለባብሳለች።ወገቧና አንገቷ ልብሷ አልደረሰበትም:

የሴት እምብርት ሲያይ ጎሮሮውን እንዳነቁት ሁሉ አይኑ የሚፈጠው ስቲቭ አጎጠጎጤ ጡቷን ደረቱ ላይ አስደግፋ ለጠጥ ብላ
ሽቅብ ተስባ ስትስመው እንደ ህፃን ልጅ በእቅፉ አልሞላ ስትለው እቅፉን ጠበቅ አድርጎ እንደ ቄጤማ አካሉ ላይ የለጠፉት ትዝ
አለው።

ገባ ብለው ክፍት ቦታ ሲያማትሩ አስተናጋጁ በስተግራ በኩል ግድግዳው ጥግ ባዶ ቦታ አሳያቸው።

የሲሊን ዲዮን ዜማ በለሆስታ ይሰማል ካርለት ድምፀ መረዋ ካናዳዊት አቀንቃኝ ስሊን ዲዮን ኒወርክ “ብራንድ ዌይ
ዳንሰሮች ጋር አይኖቿዋን እያስለመለመች, እግሮችዋን መሬት
ለመሬት እየሳበች ወለሉ ላይ እየተኛች...በለበሰችው ጃፖኒ እርቃን የሆነውን ትከሻዋን እየላሰች ስትዘፍን ስላየቻት ይበልጥ ወዳታለች::

እና! ገና "ከመግባታቸው በፊት የምትወደውን ዜማ ስትሰማ የደስታ ስሜት ተሰምቷታል።

አስተናጋጁ የምግብ ዝርዝር ይዞላቸው መጣ: ሁለቱም
ዝርዝሩን ተቀበሉና በፀጥታ አንብበው ካዘዙ በኋላ ጨዋታቸውን ሊጀምሩ ሲሉ

“የሚጠጣስ?” አይኖቹን ግራና ቀኝ እያዟዟረ  ጠየቀ
አስተናጋጁ።

“ማርቲኒ” አለችው ካርለት

“ነጭ ወይንስ ቀይ ማርቲኒ” የሾለ ፊቱን ወደ ፊት አስግጎ ጠየቃት።

ነጭ ይሁንልኝ አለችው። አስተናጋጁ ለጨዋታ
መጣደፋቸውን ተረድቶ ይቅርታ በሚጠይቅ አስተያየት ስቲቭን
እያየ አገጩን ሽቅብ ሰበቀ።

“ብሳክ ሌብል” አለው።

ካርለት ቦርሳዋን ወንበሩ ላይ አንጠልጥላ ፈገግ እያለች።

“እሺ ስቲቭ! ስትለው ስቲቭም ወንበሩ ላይ ጠረዼዛው እያስጠጋ ፈገግ ብሎ አንገቱን ወዘወዘ ደህና ነኝ ለማለት።

“…ኢንግላንድ መልም ጊዜ አሳለፍሽ?

“ከናቴ ከጓደኞቺ ጋር በመገናኘቴ ደስ ብሎኛል። ብዙዎቹ ጓደኞቼ ግን ደስተኞች አይደሉም:: ሁሉም ያለሙትን ህይወት
መኖር የቻሉ አልመሰለኝም። ከጎይቲና  ከከሎ ጋር ያሳለፍኩት ጊዜም ባመዛኙ እንግዳ ለሆነባቸው ስልጣኔ እያንዳንዷ እንደ ህፃን
ልጅ ማስረዳቱ አድካሚ ቢሆንም ወድጄዋለሁ:

“ጥናቴን በተመለከተ ማንቸስተር ያቀረብሁት ዝግጅት ለአማሪዬና ስብሰባ ተሳታፊዎቼ ጥሩ ስሜት የፈጠረ በመሆኑ ደስ ብሉኛል። ከዚህ ተጨማሪ ከማንቸስተር ዩንቨርስቲ አዳራሽ ስንወጣ ብዛት ያላቸው የ" ጋርዲያን የሄራልድ ትሪቡን…
ጋዜጠኞች ለኔ ለጎይቲና ለከሎ ያቀረቡልን ጥያቄ የሰጠነው መልስ  በቤቱ ውስጥ የነበረው የመግባባትና የማድነቅ እንድምታ ስቃይን እሚያስረሳ ነበር። “በተለይም ሴቶችን አስገድዶ መድፈርና
የወሲብ ብዝበዛ በሐመር ምድር የተወገዘና የማይፈፀም ፀያፍ ጉዳይ
መሆኑን ላስረዳቸውና ጎይቲ “ሴትን ያለፍቃዷ ማን ያስቸግራታል ደሞ." ያለችው ስሜታዊ አባባል ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ውስጥ
ዋናው ነበር።

“በተረፈ ለአንድ ሳምንት ስፔን ለአንድ ሳምንት ደግሞ
ደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ሄጄ ነበር: እንደ ማይክል ጃክሰን በዚች ፕላኔት ካለው ወፈ ሰማያት ህዝብ መሀከል የማደንቀው ሁለት ሰው ነው:: ማንዴላንና ማር ትሬዛን ብዬ ባልደመድምም በደረጃ ከማይክል አስተያየት የማላርቀውን ማንዴላንና የሱን አመራር
በቅርብ ለማየት እድል ለማግኘቴ የተደሰተሁ ሲሆን በጆሀንስበርግ ሰሜን ማዕክል ብራምፎንቴን በሚገኘው ዊትስ ዩንቨርስቲ የአባቴ ስራዎች በመታሰቢያነት ሲቀርቡ ንግግር ማድረግ መቻሌሞ ጥሩ አባት ሞቶም የደስታ ምንጭ እንደሚሆን ለማመን ችያለሁ።

የነፃነት ረጅም ጉዞ በሚል
ርዕስ በ1994 ዓ.ም
በማክዶናልድ አሳታሚ ኩባንያ በኔልስን ማንዴላ የታተመው የ ባለ 617 ገጽ መጽሐፍም በመርፌ ቀዳዳ የሚታይን ብርሃን ተከትሎ
ከፀሐይ አካል መድረስ መቻሉን የተማርኩበት ነበረ።

“የፍቅር ህይወቴን በተመለከተ ግን እግሮቼ ሁለት መሰላል ላይ ናቸው:: ባል የማግቢያዬ ልጅ የመውለጃዬ ጊዜ እያለፈ
መሆኑን ሳስብ አንጀቴ በሃዘን መኮራመቱ ባይቀርም የሰለጠነው
ዓለም ለፍቅር ቀረቤታ ያለው አነስተኛ ግምት የመመዘኛ ዝባንዝንኬው በተፈጥሮው ዓለም ደግሞ ህይወቱን ላልኖረው ሰው
ያለው አስቸጋሪነትና የፍቅር  አለመጣጣም... ለጊዜው መምረጥ ከሚያስቸግር ሁኔታ ላይ እንደጣለኝ ነው የምረዳው።

“እዚህ  ላይ ግን ልገልፅልህ የምወደው እንደማንኛውም
ሰው መጭው ህይወቴ ምን መምሰል እንዳለበት ሳስብ ብዥ ብዥ እያለ የሚታየኝ ህልም አስጨናቂና አሳሳቢ ቢሆንም ከምንም በላይ
የምፈልገው በአባቴ የሰው ልጅ ሕይወት ምርምር ጎዳና መጓዝንና ለሙያዬ መሉ መስዋዕትን መክፈል ስለሆነ መፅናኛዬ ሚዛኍን
የደፋ ነው፡፡ ስለዚህ ደስተኛነቴ አሁንም ከቁጥጥሬ አልወጣም ብላ
ፈገግ አለች::

ስቲቭ ሃሣቧን ያዝኩት ሲል ወዲያ ስታላጋው ወዲህ
ስታጋጨወ ቆይታ እንደ ጥሩ ተውኔት ጨዋታውን ባላሰበው መንገድ ደመደመችበት።

ለጥቂት ጊዜ ሁለቱም በየግል ሃሣባቸው ተውጠው እንደቆዩ ፈጣኗ ካርለት ከነበረችበት የሃሣብ ግልቢያ ድንገት ልጓሟን ስባ የስቲቭን ቀኝ እጅ በቀኝ እጅዋ ቀስ ብላ ጫን አድርጋ
ሳታስደነግጠው ሳታሽብረው ሃሣቡን ሳታምታታበት ትክ ብላ
መረጋጋቱን ካስተዋለች በኋላ፡-

“ስቲቭ! አንተስ ከተለያዬን በኋላ ጥሩ ጊዜ አሳሰፍክ?"
አለችው።

ዘናና ፈገግ ብሎ  “በስራዪ ብዙም ውጥረት አልነበረኝም የዲፕሎማት ትልቁ ሥራ ግንኙነት መፍጠር፤ የአገሪቱን
ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አዝማሚያ መከታተል፤ ተስፋን መመገብ ገደብ አልባ የሆነ ቃል ኪዳን መግባት በመሆኑ በፈቀደልኝ የጉዞ ፍጥነት እያሽከረከርኩ ስራዬን ለመወጣት ሞክሬያለሁ፡ የኢትዮጵያ ኑሮ ግን ከብዶኛል" አላት

እንዴት? የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ!" አለችው ውስጡን
ጠልቃ ለመመልከት አይኖቹን እየፈለገች።

ካርለት የሰዎችን አይን በማየት ስለ ሁኔታዎች ምንነት ለማወቅ እንደሚቻል በስነ ልቦናዊ ትምህርቷ ታውቃለች። አንድ ሰው ያስጨነቀው ነገር ትዝታውን• ፍቅሩን ጥላቻውን... ሲገልፅ
የአይኖቹ ኳሶች የት እንደሚሆኑ ወዴት እንደሚዞሩ ከስነ አዕምሮ
ባለሙያዋ እናቷ ተምራለች። ሌላው ቀርቶ እውነትና ውሸት አባባልን የአይንን እንቅስቃሴ አይታ በከፊል መግለጽ ትችላለች።
ከዚህ በተጨማሪም የአንድ ሰው አመለካከቱ በመስማት ወይንም በማየት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ከአገላለፁ በመረዳት አይኑና ሃሣቡ  ከሚሰጣት ግንዛቤ ግንኙነቷን ለመመዘንና ለመለካት
አትቸገርም። ለዚህም ካርለት ስቲቭ ሲያወራት አይኖቹን ትፈልግ ነበር: ኋላ ግን አይኑን በአይኗ ያዘችው እንቅስቃሴዋንም
አስተከለችና፡-

"...የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ? አለችው ደግማ ስቲቭ
በአፍንጫው ጫን አድርጎ ተነፈሰና፡-
👍22
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_አስር


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ

ከፖርት ፕሪንስ በስተ ምስራቅ ፓርቶሪኮ ሳንጁአን ውስጥ የግል እርሻ የጀመረው አሌክስ ቀደም  ሲል የስፔን ፋሽዝም
አራማጅና የጦር አባል ከነበረው ስመ ጥር አባቱ ጋር ወደ ፓርቶሪ
በተደጋጋሚ ከሄደ በኋላ ሳንጁአን ለመኖር እንዲወስን ተፈጥሮአዊ
ፍቅሩ አደፋፈረው፡

የሻምበልነት ማዕረግ የነበረው አባቱ ልጁ በእርሻ ትምህርት ሰልጥኖ ህይወቱ በእርሻ ምርት ላይ ቢመሰረት የወደፊት ዕድሉ
የተቃና ደስተኛና ሃብታም ሊሆን እንደሚችል በመከረው መሰረት
አሴክስ የአባቱን ህልም የእራሱ በማድረግ ህልሙን ለማሳካት የሚያስችለውን ጥረት ፈጽሞ በመጨረሻ ተሳካለት፡

አሌክስ ደጋግሞ ስለ እርሻ ዘመናዊ እርሻ ስለሚያስገኘው
ብልፅግና ስለ ተሻሉ የምርት ውጤቶች ማውራት እንጂ በፍቅሩ ተረትታ
እንደነፍስ ጡር ለምትብረከረከው
ፍቅረኛው ቁብ
አልነበረውም ሌላው ቀርቶ እግሩ ስር እንደምትታከከውና "ፔሙስ" ብሎ እንደሚጠራት ድመቱ ሲገናኙ እጁን ሰዶ ዳብሷት ካልያም እጆችዋን ስቦ ወደ ደረቱ አስጠግቷት አያውቅም አይብዛ እንጂ
አንድ ወቅት የፍቅር አባባሎችን ይለዋወጡ አብረውም እየተሻሹ
ጊዜያቸውን በደስታ ያሳልፉ የነበረ ቢሆንም! ያ የስሜት መመሳሰል ግን ከጠለቀ ብዙ ወራቶች ተቆጠሩ።

ይህ የቸልተኝነት ባህሪው ሸበላ ቁመናው የታከታት ደረቅ የአጨዋወት ስልቱ ሳይቀር አኜስን ለአሌክስ ያላትን ስሜት ከእለት
ወደ እለት እንዲያድግ አደረገው። አንዳንዴ እንዲያውም፡-
“አሌክስ! እባክህ ለፍቅራችን የሚሆን ጊዜ ይኑርህ? እባክህ በፍቅር
ስሜቴ አትጫወትበት!...” በማለት ምርር ብላ ስትነግረው፡-

“እባክሽ አኜስ ታገሽ!
ትዕግስት ይኑርሽ! ልትረጅኝ
ሞክሪ! በአሁኑ ሰዓት የፍቅር ስሜቴ በወደፊት ዓላማዬ እንደ ጉም ተሸፍኗል። አንድ ወቅት ግን ጉሙ ይበተናል፤ በሰማያዊው ሰማይ
ከምስራቅ ወደ ምዕራብ እንደምትጓዝ ፀሐይ የፍቅር ብርሃን ፍንትው ብሎ ይፈነጥቃል...'' ይላታል:

“አሌክስ! እኔ'ኮ ብዙ ላሳስብህ አልሻም። በሳምንት ቢያንስ
ለተወሰነ ደቂቃ እንኳ ፍቅር እንድንለዋወጥ ለማድረግ ሞክር ፧እየተጎዳሁ ነው” ስትለው፡-

“እስኪ እሞክራለሁ አንች ግን ጠንከር በይ: በህልሜ
ልትደሰች ሞክሪ በአትላንቲክ ውቅያኖስ በተከበበችው ሳን ጁን
ውስጥ የሚኖረው ቡቃያ ንፋሱ ጎንበስ ቀና ሲያደርገው ይታይሽ!
አዲዎስ ብሏት ይሄዳል።

አንድ ቀን ግን አሌክስ በጅፕ መኪናው መኖሪያዋ ድረስ መጥቶ ድንገት “ለሽርሽር እንሂድ? አላት።

“የት?” አለችው አኜስ ግራ ተጋብታ።

“ሱ..” አለ አፉን በቀኝ እጁ አመልካች ጣት እየጠበጠበ።

“አሌክስ የት እንደምንሄድ መንገሩን ባትፈልግ እንኳን ወጣ እንደምንል ቀደም ብለህ ፍንጭ መስጠት ነበረብህ: ከሰዓታት
ወይንም ከቀናት በፊት ወጣ እንደምንል ነግረኸኝ ቢሆን ኖሮ ነፍሴ በደስታ ከመዝለሏም በተጨማሪ ስሜቴ በጉጉት ተበረጋግዶ በናፍቆት ይጠብቅህ ነበር: አሁን ግን ልቤ በሐዘን ቀዝቅዛለች። ስሜቴም በድን
ነው። እኔም ስላልተዘጋጀሁ የትም መሄድ አልፈልግም” አሰችው።

ያልተለመደ ፈገግታ አሳይቶ ባልጠበቀችው መልክ የግራ እጅዋን ብድግ አድርጎ ጣቶችዋን ሳም ሳም አደረጋት፤ ጉንጯን በቀኝ
እጅ አመልካች ጣቱ ደባበሰላት: ሽቅብ አንስቶም ከንፈሯን በከንፈሩ
ደባበሰላት።

ወዲያው ልቧ ጋለች ሰውነቷ በሙቀት ተጥለቀለቀ፡
የፍቅር ሃይሏ ከየስርቻው ተሰባሰበ ስለዚህ! “ማሬ!
እንሂድ" አለችው::ሃሳቡን እንዳይለወጥ እየሰጋች: አሌክስ መኪናውን እያሽከረከረ ጭኖችዋን በቀኝ እጁ እየደባበሰ የምትሆነውን አሳጣት: ያ ጨካኙ አሌክስ ሳይሆን የፍቅር መልአክ ሆነባት…

“አሌክስ አልቻልሁም አለችው እየተስለመለመች
ጥቂት ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ።

“ትዕግስት ጥሩ ነው..."

“ኡፍ ስብከትህን አቁም። በሰዎች ሙያ ጣልቃ አትግባ መኪናዋን ይልቁንስ አቁም አለችው በትዕዛዝ መልክ፡ መኪናዋ ወደ
ዳር ወጥታ ቆመች ሞተሯ ጠፋ።

ከተቀመጠችበት ዞር ብላ እጆችዋን ዘርግታ የአሌክስን
አንገት አቀፈችው። ተገናኙ
ረሃብተኛዋ ከንፈሩን ጎረሰቸው እፅዋት በነፋሱ ጎንበስ ቀና ይላሉ ከርቤው እየጤሰ  መላዕክት
እያጀቧቸው ሽቅብ በፍቅር ስረገላ አረጉ።

“አሌክስ! እኔ አላምንም... እንዴት ደስ አለኝ ለካ እንዲህ የደስታ ምንጭ ነህ እሰይ እንኳን ታገስኩህ እንኳን ቻልኩህ እንግዲህ ዳግመኛ ከፍቅር ሠረገላችን አንወርድም አይደል! ከምድር ላይ ይልቅ እዚህ ነፍስ ነህ..." እያለች ላዩ ላይ ተንከባለለችበት

የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል በርቀት ከቆሙት መርከቦችና አጠገባቸው ካለው የድንጋይ ግንብ ጋር እየተላተመ አረፋ ሲደፍቅ
ከኮሎምበስ መታሰቢያ ግዙፍ ሃውልት ትይዩ የሚነፍሰው ጤሮ ንፋስ በጆሮ ግንዷ እያፋጨ ሲያልፍ ግን አይኗን ገልጣ ከገነት ወደ ምድር ተመለሰች። ምድሯን ውቅያኖሱን ስታይ አስጠሏት፡ አሌክስ
አሁንም አብሯት አለ ያ ሲያደርጉ የነበረውና አሁን አጠገቧ ባለው አሌክስ መካከል ግን ልዩነት ያለ መሰላት፤ ተጠራጠረችው።

“ማሬ የት ነው ያለነው?" ከሰመመኗ እንደነቃች ጠየቀችው።

“ሁዌልቫ ነን! ለስንብት አመች በመሆኗ የምሄድበትንም ከርቀት ላሳይሽ ስለምችል  ሁዌልቫን መርጨልሻለሁ" አላት ሳብ አድርጎ ወርቃማ ዞማ ፀጉሯን ስሞ፡

“ሁዌልቫ” ይህ ስም ምድር ላይ ያውም ስፔን ውስጥ
የምታውቃት ከተማ ስም ነው:

“ለምን ግን እዚህ አመጣኸኝ?” ተሸበረች:

“ለስንብት አልሁሽ እኮ! አላት ወደ እሱ ጠጋ አድርጎ
እያቀፋት ሰውነቱ ሰውነቷን ሲነካት እየዘገነናት

“የምን ስንብት?... ደግሞ እንዴት ጨካኝ ነህ?... በአንዴ ከደስታ ወደ መከራ ትመልሰኝ..." አለችና ልሳኗ ተዘጋ: አሌክስ ሲስማት ከንፈሯ እንደ በረዶ ቀዘቀዛት።

ዙሪያቸውን እንደ እንቦቀቅላ ህፃን ድክ ድክ የሚሉት
እርግቦች አንዳች ነገር እንደመጣባቸው ሁሉ ድንገት ግር ብለው ወደ
ሃይቁ አቅጣጫ በረሩ።
አኜስ የአሌክስን እጆች ወርውራ እርግቦችን
ተመለከታቸው።

እጥፍ ብለው እንደገና ሽቅብ ጎነው በረሩ: አሌክስ ፊቷን ወደ እሱ አዙሮ
“ሰርቶ መበልፀግ ስመኘው የኖርሁትን እድል በማግኘቴ
ረክቻለሁ። ፍቅራችን ከብልፅግና ማግስት.. ጆሮዋ ደነቆረ: ከዚያ በኋላ የሚለውን አልሰማችውም።
ፍቅር ከብልፅግና
ማግስት…" አባባሉ በአእምሮዋ አስተጋባ:
ዛሬን አበላሽቶ ነገን ማስዋብ ፍቅርን ገፍትሮ ጥቅምን ማቀፍ
ተምታታባት እሪ ብለሽ ጩሂ አሰኛት… መጮህ ግን ተሳናት::ለመጮሀም ኃይል ያስፈልጋል።

አሌክስን ጠላችው 1
ገፋችው... ከዚያ እርግቦቹ ወደ ሄዱበት አቅጣጫ በረረች “አዕዋፍ ለካ ወደው ከምድር ርቀው አይበሩም ብላ በአየር ላይ ለመብረር ወደ ሰማዬ ሰማያት ለመጎን ሞከረች ትናንሽ ፍጡራን የፈፀሙትን ግን መፈፀም ተሳናት።

ይህ ከሆነና ከአሌክስ በተለየች በአምስት ዓመቷ “አሽቀንጥሬ ጣልሁት ያለችው የከንፈር ወዳጅዋ አንደገና ራባት። ፍቅሩ አገርሽቶ ጤና አሳጣት ስለዚህ ፓርቶሪኮን ለመጎብኘት በሚል ሽፋን ወደ ሳንጁአን ሄደች።

ሳን ጁአን እንደደረስችም አሌክስ በሰጣት የእርሻ ጣቢያ ማዕከል አዳራሻ ሄዳ አሌክስን እንዲያገናኝዋት ጠየቀች። በእርግጥ
👍28
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ


ጆሮዎቹ ላይ ሉቲ አንጠልጥሏል ጥቁር ቆዳው ላይ አልፎ
አልፎ ቡግር መሣይ ነጠብጣቦች ይታያሉ: አገጩ ጠበብ ብሎ
ቁጥርጥር ያሉት ፂሙ ፀጉሮቹ አልፎ አልፎ ጉች ጉች ብለዋል።

አይኖቹ ቦዘዝ ብለው የጭካኔ የእንቢተኝነት... እይታ ይታይባቸዋል። ሶራ የኮንችትን አያት ፎቶ ግራፍ ሲመለከት ቆይቶ ሲጋራውን አቀጣጥሎ ወደ መቀመጫው ተመለሰ።

ኮንችት ከወደ ውስጥ በሩን ከፍታ ብቅ ስትል ቤቱ በምግብ ሽታ ታፈነ። ከዚያ የተጣጠፉ የጠረዼዛ ልብሶችን እያነጣጠፈች
ሰሃን ማንኪያ ሹካ እየደረደረች።

“ወንድ አያቴ ሴት አያቴን በፍቅር ልቧን ጠምዝዞ የጣላት እንዴት እንደሆነ ልንገርህ" አለችው ሙሉ ለሙሉ በፈገግታ ወደ
እሱ ዞራ።

የጡቶችዋ ጎንና ጎኖች ታዩት፡ ጫፋቸው ደግሞ ጋዋኗን ወጠር አድርጎት ተመለከተ። ሰርጓዳ እምብርቷን አይቶ ዝቅ ሲል
ደግሞ ነጭ ፓንቷን አየ የታባክ ተመለስ እንደተባለ ሁሉ እንደመርበትበት ብሎ

“ምን አልሽኝ?" አላት:

“ሴት አያቴ በወንዱ አያቴ ፍቅር እንዴት እንደወደቀች
ልንገርህ"

“እሽ በምናቸው ነው?''

በዝምታው ነው” አለችው።

“ዝምታው!” ተደንቆ አያት:

አዎ!

ዝምታው” አለችውና ቀኝ እግሯን አንዱ ወንበር
ላይ አስቀምጣ ሙሉ ለሙሉ ለስላሳ ጭኗን እያሳየችው ስታየው፡-

“አልገባኝም” አላት ግራ ትከሻውን ሰብቆ። እሷም ጠረጴዛው ላይ አስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ማዘጋጀቷን እያረጋገጠች፡-

“አዝናለሁ! እይታ እንጂ ማብራሪያ ሊገልፀው አይችልም:: ዝምታ ግን የሴት አያቴን የፍቅር ልብ ማሸነፉ እውነት ነው"
ብላው ወደ ጓዳ ገባች::

ሶራ ምክንያቷን ለመስማት ጆሮዎቹን እንዳቆመ ጠበቃት።የበሰሉና  የቆርቆሮ ምግቦችን እየደረደረች በመካከሉ ቀና ብላ አይታው፡-

“እዚህ ገባ ስትል መታጠቢያና መፀዳጃ ታገኛለህ። በኔ በኩል
አስፈላጊውን ሁሉ እዘጋጅቼ የጨረስሁ ይመስለኛል" ብላ አንድ የቲማቲም ቁራጭ በሹካዋ አንስታ ዋጠች።

ሶራ ወደ ጠቆመችው ክፍል ገብቶ ተጣጥቦ ወጣ፡

የስፔን ባህላዊ ምግብ ጃፓሾ ፒላ... ክሪም በእንቁላል ከወይን ጋር ጠረዼዛው ላይ ተደርድሯል።

“ቦና ፔቲ" አለችው ኮንችት እንብላ ለማለት በፈረንሳይኛ።

"ሳቅ ብሎ “ሜርሲ” አላት: ፈረንሳይኛ, እንግሊዘኛ መቻሏ አስተሳሰቧ በአመለካከቷ አድማስ መጨመር የሚኖረው ጠቀሜታ ታየው:: የአስተሳሰብ ብስለት ከሚያመጡ ምክንያቶች አንዱ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪ መሆንና ሌላውን ለማንበብ መቻል እንደሆነ ያውቃል።

ይህን እያሰበ የሚፈልገውን ከአነሳ በኋላ አንገቱን አቀርቅሮ ሲበላ ቆየና ቀና ሲል እሷ ሰሃን ላይ ምንም ምግብ የለም።

“አትበይም?'' አላት ወደ ምግቡ በቢላዋው እየጠቆመ፡

አይኖችቿን በልጠጥ አድርጋ አመሠግናለሁ: ደስ ሲለኝ ብዙ አልበላም" አለችው።

“ለቅርፅሽ እንዳይሆን ፈገግ ብሉ ጠቃት:

“ለዚያ ቢሆን ከልቤ ነው የምጨነቀው:"

“ለምን?”

“ቅጥነት ውበት መሆኑን ገና በመዋለ ህናት እያለሁ
ስለማውቅ" ፈገግ አለች
ጭኖቹ ላይ ያስቀመጠውን “ናፕኪን' አንስቶ አፉን እያበሰ፤

“አዎ! ሴት ልጅ ቀጠን ስትል ውበቷ ይፈካል" ሲል
አቋረጠችውና፡-

“ወንድም ቢሆን ዘርጠጥ ከሚል ከወደ ሆዱ ሰብሰብ ሲልና ትከሻው ሲሰፋ ለሴት ልጅ የደረት ላይ ዋና አመች ይሆናል" ብላ ፈገግ ስትል ሶራ ደነገጠ። ከደረቱ ይልቅ ሆዱ አብጧል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሆን
ኖር እንዴት አማረብህ?”
የሚያሰኘው ውፍረቱ ያኔ አሳፈረው፡

ሆዱ ወደ ውስጥ ሊሸልገው ሞከረ:: ህሊናው ግን “ዘገየህ”ብሎ አሾፈበት: ቅርዑን ጠላው።

መብላቱንም አቆመ።

“ምነው?” አለችው ኮንችት በመገረም እያየችው።

ምኑ?" አላት ስሜቱን ለመደበቅ እየጣረ።

“ሀሳብ የያዘህ ትመስላለህ?"

ደህና ነኝ" አለና ዘና ብሎ ቁጭ አለ።

ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ሶፋው ላይ እግሮችዋን አጣጥፋ ቁጭ ስትል ተነስቶ ወደ መታጠቢያ ክፍሉ ገባ።

ውሃውን ከፍቶ ጎረድ  ያለ  አፍንጫውን ቦግ ቦግ ያሉ
አይኖቹንን ጠይም ፊቱን ተመልክቶ ጎንበስ ብሎ ሆዱን አየው:በሁለት እጁ ሆዱን ከፍሉ የተከመረውን ትርፍ በጥላቻ ተመልከቶ
"ቆርጦ መጣል ነበር ብሎ ተመኘና ፊቱን በውሃ አበስ አበስ አድርጎ ወጣ።

“ሆዴን እንዴት ጠላሁት መሰለሽ አላት ወደ መቀመጫው እየሄደ።

“ዘገየህ” አለችው ዘና ብላ፡

“ለምኑ? አላት ፈገግ ብሎ።

“ግልፅነት ይጎድልሃል አንደ የሚያስጨንቅህ ነገር
እንደነበር ስለተረዳሁ ስጠይቅህ ደበቅኸኝ፡ አሁን ግን ሳልጠይቅህ
ነገርኸኝ... ደካማነት ነው" አለችውና፡-

“ሆድህን ግን ለምን ጠላኸው?''

“...ለዋና ስለማይመች" አላት።

“ባለህ እንኳ የምትኮራ መሆን አለብህ። ለውበትና ለጤንነት መስተካከል ሽንቃጣነት ምርጫህ ካልሆነ ለሴት ብለህ አካላዊ ለውጥ መፈለግ የለብህም: ሴት ልጅ በባህር ውስጥ ጠልቃ የፍቅር ሉል

ማውጣት በአስተሳሰብ በስለት ወይንም በሌሎች የራሷ ምክንያት
የምትፈልገውን ለመምረጥ እምትቸግር አይደለችም ግን አንድ ነገር አትጣ” ስትለው

“ምን?” አላት ፈጠን ብሎ።

"ለሴት ልጅ ቅርፅ ብቻ ወሳኝ አይደለም፡ ህሊናዊ ይዘትንም የመፈተሽ ተፈጥሮአዊ ፀጋ አላት። ብቻ የሚፈቀር ነገር አትጣ።
ይዘቱም ቅርፁም ባዶ ከሆነባት እንደ ሎጥ ሚስት ገትራህ ፊቷን ሳታዞር ትሄዳለች አለችና ራሷን ሶፋው ላይ አስተኝታ ሳቀች::
ክሊሊሊ..ሊ እያለ የሚያስተጋባው ሳቋ በውስጡ አንዳች ስሜት
ፈጠረበት:: ሳቋ የተለመደ አይነት አይደለም። ግን የሚያውቀው
እንዲያውም ሲያዳምጣቸው ስሜቱን ከሚያዝናኑት ሙዚቃዎች እንደ አንዱ ቆጠረው:

“እኔ እንደምገምተው" ብላ እግሮችዋን ፈርከክ አድርጋ
የእግሮችዋን ጣቶች በእጆችዋ ጣቶች እየደባበሰች ሳለች ነጩን ፓንት እንደገና አየው።

“በአዳምና ሔዋን ዘመን ፍቅርን የጀመረችና የሰጠች ሔዋን ናት: አዳም በእግዚአብሔር ስም ዳቦዋን ቆረሰው፤እና አብረው ተካፍለው በሉት፤ አጣጣሙት:: ከዚያን ጊዜ ወዲሆ ሴት ልጅ
በወንድ አካል ጠልቃ የፍቅር ሉል ለማውጣት የምትፈልገው አንድ
ነገር ብቻ ነው” አለችው።

“ምን?” ሲላት ኮንችት ፈገግ ብላ፦

ጊዜ አነስተኛ ጊዜ" አለችው።

“እንዳባባልሽ እንግዲህ ፍቅርን የፈጠረች ሴት ናት ማለት ነው ሲል።

“የፈጠረች የሚለውን የጀመረች ካልነው እውነተኛው  መላምት ይህ ይመስለኛል" አለችው

"ወንዶችስ?”

ወንዶችማ ሲበዛ ስሜታዊ ናችሁ: ወደ ስር ለመጥለቅና የፍቅር ሉል ለማግኘት የዋና ስልት የላችሁም:: ላይ ለላይ ያዝ ለቀቅ ማረጉን ትመርጣላችሁ: ይህ ደግሞ የተፈጥሮ ችግራችሁ ነው:
ጥልቁን የፍቅር ሉል የምትፈልጉት በሆዳችሁ እንጂ በልባችሁ
አይደለም

ሶራ ፀጥ ብሎ ማሰቡን መረጠ፡

'ውብ... ለስላሳ... አስተሳስብ በሳል. ሞልቃቃ...' እያለ ስለሷ
ሲያስብ በተከፈተው ጭኗ እንደገና አየው። ነጭ ፓንቷን…

💫ይቀጥላል💫
👍461🔥1