አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ

ከሎ ሆራ ልቡን የሰረቀችውን የሐመር ውብ ለማግኘት ብዙ መድከሙ
አልቀረም።ካርለትም ብትሆን የሐሳቡን መናወጥ
ስላጤነችና ለጥናቷም እገዛ ይኖረዋል ከሚል እምነት በመነሣት ያችን ውብ ኮረዳ ማፈላለጉ ላይ አልሰነፈችም ሻንቆና ላላ መንደር
አለመኖሯን ግን ሁለቱም በየፊናቸው አረጋግጠዋል።

እንደ ተለመደው ከሎ ሆራና ካረለት በየመንደሩ በመዞር
ለማጠናከር ሲንቀሳቀሱ፣ ከዲመካ ከተማ ወደ አምስት ኪሎ ሜትር
እራቅ ብላ ከምትገኘው ኮረብታማ መንደር ወሮ ሄዱ"ከዚያ እንደ ደረሱ ወንዶች ወደ ወንዝ፣ ሴቶችም እርሻና ማሳ ጥበቃ ሄደው ስለነበር፣ መንደሯ ውስጥ ያገኙት የሚያላዝኑ ውሾችንና አሮጊቶች
ብቻ ነበር። መሸትሸት ሲል ግን ከብትና ኗሪው ከየውሎው ወደ
መንደሯ መጠረቃቀም ጀመረ።

ይህ ትዕይንት ለካርለት እንግዳ አልነበረምና ከመንደሯ ወጣ ብለው የአካባቢውን ውበት ሲቃኙ፣ ከሎ ደንገጥ ብሎ ዓይኑን ወደ አንድ አቀጣጫ ደገነ" አንዲት ልጃገረድ ስታርስበት የዋለችበትን ሞፈርና ቀንበር ከበሬዎች ጫንቃ ስታላቅቅ፣ ከበስተኋላ ተመለከቱ"።
እግርቿ ግጥም፣ ዳሌዎ ኮራ ከወገቧ ሰርጎድ ያለችውን ኮረዳ ሁለቱም ከበስተኋላዋ በማየት ብቻ ማንነቷን አወቁ" ልጅቷ በሬዎቹን
ፈትታ ዘወር ስትል፣ ሁለቱም ዓይናቸው እሷ ላይ ነው" ኮረዳዋ አንዳችም የመደነጋገር ሁኔታ ሳታሳይ ፈገግ ብላ በዚያ ኰራ ባለው አረማመዷ ወደነሱ ሄደች"።

ከሎ ምራቁን ቶሎ ቶሎ ከማንጐራጐጭ በስተቀር የሚመለከተው ልጅቷን ነው" ካርለት ደግሞ በተመስጦ የምትከታተለው እሱን ነው"

በልጅነቷ ወንድና ሴት ተቃቅፈው አልጋ ላይ ሲተኙ የሚያደርጉትን ለማወቅና ብዙ ጊዜ ለማየት ትጓጓ ነበር" ነፍስ ካወቀች
ጊዜ ጀምሮ የምትተኛው በግል መኝታ ቤቷ ሲሆን፣ አንድ ቀን ታዲያ የናቷ ጓደኛና ባሏ በእንግድነት እቤታቸው ይመጣሉ" እንዳጋጣሚ ሆኖ ለእንግዳ የተዘጋጀው የመኝታ ከፍል ተይዞ ስለነበር እንግዶች
ካርለት መኝታ ክፍል እንዲያድሩ ተደረጉ፣ እሷ ከወላጆቿ መኝታ ቤት ካለው ትንሽ ክፍል እንድትተኛ ይደረጋል" ካርለት ግን
እንቅልፍ ከመተኛት ይልቅ አንድ ለብዙ ጊዜ ለማወቅ ትጓጓ የነበረውን ሁኔታ ለመፈጸም አሰበች" እናም፣ የቆየ የልጅነት ፍላጎቷን ለማሟላት እንግዶች እሷ ከምትተኛበት ክፍል ገብተው ከመተኛታቸው በፊት አልጋው ሥር ገብታ ተደበቀች" ባልና ሚስቱ
በመጠጥ ኃይል ሞቅ ብሏቸው ነበርና እየተሣሣቁ ተደጋግፈው ገብተው አልጋ ላይ እንደ ወጡ ተያያዙ"

ካርለት የአልጋ ላይ ጨዋታቸውን ሁሉ ልቅም አድርጋ ሰማች"ከዚያ በኋላ ሰዎቹ ሲተኙ፣ ወላጅ እናቷ ካርለት ከተኛችበት ከፍል
ልታያት ስትገባ ድንግጥ አለች ቀስ አድርጋ እጇን ልጇ አልጋ ላይ ስትጭን ጨርቅ ብቻ ሆነባት በድንጋጤ ጮኸች። አባት፣ እንግዶች
ሳይቀሩ እየተሯሯጡ ሲመጡ የለችም ቤቱ ቢታሰስ፣ ብትፈለግ
በቀላሉ ልትገኝ አልቻለችም" በጨረሻ ግን አልጋ ስር እንደ ውሻ ተጠቅልላ ተገኘች" እና ዛሬም እንደ የዛኔው እንዲታወቅባት
ስላልፈለገች የኮረዳዋንና የከሎን ሁኔታ በጥንቃቄ መከታተል ቀጠለች።

ከሎና ካርለት ከልጅቱ ጋር ፊትና ኋላ ወደ መንደሩ እንደ ደረሱ፣ከልጅቷ መኖሪያ ቤት ትይዩ ድንኳን ለመትከል እንደ ፈለገች ለከሎ
ሆራ ሆነ ብላ አማከረችው «ኢህ» ብሎ ፈቃደኛነቱን ገለጸላት ለነገሩማ እንሂድ ብትለውስ መቼ በጄ ይል ነበር።

ከሎ፣ ስለ ብዙ ነገር እንዳላወጣ እንዳላወረደ አሁን የሚፈልገውና የሚያየው ውብ ልጅ ነው  የሐመሯን ኮረዳ" አጠገቧ
ካለው ድንኳን ውስጥ ሆኖ እሩቅ ያለች ይመስል አለማት" ከሎ ሴት
አያውቅም ለማለት አይቻልም" በተለይ በገንዘብ የሚገኘውን የስሜት እርካታ በሚገባ ያውቀዋል" የሴት ጓደኛም ለመያዝ ብዙ
ሞካሮ ነበር" ግን፣ ከሙሉ ስሜቱ እንዲህ እንደ አሁኑ ነፍሱ ምንጥቅ እስክትል ወዶ አያውቅም"

ልጃገረዷ ደግሞ በሕይወቷ እንደ ወንድ ጓደኛ ግንኙነት
የጠገበችው የለም። ከሚጠይቋት ወንዶች ውስጥ ከመረጠቻቸው ጋር
ብቻ ተዝናንታለችI ዕድሜ ለሐመር ደንና ጫካ።

እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ልጃገረዷ ወላጆቿን በሥራ በመርዳት ስታገለግል ቆይታ ለምሽት ጭፈራው መሰናዳት ጀመረች"የጐረምሶችን ጩኸት እንደ ሰማች ከጓደኞቿ ጋር ለመደነስ ስትሄድ፣እነ ከሎ ተመለከቷት" አባቷ እንዳያገኛት ተጠንቅቃ አለፈች።

ልጃገረድ በኢቫንጋዲ (የምሽት ጭፈራ) መካፈሏን ባህሉ የሚፈቅድ ቢሆንም ወደ ጭፈራ ቦታ ስትሄድ ግን አባትየው ሳያይ
ሲሆን፣ ከጐረምሳ ጋር ስትዳራ ካገኘም አባት ተኵሶ ጐረምሳውን
እስከመግደል ድረስ መብት አለው" ይህ መብት እንጂ ያደርጋል ማለት ግን አይደለም። ስለዚህ፣ ለደንቡ ያህል ጭፈራውም ሆነ
ድሪያው አባት በማያየው መንግድ እንዲሆን ልጃገረዶች የራሳቸውን
ጥናቃቄ ይወስዳሉ"
በአጋጣሚ ግን እሷ ባህሉ ያደገችበት ሆነና ብትጠነቀቅም፣ አባቷ
ግን ከሌሎች የሐመር ወንዶች ለየት ያለ ነው።
በኢቫንጋዲ ጭፈራ ልጃገረዷ ኮከብ ደናሽ ስትሆን፣ የክልሉ ጎረምሶች
በፍቅር ሲያጫውቷትና ወደ ጫካ ሄድ መለስ ስትል ከሎን ግን ለዳንስ ሳትጋብዘው ቀረች። ወደ እኩለ ሌሊት አካባቢ ሲሆን የወንዶች ድምፅ ተሰማ። በመንገድ ላይ የሚያልፉ
ገበያተኞች እግረ መንገዳቸውን ለጭፈራ ሲመጡ የተለመደ ነበርና
ጨዋታው ቀጠለ። ካርለት አሁንም ክትትሏን እንደ ቀጠለች ነው" ጭፈራው ደመቀ፣ ውዝዋዚው ጦፈ፣ ከዚያ የመጨረሻው የዳንስ
ስልት ጊዜ እነ ካርለት የሚከታተሏት ኮረዳ ከአንድ መልከ መልካም ሸበላ ጋር መርፌና ክር ሆኑ ካርለት ያ ሰው ማን እንደሆነ ለመገመት ጊዜ አልፈጀባትም። መጀመሪያ እዳልነበረ እርግጠኛ ነች። ከገበያ ከተመለሱ መንገደኞች ጋር እንደ መጣ አወቀች" ደልቲና ኮረዳዋ
ወደ ጫካው ሲሠወሩ፣ ከሎና ካርለት ተፋጠጡ።

ውቢቷ ልጃገረድ ጎይቲ አንተነህ ትባላለች። በሐመርኛ ጎይቲ ማለት መንገድ ሲሆን፣ የስሟ ትርጓሜ ከመንገደኛ የተወለደች ለማለት ነው" ካርለትና ከሎ የሐመርኛ ቋንቋ አቀላጥፎ የሚናገ
ረውንና በአኗኗሩም ሆነ በአለባበሱ ሐመር የሆነው የጎይቲ ወላጅ አባት ጠዋት ከከብቶች በረት ሲመለስ፣ እንግዶች ከቤቱ ፊት ለፊት
ድንኳን ተክለው አየ አንተነህ (ጋልታምቤ) እንግዶቹን አንዳየ በጨዋ መልክ ሰላምታ ከሰጠ በኋላ፣ ጨዋታ ቢጤ ጀማመሩ።
የመጡበትን ጉዳይና ማንነታቸውን ከገለጸለት በኋላ፣ «ሸፈሮ ቡና
እንጠጣ» ብሎ፣ ወደ ቤቱ ይዟቸው ገባ።

ቡናውን ያፈላችውና የምትቀዳው ውቧ ልጃገረድ ጎይቲ አንተነህ ከአባቷ ፊት በጣም ጨዋና ረጋ ያለች ናት ካርለትና ከሎ በጣም
ጠባብ ወደ ሆነው የጎጆው በር በየተራ ገብተው ከተነጠፈው ቁርበት
ላይ እንደ ተቀመጡ፣ ጎይቲ በሾርቃ ሞልታ ሸፈሮ ቡናውን ለካርለት
አቀበለቻት ቀጥላ ለከሎ ስትሰጠው በአጋጣሚ እሷን እሷን እያየ ነበር እሷ ደግሞ ሾርቃውን የያዘ መስሏት ስትለቅለት ከመሬት
ወርዶ ተሰበረ። ሁለቱም በጣም ደነገጡ" ካርለት ድንገተኛ ሣቅ አፈናት፤ የልጃገረዷ አባትና ሌሎች ሁለቱ ሐመሮች ግን ጸጥ ብለው ሁኔታውን አረጋጉ።

ቡናው የውኃ ጥምን ስለሚከላከል ማንኛውም ሐመር በየመንደሩ
ቡና በእንስራ ተጥዶ፣ ሁለትና ከሁለት በላይ ሾርቃ ሳይጠጣ ከመንደሩ የሚርቅ የለም" አንተነህ ይመር ጎይቲ (ሴት ልጁ) ቡናውን
አጠጥታ ስትጨርስ፣ «ረሃብ፣ ችግር ከሐመር ምድር ይራቅ ከብቶች ይጥገቡ፤ ንቦች አበባ ይቅሰሙ፤ ሰማዩ ውኃ ያውረድ ፍቅር ሰላም ለሐመር ሕዝብ ቦርጆ ያውርድ አንቺም ተባረኪ የተባረh ባልና ትዳር ይስጥሽ፤ ሁላችሁም ተባረኩ» ብሎ ሸፈሮ ቡናውን ወደ አራቱም አቅጣጫና ወደ ጎይቲ፣ «ፕስስ...» አለና አማተበ።
👍171
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ከሎ ሆራ ጨርቆሉ ማዝ ሆኖ ደም፣ ወተት፣ ሥጋና ማር እየተቀለበ፣ ከሰልና ቅቤ ተቀላቅሎ ፊቱንና የተላጨውን ራሱን
ተቀብቶ፣ ከሚዜው ጋር ውሎው ጫካ ነው። ከሎ የወገኖቹን ባህላዊ
የጋብቻ ሥነ ሥርዓት ለመጀመር ምክንያቱ አንድ ነበር ፍቅር። ሥነ ሥርዓቱን እያሟላ ሲመጣ ግን፣ አዲስ ስሜት አእምሮው ማፍለቅ ጀመረ።

ወገኖቹ የሆኑት ሐመሮች በአንድ ወቅት ከማኅበረሰባቸው
አግልለውት ነበር" ያውም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ፣ እንዲሞት ተደርጎ ተጥሏል። ከሚወዳቸው ወላጆቹና እኅት ወንድሞቹ፣ ከሚያፈቅረው የፍየልና ጥጃ ጥበቃው፣ ከቦረቀበትና ከተጫወተበት ማራኪ
የሐመር ምድር ተጎትቶ ተወስዶ፣ በጦር ተወግቶ፣ ወደ ገደልም ተገፍቶ፣ የሞትን ጽዋ ጕድጓድ ውስጥ እንዲቀምስ ተደርጎ ነበር።

የሕፃንና የወጣትነት አእምሮው ይህን የደረሰበትን መራራ ጽዋ
ጠንጥኖ በገዛ አእምሮው የዛን ጊዜውን መሪ ተዋናይ ሲያስታውሰው አፉን ደም ደም ይለዋልI ልሳኑ ይዘጋበታል ሕይወቱ የላሸቀ፣ የተበላሸ እንቍላል ሆኖ ባለመጥቀሙ ተሽቀንጥሮ የተወረወረ
ይመስለዋል።

የዛኔው የቍስል ስሜት ምልክት ጥሎ ካለፈ ዓመታት ቢቈጠሩም
ሁሌም አጋጣሚውን ባስታወሰ ቍጥር ሥቃዩ ይጀምረዋል" ሞት
ጒሮሮው ላይ ቆሞ ስለታም ሰይፉን ጕሮሮው ውስጥ ሊቀረቅርበት ሲመጣ ይታየውና ይባባል፤ መሸሻ፣ መደበቂያ፣ ማምለጫ መንገድ ያጣል። ከራስ ሕሊና የሚፈጠር አስፈሪ ነገር በምን አንቀጽ
ይከሰሳል! ምን ዓይነት ጠንካራ በር ያግደዋል?

«እኮ ለምን? ምን ባደረኳቸው በእንቦቀቅላነቴ ወቅት ልሸከመው
የማልችለውን ሞትና ፍርሃት አሸከሙኝ ምን ባደረኳቸው ከእናት  ጉያ ነጥለው፣ አብሬአቸው ከምዘላቸው ጓደኞቼ ለይተው ለመከራ
ዳረጉኝ?» ባለፈው ሕይወቱ ከሎ ሆራ ራሱን በራሱ እየጠየቀ መልስ ያጣበት ጉዳይ ነው" ለብዙ ዓመታት የዕለት ተዕለት ትዕይንት ሆኖ የሚቀርበውን የቆየ ትዝታ ባስታወሰ ቍጥር የመጨረሻውን ረድፍ
ይዘው የሚደረደሩት ጥያቄዎች ከላይ የተዘረዘሩት ሲሆኑ መልሳቸው ግን ሰው ወይንም መዝገበ ቃላት ሳይመልሰው እስከ ዛሬ አብረውት ዘልቀዋል"

ከሎ ሆራ በሕይወቱ ሙሉ ያምንበት የነበረው አሁን ግን እንደ አጉም እየበነነ አልጨበጥልህ ይለው ጀምሯል" ወደ ወገኖቹ ብቻ
ሳይሆን ወደ ሐመር ምድር ለመመለስ አልሞም አያውቅም። የኖረው
እነሱን ሲረግምና ሲሸሽ ነው። አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንደ ጨረሰ በአገር አቀፍ የመሠረተ ትምህርት ዘመቻውም ወቅት፣ ከዘመቻው መቅረት ወይንም መለወጥ አልቻልህ ብሎት እንጂ እግሩንም
ለማንሣት አያስብም ነበር" የዛኔም ቢሆን ደግሞ፣ «ጌታዋን የተማመነች በግ...» እንዲሉ፣ መንግሥትን ተማምኖ እንጂ እንኳን የከፍተኛ ትምህርት ዕድሉ ሌላው ሁሉ ነገር ቢቀር ወደ ሐመር
ተመልሶ ለመምጣት አያስብም። በቆይታውም አይጥና ድመት ሆነው
ቆዩ እንጂ አልተቀራረቡም።

አሁን ግን ከሎ ሆራ አይጡም ድመቱም እሱ እንደሆነ በመቁጠር ወደ ቤቱና ወደ ባለቤቶቹ መመለስ ይከጃጅለዋል"

ከሎ ሆራ በእርግጥ አሁን ያለው ሐመር ነው" ሐመሮች በተለይም ዘመዶቹ ባዩት ቍጥር ይሳሱለታል" ወላጅ እናቱ ልክ እንደ ልጅነቱ እጆቹን እያፍተለተሉ እንባቸውን ያፈሱለታል ያላቸውንና
ቤት ያፈራውን ጎጆው ድረስ ተሸከመው ያመጡለታል፤ ከብት ለመዝለል በየዘመዶቹ ቤት ሲዞር እንደ ብርቅ ስመው አስተናግደውታል ከብት በሚዘለልበትም ወቅት ዘመዶቹ ዝግጅቱን በማሟላትና በለምለም ቅጠል መልካም ዕድልን በመመኘት አብረውት
ተጨንቀዋል ልጃገረድ ዘመዶቹም የዝምናድ ምልክት የሆነውን
ግርፋት በወኔና በፍላጎት ተገርፈውለታል።
ከሎ ሆራ ይህን ሁሉ ካመዛዘነ በኋላ ለዘመናት በአእምሮው ተቀብረው
የኖሩትን ጥያቄዎች ከመቃብራቸው እያወጣ መጣል ጀምሯል እናቱ እንደ ብርቅዬ ልጃቸው፣ ወንድምና እኅቶቹ እንደ
ተወዳጅ ወንድማቸው አድርገው ይቈጥሩታል“ ታዲያ ማንን ይጥላ?
ለሥቃዩ ሁሉ ተጠያቂው ማን ሊሆን? ለምንስ እንዲሞት አድርገው
ጣሉት?

ከሎ ሆራ አእምሮው ለጥያቄዎቹ መልስ አገኘ" ለመጣል ያበቃው ባህል ነው። እሱን ለመጉዳት፣ ከእናቱ ጉያ ለመነጠል የደፈሩት የአገር ሽማግሎች አንኳን ለሱ ከሜዳ ተነሥተው hፉ አላሰቡም”

የሐመር ሕዝብ ባህሉን አክባሪ፣ ካለ ዘመናዊ ሕግና ደምብ በባህላዊ ደምቦችና ሥርዓቶች የሚመራ፣ ተፋቅሮና ተዛዝኖ የሚኖር
ማኅበረሰብ ነው። ማንንም የማያገል፣ ባህሉን ከመከተል ዝንፍ
የማይል ሕዝብ መሆኑን አረጋግጧል። «ታዲያ ወገኖቼ በእኔ ላይ
ብቻ ልዩ ቅጣት አልፈጸሙብኝማ። ባህላዊው ደንብ መሟላት
ነበረበትና ተገደልኩ፤ ከሙትነት ተነሥቼ ስመጣ ግን ተቀበሉኝ" አሁን የተቀበሉኝ ስለ ተማርሁ፣ ከእነሱ የተለየ ሕይወት ስላየሁ አይደለም ባህሉ ስለሚፈቅድ ብቻ ነው ታዲያ ባህል ባመጣው ጦስ ወገኖቼን መጥላት አለብኝ?» ጨርቆሌ ማዝ ተብሎ ጫካ ለጫካ
የሚዞረው ከሎ ሆራ ዕድሜ ልኩን አእምሮውን ሰንገው ይዘው ያስጨንቁት የነበሩትን ጥያቄዎች መመለስ ጀመረ።
።።።።።።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣
ሰው ራሱን ማስተማር የሚችል ታላቅ ፍጡር ነው" በተለይም ታታሪ ሰዎች ከአምላክ የተሰጠውን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ
እየተጣጣሩ ናቸው። እየተሳካላቸውም ነው

በምርምር እንደ እብድ ያልለፈለፈ ፈላስፋ፣ ቀንና ሌሊት በምርምርና በሙከራ እልሁን ያልጨረሰ ሳይንቲስት፣ እንደ
ሚፈጥራቸው ገጸባሕርያት ስቅስቅ ብሎ ያላዘነ አሊያም በደስታ ያልተፍነከነከ ደራሲ፣ የሚሥለውን ሥዕል የተዋጣ ለማድረግ
ረቂቁን የተፈጥሮ ምሥጢር ለማወቅ በመጣጣር ያልዳከረ ሠዓሊ
l ሊኖር አይችልም" ካለም ከነሆድ አምላኩ ወገን የሆነ አስመሳይ መሆኑ ነው"

ካርለት የሐመር ሴቶችን ሕይወትና ማኅበራዊ ተሳትፎ የምታጠና
ወጣት አንትሮፖሎጂስት ናት ያለችበት ዘመን ሳይንስና ተክኖሎጂ የመጠቀበት፣ የሰው ልጆች በአዲስ ግኝቶች የሚንበሸበሹበት ወቅት ነው„

«እንደ ዱሮው ዘመን ይህን  ይህን ማድረግ ያስቸግራል የሚል አዳማጭም ሆነ ተመልካች አያገኝም" መሆን አለበት ብዬ ብዙ
ሞከርኩኝ ፈተናና ሥቃይም ገጠመኝ፤ በመጨረሻ ግን ተሳካልኝ ሲባል አድናቆታዊው ጭብጨባ መቅለጡን አውቃለሁ። የሰው ልጅ በውኃ ውስጥ በባቡር መጓዝ በቻለበት፣ ሕዋ ላይ ከተማ በከተመበት፣አይጥና ድመት አብረው እንዲጫወቱ በተደረገበት ወቅት እኔስ
ሰውነቴ ቢቈስል፣ የአእምሮ ጭንቀት ቢደርስብኝ፣ ብገረፍ፣ ባል ባገባ ምኑ አዲስ ነገር ነው። ከዚህስ የቀለለ የዓላማ መሥዋዕትነት ምን
ሊኖር ይችላል?» ካርለት መኝታዋ ላይ ተጋድማ የምታስበው ነበር
ካርለት ለአንድ ወር ያክል በከብት ዝላይ ወቅት የተገረፈችው ቁስል አሠቃያት ጫማ የለመደውን እግሯንም እንቅፋቱና እሾሁ
እየተተካካ አንሰፈሰፋት" እየቆየ ሲመጣ ግን ይህ ሁሉ ሥቃይ እየታገሠ፣ ቍስሉም እየደረቀ፣ እግሯም እየደነደነ መጣ ካርለት በቃን በማይሉት ማስታወሻዎቿ የየዕለት ገጠመኞቿን
እያሰፈረች፣ በካሜራዋ እይታዋን እያጠናከረች፣ በድንኳኗ አካባቢ
አገገመች ካርለት አልፈርድ ልብሶቿን በሻንጣዋ ቆልፋ፣ ቆዳዋን በመልበስ፣ በባዶ እግሯ በጨሌና አንባር አጊጣ ስትወጣ ብዙ አዲስ
👍22
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_ሦስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ከሎ ሆራ በጨርቆሌ ማዝነት በደንብ እየተቀለበ ከቆየ በኋላ ሚዜው ሰውነቱ እንደ ተመለሰ አረጋገጠ። ስለዚህ ከሎ ሆራና ሚዜው
ከተሪ (ዲክ ዲክ) ቆዳ የተተለተለ ቀበቶ መሳይና ኩርኩፋ ይዘው
በደንቡ መሠረት ጎይቲ አንተነህን በድብቅ ማሳደድ ጀመሩ።

ጎይቲ አንተነህ ከሎን አልወደደችውም እሷ ልቧ የጠፋባት ለዚያ ጀግና ለደልቲ ገልዲ ነው" መሬቱን በልበሙሉነት እየረገጠ
ሲንጐማለል፣ የሷንም ልብ እንደ ጠረማመሰው ሁሉ በፍቅር ታቃስታለች።

በኢቫንጋዲ ጭፈራ ወቅት አንዳንዴ መንደራቸው ብቅ ካለ ስሜት ቀስቃሽ የሆኑትን ሌሎቹን የዳንስ ምቶች ከሌሎች ጋር
ብትጨፍርም ጭንን በጭን የማግባቱ ጊዜ ቀድማ የምትጋብዘው እሱን ነው። ጭኑን በጭኗ ውስጥ ሲያስገባ የአእምሮዋን እንቅስቃሴ ያዛባና በቍጥጥሩ ስር ያደርጋታል" ከወገቧ ልጥጥ ብላ ወንድ ብልቱ ላይ ትለጠፍበታለች" በዚያ ወቅት ስሜት እንደ ቅቤ ይቀልጥና እሱም እሽት፣ እሷም አሽት፣ እሱም እሽት...ሲደራረጉ ይቆዩና
ሁለቱም ሲሸነፉ፣ ውጥረት ሲበዛባቸው ተያይዘው ወደ ጫካ፣ ወደ ልዩው የተፈጥሮ መኝታ ክፍል ጐራ ይላሉ“

ጫካው ውስጥ ወፎች፣ አራዊት፣ እባቦችና ሰዎችም ጭምር ፍቅራቸውን በነፃነት ይለዋወጣሉ ጫካ ውስጥ ትርዒት አቅራቢ እንጂ
ተመልካች አይኖርም። «ሁሉም ለየራሱ…» ብቻ መባባል ነው።

ጎይቲ አንተነህ ታዲያ ያ አራዊትን፣ ሰውን የገደለ ጀግና የፍቅርም ጀግና ሆኖ አግኝታዋለች" ጠምዘዝ አድርጎ በጠንካራ እጆቹ ወደ እሱ እያስጠጋ ትንፋሿ እስኪቋረጥ የሚስማትና እንደ ሕፃን ልጅ አቅፎ የሚያጫውታት ሁሉ ትዝታን ያልፈጠረባት እፎይታን ያልሰጣት ጊዜ የለም።

ከሎ ሆራ፣ ጎይቲ አንተነህን ባየ ቍጥር ከፍቅሩ ፅናት አንፃር ሰውነቱ እየተልፈሰፈሰ ቢርበተበትም ተፈቃሪዋ ግን ኵሩ ሆና ኵሩ ወንድ፣ ጅንን ጀግና፣ ስሙ የገነነ ወንድ ፈላጊ ነበረችና እሱ ለእሷ
ሲል ልብሱን አውልቆ ራቁቱን ቢሄድም፣ ሊያደርገው ያላሰበውን
እንዲያደርግ ፍቅሯ ቢያስገድደውም፣ እሷ ግን ለሱ ቁብ የማይሰማት
ሆነችበት"

የጎይቲ አንተነህ ልብ ያለው ደልቲ ገልዲ ላይ ሲሆን፣ የከሎ ሆራ ልብ የማለለው ደግሞ፣ ለጎይቲ አንተነህ ነው። ቢሆንም ከሎ
ሆራ እሷን የማግኘት ተስፋው አልጨለመበትም" እሱም ሆነ ሽያው
(ሚዜው) ከቀናቸው ጎይቲ አንተነህን ብቻዋን ሰከም ሰከም ስትል ሊያገኟት ይችላሉ።

አንድ ቀን በሬ ጠምዳ ስታርስ፣ አጥማጆቿ በርቀት ቍጥቋጦው ውስጥ ተደብቀው ሲከተሏት ዋሉ። መቼም እንደዚያን ቀን በከፊል የተመቻቸ ቀን ከዚህ በፊት አላጋጠማቸውም" በሬዎችን በጅራፍ ሸንቆጥ በማድረግ፣ ከወገቧ ወደ ጎንና ጎን ለጠጥ፣ ዳሌዎቿን ወጣ  ገባ....እያደረገች ስለ ሐመር ጀግኖች፣ ስለ ከስኬ ወንዝ፣ ስለ በልጉ ታንጐራጕራለች። አጠገቧ የአጎቷ ልጅ ብቻ ነው ያለው፤ እሱ ዘወር ካለላቸው ፈጥነው ሊይዟትና የልባቸውን ሊያደርሱ ይችላሉ " እሱ እያለ ግን ምንም መሥራት አይችሉም ጎይቲ የተዘጋጀላትን ወጥመድ በጭራሽ አላወቀችም ዝም ብላ እርሻዋን ታርሳለች። አፍቃሪዋም፣ ከዘምባባው ዙሪያ ካለው ሰንበሌጥ ውስጥ ሆኖ በገዛ ምራቁ ይታነቃል።

አጥጆቿ፣ የኦጎቷን ልጅ ቦርጆ (አምላክ) ከዚያ አካባቢ ዘወር እንዲያደርገው ይመኛሉ" የአጎቷ ልጅ ደግሞ፣ ጎይቲ አንተነህ ልጃገረድ በመሆኗ ብቻዋን ትቷት ቢሄድ ሊደርስባት የሚችለውን
አጋጣሚ አሰበ" ኋላ እሱና ሌሎች ጐረምሳ ዘመዶቿ መጠበቅ ተስኗቸው ጀግንነት፣ ሀብት ከሌለው አንዱ ቢተናኮላት የሌሎች
ልጃገረዶች ማሽሟጠጥና በጓደኞቹ «ፈሪ» ተብሎ መናቁ፣ እሱንና ዘመዶቹን ስለሚያናድዳቸው ብቻዋን ትቷት ለመሄድ አልፈለገም።
ስለዚህ አዳኞች ታዳኟን በቍጥጥር ሥር እንዳያውሉ የአጎቷ ልጅ
«ጕሮሮ አጥንት» ሆኖባቸው ሳይሳካላቸው ቀረ።

በሌላ ቀናትም ውኃ ለመቅዳት ስትሄድ፣ ገበያ ስትመላለስ ትክለ
ቁመናዋን፣ ፈገግታዋን፣ የሚነጥረውን መቀመጫዋን ቀምሶ
ያልጠገበውና እያየ በመሳሳት ላይ ያለው የመንደሯ ጐረምሳ፣ እንደ
ሴት ውሻ ከቦ ስለሚከታተላት በድብቅ ለሚከታተሏት እንቅፋት
ሆኖባቸው ሰነበተ።

ከሎ ሆራ ከሚዜው ጋር ጫካ ለጫካ ሲዞርና ጎይቲ አንተነህን  ሲከታተል ጕሮሮው ሲጮህበት ቢውልም፣ እየቆየ ግን መሰላቸት ጀመረ። ፊት ለፊት ሄዶ የደንቡን ለመፈጸም ያስብና ባህሉን ባለማክካበሩ የሚደርስበትን ውግዘትና ቅጣት እያሰበ፣ ሐሳቡን ከሕሊናው አውጥቶ ያሽቀነጥራል"

አንድ ቀን ግን፣ ጎይቲ አንተነህ ደንገዝገዝ ባለ ምሽት፣ ከቤቷ ወጥታ መንገዱን ስትነካው እነከሎ ተከተሏት" ከመንደሯ ዘወር
እንዳለች የመሮጥ ያህል እየተራመደች ወደፊት ገሰገሰች" ከሎ ሆራ፣
«የት እየሄደች ይሆን? ብቻዋን ካለፍርሃት እንዴት ትሄዳለች» በማለት ግራ ገባው ከወሮ ራቅ ብለው ካሉት መንደሮች ለመድረስ
ከመቻሏ በፊት ግን እነሱ ያቀዱትን ከመፈጸም የሚያግዳቸው የለም።

«አቤት ለስንት ጊዜ እንዳለፋን በግላጭ አገኘናት» ተባብለው
ከሎና ሚዜው ተቃቅፈው ደስታቸውን ተገላለጹና ፍጥነት ጨምረው
ለመያዝ ወደ ፊት ሽምጥ ሮጡ" እሷ ዘንድ ከመድረሳቸው በፊት ግን
ሁለቱም ሩጫቸውን ገትተው ቆሙ ከግራር ጥላው ሥር መሣሪያ የያዘና በርኮታው ላየ የተቀመጠ ሰው ያዩ መሰላቸው» አበሸቃቸው፣ ገረማቸውም፣ «ማን ይሆን?» ጠየቀ ከሎ፣ «እንጃ!» አለ ሚዜው። ስለዚህ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ወደ ቃጫው ተክል ገባ ብለው አደፈጡ። ጎይቲ አንተነህ ወደዚያ
ሰው እየቀረበች ስትሄድ እየተደነባበረች የሰካራም ጕዞ ጀመረች ሰውየው መጀመሪያ አላያትም ነበር። ዱካዋን ሲሰማ ግን
ከተቀመጠበት ፈንጠር ብሎ ተነሥቶ መሣሪያውን ሲደግን፣ ወደሱ
የምትገሰግሰው ጎይቲ አንተነህ ናት። መሣሪያውን አቃንቶ፣ እጁን ከፍቶ ጠበቃት፤ ያው እንደ ልማዱ እንደ ቀንድ የቆመው ጡቷን
ከሰውነቱ ስታሻሽለት፣ እሱም የኰራውን ዳሌዋን በሁለት እጁ ወደ
እሱ ይበልጥ እየሳበ፣ ትንፋሿ እስኪቈረጥ ድረስ ሳማት። እሷም ሆነ እሱ በተፈጠረው ሙቀት እንደ ቅቤ ቀለጡ።

ከሎ ሆራ፣ ይህን ትርዒት ራሱ እንደሚሠራ ሁሉ፣ እሱም ባለበት ደነዘዘ። ሰውነቱ ሁሉ ባለበት ሲወጣጠር ታወቀው። በእሱ ላይ የተለጠፈችበትና አቅፎ የሚስማት መሰለው። ዋና ተዋናይዎቹ ግን ወደ ዋናው እርካታ ጕዟቸው ለመሄድ አንዱ በሌላው ውስጥ ዘልቆ ሲገባ ከሎ ከሰመመኑ ነቃ። የሚወዳት ጎይቲ አንተነህ ከሱ ጋር
ሳይሆን ያለችው ከሌላ ሰው ጋር ነው። እሱ ያቀፈውና የሳመው ለካ ግንዱን ነው" እሱ ግንድ አቅፎ ሲስም፣ እሷ ሰው አቅፋ
ትቃበጣለች፣ «ዳሚት» አለ ከሎ፣ ሊቈጣጠረው በማይችለው ስሜት ተወጥሮ።

ከሎ ሆራ ሰውዬውን በደንብ ቢያስተውለውም ሊለየው
አልቻለም። ሚዜው ግን ነገረው፣ «አያ ደልቲ ገልዲ ነው» አለው።

"አዎ እሱ ነው ካለሱ እሷን እንዲህ የሚያደነባብራትና
ትንፋሿን የሚያሳጣት ወንድ የለም» በማለት፣ በእልህ ወደ ተዋጠ ሰሜት ውስጥ ገባ" ሚዜው ግን፣ ከርቀት የሚታየው ቅብጠት አፉን
አስከፍቶታል።

ፍቅረኛሞች የፍቅር ጥማቸውን ለማርካት እየደጋገሙ ሲጫወቱ ቆዩና ተለያዩ" ጎይቲ አንተነህ ወደ መንደሯ ስትመለስ ከኋላ የቀረባት ሰው እንዳለ ሁሉ ልቧ ተንጠልጥሎ አልፈጠነችም። መንደሯ
👍22🥰2
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_አራት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ደልቲ ገልዲ በካርለት ባህል አፍራሽነት ቆሽቱ አርሮ የነበረውን ያህል አሁን ግን አእምሮው መዝናናት ጀምሯል" መቼም እሱ
የያዘው ነገር መስተካከሉ የማይቀር በመሆኑ እንግዳዋ እሱን መቅረብ
ከጀመረችና ግንኙነት ካደረጉ በኋላ ብልጭልጭ ቅራቅንቦዋን አወላልቃ ጥላ ቆዳ መልበሷ፣ በባዶ እግሯ ካለ ጫማ መሄዷ፣ እንደ
ሐመር ልጃገረዶች ጸጕሯን አሳጥራ በጨሌና አምባር ማጌጥ መጀመሯ፣ እሱን ፍርሃት እንጂ ሌላ ምንም ምክንያት እንደማይኖራት ስለ ተገነዘበ ደስታ እየተሰማው፣ «ኧረ ገና ይቀራታል» ብሎ
ፎክሮባታል።

ካርለት የከሎ ሆራ ከብት ዘለላ ወቅት ከልጃገረዶች መሃል ሆና አንጋዞች ሲገርፏት ግርፊያውን ፈርታ ስትንቀጠቀጥ የነበረውንና
ከተገረፈችም በኋሳ የጮኸችውን ደልቲ ገልዲ ሰምቶ ሐፍረት
ተሰምቶቷል፣ «ባለጌ! ልጃገረድ እንዴት ለግርፋት ትንቀጠቀጣለች? ...ቆይ ብቻ ልክ ሳላገባት ከቀረሁማ እኔ አይደለሁም! እያለ ተማሮባታል"

ደልቲ ገልዲ የእንግዳዋ ልጃገረድ አቀራረብ ልቡን የሚያራራ ሆኖ ቢያገኘውም፣ የሐመር ልጃገረዶች የሚያሟሉትን ባህላዊ ደንብ
ባለማሟላቷ ግን ቅር መሰኘቱ አለቀረም" ደልቲ መቼም አንዴ ከአፉ
አውጥቶ ሊያገባት በመወሰኑ እንጂ ልቡ ያለው ከሌላ ልጃገረድ ጋር
ነው። ያችን ልጃገረድ ሊያገባትና የግሉ ሊያደርጋት ቢችል ኖሮ
መቼም በሕይወቱ ቀረኝ የሚለው ነገር ባልነበረም ነበር። ግን ልጃገረዷን ሊያገባት አይችልም" አንድ ቤተሰብ ናቸው፤ የልጅቷ
እናት የካርላ ጎሳ አባል ናት። እሱም ከዚሁ ቤተሰብ ነው። የካርላ ጎሳ የጉለትን ጎሳ ሊያገባ ይችላል" የካርላ ጎሳ የካርላን ጎሳ፣ የጉለት ጎሳ የጉለትን ጎሳ ግን ሊያገባ አይችልም" ሊጋቡ የሚችሉት ፀንጋዞች
(ባዕዳን) ብቻ ናቸው" ይህም ሆኖ ግን ደልቲ ሊያገባት ባይችልም
ሊወሽማት ይችላልI ችሏልም" ጉድ የሚፈላው ግን ባል አግብታ የሄደች እንደሆነ ነው።

ባል እንዳታገባ ደግሞ ሊያግዳት አይችልም" ይህን ላድረግ ካለ አባትየው አይቀበለውም" አባቷ ከልጁ ባል ጥሎሽ ማግኘት አለበት" ጥሎሹን ካገኘ ደግሞ የሷ ጉዳይ «ጉም መዝገን» መሆኑ ነው።
በእርግጥ ደልቲ ሌላ ባል መጥቶ ከሚወስዳት እጥፍ የሆነ ጥሎሽ ከፍሎ ሊወስዳት ይችል ነበር። ችግሩ ግን ይህ አልነበረም፤ የሱ ችግር እሷና እሱ የአንድ ጎሳ አባል በመሆናቸው ጋብቻ ሊፈጽሙ አለመቻላቸው ነው። ከሎ ሆራ ግን የጉለት ጎሳ በመሆኑና ጎይቲ
አንተነህ የካርላ ጎሳ በመሆኗ ሁለቱ ፀንጋዞች (ባዕዳን) ስለሆኑ መጋባት
ይችላሉ።

ጎይቲ አንተነህም እንደ ደልቲ ገልዲ በውኗ መቃዠቷ አልቀረም። ብዙ ወንዶች ታውቃለች፤ እንደሱ ግን ልቧን የሰረቀባት
ወንድ የለም" መጀመሪያም ቢሆን ከእሱ ጋር አካል ለአካል ከመነካካታቸው በፊት የወሮን መንደር ኗሪ እንደ አውሎ ነፋስ
በነፈሰው ወሬ የደልቲ ገልዲ ጀግንነት እየተወራ፣ ዘፈኑና ሙገሳው ሲቀልጥ፣ በዝናው በእጅጉ መጐምዠቷ አልቀረም
ከልጅነቷ ጀምሮ ከአባቷ እየሰማች ያደገችው የጀግንነት ታሪክ፣
ጀግንነት ውሎ፣ የጀግንነት ሞት ነው" ስለዚህ፣ ጀግና ትወዳለች፣ ገዳይ ታከብራለች" በየወንዙና በየእንጨት ለቀማው፣ ማንነቱን ገና ያላወቀችውን ጀግና ስም በሐመር ጫካና ተራራ ድምፅዋ እያስተጋባ
ዘፍናለታለች" ከልጃገረዶች ጋርም ገና ሳያዩት እየተሣሣቁ፣ «የኔ
ነው የኔ ነው» ተባብለው ተነታርከውበታል"

ጎይቲ አንተነህ ይህን ሰው የምትወደውና የምታደንቀው ከልቧ
ነበር። የሌሎችን ልጃገረዶች እውነተኛ ስሜት ግን አታውቅም። ያ ሰው ግን እንዲያ በቀላሉ ሊከሰትላትና ልታየው አልቻለችም"

አንድ ቀን ከሌሎች ልጃገረዶች ጋር ገበያ ውላ ስትመስ ግን ከወንዶች መሃል ሳዳጉራውን (ሽርጡን) ለብሶ፣ በላዩ ላይ ዝናር የታጠቀ፣ በአንገቱ ልጃገረዶች የሸለሙትን ጨሌ ለማስታወሻ አጥልቆ፣ ክናዱ ላይ አንባር፣ ጣቱ ላይ ደግሞ የመዳብ ቀለበት ያጠለቀ፣ ጸጕሩን በባህሉ መሠረት ተሠርቶ የሰጎን ላባ የሻጠ ሸበላ ላይ ልጃገረዶች ሲጠቋቆሙ፣ «ይእ! ምንድን ነው? ማነው?» ብላ
ጠየቀች  ጎይቲ። ልጃገረዶች «ይእ! አታውቂውም ማለት ነው? »
ተሣሣቁባት አፈረችና፣ «በቃ አላወቅሁትም ንገሩኝ» አለቻቸው
“ደለቲ ገልዲን ነው የማታውቂው? ይልቅስ አታሹፊብን» አሏት።

ያን ሁሌ የምታልመውን ሰው፣ እንዲህ እንደ ዘበት አይታው ልታልፍ፣ «እሱ ነው ለካ፣ አፈር በሆንኩት!» አለች ጎይቲ፣ ለምን
እንደዚያ እንዳለች ግን አልገባትም። «አሁን ይሄ እውነት ሰው ነው?
አቤት ውበት! አቤት ቁመና!» በማለት አፏን ከፍታ ማየቷን ቀጠለች" ጓደኞቿ እርስ በርስ እየተጨዋወቱ፣ እሷም አብራ ያለች መስሏቸው የተለመደ የወሬ ፍትፍታቸውን መጐራረስ ቀጠሉ።

«እከሌን ታውቂዋለሽ? »
«ይእ! እንዴት ነው ታውቂዋለሽ?»
«ግንኙነት አላችሁ? »
«አዎና!»
«አንችስ? »
«እኔም አዎን አውቀዋለሁ።» ይሣሣቃሉ። ደግሞ እንደገና
ሌላውን ይጠያየቃሉ። መቼም በሐመር ልጃገረዶች አንድ ላንድ ብቻ መወሰን ጥላቻንም ሊፈጥር ይችላል። የኔይቱ ቆንጆ ባትሆን ነው፣የኔው ቆንጆ ባይሆን ነው፣ ሌላው (ሌላይቱ) ያልፈለገው (ያልፈለገችው) ስለሚባባሉ መራራቅ በመሃላቸው ሊፈጠር ይችላል" በሐመር
ማኅበረሰብ ፍቅር ነፃ ጨረታ ነው" የጨረታው ዕጣ ግን በሴቷ ፍላጎት
ይወሰናል" ስለዚህ አንዲት ልጃገረድ ለብዙ ወንዶች፣ ብዙ ልጃገረዶች በአጠቃላይ ለመንደሩ ጐረምሶች ይሆኑና መቃበጥ ነው።

ጎይቲ አንተነህ ከልጃገረዶች ተለይታ ደልቲ ገልዲን እንደ
ተአምር ስትመለከት፣ ጓደኞቿን ረሳቻቸው ደልቲ ገልዲ ይህ ሁሉ ሲሆን አላያትም ነበር፤ በኋላ ግን ድንገት ዓይኑን ወርወር ሲያደርግ ዓይኗን ቀድሞ ተመለከተው አያት፤ አየችው፤ እንደገና አያት፣
እሷም አየችው። ብዙ ከቆዩ በኋላ ለሰላምታ አንገቱን አወዛወዘሳት"እሷም አጸፋውን መለሰች።

በሐመር ባህል ሰላምታ ከዕረፍት በኋላ ነው። ወዳጅም ሆነ ዘመድ
ድንገት ሲገናኝ ሮጦ አይተቃቀፍም፤ ሰላምታ አይለዋወጥም"
የሚደረገው ራቅ ራቅ ብሎ መቀጥ ወይንም መቆም ነው።ከሩቅ አካባቢ የመጣ ከሆነ እንዲያውም ካለምንም የቃል ልውውጥ ቁርቀት ይነጠፍለትና ለመቀመጫም፣ ለትራስም የሚገለገልበትን በርኮታ
ተንተርሶ ይተኛና ዕረፍት ይወስዳል። በሐመር ማኅበረሰብ መንቀዥቀዥ፣ መዘባረቅ የለም። ሁሉም የሚፈጸመው በሥርዓት ነው።

ስለዚህ እንግዳው፣ «እንደምን ናችሁ?» ይላል።
«ደህና ነን፤ እናንተስ እንደምን ናችሁ?» ይላል አባወራው ወይንም የቤተሰቡ አባል።

«ደህና ነን። ከብቶችስ ደህና ናቸው? » እንግዳው ደግሞ
ይጠይቃል።

«ደህና ናቸው። የእናንተስ?»
«ደህና ናቸው።»

«የአባካቢያችሁ ሰላምስ እንዴት ነው?»

«ደህና ነው" እናንተስ ዘንድ?»እየተባባሉ ጨዋታቸውን በሥርዓትና በእርጋታ ይቀጥላሉ እንጂ አፍ እንዳመጣ መዘላበድና
«ሲበሉ እንደላኩት» ያንንም ይህንንም ያዝ ለቀቅ ማድረግ የለም።ከዚያ በኋላ የሚበላ ይቀርብና ሚስት ለብቻዋ ወይንም ከልጆች ጋር፣ባለቤቷና እንግዳውም ለየብቻቸው ቤት ያፈራውን ይቀማምሳሉ።
👍243
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_አምስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ካርለት ቆዳ ለባሽ፣ በባዶ እግሯ ተጓዥ፣ እንጨት ለቃሚ ብትሆንም ከዓለም ሕዝብ በመንፈስ አልራቀችም" ሕይወትን እስአ ሥሯ ድረስ ጠልቀው በማየት የኳተኑና የሰው ልጅን ውድቀትና ድል፣ ሽንፈትና ግብ፣ የሕይወትን ለስሳሳና ሻካራ፣አቀበት
ቁልቁለት ጐዳና እየለዩ ሳያሳርሩ ወይም በረዶ ሳያደርጉ የቀሩት
የታታሪ ሰዎች የሕሊና ጭማቂ የሆነውን መጽሐፍ ታነባለች" አዲሳባ
ከከሉ ጋር ስድስት ጊዜ ደርሳ ስትመለስ ይዛቸው የምትመጣቸው
መጽሔቶችም በዓለም ላይ በመከናወን ላይ ያለውን የፖለቲካ የኢኮኖሚ ለውጥ እንድትገነዘብ አስተዋጽኦ ከማድረጉ ሌላ ከተለያዩ
ጣቢያዎች የሬዲዮ ፕሮግራሞችን ትከታተላለች።

ካርለት በሐመር ለጥናት ለመቆየት ያሰበችው ጊዜ ስላነሳት እንዲራዘምላት ጠይቃ የተፈቀደላት ሲሆን፣ ለዓለም የሴቶች ድርጅት
ያቀረበችው የፕሮጀክት በጀትም ተቀባይነት በማግኘቱ በጀት
ተጨምሮላታል" ይህም ከሎና ጎይቲን የእንግሊዝን አገር አንዲጎበኙ ስቲቭ የተቻለውን ሁሉ እንዲጥርላት ለመንገር አደፋፈራት ካርለት በሐመር ኑሮዋ መጽሐፍ ከማንበቡ ሌላ ሙዚቃ ማዳመጥ
የምትወድ ሲሆን ከሦስት መቶ ዓመት በፊት የኖረውን የሐይደ ሲንፎኒ፣ የጀርመናዊው የባህን የባሮክ ሙዚቃ የሞዛርትንና የቤቶ ፒያኖ ሶናታና ኮንችት ከጥንቱ ሙዚቃ የምታዳምጥ ሲሆን፣ የተለያዩ ባለ ስርቅርቅ ድምፃውያን የአገረሰብ፣ ሮክና ሮል ሙዚቃ ከማዳመ
ጧም ሌላ በዘመናዊ መንገድ በኮምፒውተር፣ በሒሳባዊ ቀመርና
በአጋጣሚ የተቀነባበሩ «አጥንት በሽ» ሙዚቃ ሰው ሠራሽ እጅ ካልገባበት የተፈጥሮ አካባቢ ሆና ስታዳምጥ እሷም እውነተኛ
ስሜት ይሰማትና እንባዋ በእርጋታ እየተንኳለለ ሲወርድ ትንሽ ወንዝ
ዳር እንዳለች ሁሉ ኮለልታው ይሰማታል። ከስሜቷ ታዳምጣለች
ትመሰጣለች ትረካለች፤ ታነባለች ወደ ታች ጠልቃ ወደ ላይ መጥቃ ትጓዛለች" ትክክኛ ስሜት ንጹሕ አየር ይፈልጋል የተፈጥሮ መዓዛና ውበትን ይሻል" የሐመር ተፈጥሮ ደግሞ ለዚህ የተፈጠረ ነው አዕዋፍ በነፃነት የሚያዜሙበት፣ ዕጽዋት ጎንበስ ቀና
የሚሉበት፣ ንጹሕ አየር እንደ ጊሽጣ የሚገመጥበት ነው የሐመር ምድር!

በዓለማችን ስንቱ ሕፃናት፣ ሴቶች፣ አሮጊቶች,በጦርነት
የእሳት ላንቃ ተጠበሱ፤ dንትና ስንት ሰው በተፈጥሮ አደጋ አለቀ ስንቱስ በረሃብ ላንቃ ተቀጠፈ አቤት ይህች ዓለም ስንት ዋይታ
ተሰማባት? ስንቱ እንባውን አፈሰሰባት? እነዚያ ሁሉ እንባዎች እስከ አሁን ብዙ ውቅያኖስና ባሕር ፈጥረዋል፤ ወደፊትም ለቁጥር የሚታክት ውቅያኖስ መፍጠራቸው አይቀሬ ነው የዘመናችን
ውጣውረድና ጠባሳ ከቶ በምን ይለካ ይሆን?

ካርለት ዋይታው፣ ለቅሶው፣ የዝናቡ ነጠብጣብ ሳይቀር ሕሊናዋን እየሰረሰሩ የሚገቡ እስኪመስላት ተመስጣ ታነባለች የሙዚቃ
ቃናዎችን ትረዳለች። አዎ ማየትማ ሁሉም ያያል መስማትማ ሁሉም ይሰማል። ሁሉም አምስት የስሜት ሕዋሳት አለው።
ብዙዎቻችን ግን አምስቱን ሕዋሶቻችንን የምንጠቀመው ለየቅል
ተናጠል ነው ጥቂቶች ብቻ አንድ አድርገው ያዩትን ይዳስሱታል ያሸቱታል፤ ይቀምሱታል፤ ይስሙታል።
ካርለትና ከሎ ሆራ የታደሉት ይህን ጸጋ ነው" የሚፈልጉትን ነገር በመላ ሕዋስ መፈተሽ፣ በሥራ መበርታት፣ ለዓላማ ስኬት
መሞት፣ ያሰቡትን ከፍጻሜ ማድረስ መቻልን ከልምድ ተማሩ።

ስለዚህ ሲጀምሩት ራሳቸውን የወቀራቸው ጭንቀት በአእምሮ ፈውስ
ተተካ። ዛሬ ዛሬ ከነበሩበት ይልቅ እየፈሩ የገቡበት ሕይወት ጥልቅና እውነተኛ ነው። ካርለት የደልቲ ገልዲ ሚስት ሆና ለመገረፍ፣
በእንብርክኳ ትንባሆ ለማቀበል፣ ሸፈሮ ቡና ለማፍላት፣ የከብት አዛባ
ለመዛቅ ቸኩላለች። ካርለት አሁን የእውነተኛ አንትሮፖሎጂስትነት
ስሜት እየተሰማት፣ ራሷን በራሷ የማትደልል፣ ከሕሊና ወቀሳ የራቀችና ከአምላክ የተሰጠውን ጸጋ የተላበሰች ናት። ሁሉን ለማወቅ፣
ከባዱን ለመሞከር መቻሏን ፈትናለች ከእንግዲህ በዚህ ውድድሯ አሸንፋ ለመውጣት ከቻለች፣ «ለመሆኑ በማሸነፍሽ ለምን ደስ አለሽ?» ተብላ ብትጠየቅ መልሷ፣ «ምክንያቱም ውድድሩ አስቸጋሪ ስለሆነ ነው» ብላ መመለሷ አይቀርም" ማሸነፍ የሚያረካው ደግሞ
የውድድሩ ውጣ ውረድ ሲበዛና ተወዳዳሪዎችም ጠንክረው ሲገኙ ነው።

«በሕይወት ውድድር ላይ ያለ ሰው ውድድሩ ከራሱ ጋር እንጂ በምድራችን ያሉትን ቢሊዮን ሕዝቦች በማሰብ መሆን የለበትም"
ይህን ካሰበ ግን በጭንቀት ብቻ ተደናቅፎ ይወድቃል» በማለት ካርለት ከሎን ደጋግማ መክራዋለች።

ደልቲ ገልዲ ካርለትን ለማግባት ኮይታው በሽማግሎች እንዲወሰን አስደረገ። ጥሎሹ ብዙም ከባድ አልነበረም፤ ቢያንስ
አራትና አምስት ዓመት በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ከፍሎ ሊጨርስና
እንግዳዋን የራሱ አድርጎ ያኔ በሚያውቀው ባህላዊ ደንብ ደህና አድርጎ ይገራታል።

ካርለት አሸዋማና ገላጣ ስፍራ ላይ፣ ዙሪያውን የፌጦ፣ የኩንኩሮ፣ የጠዬ የዝግባና ዋንዛ ዛፍና የሻንቆ መንደር ባለበት
የኢቫንጋዲ ጭፈራ ቦታ ከደልቲ ገልዲ ጋር ሲጨፍሩ በተለይም ወደ ጫካ ሲገቡ የምታወልቀው የውስጥ ሱሪ፣ ወደ ላይ ከፍ አድርጋ
የምትገልበው ልብስ፣ አሁን የላትም። የውስጥ ሱሪዋም ሆነ ልብሷ ቆዳዋ ነው፤ በውኃ መታጠቧን አቍማለች፤ ጸጕሯን በቅቤ የተለወሰ አፈር ትቀባለች። ይህን በማድረጓ የደረሰባት የጤና ችግር የለም"
በእርግጥ መጀመሪያ አካባቢ ቆዳዋ ለብ ለብ የተደረገ ለጋ ስጋ ጥብስ፣ ቀጥሎ ተዘልዝሎ የደረቀ ቋንጣ መስሉ ጠቁሮ ታይቷል።በተረፈ የቈሰለው ሁሉ ድኖላት፣ ወዟ እንደ ሐመር ልጃገረዶች ነው፤
ሕሊናዋም ደስተኛ ነው።

ደልቲ ገልዲ ግን አሁንም ብዙ የምታስተካክለው እንዳለ ያምናል" ያ ደግሞ የሚሆነው እሱ እሷን አጠቃሉ የራሱ ካደረገ
በኋላ ነው። ስለሆነም ጥሎሹን በቶሎ ለመጀመር ወስኗል።

በመካከሉ ግን፣ ከሎና ካርለት ከተመካከሩ በኋላ ከሎ ሆራ ደልቲ ገልዲ ዘንድ ሄደ። ደልቲ ገልዲ፥ ከሎ ሆራ የሱ ፍቅረኛ የሆነችውን
ጎይቲ አንተነህን ለማግባት የተሪ ቆዳ አጋድሞ፣ ኩርኩፋ
አጉርሷታል። ስታስደንሰው፣ ስታዝናናው የነበረችውን ፍቅረኛውን ሊነጥቀው ነው። ደልቲ ገልዲ እሷን ሊያጣ በመቃረቡ ልቡ እየዘለለ
ፈርጦበታል። ከከሎ ሆራ ጋር ግን ነገር የለውም። ከሎ ሆራ ሐመር ነው። በሐመርነቱም ብቻ ሳይሆን ባህላዊ ሥርዓቱንና ደንቡን
አሟልቶ እጮኛውን ለመምረጥ ዞሮ ጎይቲን መርጧል። ይህ መብት
የመላው ሐመር ማኅበረሰብ መብት ነው፣ «ፍቅረኛዬን ቀማኸኝ
እገላለሁ፤ እታነቃለሁ» እያሉ ማላዘን ንክ ያሰኛል" ጀርባን
ግርፋት፣ የበረት ከብትን ለጥፋት ይዳርጋል። በማኅበረሰቡ ትልቁ
ኃይል ያለው በዚያው በማኅበረሰቡ እጅ ነው። መሣሪያና ጕልበት
ያለው ጀግና የሚባለውም የማኅበረሰቡን ባህልና ደንብ ሲያከብር ነው። ካለበለዚያ ግን በኃይል የሚያምን ልብ እንደ ጌሾ በማኅበረሰቡ እጅ ይወቀጣል። «ከባሕር የወጣ ዓሣ» ይሆናል። ስለዚህ፣ ከሎ ደልቲ ገልዲ ዘንድ ሲሄድ በፍቅር ተቀበለውና ሲጨዋወቱ ቆዩ።በዚህ መልክ ትንሽ እንደ ቆዩ ከሎ ሆራ ወደ መጣበት ርዕሰ ጉዳይ
ተመለሰና፣ «...እንግዳዋ ለብዙ ጊዜ እዚህ አትቆይም። ከተወሰነ
ጊዜ ቆይታ በኋላ ትመለሳለች። ስለዚህ አንተን በቅርቡ ልታገባህና
ልታገለግልህ ትፈልጋለች» አለው፣ ከሎ።

«ይእ! ጥሎሹን ገና ሳልጀምር፤ እንዴት ሆኖ ይሆናል? መቆየት አለባት እንጂ። ደግሞስ የኔ ሚስት መሆን ከፈለገች የት ነው
የምትሄደው? እኔስ ይህን እፈቅድላታለሁ? የትም አትሄድም። እዚሁ ሥራ ትሠራለች» አለ ደልቲ።
👍18👎1👏1😁1
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ጎይቲ አንተነህ ከሎ ሆራ አጎት ቤት እንደ መጣች ፈጽሞ መንፈሷ ሊረጋጋላት ባለመቻሉ ካርለት የምታደርገውን አጣች" ጎይቲ ጽጕሯን ስትላጭ ካርለት ብቸኝነት እንዳይሰማት አብራት ተላጨች በከሰልና በቅቤ የተለወሰውንም ቅባት መላ ሰውነቷን ስትቀባ ካርለትም አብራት ተቀባች"

ጎይቲ አንተነህና ካርለት አልፈርድ ቆጥ ላይ ከተደበቁ በኋላ ካርለት ጎይቲን ለማጽናናትና ለማደፋፈር ብትጣጣርም አልሳካልሽ አላት ጎይቲ እንዲያውም ፊቷን ወደ ሌላ አቅጣጫ አዞረችባት
ካርለት ሁኔታው አስደንጋጭ መሆኑን ብታውቅም ሦስት ወር  እስኪሞላቸው ድረስ ቆጡ ላይ መቆየት ነበረባቸውና እስከዚያ ድረስ
በመካከላቸው እርቀ ሰላም እንደሚወርድ ተመኘች"

ቀኑንና ምሽቱን ቆጥ ላይ ከቆዩ በኋላ ለአንድ አፍታ ወረድ ብለው ከሎ ከመምጣቱ በፊት ለመናፈስ ወጡ" ጎይቲ አነተነህ ቆጥ ላይ መውጣቱ አልዋጥልሽ ብሏታል።

«አሁን እሱ የወንድ ልብ አግኝቶ እኔን ሊመታኝ? በየትኛው ወኔውና ጀግንነቱ፤ ወይ ሲያየኝ እሱ ራሱ ባልተርበተበተ አይደል?
ወይኔ ጎይቲ የወንድ ልጅ ዱላም ይናፍቃል ለካ?» አለች ለካርለት ይሁን ለማን እንደተናገረች ሳይታወቅ።

ወደ ጎጇቸው ሲመለሱ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ከከሎ ሆራ ጋር ፊት ለፊት ተገናኙ" ከሎ ሆራ ሁለቱንም ሲያይ ደንገጥ ብሎ ቆመ!
ካርለት በዓይኗ ጠቅሳ እንዲመታት ልትነግረው ፈልጋ ነበር። ለእሱ
«ና ምታት» ብላ በዓይን ለማመልከት እንዴት እንደምታደርግ ስከታስብ ግን እሱ ከቆመበት ደረሱ። ከሎ ሆራ መንገዱን ለቆ
አሳለፋቸው። ካለፉ በኋላ ግን ተሰማው፤ በባህሉ መሠረት እንዳያት ደህና አድርጎ መግረፍ ነበረበት። ያን ሲያስብ የብሽቀት ስሜት ታየበት፤ ጎይቲ አንተነህን ይወዳታል፣ ባህሉንም ያከብራል
ቅሬታና ቂም የሚይዝ ከሆነ አካል በማይጎድልበት መንገድ መምታቱ
የሚያመጣው ችግር የለም።

«ወደፊት ግን ይህን ጥፋት መድገም የለብኝም" በመምታቴ ጎይቲ አንተነህን የሚሰማት ነገር የለም። እንዲያውም እሷን ባለመደብደቤ ቅሬታ ሊያድርባት ይችል ይሆናል» እያለ፣ ራሱን ወቅሷል"
ካርለትም በበኩሏ ትንሽ በሽቋታል። ከሎ ሆራ ጎይቲ አንተነህን ፊት ለፊት ባገኛት ጊዜ ሁሉ እንዲገርፋት ተመካክረዋል። ጎይቲ
አንተነህ ደግሞ የከሎን የፍቅር ፍርሃት ባለመረዳት ሲርበተበት ስታየው ባሕርይው ያስጠላታል። ከሎ ወንድ ወንድ አልሸትሽ
ብሏታል። «ከሎ ትክክል አልሠራም። እሱ ጎይቲን ልክ ከተማ እንዳየው
ብዙ ሕይወቱን እንዳሳለፈበት በጠባይ ሊያግባባት፣ ሊያቀርባት
ፍቅሩን ሊገልጽላት ይፈልጋል" ጎይቲ ግን ወንድ ልጅ በቅድሚያ የምትፈልገው ኰስታራነት ነው ኵሩ ወንድ፣ ሸንቆጥ የሚያደርግ ወንድ፣ እሷን በፍቅር ገርቶ፣ በፍቅር አብሯት መጋለብ ይችላል
ሴት ልጅ ዱላ ሲያርፍባት የሴትነት ፍላጎቷ ከአሸለበበት ይቃል»
አምጭ አምጭ የሚላት፣ ፍቅር የሚናፍቃት፣ ድሪያ የሚታወሳት ያኔ ነው፤ ከሎ ደግሞ ይህን አልተረዳውም። እንግዳ ነገር ሆኖበታል ሕጉን እያወቀ በተግባር ግን አያከብርም። ይህ ደግሞ ስሕተቱ ነው ካርለት በእንግሊዝኛ ለጎይቲ ነገረቻት። ጎይቲ አንተነህ ግን ያለችው  በጭራሽ አልገባትም እንግሊዝኛ ደግሞ የት አውቃ

ጎይቲ አንተነህ አጠገቧ ያለችው ቀውስ ብቻዋን ስትለፈልፍ ብትደነቅም፣ እሷም ተመሳሳዩን ፈጸመች።

«ይኸዋ ይህ ቦቅቧቃ! እንኳንስ ሲያየኝ እንደ ወንዶቹ ሊገርፈ
ይቅርና መንገድ ለቆ አሳለፈኝ" ባል እኔ ነኛ! እሱ ሚስት ነው እንዴት ሆኜ ከዚህ ሴት ጋር እኖራለሁ? ምነው ያን ቀን ደልቲ
ገልዲን ብዬ ባልሄድሁ ኖሮ፤ እሱን ብዬ በመሄዴ ቀናው እንጂ የታባቱ ያገኘኝ ነበር ይህ ሴት" ሴት ልጅ የባሏ ዱላ ሕይወቷ ፍቅሯ ነው" ታዲያ ይህ ሰው እኔንኮ ሕይወቴን እያጠፋ ነው" እሽ
የኔስ ነገር ይቅር ነገር ግን የሚወለዱት የሁለት ሴት ልጆች መባላቸው አይደል? ወይኔ ያልታደሉት" ወይኔ ወይኔ» እያለች፣ እንባዋ
ታወርደው ጀመር"
ካርለት ትንሿን ቴፕ ከፍታ የምትለውን እየቀዳች በማስታወሻ ደግሞ የሚሰማትን ትከትባለች» ካርለት በአንዳንድ ሁኔታ ላይ እሷም ራሷ እየተስማማች መጣች» በአገሯም፣ አንዳንድ እውቅ ሴቶች ስለ ወንድ ፍቅረኛቸውና ከእሱ ስለሚጠብቁት ባሕርይ ሲያወሱ ነካ አድርገው የሚያልፉት ነገር አለ፣ «ከፍቅረኛዩ ጋር ስንላፋ
ስንታገል፣ የፍቅር ዱላ ገላዬ ላይ ሲያርፍ ልቤ እስኪጠፋ ድረስ ራሴን እሰጠውና የሱን ደግሞ ለመውሰድ ሙሉ ፍላጎት አሳያለሁ ከዚያ በኋላ የምንሠራው የፍቅር ጨዋታ ሁሉ እንደ አይስhሬም እየጣፈጠኝ፣ መላ አካሌ ከጸጕር እስከ እግር ጥፍሬ በርካታ
ሲንበሸበሽ ይሰማኛል" እንደዚህ አድርገው ከኔ ጋር የተጫወቱ ወዶች የፍቅር ዙፋኑን ማንም ሊነጥቃቸው አይችልም» ብለው
የተለያዩ ሴቶች አስተያየት ሲሰጡ ሰምታለች።

እሷም ቢሆን አንዳንድ ልምዶችን አሳልፋለች" አንድ ጊዜ፣ ስሜ ጃክ ነው ብሎ የተዋወቃት አሜሪካዊ፣ ማንችስተር ውስጥ
ለጉዳይ መጥቶ አንድ የምሽት ዳንስ ላይ ይተዋወቃሉ“ ካርለት
በእርግጥ ወደ ዳንሱ ቦታ የሄደችው ከወንድ ጓደኛዋ ከዴቪድ ጋር ነው ታዲያ አሜሪካዊው አንድ ሁለት ጊዜ በትእዛዝ መልክ ዳንስ
ጋበዛትና ሰውነቷን በጠንካራ እጆቹ ጠበቅ አድርጎ እያሸ፣
አሳመማት። ቀደም ብላ ባሳለፈችው ሕይወቷ ወንዶች እንደዚያ ሰው
አድርገዋት አያውቁም" ሰውነቷን የሚደባብሱት ቀስና ላላ አድርገው
ነው። ሰውዬው ግን መሞረዱ አንሶ በረጅም እጁ መቀመጫዋን ደህና አድርጎ ቸብ ቸብ አደረገላት «ተው» ማለት እየፈለገች፣ ቃሉ ግን
ከጕሮሮዋ አልወጣልሽ አላት" በእርግጥ፣ ዴቪድም ከሌላ ሴት ጋር እየደነሰ ስለነበር እነሱን ልብ አላላቸውም።

አሜሪካዊው ፍጹም በማታውቀው መንገድ ሰውነቷን እየመታ፣ እየሞረደ፣ ልቧን ስልቱን አስቀየረው ከንፈሯን እንኳን
ሲስማት የንከሻ ያህል ሆኖባት እግሯን አንሥታ ለመጮህ ትንሽ ቀርቷት ነበር ግን አልጮኸችም" ዳንሱ አብቅቶ ሲለያዩ ካለልብ ወደ ቦታዋ ተመለሰች እንደ ምንም ታግሣ ሁለት ጨዋታዎችን
አሳልፋ ልቧን ወደ ቦታው ለመመለስ ወደ አሜሪካዊው ሰው ሄደች።
ቆንጅት እንደምትመጪ አውቅ ነበር...» ብሎ አሜሪካዊው ተመጻድቆባታል" ግን ፊቷን አዙራ አልተመለሰችም፤ ተመልሳ ካቴና እጆቹ መሃል ወደቀች ሞራርዶ፤ ቸባችቦ፤ ብድግ አድርጎ ተሸክሟት ወደ አንድ ክፍል ሲገባ፣ እግሮቿ አልተፈራገጡም"
እጆቿ አልተወራጩም፤ አፏም አልቀባጠረም።

ካርለት ይህንን አሜሪካዊ እስከ አሁን ድረስ በዚያች ለሰዓታት ብቻ በዘለቀች የፍቅር ጨዋታ የማትረሳው ትዝታ አስታቅፏት ነግዷላ" ያንን ሰው ለብዙ ጊዜ የተካው ወንድ አልነበረም። ኖራ ኖራ ግን ሐመር ላይ ተመሳሳዩን አገኘች" የሷም ብቻ ሳይሆን የጎይቲም የሆነው ሰው በእርግጥ ለየት ያለ በመሆኑ ሳይወዱ በግድ ሌላ ወንድ ቢያስንቃቸው አይፈረድባቸውም"
ካርለት ቆጥ ላይ እንዳሉ እንዲህ በሐሳብ ተዘፍቃ ቆየችና እናቷ ትዝአሏት" ስለዚህ፣ ደብዳቤ ለመጻፍ ብዕርና ወረቀቷን
አስተካከለችና መጻፍ ጀመረች።

ውድ እናቴ፣

ምን ጊዜም እንደማፈቅርሽ፤ እንደማልምሽ የምትዘነጊ
👍23🤔1
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ከሎ ሆራ ጥሩ ጥሩ የባራዝ አርጩሜ ይዞ እሱና ጎይቲ በሚዞሩበት መንደር ሲጓዙ በየምክንያቱ ጎይቲ አንተነህን በአርጩሜ
ይገርፋታል” ለሽንት ስትቆም ለምን ቆምሽ፣ እንቅፋት ሲመታት ለምን መታሽ፣ ደክሟት ቁጭ ስትል ለምን ቁጭ አልሽ እያለ
በየምክንያቱ እንዲገርፍ ባህሉ ያስገድዳል" ሴት ልጅ በኋላ ከቁጥጥር ውጭ ሆና እንዳታስቸግር፣ ባሏ እየገረፈ በማሽቆጥቆጥ ቅን ታዛዥ ሽር ያለች አገልጋይ እንድትሆን ያደርጋል"

ካርለት አልፈርድ ማስታወሻ፣ ካሜራ፣ ድንኳኗን በጨርቅ
ከረጢት ይዛ፣ የፍየል ቆዳዋን በመልበስ አብራቸው እየተጓዘች ከሎ
ጎይቲ የሚያደርጉትን ትቃኛለች የከሎ ዘመዶች ለከሎ የሚያደርጉለትን ስጦታም ትመለከታለች"

ከሎ ሆራ እናቱ ዘንድ ስጦታ ለመቀበል ላላ መንደር ሲሄድ፣ ካርለት እጅግ በጣም አዘነች" ከሎም በጣም ተሰማው። እናትዬዋ
እንዳዩት አቅፈው፣ አንገቱን ሲያሻሹ ቆዩና ካርለትና ሚስቱን ሰላም ብለው ትክዝ ብለው ቁጭ አሉ" ለልጃቸው ምን እንደሚያደርጉለት ጨነቃቸው። ለሱ ስጦታ ያዘጋጁለት መካከለኛ መጠን ያለው ሁለት
ቅል ቅቤና አንድ ቅል ማር ብቻ ነው ከሎ የእናቱን ሁኔታ አይቶ ኃዘን ተሰምቶት ዘወር ሲል፣ ካርለት ተጠጋቻቸው"

«ለምን ያለቅሳሉ?» አለች ትንሽ ዐረፍ ካለች በኋላ።

«ይእ! ልጄ የሚያስፈልገውን ያህል ስጦታ አላገኘማ።»

«እርስዎ ለልጅዎ የሚሰጡት ከብት፣ ፍየል... የለዎትም?»

«የለኝም»

«ለምን?»

«ይእ! እኔ ከብት፣ ፍየል... ኖሮኝም አያውቅም ወደፊትም አይኖረኝም" በልጃገረድነቴ ከብቶች፣ ፍየሎች፣ በጎች የአባቴ
ነበሩ" ባል ሳገባ ደግሞ፣ የባሌ ነበሩ። አሁን ባሌ ሞቷል፤ የከሎ አባት ቢኖር ለልጄ ብዙ ሀብት ይሰጠው ነበር።»

«የባልዎትን ሀብት አልወረሱም?

ይእ! ሚስት እንዴት የባሏን ሀብት ትወርሳለች? ባሏ ሲሞት ለወንድሙ በውርስ ትተላለፍና ወንድሙ ሌላውን ሀብት እንደ ወረሰ
እሷንም ይወርሳል። እኔም፣ ለባሌ ታናሽ ወንድም እያገለገልኩ እኖራለሁ"» አሁንም ባልቴቷ ፍዝዝ እንዳሉ ናቸው"

«ባልዎ የሞቱ ጊዜ መቼም እንዳሁኑ የበለተቱ አይመስለኝም፤ከታናሽ ወንድምየው ጋር ይቃበጡ ነበር?»

«ይ..እ ይሄማ ይጠየቃል፤ ባሌ እያለም ቢሆን ከታናሽ
ወንድምየው ጋር እንጨዋወታለን። እንዲያውም ከሎን የወለድኩት ከሆራ ሼላ ታናሽ ወንድም ነው።» ባልቴቷ ፈርጠም አሉ፣ የሞጨሞጨውን አይናቸውን ወደ ካርለት እየመለሱ።

«ምን? ማለቴ የከሎ ወላጅ አባት ሆራ ሼላ አይደለም ነው የሚሉኝ? የሚጠራው እኮ ከሎ ሆራ ተብሎ ነው።» ካርለት መልሱን ለመስማት ጓጓች።

«ይ..እ! በኛ ባህል አንድ ሴት ከባሏ ታናሽ ወንድም ልጅ ብትወልድ የልጇ አባት የሚሆነው ባሏ ነው። ባሏ እንኳ ሞቶ ከሌላ ወንድ ብትወልድ የልጇ አባት ስም በሟቹ ባሏ ስም ነው
ሚሆነው;»

«እና የከሎ እውነተኛ ወላጅ አባት በሕይወት አለ?»

«አዎን አለ።»

«አሁን እርስዎን የሚጦርዎ ማነው? »

«እሱና ልጆቼ።» ካርለት ይህ ለሷ እስከ አሁን ያልሰማችው አዲስ ነገር ነው" ከሎ ሆራም ስለ ወላጅ አባቱ የሚያውቅ አልመሰላትም" ምክንያቱም የግል ታሪኩን ሲነግራት አባቴ ሞቷል ብሎ ነበር።
ካርለት ወደ ከሎ ሄዳ ጉዳዩን ስትነግረው በጣም ተገረመ። ይህን ምሥጢር እሱ ቀደም ብሎ አያውቅም። ወደፊትም ለማወቅ የሚችል
አልመሰለውም።

«ካርለት አሁን የምትነግሪኝ ሁሉ ለኔ አዲስ ነገር ነውኮ፤
በጥረትሽ ወላጅ አባቴን እንዳውቅና እንዳገኝ እያደረግሽኝ እኮ ነው»
አላት ከሎ።

ካርለት፣ «ምንም አይደለም፣ ይልቁንስ አባትክን ማግኘ;
ይኖርብናል» አለችው።
።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።
ጂሚ ሼላ ብዙ አላረጀም።  ሰውነቱ ስላለው ጠንካራ ቢሆንም ዕድሜውን ከ60 በላይ ነው። ካርለትና ከሎ ሆራ እሱ ዘንድ ሲመጡ ከጎጆው ፊት ለፊት በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ፀሐይ እየሞቀ አገኙት። ካርለት ጂሚን ስታየው ደንገጥ ብላ ከሎን ዞራ አየችው ከሎ ሆራና ጂሚ ሼላ በጣም ይመሳሰላሉ። ካርለት ጂሚን እንዳየች
ከሎ ሆራ አርጅቶ ከፊት ለፊት የተቀመጠ መስሏት ነበር"

ጂሚ ሼላ ከሎ ሆራን ለመጠየቅ ሻንቆ መንደር ሄዶ ሳለ ካርለትን
አይቷታል። ስለዚህ እንዳያቸው አወቃቸው" እነሱም ሄደው አጠገቡ
ቁጭ አሉና በሐመር ባህል መሠረት ዕረፍት ከወሰዱ በኋላ፣

«እንዴት ነዎት?» አሉት።

«ደህና ነኝ" እናንተስ እንዴት ናችሁ?» አለ ጂሚ ሼላ።

«ከሎ ለእርስዎ ምንዎ ነው?»

«የወንድሜ ልጅ ነው"» ጂሚ ካርለትን በተመስጦ
ተመለከታት።

«መልኩ ግን ቁርጥ እርስዎን ነው የሚመስለው?»

«ሆራ ሼላና እኔም እንመሳሰል ነበር እኮ።»

«ከሎ የእርስዎ ልጅ እንደሆነ ሰምቻለሁ" እንዴት ነው?»

ካርለት ዋናው ነጥብ ላይ ዘላ ጥቡልቅ አለች።

«እንዴት ተደርጎ?» ጂሚ ሼላ መልሶ ጠየቃት"

«እርስዎ ከከሎ እናት ጋር... ያረጉ አልነበረም? »

«ያማ ባህል ነው።»

«እና እንዴት ከሎ የማን ልጅ እንደሆነ ያጡታል?»

«ይሕ! በሐመር ባህል ልጅ ከወንድም ተወለደም፣ ከውሽማ በአባትነት የሚታወቀው ባል ነው። እኔም ከከሎ እናት ጋር ወንድሜ እያለም ሆነ፣ ከዚያን ወዲህ ግንኙነት ቢኖረኝም ከሎ ከማንኛችን
እንደ ተወለደ የምታውቀው እናቱ ብቻ ናት"»

ካርለት ነገሩ ገባት። «በሐመር ማኅበረሰብ የልጇን ትክክለኛ ወላጅ አባት የምታውቀው እናት ብቻ ናት ለካ!» ብላ፣ ተደንቃ
ቆየችና፣ «ለምን ስምዎ ጂሚ ተባለ?» አለችው፣ ጂሚ ሼላን።

«አንድ ጂሚ የሚባል ፈረንጅ እዚህ መጥቶ፣ ከአባቴ ጋር ተዋውቆ ነበር። እንዳጋጣሚ እናቴ እሱ ከዚህ ሳይሄድ እኔን ወለደችኝ በሐመር ባህል እንግዳ መጥቶ በአጋጣሚ ልጅ ቢወለድ ስሙ
በዚያው ሰው ስም ነው የሚጠራው።»

ካርለት ነገሩ ወዲያው ገባት" ምክንያቱም በዚህ መልክ በሷ ስም የሚጠሩ ሁለት ሕፃናት ታውቃለች
«የከሎ ሆራ እናት፣ የከሎን ትክክለኛ አባት ጠይቄያቸው እርስዎ እንደሆኑ ነገሩኝ» ስትለው፣ ጂሚ ምንም መልስ ሳይሰጣት ከሎ
ሆራን ዓይን ዓይኑን ሲያይ ቆየና እጁን ጎተት አድርጎ ያዘው" ከሎ የወላጅ አባቱ ጣቶች እጁን ሲነኩት፣ ደስታ አይሉት ኃዘን ቅጡ የጠፋ ስሜት በመላ አካሉ ተስለከለከበት" ትንሽ ቆይተው አባትና
ልጅ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ተቃቀፉ። የወላጅና ልጅ ፍቅር
በመካከላቸው ታየ ካርለትም የደስታ እንባ አነባች የሐመር ፀሐይ
ግን ወደ መሠወሪያዋ ወደቀች"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ከሎ ሆራ በፈቃድ ከዩኒቨርሲቲው በተገለለ በሁለተኛ ዓመቱ
ትምህርቱን ለማጠናቀቅ አዲስ አበባ ሄደ። ከሎ አዲሳባ ዩኒቨርሲቲ
ገብቶ ትምህርቱን ከጀመረ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ለስቲቭ ደወለለት። ቀጠሮ ተሰጣጡና እሑድ ዕለት ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ከሎ
ከስቲቭ ቀድሞ በቀጠሮው ቦታ ተገኘ። ስቲቭ ልክ በሰዓቱ ሲገባ፣ከሎ ገና ከበሩ ወደ ቀኝ ሲታጠፍ ተመለከተው። ስቲቭ፣ የሆነ ፖስታ ይዞ የመሮጥ ያህል ሲራመድ፣ ከሆቴሉ ማዕዘን ላይ ካለው ሶፋ ላይ ነጫጭ ጥርሶቹን የሚያብለጨልጨውን ከሎን ተመለከተው። ስቲቭ
በማስብበት ወቅት ላገኝህ በመቻሌ በጣም ተደስቻለሁ» አለ ስቲቭ፣
የፈገግታውን መጠን እየጨመረ።
👍34🥰2
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_ስሞንት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ካርለት የሁለት ዓመት ከሦስት ወር የሥራ ፈቃዷን ልትጨርስ የቀራት አንድ ሳምንት ብቻ ነው ከዚህ በፊት ከአንድም ሁለት ጊዜ፡
የጥናት ፈቃዷን አራዝማለች" ዘመናዊው ሕይወቷን በመዘንጋት ለሐመሩ ንጹሕ ሕይወት ረክታለች" ዛሬ የሐመር ሕዝብ ለሷ የለንደን
ሕዝብ ነው።
ከእንግዲህ ወዲያ ካርለት ኢትዮጵያዊት ነች" ለንደን
የሥጋ ዘመዶቿ፣ ሐመር ደግሞ የመንፈስ ወዳጆቿ የሚገኙበት ነው" በዚህ ቀን ካርለት ከከሎ ጋር ስለ ማኅበረሰቡ የወደፊት ዕጣ
ተነጋግረው ነበርu ካርለት፣ «ሐመሮች በእርግጥ የሚያውቁት ራሳቸውን ነው ከነሱ ውጭ ያለው ዓለም ምን እንደሚመስል
አያውቁም። ይሁን እንጂ ከዓለማችን ውጭ በራሳቸው ደሴት
ተጠልለው ዝንተ ዓለም መኖር አይችሉም" ተወደደም ተጠላ
በክልላቸው ሳይንስ የፈጠራቸው ተሽከርካሪዎችና በራሪዎች
ያልፋሉ። ስለ እነሱ ሌላው ሲያውቅ፣ እነሱም ስለ ሌላው ለማወቅ መቻል አለባቸው። ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ድልድይ የሐመር ወጣቶች ሲሆኑ፣ የዘመኑን ትምህርት መቅሰም መቻል አለባቸው» ብላ ነገራዋለች" ከሎም ሐሳቧ የሱም እምነት እንደሆነ አረጋግጦላታል"

ካርለት፣ ሐመርን ለመልቀቅ የተወሰኑ ቀናት ሲቀራት ሆዷ
ተሸበረ ተጨነቀች" የገርሲ፣ ፌጦ፣ ኩንኩሮ፣ ጨዋንዛ፣ ግራር ዘንባባ፣ አጋም፣ ጠዬ፣ አንቃ፣ ሌሊሚ፣ ጨውሊምባ፣ ሾላ፣ ዋንዛ፣
እንኮይ...ደኑ የአሰሌ፣ የካራ ሰንሰለታማ ተራራ፣ የላላ፣ የሻንቆ፣የወሮ…መንደር፤ የሐመር ልጃገረድ፣ ጐረምሳ፣ አዛውንት፣
ሽማግሌ፣ ባልቴት ቀብራራው ደልቲ ገልዲ በአእምሮዋ እንደ
ፔንዱለም ባለማቋረጥ እየተመላለሱ (ጨክነሽ ጥለሽን ልትሄጂ እያሉ፣ ልቧን አንጠለጠሉባት።
ካርለት ቀሪውን ጊዜዋን ከብቱን፣ ሰውን፣ ጫካውን ፎቶ ስታነሣ ሰነበተች። ልቧ ግን እንደ ታረደ ዶሮ እየተነሣ ፈረጠባት ስትመጣ
ዳር ዳር ቆመው የተመለከቷት ሐመሮች የጕዞዋን ዜና ሲሰሙ
ሕሊናቸው ኩምሽሽ ብሎ ዓይናቸው በእንባ ሲሞላ ተመለከተች ስትቀርባቸው ሊወጓት ቀንዳቸውን ያዞሩባት የነበሩት ከብቶች
ጠረኗን እየፈለጉ ተጠግተው እጆቿን ላሷት።

ካርለት በሕይወቷ እንዲህ ልብ ሰራቂ የሆነ የሰውና የተፈጥሮ ፍቅር አጋጥሟት አያውቅም። ስለዚህ፣ ልቧ ደረቷን ሲረግጥ፣
ሕሊናዋ አነባ! ዓይኖቿም አለቀሱ።

ካርለት ሐመርን ልትለቅ አንድ ቀን ሲቀራት የኢቫንጋዲ ጭፈራውን ለመካፈል አሸዋማ፣ ገላጣና ዙሪያውን በለመለሙ የሐመር እፅዋት ተከቦ ፍቅር እየተቦካ ወደሚጋገርበት፣ ንብ አበባ
ወደምትቀስምበት፣ አዕዋፍና ሰዎች ጥዑም ዜማቸውን ወደሚያዜሙበት፣ የእፅዋት፣ የአራዊት፣ የአዕዋፍ፣ የሰው ዳንኪራ
ወደሚረገጥበት ስፍራ ተጓዘች።

ካርለት በኢቫንጋዲ ጭፈራ ወቅት ሁሌም እንደምታደርገው
ጀግናውን በዓይኖቿ አማተረች" ጀግናው እየዘለሉ አየሩን ከሚቀዝፉት ጐረምሶች መካከል የለም ካርለት፣ «አምላኬ!» ብላ፣
እንደ መኪና ጎማ ተነፈሰች" በጭንቀት ዓይኖቿ ሲቅበዘበዙ ግን ደልቲ ገልዲ ካለወትሮው ተክዞ፣ ራቅ ብሎ ቆሞ አየችው" ጀግናውን ተክዞ አይታው አታውቅም። ቀጭኔ፣ አንበሳ...የገደሉት አነጣጣሪ
ዓይኖቹ ቦዘው ስታይ ሰውነቷ ተዝለፈለፈባት። ጭንቀት ያዘለው ዶፍ
ዝናብ ሊያለብሳት መጣሁ ወረድሁ እያለ አጕረመረመባት። ካርለት
በደመ ነፍስ ወደ እሱ እየተንቀሳቀሰች፣ «ምን ሆኖ ይሆን?» ብላ ራሷን ጠይቃ ፊት ለፊቱ ሄዳ ቆመች።

«ካርለት» አላትና ዝም ብሎ ዓይን ዓይኗን ተመለከተ

«ምን ሆንክ ደልቲ?» ብላ ጠየቀችው።

ዝም ብሎ ዓይኖቹን ከሷ ላይ አንሥቶ ወደ ጨረቃዋ ወረወራቸው" ካርለት ዘለሽ እቀፊው እቀፊው አሰኛት።
ካርለት» አለ ደልቲ ዓይኖቹን ሳያወርድ።
«አቤት» አለችው:
ደልቲ ገልዲ ግን ዝም አለ ተመልሶ።

እንደ ባልጩት ድንጋይ እያብለጨለጨ የተከፋፈለው የጭኑና
አጁ ጡንቻ፣ ሣንቃው ደረቱ፣ የሚንቦገቦጉት ትናንሽ ዓይኖቹ በጨረቀዋ ብርሃን ካርለት ስታይ የምትይዘው የምትጨብጠው ጠፋት
መላ አካሏ እሳት ላይ የወደቀ ቋንጣ ይመስል ኩምትርትሩ ወጣ"

«ወይ አምላኬ፣ ምናለ የልቡን በነገረኝ፤ ምናልባት
መለያየታችን አስጨንቆት ይሆን? መቼም ማለት የፈለገው ነገር አለ
ከአንደበቱ እንዳያወጣው ግን እየተናነቀው ነው» ብላ አሰበች"

ይህን ስታስብ፣ «ካርለት መሄድሽ ነው?» የሚል ከደልቲ ጕሮሮ አፈትልኮ ወጣ"

«አዎ መሄዴ ነው» አለች ካርለት፣ «ምን ሊለኝ ይሆን አምላኬ» ብላ ዓይን ዓይኑን እየተመለከተችው» ደልቲ ግን አሁንም ጸጥ አላት።

«ትወደኝ ነበር?» ብላ የሞኝ ጥያቄ ጠየቀችው ደልቲ ግን ትክ ብሎ አይቷት፣ «አይ» አላት፣ በምፀት" ካርለት መልሱ ከልቡ እንዳልሆነ በሚገባ ተረዳች" ካርለት ያኔስ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆነች ጀግናው እንደገና ጣላት። ስለዚህ፣ እጇን ሰዳ እጁን ያዘችውና ወደ
ሰንበሌጡ ይዛው ገባች“ ከዚያ ጭፈራው በዓይነት በዓይነት ቀጠለ ዳንኪራው ተመታ። አሁንም እንደ ባለፈው ተመልካች በሌለበት የተፈጥሮ አዳራሽ ትርዒታቸውን ለራሳቸው አሳዩ። ዳንኪራው ግን
እንዳለፈው ተስፋ ሰጪ ሳይሆን ለየት ያለ፣ የሰቀቀን፣ የኃዘን፣
የህምታ ውዝዋዜ ሆነ።

በነጋታው ፀሐይ ከወደቀችበት ተነሥታ ወደ መሃል ሰማይ ስትገሰግስ ካርለት ዕቃዎቿን በስቴሽን ዋገን መኪናዋ ላይ ከከሎ ጋር አስተካክለው ጭነው እንደ ጨረሱ ሐመሮች ከየመንደሩ ተሰባስበው

ሴቶቹ ደረታቸውን እየደቁ ሲያለቅሱ፣ ወንዶቹ በርኮታቸው ተቀምጠው ተከዙ። ካርለት ዓይኗ በእንባ ሊጠፋ ተቃረበ" የሁለት
ዓለም ዘመዳሞች ሲለያዩ አምርረው አዘኑ"

ካርለት፣ ከሎ ሆራና ጎይቲ በሽማግሎች ተመርቀው፣ ጀርባቸው በከብት እበት ከተቀባ በኋላ ሦስቱም መኪና ውስጥ ገብተው መኪናዋ ተንቀሳቅሳ አቧራው ሲነሣ የሐመር ጭንቅላቶች ወደ መሬት
አቀረቀሩ" ካርለት ትንሽ ከተጓዘች በኋላ ኢቫንጋዲ የጨፈረችበትንና
የቦረቀችበትን የሐመር ጫካ ለመሰናበት መኪናዋን አቁማ ስትወርድ፣ ከሎና ጎይቲም አብረው ወረዱና እንባቸውን አወረዱ..
ወፎች ግን እየዘመሩ፣ ቱር እያሉ እየበረሩ፣ እየተዳሩ ምግባቸውን መፈለጋቸውን አላቆሙም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በዋናው የመኸር ወቅት የሐመር የተፈጥሮ ውበትና ልምላሜ የክቱን አውጥቶታል" እፅዋት ለምልመው አብበዋል የከስኬ ወንዝ ከአሸዋ በላይ ሆኖ ይፈሳል። የቡስካ ተራራ አሁንም ከቦታው ሳይንቀሳቀስ የሐመሮች የታሪክ ሐውልት ሆኖ ፈገግታውን በልምላሜ ያሳያል"

ከአሰሌ ሰንሰለታማ ተራራዎች እስከ ኬንያ ጠረፍ፣ ከኤርቦ እስከ አሪ ማኅበረሰብ የሐመሮች ዘፈንና ዳንኪራ አሁንም ከጫፍ እስከ ጫፍ ያስተጋባል። የሐመር ተፈጥሮ ለሰዎች ብቻ ሳይሆን ከድንቢጥ ወፍ እስከ ጥንብ አንሳ ጆፌ አሞራ፣ ከትል እስከ ተሳቢው
ዘንዶ ከከብት እስከ ሚዳቋና ድኩላ ይፈነጭበታል"

ሁሉም የተፈጥሮ ድምፁን ባሰማ፣ እንቅስቃሴ ባደረገ ቁጥር ውብ የሙዚቃ ቅማሬ ከጋራ ጋራ፣ ከቋጥኝ ቋጥኝ ይስተጋባል" የሐመር ምድር ለሚመጡትም ለሚሄዱትም ሁሌም ያው ነው" መለምለም፣ ማበብ፣ መጠውለግ፣መድረቅ..ተልሶ ደግሞ መለምለም።

ደልቲ ገልዲን መኪናዋ የሚወዳቸውን ጭና በአራት እግሯ ከቡስካ በስተጀርባ ተሠውራበታለች መዝናኛዎቹ፣ መደሰቻዎቹን
ሌባዋ ይዛ በአቧራ ደመና ገብታ ጠፍታበታለች" ደልቲ አሁን ሁለት እግር ያለው ከሌላ ፍጡር ያልተለየ መሆኑን ሳይረዳ አልቀረም
የጎሽን ጀርባ በአንድ ምት ብቻ አከርካሪውን አድቅቆ
የሚያንበረክከው አንበሳ መጨረሻ የዝንብ መዝናኛ መሆኑ የማይቀር እውነት መሆኑን ደልቲ የግድ ሊመለከተው፣ ሊደርስበት ነው"
👍283
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ልክ በስድስተኛ ወሩ እንግሊዝ አገር ውስጥ በሚገኘው የማንቸስተር ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ ሁለት ቆዳ ለባሽ ሴቶች፣ አንድ
ሳዳጎራ ያገለደመ ወጣት፣ ተቃቅፈው በመግባት ቦታቸውን ይዘዋል"
አፉን ከፍቶ የነበረው አዳራሽ ቀስ በቀስ ሞልቶ ተጨናነቀ" የዕለቱ
አንትሮፖሎጂካዊ ጥናት አቅራቢ የአፍሪካ ውስጥ ምርምሯን ይዛ ወደ መድረክ ወጣች።

«…ክቡራትና ክቡራን፣ በተመራማሪነቴ የሠለጠነው ዓለም
ከረሳው ተፈጥሮና ሕዝብ መካከል ተገኝቼ፣ ለዘመናት የዳበረ ባህልና ጥበብ ያለውን ክልል ለማየትና ሕይወቱንም ለመኖር ችዬ እኔ ያገኘሁትን ዕውቀት ለቀሪው ዓለም ሕዝብ ለመግለጽ በመብቃቴ
ደስታዩ ወደር የለውም።

«የሐመር ተፈጥሮ፣ ሰው ሠራሽ ብክለት ያልተጠናወተው ንጹሕ
ተፈጥሮ ነው። በዓለማችን ፍጹም ደስታ ያለው ሕዝብ አለ የሚል እምነት የለኝም" ደስተኛ ሕዝብ አለ ከተባለ ግን ከሐመር ሕዝብ
የበለጠ ደስተኛ፣ ግልጽ፣ በመካከሉ ጠንካራ መፈቃቀር ያለው ያለ
አይመስለኝም።

«በዘመናችን እንደ ብርቅ የሚታየው ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ሐመሮች ለብዙ ዘመናት የሕልውናቸው የማዕዘን ድንጋይ አድርገውት ኖረዋል" ከዚህ በተጨማሪም፣ የሐመሮች የዳበረ የከብት አረባብ ዘዴ፣ የአመጋገብ ሥርዓት፣ ብሒሎችና ትውፊቶች ወዘተ.ዝብርቅርቁ የወጣውን የዘመነውን ዓለም ዓይነ ልቦና የሚስብ
እንደሆነ አምናለሁ።
«...ለማጠቃለል
ያህል፣ እኔ የምናገረው የማውቀውን ብቻ
ሳይሆን የሚሰማኝንም ጭምር ነው" በእርግጥ ሐመር ላይ ሊሻሻሉ፣
ሊያድጉና እገዛ የሚያስፈልጋቸው በርካታ ቁም ነገሮች እንዳሉ
አምናለሁ" ሆኖም ግን ከሠለጠነው ዓለም የአካባቢ ብክለት ችግር፣
የበሽታ መስፋፋት፣ ተፈጥሮአዊ ካልሆነ የአኗኗር ሥርዓት ችግር አንፃር የሐመር ተፈጥሮ ማራኪ ነው" ሕዝቡም ንጹሕ ሕሊና፣የዳበረ የአኗኗር ልምድ፣ ተፈጥሮአዊ ፍቅርና በራሱ የሚተማመን
ሕዝብ መሆኑን ሳረጋግጥ በዓለማችን እውነቱን በመመስከር ከታወቁት ምስክሮች ራሴን እንደ አንዱ እቈጥረዋለሁ።

«..ቀሪው ዓለም አፍሪቃውያንን መርዳት ብቻ ሳይሆን፣አሁንም ከአፍሪቃውያን ብዙ የሚማረው እንዳለ ማወቂያው ጊዜ
አሁን ነው» የሚለው፣ በጽሑፍና በተንቀሳቃሽ ሥዕል የተደገፈው
ጥናቷ ተመልካቿን ከመቀመጫው ናጠው።
ተመራማሪዋ በባዶ እግሯ፣ ቆዳዋን እንደ ለበሰች ጥናቷን ስታቀርብ ቆይታ ስታጠቃልል ያችን ችግርና ሰቆቃ ተቋቁማ፣ የሁለቱን ዓለም ልዩነትና አለመግባባት አስወግዳ፣ እውነተኛ ሰብአዊ ፍቅርንና ሕይወትን ያሳየች ተመራማሪ የአድናቆት ጭብጨባና ጩኸት ለደቂቃዎች በዩኒቨርሲቲው ታሪክ ታይቶ ተሰምቶ
በማይታወቅ መልክ ቀረበላት። ካርለት አልፈርድ ተባባሪዋንና ጓደኞቿን ይዛ ወደ መድረክ ስትወጣ ጭብጨባው ይበልጥ ጋለ"
ከሎና ጎይቲም ሕሊናቸው በደስታ ረካ።

ሦስቱም ጓደኛሞች በሐመር ደን መካከል እንዳደረጉት ሁሉ፣በማንቸስተሩ የጉባኤ አዳራሽም ተቃቅፈው አነቡ እየሣቁ አለቀሱ።
በአውሮፓ ሕይወት ከሎ ብዙውን ጊዜውን በትምህርት አሳለፈ
ጎይቲ ግን ከካርለት ቤተሰቦች ጋር ተቀመጠች" ጎይቲ በዓይን ማየት
ቀርቶ በወሬ እንኳን በአሳለፈችው ሕይወት ያልሰማችው ጉድ ውስጥ
ስትገባ በእውኗ መቃዠት አበዛች።

ከካርለትና ከከሎ ጋር መጀመሪያ ከሐመር ሲነሡ የመኪናው ጕዞ ደስ ብሏት ነበር" ከካርለት ጋር በመኪና መካ፣ ቱርሚ፣ ጂንካም
ሄዳ ስለነበር እንደ ልማዷ መኪናዋ ስትጓዝ የሐመር ሰዎችና እፅዋት ወደ ኋላ ሲሮጡ እሷ በሣቅ ፍርስ ብላለች" አንዴ ወደፊት፣ አንዴ ወደኋላ ስታይ እንደ ቆየች ግን የሆነ ነገር ሆዷን አሸበራት" ወዲያው
ለካርለትና ለከሎ፣ «ይእ! አያችሁልኝ የኔን ነገር አገሩን ሁሉ ስሰናበት አያ ደልቲን ግን ሳልሰናበተው ስመጣ? ምናለ እናንተዬ
ብትመልሱኝ? አሁን ባል በማግባቴ አንጀቱ የተኰማተረው አንሶት
መሄዴን ሲሰማ ሆዱ መንቦጫቦጩ ቀረ! ጀግና ሰው ልቡ ቶሎ
ይቀየማል» አለች።

«ጎይቲ አሁንማ ብዙ ርቀን መጥተናል" ቀደም ብለሽ አስበሽው ቢሆን ኖሮ ብንመለስም አይከብድም ነበር" አሁን ግን ብዙ ርቀናል" አንቺስ አያ ደልቲ የሚገኘው ከስኬ ወንዝ አሸዋ ላይ ተጋድሞ
መሆኑን እያወቅሽ ለምን ሄደሽ ሳትሰናበችው ቀረሽ?» አላት ከሎ
«ይእ! እናንተ ልቤን አጠፋችሁታ" እንዲህ አሁን ሆዴን ሊያጥወለውለኝ እዚች መኪናይቱ ላይ መውጣቱም አጓጓኝና
እረሳሁት እንጂ ምነው እናንተዬ ኧረ ኃዘኑ ቅስሙን ይሰብረዋል"ጀግና ሰው ዕድሜው አጭር ነውI መርቀኝ፣ ላገርሽ ያብቃሽ በለኝ ሳልለው ወጥቼ ስመለስ ባጣው ጸጸቱ ዕድሜ ልኬን ይወጣልኛል?» አለች"

«ጎይቲ አያ ደልቲን አሁንም ታልሚዋለሽ ማለት ነው። ድሮ የተቃበጣችሁት አይበቃም?» አላት ከሎ ፈርጠም ብሎ"

«ይእ! ኧረ እይልኝ የአያ ደልቲ ጨዋታ እንደ ከተማ ልብስ የሚወልቅና
የሚታጠብ መሰለህ! ሆድ ዕቃ ውስጥ ነው የሚቀመጥ ያ ደልቲ አንፈራጦ ብቻውን ይዞት የነበረውን ስፍራ አንተ ገብተህ እሱን ወደ ጥግ ወሰድከው እንጂ ከሆድ
አልጣልከው" እኔና እሱ የአንድ ጎሳ ልጅ መሆናችንና አንተ ባዕድ ሆንህ እኔና አንተን አገናኘን እንጂ የዚያ ጀግና ሎሌ ሆኜ ብኖር
ምንኛ ደስ ባለኝ ነበር» ብላ በሣቅ ስትፍለቀለቅ፣ ካርለትና ከሎአብረው አጀቧት።

ካርለት ጎይቲ በሐመርኛ ቋንቋ የተናገረችውን ካዳመጠች በኋላ፣
«ምነው ሰው ሁሉ እንዳንቺ ግልጽ በሆነ፣ እውነተኛ ስሜቱን ባልደበቀ እዚህ ወርቅ መሳይ ብልጭልጭ ዓለም እውነተኛው ወርቅ
ሕይወት ሐመር ላይ አለ ቢሉት ማን ጆሮውን ይሰጣል" መተማመን
ቀርቶ መጠራጠር ዘውድ በጫነበት በዚህ የውሸት ዓለም እስከ መቼ መኖር ይቻላል?» ብላ፣ ስታስብ ካይኖቿ ስር መጀመሪያ ጉም መሰለ ነገር፣ በኋላ ተከታትሎ እየተስረገረገ የሚንኳለል ትኵስ እንባ
ዓይኗን ሲሞላ፣ መኪናዋን አቁማ መሪው ላይ ተደፍታ መንሰቅሰ ጀመረች።

ጎይቲ መጀመሪያ ካርለት እየሣቀች መስሏት ነበር" የቀላው? ፊቷንና የራሰውን ዓይኗን ስታይ ግን ልቧ በኃዘን ተሰብሮ ቆየችና፣
“ይእ! ምነው አይደክማት እሷ ብቸዋን ደፋ ቀና እያለች እኛ ዝም አልናት። በይ አንቺስ ከምታለቅሺ ዕርዱኝ አትይም? እንደ እርፍ
ወዲያ ወዲህ የምታማስይውን እንደሁ አያቅተኝም። መዘወሩንም
ቢሆን አላጣውም» አለቻት

«ጎይቲዬ አመሰግናለሁ" መንዳቱ ለአንቺ እንኳ ይhብድሻል ባይሆን መኪናውን ከሎ ያሽከርክር፣ ወደፊት ግን አንቺም
ታሽከረከሪያለሽ» ብላ ቦታዋን ለቀቀችለት"

ጎይቲ አንተነህ ደስ ያላት ጕ" እያንገሸገሻት ሄደ" አንገቷ
ደፍታ የማታውቀው ጎይቲ ሆዷን አቅፋ፣ አንገቷን አዘነበለች
ጎይቲ በአውሮፕላኑ ጕዞም ሆነ በአውሮፓው ሕይወት ቋንቋውን ገጽታውን የማታውቀው ትያትር ተመልካች ሆና ሁሉም ነገር
ታከታት። ኵሩው አረማመዷ ስብር ስብር አለ ጥርሶቿ በከንፈሮቿ በጥብቅ ተጋረዱ" የሐመሯን ሸጋ ህምታ ሰፈነባት" ፀሐይ ከእሷ በጣም ርቃ ሙቀቷ ሳይሰማትና ብርሃኗ ሳያስደስታት ወጥታ ገባች
ጨረቃን ከናካቴው ከሰማይ ላይ አጣቻት" ሲያዩት የሚያብለጨልጨውና የሚያምረው ሰው ሠራሽ ውበት፣ እየቆዩ በሄዱ ቁጥር
እያፈናት መጣ" መለምለም፣ ጠውልጎ መድረቅ፣ ተልሶ
መለምለም የማያውቀው የተፈጥሮ ቅመም የጎደለው የቴክኖሎጂው
ዓለም ለውጥ አልባ በመሆኑ እጅ እጅ አላቸው። ንጹሕ አየር፣ ተለዋዋጩ የተፈጥሮ ውበትና የሚያውደው መዓዛ፣ የአዕዋፍ ዝማሬና
የአውሬዎች ጩኸትና ግሳት፣ የጨረቃ ወቅት ዳንስና ጣፋጩ የጫካ
ውስጥ ፍቅር በእዝነ ሕሊናቸው ውል እያለ አስቈዘማቸው"
👍29😁1