አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሳቤላ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

..ሚስተር ካርይልና ሳቤላ ዊልሰንን አስከትለው በምዕራብ ፈረንሳይ ቡሎን በምትባል ከተማ ደርሰው ወደ ቤንስ ሆቴል አመሩ " ፒተር የሚስ ካርላይል አሽከር
የነበረ ሲሆን ወደ ኢስትሊን ሲዛወሩ ወደነሱ ዙሮ እንደ ነበር እዚህ መጥቀሱ ተግቢ ይሆናል " ቡሎኝ እንደገቡ ወደ ቤንስ ሆቴል ሔደው ሚስዝ ዱሲ መኖሯን ጠየቁ ቀድማ ዴርሳ ልትቀበላቸውና ሳቤላንም ልታላምድ ታስባ የነበረችው ሚስዝ ዱሲ በቤተሰብ ችግር ምክንያት ወደ ጀርመን መሔዷን ከተወችላት ደብዳቤ ተረዱ"

“ ፊቱንም ቢሆን ማወቅ ነበረብኝ እንደሷ በቃሏ የማትገኝ ሴት የለችም አለች ሳቤላ "

ሚስተር ካርላይልም እሷ ከሌለች ወደ ትሩቪል መሔድ መሻሉን አማክሯት ነበር ሳቤላ ግን አንድ ጊዜ ቡሎኝ ከገባች ከዚያው መቆየቱን መረጠች " እሱም
ቤንስ ሆቴል ግርግር ይበዛበት ስለነበር፡ ጸጥታና ክብር ያለበትን ሆቴል ፈልጎ በኤኩ መንግድ በኩል ከወደቡ አጠገብ አንድ በጣም ጥሩ ሆቴል አገኘና ወዶፈደዚያ ተዛወሩ ወዟ ቶሎ ምልስ ሲል አይቶ ሚስተር ካርላይል ጉዞው ደኅና የረዳት መሰለው እሷም ብርታት እንደ ተሰማት ነገረችው አንድ ቀን ብቻ ውሎ ለመመለስ የመጣውን
የብርታቷ መታደስና የፊቷ መለምለም ሲያይ ስለ ተደሰተ የዚያች ወጭ ወራጅ አላፊ አግዳሚ የበዛባትና የተጨናነቀችውን ከተማ ሁኔታ እያየ ጭምር ሦስት ቀን አደረ።

“ እኔ እዚህ ከማንም ጋር ለመተዋወቅ አልፈልግም
አለችው ሳቤላ ከወደቡ መድረክ አንድ ጫፍ ላይ ተቀምጠው ባጠገባቸው እየተጋፉ ሲያልፉ የነበሩትን ብዙ ደስተኛ ሥራ ፈቶችን እየተመለከቱ "

“ በደፈናው እንደዚህ ማለቱ እንኳን ደግ አይሆንም ” አላት ሲመልስላት እንዳጋጣሚ የምታውቂው ሰው ታገኚ ይሆናል " ብዙ ዐይነት ሰዎች ወደዚህ
ይመጣሉ አንዳንዶቹ ሐቀኞችና የተከበሩ ሆነው ለተከበረ ዓላማ ይመጣሉ አንዳንዶቹ ደግሞ በተግላቢጦሹ በመጥፎ ጠባያቸው ዕዳና ዱቤ በማብዛታቸው ኢንግላንድ ውስጥ መኖር ስለአልቻሉ ካገር እየሸሹ በሀብት የከበሩና የቅዱሳን ኑሮ የሚኖሩ መስለው የሚታዩ አጭበርባሪዎች ናቸው "

“ አንተ ወደ ባሕር ማዶ እንኳን መጥተህ አታውቅም እንዴት ታውቃቸለህ.. አርኪባልድ ?”

“ ቦታውን ከሚያውቁ ብዙ ሰዎች ጋር እገናኛለሁ ለምሳሌ ባክስታንን ተመልከቼው እሱም አይቶኛል " ወደፊት በመምጣት ወይም ወደ ኋላ በመሸሽ መካከል ሊቆርጥ አልቻለም ።

"ማን ? የቱ ነው እሱ ?”

“ ያ ረጂም ጸጉረ ቀይ ደኅና ልብስ ለብሶ በሰዓቱ ማሰሪያ ብዙ ጌጥ ያንጠለጠለው " ሚስቱ ደግሞ ከሌሎች ሴቶች ጋር ሆና ስትከተለው ተመልከቻት
የለበሰችው ልብስ ያጠለቀቻቸው ሐብሎችና በእጅዋ ያደረገቻቸው አምባሮች ሁሉ ሰው አማኝ ከሆኑ ነጋዴዎች በማጭበርበር የተወሰዱ ናቸው " እዚህ ባለው የእንግሊዝ ኅብረተሰብ መኻል ግን ትልልቅ ስዎች መስለው ለመታየት እንደሚሞክሩ አይጠረጠርም ደከመሽ እንዴ ? አላት ።

"አዎን ትንሽ ! እንግዲህ ወደ ቤት ብገባ ይሻለኛል "

ከወደቡ መድረክ ክንድ ለክንድ ተያይዘው ቀስ እያሉ ሲወርዱ በጠቅላላ ሁኔታቸው ዐይነ ገቦች ሆኑና ብዙ ሰው አተኩሮ ይመለከታቸው ጀመር "

በበነጋው ጧት በሁለት ሰዓት በሚነሣው ጀልባ ወደ ኢንግላንድ ለመመለስ ሲሰናበታት : “ ደኅና ሁኚ . . . የኔ ፍቅር” አላትና ዝቅ ብሎ ከሳማት በኋላ “ራስሽን ጠብቂ አላት ።

“ ልጆቼን ሳምልኝ ... አርኪባልድ እና እ ... እና .. እ. እ” “ እና ምን ? ” አላት “ ሰዓት ደረሰብኝ ”

“ እኔ አለመኖሬን አይተህ ከባርባራ ሔር ጋር እንዳትዳራ ” አለችው የቀ
ለደች መስላ " እሱም እንደ ቀልድ ወሰደውና እየሣቀ ወጣ አነጋሯ ከልቧ መሆኑ አልገባውም "

ሳቤላ ተነሥታ ለቁርስ እንደ ተቀመጠች የቀሩትን ሳምንቶች እንዴት እንደ ምታሳልፋቸው ጨንቋት ትተክዝ ጀመር ። ከደሬሰችበት ቀን ጀምሮ ሁለት ጊዜ ከባሕሩ ሔዳ ታጥባ ነበር : ግን ጭንቀትና እንቅጥቅጥ ለቀቀባትና የሚስማማት ስላልመሰላት አቋረጠችው "

አየሩ በጣምደስ የሚል ስለነበር ማታ ከባሏ ጋር ካመሹበት የወደብ መድረክ ዘልቃ ለመሞከር አሰበች " ስለዚህም ፒተርን አስከትላ ሔዳ ከተቀመጠች በኋላ አንድ ሰዓት ቆይቶ እንዲመጣ ነግራ መለሰችው እሷ ከዚያ የተለያዩ ተላላፊዎችን ትመለከት ጀመር " አንድ እግረ በሺተኛ ሰውዬ በጨርቅ ማማ ሲሔድ አየች " ቀጠሉና ሦስት ቆነጃጂት ከሞግዚታቸው ጋር ብቅ አሉ ከዚያ ዴግሞ ዳንዴ ዳንዴ የሆኑ ጎረምሶች የአደን ጃኪት ለብሰው መነጽር አድርገው መጡ ሳቤላን ትንሽ ትኩር አድርገው ካዩዋት በኋላ ዐልፈው ሔዱ " ከነሱ በኋላ ትንሽ ቆይቶ ደግሞ ከሁኔታው ትልቅ ሰው የመሰለ · አንድ ረጂም መልከኛ ሰውዬ ዘለቀ » ሳቤላ
ገና ስታየው ዐይኖቿን ጣለችበት " ያ እስከዚያ ድረስ ገና ከልቧ ያልጠፋው ሰው መሆኑን ስታይ ' የጠቅላላ ሰውነቷ ሥሮች ተርገፈገፉ።

ካፔቴን ሌቪስን በበኩሉ ገና ሲያያት እንዴት ያለች ቆንጆ ነች ? ማን ትሆን?” እያለ ወደ ተቀመጠችበት መድረክ አድናቆቱንና አክብሮቱን በግንባሩ እየገለጸ ሲጠጋ ማን መሆኗን አወቃት ወዲያው ባርኔጣውን አንሥቶ' ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ
እጁን ለሰላምታ እየዘረጋ፡ “ ከእመቤት ሳቤላ ቬን ጋር እንደገና ለመገናኘት እንደታደልኩ አልጠራጠርም ” አላት

እሷም መንፈሷ ተሸብሮ የምትናገረው ጠፋት » እጅዋን ለሰላምታ ስትዘረጋላት ጥቂት ቃሎች በማልጐምጐም መለሰችለት "

ይቅርታ አድርጊልኝ ... እመቤት ሳቤላ ፡ ካርላይል ማለት ነበረብኝ ከተለያየን ብዙ ጊዜ ሆነና አሁን እንዲህ ድንገት ሳገኝሽ ጊዜ ከደስታዬ ብዛት የተነሣ
አንቺን ያሰብኩሽ ልክ ያን ዘመን እንደ ነበርሽው አድርጌ ነው "

እንደገና ተቀመጠች " በስሜት ፍላት ጉንጮቿን አልብሷት የነበረው ቅላት ቀስ በቀስ ለቀቀ " ፍራንሊዝ ሌቪሰን ከዚያ በፊት ካያት ጀምሮ እንደሷ ያማረ ፊት
አይቶ የሚያውቅ አልመሰለውም።

ከዚህ ምን እግር ጣለሽ ?” አላት ከጐኗ እየተቀመጠ ።

አመመኝና ወደ ባሕር ዳርቻ እንድሔድ ታዘዝኩ ሚስዝ ዱሊን ከዚህ እናገኛታለን ብለን ባንጠብቅ ኖሮ አንመጣም ነበር ሚስተር ካርላይልም አብሮኝ መጥቶ ሦስት ቀን ቆየና ዛሬ ጧት ተመልሶ ሔደ „

ሚስዝ ዱሲማ ወደ ኤምዝ ሄዶች እነሱን ዐልፎ 0ልፎ አያቸዋለሁ
ለጥቂት ጊዜ ፓሪስ ተቀምጠው ነበር " እውነትም የታመምሽ ትመስያለሽ ልጄ " ኣላት አስተዛዝኖ “ በጣም ታመሻል " እኔ የምረዳሽ ነገር አለ ?

እሱን ስታይ ድንገት የያዛት ድንጋጤና የመንፈስ መረበሽ እየለቀቃት ሲሔድ ደም መስሎ የነበረው ፊቷ ዐመድ ሲያለብሰው ከመጠን በላይ የታመመች
መምሰሏን ለሷም ታውቋት ነበር ። ከሱ ጋር ስለ ተገናኘች መንፈሷ በመረበሹ በራሷ በጣም ተናደደች እስከዚያች ቅጽበት ድረስ ለፍራንሲዝ ሌቬስን የተዳፈነ ስሜት ይዛ መኖሯን አልታወቃትም ነበር።

“ምናልባት በጥዋት ለመምጣት በመድፈሬ ይሆናል " አለችው እንዳዲስ ያመማት ለመምሰሏ ምክንያት ስትሰጥ “ ልመለስ መሰለኝ " አሽከሬን አገኘዋለሁ " ደኅና ዋል .. . ካፒቴን ሌቪሰን”

ግን ብቻሺን በእግርሽ ችለሽ መሔድ የምትችይ አትመስይም ስለዚህ ከቤትሽ ድረስ እንድሸኝሽ ፈቃድሽ ይሁን "

ድሮ ሲገናኙ ያደርገው እንደ ነበረው ክንዷን ሳብ አድርጎ ከብብቱ አስገብቶ
ከወደቡ መድረክ እየደገፈ አወረዳት በርግጥ ከሱ ጋር እንዶዚያ ተያይዛ መሔዱ'
ደግ ያለ መሆኑ ቢታወቃትም እሱም የቤተሰቧ ዘመድ ብዙ ስለሆነ ክንዷን ለመከልከል የምትሰጠው ምክንያት አልተገለጸላትም
👍11🔥1🥰1
“ ወይዘሮ ማውንት እስቨርንን በቅርቡ አይተሻት ታውቂያለሽ ?” አላት"

“ጥቢው ላይ ከሚስርተ ካርላይል ጋር ለንደን ሔጀ ሳለ አይቻት ነበር " አንጻጻፍም ሎርድ ማውንት እስቨርን ግን ኢስት ሊን ድረስ መጥቶ አይቶናል " እስከ
ዛሬም ገና ለንደን ሳይሆኑ አይቀሩም"

“ እኔ ግን እነሱንም ኢንግላንድ ካየሁዋቸው ዐሥር ወር ዐለፈኝ እስከ ዛሬ ፓሪስ ነበርኩ " ወደዚህ የመጣሁት ገና ትናንት ነው ። ”

ረጅም የፈቃድ ጊዜ ነው ያገኘኸው ማለት ነው ?”

ከውትድርና እኮ ወጥቻለሁ ነገሩ እንዴት መስለሽ እመቤት ሳቤላ ..
ላንቺ እውነቱን ብነግርሽም ግድ የለኝም በአሁኑ ጊዜ ኑሮ አልተሳካልኝም" አጎቴም የሚያሳሳር ነገር ፈጸመ " እንደገና ሚስት አገባ !!”

“ አዎን ሰር ፒተር ማግባታቸውን እኔም ሰምቻለሁ

ሰባ ሦስት ዓመቱ እኮ ነው ጽ የሞተ ሽማግሌ ይህ አድራጎቱ ደግሞ የኔን የሀበት ተስፋ ያቃውሰዋል “ ምናልባት ሚስቱ ወንድ ልጅ ልትወልድለት
ትችላለች " ይኸን በመፍራት ባለዕዳዎቼ ሁሉ ተነሡብኝ " የማዕረጉ " የሀብቱና ርስቱ ወራሽ መሆኔን በማወቅ የፌለግሁትን ያህል ብድር ሲሰጡኝ ኖሩና " አሁን የሱ ጋብቻ በጋዜጦች ሲወጣ ክብሬ ተገፈፈ ተዋረድኩ ዱቤ ተከከልኩ "ያለብኝን
ዕዳ እንድከፍል ተጠየቅሁ " ስለዚህ ኮበለልኩ ወደ ባሕር ማዶ መጣሁ

"ባለዕዳዎችህን ከዚያዉ ጥለህ ?''

ሌላ ምንም ማድረግ አልቻልኩም አጎቴም ሊከፍላቸው አልፈለም :
ወይ ደግሞ አበሌን አልጨመረልኝም

" አሁን ያለህ ተስፋ ምንድነው ?"

"ተስፋ ? ያ እዚያ ወደ ወደቡ ድንጋይ የሚወረውረው ድሪቶ የለበስ ልጅ ይታይሻል ? ፖሊሶች ካልደረሱበት ዕድለኛ ነው " ተስፋው ምን እንደሆነ ብትጠይቂው ዐይኑን አፍጦ ያይሽና ምንም ይልሻል የኔም ተስፋ እንደሱ ነው "

• የሆነው ሁኖ ሰር ፒተርን ትተካቸው ይሆናል "

ሊሆንም ላይሆንም ይችላል እነዚህ ደደብ ሽማሌዎች ወጣት ሚስት ሲያገቡ

“ ከሰር ፒተር ጋር ተጣልተሃል ?''

የሚጠቅም ቢሆን ኖሮ መጣላት ነበረብኝ አየሽ የራስን ጥቅም መጠበቅ አስፈላጊ ነው ስለዚህ ያቺን የሚሰጠኝን አበልም እንዳትቋረጥብኝ ስለፈራሁ
ልጣላው አልፈለግሁም "

"ቡሎኝ ውስጥ ብዙ ለመቆየት ታስባለህ ?

" እንጃ ከዚህ እንደማገኘው ደስታ ነው ፓሪስ ሞቅ ሞቅ ያለ ከተማ ነው እዚህ የመጣሁት በባሕሩ ውሃ ለጥቂት ቀን ልታጠብ ብዬ ነበረ ... ሮጥኩብሽ መሰለኝ ?"

“ ስለ ሰር ፒተር ጋብቻ እያወጋህ የኔን ደካማነት ረሳኸውና በጣም ፈጠንክ ነገር ግን ምን ያህል እንደ ተሻለኝ ለመገመት ስለ ቻልኩ ጥሩ ነው የዛሬ ሳምንት ይህን ያህል መሔድ አልችልም ነበር "

ከሆቴሏ አዶረሳትና እንዲገባ ሳይጠየቅ ዝም ብሎ ገብቶ ለሩብ ሰዓት ያህል ሲያጫውታት ቆይቶ ለመሔድ ሲነሳ “ምናልባት ኋላ ለመውጣት ያሰብሽ እንደሆነ
አሽከር አስከትለሽ ከመዞር እኔ ስለምሻልሽ እንድረዳሽ ፍቀጅልኝ " ሚስተር ካርላይል ሲመጣም ያደረግሁልሽን ዕርዳታ ሲሰማ በጣም ደስ ይለዋል ”

የሌቪሰን አቀራረብና አነጋገር በቅንነት ለመርዳት ይመስል ነበር እሷም ያ ተዳፍኖ የኖረውና አሁን ጨርሶ የጠፋ አስመስላ እፍን ድፍን አድርጋ በመያዝና
ለወደፊትም በዚያው ዐይነት ልትቈጣጠረው እንደምትችል በማመን ' የካፒቴን ሌቪሰንን ቀረቤታ በትዕግሥት ለመቀበል ወሰነች "......

💫ይቀጥላል💫
👍21
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሀያ_ሶስት

ማደግ፣ ብልህ መሆን

ልክ እንደ መጀመሪያው አመት ሁሉ ሌላኛውም አመት አለፈ እናታችን ልትጎበኘን የምትመጣበት ቀን እየቀነሰ መጣ ከስንት አንድ ጊዜ ስትመጣም
ሁሌም ከዚህ ለመውጣት ጥቂት ሳምንታት ብቻ እንደቀሩን እንድናምንና ተስፋ እንድናደርግ የሚያደርገን ቃል ትገባልናለች። በእያንዳንዱ ምሽት መጨረሻ ላይ የምናደርገው ነገር ቢኖር የቀን መቁጠሪያው ላይ በትልቁ
የኤክስ ምልክት ማድረግ ነው።

አሁን ትላልቅ ቀይ የኤክስ ምልክቶች ያሉባቸው ሶስት የቀን መቁጠሪያዎች አሉን፡ የመጀመሪያው በግማሽ ብቻ ቀይ የኤክስ ምልክት የተደረገበት ነው።
ሁለተኛው ሙሉ በሙሉ ምልክት ተደርጎበታል፡ ሶስተኛው ደግሞ ግማሹ በኤክስ ምልክት ተሞልቷል፡ እየሞተ ያለው አያታችን አሁን ስልሳ ስምንት
አመት ሆኖታል። ሁልጊዜም የመጨረሻ ትንፋሹ ነው እየተባለ እኛ በተረሳ ቦታ እየተጠባበቅን እሱ ግን አሁንም መኖሩን ቀጥሏል ስልሳ ዘጠኝ አመት
እንዲሆነው እየኖረ ይመስላል።

ሀሙስ ሀሙስ በፎክስወርዝ ቤት ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ወደ ከተማ
የሚሄዱበት ቀን ነው፡ እኔና ክሪስቶፈር ጥቁሩ ጣራ ላይ ወጥተን ጋደም በማለት የፀሀይ ብርሃን የምናገኘውና ከጨረቃና ከኮከቦች ስር ሆነን አየር
የምንቀበለው እነሱ በሚወጡ ጊዜ ነው በጣም ከፍ ያለና አደገኛ ቢሆንም ንፁህ አየር የተጠማው ቆዳችንን ማስታገስ የምንችልበት ብቸኛ ቦታ ቢኖር ጣሪያው ብቻ ነው።

እግራችንን በጭስ ማውጫው በኩል የሁለቱ ቤቶች ጣራዎች የሚገናኙበት ጥግ ላይ ስናደርግ ደህንነት ተሰማን የተደበቅንበት ቦታ መሬት ላይ ካለው ሰው ሁሉ ይከልለናል: የአያትየው ቁጣ ገና መተግበር ስላልጀመረ እኔና
ክሪስ ግዴለሾች ሆነን ነበር መታጠቢያ ቤት የምንጠቀመው ሁሌ ተጠንቅቀን አይደለም። አንዳንዴ ልብሶቻችንን ሙሉ በሙሉ ላንለብስ እንችላለን አንድ
ክፍል ቤት ውስጥ ውለን እያደርን ሁልጊዜ ውስጣዊ የአካል ክፍሎቻችንን ከተቃራኒ ፆታ ሚስጥር ማድረግ ከባድ ነበር።

እውነቱን ለመናገር ማንኛችንም ማን ምን እንዳየ ግድ አልነበረንም።

ግድ ሊኖረን ግን ይገባ ነበር

መጠንቀቅ ነበረብን መቼም ቢሆን የእናታችንን በአለንጋ የተተለተለ ጀርባ መርሳት አልነበረብንም።
እናታችን የተገረፈችበት ጊዜ እጅግ ሩቅ፣ የዘለአለም ያህል የራቀ ሆኖ
ተሰምቶን ነበር።

አሁን እስካለሁበት አስራዎቹ የእድሜ ክልል ድረስ አንድም ቀን የራሴን እርቃን ሙሉ በሙሉ አይቼው አላውቅም: እርቃኗን የሆነች ሴት በስዕልም
እንኳን አይቼ አላውቅም ከእምነበረድ የተሰሩ እርቃን ሀውልቶች አይቼ የማውቅ ቢሆንም እነሱ ግን ሁሉንም አያሳዩም።

ስለዚህ እርቃኔን ለማየት መስታወት ፈለግኩ። የመድኃኒት ማስቀመጫው ቁምሳጥን ላይ ያለው መስተዋት ከፍ ብሎ የተሰቀለ ስለሆነ በደንብ አያሳይም፡ ስለዚህ ሙሉ በሙሉ እርቃን ሆኜ ራሴን ለማየት ክፍሉ ውስጥ ብቻዬን እስክሆን መጠበቅ አለብኝ ከዚያ ከመልበሻው መስታወት ፊት እርቃኔን ቆሜ እንደፈለግኩ አተኩሬ እመለከታለሁ። በራሴ ሰውነት እደሰታለሁ፣ አደንቃለሁ።

ተሳካልቶልኝ መኝታ ክፍላችን ውስጥ ያለው መስተዋት ፊት ለፊት እርቃኔን ቆምኩ የሆርሞኖች መለወጥ ያመጣው ነገር የሚገርም ነው! በእርግጠኝነት
እዚህ ስመጣ ከነበርኩት በላይ በጣም ቆንጆ ሆኛለሁ። ፊቴን፣ ፀጉሬን፣ እግሮቼን፣ እንዲሁም ደረቴን እያየሁ ነው: ከአንድ ጎን ወደ ሌላ ጎን እየተሽከረከርኩ መስታወቱ ላይ ያለውን ምስሌን እያደነቅኩ ነው። በራሴ
ተመስጫለሁ።

የሆነ ሰው ከጀርባ እየተመለከተኝ እንደሆነ ስለተሰማኝ ድንገት ስዞር ክሪስ ቁም ሳጥኑ የፈጠረው ጥላ ውስጥ ቆሞ ሲያየኝ ያዝኩት: ጣሪያው ስር ካለው
ክፍል እየመጣ ነበር እዚያ ቆሞ የነበረው ለምን ያህል ጊዜ ይሆን? ሳደርግ የነበረውን እርቃንን የማየት ብልግና አይቶ ይሆን? አምላኬ እንዳላየ ተስፋ
አለኝ:

ክሪስ በቆመበት ደንዝዟል፡ ልክ ከዚህ በፊት አይቶኝ እንደማያውቅ ሁሉ ሰማያዊ አይኖቹ ላይ የተለየ ብርሀን ይታይ ነበር፡ ምናልባት እርቃናችንን ሆነን ፀሀይ ስንሞቅ መንትዮቹም አብረውን ስለሚሆኑ ሀሳቡን ወንድማዊና ንፁህ ያደርግ ስለነበረ አፍጥጦ አያየኝም ነበር ማለት ነው።

አይኖቹ በእፍረት ቀልተው፣ ከፊቴ ወደታች ወደ ጡቶቼ ከዚያ ወደ ታች...ወደ ታች ሄደው እግሮቼ ጋ ደረሱና እንደገና በዝግታ ወደ ላይ ተመለሱ።

በፈለገ ጊዜ እንዴት ማሾፊያ እንደሚያደርገኝ ጠንቅቆ በሚያውቀው ወንድሜ
አይን አጉል ስርአት አጥባቂ ሆኜ ላለመታየት ምን ማድረግ እንዳለብኝ እርግጠኛ ባለመሆን እየተንቀጠቀጥኩ ቆምኩ፡ ከዚህ በፊት አይቼው የማላውቀው አይነት እንግዳና ትልቅ ሰው መሰለኝ፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ሰውነቴን ለመሸፈን ብንቀሳቀስ ለማየት የተራበውን ነገር የምነጥቀው ይመስል
የደከመው፣ የፈዘዘና ግራ የተጋባ ይመስል ነበር።

እዚያው እንደተገተረ ሰአቱም የቆመ ይመስል ነበር። እኔም አይኖቹ ከኋላ መስታወት ውስጥ የሚያንፀባርቀውን ምስል በውስጣቸው ለማስቀረት ሲሞክሩ
ስመለከት እያመነታሁ “ክሪስ እባክህ ሂድ” አልኩት።

የሰማኝ አይመስልም ዝም ብሎ አፍጥጠጧል በጣም አፈርኩ ብብቴ ስር እርጥበት ተሰማኝ፡፡ ልቤም እንግዳ በሆነ ሁኔታ
መምታት ጀመረ፡ እጁን ስኳር የሚቀመጥበት ዕቃ ውስጥ ሲከት እንደተያዘ ህፃን ልጅ የሆንኩ መሰለኝ፡ ይሁንና አስተያየቱና አይኖቹ ወደ ህይወት
መለሱኝና ልቤ በሚያስፈራ ሁኔታ በከባዱ መምታት ጀመረ፡ በፍርሀት
ተሞላሁ: ለምንድነው የፈራሁት? ክሪስ እኮ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የምር የሆነ እፍረት ተሰማኝ፡ ከዚያ ፈጠን ብዬ ያወለቅኩትን
ቀሚሴን ብድግ አደረግኩ: በዚህ ራሴን መከለልና እንዲሄድ መንገር እችላለሁ።

“ተይ” አለኝ፡ ቀሚሱን በእጄ እንደያዝኩ

“አንተኮ…” ተንተባተብኩ የበለጠ ተንቀጠቀጥኩ፡

“አውቃለሁ ማየት እንደሌለብኝ፡ ግን ደግሞ በጣም ቆንጆ ነሽ፡ ከዚህ በፊት አይቼሽ የማውቅ ሁሉ አልመሰለኝም: አብሬሽ ውዬ እያደርኩ እንዴት እንደዚህ ቆንጆ ሆነሽ ስታድጊ አላስተዋልኩም?"

እሱን ከመመልከትና በአይኖቼ ከመለመን በቀር እንደዚህ አይነት ጥያቄ እንዴት ይመለሳል? ይሄኔ ከኋላዬ በበሩ የቁልፍ ማስገቢያ መክፈቻ ቁልፉ ሲገባ ሰማሁ። አያትየው! ከመግባቷ በፊት በፍጥነት ቀሚሴን በጭንቅላቴ
አጥልቄ ወደታች ጎተትኩት። አምላኬ! እጅጌውን ማግኘት አልቻልኩም ጭንቅላቴ በቀሚሱ ተሸፍኖ ሌላው ሰውነቴ ግን እርቃን ሆኖ ነበር። እናም አያትየው አጠገቤ ነች! ላያት ባልችልም ግን ተሰምቶኛል!

በመጨረሻ እንደምንም እጅጌውን አስገባሁና ቀሚሴን ወደታች ሳብኩት። ነገር ግን እነዚያ ግራጫ ድንጋይ አይኖቿ ውስጥ እርቃኔን በደንብ እንደተመለከተችኝ
አይቻለሁ አይኖቿን ከእኔ ላይ አንስታ ክሪስን ዘልቆ የሚወጋ በሚመስል አይነት አፈጠጠችበት፡ እንደፈዘዘ ነው። “በመጨረሻ ያዝኳችሁ! ፈጠነም ዘገየም እንደምይዛችሁ አውቅ ነበር!” አለች:

ይህ ልክ ከቅዠቶቼ እንደ አንዱ ነው... ልብስ ሳልለብስ በአያትየውና በእግዚአብሔር ፊት
ክሪስ ከቆመበት ጥግ ወጣና መልስ ለመስጠት ወደፊት ተራመደ። “ያዝሽን?
ምንድነው የያዝሽው? ምንም:”

ምንም...
ምንም...
ምንም...

የሚያስተጋባ ድምፅ፡፡ በእሷ አይን ግን ሁሉንም ነገር ስናደርግ ይዛናለች።
👍391
“ኃጢአተኞች!” እነዚያን ጨካኝ አይኖቿን እንደገና ወደኔ አዙራ ጮኸች። “አይኖቼ ምህረት የላቸውም ቆንጆ እንደሆንሽና እነዚያ እያደጉ ያሉ ጡቶችሽ
ማራኪ እንደሆኑ ታስቢያለሽ አይደል? በየቀኑ እያበጠርሽ የምትጠቀልይውን ይሄንን ረጅም ወርቃማ ፀጉርሽን ትወጂዋለሽ አይደል?" እያለችኝ አይቼው
የማላውቀው አይነት አስፈሪ ፈገግታ አሳየችኝ፡
ጉልበቶቼ እየተንቀጠቀጡ እርስ በርስ እየተጋጩ ነው: እጆቼም እንደዚያው፡ የቀሚሴ ዚፕ ከጆርባው ሳይዘጋ በሰፈው ተከፍቶ ስላለና የውስጥ ሱሪ ስላልለበስኩ ውርደት ተሰማኝ! አይኖቼን ወደ ክሪስ ወረወርኩ ቀስ እያለ
በአይኖቹ የሆነ መሳሪያ ፍለጋ ክፍሉን እያሰሰ ነው:

“ወንድምሽ ለምን ያህል ጊዜ ሰውነትሽን እንዲጠቀም ፈቀድሽለት?” ስትል ጮሀ ጠየቀችኝ፡፡ ምን ማለቷ እንደሆነ ስላልገባኝ መናገር አልቻልኩም።

“እንዲጠቀም? ምን ማለትሽ ነው?”

አይኖቿን አጥብባ ክሪስ ሲያፍር ለመያዝ ድንገት ዞረች: ፊቱን ስመለከት፣ እኔ ባይገባኝም እሱ ግን ምን ማለቷ እንደሆነ እንደሚያውቅ ለእኔ እንኳን
ግልፅ ነበር።

“እኔ የምለው.” አለ ክሪስ ፊቱ ደም መስሎ: “…ምንም መጥፎ ነገር
አላደረግንም ነው:: አሁን ድምፁ ወፍሮ ጎርናና እና ጠንካራ ሆኗል።
“ቀጥይ በጥርጣሬና በጥላቻ አይን ተመልከቺኝ፡ እኔና ካቲ ግን አንድም ክፉ ነገር ወይም ኃጢአት ወይም የረከሰ ነገር አላደረግንም: ካላመንሽ ማመን የፈለግሽውን ማመን ትችያለሽ”

“እህትህ እርቃኗን ነበረች: እርቃን ሰውነቷን እንድትመለከት ፈቅዳልሀለች።ስለዚህ ስህተት ሰርታችኋል" ስትል በጥላቻ በአይኖቿ ገርፋኝ ፊቷን አዙራ
ክፍሉ ወጣች እየተንቀጠቀጥኩ ነበር ክሪስ ተናደደብኝ ካቲ ለምንድነው እዚህ ክፍል ውስጥ ሆነሽ ልብስሽን ያወለቅሽው? የሆነ ነገር ስናደርግ ለመያዝ አድብታ እንደምትጠብቅ እያወቅሽ…” አለኝ፡ ተጨንቆ
ሲቆጣ ያረጀ ይመስላል: “ምንም ሳታደርግ ወጣች ማለት አትመለስም ማለት አይደለም ልትቀጣን ነው::”

“አውቃለሁ አውቃለሁ። መግረፊያ ይዛ ልትመጣ ነው"

መንትዮቹ እንቅልፋቸው መጥቶ እየተነጫነጩ ጣሪያው ስር ካለው ክፍል ተመለሱ። ኬሪ ወደ አሻንጉሊቱ ቤት ስትሄድ ኮሪ ደግሞ ቲቪው ፊትለፊት
ተረከዙ ላይ ቁጢጥ አለና ጊታሩን አንስቶ መጫወት ጀመረ። ክሪስ በር በሩን እየተመለከተ አልጋው ላይ ተቀምጧል። እኔ ደግሞ ስትመለስ ሮጬ መታጠቢያ ቤቱ ውስጥ ገብቼ ልቆልፍ ተዘጋጅቻለሁ። መታጠቢያ ቤት እገባና በሩን ቆልፌ ከዛ እኔ ..

የበሩ ቁልፍ ተከፍቶ እጄታው ተንቀሳቀሰ፡

ዘልዬ ስነሳ ክሪስም ደንግጦ በመነሳት ካቲ ወደ መታጠቢያ ቤት ግቢና እዚያው ቆይ!” ሲል ጮኸ፡

አያታችን እንደ ዛፍ ገዝፋ ወደ ክፍሉ ገባች አለንጋ አልያዘችም እጇ ላይ ያለው ሴቶች ልብስ ለመስፋት ጨርቅ የሚቆርጡበትን አይነት ትልቅ መቀስ ነው፡ መቀሱ ረጅም ሲሆን በጣም ስለት ያለው ይመስላል

“ተቀመጪ! አለችኝ “ከዚህ በኋላ መስተዋት ስታይ ኩራት እንዳይሰማሽ ፀጉርሽን በሙሉ እቆርጠዋለሁ" ድንጋጤዬን ስትመለከት በንቀትና በጭካኔ
ፈገግ አለች:

ብገረፍ ይሻለኛል። ብገረፍ ቆዳዬ ቶሎ ይድናል። አባቴ ረጅም ፀጉር ያላቸው ልጆች ደስ እንደሚሉትና የእኔም ፀጉር እንደሚያምር ከነገረኝ ጊዜ ጀምሮ ያለማቋረጥ ስንከባከበውና ስወደው የኖርኩትን የሚያምር ረጅም ፀጉር ግን ላጣው አልፈልግም። መልሶ ለማሳደግ ደግሞ አመታት ይወስዳል: አምላኬ
ሆይ! በህልሜ በየምሽቱ ወደ መኝታ ቤታችን ተደብቃ በመምጣት በተኛሁበት
ፀጉሬን ልክ እንደ በግ ፀጉር ስትሸልተው እንደማይ እንዴት አወቀች? በዛ ላይ አንዳንዴ ፀጉሬ ተሸልቶ መላጣና አስቀያሚ ሆኜ ብቻ ሳይሆን ጡቴንም
ቆርጣው ጡት አልባ ስታደርገኝ ሁሉ በህልሜ አያለሁ።

ባየችኝ ቁጥር የምታየው የሆነ ነገሬን ብቻ ነው። ሙሉ እኔን አይታኝ አታውቅም: ንዴቷን የሚያነሳሱትን ቦታዎች ብቻ ነው እየመረጠች የምትመለከተው… የተመለከተችውን ቦታ ደግሞ የተናደደች ጊዜ ልታጠፋው
ትነሳለች ማለት ነው።

ሀሳቤ ወደ መታጠቢያ ቤቱ ገብቼ በሩን ለመቆለፍ ነበር። በደንብ የሰለጠኑት የዳንሰኛ እግሮቼ ግን በሆነ ምክንያት አልንቀሳቀስ አሉ። ያንን ረጅምና አንፀባራቂ መቀስ ሳይ በተፈጠረብኝ ፍርሀት እንዲሁም በንቀትና በጥላቻ
በሚያበሩት የአያትየው አይኖች ምክንያት ሽባ ሆንኩ።

የዚያን ጊዜ ክሪስ በጠንካራ ድምፅ “የካቲን አንድ ዘለላ ፀጉር ለመቁረጥ ብትሞክሪ
በዚህ ወንበር ጭንቅላትሽን እልሻለሁ!” ብሎ ስንመገብ ከምንቀመጥባቸው ወንበሮች አንዱን አነሳ፡ ወዲያው የእሱ ሰማያዊ አይኖች እሳት፣ የእሷ ደግሞ ጥላቻ ረጩ።

ከላይ እስከታች በግልምጫ አነሳቸው፡ የእሱ ትንሽዬ ወኔ የብረት ተራራ የምትመስለዋን በጭራሽ ሊያሸንፋት እንደማይችል ሁሉ ማስፈራሪያው
ውጤት አልነበረውም። “በጣም ጥሩ… እንግዲያው ምርጫ እሰጥሻለሁ።ፀጉርሽን ብታጪ ይሻልሻል ወይስ ሳምንቱን ሙሉ ምንም አይነት ምግብም
ሆነ ወተት ባታገኚ?”

“እባክሽ መንትዮቹ ምንም አላጠፉም…” ስል ለመንኳት። “ክሪስም ቢሆን ምንም ያደረገው ነገር የለም:: ጣሪያው ስር ካለው ክፍል ሲመለስ ራቁቴን እንደሆንኩ
አላወቀም ነበር ጥፋቱ ሁሉ የእኔ ነው ሳምንቱን ሙሉ ያለ ምግብና ያለ ወተት መቆየት እችላለሁ አንቺ ግን ይህን ላድርግ ብትይ እንኳን እማዬ ይህንን እንድታደርጊ አትፈቅድልሽም: ምግብ ታመጣልናለች" አልኳት። እንደ እውነቱ ግን በልበ ሙሉነት አልነበረም ያልኳት ምክንያቱም እናታችን ከመጣች ረጅም ጊዜዋ ስለሆነ ቅጣቱ ቢጣልብኝ እንደምራብ አውቃለሁ።

“ፀጉርሽ ወይም ለሳምንት ምንም ምግብ አለማግኘት!” ስትል በማይበገርና ፍንክች በማይል አነጋገር ደገመችው: “አንቺ አሮጊት የምታደርጊው ሁሉ ስህተት ነው" አለ ክሪስ ወንበሩን አንስቶ እየተጠጋ ካቲን ድንገት ነው ያየኋት። ምንም ኃጢአት የሆነ ነገር አላደረግንም፣ አድርገንም ደግሞ አናውቅም ገና ለገና ይሆናል ብለሽ ፈርተሽ ነው”

ሁልጊዜ እንደምታደርገው ክሪስን ችላ ብላ “ፀጉርሽ ወይስ ለሳምንት
አለመብላት?” አለች: “መታጠቢያ ቤት ውስጥ ገብታችሁ ብትቆልፉም ሆነ ጣሪያው ስር ያለ ክፍል ውስጥ ብትደበቁ አንዳችሁም ለሁለት ሳምንት ምግብ አይሰጣችሁም!”

ቀጥሎ ቀዝቃዛና ስሌት የሚሰሩ በሚመስሉ አይኖቿ ክሪስን ረዘም ላለ ጊዜ ተመለከተችውና “እንዲያውም የእህትህን ቆንጆ ፀጉር የምትሸልተው አንተ
መሆን አለብህ!” ብላ ሚስጥራዊ ፈገግታ ብልጭ አደረገችና በመልበሻው አናት ላይ መቀሱን አስቀመጠች: “ተመልሼ ስመጣ እህትህ ፀጉሯ ተቆርጦ ካገኘሁ
ብቻ አራታችሁም ምግብ የማግኘት እድል ይኖራችኋል።" ስትል ክሪስ እኔ ላይ፣ እኔም ክሪስ ላይ እንዳፈጠጥን ጥላን ሄደች:...

ይቀጥላል
👍24😢11😱96
አትሮኖስ pinned «#የጣሪያ_ስር_አበቦች ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ሶስት ማደግ፣ ብልህ መሆን ልክ እንደ መጀመሪያው አመት ሁሉ ሌላኛውም አመት አለፈ እናታችን ልትጎበኘን የምትመጣበት ቀን እየቀነሰ መጣ ከስንት አንድ ጊዜ ስትመጣም ሁሌም ከዚህ ለመውጣት ጥቂት ሳምንታት ብቻ እንደቀሩን እንድናምንና ተስፋ እንድናደርግ የሚያደርገን ቃል ትገባልናለች። በእያንዳንዱ ምሽት መጨረሻ ላይ የምናደርገው ነገር ቢኖር የቀን መቁጠሪያው ላይ…»
በህይወት መንገድ ላይ……
( ታጋቾቹ)
ምዕራፍ-አንድ
(በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ)
///
እኛ የዘላለም ተጓዦች ነን…..ለዘላለም በሁለንተና ውስጥ ቅርፃችንን እየቀያርን ከአንዱ አፅናፍ ወደ ሌላ አፅናፍ እየተላጋን የምንኖር ተንከራታች እና ተቅበዝባዥ ፍጡሮች፡፡ይህ ታርክ ግን ስለዘላለም አይደለም የሚተርከው… ስለቅፅበት ነው፡፡ሰው ተብለን ከተፈጠርንበት ሬሳ ተብለን እስከምንሸኝበት ስላለችው ቅፅበት አንድ ነጠላ ታሪክ ነው…..ከዛ በፊትም ሆነ ከዛ ቡኃላ ስላለው ብዙም እውቀቱ ስለሌለን ብንናገርም መቀባጠር ብቻ ነው የሚሆንብን፡፡
ተወልደን ወደሞታችን እየተጎዝን ነው፡፡በእያንዳንዱ ቀን ተኝተን ስንነቃ ከበላያችን የተሰቀለውን የሞት ቅርንጫፍ ዘንጥለን ወደገደሉ ለመሽቀንጠር እየተንጠራራን…. በተንጠራራንበት ቅፅበት ሁሉ የሆነች መጠን ወደቅርንጫፉ እየቀረብን ነው፡፡ግን ይህን ለማሰብ ዳተኞች ነን፡፡ስለዚህም የዘላለማዊነትን ምኞት በጭንቅላታችን ጠቅጥቀን ትርምሱ ውስጥ ገብተን እንንቦራጨቃለን….ማግበስበስ ውስጥ እንዳክራለን…..ትንፋሽ እስኪያጥረን ብኩንና ተቀበዝባዥ እንሆናለን፡፡በዛም የተነሳ መንገዳችንን ለመመርመርና ለማጣጣም እድል አይኖረንም….ጉዞችን የእውር ድንብር እይታችንም በደመነፍስ ነው፡፡እኔም ያው ሰው ነኝና እንደዚሁ ነበር ጉዞዬ…

እድሜዬ ሰላሳ ስድስት ሆኖታል፡፡ይህን ያወቁት እንግዲህ ከልደት ሰርተፍኬታ ላይ መነሻውን በመውሰድ እስከአሁን ያለውን ዓመት ቆጥሬ ነው፡፡..የፀሀይ መውጣት እና መጥለቅ ከሰው ልጅ መወለድና መሞት ጋር ይመሳሰልብኛል፡፡የፀሀይ መውጣት ከመወለድ ጋር የፀሀይ መጥለቅ ደግሞ ከመሞት ጋር፡፡

ፀሐይ ወጣች ስንል ተፈጠረች ማለታችን ሳይሆን ለእኛ እይታ ተከሰተች ብርሀኗ እና ሙቀቷ ምድራችን ጎበኛት ማለታችን ነው እንጄ ከመውጣቷ በፊተ ባለው ለሊት የለችም ማለት አይደለም በትክክልም አለች፡፡አንድ ሰውም ተወለደ ስንል ከመወለዱ በፊት የለም ማለት አይደለም በሌላ ዓለም በሌላ ቅርጽ ወይም በማንገምተው ህልውና ነበር..(ምክንያቱም እግዚያብሄር የሰውን ልጅ አንድ ቀን አንድ ላይ ነው የፈጠረው..)ሲወለደ በዚህ ምድር ተከሰተ ማለታችን ነው እንጂ ስለመፈጠር ማውራታችን አይደለም፡፡ፀሀይ የቀን ውሎዋን አጠናቃ ስትጠልቅም ከሰመች ጠፋች ማለታችን አይደለም….ከጠለቀችም ቡኃላ ከነምሉዕነቷ መኖሯን እንደምትቀጥል እናምናለን እናውቃለንም ፡፡ ሰውም ሞተ ስንል ነፍሱ ከምድር ህልውና ተነጠለች፤ ጊዜያዊ ቆይታዋንም አጠናቀቀች ማለታችን እንጄ ጭሩሹኑ ወደአለመኖር ተሸጋገረች ከሰመች ማለታችን አይደለም፡፡

ያው እንደነገርኮችሁ እድሜዬ 36 ነው ፡፡ግን ደግሞ እድሜ እንደዛ አልነበረም መቆጠር ያለበት….በህይወታችን እርባነቢስ ሆነው ዝም ብለው የሚያልፉ ትርጉመቢስ የሆኑ ቀናቶች፤ ሳምንታቶች እና አመታቶች አሉ..አሁን እነሱ ከእድሜያችን ተደምረው እንደኖርንባቸው መቆጠር ነበረባቸው?፡፡ደግሞ አንዳንድ ጊዚያቶች አሉ አንፀባራቂና ወርቃማ የሆኑ…ማንነታችንን የሰራንባቸው፤ ለነፍሳችን መዝናኛ በአበባ ያጌጠ አፅድ ፤ በፍራፍሬ የተሞላ ጋርደን ማዘጋጀት የቻልንባቸው፤ ጥቂት ግን ደግሞ በተደራራቢ ድርጊት የተሞሉ..በመከራና አሰቃቂ ድርጊቶች የታጠሩ…ተስፋ በማስቆረጥ እና መልሰው ደግሞ ብጣቂ ተስፋ በመስጠት በህይወት ዥዋዝዌ እያላጉ እያፈረሱ መልሰው የሚሰሩን …ለዘመናት የገነባነውን መኮፈሳችንን የሚቦረቡሩ….ኩራታችንን ከአመድ ሚደባልቁ….የማናውቀውን እራሳችንን የሚያስተዋውቁን…በስቃይ እሾህ የታጠሩ ግን ደግሞ ፍሬያማ ጊዜያቶች…እና እነሱ ከእድሜያችን ጋ ሲደመሩ በሁለት ሶስት እጥፍ መባዘት አልነበረባቸውም….?
እና ለዚህ ነው እድሜዬን ሲጠይቁኝ ስንት ማለት እንዳለብኝ ግራ የሚገባኝ፡፡ለማንኛውም አሁን ስለነዛ በልኬት ጥቂት ግን ደግሞ በተደራራቢ ትንፋሽ አስቆራጭ ድርጊት የታጨቀ ኩነቶች ነው የማወራችሁ..ከዘልዛላው ህይወቴ ላይ ተቦጭቀው በጉልህ ስለሚነበቡ አይረሴ ቀናቶች ፡፡
እለቱ አርብ ነው፡፡ሰዓቱ ደግሞ 12.30 ….ስራ ላይ ነኝ…የስራ ቦታዬ በተፈጥሮ ውበት በደመቀችው የመዲናይቱ አዲስ አበባ ኮረዳ ጎረቤት በሆነችው ቢሾፍቱ ከተማ ነው፡፡
በትክክል ከቢሾፍቱ ከተማ እንብርቶ በሆነው ቢሾፍቱ ሀይቅ ጠርዝ ላይ ነው ያለውት ፡፡ይዚህን ሀይቅ ጠርዝ ታከን እዚህ አስቸጋሪ ገደልና ኮረብታማ ቦታ ላይ አስደማሚ ሪዞልት እየገነባን ነው፡፡በዚህ የሪዞልት ግንባታ ላይ ፕሮጀክት ኢንጂነር ሆኜ በመስራት ላይ እገኛለው፡፡ ስራ ከጀመርኩ አመት ከስድስት ወር ሆኖኛል፡፡ፕሮጀክቱ በሁለት ፌዝ የሚገነባ ሲሆን አሁን አንደኛውን ፌዝ ገንብተን ጨረሰን ፊኒሽንግ ላይ ስንሆን አንደኛውን ደግሞ ገና ቁፋሮ ጨረሰን ፋውንዴሽን እየሞላን ነው፡፡አንደኛውን ፌዝ ሰርተን ለማጠናቀቅ እጅግ በጣም ከፍተኛ የሚባል መስዋዕትነት ከፍለናል፡፡አንድ ሰው ሞቶብናል.ከአራት በላይ ሰዎች በስራ ላይ እያሉ አደጋ ደርሶባቸው አካለጎደሎ ሆነዋል፡፡ሁለተኛውን ፌሰዝ ግን ከመጀመሪያው ያገኘነው ልምድ ቀላል የሚበል ስላልሆነ በዛ መጠን እንደማንፈተን እርግጠኞች ነኝ፡፡
ሪዞርቱ የሚያሰርፍበት ቦታ እጅግ ሳቢና አስደማሚ መልካአምድር ያለበት ቢሆንም ለግንባታ ግን በጣም አስፈሪና ፈታኘ ነው፡፡አሁን የቆምኩበት አለት ላይ ሆኜ ቁልቁል የግዙፍ እስትዲዬም ሜደ የመሰለውን ክቡ ሀይቅ ከነውበቱና አስፈሪነቱ ይታየኛል፡፡፡፡በዚህ ሰዓት ሰራተኛ ሁሉ ወጥተው ሄደዋል…እኔ ፤ የሳይቱ ፎርማኑ ጋሽ አህመድ ፤ዋናው ፌራዩ(የብረት ሰራተኛ) በሪሁን እና ከአመት ቆይታ ቡኃላ ሰሞኑን ከስራ ልትሰናበት በርክክብ ላይ ያለችው እስቶር ኪፐሯ አይዳ እና እሷን ተክታ ሰሞኑን የተቀጠረች አንድ ለጊዜው ስሞን የማላውቃት ልጅ ነን በሳይቱ ውስጥ ያለነው፡፡ ፡፡ሰራተኛ ከወጣ ቡኃላ ወደኃላ ቀርቶ በእለቱ የተሰራውን ስራ ማየት የዘወትር ልምዴ ነው፡፡ሳይቱ ከግርግር ነፃ ከወጠ ቡኃላ በስክነት የእለቱን ስራ ማየት..በእለቱ የተሰራውን መልካም ስራና የጠፋና የተበላሸም ካለ ግልፅ ሆኖ ስለሚተይ የሚቀጥለውን ቀን ፐሮግራም ለመከለስ ከፍተኛ እገዛ ያደርግልኝል፡፡
ነገ ኮንክሪት ለመሙላት የተዘጋጁ አስር የሚሆኑ footing ስላሉ ዛሬውኑ የብረት ስራቸው በትክክል በዲዛይኑ መሰረት መቀመጣቸውን እያረጋገጥን ነው፡፡
አና እንደተለመደው ከአንዱ ኮረነር ወደሌላወ ኮርነር እየተዘዋወርኩ በመመልከት ላይ ሳለው ከኃለዬ ድምፅ ሰማው
‹‹…አንጂነር የምትፈልገው ነገር አለ..?ልወጣ ነበር ››አለችኝ..አዲሶ እስቶር ኪፐር
‹‹ቆይ ትንሽ ጠብቂንና መኪና ስለያዝኩ እሸኝሻለው….እነበሪሁንም አሉ አንድ ላይ እንሄዳለን…. አንድ 10 ደቂቃ ጠብቂን…እሷ ግን መሄድ ትችላለች››አልኳት..አይዳን ማለቴ እንደሆነ ሁለቱም ገብቶቸዋል፡፡እሷ.እንድትቆይ የፈለኩት ምን አልባት ከስቶር የምንፍልገው እቃ ይኖራል የሚል ግምት ስለወሰድኩ ነው፡፡
‹‹እሺ …እጠበቅሀለው››አለቺኝ
‹‹እኔም እሷን እጠብቃለው…..ሆሆይ ከስራ ሰዓት ውጭ እህቴን ሶስት ወንዶች መካከል ትቻት አልሄድም…..ምን ይታወቃል››አለች አይዳ..እንግዲህ ነገር እየፈለገች መሆኑ ነው……ከስራ የለቀቀችው እሷ ፈልጋ ሳይሆን እኔ አባርሬያት ነው….ለምን የሚለውን ሌላ ጊዜ ነግራችሆነው..እሷም ታዲያ አሁን በዚህን ሰዓት እዚህ ሳይት ላይ የተገኘችው ከአስራአምስት ቀን በፊት ስለተዋወቀቻት ሴት ደህንነት ተጨንቃ ሳይሆን እኔን ምቾት ለመንሳትና ለማበሳጨት ነው…አዎ አይዳ እንዲህ ነች፡፡የተናረችውን እንዳልሰማው ሆኜ ትኩረቴን ወደስራዬ መለስኩ፡፡
👍29👏2
ጉብኝቴ አጠናቅቄ መጨረሻ አካባቢ አንድ ተቀፍሮ ለነገ የተዘጋጀ ብረት ብቻ የታሰረበት Footing ጋር ደረስኩ…..ስመለከተው አሰራሩ የተወታተፈና ሴንተሩን ያልጠበቀ ሆኖ ታየኝ፡፡በርቀት ላይ ስራ ሲሰሩ የነበሩትን ጋሽ አህመድንና በሪሁንን ጠራዋቸው….ቦታውን በደንብ ለማየት ጨለም ስላለኝ እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም…
‹‹ማነሽ እህት…ማን ነበር ስምሽ.እስኪ ባትሪው ይዘሺልኝ ነይ››
‹‹የትኛውን?›
‹‹አንዱን… ደህና የሚያበራውን››
‹‹እሺ›› ብላ ቆርቆሮ በቆርቆሮ ወደ ተሰራው እስቶር ሮጣ ሄደች...በፍጥነት በግራዋ አንድ ባትሪ በቀኞ ሌላ ባትሪ ይዛ መጣች፡
ሁለቱንም ተራ በተራ እየሞከረች ‹‹የትኛውን ልስጥህ ››አለቺኝ…..በዚህን ጊዜ በሪሁንና ጋሽ አህመድ መጥተው ስድስት ሜትር የሚረዝመው ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ነበር…አይዳ ደግሞ ከልጅቷ ጎን ልክ እንደጋርድ ተገትራ ቆማለች፡፡እኔ የጉድጎዱ ከንፈር ላይ ቆሜ አንዱን ባትሪ ከልጅቷ ተቀበልኩና እታች ላሉት ለማቀበል ሞክር ጀመር… እሷም እንደእኔው የጉድጓዱ ከንፈር ጋር ቆማ ሁላችንም እንዲታየን ወደታች ማብራት ጀመረች፡፡
አያችሁ እዛ ጋር ያለው ኦቨርላፕ ትክክል አይመስለኝም..እስቲ ቼክ አድርጉት …››ላስረዳቸው ገና ስጀምር ….የቆምንበት አፈር የመንሸራተት ስሜት አሳየ.. እርስ በርስ ተያይተን ሌላ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል የማሰቢያ ጊዜ ከማግኘታን በፊት ከእኛ ውጭ ያለ ከጥልቁ ሲኦል የተላከላ የሚመስል ኃይል ጎትቶ እንደጨመረን አይነት እግራችን ከዳንና ወደጉድጎዱ ተስፈንጥረን ገባን…
እንግዲህ የጉድጎዱ ጥልቀት ስድስት ሜትር ከሰላሳ ነው…. የሚቀበለን እንደአልጋ የተረበረበ ባለ 32 ዲያሜትር የአርማታ ብረት ንጣፍ እና ብረቱን ዙሪያውን አቅፎ የያዘው ወፍራም ፎርምወርክ (ጣውላ )ነው….ወይንም እድለኖች ከሆን ከታች ጉድጓድ ውስጥ ስራ ላይ በሚገኙትን ጋሽ አህመድ ና በሪሁን ጭንቅላት ላይ እናርፋለን…..እኛ ከከባድ ጉዳት እንተርፋለን…እነሱ ደግሞ ምን አልባት አንገታቸው ይቀነጠሳል፡፡
ስንት ሜትር ላይ እንደሆነ አናውቅም አዲሷን እስቶርን ኪፐር በአንድ እጄ በሌላ እጄ ደግሞ የአይዳን ቀሚስ ጨምድጄ ይዤ ነበር … ..በዛ ጭንቅ ላይ ሆኜ ‹‹አሁን እንዲሀ አንድ የተከበርኩ እና የተፈራው ፕሮጅት ኢንጂነር በሁለት ሴቶች መካከል ተጣብቄ ያየኝ ሰው ምን ይላል…?›› እያልኩ አስባለው ፡፡
…አዲሶ ልጅ . ኢየሱስ ድረስልኝ….ኢየሱስ ድረስልኘ.. እያለች ትጮኸለች
ከበታቻችን‹‹ አላዋክበር …አላዋክበር….››የሚል ድምፅ ይሰማኛል…….ጋሽ አህመድ መሰለኝ
.በጉጉት ወደሚሄድበት ሽርሽር ቦታ ለመድረስ እንደጎጎ ህፃን<<ቆይ አንደርስም እንዴ?..››ስትል ጠየቀች አይዳ ነች….ምንም የመለሰላት የለም
በእውነት ግን አንደርስም እንዴ ?ስል በውስጤ እራሴን ጠየቅኩ….ስድስት ሜትር ይሄን የህል እሩቅ ነው….?ነው ወይስ የቆሪጥ መንፈስ ወደ ጥልቁ የቢሾፍቱ ሀይቅ እየጎተተን ይሆን…?ምንድነው ጉዱ ?ቢሾፍቱ ሀይቅ አፋፍ ላይም የቤርሙዳ ትርያንግልን አይነት ታአምራዊ ማጅክ አለ እንዴ…?››በውስጤ ያሰብኩት ጭንቀት ወለድ ሀሳብ ነው፡፡
ከረጅምምምም የእድሜ ልክ ያህል ከሚረዝሙ ደቂቃዎች ቡኃላ መሬት ስናርፈ እኔ በሁለቱ ሴቶች መካከል እንደተጣበቅኩ ነበር.. እርስ በርስ ተያየን….
‹‹ወይኔ እማዬ ድረሽ…ቂጤ ተጨፈለቀ…››ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማውት የአይዳ ንግግር ነው፡፡
‹‹ቂጥሽ መጨፍለቁ ምንም አይደል ነፍሽ ግን አለ?››
‹‹ቂጤ ከሌለ ነፍሴ ምን ያደርግልኛል?››የእሷ መልስ ነበር ፡፡
.ዙሪያችንን ስናይ እንደእስፖንጅ የሚያነጥር ቄጤማ የተነጠፈበት መሬት ላይ ነው ያረፍነው ….በሁለታችንም በእጃችን ያለው ባትሪ እየበራ ነው፡፡ያለንበት 2.5×2.5 ስፋት የተቆፈረ የfoothing ጉድጓድ ሳይሆን አንድ መለስተኛ ሳሎን ስፋት ያለው ግዙፍ ዋሻ መሳይ ክፍል ነው፡፡ ከእኛ ወደኣራት ሜትር እርቀት ላይ ጋሽ አህመድና በሪሁን ጎን ለጎን ተዘርረው እርስ በርስ በድንጋጤና በገረሜታ እየተያዩ ነው፡፡ምንድነው እየሆነ ያለው..?ለ foothing የተቀመጠው ብርት ከእኛ በአንድ ሜትር ርቀት ዘፍ ብሎ ቁጭ ብሎል፡፡ጣውላዎቹና መቀሰቻ እንጨቶቹ ተበታነው ወለሉን ሞልተውታል፡፡አይኔን ወደላይ አቀናው ትልቅ አለት ድንጋይ በመጣንበት አቅጣጫ ተቀርቅሮ አፈርና ብስባሽ ነገሮች ደፍነውታል፡፡አዎ ጉድጎዱ ተደርምሶል፡፡
በአስፈሪው የቢሾፍቱ ገደል ሀይቁ ጠርዝ ስር..ምን አልባትም ከሀይቁ ወላል በታችም ሊሆን ይችላል የአንድ ድርጅት ሰራተኞች የሆን ሁለት ሴት እና ሶስት ወንዶች በድምሩ አምስት ሰዎች የተፈጠሮ ታጋቾች ሆነናል…ከነነፍሳችን ተቀብረናል…ምን አልባትም አልቆልን ሊሆን ይችላል፡፡

ይቀጥላል .....


ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
❤️
👍213👎1
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰላሳ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


...የሌቪሰን አቀራረብና አነጋገር በቅንነት ለመርዳት ይመስል ነበር እሷም ያ ተዳፍኖ የኖረውና አሁን ጨርሶ የጠፋ አስመስላ እፍን ድፍን አድርጋ በመያዝና
ለወደፊትም በዚያው ዐይነት ልትቈጣጠረው እንደምትችል በማመን የካፒቴን ሌቪሰንን ቀረቤታ በትዕግሥት ለመቀበል ወሰነች እመቤት ሳቤላ ከጊዜ ወደ ጊዜ በጣም እየተሻላት ሔደ ጧት ጧት እየተነሣች ወደ ባሕሩ ዳር አሸዋ እየመጣች ትቀመጥና የባሕሩን አየር እየተቀበለች ሞገዱን ሲገፋና ሲሸሽ ትመለከታለች " ከዚያ ቦታ ከማንም ጋር አልተዋወቀችም "
አነጋጋሪ ሰው ካገኘች ሌቪሰን ብቻ ነበር" ብዙ ጊዜ ከወደቡ መድረክ እየሔዴ ሲያጫውታት አንዳንድ ጊዜም ከቤት እየመጣ ወደ ባሕሩ ይወስዳት ነበር" ይህ ሁሉ ሲሆን ሲወስዳትም ሆነ ሲመልሳት ክንድ ለክንድ ተያይዘው ስለሚጓዙ ይህን ነገር ብትተው አንደሚሻላት
ሕሊናዋ ጠቅ ያረጋት ነበር "
አንድ ቀን እንደ ቀልድ አስመስላ
አምርራ መናገር አይሆንላትም
በደንብ ስለ ጠነከረች የሱን ድጋፍና አጀብ እንደማያስፈልጋት ነገረቸው " ባሏ ባጠገቧ ተገኝቶ ሊደግትና ሊያካሒዳት እስካልቻለና እሱም እሷን ለመርዳት እስካልተቸገረ ድረስ የማትፈልግበት ምክንያት ምን እንደሆነ በመደነቅ ጠየቃት በአባባሏ የምትገፋበት ምክንያት መናግር ስለ አልቻለች በዚው ቀጠሉ ክንድ ለክንድ ተያይዘው ይመላለሱ ጀመር አትምጣብኝ
እንዳትለው ድፍረት ጠፋ ከቤት ዘግታ አልወጣም ብላ ብትቀመጥ ለጤንነት ይበጃል ተብላ የተላከችበት የባሕሩ አየር ሊቀርባት ሆነ ስለዚህ መላቀቂያ
መላ አላገኘችም እሱም ወደ መርከቡ መድሪክ ለመውሰድ ማታ ማታ ሁልጊዜ ይመጣ ጀመር ሔደው ጫጫታ ትርምስ መጣበብ ከበዛበት ቦታ ፈንጠር ብለው ለብቻቸው ይቀመጡና ! በዚያ የብርሃንና የጨለማ መሰነባበቻ በሆነው አስደሳች
የማታ ሰዓት ለሌቪስን ሐሳብና ፍላጎት የሚስማማ ለሌላ ለማንም ጆሮ አደገኛ ሊሆን የሚችል ወሬ ይይዛሉ ከዚያ ይነሡና ከበራፉ አድርሷት ይመለሳል " ማታ ከሆነ
እሶም እንዲገባ ጠይቃው አታውቅም እሱም ጧት አንዳንድ ጊዜ ያደርገው እንደ ነበረው ያለፈቃድ ለመግባት ሞክሮ አያውቅም "

hዚህ ሁኔታ ለመላቀቅ ባሏ ቶሎ መጥቶ ወደ ቤቷና ወደ ልጆቿ እንዲመልሳት በጣም ፌለች

ሚስተር ካርላይል በሔደ በሁለተኛ ሳምንቱ ስለሚመጣ ትጠብቀው ነበር እነዚያ ሁለት ሳምንቶች በእመቤት ሳቤላ የሠሩት ተአምር ግን በጣም የሚያስገርም ነበር " የልጅነቷን ትኩስ ስሜትና አዲስ ንቃት መልሳ እንዳገኘችው እየታወቃት
ስሜቶቿን ለመተንተን ምክንያቱን ለመረዳት ግን ራሷም አልደፈረች "
የጠራው ሰማይ የነጠረ ዕንቁ መሰለ በነፋስ እየዘመሙ የሚታዩት ለምለም አዝመራዎችና ዛፎች አረንጓዴ ዕንቁ መስለው አምረው ነበር አበቦች ከማንኛውም ሽቶ በበለጠ ጣፋጭ መዓዛቸውን ያውዳሉ " እነዚህ ነገሮች ሁሉ ዱሮ ከነበሩበት አለመለወጣቸውን ይህ ሁሎ ለውጥ ይህ ሁሉ የደስታ አመለካከት ይህ ሁሉ የመንፈስ
መታደስ እውነት በውጭ የምታየው ነገር ተለውጦ ሳይሆን ከውስጧ ከልቧ የፈለቀ አንደነበርም ይገባት ነበር ስለዚህ “ ለምን? ብላ ሕሊናዋን ለመመርመር መፍራቷ አያስገርምም

ከዚያ ሁሉ መዝለፍለፍና መፍዘዝ መተከዝና ማዘን ወጥታ ካሁኑ ለውጥ ስትደርስ መልኳም ወዟም ቀለሟም አብሮ በስሜቷ ልክ ታደሰ ባሏ በመጣበት ምሽት ከካፒቴን ሌቪሰን ጋር ልትቀበለው ወደ ወደቡ የወረዶች ጊዜ ሚስተር ካርላይል ከጉምሩክ መፈተሻ ክልል ሆኖ አሻግሮ ሲያያት ሌላ መሰለችው
ጉንጮቿ ሞልተውና ወዝተው የጤንነት ቅላት አየባቸው " ዐይኖቿም ከባሏ ጋር
እንደግና በመግናኘቷ የደስታ ብርሃን አበሩ "

" በሰውነትሽ ምን አድርገሽበት ይሆን ... የኔ ፍቅር ? አላት ከጉምሩክ መጣና እጆቿን ያዝ አድርጎ " " በጣም በጎ የሆንሽ ትመስያለሽ "

“ አዎን በጣም ተሽሎኛል
አርኪባልድ አሁን ግን በጣም ሞቀኝና ሰውነቴም ደም መሰለ " እዚህ አንተን ስንጠብቅህ የማታ ፀሐይ ሙሉ ለሙሉ አገኘን " ጀልባው እንዴት ይኸን ያህል ቆየ ?

“ንፋስ ከወደፊታችን በኃይል ይነፍስብን ነበር” አላት ፡ ያ አብሯት የነበረዉ አለባበሰ መልካም ሰውዬ ማን እንደሆነ አሰበ ሰውዬውን ከዚያ በፊት አይቶት የሚውቅ መሰለው "

“ ካፒርቴን ሌቪስን ይባላል ” አለች ወይዘሮ ሳቤላ “ ስለሱ እኮ በአንዱ ደብቤዬ ገልጨልህ ነበር ረሳኸው እንዴ ?” አለችው እሱ ግን እውነትም ዘንግቶት ነበር "

« ወደዚህ በምጣቴ በጣም ደስ አለኝ” አለ ስውዬው ነገራቸውን አቋርጦ " ምክንያቱም እመቤት ሳቤላ በእግሯ ስትመላለስ ለመርዳት ዕድል አገኘሁ " መጀመርያ ብቻዋን ለመምጣት አትችልም ነበር :አሁን ግን በጣም ጠንከራልች "

እመቤት ሳቤላ የባሏን ክንድ ይዛ ፍራንሲዝ ሌቪሰን በሌላሙ ጎን ሆነው ሲጓዙ እውነቱን ልንገርህ አለው ሌቪሰን ድምጡን ለካርላይል ጆሮ ብቻ እንዲደርስ
መጥኖ። “እመቤት ሳቤላን መጀመሪያ ሳያት የምትሞትበትን ቀን ብቻ የምትቆጥር መስላኝ ነበር " ስለዚህ እኔ በምችለው ሁሉ ልረዳት ግዴታ ሆነብኝ "

“ እሷም ውለታህን እንደማትረሳው እርግጠኛ ነኝ ” አለው ሚስቴር ካርላይል ጫወታውን በመቀጠል
ስለ በጐነቷ ግን እንደ ተአምር የሚታይ ነው " ከደብዳቤዎቿ እንደተረዳሁት ተሽሏት እንደማገኛት ተስፋ አድርጌ ነበር " አሁን ግን መሻል ብቻ ሳይሆን ደኅና የሆነች ትመስላለች " የምንለውን ትሰሚያለሽ ሳቤላ ? የዱሮ አበባነትሽ እንደዚህ ሆኖ የተመለሰው በተአምር ካልሆነ በቀር በሁለት ሳምንት ውስጥ ይህን ያህል መለወጥ አስቸጋሪ ነው " በውነትም ይህ አየር በበሽታ
ለተሰነከሉ ፍቱን መድኃኒት ነው ለማለት ይቻላል ” ብሎ መደነቁን ገለጸ "

የማበቧን ነገር ከሚስተር ካርላይል ስትሰማ ፊቷ የቅላት ዘረረት ጣለበት ነገር ግን መልኳን ያለመለመው ልቧን ያደስው አየሩ ወይም ቦታው አለመሆኑን ታውቅ ነበር ። ማወቁንም ለራሷ ጭምር ምስጢር አድርጋ አፍና ልትይዘው ብትመኝም ከራስ መሰወር ስለማይቻል በደንብ ታወቃት ስለዚህ የባሏን ከንድ ጭምድድ አድርጋ ይዛ ይህን ውስጥ ለውስጥ እየተስፃረግና እየተሳበ ፡ መንፈሷን የያዛውን አደገኛ ጠላት ነቅላ ለመጣል የመንፈስ ኃይል ለማግኘት ከልቧ ትጥር
ጀመር።

ስለ ልጆቹ ምንም ነገር አልነገርከኝም” አለችው ሳቤላ : ከባሏ ጋር ከክፍሎቿ ደረሱ " ፍራንሲዝ ሌቪሰን እንዲገባ ስለ አልተጠቀ ከደጅ ተመለሰ "

ሁሎም አንዳንድ ጊዜ ሳምልን አላሉህም ? አርኪባልድ ልጄስ ሳምልኝ ብሎ አልላከህም ?

ሚስተር ካርላይል ሣቀ “ እሱ አባት እንጂ እናት አይደለ " ኤርኪ በአንድ ዓመቱ እናቴን ሳምልኝ ብሎ ሊልክ ! ማሰቧም ቢጨንቃት ነው "

“ እንደኔ ከቤት ውጥተህ ብትሆን ኖሮ ጥቂት ይልክልህ ነበር እኔ ብሆን አንድ ሺ ጊዜ ስሜው ሳበቃ ለአባትህ እሰጥልሃለ እለው ነበር "

“በይ እንዲያው እኔም አሁን ስመለስ አንድ ሺ ጊዜ እስምሽና እስድለታለሁ”አላት ሚስተር ካርላይል ሚስቱን ከልቡ ልጥፍ አድርጐ እያቀፈ " የኔ ፍቅር
አንቺን በማየት ብቻ ልቤ በደስታ ተሞላ "

በበነጋው እሑድ ነበር » ፍራንሲዝ ሌቪሰን ለመጀመሪያ ጊዜ ራት ተጠርቶ መጣ " ከራት በኋላ ሳቤላ ትታቸው ስትወጣ ከሚስተር ካርላይል ጋር የምስጢር
ወግ ያዙ ህልቆ መሳፍርት የሌለውንና ውስብስብ ያለውን ችግሩንና ጣጣውን ዘከዘከለት
አሁን በዚህ የግዳጅ ስደት ካገር ወጥቸ መኖሩን አልችለው አልኩ
በተለይ የፓሪስ ነሮ አስጨነቀኝ » አሁን ለኔ ኢንግላንድ የምመለስበትን መንግድ
ብትመክረኝ ” አለው "
👍14
“ እንደምትነግረኝ ከሆነ የባለዕዳዎችህን ጥያቄ በከፊል እንኳን ካላሟላህ ምንም መንግድ አይታየኝም -ሰር ፒተር አይረዱህም ?

“ ነገሩ በደንብ ሊብራራለት ቢችል እንኳን ይረዳኝ ነበር ብዬ አስባለሁ" ግን እንዴት አድርጌ ቀርቤ ማስረደመት እችላለሁ
በቅርቡ ብዙ ደብዳቤዎች ጽፌለት ነበር አንድም መልስ አጣሁ በዚያ ወር ፒተር ሌቪሰን ስለ ታመሙ ማንኛውንም
ጉዳይ ማየት እንደማይችሉ የሚገልጽ አንድ አጠር ያለ ደብዳቤ ከወይሮ ሌቪሰን
ደረሰኝ "

ሊታመሙ አይችሉም” አለው ሚስተር ካርላይል ባለፈው ሳምንት በግልጽ ሰረግላቸው ሆነው በዌስት ሊን ሲያልፉ አይቻቸዋለሁ "

«ሊረዳኝ ይገባዋል ሚስቱ ካልወለደችለት በቀር ወራሹ እኔ ነኝ እሷም ብትሆን እስከ አሁን ማርገዟን አልሰማሁም "

“ እንደ ምንም ብለህ ልታገኛቸው ይገባል።

በርግጥ ከሱ ጋር መገናኘት እንዳለብኝ ዐውቃለሁ እነዚህ መብረቅ ያዘሉ ጥቁር ደመናዎች በኔ እያንዣበቡብኝ ፊቴን ወደ ኢንግላንድ አልመልሰውም
ከሔድኩ አፉን ከፍቶ ወደሚጠብቀኝ ወህኒ ቤት ያስገባኛል " እኔ አንዳንድ ፈተናዎችን መቀበል እችላለሁ " የወሀኒ ቤትን ነገር ግን ሳስበው እንኳን ይዘገንነኛል ።

“ ሌላ ሰው ሊያነጋግርልህ ይችላል "

“ ሌላ ሰው ማን ? ከጠበቆቼ ጋር እንደሆነ ተቆራርጫለሁ " አጎቴ ካገባ በኋላ በጣም ነው የተጫወቱብኝ

“ ታድያ ሰር ፒተር ሌቪሰንን እኔ ላነጋግርልሃ ?

"አዬ ! -- ከሆነማ ”

ከፈለግህ በወዳጅነቴ ነው
ገባህ ? በጠበቃነቴ አይደለም “ ከእኔ ጋር እንኳን ደህና አድርገን አንተዋወቅም " ከአባቴ ጋር በደንብ ይተዋወቁ ነበር "
ስለዚህ ምን ያህል እንደሚሳካልኝ አላውቅም እንጂ አንተ ሚስቴን ስለ ረዳህልኝ እኔም እሳቸውን አነጋግርልሃለሁ " ነገር ግን በነዚህ ሁለት ሦስት ሳምንቶች ውስጥ
ቃል ልገባልህ አልችልም ምክንያቱም በጣም ሥራ ይበዛብኛል ይህ ውጥረት
ባይኖርብኝ ኖሮ ከሚስቴ ጋር እዚህ እሰነብትም ነበር።"

ፍራንሲዝ ሌቪሰን ምስጋናውን ገለጸለት " ምንም እንኳን ወደ ኢንግላንድ የመመለሱ ተስፋ እሩቅና ያልተጨበጠ ቢሆንም በጣም ተደሰተ እነሱ ወጋቸውን
ሲቀጥሎ ሳቤላ ከነሱ ቀጥሎ ከነበረው ክፍል በመስኮቱ አጠገበ ተቀምጣ የእሑድ ልብሶቻቸውን ለብሰው ወዲያና ወዲሀ ሲተረማመሱ ወደቡን ያጣበቡትን ፈረንሳዮች በልቧ ሳይሆን በዐይኗ ብቻ ፍዝዝ ብላ ትመለከታቸው ነበር ልቧማ ከሷ ጋ ሙግት ገጥሞ ነበር ደስ የማይል ሙግት አንድ የጋለ ስሜት ወደ ፍራንሲዝ
ሌቪሰን የሚስብ ስሜት ሳትለው ሳትፈልገው ከቁጥጥሯ ውጭ በውስጧ እንደሚላወስ ይታወቃት ነበር " ልታምቀው እንደሌለ አድርጋ ልታጠፋው አልቻለችም
የሕሊናዋ ድምፅ ደግሞ፡ ከዚህ ስሜት ጋር ተደባልቆ ልብ ከሚያጠፋ ጭንቀት አስግብቷታል ይህን ስሜት ለማሸነፍ ከዚህ ሰው ጋር ባንድ ጊዜ ለዘለአለም ለመለያየት ያላትን ሀብት ሁሉ ብትከፍል ወይም ከቀሪው ዕደሜዋ ግማሹን ብትሰጥ ትወድ ነበር ።

ጭንቀት ሲባል ሳቤላ ቬን ራሷን ትጠራጠር ነበር ማለት አይደለም በራሷ ሥነ ምግባርና ጠባይ ትተማመን ነበር » እንደሷ ያለች የታረመች የጨዋ ልጅ የሚስትነት ግዴታዋን ትጥላለች ማለት ፀሐይ ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ ጠለቀች ማለት መሆኑን ታምንበት ነበር " እሷ የፈራችውና የጠላችው ከዚህ ሰው ጋር ጓዶኝነት መግጠሙን በተለይ ደግሞ ሁለቱ ብቻ ሲሆኑ ለሱ ያላትን ስሜት ከፍ አድርጎ
እንዳያስብና መጪው ሕይወቷንም የሀዘንና የሠቀቀን ዘመን እንዳይሆንባት ነበር ከሁሉ በላይ ደግሞ ይህን ስሜት በባሏ አንጻር ስትመለከተው ከሕሊና የማይጠፋ መራራ በደል መሆኑ ሲሰማት ሽምቅቅ ትል ነበር ።
አርኪባልድ. . . አንድ ነገር ልለምንህ " አለችው ካፒቴን ሌቪሰን ከወጣ በኋላ አብረው እንደ ተቀመጡ እሺ ልትለኝ ቃል ግባልኝ በመጀመሪያ።

" የምችለው ከሆነ ግድ የለም ። "

ከእንግዲህ እዚህ ለምቆይበት ጊዜ አብረኸኝ እንድትሰነብት እፈልጋለሁ በመገረም ቀና ብሎ አያትና የኔ ፍቅር . .. ወቅቱ ተዘዋዋሪ ዳኞች የሚመጡብት መሆኑን እያወቅሽ እንዴት እንደዚህ ብለሽ ትጠይቂኛለሽ ?

“ አርኪባልድ ምንም ቢሆን አብረኸኝ መሰንበት አለብህ …”
ቢሆንልኝ ኖሮ በጣም ደስ ባለኝ ግን የሚሆን አይደለም " የማይቻል መሆኑን አንቺም ታውቂዋለሽ " ከጥቂት ሳምንት በኋላ እንኳን ቢሆን እስከ መጨረሻ አብሬሽ መቆየት እችል ነበር በእነዚህ አሁን ወደዚህ በመጣሁባቸው ሁለት ሦስት
ቀኖች ውስጥ እንኳን ብዙ ነገር ይበላሽብኛል "

“ እና ነገ መሔድህ ነው?”

“ ለብሶት ሕግ የለውም የኔ ፍቅር

“ በል እንግዲያውስ ይዘኼኝ ሒድ

ሚስኵር ካርላይል ሣቅ አለ ። ይኸማ አይሆዓም ... ሳቤላ " ለውጡ ብዙ እንደ ረዳሽ እያየሁ አቋርጬ አልወስድሽም " ደግሞ እነዚህ ክፍሎች የስድስት ሳምንት ሒሳብ የከፈልኩባቸው ስለሆነ ባይሆን ከዚ በላይ መቆየትሽ ይቅር እንጂ የሒሳቡ ጊዜ እስከያበቃ መሰንበት አለብሽ "

ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ “ እኔ አን† በሌለህበት መቆየት አልችልም ”

“ ለምን እኮ?ምክንያቱን ንግሪኝ ” አላት ሚስተር ካርላይል ሳቅ ብሎ ምን ብላ ትንገረው ? የተሻለ መከራከሪያ መልስ ሆኖ ያኘችው አንተ አጠግቤ ከሌለህ
ሁሉ ነገር ያስጠላኛል ” ማለት ብቻ ነበር " በቂና ሊቀበላት የሚችል ምክንያት እንዳልነበርም ዐውቃው ነበር "

እውነትም ተቀባይነት አልነበረውም ሚስተር ካላይልም በበነጋው ተነሥቶ ሔደ ልክ ሲሳፈር ካፒቴን ሌቪሰን ሚስቱን እንዲረዳለት ወደፊትም ዕርዳታው
እንዳይለያት አደራ አለው የዚህ ዐይነቱ አደራ መልካም እንዳልነበር በአእምሮ አልመጣለትም የራሱን ታማኝነትና በጎ ሰውነት በማየት ካፒቴን ሌቪሰንንም ከሱ ያነሰ ምግባር ይኖሪዋል ብሎ አልጠረጠም ሚስቱን እንደሆነ ከሌቬስን ጋርም ሆነ ከሌላ ሰው ከማይኖርበት ምድረ በዳ ቢተዋትም አይሰጋባትም ነበር "
በሷ ላይ ፍጹም የሆነ እምነት ነበረውና.....

💫ይቀጥላል💫
👍112
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ


“እንዲያውም የእህትህን ቆንጆ ፀጉር የምትሸልተው አንተ
መሆን አለብህ!” ብላ ሚስጥራዊ ፈገግታ ብልጭ አደረገችና በመልበሻው አናት ላይ መቀሱን አስቀመጠች: “ተመልሼ ስመጣ እህትህ ፀጉሯ ተቆርጦ ካገኘሁ
ብቻ አራታችሁም ምግብ የማግኘት እድል ይኖራችኋል።" ስትል ክሪስ እኔ ላይ፣ እኔም ክሪስ ላይ እንዳፈጠጥን ጥላን ሄደች:...

ክሪስ ፈገግ አለ: “አይዞሽ ካቲ መቼም ቢሆን ፀጉርሽን አልቆርጥሽም።እናታችን በየትኛውም ሰአት ተመልሳ ስለምትመጣ እንነግራታለን፡ አይዞሽ አትፍሪ መቼም ቢሆን ፀጉርሽን አልቆርጥሽም::” ሊያቅፈኝ ወደኔ መጣ፡ “በዛ
ላይ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል አንድ ካርቶን ብስኩትና አይብ መደበቃችን መታደል አይደል? ያቺ ጠንቋይ አሮጊት ይህንን ስለማታውቅ ለዛሬ ምግብ
ይኖረናል:” አለ።

ድንገት እናታችን ካልመጣች ብለን በመስጋት ያን ዕለት ትንሽ ብቻ በላን።ግማሹን ወተትና ጥቂት ብርቱካኖች አስቀመጥን፡ ይሁንና እናታችን ሳትመጣ ቀኑ አለቀ: ምሽቱን ሙሉ አንዴ ስተኛ፣ አንዴ ስነቃ እንዲችው ስገላበጥ
ሌሊቱ ተጋመሰ፡ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርገኝ አሰቃቂ ቅዠት ይመጣብኛል።ኮሪና ኬሪ ጠፍተውብን ክሪስና እኔ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ ውስጥ በጨለማ ስንፈልጋቸው አየሁ ስማቸውን እየጠራን ብንፈልጋቸውም እነሱ
ግን መልስ አይሰጡንም፡ በፍርሀት ውስጥ ሆነን በጨለማ እየሮጥን ነበር።
በጣም የሚያስጨንቅ ህልም ነበር። ስነቃ ክሪስም መንትዮቹም ተኝተዋል።እንደገና እንቅልፍ እንዳይወስደኝ ፈለግኩ፡ ልከላከለው ሞከርኩ፡ ቀስ እያልኩ
እየሰመጥኩ እየሰመጥኩ እንደገና ጥልቅ ቅዠት የተቀላቀለበት አስፈሪ ህልም ውስጥ ገባሁ፡ በጨለማ እየሮጥኩ በደም የተሞላ ኩሬ ውስጥ ወደቅኩ ደሙ ልክ እንደሬንጅ ያጣብቃል ሽታውም እንደ ሬንጅ ነው: በአልማዝ ያሸበረቀ፣ጭንቅላቱ የወርቅና አይኖቹ ቀይ የሆኑ አሳ እየሳቀ ደም በደም አደረገኝ፡
ከዚያ ደጋግሞ የሚያስተጋባ ድምፅ “እይ! እይ! ማምለጥ አትችይም!” እያለ ጮኸ፡

ማለዳው ቢጫውን የተስፋ ብርሃን ከዘጋው ከባድ መጋረጃ ጀርባ የገረጣ መስሎ ይታያል፡ ኬሪ በእንቅልፍ ልቧ ወደኔ እየተጠጋች “እማዬ፣ ይህንን ቤት አልወደውም” ስትል አጉረመረመች: ኬሪ ያለ እረፍት ስትገላበጥ ላቅፋት ፈልጌ ክንዴን ለመዘርጋት ብሞክርም ማንቀሳቀስ አልቻልኩም:: ምን ሆኛለሁ? ራሴ ልክ ድንጋይ እንደተጫነ አይነት ከበደኝ፡ ከህመሙ የተነሳ ጭንቅላቴ
ሊከፈል መሰለኝ፡ የእግሮቼና የእጆቼ ጣቶች ላይ ይወረኛል። ሰውነቴ ድርቅ ብሏል ግድግዳዎቹ ሁሉ የተጣመሙ ይመስሉኛል። ሁሉም ነገር ቀጥ ያለ መስመር የለውም።

ከአልጋው ባሻገር ባለው በሚያብረቀርቀው መስተዋት ራሴን ለማየት ሞከርኩ::
ሆኖም የከበደኝን ጭንቅላቴን ዞር ላደርገው ብሞክርም አልንቀሳቀስ አለኝ::ሁልጊዜ ከመተኛቴ በፊት ጭንቅላቴን እንደልብ ማዘዋወር እንድችል ፀጉሬን ትራሱ ላይ እበትነዋለሁ ግማሹ ጉንጬ ላይ ያርፋል: እና ደስ የሚል ሽታውና ልስላሴው በጣም ደስ ይለኛል። የፀጉሬ ጉንጬ ላይ መነስነስ ወደ
ጣፋጭ የፍቅር ህልም ይወስደኛል።

ዛሬ ግን ትራሱ ላይ ፀጉር የለም: ፀጉሬ የት ሄዶ ነው?

መቀሱ አሁንም መልበሻው አናት ላይ እንደተቀመጠ ነው: በድንግዝግዝ ይታየኛል፡ ጉሮሮዬን ለማርጠብ ምራቄን ደጋግሜ ዋጥኩና በግድ ትንሽ ድምፅ
አውጥቼ የክሪስን ስም ተጣራሁ። ወንድሜ ክሪስ እንዲሰማኝ እንዲያደርግ ወደ እግዚአብሔር ፀለይኩ። በመጨረሻ እንግዳ በሆነ ድምፅ “ክሪስ፣ የሆነ
ነገር ሆኛለሁ፡” ብዬ በሹክሹክታ መናገር ቻልኩ። ደካማዎቹ ቃላቶቼ እንዴት እንደተሰሙ ባላውቅም ክሪስን አነቁት ከእንቅልፉ በደንብ ሳይነቃ አይኖቹን እያሻሽ ካቲ ምን ፈልገሽ ነው?” አለኝ።

ከአልጋው ላይ አስፈንጥሮ ያስነሳው የሆነ ነገር አልጎመጎምኩ፡ አልጋዬ
አጠገብ ደረሰ፡ ትንፋሹን ውጦ በድንጋጤና በፍርሀት ድምፅ አወጣ፡

“ካቲ… ወይኔ አምላኬ ሆይ!”

ጩኸቱ በፍርሀት አሳቀቀኝ

'ካቲ ‥. ወይኔ ካቲ" ሲል አቃሰተ።

አይኖቹ እንዲህ በድንጋጤ እንዲፈጡ ያደረጋቸው ምን እንደሆነ ለማወቅ አልታዘዝ ያሉኝን ክንዶቼንና ያበጠ የመሰለኝን ከባድ ጭንቅላቴን ለማንቀሳቀስ
ሞከርኩ፡ እንደምንም እጄን ማንሳት ቻልኩ ከዚያ ለመሰማት የሚችል ጮክ ያለ ድምጽ አገኘሁና የእውነት ጮህኩ። ደግሜ ደጋግሜ ጮህኩ ክሪስ
በክንዶቹ አቅፎ እስኪያባብለኝ ድረስ ልክ አእምሮው እንደተነካ ሰው እየጮህኩ ነበር።

“እባክሽ አቁሚ… እባክሽ” ተንሰቀሰቀ። “ስለ መንትዮቹ ስትይ... የባሰ አታስፈራሪያቸው.
እባክሽ ካቲ አትጩሂ፡ ያሳለፉት
ይበቃቸዋል።እስከመጨረሻው ፈሪ እንዲሆኑ እንደማትፈልጊ አውቃለሁ: ካልተረጋጋሽ
ይደነግጣሉ። እመኚኝ በህይወቴ እምልልሻለሁ። ዛሬ እንደምንም ሬንጁን ከፀጉርሽ ላይ አስለቅቅልሻለሁ "

አያትየው ከእንቅልፌ እንዳልነቃ የሆነ መድኃኒት የወጋችኝን ምልክት ክንዴ ላይ አገኘሁ እና እንደተኛሁ ትኩስ ሬንጅ ፀጉሬ ላይ አፍስሳብኛለች: አንድም
ዘለላ እንዳይቀር ሬንጁን ከመጠቀሟ በፊት ፀጉሬን በደንብ ሳትሰበስበው አልቀረችም።

ክሪስ መስተዋት እንዳላይ ቢከለክለኝም ገፍትሬው መስታወቱ ላይ ተሰየምኩ።
ጭንቅላቴ አስፈሪ ጥቁር ጓል የተቀመጠበት መስሎ ሳይ አፌ በድንጋጤ ተከፈተ በመጀመሪያ የነቃው ኮሪ ነበር የተዘጋውን መጋረጃ ገለጥ አድርጎ ከእሱ
የተሸሸገችውን ፀሀይ ለማየት ከአልጋው ወጥቶ ወደ መስኮቱ እየሮጠ ሳለ ድንገት ሲያየኝ አይኖቹ ፈጠጡ፡ ከዚያ ትንንሽ እጆቹ አይኖቹን ለማሻሽት
ከፍ አሉና ባለማመን እንደገና አተኩሮ ተመልክቶኝ፡-

"ካቲ አንቺ ነሽ?” አለ፡

“አዎ”

“ፀጉርሽ ለምን ጥቁር ሆነ?"
ለዚያ ጥያቄ መልስ ከመስጠቴ በፊት ኬሪ ነቃች። “ወይኔ!” ስትል ጮኸች። ካቲ ጭንቅላትሽ ምን ሆኖ ነው?! ትልልቅ እምባዎች ከአይኖቿ ወደ ጉንጮቿ ወረዱ፡ “አሁን ጭንቅላትሽን አልወደድኩትም” ስትል ሬንጁ እሷ
ፀጉር ላይ እንደሆነ ሁሉ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።

“ተረጋጊ ኬሪ” አለ ክሪስ በተረጋጋ ድምጽ። ካቲ ፀጉር ላይ ያለው ሬንጅ ነው: አሁን ስትታጠብና ሻምፑ ስታደርግበት ልክ እንደ ትናንቱ ይሆናል፡ እሷ ስትታጠብ እናንተ ሁለታችሁ ደግሞ ቁርስ እስኪቀርብ ብርቱካን እየበላችሁ
ቲቪ ተመልከቱ፡ በኋላ የካቲ ፀጉር ንፁህ ሲሆን ሁላችንም ቁርሳችንን
እንበላለን፡" አለ፡ ስለ ሁኔታችን የባሰ ፍርሀት እንዳይሰማቸው በማለት የአያታችንን ስም አልጠቀሰም ስለዚህ ወለሉ ላይ ተጠጋግተው በመቀመጥ
እርስ በርስ እየተረዳዱ ብርቱካኑን እየላጡ እየበሉ ራሳቸውን በቴሌቭዥን በሚተላለፈው የቅዳሜ ጠዋት የካርቱን ፊልም ውስጥ ከተቱ..

ክሪስ ገንዳው ውስጥ የሞቀ ውሀ ሞላልኝ: በዚያ በሚፋጅ ውሀ ውስጥ ፀጉሬን ደግሜ ደጋግሜ ነከርኩት። ክሪስ ደግሞ ሬንጁ እንዲላላ ለማድረግ ሻምፑ እያደረገ ነበር። ሬንጁ ቢላላም ከፀጉሬ ውስጥ ሊወጣ አልቻለም:
ጣቶቹ በሚያጣብቀው የሬንጅ ክምር ውስጥ ገቡ። ፀጉሮቼን ሳይነቅል ሬንጁን
ለማውጣት እየሞከረ ነው: ግብግቡ ስላደከመኝ ማሰብ የቻልኩት ስለ መቀሱ ብቻ ነው: አያትየው መልበሻው አናት ላይ ስላስቀመጠችው የሚያንፀባርቅ
መቀስ።

ክሪስ ገንዳው አጠገብ ተንበርክኮ የሬንጁን ክምር ከፀጉሬ ውስጥ ሲያወጣ ሬንጁ በፀጉሮቼ የተሸፈነ ነበር፡ ሬንጁን ከፀጉሬ ውስጥ ለማውጣት ስንሞክር
ከሁለት ሰዓት በላይ ሆኖን ነበር። “መቀሱን መጠቀም አለብህ!” ብዬ ጮህኩ።

“አይሆንም መቀስ የመጨረሻ ምርጫችን ነው” አለ እናታችን ያመጣችለትን የኬሚስትሪ ዕቃዎች በመጠቀም ፀጉሬ ሳይጎዳ ሬንጁን የሚያሟሟ ኬሚካል መቀመም እንደሚችል አስቧል።
👍303👏3
“ካቲ” አለ ጫማ ያላደረገ ተረከዙ ላይ ቁጢጥ እያለ። “ጣራ ላይ ወዳለው የመማሪያ ክፍል ሄጄ ሬንጁን ከፀጉርሽ ላይ የሚያስለቅቅ የሆነ ነገር
ለመቀመም ልሞክር” ሲል የእፍረት ፈገግታ ፈገግ አለልኝ። hኮርኒሱ ላይ የሚመጣው ብርሃን የላይኛው ከንፈሩን የሸፈነውን ሳሳ ያለ ፀጉር አሳየኝ ልክ እንደኔ በታችኛው የሰውነት ክፍሉ ላይ የዚህ አይነት የጠነከረና የጠቆረ
ፀጉር እንዳለው አውቃለሁ። “ካቲ፣ ሽንቴን መሽናት አለብኝ፡ አንቺ ፊት
አድርጌው ስለማላውቅ ትንሽ አፍሬያለሁ። ብትፈልጊ ጀርባሽን ማዞርና ጆሮዎችሽን በጣቶችሽ መድፈን ትችያለሽ፡ በሽንቱ ውስጥ ያለው አሞኒያ ፀጉርሽን ያስለቅቅልሽ ይሆናል።

በመገረም አተኩሬ ተመለከትኩት በሞቀ ውሀ ውስጥ ተቀምጨ ፀጉሬን በሽንት ልታጠብ ነው? ይህ ነገር በውኔ ነው? ሊሆን አይችልም: ይህ እውነት አይደለም ይሄ ህልም ነው አልኩ ለራሴ።

ግን እውን ነበር ኮሪና ኬሪ እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ መታጠቢያው መጡና
በጥያቄ ያደርቁኝ ጀመር።

“ካቲ፣ ፀጉርሽ ላይ ያለው ነገር ምንድነው?”

“ለምንድነው ፀጉርሽን ሬንጅ የቀባሽው?”

“በእንቅልፍ ልቤ አድርጌው መሆን አለበት”

“ሬንጁን ከየት አገኘሽው?”

“ጣሪያው ስር ካለው ክፍል”

“ሬንጅ ፀጉርሽን መቀባት የፈለግሽው ለምንድነው?”

መዋሸት አስጠልቶኛል: ለኬሪ ፀጉሬ ላይ ሬንጅ ያደረገብኝ ማን እንደሆነ ልነግራት ብፈልግም ያንን ግን ማድረግ አልችልም እሷና ኮሪ አሁንም ያቺን አሮጊት በጣም ይፈሯታል፡ “ሂዱና ቲቪ ተመልከቱ ኬሪ” ስል አዘዝኳት።
በምትጠይቃቸው ጥያቄዎች ስሜቴ በመነካቱ የጎደጎዱ ከሲታ ጉንጮቿንና ወደ ውስጥ የገቡ አይኖቿን ማየት ከብዶኛል፡

ካቲ ከአሁን በኋላ አትወጂኝም?” ጠየቀ ኮሪ

“እንዴ! እወድሀለሁ እንጂ ኮሪ… ሁለታችሁንም እወዳችኋለሁ። ሬንጁን ፀጉሬ ላይ ያደረግኩት በስህተት ነበር አሁን ግን በራሴ ተናድጃለሁ።"

ኬሪ እንደገና ኮሪ አጠገብ ሄደችና እነሱ ብቻ በሚግባቡበት የተለየ ቋንቋ ተንሾካሾኩ: አንዳንድ ጊዜ እኔና ክሪስ ከምናውቃቸው በላይ ብልሆች ይመስሉኛል።

ለሰዓታት መታጠቢያ ገንዳው ውስጥ ነበርኩ። ክሪስ በደርዘን የሚቆጠሩ ውህዶችን በትንሹ የፀጉሬ ክፍል ላይ እየሞhረ ነበር ሁሉንም ነገር ሞከረ ውሀውን ቶሎ ቶሎ እንድቀይርና በጣም ሞቅ ያለ እንዳደርገው ነገረኝ፡ ቀስ
በቀስ ሬንጁ ከፀጉሬ ላይ እየለቀቀ መጣ ብዙ ፀጉሮቼን የነቃቀለው ሬንጅ በመጨረሻ ሙሉ በሙሉ ለቀቀ 😄 አስለቅቀን ስንጨርስ ቀኑ አልቆ ነበር። በዛ ላይ እኔም ሆንኩኝ ክሪስ አንድ ጉርሻ ምግብ እንኳን በአፋችን አልዞረም ነበር።

ለልጆቹ አይብና ብስኩቶች ሰጣቸው ለራሱ በመብላት ግን ጊዜ ማባከን አልፈለገም፡ እኔም በፎጣ ተጠቅልዬ አልጋው ላይ ተቀምጬ የሳሳውን ፀጉሬን ማድረቅ ጀመርኩ። የቀረው ፀጉሬ አቅም ያጣ በቀላሉ የሚሰባበርና
ቀለሙም የተለየ ሆኖ ነበር
ክሪስ በተራበ ስሜት ሁለት ብስኩቶችን በቺዝ እየበላ “ሙሉ ፀጉርሽን እስካልቆረጥሽው ድረስ ምግብ የሚባል አታመጣም፡ ራስሽን ለማበርታት ጥረት ማድረግ አለብሽ፡" አለኝ፡፡

ብስኩትና ቺዝ ከአንድ ብርጭቆ ውሀ ጋር በሳህን ላይ አድርጎ ወደኔ ይዞ መጣና! “ብይ… ጠጪ እናሸንፋታለን፡ ነገ ምግብ ካላመጣችልንና እናታችንም
ካልመጣች ከፊት ከግንባርሽ ጋር ያለውን ፀጉርሽን እንቆርጠዋለን፡ ከዚያ ፀጉርሽ በሙሉ የተቆረጠና መላጣ መሆንሽ እንዳይታይ አፍረሽ እንዲመስል ጭንቅላትሽን በአንገት ልብስ ትጠመጥሚያለሽ፡ ፀጉርሽ ፈጥኖ ያድግልሻል::
ምንም መልስ ሳልሰጥ ቺዙንና ብስኩቶቹን በላሁ። ከመታጠቢያ ቤቱ ቧንቧ በተቀዳ አንድ ብርጭቆ ውሀ የቀኑን ምግቤን አወራረድኩት። ክሪስ ያንን
የሳሳና ብዙ ነገር የቻለ ፀጉሬን አበጠረልኝ፡ ከዚያ በጣም ደክሞኝ በጀርባዬ አልጋው ላይ ጋደም አልኩ፡ ክሪስ አልጋው ላይ ተቀምጦ እያየኝ ነው እንቅልፍ ወሰዶኝም እየጠበቀኝ ነበር፡ እጆቹ እንደ ሸረሪት ድር የቀጠነውን
ረጅሙን ፀጉሬን ይዘው ነበር።

ያን ዕለት ምሽት እንቅልፍ ሸለብ መለስ እያደረገን ማረፍ አቅቶን ነበር:: አቅመቢስነት፣ ንዴትና ተስፋ መቁረጥ ተሰማኝ፡ ከዚያ ክሪስን አየሁት።

ቀን የለበሰውን ልብስ እንደለበሰ ነው ከባዱን ወንበር በሩ አጠገብ አድርጎታል።በእጁ ደግሞ መቀስ ይዟል፡ አያትየው እንደገና ሳትታይ ገብታ መቀሱን እንዳትጠቀም መንገድ መዝጋቱ ነበር በእንቅልፍ ላይ ሆኖ እንኳን ከሷ እየጠበቀኝ ነው።

ወደ እሱ ስመለከት አይኑን ከፈተና ጥቃት ደርሶብኝ ሳይከላከልልኝ የቀረ መስሎት ዘሎ ተነሳ፡ በዚያ በተቆለፈ ክፍል ደብዛዛ ብርሀን አይኖቻችን ተገናኙ: ፈገግ አለና በቀስታ “ሰላም” አለኝ።

“ክሪስ እባክህ ተኛ! ለዘለዓለም ልትጠብቃት አትችልም” አልኩት።

“አንቺ ስትተኚ ልጠብቃት እችላለሁ”

“እንደዚያ ከሆነ ተራ እንግባ”
“ወንዱ ማነው አንቺ ወይስ እኔ? በዚያ ላይ እኔ ካንቺ የበለጠ በልቻለሁ''

“ምን አገናኘው?”

“አሁን አንቺ በጣም ቀጭን ነሽ፡፡ በዚያ ላይ ሌሊቱን ሳትተኚ ካደርሽ የበለጠ ቀጫጫ ትሆኛለሽ፡፡ እኔ ግን ትንሽ ክብደት ብቀንስ ምንም አይደል"

እሱ ራሱም ከክብደት በታች ነው: ሁላችንም እንደዚያ ነን፡ እና አያትየው የእውነት በሩን ለመክፈት ከፈለገች የሱ ክብደት ሊያስቀራት አይችልም እሱ አይሆንም ሲል አጥብቆ ቢቃወመኝም ከተኛሁበት ተነስቼ አብሬው ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡

“ግዴለህም. አንድ ላይ ከሆንን በተሻለ እንቋቋማታለን አሁን ሁለታችንም መተኛት እንችላለን"

አልኩትና እቅፍቅፍ ብለን ተኛን፡
ያለ አያትየው ያለ ምግብ ጠዋት ሆነ።

የረሀብ ቀናቶቻችን ያለማቋረጥ እያለፉ ነው በቅርቡ ቺዙና ብስኩቶቹ ያልቃሉ: ያን ጊዜ የበለጠ መሰቃየት እንጀምራለን
እኔና ክሪስ ውሀ ብቻ እየጠጣን ወተቱን ለመንትዮቹ እያስቀመጥን ነው ።

ምግቡአሁንም ስላልመጣ፣ ክሪስ አይኖቹ እምባ እንዳቀረሩ መቀሱን ይዞ ወደኔ መጣና የራስ ቅሌ እንዲታይ አድርጎ ከፊት ያለውን ፀጉሬን ቆረጠው፡ ክሪስ እንደዚያ ሲያደርግ መስታወት አላየሁም: የተረፈውን ረጅሙን ፀጉር
ጠቀለልኩትና የአንገት ልብሱን እንደ ጥምጥም ተጠቀምኩበት
እጅግ በጣም የሚያሳዝነው ነገር አያትየው ፀጉሬ መቆረጡን ለማየት እንኳ አለመምጣቷ ነው ምግብ ወይም ወተት ወይም ፎጣዎች ወይም ሊያልቁብን
የሚችሉ እንደ የልብስና የጥርስ ሳሙና የመሳሰሉትን ነገሮች እንኳን አላመጣችልንም የመፀዳጃ ወረቀትም እንኳን። አሁን ላይ ውድ ልብሶች የተገዙልን ጊዜ የተጠቀለሉበትን ለስላሳ ወረቀቶች መጣሌ ቆጨኝ። ማድረግ የምንችለው ነገር ስላልነበረ hአሮጌዎቹ መፃህፍት ገፆች እየቀደድን መጠቀም
ነበረብን።

ከዚያ የሽንት ቤቱ ማጠራቀሚያ ተዘጋና ወደ ውጪ መፍሰስ ጀመረ።ቆሻሻው መታጠቢያ ቤቱን ሲሞላው ኬሪ መጮህ ጀመረች። የተደፈነውን ቱቦ መምጠጫ ስለሌለን ክሪስና እኔ ምን ማድረግ እንዳለብን ተጨነቅን፡ ሮጦ
የልብስ መስቀያ ሽቦ አመጣና ቀጥ እንዲል አድርጎ መተላለፊያውን የዘጋውን
ነገር ወደታች ለመግፋት ሞከረ፡ እኔም ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ሄጄ ፈሳሹን የምጠርግበት አሮጌ ልብሶች አመጣሁ።

የሆነው ሆኖ ክሪስ የልብስ መስቀያ ሽቦውን በመጠቀም ሽንት ቤቱ እንደገና መስራት እንዲችል አደረገ ከዚያ ቃል ሳይናገር አጠገቤ በጉልበቱ ተንበርክኮ ጣሪያው ስር ካለው ክፍል ሻንጣዎች ውስጥ ባመጣሁት ጨርቆች ወለሉን
አብረን ማፅዳት ጀመርን።

አሁን ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ባለው ሚስጥር ላይ ቆሻሻና የሚሸቱ ጨርቆች በሻንጣዎቹ ውስጥ በመክተት ሌላ ሚስጥር ጨመርንበት....

ይቀጥላል
👍3216🔥4😢2👏1
አትሮኖስ pinned «#የጣሪያ_ስር_አበቦች ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_አራት ፡ ፡ #ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ “እንዲያውም የእህትህን ቆንጆ ፀጉር የምትሸልተው አንተ መሆን አለብህ!” ብላ ሚስጥራዊ ፈገግታ ብልጭ አደረገችና በመልበሻው አናት ላይ መቀሱን አስቀመጠች: “ተመልሼ ስመጣ እህትህ ፀጉሯ ተቆርጦ ካገኘሁ ብቻ አራታችሁም ምግብ የማግኘት እድል ይኖራችኋል።" ስትል ክሪስ እኔ ላይ፣ እኔም ክሪስ ላይ እንዳፈጠጥን ጥላን ሄደች:...…»
በህይወት መንገድ ላይ……
( ታጋቾቹ)

ምዕራፍ-2
በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
///
እንደምንም ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ቆምኩ ….ራመድ ራመድ ብዬ ተንቀሳቀስኩ.‹‹ሰላም ነሽ…?ምንም ጉዳት አልደረሰብሽም…?››አዲሷን ልጅ ነው የጠየቅኩት
‹‹ደህና ነኝ መሰለኝ..ግን ምንድነው የሆነው .?ማለቴ ህልም አይደለም አይደል?፡፡››እያለች በቀስታ ተነሳችና እኔ እንዳደረኩ በማድረግ ደህንነቷን አረጋገጠች››
ቀድማ ተነስታ በአፈር የተበከለውን ቀሚሷን እያራገፈች ያለችው አይዳ‹‹ እኔም ደህና ነኝ››አለቺኝ የአሽሙር ለዛ ባው ንግግር፡፡
እሷን ችላ አልኳትና አዲሷን ልጅ ‹‹ህልም ይሁን አይሁን እርግጠኛ አይደለሁም…››ስል መለስኩላት፡፡
‹‹እናንተስ ጋሽ አህመድ?››
‹‹አረ በአላህ….ምንድነው የሆነው?››
‹‹ተገላገልን ….በአቆራጭ ወደገነት እየተጓዝን ሳይሆን አይቀርም››በሪሁን ነው የተጋጋጠ እጁን እያሻሸ የተናገረው፡፡
‹‹.ሁላችንም አለመሰበራችንና አለመቁሰላችንም አንድ ነገር ነው፡፡››አልኩ
‹‹አለመቁሰላችንን ነው እንዴ ያያችሁት ….እሙሙዬ እኮ ቀላል አፈር አልቃመችም››ያቺው አይዳ ነች መላሿ
‹‹አሁን ምን እናድርግ?.››ጋሽ አህመድ ናቸው ተናጋሪው
‹‹ቆይ ሀሳብ መጣልኝ፡፡›እልኩና እጄን ወደኪሴ በመስደድ ሞባይሌን አወጣው ..ለመደወል ሞከርኩ …ምንም አይነት ኔት ወርክ የለም፡፡
‹‹አረ ምንም አይነት ኔት ወርክ የለም*››

ከአይዳ በስተቀር አራታችንም በየኪሳችን ሞባይላችን ይዘናል…የሁላችንም ግን ኔትወርክ ባዶ ስለነበር ለመደወልንና እርዳታ ለማግኘት አልቻልንም፡፡

‹‹ቆይ ጉድጓድ በጣም እሩቅ ነው እንዴ?››አዲሷ ልጅ ጠየቀች

‹‹እኛ ምናውቀው ጉድጓድማ ስድስት ሜትር ብቻ ነው፡፡ ይሄ ግን ጉድጓድ ጭምር ነው ተንዷ የሰመጠው...ወደታች ስንወርድ ረጂም ደቂቃ ነው የወሰደብን…. ምን አልባት 20 እና 30 ሜትር ወደውስጥ ሳንሰምጥ አልቀረንም...በጣም የሚገርመው ግን እዚህ አካባቢ ያለው መሬት አለታማና ድንጋያማ ነው፣እንዴት እንዲህ አይነት ነገር ሊከሰት እንደቻለ ለእኔ እንቆቅልሽ ነው ››ግምቴን ተናርኩ

‹‹እንደዛማ ከሆነ አልቆልናል በለኛ....ነግቶ እስከሚያዩን ድረስ ማንም አይደርስልንም ማለት ነው...ዘበኞቹም ወጥተን የሄድን ነው የሚመስላቸው" ጋሽ አህመድ ነው ስጋቱን የተናገረው፡፡

‹‹አሁን ተረጋግተን ማሠብ አለብን ››አልኳቸው እንዴት መረጋጋት እንደለብን እኮ ለራሴም አላውቅም።

አይዳ‹‹እሺ እንረጋጋ እውነትህን ነው›› ብላ ባለችበት ቁጢጥ አለች።

በሪሁን ከፊት ለፊታችን ወደ ወደቀው የ foothing ብረት ተንቀሳቀሰ….. ቀበቶው ላይ የሻጣውን ጉጠት አወጣና ስሩ ሲደርስ በርከክ በማለት በጉጠት እየተጠመዘዙና እርስ በርስ የተሳሰሩትን ብረት ለማላቀቅ ሽቦዎችን መፍታት ጀመረ ....እንደምንም አንድነጠላ ብረት አላቀቀ።ቀጥ አድርጎ ማቃናት ግን አይሞከርም።ብረቱ እንዳለ አጥብቆ ይዞ ከበላያችን ያለውን ከተቀረቀረው አለት ጎንና ጎን የተሠገሠገውን አፈር መግርጎር ጀመረ..እንግዲህ እንደገባኝ እቅዱ አፈሩ ተቦርብሮ ወደታች በመውረድ ከላይ ከመጣንበት የመሬት ወለል የሚያገናኝ ጭላንጭል ቀዳዳ ቢሆንም ማግኘት ነው።ሳስበው ጥሩ እቅድ ነው…፡፡

የታሰበው ቀዳዳ ከተገኘ ቢያንስ …. ኡ ኡ ብሎ በመጮህ ከላይ እርዳታ ለማግኘት ወይም ለምንደውለው ስልክ የሚሆን የሚቆራረጥም ቢሆን ኔት ወርክ ለማግኘት ይረዳን ይሆናል…ከዛም አልፎ በጣም እድለኞች ከሆን ደግሞ እንደምንም በመቧጠጥ ቢያንስ አንዳችን ወደላይ መውጣት እንድንችል ይረዳን ይሆናለል፡፡

በእውነት እቅዱ ጥሩ ነበር ግን ከላይ ያለውን አፈር በነካካነው መጠን አፈሩ ወደታች እየረገፈ በምትኩ ኮረትና ትላልቅ ድንጋይ እየመጣ በመሸንቀር እና በመጠቅጠቅ ክፍተቱን መድፈን ጀመረ …እንደውም ሲታይ ይበልጥ የታሰበበት ግንባታ መሠለ...ጋሽ አህመድና በሪሁን ተስፋ ከልቆረጡም፤ በእልክና በንዴት መናዳቸውን ቀጠሉ .

ድንገት የሆነ ከሰይጣን እጅ አፈትልኮ የወጣ የሚመስል አለት ድንጋይ ተምዘግዝጎ የበሪሁንን መሀል ጭንቅላት ላይ ቧ ብሎ አረፈ...ዋሻው ተናጠ…ወደኃላው ዘፍ ብሎ ወደቀ…….ዝርግትግት …ፀጥ..አለ…፡፡ ከጭንቅላቱ በቀይና በጥቁር መካከል ቀለም ያለው ደም ቡልቅ ቡልቅ እያለ ወለሉን አጠበው…..ሁለቱ ሴቶች እሪታቸውን አቀለጡት …አንደኛዋ ከጭንቅላቱ አንደኛዋ ከወደእግሩ ከበቡት…አይዳ እየተንቀተቀጠች አዲሷ ልጅ ደግሞ በመንሰቅሰቅ ላይ ነች፡፡ ..ጋሽ አህመድ ሲሰራበት የነበረውን ብረት ጥሎ ስሩ በርከከ ብሎ በህይወት መኖሩንና አለመኖሩን እጁን አንገቱ ጋር በመነካካት ለማረጋገጥ እየሞከረ ነው…..
ጌታ ሆይ ከአሁኑ የአንድ ሰው ህይወት አጣን ማለት ነው…..?ስል ደንዝዤ በቆምኩበት አሰብኩ …..መላ ሰውነቴ ልቆጣጠረው በማልችለው ፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ነው፡፡ እንግዲህ እንዲህ እንዲህ እያለ የሁላችንም ፍፃሜ በቅርብ አንደሚሆን መገመቱ ቀላል አይደለም፡፡

አዲሷ ልጅ መሬት ላይ ዘርፍጥ ብላ ቁጭ አለችና ጭንቅላቱን ሰቅስቃ በማንሳት ታፋዋን እንደትራስ በማመቻቸት አስተካክላ አስቀመጠችው… አይዳ ጭንቅላቷ ላይ ያለውን ነጭ ሻሽ መዥርጣ አነሳችና በስነስርአት አጣጥፋ በተፈነከተው ጭንቅላቱ ላይ በማድረግ ዙሪያው እየጠመጠመች አሰረችለት….ቀስ በቀስ የሚፈሰው ደም ቆመለት…..ከምን ያህል ደቂቃ ብኃላ እንደሆነ አላውቅም ከገባበት ኮማ ነቃ፡፡

"እ ምን ሆኜ ነው?"ጠየቀ

አዲሷ ልጅ በደስታ ፊቷ በርቶ‹‹ወይ ተመስገን …በእየሱስ ስም …በህይወት አለህ አልሞትክም...››አለች፡፡

"ይሞታል ብለችሁ ነበር እንዴት? ››በመገረም መለሰ

‹‹አዎ በደንብ አስበን ነበር..እኔማ መቼም አይድንም ብዬ ተስዬ ነበር….››

‹‹ምን ብለሽ››በሪሁን ጠየቃት፡፡

‹‹ካተረፍከው ባለፈው ጠይቆኝ እምቢ ያልኩትን እሰጠዋለው ብዬ››

‹‹በምስክር ፊት ነው…..እንዳትክጂ››

‹‹አንቺም እምቢ ትያለሽ እንዴ?››አልኳት በንግግራቸው መካከል ጣልቃ ገብቼ …እንደዛ ያልኳት ለዛ በሌለው ጫወታዋ ላሸማቅቃት ፈልጌ ነበር…..

እሷ እቴ‹‹አልፎ አልፎ…..እምቢ ልል እችላለው….ለማንኛውም ጠይቅና አረጋግጥ››አለችኝ

በሪሁን እንደምን ከተጋደመበት ለመነሳት ሞከረ...ግን ጭንቅላቱ ግን ከበደው መሰለኝ ወደ ነበረበት ተመለሰ‹‹የእውነት ተጎድቼያለው እንዴ?››
‹‹አዎ...ለ20 ደቂቃ እኮ እራስህን ስተህ ነበር...ትንፍሽ አልነበረህም..በዛ ላይ ጭንቅላትህ ተፈንክቶ በመከራ ነው ደሙን ማቆም የቻልነው"አዲሷ ልጅ አብራራችለት

‹‹እውነቷን ነው እንዴ ?››ብሎ እጁን ወደ ጭንቅላቱ ሰዶ መዳበስ ጀመረ…
‹‹እንዴ የምን ጨርቅ ነው?››
መቼስ እዚህ ቁስል ማፅጃ አልኮል እና ማሸጊያ ባንዴጅ እንደማናገኝ ታውቃለህ… ዝም ብዬ ነው በሻሼ አጥብቄ ያሠርኩልህ…ደግሞ ሁለት መቶ ብር የተገዛ ሻሽ ነው…እንውጣ እንጂ አፍንጫህ ይዤ ነዋ የማስከፍልህ"

‹‹አሁን ምን እናድርግ›› ጋሽ አህመድ ነው መልሶ ስለመፍትሄ ፍለጋ ጥያቄ ያነሳው፡፡
👍153😢1
‹‹ያለእቅድ መንቀሳቀስ ህይወት ሊያስከፍለን ነበር ...አሁን አረፍ ብለን እንረጋጋ ..እሱም ከህመሙ ጥቂት ያገግም ...በዚህ መካከል እግዜር የሆነ ተአምር ሊልክልን ይቾል ይሆናል።
አለችን››
‹‹በሰላም ሀሳብ እኔም እስማማለው›› አለች አይዳ
‹‹ስሟ ሰላም ነው ….ይሄንን ስም ደጋግሜ ሰምቼዋለው …እንዴት ልዘነጋው ቻልኩ?››
ማንም የተካራከራ የለም..በእያበራን ያለነውን ባትሪ አጥፍተን በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ሁላችንም ጥግ ይዘን ተጠጋግተን በመቀመጥ በየራሳችን ሀሳብና ጭንቀት ተዋጥን፣እስኪ እኔም አብረውኝ ስለታገቱት አራት ሰዎች ፀባይና አጠቃላይ አካላዊ ሁኔታ በመጠኑ በማወቀው ልክ ልንገራችሁ፡፡

በሪሁን ጠይም ቀጭንና ሞጋጋ ቢጤ ነው፡፡ግን ጫወታ አዋቂና ሰውን ወደራሱ በፍቅር የመሳብ አስማታዊ ማግኔት ያለው ሰው ነው፡፡ጫወታው አፍ ያስከፍታል ይላሉ ለእኔ ግን ቀልዶቹ አንድም ቀን ገብተውኝ ወይም እሰፈግገውኝ አያውቁም ፡፡እንደውም ከሚገባው በላይ ነው የሚያበሳጩኝ….በሪሁንን ብዙ ጊዜ ሰበብ ፈልጌ ከስራ ላባርረው አቅጄ ነበር ግን በሁለት ዋና ዋና ምክንያት አልተሳካልኝ…አንደኛው በስራው ጥንቅቅ ያለ ባለሞያ ነው….እሱ ብቻ ሳይሆን በሱ ስር ያሉ ፌራዬዎች ብዙ ተመሳሳይ የኮንስትክሽን ድርጅቶች ሊያስኮበልሏቸው የሚሞክሮቸው ግን ደግሞ ከሱ ላለመለየት ብለው ታምነው የሚሰሩ ናቸው…ሌላው ምክንያት ከሪዞልቱ ባለቤት ጋር ያለው የተለየ ቀረቤታ ነው…ሴትዬዋ ስራውን ለማየት እዛ ሳይት በተገኘችበት አጋጣሚ ሁሉ ከእሱ ጋር ሳታወራና ሳትስቅ ሄዳ አታውቅም..አንድአንድ ቀን እንደውም እኛን ሁሉ ችላ ብላ እሱን ምሳ አባላኘ ብላ ይዛው ትወጣለች፡፡እና እሱን ማባረሩን ከልብ ብፈልግም በእነዚህ ሁለት ምክንያቶች አላደረኩትም….
የምሳ ሰዓት ሁሉም ሰራተኛ በተለይ ሴቶቹ የምሳ ዕቃቸውን እየያዙ እሱ ወዳለበት በሽቅድምድም ነው የሚሄዱት፤ደግሞ የሚገርመኝ ባለትዳሯም ትዳር አልባውም በሱ ዙሪያ ለመኮልኮል ልዩነት አለማሳየታቸው ነው፡፡እሱ ብዙውን ጊዜ ስራዬ ብሎ ምሳ ይዞ አይመጣም…እንዷ አንድ ጉርሻ ሌላዋ በሞቴ ብላ ሌላ ጉርሻ ስታጎርሰው የሁሉን ጉርሻ ከማዳረሱ በፊት ይጠግባል፡፡ …አንቺን ነበር ማግባት……አንቺ ደግሞ ይሄን ሞያሽን ነገም ከደገምሽ ለእኔ ባይሆን እንኳን ለወንድሜ እድርሻላው ፡፡መሰል ቀልዶችን በመወርወር ሴቶቹን በተሰበሰቡበት ጥሎ ከመካከላቸው ሹልክ ብሎ ወደወንዶቹ ይሮጣል፡፡እዛም የሚጠብቀው አቀባበል የተለየ አይደለም፡፡በሬ ብና በእኔ ሂሳብ ነው ጠጣ….ማታ ድርፋት ጋብዝሀለው እንዳትጠፋ…ይፎካከሩበታል፡፡

ጋሽ አህመድ ከሁላችንም በእድሜ አንጋፍ ነው...በአብዛኛው ሰው ጋሽ አህመድ እየተባለ ነው የሚጠራው...በግምት ከ45_50 አመት ይሆነዎል"ግን በስራ የጎለበተ ስለሆነ የሠውነት አቋሙ ጥብቅ ነው።ከቴክኒክ እና ሞያ ማሰልጠኛ በቢውልዲንግ ኮንስትራክሽን ዲፕሎማ ያለው ሲሆን የእድሜውን አጋማሽ በዚህ ስራ ያሳለፈ በመሆኑ ሙሉ ፎርማን የሚባል ሰው ነው። ከእሱ ጋር መስራት መባረክ ነው።ጋሽ አህመድ በሰውነት አቋሙ ግዙፍ ነው….የቀይ ዳማ ሆኖ ጥቅጥቅ ፀጉር ያለው ባለ ግርማ ሞገስ ደስ የሚል ሰው ነው፡፡

ለስራ ጉዳይ ሳይት ውስጥ ጎን ለጎን እየተራመድን ስናወራ አዲስ የሚያየን ሰው እሱ ሀለቃዬ ሆኖ የስራ ትዕዛዝ እየሰጠኝ ወይም የፕሮጀክቱ ባለቤት ሆኖ ስለተሰራው ስራ ሪፖርት እያቀረብኩለት እንደሆነ ነው የሚገምተው፡፡ከጋሽ አህመድ አጠቃላይ ሁኔታ የማደንቅለት አንድ ነገር ቢኖር ለሆነ ስራ ሰዎችን የማስተባር ችሎታውን ነው፡፡በቃ መሰራት ያለበት የሆነ ስራ ካለ ቅደም ተከተሉን ለእሱ ማስረዳት ብቻ ነው..ሌላውን እሰተባብሮና አነቃቅቶ በተገቢው ጥራትና በተፈለገው ሰዓት ያደርሳል…ለዚህም በጣም የማከብረው ሰው ነው….ይሄንን ግን በግልፅ ነግሬው አላውቅም፡፡

ሌላዎ ሠላም ነች ..ስሞንም በቅጡ ያወቅኩት ዛሬ አሁን እዚ ወጥመድ ውስጥ ከገባን ብኃላ ሲጠሯት ስለሠማው ነው።በኘሮጀክታችን ከተቀጠረች ገና 15 ቀኗ ነው።እንደአጋጣሚ ሆኖ ዘመዴ ነች ብሎ ያመጣትም ባለቤቷን ጨቅጭቆ ዋስ ሆኖ ያስቀጠራትም በሪሁን ነው።እስቶር ሆኖ የሚሰራ ሰው ብዙ ንብረት በሀላፊነት የሚረከብ ስለሆነ የቤት ካርታ ዋስ ሳያመጣ የሚቀጠር ሰው አልነበረም ...በሪሁን ግን ይሄንን አሰራር አስትቶ በመታወቂያ ዋስ ብቻ አስቀጥሯታል። ሰላም ስትታይ ከሁላችንም ልጅ ትመስላለች ምናልባት 21 ወይም 22 አመት ቢሆናት ነው :: የተኮሳተረ ፊቶ የ50 አመት የሠለቻት ሴት ያስመስላታል ።ቆንጆ የምትባል አይደልችም ግን ደግሞ የደነደነ ሰውነትና ማራኪ ቅርፅ አላት፡፡ ከሁሉም በላይ ሰላም ጥልቅ መንፈሳዊ እና ቁጥብ ተናጋሪ ነች፡፡

አይዳ ጋ ደረስኩ…በሪሁንን እጠላዋለው ብያችሁ ነበር አይደል …..አይዳን ደግሞ በጣም በጣም ነው የምጠላት….ለዛም ነው ሰበብ ፈልጌ ከስራ ያሰናበትኮት.. ደሩ ምን ዋጋ አለ ጨርቆን ጠቅልላ ከአካባቢዬ እርቃ የምትሰወርበት ቀን ስናፍቅ እሷ ይሄው አሁን ከመሬት በታች አብራኝ ታግታለች….አይዳ ማንም የሚስማማባት ምጥን ቆንጆ ነች….በዝቶ ያልተዝረከረከ አንሶ ውይ እዚህች ጋ እንዲህ ቢሆን የማያሰኝ የተመጠነ ውበት አላት፣በዛ ላይ ከማውቃቸው ሴቶች ሁሉ ጀንትሏ ሴት ነች…ግን ደግሞ ጭንቅላቷን ሙሉ ለሙሉ ለጥፋት….ሰው ለማበሳጭጽ…ነገሮችን ለማውደም…..የሰውን ሞራል ለማንቀሻቀሽ ነው የምትጠቀምበት….ብላሽ የሆነች ብሽቅ ሴት ነች…እድሜዋን ከፈለጋችሁ 25 የሚሆናት ይመስለኛል፡፡እንግዲህ አብረውኝ የተጋቱት ከሞላ ጎደል እኚ ናቸው፡፡

ዋናው ጥያቄ አምስታችንም ከዚህ ወጥመድ በተአምር እንተርፍ ይሁን…..?ስንቶቻችን ሞተን ስንቶቻችን እንተርፍ ይሆን….?.እኔስ ከሞቾቹ ነኝ ወይስ ከተራፊዎቹ…?.ነው ወይስ ሁላንም በቀናቶቹ ውስጥ ታሪክ ሆነን እዚሁ ከቢሾፍቱ ሀይቅ ጠርዝ ከምድር ከርስ ስራ ተቀብረን ለዘላለም እንቀር ይሆን…?አዎ ዋናው ጥያቄ ይህ ነው፡፡ጊዜ ብቻ የሚመልሰው ጥያቄ….


ይቀጥላል....


ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
❤️
👍17👏1
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰላሳ_አንድ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

ሳቤላ ከላይኛው ከተማ ምሽጎች ትንሹ ሰፈር እየተባለ ከሚጠራው ቦታ አንድ አግዳሚ ወንበር ላይ ተቀምጣለች - ሚስተር ካርላይል ወደ ቤቱ ከተመለሰ 0ሥር ቀን ያህል አልፎታል በጤናዋ በኩል ጉልህ የሆነ መሻሻል አድርጋለች
በጥንካሬዋ የታየው ለውጥም ለማመን የሚያስቸግር ነበር ከቤቷ ወጥታ የእንግሊዛዊያኑን የመቃብር ጽሑፍ እየተዘዋወረች ስታነብ ቆየችና በመጨረሻ ልትሔድ ስትል ለማሪፍ ተቀመጠች እንደ ሁልጊዜው በእግር ስትንሸራሸር ፍራንሲዝ ሌቪስን አሁንም አብሯት ነበር እሱን አራግፋ መጣል አልሆነላትም። የመውጫ ሰዓቷን ብትለውጥ የምትሔድበትን መንገድ ብትቀይር ዱካዋን ፈልጎ ከች ይልባታል ምናልባት እሷ
እንደጠረጠረችው አስቀድሞ በመምጣት ከምቹ ቦታ እየሆነ ይጠባበቃት ኖሮ ይሆናል እሷም ቁርጥ ያለ ነገር ነግራ ዳግመኛ እንዳይመጣባት ለማድረግ አልቻለችም ቢጠይቀኝ ምን ምክንያት ልሰጠው ነው? የሚል ጭንቀት ይመጣባታል " መሰጠት ያለበትን ምክንያት ደግሞ ልትሰጠው ቀርቶ ልታስበው አትፈልግም ምንአባቱ እንግዲህ የቀረኝ ትንሽ ቀን ነው ወደ ቤቴ የምሔድበት ጊዜ ደርሷል ብላ
በማሰብ ራሷን ታጽናናለች ነገር ግን እሷ ይህን ታስብ እንጂ ከሱ ጋር መገናኘቷ እየቀጠለ •እየረዘመ ሲሔድ የራሱን ፍሬ ማፍራት ጀመረ " ብቅ ባለ ቁጥር ፊቷ
ልውጥ ልቧ ድንግጥ ይልባታል ላለመደንገጥ ላለመሸበር ብዙ ጊዜ ብትሞክርም ነፋስን እንዳይነፍስ ለማድረግ እንደ መሞከር እየሆነባት ተቸገረች።

ጊዜው መሽቷል ቅዝቃዜው የሞቃቱ የሐምሌ ማታ አይመስልም" ከነፍሳት ልዩ ልዬ ጥዝታና ጭርጭርታ በቀር ምንም ድምፅ አይሰማም " ወይዘሮ ሳቤላ አመፀኛው ልቧ በራሱ የደስታ ስሜት እየመታ ከጓዶኛዋ ጋር ጸጥ ብለው ተቀምጠዋል
በውስጧ የጠነከረባት የሕሊና ድምፅ ባያስቸግራት የትክክለኝነትና የጥፋተኝነት
ፍርድ ባይደቀንባት ባጭሩ ሚስት የመሆኗ ነገር ባይከብዳት ኖሮ የነበረው ዝምታ ሳይነካ እሷም ከተቀመጠችበት ንቅንቅ ሳትል እሱም ከጐኗ እንዳለ እስከ ዘለዓለም ቢቀጥል የምታገኘውን የሚያረጋ ደስታ ታስብ ጀመር "

“ትዝ ይልሻል እመቤት ሳቤላ ?” አላት „ “ ልክ እንዶ ዛሬው በመስለ ሁኔታ አባትሽ : ሚስዝ ቬን አንቺ ' እኔና ሌሎችም ሆነን ሪቸመንድ የሔድን ጊዜ ''

“ አዎን ትዝ ይለኛል " ጥሩ ቀን ነበር የዋልነው " ሁለቱ ሚስ ቫሎነሮች አብረውን ነበሩ " አንተ ሚስዝ ቬን በሠረገላ ወደ ቤቷ ወሰድካት እኔ ከአባባ ጋር
ሔድኩ " በኃይል እየነዳህ ሰለ አስደነገጥካት • ሁለተኛ አንተ ሠረገላ ላይ እንደማትሳፈር ከቤት ከተመለስን በኋ ነገረችህ "

“ የማትጨክነውን እኮ ነው በተናገሩት ከማይረጉ ተገለባባጮችና ታይታ ወዳድ ሴቶች ሁሉ ኤማ ማውንት እስቨርንን የሚያህል የለም አሁንም “ ኤማ ማውንት
እስቨርን” ተብላ ማዕረግ ጨምራ እንኳን ያው ነች ከመዳራት በቀር ሌላ ቁም ነገር የላትም እኔም በዚያን ጊዜ በኃይል የነዳሁት ሆነ ብዬ እሷን ለማስደንገጥ ነበር

" ምን አደረገችህ ?

"በጣም አናደደችኝ " እኔ ሌላ ወዳጅ ስፈልግ እሷ የግድ ከላዬ ተጠምጥማ ከላዬ አልለቅም አለችኝ "

"ብላንሽ ሻሎነርን ነበር አንተ የፈለግህ?

“ብላንሽ ሻሎነር ?!” አለና ጮኸ ካፒቴን ሌቪሰን » እሷ ደግሞ ምኔ ናትና? ”

ሳቤላ ያሥራ ስባት ዓመት ቆንጆ ከነበረችው ከመልከ መልካሚቷ ከብላንሽ ሻሎነር ጋር ጠንካራ ግንኙነት እንደ ነበረው አስታውሳ “ምነው ሚስስ ቬን ከሷ ጋር ብርቱ ፍቅር ይዞሃል ብላ ታማህ አልነበረም ?

“ እሷ እንኳን ከብላንሽ የበለጠ በሌላ ስው ነበር ስሜን የምታነሣው ” አላት ማንን ለማለት እንዶሆነ ለመገመት በሚያመች አነጋገርና አስተያየት "

“ እና ደግሞ የቅናት ግምቷ አለቦታው ያላረፈ አልነበረም " እኔም ልለው የፈለግሁት ብላንሽ ሻሎነርን አልነበረም " አንቺስ በዚያን ወቅት የተሻለ መገመት
አትችይም ነበር ? " አላት ወደሷ ዞር ብሎ "

ምን ለማለት እንደ ፈለገ በድምፁ አነዛዘርም ሆነ በዐይኑ አመለካከት ስለገባት መልኳ ሲለዋወጥ ተስማትና ፊቷን ወደ ሌላ አዞረች "

“የዱሮ ነገር ኣልፏል ተመልሶ ሊመጣ አይችልም በጊዜው ግን ሁለታችንም የየዕድላችንን ተውተን አሳልፈነዋል " ለመፋቀር የተጠሩ ሁለት ሰዎች ነበሩ ቢባል አንቺና እኔ ነበርን እንዲያውም ያን ጊዜ የልቤን ሐሳብ የምታነቢው ይመስለኝ ነበር "

ለጊዜው ድንግጥ ብላ በዝምታ ከቆየች በኋላ ኮስተር ብላ አቋረጠችው ::

“ ልናገር እንጂ. . .ወይዘሮ ሳቤላ ጥቂት ቃላት ልናገርና ከዚያ በኋላ ለዘላለም ምንም አልተነፍስም - ብችል ኖሮ ያን ጊዜ አሳልፌ አልሰጥሽም ነበር " ነገር ግን
ያልተደላደለው ሁኔታዬና ዕዳዎቼ ሚስት እንዲኖሬኝ አላስቻሉኝም ቁልቁል ..ተጫኑኝ ስለዚህም የሎርድ ማውንት እስቨርንን ልጅ
ለማግባት እንድጠይቅ ከሚያበቃ
ደረጃ እንዲያደርሰኝ ሰር ፒተርን በመለመን ፈንታ ተስፋዎቼን በውስጤ ከለከልኳቸውና ከእጄ አምልጠሽ ስትሔጅ “ዐይኔ እያየ ዝም ብዬ ሰደድኩሽ » ”

“ እኔ ይኸን ነገር ለመስማት አልፈልግም ካፒቴን ሌቪሰን " አለችና ተቆጥታ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች "

እንድትቀመጥ ክንዷን ነካ አድርጎ ባክሽን ትንሽ ልንግርሽ " ለምን እንዳመለጥሽኝ እነግርሻለሁ እያልኩ ከተመኘሁ ብዙ ዘመኔ ነው ሌላ ስለ ወሰደሽ እስከ ዛሬ ሆድ ሆዴን ሲያቃጥለኝ ይኖራል የሌላ ሚስት በመሆንሽ ቁርጤን ዐውቄ እስካርፍ ድረስ ምን ያህል እወድሽ እንደ ነበር መግለጽ ያቅተኛል ያ ፍቅር ዛሬም ከልቤ አልጠፋም " ሙሉ በሆነ ልባዊ ስሜት እወድሻለሁ አላት »

" እንዴት እንደዚህ ደፍረህ ትናገረኛለህ ? አለችው "

የትዳር ኃላፊነትና ግዴታ ስለነበረባት ተቆጣች ተጀነነችበት ነገር ግን ቆጣ ጅንን ትበል እንጂ ይህ አነጋገር በሌላ ወቅትና ሁኔታ ሆኖ ቢሆን ኖሮ ለልቧ ታላቅ ሐሴት የሚሰጥ ይሆን እንደ ነበረ በመግንዘቧ ለቁጣው ንግግሯ ተቃራኒ የሆነ ኃይለኛ ስሜት ውስጥ ለውስጥ በሠራ አካላቷ ሲሯሯጥባት ተስማት "

የአሁኑ ንግግሬ እኮ ምንም ጉዳት የለውም ” አለና ካፒቴን ሌቪሰን ንግግሩን በመቀጠል ' ' ነገሩ ጊዜ ያለፈበት ነው » ባለትዳርነትሽን አንችም ሆንሽ እኔ መዝንጋት አንችልም ሁለታችንም የየራሳችንን የኑሮ ጎዳና መርጠናል ስለዚህ አንድ ጊዜ የያዝነውን ፈር አክብረን መያዝ አለብን በመካከላችን ያለው ባሕር ሊያገናኘን አይችልም
በራሴ ጥፋት አምልጠሽኛል እንግዲህ በየትም አልፈ ላገኝሽ
አልችልም ያን ግዜ እንደምወድሽ
እንደምፈልግሽ ልገልጽልሽ ሲገባኝ ራስሽን ከሚስተር ካርላይል እጅ ስትጥይ ዝም ብዬ አየሁሽ

ራስሽን ስትጥይ አልክኝ ? ብላ ቱግ አለች "ሚስተር ካርይል እኮ የምወደውና የማከብረው በራሴ ምርጫ ያገባሁትና እሱን በማግባቴም የምመካበትና
የማልጸጸትበት ባሌ ነው ኧረ ለመሆኑ አንተ ከሱ ጋር ብትወዳደር ከምኑ ትደርሳለህ!
ራስህንም ረስተኽዋል . . . ፍራንሲዝ ሌቪሰን

ከንፈሩን ነከስና “ የለም አልረሳሁም ” አላት

እንዴዚህ ብለህ ልትናገረኝ አትችልም » ከዚሀ ብቸኝቴን አይቶ የሰደበኝ ካንተ ሌላ ማን አለ ? ሚስተር ካርላይል ካጠገቤ ቢኖር እንዲሀ ብለህ ልትናገረኝ አትደፍርም ነበር ? በል ደኅና እደር ጌታዬ !
👍16🔥1
ደካማው ቁመናዋ በፈቀደላት መጠን በችኮላ ውንትር ውንትር
እያለች መንገድ ጀመረች እጁዋን በግድ ያዘና በክንዱ አድርጎ እባክሽ ያመለጠኝን ንግግር እርሽውና ይቅርታ አድርጊልኝ " ፊት እንደ ነበረው አዛኝ ጓደኛሽ : አሳቢ ወንድምሽ ሚስተር ካርላይል በሌለበት በችግርሽ የምደርስ እውነተኛ ወዳጅ አድርገሽ እይኝ

ይኽንማ ብዬ ነበር እንደ እንዶ ዘመድ አይቼ የቀረብኩሀ ” አለችው ግንባሯን ቋጥራ እጁዋን ከክንዱ ነጠቀችና " ይኸን ባላስብ ኖሮ አልቀርብሀም ነበር "
አንተ ግን ምላሹን እንዲህ አድርገኸው ዐረፍክ " ባሌ አንተ ያዴረግሀልኝን አስቦ
አመሰገነህ በዚU በእምነተ ቢሱ ልብህ የቋጠርከውን ሐሳብ ለማንበብ ቢችል ኖሮ ሌላ ዐይነት ምስጋና ነበር የሚሰጥህ " "

“ አሁንም ይቅርታሽን እለምንሻለሁ " ጥፋቴን ዐውቄዋለሁ አይደግመኝም ሁለተኛ እንደዚህ አላስቀይምሽም የፍቅር ስሜቶች የኑሮን ሥርዓት ጥሰው
ትዕግሥታችንና ይሎኝታችንን ጥለው በመውጣት በይፋ እንድንጋለጥ የሚያደርጉበት ጊዜ አለ ዕብደት ነው!አሁን ብዙ መንግድ ስለ ሔድሽ ደክሞሻል • ስለዚህ ባይሆን ይህንን ከባድ ቁልቁለት ደግፌ እንዳወርድሽ ፍቀጅልኝ " "

“ ይኸን በፊት ነበር ማሰብ የሚገባህ አሁን ተወኝ አልፈልግም " እለችው " አሱም የዘረጋላትን አጁን ሰብስቦ ከጐኗ እየሔደ ያለምንም ድጋፍ ከበሯ
ደረሰችና በኩርፊያ ገጽታ “ ደኅና እደር ! አለችውና ወደ ሆቴሎ አቅጣጫ ተመለሰ።

ሳቤላ ከሆቴሏ ገብታ ፒተርን ጀፍታው ዐለፈችና ከፎቅ ወጣች " በእመቤቷ አለ መኖር አጋጣሚ የክት ልብሷን ለብሳ በሳሎኑ መስኮት ስትዘባነን የነበረችውን
ዊልሰንን በድንግት ደርሳ አስደነጠቻት "

ዊልስን ...የጽሕፈት ጠረጴዛዬን ወዲህ በይልኝ ! ፈጠን በይ ” አለቻት ጓንቲዎቿን አውልቃ ያንገት ልብሷን አኖረች " ፒተርን ደግሞ ፖስታ ቤት የሚያዶርሰው ደብዳቤ ስለአለው ተዘጋጅ በይው " ወደ ኢንግላንድ የሚላከው ፖስታ ከመታሰሩ በፊት መድረስ አንደሚኖርበት ንገሪው "

ፍራንሲዝ ሌቪሰን ስለ ፍቅሩ ሲነግራት የበዳይነት ደስታ ምልክቶች ልቧን ስልብ ሲያደርጋት ተሰማት የስብከቱ አደግኝነትና ከዚህ ሰውም ግንኙነቷን
ባስትኳይ ማቋረጥ እንዳለባት ግልጽ ሆነላት " ስለዚህ እሱ ካለበት ምድር ለቃ ባሕር ተሻግራ ለመሔድ ቆረጠች ከዚያ ቦታ መቆየት ጭራሽ ስለ አልቻለች ባስቸኳይ እንዲመጣ ለባሏ ጻፈችለት እንዲያወም ለማንኛውም አስፈጊ ነገር ከፍላ ይተርፋት የነበረውን ገንዘብ ለመጓጓዣ ቢበቃት ኖሮ የሱን መምጣት ሳትጠብቅ ሳትሔድ አትቀርም ነበር ።

ሚስተር ካርላይል ደብዳቤው ሲደርሰው ግራ ተጋባ። ካርላይል እሑዱን እንደ ሚመጣና ከዚያ ስለ መቆየቷና ስለ መመለሷ እሱ ከደረሰ በኋላ እንደሚመካከሩበት
ወዲያው ጻፈላት ከፍራንሲዝ ሌቪሰን ጋር ላለመናኘት ቆረጠችና ባሏ እስኪመጣላት ድረስ በሽፍን ሠረገላ ትወጣ ጀመር " አንድ ቀን ሊጠይቃት ቢመጣ ከሳሎን
እንዲገባ አድርጋ ከክፍሏ ሳትወጣ ፒተርን ላከችውና እሜቴ ምስጋኖቸውን አቅርበዋል ነገር ግን ዛሬ እንግዳ አይቀበሉም ” ብሎ እንዲነግር አዘዘችው "

ከዚያ ቀደም ብሎ መምጣት አልሆንለት አለና ሚስተር ካርላይል እሑድ ጠዋት ደረሰ ስድስቱን ሳምንት መጨረስ ስለሚገባት ምንም ቢሆን ሊወስዳት እንደማይችል ድርቅ ብሎ ተከራከራት እሷ ግን ምንም ቢሆን እንደማትቀር ቁርጡን ነገ
ረችው "

“ ሳቤላ...” አላት „ “ ምክንያትሽን ንገሪኝ" ለኔ እንደሚመስለኝ አንድ
ምክንያት አለሽ ። እዚህ በመሰንበትሽ በጣም ረድቶሻል ቸከኝ የምትዪው ነገር የልጅ ጫወታ ነው ከዚሀ የተለየ ምክንያት ካለሽ ንገሪኝ ” አላት "

የነበረውን ነገር ግልጽልጽ አድርጋ ልትነግረው ፈለገች ነግሩን አዙራ ስታየው ደግሞ የፍራንሲዝ ሌቪሰን ፍቅር ያገረሸባት መሆኑንና እሱም ምን ብሎ እንደ ተናገራት፡ ለባሏ መንገሩ ጥሩ ነገር ያለመሆኑ ተሰማት ከመጠን በላይ የምታከብረውን ባሏን ይኸን ደስ የማይል ነገር ነግራ ልታሳዝነው አልፈለገችም ኋላ ደግሞ በጉዳዩ
እንደገና አሰበችበት መንገሩ የበለጠ ከሚኮራባትና ከሚወዳት እንዲሁም ከማንኛውም አደጋ የበለጠ ተጠንቅቆ ከሚጠብቃት በቀር ሌላ ክፋት እንዳልነበረው
ታያት " ልትነግረው ስትል ሚስተር ካርላይል አንድ ደብዳቤ አውጥቶ ሰጣት ይህን በመሰለ እንደክር በቀጠነ ምክንያት ትልቁን ጉዳይ መልሳ ዋጠችው ሐሳቧን
ወደ ደብዳቤው መለሰች ደብዳቤው ከሚስ ካርላይል የተላከ ነበር

"አጻጻፉም እንደ ባለቤቱ እንደ ሚስ ኮርኒ ድርቅ ያለ ነበር “ ልጆቹ ደህና ናቸው ቤቱም በደንብ እየተካሔደ ነው" አንቺም በጎ እንደ ሆንሽ ተስፋ አለኝ ”
ከማስታወሻ ደብተር በተቀደዶ ወረቀት ሦስት ገጽ ሙሉ ቢሆንም ዋናው ወሬ ይኸው ነበር “ ብቻ” አለች ደብዳቤውን ስትዘጋ “ ባርባራ ሔር ከኛ ጋር ለመዋል አሁን ስለ ደረሰች ነው እንጂ ብዙ ልጽፍልሽ እችል ነበር " "

“ አሃ ! ባርባራ ሔር ከነሱ ጋር ልትውል ! ” ሳቤላ ያ ብቻ በቃት" ልቧንም እምነቷንም ከባሏ ዘጋች “ እኔ ወደ ልጆቼ መሔድ አለብኝ » ከእንግዲሀ ወዲህ ከነሱ ተለይቸ መቀመጥ አልችልም ” ብላ እያለቀስች ስትነግረው ' ' ግድ የለሽም አንቺ ወደ ቤትሽ መመለሱን እንደዚህ አጥብቀሽ ከፈለግሽ ከኔ ጋር ትመለሻለሽ ” ሲላት ልክ ከትምህርት ቤት እንደ ተለቀቀ ሕፃን በደስታ ፈነደቀች
" እንደ ልቧ መሣቅ መጫወት ጀመረች ባሏም ጥያቄዋን ስለ ተቀበላት በማመስገን እየመላለሰች ሳመችው በተለይም ከሱ ተለይታ መቀመጥ እንደማትችል ስትነግረው ለሱ የነበራትን ፍቅር መግለጿ መሆኑን አድርጎ ተረጐመው "

" ሳቤላ ” አላት በፈገግታና በፍቅር አመለካከት ወደሷ እያየ “ ያኔ ገና
አንደ ተጋባን እንደማታፈቅሪኝ የገለጽሽልኝና እኔም ፍቅር ቀስ በቀስ እያደገ እንደ ሚመጣ የነገርኩሽን ታስታውሻለሽ ? እንዳልኩሽም አሁን የመጣ መሰለኝ "
ሳቤላ በባሏ አነጋገር ፊቷ ተለዋወጠ ዕንባዋ መጣ ከፊቷ ግልጽ የሆነ ጭንቀት ታየባት ካርላይልም ያን ፈጣን መለዋወጥ ሲያይ · · አዎን ያልከው ደረሰ
ለማለት እንደ ፈለገች አድርጎ በመውሰድ ከደረቱ ዕቅፍ አደረጋት።

አንድ ቀን ብቻ ቀራቸው ከዚያ
አንድ ቀን -እሷና ያ ሰውዬ ሊለያዩ
ወዲያ በመካከላቸው ያለው ሰፊው ባሕር ይገላግላታል የመለየቷን ነገር ስታስበው እንድታመሰግን አደረጋት ። በርግጥ እሱን ጥላ መሔድ ማለት ፀሐይን ከኋላ ትታ ጨለማ ውስጥ መግባት ማለት መሆኑንና ለጊዜውም ቢሆን አገሯም ሆነ ቤቷ እሱ ከሌለበት ቀፋፊና ማስጠሎ እንደሚሆንባት ብታውቅም በመሔዷ በሙሉ ልቧ
ተደስተች " የመቤት ሳቤላ እምነት ኢያጠራጥርም " ቀና አስተሳሰብ አላት ትክክለኛ ሥራ ለመሥራት ትመኛለች ትጥራለች ክፉ ሥራ የምሯን ትጠላለች መንፈሷ ቅንና እውነተኛ ነው አስተላሰቧ ንጹሕ ነው ።

ካፒቴን ሌቪሰን መጥቶ ከሚስተር ካርላይል ጋር ተገናኘና ሰር ፒተርን ለማነጋገር ጊዜ አግኝቶ እንደሆነ ጠየቀው " ሚስተር ካርይል ግን በሥራ ብዛት አለመሞከሩን ከጥቂት ቀኖች በኋላ ግን በቂ ጊዜ ሊኖረው ስለሚችል እንደሚሞክርለት አስረዳው ።

ከቀትር በኋላ የባሕር ሞገድ ተነሣ ፎክስቶን የተባለችው ጀልባ በሰባት ሰዓት እንደምትነሣ ተገለጸ። ሚስተር ካርላይል ከሚስቱና ከሠራተኞቹ ጋር በሰዓቱ
ተሳፈረ " ካፒቴን ሌቪሰንም ወደቡ ድረስ አብሮ መጥቶ ወደ ጀልባዋ ሲገቡ ሰላምታ ሰጥቶ ተስናበታቸው " ወይዘሮ ሳቤላ ከመድረኩ ላይ ስትቀመጥ ባለቤቷ ከጐኗ ቁሞ ነበር " ገመዱ ተፈታና ጀልባዋ ተንቀሳቀሰች » ፍራንሲዝ ሌቪሰን ከድንበሩ
ቁሞ እንቅስቃሴውን ፡ በተለይ ደግሞ ሳቤላን ይመለከት ነበር "
👍13
ሌቪሰን ከዐይኗ ሲጠፋ በሠራ አካላቷ የተሰራጨው የእፎይታ ስሜቷ ከግር እስከ ራሷ አንቀጠቀጣት ሳታስበው የሚስተር ካርላይልን እጅ ጨምደድ አድርጋ ያዘችው "

“ በረደሽ እንዴ ? አላት አንገቱን ወደሷ ዘንበል አድርጎ "

“ ኧረ የለም ደኅና ተመችቶኛል በጣም ደስ ብሎኛል "

ታዲያ ምነው አንቀጠቀጠሽ ?”

ዛሬም ብቻዬን እዚያ ጥለኝ መጥጠህ ቢሆን ኖሮ ምን ይውጠኝ እንደነበር ሳስበው ነው ያንቀጠቀጠኝ " አርኪባልድ .... ካንተ ነጥለህ የትም እንዳትሰደኝ ሁልጊዜ ካጠገብህ እንዳትለየኝ »

የልመናዋን መልስ በመጠበቅ ይቁለጨለ የነበሩት ዐይኖቿን በፍቅር ስሜት ቁልቁል እየተመለከተ ፡“ ሁልጊዜ .. ሳቤላ ሁልጊዜ አልለይሺም ከኔ
ተለይተሽ በመሰንበትሽ ካንቺ የበለጠ የተጨነቅሁት እኔ ነበርኩ
ከቶ እንዴት ቃሉ ይጠረጠራል ይህ ሰው' ስትል አሰበች ....

💫ይቀጥላል💫
👍16
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


...አሁን ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ባለው ሚስጥር ላይ ቆሻሻና የሚሸቱ ጨርቆች በሻንጣዎቹ ውስጥ በመክተት ሌላ ሚስጥር ጨመርንበት.

ስለ ሁኔታው አብዝተን ባለማውራታችን ከነገሩ እጅግ አስፈሪ መሆን አመለጥን:
ጠዋት እንነሳና ፊታችን ላይ ውሀ ረጨት እናደርጋለን። ጥርሶቻችንን በባዶ ውሀ እናፀዳለን፤ ጥቂት ውሀ እንጠጣና ትንሽ ወዲያ ወዲህ እንላለን፡ ከዚያ ጋደም ብለን ቴሌቭዥን እናያለን ወይም እናነባለን፡

መንትዮቹ ምግብ ፈልገው ሲያለቅሱ መስማቴ ህይወቴን ሙሉ ልቤ ላይ የሚኖር ጠባሳ አስቀመጠልኝ፡ አያታችንን እንዴት እንደጠላኋት። ያቺ አሮጊት እና እናታችን ይህንን ስላደረጉብን ጠላኋቸው።

የመመገቢያ ሰአታችን ያለ ምግብ ሲያልፍ እንተኛለን፡ ለሰዓታት እንተኛለን::እንቅልፍ ሲወስደን የርሀብ ወይም የብቸኝነት ወይም የምሬት ስቃይ አይሰማንም በእንቅልፍ በውሸት የደስታ ስሜት ውስጥ እንሰምጣለን ከዚያ
ስንነቃ ስለምንም ነገር ግድ አይኖረንም።

እንደ ፈዘዝኩና እንደደከምኩ ጭንቅላቴን ዞር አድርጌ ክሪስንና ኮሪን እያየሁ ነበር ከዚያ ክሪስ ከኪሱ ሰንጢ አውጥቶ የእጁን አንጓ ሲቆርጥ ያለምም
ስሜት ጋደም ብዬ እየተመለከትኩ ነው። የሚደማ እጁን ወደ ኮሪ አፍ አስጠጋና ኮሪ ቢቃወምም እሱ ግን ደሙን እንዲጠጣ አደረገው: ከዚያ የኬሪ ተራ ሆነ ሁለቱ ምንም ነገር ያልበሉ በመሆናቸው፣ የትልቁ ወንድማቸውን ደም ጠጥተው፣ በደበዘዘ፣ በፈጠጠና በተቀባይነት አይን አተኩረው ተመለከቱት።

ማድረግ ባለበት ነገር የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰምቶኝ ፊቴን አዞርኩ። ያንን በማድረጉ አድናቆት ተሰምቶኛል። ሁልጊዜ ከባባድ ችግሮችን ማቃለል
ይችልበታል።

ከዚያ ክሪስ ወደኔ አልጋ መጣና፣ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ ረዘም ላሉ ደቂቃዎች ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ አይኖቹ ወደተቆረጠው አንጓው ዝቅ
አሉ አሁን መድማቱን አቁሟል። እኔም ደሙን ጠጥቼ ረሀቤን እንዳስታግስ ሌላኛውን ደም ስሩን ለማድማት ሰንጢውን አወጣ እንዳያደርገው ነግሬ ሰንጢውን ቀምቼ ወረወርኩት። ብርታት ለማግኘት ስል የእሱን ደም
እንደማልጠጣ ምዬ ተገዝቼ ብነግረውም መሀላዬን ከቁም ነገርም ሳይቆጥር ሰንጢውን በአልኮል ማፅዳት ጀመረ።

“ተመልሳ ባትመጣ ምንድነው የምናደርገው ክሪስ?" ስል ጠየቅኩት አያታችንን ለሁለት ሳምንት አላየናትም: አይጥ ለማጥመድ ወጥመዱ
ላይ ያደረግነውን ቺዝ የሚላስ የሚቀመስ ባጣን ጊዜ በልተን ጨርሰነዋል።ምግብ የሚባል ሳንቀምስ ሶስት ቀናችን ሆኗል፡ መንትዮቹ እንዲጠጡት
የተውንላቸው ወተትም ካለቀ አስረኛ ቀን ሆኖታል።

“በረሀብ አትገድለንም” አለ ክሪስ አጠገቤ ተኝቶ በደካማ ክንዱ እያቀፈኝ። “እሷ ያንን እንድታደርግ ከፈቀድንላት ደደቦች ነን ማለት ነው ነገ ምግብ ይዛ ካልመጣች ወይ ደግሞ እናታችንም ብቅ ካላለች አንሶላ ተልትለን መሰላል
እንሰራና ወደ መሬት እንወርዳለን” አለ፡

ጭንቅላቴ በደረቱ ላይ ስለሆነ ልቡ ሲመታ ይሰማኛል። “ምን እንደምታደርግ ታውቃለህ? ስለምትጠላን እንድንሞት ትፈልጋለች። መወለድ የማይገባን
የሰይጣን ልጆች መሆናችንን ስንት ጊዜ ነው የነገረችን?

ካቲ፤ ያቺ ጠንቋይ አሮጊት ደደብ አይደለችም: እናታችን ካለችበት ከመምጣቷ በፊት ምግብ ይዛ ትመጣለች::”

የተቆረጠ እጁን ላሽግለት ተንቀሳቀስኩ ከሁለት ሳምንት በፊት እኔና ክሪስ ለማምለጥ መሞከር ይገባን ነበር። የዚያን ጊዜ ሁለታችንም ጥንካሬ ነበረን
አሁን ብንሞክር ግን በእርግጠኝነት ወድቀን እንሞታለን፡ መንትዮቹን
በጀርባችን አዝለን ከሆነ ደግሞ የበለጠ ከባድ ይሆንብናል።

በማግስቱ ጠዋት ምንም ምግብ እንዳልመጣ የተመለከተው ክሪስ ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል እንድንሄድ አስገደደን፡ እኔና ክሪስ ለመራመድ እጅግ ደክመው
የነበሩትን መንትዮች ተሸከምናቸው የመማሪያ ክፍሉ ጥግ ላይ ስናስቀምጣቸው አቅማቸው ስላልቻለ እንደመተኛት
እያሉ ግድግዳውን ተደግፈው ቁጭ አሉ። ክሪስ መንትዮቹን ጀርባችን ላይ የምናስርበትን ገመድ እያዘጋጀ ነው

“በሌላ መንገድ እናደርገዋለን” አለ ክሪስ እንደገና እያሰበ “በመጀመሪያ እኔ እሄዳለሁ መሬት ስደርስ ኮሪን ታስሪውና ቀስ እያልሽ ወደታች ትለቂዋለሽ
ቀጥሎ ኬሪንም እንደዚያው ታደርጊያለሽ: በመጨረሻ አንቺ ትመጫለሽ ስለ እግዚአብሔር ብለሽ የምትችይውን ጥረት ሁሉ አርጊ! አደጋ በሚደርስበት
ወቅት ከፍተኛ ንዴት ከሰው በላይ የሆነ ጥንካሬ እንደሚፈጥር ሰምቻለሁ።"

“አንተ የበለጠ ጠንካራ ስለሆንክ እኔ መጀመሪያ ልሂድ” አልኩት በድካም ስሜት “አይሆንም! ድንገት ፈጥነው ከመጡ ለመያዝ ታች መሆን አለብኝ ያንቺ ክንዶች የኔን ያሀል ጥንካሬ የላቸውም: ክብደቱ ሁሉ አንቺ ላይ
እንዳይሆን ገመዱን ጭስ መውጫው ላይ አስርልሻለሁ እና ካቲ ይvህ የአደጋ ጊዜ ነው!”

በአይጥ መያዣ ወጥመዱ ላይ አራት የሞቱ አይጦችን በድንጋጤ ተመለከትኩ።“ትንሽ ጥንካሬ እንድናገኝ እነዚህን አይጦች መብላት አለብን፡” አለ ኮስተር ብሎ፡ “ማድረግ ያለብንን ሁሉ ማድረግ አለብን::''

እነዚያን የሞቱ ትንንሽ ወፍራም ነገሮች በመጠየፍ እየተመለከትኩ “ጥሬ ስጋ? ጥሬ አይጥ? አይሆንም!" አልኩ በቀስታ:
በጣም ተናዶና አስገዳጅ በሚመስል አይነት መንትዮቹንም ሆነ ራሴን በህይወት ለማቆየት የሚያስፈልገውን የትኛውንም ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ነገረኝ፡ “ተመልከቺ ካቲ፣ መጀመሪያ እኔ ሁለቱንም እበላለሁ ገመዶቹን
በደንብ ለመቋጠርም የልብስ መስቀያ ስለሚያስፈልገኝ ላምጣ… ታውቂያላሽ ኬቲ እጆቼ አሁን በደንብ አይሰሩም” አለ፡

ሁላችንም በጣም ከመድከማችን የተነሳ የምንንቀሳቀሰው የግዳችንን ነው::

አየት አደረገኝና “በእውነት አይጦቹ በጨውና በበርበሬ በጣም የሚጣፍጡ ይመስለኛል” አለ፡፡

ጭንቅላታቸውን ቆርጦ ቆዳቸውን ገፈፈና አንጀታቸውን አወጣው: ትንንሽ ሆዳቸውን በመሰንጠቅ ረጃጅምና ቀጫጭን አንጀቶቻቸውን እንዲሁም ትንንሽ
ልቦቻቸውንና ሌሎች የውስጥ እቃዎቻቸውን ሲያወጣ እየተመለከትኩት ነበር ሆዴ ባዶ ባይሆን ኖሮ ሊያስመልሰኝ ይችል ነበር።

ክሪስ ጨውና በርበሬ ሊያመጣ ሲሄድ አይኖቼ ቆዳቸው ተገፍፎ ለምግብነት የተዘጋጁት አይጦች ላይ ተተክለው ቀሩ። አይኖቼን ጨፍኜ የመጀመሪያውን
ጉርሻ ለመጉረስ ሞከርኩ እርቦኛል ግን ይህንን ለመብላት የሚያክል አይደለም ረሀቤ።

ወዲያው እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ግንባራቸውን አጋጥመውና አይናቸውን ጨፍነው ጥጉ ላይ የተኙትን መንትዮች አሰብኩ በእናታችን ማህፀን ውስጥም እንደዚህ ተቃቅፈው የነበሩ ይመስለኛል: ምስኪን ልጆች! በአንድ ወቅት በጣም የሚወዷቸው እናትና አባት ነበሯቸው።

እነሱን በደህና መሬት ለማድረስና ከጎረቤት ምግብ ለማግኘት አይጦቹ ለእኔና ለክሪስ በቂ ጥንካሬ እንደሚሰጡን ተስፋ አድርገናል።

ክሪስ ቀስ እያለ ወደኛ ሲመለስ ሰማሁ። በሩ ላይ ቆም ብሎ አመነታ።ሽራፊ ፈገግታ እያሳየ ነው ሰማያዊ አይኖቹ ወደኔ እየተመለከቱ አንፀባረቁ።
በሁለት እጆቹ በደንብ የምናውቀውን ትልቅ የሽርሽር ቅርጫት ይዟል። ቅርጫቱ መክደን እስከሚያስቸግር ድረስ በምግብ ተሞልቷል ሁለት ትልልቅ
ፔርሙዞች አወጣ አንደኛው ውስጥ የአትክልት ሾርባ፣ ሌላኛው ውስጥ ወተት ነበረበት በማየው ነገር ግራ ተጋባሁ። እናታችን አምጥታልን ነው?
ከሆነ ታዲያ ለምን ወደታች እንድንሄድ አልጠራችንም? ለምንስ ደግሞ እኛን ፍለጋ ወደዚህ አልመጣችም?
👍252👏2
ክሪስ ኬሪን፣ እኔ ደግሞ ኮሪን ጭኖቻችን ላይ አስቀምጠን ሾርባውን በማንኪያ
ማጉረስ ጀመርን። ደሙን እንደተቀበሉት ሁሉ ሾርባውንም እየተቀበሉ ነው:: ሳንድዊቹንም እየቆረስን አበላናቸው: እኛም ተስገብግበን በላን፡ ክሪስ
እንዳያስመልሰን እያስጠነቀቀ ነበር።

ምግቡን ሁሉ ኮሪ አፍ ውስጥ መጠቅጠቅ ፈለግኩ። እሱ ግን ቀስ እያለ ነበር ይበላ የነበረው: አእምሮዬ ውስጥ በሺ የሚቆጠሩ ሀሳቦች ተመላለሱብኝ፡ ለምን ዛሬ ዛሬ ለምን ምግብ አመጣች? ለምን ትናንትና ወይም ከዚያ በፊት
አላመጣችም? ምክንያቷ ምንድነው? በመጣልን ምግብ እየተደሰትኩ መብላቴን ትቼ ነገር አብሰለስል ጀመር እፎይ ለማለት በጣም ተጠራጣሪ ሆኜ ነበር።

ክሪስ ቀስ እያለ ጥቂት ሾርባና ግማሽ ሳንድዊች በላ፡ የተሸፈኑትን ሁሉ ሲገልጥ ደቃቅ ስኳር የተነሰነሰባቸው አራት ዶናቶች ተመለከትን፡ ምንም አይነት ጣፋጭ ተሰጥቶን ለማናውቀው ለእኛ ለመጀመሪያ ጊዜ ከምግብ በኋላ የምንመገበው ጣፋጭ ከአያትየው ተሰጠን። ይቅርታ የመጠየቂያ መንገዷ ይሆን: አላማዋ ምንም ይሁን ምን እኛ ግን የተረጎምነው በዚያ መንገድ
ነበር።

ጠኔ ሊይዘን በተቃረብንበት ሳምንት ውስጥ በእኔና በክሪስ መካከል ለየት ያለ ነገር ተከስቶ ነበር: በዚያን ቀን የተነሳሳበት ምክንያት ምናልባት እኔ የሞቀው ገንዳ ውስጥ በአረፋው መሀል ተቀምጬ እሱ ፀጉሬ ላይ ያለውን
ሬንጅ ለማስለቀቅ ልፋት ላይ ስለነበረ ሊሆን ይችላል
ከዚያ አሰቃቂ ቀን በፊት ለመንትዮቹ የወላጅነት ገፀ ባህርይ ወስደን ትወና የምንሰራ ወንድምና እህት ነበርን አሁን ግን ግንኙነታችን ተቀይሯል
ከአሁን በኋላ ትወና አንሰራም: ለኬሪና ለኮሪ ትክክለኛ ወላጆች ነን እነሱ የእኛ ሀላፊነት፣ የእኛ ግዴታ ናቸው እኛም ራሳችንን ሙሉ በሙሉ ለእነሱና ለእርስ በራሳችን ሰጥተናል።

አሁን ምንም ብንሆን እናታችን ለእኛ ግድ እንደሌላት ግልፅ ሆኖልናል።

ክሪስ የእናታችንን መለወጥ አስመልክቶ ምን እንደሚሰማው መናገር አይፈልግም፡ አይኖቹና ግድ የለሽ እንቅስቃሴዎቹ ግን የበለጠ ይናገራሉ።የእናታችንን ፎቶ አልጋው አጠገብ አስቀምጦ ነበር። አሁን ግን አንስቶታል:
እኔ ከማምናት የበለጠ ሁልጊዜ በእሷ ያምን ስለነበር በጣም የተጎዳው እሱ ነው እኔ ከታመምኩት በላይ እየታመመ ከሆነ እውነትም ስቃይ ላይ ነው:

አሁን ወደ መኝታ ክፍላችን መመለስ እንደምንችል ለማመልከት በወዳጅነት
መንፈስ እጄን ያዘኝ፡ እንቅልፍ ላይ ያሉ ጣረሞቶች መስለን ደረጃውን
ወረድን: ሁላችንም ህመምና ድካም ተሰምቶናል በተለይ መንትዮቹ::መንትዮቹም ሆነ ክሪስ ምን እንደሚመስሉ አይቻለሁ: ራሴ ምን እንደመሰልኩ ግን ማየት አልቻልኩም: መልበሻው ላይ ባለው ሰፊና ረጅም መስተዋት
ከፊቱ የተቆረጠ፣ ከኋላው ግን ረጅም ፀጉር ያላትን ዳንሰኛ ለማየት በመጠበቅ አይኖቼን ሳማትር መስታወቱ የለም።

ፈጠን ብዬ ወደ መታጠቢያ ቤቱ በመሄድ የመድኃኒት ማስቀመጫው ቁምሳጥን
ላይ ያለውን መስታወት አየሁት ተሰብሯል ተመልሼ ወደ መኝታ ክፍል ገብቼ ክሪስ እንደ ጠረጴዛ የሚጠቀምበትን የመልበሻውን ጠረጴዛ ክዳን አንስቼ ስመለከት እዛ ውስጥ ያለው መስተዋትም ተሰብሯል።

በተሰባበረው መስታወት የራሴን የተቆራረጠ ምስል ተመለከትኩ። ማየቱ ደስ አይልም:: የምግቡን ቅርጫት ክፍሉ ውስጥ ባለው ቀዝቀዝ በሚለው ጥግ ቦታ
አስቀምጬ ጋደም አልኩ። ስለተወሰደውም ሆነ ስለተሰባበሩት መስታወቶች
ክሪስን አልጠየኩትም ለምን እንዳደረገችው አውቄያለሁ። ኩራት ኃጢአት ነው ስለምትል በእሷ አይን እኔና ክሪስ እጅግ የከፋን ኃጢአተኞች ነን እኛን
ለመቅጣትም መንትዮቹም መሰቃየት ነበረባቸው:: ግን ለምን እንደገና ምግብ አመጣችልን? መገመት አልቻልኩም

የምግብ ቅርጫቶች የመጡባቸው ሌሎች ማለዳዎች መጡ፡ አያትየው የምግብ ቅርጫቱን ይዛ ብትመጣም አንድም ቀን ግን ወደኛ ማየት አልፈለገችም።
አይኖቿን ዞር ታደርግና በፍጥነት ወደበሩ ትሄዳለች: የተቆረጠውን ፀጉሬን እንዲያሳይ አድርጌ ከፎጣ የተሰራ ጥምጥም ጭንቅላቴ ላይ ጠምጥሜያለሁ። እሱን እንኳን አይታ አስተያየት ትሰጣለች ብዬ ባስብም ምንም አስተያት
አልሰጠችም አያትየው ስትመጣና ስትሄድ እናያታለን እንጂ ስለ እናታችን እንኳን ልንጠይቃት አልቻልንም: እናታችን የት እንዳለችና መቼ እንደምትመጣ
እንኳን አናውቅም: አያትየው ያለንበትን ሁኔታና የተሰማንን እንድታውቅ ዞር ብላ እንድታየን በሚል በጥላቻና በቁጣ ተሞልተን ብናፈጥባትም እሷ ግን
አይኖቻችንን መመልከት አልፈለገችም: እንድታየን ለማድረግ ስል መጮ ሁሉ እመኛለሁ መንትዮቹን እንድትመለከትና ምን ያህል እንደከሱና ትላልቅ አይኖቻቸው እንዴት እንደፈዘዙ እንድታውቀው ፈልጌያለሁ: እሷ ግን አይታይም።

ከኬሪ አጠገብ አልጋ ላይ ጋደም ብዬ ወደራሴ በጥልቀት ተመለከትኩና ነገሩን ቀድሞ ከነበረበት እንዴት የከፋ እንዳደረግኩት አስተዋልኩ ክሪስ በአንድ ወቅት ደስተኛና መልካም ነገሮችን ብቻ የሚመለከት ከነበረበት ወጥቶ አሁን ግን ተስፋ ቆራጭና የእኔ ግልባጭ ሆኗል። በፊት እንደነበረው አይነት ሳቂታ፣
ብሩህና ከመጥፎ ነገሮች መሀል ጥሩውን የሚያይ እንዲሆን እፈልጋለሁ።

ነሀሴ መጨረሻ አካባቢ አንድ ምሽት ክሪስ ወደ አልጋዬ መጣና “መንትዮቹ ድብን ያለ እንቅልፍ ይዟቸዋል እዚህ ደግሞ ይሞቃል። ወደ ዋና ብንሄድ አሪፍ አይመስልሽም?” አለኝ:

ዋና? እንዴት ያለ የደደብ ሀሳብ ነው: ብንችል እንኳን እሱ የሚያሸንፍበትን ምንም ነገር ማድረግ አልፈልግም: “የት ነው ለመዋኘት የምንሄደው?መታጠቢያ ገንዳው ላይ?” አልኩ

እናታችን የነገረችን ሀይቅ ውስጥ ነው እንጂ፣ ከዚህ ብዙም አይርቅም በዚያው የሰራነው ገመድ መሬት ያደርሰን እንደሆነ እንሞከረዋለን አሁን ጠንካሮች ስለሆንን ምናልባት እሳት ቢነሳ እንኳን በቀላሉ መሬት መድረስ
እንችላለን: ረጅም ጊዜ አንቆይም” ሲል በጣም አብዝቶ ለመነኝ፡ ህልውናው እንደምንችል ለማረጋገጥና ቢያንስ አንድ ጊዜ እንኳን ከዚህ ቤት ወጣ በማለት
ላይ የተገነባ ይመስል ነበር

“መንትዮቹ ከእንቅልፋቸው ሲነቁ ቢያጡንስ?”

“ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ እንደሆንን የሚገልፅ ማስታወሻ
እናደርግላቸዋለን፡ በዚያ ላይ እስከ ጠዋት ድረስ ለሽንት እንኳ አይነቁም”

እስክሸነፍ ድረስ ተከራከርን ብዙ ለመነኝ፡ በመጨረሻ ተስማማሁና ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ሄድን፡ ከዚያም በተተለተለ አንሶላ የሰራው መሰላል ወዳለበት የጭስ መውጫ ጣራ ላይ ወጣን፡ ጣሪያው ላይ ስምንት የጭስ
መውጫዎች አሉ ቋጠሮዎቹን አንድ በአንድ እየፈተሸ መመሪያ ሰጠኝ፡ “ትልቁን ቋጠሮ
ለመርገጫ ተጠቀሚ፤ እጆችሽን ከላይኛው ቋጠሮ በላይ አድርገሽ ቀስ እያልሽ ወደ ታች ውረጂ፡ የሚቀጥለውን ቋጠሮ በእግርሽ ፈልጊና ገመዱ በእግሮችሽ
መሀል መሆኑን እርግጠኛ ሁኚ: እንደዚያ ከሆነ ተንሸራተሽ አትወድቂም''

በልበ ሙሉነት እየሳቀ ገመዱን ወደ ጣሪያው ጠርዝ ወሰደ። ከሁለት አመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ መሬት እየወረድን ነው...

ይቀጥላል
👍46😢16😁4
በህይወት መንገድ ላይ…
(አጋቾቹ)
ምዕራፍ-3
///
ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እርስ በርስ ተጠጋግተን ተቀምጠናል...ዙሪያችንን ሽፍቶች የከበብን ይመስል ስናወራ በሹክሹክታ ነው።ከጎኔ ያለችው ሠላም ስለሆነች ለጊዜው ወሬዬ በዋናነት ከእሷ ጋር ነው።
"ደህና ነሽ አይደል?"
"ደህና ነኝ ....አንተስ እንዴት ነህ ? ተመቸህ?"አለቺኝ በለሠለሠ የእናት መሳይ ድምፅ
"በጣም ተመችቶኛል .ግን.. ትንሽ ስለሚቀዘቅዝ ማሞቂያውን ብትለኩሺው"ስል ቀለድኩባት
"ይሻላል?" አለቺኝ
"አዎ...በነገራችን ላይ ስምሽን ዘሬ ነው ያወቅኩት"ተናዘዝኩ።
"አንድ ላይ መስራት ከጀመርን እኮ 15 ቀን ሆኖናል...ስሜን ለማወቅ እስከዛሬ መጠበቅህ ይገርማል?"
"ይቅርታ ይደረግልኝ...በዚህ ጉዳይ ደካማ ሰው ነኝ"
"ድክመት እንኳን አይደለም የትኩረት ጉዳዮ ነው?"
"ትኩረት ማለት?"
"ተወው ለጫወታው ብዬ ነው...ስሜ ሰላም ይባላል"
"አሁንማ አውቄዋለው ባይሆን የእኔ...."
"የአንተንማ በደንብ አውቃለው ኢንጂነር በቃሉ ...ሀለቃዬ አይደለህ አለማወቅ እራሱ አይፈቀድልኝም እኮ።"
"ለጊዜው ኢንጂነሩን ተይውና በቃሉ ብቻ ይበቃል?..
"ካልክ እሺ"
"ይሄኔ ቤተሠቦችሽ የት ሄደች ብለው ይጨነቃሉ አይደል?"
"ያንተስ?"
"ምን ጥያቄ አለው እሰከአሁን ከመቶ ጊዜ በላይ ስልኬ ላይ ደውለዋል...ጓደኞቼን ጠቅላላ በስልክ አደንቁረዋል...እናቴማ ከሰማች ሀገር ተቃጠለ..."
"እኔስ በዚህ ምንም የሚያስጨንቅ ጉዳይ የለብኝም"አለቺኝ
"ማለት?"
"ማለትማ ማንም ትመጣለች ብሎ የሚጠብቀኝ የለም..ቢያንስ እስከ አስር ቀን"
"ምን..?"ንግግሯ አስገረመኝ።
"እሺ ለመሆኑ አስር ቀን ሙሉ ጠብቆ ዘናና ሰከን ብሎ የሚፈልግሽ ማን ነው ባክሽ?
"የቤት አከራዬ"መለሠችልኝ...
ቀላል አልሳቅኩም"በቃ"
"አዎ በቃ"
"ምንድነው እንዲህ የሚያስቃችሁ ለእኛም አጋሩን እንጂ"አይዳ ነች ሰርጎ ገብ ተናጋሪዋ
"ድንበር መዝለል አይቻልም ...እዛው ጎንሽ ካለው ሰው ጋር አውሪ"አልኳትና
ትኩረቴን ወደ ሰላም መልሼ"የቢሾፍቱ ልጅ ነሽ?"ስል ሌላ ጥያቄ ጠየቅኳት
"አይደለሁም ...የሀዋሳ ልጅ ነበርኩ .....ቢሾፍቱ ከመጣው ገና ሁለት ወሬ ነው"
"ነው ገባኝ "
"ምኑ ነው የገባህ ?"አለችኝ ጠንከር ባለ የንግግር ቃና።
"ያው ማለት እንደማንኛዋም የደረሰች ወጣት በሆነ አለመግባባት የተነሳ ከቤተሠብሽ ኮብልለሽ በራስሽ ለመቆም ተሸሽገሽ ለመኖር እየሞከርሽ ያለ መሠለኝ...?"
"በእንደዚህ አይነት ደካማ የመገመት ችሎታህ ሁለተኛ ምንም ነገር እንዳትገምት "
"እሺ..እንደዛ ካልሆነ ምንድነው ?"
"በሰላም ከወጣን አንድ ቀን እነግርሀለው"
"ካልወጣንስ?"
"ካልወጣንማ ያው ግልግል ነው...የእናንተን አላውቅም እኔ በህይወት ብኖርም ደስተኛ ነኝ...ብሞትም እንደዛው ደስተኛ ነኝ...እግዚያብሄር የፈቀደው ሁሉ ይሁን?"
"አክራሪ ሀይማኖተኛ ነሽ አይደል?"
"አክራሪ ሀይማኖተኛ ..?አይ እኔ ሀይማኖተኛ አይደለውም...መንፈሳዊ ሰው በሚለው ቢስተካከልልኝ እመርጣለው።
"ልዩነቱ ምንድነው?"
"ሀይማኖት ማለት ስለ ድርጅት አባልነትና ታማኝነት ነው የምናወራው...ሀይማኖት ከሠማያዊ ሀሳብ ጋር የተቀየጠ አለማዊ ጉዳይ ይበዛዎል...መንፈሳዊነት ግን እንደዛ አይደለም ይለያል...ግንኙነት ከእግዚአብሄር ጋር ታማኝነትህም ለሠማያዊው አለም ብቻ ነው የሚሆነው።ሀይማኖት የመንጋ ጉዞ ነው..መንፈሳዊነት ግን ለብቻህ የምትጓዝበት የፅሞና መንገድ ነው።
"አሁንም ሙሉ በሙሉ ግልፅ አልሆነልኝም..እግዚያብሄር በህብረት ሆነን እንድናመልከው ያበረታታናል.. ሁለትም ሶስትም ሆናችሁ በስሜ ካላችሁ በመካከላችሁ እገኛለሁ ብሎል...ታዲያ ካንቺ ሀሳብ ጋር አይጋጭም"
ይሄንን ጥያቄ ሳትመልስልኝ"ይቅርታ ለጊዜው ጭውውታችን እዚህ ጋር ይቁም...የሆነ ነገር ሊከሰት ነው?"
"የምን ነገር ...ምን እያልሽ ነው?"
"እመነኝ ..ትከሻዬ ነግሮኛል...ቆይ ልፀልይ "ብላ ከስሬ ተነሳች

ድሮም በቋፍ ያለ ልቤን በፍርሀት አራደችው።‹‹ይህቺ ልጅ ጥንቆላም ትሞካክራለች እንዴ?›በውስጤ ነው ያሰብኩት፡፡ስሬ ያለውን ባትሪ አነሳውና አበራው...ሰላም ከእኔ በአንድ ሜትር ርቀት እግሮቾን እንደ ብድሀ መነኩሴ እርስ በርስ አቆላልፋ መሬት ላይ በመቀመጥ እጆቾን እንደሰንደቅ አንድ ላይ አነባብራ ግንባሯ አካባቢ ሰቅላ በፍፅም መመሠጥ ውስጥ ገብታለች።ባትሪውን ዙሪያ ገባውን አበራው ..ሁሉ ነገር እንደነበረ ነው።አይዳና በሪሁን እርስ በርስ ተጣብቀው የሞቀ ወሬ ላይ ናቸው...ጋሽ አህመድ ከእነሱ ትንሽ ፈንጠር ብሎ እንቅልፉን እያስነካው ነው....ባትሪውን አጠፋውና በጭለማ ውስጥ ከፍርሀቴና ከሀሳቤ ጋር መታገል ጀመርኩ፡፡
ብዙም ሳይቆይ"ምንድነው የሚተረማመሰው?"አይዳ ጠየቀች
"ምን ሰማሽ...?"
‹‹እኔ እንጃ.. የሆነ ነገር አይሰማችሁም...?ባትሪውን አብራው እስኪ"
አበራውት"ሠላም በቦታዋ በተመስጦ ላይ ነች...ባትሪውን አርቄ ወደ ማዶ አበራው.... ከዎሻው ስንጥቅ የሆነ ነገር ፈልቅቆ ለመውጣት ሲታገል ይታየኛል... አዎ ሽብልልል እያለ ወጣ..‹‹.እባብ ነው..እባብ"እኔነኝ ያልኩት ..ስቅጥጥ ብሎኝ
"ኢንጂነር እባብ አይደለም....ዘ...ንዶ ነው"በሪሁን በሚርገበገብ ድምፅ አረመኝ።
ሰውነቴን አንድ ላይ አኮማትሬ ጭብጥብጥ አልኩ .... እውነትም ሽብልል እያለ በግማሽ ሲወጣ በፊልም ላይ እንኳን በሙሉ አይኔ ደፍሬ አይቼው የማላውቀው አስፈሪ ዘንዶ ነው..
"አሁን አፉን ከፍቶ ሊውጠን ስራችን ቢደርስ ምን አደርጋለው? ሁላችንንም ለማትረፍ እፍለማለው ወይስ ከመካከላችን አንድ ሰው ወርውሬለት እኔን እንዲምረኝ እማፀናለው?በአእምሮዬ የተሠነቀረ ቀሺም ሀሳብ ነበር..
."ምን አናድርግ?"አለ ጋሽ አህመድ...እኛ እንዲህ ስንተረማመስ ሰላም ሰላማዊ በሆነ ፅሞና ውስጥ እንዳለች ነው. .ዘንዶው ሙሉ በሙሉ ከስንጥቁ ውስጥ ወጥቶ በእኛ አቅጣጫ እየተጓዘ ግማሽ መንገድ ደርሷል...ርዝመቱን ስገምት ስድስት ወይም 7 ሜትር ይሆናል።..በሪሁን ቀስ ብሎ ልክ እንደ ዘንዶ እየተሳበ ሄደና ቅድም የተደፈነብንን ከበላያችን ያለውን አለት ሲቧረብርበት የነበረውን ብረት ቀስ ብዬ አነሳና በእጇቹ አጥብቆ ያዘ ..ጋሽ አህመድም ሌላውን ብረት ያዘ ...እኔ በቆምኩበት እንደደነዘዝኩ ነው።

".ምን እየሰራችሁ ነው?"ስትል ጠየቀቻቸው አይዳ...እንግዲህ የምናወራው ንግግራችን ዘንዶ ጆሮ እንዳይደርስ ይመስል በሹክሹክታ ነው..ግን የዘንዶን የመስማት ችሎታ ሁለታችንም የምናውቅ አይመስለኝም፡፡

"እንዴ ሊውጠን እየመጣ እኮ ነው...ቢያንስ እየተፋለምን እንሙት"በሪሁን ነው በቁርጠኝነት የመለሠው

አይዳ"ቆይ ...የተሻለ ሀሳብ አለኝ "አለችና ከእኔ እጅ ላይ አንከርፍፌ የያዝኩትን ባትሪ ተቀበለቺኝ.... ሁለተኛውን ባትሪ ከነበረበት ቦታ አነሳችና አበራችው...አንድን በቀኛ አንድን በግራ እጆ ያዘችና አንድ ላይ አቆራኝታ ቀጥታ ዘንዶ አይኖች ላይ አበራችበት፡፡ሽምቅቅ አልኩ...ከፍራቻዬ የተነሳ ሽንቴ ሁሉ ሳያመልጠኝ አልቀረም ።

"ምን እየሠራሽ ነው ?ከመካከላችን ማንን ቀድሞ መዎጥ እንዳለበት አይቶ እንዲመርጥ ነው?"አላት በሪሁን

‹‹ዝም በል እስኪ…አንዳንድ እንስሳቶች መብራት አይወዱም…እድሌን ልሞክር ነው››አለች
👍24😁3