አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ይህ አድራሻውና ከየት እንደመጣ የማይታወቀውን እንግዳ ለኮዚት
ከፈጣሪ የተላከ በመሆኑ እጅግ ስታፈቅረው ለሚስስ ቴናድዬ ግን በዓለም ላይ ካለ ፍጡር ሁሉ የሚጠላ ነው:: ሴትዮዋ ስሜትዋን አምቃ ከመያዝ በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራትም:: ጥላቻዋ ግን ለመሸከምና ለመዋጥ
ከምትችለው በላይ ነበር፡፡ ልጆችዋ እንዲተኙ አዘዘቻቸው:: ኮዜትም እንድትተኛ የእንግዳውን ፈቃድ ጠየቀች::
«ዛሬ በጣም ስትደክም ስለዋለች ብትተኛ ይሻላል» አለች በእናትነት
አንደበት፡፡ ኮዜት ካተሪንን ታቅፋ ወደ መኝታዋ ሄደች::
ከዚያ በኋላ ሰዓቱ ነጉደ ! እኩለ ሌሊት አለፈ፡፡ ጠጪዎች ወደ
የቤታቸው ለመሄድ ከሆቴሉ ወጡ፡፡ በሩ ተዘጋ። ቤቱ እርጭ አለ፡፡
የምድጃው እሳት ጠፋ፡፡ እንግዳው ግን ከመቀመጫው አልተነሳም:: ኩርምት ብሎ እንደተቀመጠ ቀረ፡፡ አገጩን የሚያስደግፍበት ክርኑን እየቆየ ፡ እየቆየ ይቀያይራል፡፡ በተለይ ኮዜት ከሄደች ጀምሮ እንድ ቃል ከአፉ አልወጣም::
ሚስተር ቴናድዩ በኃይል ከሳለ በኋላ አክታውን ተፋ፡፡ መሐረሱን
አውጥቶ ንፍጡን ተናፈጠ፡፡ ሊነቃነቅ የተቀመጠበት ወንበር ተንቋቋ፡፡
እንግዳው ሰው ግን ድምፅ ሰማሁ ብሉ አንገቱን ኣላቀናም ወይም ፊቱን አላዞረም፡፡ «ይህ ሰው እንደተቀመጠ እንቅልፍ ይዞት ሄደ እንዴ!» ሲል ሚስተር ቴናድዬ አሰበ፡፡ ዞር ብሉ ሲያየው እንቅልፍ አልወሰደውም::
ጭልጥ አድርጎ ከወሰደው አሳብ የሚመልሰው ነገር አልተገኘም:: በመጨረሻ ሚስተር ቴናድዬ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ ወደ እንግዳው አመራ፡፡
«ጌታው አልደከመህም ! አትተኛም?» ሲል ጠየቀው::
«አቤት! ልክ ነህ! ብተኛ ይሻላል፤ የምተኛበት ሥፍራ ወዴት
ነው?» ሲል ጠየቀ፡፡
«እኔ አሳይሃለሁ» አለ ሚስተር ቴናድዬ::
እንግዳው እቃውን ይዞ ተከተለው:: ወደ አንድ ክፍል ወሰደው::
ጥሩ ኣልጋ ወዳለበትና እጅግ ወደ አማረ ክፍል ነበር የወሰደው::

«ምንድነው ይኼ?» ሲል እንግዳው ጠየቀ፡፡

«ታላላቅ ሰዎች ሲመጡ የሚያርፉበትና ካሉን ክፍሎች ሁሉ የላቀ ክፍል ነው:: እኔና ባለቤቴ የምናድርበት ክፍል ብቻ ነው ይህን የሚስተካክል፡፡
ክፍሉ በዓመት ሦስት ወይም አራት ሌሊት ቢከራይ ነው» አለ ሚስተር ቴናድዬ::

«ከዚህ ያነሰ ክፍል ቀርቶ በረት እንኳን ብተኛ ደንታ አልነበረኝም?»
ሲል እንግዳው በድፍረት ተናገረ፡፡

ሚስተር ቴናድዬ ባገኘው መልስ ተገርሞ ምንም ነገር እንዳልሰማ
ሰው ዝም አለ፡፡ ሁለት ሻማዎችን አበራ:: ክፍሉ ውስጥ የእሳት ማንደጃ ስለነበር ክብሪት ለኩሶ ከምድጃው ላይ የነበረውን እንጨት አያያዝለት::

እንግዳው ይህ ሁሉ ሲሆን ፊቱን ወደ መስኮት አዞሮ ስለነበር ምንም
አላየም: በመጨረሻ ፊቱን ቢያዞር ሰውዬው ሄዷል:: «ደህና እደር ማለቱ እንኳን መዳፈር ይሆንብኛል ብሎ አስቦ ነው ዝም ብለ ወጥቶ የሄደው

ጠዋት ግን በተቻለ እንግዳውን ለመቦጥቦጥ አቅዷል፡፡....

💫ይቀጥላል💫
👍222😁2
አትሮኖስ pinned «#ምንዱባን ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ ፡ ፡ #ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ ...የሦስቱ፡ ልጆች ዕድሜ ቢደመር ሃያ አራት ዓመት አይሞላም:: እነዚህ ልጆች የኅብረተሰቡን ገጽታ የሚጠቁሙ ሲሆኑ በአንድ በኩል ቅናትን በሌላ በኩል ደግሞ ሐሜትንና ንቀትን ያመለክትል ገባ ወጣ እያለች ከወዲያ ወዲህ ትል የነበረችው ሚስስ ቴናድዬ ድንገት ዞር ስትል ኮዜት ከሥራዋ ተዘግናታ በሁለቱ ልጆች ጨዋታ መማረክዋን ተገነዘበች፡፡…»
እንኳን ለሆሳህና በአል በሰላም አደረሳችሁ

መልካም የሆሳህና በዓት እና የህማማት ሳምንት
👍10
#አንቺዬ... ...
ይዤሽ በወጣሁኝ ፣ በዚህ ድቅድቅ ምሽት
"ባሕር ያሞራል”፣ አትበይ ከኔ ልብ ሽሽት።
የባሕር ዳር ውበት ፣ በስሜትሽ ዐይተሽ
ጨረር አታድንቂ ፤ ጨረቃን ረስተሽ፤
ዕዪው... ልብ ብለሽ!
ባሕር ለጨረቃ ፣ ደረቱን ገልብጦ፤
የጨረቃ ጨረር፣ በባሕር ተውጦ፤
ሲግባቡ እያየሽ፣
አንቺ ግን ሔዋኔ
ብርሃን ፍላጋ ፣ጨለማ ላይ ቆየሽ።
ባሕር ምን ቢሰፋ ፣ጨረቃ ሞላችው
ጨረቃስ ብትሞቅ ፣ አላደረቀችው።
የመዋዋስ ፍቅር፣ከልባቸው ጠፍቶ
ሲሞላሉ ዐየሽ ፣ኀይሏቸው ሰፍቶ።
ተቃርኖ ተመልከች!
ጨረቃ ወላድ ናት፣ እናት ብርሃን፤
ባሕር ጨለማ ነው፤ የብልጭታ መሀን።
ተቃርኖ ተመልከች!
ባሕር ሕይወት አለው፤ ከሰው የረቀቀ፤
ጨረቃ ግን በድን ፣ ከሕይወት የራቀ።
የዋጡትን ዐየሽ...
የሌላትን ሕይወት በብርሃን ቀዘፋ
ጨረቃን ተመልከች ፣ ከባሕሩ ገዝፋ።
የዋጡትን ዐየሽ...
ሕይወትን ቢቀዝፍ ፤ ጨለማን ተዋርሶ፣
ዕድሜ ለጨረቃ...
ባሕሩን ተመልከች ፣ እስከሰማይ ደርሶ፡፡
ያዋጡትን ዐየሽ
ሕይወት ከጨለማ ፣ ጨለማ ከሕይወት፣
በድን ከብርሃን ፣ ብርሃን ከበደን
ሲሰጣጡ ጊዜ
ትንሿ ጨረቃ ፣ ባሕር ስትከድን።
ይዤሽ የወጣሁት ፣ በዚህ ድቅድቅ ሞሽት
ባሕር ያምራል አትበይ ፤ከኔ ልብ ሽሽት።
ጨረቃና ባሕር ፣ሲግባቡ ያስቃል፤
ያአዳሜ ና ሔዋን ፣ፍቅሩ በቃል ያልቃል።
ያዋጡትን ዐየሽ!


🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍166
#ዝግመተ_ለውጥ


#በአሌክስ_አብርሃም


...እንዲሁ ስለመምሬ እና ለትዳር ስላሰቡልኝ ልጅ እያሰብኩ የያዝኩትን ጋዜጣ መቃኘት ጀመርኩ፡፡.

በደማቅ ጥቁር ቀለም፣ “በማኅበር ተደራጅተው ጫት የሚያመርቱ አርሶ አደሮች ኑሯችን
ተለውጧል አሉ...” ይላል፡፡

ወረድ ብሎ፣ “አንዳንድ የማኅበሩ አባላት “ጫት በመሸጥ አይሱዙ መኪና ገዝተናል፣ ልጆቻችንንም
ከተማ ልከን እያስተማርን ነው ሲሉ ገልፀዋል” ከጽሑፉ ስር አይሱዙ መኪና ተደግፈው ፎቶ
የተነሱ አርሶ እደር ምስል ይታያል፡፡

ወረድ ብሎ ሌላ አርዕስት፣

አንድ አይሱዙ መኪና ሃያ ሜትር ጥልቀት ያለው ገደል ውስጥ ገብቶ ከላይ ጭኗቸው የነበሩ
ሰባት ሰዎች ሞቱ፡፡ ከሟቾቹ አራቱ ከገጠር ከተማ እየተመላለሱ የሚማሩ ተማሪዎች ሲሆኑ
ፖሊስ የአደጋው መንስዔ ሹፌሩ ጫት እየቃመ ማሽከርከሩ ነው ብሏል !"

ጋዜጣውን እጥፌ ሰፈራችንን ማየት ጀመርኩ፡፡ ቅድስት ቀይ የእራት ልብስ ለብሳ እቃ ታጥባለች፧እያንጎራጎረች፣ “በሰባራ ፎሌ ውሀ አያጠለቅም" አይ ቅድስት ! እንደኛ ሰፈር ሴት የባከነበት መንደር ያለ አይመስለኝም፡፡ ቆንጆ ናት 'ሞዴል' የመሆን ፅኑ ፍላጎት ነበራት፡፡ እንደውም የሰፈር ልጆች ሲፎግሯት፣ “ውበት ውጪያዊና ውስጣዊ ነው' ሲሉ ሰምታ ውስጣዊ ውበቷን ለማየት
እልትራሳውንድ ተነሳች” ይሏታል፡፡ ሰታንጎራጉር እየሰማኋት የድምጿ ማማር ተገረምኩ፤
“ወይ ይህቺ አገር ዘፋኞቿ በየማጀቱ እቃ እያጠቡ እቃ አጣቢዎቿ በየአደባባዩ እንዝፈን እያሉ ያደነቁሩናል" አልኩ ለራሴ፡፡ የቄሳርን ለእግዜር፡ የእግዜርን ለእግዚሃር፡፡

የመንደራችን የአንድ እሁድ ውሎ ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ነው:: ከጧቱ 12፡00 ሰዓት
አልማዝ የምትባለው ጎረቤታችን በሯ ላይ ስለተጣለው ድግምት ታማርራለች፣ ትራገማለች፡
ጠበል ታርከፈክፋለች፡፡ ድግምት በመጣል የሚጠረጠሩ ጎረቤቶቿን ታሸሙራለች፣ “እችኑ ኑሮ
ብለዋት...” እያለች፣ ብዙ ጊዜ የሞተ እይጥ ነው በሯ ላይ ተጥሎ የሚገኘው:

ከ 12፡30 እስከ ጧቱ 2፡00 ሰዓት እማማ ዘብይደሩ ጭንቅሎ የተባለውን የልጅ ልጃቸውን
ይረግማሉ፣ ይሳደባሉ፣ ይውገራሉ፡፡ አንዳንዴ ወገራው ሲበዛ ገላጋዮች ይገባሉ፡፡ “ባጭር ቅር….ይሉትና ሲታመም ሆስፒታል ለሆስፒታል አዝለውት ይዞራሉ፡፡
ከሁለት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት የመንደሩ ልጆች እኔ ቤት ፊት ለፊት ያለች (ሰርቪስ ቤት እንኳን
የማታቆም) ቢጢቃ ሜዳ ላይ ኳስ ይራገጣሉ፡፡ የሚያስነሱት አቧራ ልጆቹን ስለሚሸፍናቸው
እንደ ህልም ነው ብዥ ብለው የሚታዩት፡፡

ከሚጫወቱት ልጆች መሃል ጭንቅሎ (የእማማ ዘብይደሩ የልጅ ልጅ)፤ ሃይለሚካኤል 'አረቡ'
(የእማማ የውብዳር የልጅ ልጅ)፣ ሙስጠፋ (የእማማ ዘሃራ የልጅ ልጅ)፣ ሲቲና ወንዳወንድ ሰለሆነች 'ከቤ' ይሏታል (የነማማ ትርሃስ የልጅ ልጅ ናት)፤ ከላይ ከተዘረዘረው የዘር ሃረግ
እንደሚታየው መንደራችን አንድ እናት' የሚባል ትውልድ ገድፏል፣ አባት የሚባል ሃረግ ዘሏል
ሕፃናቱ ከአያቶቻቸው ጋር ነው ያደጉት፡፡ ያውም አቅም ከሌላቸው ደሃና እቅመ ደካሚ ባልቴት
አያቶቻቸው ጋር! እናቶቻቸው የት ሄዱ? አባቶቻቸውን ምን በላቸው?' ቢባል መልሱ ከሁለት
ጉዳዮች አያልፍም፡፡ እንድም ወልደው ለእናቶቻቸው እየሰጡ አረብ እገር ሄደዋል፡ አልያን
በኤችአይቪ አልቀዋል፡፡ የመንደራችን እውነታ ነው ይሄ !! ደግሞ ሕፃናቱ የተመካከሩ ይመስል በየምክንያቱ ሲጣሱና ሲነታረኩ የሁሉም መሃላ አንድ ዓይነት፣ እናቴ ትሙት !” የሚል ነው፡፡

ልክ ከአራት ሰዓት እስከ አምስት ሰዓት፣ ሁላቱ የመንደራችን እንጀራ ሻጮች ሙሉና ዝናሽ. ዱላ ቀረሽ ስድድብ ይጀምራሉ፡፡ በደንበኛ መቀማማት ነው የሚጣሱት፣

“ለማያውቅሽ ታጠኚ..ደግሞ ሙያ እንዳለው ሰው:: ማየት የተሳነው እንጀራ እየጠፈጠፍሽ.
እኩል ታወሪያለሽ…"

“ኤጅ እባከሽ…እኔ ሙሉ በወፍጮ ቤት ጥራጊ አይደለም ደንበኞቼን የማስተናግደው፣ ጥርት
ባለ ጤፍ ጥር…ት”

“ሂሂሂሂሂ መጣፈጡ ቀርቶ እጄን በሰቀቀኝ አሉ እትዬ አሰለፍ፣ ጥራቱ ቀርቶብሽ ቡሃቃሽን
በወር እንዴ እንኳን ባጠብሽው:: ሰዉን ሁሉ በሆድ ቁርጠት ጨረሽው” ትላለች ዝናሽ። የሙሉ
ደንበኛ ስለሆንኩ በዚህ ኣባባሏ ሆዴ ይጮሃል፣ ..ኡ... ወር ሙሉ የማይታጠብ ቡሃቓ እቺ
ስድድብ ደንበኛን ለማስከዳት ወሳኝ የቃላት ጦርነታቸው ናት፡፡

ልክ አምስት ሰዓት ሲሆን እማማ መጣፈጥና ስንቅነሽ ቡና ይጠራራሉ፡፡ ወደ ስድስት ሰዓት
ጀሚላ የቅንድቧን ኩል ጆሮና ጆሯዋ ጥግ ድረስ ተኩሳ በስልኳ እያወራች ወደላይ ትጣደፋለት፡
ሃቢቢ መጣሁ ወጥቻለሁ” እያለች፡፡ ኣፍንጫ የሚሰነፍጥ ሽቶዋ መንደሩን ያውደዋል፡፡ ጀሚላ ስታልፍ ጥርኝ ያለፈች ነው የሚመስለው:: የታከከችው ነገር ሁሉ ሽቶ ሽቶ፣ መቼም ሃቢቢዩ
የአፍንጫ መሸፈኛ ማስካ ያደረገ ሰው መሆን አለበት፡፡

ይሄን ሁሉ ሳይ ይከፋኛል። ብቸኝነት ይጫጫነኛል፡፡ ከወንዙ ተገንጥሎ ኩሬ ውስጥ እንደተኳታሪ ውሃ እዛው የምሻግት አልያም የተቀመጥኩበት በትነት የማልቅ ነገር መስሎ ነው የሚሰማኝ

ይሄን…የተረገመ እሁድ ወደዛ አልቆ ሥራዩ በገባሁ ! ለነገሩ ከእሁድ ይሻላል ብዬ እንጂ ሥራዬም ሠልችቶኛል፡፡ የባንክ ሠራተኛ ነኝ፡፡ ብዙ ሰዎች የባንክ ሠራተኛ መሆኔን እንደትልቅ እና አስደሳች ሥራ እድርገው ሲያወሩ ይገርመኛል፡፡ ለእኔ የባንክ ሥራ በምድር ላይ ካሉ አስከፊ ሥራዎች
ሁሉ አስከፊው ይመስለኛል፡፡ እንደውም ለሰው ሳይሆን ለሮቦቶች የሚስማማ ሥራ ቢኖር የባንክ ሥራ ነው እያልኩ አስባለሁ፡፡

አንድ አይነት ቅርፅ ያላቸው ብር ዮሚባሉ መርገምቶችን መቁጠር፡፡ አራት ዓመት ሙሉ
ቆጠርኳቸው..ኤጭ ድፍን አገር የሚራኮትለት ብር ለእኔ አንዳች ቆሻሻ ነገር መስሎ ነው
የሚታየኝ፡፡ ብር ይሸታል፡፡ ካላመናችሁ ወደ ኣፍንጫችሁ አስጠጉና ሞክሩት፡፡ እንደ ብር
መጥፎ ሽታ ያለው ነገር ምን አለ ? ለነገሩ የዘንድሮ ብር ላሸትተውም ብትሉ አፍንጫችሁ ላይ
ላይደርሰ ያልቃል ሰላቢ ነገር ነው::

ምስላቸው ብር ኖት ላይ ያሉት ሰዎች ከመኖር ብዛት የቢሮ ባልደረባ መስለውኛል፡፡ ደግሞ
አልወዳቸውም፡፡ ለምሳሌ አንድ ብር ኖት ላይ ምስሉ ያላውን ሰው መንገድ ላይ ባገኘው ገላምምጬው የማልፍ ይመስለኛል፡፡ አስር ብር ላይ ያለችው ሴትማ ስታበሳጨኝ፤
የሆነች ነገረኛ ነገር፡፡ በደንብ አይታችኋታል? ስፌት የምትሰፋ ትመስላለት እንጂ ጆሮዋን አቁማ
ነገር የምትሰማ እኮ ነው የምትመስለው፡፡ ደግሞ ፊቷ ላይ የአሽሙር ፈገግታ አለ፡፡ ከሁሉም
ከሁሉም የሚያበሳጨኝ ነገር ደግሞ ከንፈሯ ! የከንፈሯ ማማር የሰብለን ከንፈር እኮ ነው
የሚመስለው !! ከነስፌቷ እጎኗ ላለው አንበሳ ነበር መስጠት !!

ባንክ ቤት ስትሰሩ ስጋችሁ በሱፍ ተጀቡኖ ወሩ መጨረሻ ላይ የሱፍ ቆሎ መግዣ እንኳን የማይተርፋችሁ መናጢ ደሃ መሆናችሁን ብዙ ሰው አይረዳም፡፡ ቁጥርና ስጋት ባንድ ላይ
የሚኖሩት ባንክ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ብር ስትቆጥሩ በስጋት ነው:: አንዱን የብር ኖት ሌላ የተደራረበ እየመሰላችሁ በፍትጊያ ፍዳውን ታበሱታላችሁ፡፡ በዛ ላይ ሰው ለብር ያለውን ሟችነት፣ ስግብግብነት፣ ደግነትም ጭምር ትታዘባላችሁ፡፡
👍321👎1👏1🎉1
ሃሃሃ የሆነ ነገር ትዝ አለኝ፡፡ አንድ ቀን እንጂ እኔ ወዳለሁበት መስኮት ጠጋ አለችና ትልልቅና
የተራቆቱ ጡቶቿን መስታወቱ ጋር ጨፍልቃቸው በሸንቁሩ ታናግረኝ ጀመረ፡፡ ደረትና ጡቷን የወረራት ብጉር መሰል ነጠብጣብ ያስቅቃል፣ መቶ ሺ ቁጫራጮች የሚርመሰመሱበት ደረት ነው
የሚመስለው፡፡ እንደው አንዳንድ ሴቶች ምን “ማሳየት እና ምን መደበቅ እንዳለባቸው አያውቁም፡፡
እኔ ደግሞ ከኋላዋ ተራ የሚጠብቁ ደንበኞች ወደሷ ሲያፈጡ፣ “እቺ ሴት ታዋቂ ትሆን?” ብዬ አሰብኩ፡፡ ለካስ ወደኔ ስታጎነብስ በጣም አጭር ጉርድ ቍሚሷ ከኋላዋ ታፋዋ ድረስ በመራቆቱ ነበር ያ ሁሉ ዕይታ፣

“ምን ልታዘዝ የኔ እመቤት" አልኳት፡፡ በሚያበሳጭ መሞላቀቅ ቻፕስቲክ አውጥታ ደዘደዝ
ከንፈሯን ቀባችና ቍጭ አድርጋ ዘግታ ወደ ቦርሳዋ መለሰች፡፡ በትዕግስት ጠበቅኳት።

“ዶላር ተልኮልኝ ነበር"
"ክየት ነው?"
"ከዲሲ ..ሜሪካ"
“የላኪው ስም?”
"ዳኒዬ” አለች በፈገግታ፡፡
“ዳንኤል ነው?”
“ያ"
"ስንት ነው የላከልሽ?"

“ሰሪ ኦር ፎር ሃንድረድ ዶላር ስታወራ አንገቷን ትሰብቀዋለች፡፡
ዳንኤል የላከላት ግን አንድ መቶ ዶላር ሊያውም መላኪያው ከዛው ላይ የሚቆረጥ ነበር፡፡ይሄንኑ
ስነግራት ደዘደዟ ምልቃቃዋ እና ቁጫጫሟ ሞልቃቃ - ፊቷ ተቀያየረ፡፡ ስልኳን አውጥታ
ደወለችና ጥርት ባለ አማርኛ፣ "አንች ያ ችጋራም መቶ ዶላር ብቻ ነው የላከልኝ ዳንኤል እርገጤ ነዋ ብላ እርፍ፡፡ ወዲያው አንድ ቁሽሸ ያለ ቱታ የለበሰ ጎልማሳ ሰው መጣና፣

“ይቅርታ ይቺን ብር ትራንስፈር ታደርግልኝ” አለኝ እየተጣደፈ በልጅቱ ትከሻ ላይ የባንክ
ደብተሩን እያቀበለኝ:: ልጅቱ የቱታው መቆሸሽ ደብሯት ፊቷን እጨፈገገች።

“ወደየት ነው?” አልኩት፡፡
“ወደ ጅማ”
“አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊየን፡፡ ሞልቃቃዋ ሰውየውን ቀጥ ብላ አየችውና ፈገግ ብላ በአከብሮት
ቦታውን ለቀቀችለት:: ወዲያው የሚያደርጋትን አሳጣት፣ "ወደዚህ ጠጋ ብለህ አናግረው፣ ሶሪ
ቦታ ያዝኩብህ አለችው በፈገግታ፡፡ ዞሮ እንኳን አላያትም፡፡ (የውሸት አከብሮቷና ፈገግታዋ ከሰረ፡፡ ሰውዬው እናትዬ ስራ ልቡን ያወለቀው ላብ አደር ነገር ነው እሷን ለማየት ጊዜውም የለው…! “ሚስኪን ዳኒዬ!” አልኩ በሆዴ፡፡

በቃ ይሄ ነው ስራዬ ብር መቁጠር መስጠት፡፡ ብር ማስገባት፣ ማስወጣት..ኤጭጭ ! ቢሆንም
ከእሁድ ይሻላል፡፡

እማማ መጣፈጥ ስንቅነሽን ቡና ሲጣሩ ሰማሁ ገና አምስት ሰዓት ወይ እዳ!

ቅድስት አሁንም እያንጎራጎረች ነው፤ “የቤቱ ወለሉ ጣራ እና ግድግዳው…" የቤታቸውን ግድግዳና ጣራ ከውጭ በኩል በረዥም መጥረጊያ እያፀዳች ነበር፡፡ ቆንጆ ናት፣ ጠይም ቆዳዋ ጥረት ያለ፧ በታለይ እንዲህ ከኋላዋ ሁና ስትንጠራራ ላያት የአቦሸማኔ ሽንጥ፡፡ ቅድስት ቆንጆ ናት፡፡ እንደው ተፈራርተን እንጂ እኔና ቅድስት ሳንከጃጀልም አልቀረን፡፡ ባየኋት ቁጠር አቅፈህ ሳማት ሳማት ይለኛል። ...እሷም በሰበብ አስባቡ እቤቴ ጎራ ማለት ታበዛለች ግን - እንፈራራለን፡፡

ቅድስት፡ አርሴማ፣ ሃያት፤ ጀሚላ፣ ሜሮን፣ ሂሩት እና ሄለን አረብ አገር ለስራ ሄደው የትመለሱ የመንደራችን ሴቶች ናቸው፡፡ ያልተመለሱትንማ አረብ አገር እዛው ይቁጠራቸው፡፡

መጀመሪያ አረብ አገር የሄደችው አርሴማ ነበረች፤ እንዳሁኑ ባልተለመደበት ጊዜ። ታዲያ
አርሴማ ብዙ አልቆየችም ባልታወቀ ምክንያት በሶስት ወሯ ተመለሰች፡፡ ዘጠኝ ወር ሲሞላት
ግን ምከንያቱ ታወቀ፤ ወንድ ልጅ ተገላገለች ! የመንደሩ ሰው እርጉዝ መሆኗን ካወቀበት ቀን ጀምሮ ፥ የሚወለደው ልጅ አረብ ይመስሳል…. አይመስልም” እያለ ሲነታረክ፣ ሲወራረድና ብር
ሲያሲዝ ከረመ፡፡ አርሴማ የሚያምር ከልስ ልጅ ወለደች፡፡ ገና ከአራስ ቤት ሳትወጣ ደግሞ
መነሻው ያልታወቀ ወሬ ይናፈስ ጀመረ::

አርሴማ የወለደችው ትሰራበት የነበረ ቤት ተቀጥሮ ከሚሰራ ፓኪስታናዊ ዘበኛ ነው" ይሄ
ወሬ ለጉድ ተናፈሰ፡፡

“ቱ! ለሞላ ወንድ” ተባለ፡፡ “አንገት ደፊ እገር እጥፊ" ተባለ፡፡

ይሄ ወሬ እድሜው ከሳምንት አላለፈም፡፡ የመልስ ምት በሚመስል ሌላ ወሬ ተተካ፡፡
“አርሴማ ያረገዘችው ከኪዌቱ አሚር ሁለተኛ ልጅ አብደል ናስር ነስረዲን ነው...እነሱ ቤት
ነበር የምትሰራው” ይሄንኛው ወሬ ከመጀመሪያው የበለጠ ገነነ፡፡ እንደውም በቅርቡ መጥቶ
ሰፈራችንን በሊዝ ሊገዛውና በአርሴማ በኢትዮጵያ አንደኛ የሆነ ሕንፃ ሊገነባላት እንደሚችል
ሁሉ ተወራ፡፡

ሲወዳት መቸስ ለብቻው ነው፣ እሷን ሲያይ ጥምጣሙ እስኪበር ነው በደስታ የሚምነሸነሸው”
እየተባለ ወሬው ደመቀ፡፡ ጥምጣሙ እስኪበር የሚያፈቅር የአሚር ልጅ እዚህ ጭርንቁስ
መንደራችን ውስጥ መጥቶ ለማየት እኔ ራሱ ጓጓሁ፣ የፍቅርን ኃያልነት ለመታዘብ አሰፈሰፍኩ፡፡

ሕፃኑን ልጅ አያቱ ኃይለሚካኤል” አሉት፤ ኃይለሚካኤል ኣብደል ናስር ነስረዲን በዚህ ሁኔታ
የመንደራችን ኣባል ሆነ፡፡ (አረቡ ይሉታል በቅፅል ስም፣ በኢትዮጵያና ኩዌት መካከል ወደፊት ለሚኖረው ወዳጅነት ይህ ታሪካዊ እንቦቀቅላ ታላቅ ሚና ሳይኖረው አይቀርም.… ሂሂሂ)፡፡ አድጎ አስር ዓመት እስኪሆነው ግን አባቱ ነኝ ያለ የአሚር ልጅ አልታየም፡፡ አንድ ቀን ታዲያ አያቱ፣
ዓሚሩ ቀርቶበት ዘበኛውም በመጠና የአባትን ጣዕም ባውቀው” አሉ በቁጭት፡፡

ከአርሴማ በኋላ ሜሮንና ጀሚላ አረብ አገር በመሄድ ሁለት ዓመት ቆይተው ተመለሱ፡፡ እነጀሚላ
ቤት አዲስ ምንጣፍ ስለተነጠፈ ጫማ ሳያወልቁ መግባት ተከልከሉ ነበር፡፡ በአንድ እግሩ
ምንጣፉን የረገጠ እንግዳ በጀሚላ ጩኸት ሁለተኛ እግሩን በአየር ላይ እንዳንጠለጠለ ደርቆ
ይቆማል፡፡ እማማ ሐዋ (የጀሚላ እናት) ታዲያ “ይሄን ምንጣፍ ወዲያ ኣንሽልኝ ላታመም ጠያቂ፡
ሲቸግረኝ ደራሽ ጎረቤቶቼን አራቀብኝ አሉ፡፡ ሲቆይ ግን ምንጣፉም ቆሸሸ መዓቀቡም ተነሳ፣ መጀሪያ ቤተሰቡ ከዛም ሁላችንም መንደርተኞች ከነጫማችን መግባት ጀመርን፡፡

ሜሮን እንደመጣች እካባቢ ደግሞ የተረፈ ምግብ ቆሻሻ መጣያ ውስጥ እየደፋች አሰቸግራ
ነበር፡፡ ኧረ ለልጆቹ መክሰስ ይሆናል እህሉን እትድፊ ጡር ነው” ብትባል፣ “ላላ ላላ” እያለች
መገልበጥ ሆነ፡፡ ከወራት በኋላ እንኳን ሊተርፍ ዋናውም እያነሰ ቤተሰሱ መነጫነጭ ስለጀመረ
እህል መድፋቱ በዛው ቆመ፡፡

አረብ አገር የሄዱት ሁሉ ኮንትራታቸውን ጨርሰው ባንዴ ወደ መንደራችን በመጡበት ወቅት
የሚገርም የባህል፣ የኢኮኖሚ፣ የቋንቋ መቀየጥ ተከሰተ፡፡ ፓስፖርት፣ ቪዛ፣ ኮንትራት፣ በርሜል፣ ካርጎ፣ ጉምሩክ፣ ሃቢቢ..ሃቢብቲ የሚሉ ቃላት ተዘወትሩ፡፡ በመንደራችን ሻይ አብዝቶ መጠጣትና ሩዙን ከእንጀራ እኩል ገብታ ላይ ማቅረብም ተለመደ፡፡ በሳተላይት ዲሽ የእረብኛ ፊልሞ ተከታታይ ድራማዎችን ማየትም አንዱ ለውጥ ነበር፡፡

እርስ በእርስ መንደርተኞች ሲጣሉ አረብኛ ስድቦችን መቀላቀል ሁሉ ተጀመረ፡፡ እንደውም አንድ አረብኛ ስድብ ለእኔም ደርሶኛል፡፡ ቅድስት የአስቴርን ሲዲ ልትዋስ ቤቴ ሰትመጣ በቃሌ የሸመደድኩትን ግጥም ብቻዬን ሳነሰንብ ደረሰችና “መጅኑን!" አለችኝ፡፡ በኋላ ሜሮን
እንደተረጎመችልኝ ከሆነ “ወፈፌ" ማለት ነው አሉ፡፡

በዚህ ወቅት ሂሩት አረብ አገር እሄዳለሁ ብላ ተነሳች፡፡ “እንዴ ደግሞ አንቺ ምን አጣሽ ኑሯችሁ
ጥሩ፤ ትምህርትሽን እየተማርሽ ነው” ብትባል
👍241
“እንዴት ነው ምን አጣሽ ተውኝ..ተውኝ እባካችሁ ሆድ አታስብሱኝ፡፡ ያጣሁትን እኔ ነኝ
የማውቀው፡፡ የመንደሩ ሴት ሁሉ በአረብኛ ሲሰዳደብ እኔ እስከመቼ በአማርኛ ስሳደብ እኖራለሁ
ማን ከማን ያንሳል?!" አለች እንባ እየተናነቃት፡፡ ሄደችና ሁለት ዓመት ቆይታ ብዙ አረብኛ ስድቦችና አንድ በርሜል ልብስ ይዛ ተመለሰች፡፡

አስገራሚ በሆነ ሁኔታ በርሜሉ ውስጥ ሙሉ የቤይሩት መቶ አለቃ ዩኒፎርም ተገኘ፡፡ የሂሩት
እባት ያንን ግጥም ኣድርገው ለብሰው እንዳንድ ቤይሩት ኖረው የመጡ ሴት እህቶቻችንን
በሰላም አገር ሲያስደነግጡ ከረሙ:: ሂሩትም ሃሜት አልቀረላትም፣ “ፖሊስ ቤት ተቀጥራ ነበር የምትሰራው ልብሱን ሰርቃ አምጥታ ነው" አሏት፡፡

ሂሩት ግን አንድ ቀን ቁጭ ብለን ስናወራ ስለ ዩኒፎርሙ ይሄን ታሪከ ነገረችኝ፡፡ አንድ መቶ
አለቃ ሂሩትን ድንገት አያትና በፍቅሯ ተነደፈ፡፡ መጀመሪያ በሃር የተጠለፈ መሃረቡን ላከላት፤
(የፍቅር መግለጫ መሆኑ ነው) ዝም ስትለው አሃ አንሶብሽ ነው! ሰማዎት የፖሊስ ኮቱን
ከነ መአረጉ ላከላት፡ መጨረሻ መልስ ሲያጣ ሱሪውን ላከላት በሱሪው ተጠቅሎሎ ደግሞ ክላሽንኮቭ ጠመንጃው አብሮ ነበር፡፡ እንግዲህ ወንድ ልጅ ሱሪና ጠመንጃውን ከሰጠ ምን ቀረው ? ይሄ ምስኪን አፍቃሪ ፖሊስ እስካሁን በፓክ አውትና በግልገል ሱሪ በቤይሩት ጎዳናዎች ላይ ግዳጁን እየተወጣ ይገኛል፡፡ (አያድርስ ነው…አይሳቅም፡ እኔስ አለሁ አይደል ለዛች ሰላቢ ሰብለ ነፍሴን ሰጥቼ እርቃኔን የቀረሁ፡፡)

ሄሩት ዮኒፎርሙንም ክላሽንኮቭ ጠመንጃውንም ይዛ ወደ ኢትዮጵያ ስትገባ ኤርፖርት ፍተሻ ላይ ተያዘች።

“መሳሪያው አያልፉም ይወረሳል፣ ዩኒፎርሙን ችግር የለም ማስገባት ትችያለሽ” አሏት ፈታሾቹ፡፡

አረ የሰው ስጦታ ነው በናታችሁ!” ብትላቸው፣

ሕግ ነው” ብለው ግግም አሉባት፡፡ ወደ ሀላፊው ቢሮ ገብታ ጉዳዩን ነገረችው፡፡ ገና ክላሸ ስትለው፣ “አያልፍም አላት በቁጣ፡፡

ምናለበት ባታካብዱ ባንድ ጠመንጃ መንግሥት እይገለበጥ!” አለችው ግልፍ ብሏት፡፡

“ዋይ ተይ ባክሽ እኛም ደርግን ስንገለብጠው ባንድ ክላሽንኮቭ ነው የጀመርነው ብሎ ሸኛት፡፡
ሂሩትና ጀሚላ “ዩኒፎርም ስርቃለች” በሚለው ሐሜት አቧራ ያስነሳ ፀብ ገጠሙ፡፡ በአረብኛ እና
በአማርኛ ነበረ ስድድቡ፡፡ ቅድስት መሀል ገብታ እየገላገለች እግረ መንገዷን አረብኛ ስድቦችን
ለእኛ ለመንደርተኞች ትተረጉምልን ነበር፡፡

"ከልብ” አለች ሂሩት ጀሚላን፡፡ ቅድስት፣ ኧረ እንዲህ አይባልም እግዜር አይወደውም ሂሩት"
በማለት ነገሩ ለማብረድ እየሞከረች ወደ እኛ ዞር ብላ

“ከልብ ማለት ውሻ ማለት ነው:: ትለና ወደ ላ ማግላገሏ ትመለሳለች፡፡

እልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልል እሁድ መሽ ! ድንገት ቅድስት ዝንጥ ብላ እቤቴ
መጣች፣ ከሰዓት ሰርግ ነበራት፡፡ ኡፍፍፍ የለበሰችው ረዥም ቀሚስ እንዴት እንዳማረባት፡፡ ስናወራ ቆየንና "ለምን ቡና እናፈላም” ብላ ስታስፈቅደኝ ማቀራረብ ጀመረች፡፡ ባንዴ ቤቱን ነፍስ ዘራችለት፡፡ እጣኑ ተጫጭሶ ሙዚቃው ተከፍቶ ቅድስት ፊት ለፊቴ የሚያምር ጠይም እግሯ በቀሚሷ ቅድ እየታየ እንደተቀመጠች ደስታ መላ ሰውነቴን አጥለቀለቀኝ፡፡ እውነቱን
ልንገራችሁ አይደል፤ ማግባት ሁሉ አማረኝ፡፡

በድፍረት “ዛሬ ለምን እዚህ አታድሪም?” አልኳት፡፡

“ባለጌ ስትለኝ ለመስማት ጆሮዬን ይዤ ነበር፡፡

“እና ካሁን በኋላ ልሄድልህ ነው?” ስትለኝ ማመን አልቻልኩም፡፡ ዞር ብዪ እልጋዩን አየሁት።
እስከዛሬ እዚህ ባህር ላይ ብቻዬን የምንሳፈፍ ሚስኪን ጀልባ መሆኔ ተሰማኝ። ዘልዩ አቀፍኳትና
ግጥም አድርጌ ከንፈሯን ሳምኳት፡፡

"ሂድ መጅኑንም አለችኝ፡፡ እንደዚህ ቃል አሪፍ የፍቅር ቃል ሰምቼ አላውቅም፡፡ ራሴ ስተረጉመው
"በፍቅር የወፈፈ” ማለት ሳይሆን አይቀርም !! “ሰው ብቻውን ሆን ዘንድ መልካም አይደለም
እደግመዋለሁ.አባ ልክ ናቸው፡፡

የአሁድ ሌሊት እንዴት አጭር ነው ለዚህ ጊዜማ ይጣደፋል !

አለቀ
👍285
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

....ጠዋት ግን በተቻለ እንግዳውን ለመቦጥቦጥ አቅዷል፡፡.

ሚስተር ቴናድዬ ገና ጎሕ ሳይቀድ ከመኝታው ተነስቶ ወደ እንግዳ
መቀበያ ሥፍራ ሄደ፡፡ ሻማ አብርቶ የእንግዳውን ሂሳብ ያሰላል፡፡ ሚስቱ ከአጠገቡ አጎንብሳ ቆማለች:: ሂሣቡን ሲያሰላና ቁጥሮችን ሲጽፍ በዓይንዋ
ትከተለዋለች፡፡ ግን አሳብ አይለዋወጡም፡፡ ከቤት ውስጥ ድምፅ ተሰማ አንድ ሰው ክፍሎችን ይጠርጋል፡፡

ከአንድ ሩብ ሰዓት በኋላ ሚስተር ቴናድዬ ሂሣቡን አስልቶ ጨረሰ::
ከዚያም ክፍሉን ለቅቆ ወጣ፡፡ እርሱ ልክ ሲወጣ እንግዳው እርሱ ከነበረበት ክፍል ገባ። ሚስተር ቴናድዬ ብዙ አልራቀም፥ ሚስቱ ክፍሉ ውስጥ ሆና ታየዋለች:: እንግዳው እቃውን በእጁ ይዞ ነው ከክፍሉ የገባው::

«ምነው ቶሎ ተነሱ!» አለች ሚስስ ቴናድዬ፤ «ገና ሳይነጋ ሊሄዱ
ነው እንዴ?»

እንግዳው አሳብ የገባው መሰለ፡፡ መልስ ቶሎ አልሰጠም:: ቆይቶ
ግን «አዎን እሜቴ፤ መሄድ አለብኝ» አለ፡፡ወደ ሌላ «አገር ማለፍዎ ነው? ሞንትፌርሜ ውስጥ ሥራ የለዎትም
ማለት ነው?» ስትል ጠየቀች::

«የለም፧ ስለመሸብኝ ነው ያደርኩት እንጂ እዚህ የተለየ ጉዳይ
የለኝም» ካለ በኋላ ሂሣቡ ስንት እንደሆነ ጠየቀ፡፡

ሚስስ ቴናድዬ የቃል መልስ ሳትሰጠው ባልተቤትዋ ያዘጋጀውን
ሂሣብ ኣንስታ ሰጠችው::

መንገደኛው ወረቀቱን በማገላበጥ ሂሣቡን ተመለከተ፤ ግን ወረቀቱ
ላይ ያፍጥጥ እንጂ አሳቡ ሌላ ቦታ ነበር::

«እሜቴ» አለ፧ «ሞንትፌርሜ ውስጥ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ
እንዴት ነው?» ሲል ጠየቃት::

«ምንም አይደል» ብላ መለሰችለት በመገረም::፡ እርስዋ የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ ነበር፡፡ «ክቡርነትዎ እንደሚያውቀው መቼም ጊዜው እስከዚህም የሚያስደስት አይደለም:: ከተማዋ ውስጥ ብዙ ብር ያላቸው ሰዎች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው:: ከተማዋም እንደሚያዩዋት በጣም አነስተኛ ከተማ ናት፡፡ እንደ እርስዎ ያለ ሀብታም እንግዳ የሚያጋጥመን አልፎ አልፎ ነው፡፡
ወጪያችን ግን በጣም ብዙ ነው:: ያቺ ትንሽ ልጅ እንኳን ብዙ ታስወጣናለች»
በማለት ችግርዋን ደረደረች::
«ከእርስዋ ብትገላገሉስ?» አለ ነገሩን በማናናቅና በማንቋሸሽ፡፡
«ከማን? ከኮዜት?»
«አዎን፡፡»
የሴትዮዋ ፊት እንደማታ ጨረቃ ወገግ አለ፡፡
«አይ ጌታዬ! ውሰዷት፤ የትም አድርሷት፤ ቢፈልጉ እንደ ምግብ
ብሏት፤ እንደ ውሃ ጠጧት ብቻ ውሰዷት እንጂ እንደፈለጉ ያድርጓት፡፡እምዬ ማርያም ከእርስዋ ብትገላግለኝ ሻማ አበራታለሁ:»
«ተስማምቻለሁ፡፡»
«ይቀልዳሉ መሰለኝ፣ አሁን እውነት ከልብዎ ነው? ይዘዋት ይሄዳሉ?»
«አሁኑኑ እወስዳታሁ፤ ልጅትዋን ይጥሯት፡፡»
«ኮዜት!» ስትል ሚስስ ቴናድዬ ተጣራች::
«ልጅትዋ እስክትመጣ ሂሣቡን ላጠናቅቅ ስንት ነበር?»
ሂሣቡን ከወረቀቱ ላይ አየ:: ግን የመገረም ምልክት አላሳየም::
«ሃያ ሦስት ፍራንክ?»
በዚህ ጊዜ ሚስተር ቴናድዬ ከክፍሉ ውስጥ ገባ፡፡
«የለም ጌታው፤ ያለብህ ሃያ ስድስት ሱስ ብቻ ነው» አለ፡፡
«ሃያ ስድስት ሱስ» ስትል ሴትዮዋ ጮኸች::
«የክፍሉ ኪራይ ሃያ ሰስ ሲሆን የእራት ሂሣብ ስድስት ሱስ ነው::
ስለልጅትዋ ግን እኔና አንተ እንነጋገራለን፡፡ አንቺ ደግሞ ጉዳዩን ለእኛ ብትተይው ይሻላል፡፡»
ሚስስ ቴናድዬ በባልዋ ሁኔታ ተገርማ መልስ ሳትሰጥ ከክፍሉ
ወጥታ ሄደች::
ባለቤቱ እንደወጣች «ምነው ቆምክ? እስቲ አንዴ ቁጭ በል» በማለት ወንበር አቀረበለት:: መንገደኛው ቁጭ አለ፡፡ ሚስተር ቴናድዬ ግን አልተቀመጠም፡፡

«ጌታው» አለ ሚስተር ቴናድዬ ፤ «መቼም ይህቺ ልጅ በጣም
የማደንቃትና የምወዳት ናት፡፡»
እንግዳው ሰውዬ አተኩሮ በማፍጠጥ ተመለከተው::

«የምን ልጅ?»
ሚስተር ቴናድዬ ቀጠለ፡፡
«የእርስዋ ነገር አይሆንልኝም፤ ይህቺን ልጅ በጣም ነው የማደንቃት!»

«የትኛዋን ልጅ ነው የምትለው?» ሲል እንግዳው ጠየቀ፡፡

«ውይ አልገባህም እንዴ! ይህቺ የኛይቱ ትንሽዋ ኮዜት ናታ! እና
አሁን አንተ ልትወስድብን ትፈልጋለህ! እኔ መቼም በዚህ አልስማማም::ከሄደች እጅግ በጣም ትናፍቀኛለች፡፡ ከሕፃንነትዋ ጀምሮ ኣብራን ስለኖረች
የእርስዋ ነገር አይሆንልንም እርግጥ ነው ብዙ ታስወጣናለች፤ ብዙ ጥፋትም ታጠፋለች:፡ እኛ ደግሞ የተትረፈረፈ ሀብት የለንም፡፡ ሆኖም አንድ ጊዜ
ታማ አራት መቶ ፍራንክ ለመድኃኒት አስወጥታኛለች፡፡ ለሰማዩ ጌታ ስል ይህን ያህል ወጪ በማውጣታችን አልተማረርንም፡፡ እናትም አባት
የላትም፡፡ እኔ ግን እንደ አባትም እንደ እናትም ሁኜ አሳደግኋት:: አሁን ቢሆን ለእኔና ለእርስዋ የሚሆን የእለት እንጀራ ኣላጣም፡፡ ስለዚህ ይህቺ ልጅ እንድትሄድብኝ አልፈልግም:: መቼም የምለው ነገር ይገባሃል፡፡ ልጅትዋን
እንወዳታለን፡፡ ባለቤቴ አንዳንዴ ችኩል ናት:: ነገር ግን እርስዋም ብትሆን ልጅትዋን ትወዳታለች፡፡ እንደ ራሳችን ልጅ ነው የምናያት፡፡»

ሚስተር ቴናድዬ ይህን ሁሉ ሲለፈልፍ እንግዳው መንገደኛ ዓይኑን ከተናጋሪው ዓይን አላነሳም:: ሰውዬው ንግግሩን ቀጠለ፡፡

«ይቅርታ አድርግልኝና ማንም ሰው ቢሆን ልጁን ለማያውቀው ሰው
አንስቶ አይሰጥም፡፡ ልክ አይደለሁም? መቼም አንተ እንዲሁ ሲያዩህ የጨዋ
ልጅ እንደሆንክ ታስታውቃለህ፡፡ ሀብትም የተረፈህ ትመስላለህ፡፡ ልጅትዋን ልውሰዳት ስትል ስለልጅትዋ ብለህ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብኛል፡፡ ገባህ
አይደለም? ለእርስዋ ስል ስሜቴን ልግታ፤ ጥቅሜን መስዋዕት ላድርግ ብል እንኳን የት እንደምትወስዳት ማወቅ አለብኝ:: ሌላው ቢቀር የወደፊት
አድራሻዋ የት እንደሚሆንና ከማን ጋር እንደምትኖር ባውቅ እየተመላለስኩ እጠይቃታለሁ፡፡ አሁን ለምሳሌ ስምህን እንኳን አላውቅምና ልጅትዋን ማን
ወሰዳት ተብዬ ብጠየቅ ምን እላለሁ? ነገር ግን ልጅትዋን ልውሰዳት የምትለው ለሕፃንዋ ብለህ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ሌላው ቢቀር ፓስፖርትህን
ወይም የመታወቂያ ወረቀትህን እንኳን ማየት አለብኝ፡፡»

መንገደኛው አሁንም ዓይኑን ከዓይኑ ሳያነሳ የሚቀጥለውን መለሰ፡፡

ሚስተር ቴናድዬ፤ ሰዎች ከፓሪስ ከተማ ወጣ ባሉ ቁጥር የመታወቂያ ወረቀት አይዙም
ኮዜትን ከወሰድኳት እወስዳታለሁ፤ በቃ:: ሌላ አጀብ አያስፈልገውም፡ ለዚህ ማን እንደሆንክ፤ የት እንደምኖር፤ ልጅትዋ ወደፊት የት እንደምትኖር ማወቅ አያስፈልግህም፡፡ እንዲያውም እግርዋ ከዚህ ቤት ከወጣ ዳግም እንድታይዋት አልፈልግም፡፡ በዚህ ትስማማለህ? እሺ ወይም
ሰውየው ከባድ ሰው እንደሆነ ሕሊናው ጠረጠረ፡፡ ማታ ከጠጪዎች ጋር ቢጠጣ፤ ቢስቅና ቢያሽካካም ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ሰውየውን
አጢኖታል፡፡ ማምሻውን ዓይኑ ከኮዜት ዓይን ላይ እንዳላነሳ ልብ ብሉአል፡፡ለምን ወደዳት? ይህ ሰው ማነው? ይኸ ሁሉ ብር ተሸክሞ ሳለ ምነው አዳፋ ልብስ ለበሰ? እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አንስቶ መልስ
ለማግኘት ባለመቻሉ ተበሳጭቶ ነው ያመሽው:: አያትዋ ነው? ታዲያ ለምን ራሱን አያስተዋውቅም? አባትዋ ሊሆን አይችልም! መቼም ማንም
በሆን መብቱን አይሸሽግም፡፡ ታዲያ ይህ ሰው ማነው? ነገር ግን ሰውየው ትልቅ ሰው እንደሆነና ለመታወቅ የማይፈልገው ደግሞ በአንድ ምከንያት መሆኑን አልተጠራጠረም፡፡ ከእንግዳው ጋር ጨዋታ ሲጀምር የተደበቀ
ምስጢር መኖሩን ልቦናው አውቋል፡፡ ስለዚህ የሰውዬው ቆራጥ መልስ አላብረከረከውም፡፡ ነገር ቶሎ የሚገባው ሰው ስለሆነ ያልጠበቀው መልስ ቢመጣም አልተረበሸም፡፡ እንዲያውም እድሌ አሁን ነው ሲል አሰበ። ወዲያው ፍርጥም ብሉ ቴናድዬ ተናገረ::
👍211👏1
«ጌታው!» አላ«አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ይከፈለኝ»::
እንግዳው ከኪሱ የቆዳ ቦርሳውን አውጥቶ ከፈተው፡፡ ገንዘቡን
ከጠረጴዛው ላይ ካስቀመጠ በኋላ ጣቶቹን ከገንዘቡ ላይ አሳረፈ:: «ኮዜትን ሂደህ አምጣ» ሲል የቡና ቤቱን ጌታ አዘዘው፡፡
ወዲያው ከመቅጽበት ኮዜት ሰዎቹ ከነበሩበት ክፍል ገባች፡፡
መንገደኛው ጠቅልሎ ይዞት የነበረውን እቃ ፈታ፡፡ የሚያምሩ
የሰባት ዓመት ልጅ ልብሶች ነበሩ:: ጫማና እስካርፍ እንኳን አልቀረም።
ልብሶቹ ጥቁር ናቸው::
«ልጄ» አለ ሰውዬው፤ «ልብሶቹን ወስደሽ ቶሎ ለብሰሽ ተመለሺ።»
ኣንዲት የሀዘን ልብስ የለበሰች ትንሽ ልጅ አስከትሎ ከከተማው ወጥቶ ገና ሲነጋ ከቤቱ የወጣ የከተማው ነዋሪ ባይተዋር የሆነ ሰው መሄዱን አየ፡፡ ኮዜትም አዲሱን አሻንጉሊትዋን ይዛ ወደ ፓሪስ በሚያመራው መንገድ ባይተዋሩን ተከትላ ሄደች::

ሰውዬው ማን እንደሆነ ማንም አላወቀም:: ኮዜትም አዳዲስና እጅግ የሚያምሩ ልብሶች በመልበስዋ ብዙም ሰው አልለያትም::

ኮዜት መሄዱንስ ትሂድ፤ ግን ከማን ጋር ነው የሄደችው? በየዋህነት

እንደ በግ እየተነዳች ሄደች፡፡ የት እንደምትሄድ ታውቃለች? አታውቅም:. ነገር ግን የምታውቀው ነገር ቢኖር የእነዚያን ጨካኝ ሰዎች ሆቴል ቤት
ለቅቃ መውጣትዋን ነው፡፡ ከቤት ስትወጣ «ደህና ሁኝ» ያላት ሰው
አልነበረም፡፡ እርስዋም «ደህና ሁኑ» ብላ የተሰናበተችው ሰው የለም፡፡ ከዚያ ቤት ተጠልታና ጠልታ ነው የወጣችው::

ኮዜት ሰማይ ሰማዩን እያየች ሰውዬውን ተከትላ ሄደች፤ ነጐደች::አልፎ አልፎ ደጉን ሰውዬ ቀና ብላ ታየዋለች፡፡ የእግዜር መልእክተኛ መሰላት::

መሸት ሲል ዣን ቫልዣ ልጅትዋን ይዞ ከፓሪስ ከተማ ደረሰ፡፡ ከተማ
እንደገቡ በጋሪ ተሳፍረው ከከተማው ክልል ወጡ እርሱ ከፈለገበት ቦታ ሲደርሱ ለባለጋሪው ሂሣባቸውን ከፍለው ወረዱ፡፡ ዣን ቫልዣ የልጅትዋን ትንሽ እጅ ይዞ ጥቂት ከተጓዙ በኋላ ከአንድ አልቤርጎ ገቡ፡፡ እራታቸውን በሉ::ብዙ ስለተጓዙ ደክሞአቸዋል፡፡ ኮዜት እንደደከማት ስለተገነዘበ አቀፋት፧
እሷም አሻንጉሊትዋን ታቀፈች:: ወዲያው ከዣን ቫልዣ እጅ ላይ እንቅልፍ ይዞአት ሄደ፡፡....

💫ይቀጥላል💫
👍123
#ፈንዲሻ_ሲቆሎት_ድምፅ #ሲሰሉት_ድምፅ


#በአሌክስ_አብርሃም


የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት አድርገን እንደተቀመጥን፤ ፕሮግራሙ ቶሎ እንዲያበቃ ሌላ የህሊና ጸሎት ጀመርኩ፡፡ ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን ለማከበር የክፍለ ከተማው የሴቶች ሊግ ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ተገኝቻለሁ፡፡

ሊጉ በመሥሪያ ቤታችን በኩል ግዳጅ የተቀላቀለበት ጥሪ አቅርቦልን አለቃዬ ሂድ !" ስላለኝ
የቀበሌው አዳራሽ ውስጥ ተገኝቻለሁ። ያውም ቅዳሜን በሚያክል ቀን ከሰዓት!! ሰኔና ሰኞ
ገጥሞብኝ፡፡

አሁን ደግሞ የከፍለ ከተማችን የሕፃናትና ሴቶች ፑል ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ደርባቤ በላቸው
እንስራውን ሰብሮ ወሰዳት ልጅቱን የሚል ምርጥ ግጥም ያቀርቡልናል…" አለ ጉጉት የመሰለው መድረክ አስተዋዋቂ፡፡ አፉ ላይ የደቀነውን ማይክሮፎን ድምፅ ማጉላቱን የተጠራጠረ ይመስል በጣም እየጮኸ ነው የሚናገረው::

ቀጠለ "ወ/ሮ ደርባቤ ለክፍለ ከተማችን፣ ብሎም ለከተማችን፣ ብሎም ለኢትዮጵያ ሴቶች፣
ብሎም ለአፍሪካ ሴቶች ታላቅ ምሳሌ የሚሆኑ የዘርፈ ብዙ ሙያዎች፣ ተሰጥኦዎች፣ ትምህርቶች፣ስልጣኖች ባለቤት ናቸው” አለና፣ “…እስቲ ወ/ሮ ደርባቢን ወደ መድረክ…”

...ቿ..ቿ...ቿ..

ጥልፍ ቀሚስ የለበሱትና አንዳንድ ልማታዊ ዝግጅቶች ላይ ልማታዊ ግጥም በማቅረብ የሚታወቁት
ወ/ሮ ደርባቤ መድረክ ላይ ቆመው በፈገግታ ለሕዝቡ ጎንበስ ቀና እያሉ ምስጋና ይሁን ሰላምታ
ያለየለት ግማሽ ስግደት አቀረቡ፡፡ ግጥሙን ሊያቀርቡ ነው ብለን ፀጥ ስንል አስተዋዋቂው
ማዋደዱን ቀጠለ፣ “….ብታምኑም ባታምኑም ወ/ሮ ደርባቤ ይሄን ዝግጅት አስመልከቶ ግጥም
እንድትፅፍልን የነገርናት (አንች አላት) ትላንት ዘጠኝ ሰዓት ነው፡፡ ይገርማችኋል ሌሊቱን ስትፅፍ
አድራ ጧት ስደውልላት በስልክ ግጥሙን አነበበችልኝ…'ወይ መባረክ' ነው ያልኩት።( በሕዝብ
ስልክ ስምንት ገፅ ግጥም እያነበቡ አላየንም ባርኮት)፡፡

“...የግጥሙን ጥልቀት እና ውበት ራሳችሁ ታዘቡት እስቲ ለዚህች ብርቱ ሴት ሞቅ ያላ ጭብጨባ…" ብሎ ጭብጨባውን ራሱ ጀመረው፡፡ ማይኩን በሌላኛው እጁ ሲጠፈጥፈው አዳራሹ ጓጓጓ.. በሚል ልጆሮ የሚቀፍ እስቅያሚ ድምፅ ተሞላ፡፡ ከታዳሚው የተንቦጫረቀ ደካማ ጭብጨባ ጋር ተዳምሮ ጓጓታው በቀላል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች የታጀበ የከባድ መሳሪያ ድምፅ ነበር የሚመስለው፡፡

ብዙው ታዳሚ በየእጁ ፈንዲሻ እና ለስላሳ ይዞ ስለነበረ ማጨብጨብ አልቻለም እንጂ በጭብጨባማ የእኛን ኮፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች ማን ብሏቸው::በተለይ እጃቸው ባዶ ሲሆን የሚያጨበጭቡት ጭብጨባ ቢሾፍቱ ይሰማል፡፡ እጃቸው ባዶ ሲሆን ለዜና ያጨበጭባሉ፣ ለሪፖርት ያጨበጭባሉ፣ የቀበሌው ሊቀመንበር ሲያስነጥሱ ሁሉ
ያጨበጭባሉ፣ እጃቸው ሞላ ካለች ግን ጠቅላይ ሚንስትራችን ቢዘፍኑም አያጨበጭቡም
እንዳንዴ ታዲያ ጭብጨባዎች ሲቀንሱ ኢኮኖሚያችን ያደገ ይመስለኛል፡፡

ቀጠለ አስተዋዋቂው (ወ..ይ ዛሬ) "ወ/ሮ ደርባቤ.ገጣሚ ብቻ አይደሉም፤ የታሪክ ተመራማሪም
ናቸው፡፡ (ወ/ሮ ደርባቤ ቆመው በቁማቸው ገድላቸው ሲለፈፍ በፈገግታ ያዳምጣሉ )..ከፍተኛ
አድናቆት ያተረፈውንና የከፍላ ከተማችን የእድገት ማራቶን ሩጫ ከዘመነ ደርግ ውድቀት ቀኋላ' የሚለውን መጽሐፍ ጨምሮ አራት የግጥም መጻሕፍትን አሳትመዋል፤ ይሄን ያህል
ካልኩ እንዳላሰለቻችሁ ወደ ወ/ሮ ደርሳቤ ልምራችሁ...” ብሎ ማይኩን በአክብሮት ለሴትዬዋ
አቀበላት፡፡ (እፎይ! አንድ አዛ ለቀቅ ይላሱ እማማ ሩቅያ ሲተርቱ)

..ማይኩን ተቀብላ ጓ...ጓ አደረገችና (የፈረደበት ማይክ ተጠፍጥፎም፣ ያወሩትን ሁሉ ተቀብሎ አጉልቶም እሳዘነኝ)፡፡ እ..እኔ እንኳን የተባለውን ያህል ነኝ ብዬ አላምንም.፣ ምከንያቱም እንደ እኔ ዕድሉን ቢያገኙ እንኳን ኢትዮጵያን ዓለምን ጉድ የሚያስብሉ ሴቶች ከእናንተ መሀል አሉ ብዬ ስለማምን ነው…" አለች ወይዘሮ ደርባቤ፡፡

ጭብጨባ…! ቿቿቿቿቿቿቿቿቿ (ፈንዲሻው አለቀ ባአንዴ ጭብጨባው ደመቀኮ)
ከጎኔ የተቀመጠች ሴት “እውነት ነው" ብላ ጮኸት፡፡ (ዓለምን 'ጉድ' ከሚያስብሉት ሴቶች
መሐል እንዷ ሳትሆን አትቀርም፡፡ ዞር ብዬ ሳያት በግራ እጇ ሞባይል ስልኳን፣ በቀኟ፣ መዳፏ
እስኪወጣጠር የዘገነችውን ፈንዲሻ ይዛ በስሜት ወደ መድረኩ እያየች ቁጭ ብድግ ትላለች፡፡
..ከፈንዲሻው ኮርሽም አደረገችለት፡፡)

ሴትዮዋ ግጥሟን ከማቅረቧ በፊት ሰላሳ ደቂቓ አወራች፡፡…እንዴት የወንዶችን ተፅዕኖ ተቋቁማ ታላቅ ገጣሚ' ለመሆን እንደበቃች፣ ሴቶች የርሷን ፈለግ ይዘው እንዲከተሏት፣(ብትወዱስ እኔን ምስሉ ዳርዳርታ)ይሄን ሁሉ አወራችና “እንዳላሰለቻትሁ” በማለት ወደ ግጥሟ ተሸጋገረች
(ገና ድሮ የሰለቸንውን !?)

ወደ መድረክ ስትወጣ መነፅሯኝ ቦታዋ ላይ ረስታው ስለነበር፣ " አቀብሉኝ”ስትሳቸው የእጅ ቦርሳዋን አራት ሰዎች ግራና ቀኝ ይዘው (ማሸርገዳቸው ስላበሳጨኝ የጨመርኩት ነው) አቀበሏት፡፡ቦርሳዋ ውስጥ አስር ደቂቃ ፈልጋ መነፅሯን ቤቷ መርሳቷን አረጋገጠች፡፡..እናም ወደ ብርሃኑ ቀርባ ግጥሟን ማንበብ ጀመረች፡፡

እንስራውን ሰብሮ ወሰዳት ልጅቱን(ርዕስ)
አረ አያ ደገፋው አንተ ትልቀ ሰው፣
አንዲት ፍሬዋን ልጅ ማስቸገርህን ተው!
ውሃ ልትቀዳ ወንዝ ስትሄድ፡
ቁመሽ አውሪኝ አልካት በግድ፣
ይሄ እልበቃ ብሎህ ሰው ጭር ሲልልህ
ሕፃኗን ደፈርካት እግዜር ይይልህ (ውይ ወንዶች አለች ከጎኔ ያለችዋ ባለ ፈንዲሻ)
ደሟን እያዘራች እቤቷ ስትደርስ፣
እንስራ ሰበርሽ ብለው ጎረፉት አያድርስ.
ደሞ በሌላ ቀን እንደገና አድብተህ..፣
አሁንም ደፈርካት አንተ ምን ዓይነት ሰው ነህ። ('በስማም ጭካኔ.ሌላዋ ሴት)

አዳራሹ ፀጥ ብሎ 'ግጥሙን' እያዳመጥን ድንገት ጎኔ ያለችው ሴት ጎርደምደምደም…ከሻሸሽ…
ስታደርግ ደንግጬ ዞሬ ተመለከትኳት፡፡ ተመስገን ፈንዲሻ እየበላች ነው፡፡…እኔማ በግጥሙ
ተመስጣ በስህተት ስልኳን ቆረጣጠመቻት ብዬ ነበር፡፡
ግጥሙ ለድፍን ሀያ ሰባት ደቂቃ ተነበበ፡፡ የግጥሙ የመጨረሻ ስንኞች

ፊስቱላ ተይዛ ስትንከራተት፣
ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኛ አግኝታታ!
እዲሳባ በመኪና አመጣቻት.
መንግሥታችን በሠራው ዘመናዊ አስፓልት…?

አመሰግናለሁ !!

ቿቿቿቿቿቿቿቿቿ….(ታዳሚው ፈንዲሻውን ጨርሶ ነበር)

ለመውጣት ሳቆበቁብ አስተዋዋቂው እንዲህ አለ….

“ለሴቶች ቀን ያልሆነ ግጥም ለመቼ ይሆናል' በማለት ወይዘሪት ዘቢደር የወጣቶች ሊግ አትተባባሪ
ለግንቦት ሃያ አንብባው የተደነቀላትን 'ታታሪዋ ሥራ ፈጣሪ' የሚለውን ግጥምን ላቅርብ
ብላለችና እስቲ ወደ መድረክ…”

ተነስቼ ወጣሁ፡፡ ወደ ቤቴ ስሄድ ከኋላዬ የአስተዋዋቂው ድምፅ ይሰማኛል፡፡

"ወጣት ዘቢደር የእንስቷ ጣጣ የሚል በቅርቡ በታተመ የግጥም መድብሏ ከፍተኛ እውቅና
ያተረፈች ብርቱ ሴት ስትሆን...” እያለ ቀጠለ፡፡

ይሄ ቀበሌ ነዋሪው ሳይሰማ ማተሚያ ቤት ከፈተ እንዴ?.. እንዴት ነው ይሄ መድብል ማሳተም እንዲህ የቀሰለው ጎበዝ? ?!

አለቀ
👍24😁12👎1
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

አሮጌው ቤት

ከአርባ ዓመት በፊት እጅግ ጭር ያለ ሰፈር የነበረው ዛሬ ብዙ
ሕዝብ ይተራመስበታል፡፡ ገጠር መሆኑ ቀርቶ ወደ ከተማነት ተለውጧል፡፡ አካባቢው ዣን ቫልዣ ሲያውቀው ከፓሪስ ከተማ ወጣ ያለ ባላገር ነበር፡፡ዛሬ የከተማው አካል ሆኖአል፡፡ ብዙ ቤቶች ተሠርተዋል፤ መንገድም
ወጥቶለታል፡፡ ቢሆንም ግን የገጠርነት ስሜት አሁንም ይታይበታል፡፡ከመንገዱ ግራና ቀኝ ሳር በቅሎአል:: ቤቶቹም ቢሆኑ እስከዚህም የጸዱ አይደሉም፡፡ የፈረስ ገበያ ከዚያ አካባቢ ስለነበር የስፍራው ጽዳት ይህን
ያህል አያስደስትም::

ከዋናው መንገድ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚታይ ባለአንድ ፎቅ አሮጌ ቤት
አለ፡፡ በሮቹ በምስጥ ስለተበሉ አልፎ አልፎ ቀዳዳ ይታይባቸዋል:: የቤቱ መስኮቶች በጣም ሰፋፊ ናቸው:: የመስኮቶቹ መስታወት አንዳንዶቹ ስለተሰበሩ
በካርቶን መሳይ ወረቀቶች ተሸፍነዋል :: መጋረጃዎቹም ቢሆነ
ከመበለዛቸውም በላይ ጫፍ ጫፋቸው ተቀዳደዋል:: ወደ ፎቅ በሚያስወጣው መሰላል ሲራመዱ ደረጃው እንደ መዚቃ መሣሪያ ያፍጮሃል:: በረት የመሰለ
ትልቅ ክፍል ከሩቁ ይታያል፡፡ የዚህ ክፍል ሀለቱም መስኮቶች ሰፋፊ ሲሆኑ በዚያ በኩል ወደ ውጭ በማየት በመንገድ የሚያልፈውን ማየት ይቻላል::የቤቱ ቁጥሩ 5052 ነው

ዣን ቫልዣ ከዚህ አሮጌ ቤት አጠገብ ሲደርስ ቆም ብሎ ቤቱን
አየው:: ጭልፊት የሚያሳድዳት ጫጩት የተሰወረ ከለላ እንደምትፈልግ ሁሉ እርሱም ከነዣቬር ለመሰወር ከለላ ይፈልጋል:: የዚህ ቤት አቀማመጥ
ደግሞ በጣም የተሰወረ ስለነበር የሚፈልገውን ያገኘ መሰለው፡፡ ከኪሱ ውስጥ ቁልፍ አውጥቶ በሩን ከፈተው:: ከገባ በኋላ መልሶ ዘጋው:: ኮዜትን ታቅፎ በደረጃው ወደ ፎቅ ወጣ፡፡ ደረጃውን ወጥቶ ሲጨርስ ሌላ ቁልፍ ከኪሱ አወጣ፡፡ የተቆለፈውን በር ከፍቶ ወደ አንድ ክፍል ገባ፡፡

ስፋ ካለ ክፍል ወለል ላይ ትልቅ ፍራሽ ተዘርግቷል፡፡ ጥቂት
ቦታ ወንበሮችና ጠረጴዛም አለ፡፡ የእሳት ማንደጃ ከአንድ ጥግ ይታያል:: አንድ ትንሽ የልጅ አልጋም አለ፡፡ ዣን ቫልዣ ቀስ ብሎ ኮዜት ሳትነቃ ከትንሹ አልጋ ላይ አስተኛት::

በሩን መልሶ ከዘጋ በኋላ ሻማ አበራ:: የመንገዱ መብራት ክፍሉን
ያሳይ ስለነበር ሻማ እስካበራ ድረስ በጨለማ አልተንገዳገደም:: በአለፈው ቀን እንዳደረገው ሁሉ ኮዜት ተኝታ ሳለ ዐይኑን ከዐይንዋ አላነሳም:: ለረጅም ጊዜ ኣፍጥጦ ተመለከታት:: ኮዜት ከማን ጋርና የት እንደተኛች ሳታውቅ ለብዙ ሰዓት እንቅልፍዋን ለጠጠች::
ዣን ቫልዣ ጎንበስ ብሎ እጅዋን ሳማት:: ከዘጠኝ ወር በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ እንቅልፍ ወስዶአት ሳለ የእናትዋን እጅ ስሞ ነበር፡፡

ተመሳሳይ የሆነ የሀዘኔታና የጭንቀት ስሜት ተሰማው:: ኮዜት ከተኛችበት አልጋ አጠገብ ተንበረከከ፡፡

ወገግ ብሎ ነግቷል:: ግን ልጅትዋ አሁንም እንቅልፍ እንደወሰዳት
ናት። ከባድ እቃ የጫነ ጋሪ በዚያ ሲያልፍ ያንን አሮጌ ፎቅ ቤት አነቃነቀው፡፡ ኳኳታው በኃይል ስለነበር እንኳን የትኛን የሞተን ይቀሰቅሳል ማለቱ የድምፁን ብርታት መግለጽ እንጂ ማጋነን አይሆንም::

«እመት እመቤቴ» አለች ኮዜት ፈንጠር ብላ ከአልጋው እየተነሳች::
ቀጠለችና ደግሞ መጣሁ መጣሁ» ስትል ጮኸች:: ዓይንዋን ሳትገልጥ ካልጋው ዘላ ወረደች።
እየተንጠራራች ወደ ግድግዳው ሄደች።

«ወይ ጣጣ፤ መጥረጊያው የት አለ!» አለች::

ኣሁን ዓይንዋን ገልጣለች:: በፈገግታ ያጌጠ የዣን ቫልዣን ፊት
ተመለከተች::

«እህ! ለካስ…» አለች ልጅትዋ ፧ «እንደምን አደሩ ጌታዬ::»

ቶሉ ብሎ አካባቢውን መላመድና ባለው መደሰት የልጆች ባህርይ
ነው:: ተደሳች ሁነው ሰው ያስደስታሉ፡፡

ኮዜት ካተሪንን ከአልጋዋ ስር አየቻት፡፡ ወዲያው ብድግ አድርጋ
አቀፈቻት፡፡ ከአሻንጉሊቱ ጋር እየተጫወተች ዣን ቫልዣን የመዓት ጥያቄ ጠየቀችው:: የት ነበረች? ፓሪስ ትልቅ ከተማ ነው? አሁን መዳም ቴናድዬ ከዚህ አይመጡም? ከዚህ የሚስስ ቴናድዬ ቤት ምን ያህል ይርቃል?
ሌላም፧ ሌላም፡፡ በመስኮቱ ወደ ውጭ አይታ «እንዴት ያምራል፤ እንዴት ደስ ይላል» ስትል ተናገረች::

የነበረችበት ሁኔታ በመጠኑም ቢሆን ያስፈራ ነበር፡፡ ነገር ግን
እርስዋ ነፃ የወጣች መሰላት::

«ቤቱን ልጥረግ?» ስትል ጠየቀች::

«የለም፧ ተጫወች» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰላት::

ስትጫወት ቀኑ አለፈ:: ስላለችበት ሥፍራም ሆነ ሁኔታ ለማወቅ
ራስዋን ሳታስጨንቅ ከአሻንጉሊትዋ ጋርና ከጓደኛዋ ጋር እየተጫወተች ደስ ብሎአት ነበር የዋለችው::

በሚቀጥለው ቀን ጎሕ ሲቀድ እንዳለፈው ቀን ኮዜት ስትነቃ ለማየት ዣን ቫልዣ ከአልጋው አጠገብ ሲቀመጥ አዲስ ስሜት ተሰማው፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ በፊት ምንም ነገር አፍቅሮ አያውቅም፡፡ ትዳር ሳይዝ፣ ልጅ ሳይወልድ ፤ ሴት ሳያፈቅርና የልብ ጓደኛ ሳያበጅ ለሃያ አምስት ዓመት ብቻውን ነው የኖረው:: እስር ቤት ሆኖ ኑሮው የጨለማና የስቃይ ነበር፡፡
ዣን ቫልዣ እስር ቤት ከመግባቱ አስቀድሞ ከቤቱ ሲወጣ ልቡ በተስፋ የደነደነ፤ ሐሞተ ሙሉ ሰው ነበር:: እህቱና ልጆችዋ ከሕሊናው ጨርሰው
ባይፋቱም በአሳብ የሚታዩት እጅግ ተንነው ሲሆን እነርሱን ለማግኘት ብዙ ጥረት አደረገ፡፡ ግን አላገኛቸውም:: ጊዜ እንደሚሽረው እንደማንኛውም ነገር ከጊዜ በኋላ ግን ረሳቸው:: ሌሎችም በወጣትነት ዘመኑ የሚያውቃቸው
ነገሮች ሁሉ እንደዚሁ ከሕሊናው ውስጥ መንምነው ጠፍተዋል፡፡

ኮዜትን አግኝቶ ከዚያ የስቃይና የመከራ ኑሮ ሲያወጣትና ይዞአት
ሲሄድ ስሜቱ እጅግ ይነካል፡፡ ይህም ለሰው ልጅ የነበረውን ፍቅር ቀሰቀሰበት። የፍቅሩ ጽናት ከዚህች ልጅ ዙሪያ ተሰባሰበ፡፡ ወደ ኮዜት አልጋ ጠጋ ብሎ ሲመለከታት ልቡ በደስታ ፈካ:: እናት ለልጅዋ ፍቅር እንደምትብረከረክ ሁሉ እሱም በዚህች ልጅ ፍቅር መዋጡ ገረመው፡፡

የፍቅሩ ግለትና የሀዘኔታው ብዛት ሊገባውና በቃላት ሊገልጸው ከሚችለው እርሱ ሃምሣ አምስት ዓመቱ ሲሆን እርስዋ ስምንት ዓመትዋ ነው:: ስለዚህ ፍቅሩ ግሪኮች አጋፔ ብለው የሚጠሩት እናት ለልጅዋ ያላት ፍቅር
ዓይነት እንጂ የሌላ አልነበረም፡፡

በሕይወት ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ የሕይወት ተመስጦአዊና አስጨናቂ ትርኢት አየ፡፡ ከእስር ቤት ሲወጣ ያገኛቸው ጳጳስ የሕይወቱን አድማስ
ያሰፉለትና የሕይወት ጣዕም ሕያቀደዱለት የመጀመሪያው ፍጡር ናቸው፡፡

ኮዚት ደግሞ ተጨማሪ የፍቅር ጎሕ ከፈተችለት፡፡ ይህንኑ እያሰላሰለ ጥቂት ቀናት አለፉ::
አሳዛኝዋና ምስኪንዋ ኮዜትም ቢሆን ሳይታወቃት እየተለወጠች
ነበረ፡፡ እናትዋ ጥላት ስትሄድ ጨቅላ ልጅ ነበረች፡፡ በዚያን ጊዜ ምን ትመስል እንደነበር ለማስታወስ አትችልም፡፡ ልጆች እንደ ሐረግ ካገኙት ላይ እንደሚጠመጠሙ ሁሉ እርስዋም ከሰዎች ላይ ተጠምጥማ ለማፍቀር ብትሞክርም ሰዎች የማፍቀር እድል አልሰጥዋትም ነበር፡፡ እነሚስተር ቴናድዬ ፤ ልጆቻቸውና ሌሉችም ቢሆኑ ፍቅር አላሳይዋትም: ከቤታቸው
የነበረውን ውሻ ትወደው ነበር፡፡ ግን እሱም ሞተ፡፡ ውሻው ከሞተ ጀምሮ እንኳን ሰው የቤት እንሰሳም ቢሆን አላቀረባትም:: ስለዚህ ጥፋቱ የእርስዋ ባይሆንም ገና በስምንት ዓመትዋ ለሰው ፍቅር አልነበራትም:: ቢወድዋት
👍12
ግን ትወድ ነበር፤ ምክንያቱም የማፍቀር ኃይል ስለነበራት ነው፡፡ ያንን ደግ ሽማግሌ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ነው ያፈቀረችው:: ፍቅሯ በየእለቱ
እየዳበረ ሄደ፡፡ ከዚያ በፊት የማታውቀው ስሜት ተጠናወታት፡፡ ለእርስዋ ደጉ ጓደኛዋ አንድ ምስኪን ሽማግሌ ሳይሆን እጅግ የተዋበና ዕፁብ፣ ድንቅ
የሆነ ዣን ቫልዣ የተባለ ሰው ነው::
በዣን ቫልዣና በኮዜት መካከል ያለው የእድሜ ልዩነት በሞላ ጉደል ሃምሣ ዓመት ቢሆንም በሕይወት ዘመናቸው የደረሰባቸው ስቃይና መከራ ፤ምንም እንኳን ርዝማኔው ቢለያይም፧ አሳዛኝነቱ ተመሳሳይ ነው፡፡ ይህም
አንድ እንዲሆነና እንዲቀራረቡ ምክንያት ሆናቸው:: የኮዜት ውስጣዊ ስሜት የሚመኩበት አባት ሲፈልግ የዣን ቫልዣ ፍላጎትና ምኞት ደግሞ
የደረሰበትን የሚያቃልልለት ልጅ ማግኘት ነበር፡፡ ስለዚህ የሁለቱ መገናኘት ማለት የፍላጎትና የስሜት መርካት ማለት ስለነበር ነፍሶቻቸው እርስ በእርስ የሚፈላለጉ መሆናቸውን አወቁ፡፡ ስሜታቸውን ለማርካት ተቃቀፉ፡፡
በቃላት ኃይል ሁኔታውን አጥርቶ መግለጽ ኣይቻልም እንጂ ዣን
ቫልዣ ማለት ሞተ ተብሉ የተለቀሰለት አባትዋ ሲሆን ኮዜት ማለት ደግሞ የሙት ልጅ ናት፡፡ ስለዚህ ነው ዣን ቫልዣ የኮዜት እውነተኛ አባት ባይሆንም የመንፈስ አባትዋ ሊሆን የቻለው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ኮዜት
በጨለማ ውሃ ለመቅዳት በሄደችበትና በሞትና በሽረት መካከል በነበረችበት ሰዓት ሊረዳትና ባልዲውን ከእጅዋ ወስዶ ሲሸከምላት ከየት መጣ ሳይባል በድንገት ብቅ ያለው ፍጡር መለኮታዊ ኃይል የሰጣት አባትዋ ነው::

ዣን ቫልዣ ለመደበቂያ ብሎ የመረጠው ቤት ተስማሚ ነበር::
ከዚያ ሥፍራ ማንም ያገኘኛል ብሎ የሚጠራጠሩት ወይም ያጋልጠኛል ብለው የሚፈሩት አልነበረም፡፡ ዣን ቫልዣ ቤቱን እንዳለ አልተከራየውም::
ምድር ቤቱን ነጋዴዎች እቃ ጭነው የመጡባቸውን ከብቶች ያሳድሩበታል::ፎቁ ላይ ብዙ ክፍሎች ያሉት አፓርትመንት ቢሆንም ከእነርሱና ከአንዲት
አሮጊት በስተቀር ሌላ ሰው አልነበረበትም፡፡ አርጊትዋም ብትሆን የዣን ቫልዣ ሠራተኛ ነበረች፡፡ የተቀሩት ክፍሎች ባዶ ናቸው:: አሮጊትዋ የቤቱም ጠባቂ ሁና ትሠራ ስለነበር የነበሩበትን ክፍል ያከራየቻቸው ይህቺ ሴት ናት፡፡ እንደ አጋጣሚ ቤቱን የተከራዩት የገና እለት ነበር፡፡ ዣን ቫልዣ ራሱን ሲያስተዋውቅ ከሩቅ አገር የመጣ፤ ክስረት
የደረሰበት ነጋዴና የሚኖረውም ከልጅ ልጁ ጋር እንደሆነ አድርጎ ነው::የስድስት ወር የቤት ኪራይ በቅድሚያ ከፈለ፡፡ ቀኑ አልፎ ሳምንት፧ሳምንት አልፎ ወራት ተተኩ፡፡ ኮዜትና ዣን ቫልዣ ከዚያ አስቀያሚ ቤት ደስ እያላቸው ኖሩ፡፡
በጠዋት ተነስቶ እንደሚያዜም ወፍ ኦክትም በጠዋት እየተነሳች
ትጫወታለች፤ ትስቃለች፤ ትዘፍናለች:: ኣንዳንዴ ዣን ቫልዣ እጅዋን እየያዘ ያንሸራሽራታል፡፡
ሕይወትዋን ሙሉ በግሣዔና በድብደባ ያሳለፈች ልጅ አሁን ኑሮ በድንገት ስለተለወጠላት እንዳንዴ ግር እያላት እንደማፈር
ትላለች::

ኮዜት እንደ ድሮው የተቦጫጨቀ በትቶ አትለብስም:: እንደ ሀዘነተኛ
ጥቁር ነው የምትለብሰው:: ጥቁር ይሁን እንጂ ማራኪ ልብስ ስለሆነ
አምሮባታል፡፡ ከድህነት ወጥታ የኑሮን ምንነት እየቀመሰች ነው፡፡
ዣን ቫልዣ ፊደል ያስቆጥራት ጀመር:: ራሱ ፊደል የቆጠረው እስር ቤት ሆኖ ነው:: ኮዜትን ማስተማርና መጠበቅ የዣን ቫልዣ የእለት ተእለት ተግባር ሆነ፡፡ አንዳንዴ ቁጭ ብለው ሲጫወቱ ስለእናትዋ ያወጋታል፡፡ በጸሎትዋ እንድታስባት ያስተምራታል:: እሷም «አባባ» እያለች ነው የምትጠራው፡፡ ይህ እንግዲህ የራስዋ ግምት እንጂ የነገራት አልነበረም።

ዣን ቫልዣ ኮዜትን አግኝቶ ባፈቀራትና በራራላት ጊዜ የነበረበትን ሁኔታ መግለጽ ተገቢ ይሆናል፡፡ ኮዜትን ያገኛት የሰውን ልጅ ክፉነት፧ የህብረተሰብን ጭካኔና ችግር፤ እንዲሁም የዓለምን አንዱን ገጽታ ብቻ
ባየበት ወቅት ነበር፡፡ የሴቶችን ችግር በፋንቲን መከራና ስቃይ ተጠልለና ተጠቃሎና
የባለሥልጣንን ኃይል በዣቬር ተመስሎ በቀረበበት፣ ለሰው ደግ እሠራለሁ በማለቱ እንደገና እስር ቤት እንዲገባ በተወሰነበትና በዚህም የተነሳ እጅግ በተማረረበት ወቅት ነበር
ኮዜትን ያገኛት ምንአልባትም እኛያ ህይወቱን የለወጡት ጳጳስ ትዝታ በመነመነበትና «እንደገና ተመልሰህ ወደ ተንኮል ፧ ክፋትና ምቀኝነት ኑሮ ተመለስ» የሚል ስሜት ሕሊናው ውስጥ በተቀረጸበት ሰሞን ሊሆን ይችላል ኮዜትን ያገኛት፡፡ በዚህ ወቅት ነው ፍቅር በድንገት ብቅ ብሎ ሕይወቱን እንደገና የለወጠውና የመንፈስ ኃይል የተጎናጸፈው::
ከኮዜት ይበልጥ ጉልበትና አቅም ስለነበረው ኮዜትን ጠበቃት፤ ተንከባከባት:: እርስዋም የበለጠ ብርታት ኣጎናጸፈችው፡፡ ምስጋና ለዣን ቫልዣ ይሁንና
እርስዋም ቀጥ ብላ መራመድ ቻለች፡፡ ምስጋና ለእርስዋም ይሁንና ሕይወቱን ከቀና ጎዳና እንዲያስገባ አደረገችው፡፡ እርሱ እንደደገፋትና እንደረዳት ሁሉ
እርስዋም ደገፈችው፧ ረዳችው..

💫ይቀጥላል💫
👍196
አትሮኖስ pinned «#ምንዱባን ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ሁለት ፡ ፡ #ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ አሮጌው ቤት ከአርባ ዓመት በፊት እጅግ ጭር ያለ ሰፈር የነበረው ዛሬ ብዙ ሕዝብ ይተራመስበታል፡፡ ገጠር መሆኑ ቀርቶ ወደ ከተማነት ተለውጧል፡፡ አካባቢው ዣን ቫልዣ ሲያውቀው ከፓሪስ ከተማ ወጣ ያለ ባላገር ነበር፡፡ዛሬ የከተማው አካል ሆኖአል፡፡ ብዙ ቤቶች ተሠርተዋል፤ መንገድም ወጥቶለታል፡፡ ቢሆንም ግን የገጠርነት ስሜት አሁንም…»
#የጉድ_ሀገር ...
ከረሞናታ ልቤ
ወደድኩኝ በል ብቻ ፣ዳግሞ ተካልቤ፤
ከረምናታ ስሜ
ናፈቀችኝ በላ ፤ተጠገነ ቅስሜ።
ያቺን የቀድሞዋን
ከመቼው ወደሀት፣
ከመቼው አጣሀት፤
እስቲ ሰከን በል፤
ሰው ማፍቀር አይቀድምም ፣ልብን ከማባበል።
እባክህን ልቤ ፣ራስህን ቆንጥጥ፤
የትም አትዳረስ ፣እነደተረሳ ጥጥ።
የሄድክ የነጎድከው ፣ አዲስ ገላ ወደህ
እኔን ለማን ክደህ።
አልኖርሞ ያለሷ ያልከኝ
እኔን የት አረከኝ።
እስቲ ሰከን በል ፤ በባለፈው ቆዝም፤
ያልተረጋጋ ግንድ ፣ሥር አፈር አይዝም።
በማጣትህ እዘን፤
ነገን አያቆምም ፣ ዛሬ ሳይመዘን።
የትናንትን ፍቅር ፣ ሳታስታምም ቀርተህ
ከሴት ተኛኹ አትበል ፤ከሐዘን ተኝተህ።
የመለየት ጥጉን
ሐዘን ሳትቀመጥ ፣የትሞ አትሰደድ፤
ማስተዛዘኛ እንጂ
ፍቅር አይባልሞ ፣ ከሕመሞ ቀጥሎ ፣ የተገኘ መውደድ።
ከረምናታ ልቤ!

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍118
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_ሦስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


...እነዣን ቫልዣ ከነበሩበት አካባቢ ከቤተክርስቲያን ደጃፍ የማይጠፋ
አንድ ለማኝ ነበር:: ዣን ቫልዣ በዚያ ባለፈ ቁጥር ሣንቲም ይጥልለታል፡፡ለማኙን የሚመቀኙ የመንደሩ ሰዎች ሰላይ ነው እያሉ ያወሩበታል፡፡ አልፎ አልፎ ዣን ቫልዣ ቆም እያለ ያዋራዋል፡፡ ግን ሲያዋራው ለማኙ ቀና አይልም::

አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ በዚያ ሲያልፍ ለማኙ ዘወትር
ከሚቀመጥበት ቁጭ ብሎ ያየዋል:: ያን እለት ኮዜት አብራው አልነበረችም::ሰውዬው ከተቀመጠበት አጠገብ የመንገድ መብራት በርቶ ስለነበር በጉልህ
( ይታያል:: ዣን ቫልዣ እንደተለመደው ወደ እርሱ ሄዶ ሣንቲም ሰጠው::ለማኙ ቀና ብሎ በማየት አፈጠጠበት:: ወዲያው ወደ መሬት አቀረቀረ፡፡
ፊቱን ሲያየው ያ ዘወትር ጎብጦ እና የሰባ ዓመት ሽማግሌ መስሉ
የሰውዬው አመለካከት ቅጽበታዊ ስለነበር ገዣን ቫልዣን አስደነገጠው:: ይቀመጥ የነበረው ሰው ቀደም ሲል የሚያውቀውና የሚከታተለ ክፉ ሰው እንደሆነ ጠረጠረ፡፡ በዚህ ጊዜ ጥቅጥቅ ካለ ጫካ ነብር ያየ መሰለው::
መናገር ወይም መሮጥ ወይም መቆም ተሳነው:: ለማኙን አተኩር ከማየት ግን አልቦዘነም::
«ወይ ጉድ!» አለ ዣን ቫልዣ እርስ በራሱ ሲነጋገር፡፡ «አበድኩ፤
በሕልሜ መሆን አለበት! ሊሆን አይችልም!» አለ እየተጨነቀና እየተከዘ ወደ ቤቱ ተመልሶ ሄደ፡፡ ያየው ለማኝ ዣቬር እንደሆነ ራሱም ማመን አቃተው:: በ ቅዠት እንጂ እውነት አይሆንም ሲል ደመደመ፡፡

ያን እለት ማታ ያየው ሰው ዣቬር እንደሆነ ለማወቅ እንዲችል
ስላላናገረው በጣም ቆጨው:: በሚቀጥለው ቀን ለዓይን ያዝ ሲያደርግ ወደዚያ ሥፍራ ሄደ፡፡ ለማኙ ከተለመደው ሥፍራ ጸሎት የሚያደርስ መስሎ ቁጭ ብሎአል። እንደተለመደው ሣንቲም እየጣለለት «ታዲያስ
ደህና አመሸህ» ሲል ሰላምታ ሰጠው። ለማኙ «እግዚአብሔር ይስጥልኝ ያስንብትልኝ» ብሎ መልስ ከሰጠ በኋላ መፅዋቾቹን ለማየት አሁንም ቀና አለ፡፡ እውነትም ጠዋሪ ያጣ የሽማግሌ ለማኝ እንጂ ዣቬር እንዳልነበረ
አረጋገጠ፡፡

«እኔስ ምን ማለቴ ነው? አሁን ዣቬር ከየት መጣ ብዬ አሰብኩ? ወይ ጉድ! ዓይኔ እየደከመ ነው?» በማለት ካሰላሰለ በኋላ ነገሩን ረሳው::

ከጥቂት ቀናት በኋላ፤ ከምሽቱ ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ ይሆናል፤
ከክፍሉ ውስጥ ኮዜትን የእጅ ጽሑፍ እያለማመደ ሳለ የቤቱ ዋና መግቢያ ያለወትሮው ተከፍቶ ሲዘጋ ሰማ:: እንግዳ ነገር ሆነበት:: ከቤቱ ውስጥ የሚኖሩት እሱ ራሱ፤ ኮዜትና አሮጊትዋ ናቸው:: አሮጊትዋ እንደሆነ ሻማ ለመቆጠብ ስትል ገና ሳይጨልም ነው የምትተኛው:: ኮዜት ዝም እንድትል ምልክት ሰጣት:: በደረጃው ሰው ለመውጣቱ ኮቴ ሰማ፡፡ ምናልባት አሮጊትዋ
ትሆናለች ሲል አሰበ፡፡ አሁንም አዳመጠ፡፡ ከበድ ያላ ኮቴ ስለነበረ የወንድ ኮቴ መሰለው:: ግን አሮጊትዋ የምትጠቀምበት መጫሚያ እኮ በጣም ከባድ
ነው። ሆነም ቀረም ዣን ቫልዣ ሻማውን አጠፋ፡፡
ኮዜት እንድትተኛ ዝቅ ባለ ድምፅ ከነገራት በኋላ ግምባርዋን ሳማት፡
የኮቴው ድምፅ ፀጥ አለ። ዣን ቫልዣ ከነበረበት ሳይነቃነቅ ዝም ብሎ ከቆየ በኋላ ፊቱን ወደ በር ኣዞረ፡፡ አካባቢው ፀጥ እንዳለ ጥቂት ጊዜ አለፈ፡፡ በበሩ
የቁልፍ ቀዳዳ የሻማ መብራት ጭላንጭል አየ:: በዚህም ከበሩ አካባቢ በውጭ በኩል አንድ ሰው ሻማ ይዞ እንደቆመ አረጋገጠ፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በቁልፉ ቀዳዳ ይታይ የነበረው ጭላንጭል ጠፋ፡ ግን ኮቴ አልተስማም:: ዣን ቫልዣ ልብሱን ሳያወልቅ ከአልጋው ላይ
ተጋደመ፡፡ ሆኖም ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ አልወሰደው፡፡
ሊነጋጋ ሲል ትንሽ እንዳሸለበው በር ተከፍቶ ኖሮ በሩ ሲንጣጣ ስ
ቀስቀሰው:: ሌሊት የሰማው ዓይነት ኮቴተ ተንቀሳቀሰ:: የኮቴው ድምፅ በመቃረቡ እየጉላ ሄደ፡፡ ብድግ ብሎ ወደ በር በመሄድ በበሩ ቁልፍ ቀዳዳ ወደ ውጭ ተመለከተ፡፡ ሰፊ ቀዳዳ ስለነበር በደምብ ያሳያል፡፡ አንድ ሰው
በዣን ቫልዣ ክፍል በራፍ አለፈ፡፡ በሩ አጠገብ ሲደርስ አልቆመም፡ ብዙ ብርሃን ስላልነበረ የሰውዬውን ማንነት ለመለየት አልቻለም። የሰውዬው ሙሉ ቁመና ከጀርባው ባየ ጊዜ በጣም ረጅም ሰው መሆኑን ተገነዘበ፡፡
ቅርጹንና የለበሰውን ልብስ ከዣቬር ጋር ሲያስተያየው ተመሳስሉበት፡፡

የመስኮቱን መጋረጃ በመግለጥ በመስኮት ሰውየውን ለመየት ለመመለስ ድፍረት ስላነሰው ተወው፡፡ ይህ ሰው በሩን በቁልፍ ከፍቶ እንደገባ አልተጠራጠረም:: ታዲያ የበሩን ቁልፍ ማን ሰጠው? ምንድነው ነገሩ?

ከጠዋቱ በአንድ ሰዓት መቶ ፍራንክ ከቦርሳው አውጥቶ ካጣጠፈው በኋላ ኪሱ ውስጥ ጨመረው፡፡ እጁን ከኪሱ ሲያወጣ ሣንቲሞች ከኪሱ ሾልከው መሬት በመውደቃቸው አስደነገጡት፡፡ ወደ ምድር ቤት ወርዶ
በድብቅ ውጭውን ተመለከተ፡፡ ጭር ብሏል፤ ማንም በዚያ አካባቢ አይታይም፡፡ ሆኖም በአካባቢው ብዙ ዛፎች ስለነበሩ ማን እንደትደበቀ ለማየት አይቻልም:: ወደ ክፍሉ ተመለሰ፡፡ «ኮዜት ተነሽ» አለ። እጅዋን
ይዞ ተያይዘው ከቤታቸው ወጡ፡፡

በጨለማ የሚሸፍት ድምፅ
የለሽ ውሻ


ዣን ቫልዣ ዋናውን መንገድ ትቶ በመንደር ውስጥ ተጓዘ፡ መንደር
ቆየ ውስጥ የሚታጠፍ መንገድ ካጋጠመው ቀጥታውን ትቶ ይታጠፋል፡፡


ገበሩ ይህንንም ያደረገው ምናልባት የሚከተለው ሰው ካለ ዱካውን ለማጥፋት
ነበር፡፡

ጨረቃዋ ሙሉ ነበረች:: ይህም በመሆኑ ዣን ቫልዣ ደስ አለው።
የጨረቃው ብርሃን ሁሉንም ያሳይ ስለነበረ በተለይ ራቅ ብሎ ሲሄድ ሰው እንዳልተከተለው አረጋገጠ፡፡ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ገደማ በ14ተኛ ፖሊስ ጣቢያ አጠገብ አለፈ:: ከጣቢያው ጥቂት እንደራቀ ማጅራቱን ከበደው፡፡
ፊቱን ወደኋላ አዙሮ ተመለከተ፡፡ የጣቢው መብራት ወገግ ብሉ ይበራ ስለነበር ሦስት ሰዎች እንደሚከተሉት ተገነዘበ፡፡

«ትንሽ ፈጠን በይ ልጄ» አላት ኮዜትን፡፡ ከዚያ አካባቢ ቶሎ ለመጥፋት ፈጠን ኣለ:: ጥቂት እንደተጓዙ ከአደባባይ ደረሱ:: ጨረቃዋ ከፍ በማለትዋ የአደባባዩ አካባቢ ወለል ብሎአል፡፡ እነዚያ ሦስት ሰዎች እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ዣን ቫልዣ ጨለምለም ካለ ከአንድ በር አጠገብ ተሸጉጠ፡፡

ብርሃን ስለነበር ሰዎቹ በኤደባባዩ ሲያልፉ ሊያያቸው ይችላል:: ሰዎቹ ጊዜ አልወሰዱም፤ ወዲያው ከአደባባዩ ደረሰ፡፡ አሁን አንድ ሰው ተጨምሮ አራት ሆኑ፡፡ አራቱም ዱላ ይዘዋል፡፡ ሁሉም ግዙፍ ሰውነት ስለነበራቸው በጣም ያስፈራሉ፡፡

ከአደባባዩ ሲደርሱ ቆም ብለው ይወያዩ ጀመር፡፡ ከመካከላቸው
አንዱ መሪያቸው ሳይሆን አልቀረም፤ ዣን ቫልዣ ወደሔደበት አቅጣጫ አመለከተ፡፡ ሌላው ደግሞ ወደ ሌላው አቅጣጫ በጣቱ በመጠንቆር አሳየ::
የቡድኑ መሪ ወደ አመለከተበት አቅጣጫ ፊቱን ሲያዞር የጨረቃ ብርሃን ከፊቱ ላይ በማረፉ በግልጽ ታየ:: መሪው ዣቬር እንደነበር ዣን ቫልዣ አወቀው::

«ወዴት ይሄድ ይሆን» ሲል ዣን ቫልገ አሰበ፡፡ ሰዎቹ ቆመው
ሲከራከሩ እርሱ ለማምለጥ ፈልጎ ከተደበቀበት ወጥቶ ሳይታይ በአቋራጭ መንገዱን ቀጠለ፡፡ መንገዱ ላይ ሰው አልነበረም:: ፈጠን ፈጠን አለ፡፡ወደኋላ ዞር ብሎ ተመለከተ:: ማንም የለም::

ድልድይ ካለበት ደረሰ፡፡ አንድ ትልቅ እቃ የተጫነ ጋሪ ድልድዩን
ቀስ ብሉ ሲያቋርጥ እየ:: ጋሪው እርሱ ወደሚሄድበት አቅጣጫ ነበር የሚሄደው:: ጋሪውን ከለላ በማድረግ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ጥቂት ከተጓዘ በኋላ ፊቱን አዙሮ ወደኋላ ተመለከተ:: ከሩቁ የአራት ሰዎች ጥላ አየ፡፡ ሰዎቹ ግን በአካል አልታዩትም::
👍17😢4👏2
አዳኝ እንደደረሰባት ድኩላ ሰውነቱ ተረበሸ፧ ተስፋው መነመነ:: ብዙ
ዛፍ ከነበረበት ሜዳ ከደረሰና መንገዱን ካሳበረ እንደሚያመልጣቸው ያውቃል።
ከአንድ ቀጭን መንገድ ስለደረሰ በዚያ ታጥፎ ሩጫውን ቀጠለ፡፡ ጥቂት እንደተጓዘ ከመንታ መንገድ ደረሰ:: ወደቀኝ ይታጠፍ ወይስ ወደ ግራ፣ አላወላወለም፧ ወደ ቀኝ ታጠፈ፡፡ ለምን?

ምክንያቱም ወደ ግራ የሚታጠፈው መንገድ ነዋሪ ወደሌለበት ወደ ገጠር ነበር የሚወስደው::አልፎ ኣልፎ ወደኋላ እየዞረ ያያል፡፡ ሁልጊዜም የሚጓዘlው ብዙ ብርሃን የሌለበትንና ጨለምለም ያለውን መርጦ ነው:: ከኋላ ትቶት የመጣው መንገድ ቀጥ ያለ ነበር:: ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ ወደኋላ ዞር ሲያይ ማንም አልተከተለውም:: ምድሪቱ አሁንም ጸጥ እንዳለች ናት:: ትንሽ
ተንፈስ አለ፤ ጉዞውን ግን አላቆመም:: ጥቂት እንደተጓዘ አሁንም ፊቱን ቢያዞር በሩቁ የሚነቃነቅ ነገር ያየ መሰለው::

ፈብን፧ ፈጠን ብሎ በመሄድ የሚታጠፍ መንገድ ፈለገ::
የሚከተሉትን ሰዎች ለማሳሳት ነበር፡፡ አንድ ትልቅ ግንብ ካለበት ደረሰ: የተጓዘበት ጠባብ መንገድ ግንብ ከነበረበት ሲደርስ አለቀ:: የግንቡን ጥግ ይዞ ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ማለፍ ይቻላል:: አሁንም ዣን ቫልዣ መወሰን ነበረበት፤ ወደ ቀኝ ወይስ ወደ ግራ? ወደ ቀኝ ተመለከተ፡፡ በሩቁ ጠበብ ያለ ጉዳና ታየው:: ከመንገዱ ባሻገር ከነበሩ ፎቅ ቤቶች አጠገብ ያሉት ዛፎች መሸሸጊያ ሊሆኑ ይችላሉ።
ከዚያ ቢደርስ ራሱን ለመደበቅ የሚችል መሰለው::

ከቀጭኑ መንገድ ሲደርስ አሁንም መንገዱ ለሁለት ተከፈለ:: ወደግራ
ሲመለከት አንድ ትልቅ ነጭ ቀለም የተቀባ የግንብ አጥር አየ:: ግንቡ ወደ ሁለት መቶ እርምጃ ቢርቅ ነው፡፡ ግራው መንገድ የሚሻል መሰለው::ወደ ግራ ለመታጠፍ እንደወሰነ አንድ ሀውልት ወይም ሰው መሆነ
የሚያጠራጥር ነገር በሩቁ አየ:: እርሱን ለመከታተል ትእዛዝ ደርሶት
የሚጠባበቅ ሰው መሰለው:: ዣን ቫልዣ ደነገጠ፡፡ መንገዱን ዘግቶ ሰው እንደሚጠብቀው ተረዳ::
ምን ይሻላል?

ወደ ኋላ ለመመለስ ጊዜ የለም:: ዣቬር ከነሠራዊቱ ቶሎ ደርሶ
እንደሚይዘው ጠረጠረ:: ምናልባትም ተቃርበዋል:: እስካሁንም ያጓተተው
የመንገዱ ጠመዝማዛነትና መከፋፈል ሊሆን ይችላል፡፡ ፖሊስ እንደመሆኑ መጠን መግቢያ መውጫውን በሚገባ ያውቀዋል፡፡ በየማለፊያው ሰው አስቀምጦ ይሆናል:: ወደ ሰማይ የተበተነ አዋራ ወደየአቅጣጫው እንደሚተን ሁሉ የዣን ቫልዣም አሳብ እንዲሁ ተበተነ፡፡ ወደፊት መራመድ ማለት ቆሞ ከሚጠብቀው ሰው እጅ መውደቅ ማለት ሆነ:: ወደኋላ መመለስ
ማለት ደግሞ ከዣቬር እጅ መግባት ነው:: ዣን ቫልዣ ቀስ በቀስ በሚጠመጠም ሰንሰለት የተጠፈረ መሰለው:: ተስፋ በመቁረጥ ወደ ሰማይ
አንጋጠጠ፡፡...

💫ይቀጥላል💫
👍19😢12
#ከፍሪጅ_የተጫረ_እሳት


#በአሌክስ_አብርሃም

አዲሳባ ውስጥ ከሚኖሩ ሃምሳ ዱርዬ ሴቶች መካከል የሰላሳ ዘጠኙ ስም ሜሮን ይመስለኝ
ነበር፡ አምስቱ ሄለን አምስቱ ሃያት፣ አንዷ ግን አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ስም እየቀያየረች
የምታጭበረብርና ስሟ የማይታወቅ፤ ቦሌ ቢባል ካዛንችስ፣ ፒያሳ ቢባል አራት ኪሎ፣ ነርስ ብትሆን ሱቅ ጠባቂ፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ብትሆን ሴተኛ አዳሪ…ብቻ ስሟን የምትቀያይር ሴት ነበረች የምትመስለኝ፡፡

አዎ ስሟን እየቀያየረች በአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ስም የምትዶርር (ዱርዬ የምትሆን) ትዕግስት፣ ሳባ፣ ገነት፣ ማርታ፣ መቅደስ፣ ትርሃስ፣ ሐረገወይን፣ ወላንሳ፣ ዙሪያሽ፣ ፍሬ፤ቃልኪዳን፣ ቲቲ፣ መዓዛ፣ ራሄል፣ ሚሚ፣ ሙና፣ አስናቁ፣ ዘሪቱ፣ መንበረ፣ አለምነሽ፣ ያኔት፤ሊና፣ ላራ፣ ሃና አንድ ነጥብ አምስተኛው ላይ ሜሮን ትሆናለች፡፡ እች እስስት !!

እስስት ብያለሁ አዎ !! ስም እኮ ቀለም ነው፤ ሰው ስሙን ሲቀያይር ቀለሙን ለመቀየር መሞከሩ ነው፡፡ እና ጥሩወርቅ ጎጃምኛ ቀለሟን ቀይራ ሊያ ነኝ ስትል ምን እየሆነች ነው? አካባቢዋን እየመሰለች፤ አዲሳስባን እየመሰለች፡፡ እስስትስ ከዚህ የተለየ ምን አደረገች ? ያው አካባቢዋን ለመምሰል ቀለሟን ነው የቀየረችው፡፡ አነጋገርን ለመቀየር የሚደረግ ድካም ምንን ለመቀየር ነውጥ ? ቀለምን ! እናም ሰውና እንስሳት ከሚመሳሰሉስት ባህሪ ዋናው የተጠጉትን መምሰላቸው ይመስለኛል፡፡

ስምንተኛ ክፍል እንደነበርኩ ፍቅር ያዘኝ፡፡ ሜሮን ከምትባል፣ ሁልጊዜ በብዙ ሴት ጓደኞቿ ከምትከበብ ልጅ ደግሞ ስትስቅ ታምራለች ስትኮሳተር ግን ታምራለች፣ አነጋገሬ ተምታታ አይደል ? እንዲህ ነበር የተምታታብኝ !! ቀይ ናት፣ ከቢጫነት ጋር የሚዋሰን ቅላት፡፡ አፏ ሰፋ ያለ ከንፈሯ ቀይና ወደታች ወረድ ብሎ የሆነ “ከምታፈጥ መጥተህ አትስመኝም” ብሎ የሚጣራ ነገረኛ ከንፈር፤ ሕፃን ሆነን አባ ገመቹ አጥር ላይ ተንጠልጥሎ የሚያስጎመዥንን ፕሪም የመሰለ፡፡

የላይ እና የታች ከንፈሮቿ በአንድ ላይ ሲታዩ የሆነ ልብ የሚሰውሩ የልብ ቅርፅ፡፡ ሜሮንን በአይኔ
ሳይሆን በልቤ ነበር የማያት፡፡ ሳያት የልቤ ሽፋሽፍት ይርገበገባል ! በስንት መከራ ያውም ወደ ዘጠነኛ ክፍል ስናልፍ “ሳይሽ የልቤ ሽፋሽፍት ይርገበገባል..” ብዬ ደብዳቤ ፃፍኩላት፡፡ ሄለን እና ሃያት የሚባሉት ጋጠወጥ ጓደኞቿ ጋር በመሆን በዚች ዓረፍተ ነገር ምክንያት ዓመቱን
ሙሉ መሳቂያ መሳለቂያ አደረጉኝ:: መሪያቸው አንዲት ስሟን የማላውቃት አይጠ መጎጥ የመሰለች ልጅ ነበረች፡፡ልክ እኔ ሳልፍ ደረታቸውን በእጆቻቸው እያራገቡ በሳቅ ያውካካሉ፡፡
እይጠ መጎጧ በአካፋ ዓይኗ አሸዋ ወንድ ስትግፍ የምትውል ከንቱ !! ስሟን አላውቀውም፤
ስሟን አስር ጊዜ ትቀያይራለች ስሟ ብዙ ነው፡፡ ሁሉንም ስሞቿን የኢትዮጵያ ቄሶች ሁሉ እየተጋገዙ ይጥሩት !!

የእርሷ ሳቅ ሳቄን ገድሎታል፡፡ የእርሷ የፌዝ ዕይታ ሩቅ እንዳላይ አንገቴን አስደፍቶኛል:: የልብ ሽፋሽፍት የሚል ግጥም ፅፋ ለፀረ ምንትስ ከበብ ዓመታዊ ዝግጅት ሰልፍ ሜዳ ላይ አንብባ 843 ተማሪ ሲባዛ 32 ጥርስ = 26 976 ጥርስ ይርገፍና !! ቆይ የአስተማሪዎቹን ረስቼው ነበር፡፡ ሲደመር 23 ሲባዛ 32 = 736 ሲቀነስ 32 (ቲቸር አንድም ጊዜ አልሳቁም)፡፡

የፍቅር አፒታይቴን” ምድረ ጥርሳም በሳቃቸው ቆልፈውት አስራ ሁለተኛ ክፍል ጨርሼ ዩኒቨርስቲ እስከምገባ ድረስ ሴት የምትባል ፍጥረት አጠገብ ድርሽ ብዬ አላውቅም፡፡ እና ምን ተባልኩ ?ጨዋ !! እንኳንም ያልቀረብኩ !! ምናቸው ይቀራል? ያች አይጠ መጎጥ፣ አስቀያሚ፣ ጥርሳም፣ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ስማም ! ዛሬ የራሷ አንድ ስም እንኳን ጠፍቶ ማንም አንቺ
የሚላት የካፍቴሪያ አስተናጋጅ ሆናለች፡፡ ሻይ አዞ ስሙኒ ጉርሻ ለተወላት ሰብለ፤ ቡና ጠጥቶ ለገለፈጠላት ናኒ እየሆነች እስስቷ የስሟን ቀለም እየቀያየረች አለች፡፡ ብር ዛፍ ቁርስ ቤት ሳልፍ ሳገድም ከነቀይ ሽርጧ አያታለሁ

ዩኒቨርስቲ የተመደብኩት እዚሁ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነበር፡፡ ደስ አላለኝም፡፡ ምክንያቱም ከአዲስ አበባ ውጭ ከወላጅ ራቅ ብዬ የመኖር የቆየ ፍላጎቴ ተሰናክሏልና፡፡ አስከፊው ነገር
ደግሞ ዩኒቨርስቲው “የአዲስ አበባ ልጆች እየተመላለሳችሁ ተማሩ በቂ መኝታ የለኝም አለ ይሄ ደግሞ ዩኒቨርስቲና ሃይ ስኩል የሚለያዩበትን አንድ ድንበር አፈራረሰው፡፡ ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የገባሁ አልመስልህ አለኝ፡፡ ወደ አስራ ሶስተኛ ክፍል ያለፍኩና እዛው የነበርኩበት ትምህርት ቤት የቀጠልኩ አይነት ስሜት ነበር የተሰማኝ፡፡ ያ ሁሉ የተወራለት፣ በፊልም እና በሰመመን መጽሐፍ ብዙ የተባለለት የዩኒቨርስቲ ሕይወት፣ ላየው የጓጓሁለት “የግቢ ላይፍ ውሃ በላው !! ወይ ነዶ! አንድ አራት ወር እየተመላለስኩ እንደተማርኩ እዛው ዩኒቨርስቲው አካባቢ ቤት ተከራይቼ ለመማር ወሰንኩ፡፡ ምንም አስቤ ሳይሆን የአዲስ አበባ ታክሲ ጊዜዬን እየበላብኝ ስለተቸገርኩ ነበር፡፡ ማንም አልተከራከረኝም፤ ዩኒቨርስቲው ከሚወረውርልኝ ሳንቲም ላይ ቤተሰብ በየወሩ ድጎማ እየመረቀበት ቤት ተከራየሁ፡፡ድከም ያለች ቤት አንድ ሰፈር ውስጥ፡፡ እንግዲህ የእኔ
ቤትና ከጎኔ ያሉት ጭርንቁስ ቤቶች በመደዳ የተሰለፉ ነበሩ ፊት ለፊት ደግሞ ፊታቸውን
ወደ እኔ ቤት ያዞሩ ስስሪትም፣ በመጠንም ከእኔ ቤት ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ሌላ መደዳ ቤቶች አሉ፡፡ መስኮቴን ስከፍት ፊት ለፊት ያለው ቤት መስኮት ጋር እፋጠጣለሁ፡፡ በሬን ስከፍት ፊት
ለፊት ካለ በር ጋር ! በሁለቱ መደዳ ቤቶች መካከል ቀጭን የእግር መንገድ አለች፡፡ የእኔ ቤትና ፊት ለፊቴ ያለው ቤት ጣራቸው ሊገጣጠም ምንም ያህል ስለማይቀረው በመካከላችን በቀጭኗ የእግር መንገድ የሚያልፍ ሰው ረዥም ኮሪደር ውስጥ የሚያልፍ ሊመስለው ይችላል፡፡ ከበሬ ላይ አንድ ጠቀም ያለ ርምጃ ወደፊት ብራመድ ፊት ለፊት ያለው ቤት በር ላይ አርፋለሁ፡፡ ይሄ ነው የተከራየሁት ቤት::

ሜሮንን ትሻግሮ ሜሮን አለች ወይ…

በአንድ ርምጃ ርቀት ጣራዬ፣ ከጣራው የሚነካካው ቤት ውስጥ ፊት ለፊቴ 'ሜሮን' የምትባል
ልጅ መኖሯን ያወቅኩት ቤቱን በተከራየሁ በሁለተኛው ቀን ነበር፡፡ በጊዜና ቦታ ርቀት ትቼ የመጣሁት “ሜሮን” የሚባል እንደ ጥላ የሚከተል ስም እዚህም መጣ፡፡ ሜሮን ሜሪ ሜሪቾ ሜሪዬ…ይላታል የመንደሩ ሰው፡፡ ጥቁር ትሁን ቀይ አይቻት አላውቅም ነበር፡፡ ለሰባት ወራት
ያህል ጧት እየወጣሁ፣ ማታ እየገባሁ በሰላም ኖርኩ፡፡

በአንድ ጠራራ የግንቦት ቀን ከክላስ ወደ ቤቴ እየገባሁ ነበር፡፡ የፀሐዩ ቃጠሎ ከንፈሬን ሁሉ
አድርቆታል፤ ሰውነቴ ሁሉ የተነነ ነው የመሰለኝ፡፡ ድርቅ የመታኝ !! ቀዝቃዛ ውሃ ለመግዛት ጫፍ ላይ ወዳለች ኪዮስክ ሄድኩና “ቀዝቃዛ ውሃ ስጭኝ እስቲ” ብዬ አስር ብር ባለሰሃኑ
ሚዛን ላይ ጣል አደረግኩላት፡፡ አስር ብሩ ሚዛኑ ላይ ሲያርፍ ሚዛኑን ዝቅ አላደረገው ከፍ…

“ቀዝቃዛ የለም !” አለች እስር ብሩን በእጇ ይዛ፣
"እሽ ቀዝቃዛ ኮካ”
“ቀዝቃዛ ኮካም የለም ከውጭ ልስጥህ ?” አለች፣
ቀዝቃዛ ነገር ምንድን ነው ያለሽ ?”
“ፍሪጅ የለኝም ከውጭ ነው ሁሉም !”
“ተይው በቃ !” ብዬ ብሬን ልቀበል እጄን ዘረጋሁ፡፡ ቅር እያላት ብሬን መለሰችልኝ፡፡ ፊቴን ኮሰኮስኩ በጣም ነበር የተበሳጨሁት፡፡ ኤጭ!!
👍33
ቤቴ ገብቼ ቱታ ቀየርኩና ፍራሹ ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ በእፎይታ ተነፈስኩ፡፡ ወዲያው በር
ሲንኳኳ በግርምት ወደበሩ ተመለከትኩ፡፡ ጆሮዬን አቁሜ ብጠብቅም ምንም ድመፅ አልነበረም መልሼ ጋደም ልል ስል በድጋሜ ተንኳኳ፤ በቀስታ ! ላለፉት ሰባት ወራት አንድም ጊዜ በሬ ተንኳኩቶ ስለማያውቅ ተገረምኩ፡፡ “ማነው?” አላልኩም፡፡ በቀጥታ ሄጄ ከፈትኩት፡፡ አንዲት
ስለሚታይ ቅዝቃዜው ያስጎመዣል፡፡ ምራቄን ዋጥኩ እና ልጅቱን አየኋት፡፡ እሷም ታስጎመዥለች፣ሬራ
እሷን እንደመድኃኒት ውጦ በያዘችው ውሃ ማወራረድ ነበር!

እየፈራች “ሱቅ ውሃ ጠይቀህ ስላጣህ ከቤት አምጥቼልህ ነው"አለችኝና ውሃውን ዘረጋችልኝ፡፡
ሳላንገራግር ተቀበልኳት፡፡ 'ቴንኪው የለ ! ምን የለ !

ቆንጆ ነች !በጣም ቆንጆ ነች !በተለይ ዓይኗ፣ በተለይ ጥቁር የሚያብረቀርቅ ፀጉሯ ከቁጥርጥሩ ገና የተፈታ እንደሆነ ያስታውቃል፡፡ በተለይ ደግሞ ጡቷ ! የለበሰችውን ስስ ቦዲ ስሸካክቶ ሊተኮስ የተሰናዳ የሆነ ተተኳሽ ነገር !! በተለይ ደግሞ ሁሉም ነገሯ፡፡

የተጋለጠ ደረቷ ማር የተንጣለለበት ሜዳ ይመስላል፡፡ ቆንጆ ነበረች፣ ግን ልጅ ነበረች፤ ቢበዛ አስራ ስድስት ቢሆናት ነው፡፡ ዞር ስትል መቀመጫዋንም አይቻለሁ...(ለምን ይደበቃል?)፡፡
ለአስራ ስድስት ዓመት ልጅ ይበዛል፤ ግን ቆንጆ ቆንጆ እና ልጅ፣ ቆንጆ ልጅ !! እንትፍ ትፍ
ትፍ እደጊ ! መቼም አዲሳባ ቆንጆ እያጣመመ ነው የሚያሳድገው !! ለማንኛውም እደጊ !!

ከእኔ በር ወደ ራሷ ቤት ስትሄድ እኔም ውብ ሰውነቷን ቆሜ ስገመግም አንድ መንገደኛ
ሜሪ !” አላት፤ እርፍ !! ሜሮን ናት ለካ !! በፍቅር ውሃ ጥም ለዓመታት ያደረቀችኝ ሜሮን የምትባል ደረቅ ወንዝ ተሻግሬ በቀዝቃዛ ውሃ ጥሜን የምታስታግስ ሜሮን የምትባል ጅረት ላይ ደረስኩ፡፡

ሜሮንን ተሻግሮ ሜሮን እለች ወይ
ሞትና ውሃ ጥም አንድ አይደለም ወይ፡፡

እየጠጣህ አብርሽ ! ብዬ ራሴን ጋበዝኩት፡፡ ቀዝቃዛውን ላንደቀድቀው ነበር፤ ግን ገና አንዴ
ስጎነጭለት ጥርሶቼ ሁሉ ጠፉኝ፤ ቦታቸው ላይ ደነዘዙ፤ ምን እዳ ነው ! ልብም ጥርስም ደንዝዞ
የት ይደረሳል !? ጥርስ የሌለው ልበ ቢስ አንበሳ የሆንኩ መሰለኝ፣ ቢሆንም አንድ የተለኮስ
ነገር ነበር፡፡

ፍሪጅ እና ቦኖ ውሃ በምን ይለያያል !?

ሜሮን ትላንት ያመጣችልኝን ጆግ ልትወስድ ስትመጣ ፈገግ ብዬ ተቀበልኳት፡፡ ባዶዋን አልነበረችም፡፡ ሌላ ጆግ ሙሉ ቀዝቃዛ ውሃ ሰጥታኝ ባዶ ጆግ ወሰደች፡፡ .…ጆግ ውሃ .ጆግ
ውሃ ፤ ከብዙ የጆግና ውሃ ምልልስ በኋላ ተቀራረብን፡፡
“የት ነው የምትማሪው ?
“ሚኒሊክ…” ጆግ ውሃ …ጆግ ውሃ…

"አሳይመንት ተሰጥቶኝ ነበር ጊዜ ካለህ ትሰራልኛለህ ?”

አምጭው ኧረ !” ብጥርጥር አድርጌ ሰራሁላት፣ አስረዳኋት፤…አንዴዴዴዴ! እንዲህ አይነት
አደገኛ አስተማሪ ነበርኩ እንዴ ለካ !

ጆግ.ውሃ ጆግ..ዉሃ እና አንድ ቀን ለስላሳ ቀዝቅዝ ያለ ሚሪንዳ !!

“የምን ለስላሳ ነው ሜሮን ?”

“ታዘብኩህ ዛሬ ልደቴ ነበር፣ 16 አመቴ፤ ሃፒ በርዝደይ! ሳትለኝ” ፈገግ ብላ፡፡

“በቃ ቅዳሜ ራሴ አከብርልሻለሁ”

“ፕሮሚስ ?!” ብላ የሚያምር መዳፏን በጉጉት ዘረጋችልኝ፤ ፊቷ በፈገግታ ተጥለቅልቆ ነበር፡፡

“ፕሮሚስ !” ብዬ መዳፌን መዳፏ ላይ አስቀመጥኩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ መነካካታችን ነበር !!
እጄን አልሰበሰሰችም፤ እኔም እጄን አላነሳሁም፡፡ እግዜር መሃላውን እስካፀድቀው እጃችሁን
እንዳለ ሳይለያይ አቆዩት!” ያለን ነበር የምንመስለው፡፡ ዓይኗ ውስጥ ፀሐይ አየሁ፤ ሁለት ፀሐይ!አማረችኝ፡፡ የሆነ የሚያምር መናፈሻ መሰለችኝ፡፡ ውስጧ እረፍት የተዘራ፡፡ ሲደከም ለኖረ
አንድ እኔ ሰፊ አልጋና እረፍት ያለባት አገር፡፡

ጆግ ውሃ ጆግ ውሃ ቅዳሜ ሆነ !!

ከማክሰኞ እለከ አርብ ያላሰብኩትን ቅዳሜ ጧት ተጨነቅኩ፡፡ የእስራ ስድስት ዓመት ልጅ ይዤ የት አባቴ ነው የምጋብዛት ? ..ቤተሰቦቿስ ምን ይላሉ? (ለነገሩ ሴት አያቷ እና እሷ ብቻ ናቸው የሚኖሩት) .. ቢሆንም ጎረቤቱስ ምን ይላል?…ወይ ጉድ !

ሜሮን በጧት መጣች፤ ተኝታም ያደረች አልመሰለኝም፡፡

“አንተ እስካሁን ተኝተሃል !?” አለችኝና የተኛሁበት ፍራሹ ጫፍ ላይ ተቀመጠች፡፡ ቤቴ መግባት
ፍራሽም ላይ መቀመጥ ጀምራለች፡፡ ጧት ስትመጣ ደስ አይለኝም፤ ስስ ፒጃማ ቁምጣና
ባለማንገቻ ጉርድ ቦዲ ስለምትለብስ እፈተናለሁ፡፡ በዛ ላይ በጣም ተጠጋግተን ስለምንቀመጥ ጠረኗ አፍንጫዬን ይዞ ወደ ጡቶቿ መሃል ይጎትተኛል፡፡ ፈተና ነው በቃ !…እርሷ ደግሞ በፍፁም "ንጹህ ልብ እንደፈለገች ትሆናለች፡፡

በቃሌ መሰረት ልደቷን ልናከብር ተቀጣጠርን፡፡ ከሰፈር አብረን መውጣቱ ለጎረቤት ሃሜት
ስለሚዳርግ የሆነ እሷ የመረጠችው ሬስቶራንት ስምንት ሰዓት ላይ እንገናኝ ተባባልን፡፡....


ነገ ያልቃል
👍312
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


...ጫጫታ ከሩቅ ተሰማ:: ዣን ቫልዣ አንዱን ቤት ተጠግቶ ለመደበቅ ፈለገ፡፡ ከሩቅ የሚንቀሳቀስ ጥላ ተመለከተ:: ሰዎች ወደ እርሱ ማምራታቸውን
ተገነዘበ፡፡ ተንጠላጥሎ ድምፅ ወደሚሰማበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ የዣቬርን ግዙፍ ሰውነት መለየት አላዳገተውም፡፡ በፖሊስ ጥንቃቄ ግራና ቀኝ እያዩ
መራመዳቸውን ተመለከተ፡፡ ቆም እያሉ፣ አካባቢውን እየሰለሉ ነው
የሚሄዱት፡፡ የመደበቂያ ሥፍራ እንዳለ ኣጥርተው እንደሚፈትሹ
ያስታውቃል፡፡ ሰፈሩ ማምለጫ መንገድ የለውም::

በዚያ አካሄዳቸው ሥፍራውን እየፈተሹ ሲመጡ ዣን ቫልዣ
ከነበረበት ለመድረስ ምናልባት ሩብ ሰዓት ቢወስድባቸው ነው:: እጅግ በጣም የሚያስጨንቅ ሰዓት ነበር፡፡ በሕይወቱ ዘመን ለሦስተኛ ጊዜ ከአስፈሪ
ሕይወት ጫፍ ላይ የደረሰ መሰለው፡፡ አሁን ያስጨነቀው የእስር ቤት ኑሮ ብቻ ሳይሆን የኮዜት ከእርሱ መለየት ጭምር ነበር፡፡ ሁለት አማራጭ ነበረው፤ የመለኮት ኃይል አውጣኝ ብሎ መማጠን ወይም ባለው ጉልበት
ተጠቅሞ ሰዎቹን መጋፈጥ፡፡
እስር ቤት ባገኘው ልምድ ዣን ቫልዣ ቀጥ ካለ ግንብ፧ ቁመቱ እንደ ፈለገው ቢረዝም እንኳን፤ በቀላሉ የመውጣት ችሎታ አለው:: ከፊት ለፊቱ የነበረውን ግንብ ርዝማኔ በዓይኑ መተረው:: ወደ አምስት ሜትር ገደማ ይሆናል፡፡ በተጠረበ ድንጋይ የተሠራ ግንብ ነበር፡፡
አሁን የምታስቸግረው ኮዜት ስትሆን ኮዜት ከግንብ ላይ መውጣት አታውቅበትም:: ታዲያ ይተዋት? አሳቡ አንገሸገሸው:: እርስዋን ተሸክሞ መውጣት ደግሞ የማይቻል ነው፡፡

መፍትሔው ትልቅ ገመድ እንደሆነ ተገነዘበ፡፡ ግን ዣን ቫልዣ
ገመድ አልነበረውም:: ታዲያ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ገመድ ከየት ሊያመጣ ይችላል? በዚያች ሰዓት ዣን ቫልዣ አገረ ገዢ ቢሆን ግዛቱን በአንድ ወፍራምና ረጅም ገመድ ይለውጥ ነበር፡፡

የሚደንቀው አንዳንድ ጊዜ በጭንቀት ሰዓት የሚያስገርም ወይም ዐለማመን የሚያስቸግር ነገር ይሆናል:: ቫንቫልዣ ግራና ቀኙን ሲቃኝ መብራት የተንጠለጠለበት ገመድ አየ:: በዚያን ብርሃን ባልነበረበት ዘመን በጋዝ የሚሠሩ መብራቶች ከፍ አድርገውና የሚሰቅሉትና የሚያወርዱት በወፍራምና በረጅም ገመድ ነበር፡፡

ዣን ቫልዣ ገመዱ ወደ ተንጠለጠለበት ሮጦ በያዘው ቢላዋ ቆረጠው።ቀደም ሲል እንደተገለጸው በተለይ ያን ምሽት ጨረቃዋ ሙለ ስለነበረች
የመንገድ መብራቶች አልተለኩሰም:: ስለዚህ ዣን ቫልዣ ገመዱን ሲቆርጥ ምናልባት መብራቱ ቢሰበር ልብ የሚለው አልነበረም:: ኣካባቢውም ጭር
ያለ ነበር፡፡ዣን ቫልዣ ከወዲህ ወዲያ ሲሮጥ፤ ዓይኑ ሲቅበዘበዝ አሳብ ሲያስጨንቀው በማየትዋ ኮዜት ደነገጠች:: እርስዋ በመሆንዋ እንጂ ሌላ
ልጅ ብትሆንማ ልቅሶዋን ነበር የምትለቅቀው፡፡ የኮቱን ጭራ አጥብቃ ይዛ ዝም ብላ ነበር የምትከተለው፡፡ በአካባቢው የሚሰማው ድምፅ እየጎላ መጣ።

«አባባ» አለች ኮዜት በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ፤ «ፈራሁ፤ ማነው
የመጣው?

«ዝም በይ፤ ዝም በይ» አለ የተከፋው ሰው፤ «ሚስስ ቴናድዬ
ናት፡፡»

የኮዜት ሰውነት በፍርሃት ተንቀጠቀጠ! ሰውዬው ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አይዞሽ እኔ አለሁልሽ፤ ግን ዝም ነው፤ ካለቀስሽ ወይም ድምፅ ካለማሽ ሚስስ ቴናድዬ ትሰማሻለች፡፡ አንቺን ፍለጋ ነው የመጣችው::»

ዣቬርና ሌሎች ፖሊሶች እነርሱ ከነበሩበት ደርሰው ሊይዟቸው
ስለሚችሉ ጊዜ ማባከኑ ይበልጥ የሚያጋልጥ መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ከረባቱን አውልቆ በከረባቱ የኮዜትን ወገብ አሰረ:: ጫማውንና ካልሲውን አውልቆ ከግንቡ ላይ ወረወረ፡፡ የገመዱን አንዱን ጫፍ ከቋጠረ በኋላ ከኮዜት ወገብ
ላይ ከታሠረው ከረባት ጋር አሰረው:: ከዚያ በኋላ የገመዱን አንድ ጫፍ በእጁ ይዞ ከግንቡ ላይ መውጣት ጀመረ:: ኮዜት ከመሬት ሆና ዝም ብላ ታየዋለች:: የሚስስ ቴናድዬ ስም በመጠቀሱ በጣም ስለደነገጠች ለመናገር
ብትፈልግ እንኳን መናገር አትችልም::

ብዙ አልቆየም ወዲያው እጅግ ዝቅ ባለ ድምፅ ዣን ቫልዣ ሲጠራት ሰማች::

«ጀርባሽን ለግድግዳ ስጪ፡፡»

እንዳዘዛት አደረገች::

«እንዳትናገሪ፧ እንዳትፈሪ» አለ ዣን ቫልዣ ቀጠለና፡፡

ከግንቡ ጫፍ ደረሰች:: ወዲያው ዣን ቫልዣ እቅፍ አደረገና በጀርባው መሬት ለቅቃ ስትንጠለጠል ታወቃት፡፡ የት እንዳለች ሳታውቅ አዘላት:: እጆችዋን በግራ እጁ ያዘ፡፡ እንደገመተው ከግንቡ ኋላ ቤቶች
ነበሩ። በውስጥ በኩል የግንቡ ርቀት እስከዚህም ሩቅ አልነበረም:: ርቀቱን በዓይኑ መተረው፡፡

ልጅትዋን እንዳዘለ በቀላሉ ከአንድ ቤት ጣራ ላይ ለማረፍ ቻለ::

ከላይ ሆኖ ከአጥሩ ውጭ የዣቬርን ድምፅ ሰማ፡፡

«በየመንገዱ ፣ በየሥርቻው ቶሎ ብላችሁ ፈልጉት፡፡ በየቤቱ
እየገባችሁ ፈልጉ፡፡ ስለሚደርሰው ነገር እኔ አልፋለሁ» አለ ዣቬር እየጮኸ

ዣን ቫልዣ ከጣራው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ኮዜትን በገመዱ አንጠልጥሉ የዛፍ ግንድ ይዛ በመውረድ መሬት እስክትደርስ ጠበቃት፡፡ ኮዜት ጎብዛም
ይሁን ፈርታ ቃል አልተነፈሰችም:: እጅዋን ሲጨብጣት ግን በጣም አልቦአት ነበር፡፡

ዣን ቫልዣ ከጣራ ወርዶ ሲጓዝ ከአንድ የአትክልት ቦታ ደረሰ
አካባቢው በጣም ጭር ያለ ነበር፡፡ በመጀመሪያ ጫማውንና ካልሲው
መፈለግ ነበረበት፡፡ ጫማውን ፈልጎ ካጠለቀ በኋላ ከኮዜት ጋር ከዛፍ ስር ተቀመጡ፡፡ ምንጊዜም ቢሆን የሚሸሽ ሰው ያመለጠ ስለማይመስለው ሁልጊዜም እንደ ደነገጠ ነው፡፡ ኮዜት ስለፈራች ከጎኑ ተሸጉጠች:: እነዣቬር ከሁንም ሲጠራሩ አሁንም ይሰማል፡፡ ግን ከሩብ ሰዓት በኋላ ድምፁ እየደከመ ሄደ
ቢሆንም የዣን ቫልዣ ልብ አሁንም አልረጋም፡፡ ኮዜትም ዝምታዋን ቀጠለች ከዚህ መጣ የማይባል ድምዕ በድንገት ተሰማ:: የደናግል ዝማሪ ነበር፡፡ ደናግል ተሰባስበው የሚዘምሩት አትክልት ውስጥ ነበር፡፡ ድምጻቸው ጥርት ብሎ ነው የሚሰማው:: ዣን ቫልዣ ይህን ድምፅ ሲሰማ የድምፁ።
አቅጣጫ ፍለጋ ዞር አለ፡፡

ፊቱን ሲያዞር ከአትክልቱ ውስጥ ሰው መኖሩን አየ:: አንድ ሰው
ጎንበስ ቀና ይላል፡፡ ሰውዬው ሥራ ይዞ መሆን አለበት፧ እቃ ከአንድ
ሥፍራ አንስቶ ወደ ሌላ ቦታ እንደሚወስድ ሰው ጎንበስ ይልና ቀና ብሎ ጥቂት ይራመዳል፡፡ ተመልሶ መጥቶ ጎንበስ ይልና ቀና ብሉ ይሄዳል።

ዣን ቫልዣ ደነገጠ፡፡ ምናልባት ዣቬርና ተከታዮቹ እዚህም ጠባቂ
ያስቀመጡ መሰለው:: ይህ ሰው የእነርሱ አባል ከሆነ «ሌባ፤ ሌባ» እያለ ቢያሲዘኝስ ሲል አሰበ፡፡ የተኛችውን ኮዜት ቀስ ብሎ አንስቶ ግቢው ውስጥ ከነበረው አሮጌ አግዳሚ መቀመጫ ላይ አሳረፋት:: ኮዜት አልነቃችም፡፡
ከኮዜት አጠገብ ተቀምጦ የሰውዬውን እንቅስቃሴ ተከታተለ፡
የቃጭል ድምፅ ይሰማል፡፡ ሰውዬው አንድ ነገር ለማንሳት ጎንበስ ሲል ቃጭሉ ሲቃጨል እኩል ስለመጣ ዣን ቫልዣ ይህ አጋጣሚ ይቀጥል!እንደሆነ ጠበቀ፡፡ አሁንም እኩል መጣ፤ ጨርሶ አልተዛባም:: ሰውዬው
ሲንቀሳቀስ ቃሉ ድምፅ ያሰማል፡፡ ሲቆም ዝም ይላል፡፡ የሚደንቀው!
ደግሞ ሰውዬው ሥራውን ጨርሶ ሲያርፍ ደወሉም ፀጥ ይላል፡፡ የደወሉ ገመድ ከሰውዬው ወገብ ላይ ታስሮ ይሆን?» ሲል አሰበ፡፡
ይህን እያሰላሰለ የኮዜትን እጅ አሻሽ፡፡ እንደበረዶ ቀዝቅዟል፡፡
👍19🔥2🥰1
“ምን ይሻላል?» ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
«ኮዜት» ሲል በለሰለሰ ድምዕ ጠራት::
ዓይንዋን አልገለጠችም፡፡ ቀስ ብሎ ወገብዋን ይዞ ነቅነቅ አደረጋት፡፡
«እንዴ፤ ይህቺ ልጅ ሕይወትዋ ከሥጋዋ ተለየ እንዴ?» ሲል
በድንጋጤ ከተቀመጠበት ብድግ አለ::
አልጋ ላይ እንደተኛ ሰው እግርዋን ዘርራ ነው የተኛችው:: ትንፋሽዋን
አዳመጠ፤ ትተነፍሳለች፡፡ ሕይወቱ መለስ አለች፡፡ ብርዱ ሊጎዳት እንደሚችል ያውቃል፡፡ «ምን ላልብሳት? በምን ላማሙቃት? በብርድ ልትሞት ነው»
ሲል አሰላሰለ፡፡ ከነበረበት ጥቂት ተራምዶ ከሥፍራው ፈቀቅ አለ:: የብርድ ልብስ ያገኝ ይመስል ዓይኑ ተቅበዘበዘ፡፡ በቶሎ ኮዜት ከቤት ውስጥ ገብታ ቢቻል እሳት መሞቅ እንዳለባት አስተዋለ፡፡
በቀጥታ ሲንቀሳቀስ ወዳየው ሰውዬ ሄደ፡፡ ከሰደርያው ኪስ ውስጥ ጠቅልሎ ያስቀመጠውን ገንዘብ አወጣ፡፡ ሰውዬው አጎንብሶ ይሠራ ስለነበር ወደ እርሱ የሚመጣውን ዣን ቫልዣን አላየውም:: ዣን ቫልዣ ሰውዬው
ከነበረበት ደረሰ፡፡
ዣን ቫልዣ ጠጋ ብሉ «መቶ ፍራንክ› ሲል ተናገረ:: ሰውዬው
ደንግጦ ቀና አለ፡፡
«ካሳደርከኝ መቶ ፍራንክ እከፍላለሁ» አለ ዣን ቫልዣ፡፡
ከዣን ቫልዣ ፊት ላይ የጨረቃ ብርሃን አርፎ ነበር፡፡
«እንዴ፤ አባታችን ማንደላይን፤ ከእዚህ ምን ትሠራለህ?» ሲል
ሰውዬው ጠየቀው፡፡
በዚያ ጨለማ፤ በዚህ ባልታወቀ ቦታ፤ በዚህ በማይታወቅ ሰው ይህ
ስም ሲጠራ በመስማቱ ዣን ቫልዣ ወደኋላ ሸሽት አለ፡፡
ሰውዬው ያጠለቀውን ቆብ ብድግ አደርጎ እጅ ነሳው።
“ቁጭ በል! ቁጭ በል! ቤት ለእንግዳ:: ግን አባታችን እዚህ እንዴት መጣህ? እንዴ፤ ደግሞ ከዚህ ግቢ ውስጥ እንዴት ልትገባ ቻልክ? ከሰማይ ነው የወረድከው ወይስ ከምድር ነው የፈለቅከው?» ሲል በጥያቄ አጣደፈው::
ማን ነዎት እርስዎ? ቤቱስ የማነው? » ሲል ዣን ቫልዣ ሰውዬውን ጠየቃቸው::

«በጣም ነው ደስ ያለኝ» አሉ ሽማግሌው:: «አንተ እኮ ነህ ከዚህ ያስገባኸኝ:: ይህን ቤት ደግሞ አንተ ነህ ያሰጠኸኝ፡፡ እንዴ! እንዴት ይሆናል፧
አታስታውሰኝም?»
«ይቅርታ፧ አላስታወስኩም ኣላ ዣን ቫልዣ :: «የት ነው !
የምንተዋወቀው?»
«ሕይወቴን እኮ አድነሃታል» አለ ሰውዬው::
ዣን ቫልዣ አሁን ትዝ አለው፡፡ የሽማግሌውን ፊት አስተዋለ::
እኚያ የጭነት ጋሪ ተጭኖዋቸው ሊሞቱ ሲሉ ከጋሪው እግር ፈልቅቆ
ያወጣቸው ሰው መሆናቸውን አወቀ፡፡
«ለካ እርስዎ ነዎት!» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «አሁን አስታወስኩ ሚስተር ፎሽለማ ነዎት፤ አይደለም?»
«ጥሩ አጋጣሚ ነው» አሉ ሽማግሌው::
«እርስዎስ ከዚህ ምን ይሠራሉ?» ሲል ዣን ቫልዣ ጠየቀ፡፡
«ከዚህ ሥራ እየሠራሁ ነው፤ አንተስ ምን ትሠራለህ?» አሉ ቀጠሉና።
ዣን ቫልዣ በቀድሞ ስሙ እየጠራ የሚያናግረውና የሚያውቀው
ሰው በማግኘቱ ጥቂት ተዝናና፡፡ የእንግዳ ዓይን አውጣ እንደ መጠየቅ እርሱ ጥያቄ ያበዛል፡፡
«ጉልበትዎ ላይ ያሰሩት ደወል ምንድነው?»
«እሱማ» አሉ ሽማግሌው፧ «መምጣቴን አውቀው ከእኔ እንዲሸሹ ድምፅ የማሰማበት መሣሪያ ነው፡፡»
«ከእኔ እንዲሸሹ?»
አዎንታቸውን ለመግለጽ ሽማግሌው ግንባራቸውን ወደ ላይ ሳብ አደረጉ፡፡
«ከዚህ ግቢ ውስጥ ያለው ከእኔ በስተቀር ሁሉም ሴት ነው:: ወጣት
ልጃገረዶች በብዛት አሉ፡፡ ከእኔ ጋር መገናኘቱ አደገኛ ነው መሰለኝ፤ ደወለ ለመምጣቴ ማስጠንቀቂያ ነው:: እኔ ስደርስ ይሸሽጋሉ፡፡»
«ቤቱ የኔ ነው?»
«ምነው፧ ታውቀው የለም እንዴ?»
«የለም፤ አላውቀውም፡፡»
«ምነው፧ አንተ አይደለህም እንዴ በአትክልተኝነት ተቀጥሬ እንድሠራ
ያደረግኸው:: »
«ለምጠይቀው ጥያቄ ምንም አያውቅም ብለው በመገመት መልስ ይስጡኝ።»
«አንተ ካልክ እሺ፡፡ ይህ ገዳም እኮ በዚያን ጊዜ የፐቲ ፔክፐስ ገዳም ነበር የሚባለው፡፡»

ዣን ቫልዣ አስታወሰ፡፡ በአጋጣሚ ከሚያውቀው ገዳም መግባቱን
ተገነዘበ፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት ሽማግሌው የእቃ መጫኛ ጋሪ ወድቆባቸው እያለ የአካል ጉዳት ስለደረሰባቸው በአትክልተኝነት ገዳሙ እንዲቀጥራቸው
የድጋፍ ደብዳቤ ጽፎላቸው ነበር፡፡ የድጋፉ ደብዳቤ ነው እንዲቀጠሩ
የረዳቸው፡፡

«የፐቲ ፔክፐስ ገዳም» አለ ዣን ቫልዣ እርስ በራሱ ይነጋገር
ይመስል፡፡
«እንዴት ኣድርገህ ከዚህ ልትገባ እንደቻልክ ንገረኝ እንጂ ፤ ሰው
ስለሆንክ መልአክ ለመሆን አትችልም፡፡ በምንም መንገድ ደግሞ ወንድ ከዚህ ገዳም እንዲገባ አይፈቀድም፡፡»
«ይኸው እርስዎ ከዚህ ይኖሩ የለ!»
«ያለ እኔ እኮ ሌላ ወንድ የለም::»
«ግን» ኣለ ዣን ቫልዣ ከዚህ መኖር አለብኝ፡፡»
«ያንተ አለህ!» ሲሉ ሚስተር ፎሽለማ በመደነቅ ዓይነት ተናገሩ፡፡
ዣን ቫልዣ ወደ ሽማግሌው ጠጋ ብሉ ዝቅ ባለ ድምፅ «ምነው
ሕይወትዎን ማዳኔን ረሱት?» አላቸው::
«መዘንጋት አልነበረብኝም» አሉ ሚስተር ፎሽለማ፡፡
«እንግዲያውማ እኔ ለእርስዎ ያደረግሁትን ዛሬ እርስዎ ለእኔ ማድረግ ይኖርብዎታል፡፡›
ፎሽለማ በተጨማደደ እጃቸው የሚንቀጠቀጠውን የዣን ቫልዣን
እጅ ያዙ፡፡ ለጥቂት ሰኮንድ እጁን እንደያዘ ዝም ብለው ቆሙ:: በመጨረሻ፡-
«እኔ ለአንተ አንድ ነገር ማድረግ ከቻልኩ እግዚአብሔር ባረከኝ፣
ቀደሰኝ ማለት ነው:: የአንተ ውለታ እኮ ተከፍሎ የሚያልቅ አይደለም::
ሕይወትህን አድንልሃለሁ! ክቡር ከንቲባ ፤ ሽማግሌው በአንተ ቁጥጥር ሥር ነው:: ››

ሽማግሌወ ይህን ሲናገሩ በጣም ደስ እያላቸው ነበር:: ለዚህ
በመብቃታቸው መንፈሳቸው ረካ፡፡ ለመደሰታቸው ፊታቸው መሰከረ።
ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?» አሉ ቀጥለው::
«ግድ የለም አስረዳዎታለሁ፡፡ አንድ ክፍል አለዎት?
«ከዚያ ጥግ አንዲት የማትረባ ክፍል አለች፡፡ ግን ሰው የሚኖርባትም አትመስል፡፡ እኔ ያለሁበት ቤት ባለ ሦስት ክፍል ነው::

እውነትም የሰውዬው ቤት የማይረባ ዝቅተኛ ቤት ነበር፡
አቀማመጡም ሆን ብሎ ሰው ለመደበቂያ የተሠራ ይመስል ከአሳቻ ሥፍራ ነበር፡፡ ዣን ቫልዣ ከግቢው ውስጥ ሲገባ ያልታየው በዚህ ምክንያት ሊሆን ይችላል።

«ጥሩ ነው» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «አሁን ሁለት ነገር ነው የምጠይቅዎት
«ምንና ምን ናቸው ክቡር ከንቲባ፡፡ ብቻ እርስዎ' እያልክ ባትጠራኝ
«እሺ! አንደኛ፤ አሁን ስለራሴ የምነግርህን ለማንም እንዳታወራ፧
ሁለተኛ እኔ ከምነግርህ ውጭ ስለእኔ ለማወቅ እንዳትሞክር፡፡»

«አንተን ደስ እንዳለህ፡፡ አሳፋሪ ነገር የማትሠራና የእግዚአብሔር ሰው እንደሆንክ አውቃለሁ:: ከዚህም በላይ ከዚህ እንድትገባ የረዳኸኝ አንተ ስለሆንክ ቤትህ ነው:: እኔም ያንተ ነኝ፡፡».

«በጣም ጥሩ፧ ና አሁን ተከተለኝ፤ ልጅትዋን እናምጣት::»
«እንዴ» አሉ ፎሽለማ በመገረም:: «ልጅም አለች!»
ውሻ ጌታዋን ተከትላ እንደምትሄድ፤ ሰውዬው ሌላ ቃል ሳይናገሩ ዣን ቫልዣን ተከትለው ወጡ።

ከግማሽ ሰዓት በኋላ እሳት ተቀጣጥሎ ኮዜት እሳት ትሞቅ ጀመር።
ሽማግሌው ኮዜትን አልጋ ላይ አስተኝዋት:: ዣን ቫልዣ ወደ ግቢ
ወርውሮአቸው የነበሩትን እቃዎቹን አግኝቶ ተመለሰ፡፡ ሽማግሌው
ከጉልበታቸው ላይ ያሠሩትን ቃጭል ፈትተው አስቀመጡ:: ሁለቱ! ሽማግሌዎች እራት እየበሉ ጨዋታ ቀጠሉ፡፡

የሚገርም ነው ክቡር ከንቲባ፡፡ በመጀመሪያ አላወቅኸኝም፤ ሰዎች ሕይወታቸውን ካዳንክላቸው በኋላ ትረሳቸዋለህ? ይኸ ደግ አይደለም። እነርሱ ግን አይረሱህም:: የምትረሳ ሰው አይደለህም፡፡»

💫ይቀጥላል💫
👍275