ዣን ቫልዣ አዲሱ ስሙ ኽልቲመስ ፎሽለማ ሆነ፡፡ ኃላፊዋ ሴት እንደተነበዩት ኮዜት ግቢው ተስማምቷት በአጭር ጊዜ
ብዙ ጓደኛ ኣፈራች:: አንድዋ ጓደኛዋ ኃላፊዋ ሴር ነበሩ፡፡ ከልጃገረዶች ትምህርት ቤት ውስጥ የነፃ ትምህርት እድል ተሰጥቷት ትምህርትዋን
ቀጠለች፡፡
ኮዜት ገዳሙ ውስጥ ከሴቶች ትምህርት ቤት ገብታ ዩኒፎርም
ለበሰች፡፡ ከእነ ሚስስ ቴናድዬ ቤት ስትወጣ የለበሰችውን ጥቁር ልብስ ዣን ቫልዣ ጥሩ አድርጎ ካጣጠፈው በኋላ ሳጥን ውስጥ አስቀመጠችው:: ከዚያ
ወዲህ እርስዋ አዳሪ ትምህርት ቤት ገብታ ስትማር እርሱ የአትክልተኛነት ሥራውን ቀጠለ፡፡ ሥራውን በትጋት ስለሠራ ግቢው ውስጥ ለውጥ ታየ፡፡
ኮዜት በየቀኑ እየመጣች ለአንድ ሰዓት ያህል ከእርሱ ጋር እንድትጫወት ተፈቅዶላታል፡፡ ሴሮች ብዙውን ጊዜ ዝም ስለሚልዋትና እርሱ ዘንድ በመጣች ቁጥር ብዙ ስለሚያሳስቃት ዣን ቫልዣን ዘወትር ከሴሮች ጋር እያነፃፀረች እርሱን እንደ አምላክ ታመልከዋለች:: ሁለቱ ወንዶች የሚኖሩበት ቤት እርስዋ ስትመጣ በጣም ይደምቃል:: በእረፍት
ሰዓት ወጥተው ሲጫወቱ ዣን ቫልዣ ዘወትር በሩቁ ሆኖ ያያታል፡፡
ሳቅዋ የተለየ ስለነበር ድምፆን በሩቁ ይለየዋል ኮዜትም ያ ዝምታ ቀርቶ አሁን ሳቂታ ልጅ ሆናለች::
ከጊዜ በኋላ ኮዜት በጣም እየተለወጠች ሄደች:: ያ ኮሶ ፊትዋ
በፈገግታ ተለወጠ፡፡ ሳቅ ብርሃን ስለሆነ ጨፍግጎት የነበረው ፊትዋ ብርሃን ፈነጠቀበት::
የእረፍቱ ሰዓት አልቆ ወደ ክፍልዋ ስትገባ ዣን ቫልዣ የክፍልዋን
መስኮት በሩቁ ይመለከታል፡፡ ከዚያ ክፍል ውስጥ እንዴት ሁና እንደተቀመጠች ያሰላስላል፡፡
ገዳሙ በአጋጣሚ ሲገባበትም ለእርሱ ሁለተኛው እስር ቤት ነበር:: መጀመሪያ ታስሮበት የነበረው እስር ቤትና ገዳሙ በኣንዳንድ ነገር
ይመሳሰላሉ፡፡ ነገር ግን የመጀመሪያው እጅግ የመረረ ሲሆን የሁለተኛው እንደ መጀመሪያው የከፋ አልነበረም:: ሆኖም ሁለቱም በከባድ አጥር
የተካለሉና በራቸው በብረት መቀርቀሪያ የሚቀረቀር ነበር፡፡ አንዱ በወታደር
አጥር ሲከበብ ሌላው በብርሃን መቅረዝ የተሞላ ነው፡፡ የመጀመሪያው ቅጣት የሚቀበሉበት ሥፍራ ሲሆን ሁለተኛው በጸሎት የሚማቅቁበትና ደግነት፧ ትህትናና ሩህሩህነት የሚታሰብበት ቦታ ነው:: ከመጀመሪያው
ይበልጥ ሁለተኛው ዝምታ ይበዛበታል፡፡
ዣን ቫልዣ ሁለቱን በይበልጥ ባነፃጸረ ቁጥር ቅስሙ በይበልጥ
እየተሰበረና የኑሮ ፍላጎቱም በይበልጥ እየደከመ ሄደ፡፡ ያለፈውን ሕይወቱን ወደኋላ እያየ ለራሱ ያዝናል፡፡ አንዳንዴ እስከ ማልቀስም ይደርሳል፡፡ በዚህ
ዓይነት ከእስር ቤት ሲወጣ ያገኛቸው ጳጳስ በደግነታቸው፤ ኮዜት በፍቅርዋና ገዳሙ በተገራ ኃይል የቀረጹበትን ውስጣዊ ስሜቱን እያመቀ ስድስት ወር
ከገዳሙ ውስጥ ተቀመጠ፡፡
የአትክልቱ ቦታ ፀጥታ፤ የአበቦች መዓዛ፤ የልጆች ጫጫታ የደናግሉ
ዝማሬና ትህትና ቀስ በቀስ ሳይታወቀው ሕይወቱን ለወጡት፡፡ ልቡ በብቸኝነትና በዝምታ ኑሮ ስለተዋጠ ከመንፈሳዊ ኑሮ በስተቀር የሚያስበው
ነገር ጠፍቶት እየኖረ ብዙ ዘመናት አለፉ፡፡ኮዜትም እያደገች ሄደች፡፡....
💫ይቀጥላል💫
ብዙ ጓደኛ ኣፈራች:: አንድዋ ጓደኛዋ ኃላፊዋ ሴር ነበሩ፡፡ ከልጃገረዶች ትምህርት ቤት ውስጥ የነፃ ትምህርት እድል ተሰጥቷት ትምህርትዋን
ቀጠለች፡፡
ኮዜት ገዳሙ ውስጥ ከሴቶች ትምህርት ቤት ገብታ ዩኒፎርም
ለበሰች፡፡ ከእነ ሚስስ ቴናድዬ ቤት ስትወጣ የለበሰችውን ጥቁር ልብስ ዣን ቫልዣ ጥሩ አድርጎ ካጣጠፈው በኋላ ሳጥን ውስጥ አስቀመጠችው:: ከዚያ
ወዲህ እርስዋ አዳሪ ትምህርት ቤት ገብታ ስትማር እርሱ የአትክልተኛነት ሥራውን ቀጠለ፡፡ ሥራውን በትጋት ስለሠራ ግቢው ውስጥ ለውጥ ታየ፡፡
ኮዜት በየቀኑ እየመጣች ለአንድ ሰዓት ያህል ከእርሱ ጋር እንድትጫወት ተፈቅዶላታል፡፡ ሴሮች ብዙውን ጊዜ ዝም ስለሚልዋትና እርሱ ዘንድ በመጣች ቁጥር ብዙ ስለሚያሳስቃት ዣን ቫልዣን ዘወትር ከሴሮች ጋር እያነፃፀረች እርሱን እንደ አምላክ ታመልከዋለች:: ሁለቱ ወንዶች የሚኖሩበት ቤት እርስዋ ስትመጣ በጣም ይደምቃል:: በእረፍት
ሰዓት ወጥተው ሲጫወቱ ዣን ቫልዣ ዘወትር በሩቁ ሆኖ ያያታል፡፡
ሳቅዋ የተለየ ስለነበር ድምፆን በሩቁ ይለየዋል ኮዜትም ያ ዝምታ ቀርቶ አሁን ሳቂታ ልጅ ሆናለች::
ከጊዜ በኋላ ኮዜት በጣም እየተለወጠች ሄደች:: ያ ኮሶ ፊትዋ
በፈገግታ ተለወጠ፡፡ ሳቅ ብርሃን ስለሆነ ጨፍግጎት የነበረው ፊትዋ ብርሃን ፈነጠቀበት::
የእረፍቱ ሰዓት አልቆ ወደ ክፍልዋ ስትገባ ዣን ቫልዣ የክፍልዋን
መስኮት በሩቁ ይመለከታል፡፡ ከዚያ ክፍል ውስጥ እንዴት ሁና እንደተቀመጠች ያሰላስላል፡፡
ገዳሙ በአጋጣሚ ሲገባበትም ለእርሱ ሁለተኛው እስር ቤት ነበር:: መጀመሪያ ታስሮበት የነበረው እስር ቤትና ገዳሙ በኣንዳንድ ነገር
ይመሳሰላሉ፡፡ ነገር ግን የመጀመሪያው እጅግ የመረረ ሲሆን የሁለተኛው እንደ መጀመሪያው የከፋ አልነበረም:: ሆኖም ሁለቱም በከባድ አጥር
የተካለሉና በራቸው በብረት መቀርቀሪያ የሚቀረቀር ነበር፡፡ አንዱ በወታደር
አጥር ሲከበብ ሌላው በብርሃን መቅረዝ የተሞላ ነው፡፡ የመጀመሪያው ቅጣት የሚቀበሉበት ሥፍራ ሲሆን ሁለተኛው በጸሎት የሚማቅቁበትና ደግነት፧ ትህትናና ሩህሩህነት የሚታሰብበት ቦታ ነው:: ከመጀመሪያው
ይበልጥ ሁለተኛው ዝምታ ይበዛበታል፡፡
ዣን ቫልዣ ሁለቱን በይበልጥ ባነፃጸረ ቁጥር ቅስሙ በይበልጥ
እየተሰበረና የኑሮ ፍላጎቱም በይበልጥ እየደከመ ሄደ፡፡ ያለፈውን ሕይወቱን ወደኋላ እያየ ለራሱ ያዝናል፡፡ አንዳንዴ እስከ ማልቀስም ይደርሳል፡፡ በዚህ
ዓይነት ከእስር ቤት ሲወጣ ያገኛቸው ጳጳስ በደግነታቸው፤ ኮዜት በፍቅርዋና ገዳሙ በተገራ ኃይል የቀረጹበትን ውስጣዊ ስሜቱን እያመቀ ስድስት ወር
ከገዳሙ ውስጥ ተቀመጠ፡፡
የአትክልቱ ቦታ ፀጥታ፤ የአበቦች መዓዛ፤ የልጆች ጫጫታ የደናግሉ
ዝማሬና ትህትና ቀስ በቀስ ሳይታወቀው ሕይወቱን ለወጡት፡፡ ልቡ በብቸኝነትና በዝምታ ኑሮ ስለተዋጠ ከመንፈሳዊ ኑሮ በስተቀር የሚያስበው
ነገር ጠፍቶት እየኖረ ብዙ ዘመናት አለፉ፡፡ኮዜትም እያደገች ሄደች፡፡....
💫ይቀጥላል💫
👍20❤6
#ሸረኛ_እና_ደህና_በአንድ_ላይ #ሲሄዱ_በሸረኛው_በኩል_ተናደ #መንገዱ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
#ሸረኛ
የዶክተር ደበጫ እርገጤ መዝገበ ቃላት ሸረኛ የሚለውን ቃል ሲያብራራው እንዲህ ይላል፡
ሸረኛ ስም፣ እንዳገባቡ 'ተውላጠ ስም፣ አንዳወጣጡ ግስ'፣ ሳይገባም ሳይወጣም ራሱን ችሎ
ዓረፍተ ነገር !
ትርጉሙ፡- (በተንኮል የሰው ማንነት፣ መልካም ስም፣ መልካም ሥራ፡ መልካም ግንኙነት
የሚሸረሸር፣ የሚሰረስር፣ የሚቦረቡር፣ የሚደረምስ፣ የሚያጠለሽ... ይለዋል። መዝገበ ቃላቱ ይሄን ሁሉ ነገር ከሚያንዛዛ በቀላሉ መግለፅ ይችል ነበር ልክ እንደዚህ፣
ሸረኛ፡- ሰው አቶ እጅጉ ! በቃ! አጭር ግልፅና ወቅታዊ ፍቺ !!
ምሳሌ፣ አቶ እጅጉ ሸረኛ ነው። ትክከል !! ይሄ ምሳሌ አይደለም፣ እጅጉ (እጅ እግሩን አስሮ
ሲኦል ይወርውረውና) 'ሸረኛ' ነው፡፡ ሸረኛ ብቻ አይደለም፣ ምቀኛም ነው፡፡ የሚቀናበት ነገር
ሲያጣ እኩል በተሰጠን 24 ስዓት ይቀናል፡፡ (“እንደው በየትኛው ጊዜ ብትማሩት ነው ይሄን ሁሉ ነገር ያወቃችሁት?” ይላል የማያውቀውን ነገር አውቀን ካገኘን፡፡ ለነገሩ እሱ ምንም
አያውቅም፡፡) ምን ይሄ ብቻ! እግዜር በፈጠረው አየር ሳይቀር ይቀናል፤ የቢሯችን መስኮት
ተከፍቶ እንደልብ አየር ሲገባ ብቅ ይልና፤ ይሄን አየር በነፃ ትሉታላችሁ” ይላል፡፡ እንከፈል?
ሸረኛም ምቀኛም ብቻ አይደለም መሰሪ ተንኮለኛም ነው:: አሟልቶ አይሰጥም' ይባላል አንጂ
ይሄው የተሟላ ክፉ ሰው፡፡
እንግዲህ ሸረኛ፣ ምቀኛ፣ መሰሪ ሆኖ ደግሞ አለቃዬም ነው፡፡ ጥሎበት አይወደኝም፡፡ እኔም
ሰለማልወደው ተመስገን ቢወደኝ ምን ይውጠኝ ነበር?' እላለሁ ሁልጊዜ፤ ለምወደው ሰው
ነው የምጨነቀው፡፡ አሁን በዚች ቅፅበት በሆነ አጋጣሚ ነገር ሎተሪ ምናምን ኣይነት እድል
ገጥሞኝ በድንገት የብዙ ኢ ቢሆን የመጀመሪያ ሥሪዬ ሁለት እጆቼን ኪስና ኪሴ ከትቼ በቀዳዳ ኪሴ ውስጥ በሾለኩ ጣቶቼ ራቁት ታፋዩን በማፏጨው ሙዚቃ 'ሪትም' እየተመተምኩ ጀነን ብዪ ወደ አለቃዬ ቢሮ ሄድና አንኳኳለሁ፣ ኖ..ኖ.አላንኳኳም፤ በሩን በእግሬ ገፋ አድርጌው እገባለሁ፡፡ (ካፈቀሩ ከነፍስ፣ ከጠሉም ከነፍስ ነው የምን ማስመሰል) ፊት ለፊት፣ ጉማሬ ፊቱ አለቃዬ ሁልጊዜ በሚደፈርሱ አስቀያሚ ደመኛ አይኖቹ ያፈጥብኛል። ቀጥሎ ኪሶቼ ውስጥ የወሸቅኳቸውን እጆቼን በቁጣ ያያል፤ (ደንግጨ
ከኪሲ እንዳወጣቸው እንድርበተቡት፡፡) ፀጥ ብዪ በትዕቢት ሳየው የኢትዮጵያን ሲጋራ ሁሉ ብቻውን ያጨሰ ከሚያስመስሉት አስቀያሚና ገጣባ ከንፈሮቹ ቃላት ደፈለፈላሉ፤ ሰው ሰው የማይሸቱ እብሪተኛ ቃላት፡፡
ምናልባትም፣ “ብላችሁ ብላችሁ ማንኳኳቱንም ተዋችሁት." ይል ይሆናል፡፡ (እግዜርና ሰይጣን
ለዚህች ቅፅበት እርቅ አውርደው ይሄን ድንጋይ ራስ ኣለቃዬን በመዶሻ ያንኳኩትና።) ወይም
“ኪስህ የወሸቅከውን እጅህን አውጣ!" ሊልም ይችላል፣ አላወጣም !(ኪሴ ቀዳዳ ሲሆን
ቀዳዳውን ተሻግሮ ያለም ወንድነት የራሴ ርስት ነው . ዘራፍ ! በቀዳዳ እኛነታችን ውስጥ እያለፈ ወንድነታችንን ያኮላሹን ክፉዎች ሁሉ ከዛሬ ጀምሮ አድርጉ ያሉትን አናደርግም፡፡
ኮራ ብዬ "እእእእ አቶ እጅጉ” እለዋለሁ፡፡ (“አቶ" በማሾፍ ሲጠራ እንዴት ያለ አሪፍ ስድብ ነው፡፡) ለምሳሌ፣ እኔ "አቶ” ከሚለው ቅፅል ይልቅ ከስሜ በፊት ሰሃራን የሚያህል ባዶ ምድረ በዳ ቢዘረጋ ይሻለኛል፡፡ በተለይ አለቃዬ "አቶ" ከሚለኝ ። ...አዎ ! እሱ "አቶ"
ሲለኝ በውስጡ “መቼም ለአቶነት አትበቃም በቸርነቴ 'ከቶ'ነት ልስጥህ እሰቲ” የሚል ይመስልበታል፡፡ አቷም።
እና አቶ እጅጉ ከዛሬ ጀምሮ ሥራ ለቅቄያለሁ” እለዋለሁ በኩራት፡፡ 'እእእእ' የምትለዋን ዘገምተኛ ቃል ማስቀደም አልረሳም፡፡ አራት ዓመት ሙሉ የሱን አስቀያሚ እእእ' ችዬ ኖሬ የለ ስለዚህ የምለው እንደዚህ ነው:: “እእእእ.አቶ እጅጉ ከዛሬ ጀምር...እእእእ ሥራ ለቅቄያለሁ !”
ይደነግጣል፣ አያምንም፡፡ እኔ ስፈጋ የዋልኩበትን ሥራ ሁሉ ለአለቆቹ እንዲህ ሠርቼው እንዲህ
አድርጌው እያለ በስልክ መወሽከቱ ሊቆም ሲሆነ ይደነግጣል እሰይ ! ወሽካቶች መደንገጥ አለባቸው።
ወዲያው የበሰበሰ የማኔጅመንት 'ሲስተሙን' እኔ ላይ ሊሞክራት ይፍገመገማል፣ “አትደነግጥ
የበታች ሠራተኛህ ፊት አዋቂ፣ ልብ ሙሉ ምንትስ ሆነህ ቅረብ፣ ባትሆንም ሁን…” የምትለዋን
ያስብና ጉሮሮውን ጠራርጎ፣ “እእእ….እዚህ መሥራቱ ራስህን ለማሳደግም ሆነ ቤተሰብህን ለመርዳት አይሻልህም? ይላል፡፡ ሥራ ብለቅ ቤተሰቦቼ በረሃብ ዛሬውኑ የሚያልቁ በሚያስመስል ሁኔታ 'ቤተሰብ የምትለዋ ቃል ላይ አፅንኦት ሰጥቶ፡፡
ከፉዎች መሳሪያ ልጅህ ላይ ባይደግኑም፡ እናትና አባትህን አፍነው ባይወስዱም፣ የነገን ጨለማነት እየነገሩ ያግቱUል፡፡ ስንቱ መሰለህ ቁራጭ ዳቦ እንዳይነሱት ፈርቶ ለማንም አጋሰስ ጉልበቱን የሚገፈግፈው፤ ስንቱስ ነው ' ከሥራ መባረር የሚባል የታንክ አፈ ሙዝ ልቡ ላይ ተደግኖበት ዘመናዊ ባርያ የሆነው !! ስንቷን ሚስኪን በፀሃፊነት ስም የጭን ገረዱ ያደረጋት ጋንጩር አለ ቢሮ ይቁጠረው !
ሀላፊ ሲባል አርቲስት ነው፡፡ ወንበሩን መድረክ ያደረገ ተዋናይ፡፡ ያውም ድብን ያለ ትራጀዲ
የሚተውን፡፡ እና እኔ ምን እለዋለሁ ሃሳቤ ደስ ብሎኝ ሳምሰላስል፣ ዙፋን ዘው ብላ ወደ ቢሮዬ
ገባች፡፡ ጥሎባት ማንኳኳት አትወድም፡፡ 'እንኳኪ!' ብሏት የሚያውቅም የለም፡፡
"ብርሽዩ” ትለኛለች፡፡ (ስሟን ከነአያቷ ቄስ ይጥራትና) ! ሁልጊዜ ስትጠራኝ እንዲሁ ነው፡፡ ታዲያ አጠራርዋ ከማማሩ ብዛት እኔን ለጠራችኝ ሌሎቹ 'ወይዬ' ሊሏት ይዳዳቸዋል፡፡
እንዲህ በሀሳብ ጭልጥ ያልከው ወዴት ሄደህብኝ ነው?” ወዴትስ ብሄድ ምን አገባት፡፡ ጭራሽ
የምሄደውስ የምቀረውስ ለሷ ነው እንዴ? (ሄደህብኝ !! ጥርግ ብል እንትናዬ እያለች አንዱ ቢሮ ልትንኳተት፡፡
"እ..ምነው ጠፋሽ?” አልኩ እንደመጣልኝ፡፡ የምለው አጥቼ እንጂ ዙፋን ደግሞ መቼ ጠፍታ
ታወቅና፡፡ በአንድ ጊዜ ሰባት ቢሮ ውስጥ የምትገኘውን ዙፋንን ጠፋሽ ማለት መሬትን “ምነው
በዚህ ሳምንት መዞርሽን አቆምሽ?” ብሎ ከመጠየቅ አይተናነስም፡፡
ሆሆ ከየት ተገኘሽ፣ አሁን እንኳን ስመጣ አራተኛዬ ነው” አለችና ከጠረጴዛዬ ፊት ለፊት ወንበር
ስባ ተቀመጠች፡፡ ወንበሩ ተንጫጫ፡፡ ጉርድ ቀሚሷ ቀይ ታፋዋን ወለል አድርጎ ያሳያል…..
ኤጭጭጭጭጭ!!
“ቆንጆ ናት” ይባላል፡፡ “ትሁት ናትም” ይሏታል። “የሰለጠነች፣ ሰው አከባሪ" የሚሏትም ብዙ
ናቸው፤ እንደው ባጠቃላይ እዚህ ቢሮ ዙፋንን ለማናገር፣ ለማቅረብ፣ ሲመቸው ወደ ኣልጋው
ጎትቶ አብሯት ለመጋደም የማይመኝ ያለ አይመስለኝም፡፡
ዙፋን እኛ ቢሮ ሥራ ስትጀምር ከሥራ ልምዷ ጋር ከእግዜር የተላከ “ከዛሬ ጀምሮ ያየ አመነዘረ፤ የሚለው ጥቅስ ተሰርዟል” የሚል ደብዳቤ ይዛ የመጣች ይመስል፣ እዛ ፋይናንስ ከሚሠራው ዲያቆን ወልዱ ጀምሮ ሰው ሰላም ሲል እገጩ መሬት እስኪነካ የሚያጎነብሰው ጴንጤው ምክትል ኃላፊያችን የዙፋንን እግርና መቀመጫ አይተን እንሙት አሉ፡፡ ዙፋንም ታዲያ የዕለት እንጀራዋ የሰው አይን ይመስል ነገረ ሥራዋ ሁሉ የታይታ ነው፡፡ አቤት መታየት ስትወድ፡፡ ሰው ከኋላዋ እንደሚያያት ከጠረጠረች ለከፉ ቀን ያስቀመጠችውን መቆናጠር ሁሉ ትጠቀምበታለች፡፡
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
#ሸረኛ
የዶክተር ደበጫ እርገጤ መዝገበ ቃላት ሸረኛ የሚለውን ቃል ሲያብራራው እንዲህ ይላል፡
ሸረኛ ስም፣ እንዳገባቡ 'ተውላጠ ስም፣ አንዳወጣጡ ግስ'፣ ሳይገባም ሳይወጣም ራሱን ችሎ
ዓረፍተ ነገር !
ትርጉሙ፡- (በተንኮል የሰው ማንነት፣ መልካም ስም፣ መልካም ሥራ፡ መልካም ግንኙነት
የሚሸረሸር፣ የሚሰረስር፣ የሚቦረቡር፣ የሚደረምስ፣ የሚያጠለሽ... ይለዋል። መዝገበ ቃላቱ ይሄን ሁሉ ነገር ከሚያንዛዛ በቀላሉ መግለፅ ይችል ነበር ልክ እንደዚህ፣
ሸረኛ፡- ሰው አቶ እጅጉ ! በቃ! አጭር ግልፅና ወቅታዊ ፍቺ !!
ምሳሌ፣ አቶ እጅጉ ሸረኛ ነው። ትክከል !! ይሄ ምሳሌ አይደለም፣ እጅጉ (እጅ እግሩን አስሮ
ሲኦል ይወርውረውና) 'ሸረኛ' ነው፡፡ ሸረኛ ብቻ አይደለም፣ ምቀኛም ነው፡፡ የሚቀናበት ነገር
ሲያጣ እኩል በተሰጠን 24 ስዓት ይቀናል፡፡ (“እንደው በየትኛው ጊዜ ብትማሩት ነው ይሄን ሁሉ ነገር ያወቃችሁት?” ይላል የማያውቀውን ነገር አውቀን ካገኘን፡፡ ለነገሩ እሱ ምንም
አያውቅም፡፡) ምን ይሄ ብቻ! እግዜር በፈጠረው አየር ሳይቀር ይቀናል፤ የቢሯችን መስኮት
ተከፍቶ እንደልብ አየር ሲገባ ብቅ ይልና፤ ይሄን አየር በነፃ ትሉታላችሁ” ይላል፡፡ እንከፈል?
ሸረኛም ምቀኛም ብቻ አይደለም መሰሪ ተንኮለኛም ነው:: አሟልቶ አይሰጥም' ይባላል አንጂ
ይሄው የተሟላ ክፉ ሰው፡፡
እንግዲህ ሸረኛ፣ ምቀኛ፣ መሰሪ ሆኖ ደግሞ አለቃዬም ነው፡፡ ጥሎበት አይወደኝም፡፡ እኔም
ሰለማልወደው ተመስገን ቢወደኝ ምን ይውጠኝ ነበር?' እላለሁ ሁልጊዜ፤ ለምወደው ሰው
ነው የምጨነቀው፡፡ አሁን በዚች ቅፅበት በሆነ አጋጣሚ ነገር ሎተሪ ምናምን ኣይነት እድል
ገጥሞኝ በድንገት የብዙ ኢ ቢሆን የመጀመሪያ ሥሪዬ ሁለት እጆቼን ኪስና ኪሴ ከትቼ በቀዳዳ ኪሴ ውስጥ በሾለኩ ጣቶቼ ራቁት ታፋዩን በማፏጨው ሙዚቃ 'ሪትም' እየተመተምኩ ጀነን ብዪ ወደ አለቃዬ ቢሮ ሄድና አንኳኳለሁ፣ ኖ..ኖ.አላንኳኳም፤ በሩን በእግሬ ገፋ አድርጌው እገባለሁ፡፡ (ካፈቀሩ ከነፍስ፣ ከጠሉም ከነፍስ ነው የምን ማስመሰል) ፊት ለፊት፣ ጉማሬ ፊቱ አለቃዬ ሁልጊዜ በሚደፈርሱ አስቀያሚ ደመኛ አይኖቹ ያፈጥብኛል። ቀጥሎ ኪሶቼ ውስጥ የወሸቅኳቸውን እጆቼን በቁጣ ያያል፤ (ደንግጨ
ከኪሲ እንዳወጣቸው እንድርበተቡት፡፡) ፀጥ ብዪ በትዕቢት ሳየው የኢትዮጵያን ሲጋራ ሁሉ ብቻውን ያጨሰ ከሚያስመስሉት አስቀያሚና ገጣባ ከንፈሮቹ ቃላት ደፈለፈላሉ፤ ሰው ሰው የማይሸቱ እብሪተኛ ቃላት፡፡
ምናልባትም፣ “ብላችሁ ብላችሁ ማንኳኳቱንም ተዋችሁት." ይል ይሆናል፡፡ (እግዜርና ሰይጣን
ለዚህች ቅፅበት እርቅ አውርደው ይሄን ድንጋይ ራስ ኣለቃዬን በመዶሻ ያንኳኩትና።) ወይም
“ኪስህ የወሸቅከውን እጅህን አውጣ!" ሊልም ይችላል፣ አላወጣም !(ኪሴ ቀዳዳ ሲሆን
ቀዳዳውን ተሻግሮ ያለም ወንድነት የራሴ ርስት ነው . ዘራፍ ! በቀዳዳ እኛነታችን ውስጥ እያለፈ ወንድነታችንን ያኮላሹን ክፉዎች ሁሉ ከዛሬ ጀምሮ አድርጉ ያሉትን አናደርግም፡፡
ኮራ ብዬ "እእእእ አቶ እጅጉ” እለዋለሁ፡፡ (“አቶ" በማሾፍ ሲጠራ እንዴት ያለ አሪፍ ስድብ ነው፡፡) ለምሳሌ፣ እኔ "አቶ” ከሚለው ቅፅል ይልቅ ከስሜ በፊት ሰሃራን የሚያህል ባዶ ምድረ በዳ ቢዘረጋ ይሻለኛል፡፡ በተለይ አለቃዬ "አቶ" ከሚለኝ ። ...አዎ ! እሱ "አቶ"
ሲለኝ በውስጡ “መቼም ለአቶነት አትበቃም በቸርነቴ 'ከቶ'ነት ልስጥህ እሰቲ” የሚል ይመስልበታል፡፡ አቷም።
እና አቶ እጅጉ ከዛሬ ጀምሮ ሥራ ለቅቄያለሁ” እለዋለሁ በኩራት፡፡ 'እእእእ' የምትለዋን ዘገምተኛ ቃል ማስቀደም አልረሳም፡፡ አራት ዓመት ሙሉ የሱን አስቀያሚ እእእ' ችዬ ኖሬ የለ ስለዚህ የምለው እንደዚህ ነው:: “እእእእ.አቶ እጅጉ ከዛሬ ጀምር...እእእእ ሥራ ለቅቄያለሁ !”
ይደነግጣል፣ አያምንም፡፡ እኔ ስፈጋ የዋልኩበትን ሥራ ሁሉ ለአለቆቹ እንዲህ ሠርቼው እንዲህ
አድርጌው እያለ በስልክ መወሽከቱ ሊቆም ሲሆነ ይደነግጣል እሰይ ! ወሽካቶች መደንገጥ አለባቸው።
ወዲያው የበሰበሰ የማኔጅመንት 'ሲስተሙን' እኔ ላይ ሊሞክራት ይፍገመገማል፣ “አትደነግጥ
የበታች ሠራተኛህ ፊት አዋቂ፣ ልብ ሙሉ ምንትስ ሆነህ ቅረብ፣ ባትሆንም ሁን…” የምትለዋን
ያስብና ጉሮሮውን ጠራርጎ፣ “እእእ….እዚህ መሥራቱ ራስህን ለማሳደግም ሆነ ቤተሰብህን ለመርዳት አይሻልህም? ይላል፡፡ ሥራ ብለቅ ቤተሰቦቼ በረሃብ ዛሬውኑ የሚያልቁ በሚያስመስል ሁኔታ 'ቤተሰብ የምትለዋ ቃል ላይ አፅንኦት ሰጥቶ፡፡
ከፉዎች መሳሪያ ልጅህ ላይ ባይደግኑም፡ እናትና አባትህን አፍነው ባይወስዱም፣ የነገን ጨለማነት እየነገሩ ያግቱUል፡፡ ስንቱ መሰለህ ቁራጭ ዳቦ እንዳይነሱት ፈርቶ ለማንም አጋሰስ ጉልበቱን የሚገፈግፈው፤ ስንቱስ ነው ' ከሥራ መባረር የሚባል የታንክ አፈ ሙዝ ልቡ ላይ ተደግኖበት ዘመናዊ ባርያ የሆነው !! ስንቷን ሚስኪን በፀሃፊነት ስም የጭን ገረዱ ያደረጋት ጋንጩር አለ ቢሮ ይቁጠረው !
ሀላፊ ሲባል አርቲስት ነው፡፡ ወንበሩን መድረክ ያደረገ ተዋናይ፡፡ ያውም ድብን ያለ ትራጀዲ
የሚተውን፡፡ እና እኔ ምን እለዋለሁ ሃሳቤ ደስ ብሎኝ ሳምሰላስል፣ ዙፋን ዘው ብላ ወደ ቢሮዬ
ገባች፡፡ ጥሎባት ማንኳኳት አትወድም፡፡ 'እንኳኪ!' ብሏት የሚያውቅም የለም፡፡
"ብርሽዩ” ትለኛለች፡፡ (ስሟን ከነአያቷ ቄስ ይጥራትና) ! ሁልጊዜ ስትጠራኝ እንዲሁ ነው፡፡ ታዲያ አጠራርዋ ከማማሩ ብዛት እኔን ለጠራችኝ ሌሎቹ 'ወይዬ' ሊሏት ይዳዳቸዋል፡፡
እንዲህ በሀሳብ ጭልጥ ያልከው ወዴት ሄደህብኝ ነው?” ወዴትስ ብሄድ ምን አገባት፡፡ ጭራሽ
የምሄደውስ የምቀረውስ ለሷ ነው እንዴ? (ሄደህብኝ !! ጥርግ ብል እንትናዬ እያለች አንዱ ቢሮ ልትንኳተት፡፡
"እ..ምነው ጠፋሽ?” አልኩ እንደመጣልኝ፡፡ የምለው አጥቼ እንጂ ዙፋን ደግሞ መቼ ጠፍታ
ታወቅና፡፡ በአንድ ጊዜ ሰባት ቢሮ ውስጥ የምትገኘውን ዙፋንን ጠፋሽ ማለት መሬትን “ምነው
በዚህ ሳምንት መዞርሽን አቆምሽ?” ብሎ ከመጠየቅ አይተናነስም፡፡
ሆሆ ከየት ተገኘሽ፣ አሁን እንኳን ስመጣ አራተኛዬ ነው” አለችና ከጠረጴዛዬ ፊት ለፊት ወንበር
ስባ ተቀመጠች፡፡ ወንበሩ ተንጫጫ፡፡ ጉርድ ቀሚሷ ቀይ ታፋዋን ወለል አድርጎ ያሳያል…..
ኤጭጭጭጭጭ!!
“ቆንጆ ናት” ይባላል፡፡ “ትሁት ናትም” ይሏታል። “የሰለጠነች፣ ሰው አከባሪ" የሚሏትም ብዙ
ናቸው፤ እንደው ባጠቃላይ እዚህ ቢሮ ዙፋንን ለማናገር፣ ለማቅረብ፣ ሲመቸው ወደ ኣልጋው
ጎትቶ አብሯት ለመጋደም የማይመኝ ያለ አይመስለኝም፡፡
ዙፋን እኛ ቢሮ ሥራ ስትጀምር ከሥራ ልምዷ ጋር ከእግዜር የተላከ “ከዛሬ ጀምሮ ያየ አመነዘረ፤ የሚለው ጥቅስ ተሰርዟል” የሚል ደብዳቤ ይዛ የመጣች ይመስል፣ እዛ ፋይናንስ ከሚሠራው ዲያቆን ወልዱ ጀምሮ ሰው ሰላም ሲል እገጩ መሬት እስኪነካ የሚያጎነብሰው ጴንጤው ምክትል ኃላፊያችን የዙፋንን እግርና መቀመጫ አይተን እንሙት አሉ፡፡ ዙፋንም ታዲያ የዕለት እንጀራዋ የሰው አይን ይመስል ነገረ ሥራዋ ሁሉ የታይታ ነው፡፡ አቤት መታየት ስትወድ፡፡ ሰው ከኋላዋ እንደሚያያት ከጠረጠረች ለከፉ ቀን ያስቀመጠችውን መቆናጠር ሁሉ ትጠቀምበታለች፡፡
👍26🔥1
ጥሎብኝ አልወዳትም፣ እሷም ታውቀዋለች፤ ምንም ትልበስ፣ እንዴትም ትራመድ እንደገለባ
ትቀልብኛለች፡፡ ብትሞት ቢሮዬን ሳትረገጥ አትውልም ዛሬስ እንዴት ነኝ? ኣይነት፡፡ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ፀሃፊ ናት፡፡ ቅርብ ጊዜ ነው የተቀጠረችው ሃሃሃሃ ወይ መቀጠር፣ ቅጥር ነፍሰ ገዳይ።
የአለቃዩ አለቃ ፀሃፊ ናት፡፡ የተመቻት የሃብታም ልጅ፤ ቤት ከመዋል ብላ ፀሃፊ የሆነች። እሷ "ፀሃፊ” ሲሷት አትወድም፣ ሴክሬታሪ ነኝ ነው የምትለው፡፡ ውድ ልብሶችን የምትለብስ፣
በተረከዘ ረጅም ጫማ ከቢሮ ቢሮ ስታውደለድል የምትውል ቆንጆ እንዴት ፀሃፊ ትባላለች? የሚያማልሉ ቀያይ እግሮች ያሏት፣ የከረመና የታጀለ የወረቀት ጠረን የሞላውን ቢሮ በሽቶዋ የምትፈውስ ዙፋን እንዴት 'ፀሃፊ' ትባላለች? ገና ሳያት እንደረዥምና እንደማያልቅ መንገድ ትደከመኛለች፤ እንደ ረዥም
ለዛ ቢስ ወሬ ትሰለቸኛለች፡፡ ከልቤ ትሰለቸኛለች፡፡ ባትመጣብኝ ደስታዬ ነው፡፡ ይሄንን ነገር
ማመን አልቻለችም፡፡ በሕይወት ዘመኗ እንደኔ ፊት ነስቷት የሚያውቅ ወንድ ያለም አይሰለኝም፡፡
…ትለዋለች በተዘዋዋሪ፣ -..እከሌ እኮ ጨዋ ነው፤ የኔ ጌታ እሱን ያገባች የታደለች፡፡ቢሮው ስሄድ
ከወንበሩ ብድግ ብሎ ሥራውን እርግፍ አድርጎ ትቶ እኮ ነው የሚያዋራኝ ." እንኳን ተነሳላት
ለምን ከመነሳት አልፎ ዘሎ ኮርኒሱ ጋር አይጋጭም፡፡ እንኳን ለደቂቃ ሥራ ማቆም፣ ለምን
የሥራ መልቀቂያ አያስገባላትም፡፡ አዝግ፣ ታዝገኛለች፡፡ ኮተታም ከብር አሳዳጅ፡፡
የጠላሁባት ምክንያት እንደ አንዳንድ ወንዶች ከራሳቸው ጋር ፈተና ሲገቡ መሻታቸውን ሲሸሹ ሴት እንደሚያንቋሽሹት አይነት አይደለም፡፡ ቁልጭ ያለ አገር ያወቀው ፀሐዪ ያገረረው፣ በአምባገነን እግሯ ምንም በሆነ ሴትነቷ፣ ፍትህ ትረግጣለች፣ ያማረችው በሚስኪኖች እንባ ታጥባ ነው:: ንፅህናዋ ንፁህ ነፍሳትን ትቢያ አድርጋ ነው፡፡ ያውም ራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ሚስኪኖችን፡፡ ሸረኛ ናት፡፡ ዙፋን ሸረኛ ናት፡፡ አለቃዬ
ሸረኛ ነው፡፡ እዚህ የተሰበሰሱ ወተፈናም ኃላፊ ተብዬዎች ሁሉ ሸረኞች ናቸው:: እና፣
መዝገበ ቃላቱ፣ እና የምትለዋን ቃል አያያዥ፣ ብቻዋን የማትቆም ቁንፅል ይላታል፡፡ በአጭር
ምስሌ "እና እኔ ነኝ፡፡ በሸረኞቹ እና በደህነኞቹ መሀል ያለውኑ ወይ አልሸርር ወይ አልደህንን
“እና” እኔ ነኝ፡፡ ምንም ታሪክ፣ ምንም ትርጉም የለኝም፡፡ሥራዬም ባህሪዬም የሆኑ ነገሮች መሐል
መደበቅ ይበዛበታል “እና” ነኝ !! እና ምን ይጠበሰ፡፡
ደህና፣ እማማ መለኮት መዝገበ ቃላቱ ሳይሆን መዝገበ እግዚሃር “ደህና” ብሎ የሚላቸው
አይነት ናቸው፡፡ እማማ መለኮት እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ወይም ሃምሳ ሰባት (እራሳቸው
እንደሚሉት)፣ ትሁት፣ በዚህ እድሜያቸው ለሁሉም ሰው ታዛዥ እና የሁላችንም መካሪ፡፡
እማማ መለኮትን የማይወድ ማንም የለም. መስፈሪያው ቢለያይም፡፡ ምንም ይሰፈር በምን፡ እንደኔ የሚወዳቸው ግን የለም፡፡
የዛሬ ዓመት አካባቢ እማማ መለኮት ቢሮዬ መጥተው ከጠረጴዛዬ አንድ ሁለት እርምጃ ራቅ ብለው ቆሙና ከወገባቸው ጎንበስ በማለት ሰላምታ አቀረቡ፡፡ ያረጁ ይመስላሉ፡፡ ፊታቸው
በሀዘን አኮፍኩፎ በእድሜ እናቴን ይበልጣሉ፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁላቸው፡
በሁለት እጆቻቸው አሁንም ጎንበስ ብለው ሰላም አሉኝ፣ እጃቸው ይሻክራል፡ ልክ እንደ እናቴ....
✨ነገ ይለቅ✨
ትቀልብኛለች፡፡ ብትሞት ቢሮዬን ሳትረገጥ አትውልም ዛሬስ እንዴት ነኝ? ኣይነት፡፡ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ፀሃፊ ናት፡፡ ቅርብ ጊዜ ነው የተቀጠረችው ሃሃሃሃ ወይ መቀጠር፣ ቅጥር ነፍሰ ገዳይ።
የአለቃዩ አለቃ ፀሃፊ ናት፡፡ የተመቻት የሃብታም ልጅ፤ ቤት ከመዋል ብላ ፀሃፊ የሆነች። እሷ "ፀሃፊ” ሲሷት አትወድም፣ ሴክሬታሪ ነኝ ነው የምትለው፡፡ ውድ ልብሶችን የምትለብስ፣
በተረከዘ ረጅም ጫማ ከቢሮ ቢሮ ስታውደለድል የምትውል ቆንጆ እንዴት ፀሃፊ ትባላለች? የሚያማልሉ ቀያይ እግሮች ያሏት፣ የከረመና የታጀለ የወረቀት ጠረን የሞላውን ቢሮ በሽቶዋ የምትፈውስ ዙፋን እንዴት 'ፀሃፊ' ትባላለች? ገና ሳያት እንደረዥምና እንደማያልቅ መንገድ ትደከመኛለች፤ እንደ ረዥም
ለዛ ቢስ ወሬ ትሰለቸኛለች፡፡ ከልቤ ትሰለቸኛለች፡፡ ባትመጣብኝ ደስታዬ ነው፡፡ ይሄንን ነገር
ማመን አልቻለችም፡፡ በሕይወት ዘመኗ እንደኔ ፊት ነስቷት የሚያውቅ ወንድ ያለም አይሰለኝም፡፡
…ትለዋለች በተዘዋዋሪ፣ -..እከሌ እኮ ጨዋ ነው፤ የኔ ጌታ እሱን ያገባች የታደለች፡፡ቢሮው ስሄድ
ከወንበሩ ብድግ ብሎ ሥራውን እርግፍ አድርጎ ትቶ እኮ ነው የሚያዋራኝ ." እንኳን ተነሳላት
ለምን ከመነሳት አልፎ ዘሎ ኮርኒሱ ጋር አይጋጭም፡፡ እንኳን ለደቂቃ ሥራ ማቆም፣ ለምን
የሥራ መልቀቂያ አያስገባላትም፡፡ አዝግ፣ ታዝገኛለች፡፡ ኮተታም ከብር አሳዳጅ፡፡
የጠላሁባት ምክንያት እንደ አንዳንድ ወንዶች ከራሳቸው ጋር ፈተና ሲገቡ መሻታቸውን ሲሸሹ ሴት እንደሚያንቋሽሹት አይነት አይደለም፡፡ ቁልጭ ያለ አገር ያወቀው ፀሐዪ ያገረረው፣ በአምባገነን እግሯ ምንም በሆነ ሴትነቷ፣ ፍትህ ትረግጣለች፣ ያማረችው በሚስኪኖች እንባ ታጥባ ነው:: ንፅህናዋ ንፁህ ነፍሳትን ትቢያ አድርጋ ነው፡፡ ያውም ራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ሚስኪኖችን፡፡ ሸረኛ ናት፡፡ ዙፋን ሸረኛ ናት፡፡ አለቃዬ
ሸረኛ ነው፡፡ እዚህ የተሰበሰሱ ወተፈናም ኃላፊ ተብዬዎች ሁሉ ሸረኞች ናቸው:: እና፣
መዝገበ ቃላቱ፣ እና የምትለዋን ቃል አያያዥ፣ ብቻዋን የማትቆም ቁንፅል ይላታል፡፡ በአጭር
ምስሌ "እና እኔ ነኝ፡፡ በሸረኞቹ እና በደህነኞቹ መሀል ያለውኑ ወይ አልሸርር ወይ አልደህንን
“እና” እኔ ነኝ፡፡ ምንም ታሪክ፣ ምንም ትርጉም የለኝም፡፡ሥራዬም ባህሪዬም የሆኑ ነገሮች መሐል
መደበቅ ይበዛበታል “እና” ነኝ !! እና ምን ይጠበሰ፡፡
ደህና፣ እማማ መለኮት መዝገበ ቃላቱ ሳይሆን መዝገበ እግዚሃር “ደህና” ብሎ የሚላቸው
አይነት ናቸው፡፡ እማማ መለኮት እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ወይም ሃምሳ ሰባት (እራሳቸው
እንደሚሉት)፣ ትሁት፣ በዚህ እድሜያቸው ለሁሉም ሰው ታዛዥ እና የሁላችንም መካሪ፡፡
እማማ መለኮትን የማይወድ ማንም የለም. መስፈሪያው ቢለያይም፡፡ ምንም ይሰፈር በምን፡ እንደኔ የሚወዳቸው ግን የለም፡፡
የዛሬ ዓመት አካባቢ እማማ መለኮት ቢሮዬ መጥተው ከጠረጴዛዬ አንድ ሁለት እርምጃ ራቅ ብለው ቆሙና ከወገባቸው ጎንበስ በማለት ሰላምታ አቀረቡ፡፡ ያረጁ ይመስላሉ፡፡ ፊታቸው
በሀዘን አኮፍኩፎ በእድሜ እናቴን ይበልጣሉ፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁላቸው፡
በሁለት እጆቻቸው አሁንም ጎንበስ ብለው ሰላም አሉኝ፣ እጃቸው ይሻክራል፡ ልክ እንደ እናቴ....
✨ነገ ይለቅ✨
👍26
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ማሪየስ
ጋርቡለስ
ዣን ቫልዣና ኮዜት ገዳም ከገቡ ከስምንት ወይም ከዘጠኝ ዓመት
በኋላ አንድ ያልተጠበቀ ነገር ይሆናል፡፡ የአሥራ አንድ ወይም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ የተቀዳደደ የትልቅ ሰው ጫማና ልብስ አድርጎ ዋና ጎዳና ላይ ይንቀዋለላል፡፡ ይህ ልጅ ልብሱን ያገኘው ከአባቱ ወይም ከእናቱ
ሳይሆን ለነፍሴ ብሎ ካደረ መንገደኛ ነው፡፡ እናትና አባቱ ግን በሕይወት አሉ፡፡ አባቱ ስለልጁ ደንታ የለውም ፤ እናቱም ብትሆን እስከዚህም አትወደውም:: ይህ ልጅ እናትና አባት እያላቸው ቤተሰቦቻቸው የትም
እንደሚጥልዋቸው እንደማናቸውም ልጆች የሚታዘንለት ልጅ ነበር::
ልጁ መንገድ ለመንገድ በሚዞርበት ጊዜ በጣም ደስ ይለዋል።መንገድ ላይ የተነጠፈው ድንጋይ እንደ እናቱ ልብ ደንድኖና ጠጥሮ አይቆረቁረውም:: እናትና አባቱ ከቤት አስወጥተው የትም ጥለውታል።
ልጁ በጣም ንቁ፤ ቀልጣፋና ጮካ ልጅ ቢሆንም ታሞ የዳነ ይመስል ሰውነቱ ከመገርጣት አልፎ ክስት ብሏል፡፡ ይሮጣል፤ ይዘላል፤ ይጫወታል፧ ይዘፍናል ፧ የማያደርገው ነገር የለም:: ሲያመቸው ይሠርቃል፧ ሳያመቸው
ይለምናል:: አለዚያም ይቆምራል፡፡ ከጮሌነቱ ብዛት «ልጅ» እያሉ ሲጠሩት ከመቅጽበት ከተፍ ይላል፡፡ የሚለብሰው ልብስ፤ የሚበላው ምግብና
የሚጠለልበት ማደሪያ ወይም ደግሞ የሚወደውና የሚያፈቅረው ሰው የለውም:: ነገር ግን ነፃ ሆኖ በመኖሩ ደስተኛ ነው::
ከእንደነዚህ ያሉ ሰዎች ላይ ኅብረተሰቡ ይጨክናል፡፡ ከጭካኔው ብዛት አድቅቆ ይፈጫቸዋል፡፡ ግን ልጆች ከዚህ አይነቱ ጭካኔ አልፎ አልፎ
ያመልጣሉ:: ትንንሽ ልጆች በመሆናቸው በመጠኑም ቢሆን ህብረተሰቡ ስለሚያዝንላቸው ያልፋቸዋል:: ልጆቹም ማምለጫ ቀዳዳ አያጡም፡፡
ሆነም ቀረም፤ ይህ ብቸኛ ልጅ በየሁለት ወይም ሦስት ወር «አሁንስ እናቴ ጋ እሄዳለሁ» እያለ በየጊዜው ለራሱ ቃል ይገባል:: ወደዚያው ለመሄድ መንገድ ጀምሮ ከተወሰነ ሥፍራ ሲደርስ ‹‹
አሁንስ ወዴት ነው የምሄደው?» በማለት ራሱን በመጠየቅ ይቆማል፡፡ ቆም ብሎ ራሱን የጠየቀው ከአሁን ቀደም ከጠቀስነው ቁጥሩ 50-52 ከሆነ ቤት በራፍ ነበር፡፡
በተጠቀሰው ጊዜ ቤቱ ላይ «የሚከራዩ ክፍሎች» የሚል ጽሑፍ ከበሩ ላይ ተንጠልጥሎአል፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ ሥፍራ ክፍል በተከራየበት
ጊዜ የነበረችው የቤቱ ጠባቂ ሞታለች:: ልክ እርስዋን የምትመስል ሴት ተተክታ ትሠራለች:: ስምዋ ማዳም ቡርዧ ይባላል::
ከዚያ ቤት ውስጥ ክፍል ከተከራዩት ሰዎች መካከል አንዱ አራት ቤተሰብ ያለው መናጢ ድሃ ይገኝበታል:: እነዚህ እናት፣ አባትና ለአቅመ ሔዋን የደረሱ ሁለት ሴቶች ልጆች የሚኖሩት ከአንድ ክፍል ውስጥ ነው::መንገድ ለመንገድ የሚንከራተተውም ልጅ የዚህ ቤተሰብ ልጅ ነበር፡፡ ልጁ
ከዚያ ቤት ሲደርስ የቆመው ልግባ ወይስ አልግባ በሚል የሕሊና ሙግት ምክንያት ነበር።
ቢገባ ያው ኩርፊያና ዱላ ነው የሚጠብቀው፡፡ የመጀመሪያው ጥያቄ ደግሞ «ከየት መጣህ?» የሚል ይሆናል፡፡ መልሱም ‹‹ከበረንዳ» ይሆናል፡፡ተመልሶ ሲወጣ ደግሞ «የት ነው የምትሄደው?» ብለው ይጠይቁታል፡፡መልሱም «ወደ በረንዳ» ነው የሚሆነው፡፡ እናቱ፡ ይህን ጊዜ «ታዲያ አሁን
ለምን መጣህ?» ብላ ትጠይቀዋለች::
እውነተኛ የአባት ወይም የእናት ፍቅር ለምን እንደሆነ ስለማያውቅ ልጁ በዚ ቅር አይሰኝም። እናቱ የልጁን እህቶች በጣም ትወዳቸዋለች::ልጁ የሚጠራው በእውነተኛው አባቱ ስም ሳይሆን በሌላ ነው:: ምነው ቢሉ የዚህ ዓይነት የተበላሸና የተመሰቃቀለ ኑሮ የሚኖሩ ሰዎች ዘራቸውን መቁጠር አይፈልጉምና ነው::
እነዚህ ቤተሰቦች የሚኖሩበት ክፍል የሚገኘው ከአንድ ጥግ ሲሆን በሌላ አቅጣጫ ከጥግ ያለውን ክፍል የተከራየው ሰው ደግሞ ማሪየስ የሚባል ወጣት ነበር፡፡
ይህ ማሪየስ የተባለው ወጣት ማነው?
የታወቁ ቡርዥዋ
ፓሪስ ከተማ ውስጥ ለብዙ ዓመታት ከኖሩ ሰዎች መካከል አንዱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚባሉ አንድ ሽማግሌ ነበሩ:: በ183 1 ዓ ም «ለረጅም
ዘመን ኖረዋል» ተብለው ከሚጠቀሱት ሰዎች መካከል አንዱ እኚህ ሰው ናቸው፡፡ ሰውዬው እድሜያቸው በጣም በመግፋቱ «ትውልድ የተላለፈበት»የሚል የቅጽል ስም ይታወቃሉ፡፡ እኚህ ሰው በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን
ጥሩ የእውነተኛ ቡርዣዎች ርዝራዥ በመሆናቸው ብዙ ሀብት አላቸው::
ድሜያቸው ወደ ዘጠና ዓመት ይሆናል፡፡ ብዙ ጊዜ ቶሎ የመቆጣት ስሜት ይጠናወታቸዋል
ሲናገሩ ይጮሃሉ፡፡ በዚህ እድሜያቸው ብዙ ይጠጣሉ፤ ቀጥ ብለው ይራመዳሉ፡፡ ከሰላሳ ሁለት ጥርሶቻቸው መካከል አንዱ እንኳን ኣልወለቀም:: ዓይኖቻቸው አልደከሙም፧ ሲያነቡ ብቻ ነው መነጽር የሚያደርጉት:: ገቢያቸው ከፍተኛ ቢሆንም ድሃ እንጂ
ሀብታም ነኝ አይሉም:: አሽከሮቻቸውን መደብደብና ማንቋሸሽ ይወዳሉ::
ሃምሣ ዓመት ያለፋት ያላገባች ሴት ልጅ አለቻቸው፡፡ ሲከፋቸው ሴትዮዋን ከመቆጣት አልፈው ይገርፏታል፡፡ በእርሳቸው ዓይን ልጅቱ የሃምሣ ሳይሆን
የስምንት ዓመት ልጅ ናት::
ሰውዬው የሚኖሩት በራሳቸው ቤት ሲሆን ቤታቸው ባለ ብዙ ፎቅ
ነው:: ግቢው እጅግ በጣም ሰፊ ሲሆን በአሸበረቁ አበቦችና ዛፎች ተሸፍኖአል።ሽማግሌው በወጣትነት ዘመናቸው ብዙ ሴቶች አታልለዋቸዋል፡፡ ሆኖም
አሁንም ቢሆን በዘጠና ዓመታቸው ራሳቸውን ወጣት አድርገው ነው
የሚገምቱት:: አለባበሳቸውም እንደወጣት ነው፡፡ ነገር ግን በወጣቶች የሚመራውን የፈረንሳይ አብዮትን እጅግ በጣም ይነቅፋሉ:: እርሳቸው እየሰሙ አንድ ሰው የነገሥታትን አገዛዝ ነቅፎ ሪፐብሊክ የሚመሠረትበትን
ሁኔታ ቢናገር ፊታቸው ከመቅጽበት ደም ይለብሳል:: ይህን ሲሰሙ በጣም ስለሚቆጡ ራሳቸውን እስከ መሳት የሚደርሱበት ጊዜ ነበር፡፡
የወንድና የሴት አሽከሮች በብዛት አሉዋቸው:: ሠራተኞቹን በጎሣቸው
እንጂ በራሳቸው ስም አይጠሯቸውም:: ለምሳሌ አንድ ቀን አዲስ የወጥ ቤት ሠራተኛ ለመቅጠር ፈልገው ሰዎችን ያነጋግራሉ፡፡
«ደመወዝ ስንት ትጠይቂአለሽ?»
«ሰላሣ ፍራንክ›
«ስምሽ ማነው?»
«ኦሎምፒ»
«ሃምሣ ፍራንክ እንከፍልሻለን፤ ስምሽ ግን ኒኮሌት ይሆናል፡፡» (ኒኮሌት የአንድ ጎሣ ስም መሆኑ ነው፡፡)
ሁለት ሚስቶች ነበሩዋቸው:: ከሁለቱም አንዳንድ ሴት ልጅ ሲወለዱ አንደኛዋ ልጅ በሰላሣ ዓመትዋ ነው የሞተችው:: ባል አግብታ ነበር ባልዋን ያገባችው አፍቅራና ተፈቅራ ወይም በአጋጣሚ ይሁን አይታወቅም
ወታደር ነበር፡፡ በትልቅ እህትዋና በእርስዋ መካከል የአሥር ዐመት የዕድሜ ልዩነት ነበር:: ትንሽዋ ስታገባ ትልቅዋ ቆማ ትቀራለች:: ምናልባት በዚህ ምክንያት ሳይሆን አይቀርም፧ ትልቅዋ ልጅ ዘወትር ትተክዛለች፡፡የምትተክዝበትን ትክክለኛ ምክንያት ግን ከራስዋ በስተቀር የሚያውቀው የለም:: ሕይወትዋ በድን ለመሆኑ ፊትዋ ይመሰክራል፡፡
ከአባትዋ ጋር ነው የምትኖረው:: በታሪኩ መጀመሪያ ያየናቸው!
ጳጳስ ከእህታቸው ጋር እንዲኖሩ ሁሉ እኚህ ከበርቴ ደግሞ ከልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት፡፡ አንደኛው የሌላው ደጋፊ ነው::
ከቤቱ ውስጥ ከአባትና ልጅ ሌላ አንድ ልጅ ነበር፡፡ ይህ ልጅ
ተሽቆጥቁጦና ተንቀጥቅጦ ነው ያደገው፡፡ ሚስተር ጊልኖርማንድ ልጁን በቁጣ እንጂ በለዘበ አንደበት አናግረውት አያውቁም፡፡
«ና በል! ወሮበላ፤ ጥፋ፧ ሰማህ፤ ዱርዬ፤ መልስ እንጂ፤ አህያ»
( በእንደነዚህ ዓይነት ስሞች በቁጣ ሲጠሩት በእጃቸው ሰበቅ ይዘው ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ማሪየስ
ጋርቡለስ
ዣን ቫልዣና ኮዜት ገዳም ከገቡ ከስምንት ወይም ከዘጠኝ ዓመት
በኋላ አንድ ያልተጠበቀ ነገር ይሆናል፡፡ የአሥራ አንድ ወይም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ የተቀዳደደ የትልቅ ሰው ጫማና ልብስ አድርጎ ዋና ጎዳና ላይ ይንቀዋለላል፡፡ ይህ ልጅ ልብሱን ያገኘው ከአባቱ ወይም ከእናቱ
ሳይሆን ለነፍሴ ብሎ ካደረ መንገደኛ ነው፡፡ እናትና አባቱ ግን በሕይወት አሉ፡፡ አባቱ ስለልጁ ደንታ የለውም ፤ እናቱም ብትሆን እስከዚህም አትወደውም:: ይህ ልጅ እናትና አባት እያላቸው ቤተሰቦቻቸው የትም
እንደሚጥልዋቸው እንደማናቸውም ልጆች የሚታዘንለት ልጅ ነበር::
ልጁ መንገድ ለመንገድ በሚዞርበት ጊዜ በጣም ደስ ይለዋል።መንገድ ላይ የተነጠፈው ድንጋይ እንደ እናቱ ልብ ደንድኖና ጠጥሮ አይቆረቁረውም:: እናትና አባቱ ከቤት አስወጥተው የትም ጥለውታል።
ልጁ በጣም ንቁ፤ ቀልጣፋና ጮካ ልጅ ቢሆንም ታሞ የዳነ ይመስል ሰውነቱ ከመገርጣት አልፎ ክስት ብሏል፡፡ ይሮጣል፤ ይዘላል፤ ይጫወታል፧ ይዘፍናል ፧ የማያደርገው ነገር የለም:: ሲያመቸው ይሠርቃል፧ ሳያመቸው
ይለምናል:: አለዚያም ይቆምራል፡፡ ከጮሌነቱ ብዛት «ልጅ» እያሉ ሲጠሩት ከመቅጽበት ከተፍ ይላል፡፡ የሚለብሰው ልብስ፤ የሚበላው ምግብና
የሚጠለልበት ማደሪያ ወይም ደግሞ የሚወደውና የሚያፈቅረው ሰው የለውም:: ነገር ግን ነፃ ሆኖ በመኖሩ ደስተኛ ነው::
ከእንደነዚህ ያሉ ሰዎች ላይ ኅብረተሰቡ ይጨክናል፡፡ ከጭካኔው ብዛት አድቅቆ ይፈጫቸዋል፡፡ ግን ልጆች ከዚህ አይነቱ ጭካኔ አልፎ አልፎ
ያመልጣሉ:: ትንንሽ ልጆች በመሆናቸው በመጠኑም ቢሆን ህብረተሰቡ ስለሚያዝንላቸው ያልፋቸዋል:: ልጆቹም ማምለጫ ቀዳዳ አያጡም፡፡
ሆነም ቀረም፤ ይህ ብቸኛ ልጅ በየሁለት ወይም ሦስት ወር «አሁንስ እናቴ ጋ እሄዳለሁ» እያለ በየጊዜው ለራሱ ቃል ይገባል:: ወደዚያው ለመሄድ መንገድ ጀምሮ ከተወሰነ ሥፍራ ሲደርስ ‹‹
አሁንስ ወዴት ነው የምሄደው?» በማለት ራሱን በመጠየቅ ይቆማል፡፡ ቆም ብሎ ራሱን የጠየቀው ከአሁን ቀደም ከጠቀስነው ቁጥሩ 50-52 ከሆነ ቤት በራፍ ነበር፡፡
በተጠቀሰው ጊዜ ቤቱ ላይ «የሚከራዩ ክፍሎች» የሚል ጽሑፍ ከበሩ ላይ ተንጠልጥሎአል፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ ሥፍራ ክፍል በተከራየበት
ጊዜ የነበረችው የቤቱ ጠባቂ ሞታለች:: ልክ እርስዋን የምትመስል ሴት ተተክታ ትሠራለች:: ስምዋ ማዳም ቡርዧ ይባላል::
ከዚያ ቤት ውስጥ ክፍል ከተከራዩት ሰዎች መካከል አንዱ አራት ቤተሰብ ያለው መናጢ ድሃ ይገኝበታል:: እነዚህ እናት፣ አባትና ለአቅመ ሔዋን የደረሱ ሁለት ሴቶች ልጆች የሚኖሩት ከአንድ ክፍል ውስጥ ነው::መንገድ ለመንገድ የሚንከራተተውም ልጅ የዚህ ቤተሰብ ልጅ ነበር፡፡ ልጁ
ከዚያ ቤት ሲደርስ የቆመው ልግባ ወይስ አልግባ በሚል የሕሊና ሙግት ምክንያት ነበር።
ቢገባ ያው ኩርፊያና ዱላ ነው የሚጠብቀው፡፡ የመጀመሪያው ጥያቄ ደግሞ «ከየት መጣህ?» የሚል ይሆናል፡፡ መልሱም ‹‹ከበረንዳ» ይሆናል፡፡ተመልሶ ሲወጣ ደግሞ «የት ነው የምትሄደው?» ብለው ይጠይቁታል፡፡መልሱም «ወደ በረንዳ» ነው የሚሆነው፡፡ እናቱ፡ ይህን ጊዜ «ታዲያ አሁን
ለምን መጣህ?» ብላ ትጠይቀዋለች::
እውነተኛ የአባት ወይም የእናት ፍቅር ለምን እንደሆነ ስለማያውቅ ልጁ በዚ ቅር አይሰኝም። እናቱ የልጁን እህቶች በጣም ትወዳቸዋለች::ልጁ የሚጠራው በእውነተኛው አባቱ ስም ሳይሆን በሌላ ነው:: ምነው ቢሉ የዚህ ዓይነት የተበላሸና የተመሰቃቀለ ኑሮ የሚኖሩ ሰዎች ዘራቸውን መቁጠር አይፈልጉምና ነው::
እነዚህ ቤተሰቦች የሚኖሩበት ክፍል የሚገኘው ከአንድ ጥግ ሲሆን በሌላ አቅጣጫ ከጥግ ያለውን ክፍል የተከራየው ሰው ደግሞ ማሪየስ የሚባል ወጣት ነበር፡፡
ይህ ማሪየስ የተባለው ወጣት ማነው?
የታወቁ ቡርዥዋ
ፓሪስ ከተማ ውስጥ ለብዙ ዓመታት ከኖሩ ሰዎች መካከል አንዱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚባሉ አንድ ሽማግሌ ነበሩ:: በ183 1 ዓ ም «ለረጅም
ዘመን ኖረዋል» ተብለው ከሚጠቀሱት ሰዎች መካከል አንዱ እኚህ ሰው ናቸው፡፡ ሰውዬው እድሜያቸው በጣም በመግፋቱ «ትውልድ የተላለፈበት»የሚል የቅጽል ስም ይታወቃሉ፡፡ እኚህ ሰው በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን
ጥሩ የእውነተኛ ቡርዣዎች ርዝራዥ በመሆናቸው ብዙ ሀብት አላቸው::
ድሜያቸው ወደ ዘጠና ዓመት ይሆናል፡፡ ብዙ ጊዜ ቶሎ የመቆጣት ስሜት ይጠናወታቸዋል
ሲናገሩ ይጮሃሉ፡፡ በዚህ እድሜያቸው ብዙ ይጠጣሉ፤ ቀጥ ብለው ይራመዳሉ፡፡ ከሰላሳ ሁለት ጥርሶቻቸው መካከል አንዱ እንኳን ኣልወለቀም:: ዓይኖቻቸው አልደከሙም፧ ሲያነቡ ብቻ ነው መነጽር የሚያደርጉት:: ገቢያቸው ከፍተኛ ቢሆንም ድሃ እንጂ
ሀብታም ነኝ አይሉም:: አሽከሮቻቸውን መደብደብና ማንቋሸሽ ይወዳሉ::
ሃምሣ ዓመት ያለፋት ያላገባች ሴት ልጅ አለቻቸው፡፡ ሲከፋቸው ሴትዮዋን ከመቆጣት አልፈው ይገርፏታል፡፡ በእርሳቸው ዓይን ልጅቱ የሃምሣ ሳይሆን
የስምንት ዓመት ልጅ ናት::
ሰውዬው የሚኖሩት በራሳቸው ቤት ሲሆን ቤታቸው ባለ ብዙ ፎቅ
ነው:: ግቢው እጅግ በጣም ሰፊ ሲሆን በአሸበረቁ አበቦችና ዛፎች ተሸፍኖአል።ሽማግሌው በወጣትነት ዘመናቸው ብዙ ሴቶች አታልለዋቸዋል፡፡ ሆኖም
አሁንም ቢሆን በዘጠና ዓመታቸው ራሳቸውን ወጣት አድርገው ነው
የሚገምቱት:: አለባበሳቸውም እንደወጣት ነው፡፡ ነገር ግን በወጣቶች የሚመራውን የፈረንሳይ አብዮትን እጅግ በጣም ይነቅፋሉ:: እርሳቸው እየሰሙ አንድ ሰው የነገሥታትን አገዛዝ ነቅፎ ሪፐብሊክ የሚመሠረትበትን
ሁኔታ ቢናገር ፊታቸው ከመቅጽበት ደም ይለብሳል:: ይህን ሲሰሙ በጣም ስለሚቆጡ ራሳቸውን እስከ መሳት የሚደርሱበት ጊዜ ነበር፡፡
የወንድና የሴት አሽከሮች በብዛት አሉዋቸው:: ሠራተኞቹን በጎሣቸው
እንጂ በራሳቸው ስም አይጠሯቸውም:: ለምሳሌ አንድ ቀን አዲስ የወጥ ቤት ሠራተኛ ለመቅጠር ፈልገው ሰዎችን ያነጋግራሉ፡፡
«ደመወዝ ስንት ትጠይቂአለሽ?»
«ሰላሣ ፍራንክ›
«ስምሽ ማነው?»
«ኦሎምፒ»
«ሃምሣ ፍራንክ እንከፍልሻለን፤ ስምሽ ግን ኒኮሌት ይሆናል፡፡» (ኒኮሌት የአንድ ጎሣ ስም መሆኑ ነው፡፡)
ሁለት ሚስቶች ነበሩዋቸው:: ከሁለቱም አንዳንድ ሴት ልጅ ሲወለዱ አንደኛዋ ልጅ በሰላሣ ዓመትዋ ነው የሞተችው:: ባል አግብታ ነበር ባልዋን ያገባችው አፍቅራና ተፈቅራ ወይም በአጋጣሚ ይሁን አይታወቅም
ወታደር ነበር፡፡ በትልቅ እህትዋና በእርስዋ መካከል የአሥር ዐመት የዕድሜ ልዩነት ነበር:: ትንሽዋ ስታገባ ትልቅዋ ቆማ ትቀራለች:: ምናልባት በዚህ ምክንያት ሳይሆን አይቀርም፧ ትልቅዋ ልጅ ዘወትር ትተክዛለች፡፡የምትተክዝበትን ትክክለኛ ምክንያት ግን ከራስዋ በስተቀር የሚያውቀው የለም:: ሕይወትዋ በድን ለመሆኑ ፊትዋ ይመሰክራል፡፡
ከአባትዋ ጋር ነው የምትኖረው:: በታሪኩ መጀመሪያ ያየናቸው!
ጳጳስ ከእህታቸው ጋር እንዲኖሩ ሁሉ እኚህ ከበርቴ ደግሞ ከልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት፡፡ አንደኛው የሌላው ደጋፊ ነው::
ከቤቱ ውስጥ ከአባትና ልጅ ሌላ አንድ ልጅ ነበር፡፡ ይህ ልጅ
ተሽቆጥቁጦና ተንቀጥቅጦ ነው ያደገው፡፡ ሚስተር ጊልኖርማንድ ልጁን በቁጣ እንጂ በለዘበ አንደበት አናግረውት አያውቁም፡፡
«ና በል! ወሮበላ፤ ጥፋ፧ ሰማህ፤ ዱርዬ፤ መልስ እንጂ፤ አህያ»
( በእንደነዚህ ዓይነት ስሞች በቁጣ ሲጠሩት በእጃቸው ሰበቅ ይዘው ነው፡፡
👍20🥰1
ልጁ ዘወትር የሚሰማቸው ቃሎች ናቸው:: ሚስተር ጊልኖርማንድ ልጁን ልጁ ግን ሰውዬውን እንደ አምላክ ነው የሚያያቸው:: ልጁ የሽማግሌው የልጅ ልጅ ሲሆን ስለልጁ ወደፊት ብዙ እንሰማለን፡፡
አያትና የልጅ ልጅ
ቬርኖን ከተባለች ትንሽ ከተማ ያለፈ ሁሉ አንድ ወደ ሃምሣ ዓመት እድሜ ያለው ከእድሜው በላይ ያረጀ ፤ የተጨማደደ ቆብ ያጠለቀ፣ የተቦጫጨቀ ልብስ የለበሰ፤ ፊቱ በፀሐይ ብዛት የጠቆረ፤ ፀጉሩ የሸበተ፧
ፊቱ ላይ ትልቅ ጠባሳ ያለበት፧ ወገቡ የጎበጠ፤ ዘወትር አካፋና የአትክልት መከርከሚያ ይዞ የሚራመድ፤ ከሴን ወንዝ ድልድይ አካባቢ የማይጠፋ ሰው ሳያይ አያልፍም:: የተጠቀሰው ሰው በ1817 ዓ.ም. እጅግ በጣም
አነስተኛ ከሆነ ቤት ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ይህ ሰው በድኀነት እየማቀቀ ካንዲት አሮጊት አይልዋት ልጅ ፤ ቆንጆ አይልዋት ፉንጋ፧ ከበርቴ አይልዋት ድሃ፧ ከተሜ አይልዋት ገጠሬ ሴት ጋር ይኖራል፡፡ ሰውዬው ጠዋት ማታ
ከሚንከባከበው የአበባ ሥፍራ
ተለይቶ አያውቅም:: ኑሮውን የሚገፋው አበባ እየሸጠ ነው፡፡
ይህ ሰው በአፍላው ዘመን ጦር ሜዳ ትልቅ ጀብዱ የፈጸመ ሲሆን
ስሙ ጆርጅ ፓንትመርሲ ይባላል፡፡ በልጅነቱ በወታደርነት ተቀጥሮ ዋተርሉ ከተባለ ጦር ሜዳ ሠራዊት እየመራ ዘምቷል:: ጦር ሜዳ ላይ የጠላት መሣሪያ ማርኮና በደም ተበክሉ ከንጉሡ ፊት በቀረበ ጊዜ «አይ ጀግና
የጀግና ዘር ተብሎ ከተሞገሱ በኋላ የኰሎኔልነት ማዕረግና የጀግና ሜዳሊያ ሽልማት ይፈቀድለታል:: ማዕረጉና ሽልማቱ እንደተፈቀደለት
«ግርማዊ ሆይ! በባል አልባ ባለቤቴ ስም አመሰግናለሁ» ብሎ ይናገራል፡፡ይህንን ከተናገረ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሕሊናውን ስቶ ከመሬት ይዘረራል፡፡ ይህ
ጀግና ወታደር ነው ዛሬ የአበባ ሻጭ ሆኖ በችግር የሚማቅቀው::
ጆርጅ ፓንትመርሲ በጦርነቱ ስለተጎዳ እጅግ አነስተኛ የሆነ የጡረታ እበል ተፈቅዶለት ቬርኖን ከተማ እንዲመለስ ተደረገ፡፡ የሚያሳዝነው ንጉሡ
ቃላቸውን ረስተው ለሰውዬው ምንም እንኳን ሹመቱና ሜዳሊያው ቢሰጠውም እነዚህ ነገሮች ያስገኙት የነበረውን ጥቅም ሳያገኝ ቀረ፡፡ ሆኖም
ከቤቱ በወጣ ቁጥር የጀግንነት ሜዳልያውን ሳያደርግ አይወጣም::
የጡረታው ገንዘብ በጣም ትንሽ ስለነበር በጣም ዝቅተኛ የሆነ ቤት
ተከራየ:: በዚህ ጊዜ ነበር የከበርቴው መሴይ ጊልኖርማንድን ልጅ ያገባው::
የከበርቴው ልጅ ይህን ድሃ በማፍቀርዋ አባትዋ ከማዘን አልፈው በጣም ይናደዳሉ፡፡ ነገር ግን እርስዋ ከፈለገች መቼስ ምን ይደረጋል በሚል በጋብቻው
ተስማሙ:: የሚያሳዝነው ግን ሴትዮዋ ምንም እንኳን እጅግ ተናፋቂና ተወዳጅ ሴት ብትሆንም ብዙ አልኖረችም፡፡ በ1815 ዓ.ም ሕፃን ልጅ ከኋላዋ ትታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች:: ልጁ የኰሎኔሉን የብቸኝነት ኑር
ለመለወጥ የደስታ ምንጭ መሆን ይገባው ነበር፡፡ ግን ሊሆን አልቻለም ፤ምክንያቱም አያቱ «ልጁ ለእኔ ካልተሰጠኝ ሀብቴን አላወርሰውም» ስላሉ ልጁ ከአባቱ ተነጠለ፡፡ አባት ጥያቄውን የተቀበለው ለልጁ ሲል ነበር፡፡
የወለደውን ልጅ ለማግኘት ባለመቻሉ የልጁን ፍቅር በአበባ ፍቅር ለወጠው::
መሴይ ጊልኖርማንድ ከሴት ልጃቸው ባለቤት ጋር የቀረበ ግንኙነት አልነበራቸውም:: ለእርሳቸው ከሎኔሉ «ሽፍታ» ነው:: ኮሎኔሉም ሽማግሌውን ነገር እንደማይገባቸው «ደደብ» ሰው ነበር የሚያያቸው፡፡
መሴይ ጊልኖርማንድ ሁናቴ ካላስገደዳቸው ወይም ለመፎተት ካልሆነ በስተቀር ስለኰሎኔሉ ማንሳት አይፈልጉም:: አባት «ልጄን ካላየሁ ወይም
ካላነጋገርኩ» እያለ ቢያስቸግር ልጁ የአያቱን ሀብት ሊወርስ እንደማይችል ለኵሎኔሉ በቅድሚያ ተገልጾለታል፡፡ ኰሎኔሉ በዚህ መስማማቱ ምናልባት
ጥፋተኛ ሳይሆን አልቀረም፡፡ ግን ይህን ግዳጅ የተቀበለው ለልጁ በማሰብና የራሱን ደስታ በመሰዋት ሊሆን የወሰደው እርምጃ ትክክል መሆኑን ስላመነ ነው::
ልጁ በቀጥታ ከአያቱ ሊወርሰው የሚችለው ሀብት እስከዚህም ብዙ አልነበረም፡፡ ከእናቱ ታላቅ እህት ማለት ከከክስቱ ሊወርሰው የሚችለው ሀብት ግን እጅግ ብዙ ነበር፡፡ እክስቱ በእናትዋ በኩል የወረሰችው ብዙ ሀብት ነበራት:: የእህትዋ ልጅ ደግሞ ቀጥተኛ ወራሽ ነው:: የልጁ ስም ማሪየስ ይባላል:: ማሪየስ አባት እንዳለው ያውቃል:: ከዚያ ወዲያ ስለአባቷ
የሚያውቀው ነገር የለም:: እንዲያውም ከነአካቴው በአካባቢው የሚወራውን ወሬ ስለሰማ በአባቱ ያፍራል።.....
💫ይቀጥላል💫
አያትና የልጅ ልጅ
ቬርኖን ከተባለች ትንሽ ከተማ ያለፈ ሁሉ አንድ ወደ ሃምሣ ዓመት እድሜ ያለው ከእድሜው በላይ ያረጀ ፤ የተጨማደደ ቆብ ያጠለቀ፣ የተቦጫጨቀ ልብስ የለበሰ፤ ፊቱ በፀሐይ ብዛት የጠቆረ፤ ፀጉሩ የሸበተ፧
ፊቱ ላይ ትልቅ ጠባሳ ያለበት፧ ወገቡ የጎበጠ፤ ዘወትር አካፋና የአትክልት መከርከሚያ ይዞ የሚራመድ፤ ከሴን ወንዝ ድልድይ አካባቢ የማይጠፋ ሰው ሳያይ አያልፍም:: የተጠቀሰው ሰው በ1817 ዓ.ም. እጅግ በጣም
አነስተኛ ከሆነ ቤት ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ይህ ሰው በድኀነት እየማቀቀ ካንዲት አሮጊት አይልዋት ልጅ ፤ ቆንጆ አይልዋት ፉንጋ፧ ከበርቴ አይልዋት ድሃ፧ ከተሜ አይልዋት ገጠሬ ሴት ጋር ይኖራል፡፡ ሰውዬው ጠዋት ማታ
ከሚንከባከበው የአበባ ሥፍራ
ተለይቶ አያውቅም:: ኑሮውን የሚገፋው አበባ እየሸጠ ነው፡፡
ይህ ሰው በአፍላው ዘመን ጦር ሜዳ ትልቅ ጀብዱ የፈጸመ ሲሆን
ስሙ ጆርጅ ፓንትመርሲ ይባላል፡፡ በልጅነቱ በወታደርነት ተቀጥሮ ዋተርሉ ከተባለ ጦር ሜዳ ሠራዊት እየመራ ዘምቷል:: ጦር ሜዳ ላይ የጠላት መሣሪያ ማርኮና በደም ተበክሉ ከንጉሡ ፊት በቀረበ ጊዜ «አይ ጀግና
የጀግና ዘር ተብሎ ከተሞገሱ በኋላ የኰሎኔልነት ማዕረግና የጀግና ሜዳሊያ ሽልማት ይፈቀድለታል:: ማዕረጉና ሽልማቱ እንደተፈቀደለት
«ግርማዊ ሆይ! በባል አልባ ባለቤቴ ስም አመሰግናለሁ» ብሎ ይናገራል፡፡ይህንን ከተናገረ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሕሊናውን ስቶ ከመሬት ይዘረራል፡፡ ይህ
ጀግና ወታደር ነው ዛሬ የአበባ ሻጭ ሆኖ በችግር የሚማቅቀው::
ጆርጅ ፓንትመርሲ በጦርነቱ ስለተጎዳ እጅግ አነስተኛ የሆነ የጡረታ እበል ተፈቅዶለት ቬርኖን ከተማ እንዲመለስ ተደረገ፡፡ የሚያሳዝነው ንጉሡ
ቃላቸውን ረስተው ለሰውዬው ምንም እንኳን ሹመቱና ሜዳሊያው ቢሰጠውም እነዚህ ነገሮች ያስገኙት የነበረውን ጥቅም ሳያገኝ ቀረ፡፡ ሆኖም
ከቤቱ በወጣ ቁጥር የጀግንነት ሜዳልያውን ሳያደርግ አይወጣም::
የጡረታው ገንዘብ በጣም ትንሽ ስለነበር በጣም ዝቅተኛ የሆነ ቤት
ተከራየ:: በዚህ ጊዜ ነበር የከበርቴው መሴይ ጊልኖርማንድን ልጅ ያገባው::
የከበርቴው ልጅ ይህን ድሃ በማፍቀርዋ አባትዋ ከማዘን አልፈው በጣም ይናደዳሉ፡፡ ነገር ግን እርስዋ ከፈለገች መቼስ ምን ይደረጋል በሚል በጋብቻው
ተስማሙ:: የሚያሳዝነው ግን ሴትዮዋ ምንም እንኳን እጅግ ተናፋቂና ተወዳጅ ሴት ብትሆንም ብዙ አልኖረችም፡፡ በ1815 ዓ.ም ሕፃን ልጅ ከኋላዋ ትታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች:: ልጁ የኰሎኔሉን የብቸኝነት ኑር
ለመለወጥ የደስታ ምንጭ መሆን ይገባው ነበር፡፡ ግን ሊሆን አልቻለም ፤ምክንያቱም አያቱ «ልጁ ለእኔ ካልተሰጠኝ ሀብቴን አላወርሰውም» ስላሉ ልጁ ከአባቱ ተነጠለ፡፡ አባት ጥያቄውን የተቀበለው ለልጁ ሲል ነበር፡፡
የወለደውን ልጅ ለማግኘት ባለመቻሉ የልጁን ፍቅር በአበባ ፍቅር ለወጠው::
መሴይ ጊልኖርማንድ ከሴት ልጃቸው ባለቤት ጋር የቀረበ ግንኙነት አልነበራቸውም:: ለእርሳቸው ከሎኔሉ «ሽፍታ» ነው:: ኮሎኔሉም ሽማግሌውን ነገር እንደማይገባቸው «ደደብ» ሰው ነበር የሚያያቸው፡፡
መሴይ ጊልኖርማንድ ሁናቴ ካላስገደዳቸው ወይም ለመፎተት ካልሆነ በስተቀር ስለኰሎኔሉ ማንሳት አይፈልጉም:: አባት «ልጄን ካላየሁ ወይም
ካላነጋገርኩ» እያለ ቢያስቸግር ልጁ የአያቱን ሀብት ሊወርስ እንደማይችል ለኵሎኔሉ በቅድሚያ ተገልጾለታል፡፡ ኰሎኔሉ በዚህ መስማማቱ ምናልባት
ጥፋተኛ ሳይሆን አልቀረም፡፡ ግን ይህን ግዳጅ የተቀበለው ለልጁ በማሰብና የራሱን ደስታ በመሰዋት ሊሆን የወሰደው እርምጃ ትክክል መሆኑን ስላመነ ነው::
ልጁ በቀጥታ ከአያቱ ሊወርሰው የሚችለው ሀብት እስከዚህም ብዙ አልነበረም፡፡ ከእናቱ ታላቅ እህት ማለት ከከክስቱ ሊወርሰው የሚችለው ሀብት ግን እጅግ ብዙ ነበር፡፡ እክስቱ በእናትዋ በኩል የወረሰችው ብዙ ሀብት ነበራት:: የእህትዋ ልጅ ደግሞ ቀጥተኛ ወራሽ ነው:: የልጁ ስም ማሪየስ ይባላል:: ማሪየስ አባት እንዳለው ያውቃል:: ከዚያ ወዲያ ስለአባቷ
የሚያውቀው ነገር የለም:: እንዲያውም ከነአካቴው በአካባቢው የሚወራውን ወሬ ስለሰማ በአባቱ ያፍራል።.....
💫ይቀጥላል💫
👍23❤4🔥2
#ሸረኛ_እና_ደህና_በአንድ_ላይ
#ሲሄዱ_በሸረኛው_በኩል_ተናደ
#መንገዱ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ፊታቸው በሀዘን አኮፍኩፎ በእድሜ እናቴን ይበልጣሉ፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁላቸው፡
በሁለት እጆቻቸው አሁንም ጎንበስ ብለው ሰላም አሉኝ፣ እጃቸው ይሻክራል፡ ልክ እንደ እናቴ.
እነዚህ ሞረድ እጆች የስንቶቻችንን ባለ ለስላሳ እጆች ሆይወት እንደሞረዱ ፈጣሪ ይወቅ!
እንዲቀመጡ ወዳመለከትኳቸው ወንበር ቀስ ብለው ተቀመጡና የመጡበትን ጉዳይ ቀስ ብለው
እንደምታውቀው እዚህ ቤት ነገረ ሥራቸው ሁሉ ውስጥ ለውስጥ ነው:: ደከመኝ፣ ሰለቸኝ
አስረዱን፣ አቶ አብረሃም (አቤት አቶ በእሳቸው አንደበት እንዴት ክብር እንዳለው ) ያው እንደምታውቀው እዚህ ቤት ነገረ ስራቸው ሁሉ ውስጥ ለውስጥ ነው ደከመኝ ሰለችኝ ሳልል በሰራህ ለትንሽ ትልቁ 'እሺ' ብዬ ባደርኩ ድንገት ከሥራዬ ነቀሉኝ፡፡" አሉና እንባቸው ተዘረገፈ፡ እድሜ በሸነተረው የቆዳቸው እጥፋት ሽብሽብ ውስጥ እንባቸው ጎረፈ፡፡ በነጠላቸው ጫፍ እይናቸውን ጠረጉ፡፡ (እዚህች ባልቴት ውስጥ ይሄ ሁሉ እንባ እንዴት ሊኖር ቻለ? እድሜ ልካቸውን ያጠራቀሙት ይሆን?) እማማ መለኮት ከፅዳት የሥራ ገደብ ተነስተው በሀያ ዓመት የሰርክራሲ ባቡር ተጉዘው ፅሃፈ ለመሆን የበቁ ፅኑ ሴት ናቸው፡፡ ከልምድ እንዳየሁት ብዙ
ታላላቅ ድርጅቶች ሱፍ ለብሰው በሚኮፈሱት አለቆቻቸው ሳይሆን በሚስኪኖች ትከሻ ላይ
ተጭነው ነው የቆሙት፡፡ እማማ መለኮት የድርጅታችን ዋልታ ይሄው ተባረሩ፡፡
ከዛ በፊት፡ ከመባረራቸው በፊት፤ አሽሙር የሚመስል ስብሰባ ተደረገ፡፡ አንዲት ረዳት የሌላቸው
ሚስኪን ባልቴት ለማባረር ቱባ ቱባ ባለስልጣን፣ ከቱባው የተተረተሩ ክር አቃጣሪዎች እና እኛዎች" ውሃ ቡና ቀርቦ ስብሰባ ተደረገ፡፡የስብሰባው መሪ፣ "ሸረኛው" እጅጉ፣ ፀሃፊው “ሽረኛው"
አለሙ፣ ተላላኪው፣ ወሬ አቀባዩ (እንደ ሰው አልባ አውሮፕላን እያንዣበባ ሰላሉት አለቆቹ ወሬ ይቃርማል፡፡ “መታዘዝ ፅድቅ ነው” ሲባል የመታዘዝ ፅድቅነትን የማያመዛዝን አዕምሮ ተሸክሞ የሌሎች ባሪያ መሆን ማለት አይደለም፡፡ ሰብዓዊ ትዕዛዝ፣ ሰው መሆን ይቅርብሆ ተብለህ ሳይሆን፣ ለእኔ ማለት ይቆየኝ፣ ቅድሚያ ለሌሎች ከሚል በጎነት መነሳት ነው:: በጎነት በትዕዛዝ አይመጣም፡፡)
ስብሰባው ተጀመረ፡፡ ለአንዲት ባልቴት ተሰበሰቡ እንዳይባል የማይረባ አርሲ ኩርሲ አጀንዳ
ጋር ተደምሮ የእማማ መለኮት መባረር መቀነስ” የሚል የዳቦ ስም ተሰጥቶት አጀንዳ ሆነ፡፡
“ባንድ ላይ ሲሄዱ” መዝገብ ቃላቱ በአንድ ላይ መሄድን በአንድ ላይ ከመታየት ነጥሎ አለማየቱ ትልቅ ጉድለት ነው::
የሸረኛ፣ “እና” ና “ደህና” ስብሰባው ላይ በአንድ ላይ ተገናኘን፣ በማንኛችን በኩል መንገዱ እንደሚናድ ልናይ - ቀድሞ የተናደውን፡፡
“ተናደ"
ስብሰባውን የጀመረው አለቃችን አቶ እጅጉ ነበር፡፡ ኩፍስ ብሎ የኮቱ አጥፋት ሸብዳዳ ትከሻው ላይ ተከምሮ (ከኮቱ ውስጥ ትንሽ የሶፋ ትራስ ያስቀመጠ ይመስለኛል)፡፡ ጨዋ ለመምሰል በሚዳዳው ድምፅ ስብሰባው መጀመሩን አረዳ (አበሰረ የሚሉም አሉ “ከሸረኞች ወገን ናቸው)
እ...ያው እንደምታውቁት…" አለ (ምንም በማናውቀው ነገር) ...መሥሪያ ቤታችን ያለውን
መልካም ሰምና ዝና ለማስቀጠል (ሂሂሂሂ ጉድ ፈላ በቀን የሚመጣው ባለጉዳይ ሁሉ እዩዬ እያለ ተራግሞ የሚሄድበት መሥሪያ ቤት መልካም ስምና ዝና ይሁና) ዘመናዊ የአሠራር ሲሰተም
ዘመን አፈራሽ መሳሪያዎች እንደሚያስፈልጉ በማመን የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ወስደን
እየተንቀሳቀሰን 'ያለበት ሁኔታ ነው ያለው….
እነዚህ ዘመናዊ መሳሪያዎች ደግሞ ብቻቸውን ጠብ የሚል ለውጥ እንደማያመጡ እሙን
ነው፣ ስለዚህ ቢሯችንን 'በአመለካከት በእውቀት እና በተግባር ከመሳሪያዎቹ ጋር አብሮ
በሚሄድ ወጣት የሰው ኃይል ማደራጀቱ ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ተግባር ነውሸ
(እማማ መለኮት በኩል መንገዱ ተናደ:: ጨዋነትን የጫነው መኪና ገደል ገባ፡፡ ትህትና ተሽቀነጠረ፡፡ መንገድ ስለሌለ ወደኋላ ተመለስን፡፡ መንገድ አፍራሽ ሸረኞች ራእይ እንደ ህልም
ያያሉ፡፡ ከመድረስም ተጣልተዋል፡፡ መንገድ የለማ ...! ከአባይ ወዲያ ማዶ ያለ ዘመድ ሆነ የእማማ መለኮት ሥራ፣ እንባቸው በአይናቸው የሞላ እለት ዋይ ብለው ቀሩ፡፡
እንዲት በእድሜ የገፉ ሚስኪን አባሮ በየቢሮው እየዞረች ምስጋና የምትቀላውጥ ገልቱ
ለመቅጠር ምድረ ጉማሬ ሚስኪኑን ላብ አደር ሰብስቦ አላዘነ፡፡ ደግሞ ስላዘመናዊነት
ያወራሉ፣ እግዚኦ አለቆቻችን ስለዘመናዊነት አወሩ፡፡ስልካቸው ባትሪ ሲጨርስ ተበላሸ
ብለው ሠሪ ቤት የሚሮጡ አለቆቻችን ዘመናዊነትን ሰበኩ፡፡ ከፕሪንተር የሚወጣ ወረቀት ደመና ሰንጥቆ እንደሚወጣ መልአክ በግርምት የሚመለከቱ፡፡ (አይ ፈረንጅ ነፍስ መፍጠር እኮ ነው የቀረው!' እየተባባሉ፡፡) እለቆቻችን ዘመናዊ እንሁን አሉ፡፡
እማማ መለኮት በጡረታ ስም ተባረሩ፡፡ (ተቀነሱ በል አቶ አብረሃም ተብያለሁ፡፡) ዙፋን
ተቀጠረች አሁን ድርጅቱ ዘመናዊ ሆነ፡፡ “እንደምን ዋላችሁ…”፣ “ሃይ ጋይስ” በሚል ሰላምታ .
በመተካቱ እልልል ቢሯችን ዘመናዊ ሆነ፡፡
ዙፋን የዘመናዊነት ፋና ወጊ፣ አንድ ገፅ ደብዳቤ ስትፅፍ አንድ ከግማሽ ገፅ ስህተት የምትዘራ
ጉድ፡፡ ወሬ ብቻ መሽኮርመም ብቻ፣ በየሰሙ ላይ “ዬ" መጨመር ብቻ (አብርሽዬ..ቶማስዬ.
ጋሽ ሰይድዬ ተፈራዬ... ሐጎስዬ.. ገኒዬ..እግዚያብሄርዬ..ጂሰስዬ_) እንደ ዬ ፈደል ትልቅ አፍ ብቻ
ያላት መርገምት፡፡ደህና ነገር ሲናገር ከንፈሩ እንደደረቀ ሰው በየደቂቃው ቻፕስቲክ እየተለቀለቀች በየቢሮው ማውራት !! (ውይ ጥርስ አታስከድንም፤ ተጫዋች ምናምን ይሏታል የሸረኛው መንጋ፡፡
ቆንጆ ብቻ መሆን እንዴት ይቃፋል፡፡ ሴት ብቻ በመሆን ከወንድ የሚቻር ወሲባዊ ክብር ምንኛ ውድቀት ነው?! ዕድሜ ከፍ ባለ ቁጥር የሚናድ የእንቧይ ካብ፡፡ እንዴት ሰውን ያህል ፍጥረት
ያውም እናትነትን ያሀል አደራ ትቀበል ዘንድ ተፈጥሮ የወከለቻት ሴት ስለጥፍር አንድ ሰዓት ሙሉ ታወራለች? ስለፀጉር ሁለት ሰአት፣ ስለጥፍር ቀለም ሙሉ ሸን፣ስለ ልብስ...
የመታየት ልክፍት (ኤግዝቢሽኒያም ይለዋል በሬቻ)፡፡ በፋሽን ስም ነጋቸው ላይ ውበት ሊዘሩለት ሚችሉትን ዛሬ አርሲ ኩርሲ የውበት ኮተት እያወሩ ይፈጁታል፡፡ ይሄ የሴት ውበት ነው የሴት ብክነት፡፡ ስለውበት የሚደሰኩር ሚዲያ ላይ አፍጥጣ የምትውል ዙፋን፣ ቆዳዋን በምናምን አደንድና ፍቅር እንዳይስርአት ራሷን ሳታዋድድ ትኖራለች። ሴት ከምልክ የተሻለ መወዳደሪያ በሌላት ውድድሩ ውስጥም የምትኖረው ቢበዛ ለጥቂት ዓመታት ነው፡፡ ባካና ! ዙፋን ባካና ናት፤ ስሟ ራሱ እሷ ላይ ሲደርስ 'ዙፋን' የሆነ፣ የመወዘፍ አይነት ደውል ነው፡፡ (ውዝፍ ከሚለው ስረወ ቃል የመጣ)
ከአለቃዬ ጋር በአይኗ ስትዳራ ስንት ጊዜ ታዘብኩ፡፡ እማማ መለኮትን ነቅላ ላትፀድቅ ነገር
ራሷን የተከለችበትን ቆሻሻ መንገዷን አይቻለሁ፡፡ ለፀሃፊነት ሥራ ውድድር መሰለፍ የማይችል
ባልጩት ጨንቅላቷ ላይ ሰው ሰራሽ ፀር ጎዝጉዛ ክቡር ሴትነቷን በየቢሮው ስትጎዘጉዝ ሳናይ
አላወራንም፤ “ጭስ ካለ እሳት አለ” ብለንም እይደለም፡፡ ቆይቶ የተደረገ ግምገማ ላይ የተገደደች
አስመስላ ቀባጠረችው እንጂ፡፡ (የሸረኞች መንገድ የተናደች" እለት)
#ሲሄዱ_በሸረኛው_በኩል_ተናደ
#መንገዱ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ፊታቸው በሀዘን አኮፍኩፎ በእድሜ እናቴን ይበልጣሉ፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁላቸው፡
በሁለት እጆቻቸው አሁንም ጎንበስ ብለው ሰላም አሉኝ፣ እጃቸው ይሻክራል፡ ልክ እንደ እናቴ.
እነዚህ ሞረድ እጆች የስንቶቻችንን ባለ ለስላሳ እጆች ሆይወት እንደሞረዱ ፈጣሪ ይወቅ!
እንዲቀመጡ ወዳመለከትኳቸው ወንበር ቀስ ብለው ተቀመጡና የመጡበትን ጉዳይ ቀስ ብለው
እንደምታውቀው እዚህ ቤት ነገረ ሥራቸው ሁሉ ውስጥ ለውስጥ ነው:: ደከመኝ፣ ሰለቸኝ
አስረዱን፣ አቶ አብረሃም (አቤት አቶ በእሳቸው አንደበት እንዴት ክብር እንዳለው ) ያው እንደምታውቀው እዚህ ቤት ነገረ ስራቸው ሁሉ ውስጥ ለውስጥ ነው ደከመኝ ሰለችኝ ሳልል በሰራህ ለትንሽ ትልቁ 'እሺ' ብዬ ባደርኩ ድንገት ከሥራዬ ነቀሉኝ፡፡" አሉና እንባቸው ተዘረገፈ፡ እድሜ በሸነተረው የቆዳቸው እጥፋት ሽብሽብ ውስጥ እንባቸው ጎረፈ፡፡ በነጠላቸው ጫፍ እይናቸውን ጠረጉ፡፡ (እዚህች ባልቴት ውስጥ ይሄ ሁሉ እንባ እንዴት ሊኖር ቻለ? እድሜ ልካቸውን ያጠራቀሙት ይሆን?) እማማ መለኮት ከፅዳት የሥራ ገደብ ተነስተው በሀያ ዓመት የሰርክራሲ ባቡር ተጉዘው ፅሃፈ ለመሆን የበቁ ፅኑ ሴት ናቸው፡፡ ከልምድ እንዳየሁት ብዙ
ታላላቅ ድርጅቶች ሱፍ ለብሰው በሚኮፈሱት አለቆቻቸው ሳይሆን በሚስኪኖች ትከሻ ላይ
ተጭነው ነው የቆሙት፡፡ እማማ መለኮት የድርጅታችን ዋልታ ይሄው ተባረሩ፡፡
ከዛ በፊት፡ ከመባረራቸው በፊት፤ አሽሙር የሚመስል ስብሰባ ተደረገ፡፡ አንዲት ረዳት የሌላቸው
ሚስኪን ባልቴት ለማባረር ቱባ ቱባ ባለስልጣን፣ ከቱባው የተተረተሩ ክር አቃጣሪዎች እና እኛዎች" ውሃ ቡና ቀርቦ ስብሰባ ተደረገ፡፡የስብሰባው መሪ፣ "ሸረኛው" እጅጉ፣ ፀሃፊው “ሽረኛው"
አለሙ፣ ተላላኪው፣ ወሬ አቀባዩ (እንደ ሰው አልባ አውሮፕላን እያንዣበባ ሰላሉት አለቆቹ ወሬ ይቃርማል፡፡ “መታዘዝ ፅድቅ ነው” ሲባል የመታዘዝ ፅድቅነትን የማያመዛዝን አዕምሮ ተሸክሞ የሌሎች ባሪያ መሆን ማለት አይደለም፡፡ ሰብዓዊ ትዕዛዝ፣ ሰው መሆን ይቅርብሆ ተብለህ ሳይሆን፣ ለእኔ ማለት ይቆየኝ፣ ቅድሚያ ለሌሎች ከሚል በጎነት መነሳት ነው:: በጎነት በትዕዛዝ አይመጣም፡፡)
ስብሰባው ተጀመረ፡፡ ለአንዲት ባልቴት ተሰበሰቡ እንዳይባል የማይረባ አርሲ ኩርሲ አጀንዳ
ጋር ተደምሮ የእማማ መለኮት መባረር መቀነስ” የሚል የዳቦ ስም ተሰጥቶት አጀንዳ ሆነ፡፡
“ባንድ ላይ ሲሄዱ” መዝገብ ቃላቱ በአንድ ላይ መሄድን በአንድ ላይ ከመታየት ነጥሎ አለማየቱ ትልቅ ጉድለት ነው::
የሸረኛ፣ “እና” ና “ደህና” ስብሰባው ላይ በአንድ ላይ ተገናኘን፣ በማንኛችን በኩል መንገዱ እንደሚናድ ልናይ - ቀድሞ የተናደውን፡፡
“ተናደ"
ስብሰባውን የጀመረው አለቃችን አቶ እጅጉ ነበር፡፡ ኩፍስ ብሎ የኮቱ አጥፋት ሸብዳዳ ትከሻው ላይ ተከምሮ (ከኮቱ ውስጥ ትንሽ የሶፋ ትራስ ያስቀመጠ ይመስለኛል)፡፡ ጨዋ ለመምሰል በሚዳዳው ድምፅ ስብሰባው መጀመሩን አረዳ (አበሰረ የሚሉም አሉ “ከሸረኞች ወገን ናቸው)
እ...ያው እንደምታውቁት…" አለ (ምንም በማናውቀው ነገር) ...መሥሪያ ቤታችን ያለውን
መልካም ሰምና ዝና ለማስቀጠል (ሂሂሂሂ ጉድ ፈላ በቀን የሚመጣው ባለጉዳይ ሁሉ እዩዬ እያለ ተራግሞ የሚሄድበት መሥሪያ ቤት መልካም ስምና ዝና ይሁና) ዘመናዊ የአሠራር ሲሰተም
ዘመን አፈራሽ መሳሪያዎች እንደሚያስፈልጉ በማመን የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ወስደን
እየተንቀሳቀሰን 'ያለበት ሁኔታ ነው ያለው….
እነዚህ ዘመናዊ መሳሪያዎች ደግሞ ብቻቸውን ጠብ የሚል ለውጥ እንደማያመጡ እሙን
ነው፣ ስለዚህ ቢሯችንን 'በአመለካከት በእውቀት እና በተግባር ከመሳሪያዎቹ ጋር አብሮ
በሚሄድ ወጣት የሰው ኃይል ማደራጀቱ ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ተግባር ነውሸ
(እማማ መለኮት በኩል መንገዱ ተናደ:: ጨዋነትን የጫነው መኪና ገደል ገባ፡፡ ትህትና ተሽቀነጠረ፡፡ መንገድ ስለሌለ ወደኋላ ተመለስን፡፡ መንገድ አፍራሽ ሸረኞች ራእይ እንደ ህልም
ያያሉ፡፡ ከመድረስም ተጣልተዋል፡፡ መንገድ የለማ ...! ከአባይ ወዲያ ማዶ ያለ ዘመድ ሆነ የእማማ መለኮት ሥራ፣ እንባቸው በአይናቸው የሞላ እለት ዋይ ብለው ቀሩ፡፡
እንዲት በእድሜ የገፉ ሚስኪን አባሮ በየቢሮው እየዞረች ምስጋና የምትቀላውጥ ገልቱ
ለመቅጠር ምድረ ጉማሬ ሚስኪኑን ላብ አደር ሰብስቦ አላዘነ፡፡ ደግሞ ስላዘመናዊነት
ያወራሉ፣ እግዚኦ አለቆቻችን ስለዘመናዊነት አወሩ፡፡ስልካቸው ባትሪ ሲጨርስ ተበላሸ
ብለው ሠሪ ቤት የሚሮጡ አለቆቻችን ዘመናዊነትን ሰበኩ፡፡ ከፕሪንተር የሚወጣ ወረቀት ደመና ሰንጥቆ እንደሚወጣ መልአክ በግርምት የሚመለከቱ፡፡ (አይ ፈረንጅ ነፍስ መፍጠር እኮ ነው የቀረው!' እየተባባሉ፡፡) እለቆቻችን ዘመናዊ እንሁን አሉ፡፡
እማማ መለኮት በጡረታ ስም ተባረሩ፡፡ (ተቀነሱ በል አቶ አብረሃም ተብያለሁ፡፡) ዙፋን
ተቀጠረች አሁን ድርጅቱ ዘመናዊ ሆነ፡፡ “እንደምን ዋላችሁ…”፣ “ሃይ ጋይስ” በሚል ሰላምታ .
በመተካቱ እልልል ቢሯችን ዘመናዊ ሆነ፡፡
ዙፋን የዘመናዊነት ፋና ወጊ፣ አንድ ገፅ ደብዳቤ ስትፅፍ አንድ ከግማሽ ገፅ ስህተት የምትዘራ
ጉድ፡፡ ወሬ ብቻ መሽኮርመም ብቻ፣ በየሰሙ ላይ “ዬ" መጨመር ብቻ (አብርሽዬ..ቶማስዬ.
ጋሽ ሰይድዬ ተፈራዬ... ሐጎስዬ.. ገኒዬ..እግዚያብሄርዬ..ጂሰስዬ_) እንደ ዬ ፈደል ትልቅ አፍ ብቻ
ያላት መርገምት፡፡ደህና ነገር ሲናገር ከንፈሩ እንደደረቀ ሰው በየደቂቃው ቻፕስቲክ እየተለቀለቀች በየቢሮው ማውራት !! (ውይ ጥርስ አታስከድንም፤ ተጫዋች ምናምን ይሏታል የሸረኛው መንጋ፡፡
ቆንጆ ብቻ መሆን እንዴት ይቃፋል፡፡ ሴት ብቻ በመሆን ከወንድ የሚቻር ወሲባዊ ክብር ምንኛ ውድቀት ነው?! ዕድሜ ከፍ ባለ ቁጥር የሚናድ የእንቧይ ካብ፡፡ እንዴት ሰውን ያህል ፍጥረት
ያውም እናትነትን ያሀል አደራ ትቀበል ዘንድ ተፈጥሮ የወከለቻት ሴት ስለጥፍር አንድ ሰዓት ሙሉ ታወራለች? ስለፀጉር ሁለት ሰአት፣ ስለጥፍር ቀለም ሙሉ ሸን፣ስለ ልብስ...
የመታየት ልክፍት (ኤግዝቢሽኒያም ይለዋል በሬቻ)፡፡ በፋሽን ስም ነጋቸው ላይ ውበት ሊዘሩለት ሚችሉትን ዛሬ አርሲ ኩርሲ የውበት ኮተት እያወሩ ይፈጁታል፡፡ ይሄ የሴት ውበት ነው የሴት ብክነት፡፡ ስለውበት የሚደሰኩር ሚዲያ ላይ አፍጥጣ የምትውል ዙፋን፣ ቆዳዋን በምናምን አደንድና ፍቅር እንዳይስርአት ራሷን ሳታዋድድ ትኖራለች። ሴት ከምልክ የተሻለ መወዳደሪያ በሌላት ውድድሩ ውስጥም የምትኖረው ቢበዛ ለጥቂት ዓመታት ነው፡፡ ባካና ! ዙፋን ባካና ናት፤ ስሟ ራሱ እሷ ላይ ሲደርስ 'ዙፋን' የሆነ፣ የመወዘፍ አይነት ደውል ነው፡፡ (ውዝፍ ከሚለው ስረወ ቃል የመጣ)
ከአለቃዬ ጋር በአይኗ ስትዳራ ስንት ጊዜ ታዘብኩ፡፡ እማማ መለኮትን ነቅላ ላትፀድቅ ነገር
ራሷን የተከለችበትን ቆሻሻ መንገዷን አይቻለሁ፡፡ ለፀሃፊነት ሥራ ውድድር መሰለፍ የማይችል
ባልጩት ጨንቅላቷ ላይ ሰው ሰራሽ ፀር ጎዝጉዛ ክቡር ሴትነቷን በየቢሮው ስትጎዘጉዝ ሳናይ
አላወራንም፤ “ጭስ ካለ እሳት አለ” ብለንም እይደለም፡፡ ቆይቶ የተደረገ ግምገማ ላይ የተገደደች
አስመስላ ቀባጠረችው እንጂ፡፡ (የሸረኞች መንገድ የተናደች" እለት)
👍19❤2
ባለቤት የለሽ ስጥ ማንም አላፊ አግዳሚ የሚዘግናት፡፡ ወንዶች በምናምናቸው እየተመሩ
የሚደርሱባት ጥግ፡፡ የሴትነት ባንዲራ ዝቅ ብሎ የሚውለበለብባት ፀያፍ ምሶሶ፡፡ ለወረደ የሴትነት ባንዲራ ሴሰኛ ወንዶች ሲዘምሩ ምሰሶው እንዴት ቴንኪው' እያለ ይሽኮረመማል?
የእድሜ ጉዳይ ነው፡ ያች የሴትነት ባንዲራ ትወርዳለች፡፡ ያኔ ዘማሪ ሲጠፋ ሴትነት የተነጠለው
“ሰው መሆን ብቻውን” ሲቆም ይሄ ከተማውን የሞላው አላፊ አግዳሚውን በቅናት ግልምጫ
የሚጎነትል፣ “ምከሩ ላይ ስቆ የመከራ ዱላ መድረሻ ያሳጣው፣ ፍቅር እልባ የሴት ፊት ሁሉ”
ዙፋን ተባለች መሀበርትኛ ይመረቅለታል፡፡
አቀባበል ይደረግላት ተባለ ዙፋን፡፡ ሰው እንዴት ምንም ይቀበላል? በግ ታርዶ፣ ቢራ ቀርቦ
“አንዲት ፀሃፊ ለመቀበል ይሄ ሁሉ ድግስ” እንዳይባል፣ ለአቀባበሉ ህዝባዊ ስም ወጣለት
“የሩብ ዓመቱ የግምገማ ማጠቃለያ'፡፡ ሲበላ፣ ሲጠጣ ሸረኞች የሸረኛ ልዕልታቸውን ከብበው እያውካኩ ጥሬ ከብስል ሲሰለቅጡ እማማ መለኮች ናፈቁኝ፡፡ እንዲህ ዝግጅት ሲኖር እሳቸው ሌሊት ሁሉ እያደሩ ወጥ ይሰሩ ነበር አምስት ሳይከፈላቸው፡፡ ነጭ ልብሳቸውን ለብሰው፣ምድረ ሆዳም ሲያስተናግዱ ይውሉ ነበር፡፡
መንገዱ
ግብዣው ሹልክ ብየ ወጣሁና፤ አጠያይቄ እማማ መለኮት ቤት ሄድኩ፡፡ በራቸው ላይ ቁጭ ብለው
ምስር እየለቀሙ ነበር፡፡ ሲያዩኝ በድንጋጤና በግርምት ተርበተበቱ፡፡ የምስር ክክ የያዘውን
ትሪ ወደቀኛቸው ካለች መደብ ነገር ላይ ሲያስቀምጡ የተለቀመው ካልተለቀመው ተቀላቀለ፡፡
ኣንደእኛ ቢሮ፣ እንደእኛ ሃሳብ፣ እንደእኛ ፖለቲካ፣እንደእኛ እኛነት ተመልሶ መልቀም፡፡ አዲስ እንግዳ
ሃሳብ፣ እንግዳ አሰራር፡ እንግዳ ርዕዮተ ዓለም ሊመጣ ያከበርን መስሎን የሰራነውን ማፍረስ፡፡
ከመቀመጫቸው ተብድግ ብሰው በእከብሮት ቆሙ፡ "ውይ በሞትኩት እዚህ ድረስ ምን አለፋህ
አቶ አብረሃም - እጄ ቆሻሻ ነው ቆይ” ብለው ቀሚሳቸው ጋር ጠራረጉና በተስፋ እያዩኝ
ጨበጥኳቸው፣ ምናልባት ወደሥራ ልመልሳቸው የሄድኩ ይመስላቸው ይሆን? ግባ አሉኝ፤ ገባሁ
ንፁህና ጠባብ ናት ክፍላቸው፡፡ ወደጓዳ መግቢያ ላይ ባለጥልፍ ነጭ መጋረጃ፡፡ ባለመደገፈያ
የቀርከሃ ሶፋ:: ግድግዳ ላይ አንድ ጥቁርና ነጭ የትልቅ ሰው ፎቶ አለ (ባላቸው ይሆኑ?)፡፡
ከጎኑ ባለድግሪ ወጣት ባለቀለም ፎቶ፡፡ እማማ መለኮት መጋረጃዋን ገለጥ አድርገው ወደ ጓዳ ገቡ፡፡
ቡና እንደምወድ ያውቃሉ፡፡ ላፍላልህ ሳይሱ ቡናውን አቀራረቡ፡፡ አወሩኝ ስለነበረው፡
“ግራ ገብቶኛል፣ እንቅልፍም አልወስድሽ ብሎኝ ነው ያደርኩት፡፡ እንግዲህ በዚህ ዕድሜ ሰው
ቤት ልብስ ላጥብ ነው ? እንጀራ ልጋግር ? እኔኮ ሌላው አይደለም ያሳዘነኝ፣ ይሄን ያህል ዓመት
ያገለገልኩበት ቤት ነው፡፡ ምናላ ለወጉ ጠርተው እንግዲህ በቃሽ ቢሉኝ፡፡ አቶ እጅጉ መጥቶ
ሰሜን እንኳን አልጠራኝም፡ ይሄን ኮምፒተር አፀዳጅው፤ እንግዲህ ጡረታ መውጫሽም እየደረሰ
ነው፤ በቃ እንዲህ ነው ያለኝ፡፡ የዛሬን ቀን አያምሽልኝ፣ እንዲሁ አለኝ..ይባላል ? አቶ ኣብርሃም
እስቲ ፍረድ፣ ፍርድ ለራስ ነው መቸም…"
አለቀሱ እማማ መለኮት:: የማደርገው ነገር ጠፋብኝ፡፡ “ብዙ ያየሁ ሰው ነኝ፣ ይከፋኛል፣
ማግኘትም ማጣትም ማጀቴን የጎበኘው ሰው ነኝ፡፡ባሌ የሞተብኝ ሴት ነኝ አርጅቻለሁ፡፡ ልጄ
ምጥ ይግባ ስምጥ የጠፋብኝ ብሶተኛ ነኝ፡፡ ለትንሽ ትልቁ ደፋ ቀና የምለው ቀባሪ የለኝም፣
'የአገሬ ሰው ነው ቀባሪዩ” ብዬ ነው:: እንዴት እንዲህ ያመንኩት ህዝብ ይተፋኛል? እንዴት
ባዕድ እሆናለሁ? አይዞሽ ማንን ገደለ? ፀሃፊነቱን ይተዉት እናትነት ይወረወራል ? አንድ ሰው
በሬ ዝር አይልም ? በሃዘን በደስታው ከሥራዬ አልፎ ተርፎ ለድግሳቸው ጉልበቴን ገብሬ
ቤታቸውን አላቀናሁም ? ፍረድ አቶ አብረሃም - ፍርድ እንደራስ ነው” ስኳር ወደ ስኒዎቹ ጨመሩ፡፡ በዝምታችን ውስጥ ቡናው ሲቀዳ ደስ የሚል ድምፁ ጠባቧን ቤት ሞላት፡፡ አንዲት ክስት ያላች ጥቁር ድመት ገብታ ረከቦቱ አጠገብ ቆመች፡፡ ለቡና ቁርስ ከተቆራረሰው ዳቦ ቆንጥረው ሰጧት፡፡
"እማማ መለኮት!” አልኩ ቀስ ብዬ፣
“ወይዩ!” አሉ ቡናውን እያቀበሉኝ፡፡
“ልጄ ጠፋ ነው ያሉኝ?” ወይ ወሬ መውደድ አሁን የሰው ብሶት ከመቀስቀስ ውጭ ምንም
ላልፈይድ ምን አጠያየቀኝ…::
“አዎ.ይሄ ፎቶ የሱ ነው” አሉ ወደ ባለድግሪው ወጣት እየጠቆሙኝ፡፡ ጭራሽ ተነስተው ፎቶውን
ከተሰቀለበት አወረዱና ሰጡኝ፡፡ መልከ መልካም ወጣት ነው፣ ሳቂታ፡፡
ልጄ ነው አንድ ልጄ፡፡ ስድስት ኪሎ በድግሪ ተመርቆ ወር ሳደቆይ 'ወደ ውጭ አገር ልሂድ ብሎ ተነሳ፡፡
ኬኒያ የሚባል አገር ደረስኩ ብሎ ደወለልኝ፡፡ ይሄውልህ ከዛ በኋላ ይኑርም ይሙትም ወሬው የለም ብለው እንባቸውን ዘረገፉት፡፡
“ከሄደ ቆየ ?..." በሃሳቢ ኬኒያ ያሉ ጓደኞቼን 'ይሄን ልጅ ካላገኛችሁ ወዮላችሁ! ልል ተዘጋጅቼ፡፡
እንግዲህ ወደ አስራ አምስት ዓመት አይሆነውም ብለህ ነው” ፎቶው ላይ አፍጥጬ ቀረሁ፡፡
“ቡናው ቀዘቀዘብህ፣ የኔ ነገር" ብለው ፎቶውን ከእጄ ተቀበሉና ቦታው መለሱት፡፡
ስናወራ ቆይተን እንደምጠይቃቸው ነግሬያቸው ስወጣ፣ "አቶ አብረሃም፣ ካላስቸገርኩህ በቅደም
ተጣድፌ እኔ መሳቢያ ውስጥ መሃረቤን ረስቸው መጣሁ፡፡
እንደው ላቶ ሽብሩ
ብትሰጥልኝ በዚሁ ሲያልፍ ያቀብለኛል" አሉ፡፡ አቶ ሽብሩ የመስሪያ ቤታችን ሹፌር ነው፡፡
የችን ተዓምረኛ መሃረብ የቢሮው ሰው ያውቃታል፡፡ እማማ መለኮት ፀበል ቤት ይሄዱና ወይም
ቤታቸው ዝክር ብጤ ትኖራቸውና በምንቀርባቸው ባልደረቦቻቸው የፀበል ቤት ዳቦ በመሃረባቸው
ጠቅልለው ያመጡልናል - በቀይ ክር የሀረግ ጥልፍ ዙሪያውን የተጠለፈበት መሃረብ::
፡
በቀጣዩ ቀን ቢሮ ስገባ አቶ እጅጉ ደረጃው ላይ አገኘኝና፣ ”አቶ አብረሃም፣ ምነው ድግስ ረግጠህ
ወጣህ?” አለኝ፡፡ “አጋሰስ” አላልኩትም፡፡
የእማማ መለኮትን መሃረብ ለማምጣት ወደ ዙፋን ቢሮ ሄድኩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር እማማ መለኮት ከለቀቁ በኋላ ወደዚህ ቢሮ የመጣሁት፡፡ ዙፋን እፏን ከፈተችው፣ "አ..ንተ በመጨረሻ መጣህ፡፡ ዝም ብለህ ትንቀባረራለህ መምጣትህ ላይቀር" አለች ፊቷ አንበሳ ገዳይ አይነት ፉከራ ሰፍሮበት - ደነዝ!! አጎንብሳ እግሯን የሆነ ነገር እያደረገች ነበር የምታወራኝ - ጠረጴዛሁ እግሯን ጋርዶኛል፡፡
“ምን እዚህ ይሄ መንገዳችሁ አቧራ ብቻ ነው ኤጭ":: ተሽከርካሪ ወንበሯን ወደእኔ ስታዞረው የተራቆተ ቀኝ ታፋዋ ስለተቀመጠች በጣም ገዝፎ ታየኝ፡፡ አይኔን ወደታች ስልከ ባለተረከዝ ጫማዋን እየወለወለች እንደነበር ገባኝ፡፡ ቀእጂ፣ በቀይ ክር ሃረግ የተጠለፈበት የእማማ መለኮት መሃረብ በከፊል አቧራ ለብሶ...
✨አለቀ✨
የሚደርሱባት ጥግ፡፡ የሴትነት ባንዲራ ዝቅ ብሎ የሚውለበለብባት ፀያፍ ምሶሶ፡፡ ለወረደ የሴትነት ባንዲራ ሴሰኛ ወንዶች ሲዘምሩ ምሰሶው እንዴት ቴንኪው' እያለ ይሽኮረመማል?
የእድሜ ጉዳይ ነው፡ ያች የሴትነት ባንዲራ ትወርዳለች፡፡ ያኔ ዘማሪ ሲጠፋ ሴትነት የተነጠለው
“ሰው መሆን ብቻውን” ሲቆም ይሄ ከተማውን የሞላው አላፊ አግዳሚውን በቅናት ግልምጫ
የሚጎነትል፣ “ምከሩ ላይ ስቆ የመከራ ዱላ መድረሻ ያሳጣው፣ ፍቅር እልባ የሴት ፊት ሁሉ”
ዙፋን ተባለች መሀበርትኛ ይመረቅለታል፡፡
አቀባበል ይደረግላት ተባለ ዙፋን፡፡ ሰው እንዴት ምንም ይቀበላል? በግ ታርዶ፣ ቢራ ቀርቦ
“አንዲት ፀሃፊ ለመቀበል ይሄ ሁሉ ድግስ” እንዳይባል፣ ለአቀባበሉ ህዝባዊ ስም ወጣለት
“የሩብ ዓመቱ የግምገማ ማጠቃለያ'፡፡ ሲበላ፣ ሲጠጣ ሸረኞች የሸረኛ ልዕልታቸውን ከብበው እያውካኩ ጥሬ ከብስል ሲሰለቅጡ እማማ መለኮች ናፈቁኝ፡፡ እንዲህ ዝግጅት ሲኖር እሳቸው ሌሊት ሁሉ እያደሩ ወጥ ይሰሩ ነበር አምስት ሳይከፈላቸው፡፡ ነጭ ልብሳቸውን ለብሰው፣ምድረ ሆዳም ሲያስተናግዱ ይውሉ ነበር፡፡
መንገዱ
ግብዣው ሹልክ ብየ ወጣሁና፤ አጠያይቄ እማማ መለኮት ቤት ሄድኩ፡፡ በራቸው ላይ ቁጭ ብለው
ምስር እየለቀሙ ነበር፡፡ ሲያዩኝ በድንጋጤና በግርምት ተርበተበቱ፡፡ የምስር ክክ የያዘውን
ትሪ ወደቀኛቸው ካለች መደብ ነገር ላይ ሲያስቀምጡ የተለቀመው ካልተለቀመው ተቀላቀለ፡፡
ኣንደእኛ ቢሮ፣ እንደእኛ ሃሳብ፣ እንደእኛ ፖለቲካ፣እንደእኛ እኛነት ተመልሶ መልቀም፡፡ አዲስ እንግዳ
ሃሳብ፣ እንግዳ አሰራር፡ እንግዳ ርዕዮተ ዓለም ሊመጣ ያከበርን መስሎን የሰራነውን ማፍረስ፡፡
ከመቀመጫቸው ተብድግ ብሰው በእከብሮት ቆሙ፡ "ውይ በሞትኩት እዚህ ድረስ ምን አለፋህ
አቶ አብረሃም - እጄ ቆሻሻ ነው ቆይ” ብለው ቀሚሳቸው ጋር ጠራረጉና በተስፋ እያዩኝ
ጨበጥኳቸው፣ ምናልባት ወደሥራ ልመልሳቸው የሄድኩ ይመስላቸው ይሆን? ግባ አሉኝ፤ ገባሁ
ንፁህና ጠባብ ናት ክፍላቸው፡፡ ወደጓዳ መግቢያ ላይ ባለጥልፍ ነጭ መጋረጃ፡፡ ባለመደገፈያ
የቀርከሃ ሶፋ:: ግድግዳ ላይ አንድ ጥቁርና ነጭ የትልቅ ሰው ፎቶ አለ (ባላቸው ይሆኑ?)፡፡
ከጎኑ ባለድግሪ ወጣት ባለቀለም ፎቶ፡፡ እማማ መለኮት መጋረጃዋን ገለጥ አድርገው ወደ ጓዳ ገቡ፡፡
ቡና እንደምወድ ያውቃሉ፡፡ ላፍላልህ ሳይሱ ቡናውን አቀራረቡ፡፡ አወሩኝ ስለነበረው፡
“ግራ ገብቶኛል፣ እንቅልፍም አልወስድሽ ብሎኝ ነው ያደርኩት፡፡ እንግዲህ በዚህ ዕድሜ ሰው
ቤት ልብስ ላጥብ ነው ? እንጀራ ልጋግር ? እኔኮ ሌላው አይደለም ያሳዘነኝ፣ ይሄን ያህል ዓመት
ያገለገልኩበት ቤት ነው፡፡ ምናላ ለወጉ ጠርተው እንግዲህ በቃሽ ቢሉኝ፡፡ አቶ እጅጉ መጥቶ
ሰሜን እንኳን አልጠራኝም፡ ይሄን ኮምፒተር አፀዳጅው፤ እንግዲህ ጡረታ መውጫሽም እየደረሰ
ነው፤ በቃ እንዲህ ነው ያለኝ፡፡ የዛሬን ቀን አያምሽልኝ፣ እንዲሁ አለኝ..ይባላል ? አቶ ኣብርሃም
እስቲ ፍረድ፣ ፍርድ ለራስ ነው መቸም…"
አለቀሱ እማማ መለኮት:: የማደርገው ነገር ጠፋብኝ፡፡ “ብዙ ያየሁ ሰው ነኝ፣ ይከፋኛል፣
ማግኘትም ማጣትም ማጀቴን የጎበኘው ሰው ነኝ፡፡ባሌ የሞተብኝ ሴት ነኝ አርጅቻለሁ፡፡ ልጄ
ምጥ ይግባ ስምጥ የጠፋብኝ ብሶተኛ ነኝ፡፡ ለትንሽ ትልቁ ደፋ ቀና የምለው ቀባሪ የለኝም፣
'የአገሬ ሰው ነው ቀባሪዩ” ብዬ ነው:: እንዴት እንዲህ ያመንኩት ህዝብ ይተፋኛል? እንዴት
ባዕድ እሆናለሁ? አይዞሽ ማንን ገደለ? ፀሃፊነቱን ይተዉት እናትነት ይወረወራል ? አንድ ሰው
በሬ ዝር አይልም ? በሃዘን በደስታው ከሥራዬ አልፎ ተርፎ ለድግሳቸው ጉልበቴን ገብሬ
ቤታቸውን አላቀናሁም ? ፍረድ አቶ አብረሃም - ፍርድ እንደራስ ነው” ስኳር ወደ ስኒዎቹ ጨመሩ፡፡ በዝምታችን ውስጥ ቡናው ሲቀዳ ደስ የሚል ድምፁ ጠባቧን ቤት ሞላት፡፡ አንዲት ክስት ያላች ጥቁር ድመት ገብታ ረከቦቱ አጠገብ ቆመች፡፡ ለቡና ቁርስ ከተቆራረሰው ዳቦ ቆንጥረው ሰጧት፡፡
"እማማ መለኮት!” አልኩ ቀስ ብዬ፣
“ወይዩ!” አሉ ቡናውን እያቀበሉኝ፡፡
“ልጄ ጠፋ ነው ያሉኝ?” ወይ ወሬ መውደድ አሁን የሰው ብሶት ከመቀስቀስ ውጭ ምንም
ላልፈይድ ምን አጠያየቀኝ…::
“አዎ.ይሄ ፎቶ የሱ ነው” አሉ ወደ ባለድግሪው ወጣት እየጠቆሙኝ፡፡ ጭራሽ ተነስተው ፎቶውን
ከተሰቀለበት አወረዱና ሰጡኝ፡፡ መልከ መልካም ወጣት ነው፣ ሳቂታ፡፡
ልጄ ነው አንድ ልጄ፡፡ ስድስት ኪሎ በድግሪ ተመርቆ ወር ሳደቆይ 'ወደ ውጭ አገር ልሂድ ብሎ ተነሳ፡፡
ኬኒያ የሚባል አገር ደረስኩ ብሎ ደወለልኝ፡፡ ይሄውልህ ከዛ በኋላ ይኑርም ይሙትም ወሬው የለም ብለው እንባቸውን ዘረገፉት፡፡
“ከሄደ ቆየ ?..." በሃሳቢ ኬኒያ ያሉ ጓደኞቼን 'ይሄን ልጅ ካላገኛችሁ ወዮላችሁ! ልል ተዘጋጅቼ፡፡
እንግዲህ ወደ አስራ አምስት ዓመት አይሆነውም ብለህ ነው” ፎቶው ላይ አፍጥጬ ቀረሁ፡፡
“ቡናው ቀዘቀዘብህ፣ የኔ ነገር" ብለው ፎቶውን ከእጄ ተቀበሉና ቦታው መለሱት፡፡
ስናወራ ቆይተን እንደምጠይቃቸው ነግሬያቸው ስወጣ፣ "አቶ አብረሃም፣ ካላስቸገርኩህ በቅደም
ተጣድፌ እኔ መሳቢያ ውስጥ መሃረቤን ረስቸው መጣሁ፡፡
እንደው ላቶ ሽብሩ
ብትሰጥልኝ በዚሁ ሲያልፍ ያቀብለኛል" አሉ፡፡ አቶ ሽብሩ የመስሪያ ቤታችን ሹፌር ነው፡፡
የችን ተዓምረኛ መሃረብ የቢሮው ሰው ያውቃታል፡፡ እማማ መለኮት ፀበል ቤት ይሄዱና ወይም
ቤታቸው ዝክር ብጤ ትኖራቸውና በምንቀርባቸው ባልደረቦቻቸው የፀበል ቤት ዳቦ በመሃረባቸው
ጠቅልለው ያመጡልናል - በቀይ ክር የሀረግ ጥልፍ ዙሪያውን የተጠለፈበት መሃረብ::
፡
በቀጣዩ ቀን ቢሮ ስገባ አቶ እጅጉ ደረጃው ላይ አገኘኝና፣ ”አቶ አብረሃም፣ ምነው ድግስ ረግጠህ
ወጣህ?” አለኝ፡፡ “አጋሰስ” አላልኩትም፡፡
የእማማ መለኮትን መሃረብ ለማምጣት ወደ ዙፋን ቢሮ ሄድኩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር እማማ መለኮት ከለቀቁ በኋላ ወደዚህ ቢሮ የመጣሁት፡፡ ዙፋን እፏን ከፈተችው፣ "አ..ንተ በመጨረሻ መጣህ፡፡ ዝም ብለህ ትንቀባረራለህ መምጣትህ ላይቀር" አለች ፊቷ አንበሳ ገዳይ አይነት ፉከራ ሰፍሮበት - ደነዝ!! አጎንብሳ እግሯን የሆነ ነገር እያደረገች ነበር የምታወራኝ - ጠረጴዛሁ እግሯን ጋርዶኛል፡፡
“ምን እዚህ ይሄ መንገዳችሁ አቧራ ብቻ ነው ኤጭ":: ተሽከርካሪ ወንበሯን ወደእኔ ስታዞረው የተራቆተ ቀኝ ታፋዋ ስለተቀመጠች በጣም ገዝፎ ታየኝ፡፡ አይኔን ወደታች ስልከ ባለተረከዝ ጫማዋን እየወለወለች እንደነበር ገባኝ፡፡ ቀእጂ፣ በቀይ ክር ሃረግ የተጠለፈበት የእማማ መለኮት መሃረብ በከፊል አቧራ ለብሶ...
✨አለቀ✨
👍22
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...የማሪየስ አባት በየሁለትና ሃ'ስት ወር ፓሪስ ከተማ እየመጣ ልጁ
ከአያቱ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ያየዋል:: የገባውን ቃል አፍርሶ ስለሆነ የሚያየው ሰው እንዳያየው ተጠንቅቆ ከአሳቻ ሥፍራ በመደበቅ ነበር ልጁን የሚያየው።
ማሪየስ እንደማንኛውም ልጅ ትምህርት ቤት ገብቶ ይማራል። የታወቀ ጎበዝ አስተማሪ ከቤት ተቀጥርለት ትምህርቱን በሚገባ ይከታተላል: ኮሌጅ ከጨረሰ በኋላ የሕግ ትምህርት ለመከታተል ከሕግ ትምህርት ቤት ገባ፡፡
ለአያቱ ብዙም ፍቅር የለውም:: የአያቱ፡ አሽሙርና ንቀት ልቡን አቁስሎታል፡፡የወላጅ አባቱ ጉዳይ ግን ዘወትር ያሳስበዋል:: ልጁ በተፈጥሮው ጨዋ ረጋ ያለ ፤ በራሱ የሚተማመን ኩሩ ልጅ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ ፈሪሃ
እግዚአብሔር ያደረበት ነው፡፡ በ1827 ዓ.ም ማሪየስ የአሥራ ስምንት ዓመት ወጣት ነው:: አንድ ቀን ማታ አያቱ ከነበሩበት ክፍል ሲገባ ደብዳቤ በእጃቸው ይዘው ደረሰ፡፡
«ማሪየስ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ ነገ ጠዋት ወደ ቬርኖን ትሄዳለህ፡፡»
«ለምን?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
«አባትህን ለማየት::»
ማሪየስ ደነገጠ፡፡ አንድ ቀን ከአባቴ ጋር እገናኛለሁ የሚል ሀሳብ
በእውኑም ሆነ በሕልሙ አስቦት አያውቅም:: ምንም ነገር ከዚህ ይበልጥ አስደንጋጭና ያልተጠበቀ ሊሆንበት አይችልም ነበር፡፡
በሀገሪቱ ውስጥ ስለነበረው የፖለቲካ አቋም የተቃውሞ አሳብ
ሊኖረውም እያቱ እንደሚሉት አባቱ የቡርዥዋን አገዛዝ የሚቃወም
የማይረባ ወታደር» ነው:: በዚህ የተነሣ ለአባቱ የነበረው ፍቅር ይህን ያህል አልነበረም:: ከዚህም በላይ ወላጅ አባቱ እርሱን ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠቱ ጭካኔ ስለመሰለው ጠላው:: «አባቴ አይወደኝም» ሲል አምነ።
ይዞ በዚህ እንዳለ በዚያች ቅጽበት ያልጠበቀው ጥያቄ ከአያቱ ስለመጣዐበመደንገጡ የአዎንታም ሆነ የእምቢታ መልስ ለመስጠት አልቻልንም። አያቱ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡
«አባትህ ታሟል መሰለኝ፤ ሊያይህ ይፈልጋል::
በሚቀጥለው ቀን ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ማሪየስ ክሼርኖን ከተማ ደረሰ በመጀመሪያ ያገኘውን ሰው «የመሴይ ፓንት መርሲ ቤት የት እንደሆነ ያውቃሉ?ሲል ይጠይቃል::
ተጠያቂው ቤቱን ያውቅ ኖሮ አመላከተው:: ከቤቱ ሲደርስ በሩን
በመደብደብ አንኳኳ፡፡ አንዲት ሴት በሩን ከፈተችለት::
«መሴይ ፓንትመርሲ አሉ?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
ሴትዮዋ ደንግጣ መልስ ሳትሰጠው ዝም ብላ ቆመች::
«አሉ እንዴ?» ሲል እንደገና ጠየቀ፡፡
ለመኖሩ ግምባርዋን ወደ ላይ በመግፋት አረጋገጠችለት::
«ላነጋግራቸው እችላለሁ?»
እንደማይቻል ጭንቅላትዋን በመነቅነቅ ገለጸችለት::
«እኔኮ ልጃቸው ነኝ» አለ ማሪየስ፡፡ «እንደምመጣ ደግሞ ስለሚያወቁ
ይጠብቁኛል፡፡»
«ከእንግዲህ ወዲያ አይጠብቅህም» አለች ሴትዮዋ፡፡
በዚህ ጊዜ አተኩሮ ሲመለከታት ቀደም ሲል ታለቅስ እንደነበር አወቀ።
ወደ አንድ ክፍል ባመለከተችው ጊዜ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ክፍሉ
ውስጥ ሦስት ሰዎች ነበሩ፡፡ አንዱ ቆሞአል፤ ሌላው ተንበርክኮአል፡፡ ሦስተኛ ከመሬት ላይ ተንጋልሎ ተኝቷል፡፡ ተጋልሎ የተኛው አባቱ ነው::ከሁለቱ ሰዎች አንደኛው ሐኪም ሲሆን ሌላው ጸሉት የሚያደርሱ ቄስ ነበሩ፡፡
ኵሎኔሉ በጠና ከታመመ ሦስት ቀን ሆኖታል። ወዲያው ሕመሙ
እንደጀመረው ነበር ልጁ እንዲመጣለት በመልክተኛ ደብዳቤ ለመሴይ ጊልኖርማንድ የላከው:: ደብዳቤውን እንደላከ ሕመሙ እየጠናበት ሄደ።
ማሪየስ ቬርኖን በደረሰበት እለት ልጁ ከመድረሱ በፊት «ልጄ አልመጣም?
እሱ ካልመጣ እኔ ሄጄ እገናኘዋለሁ» እያለ ካልጋው ዘሎ ይወርዳል፡፡
ሠራተኞች ሊይዙት ቢሞክሩም ሊይዘት ባለመቻላቸው ከክፍሉ ወጥቶ ከበረዳ ሲደርስ ይወድቃል፡፡ እዚያው እንደወደቀ ሕይወቱ አለፈች፡፡
ሕይወቱ ከማለፉ በፊት ሐኪም እንዲመጣ ሰዎች ተራራጡ፡፡
ነገር ግን ሐኪሙ ከመድረሳቸው በፊት ኰሎኔሉ ሞተ:: ቄሱም ቢሆኑ ነፍሱ ከወጣ በኋላ እንጂ አስቀድመው አልደረሱም:: ልጁ ግን የደረሰው ዘግይቶ ነው::
ክፍሉ ውስጥ የነበረው መብራት ደብዛዛ ቢሆንም ከኩሎኔሉ ጉንጭ
ላይ ከመሞቱ በፊት እምባ መውረዱ ያስታውቃል፡፡ እንዲያውም እምባው
ጨርሶ አልደረቀም:፡ ያለቀሰው ልጁ በጊዜው ስላልደረሰለት ነበር፡፡
ማሪየስ ሰውዬውን አፍጥጦ ተመለከተው:: ለመጀመሪያና
ለመጨረሻ ጊዜ ነበር አባቱን ያየው:: የአባቱ ዓይኖች ሲገለጡም እርሱ ያያቸዋል እንጂ እነርሱ አያዩትም:: የአባቱ እጅ ተገልጦ ስለነበረ የጦር
ሜዳ ቁስሎቹ ጠባሳ በብዛት ይታያሉ፡፡ ከፊቱም ላይ ትልቅ ጠባሳ አለ፡፡
አባቱ እንደሆነና ሕይወቱ እንዳለፈች ማሪየስ አወቀ፡፡ በድንጋጤ ክው ስላለ
ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ያዘነው ሀዘን ወደር አልነበረውም፡፡ እንኳን
የወለደው አባቱ ማንም ሰው ቢሆን እንደዚያ ተዘርሮና ሞቶ ቢያይ በጣም ማዘኑ አይቀርም።
ሀዘን፤ መሪር ሀዘን ከዚያች ክፍል ውስጥ ሰፍኖአል፡፡ ሠራተኛዋ
ከጥግ ቆማ ታነባዋለች፡፡ ቄሱ ይጸልያሉ፤ ግን እየጸለዩ ሲንሰቀሰቁ ይሰማል፡፡
ሐኪሙ ወዲያው፧ ወዲያው ዓይናቸውን በመሐረብ ይጠርጋሉ፡፡ ሬሳውም
ቢሆን የሚያለቅስ ይመስላል::
ሐኪሙ፤ ቄሱ፤ ሴትዬዋ ቃል ሳይተነፍሱ ማሪየስን አዩት:: ከውጭ የመጣ እንግዳ እሱ ብቻ ነው:: ማሪየስ ከነበረበት ትንሽ ነቅነቅ አለ። በጣም እፍረት ተሰማው፡፡ ያደረገውን ቆብ አውልቆ በእጅ ይዞት ስለነበር
ሳይታወቀው ከእጁ አምልጦ ከመሬት ወደቀ፡፡ ነገር ግን በጣም ከማዘኑ የተነሣ ቆቡን እንኳን ለመያዝ አቅም እንደሌለው ለማሳየት እንጂ እውነትም
አምልጦት አልነበረም::
ስለአባቱ የነበረውን አመለካከትና ግምት አስታውሶ ተጸጸተ::
መጸጸት ብቻ ሳይሆን ራሱን በጣም ነቀፈ:: ግን ጥፋቱ የእርሱ ነው? ኰሎኔሉ ወደኋላ የተወው ሀብት አልነበረም:: ከቤቱ ውስጥ የነበሩት እቃዎች ተሽጠው ለቀብሩ የወጣውን ወጪ እንኳን ለመሸፈን አልቻሉም፡፡ሠራተኛዋ አንዲት ወረቀት አግኝታ ለማሪየስ ሰጠችው:: ኩሎኔሉ ከመሞቱ
በፊት የጻፈው ማስታወሻ ሲሆን ቃሉም የሚከተለው ነው፡፡
«ለምወድህ ልጄ ፤ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ፡፡ እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል
ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ከወረቀቱ ጀርባ ላይ ኲሉኔሉ የጻፈው ማስታወሻ ደግሞ ‹‹በዚሁ በዋተርሉ ጦርነት አንድ የሃምሣ አለቃ ሕይወቴን አድኖአል:: ስሙ ቴናድዬ ይባላል:: ከፓሪስ ከተማ ወጣ ብሎ
ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንዲት አነስተኛ ሆቴል እንደነበረው አውቃለሁ:: ድንገት ካገኘኸው በተቻለህ እርሱን እርዳልኝ» የሚል ነበር፡፡
የአባቱ ፍቅር አስገድዶት ሳይሆን «የሞተን አክብር.» ብሎ በሚገፋፋን ውስጣዊ ኃይል ተመስጦ ማሪየስ ወረቀቱን በኃይል ጨመደደው::
ስለኩሎኔሉ ከዚያ በኋላ የታወቀ ነገር የለም:: ዩኒፎርሙንና
ጉራዴውን መሴይ ጊልኖርማንድ ለውራጅ እቃ ሸማች ሸጡት፡፡ ኰሎኔሉ የተከላቸውን አበቦች ጎረቤቱ ቀጥፈውና አትክልቱን አበላሽተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ድራሹን አጠፉት::
ማሪየስ ለሁለት ቀን እዚያው ቬርኖን ቆይቶ ከቀብሩ ሥነሥርዓት
በኋላ ወደ ፓሪስ ተመለሰ፡፡ ከዚያም የአባቱ መሞት ብዙም ሳይረብሸው ትምህርቱን ቀጠለ፡፡ ኵሎኔሉ በሞተ በሁለተኛው ቀን ተቀበረ፤ በሦስተኛ ቀን ተረሳ፡፡
ማሪየስ ለጥቂት ቀናት ከኮቱ ኮሌታ ላይ ጥቁር ጨርቅ አደረገ፡፡
የሀዘን ምልክት መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ሌላ የተደረገ ነገር አልነበረም::
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...የማሪየስ አባት በየሁለትና ሃ'ስት ወር ፓሪስ ከተማ እየመጣ ልጁ
ከአያቱ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ያየዋል:: የገባውን ቃል አፍርሶ ስለሆነ የሚያየው ሰው እንዳያየው ተጠንቅቆ ከአሳቻ ሥፍራ በመደበቅ ነበር ልጁን የሚያየው።
ማሪየስ እንደማንኛውም ልጅ ትምህርት ቤት ገብቶ ይማራል። የታወቀ ጎበዝ አስተማሪ ከቤት ተቀጥርለት ትምህርቱን በሚገባ ይከታተላል: ኮሌጅ ከጨረሰ በኋላ የሕግ ትምህርት ለመከታተል ከሕግ ትምህርት ቤት ገባ፡፡
ለአያቱ ብዙም ፍቅር የለውም:: የአያቱ፡ አሽሙርና ንቀት ልቡን አቁስሎታል፡፡የወላጅ አባቱ ጉዳይ ግን ዘወትር ያሳስበዋል:: ልጁ በተፈጥሮው ጨዋ ረጋ ያለ ፤ በራሱ የሚተማመን ኩሩ ልጅ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ ፈሪሃ
እግዚአብሔር ያደረበት ነው፡፡ በ1827 ዓ.ም ማሪየስ የአሥራ ስምንት ዓመት ወጣት ነው:: አንድ ቀን ማታ አያቱ ከነበሩበት ክፍል ሲገባ ደብዳቤ በእጃቸው ይዘው ደረሰ፡፡
«ማሪየስ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ ነገ ጠዋት ወደ ቬርኖን ትሄዳለህ፡፡»
«ለምን?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
«አባትህን ለማየት::»
ማሪየስ ደነገጠ፡፡ አንድ ቀን ከአባቴ ጋር እገናኛለሁ የሚል ሀሳብ
በእውኑም ሆነ በሕልሙ አስቦት አያውቅም:: ምንም ነገር ከዚህ ይበልጥ አስደንጋጭና ያልተጠበቀ ሊሆንበት አይችልም ነበር፡፡
በሀገሪቱ ውስጥ ስለነበረው የፖለቲካ አቋም የተቃውሞ አሳብ
ሊኖረውም እያቱ እንደሚሉት አባቱ የቡርዥዋን አገዛዝ የሚቃወም
የማይረባ ወታደር» ነው:: በዚህ የተነሣ ለአባቱ የነበረው ፍቅር ይህን ያህል አልነበረም:: ከዚህም በላይ ወላጅ አባቱ እርሱን ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠቱ ጭካኔ ስለመሰለው ጠላው:: «አባቴ አይወደኝም» ሲል አምነ።
ይዞ በዚህ እንዳለ በዚያች ቅጽበት ያልጠበቀው ጥያቄ ከአያቱ ስለመጣዐበመደንገጡ የአዎንታም ሆነ የእምቢታ መልስ ለመስጠት አልቻልንም። አያቱ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡
«አባትህ ታሟል መሰለኝ፤ ሊያይህ ይፈልጋል::
በሚቀጥለው ቀን ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ማሪየስ ክሼርኖን ከተማ ደረሰ በመጀመሪያ ያገኘውን ሰው «የመሴይ ፓንት መርሲ ቤት የት እንደሆነ ያውቃሉ?ሲል ይጠይቃል::
ተጠያቂው ቤቱን ያውቅ ኖሮ አመላከተው:: ከቤቱ ሲደርስ በሩን
በመደብደብ አንኳኳ፡፡ አንዲት ሴት በሩን ከፈተችለት::
«መሴይ ፓንትመርሲ አሉ?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
ሴትዮዋ ደንግጣ መልስ ሳትሰጠው ዝም ብላ ቆመች::
«አሉ እንዴ?» ሲል እንደገና ጠየቀ፡፡
ለመኖሩ ግምባርዋን ወደ ላይ በመግፋት አረጋገጠችለት::
«ላነጋግራቸው እችላለሁ?»
እንደማይቻል ጭንቅላትዋን በመነቅነቅ ገለጸችለት::
«እኔኮ ልጃቸው ነኝ» አለ ማሪየስ፡፡ «እንደምመጣ ደግሞ ስለሚያወቁ
ይጠብቁኛል፡፡»
«ከእንግዲህ ወዲያ አይጠብቅህም» አለች ሴትዮዋ፡፡
በዚህ ጊዜ አተኩሮ ሲመለከታት ቀደም ሲል ታለቅስ እንደነበር አወቀ።
ወደ አንድ ክፍል ባመለከተችው ጊዜ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ክፍሉ
ውስጥ ሦስት ሰዎች ነበሩ፡፡ አንዱ ቆሞአል፤ ሌላው ተንበርክኮአል፡፡ ሦስተኛ ከመሬት ላይ ተንጋልሎ ተኝቷል፡፡ ተጋልሎ የተኛው አባቱ ነው::ከሁለቱ ሰዎች አንደኛው ሐኪም ሲሆን ሌላው ጸሉት የሚያደርሱ ቄስ ነበሩ፡፡
ኵሎኔሉ በጠና ከታመመ ሦስት ቀን ሆኖታል። ወዲያው ሕመሙ
እንደጀመረው ነበር ልጁ እንዲመጣለት በመልክተኛ ደብዳቤ ለመሴይ ጊልኖርማንድ የላከው:: ደብዳቤውን እንደላከ ሕመሙ እየጠናበት ሄደ።
ማሪየስ ቬርኖን በደረሰበት እለት ልጁ ከመድረሱ በፊት «ልጄ አልመጣም?
እሱ ካልመጣ እኔ ሄጄ እገናኘዋለሁ» እያለ ካልጋው ዘሎ ይወርዳል፡፡
ሠራተኞች ሊይዙት ቢሞክሩም ሊይዘት ባለመቻላቸው ከክፍሉ ወጥቶ ከበረዳ ሲደርስ ይወድቃል፡፡ እዚያው እንደወደቀ ሕይወቱ አለፈች፡፡
ሕይወቱ ከማለፉ በፊት ሐኪም እንዲመጣ ሰዎች ተራራጡ፡፡
ነገር ግን ሐኪሙ ከመድረሳቸው በፊት ኰሎኔሉ ሞተ:: ቄሱም ቢሆኑ ነፍሱ ከወጣ በኋላ እንጂ አስቀድመው አልደረሱም:: ልጁ ግን የደረሰው ዘግይቶ ነው::
ክፍሉ ውስጥ የነበረው መብራት ደብዛዛ ቢሆንም ከኩሎኔሉ ጉንጭ
ላይ ከመሞቱ በፊት እምባ መውረዱ ያስታውቃል፡፡ እንዲያውም እምባው
ጨርሶ አልደረቀም:፡ ያለቀሰው ልጁ በጊዜው ስላልደረሰለት ነበር፡፡
ማሪየስ ሰውዬውን አፍጥጦ ተመለከተው:: ለመጀመሪያና
ለመጨረሻ ጊዜ ነበር አባቱን ያየው:: የአባቱ ዓይኖች ሲገለጡም እርሱ ያያቸዋል እንጂ እነርሱ አያዩትም:: የአባቱ እጅ ተገልጦ ስለነበረ የጦር
ሜዳ ቁስሎቹ ጠባሳ በብዛት ይታያሉ፡፡ ከፊቱም ላይ ትልቅ ጠባሳ አለ፡፡
አባቱ እንደሆነና ሕይወቱ እንዳለፈች ማሪየስ አወቀ፡፡ በድንጋጤ ክው ስላለ
ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ያዘነው ሀዘን ወደር አልነበረውም፡፡ እንኳን
የወለደው አባቱ ማንም ሰው ቢሆን እንደዚያ ተዘርሮና ሞቶ ቢያይ በጣም ማዘኑ አይቀርም።
ሀዘን፤ መሪር ሀዘን ከዚያች ክፍል ውስጥ ሰፍኖአል፡፡ ሠራተኛዋ
ከጥግ ቆማ ታነባዋለች፡፡ ቄሱ ይጸልያሉ፤ ግን እየጸለዩ ሲንሰቀሰቁ ይሰማል፡፡
ሐኪሙ ወዲያው፧ ወዲያው ዓይናቸውን በመሐረብ ይጠርጋሉ፡፡ ሬሳውም
ቢሆን የሚያለቅስ ይመስላል::
ሐኪሙ፤ ቄሱ፤ ሴትዬዋ ቃል ሳይተነፍሱ ማሪየስን አዩት:: ከውጭ የመጣ እንግዳ እሱ ብቻ ነው:: ማሪየስ ከነበረበት ትንሽ ነቅነቅ አለ። በጣም እፍረት ተሰማው፡፡ ያደረገውን ቆብ አውልቆ በእጅ ይዞት ስለነበር
ሳይታወቀው ከእጁ አምልጦ ከመሬት ወደቀ፡፡ ነገር ግን በጣም ከማዘኑ የተነሣ ቆቡን እንኳን ለመያዝ አቅም እንደሌለው ለማሳየት እንጂ እውነትም
አምልጦት አልነበረም::
ስለአባቱ የነበረውን አመለካከትና ግምት አስታውሶ ተጸጸተ::
መጸጸት ብቻ ሳይሆን ራሱን በጣም ነቀፈ:: ግን ጥፋቱ የእርሱ ነው? ኰሎኔሉ ወደኋላ የተወው ሀብት አልነበረም:: ከቤቱ ውስጥ የነበሩት እቃዎች ተሽጠው ለቀብሩ የወጣውን ወጪ እንኳን ለመሸፈን አልቻሉም፡፡ሠራተኛዋ አንዲት ወረቀት አግኝታ ለማሪየስ ሰጠችው:: ኩሎኔሉ ከመሞቱ
በፊት የጻፈው ማስታወሻ ሲሆን ቃሉም የሚከተለው ነው፡፡
«ለምወድህ ልጄ ፤ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ፡፡ እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል
ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ከወረቀቱ ጀርባ ላይ ኲሉኔሉ የጻፈው ማስታወሻ ደግሞ ‹‹በዚሁ በዋተርሉ ጦርነት አንድ የሃምሣ አለቃ ሕይወቴን አድኖአል:: ስሙ ቴናድዬ ይባላል:: ከፓሪስ ከተማ ወጣ ብሎ
ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንዲት አነስተኛ ሆቴል እንደነበረው አውቃለሁ:: ድንገት ካገኘኸው በተቻለህ እርሱን እርዳልኝ» የሚል ነበር፡፡
የአባቱ ፍቅር አስገድዶት ሳይሆን «የሞተን አክብር.» ብሎ በሚገፋፋን ውስጣዊ ኃይል ተመስጦ ማሪየስ ወረቀቱን በኃይል ጨመደደው::
ስለኩሎኔሉ ከዚያ በኋላ የታወቀ ነገር የለም:: ዩኒፎርሙንና
ጉራዴውን መሴይ ጊልኖርማንድ ለውራጅ እቃ ሸማች ሸጡት፡፡ ኰሎኔሉ የተከላቸውን አበቦች ጎረቤቱ ቀጥፈውና አትክልቱን አበላሽተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ድራሹን አጠፉት::
ማሪየስ ለሁለት ቀን እዚያው ቬርኖን ቆይቶ ከቀብሩ ሥነሥርዓት
በኋላ ወደ ፓሪስ ተመለሰ፡፡ ከዚያም የአባቱ መሞት ብዙም ሳይረብሸው ትምህርቱን ቀጠለ፡፡ ኵሎኔሉ በሞተ በሁለተኛው ቀን ተቀበረ፤ በሦስተኛ ቀን ተረሳ፡፡
ማሪየስ ለጥቂት ቀናት ከኮቱ ኮሌታ ላይ ጥቁር ጨርቅ አደረገ፡፡
የሀዘን ምልክት መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ሌላ የተደረገ ነገር አልነበረም::
👍12
ማሪየስ ካደገ በኋላም እንደ ልጅነቱ ቤተክርስቲያን መሄዱን
አላቋረጠም:: በልጅነቱ ከአክስቱና ከአያቱ ጋር ዘወትር ነበር የሚሄዱት፡፡
የሚሄዱት ደግሞ ቀደም ሲል ከተነጋገርንበት ከደግናል ጸሎት ቤት ነበር፡፡
አንድን ቀን እሑድ እንደለመደው ቤተክርስቲያን ሄዶ ከጀርባው
«መሴይ ማብዩፍ ቸርች ዎርደን» ተብሎ ከተጻፈበትና በወይን ጠጅ ቀለም ከተለበደ ወንበር ላይ ይቀመጣል፡፡ ጥቂት እንደቆየ አንድ ሽማግሌ ይመጠና
«ወንድም ይቅርታ፧ ይህ ቦታ ለእኔ የተመደበ ነው» ይሉታል፡፡ ማሪየስ
በአሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ነበር፡፡ ከአሳቡ ሲነቃ ማሪየስ ወንበሩን ለሽማግሌው ይለቅላቸውና ሽማግሌው ይቀመጣሉ፡፡
ቅዳሴ ካለቀ በኋላ እንኳን ማሪየስ ከሐሳቡ አልወጣም፡፡ ለሽማግሌው ወንበሩን ይልቀቅላቸው እንጂ ከሥፍራው ርቆ አልሄደም:: ሽማግሌው
የማሪየስ ከሐሳብ ባህር መዘፈቅ አይተው ከቅዳሴ በኋላ አናገሩት፡፡
«ይቅርታህን ልጄ፧ ቅድም አስቀየምኩህ መሰለኝ:: ምናልባት ምን ዓይነት ደፋር ሰው ነው' ብለህ ታዝበኸኝ እንደሆነ ላስረዳህ፡፡»
«ጌታዬ» አለ ማሪየስ፤ «ምንም አያስፈልግም፡፡»
«የለም» ሲሉ ሽማግሌው ቀጠሉ፤ «ተቀይመኸኝ እንድትሄድ
አልፈልግም፡፡ ስለዚያች ቦታ ብዙ የማስታውሰው ነገር ኣለኝ:: ለዚህች ቦታ የተለየ ስሜት አለኝ፡፡ እንደዚያ ያልኩትም ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ታሪኩን ላጫውትህ፡፡
«አንድ ብርቱ፡ ሰው ነበረ፡፡ ይህ ሰው እጅግ በጣም የሚወደው ልጅ ነበረው:: ሰውዬው በኣንድ ውርስ ምክንያት ከልጁ ጋር ይለያያል፡፡ ከተለያየም
በኋላ ልጁን ተመልሶ እንዳያይ ይደረጋል፡፡ አባት ልጁን ይወድ ስለነበር በየሁለት ወይም ሦስት ወር ከዚህች ሥፍራ እየመጣ ካስነሳሁህ ቦታ አጠገብ ካለው ምሰሶ ተደብቆ ልጁን አይቶ ይሄዳል:: አሥር ዓመት ሙሉ
ሌላ ሥራ ሳይኖረው ከዚህ እየመጣ ልጁን አይቶና እንባውን አፍስሶ ይሄዳል፡፡ ልጁ አባቱን ስለማያውቅ የሰውዬው መመላለስ ልብም አይልም::
ከሰውዬው ጋር ከጊዜ በኋላ ተዋውቀን ነው ታሪኩን ያጫወተኝ፡፡ ሰውየው
አንድ ሀብታም አማች ነበረው:: አባት ልጁን መጥቶ ቢያይ የአያቱንና የአክስቱን ሀብት ሊወርስ አይችልም ብሎ ማን እንዳስፈራራው ትዝ አይለኝም:: ብቻ አባት ልጁ አንድ ቀን ያንን ሀብት ወርሶ ደስ ብሎት
ይኖራል በሚል እምነት የራሱን ደስታና ፍቅር መስዋዕት አደረገ፡፡ የልጁ አባትና አያት ደግሞ በዘመነ ባለው የፖለቲካ ሽኩቻ የተነሣ
እንደማይስማሙም አጫውቶኛል፡፡ ስለፖለቲካ ጉዳይ መወያየቱ መልካም ነው:: ግን አንዳንድ ሰዎች የፖለቲካ ወሬ ከጀመሩ ማባሪያ የላቸውም::
ከዚህም በላይ የአንዱን ወገን ይዘው ጭልጥ ብለው ወደ አንድ አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው አንዱን ወገን ተከትሎ ዋተርሉ ላይ ስለተዋጋ ብቻ መጥፎ ሰው ነው ለማለት ያዳግታል:: አባትንና ልጅን በዚህ የተነሣ ማለያየት ደግሞ ተገቢ አይሆንም:: አሁን የምልህ ሰው ከቦናፓርቴ ጦር ውስጥ ኩለኔል ነበር፡፡ ዛሬ እንኳን ሰውዬው የሞተ ይመስለኛል፤ ቬርኖን
ከተባለ ከተማ ይኖር ነበር፡፡ ወንድሜ ቄስ ሲሆን የሚኖረው ከዚያ ከተማ ውስጥ ነው:: የሰውዬው ስም ፓንትመርሲ ይባላል፡፡»
ልጁ «ፓንትመርሲ!» ብሎ ስሙን ደግሞ ከተናገረ በኋላ ፊቱ
ኃይል ይለዋወጣል፡፡
«አዎን ፓንትመርሲ፧»
ታውቀዋለህ?»
«አባቴን» አለ ማሪየስ፧ «የሚሉት ሰው አባቴ ነበር፡፡»
ሽማግሌው እጁን በእጁ መታ:: «ያ ልጅ ማለት አንተ ነህ! ልክ
ነው፤ ልጁ የአንተን እድሜ ሊይዝ ይችላል:: እንግዲያውስ ልጁን በጣም የሚወድ አባት ነበረኝ ብለህ ልትኩራራ ይገባሃል፡፡»
ሽማግሌውና ማሪየስ ብዙ ተጫወቱ:: በመጨረሻ እጅ ለእጅ
ተያይዘው ወደ ሽማግሌው ቤት ሄዱ፡፡ በሚቀጥለው ቀን ማሪየስ አያቱን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
«ከጥቂት ጓደኞቼ ጋር አደን ለመሄድ ተነጋግረን ነበር፡፡ ለሦስት
ቀን ከእነርሱ ጋር ብሄድ ትፈቅድልኛለህ? »
«ለአራት ቀንም መሄድ ትችላለህ፡፡ ሂድና ራስህን አስደስት» አሉት..
ሽማግሌው ወደ ሴት ልጃቸው ዞር ብለው ከጠቀስዋት በኋላ «የፍቅር
ጉዳይ ይሆናል!» አሉዋት በሹክሹክታ፡ ሽማግሌው ያሰቡት ዓይነት ፍቅር ሳይሆን የአባት ፍቅር ነበር፡፡
ማሪየስ ወደ ቬርኖን ሄዶ ከአባቱ መቃብር አጠገብ ብዙ ጊዜ
አጠፋ:: ከቬርኖን ሲመለስ በቀጥታ ወደ ሕግ ትምህርት ቤት ቤተ መጻሕፍት ሄደ:: የቆዩ ጋዜጦችን ጠየቀ::ስለሪፑብሊኩና ስለንጉሠ ነገሥቱ ግዛት ታሪክና ስለሴንት ሄለና የተጻፉትን ብዙ አነበበ፡፡ ጋዜጣን፧ መጽሔትንና መጻሕፍትን አገላበጠ::ስለታላቁ ጦር ሠራዊት ባነበበ ጊዜ የአባቱ ስም ከዚያ ተጠቅሶ አየ:: አባቱ
ጆርጅ ፓንትመርሲ ከየትኛው ጄኔራል ጦር ስር እንደነበረ ሲፈልግ ከጄኔራል ማብዩፍ ቸርችዎርደን ጦር ስር እንደነበር ደረሰበት:: ጄኔራሉ ቤተክርስቲያን
ውስጥ ያገኛቸው ሽማግሌ እንደሆነ አወቀ:: እየተመላለሰ ጠየቃቸው፡፡ጄኔራሉ ስለአባቱ የጦር ሜዳ ጀብዱ ፤ስለሚሸጠው አበባ፤ ስለብቸኝነቱ ብዙ ነገሩት:: ማሪየስም ስለዚህ ተንኖ ስለጠፋውና ስለተረሳው ጀግና አባቱ ብዙ ተማረ::
በጀመረው ምርምር ብዙ ስለተዋጠ እነመሴይ ጊልኖርማንድን ረሳቸው:: ብዙ ጊዜ አይገናኙም:: የሚተያዩት በገበታ ጊዜ ብቻ ሆነ፡፡ሲፈልጉት አያገኙትም፤ «አሁን ወጣ» ይባላል፡፡ አክስትየው ማጉረምረም ጀመረች:: አያት ፈገግ እያሉ «እባክሽ ተይው፧ ከሚያቅበጠብጥ እድሜ ላይ
ስለሆነ ነው» ይላሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን «ይኼ ሰይጣን! ሙያ ያለው ነገር የሚሠራ መስሎኝ ነበር፤ ለካስ ለስሜቱ ነው ተገዥ የሆነው» ብለው ይናገራሉ፡፡
እውነትም የስሜት ተገዥ! ማሪየስ ስሜቱ አስገድዶት የአባቱ
ተገዥ ሆነ፡፡ በአጓዳኝ ደግሞ ከፍተኛ የሆነ የአመለካከት ለውጥ አደረበት። ቀስ እያለ በፊት የነበረው አሳብ በሌላ ተቀየረ:: የአስተሳሰብ አድማሱ
እየሰፋና እየተለወጠ መሄዱ ታወቀው:: ይኸው ነው፣ ብዙ ነገር ባጋጠመን ቁጥር የአስተሳሰብ ይዞታችንን ደረጃ በደረጃ መልኩን እየቀየረ ይሄዳል፡፡
የሚያነበው ታሪክ አስገረመው:: በመጀመሪያ ነገሩ ሁሉ ተምታቶበት ነበር፡፡ ሪፐብሊክ ወይም የንጉሠ ነገሥት ግዛት ማለት ለእርሱ ዝም ብሎ
በይበልጥ ይገረማል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ያለበት ይጠፋዋል፡፡ ቀስ በቀስ የመደነቁና ቃላት መስለውት ነበር፡፡ ስለሁለቱ የአስተዳደር ዘይቤዎች ባነበበ ቁጥር
የመገረሙ ነገር እየጠፉ ነገሮችን በግልጽ ወደማየትና ወደማመኑ አዘነበለ፡፡አርእስተ-ጉዳዮችን ያለ ስህተት መተንተን ቻለ:: አብዮትና የንጉሠ አገዛዝ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ቁልጭ ብሎ ታየው:: ሰዎች ራሳቸውን እንዴት እንደሚከፋፍሉ ታወቀው። እውነተኛ ሪፑብሊክ የሰዎች መብት ማስከበሪያና የንጉሠ ነገሥት አገዛዝ ማክተሚያ መሆኑን ተረዳ፡፡ «ይዂማ ጥሩ ነው» ሲል አሰበ
በጣም ተጸጸተ፡፡ ራሱንም ወቀሰ፡፡ አባቱ በሕይወት ቢኖርና ሊያገኘው
ቢችል ወይም በአንድ ዓይነት ተአምር ከተቀበረበት ነፍስ ዘርቶ ቢነሣ እንዴት አድርጎ ወደ እርሱ በርሮና ሮጦ ሄዶ በማልቀስ «አባዬ፣ መጣሁልህ!
እኔ ልጅህ ነኝ! የእኔ ልብ እንዳንተው ልብ ነው!» ቢለው ምንኛ ደስ ባለው::ይህ ቢሆን ያቅፈዋል፤ ይስመዋል፤ ፀጉሩን በእንባ ያርስለታል፤ ከፊቱ ላይ
የነበረውን ጠባሳ ያሻሽለታል፤ እጆቹን ጥብቅ አድርጎ ይይዛል፤ ልብሱን ይነካካል፤ ጫማውን ይስማል::
አላቋረጠም:: በልጅነቱ ከአክስቱና ከአያቱ ጋር ዘወትር ነበር የሚሄዱት፡፡
የሚሄዱት ደግሞ ቀደም ሲል ከተነጋገርንበት ከደግናል ጸሎት ቤት ነበር፡፡
አንድን ቀን እሑድ እንደለመደው ቤተክርስቲያን ሄዶ ከጀርባው
«መሴይ ማብዩፍ ቸርች ዎርደን» ተብሎ ከተጻፈበትና በወይን ጠጅ ቀለም ከተለበደ ወንበር ላይ ይቀመጣል፡፡ ጥቂት እንደቆየ አንድ ሽማግሌ ይመጠና
«ወንድም ይቅርታ፧ ይህ ቦታ ለእኔ የተመደበ ነው» ይሉታል፡፡ ማሪየስ
በአሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ነበር፡፡ ከአሳቡ ሲነቃ ማሪየስ ወንበሩን ለሽማግሌው ይለቅላቸውና ሽማግሌው ይቀመጣሉ፡፡
ቅዳሴ ካለቀ በኋላ እንኳን ማሪየስ ከሐሳቡ አልወጣም፡፡ ለሽማግሌው ወንበሩን ይልቀቅላቸው እንጂ ከሥፍራው ርቆ አልሄደም:: ሽማግሌው
የማሪየስ ከሐሳብ ባህር መዘፈቅ አይተው ከቅዳሴ በኋላ አናገሩት፡፡
«ይቅርታህን ልጄ፧ ቅድም አስቀየምኩህ መሰለኝ:: ምናልባት ምን ዓይነት ደፋር ሰው ነው' ብለህ ታዝበኸኝ እንደሆነ ላስረዳህ፡፡»
«ጌታዬ» አለ ማሪየስ፤ «ምንም አያስፈልግም፡፡»
«የለም» ሲሉ ሽማግሌው ቀጠሉ፤ «ተቀይመኸኝ እንድትሄድ
አልፈልግም፡፡ ስለዚያች ቦታ ብዙ የማስታውሰው ነገር ኣለኝ:: ለዚህች ቦታ የተለየ ስሜት አለኝ፡፡ እንደዚያ ያልኩትም ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ታሪኩን ላጫውትህ፡፡
«አንድ ብርቱ፡ ሰው ነበረ፡፡ ይህ ሰው እጅግ በጣም የሚወደው ልጅ ነበረው:: ሰውዬው በኣንድ ውርስ ምክንያት ከልጁ ጋር ይለያያል፡፡ ከተለያየም
በኋላ ልጁን ተመልሶ እንዳያይ ይደረጋል፡፡ አባት ልጁን ይወድ ስለነበር በየሁለት ወይም ሦስት ወር ከዚህች ሥፍራ እየመጣ ካስነሳሁህ ቦታ አጠገብ ካለው ምሰሶ ተደብቆ ልጁን አይቶ ይሄዳል:: አሥር ዓመት ሙሉ
ሌላ ሥራ ሳይኖረው ከዚህ እየመጣ ልጁን አይቶና እንባውን አፍስሶ ይሄዳል፡፡ ልጁ አባቱን ስለማያውቅ የሰውዬው መመላለስ ልብም አይልም::
ከሰውዬው ጋር ከጊዜ በኋላ ተዋውቀን ነው ታሪኩን ያጫወተኝ፡፡ ሰውየው
አንድ ሀብታም አማች ነበረው:: አባት ልጁን መጥቶ ቢያይ የአያቱንና የአክስቱን ሀብት ሊወርስ አይችልም ብሎ ማን እንዳስፈራራው ትዝ አይለኝም:: ብቻ አባት ልጁ አንድ ቀን ያንን ሀብት ወርሶ ደስ ብሎት
ይኖራል በሚል እምነት የራሱን ደስታና ፍቅር መስዋዕት አደረገ፡፡ የልጁ አባትና አያት ደግሞ በዘመነ ባለው የፖለቲካ ሽኩቻ የተነሣ
እንደማይስማሙም አጫውቶኛል፡፡ ስለፖለቲካ ጉዳይ መወያየቱ መልካም ነው:: ግን አንዳንድ ሰዎች የፖለቲካ ወሬ ከጀመሩ ማባሪያ የላቸውም::
ከዚህም በላይ የአንዱን ወገን ይዘው ጭልጥ ብለው ወደ አንድ አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው አንዱን ወገን ተከትሎ ዋተርሉ ላይ ስለተዋጋ ብቻ መጥፎ ሰው ነው ለማለት ያዳግታል:: አባትንና ልጅን በዚህ የተነሣ ማለያየት ደግሞ ተገቢ አይሆንም:: አሁን የምልህ ሰው ከቦናፓርቴ ጦር ውስጥ ኩለኔል ነበር፡፡ ዛሬ እንኳን ሰውዬው የሞተ ይመስለኛል፤ ቬርኖን
ከተባለ ከተማ ይኖር ነበር፡፡ ወንድሜ ቄስ ሲሆን የሚኖረው ከዚያ ከተማ ውስጥ ነው:: የሰውዬው ስም ፓንትመርሲ ይባላል፡፡»
ልጁ «ፓንትመርሲ!» ብሎ ስሙን ደግሞ ከተናገረ በኋላ ፊቱ
ኃይል ይለዋወጣል፡፡
«አዎን ፓንትመርሲ፧»
ታውቀዋለህ?»
«አባቴን» አለ ማሪየስ፧ «የሚሉት ሰው አባቴ ነበር፡፡»
ሽማግሌው እጁን በእጁ መታ:: «ያ ልጅ ማለት አንተ ነህ! ልክ
ነው፤ ልጁ የአንተን እድሜ ሊይዝ ይችላል:: እንግዲያውስ ልጁን በጣም የሚወድ አባት ነበረኝ ብለህ ልትኩራራ ይገባሃል፡፡»
ሽማግሌውና ማሪየስ ብዙ ተጫወቱ:: በመጨረሻ እጅ ለእጅ
ተያይዘው ወደ ሽማግሌው ቤት ሄዱ፡፡ በሚቀጥለው ቀን ማሪየስ አያቱን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
«ከጥቂት ጓደኞቼ ጋር አደን ለመሄድ ተነጋግረን ነበር፡፡ ለሦስት
ቀን ከእነርሱ ጋር ብሄድ ትፈቅድልኛለህ? »
«ለአራት ቀንም መሄድ ትችላለህ፡፡ ሂድና ራስህን አስደስት» አሉት..
ሽማግሌው ወደ ሴት ልጃቸው ዞር ብለው ከጠቀስዋት በኋላ «የፍቅር
ጉዳይ ይሆናል!» አሉዋት በሹክሹክታ፡ ሽማግሌው ያሰቡት ዓይነት ፍቅር ሳይሆን የአባት ፍቅር ነበር፡፡
ማሪየስ ወደ ቬርኖን ሄዶ ከአባቱ መቃብር አጠገብ ብዙ ጊዜ
አጠፋ:: ከቬርኖን ሲመለስ በቀጥታ ወደ ሕግ ትምህርት ቤት ቤተ መጻሕፍት ሄደ:: የቆዩ ጋዜጦችን ጠየቀ::ስለሪፑብሊኩና ስለንጉሠ ነገሥቱ ግዛት ታሪክና ስለሴንት ሄለና የተጻፉትን ብዙ አነበበ፡፡ ጋዜጣን፧ መጽሔትንና መጻሕፍትን አገላበጠ::ስለታላቁ ጦር ሠራዊት ባነበበ ጊዜ የአባቱ ስም ከዚያ ተጠቅሶ አየ:: አባቱ
ጆርጅ ፓንትመርሲ ከየትኛው ጄኔራል ጦር ስር እንደነበረ ሲፈልግ ከጄኔራል ማብዩፍ ቸርችዎርደን ጦር ስር እንደነበር ደረሰበት:: ጄኔራሉ ቤተክርስቲያን
ውስጥ ያገኛቸው ሽማግሌ እንደሆነ አወቀ:: እየተመላለሰ ጠየቃቸው፡፡ጄኔራሉ ስለአባቱ የጦር ሜዳ ጀብዱ ፤ስለሚሸጠው አበባ፤ ስለብቸኝነቱ ብዙ ነገሩት:: ማሪየስም ስለዚህ ተንኖ ስለጠፋውና ስለተረሳው ጀግና አባቱ ብዙ ተማረ::
በጀመረው ምርምር ብዙ ስለተዋጠ እነመሴይ ጊልኖርማንድን ረሳቸው:: ብዙ ጊዜ አይገናኙም:: የሚተያዩት በገበታ ጊዜ ብቻ ሆነ፡፡ሲፈልጉት አያገኙትም፤ «አሁን ወጣ» ይባላል፡፡ አክስትየው ማጉረምረም ጀመረች:: አያት ፈገግ እያሉ «እባክሽ ተይው፧ ከሚያቅበጠብጥ እድሜ ላይ
ስለሆነ ነው» ይላሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን «ይኼ ሰይጣን! ሙያ ያለው ነገር የሚሠራ መስሎኝ ነበር፤ ለካስ ለስሜቱ ነው ተገዥ የሆነው» ብለው ይናገራሉ፡፡
እውነትም የስሜት ተገዥ! ማሪየስ ስሜቱ አስገድዶት የአባቱ
ተገዥ ሆነ፡፡ በአጓዳኝ ደግሞ ከፍተኛ የሆነ የአመለካከት ለውጥ አደረበት። ቀስ እያለ በፊት የነበረው አሳብ በሌላ ተቀየረ:: የአስተሳሰብ አድማሱ
እየሰፋና እየተለወጠ መሄዱ ታወቀው:: ይኸው ነው፣ ብዙ ነገር ባጋጠመን ቁጥር የአስተሳሰብ ይዞታችንን ደረጃ በደረጃ መልኩን እየቀየረ ይሄዳል፡፡
የሚያነበው ታሪክ አስገረመው:: በመጀመሪያ ነገሩ ሁሉ ተምታቶበት ነበር፡፡ ሪፐብሊክ ወይም የንጉሠ ነገሥት ግዛት ማለት ለእርሱ ዝም ብሎ
በይበልጥ ይገረማል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ያለበት ይጠፋዋል፡፡ ቀስ በቀስ የመደነቁና ቃላት መስለውት ነበር፡፡ ስለሁለቱ የአስተዳደር ዘይቤዎች ባነበበ ቁጥር
የመገረሙ ነገር እየጠፉ ነገሮችን በግልጽ ወደማየትና ወደማመኑ አዘነበለ፡፡አርእስተ-ጉዳዮችን ያለ ስህተት መተንተን ቻለ:: አብዮትና የንጉሠ አገዛዝ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ቁልጭ ብሎ ታየው:: ሰዎች ራሳቸውን እንዴት እንደሚከፋፍሉ ታወቀው። እውነተኛ ሪፑብሊክ የሰዎች መብት ማስከበሪያና የንጉሠ ነገሥት አገዛዝ ማክተሚያ መሆኑን ተረዳ፡፡ «ይዂማ ጥሩ ነው» ሲል አሰበ
በጣም ተጸጸተ፡፡ ራሱንም ወቀሰ፡፡ አባቱ በሕይወት ቢኖርና ሊያገኘው
ቢችል ወይም በአንድ ዓይነት ተአምር ከተቀበረበት ነፍስ ዘርቶ ቢነሣ እንዴት አድርጎ ወደ እርሱ በርሮና ሮጦ ሄዶ በማልቀስ «አባዬ፣ መጣሁልህ!
እኔ ልጅህ ነኝ! የእኔ ልብ እንዳንተው ልብ ነው!» ቢለው ምንኛ ደስ ባለው::ይህ ቢሆን ያቅፈዋል፤ ይስመዋል፤ ፀጉሩን በእንባ ያርስለታል፤ ከፊቱ ላይ
የነበረውን ጠባሳ ያሻሽለታል፤ እጆቹን ጥብቅ አድርጎ ይይዛል፤ ልብሱን ይነካካል፤ ጫማውን ይስማል::
👍21
ለምን አባቱ ያለ እድሜ ይሞታል? ትክክለኛውን ፍርድ ሳይቀበል
በልጅ ፍቅር ሳይረካ ለምን ቶሎ ሞተ? ማሪየስ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡እውቀቱ እየጎለበተና እምነቱ እየጠና ሄደ፡፡ ለአባቱና ለአገሩ ያለው ፍቅር ሰውነቱ ውስጥ ሠርጾ ገብቶ አንገበገበው:: በየደቂቃው እውነት እየጎላ መጥቶ የአስተሳሰቡን አድማስ አሰፋለት:: በመንፈስ ያደገ መሰለው::
አንድ ቀን ማታ ሻማ አብርቶ መጽሐፍ እያነበበ ከክፍሉ ውስጥ
ብቻውን ቁጭ ይላል:: የነበረበት ክፍል መስኮት ተከፍቶአል። ብዙ ዓይነት ነገር ከጭንቅላቱ ውስጥ ገብቶ አሳቡን አመሰቃቀለበት:: ሌሊት ሌሊት እኮ ስንት ነገር ይታያል! የሚርመሰመስ ድምፅ ይሰማል፤ ከየት እንደሚመጣ
ግን አይታወቅም:: ካለንበት ምድር አንድ ሺህ ሁለት መቶ ጊዜ የምትተልቀው ጁፒተር እንደ ቁርበተ-አሊም እያበራች ማታ ማታ ነው የምትታየው::ማታ ማታ ከዋክብት ይብለጨለጫሉ፤ ሌሊት ደግሞ የፍርሃት መስፈሪያ ነው....
💫ይቀጥላል💫
በልጅ ፍቅር ሳይረካ ለምን ቶሎ ሞተ? ማሪየስ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡እውቀቱ እየጎለበተና እምነቱ እየጠና ሄደ፡፡ ለአባቱና ለአገሩ ያለው ፍቅር ሰውነቱ ውስጥ ሠርጾ ገብቶ አንገበገበው:: በየደቂቃው እውነት እየጎላ መጥቶ የአስተሳሰቡን አድማስ አሰፋለት:: በመንፈስ ያደገ መሰለው::
አንድ ቀን ማታ ሻማ አብርቶ መጽሐፍ እያነበበ ከክፍሉ ውስጥ
ብቻውን ቁጭ ይላል:: የነበረበት ክፍል መስኮት ተከፍቶአል። ብዙ ዓይነት ነገር ከጭንቅላቱ ውስጥ ገብቶ አሳቡን አመሰቃቀለበት:: ሌሊት ሌሊት እኮ ስንት ነገር ይታያል! የሚርመሰመስ ድምፅ ይሰማል፤ ከየት እንደሚመጣ
ግን አይታወቅም:: ካለንበት ምድር አንድ ሺህ ሁለት መቶ ጊዜ የምትተልቀው ጁፒተር እንደ ቁርበተ-አሊም እያበራች ማታ ማታ ነው የምትታየው::ማታ ማታ ከዋክብት ይብለጨለጫሉ፤ ሌሊት ደግሞ የፍርሃት መስፈሪያ ነው....
💫ይቀጥላል💫
👍10❤3
#ጌታችን_ተነስቷል…!
በቃሉ መሠረት፤ ጌታ ከድንግል ተወለደ፣
ከሠማየ ሠማያት መጣ፤ እኛን ስለወደደ፡፡
ሠውን ሊያድን መጣ፣
ከሐጢዓት አረንቋ፤
………….ሃርነት ሊያወጣ፣
ሞትን በሞቱ ሊደመስስ፤
…………ሠይጣንን ሊቀጣ፡፡
እንትፍ ብሎ ምራቁን፤ እውሩን አበራ፣
የዓለም ብርሃንነቱ፤ በምድር ላይ በራ፡፡
የሚያዩም …. እንዲታወሩ፣
…… በሐጢዓታቸው እንዲታሰሩ፡፡
ጌታ ለፍርድ መጣ፣
ምኩራቡን ሊገለብጥ ስህተትን ሊያወጣ፡፡
የማያዩ …. እንዲያዩ ፣
……….. ጌታን እንዲለዩ፡፡
መስዋዕት ሆኖ መጣ፣
ዓለምን ነፃ ሊያወጣ፡፡
አይሁድ ሊወግሩት፤ ድንጋይን ቢያነሱ፣
ቀኑ ስላልሆነ፤ እምቢ አለ መንፈሱ፡፡
የኔ ጌታ…..
አልዓዛርን ከተኛበት፤ በድምፁ ቀሰቀሰ፣
ድውያውንን ሁሉ፤ አንድ በአንድ ፈወሰ፡፡
የአላዛር ወላጆች፤ አይሁድን ስለፈሩ፣
ድንቅ ታምራቱን፤ ሳይናገሩ ቀሩ፡፡
እሱ ሙሉ ሠው ነው፤ ጠይቁት ቢሉም፣
ፈሪሳውያኑ፤ ሊያምኑ ግን አልቻሉም፡፡
የእግዚአብሔርን ስራ፤ በብዙ ገለጠ፣
እልፍ ታዓምር ሠራ፣ ክፋትን ለወጠ፡፡
በዓለም እያለ፤ የዓለም ብርሃን ሆነ፣
የተኛውን ሁሉ፤ በፍቅሩ አባነነ፡፡
የካህናት አለቆች፤ ሸንጎ ተቀመጡ፣
ፈሪሳውያኑ፤ መያዣ አወጡ፡፡
መከሩ.. ዘከሩ፤ እቅዳቸውን ነደፉ፣
የቀያፋን ምክር፤ በድምፅ አሳለፉ፡፡
ከራሱ አይደለም፤ ቀያፋ የተናገረ፣
ስለህዝቡ ይሞት ዘንድ፤ ቃል ስለነበረ፡፡
ትዕንቢቱ ሊፈፀም፤ የግድ ስለሆነ፣
የቀያፋ ምክር፤ ተፈፃሚ ሆነ፡፡
የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉ፣
መጡ ህዝቡ ሁሉ፣
ሆሳዕና በአርያም እያሉ፡፡
ትዕንቢቱ እንዲፈፀም፤ ኢየሩሳሌም ተመረጠ፣
በአህያ ውርንጫ፤ ጌታ ተቀመጠ፡፡
የሠው ልጅ ሊከብር፤ ሠዓቱ ደረሰ፣
ነፍሴ ታውካለች፤ ብሎ እየመለሰ፡፡
በዓሉ ቢደርስም የአይሁዶች ፋሲካ፣
የእኛ ፋሲካችን፤ በፍቅር ተተካ፡፡
እኔ ቁራሽ አጥቅሼ፤ ለሱ የምሠጠው፣
እሱ ነው እኔን፤ በገንዘብ የሚሸጠው፤
………………………ብሎ ተናገረ፣
………………………ቀድሞ መሠከረ፡፡
ዲያቢሎስ ይሁዳን በሃሳቡ ደለለ፣
የአስቆሮቱ ይሁዳ፤ ለመሸጥ ቸኮለ፣
ጌታን አሳልፎ ሊሠጥ፤ ልቦናው ታለለ፡፡
ልባችሁ አይታወክ በእግዚአብሄር እመኑ፣
ቀኔ ደርሷልና፤ ምንም አትዘኑ፡፡
አላቸው ኢየሱስ፤ ለደቀመዛሙርቱ፣
ስፍራ ሊያዘጋጅላቸው፤ ሊፈፀም ትእንቢቱ፡፡
የካህናት አለቆች፤ ወደ ጌታ መጡ፣
በይሁዳ መሪነት፤ ኢየሱስን ሊይዙ፤
……………………. አምላክን ሊቀጡ፡፡
ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ቢጠይቃቸው፣
‹‹የናዝሬቱ ኢየሱስን›› ሲሉ፤
……………………‹‹እኔ ነኝ›› አላቸው፡፡
ስምዖን ጴጥሮስም፤ መዘዘ ሠይፉን፣
የማልኮስን ጆሮ ቆረጠ፤
…………………………… ሊዘጋ አፉን፡፡
ኢየሱስም አለ፤
………. ‹‹ሠይፍህን ወደ ሠገባው ክተት››፣
አብ የሠጠኝን ፅዋ፤ ልጠጣት በድፍረት፡፡
ለእኔ ብሎ ጌታ፤ ሕመሜን ታመመ ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ መስቀል ተሸከመ፡፡
ጌታችን ታሠረ፤ ምንም ሳያጠፋ፣
ቃሉ ሊፈፀም፤ ምክሩ የቀያፋ፡፡
ክርስቶስ ኢየሱስን፤ ጲላጦስ ገረፈው፣
የእሾህ አክሊል ጎንጉኖ፤
…………….. ከአናቱ አሳረፈው፡፡
ተሳለቁበት ጌታን፣ በጥፊ መቱት፣
በውጪ አውጥተው፤ ለህዝቡ ሠጡት፡፡
ለእኔ ብሎ ጌታ፤ ሕመሜን ታመመ ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ መስቀል ተሸከመ፡፡
መስቀሉን አሸክመው፤ ወሰዱት ጎልጎታ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ ነፍሱን ሊሠጥ ጌታ፡፡
ከሌቦቹ መሃል፤ ጌታዬን ሠቀሉት፣
ባልዋለበት ሃጢያት፤ አውለው አኖሩት፡፡
ጲላጦስም ፃፈ፣ የአይሁድ ንጉስ ብሎ፤
ከጭፍራዎቹ አንዱ፤ ጎኑ ላይ ጦሩን ተክሎ፡፡
ደምና ውሃ ወጣ፤ ከተወጋው ጎኑ፣
ስለኛ ሲሠዋ፤ ጌታ ማሳዘኑ፡፡
ለእኔ ብሎ ጌታ፤ ሕመሜን ታመመ ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ መስቀል ተሸከመ፡፡
ጌታ ነፍሱን ሠጠ፤ ዓለምን ፈወሰ፣
ሠውን ለማዳን ብሎ፤ ደሙን አፈሰሰ፡፡
የአርማትያሱ ዮሴፍ፤ ስጋውን ለመነ፣
ገንዞ ሊቀብር፤ ፍፁም እያዘነ፡፡
እንደአይሁድ ልማድ፤ ገንዘው ቀበሩት፣
በአትክልቱ ስፍራ፤ ጌታዬን አኖሩት፡፡
መግደላዊት ማርያም መጣች በማለዳ፣
ቢፈለግ ባዶ ነው፤ የመቃብሩ ጓዳ፡፡
ደቀመዛሙርቱ ሁሉ፤ ወደ መቃብር ሄዱ፣
የመፅሐፉን ቃል፤ ከቶ ሳይረዱ፡፡
እልል በሉ ሠዎች፤ ጌታችን ተነስቷል፣
የፋሲካው ንጉስ፤ ሞትን ድል አድርጓል፡፡
መልካም የፋሲካ በዓል…!
🔘እሸቱ ብሩ ይትባረክ🔘
በቃሉ መሠረት፤ ጌታ ከድንግል ተወለደ፣
ከሠማየ ሠማያት መጣ፤ እኛን ስለወደደ፡፡
ሠውን ሊያድን መጣ፣
ከሐጢዓት አረንቋ፤
………….ሃርነት ሊያወጣ፣
ሞትን በሞቱ ሊደመስስ፤
…………ሠይጣንን ሊቀጣ፡፡
እንትፍ ብሎ ምራቁን፤ እውሩን አበራ፣
የዓለም ብርሃንነቱ፤ በምድር ላይ በራ፡፡
የሚያዩም …. እንዲታወሩ፣
…… በሐጢዓታቸው እንዲታሰሩ፡፡
ጌታ ለፍርድ መጣ፣
ምኩራቡን ሊገለብጥ ስህተትን ሊያወጣ፡፡
የማያዩ …. እንዲያዩ ፣
……….. ጌታን እንዲለዩ፡፡
መስዋዕት ሆኖ መጣ፣
ዓለምን ነፃ ሊያወጣ፡፡
አይሁድ ሊወግሩት፤ ድንጋይን ቢያነሱ፣
ቀኑ ስላልሆነ፤ እምቢ አለ መንፈሱ፡፡
የኔ ጌታ…..
አልዓዛርን ከተኛበት፤ በድምፁ ቀሰቀሰ፣
ድውያውንን ሁሉ፤ አንድ በአንድ ፈወሰ፡፡
የአላዛር ወላጆች፤ አይሁድን ስለፈሩ፣
ድንቅ ታምራቱን፤ ሳይናገሩ ቀሩ፡፡
እሱ ሙሉ ሠው ነው፤ ጠይቁት ቢሉም፣
ፈሪሳውያኑ፤ ሊያምኑ ግን አልቻሉም፡፡
የእግዚአብሔርን ስራ፤ በብዙ ገለጠ፣
እልፍ ታዓምር ሠራ፣ ክፋትን ለወጠ፡፡
በዓለም እያለ፤ የዓለም ብርሃን ሆነ፣
የተኛውን ሁሉ፤ በፍቅሩ አባነነ፡፡
የካህናት አለቆች፤ ሸንጎ ተቀመጡ፣
ፈሪሳውያኑ፤ መያዣ አወጡ፡፡
መከሩ.. ዘከሩ፤ እቅዳቸውን ነደፉ፣
የቀያፋን ምክር፤ በድምፅ አሳለፉ፡፡
ከራሱ አይደለም፤ ቀያፋ የተናገረ፣
ስለህዝቡ ይሞት ዘንድ፤ ቃል ስለነበረ፡፡
ትዕንቢቱ ሊፈፀም፤ የግድ ስለሆነ፣
የቀያፋ ምክር፤ ተፈፃሚ ሆነ፡፡
የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉ፣
መጡ ህዝቡ ሁሉ፣
ሆሳዕና በአርያም እያሉ፡፡
ትዕንቢቱ እንዲፈፀም፤ ኢየሩሳሌም ተመረጠ፣
በአህያ ውርንጫ፤ ጌታ ተቀመጠ፡፡
የሠው ልጅ ሊከብር፤ ሠዓቱ ደረሰ፣
ነፍሴ ታውካለች፤ ብሎ እየመለሰ፡፡
በዓሉ ቢደርስም የአይሁዶች ፋሲካ፣
የእኛ ፋሲካችን፤ በፍቅር ተተካ፡፡
እኔ ቁራሽ አጥቅሼ፤ ለሱ የምሠጠው፣
እሱ ነው እኔን፤ በገንዘብ የሚሸጠው፤
………………………ብሎ ተናገረ፣
………………………ቀድሞ መሠከረ፡፡
ዲያቢሎስ ይሁዳን በሃሳቡ ደለለ፣
የአስቆሮቱ ይሁዳ፤ ለመሸጥ ቸኮለ፣
ጌታን አሳልፎ ሊሠጥ፤ ልቦናው ታለለ፡፡
ልባችሁ አይታወክ በእግዚአብሄር እመኑ፣
ቀኔ ደርሷልና፤ ምንም አትዘኑ፡፡
አላቸው ኢየሱስ፤ ለደቀመዛሙርቱ፣
ስፍራ ሊያዘጋጅላቸው፤ ሊፈፀም ትእንቢቱ፡፡
የካህናት አለቆች፤ ወደ ጌታ መጡ፣
በይሁዳ መሪነት፤ ኢየሱስን ሊይዙ፤
……………………. አምላክን ሊቀጡ፡፡
ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ቢጠይቃቸው፣
‹‹የናዝሬቱ ኢየሱስን›› ሲሉ፤
……………………‹‹እኔ ነኝ›› አላቸው፡፡
ስምዖን ጴጥሮስም፤ መዘዘ ሠይፉን፣
የማልኮስን ጆሮ ቆረጠ፤
…………………………… ሊዘጋ አፉን፡፡
ኢየሱስም አለ፤
………. ‹‹ሠይፍህን ወደ ሠገባው ክተት››፣
አብ የሠጠኝን ፅዋ፤ ልጠጣት በድፍረት፡፡
ለእኔ ብሎ ጌታ፤ ሕመሜን ታመመ ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ መስቀል ተሸከመ፡፡
ጌታችን ታሠረ፤ ምንም ሳያጠፋ፣
ቃሉ ሊፈፀም፤ ምክሩ የቀያፋ፡፡
ክርስቶስ ኢየሱስን፤ ጲላጦስ ገረፈው፣
የእሾህ አክሊል ጎንጉኖ፤
…………….. ከአናቱ አሳረፈው፡፡
ተሳለቁበት ጌታን፣ በጥፊ መቱት፣
በውጪ አውጥተው፤ ለህዝቡ ሠጡት፡፡
ለእኔ ብሎ ጌታ፤ ሕመሜን ታመመ ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ መስቀል ተሸከመ፡፡
መስቀሉን አሸክመው፤ ወሰዱት ጎልጎታ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ ነፍሱን ሊሠጥ ጌታ፡፡
ከሌቦቹ መሃል፤ ጌታዬን ሠቀሉት፣
ባልዋለበት ሃጢያት፤ አውለው አኖሩት፡፡
ጲላጦስም ፃፈ፣ የአይሁድ ንጉስ ብሎ፤
ከጭፍራዎቹ አንዱ፤ ጎኑ ላይ ጦሩን ተክሎ፡፡
ደምና ውሃ ወጣ፤ ከተወጋው ጎኑ፣
ስለኛ ሲሠዋ፤ ጌታ ማሳዘኑ፡፡
ለእኔ ብሎ ጌታ፤ ሕመሜን ታመመ ፣
ለሠው ፍቅር ብሎ፤ መስቀል ተሸከመ፡፡
ጌታ ነፍሱን ሠጠ፤ ዓለምን ፈወሰ፣
ሠውን ለማዳን ብሎ፤ ደሙን አፈሰሰ፡፡
የአርማትያሱ ዮሴፍ፤ ስጋውን ለመነ፣
ገንዞ ሊቀብር፤ ፍፁም እያዘነ፡፡
እንደአይሁድ ልማድ፤ ገንዘው ቀበሩት፣
በአትክልቱ ስፍራ፤ ጌታዬን አኖሩት፡፡
መግደላዊት ማርያም መጣች በማለዳ፣
ቢፈለግ ባዶ ነው፤ የመቃብሩ ጓዳ፡፡
ደቀመዛሙርቱ ሁሉ፤ ወደ መቃብር ሄዱ፣
የመፅሐፉን ቃል፤ ከቶ ሳይረዱ፡፡
እልል በሉ ሠዎች፤ ጌታችን ተነስቷል፣
የፋሲካው ንጉስ፤ ሞትን ድል አድርጓል፡፡
መልካም የፋሲካ በዓል…!
🔘እሸቱ ብሩ ይትባረክ🔘
👍16
#የመደርደሪያው_ጫፍ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
“አብርሃም !"
“አቤት”
“ስምህ ማነው ?” አለኝ ፊቴ የተቀመጠው ደግ ፖሊስ፡፡ ፊቱን ሳየው ማፏጨት ጀምሮ መሐል
ላይ ሲደርስ ሊያፏጭ የፈለገው ዜማ የጠፋበት ጎረምሳ ይመስላል፡፡ ስሜን ጠርቶ ስምህ
ማነው? ሲለኝ ቢጎርመኝም በትህትና ተናገርኩ፡፡
“አብረሃም”
“አ.ብ.ር.ሃ.ም”ፊደል የቆጠረ ፃፈ፡፡
የአባትህ ስም" ነገርኩት ጻፈ፡፡
“አብረሃም ! ለምንድነው የሰው ባል ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በሚዛን ስሀን የፈነከትከው”
አለኝ፡፡ አጠያየቁ 'ባትመልስልኝም ግድ የለም” የሚመስል ሰሜት ነበረበት፡፡
ኧረ ስላበሳጨኝ ነው እንጂ እኔ ሰው ጋር ተሰዳድቤ እንኳን አላውቅም፤ እንኳን በጭካኔ..
ዓረፍተ ነገሬ እየተወለጋገደ መለስኩ፡፡
“እሱማ ታስታውቃለህ፡፡ ጨዋ ልጅ ነህ፡፡ ጨዋ ባትሆን ኖሮ ሰሀኑ ላይ የተቀመጠውን አንድ ኪሎ መመዘኛ ብረት ትተህ በሰሃኑ ብቻ ኣትፈነከተውም ነበር፡፡ ጎበዝ ራስህን መግዛትህ ትልቅ ነገር ነው:: ራሱን የሚገዛ አገር ከሚገዛ ይበልጣል ይባላል፡፡ ቢሆንም ግን አብረሃም ዋስ ትጠራለሁ፡፡
“እሺ አልኩና ትዝ ሲለኝ የሚዋስ ሰው የለኝም፡፡
እንካ ደውልና ጥራ !" ብሎ ቅድም ወደ ማረፊያ ቤት ስገባ የተቀብለኝን ስልኬን ወደ ፊቴ
ገፋልኝ፡፡
ወደ አእምሮዬ የመጣችው ሂሉ ነበረች፡፡ ግን ሀሳቡ በራሱ ሳቁን አመጣብኝና ተውኩት፡፡ ባሏን
ፈንክቼ ሚስቱን ዋስ ሁነኝ ማለት በእርግጥ ያስቃል፡፡ ዝም ብዬ ዋስ የሚሆነኝ ሰው ሳወጣና ሳወርድ ቆየሁና "ዋስ የለኝም !" አልኩት ለደጉ ፖሊስ፡፡
እንዴት ዋስ አይኖርህም? ከሰው አልተወለድክም ? ጓደኛ የለህም? ወይም ጎረቤት ” አለ ፖሊሱ፡፡ እንዲህ ሲለኝ ዘመድም ጓደኛም የምለው ሰው እንደሌለኝ ትዝ አለኝና እንባዬ በዐይኔ
ግጥም አለ፡፡
“ደህና እስቲ የአንድ ሰው ስም ንገረኝ አለ ለመፃፍ እየተመቻቸ፡፡
“የአንድ ሰው ማለት?
"በቃ ዝም ብለህ የአንድ ሰው ስም ንገረኝ” አለ፡፡
"እበራ " ማረፊያ ቤቷ ውስጥ አበራ አንበሳው ! የሚል ስም በተወለጋገደ የእጅ ጽሁፍ አይቼ
ሰለነበር አፌ ላይ ድንገት መጣልኝ፡፡
“የአባቱ ስም ማነው ?"
"እኔ ንጃ ተገርሞ አየኝና ፈገግ ብሎ አጉተመተመ፡፡
“በቃ አበራ ቀለጠ ብዬዋለሁ - ዋስሀ ነው:: አብረሃም አምንሃለሁ፤ ጥሩ ልጅ ነህ፤ ይሄ መቼም
የዕለት ግጭት ነው:: ከአሁን በኋላ እዛ ሱቅ አካባቢ ብትደርስ ግን ዋስህን እቀፈድደዋለሁ፤
' ነግሬያለሁ” አለ እየሳቀ፡፡
እዚች ምድር ላይ ይኑር አይኑር በማይታወቅ ዋስ ከእስር የወጣሁ ሚስኪን ሰው፣ ቀበቶዬን
ተቀብዬ ከታጠቅኩ በኋላ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ ፖሊሱ ያሳየኝ እምነት በጣም ነው የገረመኝ፡፡
ለምን እንደሆነ ባላውቅም ሰው ከመሬት ተነስቶ ያምነኛል፡፡ ሌባ ብሆን መቼም ባንዴ ሃብታም
ነበር የምሆነው፤ ሰዎች እንዲያምኑህ እና እንዲዘናጉ ማድረግ ትልቁ የሌብነት ጥበብ ነውና፡፡
ሰፈሬ ስደርስ ወደ ህሊና ሱቅ መንገድ ጀመርኩና ትዝ ሲሰኝ ደንግጬ መንገዴን ቀየርኩት፡፡ ሱቅ አካባቢ እንዳልደርስ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኛል፡፡ ወይኔ ከሁሉም ከሁሉም ህሌናን ሳላይ መዋል እንዴት ያስጠላል?! ህሊናን እንዳላይ በህግ ተከልክያለሁ፡፡ ያ ፖሊስ በሕግ አላስፈራራኝም
ሕጉን ነው አእምሮዬ ውስጥ ተክሎ በፍቅር ያጠረው፡፡
ሂሉ እስካሁኝ በዱቄት የተበከለ ጋውኗን ስብሳ ፊቷ በሚነድ ሻማ የሆነ ነገር እያደረጋች ይሆናል፤
ወይም የለስላሳ ሳጥን ላይ ቆማ እንደ ነብር ሽንጧ ተመዞ የላይኞቹ መደርደሪያዎት ላይ ሳሙና
እየደረደረች ይሆናል፡፡ ስትንጠራራ እኮ ስታምር! ሰማይ ላይ በተቀመጠ ገብታ በሚያማምሩ
ጣቶቿ እግዜር ጋር ቼዝ የምትጫወት ነው የሚመስለኝ፡፡
ሂሉ የኔ ውብ ! የኔ ቆንጆ! የግርማ
ሚስት ፤ ሰው እንዴት ግርማን ያገባል በእግዚኣብሔር
ብቸኛ ነኝ ! ሁሉም ነገር የሰለቸኝ የሃያ ሰባት ዓመት ወጣት፡፡ ቤቴ እገባለሁ፤ እወጣለሁ ሶስት ዓመት ሙሉ እዚህ ሰፈር ስኖር የማውቃት ህሌናን ብቻ ነው፡፡ መንገዴ ላይ ሱቅ አላት፣ድምቅ ያለ ሱቅ፡፡ የሱቁ ድምቀት ህሊና ራሷ ሳትሆን አትቀርም፡፡
ህሊና ጨዋ ሴት ነበረች። እኔም ጨዋ ልጅ ነበርኩኝ፡፡ የህሊና ባል ግን ጨዋ ስላልነበረ ሊያሳሰተኝ
ሞከረ፡፡ ይሄ አሳሳች ደስ ይበለው፤ ተሳክቶለት ተሳሳትን፡፡ በእርግጥ ስሀተታችን ጣፋጭ ነበር፡፡
ለሚስቱ ሱቅ ከፍቶ ወንድ ደንበኛ በመጣ ቁጥር 0ይኑን ማጉረጥረጥ ተገቢ ነው? ገበያተኛ በመጣ ቁጥር የሚስቱን ፈገግታ መለካት እና ማታ ማታ በልክ ፈገግ በይ እያለ መነትረክ
እግዚር ይወደዋል? እሽ ይሄ ይሁን ግዴለም…ግን አብረሃም የሚባል ልጅ እዚህ ሱቅ ለምን ይመጣል ለሞላ ሱቅ?!” ብሎ መጠየቅ ከአንድ ባለ ሱቅ ይጠበቃል? ... መንግስት ሳያዳላ ሕዝብ
እንዲያገለግልበት በሰጠው ንግድ ፈቃድ እከሌ ይምጣ እከሌ ይሂድ ብሎ ሰው ይመርጣል?
እሺ (ሂሂሂሂ…ኧረ ይሄስ ያሳፍራል) ግን ሚስቱ ጋር፤ ቆንጅዬ ሚስቱ ጋር እቅፍቅፍ ብሎ ከመተቃቀፍም አልፎ መርፌና ክር ሆነው ሌላ ዓለም ውስጥ ሲዋኙ ድንገት የማይቋረጥ ነገር
አቋርጦ፣ “ለምንድን ነው አብረሃም ቲማቲም የሚገዛው? ማን ሊያበስልለት?” ብሎ ሚስቱን
ይጠይቃል፥ እንዲህ ይደረጋል ?
ሂሉዬ ብስጭት ብላ “ራሱ ይሰራላ” ስትለው፣ ራሱ እንደሚሰራ በምን አወቅሽ ?” ይባላል ?ለጥያቄና መልስ ይሄ ቦታው ነው ? ሰዓቱስ ነው ?
ባሏ ቀልቡ አይወደኝም፥ እቀፈዋለሁ፡፡ እኔ ሱቁ በር ላይ ስቆም ዐይኔን ላለማየት የማያየው ነገር የለም፡፡ የተደረደረውን ሳሙና፣ የተሰቀለውን ሙዝ፣ የተለጠፈውን "ዱቤ ክልክል" ነው የሚል ማስታወቂያ...ብቻ ማየት የቻለውን ሁሉ ፌቱን እጨፍግጎ ይቃኛል፡፡ አናቴን ሊፈነከተኝ ፈልጎ
ደህና መፈንከቻ ያጣ ነው የሚመስለው:: በዛ ላይ ሆነ ብሎ ህሊናን በወሬ ያጨናንቃታል፡፡
እንዳናወራ መከላከሉ እኮ ነው፡፡
እጃክስ አለቀ እንዴ?” ይላታል፤
ኧረ አለ!"
"ለስላሳ ዛሬ አላወረድሽም ?"
“ገና ትላንት እኮ ነው ያወረድኩት !”
በቃ የማይቀባጥረው ነገር የለም፡፡
እንግዲህ ስገባና ስወጣ ሰላም የምላት ብቸኛ ሴት ባለ ሱቋ ህሊና ነች፡፡ ሱቋ መንገዴ ላይ
ስለሆነች አስቤዛዬን የምሸምተው ከሷው ነው፡፡ ታዲያ ህሊና ጥሩ ልጅ ስለሆነች ነው መሰል
ከደንበኝነት ከፍ ያለ ቅርርብ ነው ያለን፡፡
ዛሬም ልክ ደመወዝ እንደተቀበልኩ ሄድኩ፤ ባሏ የለም፡፡ ሁለታችንም ደስ አለን፡፡
አንተ?" ትለኛለች፡
በቃ ስሜን ጠርታኝ አታውቅም፡፡ አንተ ነው የምትለኝ፡፡ እውነቱን ለመናገር ህሊና 'አንተ'
ስትለኝ ስሜን ያቀናጣችው ነው የሚመስለኝ፡፡ አብርሃም ሲቀናጣ 'አንተ ! በእኔ ጆሮ ብትሰሙት
በጣም ይገጣጠማል !!
ሰላም 'ሂሉ' ባሏ ከሌለ ሂሉ ነው የምላት፤ በእርግጥ አንዳንዴ እሱም እያለ ያመልጠኛል፡፡
“ምን ሆነህ ነው ዐይንህ የቦዘዘው” ትላለች በትልልቅ ዐይኗ እያየችኝ፡፡ ዐይኖቿ ዐይኔን
ይስሙኛል፡፡
“ዱቤ ልከፍል ስለሆነ ይሆናላ !”
በዚህ ሁኔታ መቀለድ መቻሌ ግዴላችሁም ብርቱ ሰው ብሆን ነው!
ሂሂሂሂሂሂሂሂ….ውይ አታስቀኝ ከምሬ ነው!” ትላለች፣ ስቃ ከወጣላት በኋላ እኮ ነው፡፡ ከዛም
የወሩ እዳዩን እንተሳሰባለን፡፡
"ዱቤ ክልክል ነው" ከሚለው ጽሑፍ ስር ያስቀመጠችውን የዱቤ መጻፊያ ደብተር ታወጣና
ቁልቁል በእስክርቢቶዋ እየጠቆመች “ካርድ የ 100 ብር ግን መቶ ብር ካርድ ምን ያደርግልሃል?
ወሬ እንኳን አታበዛ” ትላለች፤
ዳቦ
ዳቦ
ዳቦ ሰነፍ ስለሆንክ እኮ ነው ዳቦ የምትበላው ! ብቻ አንጀትህ እንዳይደርቅ ፤ ምናለ እንደ
ወንዶቹ እንቁላል እንኳን ብትጠብስ …" ትቀጥላለች፡፡
“…የተፈጨ ቡና…!
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
“አብርሃም !"
“አቤት”
“ስምህ ማነው ?” አለኝ ፊቴ የተቀመጠው ደግ ፖሊስ፡፡ ፊቱን ሳየው ማፏጨት ጀምሮ መሐል
ላይ ሲደርስ ሊያፏጭ የፈለገው ዜማ የጠፋበት ጎረምሳ ይመስላል፡፡ ስሜን ጠርቶ ስምህ
ማነው? ሲለኝ ቢጎርመኝም በትህትና ተናገርኩ፡፡
“አብረሃም”
“አ.ብ.ር.ሃ.ም”ፊደል የቆጠረ ፃፈ፡፡
የአባትህ ስም" ነገርኩት ጻፈ፡፡
“አብረሃም ! ለምንድነው የሰው ባል ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በሚዛን ስሀን የፈነከትከው”
አለኝ፡፡ አጠያየቁ 'ባትመልስልኝም ግድ የለም” የሚመስል ሰሜት ነበረበት፡፡
ኧረ ስላበሳጨኝ ነው እንጂ እኔ ሰው ጋር ተሰዳድቤ እንኳን አላውቅም፤ እንኳን በጭካኔ..
ዓረፍተ ነገሬ እየተወለጋገደ መለስኩ፡፡
“እሱማ ታስታውቃለህ፡፡ ጨዋ ልጅ ነህ፡፡ ጨዋ ባትሆን ኖሮ ሰሀኑ ላይ የተቀመጠውን አንድ ኪሎ መመዘኛ ብረት ትተህ በሰሃኑ ብቻ ኣትፈነከተውም ነበር፡፡ ጎበዝ ራስህን መግዛትህ ትልቅ ነገር ነው:: ራሱን የሚገዛ አገር ከሚገዛ ይበልጣል ይባላል፡፡ ቢሆንም ግን አብረሃም ዋስ ትጠራለሁ፡፡
“እሺ አልኩና ትዝ ሲለኝ የሚዋስ ሰው የለኝም፡፡
እንካ ደውልና ጥራ !" ብሎ ቅድም ወደ ማረፊያ ቤት ስገባ የተቀብለኝን ስልኬን ወደ ፊቴ
ገፋልኝ፡፡
ወደ አእምሮዬ የመጣችው ሂሉ ነበረች፡፡ ግን ሀሳቡ በራሱ ሳቁን አመጣብኝና ተውኩት፡፡ ባሏን
ፈንክቼ ሚስቱን ዋስ ሁነኝ ማለት በእርግጥ ያስቃል፡፡ ዝም ብዬ ዋስ የሚሆነኝ ሰው ሳወጣና ሳወርድ ቆየሁና "ዋስ የለኝም !" አልኩት ለደጉ ፖሊስ፡፡
እንዴት ዋስ አይኖርህም? ከሰው አልተወለድክም ? ጓደኛ የለህም? ወይም ጎረቤት ” አለ ፖሊሱ፡፡ እንዲህ ሲለኝ ዘመድም ጓደኛም የምለው ሰው እንደሌለኝ ትዝ አለኝና እንባዬ በዐይኔ
ግጥም አለ፡፡
“ደህና እስቲ የአንድ ሰው ስም ንገረኝ አለ ለመፃፍ እየተመቻቸ፡፡
“የአንድ ሰው ማለት?
"በቃ ዝም ብለህ የአንድ ሰው ስም ንገረኝ” አለ፡፡
"እበራ " ማረፊያ ቤቷ ውስጥ አበራ አንበሳው ! የሚል ስም በተወለጋገደ የእጅ ጽሁፍ አይቼ
ሰለነበር አፌ ላይ ድንገት መጣልኝ፡፡
“የአባቱ ስም ማነው ?"
"እኔ ንጃ ተገርሞ አየኝና ፈገግ ብሎ አጉተመተመ፡፡
“በቃ አበራ ቀለጠ ብዬዋለሁ - ዋስሀ ነው:: አብረሃም አምንሃለሁ፤ ጥሩ ልጅ ነህ፤ ይሄ መቼም
የዕለት ግጭት ነው:: ከአሁን በኋላ እዛ ሱቅ አካባቢ ብትደርስ ግን ዋስህን እቀፈድደዋለሁ፤
' ነግሬያለሁ” አለ እየሳቀ፡፡
እዚች ምድር ላይ ይኑር አይኑር በማይታወቅ ዋስ ከእስር የወጣሁ ሚስኪን ሰው፣ ቀበቶዬን
ተቀብዬ ከታጠቅኩ በኋላ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ ፖሊሱ ያሳየኝ እምነት በጣም ነው የገረመኝ፡፡
ለምን እንደሆነ ባላውቅም ሰው ከመሬት ተነስቶ ያምነኛል፡፡ ሌባ ብሆን መቼም ባንዴ ሃብታም
ነበር የምሆነው፤ ሰዎች እንዲያምኑህ እና እንዲዘናጉ ማድረግ ትልቁ የሌብነት ጥበብ ነውና፡፡
ሰፈሬ ስደርስ ወደ ህሊና ሱቅ መንገድ ጀመርኩና ትዝ ሲሰኝ ደንግጬ መንገዴን ቀየርኩት፡፡ ሱቅ አካባቢ እንዳልደርስ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኛል፡፡ ወይኔ ከሁሉም ከሁሉም ህሌናን ሳላይ መዋል እንዴት ያስጠላል?! ህሊናን እንዳላይ በህግ ተከልክያለሁ፡፡ ያ ፖሊስ በሕግ አላስፈራራኝም
ሕጉን ነው አእምሮዬ ውስጥ ተክሎ በፍቅር ያጠረው፡፡
ሂሉ እስካሁኝ በዱቄት የተበከለ ጋውኗን ስብሳ ፊቷ በሚነድ ሻማ የሆነ ነገር እያደረጋች ይሆናል፤
ወይም የለስላሳ ሳጥን ላይ ቆማ እንደ ነብር ሽንጧ ተመዞ የላይኞቹ መደርደሪያዎት ላይ ሳሙና
እየደረደረች ይሆናል፡፡ ስትንጠራራ እኮ ስታምር! ሰማይ ላይ በተቀመጠ ገብታ በሚያማምሩ
ጣቶቿ እግዜር ጋር ቼዝ የምትጫወት ነው የሚመስለኝ፡፡
ሂሉ የኔ ውብ ! የኔ ቆንጆ! የግርማ
ሚስት ፤ ሰው እንዴት ግርማን ያገባል በእግዚኣብሔር
ብቸኛ ነኝ ! ሁሉም ነገር የሰለቸኝ የሃያ ሰባት ዓመት ወጣት፡፡ ቤቴ እገባለሁ፤ እወጣለሁ ሶስት ዓመት ሙሉ እዚህ ሰፈር ስኖር የማውቃት ህሌናን ብቻ ነው፡፡ መንገዴ ላይ ሱቅ አላት፣ድምቅ ያለ ሱቅ፡፡ የሱቁ ድምቀት ህሊና ራሷ ሳትሆን አትቀርም፡፡
ህሊና ጨዋ ሴት ነበረች። እኔም ጨዋ ልጅ ነበርኩኝ፡፡ የህሊና ባል ግን ጨዋ ስላልነበረ ሊያሳሰተኝ
ሞከረ፡፡ ይሄ አሳሳች ደስ ይበለው፤ ተሳክቶለት ተሳሳትን፡፡ በእርግጥ ስሀተታችን ጣፋጭ ነበር፡፡
ለሚስቱ ሱቅ ከፍቶ ወንድ ደንበኛ በመጣ ቁጥር 0ይኑን ማጉረጥረጥ ተገቢ ነው? ገበያተኛ በመጣ ቁጥር የሚስቱን ፈገግታ መለካት እና ማታ ማታ በልክ ፈገግ በይ እያለ መነትረክ
እግዚር ይወደዋል? እሽ ይሄ ይሁን ግዴለም…ግን አብረሃም የሚባል ልጅ እዚህ ሱቅ ለምን ይመጣል ለሞላ ሱቅ?!” ብሎ መጠየቅ ከአንድ ባለ ሱቅ ይጠበቃል? ... መንግስት ሳያዳላ ሕዝብ
እንዲያገለግልበት በሰጠው ንግድ ፈቃድ እከሌ ይምጣ እከሌ ይሂድ ብሎ ሰው ይመርጣል?
እሺ (ሂሂሂሂ…ኧረ ይሄስ ያሳፍራል) ግን ሚስቱ ጋር፤ ቆንጅዬ ሚስቱ ጋር እቅፍቅፍ ብሎ ከመተቃቀፍም አልፎ መርፌና ክር ሆነው ሌላ ዓለም ውስጥ ሲዋኙ ድንገት የማይቋረጥ ነገር
አቋርጦ፣ “ለምንድን ነው አብረሃም ቲማቲም የሚገዛው? ማን ሊያበስልለት?” ብሎ ሚስቱን
ይጠይቃል፥ እንዲህ ይደረጋል ?
ሂሉዬ ብስጭት ብላ “ራሱ ይሰራላ” ስትለው፣ ራሱ እንደሚሰራ በምን አወቅሽ ?” ይባላል ?ለጥያቄና መልስ ይሄ ቦታው ነው ? ሰዓቱስ ነው ?
ባሏ ቀልቡ አይወደኝም፥ እቀፈዋለሁ፡፡ እኔ ሱቁ በር ላይ ስቆም ዐይኔን ላለማየት የማያየው ነገር የለም፡፡ የተደረደረውን ሳሙና፣ የተሰቀለውን ሙዝ፣ የተለጠፈውን "ዱቤ ክልክል" ነው የሚል ማስታወቂያ...ብቻ ማየት የቻለውን ሁሉ ፌቱን እጨፍግጎ ይቃኛል፡፡ አናቴን ሊፈነከተኝ ፈልጎ
ደህና መፈንከቻ ያጣ ነው የሚመስለው:: በዛ ላይ ሆነ ብሎ ህሊናን በወሬ ያጨናንቃታል፡፡
እንዳናወራ መከላከሉ እኮ ነው፡፡
እጃክስ አለቀ እንዴ?” ይላታል፤
ኧረ አለ!"
"ለስላሳ ዛሬ አላወረድሽም ?"
“ገና ትላንት እኮ ነው ያወረድኩት !”
በቃ የማይቀባጥረው ነገር የለም፡፡
እንግዲህ ስገባና ስወጣ ሰላም የምላት ብቸኛ ሴት ባለ ሱቋ ህሊና ነች፡፡ ሱቋ መንገዴ ላይ
ስለሆነች አስቤዛዬን የምሸምተው ከሷው ነው፡፡ ታዲያ ህሊና ጥሩ ልጅ ስለሆነች ነው መሰል
ከደንበኝነት ከፍ ያለ ቅርርብ ነው ያለን፡፡
ዛሬም ልክ ደመወዝ እንደተቀበልኩ ሄድኩ፤ ባሏ የለም፡፡ ሁለታችንም ደስ አለን፡፡
አንተ?" ትለኛለች፡
በቃ ስሜን ጠርታኝ አታውቅም፡፡ አንተ ነው የምትለኝ፡፡ እውነቱን ለመናገር ህሊና 'አንተ'
ስትለኝ ስሜን ያቀናጣችው ነው የሚመስለኝ፡፡ አብርሃም ሲቀናጣ 'አንተ ! በእኔ ጆሮ ብትሰሙት
በጣም ይገጣጠማል !!
ሰላም 'ሂሉ' ባሏ ከሌለ ሂሉ ነው የምላት፤ በእርግጥ አንዳንዴ እሱም እያለ ያመልጠኛል፡፡
“ምን ሆነህ ነው ዐይንህ የቦዘዘው” ትላለች በትልልቅ ዐይኗ እያየችኝ፡፡ ዐይኖቿ ዐይኔን
ይስሙኛል፡፡
“ዱቤ ልከፍል ስለሆነ ይሆናላ !”
በዚህ ሁኔታ መቀለድ መቻሌ ግዴላችሁም ብርቱ ሰው ብሆን ነው!
ሂሂሂሂሂሂሂሂ….ውይ አታስቀኝ ከምሬ ነው!” ትላለች፣ ስቃ ከወጣላት በኋላ እኮ ነው፡፡ ከዛም
የወሩ እዳዩን እንተሳሰባለን፡፡
"ዱቤ ክልክል ነው" ከሚለው ጽሑፍ ስር ያስቀመጠችውን የዱቤ መጻፊያ ደብተር ታወጣና
ቁልቁል በእስክርቢቶዋ እየጠቆመች “ካርድ የ 100 ብር ግን መቶ ብር ካርድ ምን ያደርግልሃል?
ወሬ እንኳን አታበዛ” ትላለች፤
ዳቦ
ዳቦ
ዳቦ ሰነፍ ስለሆንክ እኮ ነው ዳቦ የምትበላው ! ብቻ አንጀትህ እንዳይደርቅ ፤ ምናለ እንደ
ወንዶቹ እንቁላል እንኳን ብትጠብስ …" ትቀጥላለች፡፡
“…የተፈጨ ቡና…!
👍23👏1😁1
ሻይ ቅጠል…!
ኮካ !
አምቦ ውሃ ሂሂሂሂሂሂሂሂ እስኪ ሰው ዳቦ እየበላ አምቦ ውሃ ሆሆ ስትስቅ ደሰ ስለምትለኝ
ዝም ብዬ አያታለሁ፥ ስታምር!
እ.እ.እና አንድ ሊትሯን ውሃ በድምሩ…መቶ ሰላሳ ሁለት ብር”
ሀምሳ ብሩን ረስተሻል ! እላታለሁ፡፡
“የምን ሃምሳ ብር?" ትለኛለች፡፡
“አንድ ቀን ተበድሬሽ ለታክሲ እንኳ."
“አላስታውስም
እኔ አስታውሳለሁ” እላትና ሁለት መቶ ብር እዘረጋላታለሁ፡፡ አንዱን ብቻ አንስታ አንዱን
እጄ ላይ ትተወዋለች፡፡
“ብር አለህ ግን?" ትለኛለች፣ደግሞ ከልቧ መሆኑን ዐይኗ ያስታውቃል።
ዛሬማ ሃብታም ነኝ
“ያንተ ሀብታምነት እንደሁ እድሜው ሦስት ቀን ነው” ታየኛለች፤ በዕይኗ የነካችኝ ነው
የሚመስለኝ፡፡
አእምሮዬ ባለትዳር መሆኗን እንዳያምን ጣቷን ላለማየት እጥራለሁ፡፡ የሆነች ለስላሳ ነገር ነች፣አንገቷን በዐይኔ ስነካው ይለሰልሶኛል፡፡ ባሏ ግርማ ሲያቅፉት የሚኮሰኩሳት ነው የሚመስለኝ፣ የሆነ ሰውነቷ የሚንደበደብ።
ሂሉን ሱቅ ውስጥ ቆማ ሳያት መደርደሪያው ሁሉ የተሞላው በፍቅር ይመስለኛል። “ማነሽ
ሁሉንም በጅምላ ገዝቼዋለሁ፤ ከነመደርደሪያው፣ ከነሚዛኑ፣ ከነመዛኟ !!
በትልቅ ጥቁር ፌስታል ቋጥሮ እኔንም እዛው ውስጥ መጨመር፧ ወደ ውጭ ማየት የለ፣ ወደ
ውስጥ የሚመለከት የለ፤ እርፍ !
ኤጭጭ! ከኋላዬ ጥላው ሲከብደኝ ታወቀኝ…ግርማ መጣ፤ ባሏ መጣ የተደገፍኩትን መደርደሪያ ከፍቶ ሲገባ ወድቄ ነበር፡፡
ይቅርታ ልገባ ነው አይባልም ? ሂሉ በባሏ ብልግና ስትሳቀቅ ይታወቀኛል፡፡ ይሄ ውሻ የሆነ ሰው
በቃ የሂሉም ፊት ኮስትር የእኔም ፊት ኮስተር !! መደርደሪያው ይንኳተትብኛል፡፡ ማካሮኒ፣
ፖስታ፣ ሳሙና፣ ምንትስ…ያ ሁሉ ፍቅር እልም ! ይሄ ሰሐራ ባሏ ሲገባ ፍቅር ይተናል፡፡
ሰላፈው ከስራ ወጥቼ ወደ ቤቴ አዘግማለሁ፡፡ ድክም ብሎኝ ስለነበር ሂሉን ረስቻት ነበር፡፡
ልክ በሱቋ ሳልፍ “እንተ ብላ ጮኸች፡፡ የሂሉን ድምፅ ሲሰሙ ድካም፣ ድንዛዜ ሁሉ ጠጠር
እንደተወረወረበት የወፍ መንጋ እኔ ከምባል ዛፋቸው ላይ ግርር ብለው ሲበሩ ታውቀኝ፡፡ከንፈሬ ሳላዘው ግራና ቀኝ ሸሽ፤ ፈገግ አልኩ፡፡ እናም ወደ ሱቋ ሄደኩ፤ ከድካሜ ብዛት ደረጃውን
ስወጣ ገድገድ ብዬ ነበር፡፡
"እኔን!" አለች ሂሉ፤
ሱቁ ላይ ስደርስ ግርማ ተቀምጧል፡፡ ድካሞቼ ሁሉ ተጠራርተው ድብርትን ጨምረው
ስፈሩብኝ፤“ሰላም ዋላችሁ! አልኩ፤
እግዚያብሄር ይመስገን!” አለች ሂሉ፣ እግዜር ቀኑን የሰጠው ለሷ ብቻ ይመስል፡፡ ያ ጋግርታም
ባሏ ዘጋኝ! ይዝጋው ! ምን እንደማወራ ጠፍቶብኝ አንዴ መደርደሪያው ላይ ያሉትን እቃዎች፣ አንዴ ሂሉን ስቃኝ
ቆየሁና…“ሳሙና ስጭኝ!" አልኩ፡፡ ሂሉ ሳቋ መጥቷል፤ ድንገት አንደዘባረቅኩ አውቃለች፡፡
ቢሆንም ከመጨረሻው መደርደሪያ ላይ ልታወርድ የላስላሳ ሳጥኑን አስጠጋችና ጫማዋን አውልቃ
ኩርሲዋ ላይ ቆመች። እግሯ እንዴት ነው የሚያምረው ! ተረከዟ ነጣ ብሏል፤ ተንጠራራች፤
ተመዘዘ ሽንጧ …! ሽንጧ የሚመስለው…የምንትስ ሃረግ.” እያልኩ በሃሳቤ ስዘፍን እና ምራቄን ስውጥ ቆይቼ ዞር
ስል ግርማ ዐይኑ ቀልቶ እኔ ላይ አፍጥሏል፡፡ “ነብር አየኝ በል!” አይነት ዛቻ ቀመስ ዕይታ…!
የሚጮህ ዐይን ያየሁት ግርማ ላይ ነው፡፡ ዐይኔን ከዚህ ፈጣጣ ላይ ነቅዬ በጥግ በኲል ስልክ
የኮንዶም ካርቶኑ ላይ አረፈ፡፡ የግርማም ዐይን ዐይኔን ተከትሎ ይሁን ወይም የዐይኑ እግር
ጥሎት እዛው ላይ አረፈ! ወይም ያረፈ መሰለኝ፡፡
ሂሎ የቆመችበት ኩርሲ ነቅነቅ ሲል “እኔን ብዬ በድንጋጤ ጮህኩ፤ አደነጋገጤ ለራሴም
ገርሞኛል። ውሃ ጠገብ ባሏ ምንም ያልመሰለውን እኔን ምን ቆርጦኝ ነው የደነገጥኩት? ምን
አስበረገገኝ? “የምጣዱ ሳለ የእንቅቡ ተንጣጣ" አሉ! እንደውም የግርማ አስተያየት ምነው በፈረጥሽ! የሚል ያስመስልበታል፡፡
ሳሙናዬን ተቀብዬ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ በቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ሂሉ እንባዋ ጠብ እስኪል እየሳቀች ሳሙናውን ገዝቼ ከሄድኩ በኋላ ከግርማ ጋር የተባባሉትን እንዲህ ስትል ነገረችኝ፡፡....
✨ነገ ያልቃል✨
ኮካ !
አምቦ ውሃ ሂሂሂሂሂሂሂሂ እስኪ ሰው ዳቦ እየበላ አምቦ ውሃ ሆሆ ስትስቅ ደሰ ስለምትለኝ
ዝም ብዬ አያታለሁ፥ ስታምር!
እ.እ.እና አንድ ሊትሯን ውሃ በድምሩ…መቶ ሰላሳ ሁለት ብር”
ሀምሳ ብሩን ረስተሻል ! እላታለሁ፡፡
“የምን ሃምሳ ብር?" ትለኛለች፡፡
“አንድ ቀን ተበድሬሽ ለታክሲ እንኳ."
“አላስታውስም
እኔ አስታውሳለሁ” እላትና ሁለት መቶ ብር እዘረጋላታለሁ፡፡ አንዱን ብቻ አንስታ አንዱን
እጄ ላይ ትተወዋለች፡፡
“ብር አለህ ግን?" ትለኛለች፣ደግሞ ከልቧ መሆኑን ዐይኗ ያስታውቃል።
ዛሬማ ሃብታም ነኝ
“ያንተ ሀብታምነት እንደሁ እድሜው ሦስት ቀን ነው” ታየኛለች፤ በዕይኗ የነካችኝ ነው
የሚመስለኝ፡፡
አእምሮዬ ባለትዳር መሆኗን እንዳያምን ጣቷን ላለማየት እጥራለሁ፡፡ የሆነች ለስላሳ ነገር ነች፣አንገቷን በዐይኔ ስነካው ይለሰልሶኛል፡፡ ባሏ ግርማ ሲያቅፉት የሚኮሰኩሳት ነው የሚመስለኝ፣ የሆነ ሰውነቷ የሚንደበደብ።
ሂሉን ሱቅ ውስጥ ቆማ ሳያት መደርደሪያው ሁሉ የተሞላው በፍቅር ይመስለኛል። “ማነሽ
ሁሉንም በጅምላ ገዝቼዋለሁ፤ ከነመደርደሪያው፣ ከነሚዛኑ፣ ከነመዛኟ !!
በትልቅ ጥቁር ፌስታል ቋጥሮ እኔንም እዛው ውስጥ መጨመር፧ ወደ ውጭ ማየት የለ፣ ወደ
ውስጥ የሚመለከት የለ፤ እርፍ !
ኤጭጭ! ከኋላዬ ጥላው ሲከብደኝ ታወቀኝ…ግርማ መጣ፤ ባሏ መጣ የተደገፍኩትን መደርደሪያ ከፍቶ ሲገባ ወድቄ ነበር፡፡
ይቅርታ ልገባ ነው አይባልም ? ሂሉ በባሏ ብልግና ስትሳቀቅ ይታወቀኛል፡፡ ይሄ ውሻ የሆነ ሰው
በቃ የሂሉም ፊት ኮስትር የእኔም ፊት ኮስተር !! መደርደሪያው ይንኳተትብኛል፡፡ ማካሮኒ፣
ፖስታ፣ ሳሙና፣ ምንትስ…ያ ሁሉ ፍቅር እልም ! ይሄ ሰሐራ ባሏ ሲገባ ፍቅር ይተናል፡፡
ሰላፈው ከስራ ወጥቼ ወደ ቤቴ አዘግማለሁ፡፡ ድክም ብሎኝ ስለነበር ሂሉን ረስቻት ነበር፡፡
ልክ በሱቋ ሳልፍ “እንተ ብላ ጮኸች፡፡ የሂሉን ድምፅ ሲሰሙ ድካም፣ ድንዛዜ ሁሉ ጠጠር
እንደተወረወረበት የወፍ መንጋ እኔ ከምባል ዛፋቸው ላይ ግርር ብለው ሲበሩ ታውቀኝ፡፡ከንፈሬ ሳላዘው ግራና ቀኝ ሸሽ፤ ፈገግ አልኩ፡፡ እናም ወደ ሱቋ ሄደኩ፤ ከድካሜ ብዛት ደረጃውን
ስወጣ ገድገድ ብዬ ነበር፡፡
"እኔን!" አለች ሂሉ፤
ሱቁ ላይ ስደርስ ግርማ ተቀምጧል፡፡ ድካሞቼ ሁሉ ተጠራርተው ድብርትን ጨምረው
ስፈሩብኝ፤“ሰላም ዋላችሁ! አልኩ፤
እግዚያብሄር ይመስገን!” አለች ሂሉ፣ እግዜር ቀኑን የሰጠው ለሷ ብቻ ይመስል፡፡ ያ ጋግርታም
ባሏ ዘጋኝ! ይዝጋው ! ምን እንደማወራ ጠፍቶብኝ አንዴ መደርደሪያው ላይ ያሉትን እቃዎች፣ አንዴ ሂሉን ስቃኝ
ቆየሁና…“ሳሙና ስጭኝ!" አልኩ፡፡ ሂሉ ሳቋ መጥቷል፤ ድንገት አንደዘባረቅኩ አውቃለች፡፡
ቢሆንም ከመጨረሻው መደርደሪያ ላይ ልታወርድ የላስላሳ ሳጥኑን አስጠጋችና ጫማዋን አውልቃ
ኩርሲዋ ላይ ቆመች። እግሯ እንዴት ነው የሚያምረው ! ተረከዟ ነጣ ብሏል፤ ተንጠራራች፤
ተመዘዘ ሽንጧ …! ሽንጧ የሚመስለው…የምንትስ ሃረግ.” እያልኩ በሃሳቤ ስዘፍን እና ምራቄን ስውጥ ቆይቼ ዞር
ስል ግርማ ዐይኑ ቀልቶ እኔ ላይ አፍጥሏል፡፡ “ነብር አየኝ በል!” አይነት ዛቻ ቀመስ ዕይታ…!
የሚጮህ ዐይን ያየሁት ግርማ ላይ ነው፡፡ ዐይኔን ከዚህ ፈጣጣ ላይ ነቅዬ በጥግ በኲል ስልክ
የኮንዶም ካርቶኑ ላይ አረፈ፡፡ የግርማም ዐይን ዐይኔን ተከትሎ ይሁን ወይም የዐይኑ እግር
ጥሎት እዛው ላይ አረፈ! ወይም ያረፈ መሰለኝ፡፡
ሂሎ የቆመችበት ኩርሲ ነቅነቅ ሲል “እኔን ብዬ በድንጋጤ ጮህኩ፤ አደነጋገጤ ለራሴም
ገርሞኛል። ውሃ ጠገብ ባሏ ምንም ያልመሰለውን እኔን ምን ቆርጦኝ ነው የደነገጥኩት? ምን
አስበረገገኝ? “የምጣዱ ሳለ የእንቅቡ ተንጣጣ" አሉ! እንደውም የግርማ አስተያየት ምነው በፈረጥሽ! የሚል ያስመስልበታል፡፡
ሳሙናዬን ተቀብዬ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ በቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ሂሉ እንባዋ ጠብ እስኪል እየሳቀች ሳሙናውን ገዝቼ ከሄድኩ በኋላ ከግርማ ጋር የተባባሉትን እንዲህ ስትል ነገረችኝ፡፡....
✨ነገ ያልቃል✨
👍18❤8😁2
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ማሪየስ በመጨረሻ ስለናፖሊዮን ጦር ሠራዊት ነበር ከሚያነብበው::መፅሀፍ አልፎ አልፎ የአባቱ ስም ያያል የንጉሱ ስም ግን በየምራፍ ይጠቀሳል
አገሪትዋ በሙሉ ለንጉሱ እንደተሰራች ተደርጎ ነበር ፅሁፉ የቀረቡት እንደ መአበል ከውስጥ አካሉ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው:: አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሹክሹክታ ያነጋገረው መሰለው::
ተደርጎ ነበር ጸሐፉ የቀረበው:: እንደ ማዕበል ከውስጥ አካለ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው
አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሽኩክታ ያነጋገረው መሰለው የከበሮ፤ የመድፍ፤ የመለከት፤ በሩቁ የሚሰማ የሠራዊትና የፈረስ ኮቴ
ከፊቱ ድቅን አለ፡፡ ማንበቡን ትቶ በመስኮት ወደ ሰማይ ተመለከተ::
የሚያብለጨልጭ ነገር ከሰማይ ተወርውሮ የሚያነብበው መጽሐፍ ውስጥ የወደቀ መሰለው፡፡ ፍርሃት፣ ፍርሃት አለው፡፡ የሚተነፍሰው በግድ ሆነ::
ሰውነቱ ራደ:: ማን እንዳዘዘውና ምን እንዳስገደደው ሳይታወቀው
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡ ወደ መስኮቱ ሄዶ እጆቹን ወደ ውጭ ዘረጋ::
በጨለማ ሰማዩንና ምድሩን በዓይኑ ማተረ፡፡ ዓለም ጸጥ ረጭ ብላለች::በድንገት «እድሜ ለንገሠ ነገሥቱ» ሲል ጮኸ፤ በማፌዝ፡፡
ከዚያን እለት ጀምሮ ማሪየስ ጨርሶ ተለወጠ፡፡ ለአባቱ ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተወዳጅ ካፕቴን እንደነበሩ ተገነዘበ፡፡ ተወዳጁን ካፕቴን ያደንቅና ለእርሱም ሕይወቱን አሳልፎ እንደሰጠ ታወቀው:: ለማሪየስ ናፖሊዮን ማለት ግን ከዚህ የበለጠ ነበር፡፡ የወደፊት ተስፋ ፧ የድምበር
መከታና የፈረንሳይ አለኝታ ከናፖሊዮን ቦናፓርቴ ላይ አየ:: ናፖሊዮን ጨካኝ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን እርሱ መታየት ያለበት ከሪፑብሊክ ምስረታ፧
ከለውጥ፤ ከአብዮት ጋር ነው:: ናፖሊዮን የሕዝብ ሰው እንደሆነ አመነ፡፡አባቱ ጦር ሜዳ የተዋጋውና ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠው ለሰዎች እኩልነትና "
ለሪፑብሊኩ ምሥረታ እንደሆነ በፍጹም ልቡ ተቀበለ፡፡ የዚህ ተቃዋሚ የሆነውን የቡርዣን አገዛዝ ጠላ፡፡
አያቱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚደግፉት እርሱ የጠላውን ነበር፡፡ በዚህ የተነሣ በአያትና በልጅ ልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጠረ:: ከነአካቴው አያቱ ከአባቱ ጋር ያለያዩት በዚህ መሠረታዊ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት እንደሆነ በተገነዘበ ጊዜ አያቱን በጣም ጠላቸው:: በዚህ በግል ጥቅም በታወሩ ሰው ምክንያት ርህራሄ በተለየው ጭካኔ ልጅ ሊያፈቅረው ከሚችል አባቱ፧ አባት ከሚወደው ልጁ መለያየታቸው እጅግ በጣም አሳዘነው። ማሪየስ ከአባቱ ጋር የተለያየው በዚህ ምክንያት መሆኑን ባወቀ ጊዜ ለአባቱ
ያለው ፍቅር ሲገነፍል ለአያቱ የነበረው ጥላቻ ግን ከደሙ ጋር ተዋሃደ። አባቱ ማለት ለሰዎች ደኅንነት፤ ለሰዎች እኩልነትና ለትክክለኛ ፍርድ የቆመ ታላቅ ሰው ማለት ሲሆን፧ መሴይ ጊልኖርማንድ ማለት ደግሞ
በግል ጥቅም የታወሩ፤ ለጥቂት ሰዎች ደኅንነት ጥብቅና የቆመና እንደ መዥገር በሰዎች ደም የሰቡ ሰው ናቸው።ስለዚህ ቅራኔያቸው የሚታረቅ አልሆነም፡፡ ይህም የአያቱን ዓይን ላለማየት አስወሰነው:: ሰበብ አስባብ
እየፈጠረ ከቤት ይጠፋ ጀመር፡፡ አክስቱ ድንገት አግኝተው የት እንደነበር ሲጠይቁት «ጥናት በዝቶብኝ ከጓደኞቼ ጋር ሳጠና፧ ፈተና ስለነበረብን ከአንድ ጓደኛዬ ቤት ውስጥ ተዘግተን ስናጠና፧ ፍርድ ቤት ሄደን ስለፍርድ
አሰጣጥ ትምህርት ስንቀስም፤ አሁን ትምህርቴን ወደማጠናቀቁ ስለሆነ የመመረቂያ ጽሑፍ መጻፍ ስለጀመርሁ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ስለምውል»እያለ ሌላም፤ ሌላም መልስ ይሰጣቸዋል::
አያቱ ግን «ማሪየስ ፍቅር ይዞት ፍቅረኛው እያንከራተተችው ነው»
በሚል መደምደሚያ ላይ ስለደረሰና እርሳቸውም በዚህ ዓይነት ገጠመኝ ያለፉ ስለሆነ ብዙም አልተጨነቁበትም:: ሆኖም ማሪየስ እንኳን ቀን ሊገባ አድሮም የሚመጣበት ጊዜ በረከተ።
አንድ ቀን ‹‹የት ሊሄድ ይችላል?» ሲሉ አክስቱ ጠየቁ::
ማሪየስ አባቱ በጻፈለት ማስታወሻ መሠረት ተናድዬን ለመጠየቅ
ሞንትፌርሜ ሄዶአል፡፡ ከዚያም የቀድሞውን የዋተርሉ ሃምሣ አለቃ ፧የዛሬው የሆቴል ቤት ጌታ ሚስተር ቴናድዬ ከስሮ ሆቴል ቤቱ ስለተዘጋ ፍለጋው አራት ቀን ወሰደበት።
በእርግጥ ፈሩን እየለቀቀ ነው» አሉ አያቱ እንደዚያ ሲቆይ፡፡
በጥቁር ጨርቅ የተንጠለጠለ አንድ ነገር ከሸሚዞ ስር ከአንገቱ ላይ ማሰሩን አባትና ልጅ ቀደም ሲል ማየታቸውን አንስተው ተወያዩ::
ማሪየስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፓሪስ ከተማ ሲጠፋ የሄደው ወደ ቬርኖን ነበር። ቬርኖን ከተማ ሄዶ በጠፋ ቁጥር አያቱ «ተኝቶ ነው» ይላሉ፡፡
አንድ ቀን ጠዋት ማሪየስ ከቬርኖን ተመልሶ ከቤት ሲገባ አያቱ
ይሰሙታል፡፡ ከሁለት ቀን የአሳብ ጭንቀትና መንገድ በኋላ ስለነበረ
የተመለሰው በጣም ደክሞታል:: ብዙ እንቅልፍ ስላላገኘ ቶሎ ብሎ ለአንድ ሰአት እንኳን ቢሆን ለመተኛት ይፈልጋል፡፡ ኮቱንና አንገቱ ላይ ያጠለቀውን
አውልቆ አልጋው ላይ ወረወረ፡፡ እንዳይረበሽ ከመዋኛ ሥፍራ አጠገብ በሚገኝ ክፍል ውስጥ ለመተኛት ፈልጎ ወደዚያው ሄደ:: ጤነኛ የሆነ ሽማግሌዎች በጠዋት መንቃታቸው የተለመደ ስለሆነ መሴይ ጊልኖርማንድ በዚያን እለት በጠዋት በመንቃታቸው ማርየስ ከውጭ ሲገባ ሰሙት ካልጋቸው ተነስተው በሽማግሌ እግር ቶሉ ቶሉ በመራመድ የማሪየስ የመኝታ ቤት ወደነበረበት ክፍል ወደ ፎቅ ወጡ:: የወጡት ሊያቅፉና
ሊስሙት፧ በዚያውም ከየት እንደሚመጣ ሊጠይቁት ነበር፡፡ ግን ከክፍሉ ሲደርሱ ማሪየስ አልነበረም:: አልጋው እንደተነጠፈ ነው:: ኮቱና አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለው በጥቁር ሪሪበ የታሠረው ነገር ከአልጋው ላይ
ተቀምጠዋል፡፡
«ይህቺ ጥሩ ናት» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ::
ልጃቸው ወደ ነበሩበት ወደ ምድር ቤት ሳሉን ወረዱ:: እህትየው
ተነስተው ኖሮ ከሳሉን ቤት ቁጭ ብለው ጥልፍ ይጠልፋሉ፡፡ መሴይ
ጊልኖርማንድ በአንድ እጃቸው የማሪየስን ኮት በሌላ እጃቸው አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለውን ነገር ይዘዋል::
«ድል ይሉሻል ይኼ ነው ፤ ምስጢሩን ሳንደርስበት አንቀርም::
መጨረሻውን እንደርስበታለን፤ ይኸውልሽ ጉዳ» ሲሉ ጮሁ ፤ ልጃቸው ከነበሩበት ክፍል እንደገቡ፡፡
በሪበን የተንጠለጠለው ነገር የሳጥን ቅርጽ ያለውና የሚከፈት ነው ሽማግሌው ሳይከፍቱት አተኩረው ተመለከቱት::
‹‹አባባ ፧ ክፈተውና እንየው» አለች ልጃቸው::
ሳጥኑን ጫን ሲሉት ይከፈታል፡፡ በውስጠ ያገኙት ከብጣሽ ወረቀት
በስተቀር ሌላ ነገር አልነበረም::
«ከአንድዋ ፍቅረኛው ወደ ሌላዋ» አለ መሴይ ጊልኖርማንድ በኃይል
እየሳቀ:: «ምን እንደሆነ አውቀዋለሁ ፤ የፍቅር ደብዳቤ!››
‹‹ይሆናል፧ ይነበባ!» አለች የማሪየስ አክስት::
መነጽርዋን አደረገች፡፡ ወረቀቱን ዘረጋጋችና አነበበችው::
«ለምወድህ ልጄ ፣ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ:: እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ››
የአባትና የልጅ ፊት እንዴት እንደተለዋወጠና ስሜታቸው ምን እንደነበር መግለጽ ያዳግታል:: የሞት ጥላ እንደተጋረደበት ሰው በብሽቀት ደነዘዙ፤ እብድ ሆኑ:: በንዴት ሰከኑ:: ዝም ዝም ተባባሉ፡፡ በመጨረሻ መሴይ ጊልኖርማንድ እርስ በራሱ እንደሚናገር ሰው እጅግ ዝቅ ባለ ድምፅ ተናገሩ::
‹‹የዚያ ጦረኛ የእጅ ጽሑፍ ነው::»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ማሪየስ በመጨረሻ ስለናፖሊዮን ጦር ሠራዊት ነበር ከሚያነብበው::መፅሀፍ አልፎ አልፎ የአባቱ ስም ያያል የንጉሱ ስም ግን በየምራፍ ይጠቀሳል
አገሪትዋ በሙሉ ለንጉሱ እንደተሰራች ተደርጎ ነበር ፅሁፉ የቀረቡት እንደ መአበል ከውስጥ አካሉ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው:: አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሹክሹክታ ያነጋገረው መሰለው::
ተደርጎ ነበር ጸሐፉ የቀረበው:: እንደ ማዕበል ከውስጥ አካለ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው
አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሽኩክታ ያነጋገረው መሰለው የከበሮ፤ የመድፍ፤ የመለከት፤ በሩቁ የሚሰማ የሠራዊትና የፈረስ ኮቴ
ከፊቱ ድቅን አለ፡፡ ማንበቡን ትቶ በመስኮት ወደ ሰማይ ተመለከተ::
የሚያብለጨልጭ ነገር ከሰማይ ተወርውሮ የሚያነብበው መጽሐፍ ውስጥ የወደቀ መሰለው፡፡ ፍርሃት፣ ፍርሃት አለው፡፡ የሚተነፍሰው በግድ ሆነ::
ሰውነቱ ራደ:: ማን እንዳዘዘውና ምን እንዳስገደደው ሳይታወቀው
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡ ወደ መስኮቱ ሄዶ እጆቹን ወደ ውጭ ዘረጋ::
በጨለማ ሰማዩንና ምድሩን በዓይኑ ማተረ፡፡ ዓለም ጸጥ ረጭ ብላለች::በድንገት «እድሜ ለንገሠ ነገሥቱ» ሲል ጮኸ፤ በማፌዝ፡፡
ከዚያን እለት ጀምሮ ማሪየስ ጨርሶ ተለወጠ፡፡ ለአባቱ ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተወዳጅ ካፕቴን እንደነበሩ ተገነዘበ፡፡ ተወዳጁን ካፕቴን ያደንቅና ለእርሱም ሕይወቱን አሳልፎ እንደሰጠ ታወቀው:: ለማሪየስ ናፖሊዮን ማለት ግን ከዚህ የበለጠ ነበር፡፡ የወደፊት ተስፋ ፧ የድምበር
መከታና የፈረንሳይ አለኝታ ከናፖሊዮን ቦናፓርቴ ላይ አየ:: ናፖሊዮን ጨካኝ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን እርሱ መታየት ያለበት ከሪፑብሊክ ምስረታ፧
ከለውጥ፤ ከአብዮት ጋር ነው:: ናፖሊዮን የሕዝብ ሰው እንደሆነ አመነ፡፡አባቱ ጦር ሜዳ የተዋጋውና ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠው ለሰዎች እኩልነትና "
ለሪፑብሊኩ ምሥረታ እንደሆነ በፍጹም ልቡ ተቀበለ፡፡ የዚህ ተቃዋሚ የሆነውን የቡርዣን አገዛዝ ጠላ፡፡
አያቱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚደግፉት እርሱ የጠላውን ነበር፡፡ በዚህ የተነሣ በአያትና በልጅ ልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጠረ:: ከነአካቴው አያቱ ከአባቱ ጋር ያለያዩት በዚህ መሠረታዊ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት እንደሆነ በተገነዘበ ጊዜ አያቱን በጣም ጠላቸው:: በዚህ በግል ጥቅም በታወሩ ሰው ምክንያት ርህራሄ በተለየው ጭካኔ ልጅ ሊያፈቅረው ከሚችል አባቱ፧ አባት ከሚወደው ልጁ መለያየታቸው እጅግ በጣም አሳዘነው። ማሪየስ ከአባቱ ጋር የተለያየው በዚህ ምክንያት መሆኑን ባወቀ ጊዜ ለአባቱ
ያለው ፍቅር ሲገነፍል ለአያቱ የነበረው ጥላቻ ግን ከደሙ ጋር ተዋሃደ። አባቱ ማለት ለሰዎች ደኅንነት፤ ለሰዎች እኩልነትና ለትክክለኛ ፍርድ የቆመ ታላቅ ሰው ማለት ሲሆን፧ መሴይ ጊልኖርማንድ ማለት ደግሞ
በግል ጥቅም የታወሩ፤ ለጥቂት ሰዎች ደኅንነት ጥብቅና የቆመና እንደ መዥገር በሰዎች ደም የሰቡ ሰው ናቸው።ስለዚህ ቅራኔያቸው የሚታረቅ አልሆነም፡፡ ይህም የአያቱን ዓይን ላለማየት አስወሰነው:: ሰበብ አስባብ
እየፈጠረ ከቤት ይጠፋ ጀመር፡፡ አክስቱ ድንገት አግኝተው የት እንደነበር ሲጠይቁት «ጥናት በዝቶብኝ ከጓደኞቼ ጋር ሳጠና፧ ፈተና ስለነበረብን ከአንድ ጓደኛዬ ቤት ውስጥ ተዘግተን ስናጠና፧ ፍርድ ቤት ሄደን ስለፍርድ
አሰጣጥ ትምህርት ስንቀስም፤ አሁን ትምህርቴን ወደማጠናቀቁ ስለሆነ የመመረቂያ ጽሑፍ መጻፍ ስለጀመርሁ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ስለምውል»እያለ ሌላም፤ ሌላም መልስ ይሰጣቸዋል::
አያቱ ግን «ማሪየስ ፍቅር ይዞት ፍቅረኛው እያንከራተተችው ነው»
በሚል መደምደሚያ ላይ ስለደረሰና እርሳቸውም በዚህ ዓይነት ገጠመኝ ያለፉ ስለሆነ ብዙም አልተጨነቁበትም:: ሆኖም ማሪየስ እንኳን ቀን ሊገባ አድሮም የሚመጣበት ጊዜ በረከተ።
አንድ ቀን ‹‹የት ሊሄድ ይችላል?» ሲሉ አክስቱ ጠየቁ::
ማሪየስ አባቱ በጻፈለት ማስታወሻ መሠረት ተናድዬን ለመጠየቅ
ሞንትፌርሜ ሄዶአል፡፡ ከዚያም የቀድሞውን የዋተርሉ ሃምሣ አለቃ ፧የዛሬው የሆቴል ቤት ጌታ ሚስተር ቴናድዬ ከስሮ ሆቴል ቤቱ ስለተዘጋ ፍለጋው አራት ቀን ወሰደበት።
በእርግጥ ፈሩን እየለቀቀ ነው» አሉ አያቱ እንደዚያ ሲቆይ፡፡
በጥቁር ጨርቅ የተንጠለጠለ አንድ ነገር ከሸሚዞ ስር ከአንገቱ ላይ ማሰሩን አባትና ልጅ ቀደም ሲል ማየታቸውን አንስተው ተወያዩ::
ማሪየስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፓሪስ ከተማ ሲጠፋ የሄደው ወደ ቬርኖን ነበር። ቬርኖን ከተማ ሄዶ በጠፋ ቁጥር አያቱ «ተኝቶ ነው» ይላሉ፡፡
አንድ ቀን ጠዋት ማሪየስ ከቬርኖን ተመልሶ ከቤት ሲገባ አያቱ
ይሰሙታል፡፡ ከሁለት ቀን የአሳብ ጭንቀትና መንገድ በኋላ ስለነበረ
የተመለሰው በጣም ደክሞታል:: ብዙ እንቅልፍ ስላላገኘ ቶሎ ብሎ ለአንድ ሰአት እንኳን ቢሆን ለመተኛት ይፈልጋል፡፡ ኮቱንና አንገቱ ላይ ያጠለቀውን
አውልቆ አልጋው ላይ ወረወረ፡፡ እንዳይረበሽ ከመዋኛ ሥፍራ አጠገብ በሚገኝ ክፍል ውስጥ ለመተኛት ፈልጎ ወደዚያው ሄደ:: ጤነኛ የሆነ ሽማግሌዎች በጠዋት መንቃታቸው የተለመደ ስለሆነ መሴይ ጊልኖርማንድ በዚያን እለት በጠዋት በመንቃታቸው ማርየስ ከውጭ ሲገባ ሰሙት ካልጋቸው ተነስተው በሽማግሌ እግር ቶሉ ቶሉ በመራመድ የማሪየስ የመኝታ ቤት ወደነበረበት ክፍል ወደ ፎቅ ወጡ:: የወጡት ሊያቅፉና
ሊስሙት፧ በዚያውም ከየት እንደሚመጣ ሊጠይቁት ነበር፡፡ ግን ከክፍሉ ሲደርሱ ማሪየስ አልነበረም:: አልጋው እንደተነጠፈ ነው:: ኮቱና አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለው በጥቁር ሪሪበ የታሠረው ነገር ከአልጋው ላይ
ተቀምጠዋል፡፡
«ይህቺ ጥሩ ናት» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ::
ልጃቸው ወደ ነበሩበት ወደ ምድር ቤት ሳሉን ወረዱ:: እህትየው
ተነስተው ኖሮ ከሳሉን ቤት ቁጭ ብለው ጥልፍ ይጠልፋሉ፡፡ መሴይ
ጊልኖርማንድ በአንድ እጃቸው የማሪየስን ኮት በሌላ እጃቸው አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለውን ነገር ይዘዋል::
«ድል ይሉሻል ይኼ ነው ፤ ምስጢሩን ሳንደርስበት አንቀርም::
መጨረሻውን እንደርስበታለን፤ ይኸውልሽ ጉዳ» ሲሉ ጮሁ ፤ ልጃቸው ከነበሩበት ክፍል እንደገቡ፡፡
በሪበን የተንጠለጠለው ነገር የሳጥን ቅርጽ ያለውና የሚከፈት ነው ሽማግሌው ሳይከፍቱት አተኩረው ተመለከቱት::
‹‹አባባ ፧ ክፈተውና እንየው» አለች ልጃቸው::
ሳጥኑን ጫን ሲሉት ይከፈታል፡፡ በውስጠ ያገኙት ከብጣሽ ወረቀት
በስተቀር ሌላ ነገር አልነበረም::
«ከአንድዋ ፍቅረኛው ወደ ሌላዋ» አለ መሴይ ጊልኖርማንድ በኃይል
እየሳቀ:: «ምን እንደሆነ አውቀዋለሁ ፤ የፍቅር ደብዳቤ!››
‹‹ይሆናል፧ ይነበባ!» አለች የማሪየስ አክስት::
መነጽርዋን አደረገች፡፡ ወረቀቱን ዘረጋጋችና አነበበችው::
«ለምወድህ ልጄ ፣ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ:: እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ››
የአባትና የልጅ ፊት እንዴት እንደተለዋወጠና ስሜታቸው ምን እንደነበር መግለጽ ያዳግታል:: የሞት ጥላ እንደተጋረደበት ሰው በብሽቀት ደነዘዙ፤ እብድ ሆኑ:: በንዴት ሰከኑ:: ዝም ዝም ተባባሉ፡፡ በመጨረሻ መሴይ ጊልኖርማንድ እርስ በራሱ እንደሚናገር ሰው እጅግ ዝቅ ባለ ድምፅ ተናገሩ::
‹‹የዚያ ጦረኛ የእጅ ጽሑፍ ነው::»
👍22
«አክስቱ ጽሑፉን አገላብጣ መረመረችው:: አገላብጣ ካየችው በኋላ ከሳጥኑ ውስጥ መልሳ ከተተችው:: እርስዋ ወረቀቱን ስትጨምር ለአላውቅ
ሰማያዊ ቀለም ያለው ወረቀት ከማሪየስ ኮት ኪስ ወደቀ:: ብድግ አደረገችው አንድ መቶ የግል ካርዶች ነበሩ፡፡ እንዱን ለመሴይ ጊልኖርማንድ ሰጠቻቸው
ከካርዶቹ ጀርባ ባሮን ማሪየስ ፓንትመርሲ የሚል ጽሑፍ ተጽፎበታል፡፡ ፍሉም
ሽማግሌው ደወል ደወሉ:: አሽከር ገባ:: ሪበኑንና ሳጥን መሳዩን ነገር!
እንዲሁም የማሪየስን ኮት ከመሬት ከወረወርዋቸው በኋላ «ከዚህ አጥፋልኝ ! ሲሉ ተናገሩ፡፡
አንድ ሰዓት ሙሉ በዝምታ አለፈ:: ኣባትና ልጅ ጀርባ ተሰጣጥተው
ዝም ተባብለው ተቀመጡ:: ምናልባት ስለተመሳሳይ ነገር ሳያስቡ አልቀሩም ፡
ከአንድ ሰዓት በኋላ የማሪየስ አክስት «ይሁና፤ ደህና ነዋ!» ስትል ተናገረች::
ወዲያው ማሪየስ ሰዎቹ ከነበሩበት ክፍል ገባ፡፡ ከሳሎኑ እንደገባ
ካሳተመው ካርድ አንዱን አያቱ ይዘውት ተመለከተ:: የማሪየስ ወደ ሳሎን መግባት ሽማግሌው ባዩ ጊዜ ‹‹ቁም! ቁም! ቁም! አሁን እኮ አንተ ባሮን ነህ::
እንኳን ደስ ያለህ እልሃለሁ:: እስቲ ይህ ምን ማለት እንደሆነ አስረዳን?» ሲሉ ተናገሩ::
ማሪየስ ጥቂት ደንገጥ ቢልም ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ ሰጠ፡፡
«ትርጉሙማ እኔ የአባቴ ልጅ ነኝ ማለት ነው» አለ፡፡
«አባትህ! አባትህማ እኔ ነኝ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ
«አባቴ» አለ ማሪየስ በመደንገጥ የመሴይ ጊልኖርማንድን ዓይን፥
ኮስተር ብሎ እያየ፤ «አባቴ ሪፑብሊኩንና ፈረንሳይን ያገለገለ ጀግና ሰው ነበር፡፡ ስሙ ከጀግኖች ታሪክ ማኅደር ውስጥ ተጽፎ ይገኛል፡፡ የአገሩን ድምበር ላለማስደፈር ለሃያ አምስት ዓመታት የቀን ፀሐይ፣ የማታ ቁር
ሳይበግረው ቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ ኖሮአል:: የአገሩን ክብር ለማስጠበቅ ሲዋጋ ከሃያ ቦታ ላይ ቆስሉአል:: ሆኖም ለአገሩ የሰጠው አገልግሎት ተረስቶ እንዳልሆነ ሆኖ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ:: አባቴ የፈጸመው ስህተት ቢኖር ሁለት ነው:: እነርሱም አገሩንና እኔን ከመጠን በላይ መውደዱ ናቸው::
ይህ አነጋገር የመሴይ ጊልኖርማንድ ሕሊና ሊቀበለውና ሊያደምጠው የሚችል አልነበረም:: ገና ሪፑብሊክ የሚል ቃል ሲሰሙ ከመቀመጫቸው
ብድግ አሉ:: ራሳቸው የንጉሠ ነገሥቱ ወገን ነኝ» ብለው ስለሚያምኑ ማሪየስ አፍ የወጣው እያንዳንዱ ቃል እንደ ጦር እየወጋ ፊታቸውን አከሰመው::
«ማሪየስ» ሲሉ ጮሁ:: አንተ ትፋታም! አባትህ ምን እንደነበር
- ባውቅም፤ ለማወቅም አልፈልግም ስለእርሱ የማውቀው ነገር የለኝም:: እሱነቱንም አላውቅም:: የማውቀው ነገር ቢኖር በአንድ ወቅት ርባነቢስ
የሆኑ ጥቂት ሰዎች እንደነበሩ ነው እነሱም ቢሆኑ ለማኞች ነፍሰገዳዮች የሚሊቴር ፖሊሶች ሌቦች ነበሩ፡፡ ሁሉም ሁሉም ነው
የምለው:: ከዚህ የተለዩ አልነበሩም:: ከዚህ የተለየ እኔ ማንንም አላውቅም::ሁሉንም ነው የምለው:: ማሪየስ ፤ ሰማህ? አንተ ብሎ ባሮን እነዚያ ሽፍቶች ፤ ቀማኞች ፧ አታላዮች ፤ አታላዮች ፤ አታላዮች እውነተኛውን ንጉስ
ከድተው ቦናገርቴን የተከተሉ ፈሪዎች ፧ የፈሪ ፈሪዎች ናቸው:: ዋተርሉ ላይ ጠላቶችን ፈርተው የሸሹ ወርቦለች! ይኽ ነው እኔ የማውቀው::አባትህ ከነዚህ ዉስጥ ከሆነ አዝናለሁ አላውቀውም ብል ይሻላል::....
💫ይቀጥላል💫
ሰማያዊ ቀለም ያለው ወረቀት ከማሪየስ ኮት ኪስ ወደቀ:: ብድግ አደረገችው አንድ መቶ የግል ካርዶች ነበሩ፡፡ እንዱን ለመሴይ ጊልኖርማንድ ሰጠቻቸው
ከካርዶቹ ጀርባ ባሮን ማሪየስ ፓንትመርሲ የሚል ጽሑፍ ተጽፎበታል፡፡ ፍሉም
ሽማግሌው ደወል ደወሉ:: አሽከር ገባ:: ሪበኑንና ሳጥን መሳዩን ነገር!
እንዲሁም የማሪየስን ኮት ከመሬት ከወረወርዋቸው በኋላ «ከዚህ አጥፋልኝ ! ሲሉ ተናገሩ፡፡
አንድ ሰዓት ሙሉ በዝምታ አለፈ:: ኣባትና ልጅ ጀርባ ተሰጣጥተው
ዝም ተባብለው ተቀመጡ:: ምናልባት ስለተመሳሳይ ነገር ሳያስቡ አልቀሩም ፡
ከአንድ ሰዓት በኋላ የማሪየስ አክስት «ይሁና፤ ደህና ነዋ!» ስትል ተናገረች::
ወዲያው ማሪየስ ሰዎቹ ከነበሩበት ክፍል ገባ፡፡ ከሳሎኑ እንደገባ
ካሳተመው ካርድ አንዱን አያቱ ይዘውት ተመለከተ:: የማሪየስ ወደ ሳሎን መግባት ሽማግሌው ባዩ ጊዜ ‹‹ቁም! ቁም! ቁም! አሁን እኮ አንተ ባሮን ነህ::
እንኳን ደስ ያለህ እልሃለሁ:: እስቲ ይህ ምን ማለት እንደሆነ አስረዳን?» ሲሉ ተናገሩ::
ማሪየስ ጥቂት ደንገጥ ቢልም ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ ሰጠ፡፡
«ትርጉሙማ እኔ የአባቴ ልጅ ነኝ ማለት ነው» አለ፡፡
«አባትህ! አባትህማ እኔ ነኝ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ
«አባቴ» አለ ማሪየስ በመደንገጥ የመሴይ ጊልኖርማንድን ዓይን፥
ኮስተር ብሎ እያየ፤ «አባቴ ሪፑብሊኩንና ፈረንሳይን ያገለገለ ጀግና ሰው ነበር፡፡ ስሙ ከጀግኖች ታሪክ ማኅደር ውስጥ ተጽፎ ይገኛል፡፡ የአገሩን ድምበር ላለማስደፈር ለሃያ አምስት ዓመታት የቀን ፀሐይ፣ የማታ ቁር
ሳይበግረው ቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ ኖሮአል:: የአገሩን ክብር ለማስጠበቅ ሲዋጋ ከሃያ ቦታ ላይ ቆስሉአል:: ሆኖም ለአገሩ የሰጠው አገልግሎት ተረስቶ እንዳልሆነ ሆኖ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ:: አባቴ የፈጸመው ስህተት ቢኖር ሁለት ነው:: እነርሱም አገሩንና እኔን ከመጠን በላይ መውደዱ ናቸው::
ይህ አነጋገር የመሴይ ጊልኖርማንድ ሕሊና ሊቀበለውና ሊያደምጠው የሚችል አልነበረም:: ገና ሪፑብሊክ የሚል ቃል ሲሰሙ ከመቀመጫቸው
ብድግ አሉ:: ራሳቸው የንጉሠ ነገሥቱ ወገን ነኝ» ብለው ስለሚያምኑ ማሪየስ አፍ የወጣው እያንዳንዱ ቃል እንደ ጦር እየወጋ ፊታቸውን አከሰመው::
«ማሪየስ» ሲሉ ጮሁ:: አንተ ትፋታም! አባትህ ምን እንደነበር
- ባውቅም፤ ለማወቅም አልፈልግም ስለእርሱ የማውቀው ነገር የለኝም:: እሱነቱንም አላውቅም:: የማውቀው ነገር ቢኖር በአንድ ወቅት ርባነቢስ
የሆኑ ጥቂት ሰዎች እንደነበሩ ነው እነሱም ቢሆኑ ለማኞች ነፍሰገዳዮች የሚሊቴር ፖሊሶች ሌቦች ነበሩ፡፡ ሁሉም ሁሉም ነው
የምለው:: ከዚህ የተለዩ አልነበሩም:: ከዚህ የተለየ እኔ ማንንም አላውቅም::ሁሉንም ነው የምለው:: ማሪየስ ፤ ሰማህ? አንተ ብሎ ባሮን እነዚያ ሽፍቶች ፤ ቀማኞች ፧ አታላዮች ፤ አታላዮች ፤ አታላዮች እውነተኛውን ንጉስ
ከድተው ቦናገርቴን የተከተሉ ፈሪዎች ፧ የፈሪ ፈሪዎች ናቸው:: ዋተርሉ ላይ ጠላቶችን ፈርተው የሸሹ ወርቦለች! ይኽ ነው እኔ የማውቀው::አባትህ ከነዚህ ዉስጥ ከሆነ አዝናለሁ አላውቀውም ብል ይሻላል::....
💫ይቀጥላል💫
👍21❤3
#የመደርደሪያው_ጫፍ
፡
፡(የመጨረሻ ክፍል)
#በአሌክስ_አብርሃም
....ሳሙናዬን ተቀብዬ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ በቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ሂሉ እንባዋ ጠብ እስኪል እየሳቀች ሳሙናውን ገዝቼ ከሄድኩ በኋላ ከግርማ ጋር የተባባሉትን እንዲህ ስትል ነገረችኝ፡፡.አወራሯ
ድራማ ነው የሚመስለኝ። ሂሉ ሲበዛ ነፃ ነች፡፡
እንተ ” በሳቅ ፍርስርስ አለች፤
“ምን ያስቅሻል?”
"እይውልህማ…ብታይ…ትላንት ሳሙና ስጭኝ ስትለኝ ሰጥቼህ (ረዥም ሳቅ )..ሰጥቼህ ከሄድክ
በኋላ ግርምሽ ብስጭት ብሎ ሲነዘንዘኝ አላመሽ መሰለህ! ሆሆ!”
“ምን አነዛነዘው ?”
ነገረችኝ፤ ልከ እኔ እንደወጣሁ ግርማ ሂሉን ጠየቃት፣
".…እኔ የምልሽ! አብረሃም 'ሳሙና ስጭኝ' ነው ያለሽ አይደለም እንዴ?”
“እዎ እና እኔስ ሌላ ምን ሰጠሁት?”
“ምን እንደሰጠሽውማ አንችው ታውቂያለሽ”
“እንዴ! ግርምሽ ምን ማለትህ ነው?”
“የሳሙናውን ዓይነት አልተናገረም፡፡ እንዴት ዘለሽ እዛ ትንጠላጠያለሽ? እዚህ የገላ ሳሙና አለ፥ እዛጋ አጃክስ አለ፤ ላርጎ ፈሳሽ ሳሙና አለ፤ ምን እንደፈለገ በምን አወቅሽ ?”
ሂሉ ደነገጠች፡፡ ቢሆንም ኮስተር ብላ መለሰችለት፡፡
“ሁልጊዜ የሚወስደው ይሄንን ነዋ!"
“እስኪ እሱን የዱቤ ደብተር አቀብይኝ አለ፤ አቀበለችው፡፡ የወሰድኩትን ዝርዝር አየና የታለ
ሳሙና ወስዶ የሚያውቀው?” አላት በብስጭት፡፡
“እየከፈለ ነው የሚወስደው"
“ያሁኑን መቼ ከፈለ ?
“ኤጭ እንግዲህ አትጨቅጭቀኝ ! ወይ 'ሱቁን ዝጊና ቤት ተቀመጭ! በለኝ አለች ብስጨት ብላ፤
በዱቤ ደብተሩ ወርውሮ ሳታት፡፡ ከፀያፍ ስድብ ጋር “ሸርሙጣ!"
ይህን ሰትነግረኝ ሁለታችንም ከልባችን ሳቅን፡፡ ስቃ ስቃ ሲወጣላት “እንተ ምናለብህ ሳቅ ገብተህ በሰላም ለጥ ትላለህ፤ የሰው ትዳር እየበጠበጥክ ልክ ስለሌላ ሰው ትዳር የምታወራ ነበር የምትመስለው።
ባሏ ግርማ ከሌለ ወሬያችን መቆሚያ የለውም፡፡ እንደማልወደው ታውቃለች፡፡ እሱም እንደማይወደኝ ታውቃለች። ይሄ ነገር ሳያስቃት አይቀርም፡፡ ሰው ከመሬት ተነስቶ ይጠማመዳል?ሆሆሆ ትላላች። ከዛም ልክ የመጀመሪያው ወሬ አካል እስኪመስለኝ ሌላ ርዕስ ውስጥ ትገባለች፡፡
"አንተ እቺ ሸሚዝ አሁንም አለች?” አለችኝ ድንገት የለሰስኳትን ሸሚዝ በግርምት እየተመለከተች፡፡
"አዎ የት ትሄዳለች ?”
የመጀመሪያ ቀን እዚህ ሱቅ ስትመጣ እችን ነበር የለበስከው..ፀጉርህ ጨብረር ብሎ እዚች ጋ ቆመህ.ወረፉ ነበር፣ ሰው ሁሉ እያለፈህ ገዝቶ ሲሄድ እንተ ዝም ብለህ ቆመህ ..ሂሂሂሂ
ሌባ መስለከኝ፣ ስልኬን አንስቼ መሳሲያዩ ውስጥ አስቀመጥኩት ሃሃሃሃ…ከዛ በአንድ ዐይኔ አንተን
እያየሁ፡ በአንድ ዐይኔ ደንበኞቼን ሳስተናግድ ነበር፡፡…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ !” አወራሯ ያስቃል፡፡ ሌባ ትመስላለህ እያለች እንኳን ታስቃኛለች።.ደግሞ የሚገርመኝ አሳሳቋ ሳቁ
እንሳቅ ዓይነት ግብዣ ነው በቃ !
ግርምሽም ሌባ ነበር የምትመስለው አሁንም ሐሳቡን የቀየረ አይመስለኝም፡፡
ሃሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂ…” ሁለተኛዋን አረፍተ ነገር ስራዬ ብላ እኔን ለማብሸቅ የጨመረቻት
ብትሆንም እያውቅኩም ተበሳጨሁ፡፡
"እናትክን በይው እሺ!”
"ሃሃሃሃ አንተ ባለጌ ስድ ባሌ እኮ ነው! ሂሂሂሂሂሂሂ…»
"እኮ ባልሸን እናትክን በይው!.…ማታ እቅፍ አድርገሽ ጉንጩን እየሳምሽ : መቼም ይሄ ማቀፍም
መሳምም አይገባው…'የኔ ቆንጆ አብርሃም እናትክን ብሎሃል እሽ ! በይው"
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃም የሚያልፈው ሰው እየዞረ እስኪመለከት ሳቋን ለቀቀችው፤
እየሳቀች እንባዋ ሲፈስ ገርሞኝ ነበር፡፡ በቀጥታ እየሳቀች ማልቀስ መጀመሯን ያወቅኩት ወዲያው
ነበር፡፡
እንዴት እንደመረረኝ!” አለችኝ፡፡ ደነገጥኩ፡፡ ብሶቷን ዘረገፈችው፡፡
የሐረር ልጅ ናት፡፡ ዘጠነኛ ክፍል እያለች ይሄ ያሁኑ ባሏ ግርማ ወታደር ሆኖ ሰፈራቸው የነበረ
ካምፕ ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ያኔ ተጫዋች፣ ወንዳወንድ፣ በቃ የሚፈቀር ሰው ነበር፡፡ ለጓደኝነት
ሲጠይቃት አላንገራገረችም፡፡ “
ይዤሽ ልጥፋ!” ሲላት አምናዋለች፡፡ ካለ እናት ያሳደጋትን አንድ አባቷን ጣጥላ ይሄን መዶሻ ራስ ተከትላ እዲስ አበባ ገባች፡፡ እናቱ፣ እህቶቹ፣ ወንድሞቹ
ሳይቀሩ አተካኗት፡፡ ለጎብረት ያገቧት ይመስል በትዳሯ እየገቡ መፈትፈት ጀመሩ፡፡ ነፃ ሆኗን
አለሌነት፣ ሳቋን የሽርሙጥና ደውል አድርገው ዐይንሽን ላፈር አሏት፤ እንደ አዲሳባ ሰው በሯንም
ጥርሷም በልኩ መከፈት ያላደገባትን፡፡ ሚስኪን ! ልለማመድህ ብትለውም አልሆነላትም፡፡
" ኤጭጭ አቦ እንደፈለጉ ይሁኑ!" ብላ ሳቋንም ነፃነቷንም ተያያዘችው፡፡ ይባስ ብሎ ሳቋ ማርኮት እንዳልወደዳት “ሳቅሽን አቁሚ!“ አላትና አረፈው!! ብዙ ባሎች የባል ድንበሩ የት ድረስ እንደሆነ አያውቁም፡፡ ትንሽ ባሎች ደግሞ ድንበራቸው ላይ ሳይደርሱ ይቆማሉ፡፡
አባቷ እሷን ፍለጋ ተከራትቶ ተንከራትቶ ሲሞት አፈር አላለበሰችውም፡፡ የሐረር ሰው ውሎ ይግባ አልቅሶ ቀበረው፡፡ በምድር ላይ የነበራት አንድ መሸሻ ዋሻ ተደፈነ፡፡አሁን ግርማ መድረሻ
የሌላት ከንፏ የተሰበረ ወፍ አደረጋት። “በየመንገዱ ስታገጭ ነው ያገኘሁሽ" አላት ፣ እንደ
ሚስት ሳይሆን እንደ ሰራተኛ ከፍ ዝቅ አድርጎ ያዝዛት ጀመረ፡፡ ያኔ ካስቀመጠባት መንበር ጎትቱ
አወረዳዳት፡፡ ለሴት ልጅ ትልቁ ከብሯ ቤተሰቧ መሆኑን አመነች፡፡ ለምን አፈር ጠርጎ የሚተኛ
ደሃ አይሆንም ቤተሰብ አለኝታ ነው ! ፍቅር ይወጣል፣ ይጠልቃል፡፡ እቃ ! የሰው ፍቅር እንደ ፀሐይ ምስራቅና ምዕራብ አለው:: እየጣፈጠ ወጥቶ፣ እያቃጠለ ይጠልቃል! ቤተሰብ ግን ሰማይ ነው:: የሕይወት ፀሐይና ጨረቃ ሰፈራረቅ የማይቀያየር፣ የማይጠልቅ፣ የማይጠቀለል ቦታውንም
የማይቀይር ሰፊ ሰማይ ማለት ቤተስብ ነው፡፡ ሂሉ ቤተሰብ የላትም፡፡ ሰማይ የለም፡፡ ቀጥ ስትል ኦና ነው ባዶ ነው ! ኮከብ የለም፣ ጨረቃ የለችም፣ ፀሐይም የለችም፡፡ ሰማይ በሌለበት
ምንም የለም፡፡ እግዜር የት ይሆን መቀመጫው ? የት ሆኖ ይሆን ይህን ጉድ የሚመለከተው?!
የአዲስ አበባ ኑሮ አንሸገሻት። ለምሬቷ ጣዕም ኮሶ የጨመረው ባሏ ነው:: “ታምናለህ…. ከሳመኝ
ስንት ጊዜው ? አለችኝ፡፡ ግን እወደዋለሁ ! ስድቡ፣ ማቃለሉ እያቃጠለኝ እንኳን እወደዋለሁ !
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ አንተ እስለፈለፍከኝ :" አለችና ሳቋን ለቀቀችው:: የኔ ሚስኪን !!
ባለፈው ሐሙስ ደግሞ ሂሉ ወደኔ ጠጋ ብላ ፊት ለፊቴ ቆመች::መሐላችን ላይ ሚዛኑ አለ፡፡ ፊቷ ልክ አልነበረም፡፡ ቶሎ እንድሄድባት መፈለጓ በግልፅ ያስታውቃል፡፡
አንድ ትንሽ ልጅ መጥቶ "ሳሙና ስጭኝ ! ቢጫውን አላት፤
“የለም " አለች፣ ግን ፊት ለፊት ተደርድሮ ነበር፡፡
ሌላ ሴት መጣችና “ስኳር ስጭኝ ሕሊና ኣለቻት፡፡
“የለም !" ፈት ለፊት ኩንታል ስኳር ተቀምጧል፡፡ ገርሞኝ ጠየቅኳት፡፡
“ሂሂሂ.አንተ ካልሄድhልኝ በስተቀር ምንም ነገር አልሸጥም ዛሬ እየቀለደች መስሎኝ ነበር።
“ማሪያምን !" ስትለኝ የላፕቶፕ ቦርሳዬን እንስቼ፣ “በይ ቻው !” አልኳት፡፡
“ቻው አብርሽ !" አለችኝ በቅሬታ ፈገግታ፡፡ “አብርሽ ብላኝ አታውቅም፤ ግራ ገባኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን ሂሉ የለችም ነበር፤ ባሏ ተገትሯል፡፡
"ሰላም ዓርማ"
“ምን ልስጥህ?” አለኝ ኮስተር ብሎ፣
"ኮካ"
"የለም"
"እሺ ቀዝቃዛ ሰፕራይት አድርገው"
"የለም"
፡
፡(የመጨረሻ ክፍል)
#በአሌክስ_አብርሃም
....ሳሙናዬን ተቀብዬ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ በቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ሂሉ እንባዋ ጠብ እስኪል እየሳቀች ሳሙናውን ገዝቼ ከሄድኩ በኋላ ከግርማ ጋር የተባባሉትን እንዲህ ስትል ነገረችኝ፡፡.አወራሯ
ድራማ ነው የሚመስለኝ። ሂሉ ሲበዛ ነፃ ነች፡፡
እንተ ” በሳቅ ፍርስርስ አለች፤
“ምን ያስቅሻል?”
"እይውልህማ…ብታይ…ትላንት ሳሙና ስጭኝ ስትለኝ ሰጥቼህ (ረዥም ሳቅ )..ሰጥቼህ ከሄድክ
በኋላ ግርምሽ ብስጭት ብሎ ሲነዘንዘኝ አላመሽ መሰለህ! ሆሆ!”
“ምን አነዛነዘው ?”
ነገረችኝ፤ ልከ እኔ እንደወጣሁ ግርማ ሂሉን ጠየቃት፣
".…እኔ የምልሽ! አብረሃም 'ሳሙና ስጭኝ' ነው ያለሽ አይደለም እንዴ?”
“እዎ እና እኔስ ሌላ ምን ሰጠሁት?”
“ምን እንደሰጠሽውማ አንችው ታውቂያለሽ”
“እንዴ! ግርምሽ ምን ማለትህ ነው?”
“የሳሙናውን ዓይነት አልተናገረም፡፡ እንዴት ዘለሽ እዛ ትንጠላጠያለሽ? እዚህ የገላ ሳሙና አለ፥ እዛጋ አጃክስ አለ፤ ላርጎ ፈሳሽ ሳሙና አለ፤ ምን እንደፈለገ በምን አወቅሽ ?”
ሂሉ ደነገጠች፡፡ ቢሆንም ኮስተር ብላ መለሰችለት፡፡
“ሁልጊዜ የሚወስደው ይሄንን ነዋ!"
“እስኪ እሱን የዱቤ ደብተር አቀብይኝ አለ፤ አቀበለችው፡፡ የወሰድኩትን ዝርዝር አየና የታለ
ሳሙና ወስዶ የሚያውቀው?” አላት በብስጭት፡፡
“እየከፈለ ነው የሚወስደው"
“ያሁኑን መቼ ከፈለ ?
“ኤጭ እንግዲህ አትጨቅጭቀኝ ! ወይ 'ሱቁን ዝጊና ቤት ተቀመጭ! በለኝ አለች ብስጨት ብላ፤
በዱቤ ደብተሩ ወርውሮ ሳታት፡፡ ከፀያፍ ስድብ ጋር “ሸርሙጣ!"
ይህን ሰትነግረኝ ሁለታችንም ከልባችን ሳቅን፡፡ ስቃ ስቃ ሲወጣላት “እንተ ምናለብህ ሳቅ ገብተህ በሰላም ለጥ ትላለህ፤ የሰው ትዳር እየበጠበጥክ ልክ ስለሌላ ሰው ትዳር የምታወራ ነበር የምትመስለው።
ባሏ ግርማ ከሌለ ወሬያችን መቆሚያ የለውም፡፡ እንደማልወደው ታውቃለች፡፡ እሱም እንደማይወደኝ ታውቃለች። ይሄ ነገር ሳያስቃት አይቀርም፡፡ ሰው ከመሬት ተነስቶ ይጠማመዳል?ሆሆሆ ትላላች። ከዛም ልክ የመጀመሪያው ወሬ አካል እስኪመስለኝ ሌላ ርዕስ ውስጥ ትገባለች፡፡
"አንተ እቺ ሸሚዝ አሁንም አለች?” አለችኝ ድንገት የለሰስኳትን ሸሚዝ በግርምት እየተመለከተች፡፡
"አዎ የት ትሄዳለች ?”
የመጀመሪያ ቀን እዚህ ሱቅ ስትመጣ እችን ነበር የለበስከው..ፀጉርህ ጨብረር ብሎ እዚች ጋ ቆመህ.ወረፉ ነበር፣ ሰው ሁሉ እያለፈህ ገዝቶ ሲሄድ እንተ ዝም ብለህ ቆመህ ..ሂሂሂሂ
ሌባ መስለከኝ፣ ስልኬን አንስቼ መሳሲያዩ ውስጥ አስቀመጥኩት ሃሃሃሃ…ከዛ በአንድ ዐይኔ አንተን
እያየሁ፡ በአንድ ዐይኔ ደንበኞቼን ሳስተናግድ ነበር፡፡…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ !” አወራሯ ያስቃል፡፡ ሌባ ትመስላለህ እያለች እንኳን ታስቃኛለች።.ደግሞ የሚገርመኝ አሳሳቋ ሳቁ
እንሳቅ ዓይነት ግብዣ ነው በቃ !
ግርምሽም ሌባ ነበር የምትመስለው አሁንም ሐሳቡን የቀየረ አይመስለኝም፡፡
ሃሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂ…” ሁለተኛዋን አረፍተ ነገር ስራዬ ብላ እኔን ለማብሸቅ የጨመረቻት
ብትሆንም እያውቅኩም ተበሳጨሁ፡፡
"እናትክን በይው እሺ!”
"ሃሃሃሃ አንተ ባለጌ ስድ ባሌ እኮ ነው! ሂሂሂሂሂሂሂ…»
"እኮ ባልሸን እናትክን በይው!.…ማታ እቅፍ አድርገሽ ጉንጩን እየሳምሽ : መቼም ይሄ ማቀፍም
መሳምም አይገባው…'የኔ ቆንጆ አብርሃም እናትክን ብሎሃል እሽ ! በይው"
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃም የሚያልፈው ሰው እየዞረ እስኪመለከት ሳቋን ለቀቀችው፤
እየሳቀች እንባዋ ሲፈስ ገርሞኝ ነበር፡፡ በቀጥታ እየሳቀች ማልቀስ መጀመሯን ያወቅኩት ወዲያው
ነበር፡፡
እንዴት እንደመረረኝ!” አለችኝ፡፡ ደነገጥኩ፡፡ ብሶቷን ዘረገፈችው፡፡
የሐረር ልጅ ናት፡፡ ዘጠነኛ ክፍል እያለች ይሄ ያሁኑ ባሏ ግርማ ወታደር ሆኖ ሰፈራቸው የነበረ
ካምፕ ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ያኔ ተጫዋች፣ ወንዳወንድ፣ በቃ የሚፈቀር ሰው ነበር፡፡ ለጓደኝነት
ሲጠይቃት አላንገራገረችም፡፡ “
ይዤሽ ልጥፋ!” ሲላት አምናዋለች፡፡ ካለ እናት ያሳደጋትን አንድ አባቷን ጣጥላ ይሄን መዶሻ ራስ ተከትላ እዲስ አበባ ገባች፡፡ እናቱ፣ እህቶቹ፣ ወንድሞቹ
ሳይቀሩ አተካኗት፡፡ ለጎብረት ያገቧት ይመስል በትዳሯ እየገቡ መፈትፈት ጀመሩ፡፡ ነፃ ሆኗን
አለሌነት፣ ሳቋን የሽርሙጥና ደውል አድርገው ዐይንሽን ላፈር አሏት፤ እንደ አዲሳባ ሰው በሯንም
ጥርሷም በልኩ መከፈት ያላደገባትን፡፡ ሚስኪን ! ልለማመድህ ብትለውም አልሆነላትም፡፡
" ኤጭጭ አቦ እንደፈለጉ ይሁኑ!" ብላ ሳቋንም ነፃነቷንም ተያያዘችው፡፡ ይባስ ብሎ ሳቋ ማርኮት እንዳልወደዳት “ሳቅሽን አቁሚ!“ አላትና አረፈው!! ብዙ ባሎች የባል ድንበሩ የት ድረስ እንደሆነ አያውቁም፡፡ ትንሽ ባሎች ደግሞ ድንበራቸው ላይ ሳይደርሱ ይቆማሉ፡፡
አባቷ እሷን ፍለጋ ተከራትቶ ተንከራትቶ ሲሞት አፈር አላለበሰችውም፡፡ የሐረር ሰው ውሎ ይግባ አልቅሶ ቀበረው፡፡ በምድር ላይ የነበራት አንድ መሸሻ ዋሻ ተደፈነ፡፡አሁን ግርማ መድረሻ
የሌላት ከንፏ የተሰበረ ወፍ አደረጋት። “በየመንገዱ ስታገጭ ነው ያገኘሁሽ" አላት ፣ እንደ
ሚስት ሳይሆን እንደ ሰራተኛ ከፍ ዝቅ አድርጎ ያዝዛት ጀመረ፡፡ ያኔ ካስቀመጠባት መንበር ጎትቱ
አወረዳዳት፡፡ ለሴት ልጅ ትልቁ ከብሯ ቤተሰቧ መሆኑን አመነች፡፡ ለምን አፈር ጠርጎ የሚተኛ
ደሃ አይሆንም ቤተሰብ አለኝታ ነው ! ፍቅር ይወጣል፣ ይጠልቃል፡፡ እቃ ! የሰው ፍቅር እንደ ፀሐይ ምስራቅና ምዕራብ አለው:: እየጣፈጠ ወጥቶ፣ እያቃጠለ ይጠልቃል! ቤተሰብ ግን ሰማይ ነው:: የሕይወት ፀሐይና ጨረቃ ሰፈራረቅ የማይቀያየር፣ የማይጠልቅ፣ የማይጠቀለል ቦታውንም
የማይቀይር ሰፊ ሰማይ ማለት ቤተስብ ነው፡፡ ሂሉ ቤተሰብ የላትም፡፡ ሰማይ የለም፡፡ ቀጥ ስትል ኦና ነው ባዶ ነው ! ኮከብ የለም፣ ጨረቃ የለችም፣ ፀሐይም የለችም፡፡ ሰማይ በሌለበት
ምንም የለም፡፡ እግዜር የት ይሆን መቀመጫው ? የት ሆኖ ይሆን ይህን ጉድ የሚመለከተው?!
የአዲስ አበባ ኑሮ አንሸገሻት። ለምሬቷ ጣዕም ኮሶ የጨመረው ባሏ ነው:: “ታምናለህ…. ከሳመኝ
ስንት ጊዜው ? አለችኝ፡፡ ግን እወደዋለሁ ! ስድቡ፣ ማቃለሉ እያቃጠለኝ እንኳን እወደዋለሁ !
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ አንተ እስለፈለፍከኝ :" አለችና ሳቋን ለቀቀችው:: የኔ ሚስኪን !!
ባለፈው ሐሙስ ደግሞ ሂሉ ወደኔ ጠጋ ብላ ፊት ለፊቴ ቆመች::መሐላችን ላይ ሚዛኑ አለ፡፡ ፊቷ ልክ አልነበረም፡፡ ቶሎ እንድሄድባት መፈለጓ በግልፅ ያስታውቃል፡፡
አንድ ትንሽ ልጅ መጥቶ "ሳሙና ስጭኝ ! ቢጫውን አላት፤
“የለም " አለች፣ ግን ፊት ለፊት ተደርድሮ ነበር፡፡
ሌላ ሴት መጣችና “ስኳር ስጭኝ ሕሊና ኣለቻት፡፡
“የለም !" ፈት ለፊት ኩንታል ስኳር ተቀምጧል፡፡ ገርሞኝ ጠየቅኳት፡፡
“ሂሂሂ.አንተ ካልሄድhልኝ በስተቀር ምንም ነገር አልሸጥም ዛሬ እየቀለደች መስሎኝ ነበር።
“ማሪያምን !" ስትለኝ የላፕቶፕ ቦርሳዬን እንስቼ፣ “በይ ቻው !” አልኳት፡፡
“ቻው አብርሽ !" አለችኝ በቅሬታ ፈገግታ፡፡ “አብርሽ ብላኝ አታውቅም፤ ግራ ገባኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን ሂሉ የለችም ነበር፤ ባሏ ተገትሯል፡፡
"ሰላም ዓርማ"
“ምን ልስጥህ?” አለኝ ኮስተር ብሎ፣
"ኮካ"
"የለም"
"እሺ ቀዝቃዛ ሰፕራይት አድርገው"
"የለም"
👍32👎2
“ትንሿን ውሃ ስጠኝ እሺ ! ውሃውን ሊሰጠኝ ዘወር ሲል ፊት ለፊት ሰማያዊ መደብ ላይ በነጭ የተጻፈ ማስታወቂያ መለጠፉን ተመለከትኩ፡፡ “የኔ ብጤና ዱሴ ፈላጊ እግዘር ይስጥል ይላል።" የብልግና ጥግ ! ሂሉዩ ይሄን ለመጋረድ ነበር ትላንት ፊቴ እንደ ጨው አምድ ተገትራ
የነበረው፡፡
ይሄን ብትገነጥይ እገነጥልሻለሁ” ብሎ ፎከረባት፡፡ ግርማ እንደለጠፈው ቆይቶ ሰማሁ፡፡ እኔን
ለማኝ! ለማለት ፒያሳ ሂዶ ማስታወቂያ ያጽፋል !?…ጓጉንቸር!!
ህሊና ከሰዓት እፏን በስካርቭ ሸፍና ቆማ አገኘኋት፡፡
"ምነው ሂሉ?"
ትንሽ ጥርሴን አሞኝ ! ፊቷ ሞቶ ነበር፡፡ ዐይኖቿ ባዶ ቀፎ፤ አንድ የሕይወት ምዕራፍ በሆነ
ምክንያት የተዘጋ አይነት። ህሊና የትላንቷ አልነበረችም፡፡ ባላወቅኩት ምከንያት ተቆጣሁ፡፡
እስቲ ስካርቭዥን አንሺው” አልኳት፡፡
" ሂድ በቃ አብርሽ !" ብላ እንባዋ ተዘረገፈ፡፡ ከዛ በኋላ ህሊናን ለአንድ ሳምንት አላየኋትም፡፡
ለሁለት ለሦስት…ለስድስት ወር !!
ከአንድ ሳምንታ በኋላ ወደ ሱቁ ስሄድ ግርማ ከአንዲት የማልወዳት ሴት ጋር ቆሞ እያወራ
ነበር፡፡ ቀንቀት እያየኝ፡ “ አሁን ደግሞ ምን ቀረህ? ከሚስቴ ጋር አጣላኸን !” አለኝ፡፡ ዞር ብዬ
ሌላ ሰው መኖሩን ተመለከትኩ፤ እኔን አልመሰለኝም ነበር፡፡
አንተን ነው ባክህ ምን ታስመስላለህ አለኝ እያመናጨቀ። አንዲት የህሊናን እግር መውጣት
ተከትላ ግርማን እንደ ጭልፊት ለመንጠቅ ያሰበች የምትመስል ማዲያታም ሴት “ሆሆ..የልብን
ሰርቶ እንደገና ዐይንን በጨው አጥቦ መምጣት አለ እንዴ?” አለች፡፡ ይህቺ ሴት ካሁንም በፊት እኔና ህሊናን ስትመለከት ዐይኗ ደም የሚለብስ በተሳሳቅን ቁጥር በርሷ እየመሰላት የምትመናቀር
ለግርማም ነገር የምታመላልስ ነገረኛ ነበረች፡፡
“በሰላም ነው አልኩት።
“ወደዛ ሂድ ባክህ ' ሁለተኛ ሱቄ በር እንዳትደርስ፡፡ እዚህ አካባቢ ባይህ ጥርስህን ነው የማራግፈው!” አለ እያመናጨቀኝ፡፡ አሁን ዩኒፎርሙ ብቻ ሲቀር ወታደርነቱ ተመለሰበት፡፡ አብራው ያለችው ሴት “ግርምዬ በመቤቴ ተረጋጋ! የማይረባ ሰው ጋር አትጋጭ ፡ እጅህ ላይ አንድ ነገር ይሆንብሃል ? አለች፡፡
እንዲህ ስትለው ጭራሽ ለያዥ ለገናዥ አስቸግር ቁጭ አለ፡፡ እውነቱን ለመናገር ግርማንም ሆነ
ሴትዮዋን ከቁም ነገር አልፃፍኳቸውም፡፡ እንደው ነገሩ ገረመኝ እንጂ !
“አንተ ልክስክስ የሸርሙጣ ልጅ " ብሎኝ ቁጭ ! ቀኝ እጄኝ ጌታ ይባርከው !! ከቁጥጥሬ
ውጭ ተወንጭፍ ግርማ ጉንጭ ላይ በብርሃን ፍጥነት ሲያርፍ በመደርደሪያው ስር ተንገዳግዶ
ወደቀና ወዲያው አፈፍ ብሎ ተነሳ፡፡ ፊት ለፊቴ የነበረውን የሚዛን ሰሀን አነሳሁት፡፡ በአንድ
በኩል አንድ ኪሎ ግራም ብረት ነበር፡፡ እኔ ግን ሰሀኑን አንስቼ በቀጥታ ግርማ ግንባር ላይ
በጠርዙ በኩል አሳረፍኩት፡፡ ባባቴ ወንድ ነኝ፡፡
እልወጣልኝም፡፡ እሪታዋን የምታቀልጠውን አቃጣሪ በጥፊ አቃጠልኳት! ከዛ አገር ምድሩ
ተሰብስቦ ገላጋይ ሆነ። ግርማ ደሙን እያዘራ ይፎክራል፡፡ ወደፊት “ደሜን አፍስሼ ባቆምኩት
ሱቅ” እያለ ታሪክ ያዛባ ይሆናል፤ ይሄ የማይረባ ! ታሰርኩ፡፡ እናም ደግ ፖሊስ ገጥሞኝ ተፈታሁ፤ “ሂሉ ጋ እንዳትደርስም ብባልም ከዛ በኋላ እሷም ራሷ እንደጠፋች ሰማሁ፡፡ ስልክ እንኳን አልነበራትም ሂሉ፡፡ ከዛ ሰፈር ቤት የቀየርኩበት ምክንያት ያንን የመቃብር ቦታ የመሰለ ሱቅ ላለማየት ነበር፡፡
አንድ ምሽት ከስድስት ወር ይሁን ሰባት ወር በኋላ ስልኬ ሲጮህ አነሳሁት፡፡
“እንተ!"
ዝም.. ደንግጬ ነበር፡፡
“እብርሽ !"
ሄሉ !”
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…ተኝተህ ነው ? እንቅልፋም !" ልክ ትላንት የተገናኘን ነበር የሚመስለው
አነጋገሯ፡፡ ልታገኘኝ ቀጠረችኝ፡፡ ነገ ቅዳሚ ነው፤ እንኳን የሂሉ ቀጠሮ ተጨምሮቀት
ሂሉዬ አምሮባታል፤ አወራን፡፡
የዚያን ግዜ ግርማ የሚያስጠላ ማስታወቂያ ለጥፎ እንዳትገነጥይ አለኝ፤ እኔ ግን በብስጭት ገንጥዬ
ስጥለው በቦብስ ጥርሴን መታኝ፡፡ ሰማይ ምድሩ ነበር የዞረብኝ፡፡ ሴት በቦክስ ይመታል…ያውም እኔን ግልምጫ የሚበቃኝ ሂሂሂሂ" አለች፡፡ በጣቷ ነጭ ጥርሶቿ መሐል በግራ በኩል የተተካች
ሰው ሰራሽ ጥርስ እያሳየችኝ፡፡ አነጋገሯ ልብ ይሰብር ነበር፤ አጋዥ የሌለው አቅመቢስ ሰው
ዓይነት። በቃ ስካርፍ አድርጌ ያየኸኝ ቀን ማታ በሚኒባስ ተሳፍሬ ወደ ሐረር…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
ትንሽ እንደ መተከዝ አለች፡፡
አባቴ ሲሞት ሐረርም የሞተች መስሎኝ ነበር፡፡ ጓዋደኞቼ፣ የአባቴ ጓደኞች፣ ጎረቤቱ እንደ አዲስ ልቅሶ ተቀምጦ የአባቴን ሞት አዲስ አደረገው፡፡ አይዞሽ! አለኝ፡፡ ሰው ሁሉ የአባቴን ሞት ያፅናኑ መስሏቸው እኔን ከሞት ቀሰቀሱኝ፡፡ ሐረር ፍቅር ናት ሰው ሰው ይሸታሉ ሰዎቹ እንባዋና የደስታ ፈገግታዋ ተቀላቀለ፡፡ ሰው በሰው ሲረካ እንደዛን ቀን ተመልክቼ አላውቅም፡፡
ሂሉ አቤትትትትት እንዴት ስወድሽ እንደነበር እኮ !" አልኳት።
"አንተ አንድ ጥርስ አለብህ ላንተ የከፈልኩት ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
እየተንጠራራን ነበር ከሕይወት መደርደሪያ ላይ አስከፊ ትላንታችንን የምናጥብበት ሳሙና
ልናወርድ !
ሂሉ ባልሽን በሚዛን ፈነከትኩት እኮ…" አልኳት፡፡ አነጋገሬ “ተበቀልኩልሽ” ይሁን፣ አልያም
ጀግና ነኝ” ማለት ለራሴም አልገባኝ !
"ሃሃሃሃሃሃሃ ሰማሁ እኮ… አቦ ጌታ ይባርከህ! ሃሃሃሃሃሃ ባለጌ ነህ ግን.…ገና ሰማኒያችን
አልተቀደድም እኮ ! አሁን የመጣሁት ለዛ ነው...”
እየተንጠራራን ነበር፡፡ ከአዲስ አበባ ሐረር፣ ከሐረር አዲስ አበባ መደርደሪያው ቢርቅም ያቆምንበት የማፈላለግ ኩርሲ እንደምንም እያደራረሰን፡፡ ሂሉዪ አዲስ ኣበባ ዘመድ የላትም፡፡ እኔም ሐረር የማውቀው ሰው የለም፡፡ ግን እኔንም ሐረር ፣ ሂሉንም አዲስ አበባ ደጋግሞ ያስረገጠን ጉዳይ ምንድን ነው ? “ከምር ግን ምንድን ነው ? የሚሉ ጠያቂዎች ቢከሰቱ መልሳችን አንድ ነው፡፡
አቦ አትነዝንዙና !"
✨አለቀ✨
የነበረው፡፡
ይሄን ብትገነጥይ እገነጥልሻለሁ” ብሎ ፎከረባት፡፡ ግርማ እንደለጠፈው ቆይቶ ሰማሁ፡፡ እኔን
ለማኝ! ለማለት ፒያሳ ሂዶ ማስታወቂያ ያጽፋል !?…ጓጉንቸር!!
ህሊና ከሰዓት እፏን በስካርቭ ሸፍና ቆማ አገኘኋት፡፡
"ምነው ሂሉ?"
ትንሽ ጥርሴን አሞኝ ! ፊቷ ሞቶ ነበር፡፡ ዐይኖቿ ባዶ ቀፎ፤ አንድ የሕይወት ምዕራፍ በሆነ
ምክንያት የተዘጋ አይነት። ህሊና የትላንቷ አልነበረችም፡፡ ባላወቅኩት ምከንያት ተቆጣሁ፡፡
እስቲ ስካርቭዥን አንሺው” አልኳት፡፡
" ሂድ በቃ አብርሽ !" ብላ እንባዋ ተዘረገፈ፡፡ ከዛ በኋላ ህሊናን ለአንድ ሳምንት አላየኋትም፡፡
ለሁለት ለሦስት…ለስድስት ወር !!
ከአንድ ሳምንታ በኋላ ወደ ሱቁ ስሄድ ግርማ ከአንዲት የማልወዳት ሴት ጋር ቆሞ እያወራ
ነበር፡፡ ቀንቀት እያየኝ፡ “ አሁን ደግሞ ምን ቀረህ? ከሚስቴ ጋር አጣላኸን !” አለኝ፡፡ ዞር ብዬ
ሌላ ሰው መኖሩን ተመለከትኩ፤ እኔን አልመሰለኝም ነበር፡፡
አንተን ነው ባክህ ምን ታስመስላለህ አለኝ እያመናጨቀ። አንዲት የህሊናን እግር መውጣት
ተከትላ ግርማን እንደ ጭልፊት ለመንጠቅ ያሰበች የምትመስል ማዲያታም ሴት “ሆሆ..የልብን
ሰርቶ እንደገና ዐይንን በጨው አጥቦ መምጣት አለ እንዴ?” አለች፡፡ ይህቺ ሴት ካሁንም በፊት እኔና ህሊናን ስትመለከት ዐይኗ ደም የሚለብስ በተሳሳቅን ቁጥር በርሷ እየመሰላት የምትመናቀር
ለግርማም ነገር የምታመላልስ ነገረኛ ነበረች፡፡
“በሰላም ነው አልኩት።
“ወደዛ ሂድ ባክህ ' ሁለተኛ ሱቄ በር እንዳትደርስ፡፡ እዚህ አካባቢ ባይህ ጥርስህን ነው የማራግፈው!” አለ እያመናጨቀኝ፡፡ አሁን ዩኒፎርሙ ብቻ ሲቀር ወታደርነቱ ተመለሰበት፡፡ አብራው ያለችው ሴት “ግርምዬ በመቤቴ ተረጋጋ! የማይረባ ሰው ጋር አትጋጭ ፡ እጅህ ላይ አንድ ነገር ይሆንብሃል ? አለች፡፡
እንዲህ ስትለው ጭራሽ ለያዥ ለገናዥ አስቸግር ቁጭ አለ፡፡ እውነቱን ለመናገር ግርማንም ሆነ
ሴትዮዋን ከቁም ነገር አልፃፍኳቸውም፡፡ እንደው ነገሩ ገረመኝ እንጂ !
“አንተ ልክስክስ የሸርሙጣ ልጅ " ብሎኝ ቁጭ ! ቀኝ እጄኝ ጌታ ይባርከው !! ከቁጥጥሬ
ውጭ ተወንጭፍ ግርማ ጉንጭ ላይ በብርሃን ፍጥነት ሲያርፍ በመደርደሪያው ስር ተንገዳግዶ
ወደቀና ወዲያው አፈፍ ብሎ ተነሳ፡፡ ፊት ለፊቴ የነበረውን የሚዛን ሰሀን አነሳሁት፡፡ በአንድ
በኩል አንድ ኪሎ ግራም ብረት ነበር፡፡ እኔ ግን ሰሀኑን አንስቼ በቀጥታ ግርማ ግንባር ላይ
በጠርዙ በኩል አሳረፍኩት፡፡ ባባቴ ወንድ ነኝ፡፡
እልወጣልኝም፡፡ እሪታዋን የምታቀልጠውን አቃጣሪ በጥፊ አቃጠልኳት! ከዛ አገር ምድሩ
ተሰብስቦ ገላጋይ ሆነ። ግርማ ደሙን እያዘራ ይፎክራል፡፡ ወደፊት “ደሜን አፍስሼ ባቆምኩት
ሱቅ” እያለ ታሪክ ያዛባ ይሆናል፤ ይሄ የማይረባ ! ታሰርኩ፡፡ እናም ደግ ፖሊስ ገጥሞኝ ተፈታሁ፤ “ሂሉ ጋ እንዳትደርስም ብባልም ከዛ በኋላ እሷም ራሷ እንደጠፋች ሰማሁ፡፡ ስልክ እንኳን አልነበራትም ሂሉ፡፡ ከዛ ሰፈር ቤት የቀየርኩበት ምክንያት ያንን የመቃብር ቦታ የመሰለ ሱቅ ላለማየት ነበር፡፡
አንድ ምሽት ከስድስት ወር ይሁን ሰባት ወር በኋላ ስልኬ ሲጮህ አነሳሁት፡፡
“እንተ!"
ዝም.. ደንግጬ ነበር፡፡
“እብርሽ !"
ሄሉ !”
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…ተኝተህ ነው ? እንቅልፋም !" ልክ ትላንት የተገናኘን ነበር የሚመስለው
አነጋገሯ፡፡ ልታገኘኝ ቀጠረችኝ፡፡ ነገ ቅዳሚ ነው፤ እንኳን የሂሉ ቀጠሮ ተጨምሮቀት
ሂሉዬ አምሮባታል፤ አወራን፡፡
የዚያን ግዜ ግርማ የሚያስጠላ ማስታወቂያ ለጥፎ እንዳትገነጥይ አለኝ፤ እኔ ግን በብስጭት ገንጥዬ
ስጥለው በቦብስ ጥርሴን መታኝ፡፡ ሰማይ ምድሩ ነበር የዞረብኝ፡፡ ሴት በቦክስ ይመታል…ያውም እኔን ግልምጫ የሚበቃኝ ሂሂሂሂ" አለች፡፡ በጣቷ ነጭ ጥርሶቿ መሐል በግራ በኩል የተተካች
ሰው ሰራሽ ጥርስ እያሳየችኝ፡፡ አነጋገሯ ልብ ይሰብር ነበር፤ አጋዥ የሌለው አቅመቢስ ሰው
ዓይነት። በቃ ስካርፍ አድርጌ ያየኸኝ ቀን ማታ በሚኒባስ ተሳፍሬ ወደ ሐረር…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
ትንሽ እንደ መተከዝ አለች፡፡
አባቴ ሲሞት ሐረርም የሞተች መስሎኝ ነበር፡፡ ጓዋደኞቼ፣ የአባቴ ጓደኞች፣ ጎረቤቱ እንደ አዲስ ልቅሶ ተቀምጦ የአባቴን ሞት አዲስ አደረገው፡፡ አይዞሽ! አለኝ፡፡ ሰው ሁሉ የአባቴን ሞት ያፅናኑ መስሏቸው እኔን ከሞት ቀሰቀሱኝ፡፡ ሐረር ፍቅር ናት ሰው ሰው ይሸታሉ ሰዎቹ እንባዋና የደስታ ፈገግታዋ ተቀላቀለ፡፡ ሰው በሰው ሲረካ እንደዛን ቀን ተመልክቼ አላውቅም፡፡
ሂሉ አቤትትትትት እንዴት ስወድሽ እንደነበር እኮ !" አልኳት።
"አንተ አንድ ጥርስ አለብህ ላንተ የከፈልኩት ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
እየተንጠራራን ነበር ከሕይወት መደርደሪያ ላይ አስከፊ ትላንታችንን የምናጥብበት ሳሙና
ልናወርድ !
ሂሉ ባልሽን በሚዛን ፈነከትኩት እኮ…" አልኳት፡፡ አነጋገሬ “ተበቀልኩልሽ” ይሁን፣ አልያም
ጀግና ነኝ” ማለት ለራሴም አልገባኝ !
"ሃሃሃሃሃሃሃ ሰማሁ እኮ… አቦ ጌታ ይባርከህ! ሃሃሃሃሃሃ ባለጌ ነህ ግን.…ገና ሰማኒያችን
አልተቀደድም እኮ ! አሁን የመጣሁት ለዛ ነው...”
እየተንጠራራን ነበር፡፡ ከአዲስ አበባ ሐረር፣ ከሐረር አዲስ አበባ መደርደሪያው ቢርቅም ያቆምንበት የማፈላለግ ኩርሲ እንደምንም እያደራረሰን፡፡ ሂሉዪ አዲስ ኣበባ ዘመድ የላትም፡፡ እኔም ሐረር የማውቀው ሰው የለም፡፡ ግን እኔንም ሐረር ፣ ሂሉንም አዲስ አበባ ደጋግሞ ያስረገጠን ጉዳይ ምንድን ነው ? “ከምር ግን ምንድን ነው ? የሚሉ ጠያቂዎች ቢከሰቱ መልሳችን አንድ ነው፡፡
አቦ አትነዝንዙና !"
✨አለቀ✨
👍52
#አለሁላት…!
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እናቴ ሁልጊዜ ሁለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ ትለዋለች፣
“አብርሽዬ የሚያገባትን ሴት ሳታሳየኝ እንዳትገለኝ፡፡
አገባሁ !
እናቴ እለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ አለችው፣
“ምነው ይሄንንስ ከሚያሳየኝ በገደለኝ
ሀና ምንተስኖት ትባላለች የምኮራባት ሚስቴ፡፡ እወዳታለሁ፣ አፈቅራታለሁ፡፡ ክፉ ነገር በሰፈሯ
እንዲያልፍ አልፈልግም፡፡ ሀኒዬ የእኔ ጥሩ ሱስ፣ ካላየኋት ያዛጋኛል' ስል ሰዎች አያምኑኝም፤ ሀኒ
የእኔ ልብ፣ የጠላችው ጠላቴ ነው:: ይሄ አባማ የሚባል ሰውዬ በቴሌቪዥን ያደረገው ንግግር
አስጠላኝ ብትለኝ፣ ሲ አይ ኤን ሳልፈራ፣ ኤፍ.ቢ.አይን ከቁብም ሳልቆጥረው ኦሳማ ላይ የግድያ
ሙከራ ባደርግ ደስታዬ ነው:: እንቅ አድርጌ አይኑን አፍጥጦ፣ “ኧረ አብርሽ በእናትህ የዛሬን
ማረኝ..ሁለተኛ በየትኛውም ሚዲያ ከመቅረቤ በፊት ንግግሬን ለሀና ምንተስኖት ኣሳውቃታለሁ..
ካልፈቀደችልኝ ኣላደርጎውም” ቢለኝ አልምረውም፡፡ እማምላክን አልምረውም !!
ሀናዬ የነብሴ ፍራሽ…ላያት ድሎቴ ናት። ሀና ካዘዘችኝ…አቤት ፍጥነቴ ገና ልትናገር ስትጀምር እኔ ሮጫለሁ፡፡ አልጋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዥን እያየች እኔ ቆንጆ ቡና እያፈላሁላት…የሆነ ነገር ብትፈልግል ልትናገር ስትጀምረው ነገሩን አምጥቼዋለሁ ፡፡ ለምን ትጨርሰዋለች.…ቃሏ ፍቅር
ነው..ፊደሎቾ እንደ ረሀብ ቀን እህል ያሳሱኛል፡፡
“አብርሽ " ስትለኝ በቦታህ!' እንዳሉት ሯጭ እዘጋጃለሁ፡፡ ወደ መሻቷ ተፈትልኮ በምድር
ላይ ያሉ ወንዶች ሁሉ የሚሰቶቻቸውን ፍላጎት ካሟሉበት ሰዓት የተሻለውን ለማስመዝገብ፡፡
"ድ." ብላ ስትጀምር ፈትለክ ብዬ ድስት…ድራፍት…ድንች ድልህ...ድፍድፍ (ከእማማ ፈጠኑ ቤት ድመት...ድንጋይ..ድራማ (ሲዲ) ይዤላት እያለከለኩ ከተፍ ስል፣ "ውይ አብርሽዬ…በቲቪ ድብ አይቼ ድቡን እየው ልልህ ነበር እኮ" ትለኛለች በፍቅር ዐይን እያየችኝ...!! አይከፋኝም ለምን እከፋለሁ፡፡ እንደገና ድብ ባየችና “ድ ብላ ስትጀምር፣ አሁን ባመጣኋቸው ነገሮች ላይ
ድብ ጨምሬ ባመጣሁላት..የእኔ ሀኒ መክሊት ብያታለሁ፡፡ እሷ ናት ቀኝም ግራም ጎኔ፡፡
ሀኒዬን እናቴ አትወዳትም፡፡ “አንዳች አስነክታው ነው ልጄን እቺ የሰው ጉድ” ትላታለች፡፡
አባቴ ገና ሲያያት የእናቱ፣ የአባቱ፣ የሁለት እህቶቹ ገዳይ ነው የምትመስለው አቤት ሲጠላት፡፡ በወሬ ወሬ “መንገድ ላይ አብረሃም እና... ሲሉት፣ "በቃ " ብሎ ይጮሀል።አብርሃም ካላችሁ አይበቃም….እናን ምን አመጣው?” ይላል፡፡ ያውቃል ማንም ጋር እንደማልታይ፤
ሀኒ ጋር ነኝ ቤት ውስጥ የምትበላውን እየሰራሁላት፡፡ ሀኒ ጋር ነኝ መንገድ ላይ ቦርሳዋን ይዤላት፤….ዣንጥላዋን ይዤላት ዕቃ ከገዛን አስቤዛም ቢሆን እኔ ይዣላት ሀኒ ጋር ነኝ የትም!!
ሀኒን እህቴ አትወዳትም፡፡ ከዘመናዊ ጓደኞቿ ጋር ሆና ከሩቅ ካየችኝ በሬ እንዳሯሯጠው ሰው መንገድ አሳብራ የጓደኞቿን እጅ እየጎተተች ትሸሻለች፡፡ “ወንድሜ በሬ አገባ” እያለች ነው የምታወራው አሉ!
ወንድሜ ሀናን አይወዳትም፡፡
"ለስንት ስንጠብቅህ እዚሂች አዚፋ ጋር ትወዘፋለህ” ይለኛል፡
&አዚፋ' ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ግዴለም ሀኒዬ 'አዚፋ ከሆነች፣ አዚፉ ይባረክ ! ስድብ ሰውን ካረከሰው፡ ሰው ስድቡን ስለምን አያከብረውም? ሀኒዬ አዚፉን አከበረች… እወዳታለሁ፡፡
ሀኒ ቆንጆ አይደለችም፡፡ የኔ ቆንጆ፣ ቆንጆ አይደለችም፡፡ "ኪንኪ ፀጉሯ ጠዋት ስትነሳ ያስፈራል”
ይላሉ፣ አዎ እውነት ነው፡፡ “አፍንጫዋ በአይኗና ቀላይኛው ከንፈሯ መካከል ያለ ሁለት የሽንቁር ነጥብ ነው እያሉ ያሟታል…እውነት ነው !!
ከንፈሯ ወጣ ወጣ ባሉ ጥርሶቿ (ገጣጣ ነው እነሱ የሚሉት) ከርስቱ ተገፍቷል፡፡ በዛ ላይ
ብትስቅ ዞሮ ማጅራቷ ላይ ይዘያየራል ይላሉ፡፡ አዎ እውነት ነው !!
የጣቶቿ መዶልዶም ከዘጠኝ ዓመቷ እስከ አስራ ዘጠኝ ዓመቷ 10000000000000000000
ኩንታል ገብስ ሳታቋርጥ የወቀጠች ያስመስላታል" ቢሉም (ተጋነነ እንጂ) እውነት ነው !!
“እግሯ ከየትኛውም ጫማ እንዲጣላ ተደርጎ ነው የተፈጠረው” ያሉትም አልዋሹም፡፡
lዚህ ሁሉ መናቅ፣ በዚህ ሁሉ መገፋት ተገፍታ እኔ የምባል ጥግ ላይ ደረሰች የሀኒ ዓለም
መጨረሻ፡፡የት ትሂድላቸው? አለሁላት ወንድሟ ነኝ:: ፍቅረኛዋ ነኝ፡፡ባሏም ነኝ!! አላፍርባትም፡፡
ኮራባታለሁ !! ሀኒዬ የኔ ናት:: ማነው እኔን አልፎ የሚዘልፉት ወንድ ?' የኤሌክትሪክ አጥሯ
ጠባቂ ውሻዋ ነኝ፡፡ ከእግሯ ስር የማልጠፋ::ባለቤቱ ያላከበረው አሞሌ፡ ወላ መልኩ ወላ
ዘመናዊነቱ አያስከብረውም፡፡ አንዱ የወረወራቸው አይደሉ ሌላኛው መኪና ላይ የሚኮፈሱት!
የተናቁ አሞሌዎች !! ሀኒዬን አከብራታለሁ !! እግዜር ያውቃል ልቤን !!
“ጥርስሽ አያምርም ቢሏት ከሳቅ ተጣላችላቸው፡፡ ሰው ፊት አትስቅም ሀኒ፡፡ የመጻፍ መብታችን፣የመሰለፍ መብታችን ተነካ የሚሉ የአገሬ ልጆች፣ የህኒዩን የመሳቅ መብት በአደባባይ ነጠነቁ፡፡እስካሁን ሻይ ቡና ለማላት ካፍቴሪያ መግባት ያስፈራታል፡፡ ራሷ ቤት ውስጥ ስትቀመጥ እንኳን እግሮቿን ሶፋ ስር ልትደብቅ ይከጅላታል፡፡ በመንገድ ዳር ዘለፋ መሳቀቅን ሸልመዋታል፡፡ ሰው ለሰላምታ ስትጨብጥ ትሳቀቃለች፡፡ የመዳፏን ሻካራነት በየጭብጡ የሚጮኸ አዋጅ አድርገው
ልቧ ውስጥ ተክለውባት፡፡
ሆኒዩን ቆንጆ ካልሆንሽ ሰው ከመሆን መንበር ተንኮታኩተሻል” ብለዋታልና ቆንጆዎች አምላክ
ይመስሏታል፡፡ የሴት ልጅ የክብር ጥጉ በየሆቴሉ ወንበር ተጎትቶላት መቀመጧ ነውን ? በአደባባይ
መታቀፍስ የፍቅር ኦሜጋ ሆኖ የታወጀው መቼ ነው ? እየተውረገረጉ የወንድ ጭብጨባ
ያደነቆራቸው ሀኒዬን ቃል ሳያወጡ በድርጊት ቀበሯት፡፡
አነሆ ለአንዲት ደሀ.ለአንዲት መልከ ጥፉ ደሀ ተልኬ የምታስተናግድበት ተራ ሻይ ቤት ተከሰትኩ፡ ያውም 'አዩኝ' ብሎ የሚቆሽሽ ነጭ ሸሚዝ ባማረ ጂንስ ሱሪ ለብሼ፣ ጥቁር መነፅሬን ሰክቼ እየተቆነንኩ በረንዳው ላይ ካሉት ወንበሮች በአንዱ ላይ ሰፈርኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ!” አለች ሀኒዬ እየተሸቆጠቆጠች፡፡ ሳያት ላማትብ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ እግዜር ሰውን
የት ድረስ ውብ እንደሚያደርግ አውቃለሁ፡፡ የት ድረስ መልከ ጥፉ አድርጎ እንደሚፈጥር እነሆ
የእጁን ውጤት ፊቴ አቁሞ አሳየኝ፡፡ “አቤት ችሎታው ምን ይሳነዋል!” አልኩ ::
ስራዬ በዛው ግድም ነበርና ደጋግሜ ሳያት ከቀን ወደቀን እየባሰ የሚሄድ ይሄ ጎደለው የማይባል ፍፁም የሆነ አስቀያሚነት እንዳሸከማት እየተገረምኩ ታዘብኩ፡፡ ግና የገረመኝ፣ “አቤት ስታስጠላ
እያልኩ ላያት መፈለጌ ደንበኛ ሆንኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ?"
"ቡና"
"ምን ላምጣልህ?"
“ቡና”
“ሰላም! ምን ላምጣልህ?”
“ቡና”
“ቡና ነው ዛሬም” (ፈገግ ለማለት እየሞከረች)
"አዎ" (በፈገግታ)
ከዛ ሳላዛት ቡና አመጣችልኝ…ቡና..ቡና….ቡና.…ሰላምታ ሀና ነው ስሟ፣ አንድ ቀን ጠየቅኳት…
ነገረችኝ፡፡ ስራ ከሌላት አጠገቤ ትመጣለች እናወራለን…እንዴት ደስ እንደምትል፡፡ ትልልቅ ጡቶቿን አልፎ ልቧ ይታያል ንጹህ ነው !
አንድ ቀን ከጎኔ የተቀመጡ ተስተናጋጆች "የሰው ጅብ” ሲሏት ጆሮዬ ጥልቅ አለ ያዘዝነው ዘገየብን ብለው !! በመሰደቧ ሳይሆን እኔ ፊት በመሰደቧ
በመሰደቧ የቅስሟ መስተዋት
ክፍት አፍ በወረወረው የዘለፉ ጠጠር ሲንኮታኮት ፊቷ ላይ እንዴት አንጀት የሚበላ መሳቀቅ አየሁ፡፡ ተሳዳቢዎቹ ጋር
የነበረች አንዲት ሴትም ላንቃዋ እስኪላቀቅ ሳቀች፡፡ አዘንኩ፡፡ ለምን አዘንኩ እኔንጃ !!
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እናቴ ሁልጊዜ ሁለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ ትለዋለች፣
“አብርሽዬ የሚያገባትን ሴት ሳታሳየኝ እንዳትገለኝ፡፡
አገባሁ !
እናቴ እለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ አለችው፣
“ምነው ይሄንንስ ከሚያሳየኝ በገደለኝ
ሀና ምንተስኖት ትባላለች የምኮራባት ሚስቴ፡፡ እወዳታለሁ፣ አፈቅራታለሁ፡፡ ክፉ ነገር በሰፈሯ
እንዲያልፍ አልፈልግም፡፡ ሀኒዬ የእኔ ጥሩ ሱስ፣ ካላየኋት ያዛጋኛል' ስል ሰዎች አያምኑኝም፤ ሀኒ
የእኔ ልብ፣ የጠላችው ጠላቴ ነው:: ይሄ አባማ የሚባል ሰውዬ በቴሌቪዥን ያደረገው ንግግር
አስጠላኝ ብትለኝ፣ ሲ አይ ኤን ሳልፈራ፣ ኤፍ.ቢ.አይን ከቁብም ሳልቆጥረው ኦሳማ ላይ የግድያ
ሙከራ ባደርግ ደስታዬ ነው:: እንቅ አድርጌ አይኑን አፍጥጦ፣ “ኧረ አብርሽ በእናትህ የዛሬን
ማረኝ..ሁለተኛ በየትኛውም ሚዲያ ከመቅረቤ በፊት ንግግሬን ለሀና ምንተስኖት ኣሳውቃታለሁ..
ካልፈቀደችልኝ ኣላደርጎውም” ቢለኝ አልምረውም፡፡ እማምላክን አልምረውም !!
ሀናዬ የነብሴ ፍራሽ…ላያት ድሎቴ ናት። ሀና ካዘዘችኝ…አቤት ፍጥነቴ ገና ልትናገር ስትጀምር እኔ ሮጫለሁ፡፡ አልጋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዥን እያየች እኔ ቆንጆ ቡና እያፈላሁላት…የሆነ ነገር ብትፈልግል ልትናገር ስትጀምረው ነገሩን አምጥቼዋለሁ ፡፡ ለምን ትጨርሰዋለች.…ቃሏ ፍቅር
ነው..ፊደሎቾ እንደ ረሀብ ቀን እህል ያሳሱኛል፡፡
“አብርሽ " ስትለኝ በቦታህ!' እንዳሉት ሯጭ እዘጋጃለሁ፡፡ ወደ መሻቷ ተፈትልኮ በምድር
ላይ ያሉ ወንዶች ሁሉ የሚሰቶቻቸውን ፍላጎት ካሟሉበት ሰዓት የተሻለውን ለማስመዝገብ፡፡
"ድ." ብላ ስትጀምር ፈትለክ ብዬ ድስት…ድራፍት…ድንች ድልህ...ድፍድፍ (ከእማማ ፈጠኑ ቤት ድመት...ድንጋይ..ድራማ (ሲዲ) ይዤላት እያለከለኩ ከተፍ ስል፣ "ውይ አብርሽዬ…በቲቪ ድብ አይቼ ድቡን እየው ልልህ ነበር እኮ" ትለኛለች በፍቅር ዐይን እያየችኝ...!! አይከፋኝም ለምን እከፋለሁ፡፡ እንደገና ድብ ባየችና “ድ ብላ ስትጀምር፣ አሁን ባመጣኋቸው ነገሮች ላይ
ድብ ጨምሬ ባመጣሁላት..የእኔ ሀኒ መክሊት ብያታለሁ፡፡ እሷ ናት ቀኝም ግራም ጎኔ፡፡
ሀኒዬን እናቴ አትወዳትም፡፡ “አንዳች አስነክታው ነው ልጄን እቺ የሰው ጉድ” ትላታለች፡፡
አባቴ ገና ሲያያት የእናቱ፣ የአባቱ፣ የሁለት እህቶቹ ገዳይ ነው የምትመስለው አቤት ሲጠላት፡፡ በወሬ ወሬ “መንገድ ላይ አብረሃም እና... ሲሉት፣ "በቃ " ብሎ ይጮሀል።አብርሃም ካላችሁ አይበቃም….እናን ምን አመጣው?” ይላል፡፡ ያውቃል ማንም ጋር እንደማልታይ፤
ሀኒ ጋር ነኝ ቤት ውስጥ የምትበላውን እየሰራሁላት፡፡ ሀኒ ጋር ነኝ መንገድ ላይ ቦርሳዋን ይዤላት፤….ዣንጥላዋን ይዤላት ዕቃ ከገዛን አስቤዛም ቢሆን እኔ ይዣላት ሀኒ ጋር ነኝ የትም!!
ሀኒን እህቴ አትወዳትም፡፡ ከዘመናዊ ጓደኞቿ ጋር ሆና ከሩቅ ካየችኝ በሬ እንዳሯሯጠው ሰው መንገድ አሳብራ የጓደኞቿን እጅ እየጎተተች ትሸሻለች፡፡ “ወንድሜ በሬ አገባ” እያለች ነው የምታወራው አሉ!
ወንድሜ ሀናን አይወዳትም፡፡
"ለስንት ስንጠብቅህ እዚሂች አዚፋ ጋር ትወዘፋለህ” ይለኛል፡
&አዚፋ' ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ግዴለም ሀኒዬ 'አዚፋ ከሆነች፣ አዚፉ ይባረክ ! ስድብ ሰውን ካረከሰው፡ ሰው ስድቡን ስለምን አያከብረውም? ሀኒዬ አዚፉን አከበረች… እወዳታለሁ፡፡
ሀኒ ቆንጆ አይደለችም፡፡ የኔ ቆንጆ፣ ቆንጆ አይደለችም፡፡ "ኪንኪ ፀጉሯ ጠዋት ስትነሳ ያስፈራል”
ይላሉ፣ አዎ እውነት ነው፡፡ “አፍንጫዋ በአይኗና ቀላይኛው ከንፈሯ መካከል ያለ ሁለት የሽንቁር ነጥብ ነው እያሉ ያሟታል…እውነት ነው !!
ከንፈሯ ወጣ ወጣ ባሉ ጥርሶቿ (ገጣጣ ነው እነሱ የሚሉት) ከርስቱ ተገፍቷል፡፡ በዛ ላይ
ብትስቅ ዞሮ ማጅራቷ ላይ ይዘያየራል ይላሉ፡፡ አዎ እውነት ነው !!
የጣቶቿ መዶልዶም ከዘጠኝ ዓመቷ እስከ አስራ ዘጠኝ ዓመቷ 10000000000000000000
ኩንታል ገብስ ሳታቋርጥ የወቀጠች ያስመስላታል" ቢሉም (ተጋነነ እንጂ) እውነት ነው !!
“እግሯ ከየትኛውም ጫማ እንዲጣላ ተደርጎ ነው የተፈጠረው” ያሉትም አልዋሹም፡፡
lዚህ ሁሉ መናቅ፣ በዚህ ሁሉ መገፋት ተገፍታ እኔ የምባል ጥግ ላይ ደረሰች የሀኒ ዓለም
መጨረሻ፡፡የት ትሂድላቸው? አለሁላት ወንድሟ ነኝ:: ፍቅረኛዋ ነኝ፡፡ባሏም ነኝ!! አላፍርባትም፡፡
ኮራባታለሁ !! ሀኒዬ የኔ ናት:: ማነው እኔን አልፎ የሚዘልፉት ወንድ ?' የኤሌክትሪክ አጥሯ
ጠባቂ ውሻዋ ነኝ፡፡ ከእግሯ ስር የማልጠፋ::ባለቤቱ ያላከበረው አሞሌ፡ ወላ መልኩ ወላ
ዘመናዊነቱ አያስከብረውም፡፡ አንዱ የወረወራቸው አይደሉ ሌላኛው መኪና ላይ የሚኮፈሱት!
የተናቁ አሞሌዎች !! ሀኒዬን አከብራታለሁ !! እግዜር ያውቃል ልቤን !!
“ጥርስሽ አያምርም ቢሏት ከሳቅ ተጣላችላቸው፡፡ ሰው ፊት አትስቅም ሀኒ፡፡ የመጻፍ መብታችን፣የመሰለፍ መብታችን ተነካ የሚሉ የአገሬ ልጆች፣ የህኒዩን የመሳቅ መብት በአደባባይ ነጠነቁ፡፡እስካሁን ሻይ ቡና ለማላት ካፍቴሪያ መግባት ያስፈራታል፡፡ ራሷ ቤት ውስጥ ስትቀመጥ እንኳን እግሮቿን ሶፋ ስር ልትደብቅ ይከጅላታል፡፡ በመንገድ ዳር ዘለፋ መሳቀቅን ሸልመዋታል፡፡ ሰው ለሰላምታ ስትጨብጥ ትሳቀቃለች፡፡ የመዳፏን ሻካራነት በየጭብጡ የሚጮኸ አዋጅ አድርገው
ልቧ ውስጥ ተክለውባት፡፡
ሆኒዩን ቆንጆ ካልሆንሽ ሰው ከመሆን መንበር ተንኮታኩተሻል” ብለዋታልና ቆንጆዎች አምላክ
ይመስሏታል፡፡ የሴት ልጅ የክብር ጥጉ በየሆቴሉ ወንበር ተጎትቶላት መቀመጧ ነውን ? በአደባባይ
መታቀፍስ የፍቅር ኦሜጋ ሆኖ የታወጀው መቼ ነው ? እየተውረገረጉ የወንድ ጭብጨባ
ያደነቆራቸው ሀኒዬን ቃል ሳያወጡ በድርጊት ቀበሯት፡፡
አነሆ ለአንዲት ደሀ.ለአንዲት መልከ ጥፉ ደሀ ተልኬ የምታስተናግድበት ተራ ሻይ ቤት ተከሰትኩ፡ ያውም 'አዩኝ' ብሎ የሚቆሽሽ ነጭ ሸሚዝ ባማረ ጂንስ ሱሪ ለብሼ፣ ጥቁር መነፅሬን ሰክቼ እየተቆነንኩ በረንዳው ላይ ካሉት ወንበሮች በአንዱ ላይ ሰፈርኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ!” አለች ሀኒዬ እየተሸቆጠቆጠች፡፡ ሳያት ላማትብ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ እግዜር ሰውን
የት ድረስ ውብ እንደሚያደርግ አውቃለሁ፡፡ የት ድረስ መልከ ጥፉ አድርጎ እንደሚፈጥር እነሆ
የእጁን ውጤት ፊቴ አቁሞ አሳየኝ፡፡ “አቤት ችሎታው ምን ይሳነዋል!” አልኩ ::
ስራዬ በዛው ግድም ነበርና ደጋግሜ ሳያት ከቀን ወደቀን እየባሰ የሚሄድ ይሄ ጎደለው የማይባል ፍፁም የሆነ አስቀያሚነት እንዳሸከማት እየተገረምኩ ታዘብኩ፡፡ ግና የገረመኝ፣ “አቤት ስታስጠላ
እያልኩ ላያት መፈለጌ ደንበኛ ሆንኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ?"
"ቡና"
"ምን ላምጣልህ?"
“ቡና”
“ሰላም! ምን ላምጣልህ?”
“ቡና”
“ቡና ነው ዛሬም” (ፈገግ ለማለት እየሞከረች)
"አዎ" (በፈገግታ)
ከዛ ሳላዛት ቡና አመጣችልኝ…ቡና..ቡና….ቡና.…ሰላምታ ሀና ነው ስሟ፣ አንድ ቀን ጠየቅኳት…
ነገረችኝ፡፡ ስራ ከሌላት አጠገቤ ትመጣለች እናወራለን…እንዴት ደስ እንደምትል፡፡ ትልልቅ ጡቶቿን አልፎ ልቧ ይታያል ንጹህ ነው !
አንድ ቀን ከጎኔ የተቀመጡ ተስተናጋጆች "የሰው ጅብ” ሲሏት ጆሮዬ ጥልቅ አለ ያዘዝነው ዘገየብን ብለው !! በመሰደቧ ሳይሆን እኔ ፊት በመሰደቧ
በመሰደቧ የቅስሟ መስተዋት
ክፍት አፍ በወረወረው የዘለፉ ጠጠር ሲንኮታኮት ፊቷ ላይ እንዴት አንጀት የሚበላ መሳቀቅ አየሁ፡፡ ተሳዳቢዎቹ ጋር
የነበረች አንዲት ሴትም ላንቃዋ እስኪላቀቅ ሳቀች፡፡ አዘንኩ፡፡ ለምን አዘንኩ እኔንጃ !!
👍30😁4