አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

....ጠዋት ግን በተቻለ እንግዳውን ለመቦጥቦጥ አቅዷል፡፡.

ሚስተር ቴናድዬ ገና ጎሕ ሳይቀድ ከመኝታው ተነስቶ ወደ እንግዳ
መቀበያ ሥፍራ ሄደ፡፡ ሻማ አብርቶ የእንግዳውን ሂሳብ ያሰላል፡፡ ሚስቱ ከአጠገቡ አጎንብሳ ቆማለች:: ሂሣቡን ሲያሰላና ቁጥሮችን ሲጽፍ በዓይንዋ
ትከተለዋለች፡፡ ግን አሳብ አይለዋወጡም፡፡ ከቤት ውስጥ ድምፅ ተሰማ አንድ ሰው ክፍሎችን ይጠርጋል፡፡

ከአንድ ሩብ ሰዓት በኋላ ሚስተር ቴናድዬ ሂሣቡን አስልቶ ጨረሰ::
ከዚያም ክፍሉን ለቅቆ ወጣ፡፡ እርሱ ልክ ሲወጣ እንግዳው እርሱ ከነበረበት ክፍል ገባ። ሚስተር ቴናድዬ ብዙ አልራቀም፥ ሚስቱ ክፍሉ ውስጥ ሆና ታየዋለች:: እንግዳው እቃውን በእጁ ይዞ ነው ከክፍሉ የገባው::

«ምነው ቶሎ ተነሱ!» አለች ሚስስ ቴናድዬ፤ «ገና ሳይነጋ ሊሄዱ
ነው እንዴ?»

እንግዳው አሳብ የገባው መሰለ፡፡ መልስ ቶሎ አልሰጠም:: ቆይቶ
ግን «አዎን እሜቴ፤ መሄድ አለብኝ» አለ፡፡ወደ ሌላ «አገር ማለፍዎ ነው? ሞንትፌርሜ ውስጥ ሥራ የለዎትም
ማለት ነው?» ስትል ጠየቀች::

«የለም፧ ስለመሸብኝ ነው ያደርኩት እንጂ እዚህ የተለየ ጉዳይ
የለኝም» ካለ በኋላ ሂሣቡ ስንት እንደሆነ ጠየቀ፡፡

ሚስስ ቴናድዬ የቃል መልስ ሳትሰጠው ባልተቤትዋ ያዘጋጀውን
ሂሣብ ኣንስታ ሰጠችው::

መንገደኛው ወረቀቱን በማገላበጥ ሂሣቡን ተመለከተ፤ ግን ወረቀቱ
ላይ ያፍጥጥ እንጂ አሳቡ ሌላ ቦታ ነበር::

«እሜቴ» አለ፧ «ሞንትፌርሜ ውስጥ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ
እንዴት ነው?» ሲል ጠየቃት::

«ምንም አይደል» ብላ መለሰችለት በመገረም::፡ እርስዋ የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ ነበር፡፡ «ክቡርነትዎ እንደሚያውቀው መቼም ጊዜው እስከዚህም የሚያስደስት አይደለም:: ከተማዋ ውስጥ ብዙ ብር ያላቸው ሰዎች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው:: ከተማዋም እንደሚያዩዋት በጣም አነስተኛ ከተማ ናት፡፡ እንደ እርስዎ ያለ ሀብታም እንግዳ የሚያጋጥመን አልፎ አልፎ ነው፡፡
ወጪያችን ግን በጣም ብዙ ነው:: ያቺ ትንሽ ልጅ እንኳን ብዙ ታስወጣናለች»
በማለት ችግርዋን ደረደረች::
«ከእርስዋ ብትገላገሉስ?» አለ ነገሩን በማናናቅና በማንቋሸሽ፡፡
«ከማን? ከኮዜት?»
«አዎን፡፡»
የሴትዮዋ ፊት እንደማታ ጨረቃ ወገግ አለ፡፡
«አይ ጌታዬ! ውሰዷት፤ የትም አድርሷት፤ ቢፈልጉ እንደ ምግብ
ብሏት፤ እንደ ውሃ ጠጧት ብቻ ውሰዷት እንጂ እንደፈለጉ ያድርጓት፡፡እምዬ ማርያም ከእርስዋ ብትገላግለኝ ሻማ አበራታለሁ:»
«ተስማምቻለሁ፡፡»
«ይቀልዳሉ መሰለኝ፣ አሁን እውነት ከልብዎ ነው? ይዘዋት ይሄዳሉ?»
«አሁኑኑ እወስዳታሁ፤ ልጅትዋን ይጥሯት፡፡»
«ኮዜት!» ስትል ሚስስ ቴናድዬ ተጣራች::
«ልጅትዋ እስክትመጣ ሂሣቡን ላጠናቅቅ ስንት ነበር?»
ሂሣቡን ከወረቀቱ ላይ አየ:: ግን የመገረም ምልክት አላሳየም::
«ሃያ ሦስት ፍራንክ?»
በዚህ ጊዜ ሚስተር ቴናድዬ ከክፍሉ ውስጥ ገባ፡፡
«የለም ጌታው፤ ያለብህ ሃያ ስድስት ሱስ ብቻ ነው» አለ፡፡
«ሃያ ስድስት ሱስ» ስትል ሴትዮዋ ጮኸች::
«የክፍሉ ኪራይ ሃያ ሰስ ሲሆን የእራት ሂሣብ ስድስት ሱስ ነው::
ስለልጅትዋ ግን እኔና አንተ እንነጋገራለን፡፡ አንቺ ደግሞ ጉዳዩን ለእኛ ብትተይው ይሻላል፡፡»
ሚስስ ቴናድዬ በባልዋ ሁኔታ ተገርማ መልስ ሳትሰጥ ከክፍሉ
ወጥታ ሄደች::
ባለቤቱ እንደወጣች «ምነው ቆምክ? እስቲ አንዴ ቁጭ በል» በማለት ወንበር አቀረበለት:: መንገደኛው ቁጭ አለ፡፡ ሚስተር ቴናድዬ ግን አልተቀመጠም፡፡

«ጌታው» አለ ሚስተር ቴናድዬ ፤ «መቼም ይህቺ ልጅ በጣም
የማደንቃትና የምወዳት ናት፡፡»
እንግዳው ሰውዬ አተኩሮ በማፍጠጥ ተመለከተው::

«የምን ልጅ?»
ሚስተር ቴናድዬ ቀጠለ፡፡
«የእርስዋ ነገር አይሆንልኝም፤ ይህቺን ልጅ በጣም ነው የማደንቃት!»

«የትኛዋን ልጅ ነው የምትለው?» ሲል እንግዳው ጠየቀ፡፡

«ውይ አልገባህም እንዴ! ይህቺ የኛይቱ ትንሽዋ ኮዜት ናታ! እና
አሁን አንተ ልትወስድብን ትፈልጋለህ! እኔ መቼም በዚህ አልስማማም::ከሄደች እጅግ በጣም ትናፍቀኛለች፡፡ ከሕፃንነትዋ ጀምሮ ኣብራን ስለኖረች
የእርስዋ ነገር አይሆንልንም እርግጥ ነው ብዙ ታስወጣናለች፤ ብዙ ጥፋትም ታጠፋለች:፡ እኛ ደግሞ የተትረፈረፈ ሀብት የለንም፡፡ ሆኖም አንድ ጊዜ
ታማ አራት መቶ ፍራንክ ለመድኃኒት አስወጥታኛለች፡፡ ለሰማዩ ጌታ ስል ይህን ያህል ወጪ በማውጣታችን አልተማረርንም፡፡ እናትም አባት
የላትም፡፡ እኔ ግን እንደ አባትም እንደ እናትም ሁኜ አሳደግኋት:: አሁን ቢሆን ለእኔና ለእርስዋ የሚሆን የእለት እንጀራ ኣላጣም፡፡ ስለዚህ ይህቺ ልጅ እንድትሄድብኝ አልፈልግም:: መቼም የምለው ነገር ይገባሃል፡፡ ልጅትዋን
እንወዳታለን፡፡ ባለቤቴ አንዳንዴ ችኩል ናት:: ነገር ግን እርስዋም ብትሆን ልጅትዋን ትወዳታለች፡፡ እንደ ራሳችን ልጅ ነው የምናያት፡፡»

ሚስተር ቴናድዬ ይህን ሁሉ ሲለፈልፍ እንግዳው መንገደኛ ዓይኑን ከተናጋሪው ዓይን አላነሳም:: ሰውዬው ንግግሩን ቀጠለ፡፡

«ይቅርታ አድርግልኝና ማንም ሰው ቢሆን ልጁን ለማያውቀው ሰው
አንስቶ አይሰጥም፡፡ ልክ አይደለሁም? መቼም አንተ እንዲሁ ሲያዩህ የጨዋ
ልጅ እንደሆንክ ታስታውቃለህ፡፡ ሀብትም የተረፈህ ትመስላለህ፡፡ ልጅትዋን ልውሰዳት ስትል ስለልጅትዋ ብለህ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብኛል፡፡ ገባህ
አይደለም? ለእርስዋ ስል ስሜቴን ልግታ፤ ጥቅሜን መስዋዕት ላድርግ ብል እንኳን የት እንደምትወስዳት ማወቅ አለብኝ:: ሌላው ቢቀር የወደፊት
አድራሻዋ የት እንደሚሆንና ከማን ጋር እንደምትኖር ባውቅ እየተመላለስኩ እጠይቃታለሁ፡፡ አሁን ለምሳሌ ስምህን እንኳን አላውቅምና ልጅትዋን ማን
ወሰዳት ተብዬ ብጠየቅ ምን እላለሁ? ነገር ግን ልጅትዋን ልውሰዳት የምትለው ለሕፃንዋ ብለህ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ሌላው ቢቀር ፓስፖርትህን
ወይም የመታወቂያ ወረቀትህን እንኳን ማየት አለብኝ፡፡»

መንገደኛው አሁንም ዓይኑን ከዓይኑ ሳያነሳ የሚቀጥለውን መለሰ፡፡

ሚስተር ቴናድዬ፤ ሰዎች ከፓሪስ ከተማ ወጣ ባሉ ቁጥር የመታወቂያ ወረቀት አይዙም
ኮዜትን ከወሰድኳት እወስዳታለሁ፤ በቃ:: ሌላ አጀብ አያስፈልገውም፡ ለዚህ ማን እንደሆንክ፤ የት እንደምኖር፤ ልጅትዋ ወደፊት የት እንደምትኖር ማወቅ አያስፈልግህም፡፡ እንዲያውም እግርዋ ከዚህ ቤት ከወጣ ዳግም እንድታይዋት አልፈልግም፡፡ በዚህ ትስማማለህ? እሺ ወይም
ሰውየው ከባድ ሰው እንደሆነ ሕሊናው ጠረጠረ፡፡ ማታ ከጠጪዎች ጋር ቢጠጣ፤ ቢስቅና ቢያሽካካም ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ሰውየውን
አጢኖታል፡፡ ማምሻውን ዓይኑ ከኮዜት ዓይን ላይ እንዳላነሳ ልብ ብሉአል፡፡ለምን ወደዳት? ይህ ሰው ማነው? ይኸ ሁሉ ብር ተሸክሞ ሳለ ምነው አዳፋ ልብስ ለበሰ? እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አንስቶ መልስ
ለማግኘት ባለመቻሉ ተበሳጭቶ ነው ያመሽው:: አያትዋ ነው? ታዲያ ለምን ራሱን አያስተዋውቅም? አባትዋ ሊሆን አይችልም! መቼም ማንም
በሆን መብቱን አይሸሽግም፡፡ ታዲያ ይህ ሰው ማነው? ነገር ግን ሰውየው ትልቅ ሰው እንደሆነና ለመታወቅ የማይፈልገው ደግሞ በአንድ ምከንያት መሆኑን አልተጠራጠረም፡፡ ከእንግዳው ጋር ጨዋታ ሲጀምር የተደበቀ
ምስጢር መኖሩን ልቦናው አውቋል፡፡ ስለዚህ የሰውዬው ቆራጥ መልስ አላብረከረከውም፡፡ ነገር ቶሎ የሚገባው ሰው ስለሆነ ያልጠበቀው መልስ ቢመጣም አልተረበሸም፡፡ እንዲያውም እድሌ አሁን ነው ሲል አሰበ። ወዲያው ፍርጥም ብሉ ቴናድዬ ተናገረ::
👍211👏1
«ጌታው!» አላ«አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ይከፈለኝ»::
እንግዳው ከኪሱ የቆዳ ቦርሳውን አውጥቶ ከፈተው፡፡ ገንዘቡን
ከጠረጴዛው ላይ ካስቀመጠ በኋላ ጣቶቹን ከገንዘቡ ላይ አሳረፈ:: «ኮዜትን ሂደህ አምጣ» ሲል የቡና ቤቱን ጌታ አዘዘው፡፡
ወዲያው ከመቅጽበት ኮዜት ሰዎቹ ከነበሩበት ክፍል ገባች፡፡
መንገደኛው ጠቅልሎ ይዞት የነበረውን እቃ ፈታ፡፡ የሚያምሩ
የሰባት ዓመት ልጅ ልብሶች ነበሩ:: ጫማና እስካርፍ እንኳን አልቀረም።
ልብሶቹ ጥቁር ናቸው::
«ልጄ» አለ ሰውዬው፤ «ልብሶቹን ወስደሽ ቶሎ ለብሰሽ ተመለሺ።»
ኣንዲት የሀዘን ልብስ የለበሰች ትንሽ ልጅ አስከትሎ ከከተማው ወጥቶ ገና ሲነጋ ከቤቱ የወጣ የከተማው ነዋሪ ባይተዋር የሆነ ሰው መሄዱን አየ፡፡ ኮዜትም አዲሱን አሻንጉሊትዋን ይዛ ወደ ፓሪስ በሚያመራው መንገድ ባይተዋሩን ተከትላ ሄደች::

ሰውዬው ማን እንደሆነ ማንም አላወቀም:: ኮዜትም አዳዲስና እጅግ የሚያምሩ ልብሶች በመልበስዋ ብዙም ሰው አልለያትም::

ኮዜት መሄዱንስ ትሂድ፤ ግን ከማን ጋር ነው የሄደችው? በየዋህነት

እንደ በግ እየተነዳች ሄደች፡፡ የት እንደምትሄድ ታውቃለች? አታውቅም:. ነገር ግን የምታውቀው ነገር ቢኖር የእነዚያን ጨካኝ ሰዎች ሆቴል ቤት
ለቅቃ መውጣትዋን ነው፡፡ ከቤት ስትወጣ «ደህና ሁኝ» ያላት ሰው
አልነበረም፡፡ እርስዋም «ደህና ሁኑ» ብላ የተሰናበተችው ሰው የለም፡፡ ከዚያ ቤት ተጠልታና ጠልታ ነው የወጣችው::

ኮዜት ሰማይ ሰማዩን እያየች ሰውዬውን ተከትላ ሄደች፤ ነጐደች::አልፎ አልፎ ደጉን ሰውዬ ቀና ብላ ታየዋለች፡፡ የእግዜር መልእክተኛ መሰላት::

መሸት ሲል ዣን ቫልዣ ልጅትዋን ይዞ ከፓሪስ ከተማ ደረሰ፡፡ ከተማ
እንደገቡ በጋሪ ተሳፍረው ከከተማው ክልል ወጡ እርሱ ከፈለገበት ቦታ ሲደርሱ ለባለጋሪው ሂሣባቸውን ከፍለው ወረዱ፡፡ ዣን ቫልዣ የልጅትዋን ትንሽ እጅ ይዞ ጥቂት ከተጓዙ በኋላ ከአንድ አልቤርጎ ገቡ፡፡ እራታቸውን በሉ::ብዙ ስለተጓዙ ደክሞአቸዋል፡፡ ኮዜት እንደደከማት ስለተገነዘበ አቀፋት፧
እሷም አሻንጉሊትዋን ታቀፈች:: ወዲያው ከዣን ቫልዣ እጅ ላይ እንቅልፍ ይዞአት ሄደ፡፡....

💫ይቀጥላል💫
👍123
#ፈንዲሻ_ሲቆሎት_ድምፅ #ሲሰሉት_ድምፅ


#በአሌክስ_አብርሃም


የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት አድርገን እንደተቀመጥን፤ ፕሮግራሙ ቶሎ እንዲያበቃ ሌላ የህሊና ጸሎት ጀመርኩ፡፡ ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን ለማከበር የክፍለ ከተማው የሴቶች ሊግ ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ተገኝቻለሁ፡፡

ሊጉ በመሥሪያ ቤታችን በኩል ግዳጅ የተቀላቀለበት ጥሪ አቅርቦልን አለቃዬ ሂድ !" ስላለኝ
የቀበሌው አዳራሽ ውስጥ ተገኝቻለሁ። ያውም ቅዳሜን በሚያክል ቀን ከሰዓት!! ሰኔና ሰኞ
ገጥሞብኝ፡፡

አሁን ደግሞ የከፍለ ከተማችን የሕፃናትና ሴቶች ፑል ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ደርባቤ በላቸው
እንስራውን ሰብሮ ወሰዳት ልጅቱን የሚል ምርጥ ግጥም ያቀርቡልናል…" አለ ጉጉት የመሰለው መድረክ አስተዋዋቂ፡፡ አፉ ላይ የደቀነውን ማይክሮፎን ድምፅ ማጉላቱን የተጠራጠረ ይመስል በጣም እየጮኸ ነው የሚናገረው::

ቀጠለ "ወ/ሮ ደርባቤ ለክፍለ ከተማችን፣ ብሎም ለከተማችን፣ ብሎም ለኢትዮጵያ ሴቶች፣
ብሎም ለአፍሪካ ሴቶች ታላቅ ምሳሌ የሚሆኑ የዘርፈ ብዙ ሙያዎች፣ ተሰጥኦዎች፣ ትምህርቶች፣ስልጣኖች ባለቤት ናቸው” አለና፣ “…እስቲ ወ/ሮ ደርባቢን ወደ መድረክ…”

...ቿ..ቿ...ቿ..

ጥልፍ ቀሚስ የለበሱትና አንዳንድ ልማታዊ ዝግጅቶች ላይ ልማታዊ ግጥም በማቅረብ የሚታወቁት
ወ/ሮ ደርባቤ መድረክ ላይ ቆመው በፈገግታ ለሕዝቡ ጎንበስ ቀና እያሉ ምስጋና ይሁን ሰላምታ
ያለየለት ግማሽ ስግደት አቀረቡ፡፡ ግጥሙን ሊያቀርቡ ነው ብለን ፀጥ ስንል አስተዋዋቂው
ማዋደዱን ቀጠለ፣ “….ብታምኑም ባታምኑም ወ/ሮ ደርባቤ ይሄን ዝግጅት አስመልከቶ ግጥም
እንድትፅፍልን የነገርናት (አንች አላት) ትላንት ዘጠኝ ሰዓት ነው፡፡ ይገርማችኋል ሌሊቱን ስትፅፍ
አድራ ጧት ስደውልላት በስልክ ግጥሙን አነበበችልኝ…'ወይ መባረክ' ነው ያልኩት።( በሕዝብ
ስልክ ስምንት ገፅ ግጥም እያነበቡ አላየንም ባርኮት)፡፡

“...የግጥሙን ጥልቀት እና ውበት ራሳችሁ ታዘቡት እስቲ ለዚህች ብርቱ ሴት ሞቅ ያላ ጭብጨባ…" ብሎ ጭብጨባውን ራሱ ጀመረው፡፡ ማይኩን በሌላኛው እጁ ሲጠፈጥፈው አዳራሹ ጓጓጓ.. በሚል ልጆሮ የሚቀፍ እስቅያሚ ድምፅ ተሞላ፡፡ ከታዳሚው የተንቦጫረቀ ደካማ ጭብጨባ ጋር ተዳምሮ ጓጓታው በቀላል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች የታጀበ የከባድ መሳሪያ ድምፅ ነበር የሚመስለው፡፡

ብዙው ታዳሚ በየእጁ ፈንዲሻ እና ለስላሳ ይዞ ስለነበረ ማጨብጨብ አልቻለም እንጂ በጭብጨባማ የእኛን ኮፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች ማን ብሏቸው::በተለይ እጃቸው ባዶ ሲሆን የሚያጨበጭቡት ጭብጨባ ቢሾፍቱ ይሰማል፡፡ እጃቸው ባዶ ሲሆን ለዜና ያጨበጭባሉ፣ ለሪፖርት ያጨበጭባሉ፣ የቀበሌው ሊቀመንበር ሲያስነጥሱ ሁሉ
ያጨበጭባሉ፣ እጃቸው ሞላ ካለች ግን ጠቅላይ ሚንስትራችን ቢዘፍኑም አያጨበጭቡም
እንዳንዴ ታዲያ ጭብጨባዎች ሲቀንሱ ኢኮኖሚያችን ያደገ ይመስለኛል፡፡

ቀጠለ አስተዋዋቂው (ወ..ይ ዛሬ) "ወ/ሮ ደርባቤ.ገጣሚ ብቻ አይደሉም፤ የታሪክ ተመራማሪም
ናቸው፡፡ (ወ/ሮ ደርባቤ ቆመው በቁማቸው ገድላቸው ሲለፈፍ በፈገግታ ያዳምጣሉ )..ከፍተኛ
አድናቆት ያተረፈውንና የከፍላ ከተማችን የእድገት ማራቶን ሩጫ ከዘመነ ደርግ ውድቀት ቀኋላ' የሚለውን መጽሐፍ ጨምሮ አራት የግጥም መጻሕፍትን አሳትመዋል፤ ይሄን ያህል
ካልኩ እንዳላሰለቻችሁ ወደ ወ/ሮ ደርሳቤ ልምራችሁ...” ብሎ ማይኩን በአክብሮት ለሴትዬዋ
አቀበላት፡፡ (እፎይ! አንድ አዛ ለቀቅ ይላሱ እማማ ሩቅያ ሲተርቱ)

..ማይኩን ተቀብላ ጓ...ጓ አደረገችና (የፈረደበት ማይክ ተጠፍጥፎም፣ ያወሩትን ሁሉ ተቀብሎ አጉልቶም እሳዘነኝ)፡፡ እ..እኔ እንኳን የተባለውን ያህል ነኝ ብዬ አላምንም.፣ ምከንያቱም እንደ እኔ ዕድሉን ቢያገኙ እንኳን ኢትዮጵያን ዓለምን ጉድ የሚያስብሉ ሴቶች ከእናንተ መሀል አሉ ብዬ ስለማምን ነው…" አለች ወይዘሮ ደርባቤ፡፡

ጭብጨባ…! ቿቿቿቿቿቿቿቿቿ (ፈንዲሻው አለቀ ባአንዴ ጭብጨባው ደመቀኮ)
ከጎኔ የተቀመጠች ሴት “እውነት ነው" ብላ ጮኸት፡፡ (ዓለምን 'ጉድ' ከሚያስብሉት ሴቶች
መሐል እንዷ ሳትሆን አትቀርም፡፡ ዞር ብዬ ሳያት በግራ እጇ ሞባይል ስልኳን፣ በቀኟ፣ መዳፏ
እስኪወጣጠር የዘገነችውን ፈንዲሻ ይዛ በስሜት ወደ መድረኩ እያየች ቁጭ ብድግ ትላለች፡፡
..ከፈንዲሻው ኮርሽም አደረገችለት፡፡)

ሴትዮዋ ግጥሟን ከማቅረቧ በፊት ሰላሳ ደቂቓ አወራች፡፡…እንዴት የወንዶችን ተፅዕኖ ተቋቁማ ታላቅ ገጣሚ' ለመሆን እንደበቃች፣ ሴቶች የርሷን ፈለግ ይዘው እንዲከተሏት፣(ብትወዱስ እኔን ምስሉ ዳርዳርታ)ይሄን ሁሉ አወራችና “እንዳላሰለቻትሁ” በማለት ወደ ግጥሟ ተሸጋገረች
(ገና ድሮ የሰለቸንውን !?)

ወደ መድረክ ስትወጣ መነፅሯኝ ቦታዋ ላይ ረስታው ስለነበር፣ " አቀብሉኝ”ስትሳቸው የእጅ ቦርሳዋን አራት ሰዎች ግራና ቀኝ ይዘው (ማሸርገዳቸው ስላበሳጨኝ የጨመርኩት ነው) አቀበሏት፡፡ቦርሳዋ ውስጥ አስር ደቂቃ ፈልጋ መነፅሯን ቤቷ መርሳቷን አረጋገጠች፡፡..እናም ወደ ብርሃኑ ቀርባ ግጥሟን ማንበብ ጀመረች፡፡

እንስራውን ሰብሮ ወሰዳት ልጅቱን(ርዕስ)
አረ አያ ደገፋው አንተ ትልቀ ሰው፣
አንዲት ፍሬዋን ልጅ ማስቸገርህን ተው!
ውሃ ልትቀዳ ወንዝ ስትሄድ፡
ቁመሽ አውሪኝ አልካት በግድ፣
ይሄ እልበቃ ብሎህ ሰው ጭር ሲልልህ
ሕፃኗን ደፈርካት እግዜር ይይልህ (ውይ ወንዶች አለች ከጎኔ ያለችዋ ባለ ፈንዲሻ)
ደሟን እያዘራች እቤቷ ስትደርስ፣
እንስራ ሰበርሽ ብለው ጎረፉት አያድርስ.
ደሞ በሌላ ቀን እንደገና አድብተህ..፣
አሁንም ደፈርካት አንተ ምን ዓይነት ሰው ነህ። ('በስማም ጭካኔ.ሌላዋ ሴት)

አዳራሹ ፀጥ ብሎ 'ግጥሙን' እያዳመጥን ድንገት ጎኔ ያለችው ሴት ጎርደምደምደም…ከሻሸሽ…
ስታደርግ ደንግጬ ዞሬ ተመለከትኳት፡፡ ተመስገን ፈንዲሻ እየበላች ነው፡፡…እኔማ በግጥሙ
ተመስጣ በስህተት ስልኳን ቆረጣጠመቻት ብዬ ነበር፡፡
ግጥሙ ለድፍን ሀያ ሰባት ደቂቃ ተነበበ፡፡ የግጥሙ የመጨረሻ ስንኞች

ፊስቱላ ተይዛ ስትንከራተት፣
ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኛ አግኝታታ!
እዲሳባ በመኪና አመጣቻት.
መንግሥታችን በሠራው ዘመናዊ አስፓልት…?

አመሰግናለሁ !!

ቿቿቿቿቿቿቿቿቿ….(ታዳሚው ፈንዲሻውን ጨርሶ ነበር)

ለመውጣት ሳቆበቁብ አስተዋዋቂው እንዲህ አለ….

“ለሴቶች ቀን ያልሆነ ግጥም ለመቼ ይሆናል' በማለት ወይዘሪት ዘቢደር የወጣቶች ሊግ አትተባባሪ
ለግንቦት ሃያ አንብባው የተደነቀላትን 'ታታሪዋ ሥራ ፈጣሪ' የሚለውን ግጥምን ላቅርብ
ብላለችና እስቲ ወደ መድረክ…”

ተነስቼ ወጣሁ፡፡ ወደ ቤቴ ስሄድ ከኋላዬ የአስተዋዋቂው ድምፅ ይሰማኛል፡፡

"ወጣት ዘቢደር የእንስቷ ጣጣ የሚል በቅርቡ በታተመ የግጥም መድብሏ ከፍተኛ እውቅና
ያተረፈች ብርቱ ሴት ስትሆን...” እያለ ቀጠለ፡፡

ይሄ ቀበሌ ነዋሪው ሳይሰማ ማተሚያ ቤት ከፈተ እንዴ?.. እንዴት ነው ይሄ መድብል ማሳተም እንዲህ የቀሰለው ጎበዝ? ?!

አለቀ
👍24😁12👎1
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

አሮጌው ቤት

ከአርባ ዓመት በፊት እጅግ ጭር ያለ ሰፈር የነበረው ዛሬ ብዙ
ሕዝብ ይተራመስበታል፡፡ ገጠር መሆኑ ቀርቶ ወደ ከተማነት ተለውጧል፡፡ አካባቢው ዣን ቫልዣ ሲያውቀው ከፓሪስ ከተማ ወጣ ያለ ባላገር ነበር፡፡ዛሬ የከተማው አካል ሆኖአል፡፡ ብዙ ቤቶች ተሠርተዋል፤ መንገድም
ወጥቶለታል፡፡ ቢሆንም ግን የገጠርነት ስሜት አሁንም ይታይበታል፡፡ከመንገዱ ግራና ቀኝ ሳር በቅሎአል:: ቤቶቹም ቢሆኑ እስከዚህም የጸዱ አይደሉም፡፡ የፈረስ ገበያ ከዚያ አካባቢ ስለነበር የስፍራው ጽዳት ይህን
ያህል አያስደስትም::

ከዋናው መንገድ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚታይ ባለአንድ ፎቅ አሮጌ ቤት
አለ፡፡ በሮቹ በምስጥ ስለተበሉ አልፎ አልፎ ቀዳዳ ይታይባቸዋል:: የቤቱ መስኮቶች በጣም ሰፋፊ ናቸው:: የመስኮቶቹ መስታወት አንዳንዶቹ ስለተሰበሩ
በካርቶን መሳይ ወረቀቶች ተሸፍነዋል :: መጋረጃዎቹም ቢሆነ
ከመበለዛቸውም በላይ ጫፍ ጫፋቸው ተቀዳደዋል:: ወደ ፎቅ በሚያስወጣው መሰላል ሲራመዱ ደረጃው እንደ መዚቃ መሣሪያ ያፍጮሃል:: በረት የመሰለ
ትልቅ ክፍል ከሩቁ ይታያል፡፡ የዚህ ክፍል ሀለቱም መስኮቶች ሰፋፊ ሲሆኑ በዚያ በኩል ወደ ውጭ በማየት በመንገድ የሚያልፈውን ማየት ይቻላል::የቤቱ ቁጥሩ 5052 ነው

ዣን ቫልዣ ከዚህ አሮጌ ቤት አጠገብ ሲደርስ ቆም ብሎ ቤቱን
አየው:: ጭልፊት የሚያሳድዳት ጫጩት የተሰወረ ከለላ እንደምትፈልግ ሁሉ እርሱም ከነዣቬር ለመሰወር ከለላ ይፈልጋል:: የዚህ ቤት አቀማመጥ
ደግሞ በጣም የተሰወረ ስለነበር የሚፈልገውን ያገኘ መሰለው፡፡ ከኪሱ ውስጥ ቁልፍ አውጥቶ በሩን ከፈተው:: ከገባ በኋላ መልሶ ዘጋው:: ኮዜትን ታቅፎ በደረጃው ወደ ፎቅ ወጣ፡፡ ደረጃውን ወጥቶ ሲጨርስ ሌላ ቁልፍ ከኪሱ አወጣ፡፡ የተቆለፈውን በር ከፍቶ ወደ አንድ ክፍል ገባ፡፡

ስፋ ካለ ክፍል ወለል ላይ ትልቅ ፍራሽ ተዘርግቷል፡፡ ጥቂት
ቦታ ወንበሮችና ጠረጴዛም አለ፡፡ የእሳት ማንደጃ ከአንድ ጥግ ይታያል:: አንድ ትንሽ የልጅ አልጋም አለ፡፡ ዣን ቫልዣ ቀስ ብሎ ኮዜት ሳትነቃ ከትንሹ አልጋ ላይ አስተኛት::

በሩን መልሶ ከዘጋ በኋላ ሻማ አበራ:: የመንገዱ መብራት ክፍሉን
ያሳይ ስለነበር ሻማ እስካበራ ድረስ በጨለማ አልተንገዳገደም:: በአለፈው ቀን እንዳደረገው ሁሉ ኮዜት ተኝታ ሳለ ዐይኑን ከዐይንዋ አላነሳም:: ለረጅም ጊዜ ኣፍጥጦ ተመለከታት:: ኮዜት ከማን ጋርና የት እንደተኛች ሳታውቅ ለብዙ ሰዓት እንቅልፍዋን ለጠጠች::
ዣን ቫልዣ ጎንበስ ብሎ እጅዋን ሳማት:: ከዘጠኝ ወር በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ እንቅልፍ ወስዶአት ሳለ የእናትዋን እጅ ስሞ ነበር፡፡

ተመሳሳይ የሆነ የሀዘኔታና የጭንቀት ስሜት ተሰማው:: ኮዜት ከተኛችበት አልጋ አጠገብ ተንበረከከ፡፡

ወገግ ብሎ ነግቷል:: ግን ልጅትዋ አሁንም እንቅልፍ እንደወሰዳት
ናት። ከባድ እቃ የጫነ ጋሪ በዚያ ሲያልፍ ያንን አሮጌ ፎቅ ቤት አነቃነቀው፡፡ ኳኳታው በኃይል ስለነበር እንኳን የትኛን የሞተን ይቀሰቅሳል ማለቱ የድምፁን ብርታት መግለጽ እንጂ ማጋነን አይሆንም::

«እመት እመቤቴ» አለች ኮዜት ፈንጠር ብላ ከአልጋው እየተነሳች::
ቀጠለችና ደግሞ መጣሁ መጣሁ» ስትል ጮኸች:: ዓይንዋን ሳትገልጥ ካልጋው ዘላ ወረደች።
እየተንጠራራች ወደ ግድግዳው ሄደች።

«ወይ ጣጣ፤ መጥረጊያው የት አለ!» አለች::

ኣሁን ዓይንዋን ገልጣለች:: በፈገግታ ያጌጠ የዣን ቫልዣን ፊት
ተመለከተች::

«እህ! ለካስ…» አለች ልጅትዋ ፧ «እንደምን አደሩ ጌታዬ::»

ቶሉ ብሎ አካባቢውን መላመድና ባለው መደሰት የልጆች ባህርይ
ነው:: ተደሳች ሁነው ሰው ያስደስታሉ፡፡

ኮዜት ካተሪንን ከአልጋዋ ስር አየቻት፡፡ ወዲያው ብድግ አድርጋ
አቀፈቻት፡፡ ከአሻንጉሊቱ ጋር እየተጫወተች ዣን ቫልዣን የመዓት ጥያቄ ጠየቀችው:: የት ነበረች? ፓሪስ ትልቅ ከተማ ነው? አሁን መዳም ቴናድዬ ከዚህ አይመጡም? ከዚህ የሚስስ ቴናድዬ ቤት ምን ያህል ይርቃል?
ሌላም፧ ሌላም፡፡ በመስኮቱ ወደ ውጭ አይታ «እንዴት ያምራል፤ እንዴት ደስ ይላል» ስትል ተናገረች::

የነበረችበት ሁኔታ በመጠኑም ቢሆን ያስፈራ ነበር፡፡ ነገር ግን
እርስዋ ነፃ የወጣች መሰላት::

«ቤቱን ልጥረግ?» ስትል ጠየቀች::

«የለም፧ ተጫወች» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰላት::

ስትጫወት ቀኑ አለፈ:: ስላለችበት ሥፍራም ሆነ ሁኔታ ለማወቅ
ራስዋን ሳታስጨንቅ ከአሻንጉሊትዋ ጋርና ከጓደኛዋ ጋር እየተጫወተች ደስ ብሎአት ነበር የዋለችው::

በሚቀጥለው ቀን ጎሕ ሲቀድ እንዳለፈው ቀን ኮዜት ስትነቃ ለማየት ዣን ቫልዣ ከአልጋው አጠገብ ሲቀመጥ አዲስ ስሜት ተሰማው፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ በፊት ምንም ነገር አፍቅሮ አያውቅም፡፡ ትዳር ሳይዝ፣ ልጅ ሳይወልድ ፤ ሴት ሳያፈቅርና የልብ ጓደኛ ሳያበጅ ለሃያ አምስት ዓመት ብቻውን ነው የኖረው:: እስር ቤት ሆኖ ኑሮው የጨለማና የስቃይ ነበር፡፡
ዣን ቫልዣ እስር ቤት ከመግባቱ አስቀድሞ ከቤቱ ሲወጣ ልቡ በተስፋ የደነደነ፤ ሐሞተ ሙሉ ሰው ነበር:: እህቱና ልጆችዋ ከሕሊናው ጨርሰው
ባይፋቱም በአሳብ የሚታዩት እጅግ ተንነው ሲሆን እነርሱን ለማግኘት ብዙ ጥረት አደረገ፡፡ ግን አላገኛቸውም:: ጊዜ እንደሚሽረው እንደማንኛውም ነገር ከጊዜ በኋላ ግን ረሳቸው:: ሌሎችም በወጣትነት ዘመኑ የሚያውቃቸው
ነገሮች ሁሉ እንደዚሁ ከሕሊናው ውስጥ መንምነው ጠፍተዋል፡፡

ኮዜትን አግኝቶ ከዚያ የስቃይና የመከራ ኑሮ ሲያወጣትና ይዞአት
ሲሄድ ስሜቱ እጅግ ይነካል፡፡ ይህም ለሰው ልጅ የነበረውን ፍቅር ቀሰቀሰበት። የፍቅሩ ጽናት ከዚህች ልጅ ዙሪያ ተሰባሰበ፡፡ ወደ ኮዜት አልጋ ጠጋ ብሎ ሲመለከታት ልቡ በደስታ ፈካ:: እናት ለልጅዋ ፍቅር እንደምትብረከረክ ሁሉ እሱም በዚህች ልጅ ፍቅር መዋጡ ገረመው፡፡

የፍቅሩ ግለትና የሀዘኔታው ብዛት ሊገባውና በቃላት ሊገልጸው ከሚችለው እርሱ ሃምሣ አምስት ዓመቱ ሲሆን እርስዋ ስምንት ዓመትዋ ነው:: ስለዚህ ፍቅሩ ግሪኮች አጋፔ ብለው የሚጠሩት እናት ለልጅዋ ያላት ፍቅር
ዓይነት እንጂ የሌላ አልነበረም፡፡

በሕይወት ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ የሕይወት ተመስጦአዊና አስጨናቂ ትርኢት አየ፡፡ ከእስር ቤት ሲወጣ ያገኛቸው ጳጳስ የሕይወቱን አድማስ
ያሰፉለትና የሕይወት ጣዕም ሕያቀደዱለት የመጀመሪያው ፍጡር ናቸው፡፡

ኮዚት ደግሞ ተጨማሪ የፍቅር ጎሕ ከፈተችለት፡፡ ይህንኑ እያሰላሰለ ጥቂት ቀናት አለፉ::
አሳዛኝዋና ምስኪንዋ ኮዜትም ቢሆን ሳይታወቃት እየተለወጠች
ነበረ፡፡ እናትዋ ጥላት ስትሄድ ጨቅላ ልጅ ነበረች፡፡ በዚያን ጊዜ ምን ትመስል እንደነበር ለማስታወስ አትችልም፡፡ ልጆች እንደ ሐረግ ካገኙት ላይ እንደሚጠመጠሙ ሁሉ እርስዋም ከሰዎች ላይ ተጠምጥማ ለማፍቀር ብትሞክርም ሰዎች የማፍቀር እድል አልሰጥዋትም ነበር፡፡ እነሚስተር ቴናድዬ ፤ ልጆቻቸውና ሌሉችም ቢሆኑ ፍቅር አላሳይዋትም: ከቤታቸው
የነበረውን ውሻ ትወደው ነበር፡፡ ግን እሱም ሞተ፡፡ ውሻው ከሞተ ጀምሮ እንኳን ሰው የቤት እንሰሳም ቢሆን አላቀረባትም:: ስለዚህ ጥፋቱ የእርስዋ ባይሆንም ገና በስምንት ዓመትዋ ለሰው ፍቅር አልነበራትም:: ቢወድዋት
👍12
ግን ትወድ ነበር፤ ምክንያቱም የማፍቀር ኃይል ስለነበራት ነው፡፡ ያንን ደግ ሽማግሌ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ነው ያፈቀረችው:: ፍቅሯ በየእለቱ
እየዳበረ ሄደ፡፡ ከዚያ በፊት የማታውቀው ስሜት ተጠናወታት፡፡ ለእርስዋ ደጉ ጓደኛዋ አንድ ምስኪን ሽማግሌ ሳይሆን እጅግ የተዋበና ዕፁብ፣ ድንቅ
የሆነ ዣን ቫልዣ የተባለ ሰው ነው::
በዣን ቫልዣና በኮዜት መካከል ያለው የእድሜ ልዩነት በሞላ ጉደል ሃምሣ ዓመት ቢሆንም በሕይወት ዘመናቸው የደረሰባቸው ስቃይና መከራ ፤ምንም እንኳን ርዝማኔው ቢለያይም፧ አሳዛኝነቱ ተመሳሳይ ነው፡፡ ይህም
አንድ እንዲሆነና እንዲቀራረቡ ምክንያት ሆናቸው:: የኮዜት ውስጣዊ ስሜት የሚመኩበት አባት ሲፈልግ የዣን ቫልዣ ፍላጎትና ምኞት ደግሞ
የደረሰበትን የሚያቃልልለት ልጅ ማግኘት ነበር፡፡ ስለዚህ የሁለቱ መገናኘት ማለት የፍላጎትና የስሜት መርካት ማለት ስለነበር ነፍሶቻቸው እርስ በእርስ የሚፈላለጉ መሆናቸውን አወቁ፡፡ ስሜታቸውን ለማርካት ተቃቀፉ፡፡
በቃላት ኃይል ሁኔታውን አጥርቶ መግለጽ ኣይቻልም እንጂ ዣን
ቫልዣ ማለት ሞተ ተብሉ የተለቀሰለት አባትዋ ሲሆን ኮዜት ማለት ደግሞ የሙት ልጅ ናት፡፡ ስለዚህ ነው ዣን ቫልዣ የኮዜት እውነተኛ አባት ባይሆንም የመንፈስ አባትዋ ሊሆን የቻለው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ኮዜት
በጨለማ ውሃ ለመቅዳት በሄደችበትና በሞትና በሽረት መካከል በነበረችበት ሰዓት ሊረዳትና ባልዲውን ከእጅዋ ወስዶ ሲሸከምላት ከየት መጣ ሳይባል በድንገት ብቅ ያለው ፍጡር መለኮታዊ ኃይል የሰጣት አባትዋ ነው::

ዣን ቫልዣ ለመደበቂያ ብሎ የመረጠው ቤት ተስማሚ ነበር::
ከዚያ ሥፍራ ማንም ያገኘኛል ብሎ የሚጠራጠሩት ወይም ያጋልጠኛል ብለው የሚፈሩት አልነበረም፡፡ ዣን ቫልዣ ቤቱን እንዳለ አልተከራየውም::
ምድር ቤቱን ነጋዴዎች እቃ ጭነው የመጡባቸውን ከብቶች ያሳድሩበታል::ፎቁ ላይ ብዙ ክፍሎች ያሉት አፓርትመንት ቢሆንም ከእነርሱና ከአንዲት
አሮጊት በስተቀር ሌላ ሰው አልነበረበትም፡፡ አርጊትዋም ብትሆን የዣን ቫልዣ ሠራተኛ ነበረች፡፡ የተቀሩት ክፍሎች ባዶ ናቸው:: አሮጊትዋ የቤቱም ጠባቂ ሁና ትሠራ ስለነበር የነበሩበትን ክፍል ያከራየቻቸው ይህቺ ሴት ናት፡፡ እንደ አጋጣሚ ቤቱን የተከራዩት የገና እለት ነበር፡፡ ዣን ቫልዣ ራሱን ሲያስተዋውቅ ከሩቅ አገር የመጣ፤ ክስረት
የደረሰበት ነጋዴና የሚኖረውም ከልጅ ልጁ ጋር እንደሆነ አድርጎ ነው::የስድስት ወር የቤት ኪራይ በቅድሚያ ከፈለ፡፡ ቀኑ አልፎ ሳምንት፧ሳምንት አልፎ ወራት ተተኩ፡፡ ኮዜትና ዣን ቫልዣ ከዚያ አስቀያሚ ቤት ደስ እያላቸው ኖሩ፡፡
በጠዋት ተነስቶ እንደሚያዜም ወፍ ኦክትም በጠዋት እየተነሳች
ትጫወታለች፤ ትስቃለች፤ ትዘፍናለች:: ኣንዳንዴ ዣን ቫልዣ እጅዋን እየያዘ ያንሸራሽራታል፡፡
ሕይወትዋን ሙሉ በግሣዔና በድብደባ ያሳለፈች ልጅ አሁን ኑሮ በድንገት ስለተለወጠላት እንዳንዴ ግር እያላት እንደማፈር
ትላለች::

ኮዜት እንደ ድሮው የተቦጫጨቀ በትቶ አትለብስም:: እንደ ሀዘነተኛ
ጥቁር ነው የምትለብሰው:: ጥቁር ይሁን እንጂ ማራኪ ልብስ ስለሆነ
አምሮባታል፡፡ ከድህነት ወጥታ የኑሮን ምንነት እየቀመሰች ነው፡፡
ዣን ቫልዣ ፊደል ያስቆጥራት ጀመር:: ራሱ ፊደል የቆጠረው እስር ቤት ሆኖ ነው:: ኮዜትን ማስተማርና መጠበቅ የዣን ቫልዣ የእለት ተእለት ተግባር ሆነ፡፡ አንዳንዴ ቁጭ ብለው ሲጫወቱ ስለእናትዋ ያወጋታል፡፡ በጸሎትዋ እንድታስባት ያስተምራታል:: እሷም «አባባ» እያለች ነው የምትጠራው፡፡ ይህ እንግዲህ የራስዋ ግምት እንጂ የነገራት አልነበረም።

ዣን ቫልዣ ኮዜትን አግኝቶ ባፈቀራትና በራራላት ጊዜ የነበረበትን ሁኔታ መግለጽ ተገቢ ይሆናል፡፡ ኮዜትን ያገኛት የሰውን ልጅ ክፉነት፧ የህብረተሰብን ጭካኔና ችግር፤ እንዲሁም የዓለምን አንዱን ገጽታ ብቻ
ባየበት ወቅት ነበር፡፡ የሴቶችን ችግር በፋንቲን መከራና ስቃይ ተጠልለና ተጠቃሎና
የባለሥልጣንን ኃይል በዣቬር ተመስሎ በቀረበበት፣ ለሰው ደግ እሠራለሁ በማለቱ እንደገና እስር ቤት እንዲገባ በተወሰነበትና በዚህም የተነሳ እጅግ በተማረረበት ወቅት ነበር
ኮዜትን ያገኛት ምንአልባትም እኛያ ህይወቱን የለወጡት ጳጳስ ትዝታ በመነመነበትና «እንደገና ተመልሰህ ወደ ተንኮል ፧ ክፋትና ምቀኝነት ኑሮ ተመለስ» የሚል ስሜት ሕሊናው ውስጥ በተቀረጸበት ሰሞን ሊሆን ይችላል ኮዜትን ያገኛት፡፡ በዚህ ወቅት ነው ፍቅር በድንገት ብቅ ብሎ ሕይወቱን እንደገና የለወጠውና የመንፈስ ኃይል የተጎናጸፈው::
ከኮዜት ይበልጥ ጉልበትና አቅም ስለነበረው ኮዜትን ጠበቃት፤ ተንከባከባት:: እርስዋም የበለጠ ብርታት ኣጎናጸፈችው፡፡ ምስጋና ለዣን ቫልዣ ይሁንና
እርስዋም ቀጥ ብላ መራመድ ቻለች፡፡ ምስጋና ለእርስዋም ይሁንና ሕይወቱን ከቀና ጎዳና እንዲያስገባ አደረገችው፡፡ እርሱ እንደደገፋትና እንደረዳት ሁሉ
እርስዋም ደገፈችው፧ ረዳችው..

💫ይቀጥላል💫
👍196
አትሮኖስ pinned «#ምንዱባን ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ሁለት ፡ ፡ #ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ አሮጌው ቤት ከአርባ ዓመት በፊት እጅግ ጭር ያለ ሰፈር የነበረው ዛሬ ብዙ ሕዝብ ይተራመስበታል፡፡ ገጠር መሆኑ ቀርቶ ወደ ከተማነት ተለውጧል፡፡ አካባቢው ዣን ቫልዣ ሲያውቀው ከፓሪስ ከተማ ወጣ ያለ ባላገር ነበር፡፡ዛሬ የከተማው አካል ሆኖአል፡፡ ብዙ ቤቶች ተሠርተዋል፤ መንገድም ወጥቶለታል፡፡ ቢሆንም ግን የገጠርነት ስሜት አሁንም…»
#የጉድ_ሀገር ...
ከረሞናታ ልቤ
ወደድኩኝ በል ብቻ ፣ዳግሞ ተካልቤ፤
ከረምናታ ስሜ
ናፈቀችኝ በላ ፤ተጠገነ ቅስሜ።
ያቺን የቀድሞዋን
ከመቼው ወደሀት፣
ከመቼው አጣሀት፤
እስቲ ሰከን በል፤
ሰው ማፍቀር አይቀድምም ፣ልብን ከማባበል።
እባክህን ልቤ ፣ራስህን ቆንጥጥ፤
የትም አትዳረስ ፣እነደተረሳ ጥጥ።
የሄድክ የነጎድከው ፣ አዲስ ገላ ወደህ
እኔን ለማን ክደህ።
አልኖርሞ ያለሷ ያልከኝ
እኔን የት አረከኝ።
እስቲ ሰከን በል ፤ በባለፈው ቆዝም፤
ያልተረጋጋ ግንድ ፣ሥር አፈር አይዝም።
በማጣትህ እዘን፤
ነገን አያቆምም ፣ ዛሬ ሳይመዘን።
የትናንትን ፍቅር ፣ ሳታስታምም ቀርተህ
ከሴት ተኛኹ አትበል ፤ከሐዘን ተኝተህ።
የመለየት ጥጉን
ሐዘን ሳትቀመጥ ፣የትሞ አትሰደድ፤
ማስተዛዘኛ እንጂ
ፍቅር አይባልሞ ፣ ከሕመሞ ቀጥሎ ፣ የተገኘ መውደድ።
ከረምናታ ልቤ!

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍118
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_ሦስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


...እነዣን ቫልዣ ከነበሩበት አካባቢ ከቤተክርስቲያን ደጃፍ የማይጠፋ
አንድ ለማኝ ነበር:: ዣን ቫልዣ በዚያ ባለፈ ቁጥር ሣንቲም ይጥልለታል፡፡ለማኙን የሚመቀኙ የመንደሩ ሰዎች ሰላይ ነው እያሉ ያወሩበታል፡፡ አልፎ አልፎ ዣን ቫልዣ ቆም እያለ ያዋራዋል፡፡ ግን ሲያዋራው ለማኙ ቀና አይልም::

አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ በዚያ ሲያልፍ ለማኙ ዘወትር
ከሚቀመጥበት ቁጭ ብሎ ያየዋል:: ያን እለት ኮዜት አብራው አልነበረችም::ሰውዬው ከተቀመጠበት አጠገብ የመንገድ መብራት በርቶ ስለነበር በጉልህ
( ይታያል:: ዣን ቫልዣ እንደተለመደው ወደ እርሱ ሄዶ ሣንቲም ሰጠው::ለማኙ ቀና ብሎ በማየት አፈጠጠበት:: ወዲያው ወደ መሬት አቀረቀረ፡፡
ፊቱን ሲያየው ያ ዘወትር ጎብጦ እና የሰባ ዓመት ሽማግሌ መስሉ
የሰውዬው አመለካከት ቅጽበታዊ ስለነበር ገዣን ቫልዣን አስደነገጠው:: ይቀመጥ የነበረው ሰው ቀደም ሲል የሚያውቀውና የሚከታተለ ክፉ ሰው እንደሆነ ጠረጠረ፡፡ በዚህ ጊዜ ጥቅጥቅ ካለ ጫካ ነብር ያየ መሰለው::
መናገር ወይም መሮጥ ወይም መቆም ተሳነው:: ለማኙን አተኩር ከማየት ግን አልቦዘነም::
«ወይ ጉድ!» አለ ዣን ቫልዣ እርስ በራሱ ሲነጋገር፡፡ «አበድኩ፤
በሕልሜ መሆን አለበት! ሊሆን አይችልም!» አለ እየተጨነቀና እየተከዘ ወደ ቤቱ ተመልሶ ሄደ፡፡ ያየው ለማኝ ዣቬር እንደሆነ ራሱም ማመን አቃተው:: በ ቅዠት እንጂ እውነት አይሆንም ሲል ደመደመ፡፡

ያን እለት ማታ ያየው ሰው ዣቬር እንደሆነ ለማወቅ እንዲችል
ስላላናገረው በጣም ቆጨው:: በሚቀጥለው ቀን ለዓይን ያዝ ሲያደርግ ወደዚያ ሥፍራ ሄደ፡፡ ለማኙ ከተለመደው ሥፍራ ጸሎት የሚያደርስ መስሎ ቁጭ ብሎአል። እንደተለመደው ሣንቲም እየጣለለት «ታዲያስ
ደህና አመሸህ» ሲል ሰላምታ ሰጠው። ለማኙ «እግዚአብሔር ይስጥልኝ ያስንብትልኝ» ብሎ መልስ ከሰጠ በኋላ መፅዋቾቹን ለማየት አሁንም ቀና አለ፡፡ እውነትም ጠዋሪ ያጣ የሽማግሌ ለማኝ እንጂ ዣቬር እንዳልነበረ
አረጋገጠ፡፡

«እኔስ ምን ማለቴ ነው? አሁን ዣቬር ከየት መጣ ብዬ አሰብኩ? ወይ ጉድ! ዓይኔ እየደከመ ነው?» በማለት ካሰላሰለ በኋላ ነገሩን ረሳው::

ከጥቂት ቀናት በኋላ፤ ከምሽቱ ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ ይሆናል፤
ከክፍሉ ውስጥ ኮዜትን የእጅ ጽሑፍ እያለማመደ ሳለ የቤቱ ዋና መግቢያ ያለወትሮው ተከፍቶ ሲዘጋ ሰማ:: እንግዳ ነገር ሆነበት:: ከቤቱ ውስጥ የሚኖሩት እሱ ራሱ፤ ኮዜትና አሮጊትዋ ናቸው:: አሮጊትዋ እንደሆነ ሻማ ለመቆጠብ ስትል ገና ሳይጨልም ነው የምትተኛው:: ኮዜት ዝም እንድትል ምልክት ሰጣት:: በደረጃው ሰው ለመውጣቱ ኮቴ ሰማ፡፡ ምናልባት አሮጊትዋ
ትሆናለች ሲል አሰበ፡፡ አሁንም አዳመጠ፡፡ ከበድ ያላ ኮቴ ስለነበረ የወንድ ኮቴ መሰለው:: ግን አሮጊትዋ የምትጠቀምበት መጫሚያ እኮ በጣም ከባድ
ነው። ሆነም ቀረም ዣን ቫልዣ ሻማውን አጠፋ፡፡
ኮዜት እንድትተኛ ዝቅ ባለ ድምፅ ከነገራት በኋላ ግምባርዋን ሳማት፡
የኮቴው ድምፅ ፀጥ አለ። ዣን ቫልዣ ከነበረበት ሳይነቃነቅ ዝም ብሎ ከቆየ በኋላ ፊቱን ወደ በር ኣዞረ፡፡ አካባቢው ፀጥ እንዳለ ጥቂት ጊዜ አለፈ፡፡ በበሩ
የቁልፍ ቀዳዳ የሻማ መብራት ጭላንጭል አየ:: በዚህም ከበሩ አካባቢ በውጭ በኩል አንድ ሰው ሻማ ይዞ እንደቆመ አረጋገጠ፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በቁልፉ ቀዳዳ ይታይ የነበረው ጭላንጭል ጠፋ፡ ግን ኮቴ አልተስማም:: ዣን ቫልዣ ልብሱን ሳያወልቅ ከአልጋው ላይ
ተጋደመ፡፡ ሆኖም ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ አልወሰደው፡፡
ሊነጋጋ ሲል ትንሽ እንዳሸለበው በር ተከፍቶ ኖሮ በሩ ሲንጣጣ ስ
ቀስቀሰው:: ሌሊት የሰማው ዓይነት ኮቴተ ተንቀሳቀሰ:: የኮቴው ድምፅ በመቃረቡ እየጉላ ሄደ፡፡ ብድግ ብሎ ወደ በር በመሄድ በበሩ ቁልፍ ቀዳዳ ወደ ውጭ ተመለከተ፡፡ ሰፊ ቀዳዳ ስለነበር በደምብ ያሳያል፡፡ አንድ ሰው
በዣን ቫልዣ ክፍል በራፍ አለፈ፡፡ በሩ አጠገብ ሲደርስ አልቆመም፡ ብዙ ብርሃን ስላልነበረ የሰውዬውን ማንነት ለመለየት አልቻለም። የሰውዬው ሙሉ ቁመና ከጀርባው ባየ ጊዜ በጣም ረጅም ሰው መሆኑን ተገነዘበ፡፡
ቅርጹንና የለበሰውን ልብስ ከዣቬር ጋር ሲያስተያየው ተመሳስሉበት፡፡

የመስኮቱን መጋረጃ በመግለጥ በመስኮት ሰውየውን ለመየት ለመመለስ ድፍረት ስላነሰው ተወው፡፡ ይህ ሰው በሩን በቁልፍ ከፍቶ እንደገባ አልተጠራጠረም:: ታዲያ የበሩን ቁልፍ ማን ሰጠው? ምንድነው ነገሩ?

ከጠዋቱ በአንድ ሰዓት መቶ ፍራንክ ከቦርሳው አውጥቶ ካጣጠፈው በኋላ ኪሱ ውስጥ ጨመረው፡፡ እጁን ከኪሱ ሲያወጣ ሣንቲሞች ከኪሱ ሾልከው መሬት በመውደቃቸው አስደነገጡት፡፡ ወደ ምድር ቤት ወርዶ
በድብቅ ውጭውን ተመለከተ፡፡ ጭር ብሏል፤ ማንም በዚያ አካባቢ አይታይም፡፡ ሆኖም በአካባቢው ብዙ ዛፎች ስለነበሩ ማን እንደትደበቀ ለማየት አይቻልም:: ወደ ክፍሉ ተመለሰ፡፡ «ኮዜት ተነሽ» አለ። እጅዋን
ይዞ ተያይዘው ከቤታቸው ወጡ፡፡

በጨለማ የሚሸፍት ድምፅ
የለሽ ውሻ


ዣን ቫልዣ ዋናውን መንገድ ትቶ በመንደር ውስጥ ተጓዘ፡ መንደር
ቆየ ውስጥ የሚታጠፍ መንገድ ካጋጠመው ቀጥታውን ትቶ ይታጠፋል፡፡


ገበሩ ይህንንም ያደረገው ምናልባት የሚከተለው ሰው ካለ ዱካውን ለማጥፋት
ነበር፡፡

ጨረቃዋ ሙሉ ነበረች:: ይህም በመሆኑ ዣን ቫልዣ ደስ አለው።
የጨረቃው ብርሃን ሁሉንም ያሳይ ስለነበረ በተለይ ራቅ ብሎ ሲሄድ ሰው እንዳልተከተለው አረጋገጠ፡፡ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ገደማ በ14ተኛ ፖሊስ ጣቢያ አጠገብ አለፈ:: ከጣቢያው ጥቂት እንደራቀ ማጅራቱን ከበደው፡፡
ፊቱን ወደኋላ አዙሮ ተመለከተ፡፡ የጣቢው መብራት ወገግ ብሉ ይበራ ስለነበር ሦስት ሰዎች እንደሚከተሉት ተገነዘበ፡፡

«ትንሽ ፈጠን በይ ልጄ» አላት ኮዜትን፡፡ ከዚያ አካባቢ ቶሎ ለመጥፋት ፈጠን ኣለ:: ጥቂት እንደተጓዙ ከአደባባይ ደረሱ:: ጨረቃዋ ከፍ በማለትዋ የአደባባዩ አካባቢ ወለል ብሎአል፡፡ እነዚያ ሦስት ሰዎች እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ዣን ቫልዣ ጨለምለም ካለ ከአንድ በር አጠገብ ተሸጉጠ፡፡

ብርሃን ስለነበር ሰዎቹ በኤደባባዩ ሲያልፉ ሊያያቸው ይችላል:: ሰዎቹ ጊዜ አልወሰዱም፤ ወዲያው ከአደባባዩ ደረሰ፡፡ አሁን አንድ ሰው ተጨምሮ አራት ሆኑ፡፡ አራቱም ዱላ ይዘዋል፡፡ ሁሉም ግዙፍ ሰውነት ስለነበራቸው በጣም ያስፈራሉ፡፡

ከአደባባዩ ሲደርሱ ቆም ብለው ይወያዩ ጀመር፡፡ ከመካከላቸው
አንዱ መሪያቸው ሳይሆን አልቀረም፤ ዣን ቫልዣ ወደሔደበት አቅጣጫ አመለከተ፡፡ ሌላው ደግሞ ወደ ሌላው አቅጣጫ በጣቱ በመጠንቆር አሳየ::
የቡድኑ መሪ ወደ አመለከተበት አቅጣጫ ፊቱን ሲያዞር የጨረቃ ብርሃን ከፊቱ ላይ በማረፉ በግልጽ ታየ:: መሪው ዣቬር እንደነበር ዣን ቫልዣ አወቀው::

«ወዴት ይሄድ ይሆን» ሲል ዣን ቫልገ አሰበ፡፡ ሰዎቹ ቆመው
ሲከራከሩ እርሱ ለማምለጥ ፈልጎ ከተደበቀበት ወጥቶ ሳይታይ በአቋራጭ መንገዱን ቀጠለ፡፡ መንገዱ ላይ ሰው አልነበረም:: ፈጠን ፈጠን አለ፡፡ወደኋላ ዞር ብሎ ተመለከተ:: ማንም የለም::

ድልድይ ካለበት ደረሰ፡፡ አንድ ትልቅ እቃ የተጫነ ጋሪ ድልድዩን
ቀስ ብሉ ሲያቋርጥ እየ:: ጋሪው እርሱ ወደሚሄድበት አቅጣጫ ነበር የሚሄደው:: ጋሪውን ከለላ በማድረግ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ጥቂት ከተጓዘ በኋላ ፊቱን አዙሮ ወደኋላ ተመለከተ:: ከሩቁ የአራት ሰዎች ጥላ አየ፡፡ ሰዎቹ ግን በአካል አልታዩትም::
👍17😢4👏2
አዳኝ እንደደረሰባት ድኩላ ሰውነቱ ተረበሸ፧ ተስፋው መነመነ:: ብዙ
ዛፍ ከነበረበት ሜዳ ከደረሰና መንገዱን ካሳበረ እንደሚያመልጣቸው ያውቃል።
ከአንድ ቀጭን መንገድ ስለደረሰ በዚያ ታጥፎ ሩጫውን ቀጠለ፡፡ ጥቂት እንደተጓዘ ከመንታ መንገድ ደረሰ:: ወደቀኝ ይታጠፍ ወይስ ወደ ግራ፣ አላወላወለም፧ ወደ ቀኝ ታጠፈ፡፡ ለምን?

ምክንያቱም ወደ ግራ የሚታጠፈው መንገድ ነዋሪ ወደሌለበት ወደ ገጠር ነበር የሚወስደው::አልፎ ኣልፎ ወደኋላ እየዞረ ያያል፡፡ ሁልጊዜም የሚጓዘlው ብዙ ብርሃን የሌለበትንና ጨለምለም ያለውን መርጦ ነው:: ከኋላ ትቶት የመጣው መንገድ ቀጥ ያለ ነበር:: ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ ወደኋላ ዞር ሲያይ ማንም አልተከተለውም:: ምድሪቱ አሁንም ጸጥ እንዳለች ናት:: ትንሽ
ተንፈስ አለ፤ ጉዞውን ግን አላቆመም:: ጥቂት እንደተጓዘ አሁንም ፊቱን ቢያዞር በሩቁ የሚነቃነቅ ነገር ያየ መሰለው::

ፈብን፧ ፈጠን ብሎ በመሄድ የሚታጠፍ መንገድ ፈለገ::
የሚከተሉትን ሰዎች ለማሳሳት ነበር፡፡ አንድ ትልቅ ግንብ ካለበት ደረሰ: የተጓዘበት ጠባብ መንገድ ግንብ ከነበረበት ሲደርስ አለቀ:: የግንቡን ጥግ ይዞ ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ማለፍ ይቻላል:: አሁንም ዣን ቫልዣ መወሰን ነበረበት፤ ወደ ቀኝ ወይስ ወደ ግራ? ወደ ቀኝ ተመለከተ፡፡ በሩቁ ጠበብ ያለ ጉዳና ታየው:: ከመንገዱ ባሻገር ከነበሩ ፎቅ ቤቶች አጠገብ ያሉት ዛፎች መሸሸጊያ ሊሆኑ ይችላሉ።
ከዚያ ቢደርስ ራሱን ለመደበቅ የሚችል መሰለው::

ከቀጭኑ መንገድ ሲደርስ አሁንም መንገዱ ለሁለት ተከፈለ:: ወደግራ
ሲመለከት አንድ ትልቅ ነጭ ቀለም የተቀባ የግንብ አጥር አየ:: ግንቡ ወደ ሁለት መቶ እርምጃ ቢርቅ ነው፡፡ ግራው መንገድ የሚሻል መሰለው::ወደ ግራ ለመታጠፍ እንደወሰነ አንድ ሀውልት ወይም ሰው መሆነ
የሚያጠራጥር ነገር በሩቁ አየ:: እርሱን ለመከታተል ትእዛዝ ደርሶት
የሚጠባበቅ ሰው መሰለው:: ዣን ቫልዣ ደነገጠ፡፡ መንገዱን ዘግቶ ሰው እንደሚጠብቀው ተረዳ::
ምን ይሻላል?

ወደ ኋላ ለመመለስ ጊዜ የለም:: ዣቬር ከነሠራዊቱ ቶሎ ደርሶ
እንደሚይዘው ጠረጠረ:: ምናልባትም ተቃርበዋል:: እስካሁንም ያጓተተው
የመንገዱ ጠመዝማዛነትና መከፋፈል ሊሆን ይችላል፡፡ ፖሊስ እንደመሆኑ መጠን መግቢያ መውጫውን በሚገባ ያውቀዋል፡፡ በየማለፊያው ሰው አስቀምጦ ይሆናል:: ወደ ሰማይ የተበተነ አዋራ ወደየአቅጣጫው እንደሚተን ሁሉ የዣን ቫልዣም አሳብ እንዲሁ ተበተነ፡፡ ወደፊት መራመድ ማለት ቆሞ ከሚጠብቀው ሰው እጅ መውደቅ ማለት ሆነ:: ወደኋላ መመለስ
ማለት ደግሞ ከዣቬር እጅ መግባት ነው:: ዣን ቫልዣ ቀስ በቀስ በሚጠመጠም ሰንሰለት የተጠፈረ መሰለው:: ተስፋ በመቁረጥ ወደ ሰማይ
አንጋጠጠ፡፡...

💫ይቀጥላል💫
👍19😢12
#ከፍሪጅ_የተጫረ_እሳት


#በአሌክስ_አብርሃም

አዲሳባ ውስጥ ከሚኖሩ ሃምሳ ዱርዬ ሴቶች መካከል የሰላሳ ዘጠኙ ስም ሜሮን ይመስለኝ
ነበር፡ አምስቱ ሄለን አምስቱ ሃያት፣ አንዷ ግን አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ስም እየቀያየረች
የምታጭበረብርና ስሟ የማይታወቅ፤ ቦሌ ቢባል ካዛንችስ፣ ፒያሳ ቢባል አራት ኪሎ፣ ነርስ ብትሆን ሱቅ ጠባቂ፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ብትሆን ሴተኛ አዳሪ…ብቻ ስሟን የምትቀያይር ሴት ነበረች የምትመስለኝ፡፡

አዎ ስሟን እየቀያየረች በአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ስም የምትዶርር (ዱርዬ የምትሆን) ትዕግስት፣ ሳባ፣ ገነት፣ ማርታ፣ መቅደስ፣ ትርሃስ፣ ሐረገወይን፣ ወላንሳ፣ ዙሪያሽ፣ ፍሬ፤ቃልኪዳን፣ ቲቲ፣ መዓዛ፣ ራሄል፣ ሚሚ፣ ሙና፣ አስናቁ፣ ዘሪቱ፣ መንበረ፣ አለምነሽ፣ ያኔት፤ሊና፣ ላራ፣ ሃና አንድ ነጥብ አምስተኛው ላይ ሜሮን ትሆናለች፡፡ እች እስስት !!

እስስት ብያለሁ አዎ !! ስም እኮ ቀለም ነው፤ ሰው ስሙን ሲቀያይር ቀለሙን ለመቀየር መሞከሩ ነው፡፡ እና ጥሩወርቅ ጎጃምኛ ቀለሟን ቀይራ ሊያ ነኝ ስትል ምን እየሆነች ነው? አካባቢዋን እየመሰለች፤ አዲሳስባን እየመሰለች፡፡ እስስትስ ከዚህ የተለየ ምን አደረገች ? ያው አካባቢዋን ለመምሰል ቀለሟን ነው የቀየረችው፡፡ አነጋገርን ለመቀየር የሚደረግ ድካም ምንን ለመቀየር ነውጥ ? ቀለምን ! እናም ሰውና እንስሳት ከሚመሳሰሉስት ባህሪ ዋናው የተጠጉትን መምሰላቸው ይመስለኛል፡፡

ስምንተኛ ክፍል እንደነበርኩ ፍቅር ያዘኝ፡፡ ሜሮን ከምትባል፣ ሁልጊዜ በብዙ ሴት ጓደኞቿ ከምትከበብ ልጅ ደግሞ ስትስቅ ታምራለች ስትኮሳተር ግን ታምራለች፣ አነጋገሬ ተምታታ አይደል ? እንዲህ ነበር የተምታታብኝ !! ቀይ ናት፣ ከቢጫነት ጋር የሚዋሰን ቅላት፡፡ አፏ ሰፋ ያለ ከንፈሯ ቀይና ወደታች ወረድ ብሎ የሆነ “ከምታፈጥ መጥተህ አትስመኝም” ብሎ የሚጣራ ነገረኛ ከንፈር፤ ሕፃን ሆነን አባ ገመቹ አጥር ላይ ተንጠልጥሎ የሚያስጎመዥንን ፕሪም የመሰለ፡፡

የላይ እና የታች ከንፈሮቿ በአንድ ላይ ሲታዩ የሆነ ልብ የሚሰውሩ የልብ ቅርፅ፡፡ ሜሮንን በአይኔ
ሳይሆን በልቤ ነበር የማያት፡፡ ሳያት የልቤ ሽፋሽፍት ይርገበገባል ! በስንት መከራ ያውም ወደ ዘጠነኛ ክፍል ስናልፍ “ሳይሽ የልቤ ሽፋሽፍት ይርገበገባል..” ብዬ ደብዳቤ ፃፍኩላት፡፡ ሄለን እና ሃያት የሚባሉት ጋጠወጥ ጓደኞቿ ጋር በመሆን በዚች ዓረፍተ ነገር ምክንያት ዓመቱን
ሙሉ መሳቂያ መሳለቂያ አደረጉኝ:: መሪያቸው አንዲት ስሟን የማላውቃት አይጠ መጎጥ የመሰለች ልጅ ነበረች፡፡ልክ እኔ ሳልፍ ደረታቸውን በእጆቻቸው እያራገቡ በሳቅ ያውካካሉ፡፡
እይጠ መጎጧ በአካፋ ዓይኗ አሸዋ ወንድ ስትግፍ የምትውል ከንቱ !! ስሟን አላውቀውም፤
ስሟን አስር ጊዜ ትቀያይራለች ስሟ ብዙ ነው፡፡ ሁሉንም ስሞቿን የኢትዮጵያ ቄሶች ሁሉ እየተጋገዙ ይጥሩት !!

የእርሷ ሳቅ ሳቄን ገድሎታል፡፡ የእርሷ የፌዝ ዕይታ ሩቅ እንዳላይ አንገቴን አስደፍቶኛል:: የልብ ሽፋሽፍት የሚል ግጥም ፅፋ ለፀረ ምንትስ ከበብ ዓመታዊ ዝግጅት ሰልፍ ሜዳ ላይ አንብባ 843 ተማሪ ሲባዛ 32 ጥርስ = 26 976 ጥርስ ይርገፍና !! ቆይ የአስተማሪዎቹን ረስቼው ነበር፡፡ ሲደመር 23 ሲባዛ 32 = 736 ሲቀነስ 32 (ቲቸር አንድም ጊዜ አልሳቁም)፡፡

የፍቅር አፒታይቴን” ምድረ ጥርሳም በሳቃቸው ቆልፈውት አስራ ሁለተኛ ክፍል ጨርሼ ዩኒቨርስቲ እስከምገባ ድረስ ሴት የምትባል ፍጥረት አጠገብ ድርሽ ብዬ አላውቅም፡፡ እና ምን ተባልኩ ?ጨዋ !! እንኳንም ያልቀረብኩ !! ምናቸው ይቀራል? ያች አይጠ መጎጥ፣ አስቀያሚ፣ ጥርሳም፣ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ስማም ! ዛሬ የራሷ አንድ ስም እንኳን ጠፍቶ ማንም አንቺ
የሚላት የካፍቴሪያ አስተናጋጅ ሆናለች፡፡ ሻይ አዞ ስሙኒ ጉርሻ ለተወላት ሰብለ፤ ቡና ጠጥቶ ለገለፈጠላት ናኒ እየሆነች እስስቷ የስሟን ቀለም እየቀያየረች አለች፡፡ ብር ዛፍ ቁርስ ቤት ሳልፍ ሳገድም ከነቀይ ሽርጧ አያታለሁ

ዩኒቨርስቲ የተመደብኩት እዚሁ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነበር፡፡ ደስ አላለኝም፡፡ ምክንያቱም ከአዲስ አበባ ውጭ ከወላጅ ራቅ ብዬ የመኖር የቆየ ፍላጎቴ ተሰናክሏልና፡፡ አስከፊው ነገር
ደግሞ ዩኒቨርስቲው “የአዲስ አበባ ልጆች እየተመላለሳችሁ ተማሩ በቂ መኝታ የለኝም አለ ይሄ ደግሞ ዩኒቨርስቲና ሃይ ስኩል የሚለያዩበትን አንድ ድንበር አፈራረሰው፡፡ ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የገባሁ አልመስልህ አለኝ፡፡ ወደ አስራ ሶስተኛ ክፍል ያለፍኩና እዛው የነበርኩበት ትምህርት ቤት የቀጠልኩ አይነት ስሜት ነበር የተሰማኝ፡፡ ያ ሁሉ የተወራለት፣ በፊልም እና በሰመመን መጽሐፍ ብዙ የተባለለት የዩኒቨርስቲ ሕይወት፣ ላየው የጓጓሁለት “የግቢ ላይፍ ውሃ በላው !! ወይ ነዶ! አንድ አራት ወር እየተመላለስኩ እንደተማርኩ እዛው ዩኒቨርስቲው አካባቢ ቤት ተከራይቼ ለመማር ወሰንኩ፡፡ ምንም አስቤ ሳይሆን የአዲስ አበባ ታክሲ ጊዜዬን እየበላብኝ ስለተቸገርኩ ነበር፡፡ ማንም አልተከራከረኝም፤ ዩኒቨርስቲው ከሚወረውርልኝ ሳንቲም ላይ ቤተሰብ በየወሩ ድጎማ እየመረቀበት ቤት ተከራየሁ፡፡ድከም ያለች ቤት አንድ ሰፈር ውስጥ፡፡ እንግዲህ የእኔ
ቤትና ከጎኔ ያሉት ጭርንቁስ ቤቶች በመደዳ የተሰለፉ ነበሩ ፊት ለፊት ደግሞ ፊታቸውን
ወደ እኔ ቤት ያዞሩ ስስሪትም፣ በመጠንም ከእኔ ቤት ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ሌላ መደዳ ቤቶች አሉ፡፡ መስኮቴን ስከፍት ፊት ለፊት ያለው ቤት መስኮት ጋር እፋጠጣለሁ፡፡ በሬን ስከፍት ፊት
ለፊት ካለ በር ጋር ! በሁለቱ መደዳ ቤቶች መካከል ቀጭን የእግር መንገድ አለች፡፡ የእኔ ቤትና ፊት ለፊቴ ያለው ቤት ጣራቸው ሊገጣጠም ምንም ያህል ስለማይቀረው በመካከላችን በቀጭኗ የእግር መንገድ የሚያልፍ ሰው ረዥም ኮሪደር ውስጥ የሚያልፍ ሊመስለው ይችላል፡፡ ከበሬ ላይ አንድ ጠቀም ያለ ርምጃ ወደፊት ብራመድ ፊት ለፊት ያለው ቤት በር ላይ አርፋለሁ፡፡ ይሄ ነው የተከራየሁት ቤት::

ሜሮንን ትሻግሮ ሜሮን አለች ወይ…

በአንድ ርምጃ ርቀት ጣራዬ፣ ከጣራው የሚነካካው ቤት ውስጥ ፊት ለፊቴ 'ሜሮን' የምትባል
ልጅ መኖሯን ያወቅኩት ቤቱን በተከራየሁ በሁለተኛው ቀን ነበር፡፡ በጊዜና ቦታ ርቀት ትቼ የመጣሁት “ሜሮን” የሚባል እንደ ጥላ የሚከተል ስም እዚህም መጣ፡፡ ሜሮን ሜሪ ሜሪቾ ሜሪዬ…ይላታል የመንደሩ ሰው፡፡ ጥቁር ትሁን ቀይ አይቻት አላውቅም ነበር፡፡ ለሰባት ወራት
ያህል ጧት እየወጣሁ፣ ማታ እየገባሁ በሰላም ኖርኩ፡፡

በአንድ ጠራራ የግንቦት ቀን ከክላስ ወደ ቤቴ እየገባሁ ነበር፡፡ የፀሐዩ ቃጠሎ ከንፈሬን ሁሉ
አድርቆታል፤ ሰውነቴ ሁሉ የተነነ ነው የመሰለኝ፡፡ ድርቅ የመታኝ !! ቀዝቃዛ ውሃ ለመግዛት ጫፍ ላይ ወዳለች ኪዮስክ ሄድኩና “ቀዝቃዛ ውሃ ስጭኝ እስቲ” ብዬ አስር ብር ባለሰሃኑ
ሚዛን ላይ ጣል አደረግኩላት፡፡ አስር ብሩ ሚዛኑ ላይ ሲያርፍ ሚዛኑን ዝቅ አላደረገው ከፍ…

“ቀዝቃዛ የለም !” አለች እስር ብሩን በእጇ ይዛ፣
"እሽ ቀዝቃዛ ኮካ”
“ቀዝቃዛ ኮካም የለም ከውጭ ልስጥህ ?” አለች፣
ቀዝቃዛ ነገር ምንድን ነው ያለሽ ?”
“ፍሪጅ የለኝም ከውጭ ነው ሁሉም !”
“ተይው በቃ !” ብዬ ብሬን ልቀበል እጄን ዘረጋሁ፡፡ ቅር እያላት ብሬን መለሰችልኝ፡፡ ፊቴን ኮሰኮስኩ በጣም ነበር የተበሳጨሁት፡፡ ኤጭ!!
👍33
ቤቴ ገብቼ ቱታ ቀየርኩና ፍራሹ ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ በእፎይታ ተነፈስኩ፡፡ ወዲያው በር
ሲንኳኳ በግርምት ወደበሩ ተመለከትኩ፡፡ ጆሮዬን አቁሜ ብጠብቅም ምንም ድመፅ አልነበረም መልሼ ጋደም ልል ስል በድጋሜ ተንኳኳ፤ በቀስታ ! ላለፉት ሰባት ወራት አንድም ጊዜ በሬ ተንኳኩቶ ስለማያውቅ ተገረምኩ፡፡ “ማነው?” አላልኩም፡፡ በቀጥታ ሄጄ ከፈትኩት፡፡ አንዲት
ስለሚታይ ቅዝቃዜው ያስጎመዣል፡፡ ምራቄን ዋጥኩ እና ልጅቱን አየኋት፡፡ እሷም ታስጎመዥለች፣ሬራ
እሷን እንደመድኃኒት ውጦ በያዘችው ውሃ ማወራረድ ነበር!

እየፈራች “ሱቅ ውሃ ጠይቀህ ስላጣህ ከቤት አምጥቼልህ ነው"አለችኝና ውሃውን ዘረጋችልኝ፡፡
ሳላንገራግር ተቀበልኳት፡፡ 'ቴንኪው የለ ! ምን የለ !

ቆንጆ ነች !በጣም ቆንጆ ነች !በተለይ ዓይኗ፣ በተለይ ጥቁር የሚያብረቀርቅ ፀጉሯ ከቁጥርጥሩ ገና የተፈታ እንደሆነ ያስታውቃል፡፡ በተለይ ደግሞ ጡቷ ! የለበሰችውን ስስ ቦዲ ስሸካክቶ ሊተኮስ የተሰናዳ የሆነ ተተኳሽ ነገር !! በተለይ ደግሞ ሁሉም ነገሯ፡፡

የተጋለጠ ደረቷ ማር የተንጣለለበት ሜዳ ይመስላል፡፡ ቆንጆ ነበረች፣ ግን ልጅ ነበረች፤ ቢበዛ አስራ ስድስት ቢሆናት ነው፡፡ ዞር ስትል መቀመጫዋንም አይቻለሁ...(ለምን ይደበቃል?)፡፡
ለአስራ ስድስት ዓመት ልጅ ይበዛል፤ ግን ቆንጆ ቆንጆ እና ልጅ፣ ቆንጆ ልጅ !! እንትፍ ትፍ
ትፍ እደጊ ! መቼም አዲሳባ ቆንጆ እያጣመመ ነው የሚያሳድገው !! ለማንኛውም እደጊ !!

ከእኔ በር ወደ ራሷ ቤት ስትሄድ እኔም ውብ ሰውነቷን ቆሜ ስገመግም አንድ መንገደኛ
ሜሪ !” አላት፤ እርፍ !! ሜሮን ናት ለካ !! በፍቅር ውሃ ጥም ለዓመታት ያደረቀችኝ ሜሮን የምትባል ደረቅ ወንዝ ተሻግሬ በቀዝቃዛ ውሃ ጥሜን የምታስታግስ ሜሮን የምትባል ጅረት ላይ ደረስኩ፡፡

ሜሮንን ተሻግሮ ሜሮን እለች ወይ
ሞትና ውሃ ጥም አንድ አይደለም ወይ፡፡

እየጠጣህ አብርሽ ! ብዬ ራሴን ጋበዝኩት፡፡ ቀዝቃዛውን ላንደቀድቀው ነበር፤ ግን ገና አንዴ
ስጎነጭለት ጥርሶቼ ሁሉ ጠፉኝ፤ ቦታቸው ላይ ደነዘዙ፤ ምን እዳ ነው ! ልብም ጥርስም ደንዝዞ
የት ይደረሳል !? ጥርስ የሌለው ልበ ቢስ አንበሳ የሆንኩ መሰለኝ፣ ቢሆንም አንድ የተለኮስ
ነገር ነበር፡፡

ፍሪጅ እና ቦኖ ውሃ በምን ይለያያል !?

ሜሮን ትላንት ያመጣችልኝን ጆግ ልትወስድ ስትመጣ ፈገግ ብዬ ተቀበልኳት፡፡ ባዶዋን አልነበረችም፡፡ ሌላ ጆግ ሙሉ ቀዝቃዛ ውሃ ሰጥታኝ ባዶ ጆግ ወሰደች፡፡ .…ጆግ ውሃ .ጆግ
ውሃ ፤ ከብዙ የጆግና ውሃ ምልልስ በኋላ ተቀራረብን፡፡
“የት ነው የምትማሪው ?
“ሚኒሊክ…” ጆግ ውሃ …ጆግ ውሃ…

"አሳይመንት ተሰጥቶኝ ነበር ጊዜ ካለህ ትሰራልኛለህ ?”

አምጭው ኧረ !” ብጥርጥር አድርጌ ሰራሁላት፣ አስረዳኋት፤…አንዴዴዴዴ! እንዲህ አይነት
አደገኛ አስተማሪ ነበርኩ እንዴ ለካ !

ጆግ.ውሃ ጆግ..ዉሃ እና አንድ ቀን ለስላሳ ቀዝቅዝ ያለ ሚሪንዳ !!

“የምን ለስላሳ ነው ሜሮን ?”

“ታዘብኩህ ዛሬ ልደቴ ነበር፣ 16 አመቴ፤ ሃፒ በርዝደይ! ሳትለኝ” ፈገግ ብላ፡፡

“በቃ ቅዳሜ ራሴ አከብርልሻለሁ”

“ፕሮሚስ ?!” ብላ የሚያምር መዳፏን በጉጉት ዘረጋችልኝ፤ ፊቷ በፈገግታ ተጥለቅልቆ ነበር፡፡

“ፕሮሚስ !” ብዬ መዳፌን መዳፏ ላይ አስቀመጥኩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ መነካካታችን ነበር !!
እጄን አልሰበሰሰችም፤ እኔም እጄን አላነሳሁም፡፡ እግዜር መሃላውን እስካፀድቀው እጃችሁን
እንዳለ ሳይለያይ አቆዩት!” ያለን ነበር የምንመስለው፡፡ ዓይኗ ውስጥ ፀሐይ አየሁ፤ ሁለት ፀሐይ!አማረችኝ፡፡ የሆነ የሚያምር መናፈሻ መሰለችኝ፡፡ ውስጧ እረፍት የተዘራ፡፡ ሲደከም ለኖረ
አንድ እኔ ሰፊ አልጋና እረፍት ያለባት አገር፡፡

ጆግ ውሃ ጆግ ውሃ ቅዳሜ ሆነ !!

ከማክሰኞ እለከ አርብ ያላሰብኩትን ቅዳሜ ጧት ተጨነቅኩ፡፡ የእስራ ስድስት ዓመት ልጅ ይዤ የት አባቴ ነው የምጋብዛት ? ..ቤተሰቦቿስ ምን ይላሉ? (ለነገሩ ሴት አያቷ እና እሷ ብቻ ናቸው የሚኖሩት) .. ቢሆንም ጎረቤቱስ ምን ይላል?…ወይ ጉድ !

ሜሮን በጧት መጣች፤ ተኝታም ያደረች አልመሰለኝም፡፡

“አንተ እስካሁን ተኝተሃል !?” አለችኝና የተኛሁበት ፍራሹ ጫፍ ላይ ተቀመጠች፡፡ ቤቴ መግባት
ፍራሽም ላይ መቀመጥ ጀምራለች፡፡ ጧት ስትመጣ ደስ አይለኝም፤ ስስ ፒጃማ ቁምጣና
ባለማንገቻ ጉርድ ቦዲ ስለምትለብስ እፈተናለሁ፡፡ በዛ ላይ በጣም ተጠጋግተን ስለምንቀመጥ ጠረኗ አፍንጫዬን ይዞ ወደ ጡቶቿ መሃል ይጎትተኛል፡፡ ፈተና ነው በቃ !…እርሷ ደግሞ በፍፁም "ንጹህ ልብ እንደፈለገች ትሆናለች፡፡

በቃሌ መሰረት ልደቷን ልናከብር ተቀጣጠርን፡፡ ከሰፈር አብረን መውጣቱ ለጎረቤት ሃሜት
ስለሚዳርግ የሆነ እሷ የመረጠችው ሬስቶራንት ስምንት ሰዓት ላይ እንገናኝ ተባባልን፡፡....


ነገ ያልቃል
👍312
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


...ጫጫታ ከሩቅ ተሰማ:: ዣን ቫልዣ አንዱን ቤት ተጠግቶ ለመደበቅ ፈለገ፡፡ ከሩቅ የሚንቀሳቀስ ጥላ ተመለከተ:: ሰዎች ወደ እርሱ ማምራታቸውን
ተገነዘበ፡፡ ተንጠላጥሎ ድምፅ ወደሚሰማበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ የዣቬርን ግዙፍ ሰውነት መለየት አላዳገተውም፡፡ በፖሊስ ጥንቃቄ ግራና ቀኝ እያዩ
መራመዳቸውን ተመለከተ፡፡ ቆም እያሉ፣ አካባቢውን እየሰለሉ ነው
የሚሄዱት፡፡ የመደበቂያ ሥፍራ እንዳለ ኣጥርተው እንደሚፈትሹ
ያስታውቃል፡፡ ሰፈሩ ማምለጫ መንገድ የለውም::

በዚያ አካሄዳቸው ሥፍራውን እየፈተሹ ሲመጡ ዣን ቫልዣ
ከነበረበት ለመድረስ ምናልባት ሩብ ሰዓት ቢወስድባቸው ነው:: እጅግ በጣም የሚያስጨንቅ ሰዓት ነበር፡፡ በሕይወቱ ዘመን ለሦስተኛ ጊዜ ከአስፈሪ
ሕይወት ጫፍ ላይ የደረሰ መሰለው፡፡ አሁን ያስጨነቀው የእስር ቤት ኑሮ ብቻ ሳይሆን የኮዜት ከእርሱ መለየት ጭምር ነበር፡፡ ሁለት አማራጭ ነበረው፤ የመለኮት ኃይል አውጣኝ ብሎ መማጠን ወይም ባለው ጉልበት
ተጠቅሞ ሰዎቹን መጋፈጥ፡፡
እስር ቤት ባገኘው ልምድ ዣን ቫልዣ ቀጥ ካለ ግንብ፧ ቁመቱ እንደ ፈለገው ቢረዝም እንኳን፤ በቀላሉ የመውጣት ችሎታ አለው:: ከፊት ለፊቱ የነበረውን ግንብ ርዝማኔ በዓይኑ መተረው:: ወደ አምስት ሜትር ገደማ ይሆናል፡፡ በተጠረበ ድንጋይ የተሠራ ግንብ ነበር፡፡
አሁን የምታስቸግረው ኮዜት ስትሆን ኮዜት ከግንብ ላይ መውጣት አታውቅበትም:: ታዲያ ይተዋት? አሳቡ አንገሸገሸው:: እርስዋን ተሸክሞ መውጣት ደግሞ የማይቻል ነው፡፡

መፍትሔው ትልቅ ገመድ እንደሆነ ተገነዘበ፡፡ ግን ዣን ቫልዣ
ገመድ አልነበረውም:: ታዲያ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ገመድ ከየት ሊያመጣ ይችላል? በዚያች ሰዓት ዣን ቫልዣ አገረ ገዢ ቢሆን ግዛቱን በአንድ ወፍራምና ረጅም ገመድ ይለውጥ ነበር፡፡

የሚደንቀው አንዳንድ ጊዜ በጭንቀት ሰዓት የሚያስገርም ወይም ዐለማመን የሚያስቸግር ነገር ይሆናል:: ቫንቫልዣ ግራና ቀኙን ሲቃኝ መብራት የተንጠለጠለበት ገመድ አየ:: በዚያን ብርሃን ባልነበረበት ዘመን በጋዝ የሚሠሩ መብራቶች ከፍ አድርገውና የሚሰቅሉትና የሚያወርዱት በወፍራምና በረጅም ገመድ ነበር፡፡

ዣን ቫልዣ ገመዱ ወደ ተንጠለጠለበት ሮጦ በያዘው ቢላዋ ቆረጠው።ቀደም ሲል እንደተገለጸው በተለይ ያን ምሽት ጨረቃዋ ሙለ ስለነበረች
የመንገድ መብራቶች አልተለኩሰም:: ስለዚህ ዣን ቫልዣ ገመዱን ሲቆርጥ ምናልባት መብራቱ ቢሰበር ልብ የሚለው አልነበረም:: ኣካባቢውም ጭር
ያለ ነበር፡፡ዣን ቫልዣ ከወዲህ ወዲያ ሲሮጥ፤ ዓይኑ ሲቅበዘበዝ አሳብ ሲያስጨንቀው በማየትዋ ኮዜት ደነገጠች:: እርስዋ በመሆንዋ እንጂ ሌላ
ልጅ ብትሆንማ ልቅሶዋን ነበር የምትለቅቀው፡፡ የኮቱን ጭራ አጥብቃ ይዛ ዝም ብላ ነበር የምትከተለው፡፡ በአካባቢው የሚሰማው ድምፅ እየጎላ መጣ።

«አባባ» አለች ኮዜት በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ፤ «ፈራሁ፤ ማነው
የመጣው?

«ዝም በይ፤ ዝም በይ» አለ የተከፋው ሰው፤ «ሚስስ ቴናድዬ
ናት፡፡»

የኮዜት ሰውነት በፍርሃት ተንቀጠቀጠ! ሰውዬው ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አይዞሽ እኔ አለሁልሽ፤ ግን ዝም ነው፤ ካለቀስሽ ወይም ድምፅ ካለማሽ ሚስስ ቴናድዬ ትሰማሻለች፡፡ አንቺን ፍለጋ ነው የመጣችው::»

ዣቬርና ሌሎች ፖሊሶች እነርሱ ከነበሩበት ደርሰው ሊይዟቸው
ስለሚችሉ ጊዜ ማባከኑ ይበልጥ የሚያጋልጥ መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ከረባቱን አውልቆ በከረባቱ የኮዜትን ወገብ አሰረ:: ጫማውንና ካልሲውን አውልቆ ከግንቡ ላይ ወረወረ፡፡ የገመዱን አንዱን ጫፍ ከቋጠረ በኋላ ከኮዜት ወገብ
ላይ ከታሠረው ከረባት ጋር አሰረው:: ከዚያ በኋላ የገመዱን አንድ ጫፍ በእጁ ይዞ ከግንቡ ላይ መውጣት ጀመረ:: ኮዜት ከመሬት ሆና ዝም ብላ ታየዋለች:: የሚስስ ቴናድዬ ስም በመጠቀሱ በጣም ስለደነገጠች ለመናገር
ብትፈልግ እንኳን መናገር አትችልም::

ብዙ አልቆየም ወዲያው እጅግ ዝቅ ባለ ድምፅ ዣን ቫልዣ ሲጠራት ሰማች::

«ጀርባሽን ለግድግዳ ስጪ፡፡»

እንዳዘዛት አደረገች::

«እንዳትናገሪ፧ እንዳትፈሪ» አለ ዣን ቫልዣ ቀጠለና፡፡

ከግንቡ ጫፍ ደረሰች:: ወዲያው ዣን ቫልዣ እቅፍ አደረገና በጀርባው መሬት ለቅቃ ስትንጠለጠል ታወቃት፡፡ የት እንዳለች ሳታውቅ አዘላት:: እጆችዋን በግራ እጁ ያዘ፡፡ እንደገመተው ከግንቡ ኋላ ቤቶች
ነበሩ። በውስጥ በኩል የግንቡ ርቀት እስከዚህም ሩቅ አልነበረም:: ርቀቱን በዓይኑ መተረው፡፡

ልጅትዋን እንዳዘለ በቀላሉ ከአንድ ቤት ጣራ ላይ ለማረፍ ቻለ::

ከላይ ሆኖ ከአጥሩ ውጭ የዣቬርን ድምፅ ሰማ፡፡

«በየመንገዱ ፣ በየሥርቻው ቶሎ ብላችሁ ፈልጉት፡፡ በየቤቱ
እየገባችሁ ፈልጉ፡፡ ስለሚደርሰው ነገር እኔ አልፋለሁ» አለ ዣቬር እየጮኸ

ዣን ቫልዣ ከጣራው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ኮዜትን በገመዱ አንጠልጥሉ የዛፍ ግንድ ይዛ በመውረድ መሬት እስክትደርስ ጠበቃት፡፡ ኮዜት ጎብዛም
ይሁን ፈርታ ቃል አልተነፈሰችም:: እጅዋን ሲጨብጣት ግን በጣም አልቦአት ነበር፡፡

ዣን ቫልዣ ከጣራ ወርዶ ሲጓዝ ከአንድ የአትክልት ቦታ ደረሰ
አካባቢው በጣም ጭር ያለ ነበር፡፡ በመጀመሪያ ጫማውንና ካልሲው
መፈለግ ነበረበት፡፡ ጫማውን ፈልጎ ካጠለቀ በኋላ ከኮዜት ጋር ከዛፍ ስር ተቀመጡ፡፡ ምንጊዜም ቢሆን የሚሸሽ ሰው ያመለጠ ስለማይመስለው ሁልጊዜም እንደ ደነገጠ ነው፡፡ ኮዜት ስለፈራች ከጎኑ ተሸጉጠች:: እነዣቬር ከሁንም ሲጠራሩ አሁንም ይሰማል፡፡ ግን ከሩብ ሰዓት በኋላ ድምፁ እየደከመ ሄደ
ቢሆንም የዣን ቫልዣ ልብ አሁንም አልረጋም፡፡ ኮዜትም ዝምታዋን ቀጠለች ከዚህ መጣ የማይባል ድምዕ በድንገት ተሰማ:: የደናግል ዝማሪ ነበር፡፡ ደናግል ተሰባስበው የሚዘምሩት አትክልት ውስጥ ነበር፡፡ ድምጻቸው ጥርት ብሎ ነው የሚሰማው:: ዣን ቫልዣ ይህን ድምፅ ሲሰማ የድምፁ።
አቅጣጫ ፍለጋ ዞር አለ፡፡

ፊቱን ሲያዞር ከአትክልቱ ውስጥ ሰው መኖሩን አየ:: አንድ ሰው
ጎንበስ ቀና ይላል፡፡ ሰውዬው ሥራ ይዞ መሆን አለበት፧ እቃ ከአንድ
ሥፍራ አንስቶ ወደ ሌላ ቦታ እንደሚወስድ ሰው ጎንበስ ይልና ቀና ብሎ ጥቂት ይራመዳል፡፡ ተመልሶ መጥቶ ጎንበስ ይልና ቀና ብሉ ይሄዳል።

ዣን ቫልዣ ደነገጠ፡፡ ምናልባት ዣቬርና ተከታዮቹ እዚህም ጠባቂ
ያስቀመጡ መሰለው:: ይህ ሰው የእነርሱ አባል ከሆነ «ሌባ፤ ሌባ» እያለ ቢያሲዘኝስ ሲል አሰበ፡፡ የተኛችውን ኮዜት ቀስ ብሎ አንስቶ ግቢው ውስጥ ከነበረው አሮጌ አግዳሚ መቀመጫ ላይ አሳረፋት:: ኮዜት አልነቃችም፡፡
ከኮዜት አጠገብ ተቀምጦ የሰውዬውን እንቅስቃሴ ተከታተለ፡
የቃጭል ድምፅ ይሰማል፡፡ ሰውዬው አንድ ነገር ለማንሳት ጎንበስ ሲል ቃጭሉ ሲቃጨል እኩል ስለመጣ ዣን ቫልዣ ይህ አጋጣሚ ይቀጥል!እንደሆነ ጠበቀ፡፡ አሁንም እኩል መጣ፤ ጨርሶ አልተዛባም:: ሰውዬው
ሲንቀሳቀስ ቃሉ ድምፅ ያሰማል፡፡ ሲቆም ዝም ይላል፡፡ የሚደንቀው!
ደግሞ ሰውዬው ሥራውን ጨርሶ ሲያርፍ ደወሉም ፀጥ ይላል፡፡ የደወሉ ገመድ ከሰውዬው ወገብ ላይ ታስሮ ይሆን?» ሲል አሰበ፡፡
ይህን እያሰላሰለ የኮዜትን እጅ አሻሽ፡፡ እንደበረዶ ቀዝቅዟል፡፡
👍19🔥2🥰1
“ምን ይሻላል?» ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
«ኮዜት» ሲል በለሰለሰ ድምዕ ጠራት::
ዓይንዋን አልገለጠችም፡፡ ቀስ ብሎ ወገብዋን ይዞ ነቅነቅ አደረጋት፡፡
«እንዴ፤ ይህቺ ልጅ ሕይወትዋ ከሥጋዋ ተለየ እንዴ?» ሲል
በድንጋጤ ከተቀመጠበት ብድግ አለ::
አልጋ ላይ እንደተኛ ሰው እግርዋን ዘርራ ነው የተኛችው:: ትንፋሽዋን
አዳመጠ፤ ትተነፍሳለች፡፡ ሕይወቱ መለስ አለች፡፡ ብርዱ ሊጎዳት እንደሚችል ያውቃል፡፡ «ምን ላልብሳት? በምን ላማሙቃት? በብርድ ልትሞት ነው»
ሲል አሰላሰለ፡፡ ከነበረበት ጥቂት ተራምዶ ከሥፍራው ፈቀቅ አለ:: የብርድ ልብስ ያገኝ ይመስል ዓይኑ ተቅበዘበዘ፡፡ በቶሎ ኮዜት ከቤት ውስጥ ገብታ ቢቻል እሳት መሞቅ እንዳለባት አስተዋለ፡፡
በቀጥታ ሲንቀሳቀስ ወዳየው ሰውዬ ሄደ፡፡ ከሰደርያው ኪስ ውስጥ ጠቅልሎ ያስቀመጠውን ገንዘብ አወጣ፡፡ ሰውዬው አጎንብሶ ይሠራ ስለነበር ወደ እርሱ የሚመጣውን ዣን ቫልዣን አላየውም:: ዣን ቫልዣ ሰውዬው
ከነበረበት ደረሰ፡፡
ዣን ቫልዣ ጠጋ ብሉ «መቶ ፍራንክ› ሲል ተናገረ:: ሰውዬው
ደንግጦ ቀና አለ፡፡
«ካሳደርከኝ መቶ ፍራንክ እከፍላለሁ» አለ ዣን ቫልዣ፡፡
ከዣን ቫልዣ ፊት ላይ የጨረቃ ብርሃን አርፎ ነበር፡፡
«እንዴ፤ አባታችን ማንደላይን፤ ከእዚህ ምን ትሠራለህ?» ሲል
ሰውዬው ጠየቀው፡፡
በዚያ ጨለማ፤ በዚህ ባልታወቀ ቦታ፤ በዚህ በማይታወቅ ሰው ይህ
ስም ሲጠራ በመስማቱ ዣን ቫልዣ ወደኋላ ሸሽት አለ፡፡
ሰውዬው ያጠለቀውን ቆብ ብድግ አደርጎ እጅ ነሳው።
“ቁጭ በል! ቁጭ በል! ቤት ለእንግዳ:: ግን አባታችን እዚህ እንዴት መጣህ? እንዴ፤ ደግሞ ከዚህ ግቢ ውስጥ እንዴት ልትገባ ቻልክ? ከሰማይ ነው የወረድከው ወይስ ከምድር ነው የፈለቅከው?» ሲል በጥያቄ አጣደፈው::
ማን ነዎት እርስዎ? ቤቱስ የማነው? » ሲል ዣን ቫልዣ ሰውዬውን ጠየቃቸው::

«በጣም ነው ደስ ያለኝ» አሉ ሽማግሌው:: «አንተ እኮ ነህ ከዚህ ያስገባኸኝ:: ይህን ቤት ደግሞ አንተ ነህ ያሰጠኸኝ፡፡ እንዴ! እንዴት ይሆናል፧
አታስታውሰኝም?»
«ይቅርታ፧ አላስታወስኩም ኣላ ዣን ቫልዣ :: «የት ነው !
የምንተዋወቀው?»
«ሕይወቴን እኮ አድነሃታል» አለ ሰውዬው::
ዣን ቫልዣ አሁን ትዝ አለው፡፡ የሽማግሌውን ፊት አስተዋለ::
እኚያ የጭነት ጋሪ ተጭኖዋቸው ሊሞቱ ሲሉ ከጋሪው እግር ፈልቅቆ
ያወጣቸው ሰው መሆናቸውን አወቀ፡፡
«ለካ እርስዎ ነዎት!» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «አሁን አስታወስኩ ሚስተር ፎሽለማ ነዎት፤ አይደለም?»
«ጥሩ አጋጣሚ ነው» አሉ ሽማግሌው::
«እርስዎስ ከዚህ ምን ይሠራሉ?» ሲል ዣን ቫልዣ ጠየቀ፡፡
«ከዚህ ሥራ እየሠራሁ ነው፤ አንተስ ምን ትሠራለህ?» አሉ ቀጠሉና።
ዣን ቫልዣ በቀድሞ ስሙ እየጠራ የሚያናግረውና የሚያውቀው
ሰው በማግኘቱ ጥቂት ተዝናና፡፡ የእንግዳ ዓይን አውጣ እንደ መጠየቅ እርሱ ጥያቄ ያበዛል፡፡
«ጉልበትዎ ላይ ያሰሩት ደወል ምንድነው?»
«እሱማ» አሉ ሽማግሌው፧ «መምጣቴን አውቀው ከእኔ እንዲሸሹ ድምፅ የማሰማበት መሣሪያ ነው፡፡»
«ከእኔ እንዲሸሹ?»
አዎንታቸውን ለመግለጽ ሽማግሌው ግንባራቸውን ወደ ላይ ሳብ አደረጉ፡፡
«ከዚህ ግቢ ውስጥ ያለው ከእኔ በስተቀር ሁሉም ሴት ነው:: ወጣት
ልጃገረዶች በብዛት አሉ፡፡ ከእኔ ጋር መገናኘቱ አደገኛ ነው መሰለኝ፤ ደወለ ለመምጣቴ ማስጠንቀቂያ ነው:: እኔ ስደርስ ይሸሽጋሉ፡፡»
«ቤቱ የኔ ነው?»
«ምነው፧ ታውቀው የለም እንዴ?»
«የለም፤ አላውቀውም፡፡»
«ምነው፧ አንተ አይደለህም እንዴ በአትክልተኝነት ተቀጥሬ እንድሠራ
ያደረግኸው:: »
«ለምጠይቀው ጥያቄ ምንም አያውቅም ብለው በመገመት መልስ ይስጡኝ።»
«አንተ ካልክ እሺ፡፡ ይህ ገዳም እኮ በዚያን ጊዜ የፐቲ ፔክፐስ ገዳም ነበር የሚባለው፡፡»

ዣን ቫልዣ አስታወሰ፡፡ በአጋጣሚ ከሚያውቀው ገዳም መግባቱን
ተገነዘበ፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት ሽማግሌው የእቃ መጫኛ ጋሪ ወድቆባቸው እያለ የአካል ጉዳት ስለደረሰባቸው በአትክልተኝነት ገዳሙ እንዲቀጥራቸው
የድጋፍ ደብዳቤ ጽፎላቸው ነበር፡፡ የድጋፉ ደብዳቤ ነው እንዲቀጠሩ
የረዳቸው፡፡

«የፐቲ ፔክፐስ ገዳም» አለ ዣን ቫልዣ እርስ በራሱ ይነጋገር
ይመስል፡፡
«እንዴት ኣድርገህ ከዚህ ልትገባ እንደቻልክ ንገረኝ እንጂ ፤ ሰው
ስለሆንክ መልአክ ለመሆን አትችልም፡፡ በምንም መንገድ ደግሞ ወንድ ከዚህ ገዳም እንዲገባ አይፈቀድም፡፡»
«ይኸው እርስዎ ከዚህ ይኖሩ የለ!»
«ያለ እኔ እኮ ሌላ ወንድ የለም::»
«ግን» ኣለ ዣን ቫልዣ ከዚህ መኖር አለብኝ፡፡»
«ያንተ አለህ!» ሲሉ ሚስተር ፎሽለማ በመደነቅ ዓይነት ተናገሩ፡፡
ዣን ቫልዣ ወደ ሽማግሌው ጠጋ ብሉ ዝቅ ባለ ድምፅ «ምነው
ሕይወትዎን ማዳኔን ረሱት?» አላቸው::
«መዘንጋት አልነበረብኝም» አሉ ሚስተር ፎሽለማ፡፡
«እንግዲያውማ እኔ ለእርስዎ ያደረግሁትን ዛሬ እርስዎ ለእኔ ማድረግ ይኖርብዎታል፡፡›
ፎሽለማ በተጨማደደ እጃቸው የሚንቀጠቀጠውን የዣን ቫልዣን
እጅ ያዙ፡፡ ለጥቂት ሰኮንድ እጁን እንደያዘ ዝም ብለው ቆሙ:: በመጨረሻ፡-
«እኔ ለአንተ አንድ ነገር ማድረግ ከቻልኩ እግዚአብሔር ባረከኝ፣
ቀደሰኝ ማለት ነው:: የአንተ ውለታ እኮ ተከፍሎ የሚያልቅ አይደለም::
ሕይወትህን አድንልሃለሁ! ክቡር ከንቲባ ፤ ሽማግሌው በአንተ ቁጥጥር ሥር ነው:: ››

ሽማግሌወ ይህን ሲናገሩ በጣም ደስ እያላቸው ነበር:: ለዚህ
በመብቃታቸው መንፈሳቸው ረካ፡፡ ለመደሰታቸው ፊታቸው መሰከረ።
ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?» አሉ ቀጥለው::
«ግድ የለም አስረዳዎታለሁ፡፡ አንድ ክፍል አለዎት?
«ከዚያ ጥግ አንዲት የማትረባ ክፍል አለች፡፡ ግን ሰው የሚኖርባትም አትመስል፡፡ እኔ ያለሁበት ቤት ባለ ሦስት ክፍል ነው::

እውነትም የሰውዬው ቤት የማይረባ ዝቅተኛ ቤት ነበር፡
አቀማመጡም ሆን ብሎ ሰው ለመደበቂያ የተሠራ ይመስል ከአሳቻ ሥፍራ ነበር፡፡ ዣን ቫልዣ ከግቢው ውስጥ ሲገባ ያልታየው በዚህ ምክንያት ሊሆን ይችላል።

«ጥሩ ነው» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «አሁን ሁለት ነገር ነው የምጠይቅዎት
«ምንና ምን ናቸው ክቡር ከንቲባ፡፡ ብቻ እርስዎ' እያልክ ባትጠራኝ
«እሺ! አንደኛ፤ አሁን ስለራሴ የምነግርህን ለማንም እንዳታወራ፧
ሁለተኛ እኔ ከምነግርህ ውጭ ስለእኔ ለማወቅ እንዳትሞክር፡፡»

«አንተን ደስ እንዳለህ፡፡ አሳፋሪ ነገር የማትሠራና የእግዚአብሔር ሰው እንደሆንክ አውቃለሁ:: ከዚህም በላይ ከዚህ እንድትገባ የረዳኸኝ አንተ ስለሆንክ ቤትህ ነው:: እኔም ያንተ ነኝ፡፡».

«በጣም ጥሩ፧ ና አሁን ተከተለኝ፤ ልጅትዋን እናምጣት::»
«እንዴ» አሉ ፎሽለማ በመገረም:: «ልጅም አለች!»
ውሻ ጌታዋን ተከትላ እንደምትሄድ፤ ሰውዬው ሌላ ቃል ሳይናገሩ ዣን ቫልዣን ተከትለው ወጡ።

ከግማሽ ሰዓት በኋላ እሳት ተቀጣጥሎ ኮዜት እሳት ትሞቅ ጀመር።
ሽማግሌው ኮዜትን አልጋ ላይ አስተኝዋት:: ዣን ቫልዣ ወደ ግቢ
ወርውሮአቸው የነበሩትን እቃዎቹን አግኝቶ ተመለሰ፡፡ ሽማግሌው
ከጉልበታቸው ላይ ያሠሩትን ቃጭል ፈትተው አስቀመጡ:: ሁለቱ! ሽማግሌዎች እራት እየበሉ ጨዋታ ቀጠሉ፡፡

የሚገርም ነው ክቡር ከንቲባ፡፡ በመጀመሪያ አላወቅኸኝም፤ ሰዎች ሕይወታቸውን ካዳንክላቸው በኋላ ትረሳቸዋለህ? ይኸ ደግ አይደለም። እነርሱ ግን አይረሱህም:: የምትረሳ ሰው አይደለህም፡፡»

💫ይቀጥላል💫
👍275
መዝሙር_በሰሙነ_ሕማማት_የሚደመጥ

በ''ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ''


SUBSCRIBE 👇

https://youtube.com/watch?v=T1GfR3zJnoM&feature=share
👍2
ሥርዐተ ጸሎት ወስግደት ዐርብ.pdf
216.2 KB
የፀሎት ስርዓት በጥቂቱ
➤ ለካህናት // ለአገልጋዮች
➢ ሼር // SHARE
@Z_TEWODROS
👍4
#ዓለሞን_ትቻለሁ
ሁሉንም ንቄያለሁ
አንተን ናፍቄያለሁ
ጌታዬ ደፋ ቀና ያልኩት
የእሳትን ቅጣት ፣ ስለምፈራ ነው ፣አንተን ያመለኩት፤
ግና መስገዴ ለጥቅሜ
እሳትን ጫረብኝ ፣ የብልጥነት አቅሜ።
ገነትን እየሻትኩ
የልጅ ጠረን ሳይኾን ፣ እጣን እያሸተትኩ፤
ለመኖር ማለሜ ፣ በሐሳብ መንኜ
ገነትን አሳጣኝ ፣ ምኞት ሲዖል ሆኜ፤
ጌታዬ ፈለግሁ
ጌታዬ አጣሁህ ...
እሰማይ ላይ ባስስ ፣ብፈልግ ላመልክህ
ከምድርም አለ ፣ የዘላለሞ መልክህ፤
አንድዬ
ዓለምን አልተዉኩሞ፤
ሁሉንም አልናቅኩሞ፤
ምን በሰው ብቆስል፣ ምን ጣሬ ቢበዛ
ጣሬን አልጠላውሞ፤ ሰውን አልጥለውም ፣ አንተ አለህ በዚያ፧
9👍8🥰1
#ከፍሪጅ_የተጫረ_እሳት


#በአሌክስ_አብርሃም

...በቃሌ መሰረት ልደቷን ልናከብር ተቀጣጠርን፡፡ ከሰፈር አብረን መውጣቱ ለጎረቤት ሃሜት
ስለሚዳርግ የሆነ እሷ የመረጠችው ሬስቶራንት ስምንት ሰዓት ላይ እንገናኝ ተባባልን፡፡....
እኔ በበኩሌ የዚህ ዓይነት ሴት አይቼ አላውቅም፤ ቀድሚያት ነበር የደረስኩት፡፡ ቀይ የለበሱት
ጠረጴዛዎች የአገር ሹካና ማንኪያ፣ ቢላዋና የጨው የምናምን እቃ ዙሪያቸውን ተደርድሮባቸው፣ፈዘዝ ያለ ብርሃን ያለበት አዳራሽ ውስጥ በሰፊው ተንጣለዋል፡፡

ምቾት አይመቸኝም፤ ቅንጦት አያቀናጣኝም፤ ጨነቀኝ !
ሜሮን ስትደርስ ልቤ በድንጋጤ ልትቆም ምንም አልቀራትም፡፡ የሚያምር አጭር ጉልበቷ ላይ
የቆመ ቡና ዓይነት ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ውብ እግሮቿን ለማሳየት ሆን ተብሎ የተሰራ የሚመስል ረዥም ተረከዝ ያለው ጫማ፣ ጥልፍልፉ ፍርጥም ያለ ባቷ ላይ እንደሃረግ እየተጠመጠሙ ወጥቶ ጉልበቷ ላይ የደረሰ፣ ጡቶቿ ደረቷ ላይ ክፍት በሆነው ቀሚሷ ታቅፈውና ተሳስመው የሲኦል ሸለቆ እንደሰሩ፣ ፀጉሯ ወደ አንድ በኩል ተሰብስቦ በማስያዣ ተይዟል፤ ዓይኗ በኩል ተከቧል፣ ኦህህህህህህ ስታምር! የአዲስ አበባ እናቶች እድሜ አቆጣጠር አይችሉም ይሆናል እንጂ ይህቺ ልጅ አስራ ስድስት ዓመቷ ብቻ አይመስለኝም፡፡ በዚህ እድሜ ቀጠሮን የመከሸን ሳይንስ እንዴት ነው መካን የሚቻለው? እኔ እኮ በዚህ እድሜም አልችልበትም፡፡

ቆሜ ተቀበልኳት፤ ጉንጫችንን አነካካነው፤ መሳሳም መሆኑ ነው፡፡ አቤት ሽቶዋ! ..ፊቴ ዝም
ብላ ቆመች ! ..ቆምኩ …አሃ ለካ ወንበር ይሳባል ! ሳብኩላት፤
“ቴንኪው !” ብላ ተቀመጠች፤

“በጣም ቆንጆ ሆነሻል”

“እመሰግናለሁ” የተጠና ምልልስ መሰለብኝ እንጂ ከልቤ ነበር የተናገርኩት፡፡ በዚህ ቀን ከሜሮን
ጋር ከዘፍጥረት እስከ ራእይ አወራን፡፡ ሜሮን ካለ እድሜዋ የበሰለች ጉድ ነበረች፤ እናም
እንዲህ አልኩ፣

“ 'አዲስ አበባ ውስጥ ከሚኖሩ ሃምሳ ዱርዬ ሴቶች ውስጥ ሰላሳ ዘጠኙ ስማቸው ሜሮን
ይመስለኛል ግን ማናባቱ ነው ይሄን ቆጠራ ያካሄደው ደደብ!”ሜሮን ጋር ተዋድደን
ነበር በቃ ! እኔ ጋር በመሆኗ ነፍሷን እስክትስት ተደስታ ነበር፡፡እኔማ ነፍሴን ከሳትኩ ሰንብቻለሁ፡፡ ልዩ ሰው አድርጋ እንደምታስበኝ ነገረችኝ፤ ሰፈር ውስጥ ዝምታዬ መስጧታል።

ደግሞ ወሬው ሁሉ ከየት መጣልኝ ? የሰው ሰው በሳቅ ልገድል !! እግዜር ሲያስወድድህ ብዙ ሳቅ የወደደህ ሰው ልብ ውስጥ ያስቀምጣል፤ ከዛም የውድህ ሳቅ መውጫ በር፣ መተንፈሻ መስኮት ያደርግሃል፡፡ አንተ በፈለግከው መንገድ አፍህን ክፈት፣ ቃላትን አውጣ፤ ሜሪዬ የኔ ውብ አቤት ሳቋ ሲያምር ! እዛ ዩኒቨርስቲ “ሄይይ ምን አዲስ ነገር አለ ” እያሉ ሳቅ ፍለጋ እንደሚባዝኑ ሕይወታቸውን በጊዜ ያሟጠጡ ደነዝ ሴቶች አይደለችም፡፡ ቻፕስቲካም ከንፈራቸውን እስከጆር
ግንዳቸው ለቀው በ 'ዊትኒ ሆስተንኖ ለመሳቅ ቆርቆሮ ድምፃቸውን እንደሚያንኳኩ ኳኳታሞች አይደለችም፤ ሜሪ ራሷ ሳቅ ነበረች፤ ፍንትው ስትል ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ በሳቅ
የምትጥለቀለቅ ! እንደእኔ አይነቱ ሰው ተሳቀልኝ ቢል ያምርበታል፤

ልብ ነበራት፤ የፍቅር የሰላም ያልተነካካ፡፡ 'ውይ ወንዶች? እያሉ ያለፈ እንኩሮ ሕይወታቸውን
አዲስ የፍቅረኛ ምጣድ ላይ በትዝታ ስም እንደሚጠፈጥፉ ሴቶች አልነበረችም፡፡ ብታውቀውም ባታውቀውም ነገ ይናፍቃታል፡፡ ማንንም አልጎዳች፣ ማንም አልጎዳትም፡፡ ተረት የላትም ! ተረት አይደለችም፡፡ እነእከሌ ተፋቀሩ” ስትባል አትቀናም፡፡ “ተለያዩ" ሲባል አትፈርድም፤ ከተማውን የሞላው ፈራጅኮ ግማሽ ፍርዱ በቀል ነው፡፡ የደረሰበትን ሊስቀል፣ ያደረሰውን
ሊያስተባብል! ሜሪ ግን ብቻዋን ናት፡፡ ብቻዋን ወደ ሕይወቴ መጣች፤ አልከበደችኝም፡፡

ከዛን ቀን ጀምሮ ሁልጊዜ ማታ ማታ በር ላይ እንቆምና ስናወራ እናመሻለን፡፡ ውሃ ልትደፋ
ወጥታ ሊሆን ይችላል፡፡ “ቻው በቃ መሸ !” ትለኝና ቆም ትላለች፡፡ ከቻው በኋላ አንድ የሆነ
ነገር የማድረግ ፍላጎት ሁለታችንም ልብ ውስጥ አለ፡፡ ግን ማን ይድፈር ? ከቻው በኋላ
አንድ ሰዓት እናወራለን፡፡ “ምን አወራችሁ ?” ቢባል እንጃ !! ብዙ ጊዜ ቤቴ እንዳትገባ ሆነ
ብዬ እከላከላለሁ፤ ፈተናው ይከብደኛል፤ ስለዚህ በር ላይ ቆመን እናወራለን፡፡ ወሬኛ ነኝ፡፡
የማላወራላት ነገር የለም !! ባወራሁበት የምከፈለው ደመወዝ ሳቋ ነው፡፡ የጠገበ ደመወዝ፡፡
እግዜርዬ የፍቅር ዩኒቨርስቲ አስመርቆ የሰጠኝ ምርጥ ስራ - ሃሌ ሉያ !” አስመርቆ 'ስራ ፍጠር
ቢለኝ ምን ይውጠኝ ነበር ? ሳቋ ደመወዜ ነው፡፡….ስቃታለሁ፤ የማወራላት ምንም የማይጠቅም
ነገር ቢሆንም የሳቅ ደመወዜን አስቀርታብኝ አታውቅም፡፡

ታዲያ አንዳንዴ ማታ ቆመን ስናወራ ከሩቅ የጅብ ድምፅ ይሰማል፡፡ አውውውው…! ወደ እኔ
ጠጋ ትላለች፤ ሜሪዬ የመጨረሻ ፈሪ ናት፡፡ ጠረኗ ይጠርነኛል፡፡ ከምሽቱ አየር ጋር ወደ ሳንባዬ
ተስገብግቤ እስበዋለሁ፤ ጠረኗን !! እሷን ራሷን እንደአየር ስቤ ውስጤ ያስገባኋት እስኪመስለኝ፤ ጅቡን እድሜውን ያርዝምልኝና በጣም ትጠጋኛለች፡፡

ስለጅብ አወራላታለሁ፡፡ “የጅብ ጥፍር አንገትሽ ላይ ካሰርሽ በቃ የሄድሽበት ሁሉ ሲበሉ ነው
የሚያደርስሽ”
“ውሸትህን ነው ! ሂሂሂሂሂሂሂ…”
“ለምን እዋሽሻለሁ በሳይንስ የተረጋገጠ ነው”
“አላምንህም ! ሃሃሃሃሃሃ…”
እይውልሽ የአሜሪካ ሳይንቲስቶች ናቸው እኮ ያጠኑት”
“ውይ ውሸት አላምንልህም ! እንዴት አድርገው ያጠኑታል ? ... ታየኝ እኮ ስንት ስራ ትተው
አንገታቸው ላይ የጅብ ጥፍር አስረው ሲዞሩ ! ሂሂሂሂሂሂሂሂሂ…” ፍልቅልቅ ትላለች፡፡

ቀላል ነው፤ አንድ ጊዜ ይህን ጥናት እናጥና ብለው አለቃቸውን ሊያስፈቅዱት የጅብ ጥፍር አንገታቸው ላይ ልክ እንደዚህ እንደማተብ (እንገቷ ላይ ያሰረችውን ማተብ እየነካካሁ) አስረው ሳይንቲስቶቹ
ወደ ኃላፊያቸው ክፍል ሊገቡ ኃላፊው ምን እያደረገ አገኙት መሰለሽ…? በርገሩን እየገመጠ፡፡

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…ውሸት ! ውሸት ”

“..ከዛ ጥናቱ ተፈቀደላቸውና ወደ አፍሪካ መጡ፤ የሆነ ሰው የማይኖርበት ጫካ እካባቢ
አውሮፕላናቸው ተከለከሰ”
ኦ ማይ ጋድ! እውነትህን ነው ?” አለች ደንገጥ ብላ፡፡
ያ! ግን ማንም አልሞተም፡፡በተዓምር ተረፉ፡፡ ሁሉም አንገታቸው ላይ የጅብ ጥፍር አስረዋል፤ ከዛ የሆነ
ነገር ሸትቷቸው ዞር ሲሉ ጫካው ውስጥ የሚኖሩ አዳኞች ምን የመሰለች ጥንቸል ለምሳቸው እየጠበሱ:

“ወይኔ ውሸትህ ሂሂሂሂሂ…አልሰማህም !”

“እስኪ ጥናቱን የበለጠ ለማረጋገጥ ወደ ሌላ ዓለም እንውሰደው አሉና ናሳ ጋር ተነጋግረው ወደ ጨረቃ የሚጓዙ ጠፈርተኞች አንገት ላይ የጅቡን ጥፍር አሰሩላቸው፡”

“አሁንስ አበዛኸው ሕፃን ልጅ መሰልኩህ እንዴ ?” ብላ የውሸት ተቆጣች፡፡ ሜሪ ከዚህ »
ቀጥሎ የሚፈነዳውን ሳቅ ስለማውቅ ውሸቴን ቀጠልኩበት፡፡
“ልክ ጠፈርተኞቹ ጨረቃ ላይ ሲያርፉ ከእነሱ ቀድመው ጨረቃ ላይ ያረፉ የሩሲያ ጠፈርተኞት
ራት ሊበሉ ሲዘገጃጁ ደረሱ እልሻለሁ”

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ ሁለተኛ አላዋራህም እሺ ! ስታስጠላ ! እኔ ቁም ነገር የምታወራ መስሎኝ ! ሂሂሂሂ…” ሳቋ መቆሚያ የለውም፡፡ እኔም በሳቋ ልቤ ሃሴት ያደርጋል፡፡
👍31👏1
እስካሁን ስሚያት አላውቅም፡፡ ሳማት ሳማት…ከንፈሯን ጉረሰው ጉረሰው ይለኛል፤ ጨለማ
የሆነ ሰይጣን ነገር ሳይኖረው አይቀርም ! ቀን እዚሁ ቦታ ላይ ቆመን በጭራሽ የማይሰማኝ
ስሜት ማታ የሚገፋፋ አንዳች ነገር አለው፡፡ ወደ ደረቴ ስትጠጋኝ የጡቱቿ ጫፎች ደረቴን
ሸንቁረው በጀርባዬ በኩል ብቅ ያሉ ይመስለኛል፡፡ ..ፈተና ነው !
ጅብ ሲጮህ ስለጅብ አወራታለሁ፡፡ ድመት ከጮኸ ስለድመት፤ አባባ ካለች ስለአበባ…፡፡ ስናወራ
ስናወራ ሰካራሙ ጎረቤታችን ጉግሳ እየተወላገደ፣ እየዘፈነ ይመጣል፡፡

“አንተ ጉግሳ መጣ አራት ሰዓት…” ትላለች ሜሪ፡፡ ጉግሳ አራት ሰዓት ላይ እንደሚመጣ የታወቀ
ነው፤ የመንደሩ ሰዓት ነው ጉግሳ፡፡ ወሬ ሲወራ ሁሉ ልክ ጉግሳ ሲመጣ ይባላል፡፡ ልክ
አራት ሰዓት እንደማለት፡፡ እየዘፈነ፣ እየገጠመ (እያዝናና እና እያስተማረ ይሉታል ሲፎግሩ)
ከተፍ ይላል፤ ጉግሳ፡፡

ለእግሩ ጫማ የለው ለራሱ ባርኔጣ፡
የቅጣቸው አባት አሁን ገና መጣ፡፡

ይላል ጉግሳ (ቅጣቸው ልጁ ነው)፡፡ ወተር ወተር እያለ በጨለማው ውስጥ ሲራመድ የእማማ ትሩፋት ቡችላ ትጮህበታለች፡፡ ው ው ው ው ው ው ው…!!

ጉግሳ ቆም ብሎ ቡችላዋ ወዳለችበት ግቢ በንቀት እየተመለከት፤

•ቡችላ! ወንድ ከሆንሽ…የእመቤትሽ ውሽሞች አጥር ሲዘሉ አትጮሂም ? በአገልግል ዶሮው ተቋጥሮ በጓሮ በር ለውሽሞች ሲላክ አትጮሂም ? .…ውሻ ..የውሻ ልጅ !! ..ይቅርታ ! ደግ እናትሽን አሰደብሽኝ..! ነፍሷን ይማርና እናትሽ ጥሩሩሩሩሩሩ ውሻ ነበረች፡፡ ቤቴ ድረስ ሸኝታኝ
ነበር ቤቷ የምትገባው፡፡ ..የልጅ ዘመድ የለውም አንች…”
አይጨርሰውም፡፡

ጉግሳ እኔና ሜሪን ያየናል፡፡ ከእርሱ በፊት ቀድሞ አጠገባችን የሚደርሰው የአረቄና ጠጅ ሽታው
ነው፡፡ ቆም ብሎ ንፋስ እንደገፋው ዛፍ እየተወዛወዘ ኮፍያውን ያወልቅና በአክብሮት ጎንበስ ብሎ
(በግንባሩ እንዳይደፋ እሰጋለሁ) “ወጣቶች ልጆቻችን…የነገ አገር ተረካቢ እንደምን አመሻችሁ…!
ሃሃሃሃሃ…!! እኛንም እንዲህ ነበር ድሮሮሮሮሮ የሚሉን፤ ኪኪኪኪ…፡፡ የአገር ርክክቡ ሲዘገይ
እየጠጣን እንጠብቀው ብለን ሰካራም ሆንን ! ሃሃሃ…" ይላል በስካር ድምፅ፡፡

“ደህና አመሹ ጋሽ ጉግሳ!” እንለዋለን፡፡

ትከ ብሎ ያየንና፣ “መፋቀር ጥሩ ነው፤ እጅግ በጣም በጣም ጥሩ ነው ! ይሄ ቡዳ ሰፈር! በቡዳ
እንዳይበላችሁ ቤት ግቡ!” ይለናል፡፡ ሜሪ ሳቋን አፍና ዝም ትላለች፡፡

“መጽሐፉጋብቻ ቅዱስ ነው ይላል፤ ደግሞ ፍቅር ከሌለ ቆርቆሮ ቁራሌ ቆረቆንዳ ነህ ይላል፤ እኔ አሁን አምሳልን አፈቅራታለሁ፡፡ አስራ ሶስት ዓመት ስንኖር ተጣልተን አናውቅም፡፡ ለምን
?…ፍቅር ይሻላላ ! መጽሐፉ ተፋቀሩ ይላል !.…ጎበዞች ! አይዟችሁ ደህና እደሩ !” ይልና
እየተወላገደ ያልፋል፡፡ ሜሪ ደረቴ ላይ ድፍት ብላ ስሳቅ ፍርስስስስ ትላለች፡፡

ጉግሳ ትንሽ አለፍ እንዳለ፣ “እያንዳንድሽ ወየውልሽ ! ..በየጥጋጥጉ እየቆምሽ የምትባልጊ ሁሉ!
..ወየውልሽ !” ይላል እጁን ወደ ሰማይ ዘርግቶ፤ አመልኮች ጣቱን እየነቀነቀ፡፡ “መጽሐፉ በጨለማ የሰራሽውን ሁሉ በፀሐይ እገልፀዋለሁ፤ ስራሽን እንደ በርበሬ ዛላ፣ እንደታጠበ ልብስ፣
ለወፍጮ እንደተዘጋጀ የሽሮ ክክ ፀሐይ ላይ አሰጣዋለሁ ይላል መጽሐፉ!…ወዮልሽ! አርፈሽ
አትማሪና ኮከብ ስትቆጥሪ አምሺ…” ካለ በኋላ በዜማ ይቀጥላል፤

እንኳን ቤትና የለኝም እግር፣
እደጅ ድራለሁ ኮከብ ስቆጥር

“ኮከብ ቆጣሪ አስማተኛ ሁሉ...” ሌላ ርዕስ ውስጥ ይገባል፤ ጉግሳ እንዲህ ነው::

ሜሪ ጋር አንዳንዴ 'ወክ' እናደርጋለን፡፡ ንፁህና ፀጥ ያለ ኤምባሲ አለ፡፡ በሱ በኩል ማታ ክንዴን ደገፍ ብላኝ በጣም ተነካክተን ብርዱ ለስላሳ ቆዳችን ላይ የፈጠራቸው እንድብድቦችና የሜሪ እንድብድቦች እየተነካኩ፣ ሽቶዋ እየተቀላቀለብኝ ደስ ብሎን እንዝናናለን፡፡ስንሄድም ሆነ ስንመለስ አገር ሲያየን ግድ አልነበረንም፡፡ አሁን አውርተናል፡፡ 'ውስጤ ውስጥ ነሽ ብያታለሁ፤ 'ወድጄሻለሁ! ብያታለሁ፤ ምንም አላለችኝም፤ ግን እንባዋ መጥቶ ነበር።

አንድ ቀን ከ'ወክ' ስንመለስ እኔ ቤት ገባን፡፡ ፍራሽ ላይ እግሯን አነባብራ ዘርግታ ተቀመጠች፡፡ ቀሚሷ ስላጠራት ትንሽ ተጨናንቃ ነበር፡፡ እጠገቧ ተቀመጥኩ፡፡ ሁለታችንም የሆነ ነገር በጣም በጣም ፈልገናል፤ ግን…፤እዮኋት ቀሚሷ ላይ ባለች ቁልፍ ትጫወታለች፡፡ ፈራሁ! … አዕምሮዬ በሀሳብተራወጠ፤

1 የኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ አንዲት ሴት አስራ ስምንት ዓመት ሳይሞላት ወዳና
ፈቅዳም ሆነ ሳትወድና ሳትፈቅድ ወሲብ ብትፈፅም፣ ወሲብ የፈፀመባትን ሰው ዘብጥያ ..ከርቸሌን
ወላ ጀሜ አስገባው ይላል!!

2. ሕገ እግዜር ወዳ ፈቅዳ ሴት ወንድ ምናምን አይልም፤ “አታመንዝር!” በቃ !! ከፈለግክ
የከጀልካትን ሴት አግብተህ እንዳሻህ ሁን፡፡ አለበለዚያ አምሮትህን 'ሲያምርህ ይቅር!' ብለህ ገስፀው፡፡ ከዚህ በተረፈ ሲኦል ወላ ጀሀነም ትወረወራታለህ ! ይላል፡፡

3 የእኔ ይዞ ሟች ልብ የሜሪን የሚያምር ባት፣ የፈረጠመ ዳሌና ጫፋቸው የሚጣራ ጠይም
ጡቶች እያየ ከምድራዊውም ከሰማያዊውም ሕግ ሊያጋጨኝ በደም ፍላት ደም ይረጫል፡፡ ልቤ
ሲደልቅ ግግም ግግምግም ሲል አንድ ታዋቂ ትግረኛ ዘፋኝ ከነከበሮ ደላቂው በልቤ አዳራሽ
የሙዚቃ ስራውን የሚያቀርብ ይመስለኛል፡፡

የልቤ ምከር፣ “አብርሽ ሜሪ ትወድሃለች፡፡ ያደረጋችሁትን ለማንም አትናገርም፡፡ ደግሞ እያት
ከንፈሯ እንዴት እንደሚንቀጠቀጥ…ስትንከረፈፍ አንዱ እንዳይልፍህ !…እጆችህን ጡቶቿ ላይ አሳርፋቸው - አይዞህ ጠጋ ስላት፡፡ ኤጭጭጭ የምን መጨናነቅ ነው…የወንጀል ሕጉ አንጀባ ነው ባክህ !እግዜር ደግሞ እንኳን አንተን ስንቱን ይቅር ብሎ የለ !? ..ኧረ ሳይመሽ ፍጠን !
ነገ በዚህ ስሜት አታገኛትም፡፡ እንደውም ያልፈለካት መስሏት በዛው ነው የምትቀረው…...”
ብሎ ደም ይተፋል ልቤ፤

እነሆ በህገ እግዜር፣ በወንጀለኛ መቅጫ ህግና በግልፍተኛ ልብ መሃል ሚስኪኑ አብረሃም

ሜሪ አንድ እግሯን ሰብሰብ ስታደርገው ከጠይምነቷ የቀላ ለስላሳ ታፋዋ ተጋለጠ፡፡ ቀሚሷን
ሳብ አደረገችው፤ ግን አልሸፈናትም፡፡ ቀጥ ብላ አየችኝ፡፡ አይኗ ቡዝዝ ብሎ ነበር፡፡ ትከሻዬ
ላይ ራሷን ደገፍ አደረገችው፡፡ …ኡኡኡኡኡኡኡ ኡኡኡኡኡ ጠረኗ አመንዝር ይለኛል፡፡ውበቷ አመንዝር ይለኛል፡፡ ልቤ አመንዝር ይለኛል፡፡ ቤቱ አመንዝር ይለኛል፡፡ ሁኔታው አመንዝር ይለኛል፡፡ፍራሹ “ኑ እንጂ እየጠበቅኳችሁ አይደለም እንዴ! የምን መጎለት ነው! ይለኛል፡፡ እርግጠኛ ነኝ ሰይጣንም እንደአምፊ ቲያትር ከነጅሪው ተሰብስቦ እያየን ነው፡፡

ሜሪ በቀኝ እጄ ጣቶች እየተጫወተች ነበር፡፡ አቤት እጇ አለሳለሱ !! ደግሞ ይሞቃል ! ….ቆይ ምናባቴ ነው የማደርገው ? ... ሕግ ይሄን ያያል ? አያይም ! ?

ሕግ የሜሪ ጡቶች ማማራቸውን እንደቅጣት ማቅለያ ያያል…?
እናቴ አበባ ይዛ ምርቃቴ ላይ ለመገኘት ካሁኑ ስታወራ ምን ያህል በደስታ እንደምትምነሸነሽ
እያወቅኩ ምርቃት በቴሌቪዥን ባየች ቁጥር “አሁን የኔ ልጅ…” እያለች በደስታ እና በተስፋ ፊቷ
👍20
ላይ የምትለኩሰውን ብርሃን እፍ ብዬ ላጥፋው ? “ልጅሽስ ?” ስትባል (ኧረ ባትባልም፡፡) በኩራት
“ዩኒበርስቲ ገባኮ” እያለች በሳቅ የምትምነሸነሽ እናቴን በሐዘን አንገቷን ደፍታ እስር ቤት ሰሃን ይዛ
እድሜ ልኳን እንድትመላለስ ልፍረድ ? ከሁሉም በላይ እግዚያብሄር ይቅር ባይ ነው፤ ልክ
ነው ! የንስሃ ቀብድ ግን አይቀበልም፡፡ “ላጥፋ እንዴ፣ ይቅር ትለኝ እንደሆን ?” እንደማለት !!
የሜሪን እጅ ከእጄ ላይ አነሳሁ፡፡ ከፍራሹ ላይ ተነስቼ ቆምኩ፤ ከዛም “መሸ አይደል ?!”
አልኳት፤ “ውጪ” ነበር የሚመስለው አነጋገሬ ገብቷታል፡፡ ተነስታ ልብሷን አስተካከለችና
“አንተ ፍሪጅ አያስፈልግህም፤ ራስህ ማቀዝቀዣ ነገር ነህ” አለችኝ፡፡ “ደህና እደር!” ሳትለኝ
ወጣች፤ አልተመለሰችም!! የፍሪጅ ውሃውም በዛው ቆመ !

እግዚያብሔር ታዲያ እንዲህ ሲል በታላቅ ድምፅ ያወጀ መሰለኝ፣

“ልጄ አብረሃም ሆይ ! ህግጋቴን ላከበሩ፣ በፈተና ሰዓትም የቃሌን ጭላንጭል ሊመለከቱ
ለተፍገመገሙ ሁሉ፣ አንድ ጆግ ቀዝቃዛ ውሃ ሲከለከሉ እንኳን ስለነሱ ዓለምን በቀዝቃዛ ውሃ
አረሰርሳታለሁ !!!”

ክረምት ገባ !!
..
ዝናብ፣ ውሽንፍሩ፣ ደመናው
አዲስ አበባ ቀዝቀዝ አለች !! ክረምቱ የእኔ ክረምት መሰለኝ፡፡
አዲሳባ ውስጥ ፍሪጅ ካላቸው ሃምሳ ሴቶች መካከል ሃምሳውም ስማቸው ሜሮን ይመስለኛል፤
የፍሪጆቹ ዓይነትና ስም ቢለያይም ባህሪያቸው አንድ ነው፣ "አመድ በዱቄት መለወጥ” በሰጣት
ጠብታ ውሃ ጎርፍ ማንነትን በውለታ መልክ መቀበል ያምረዋል ፍሪጁ !! ፍሪጁን ከነስጦታው
የሚሹ ይሄ ታላቅ ክረምት የእነርሱ አይደለም !!

ፍራሼን ተመለከትኩት፤ ሰፊና ንፁህ ነው:: ብቸኝነት ሰላም፣ ፍራሹም ሰፊ ነው፡፡

አለቀ
👍26👏7
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

....ዣን ቫልዣ ለመተኛት ዓይኑን ከመጨፈኑ በፊት «ከዛሬ ጀምሮ
ከዚህ እኖራለሁ» ሲል ተናገረ:: እነዚህ ቃላት የሚስተር ፎሽለማን ጭንቅላት ሲበጠብጡ አደሩ:: ሁለቱም እንቅልፍ ሳይወስዳቸው ነው ያደሩት:: ዣቬር ፍለጋውን እንደሚያጧጥፍ ዣን ቫልዣ ያውቃል፡፡ ኮዜትና ዣን ቫልዣ
ወደ ከተማ የተመለሱ እንደሆነ ይያዛል፡፡ ስለዚህ ከገዳሙ ውስጥ መቆየት እንደሚሻል ዣን ቫልዣ አመነ፡፡ ሆኖም ለመደበቅ የሚያመች ስፍራ ቢሆንም ወንድ ከዚያ ስለማይገባ አደገኛ ነው፡፡ ከገዳሙ ውስጥ መኖሩ
ከታወቀ በወንጀል ተከስሶ ይታሰራል::

ሚስተር ፎሽለማ ደግሞ ስለነገሩ ግራ ገብቷቸው ስለተጨነቁ እንቅልፍ አልወሰዳቸውም፡፡ «እንዴት ከንቲባው ከዚያ ሊገባ ቻለ? ጋዳሙ ዙሪያውን በግንብ አጥር በመታጠሩ ሰው ከዚያ ሊገባ አይችልም:: ልጅትዋን ከየት አመጣት? ማንም ቢሆን ልጅ አዝሎ ከግንብ ላይ ሊወጣ አይችልም:: ልጅትዋስ የማን ልጅ ናት? ከየት ነው የመጡት? ምናልባት ገንዘብ አጉድሎ
እየሽሽ ይሆን? ወይስ በፖለቲካ ጉዳይ እየተፈለገ ነው?» ሲሉ ሽማግሌው ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ «ምናልባት ገዳሙን የመረጠው ጥሩ የመደበቂያ ሥፍራ
ስለሆነ ይሆን?» ሲለም አሰበ::

«መሴይ ማንደላይን ከሞት ያዳነኝ ሰው ስለሆነ አሁን የእኔ ተራ
ነው» በማለት ዣን ቫልዣን ለመርዳት ወሰኑ፡፡

«ለሕይወቱ ሳይሳሳ ያንን የሚያህል ጭነት ከጫነው ጋሪ ስር ገብቶ ነው ሕይወቴን ያዳናት! ግን እርሱን ከዚህ ማኖር ወንጀል ነው:: ብያዝ ምን እመልሳለሁ ሲሉ
ተጨነቁ

ሽማግሌው እስከዚህም ለሰው የሚጨነቁና ይሉኝታ የሚያጠቃቸው ሰው አልነበሩም:: አሁን ግን በእድሜም እያረጁ ስለሄዱ ፣በስተእርጅና ሰው ላይ ምን አስጨከነኝ፣ የሚል ስሜት ተሰማቸው:: የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ገዳም ውስጥ ለሁለት ዓመት ስለኖሩ ስለሕይወት የነበራቸው አመለካከት
ሳይለወጥ አልቀረም:: በመጨረሻ ሕይወታቸውን ለመሴይ ማንደላይን ለመሰዋት ወሰኑ።

ሚስተር ፎሽለማ ቀስ ብለው በር ሲያንኳኩ «ይግቡ» የሚል መልስ
አገኙ:: የገዳሙ ኃላፊዎች ቢሮ ነበር፡፡ ከቢሮው እንደጎቡ ለጥ ብለው እጅ

«እርስዎ ነዎት እንዴ አባታችን፡፡›
እንደገና ለጥ ብለው እጅ ነሱ፡፡
«እኔ ነኝ ያስጠራሁዎት፡፡»
«በጥሪው መሠረት መጥቻለሁ::»
«ለምን ነበር እኔን ለማነጋገር የፈለጉት?»
«ጉዳይ ነበረኝ፡፡»
«የምን ጉዳይ?»

ሚስተር ፎሽለማ ለሁለት ዓመት ገዳሙ ውስጥ ሲኖሩ ከተማው
ውስጥ የሚነገረውን ሁሉ ይሰማሉ፡፡ ግን የሰሙትን ሁሉ የመደበቅ ችሎታ ነበራቸው:: የገዳሙ ነዋሪ እንደቂል ነበር የሚያያቸው:: ሴሮች ግን
በጣም ያከብሯቸዋል። ሽማግሌው ስለሥራቸው ስፋት ለሴሮች ኃላፊ ብዙ አወሩ። ቀኑ አልበቃ ብሏቸው ሌሊቱን ሁሉ በጨረቃ ብርሃን እንደሚሠሩም «ብዙ ለኃላፊዋ ከገለጹ በኋላ አንድ ወንድም እንዳላቸውና
እርሱም ከእርሳቸው
በእድሜ ይነስ እንጂ ልጅ አለመሆኑን አስረዱ፡፡ ወንድማቸው ከእርሳቸው ጋር እንዲኖር ቢፈቀድላቸው በሥራ ብዙ ሊረዳቸው እንደሚችል ሲናገሩ
የኃላፊዋ ሰውነት ተሸማቀቀ፡፡

ሽማግሌው ንግግራቸውን በመቀጠል ወንድማቸው ጎበዝ አትክልተኛ መሆኑን እርሱ ካልረዳቸው በእድሜ ምክንያት ሥራው ስለሚከብዳቸው
ምናልባት ሥራውን ለመልቀቅ እንደሚገደዱ ተናገሩ፡፡ በተጨማሪም ወንድማቸው ትንሽ ሴት ልጅ እንዳለውና ከእርሳቸው ጋር እንዲኖር ከተፈቀደላቸው ልጅትዋ በሃይማኖት ተኮትኩታ ልታድግ እንደምትችልገለጹ:: ምናልባት አንድ ቀን ይህቺ ልጅ መንኩሳ ቤተክርስቲያንን ልታገለግል እንደምትችልም አስረዱ፡፡

ሽማግሌው እንደጨረሱ ኃላፊዋ መነኩሲት ሥራ እንዲሠሩ
አዘዝዋቸው፡፡

«እስከ ነገ ማታ አንድ ወፍራም ብረት ሊገዙልኝ ይችላሉ?»
«ለምን ሥራ?»
«ለአንድ ሥራ!»
«ምን ገድዶኝ፣ እችላለሁ እንጂ!» ሲሉ መለሱ ሽማግሌው፡፡
ኃላፊዋ መነኩሲት ይህን ተናግረው ወጥተው ሄዱ:: ፎሽለማ ብቻቸውን ቀሩ

አንድ ሩብ ሰዓት አለፈ፡፡ ኃላፊዋ ሴር ተመልሰው ከመቀመጫቸው
ተቀመጡ፡፡ ሁለቱም አሳብ የያዛቸው መሰሉ፡፡
«አባታችን?»
«እማሆይ!»
«የጸሎት ቤቱን ያውቁታል?»
«ለቅዳሴ አልፎ አልፎ ወደዚያ ስለምሄድ አውቀዋለሁ፡፡»
«ከዚያ ይሄዳሉዋ?»
«ከአንዴም ሁለቴ፤ ከሁለቴም ሦስቴ ሄጃለሁ፡፡»
«ከዚያ የሚፈነቀል ትልቅ ድንጋይ አለ፡፡
«ከባድ ነው?»
«የሚፈነቀለው ድንጋይ ያለው ከቤተመቅደሱ አጠገብ ነው::»
«ብዙ ቦታ ከሆነ አንድ ሰው ብቻውን መፈንቀል አይችልም:: ሁለት ወንዶች ያስፈልጋሉ፡፡»
«ከመነኮሳቱ መካከል አራቱ ይረዱዎታል፡፡»
«ይኸው ነው ሥራው?»
«ዛሬ ጠዋት አንዲት ሴር እንደሞቱ ያውቃሉ?»
«የለም፤ አላወቅሁም::»
«ለሙታን የሚደረገውን ሁሉ ማድረግ አለብን፡፡ ሟችዋ ሴር ቆመው ይጸልዩበት ከነበረው መሬት ስር አጽማቸው ያለሳጥን ማረፍ አለበት፡፡
ነፍሳቸው ከሥጋቸው ከመለየቱ አስቀድሞ የጠየቁት ጥያቄ ነው:: መጠየቅ ሳይሆን ያዘዙት ነገር ስለሆነ መፈጸም ይኖርበታል፡፡
«ከዚያ ጸሎት ቤት ሰው መቅበር እኮ የተከለከለ መሆኑን ያውቁ
የለ፡፡»
«ወንዶች ናቸው የከለከሉት? ፤ እግዚአብሔር ግን ይፈቅዳል፡፡
«ወሬ ቢሰማስ?»
«በእርስዎ ላይ እምነት አለኝ፡፡»
«ግን እማሆይ፤ የጤና ጥበቃ ተወካይ..»
«የሃይማኖት መሪዎች ስለቀብር የደነገጉት ሕግ አለ፡፡»
«ሆኖም የፖሊስ አዛዥ ...
«የጥንት ነገሥታት ፈቅደዋል፡፡»
«አስተዳዳሪው...»
«በእግዚአብሔር ፊት እርሱም ከቁጥር አይገባም::»
«አሁን እማሆይ?» አሉ ሽማግሌው::
«እምነት እንጣልብዎ?»
«እታዘዛለሁ::»
«በዚሁ ይለቅ፡፡»
«እማሆይ ለጠቀሱት ሥራ ሁለት ሜትር የሚሆን ወፍራም ብረት
ያስፈልገኛል፡፡»
«የት ታገኛለህ?»
«እዚሁ ግቢ ውስጥ እቃ ከምናስቀምጥበት ሥፍራ ብረት ያለ ይመስለኛል፡፡»
«ይኸው ነው እማሆይ? አሁን ስላሉት በሰዓቱ እገኛለሁ::»
««የለም፤ ሌላም ነገር አለ፡፡»
«ምን አለ?»

«የተገዛው የሬሣ ሣጥን ጉዳይ::»
ሁለቱም መልስ ሳይሰጡ ተፋጥጠው ለጥቂት ሰኮንድ ቆዩ::
«የሬሣ ሣጥኑን ምን እናደርገዋለን?» ሲሉ ኃላፊዋ ጠየቁ፡፡
«ይቀበራላ!»
«ባዶውን?»
«እማሆይ፤ እኔ ባፈር እሞላዋለሁ:: አፈር ቢሞላበት ሰው ያለው
ይመስላል፡፡»
«ልክ ነዎት፡፡ ሰውም ቢሆን እኮ ከአፈር ነው የተሠራው:: እንግዲህ
ባዶውን ሣጥን እርስዎ ያዘጋጁታል?»
«በሚገባ!» ብለው ከመለሱ በኋላ ለመሄድ ወደ በር አመሩ፡፡

«በመልዕክት አቀባበልዎ ደስ ነው ያለኝ:: ወንድምዎን ነገ ከእኔ
ዘንድ ያምጡት፡፡ ልጁንም ይዞ ይምጣ፡፡

ያን እለት ማታ ዣን ቫልዣ ኮዜትን ይዞ ወደ ኃላፊዋ ሴር ሄደ፡፡
ሴርዋ ዣን ቫልዣን ከእግር እስከ ራስ አዩት:: ኮዜትንም እንደዚሁ ከአዩዋት በኋላ

«ይህ ቤት ሳያስማማት አያቀርም» ሲሉ ተናገሩ::

ኃላፊዋ ሴር አብረዋቸው ከነበሩት ከሌሎች ሁለት ሴሮች ጋር
ጥቂት ተወያዩ:: ከዚያም ኃላፊዋ ሚስተር ፍሽለማን እያዩ፡- «አባታችን፤ ሌላ ጉልበት ላይ የሚታሰር ቃጭል ይሰጥዎታል፡፡ አሁን እንግዲህ ሁለት ወንዶች ስለምትሆኑ ሁለት ቃጭል ነው የሚያስፈልጋችሁ» አሉ፡፡
በሚቀጥሉት ቀኖች የሁለት ቃጭል ድምፅ ከአትክልቱ ውስጥ ተሰማ፡፡
ሴሮች በዚያ ባለፉ ቁጥር ሁለት አትክልተኞች ጎን ለጎን ሁነው አበባውን ሲኮተኩቱ ተመለከቱ፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ሴሮች በብዛት በዚያ አለፉ፡፡ሁለቱ አትክልተኞች ድምፅ ሳያሰሙ ይኮተኩታሉ፡፡ ፀጥታው ድንገት ደፈረሰ፡፡

«አብሮ የሚኮተኩተው ረዳት አትክልተኛ ነው» ካለ በኋላ የአባታችን የሚስተር ፎሽለማ ወንድም ነው» ሲሉ ተናገሩ፡፡
👍19👎2