ቢጡ ስንስቅ ሰምታን በሩን አንኳኳችና፣ “አብልሽ ኮሚቴው ውስጥ አስገባኝ አለችኝ፡፡ ሳቅ ሁሉ ደስታ የሚመስላቸው ሚስኪኖች ስንቱ ኮሚቴ ውስጥ ገብተው እንደቀለጡ ባወቀች…
"ቢጣ ተመለሽ! ማንበብ ትችይ የለ…የተለጠፈውን አታነቢም ?” አልኳት፡፡
እየጮኸች ማንበብ ጀመረች፣ ቆጠራ…
ላይ….ስ.….ለ…ሆ…ን…ን…አብልሽ እኔም እኮ ቁጥር እስከ መቶ እችላለሁ፡፡ ልቁጠርልህ ? ስማኝ…ዋን…ቱ…ስሪ ፎር ፋይፍ……” የፈረንጁን ፎቶ እያየሁ የቢጣን እንግሊዝኛ ሳዳምጥ፣ “ተከብበናል…" አልኩ ለራሴ፡፡ ምናልክ አብልሽ አልገባህም በአምሀሪክ ልቁጠርልህ ? አንድ…ሁለት…ሶስት…"
ለምሳ ስንወጣ ቢጣ በሩ ስር እንቅልፍ ወስዷት በእንቅልፍ ልቧ ትቆጥራለች፡ “አርባ ሾሽት ባ አራት ባ አምስት እንደገና ኮሚቴው ባሳቅ ፍርስስስስስስ፡፡ የራበው ኮሚቴ ሲስቅ ይደብራል…!
✨አለቀ✨
"ቢጣ ተመለሽ! ማንበብ ትችይ የለ…የተለጠፈውን አታነቢም ?” አልኳት፡፡
እየጮኸች ማንበብ ጀመረች፣ ቆጠራ…
ላይ….ስ.….ለ…ሆ…ን…ን…አብልሽ እኔም እኮ ቁጥር እስከ መቶ እችላለሁ፡፡ ልቁጠርልህ ? ስማኝ…ዋን…ቱ…ስሪ ፎር ፋይፍ……” የፈረንጁን ፎቶ እያየሁ የቢጣን እንግሊዝኛ ሳዳምጥ፣ “ተከብበናል…" አልኩ ለራሴ፡፡ ምናልክ አብልሽ አልገባህም በአምሀሪክ ልቁጠርልህ ? አንድ…ሁለት…ሶስት…"
ለምሳ ስንወጣ ቢጣ በሩ ስር እንቅልፍ ወስዷት በእንቅልፍ ልቧ ትቆጥራለች፡ “አርባ ሾሽት ባ አራት ባ አምስት እንደገና ኮሚቴው ባሳቅ ፍርስስስስስስ፡፡ የራበው ኮሚቴ ሲስቅ ይደብራል…!
✨አለቀ✨
👍27
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ለአሥራ ዘጠኝ ዓመት እስር ቤት ውስጥ ሲቀመጥ ኣንድ ቀን እንኳን እንባ አልወጣውም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከቤተክርስቲያን አናት ላይ የተሰቀለው ሰዓት ስምንት ሰዓት ሲደውል ዣን ቫልዣ ከእንቅልፉ እንደገና ነቃ፡፡ ከአራት ሰዓት በላይ ጥሩ እንቅልፍ ወስዶት ተኝቷል፡፡ ድካሙ ሁሉ ወጣለት:: ለዚህን ያህል ጊዜ የእረፍት ሰዓት ኣግኝቶ አያውቅም፡፡ ዓይኑን ገልጦ በአካባቢው በሰፈነው ጨለማ
ዘልቆ ለማየት ሞከረ፡፡ ለማየት ባለመቻሉ እንደገና እንቅልፍ እንዲወስደው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
ቀኑን ሙሉ አእምሮ በብዙ ነገሮች ተበጥብጦ ከዋለና የተለያዩ ነገሮች ከተመላለሱበት አንድ ጊዜ እንጂ ሁለት ጊዜ እንቅልፍ ሊወስድ እንደማይችል
ሁሉ ዣን ቫልዣንም ሊወስደው አልቻለም:: እንቅልፍ መጀመሪያ ሲመጣ ያዳፋል፡፡ ሁለተኛ ግን ቢለማመጡትም በዓይን አይዞርም:: እንደገና እንቅልፍ
ሊወስደው ስላልቻላ ማሰብ ጀመረ::
ብዙ ዓይነት አሳብ ከኀሊናው ውስጥ ገባ፡፡ ግን ሌሎቹን ሁሉ እየዋጠ እርሱ ብቻ እየተመላለሰ ያስቸገረው አንድ አሳብ ነበር፡፡ እነዚያ መዳም ማግልዋር ከጠረጴዛው ላይ የደረደሩዋቸው የሚያማምሩ ስድስት ከብር
የተሠሩ ሣህኖችና ትልቅ የብር ጭልፋ በዓይኑ ዞሩ፡፡ በጣም ወዷቸዋል:: አጠገቡ ከጳጳሱ ትራስጌ በኩል ቡፌ ውስጥ ሴትዬዋ ሲያስቀምጧቸው
አይቶአል፡፡ ከብር የተሠሩ ጥንታዊ ቅርስ በመሆናቸው ከነጭልፋው እስካ 200 ፍራንክ እንደሚያወጡ ያውቃል፡፡
ኅሊናው ከወዲያ ወዲህ እየዋለለ አንድ ሰዓት አለፈ፡፡ በአሳብ እየዋተቱ አንድ ሰዓት ማሳለፍ፤ ያውም ሌሊት በጨለማ ምን ያህል ረጅም እንደሆነ
የደረሰበት ያውቀዋል፡፡ የቤተክርስቲያኑ ሰዓት ደወል ዘጠኝ ሰዓት መሆኑን አበሰረ:: ዓይኑን በድንገት ገልጦ ከአልጋው ዘልሉ ወረደ:: ስልቻውን በእጁ
እየዳሰሰ ፈለገና እንደያዘው ከአልጋው ጠርዝ ቁጭ አለ፡፡ ሳያውቀው ብዙ ተቀመጠ፡፡ ሰዓቱ በየአሥራ አምስት ደቂቃና ግማሽ ሰዓት ደወል እየደወለ ባይቀሰቅሰውማ እስኪነጋ ድረስ በተቀመጠ፡፡ ደወሉ «አይዞህ፣ በርታ» የሚለው መሰለው::
ተነስቶ ቆመ፤ ለመራመድ ግን አመነታ:: አንድ እርምጃ ወደፊት
ተራምዶ አዳመጠ፡፡ ሁሉም ነገር ጸጥ ብሎአል:: ቀስ ብሎ በጥንቃቄ ወደ መስኮቱ ተጠጋ፡፡ ሌሊቱ ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ የተዋጠ ኣልነበረም:: ጨረቃ
በሩቁ ትታያለች:: ሆኖም ደመና ዞሮባታል፡፡ ደመና ጨረቃዋን በጋረዳት ቁጥር ቤቱ ትንሽ ጨለም ይላል፡፡ ውጪው በደምብ ሲታይ እቤት ውስጥ ግን ያንገዳግዳል፡፡ መስኮቱ አጠገብ ደርሶ መስኮቱን ሲመለከት በቀላሉ
እንደሚከፈት ስለተገነዘበ ከፈተው:: ሆኖም ኃይለኛ ብርድ ስለገባ መልሶ ዘጋው:: መስኮቱ መስታወት ስለነበር እንደተዘጋ ግቢውን ቃኘ፡፡ ግቢው
በአነስተኛ ግምብ መከለሉን ተመለከተ:: ከግምቡ ውጭ ረጃጅም ዛፎች ነበሩ፡፡ በሁለት ዛፎች መካከል ያለውን ርቀት ሲያጤን ርቀታቸው ተመሳሳይ
ሆኖ ስላየው ምናልባት ማዘጋጃ ቤቱ የተከላቸው ዛፎች መሆናቸውን በመገመት ከአጥሩ ውጭ ያለው መንገድ አውራ ጎዳና መሆን አለበት ብሎ ደመደመ::
ወደ ውሳኔ አሳብ እንደደረሰ ሰው በቆራጥነት ወደ አልጋው ተመለሰ፡፡ አቆማዳውን አንስቶ ከፈተውና ከውስጠ ምናምን ፈለገ፡፡ ኣንድ ነገር አውጥቶ
አልጋው ላይ አስቀመጠ፡፡ ጫማውን ኪሱ ውስጥ ከተተ፡፡ ኣልጋው ላይ ካስቀመጠው እቃ ሌላ የተቀሩትን እሳስሮ ትከሻው ላይ አኖረ፡፡ ቆቡን አጠለቀና ዱላውን ፈልጎ ከያዘ በኋላ ያሰረውን እቃ ከመስኮቱ ሥር
አስቀመጠው:: ወደ ኣልጋው ተመልሶ ያስቀመጠውን እቃ አነሳ:: እቃው ከአንድ ጫፍ እንደ ጦር የሾለ፣ ከሌላው ጫፍ ቋር ያለው ወፍራም ብረት ነበር፡፡ በዚያ ጨለማ ብረቱ ለምን ሥራ እንደተዘጋጀ ለመለየት አስቸጋሪ
ነበር፡፡ ዱላ ነው ወይስ እቃ ማንሻ? አይታወቅም:: ቀን እንኳን ቢሆን
የማዕድን ሠራተኞች መቆፈሪያ ነው ለማለት ያስችላል፡፡ በዚያን ጊዜ ቱሉን ከተባለ ቦታ አካባቢ በሚገኙ ከፍተኛ ኮረብታዎች ላይ ድንጋይ እንዲፈልጡ
የተፈረደባቸው ወንጀለኞች ይቀጠሩ ነበር፡፡ ወንጀለኞቹ ብዙውን ጊዜ የዚያን ዓይነት ብረት የመሰለ መፍለጫ ይይዛሉ፡፡
ዣን ቫልዣ ያን ብረት በቀኝ እጁ ያዘ፡፡ ትንፋሹን ውጦ በዝግታ
ተራመደ:: ወደ ጳጳሱ መኝታ ቤት አመራ:: ወደ በሩ ሲጠጋ አለመቀርቀሩን ተመለከተ፡፡ «አባታችን በራቸውን ሳይቆልፉ ነው የሚተኙት» አለ በልቡ፡፡
ዣን ቫልዣ ጆሮውን አቅንቶ አዳመጠ፡፡ ድምፅ የሚሉት ነገር
የለም:: በሩን ከፈት አድርጎ ሲፈራ ሲቸር በጣቶቹ ጫፍ ቀስ ብሎ ገፋው::ጥንቃቄው ከድመት ይበልጣል:: በሩ ምንም ድምፅ ሳያሰማና ለመንቀሳቀሱ
እንኳን በሚያጠራጥር ሁኔታ በዝግታ በመገፋቱ ከመጀመሪያው ይበልጥ ጥቂት ከፈት አለ፡
ለጥቂት ጊዜ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ አሁን ግን በይበልጥ ድፍረቱ
ስለተሰባሰበለት ከቀድሞ በበለጠ ጉልበት በሩን ገፋ አደረገው:: በዚህ ጊዜ የበሩ ማያያገዥ የዛገ ብረት ረዘም ያለ የሚሰቀጥጥ ድምፅ አሰማ፡፡
ልቡ የተሰነጠቀ መሰለው:: እንደ እንጨት ደርቆ ከቆመበት ሐውልት
ይመስል ሳይንቀሳቀስ ለጥቂት ጊዜ ተገተረ:: ለመነቃነቅ አቅም አነሰው ድፍረትም አልነበረውም:: ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ:: በሩ ወለል ብሎ ተከፍቷል:: ወደ ክፍሉ ተመለከተ:: የተንቀሳቀሰ ነገር የለም:: አዳመጠ፤ የሚንቀሳቀስ ወይም ድምፅ የሚሰጥ ነገር አሁንም ከጆሮው ኣልገባም::
የበሩ ድምፅ ማንንም አልቀሰቀሰም ማለት ነው::
የመጀመሪያው አደጋ አለፈ:: ልቡ ግን በጣም ፈርቷል ፤ ሆኖም
አላወላወለም:: የፈለገውን ቶሎ ለመጨረስ ቁርጥ አሳብ አደረገ፡፡ በአንድ እርምጃ ከክፍለ ውስጥ ገባ፡፡ ክፍሉ ውስጥ ጸጥታ ሰፍኖበታል፡፡ ዣን ቫልገዣ ከወንበርና ጠረጴዛ ጋር እንዳይጋጭ እየተጠነቀቀ ወደፊት ተራመደ::ጳጳሱ ክፍለ ውስጥ ጥግ ይዘው ተኝተው በኃይል ሲተነፍሱ አዳመጠ፡፡በድንገት ቆም አለ:: ከጳጳሰ አልጋ አጠገብ ደርሷል፡፡
ቶሉ የደረሰ መሰለው::አንዳንድ ጊዜ ተፈጥሮ የምንሠራውን ሥራ ለማራገብ ከእኛ ጋር ታብራለች:: ለግማሽ ሰዓት ያህል ደመና ጨረቃን በመጋረድዋ አካባቢው
ጨልሞ ነበር፡፡ አሁን ግን ልክ እንደተማከረ ሰው ዣን ቫልዣ ከጳጳሱ አልጋ አጠገብ እንደቆመ ደመና ለጨረቃ ቦታዋን ለቀቀች:: የጨረቃ ብርሃን በመስኮት በኩል ዘልቆ በመግባት ከጳጳሱ የገረጣ ፊት ላይ አበራ:: ጭልጥ
አድርጎ እንቅልፍ ወስዷቸዋል። የሌሊቱ ብርድ ከባድ ስለነበር ወፈር ያለ የሌሊት ልብስ ለብሰው በጀርባቸው ተዘርረው ነው የተኙት፡፡ ስንት ደግ ሥራ የሠራው ታማኙና ነዳያን የሳሙት እጃቸው ካልጋው ጠርዝ አልፎ ወደመሬት ተንጠልጥሎአል፡፡ ሌላው እጃቸው ከደረታቸው ላይ በማረፉ
የጵጵስና ቀለበታቸው ያበራል፡፡ እዚያ ተጋድመው ሲያይዋቸው መላ አካላቸው የተስፋ ፣ የደስታና የእርካታ ማኅደር እንደሆነ ይናገራል:: በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት የማይታይ ብርሃን ከግንባራቸው ላይ አርፎአል፡፡
የጨረቃው በሰማይ ላይ መንጣለል፤ የምድር በከፊል የተኛች መምሰል ፤ የግቢው አትክልት እርጭ ማለትና የቤቱና የዚያች ሰዓት ፀጥታ እኚህ መለኮት የቀረባቸውን ሰው «አክብሩ አትድፈሯቸው» የሚያሰኝ
ነበር፡፡ ዓይናቸውን ጨፍነው እንደተኙ የነበራቸው ግርማ ሞገስና ለተስፋ ምንጭ የሆነውና በጨርቅ ያልተሽፈነው ግንባራቸው ሲያዩት በፍርሃት የሚያርበደብድ ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ለአሥራ ዘጠኝ ዓመት እስር ቤት ውስጥ ሲቀመጥ ኣንድ ቀን እንኳን እንባ አልወጣውም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከቤተክርስቲያን አናት ላይ የተሰቀለው ሰዓት ስምንት ሰዓት ሲደውል ዣን ቫልዣ ከእንቅልፉ እንደገና ነቃ፡፡ ከአራት ሰዓት በላይ ጥሩ እንቅልፍ ወስዶት ተኝቷል፡፡ ድካሙ ሁሉ ወጣለት:: ለዚህን ያህል ጊዜ የእረፍት ሰዓት ኣግኝቶ አያውቅም፡፡ ዓይኑን ገልጦ በአካባቢው በሰፈነው ጨለማ
ዘልቆ ለማየት ሞከረ፡፡ ለማየት ባለመቻሉ እንደገና እንቅልፍ እንዲወስደው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
ቀኑን ሙሉ አእምሮ በብዙ ነገሮች ተበጥብጦ ከዋለና የተለያዩ ነገሮች ከተመላለሱበት አንድ ጊዜ እንጂ ሁለት ጊዜ እንቅልፍ ሊወስድ እንደማይችል
ሁሉ ዣን ቫልዣንም ሊወስደው አልቻለም:: እንቅልፍ መጀመሪያ ሲመጣ ያዳፋል፡፡ ሁለተኛ ግን ቢለማመጡትም በዓይን አይዞርም:: እንደገና እንቅልፍ
ሊወስደው ስላልቻላ ማሰብ ጀመረ::
ብዙ ዓይነት አሳብ ከኀሊናው ውስጥ ገባ፡፡ ግን ሌሎቹን ሁሉ እየዋጠ እርሱ ብቻ እየተመላለሰ ያስቸገረው አንድ አሳብ ነበር፡፡ እነዚያ መዳም ማግልዋር ከጠረጴዛው ላይ የደረደሩዋቸው የሚያማምሩ ስድስት ከብር
የተሠሩ ሣህኖችና ትልቅ የብር ጭልፋ በዓይኑ ዞሩ፡፡ በጣም ወዷቸዋል:: አጠገቡ ከጳጳሱ ትራስጌ በኩል ቡፌ ውስጥ ሴትዬዋ ሲያስቀምጧቸው
አይቶአል፡፡ ከብር የተሠሩ ጥንታዊ ቅርስ በመሆናቸው ከነጭልፋው እስካ 200 ፍራንክ እንደሚያወጡ ያውቃል፡፡
ኅሊናው ከወዲያ ወዲህ እየዋለለ አንድ ሰዓት አለፈ፡፡ በአሳብ እየዋተቱ አንድ ሰዓት ማሳለፍ፤ ያውም ሌሊት በጨለማ ምን ያህል ረጅም እንደሆነ
የደረሰበት ያውቀዋል፡፡ የቤተክርስቲያኑ ሰዓት ደወል ዘጠኝ ሰዓት መሆኑን አበሰረ:: ዓይኑን በድንገት ገልጦ ከአልጋው ዘልሉ ወረደ:: ስልቻውን በእጁ
እየዳሰሰ ፈለገና እንደያዘው ከአልጋው ጠርዝ ቁጭ አለ፡፡ ሳያውቀው ብዙ ተቀመጠ፡፡ ሰዓቱ በየአሥራ አምስት ደቂቃና ግማሽ ሰዓት ደወል እየደወለ ባይቀሰቅሰውማ እስኪነጋ ድረስ በተቀመጠ፡፡ ደወሉ «አይዞህ፣ በርታ» የሚለው መሰለው::
ተነስቶ ቆመ፤ ለመራመድ ግን አመነታ:: አንድ እርምጃ ወደፊት
ተራምዶ አዳመጠ፡፡ ሁሉም ነገር ጸጥ ብሎአል:: ቀስ ብሎ በጥንቃቄ ወደ መስኮቱ ተጠጋ፡፡ ሌሊቱ ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ የተዋጠ ኣልነበረም:: ጨረቃ
በሩቁ ትታያለች:: ሆኖም ደመና ዞሮባታል፡፡ ደመና ጨረቃዋን በጋረዳት ቁጥር ቤቱ ትንሽ ጨለም ይላል፡፡ ውጪው በደምብ ሲታይ እቤት ውስጥ ግን ያንገዳግዳል፡፡ መስኮቱ አጠገብ ደርሶ መስኮቱን ሲመለከት በቀላሉ
እንደሚከፈት ስለተገነዘበ ከፈተው:: ሆኖም ኃይለኛ ብርድ ስለገባ መልሶ ዘጋው:: መስኮቱ መስታወት ስለነበር እንደተዘጋ ግቢውን ቃኘ፡፡ ግቢው
በአነስተኛ ግምብ መከለሉን ተመለከተ:: ከግምቡ ውጭ ረጃጅም ዛፎች ነበሩ፡፡ በሁለት ዛፎች መካከል ያለውን ርቀት ሲያጤን ርቀታቸው ተመሳሳይ
ሆኖ ስላየው ምናልባት ማዘጋጃ ቤቱ የተከላቸው ዛፎች መሆናቸውን በመገመት ከአጥሩ ውጭ ያለው መንገድ አውራ ጎዳና መሆን አለበት ብሎ ደመደመ::
ወደ ውሳኔ አሳብ እንደደረሰ ሰው በቆራጥነት ወደ አልጋው ተመለሰ፡፡ አቆማዳውን አንስቶ ከፈተውና ከውስጠ ምናምን ፈለገ፡፡ ኣንድ ነገር አውጥቶ
አልጋው ላይ አስቀመጠ፡፡ ጫማውን ኪሱ ውስጥ ከተተ፡፡ ኣልጋው ላይ ካስቀመጠው እቃ ሌላ የተቀሩትን እሳስሮ ትከሻው ላይ አኖረ፡፡ ቆቡን አጠለቀና ዱላውን ፈልጎ ከያዘ በኋላ ያሰረውን እቃ ከመስኮቱ ሥር
አስቀመጠው:: ወደ ኣልጋው ተመልሶ ያስቀመጠውን እቃ አነሳ:: እቃው ከአንድ ጫፍ እንደ ጦር የሾለ፣ ከሌላው ጫፍ ቋር ያለው ወፍራም ብረት ነበር፡፡ በዚያ ጨለማ ብረቱ ለምን ሥራ እንደተዘጋጀ ለመለየት አስቸጋሪ
ነበር፡፡ ዱላ ነው ወይስ እቃ ማንሻ? አይታወቅም:: ቀን እንኳን ቢሆን
የማዕድን ሠራተኞች መቆፈሪያ ነው ለማለት ያስችላል፡፡ በዚያን ጊዜ ቱሉን ከተባለ ቦታ አካባቢ በሚገኙ ከፍተኛ ኮረብታዎች ላይ ድንጋይ እንዲፈልጡ
የተፈረደባቸው ወንጀለኞች ይቀጠሩ ነበር፡፡ ወንጀለኞቹ ብዙውን ጊዜ የዚያን ዓይነት ብረት የመሰለ መፍለጫ ይይዛሉ፡፡
ዣን ቫልዣ ያን ብረት በቀኝ እጁ ያዘ፡፡ ትንፋሹን ውጦ በዝግታ
ተራመደ:: ወደ ጳጳሱ መኝታ ቤት አመራ:: ወደ በሩ ሲጠጋ አለመቀርቀሩን ተመለከተ፡፡ «አባታችን በራቸውን ሳይቆልፉ ነው የሚተኙት» አለ በልቡ፡፡
ዣን ቫልዣ ጆሮውን አቅንቶ አዳመጠ፡፡ ድምፅ የሚሉት ነገር
የለም:: በሩን ከፈት አድርጎ ሲፈራ ሲቸር በጣቶቹ ጫፍ ቀስ ብሎ ገፋው::ጥንቃቄው ከድመት ይበልጣል:: በሩ ምንም ድምፅ ሳያሰማና ለመንቀሳቀሱ
እንኳን በሚያጠራጥር ሁኔታ በዝግታ በመገፋቱ ከመጀመሪያው ይበልጥ ጥቂት ከፈት አለ፡
ለጥቂት ጊዜ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ አሁን ግን በይበልጥ ድፍረቱ
ስለተሰባሰበለት ከቀድሞ በበለጠ ጉልበት በሩን ገፋ አደረገው:: በዚህ ጊዜ የበሩ ማያያገዥ የዛገ ብረት ረዘም ያለ የሚሰቀጥጥ ድምፅ አሰማ፡፡
ልቡ የተሰነጠቀ መሰለው:: እንደ እንጨት ደርቆ ከቆመበት ሐውልት
ይመስል ሳይንቀሳቀስ ለጥቂት ጊዜ ተገተረ:: ለመነቃነቅ አቅም አነሰው ድፍረትም አልነበረውም:: ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ:: በሩ ወለል ብሎ ተከፍቷል:: ወደ ክፍሉ ተመለከተ:: የተንቀሳቀሰ ነገር የለም:: አዳመጠ፤ የሚንቀሳቀስ ወይም ድምፅ የሚሰጥ ነገር አሁንም ከጆሮው ኣልገባም::
የበሩ ድምፅ ማንንም አልቀሰቀሰም ማለት ነው::
የመጀመሪያው አደጋ አለፈ:: ልቡ ግን በጣም ፈርቷል ፤ ሆኖም
አላወላወለም:: የፈለገውን ቶሎ ለመጨረስ ቁርጥ አሳብ አደረገ፡፡ በአንድ እርምጃ ከክፍለ ውስጥ ገባ፡፡ ክፍሉ ውስጥ ጸጥታ ሰፍኖበታል፡፡ ዣን ቫልገዣ ከወንበርና ጠረጴዛ ጋር እንዳይጋጭ እየተጠነቀቀ ወደፊት ተራመደ::ጳጳሱ ክፍለ ውስጥ ጥግ ይዘው ተኝተው በኃይል ሲተነፍሱ አዳመጠ፡፡በድንገት ቆም አለ:: ከጳጳሰ አልጋ አጠገብ ደርሷል፡፡
ቶሉ የደረሰ መሰለው::አንዳንድ ጊዜ ተፈጥሮ የምንሠራውን ሥራ ለማራገብ ከእኛ ጋር ታብራለች:: ለግማሽ ሰዓት ያህል ደመና ጨረቃን በመጋረድዋ አካባቢው
ጨልሞ ነበር፡፡ አሁን ግን ልክ እንደተማከረ ሰው ዣን ቫልዣ ከጳጳሱ አልጋ አጠገብ እንደቆመ ደመና ለጨረቃ ቦታዋን ለቀቀች:: የጨረቃ ብርሃን በመስኮት በኩል ዘልቆ በመግባት ከጳጳሱ የገረጣ ፊት ላይ አበራ:: ጭልጥ
አድርጎ እንቅልፍ ወስዷቸዋል። የሌሊቱ ብርድ ከባድ ስለነበር ወፈር ያለ የሌሊት ልብስ ለብሰው በጀርባቸው ተዘርረው ነው የተኙት፡፡ ስንት ደግ ሥራ የሠራው ታማኙና ነዳያን የሳሙት እጃቸው ካልጋው ጠርዝ አልፎ ወደመሬት ተንጠልጥሎአል፡፡ ሌላው እጃቸው ከደረታቸው ላይ በማረፉ
የጵጵስና ቀለበታቸው ያበራል፡፡ እዚያ ተጋድመው ሲያይዋቸው መላ አካላቸው የተስፋ ፣ የደስታና የእርካታ ማኅደር እንደሆነ ይናገራል:: በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት የማይታይ ብርሃን ከግንባራቸው ላይ አርፎአል፡፡
የጨረቃው በሰማይ ላይ መንጣለል፤ የምድር በከፊል የተኛች መምሰል ፤ የግቢው አትክልት እርጭ ማለትና የቤቱና የዚያች ሰዓት ፀጥታ እኚህ መለኮት የቀረባቸውን ሰው «አክብሩ አትድፈሯቸው» የሚያሰኝ
ነበር፡፡ ዓይናቸውን ጨፍነው እንደተኙ የነበራቸው ግርማ ሞገስና ለተስፋ ምንጭ የሆነውና በጨርቅ ያልተሽፈነው ግንባራቸው ሲያዩት በፍርሃት የሚያርበደብድ ነበር፡፡
👍19❤1
በዚህ የተነሣ ዣን ቫልዣ በፍርሃት ተውጦና ሐውልት መስሎ
ድምፅ ሳያሰማ ከጥላ ሥር ባለቋሩን ብረት ይዞ ከእኚህ ደግ ሰው ፊት ቆሞአል፡፡ በሕይወቱ እንደዚያ ያለ ሁናቴ ገጥሞት አያውቅም፡፡ ይህም በይበልጥ እንዲፈራ አደረገው፡፡ የተብከነከነና የተቅበጠበጠ ሕሊና ክፉ
ተግባር ለመፈጸም ከዚያ ቆሞ ሳለ ንጹሑ ነፍስ እንቅልፍ ወስዶት ከእዚያ ተኝቷል፡፡
ጥቂት ቆሞ ሁኔታውን ከተመለከተ በኋላ በግራ እጁ ቀስ ብሉ ቆቡን
አወለቀ፡፡ ከዚያም ቆቡን ለማውለቅ ያነሳውን እጁን አሁንም በዝግታ አውርዶ እንደገና ዣን ቫልዣ ማሰላሰል ጀመረ:: ቆቡን በግራ እጁ፣ የብረት ዱላውን በቀኝ እጁ ይዟል፡፡ ጳጳሱ ግን ከተኙበት ነቅነቅ አላሉም፡፡
በድንገት ዣን ቫልዣ ቆቡን አጠለቀ፡፡ ከዚያም ወደ ጳጳሱ ሳያይ ከአልጋቸው እልፍ ብሎ ወደ ነበረው ቡፌ ሄደ፡፡ የቡፌው ቁልፍ ከላዩ ላይ ስለነበር ከፈተው:: በመጀመሪያ ያየው እነዚያን ከብር የተሠሩ የሚያማምሩ ሣህኖችን ነበር፡፡ ሳህኖቹን ከነጭልፋው ይዞ ወደ በሩ አመራ:: የእግሬ ኮቴ
ይሰማል በማለት ብዙም ሳይጨነቅ በኃይል እየተራመደ ከክፍሉ ወጥቶ ሄደ፡፡ የብር እቃዎቹን ከአቅማዳው ውስጥ ከተተ:: በኣትክልቱ መካከል
አልፎ ሄዶ ኣጥሩን በመዝለል ከግቢው ከወጣ በኋላ መንገዱን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በጠዋት ፀሐይ እንደ ወጣች ጳጳሱ ከአትክልት ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡
መዳም ማግልዋር እየሮጠ መጡ፡፡
«አባታችን ሰውዬው ሄዷል፤ እነዚያ የብር ሣህኖችም ተሠርቀዋል፡፡»
ሴትዮዋ ይህን ሲናገሩ ከአትክልቱ ውስጥ የእግር ኮቴ ተመለከቱ፡፡
ኮቴውን ተከትለው ግምቡን ሲያዩ ከአንድ ፊት መሸረፉን ተገነዘቡ፡፡
«አባታችን አዩ፤ በዚያ በኩል ነው የወጣው:: በአጥር ዘልሉ ነው
የሄደው:: ምን ዓይነት ቀበኛ ነው:: ሣህኖቻችንን ሠርቆ ነው የሄደው፡፡»
ጳጳሱ ለጥቂት ጊዜ ዝም አሉ:: ከዚያም አንገታቸውን ቀና አድርገው ሴትዮዋን እየተመለከቱ «ጥንትም ቢሆን እኮ ሣህኖቹ የእኛ ነበሩ እንዴ?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
መዳም ማግልዋር አልመለሱም:: ለጥያቄያቸው መልስ ስላላገኙ
ጳጳሱ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡
«መዳም ማግልዋር፤ እነዚህን ሣህኖች የነዳያን ሀብት ሆነው ሳለ ለረጅም ጊዜ ያለ አግባብ አስቀመጥናቸው:: ይህ ሰው ማነው? ከነዳያን አንዱ ነው፡፡»
«ይገርማል» አሉ መዳም ማግልዋር፡፡ «እኔም ሆንኩ እህትዎ ግድ የለንም፤ ለእኛ እንደሆነ ሴቶች እንደመሆናችን ለውጥ አያመጣም:: ግን
ለብፁዕነትዎ ገበታ ሲቀርብ አሁን የትኛው ሳህን ሊቀርብ ነው?»
ጳጳሱ በመገረም ሴትዮዋን አተኩረው ተመለከቱ፡፡
«እንዴት እኮ! የቆርቆሮ ሣህን ቢሆን እንኳን! ሌላ ሣህን የለንም
ማለት ነው?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
መዳም ማግልዋር ትከሻቸውን ነቀነቁ፡፡
«የቆርቆሮ ሣህን እኮ ሽታ ያመጣል፡፡»
«እንግዲያውማ ከብረት የተሠራ ሣህን ካለ እርሱ ሊሆን ይችላል።»
መዳም ማግልቀር ፈገግ ብለው «እሱም ቢሆን ብረት ብረት ማለቱ
ይቀራል!» አሉ::
«እንግዲያውማ» አሉ ብፁዕነታቸው፤ «የእንጨት ወይም የሸክላ ሣህን መፈለግ ነዋ!»
ከጥቂት ጊዜ በኋላ በአለፈው ሌሊት ዣን ቫልዣ አብሮ ከቀረበበት ጠረጴዛ ላይ ቁርስ ተዘጋጀ:: ቁርስ እየበሉ ምንም ዓይነት አስተያየት ላልሰጡት እህታቸውና ለሚያጉረመርሙት ለመዳም ማግልዋር ዳቦ ሻይ
ውስጥ ነክሮ ለመብላት ማንኪያ ወይም ሹካ የማያስፈልግ መሆኑን በመግለጽ ሳቅ እያሉ ይናገራሉ::: ወዲያው እህትና ወንድም ቀና ብለው ሲተያዩ በር ይንኳኳል::
«ይግቡ» አሉ ጳጳሱ::
በሩ ተከፈተ:: ሦስት የሚያስፈሩና ለቤቱ እንግዳ የሆኑ ሰዎች ገቡ::
ሰዎቹ የአራተኛ ሰው አንገት ጨምድደው ይዘዋል:: ሦስቱ ሰዎች ፖሊሶች ሲሆኑ አራተኛው ሰው ዣን ቫልዣ ነበር፡፡
አዛዡ ወደፊት ቀደም ቀደም ብሎ በወታደር ደምብ መሠረት ለጳጳሱ
የክብር ሰላምታ ሰጠ፡፡
«ብፁዕነትዎ» አለ፡፡
እስከዚያች ደቂቃ ድረስ አኩርፎ ዝም ያለውና ያቀረቀረው ዣን
ቫልዣ ያዛዡን ንግግር አቋርጦ ጣልቃ በመግባት እፍረት እየተሰማው አንገቱን ቀና አደረገ፡፡
«አባታችን፤ የደብር ኣለቃ ብቻ አይደሉማ!» ሲል ተናገረ::
«ዝም በል!» አለ ፖሊሱ፡፡ «አባታችን እኮ ናቸው:: የብፁዕነታቸውን ማዕረግ እንኳን አታውቅም?»
ብፁዕነታቸው እድሜያቸው በፈቀደው መጠን በቶሎ ከገበታው ብድግ ብለው ወደ ሰዎቹ ጠጋ አሉ::
«መጣህ» አሉ ወደ ዣን ቫልዣ እየተመለከቱ፡፡ እንደገና በመገናኘ
ታችን ደስ ብሎኛል፡፡ ግን የሻማ ማብሪያዎችንም ጭምር ሰጥቼህ አልነበረም እንዴ፧ ምነው ተውካቸው? እነርሱም እኮ ከንጹህ ብር የተሠሩ ናቸው:: እስከ 200 ፍራንክ ያወጡልሃል፡፡ ከሣህኖቹ ነጥለህ ምነው አስቀረሃቸው?
ሲሉ ጠየቁት::
ዣን ቫልዣ አፉን ከፍቶ ብፁዕነታቸውን አፍጥጦ ተመለከተ፡፡ የሚሰማው ነገር እውነት መሆኑን ማመን አቃተው::
«አባታችን» አለ አዛዡ፣ «እንግዲያውስ ይህ ሰው ያለው ትክክል ነው ማለት ነዋ? እኛ ስንይዘው እንደገመገምነው የሚሸሽ ሰው ዓይነት መስሎን
ነበር፡፡ ስለዚህ ተጠራጥረን ያዝነው:: እነዚያን የብር እቃዎች መያዙ ደግሞ በይበልጥ አጠራጠረን፡፡»
«እና ተነጋግራችኋላ!» አሉ ጳጳሱ ፈገግ ብለው፤ «ትናንት ሌሊት ካስጠጉት ከአንድ ሽማግሌ መነኩሴ የተሰጠው እቃ ለመሆኑ ገልጾላችኋላ!
እናንተ ግን በመጠራጠር ይዛችሁት መጣችሁ! ተሳስታችኋል፡፡ እቃው
የራሱ ነው፡፡»
«እንዲህ ከሆነማ ሰውዬን በነፃ ልንለቅቀው እንችላለን» አለ አዛዡ፡፡
«ያለ ጥርጥር» ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ፡፡
ፖሊሶቹ ዣን ቫልዣን ለቀቁት:: ወደኋላ አፈገፈገ፡፡
«አሁን በእርግጥ በነፃ ሊለቁኝ ነው?» ሲል ዣን ቫልዣ እጅግ በጣም ዝቅተኛ በሆነ ድምፅ አጉረመረመ:: ቅዠት መሰለው እንጂ በውኑ እንደሆነ
አላመነም::
«አዎን፥ ልትሄድ ትችላለህ ፤ ነገር አይገባህም» አለ ፖሊሱ፡፡
«ወዳጄ» አሉ ጳጳሱ፤ «ከመሄድህ በፊት እነዚያም የሻማ ማብሪያዎች
የአንተ ስለሆኑ ውሰዳቸው::»
ጳጳሱ ወደ ምግብ ጠረጴዛ ሄደው የሻማ ማብሪያዎችን አምጥተው
ለዣን ቫልዣ ሰጡት:: ሁለቱ ሴቶች ተገርመው ከእዚያው ከገበታ ላይ
አቀርቅረው ቀሩ፡፡ ቃል አልተነፈሱም::
ዣን ቫልዣ ሰውነቱ ርድኦ መቆም ተሳነው:: የሻማ ማብሪያዎቹን
ተቀበለ፡፡ ፊቱ የኣውሬ መሰለ፡፡
«አሁን» አሉ ብፁዕነታቸው በሰላም መሄድ ትችላለህ፡፡» ከዚያም ብፁዕነታቸው ፊታቸውን ወደ ፖሊሶቹ ኣዙረው፤ «ልጆቼ፤ ወደ ሥራችሁ ልትመለሱ ትችላላችሁ» አሉ:: ፖሊሶቹ ወጥተው ሄዱ፡፡
ዣን ቫልዣ ራሱን ስቶ ከመሬት እንደሚዘረር ሰው ተንገዳገደ ፤ ግን አልወደቀም:: ጳጳሱ ወደ እርሱ ጠጋ ብለው ዝቅ ባለ ድምፅ የሚከተለውን ተናገሩ፡፡
«አትርሳ፣ ገንዘቡን እውነተኛና ታማኝ ሰው ለመሆን እጠቀምበታለሁ ብለህ ቃል የገባኸውን እስከ እድሜ ልክህ እንዳትረሳ፡፡»
ዣን ቫልዣ መቼ ቃል እንደገባላቸው ማስታወስ አቅቶት በመደናገር ዝም ብሎ ቆመ:: ጳጳሱ «ቃል የገባኸውን አትርሳ» በማለት አጥብቀው ጠይቀውታል፡: ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዣን ቫልዣ ፤ ከእንግዲህ
አንተ ለጥፋት ዓለም ሳይሆን ለደግነት የተመረጥህ ነህ:: ነፍስህን ነው የምገዛልህ:: የአንተን ነፍስ የምሰጠው የሁሉም በላይ ለሆነው ለአንድ
አምላክ ነው::»
ዣን ቫልዣ አገር ጥሎ እንደሚሸሽ ሰው እግሬ አውጪኝ በማለት
ድምፅ ሳያሰማ ከጥላ ሥር ባለቋሩን ብረት ይዞ ከእኚህ ደግ ሰው ፊት ቆሞአል፡፡ በሕይወቱ እንደዚያ ያለ ሁናቴ ገጥሞት አያውቅም፡፡ ይህም በይበልጥ እንዲፈራ አደረገው፡፡ የተብከነከነና የተቅበጠበጠ ሕሊና ክፉ
ተግባር ለመፈጸም ከዚያ ቆሞ ሳለ ንጹሑ ነፍስ እንቅልፍ ወስዶት ከእዚያ ተኝቷል፡፡
ጥቂት ቆሞ ሁኔታውን ከተመለከተ በኋላ በግራ እጁ ቀስ ብሉ ቆቡን
አወለቀ፡፡ ከዚያም ቆቡን ለማውለቅ ያነሳውን እጁን አሁንም በዝግታ አውርዶ እንደገና ዣን ቫልዣ ማሰላሰል ጀመረ:: ቆቡን በግራ እጁ፣ የብረት ዱላውን በቀኝ እጁ ይዟል፡፡ ጳጳሱ ግን ከተኙበት ነቅነቅ አላሉም፡፡
በድንገት ዣን ቫልዣ ቆቡን አጠለቀ፡፡ ከዚያም ወደ ጳጳሱ ሳያይ ከአልጋቸው እልፍ ብሎ ወደ ነበረው ቡፌ ሄደ፡፡ የቡፌው ቁልፍ ከላዩ ላይ ስለነበር ከፈተው:: በመጀመሪያ ያየው እነዚያን ከብር የተሠሩ የሚያማምሩ ሣህኖችን ነበር፡፡ ሳህኖቹን ከነጭልፋው ይዞ ወደ በሩ አመራ:: የእግሬ ኮቴ
ይሰማል በማለት ብዙም ሳይጨነቅ በኃይል እየተራመደ ከክፍሉ ወጥቶ ሄደ፡፡ የብር እቃዎቹን ከአቅማዳው ውስጥ ከተተ:: በኣትክልቱ መካከል
አልፎ ሄዶ ኣጥሩን በመዝለል ከግቢው ከወጣ በኋላ መንገዱን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በጠዋት ፀሐይ እንደ ወጣች ጳጳሱ ከአትክልት ውስጥ ይንሸራሸራሉ፡፡
መዳም ማግልዋር እየሮጠ መጡ፡፡
«አባታችን ሰውዬው ሄዷል፤ እነዚያ የብር ሣህኖችም ተሠርቀዋል፡፡»
ሴትዮዋ ይህን ሲናገሩ ከአትክልቱ ውስጥ የእግር ኮቴ ተመለከቱ፡፡
ኮቴውን ተከትለው ግምቡን ሲያዩ ከአንድ ፊት መሸረፉን ተገነዘቡ፡፡
«አባታችን አዩ፤ በዚያ በኩል ነው የወጣው:: በአጥር ዘልሉ ነው
የሄደው:: ምን ዓይነት ቀበኛ ነው:: ሣህኖቻችንን ሠርቆ ነው የሄደው፡፡»
ጳጳሱ ለጥቂት ጊዜ ዝም አሉ:: ከዚያም አንገታቸውን ቀና አድርገው ሴትዮዋን እየተመለከቱ «ጥንትም ቢሆን እኮ ሣህኖቹ የእኛ ነበሩ እንዴ?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
መዳም ማግልዋር አልመለሱም:: ለጥያቄያቸው መልስ ስላላገኙ
ጳጳሱ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡
«መዳም ማግልዋር፤ እነዚህን ሣህኖች የነዳያን ሀብት ሆነው ሳለ ለረጅም ጊዜ ያለ አግባብ አስቀመጥናቸው:: ይህ ሰው ማነው? ከነዳያን አንዱ ነው፡፡»
«ይገርማል» አሉ መዳም ማግልዋር፡፡ «እኔም ሆንኩ እህትዎ ግድ የለንም፤ ለእኛ እንደሆነ ሴቶች እንደመሆናችን ለውጥ አያመጣም:: ግን
ለብፁዕነትዎ ገበታ ሲቀርብ አሁን የትኛው ሳህን ሊቀርብ ነው?»
ጳጳሱ በመገረም ሴትዮዋን አተኩረው ተመለከቱ፡፡
«እንዴት እኮ! የቆርቆሮ ሣህን ቢሆን እንኳን! ሌላ ሣህን የለንም
ማለት ነው?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
መዳም ማግልዋር ትከሻቸውን ነቀነቁ፡፡
«የቆርቆሮ ሣህን እኮ ሽታ ያመጣል፡፡»
«እንግዲያውማ ከብረት የተሠራ ሣህን ካለ እርሱ ሊሆን ይችላል።»
መዳም ማግልቀር ፈገግ ብለው «እሱም ቢሆን ብረት ብረት ማለቱ
ይቀራል!» አሉ::
«እንግዲያውማ» አሉ ብፁዕነታቸው፤ «የእንጨት ወይም የሸክላ ሣህን መፈለግ ነዋ!»
ከጥቂት ጊዜ በኋላ በአለፈው ሌሊት ዣን ቫልዣ አብሮ ከቀረበበት ጠረጴዛ ላይ ቁርስ ተዘጋጀ:: ቁርስ እየበሉ ምንም ዓይነት አስተያየት ላልሰጡት እህታቸውና ለሚያጉረመርሙት ለመዳም ማግልዋር ዳቦ ሻይ
ውስጥ ነክሮ ለመብላት ማንኪያ ወይም ሹካ የማያስፈልግ መሆኑን በመግለጽ ሳቅ እያሉ ይናገራሉ::: ወዲያው እህትና ወንድም ቀና ብለው ሲተያዩ በር ይንኳኳል::
«ይግቡ» አሉ ጳጳሱ::
በሩ ተከፈተ:: ሦስት የሚያስፈሩና ለቤቱ እንግዳ የሆኑ ሰዎች ገቡ::
ሰዎቹ የአራተኛ ሰው አንገት ጨምድደው ይዘዋል:: ሦስቱ ሰዎች ፖሊሶች ሲሆኑ አራተኛው ሰው ዣን ቫልዣ ነበር፡፡
አዛዡ ወደፊት ቀደም ቀደም ብሎ በወታደር ደምብ መሠረት ለጳጳሱ
የክብር ሰላምታ ሰጠ፡፡
«ብፁዕነትዎ» አለ፡፡
እስከዚያች ደቂቃ ድረስ አኩርፎ ዝም ያለውና ያቀረቀረው ዣን
ቫልዣ ያዛዡን ንግግር አቋርጦ ጣልቃ በመግባት እፍረት እየተሰማው አንገቱን ቀና አደረገ፡፡
«አባታችን፤ የደብር ኣለቃ ብቻ አይደሉማ!» ሲል ተናገረ::
«ዝም በል!» አለ ፖሊሱ፡፡ «አባታችን እኮ ናቸው:: የብፁዕነታቸውን ማዕረግ እንኳን አታውቅም?»
ብፁዕነታቸው እድሜያቸው በፈቀደው መጠን በቶሎ ከገበታው ብድግ ብለው ወደ ሰዎቹ ጠጋ አሉ::
«መጣህ» አሉ ወደ ዣን ቫልዣ እየተመለከቱ፡፡ እንደገና በመገናኘ
ታችን ደስ ብሎኛል፡፡ ግን የሻማ ማብሪያዎችንም ጭምር ሰጥቼህ አልነበረም እንዴ፧ ምነው ተውካቸው? እነርሱም እኮ ከንጹህ ብር የተሠሩ ናቸው:: እስከ 200 ፍራንክ ያወጡልሃል፡፡ ከሣህኖቹ ነጥለህ ምነው አስቀረሃቸው?
ሲሉ ጠየቁት::
ዣን ቫልዣ አፉን ከፍቶ ብፁዕነታቸውን አፍጥጦ ተመለከተ፡፡ የሚሰማው ነገር እውነት መሆኑን ማመን አቃተው::
«አባታችን» አለ አዛዡ፣ «እንግዲያውስ ይህ ሰው ያለው ትክክል ነው ማለት ነዋ? እኛ ስንይዘው እንደገመገምነው የሚሸሽ ሰው ዓይነት መስሎን
ነበር፡፡ ስለዚህ ተጠራጥረን ያዝነው:: እነዚያን የብር እቃዎች መያዙ ደግሞ በይበልጥ አጠራጠረን፡፡»
«እና ተነጋግራችኋላ!» አሉ ጳጳሱ ፈገግ ብለው፤ «ትናንት ሌሊት ካስጠጉት ከአንድ ሽማግሌ መነኩሴ የተሰጠው እቃ ለመሆኑ ገልጾላችኋላ!
እናንተ ግን በመጠራጠር ይዛችሁት መጣችሁ! ተሳስታችኋል፡፡ እቃው
የራሱ ነው፡፡»
«እንዲህ ከሆነማ ሰውዬን በነፃ ልንለቅቀው እንችላለን» አለ አዛዡ፡፡
«ያለ ጥርጥር» ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ፡፡
ፖሊሶቹ ዣን ቫልዣን ለቀቁት:: ወደኋላ አፈገፈገ፡፡
«አሁን በእርግጥ በነፃ ሊለቁኝ ነው?» ሲል ዣን ቫልዣ እጅግ በጣም ዝቅተኛ በሆነ ድምፅ አጉረመረመ:: ቅዠት መሰለው እንጂ በውኑ እንደሆነ
አላመነም::
«አዎን፥ ልትሄድ ትችላለህ ፤ ነገር አይገባህም» አለ ፖሊሱ፡፡
«ወዳጄ» አሉ ጳጳሱ፤ «ከመሄድህ በፊት እነዚያም የሻማ ማብሪያዎች
የአንተ ስለሆኑ ውሰዳቸው::»
ጳጳሱ ወደ ምግብ ጠረጴዛ ሄደው የሻማ ማብሪያዎችን አምጥተው
ለዣን ቫልዣ ሰጡት:: ሁለቱ ሴቶች ተገርመው ከእዚያው ከገበታ ላይ
አቀርቅረው ቀሩ፡፡ ቃል አልተነፈሱም::
ዣን ቫልዣ ሰውነቱ ርድኦ መቆም ተሳነው:: የሻማ ማብሪያዎቹን
ተቀበለ፡፡ ፊቱ የኣውሬ መሰለ፡፡
«አሁን» አሉ ብፁዕነታቸው በሰላም መሄድ ትችላለህ፡፡» ከዚያም ብፁዕነታቸው ፊታቸውን ወደ ፖሊሶቹ ኣዙረው፤ «ልጆቼ፤ ወደ ሥራችሁ ልትመለሱ ትችላላችሁ» አሉ:: ፖሊሶቹ ወጥተው ሄዱ፡፡
ዣን ቫልዣ ራሱን ስቶ ከመሬት እንደሚዘረር ሰው ተንገዳገደ ፤ ግን አልወደቀም:: ጳጳሱ ወደ እርሱ ጠጋ ብለው ዝቅ ባለ ድምፅ የሚከተለውን ተናገሩ፡፡
«አትርሳ፣ ገንዘቡን እውነተኛና ታማኝ ሰው ለመሆን እጠቀምበታለሁ ብለህ ቃል የገባኸውን እስከ እድሜ ልክህ እንዳትረሳ፡፡»
ዣን ቫልዣ መቼ ቃል እንደገባላቸው ማስታወስ አቅቶት በመደናገር ዝም ብሎ ቆመ:: ጳጳሱ «ቃል የገባኸውን አትርሳ» በማለት አጥብቀው ጠይቀውታል፡: ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዣን ቫልዣ ፤ ከእንግዲህ
አንተ ለጥፋት ዓለም ሳይሆን ለደግነት የተመረጥህ ነህ:: ነፍስህን ነው የምገዛልህ:: የአንተን ነፍስ የምሰጠው የሁሉም በላይ ለሆነው ለአንድ
አምላክ ነው::»
ዣን ቫልዣ አገር ጥሎ እንደሚሸሽ ሰው እግሬ አውጪኝ በማለት
👍20❤3😁2
ከተማውን ጥሎ ወጣ፡፡ ከተማውን ለቅቆ ገጠር እስከገባ ድረስ እየተጣራ ነበር የሚሄደው፡፡ ወዴት እንደሚሄድ ሳያስተውል መንገድ እንደመራው ዝም እያለ ተጓዘ፡፡ ከነጋ ጀምሮ እህል አልቀመሰም:: ሆኖም የረሃብ ስሜት አልተሰማውም፡፡ ቁጣ ቁጣ ብሉታል፡፡ በማን ላይ ወይም በምን ምክንያት እንደተቆጣ ግን አያውቅም:: የሚቀጥለው ምን ይሆን ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
የገጠር አየር የልጅነት ጊዜውን አስታወሰው:: የልጅነት ዘመኑን ካስታወሰ በጣም ቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም ብዙ ኣሳቦች ተፈራረቁበት፡፡».....
💫ይቀጥላል💫
የገጠር አየር የልጅነት ጊዜውን አስታወሰው:: የልጅነት ዘመኑን ካስታወሰ በጣም ቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም ብዙ ኣሳቦች ተፈራረቁበት፡፡».....
💫ይቀጥላል💫
👍11❤1
#እብድ_እና_ዘመናይ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ጓደኛችን አመሃ አበደ !!
ድንገት ነው እንደ ትንታ፣ እንደ ሳል፣ እንደ ንጥሻ እብደቱ ያመለጠው፡፡ እቺ አይምሯችን ግን ከንቱ ናት ለካ! ደርሰን እናሞካሻታለን እንጂ አንዳንዴ እንዲህ ሜዳ ላይ ጣጥላን ትወፍፋለች ለካ፡፡
ሰው ከንቱ !! አይምሯችንን ልንጠብቃት ይገባል፣ አለች ስንላት ገደል ገብታ ገደል ታስገባናለች፣ወይኔ አምሽ! ምነው ሴት ሆኖ ተፈጥሮ በነበር !?..ይሻለው ነበር ! ባንዴ ከማበድ በየቀኑ ትንሽ ትንሽ ማበድ !
የስነ አእምሮ ጠበብት ሴቶች የማበድ እድላቸው ከወንዶች ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ ነው፤ ምክንያቱም ሴቶች ብስጭታቸውን፣ መከፋታቸውን በእንባ ይሸኙታል፤ በጩኸት ይሸውዱታል፤
ወንዶች ግን አፍነው ስለሚይዙት ውስጣቸው ይጠራቀምና ድንገት ገንፍሎ ጉድ ያደርጋቸዋል ይላሉ፡፡ በነጋዴ ቋንቋ ስንገልፀው ሴቶች የሚያብዱት በችርቻሮ ሲሆን ወንዶች ግን በጅምላ
ነው እንደማለት፡፡
ጓደኛችን አመሃ ኮሌጃችን ውስጥ ወላ ባለባበስ፣ ወላ በትምህርት የሚደነቅ ሲበዛ ዝምተኛ ልጅ ነበር፡፡ ሀይ፣ ባይ ነው ቅፅል ስሙ፡፡ በቃ ስንገናኝ ሃይ ይላል፡፡ አንዲት ቃል ሳይተነፍስ ስንለያይ፣ ባይ ! አምሻ ልዩ ልጅ ነበር፡፡ ምድረ ኩታራ ከየዶርማችን ሱክ ሱክ እያልን ወደ
ክላስ ስንጣደፍ አምሃ ፀዳ ባለ ፓጃሮ መኪናው ከተፍ ይላል፡፡ እንግዲህ እኛ ባየነው ነገር ሰላምን የምንለካ የዋህ ከተሜዎች የአመሃ ተድላ እና ሀብት ተደማምሮ እንኳን እብደት ድብርት
አመሃ አጠገብ ያልፋል ብለን በምን አባታችን ጠርጥረን፡፡ “ፀጉራም ውሻ አለ ሲባል ይሞታል እንዲሉ አበው በሀብት ፀጉር የደለበ የመሰለን አመሃ 'አለ' ስንለው ለቀቀ !!
አመሃ እና እኔ ጓደኞች ነን፡፡ እንደውም አመሃ ሁለት ጓደኛ ብቻ ነው ያለው፤ እኔና ናትናኤል የሚባል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አብረው ሳንፎርድ የተማሩ ልጅ፡፡ በቃ ሌላ ጓደኛ የለውም፡፡ያው ፍቅረኛው እንዳለች ሆና !! ቤቱ ሁሉ ወስዶ ከሞልቃቃ እናቱ ጋር አስተዋውቆኛል፡፡
እንደ አመሃ እናት በጣም አጭር ጅንስ ቁምጣ የለበሰች ወጣት እናት ከዛ በፊትም ከዛ በኋላም አይቼ አላውቅም፡፡ የእግሮቿ አረዛዘም፣ ሰበር ሰካ አረማመዷ ወጣት ይፈትናል፡፡ ከላይ ጣል
ያደረገችው ስስ ቦዲ ነገር የጡት መያዣዋን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ አምሃ ሁለታችንን ትቶን ወደ ውስጥ ሲገባ፣ “የዛሬ ልጆች ቆንጆዎች ናችሁ” አለችኝ፡፡ አነጋሯ እንደ ማስቲካ ይለጠጣል፤
ከአስተያየቷ ጋር ተዳምሮ አድናቆቷ እናታዊ አድናቆት አልመስልህ አለኝ፡፡ የለም የለም እቺ ሴት የእናት ቀለም የላትም፡፡
ፊት ለፊቴ ተቀምጣ አንድ እግሯን ሶፋው ላይ አውጥታ በረዥም የእጁ ጣቶች ጉልበቷን በስሱ እንደማከክ አደረገችው፡፡ ቁምጣዋ ተሰብስቦ የተላጠ ብርቱካን የመሰለ የደላው ሰውነቷን አጋለጠው፡፡ ጥርት ያለ የታፋዋ ቆዳ ላይና የሚያማምሩ የእግሯ ጣቶች ላይ ዓይኔን አለማሳረፍ አልቻልኩም፡፡ በዛ ላይ ውስጥን ሰርስሮ የሚያይ የሚመስል አስተያየቷ “ምነው ባልመጣሁ!"
አስባለኝ፡፡
በምድር ላይ ያሉ እናቶች ሁሉ ሽንሽን ቀሚስ ዩኒፎርማቸው ይመስለኝ ነበር። ያደግኩበት መንደር ሁሉም የሚለብሱት እንደዛ ስለነበረ ሲቀመጡ እንኳን ዘርፋፋ ቀሚሳቸውን እንዴት ሰብሰብ አድርገው እንደሚቀመጡ ሳስብ የዚች “እናት” ነገር ግራ ገባኝ፡፡ መቼም እናት ምን
መምሰል አለባት?” የሚል ጥያቄ ቢነሳ ያው “እናት መምሰል አለባት” ነው መልሱ፡፡ እቺ ሴት ግን ምኗም እናት አይመስልም፡፡ የእናት ለዛ የላትም፤ የእናት የዋህነት፣ ደግነት ፊቷ ላይ ከነአካቴው
የለም፡፡ ዘላ ያልጠገበች የአስረኛ ክፍል ተማሪ ነው የምትመስለው፡፡
የአመሃ አባት ውጭ አገር በሚገኝ ዩኒቨርስቲ መምህር ናቸው:: እናቱ አብራቸው ። እዛ እንዲኖሩ ብትለመን፣ ብትመከር “በአንገቴ ገመድ ቢገባ አልሄድም!” በማለቷ ሁለቱ ብቻውን
እዚህ በቅንጦት የተምነሸነሸ ቪላ ውስጥ ይኖራሉ፡፡ አባቱ በስድስት ወር አንዴ ብቅ እያሉ ይጎበኟቸዋል ራሱ አመሃ ነው የነገረኝ፡፡ ሁልጊዜም አባቱ ሲመጡ ታዲያ እናትና አባት ዱላ ቀረሽ ንትርክ ውስጥ ናቸው፡፡ ኣባት የሚስታቸውን ባህሪ ያውቁታል፡፡ ሚስትም የባሏን ባልነት
ባትረሳም የትዳሩ ነገር እጅ እጅ ብሏታል፡፡
የሆነው ሆኖ አምሃ አበደ፡፡ ከማበዱ በፊት የሚጠረጥር ዘመድ፣ በጊዜ አፋፍሶ ፀበል የሚወስድ ወዳጅ ዘመድ አጥቶ እንጂ አምሃ ግልፅ የሆኑ ምልከቶች ሲያሳይ ነበር በተለይ ለእኔ፡፡
ምልክት አንድ፡- ህዳር ላይ የሚያብድ፣ መስከረም ላይ ሱሪውን ከፍ ከፍ ያደርጋል ይላሉ እማማ ሩቂያ፣
አንድ ቀን አመሃ (ለይቶለት ከማበዱ አንድ ወር በፊት) ሱሪውን አስር ጊዜ ከፍ ከፍ ያደርጋል፡፡
“ሰፍቶሀል እንዴ ይሄ ሱሪ ? አልኩት፡፡ አይ ቀበቶዬን ረስቼ ሳላረገው ነው የመጣሁት አለኝ፣እንዲህ የምንባባለው ወደ ላይብረሪ እየሄድን ነበር፡፡ ላይብረሪ ውስጥ ጎን ለጎን
ለመቀመጥ ቦታ ስላልነበር በያገኘነው ወንበር ተራርቀን ተቀመጥን፡፡ ድንገት አመሃ ቁጭ ሲል ሸሚዙ ከኋላው
ሰብሰብ አለና ቀበቶ ማድረጉን አየሁ:: ያውም ጥቁር የቆዳ ቀበቶ፡፡ “ቀበቶ አላደረግኩም ማለቱ ገርሞኝ ሰንወጣ እጠይቀዋለሁ ብዬ በዛው ረሳሁት፡፡
ምልክት ሁለት፡- “አላህ ሲቆጣ በትር አይቆርጥም፡ ያደርጋል እንጂ ነገር እንዳይጥም” ይላሉ እማማ ሩቅያ፡ የሰፈራችን አድባር፡
እኔና አመሃ እንድ ታዋቂ ሬስቶራንት ውስጥ ገባንና ምግብ አዘዝን ፒዛ
አምሃ ቀመስ አደረገና አስተናጋጇን ጠርቶ ምንድን ነው ይሄ ሁሉ ጨው ቤቱ ውስጥ ያለውን ጨው ሁሉ ነው የሞጀራችሁት ?” ብሎ ጮኸባት፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ አመሃ ሲጮህም ሆነ በቁጣ ሲናገር ሰምቼ ስለማላውቅ ከምላሴ ያልቅ አመሃን እምኜው ነበር፡፡ አስተናጋጇ ግን በትህትና፣
“ይቅርታ እኛ ፒዛ ስናዘጋጅ ጨው እንጠቀምም፡ ደንበኛው ራሱ በሚፈልገው መጠን እንዲጠቀም ለብቻ ነው የምናቀርበው" አለች ፈታችን የተቀመጠውን የጨው እቃ እያሳየችን፡፡
“ሂጂ ወደዛ ! ይሄን ልመን እንችን ?” አላት ምላሱን በአስፈሪ ሁኔታ ጎልጉሎ በግራ እጁ ጫፉን በመያዝ በሹካው ጫፍ ለአስተናጋጇ እያሳያት፡ ፒዛውን ትተነው ሌላ ቤት ገባን፡፡ አመሃ ለስላሳ አዘዘ፡፡ አንድ ጊዜ ተጎንጭቶ ፊቱን አጨፈገገና፡ “ቱ " ብሎ ወለሉ ላይ ተፋው፡፡ ፊት ለፊት
ተቀምጠው የነበሩ ወንድና ሴት ፍቅረኛሞች ፊታቸውን አጨፈገጉና ተመለከቱት፡፡ “እንዴት ሚሪንዳ ውስጥ ሎሚ ትጨምራላችሁ ?” ብሎ እዛም ግብ ግብ ፈጠረ፡፡ በቃ ይሄ ልጅ ነገር
ሁሉ አልጥመው አለው፡፡ (ሊያብድ እስር ቀናት ብቻ ነበሩ የቀሩት)
ሦስተኛ ምልክት፡ እብድ
ሌላ ቀን መኪናውን እያሽከረከረ ወደ ማቆሚያው አመራና የዶክተር ታደሰን አሮጌ ዲኤክስ መኪና አርፋ በቆመችበት ከኋላዋ ገጫት፡፡ ድሮም ሆድ የባሳት ነበረች፡፡ ከዛም ሰው ተሰብስቦ ወሬ ሲያይ
አመሃ ረጋ ብሎ ወረደና ልክ እንደ ትራፊክ ፖሊስ ኮስተር ብሎ ግጭቱን ከተለያየ አቅጣጫ አይኑን እያጨነቆረና አንገቱን እየሰበቀ ከተመለከተ በኋላ (ፎቶ የሚያነሳ ነበር የሚመስለው) ወደ ዶክተር ታደሰ ቢሮ ሄደ፡፡ ሳያንኳኳ በሩን በርግዶ ገባና ዶክተሩ ላይ አፍጥጦ፣ “አንተን ብሎ
ዶከተር መኪና እንኳን በስርዓት ማቆም የማትችል…” ብሎ ሙልጭ አድርጎ ሰድቧቸው ወጣ፤
“ይሄ ልጅ እብድ ነው እንዴ ! አሉ ዶክተሩ፡፡
አራተኛው ምልክት፡- ዘመናይ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ጓደኛችን አመሃ አበደ !!
ድንገት ነው እንደ ትንታ፣ እንደ ሳል፣ እንደ ንጥሻ እብደቱ ያመለጠው፡፡ እቺ አይምሯችን ግን ከንቱ ናት ለካ! ደርሰን እናሞካሻታለን እንጂ አንዳንዴ እንዲህ ሜዳ ላይ ጣጥላን ትወፍፋለች ለካ፡፡
ሰው ከንቱ !! አይምሯችንን ልንጠብቃት ይገባል፣ አለች ስንላት ገደል ገብታ ገደል ታስገባናለች፣ወይኔ አምሽ! ምነው ሴት ሆኖ ተፈጥሮ በነበር !?..ይሻለው ነበር ! ባንዴ ከማበድ በየቀኑ ትንሽ ትንሽ ማበድ !
የስነ አእምሮ ጠበብት ሴቶች የማበድ እድላቸው ከወንዶች ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ ነው፤ ምክንያቱም ሴቶች ብስጭታቸውን፣ መከፋታቸውን በእንባ ይሸኙታል፤ በጩኸት ይሸውዱታል፤
ወንዶች ግን አፍነው ስለሚይዙት ውስጣቸው ይጠራቀምና ድንገት ገንፍሎ ጉድ ያደርጋቸዋል ይላሉ፡፡ በነጋዴ ቋንቋ ስንገልፀው ሴቶች የሚያብዱት በችርቻሮ ሲሆን ወንዶች ግን በጅምላ
ነው እንደማለት፡፡
ጓደኛችን አመሃ ኮሌጃችን ውስጥ ወላ ባለባበስ፣ ወላ በትምህርት የሚደነቅ ሲበዛ ዝምተኛ ልጅ ነበር፡፡ ሀይ፣ ባይ ነው ቅፅል ስሙ፡፡ በቃ ስንገናኝ ሃይ ይላል፡፡ አንዲት ቃል ሳይተነፍስ ስንለያይ፣ ባይ ! አምሻ ልዩ ልጅ ነበር፡፡ ምድረ ኩታራ ከየዶርማችን ሱክ ሱክ እያልን ወደ
ክላስ ስንጣደፍ አምሃ ፀዳ ባለ ፓጃሮ መኪናው ከተፍ ይላል፡፡ እንግዲህ እኛ ባየነው ነገር ሰላምን የምንለካ የዋህ ከተሜዎች የአመሃ ተድላ እና ሀብት ተደማምሮ እንኳን እብደት ድብርት
አመሃ አጠገብ ያልፋል ብለን በምን አባታችን ጠርጥረን፡፡ “ፀጉራም ውሻ አለ ሲባል ይሞታል እንዲሉ አበው በሀብት ፀጉር የደለበ የመሰለን አመሃ 'አለ' ስንለው ለቀቀ !!
አመሃ እና እኔ ጓደኞች ነን፡፡ እንደውም አመሃ ሁለት ጓደኛ ብቻ ነው ያለው፤ እኔና ናትናኤል የሚባል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አብረው ሳንፎርድ የተማሩ ልጅ፡፡ በቃ ሌላ ጓደኛ የለውም፡፡ያው ፍቅረኛው እንዳለች ሆና !! ቤቱ ሁሉ ወስዶ ከሞልቃቃ እናቱ ጋር አስተዋውቆኛል፡፡
እንደ አመሃ እናት በጣም አጭር ጅንስ ቁምጣ የለበሰች ወጣት እናት ከዛ በፊትም ከዛ በኋላም አይቼ አላውቅም፡፡ የእግሮቿ አረዛዘም፣ ሰበር ሰካ አረማመዷ ወጣት ይፈትናል፡፡ ከላይ ጣል
ያደረገችው ስስ ቦዲ ነገር የጡት መያዣዋን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ አምሃ ሁለታችንን ትቶን ወደ ውስጥ ሲገባ፣ “የዛሬ ልጆች ቆንጆዎች ናችሁ” አለችኝ፡፡ አነጋሯ እንደ ማስቲካ ይለጠጣል፤
ከአስተያየቷ ጋር ተዳምሮ አድናቆቷ እናታዊ አድናቆት አልመስልህ አለኝ፡፡ የለም የለም እቺ ሴት የእናት ቀለም የላትም፡፡
ፊት ለፊቴ ተቀምጣ አንድ እግሯን ሶፋው ላይ አውጥታ በረዥም የእጁ ጣቶች ጉልበቷን በስሱ እንደማከክ አደረገችው፡፡ ቁምጣዋ ተሰብስቦ የተላጠ ብርቱካን የመሰለ የደላው ሰውነቷን አጋለጠው፡፡ ጥርት ያለ የታፋዋ ቆዳ ላይና የሚያማምሩ የእግሯ ጣቶች ላይ ዓይኔን አለማሳረፍ አልቻልኩም፡፡ በዛ ላይ ውስጥን ሰርስሮ የሚያይ የሚመስል አስተያየቷ “ምነው ባልመጣሁ!"
አስባለኝ፡፡
በምድር ላይ ያሉ እናቶች ሁሉ ሽንሽን ቀሚስ ዩኒፎርማቸው ይመስለኝ ነበር። ያደግኩበት መንደር ሁሉም የሚለብሱት እንደዛ ስለነበረ ሲቀመጡ እንኳን ዘርፋፋ ቀሚሳቸውን እንዴት ሰብሰብ አድርገው እንደሚቀመጡ ሳስብ የዚች “እናት” ነገር ግራ ገባኝ፡፡ መቼም እናት ምን
መምሰል አለባት?” የሚል ጥያቄ ቢነሳ ያው “እናት መምሰል አለባት” ነው መልሱ፡፡ እቺ ሴት ግን ምኗም እናት አይመስልም፡፡ የእናት ለዛ የላትም፤ የእናት የዋህነት፣ ደግነት ፊቷ ላይ ከነአካቴው
የለም፡፡ ዘላ ያልጠገበች የአስረኛ ክፍል ተማሪ ነው የምትመስለው፡፡
የአመሃ አባት ውጭ አገር በሚገኝ ዩኒቨርስቲ መምህር ናቸው:: እናቱ አብራቸው ። እዛ እንዲኖሩ ብትለመን፣ ብትመከር “በአንገቴ ገመድ ቢገባ አልሄድም!” በማለቷ ሁለቱ ብቻውን
እዚህ በቅንጦት የተምነሸነሸ ቪላ ውስጥ ይኖራሉ፡፡ አባቱ በስድስት ወር አንዴ ብቅ እያሉ ይጎበኟቸዋል ራሱ አመሃ ነው የነገረኝ፡፡ ሁልጊዜም አባቱ ሲመጡ ታዲያ እናትና አባት ዱላ ቀረሽ ንትርክ ውስጥ ናቸው፡፡ ኣባት የሚስታቸውን ባህሪ ያውቁታል፡፡ ሚስትም የባሏን ባልነት
ባትረሳም የትዳሩ ነገር እጅ እጅ ብሏታል፡፡
የሆነው ሆኖ አምሃ አበደ፡፡ ከማበዱ በፊት የሚጠረጥር ዘመድ፣ በጊዜ አፋፍሶ ፀበል የሚወስድ ወዳጅ ዘመድ አጥቶ እንጂ አምሃ ግልፅ የሆኑ ምልከቶች ሲያሳይ ነበር በተለይ ለእኔ፡፡
ምልክት አንድ፡- ህዳር ላይ የሚያብድ፣ መስከረም ላይ ሱሪውን ከፍ ከፍ ያደርጋል ይላሉ እማማ ሩቂያ፣
አንድ ቀን አመሃ (ለይቶለት ከማበዱ አንድ ወር በፊት) ሱሪውን አስር ጊዜ ከፍ ከፍ ያደርጋል፡፡
“ሰፍቶሀል እንዴ ይሄ ሱሪ ? አልኩት፡፡ አይ ቀበቶዬን ረስቼ ሳላረገው ነው የመጣሁት አለኝ፣እንዲህ የምንባባለው ወደ ላይብረሪ እየሄድን ነበር፡፡ ላይብረሪ ውስጥ ጎን ለጎን
ለመቀመጥ ቦታ ስላልነበር በያገኘነው ወንበር ተራርቀን ተቀመጥን፡፡ ድንገት አመሃ ቁጭ ሲል ሸሚዙ ከኋላው
ሰብሰብ አለና ቀበቶ ማድረጉን አየሁ:: ያውም ጥቁር የቆዳ ቀበቶ፡፡ “ቀበቶ አላደረግኩም ማለቱ ገርሞኝ ሰንወጣ እጠይቀዋለሁ ብዬ በዛው ረሳሁት፡፡
ምልክት ሁለት፡- “አላህ ሲቆጣ በትር አይቆርጥም፡ ያደርጋል እንጂ ነገር እንዳይጥም” ይላሉ እማማ ሩቅያ፡ የሰፈራችን አድባር፡
እኔና አመሃ እንድ ታዋቂ ሬስቶራንት ውስጥ ገባንና ምግብ አዘዝን ፒዛ
አምሃ ቀመስ አደረገና አስተናጋጇን ጠርቶ ምንድን ነው ይሄ ሁሉ ጨው ቤቱ ውስጥ ያለውን ጨው ሁሉ ነው የሞጀራችሁት ?” ብሎ ጮኸባት፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ አመሃ ሲጮህም ሆነ በቁጣ ሲናገር ሰምቼ ስለማላውቅ ከምላሴ ያልቅ አመሃን እምኜው ነበር፡፡ አስተናጋጇ ግን በትህትና፣
“ይቅርታ እኛ ፒዛ ስናዘጋጅ ጨው እንጠቀምም፡ ደንበኛው ራሱ በሚፈልገው መጠን እንዲጠቀም ለብቻ ነው የምናቀርበው" አለች ፈታችን የተቀመጠውን የጨው እቃ እያሳየችን፡፡
“ሂጂ ወደዛ ! ይሄን ልመን እንችን ?” አላት ምላሱን በአስፈሪ ሁኔታ ጎልጉሎ በግራ እጁ ጫፉን በመያዝ በሹካው ጫፍ ለአስተናጋጇ እያሳያት፡ ፒዛውን ትተነው ሌላ ቤት ገባን፡፡ አመሃ ለስላሳ አዘዘ፡፡ አንድ ጊዜ ተጎንጭቶ ፊቱን አጨፈገገና፡ “ቱ " ብሎ ወለሉ ላይ ተፋው፡፡ ፊት ለፊት
ተቀምጠው የነበሩ ወንድና ሴት ፍቅረኛሞች ፊታቸውን አጨፈገጉና ተመለከቱት፡፡ “እንዴት ሚሪንዳ ውስጥ ሎሚ ትጨምራላችሁ ?” ብሎ እዛም ግብ ግብ ፈጠረ፡፡ በቃ ይሄ ልጅ ነገር
ሁሉ አልጥመው አለው፡፡ (ሊያብድ እስር ቀናት ብቻ ነበሩ የቀሩት)
ሦስተኛ ምልክት፡ እብድ
ሌላ ቀን መኪናውን እያሽከረከረ ወደ ማቆሚያው አመራና የዶክተር ታደሰን አሮጌ ዲኤክስ መኪና አርፋ በቆመችበት ከኋላዋ ገጫት፡፡ ድሮም ሆድ የባሳት ነበረች፡፡ ከዛም ሰው ተሰብስቦ ወሬ ሲያይ
አመሃ ረጋ ብሎ ወረደና ልክ እንደ ትራፊክ ፖሊስ ኮስተር ብሎ ግጭቱን ከተለያየ አቅጣጫ አይኑን እያጨነቆረና አንገቱን እየሰበቀ ከተመለከተ በኋላ (ፎቶ የሚያነሳ ነበር የሚመስለው) ወደ ዶክተር ታደሰ ቢሮ ሄደ፡፡ ሳያንኳኳ በሩን በርግዶ ገባና ዶክተሩ ላይ አፍጥጦ፣ “አንተን ብሎ
ዶከተር መኪና እንኳን በስርዓት ማቆም የማትችል…” ብሎ ሙልጭ አድርጎ ሰድቧቸው ወጣ፤
“ይሄ ልጅ እብድ ነው እንዴ ! አሉ ዶክተሩ፡፡
አራተኛው ምልክት፡- ዘመናይ
👍19❤1🤔1
ሄለን የምትባል ዘመናዊ የዲፓርትመንታችን ልጅ አለች፡፡ ምንም ነገር ስትናገር ለነገ የማትል፤
“ውይ እሷ ጣጣ የላትም፣ ፍሪ እኮ ነች” እያለ ለእብደት የቀረበ ዘመናዊነቷን ተማሪው ያባባሰባት፡፡ አመሃ ጋር አንድ ሰፈር ናቸው፡፡ እንደውም ቤተሰብ ናቸው ማለት ይቀላል፡፡
አንድ ቀን አምሃ፣ እኔ፣ እሷ ሆነን ዩኒቨርስቲው መናፈሻ ውስጥ እንደተቀመጥን አንዱ አስተማሪ በፊታችን ሲያልፍ፣ “ይሄ ስድ የሆነ ሰውዬ ባለፈው ቢሮው አስገብቶ ቀሚሴን ሊገልበው…” አለች፡፡
"ምን? ያንቺን ቀሚስ ሊገልብ ይሄ ቆሻሻ ብሎ አምሃ ወደ ሰውየው ሲንደረደር ሲነሳ
እንቅ አድርጌ ያዝኩት መጠርጠር ጀምሬ ነበር አምሽ ለቀቅ እያደረገ እንደነበር፡፡
"ምን ነካህ አምሃ ስትቀልድ እኮ ነው እሷ !" አልኩት፡፡
እየቀለድሽ ነው ? አላት አምሃ ወደ ሄለን ዞሮ፡፡ አዎ እንድትል ጠቀስኳት፣
"አዎ" ከማለቷ፣ አመሃ በጥፊ አጮላት፡፡ አስደንጋጭ ነገር ነበር፡፡ ስድድብ ጀመሩ፤
"ጀዝባ" አለችው፡፡ ሰው ስትሳደብ አይቻት አላውቅም፡፡ መናፈሻው ውስጥ ያለ ተማሪ ሁሉ ወደ እኛ ዞረ፡፡
"ሸርሙጣ" : አላት፡፡ ከአምሃ ይሄ ቃል ይውጣል ብሎ ማንም አይገምትም፡፡
"ቆሻሻ" : አለችው::
“ግማታም!” አላት፡፡
"ስማ አባትህ ቾክ እያቦነነ ባመጣው ገንዘብ ስትሞላቀቅ ጠገብክ !"
"እና እንዳንቺ እናት በመሸርሞጥ ሃብታም መሆን ይሻላል ?” ተማሪ በተሰበሰበበት እብድና ዘመናይ ልክ ልካቸውን ተነጋገሩ፡፡ አመሃ ሊለይለት ሶስት ቀን ቀርቶት ነበር፡፡
ስድስተኛው ምልክት፡- ልበቢስ
የመጀመሪያውን ሴሚስተር ጨርሰን ሁለተኛውን መጀመራችን ነበር፡፡አዲስ ኮርስ የሚሰጡን መምህር ወደ ክላስ ገቡ፡፡ ፀጉራቸው ወደ ኋላ የተደለሰ ህንዳዊ ናቸው፡፡ ስታትስቲክስ
የሚባል ኮርስ ነው የሚያስተምሩት፡፡ ይሄ መምህር ከአንድ የመንግስት የኒቨርስቲ
በተማሪዎቹ የአንፈልጋቸውም ተቃውሞ የተባረሩ ህንዳዊ ቢሆኑም አሁን የምንማርበት ኮሌጅ ግን፣ ከውጭ በመጡ ታዋቂ መምህራን..." እያለ የቴሌቪዥን ማስታወቂያ የሚሰራባቸው የስንፍና ጥግ ናቸው፡፡ ያው እንግዳ ተቀባይ ነንና አከብረን ተቀበልናቸው፡፡
በተኮላተፈ እንግሊዝኛቸው ማስተማር ጀመሩ፤
ስታትስቲክስ ከሌሎች የጥናት መስኮች የሚለየው አንዲት አገር የልብ ምቷን' የምታዳምጥበት መሳሪያ በመሆኑ ነው አሉ በኩራት፡፡
አምሃ ድንገት ብድግ ብሎ "ዝም በል" አላቸው፡፡
“ቲቸርን ከራማቸውን ነው የገፈፈው፡፡ እኛንም እንጂ !
አመሃ በብስጭት ዲስኩሩን ቀጠለ፡፡ “ሁሉም አስተማሪ እየመጣ 'የልብ ምት፣ የልብ ምት ይልብናል፡፡ ኢኮኖሚክስ¨ የአንዲት አገር የልብ ምት የሚለካበት የጥናት መስክ ነው ሕግ የአንዲት አገር የልብ ምት የሚለካበት ፖለቲካል ሳይንስ ሁለንተናዊ የአገር የልብ ትርታን
የሚያዳምጥ የጥናት ዘርፍ ነው… ቆይ የዚች አገር ልብ በስንቱ ነው የሚለካው? ሲጀመር አገራችን ልብ ቢኖራት እንዳንተ አይነቱ ፊት ታስቀምጠን ነበር?
አገራችን ልብ አላት ወይስ የላትም? የሚለውን ሃቅ የሚያጠና የትምህርት ዘርፍ ያስፈልገናል፤ የልብ ትርታ ከመለካታችን በፊት ልብ መለኪያውን ይዞ ከየዩንቨርስቲው በየዓመቱ ወደ ሕዝብ
የሚጎርፈው ሁሉ እዚህ ልብ የለም፣ የምትሄድበት ሄደህ ፈልግ፣ ካልሆነም ልብ ፍጠር እየተባለ ስለ የትኛው ልብ፣ ስለየትኛው ትርታ ነው የምትቀባጥረው ? ሳልፈልግ ብዙ አታስወራኝ ሃሃሃሃሃሃሃ
አመሃ ለየለት !! አፋፍሰን አማኑኤል ወሰድነው፡፡ እዛው ቀረ !! እናቱ ተጠርታ መጣች::ሰውነቷ ላይ ጥብቅ ያለች አጭር ሚኒስከርት ለብሳ ከመኪናዋ ወረደችና ሰበር ሰካ እያለች ወደ እኔ መጣች፡፡
“ምን ሆኖ ነው ” አለችኝ፣
ነገርኳት፡፡
“ድሮም የአባቱ ልጅ ነው፣ ሴታ ሴት፣ ለየለት” አለች በብስጭት፡፡ ምን እንዳበሳጫት አላወቅኩም፤
ከብዙ ጊዜ በኋላ ሄለን አመሃ በእናቱ ምከንያት አዕምሮው እንደተናጋ አወጋችኝ፡፡
"አንድ ቀን አምሃ ሶደሬ ሲሄድ ከሴት ጓደኛው ጋር ቀጠሮ ያዙ፡፡ ታውቃት የለ ያች ሚዳቆ የመሰለች ጓደኛው፡፡ እናልህ ለእናቱም ይሄንኑ ነግሯት መንገድ እንደ ጀመሩ የጓደኛው እናት የደም ግፊታቸው ከፍ ብሎ ጉዟቸው ተሰናከለ፡፡ ሆስፒታል ቆይቶ ወደ ቤቱ ሲመለስ እናቱ
ናትናኤል ከሚባለው ከራሱ ከአመሃ ጓደኛ ጋር ያውም አባቱ አልጋ ላይ…ሂሂሂሂሂሂ”
ሄለን 'ፍሪ ስለሆነች በሚያሳብድ ቃል ነው የነገረችኝ፤ መሳቋ አበሳጨኝ፡፡
“አብርሽ” አለችኝ እየሳቀች፡፡
“ምን ሆንሽ !” አወራሯ አበሳጭቶኝ ነበር፡፡
“ተረኛው አንተ ነህ.…ሂሂሂሂሂ”
ተራዬ ለእብደቱ ይሁን ... አልገባኝም፤ ግን አልጠየቅኳትም፡፡ ምክንያቱም ሄለንም በጅምላ አብዳ ሳይንሱን ጉድ ልታደርገው እየተዘጋጀች ስለመሰለኝ ነበር፡፡
✨አለቀ✨
“ውይ እሷ ጣጣ የላትም፣ ፍሪ እኮ ነች” እያለ ለእብደት የቀረበ ዘመናዊነቷን ተማሪው ያባባሰባት፡፡ አመሃ ጋር አንድ ሰፈር ናቸው፡፡ እንደውም ቤተሰብ ናቸው ማለት ይቀላል፡፡
አንድ ቀን አምሃ፣ እኔ፣ እሷ ሆነን ዩኒቨርስቲው መናፈሻ ውስጥ እንደተቀመጥን አንዱ አስተማሪ በፊታችን ሲያልፍ፣ “ይሄ ስድ የሆነ ሰውዬ ባለፈው ቢሮው አስገብቶ ቀሚሴን ሊገልበው…” አለች፡፡
"ምን? ያንቺን ቀሚስ ሊገልብ ይሄ ቆሻሻ ብሎ አምሃ ወደ ሰውየው ሲንደረደር ሲነሳ
እንቅ አድርጌ ያዝኩት መጠርጠር ጀምሬ ነበር አምሽ ለቀቅ እያደረገ እንደነበር፡፡
"ምን ነካህ አምሃ ስትቀልድ እኮ ነው እሷ !" አልኩት፡፡
እየቀለድሽ ነው ? አላት አምሃ ወደ ሄለን ዞሮ፡፡ አዎ እንድትል ጠቀስኳት፣
"አዎ" ከማለቷ፣ አመሃ በጥፊ አጮላት፡፡ አስደንጋጭ ነገር ነበር፡፡ ስድድብ ጀመሩ፤
"ጀዝባ" አለችው፡፡ ሰው ስትሳደብ አይቻት አላውቅም፡፡ መናፈሻው ውስጥ ያለ ተማሪ ሁሉ ወደ እኛ ዞረ፡፡
"ሸርሙጣ" : አላት፡፡ ከአምሃ ይሄ ቃል ይውጣል ብሎ ማንም አይገምትም፡፡
"ቆሻሻ" : አለችው::
“ግማታም!” አላት፡፡
"ስማ አባትህ ቾክ እያቦነነ ባመጣው ገንዘብ ስትሞላቀቅ ጠገብክ !"
"እና እንዳንቺ እናት በመሸርሞጥ ሃብታም መሆን ይሻላል ?” ተማሪ በተሰበሰበበት እብድና ዘመናይ ልክ ልካቸውን ተነጋገሩ፡፡ አመሃ ሊለይለት ሶስት ቀን ቀርቶት ነበር፡፡
ስድስተኛው ምልክት፡- ልበቢስ
የመጀመሪያውን ሴሚስተር ጨርሰን ሁለተኛውን መጀመራችን ነበር፡፡አዲስ ኮርስ የሚሰጡን መምህር ወደ ክላስ ገቡ፡፡ ፀጉራቸው ወደ ኋላ የተደለሰ ህንዳዊ ናቸው፡፡ ስታትስቲክስ
የሚባል ኮርስ ነው የሚያስተምሩት፡፡ ይሄ መምህር ከአንድ የመንግስት የኒቨርስቲ
በተማሪዎቹ የአንፈልጋቸውም ተቃውሞ የተባረሩ ህንዳዊ ቢሆኑም አሁን የምንማርበት ኮሌጅ ግን፣ ከውጭ በመጡ ታዋቂ መምህራን..." እያለ የቴሌቪዥን ማስታወቂያ የሚሰራባቸው የስንፍና ጥግ ናቸው፡፡ ያው እንግዳ ተቀባይ ነንና አከብረን ተቀበልናቸው፡፡
በተኮላተፈ እንግሊዝኛቸው ማስተማር ጀመሩ፤
ስታትስቲክስ ከሌሎች የጥናት መስኮች የሚለየው አንዲት አገር የልብ ምቷን' የምታዳምጥበት መሳሪያ በመሆኑ ነው አሉ በኩራት፡፡
አምሃ ድንገት ብድግ ብሎ "ዝም በል" አላቸው፡፡
“ቲቸርን ከራማቸውን ነው የገፈፈው፡፡ እኛንም እንጂ !
አመሃ በብስጭት ዲስኩሩን ቀጠለ፡፡ “ሁሉም አስተማሪ እየመጣ 'የልብ ምት፣ የልብ ምት ይልብናል፡፡ ኢኮኖሚክስ¨ የአንዲት አገር የልብ ምት የሚለካበት የጥናት መስክ ነው ሕግ የአንዲት አገር የልብ ምት የሚለካበት ፖለቲካል ሳይንስ ሁለንተናዊ የአገር የልብ ትርታን
የሚያዳምጥ የጥናት ዘርፍ ነው… ቆይ የዚች አገር ልብ በስንቱ ነው የሚለካው? ሲጀመር አገራችን ልብ ቢኖራት እንዳንተ አይነቱ ፊት ታስቀምጠን ነበር?
አገራችን ልብ አላት ወይስ የላትም? የሚለውን ሃቅ የሚያጠና የትምህርት ዘርፍ ያስፈልገናል፤ የልብ ትርታ ከመለካታችን በፊት ልብ መለኪያውን ይዞ ከየዩንቨርስቲው በየዓመቱ ወደ ሕዝብ
የሚጎርፈው ሁሉ እዚህ ልብ የለም፣ የምትሄድበት ሄደህ ፈልግ፣ ካልሆነም ልብ ፍጠር እየተባለ ስለ የትኛው ልብ፣ ስለየትኛው ትርታ ነው የምትቀባጥረው ? ሳልፈልግ ብዙ አታስወራኝ ሃሃሃሃሃሃሃ
አመሃ ለየለት !! አፋፍሰን አማኑኤል ወሰድነው፡፡ እዛው ቀረ !! እናቱ ተጠርታ መጣች::ሰውነቷ ላይ ጥብቅ ያለች አጭር ሚኒስከርት ለብሳ ከመኪናዋ ወረደችና ሰበር ሰካ እያለች ወደ እኔ መጣች፡፡
“ምን ሆኖ ነው ” አለችኝ፣
ነገርኳት፡፡
“ድሮም የአባቱ ልጅ ነው፣ ሴታ ሴት፣ ለየለት” አለች በብስጭት፡፡ ምን እንዳበሳጫት አላወቅኩም፤
ከብዙ ጊዜ በኋላ ሄለን አመሃ በእናቱ ምከንያት አዕምሮው እንደተናጋ አወጋችኝ፡፡
"አንድ ቀን አምሃ ሶደሬ ሲሄድ ከሴት ጓደኛው ጋር ቀጠሮ ያዙ፡፡ ታውቃት የለ ያች ሚዳቆ የመሰለች ጓደኛው፡፡ እናልህ ለእናቱም ይሄንኑ ነግሯት መንገድ እንደ ጀመሩ የጓደኛው እናት የደም ግፊታቸው ከፍ ብሎ ጉዟቸው ተሰናከለ፡፡ ሆስፒታል ቆይቶ ወደ ቤቱ ሲመለስ እናቱ
ናትናኤል ከሚባለው ከራሱ ከአመሃ ጓደኛ ጋር ያውም አባቱ አልጋ ላይ…ሂሂሂሂሂሂ”
ሄለን 'ፍሪ ስለሆነች በሚያሳብድ ቃል ነው የነገረችኝ፤ መሳቋ አበሳጨኝ፡፡
“አብርሽ” አለችኝ እየሳቀች፡፡
“ምን ሆንሽ !” አወራሯ አበሳጭቶኝ ነበር፡፡
“ተረኛው አንተ ነህ.…ሂሂሂሂሂ”
ተራዬ ለእብደቱ ይሁን ... አልገባኝም፤ ግን አልጠየቅኳትም፡፡ ምክንያቱም ሄለንም በጅምላ አብዳ ሳይንሱን ጉድ ልታደርገው እየተዘጋጀች ስለመሰለኝ ነበር፡፡
✨አለቀ✨
👍25❤5🤔1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ከተማውን ጥሎ ወጣ፡፡ ከተማውን ለቅቆ ገጠር እስከገባ ድረስ እየተጣራ ነበር የሚሄደው፡፡ ወዴት እንደሚሄድ ሳያስተውል መንገድ እንደመራው ዝም እያለ ተጓዘ፡፡ ከነጋ ጀምሮ እህል አልቀመሰም:: ሆኖም የረሃብ ስሜት አልተሰማውም፡፡ ቁጣ ቁጣ ብሉታል፡፡ በማን ላይ ወይም በምን ምክንያት እንደተቆጣ ግን አያውቅም:: የሚቀጥለው ምን ይሆን ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
የገጠር አየር የልጅነት ጊዜውን አስታወሰው:: የልጅነት ዘመኑን ካስታወሰ በጣም ቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም ብዙ ኣሳቦች ተፈራረቁበት፡፡»
ፀሐይ አሽቆልቁላ ገብታ ከአድማስ ውስጥ ልትገባ ስትል ዣን ቫልዣ
እልም ካለ ጫካ ውስጥ ከአንዲት ጉብታ ላይ ቁጭ ብሎአል፡፡ የአልፕስ ተራራ በሩቁ ይታያል፡፡ ከጫካው ወጣ እንዳለ አንድ ቀጭን የእግር መንገድ አለ፡፡
ከዚህ ቁጭ ብሎ ሲያሰላስል ደስ የሚል ድምፅ ይሰማል፡፡ ፊቱን
ሲያዞር ወደ አሥራ ሁለት ዓመት የሚሆነው ልጅ እየዘመረ ወደ እርሱ ይመጣል:: ልጁ በጭንቅላቱ ሣጥን መሳይ ነገር ተሸክሞአል፡፡ ልጁ ጥቂት
ከተራመደ በኋላ ቆም ብሎ በእጁ የያዘውን ሣንቲም ወደ ሰማይ እያጎነ ይጫወታል:: የልጁ ሀብት ምናልባት ይኸው ነጭ ሽልንግ ብቻ ሳይሆን አልቀረም::
ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት ሲደርስ የሰውዬው ከእዚያ መኖር ሳይገነዘብ ቆም አለ፡፡ እንደ ልማዱ ሣንቲሙን ወደ ሰማይ አጎነ፡ ሣንቲሙ አምልጦት
ከመሬት ሊወድቅ ዣን ቫልዣ ወደ ተቀመጠበት በረረ:: ዣን ቫልዣ
ሽልንጉን በእግሩ ረግጦ ያዘበት:: የልጁ ዓይን ሣንቲሙን ተከትሎ ስለሄደ የት ላይ እንዳለ ያውቃል፡፡ ልጁ አልፈራም፤ በቀጥታ ወደ ሰውዬው ሄደ::
«ጌታዬ ገንዘቤን» አለ ልጁ የዋህነትና ድንቁርና በተሞላበት አንደበት::
«ስምህ ማነው?» ሲል ዣን ቫልዣ ጠየቀው::
«ትንሹ ዥራቪ ነው ጌታዬ::»
«ቶሉ ከዚህ ጥፋ» አለው ዣን ቫልዣ ::
«ፍራንኬስ?» ሲል ልጁ ጠየቀ፡፡
ዣን ቫልዣ እንዳቀረቀረ ቀረ::
«ገንዘቤን» አለ ልጁ እምባ እየተናነቀወ :: ሽልንጌን!»
ዣን ቫልዣ ምንም ነገር እንዳልሰማ ሰው ፀጥ አለ፡፡ ልጁ የሰውየውን ሸሚዝ ኮሌታ በአንድ እጁ ያዘ፡፡ በሌላው እጁ ሣንቲሙን ለማስለቀቅ የሰውየውን እግር ለማንሳት ሞከረ::
«ገንዘቤን እፈልጋለሁ ፧ ሽልጌን!» ብሎ ከጮኸ በኋላ ትንሹ ዠራቬ
ማልቀስ ጀመረ:: ዣን ቫልዣ አንገቱን ቀና አደረገ፡፡ ከተቀመጠበት ግን አልተነሳም:: ፊቱ፡ በአሳብ የተዋጠና የተጨነቀ ይመስላል፡፡ በመገረም ልጁን
አትኩሮ አየው:: ዱላውን ሳብ ኣድርጎ «አንተ ማነህ? እህ! ምንድነው የምትፈልገው? እስካሁን አልሄድክም እንዴ» ሲል በሚያስፈራ ድምፅ ጮኸበት:: ሣንቲሙን እንደረገጠ ከመቀመጫው ብድግ ብላ «ራስህን ብትጠብቅ ይሻልሃል» አለው::
ልጁ በፍርሃት ተወጦ ቀና ብላ አየወ:: ሰውነቱ ይንቀጠቀጥ
ጀመር፡፡ ወዲያው ከጥቂት ሰኮንድ መርበትበት በኋላ ልጁ አግሬ አውጪኝ ብሎ ሸመጠጠ፡፡ ዞር ብሎ ለማየት ወይም ጩኸት ለማሰማት እንኳን አልደፈረም፡፡ ሆኖም ጥቂት እንደተጓዘ ትንፋሽ አጥሮት ቆም አለ:: ግን ብዙ
አልቆመም፧ መንገዱን ቀጠለ፡፡
ፀሐይዋ ጠለቀች፡፡ ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት አካባቢ ብርሃን ለጨለማ ሥፍራዋን ለቀቀች:: ቀኑን መሉ ምግብ የሚሉት ነገር አልቀመሰም::ምናልባትም ትንሽ እንደትኩሳት ብጤ ሳይሞካክረው አልቀረም::
ልጁ ከሄደ ጀምሮ ከተቀመጠበት ነቅነቅ አላለም:: በኃይል ነው
የሚተነፍሰው:: ከተቀመጠበት ጥቂት ራቅ ብሎ ከነበረው የሸክላ ስባሪ ገል ላይ ዓይኑን ተከለ፡፡ ስለገሉ ይመራመር ጀመር፡፡ ግን በድንገት መላ ሰውነቱ
ተንቀጠቀጠ፡፡ የሌሊቱ ቁር እየተሰማው ሄደ፡፡
ቆቡን ሳብ አድርጎ ግንባሩን ሸፈነ:: የሸሚዙን አዝራር ለመቆለፍ
ጣቶቹ አዝራር ፍለጋ ላይ ታች አሉ:: ብድግ ብሎ ወደፊት ራመድ ካለ ከኋላ መለስ ብሉ ዱላውን ለማንሳት ጎንበስ አለ፡፡
በእግሩ ረግጦ ይዞት የነበረው ሽልንግ በማብረቅረቁ ዓይኑ ወደዚያ ተሳበ፡፡ ኮረንቲ እንደያዘው ሰው ተሸማቀቀ፡፡ «ምንድነው ነገሩ?» ሲል ጥርሱን በማፋጨት ራሱን ጠየቀ:: እንደገና ወደኋላ መለስ ብሉ ሣንቲሙን በእግሩ በመርገጥ ሸፈነው:: ሣንቲሙ ዓይን አብቅሎ የሚያየው መሰለው::
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ እግሩን መነጨቀና ጎንበስ ብሎ ሣንቲሙን
አነሳ፡፡ ቀና ብሎ አካባቢውን ተመለከተ:: ጋራውና ሸንተረሩ ሁሉ የሚያየው ስለመሰለው በፍርሃት ተውጦ መወጊያ እንደምትፈልግ ዱኮላ ዓይኑ በፍርሃት ተቅበዘበዘ፡፡ ከቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡
ምንም ነገር አላየም:: ጊዜው እየጨለመና አየሩ እጅግ እየቀዘቀዘ ሄደ:: ሰማዩ በጭጋግ ተሸፈነ፡፡
«ወይ ጣጣ» ሲል ልጁ በሄደበት አቅጣጫ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ አንድ
ሰላሳ - እርምጃ ያህል እንደተራመደ ቆም ኣለ፡፡ አካባቢውን ተመለከቱ።
ምንም ነገር የለም:: ድምፁን እጅግ ከፍ አድርጎ «ዠራቬ» ሲል ተጣራ፡፡ ከዚያም ድምፁ
አጥፍቶ አዳመጠ:: መልስ አላገኘም፡፡
አገሩ ጭር ያለና ጭጋጋም ቢሆንም አካባቢው በግልጽ ይታያል ከዝምታና ከራሱ ጥላ በስተቀር የሚንቀሳቀስ ፍጠር ጨርሶ አልነበረም ዣን ቫልዣ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የሚወስደውን እርምጃ ፍጥነት በመጨመር እንደ መሮጥ አለ። አልፎ አልፎ ቆም እያለ በሚያስፈራ ሻካራ ድምፅ «ዠራቬ» ሲል እንደገና ተጣራ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ልጁ ቢሰማው
እንኳን በፍርሃት ስለሚዋጥ ይደበቃል እንጂ መልስ አይሰጠውም:: ነገር ግን ልጁ በርግጥም በጣም ርቆ ሄዷል፡፡
ዣን ቫልዣ እንደገና ልጁ በሄደበት ኣቅጣጫ መሮጥ ጀመረ
እየተገላመጠ፣ እየጮኸ፣ እየተጣራ ብዘ ተጓዘ፡፡ ግን ማንንም አላገኘም በደረቱ ተንፏቅቆ የሚሄድ ወይም ድምፁን አጥፍቶ ያደፈጠ እየመሰለ ከአንዴም ሁለቴ፣ ከሁለቴም ሦስቴ መንገዱን ለቅቆ ወደ ጥሻው ዞር እያለ
ተመለከተ፡፡ ግን ሰው የመሰለው ነገር ጠጋ ሲል ቁጥቋጦ ወይም ድንጋ ሆኖ ያገኘዋል፡፡ በመጨረሻ ሦስት መንታ መንገዶች ከሚገናኙበት ደረሰ ከመሐል መንገድ ላይ ቆመ:: ጨረቃዋ ብቅ ብላለች:: ለማየት እስከቻለ
ድረስ አርቆ ተመለከተ:: «ዥራቬ፣ ትንሹ ዥራቬ፣ ዠራቬ» በማለት
ሦስት ጊዜ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተጣራ:: ድምፁ የገደል ማሚቶ እንኳ ሳያዕማ ከጭጋጉ ውስጥ ተውጦ ቀረ:: «ትንሹ ዥራቬ» ሲል ዝግ በደከመ ድምፅ አጉረመረመ:: ያ የመጨረሻው ሙከራ ነበር፡፡ በዓይ የማይታይ ኃይል በዱላ እንደመታው ሰው በድንገት እግሩ ተሳስሮ ጉልበቱ እጥፍጥፍ አለበት:: ፀጉሩን በእጁ ጨብጦና ፊቱን ጉልበቱ ላይ አሳርፎ
ከቋጥኝ ድንጋይ ላይ በመቀመጥ «ምን ዓይነት እድለቢስ ሰው ነኝ» አለ ጮኸ፡፡ ልቡ እያበጠ ሄደ፡፡ ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ ከአሥራ ዘጠኝ ዓመት ወዲህ ሲያለቅስ የመጀመሪያው ነበር:: ዣን ቫልዣ ብዙ አለቀሰ፡፡ ከሕፃኑ መባባትና ከሴቶች መርበትበት ይበልጥ በፍርሃት ተውጦ ከዓይኑ እምባ የወጣ እስኪመስለው ድረስ በማልቀስ አንጀቱን እርር ድብን አደረገ እያለቀሰ ሳለ ከሕሊናው ውስጥ የነበረው ብርሃን እየፈካ ሄደ፡፡
የተለየ ብርሃን ነበር፡፡ ያ ብርሃን አሳደደው፤ አስፈራራው፡፡ ያለፈው የሕይወቱ ዘመን፤ የመጀመሪያው ወንጀሉ፤ የረጅም ጊዜ ስቃዩ ፧ ጨካኙ ዓለም፤ የደነደነው ልቡ ፣ ከእስር ቤት ማምለጡ፤ ከጳጳሱ ቤት በእርሱ ላይ የደረሰው! የመጨረሻው አሳፋሪ ድርጊቱ ፤ ከሕፃን ልጅ ገንዘብ መዝረፉ፤
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ከተማውን ጥሎ ወጣ፡፡ ከተማውን ለቅቆ ገጠር እስከገባ ድረስ እየተጣራ ነበር የሚሄደው፡፡ ወዴት እንደሚሄድ ሳያስተውል መንገድ እንደመራው ዝም እያለ ተጓዘ፡፡ ከነጋ ጀምሮ እህል አልቀመሰም:: ሆኖም የረሃብ ስሜት አልተሰማውም፡፡ ቁጣ ቁጣ ብሉታል፡፡ በማን ላይ ወይም በምን ምክንያት እንደተቆጣ ግን አያውቅም:: የሚቀጥለው ምን ይሆን ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
የገጠር አየር የልጅነት ጊዜውን አስታወሰው:: የልጅነት ዘመኑን ካስታወሰ በጣም ቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም ብዙ ኣሳቦች ተፈራረቁበት፡፡»
ፀሐይ አሽቆልቁላ ገብታ ከአድማስ ውስጥ ልትገባ ስትል ዣን ቫልዣ
እልም ካለ ጫካ ውስጥ ከአንዲት ጉብታ ላይ ቁጭ ብሎአል፡፡ የአልፕስ ተራራ በሩቁ ይታያል፡፡ ከጫካው ወጣ እንዳለ አንድ ቀጭን የእግር መንገድ አለ፡፡
ከዚህ ቁጭ ብሎ ሲያሰላስል ደስ የሚል ድምፅ ይሰማል፡፡ ፊቱን
ሲያዞር ወደ አሥራ ሁለት ዓመት የሚሆነው ልጅ እየዘመረ ወደ እርሱ ይመጣል:: ልጁ በጭንቅላቱ ሣጥን መሳይ ነገር ተሸክሞአል፡፡ ልጁ ጥቂት
ከተራመደ በኋላ ቆም ብሎ በእጁ የያዘውን ሣንቲም ወደ ሰማይ እያጎነ ይጫወታል:: የልጁ ሀብት ምናልባት ይኸው ነጭ ሽልንግ ብቻ ሳይሆን አልቀረም::
ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት ሲደርስ የሰውዬው ከእዚያ መኖር ሳይገነዘብ ቆም አለ፡፡ እንደ ልማዱ ሣንቲሙን ወደ ሰማይ አጎነ፡ ሣንቲሙ አምልጦት
ከመሬት ሊወድቅ ዣን ቫልዣ ወደ ተቀመጠበት በረረ:: ዣን ቫልዣ
ሽልንጉን በእግሩ ረግጦ ያዘበት:: የልጁ ዓይን ሣንቲሙን ተከትሎ ስለሄደ የት ላይ እንዳለ ያውቃል፡፡ ልጁ አልፈራም፤ በቀጥታ ወደ ሰውዬው ሄደ::
«ጌታዬ ገንዘቤን» አለ ልጁ የዋህነትና ድንቁርና በተሞላበት አንደበት::
«ስምህ ማነው?» ሲል ዣን ቫልዣ ጠየቀው::
«ትንሹ ዥራቪ ነው ጌታዬ::»
«ቶሉ ከዚህ ጥፋ» አለው ዣን ቫልዣ ::
«ፍራንኬስ?» ሲል ልጁ ጠየቀ፡፡
ዣን ቫልዣ እንዳቀረቀረ ቀረ::
«ገንዘቤን» አለ ልጁ እምባ እየተናነቀወ :: ሽልንጌን!»
ዣን ቫልዣ ምንም ነገር እንዳልሰማ ሰው ፀጥ አለ፡፡ ልጁ የሰውየውን ሸሚዝ ኮሌታ በአንድ እጁ ያዘ፡፡ በሌላው እጁ ሣንቲሙን ለማስለቀቅ የሰውየውን እግር ለማንሳት ሞከረ::
«ገንዘቤን እፈልጋለሁ ፧ ሽልጌን!» ብሎ ከጮኸ በኋላ ትንሹ ዠራቬ
ማልቀስ ጀመረ:: ዣን ቫልዣ አንገቱን ቀና አደረገ፡፡ ከተቀመጠበት ግን አልተነሳም:: ፊቱ፡ በአሳብ የተዋጠና የተጨነቀ ይመስላል፡፡ በመገረም ልጁን
አትኩሮ አየው:: ዱላውን ሳብ ኣድርጎ «አንተ ማነህ? እህ! ምንድነው የምትፈልገው? እስካሁን አልሄድክም እንዴ» ሲል በሚያስፈራ ድምፅ ጮኸበት:: ሣንቲሙን እንደረገጠ ከመቀመጫው ብድግ ብላ «ራስህን ብትጠብቅ ይሻልሃል» አለው::
ልጁ በፍርሃት ተወጦ ቀና ብላ አየወ:: ሰውነቱ ይንቀጠቀጥ
ጀመር፡፡ ወዲያው ከጥቂት ሰኮንድ መርበትበት በኋላ ልጁ አግሬ አውጪኝ ብሎ ሸመጠጠ፡፡ ዞር ብሎ ለማየት ወይም ጩኸት ለማሰማት እንኳን አልደፈረም፡፡ ሆኖም ጥቂት እንደተጓዘ ትንፋሽ አጥሮት ቆም አለ:: ግን ብዙ
አልቆመም፧ መንገዱን ቀጠለ፡፡
ፀሐይዋ ጠለቀች፡፡ ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት አካባቢ ብርሃን ለጨለማ ሥፍራዋን ለቀቀች:: ቀኑን መሉ ምግብ የሚሉት ነገር አልቀመሰም::ምናልባትም ትንሽ እንደትኩሳት ብጤ ሳይሞካክረው አልቀረም::
ልጁ ከሄደ ጀምሮ ከተቀመጠበት ነቅነቅ አላለም:: በኃይል ነው
የሚተነፍሰው:: ከተቀመጠበት ጥቂት ራቅ ብሎ ከነበረው የሸክላ ስባሪ ገል ላይ ዓይኑን ተከለ፡፡ ስለገሉ ይመራመር ጀመር፡፡ ግን በድንገት መላ ሰውነቱ
ተንቀጠቀጠ፡፡ የሌሊቱ ቁር እየተሰማው ሄደ፡፡
ቆቡን ሳብ አድርጎ ግንባሩን ሸፈነ:: የሸሚዙን አዝራር ለመቆለፍ
ጣቶቹ አዝራር ፍለጋ ላይ ታች አሉ:: ብድግ ብሎ ወደፊት ራመድ ካለ ከኋላ መለስ ብሉ ዱላውን ለማንሳት ጎንበስ አለ፡፡
በእግሩ ረግጦ ይዞት የነበረው ሽልንግ በማብረቅረቁ ዓይኑ ወደዚያ ተሳበ፡፡ ኮረንቲ እንደያዘው ሰው ተሸማቀቀ፡፡ «ምንድነው ነገሩ?» ሲል ጥርሱን በማፋጨት ራሱን ጠየቀ:: እንደገና ወደኋላ መለስ ብሉ ሣንቲሙን በእግሩ በመርገጥ ሸፈነው:: ሣንቲሙ ዓይን አብቅሎ የሚያየው መሰለው::
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ እግሩን መነጨቀና ጎንበስ ብሎ ሣንቲሙን
አነሳ፡፡ ቀና ብሎ አካባቢውን ተመለከተ:: ጋራውና ሸንተረሩ ሁሉ የሚያየው ስለመሰለው በፍርሃት ተውጦ መወጊያ እንደምትፈልግ ዱኮላ ዓይኑ በፍርሃት ተቅበዘበዘ፡፡ ከቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡
ምንም ነገር አላየም:: ጊዜው እየጨለመና አየሩ እጅግ እየቀዘቀዘ ሄደ:: ሰማዩ በጭጋግ ተሸፈነ፡፡
«ወይ ጣጣ» ሲል ልጁ በሄደበት አቅጣጫ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ አንድ
ሰላሳ - እርምጃ ያህል እንደተራመደ ቆም ኣለ፡፡ አካባቢውን ተመለከቱ።
ምንም ነገር የለም:: ድምፁን እጅግ ከፍ አድርጎ «ዠራቬ» ሲል ተጣራ፡፡ ከዚያም ድምፁ
አጥፍቶ አዳመጠ:: መልስ አላገኘም፡፡
አገሩ ጭር ያለና ጭጋጋም ቢሆንም አካባቢው በግልጽ ይታያል ከዝምታና ከራሱ ጥላ በስተቀር የሚንቀሳቀስ ፍጠር ጨርሶ አልነበረም ዣን ቫልዣ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የሚወስደውን እርምጃ ፍጥነት በመጨመር እንደ መሮጥ አለ። አልፎ አልፎ ቆም እያለ በሚያስፈራ ሻካራ ድምፅ «ዠራቬ» ሲል እንደገና ተጣራ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ልጁ ቢሰማው
እንኳን በፍርሃት ስለሚዋጥ ይደበቃል እንጂ መልስ አይሰጠውም:: ነገር ግን ልጁ በርግጥም በጣም ርቆ ሄዷል፡፡
ዣን ቫልዣ እንደገና ልጁ በሄደበት ኣቅጣጫ መሮጥ ጀመረ
እየተገላመጠ፣ እየጮኸ፣ እየተጣራ ብዘ ተጓዘ፡፡ ግን ማንንም አላገኘም በደረቱ ተንፏቅቆ የሚሄድ ወይም ድምፁን አጥፍቶ ያደፈጠ እየመሰለ ከአንዴም ሁለቴ፣ ከሁለቴም ሦስቴ መንገዱን ለቅቆ ወደ ጥሻው ዞር እያለ
ተመለከተ፡፡ ግን ሰው የመሰለው ነገር ጠጋ ሲል ቁጥቋጦ ወይም ድንጋ ሆኖ ያገኘዋል፡፡ በመጨረሻ ሦስት መንታ መንገዶች ከሚገናኙበት ደረሰ ከመሐል መንገድ ላይ ቆመ:: ጨረቃዋ ብቅ ብላለች:: ለማየት እስከቻለ
ድረስ አርቆ ተመለከተ:: «ዥራቬ፣ ትንሹ ዥራቬ፣ ዠራቬ» በማለት
ሦስት ጊዜ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተጣራ:: ድምፁ የገደል ማሚቶ እንኳ ሳያዕማ ከጭጋጉ ውስጥ ተውጦ ቀረ:: «ትንሹ ዥራቬ» ሲል ዝግ በደከመ ድምፅ አጉረመረመ:: ያ የመጨረሻው ሙከራ ነበር፡፡ በዓይ የማይታይ ኃይል በዱላ እንደመታው ሰው በድንገት እግሩ ተሳስሮ ጉልበቱ እጥፍጥፍ አለበት:: ፀጉሩን በእጁ ጨብጦና ፊቱን ጉልበቱ ላይ አሳርፎ
ከቋጥኝ ድንጋይ ላይ በመቀመጥ «ምን ዓይነት እድለቢስ ሰው ነኝ» አለ ጮኸ፡፡ ልቡ እያበጠ ሄደ፡፡ ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ ከአሥራ ዘጠኝ ዓመት ወዲህ ሲያለቅስ የመጀመሪያው ነበር:: ዣን ቫልዣ ብዙ አለቀሰ፡፡ ከሕፃኑ መባባትና ከሴቶች መርበትበት ይበልጥ በፍርሃት ተውጦ ከዓይኑ እምባ የወጣ እስኪመስለው ድረስ በማልቀስ አንጀቱን እርር ድብን አደረገ እያለቀሰ ሳለ ከሕሊናው ውስጥ የነበረው ብርሃን እየፈካ ሄደ፡፡
የተለየ ብርሃን ነበር፡፡ ያ ብርሃን አሳደደው፤ አስፈራራው፡፡ ያለፈው የሕይወቱ ዘመን፤ የመጀመሪያው ወንጀሉ፤ የረጅም ጊዜ ስቃዩ ፧ ጨካኙ ዓለም፤ የደነደነው ልቡ ፣ ከእስር ቤት ማምለጡ፤ ከጳጳሱ ቤት በእርሱ ላይ የደረሰው! የመጨረሻው አሳፋሪ ድርጊቱ ፤ ከሕፃን ልጅ ገንዘብ መዝረፉ፤
👍22😁1
ጳጳሱ ይቅርታ ካወረዱለት በኋላ የተፈጸመ አሰቃቂና አስፈሪ ወንጀል መሆኑ፤ ይህ ሁሉ ከዓይነ ልቦናው ውስጥ እየተመላለሰ ከዚያ በፊት ታይቶት በማይታወቅ ዓይነት ቁልጭ ብሎ ታየው:: ያለፈውን የሕይወቱን ምዕራፍ በአሳብ በተመለከተው ጊዜ እጅግ አስቀያሚና አስከፊ መሆኑን
ተረዳ፡፡ የነፍሱንም መኮነን አልተጠራጠረም:: ሆኖም ነፍሱ 'የተስፋ ጭላንጭል ብርሃን ጨርሶ የተለየው አልነበረም:: ቢሆንም ከዚያ የተስፋ
ጭላንጭል ባሻገር ይመለከተው የነበረው የሰይጣን ጥላ ነበር፡፡
ይህም በመሆኑ ከማልቀስ አልተገታም:: ከልቅሶው በኋላ ምን ሆነ? ምን አደረገ? የት ሄደ? ማንም አላወቀም:: ነገር ግን በዚያን እለት ምሽት በዚያ በኩል ያለፈ ባላጋሪ ከእኚያ ደግና ቸር ጳጳስ ቤት በራፍ ከመንገዱ
ጠርዝ ፈቀቅ ብሎ ጥላ ስር ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ተንበርክኮ በስሜት ይጸልይ የነበረ ሰው ማየቱለን ተናግሯል፡፡...
💫ይቀጥላል💫
ተረዳ፡፡ የነፍሱንም መኮነን አልተጠራጠረም:: ሆኖም ነፍሱ 'የተስፋ ጭላንጭል ብርሃን ጨርሶ የተለየው አልነበረም:: ቢሆንም ከዚያ የተስፋ
ጭላንጭል ባሻገር ይመለከተው የነበረው የሰይጣን ጥላ ነበር፡፡
ይህም በመሆኑ ከማልቀስ አልተገታም:: ከልቅሶው በኋላ ምን ሆነ? ምን አደረገ? የት ሄደ? ማንም አላወቀም:: ነገር ግን በዚያን እለት ምሽት በዚያ በኩል ያለፈ ባላጋሪ ከእኚያ ደግና ቸር ጳጳስ ቤት በራፍ ከመንገዱ
ጠርዝ ፈቀቅ ብሎ ጥላ ስር ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ተንበርክኮ በስሜት ይጸልይ የነበረ ሰው ማየቱለን ተናግሯል፡፡...
💫ይቀጥላል💫
👍12👏2❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አንዳንዴ ኃላፊነትን ከመሸከም አሳልፎ መስጠት
በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፓሪስ አጠገብ ከሚገኘው ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንድ አነስተኛ ሆቴል ቤት ነበር፡፡ ዛሬ ግን የለም:: ሆቴል ቤቱ፡ ዘቴናድዬስ የተባሉ ባልና ሚስት ንብረት ሲሆን የሚገኘው በላንገር ከተባለ ቀጭን መንገድ ላይ ነበር፡፡ ከቤቱ በራፍ ላይ ስዕል
ተንጠልጥለአል:: ስዕለ ላይ ሜዳሊያ የተሰካላትና በደም ተበክሎ የተቦጫጨቀ የጄኔራል ልብስ የለበሰ ሰው ሸክም ተሸክሞ ነው የሚታየው::በተጨማሪም ከምስሉ ባዶ ሥፍራ ላይ ጭስ በብዛት አለ:: የሚያመለክተው
የጦር ሜዳን ሳይሆን አይቀርም:: ከምስሉ ስር «የዋተርሉ ጦር ሜዳ
ጀግና የሃምሳ አለቃ» የሚል ጽሑፍ ተጽፎበታል:: ከዚህ ሆቴል ቤት በራፍ ጋሪ ቆሞ ማየት አዲስ ነገር አልነበረም:: ሆኖም «ከዋተርሉ የጦር ሜዳ ጀግናው የሃምሳ አለቃ» ሆቴል ቤት በራፍ
የተሰባበረ ጋሪ መንገድ ዘግቶ ሲቆም ዘወትር የሚታይ ትርኢት አይደለም::ጊዜው የፀደይ ወራት ሲሆን ዓመተ ምህረቱ 1818 ዓ.ም ነው፡፡ የጋሪው መንገድ ዘግቶ መቆም ፤ ያን የመሰለ ስዕል ከዚያ ቤት በራፍ መሰቀል በዚያ
ያለፈ የማንኛውም ሰዓሊ ዓይን የሚማርክ ትርዒት ነበር::
ጋሪው ትላልቅ ግንዲላዎችን ጭኖአል፡፡ ታዲያ ይህ ጋሪ ከዚህ ስፍራ ምን ይሠራ ነበር የሚል ጥያቄ ቢነሳ «ከዚያ የተገተረውማ መንገድ ለመዝጋትና የትጉህ ሠራተኞችን ተግባር ለማደናቀፍ ነው» የሚል ትርጉም
ሊያሰጥ ይችላል፡፡
ከጋሪው የእቃ መጫኛ ሥር የተንጠለጠለው ወፍራም ሰንሰለት መሬት ሊነካ ምንም አልቀረው:: አንዲት ሁለት ዓመት ተመንፈቅ የሚሆናት ልጅ ሌላ ዓመት ከስድስት ወር የሚሆናትን ሕፃን ጭንዋ ላይ አሳርፋ
ከሰንሰለቱ ላይ ተቀምጣለች:: ልጆቹ ጅዋጅዌ ላይ እንደወጡ ደስ ብሎአቸዋል፡፡ አንዲት ሴት አቀማመጣቸውን አይታ «ልጆቼ መጫወቻ አገኘ» በማለት ደስ እንደሚላት ማንኛዋም እናት በማተኮር ታያቸዋለች::አተኩሮ ለተመለከታት አንጀት የምትበላ፧ አንዴ እንኳን ለማየት የምትቀፍና
ኑሮ እጅግ ያጎሳቆላት ሌላ ሴት ከበራፉ አጠገብ ተቀምጣለች፡፡ ልጆቹ ደስ ብሏቸው ሲጫወቱ «ምናልባት ፈረሱ ደምብሮ ይጐዳቸው ይሆን» እያለች
የመጀመሪያዋ ሴት አሁንም እንደማንኛውም እናት ማሰብዋ ኣልቀረም::ሰንሰለቱ በተነቃነቀ ቁጥር ሲጥጥ እያለ ይጮሃል:: ድምፁ ሕፃናቱን አልረሸሻቸወም:: የማታ ጨረር ከልጆቹ ላይ በማረፉ ልብ ብሉ ለተመለከታቸው ዓይንን ይማርካለ::
የልጆቹ እናት በድንገት ድምፅ ትሰማለች:: «እሜቴ ደስ የሚሉ
ልጆች ነው ያሉዎት!»
ከምግብ ቤቱ በራፍ የተቀመጠችው ሌላዋ ሴትም ልጅ ታቅፋ ነበር::ከባድ የሚመስል እቃ በጀርባዋ አዝላለች:: እርስዋም የታቀፈቻት ልጅ ሁለት ወይም ሦስት ዓመት ቢሆናት ነው:: በአለባበስ ከሁለቱ ልጆች
ምንም ያህል አትለይም:: ሻሽ መሳይ ጨርቅ አስራለች:: የተቦጫጨቀ ቀሚስዋ ቀዳዳው እስከጭንዋ ሊደርስ ምንም አልቀረ:: ሆኖም ጤነኛ ነበረች:: መልክዋ ድምቡሽቡሽ ያለ ስለሆነ ንከሰኝ፣ ንከሰኝ ትላለች፡፡ዓይኖችዋ ትላልቅ ስለነበሩ እንቅልፍ ቢወስዳትም ሙሉ ለመሉ
አልተከደነም:: ለስለስ ካለው የእናትዋ ክንድ ላይ ተመችቶአት ስለተኛች እንቅልፍ ሳይጠግብ ሲቀሰቅሱት እንደማይስማው እንደማንኛውም ሕፃን
እርስዋም ቢቀሰቅሱዋት እንኳ አትሰማም::እናትየዋ ሲያዩዋት የተከፋች ምስኪንና ከተማ ስራ ፍለጋ የመጣች የገጠር ሴት ለመሆንዋ ታስታውቃለች:: በእድሜ ልጅ ናት:: ተፈጥሮ
ውበት ቢቸራትም በዚያ ሁኔታዋ ውበትዋ ጎላ ብሎ አይታይም ፀጉርዋ ዞማ እንደሆነ ቢያስታውቅም ተንጨባሮአል:: የተቀዳደደ ሻሽዋ ተፈትቶ
ሊወድቅ ብሎ ከወደኋላዋ ተንጠልጥሎአል፡፡ የደላው ሲስቅ ነጭ ጥርሱን ያሳያል እንጂ የተከፋ ስለማይስቅ ስለጥርሶችዋ ለመናገር አይቻልም:: ለረጅም
ጊዜ ለማልቀስዋ ዓይኖችዋ ይመሰክራለ:: ገርጥታለች፤ ሰውነትዋ በመዛሉ የደከማት ለመሆነ ያስታውቃል፡፡ ምናልባትም ሳትታመም አልቀረችም::ጭንዋ ላይ የተኛችዋን ልጅ አትኩራ በፍቅር ዓይን ትመለከታታለች፡፡ ልጅዋን ደግፋ የያዘችበት እጅ ሲታይ በሥራ ብዛት ለመሻከሩ ጉልህ ነው::
ጠቅላላ ሀናቴዋ ሲታይ ሩህሩህ ልብ ያላቸው ሁሉ የማያልፍዋት
ዓይነት ስለነበረች አንጀት ትበላለች:: በይበልጥ የሚያሳዝነው ግን ማን
ትሁን፤ ከየት ትምጣ ማንም አለማወቁ ነው:: እርስዋም ራስዋ ብትሆን አባትዋና እናትዋ እነማን እንደሆኑ ማለት ማን እንደወለዳት አታውቅም፡፡ስምዋ ፋንቲን ይባላል፡፡ ቤተሰብ ስላልነበራት የአባት ስም የላትም:: የክርስትና
ስምም አልወጣላትም፡፡ ምክንያቱም በዚያ አካባቢ ቤተክርስቲያን ምን እንደሆነ
አይታወቅም:: ፋንቲን ብሎ ስም ያወጣላት በዚያ ሲያልፍ ያገኛት መንገደኛ ነው ይባላል፡፡ ይህ ሰው ይህችን ሕፃን መንገድ ወድቃ ዝናብ ሲዘንብባት ነው ፋንቲን የሚል ስም ያወጣላት:: «ፋንቲን» ማለት ውሃ ወይም ምንጭ
እንደማለት ነው::
ስለዚህች ሴተ ታሪክ ከዚህ ይበልጥ የሚያውቅ ስለሌላ ስላለፈው ታሪክዋ ከዚህ ይበልጥ መናገር አይቻልም:: ሆኖም ፋንቲን ወደዚህች ዓለም ለስቃይ የመጣች በዚህ ዓይነት ነበር ብሎ ለማጠቃለል ይቻላል፡፡ ወደኋላ
እንደተደረሰበት ደግሞ አሥር ዓመት ገደማ ሲሆናት ከከተማ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ መንደር ሥራ ፍለጋ ትሄዳለች:: አሥራ አምስት ዓመትዋ አሁንም ሥራ ፍለጋ ወደ ፓሪስ ከተማ ትመጣለች::
በመጨረሻ ጥርሶችዋ ታዩ ፧ እንደወተት የነጡ ነበሩ፡፡ ሌላ ቢጠፋ የእንጨት መፋቂያ አላጣችም ማለት ነው:: ስታገባ የተሰጣት ሳይሆን አይቀርም የሚያማምሩ ጌጣጌጦች አንገትዋ ላይ አስራለች:: ወይም ደግሞ ሥራ ብጤ አግኝታ ትንሽ ከሠራች በኋላ ፤ የገዛቻቸው ይሆናሉ፡፡ ሴት ናትና ማጌጥ አይቀርም:: እርስዋም እንደ ዓቅምዋ ለመኖር ፈልጋ ሥራ
ይዛ ነበር ማለት ነው:: ለመኖር ሆድ እንጀራ እንደሚርበው ሁሉ ልብም ፍቅር ይርበዋልና ልጅዋን እንደዚያ የምታያት የፍቅር ረሃብዋን ለማርካት ነበር፡፡
ያ ስሜት ለሕፃንዋ የእናት ፍቅር ሲሆን ለእናትዮዋ ግን የስሜት
መገንፈል ነበር፡፡ እናትና ልጅ ከተቀመጡበት አቅራቢያ የሚተላለፉ መንገደኞችና ተማሪዎች ቁጥር እጅግ ብዙ ነበር፡፡ ሕፃን ሆና ሕፃን
የታቀፈችዋን ሴት ሁሉም አይቶ አለፋት እንጂ ከመጤፍ የቆጠራት
አልነበረም::
የሕፃንዋ አባት ልጅቱ፡ እንደተወለደች ሚስቱንና ልጁን ጥሎ ከአገር ይጠፋል፡፡ አባት አንዴ ቤተሰቡን ጥሎ። ከሄደ መመለሱ ያጠራጥራል፡፡
ይህም በመሆኑ ልጅትዋ በብቸኝነት ዓለም ውስጥ እየዋዠቀች ስለነበር ተስፋ ከሚፈጥረው ደስታ ርቃለች:: በአንድ ወቅት ተሳሳተች እንጂ
በአፈጣጠርዋ ገራምና ትምክህት የተለያት ለመሆኑ ገፅታዋ ይመሰክራል በፊትዋ ገጽታ ላይ የሚነበብ ገራምነትዋ ብቻ አልነበረም፡፡ ተስፋ
መቁረጥዋን! ቀባሪና ጧሪ የሌላት መሆኑንና ከባድ ችግር ውስጥ
መዘፈቅዋንም ያሳያል፡፡ ሆኖም ፋንቲን ቆራጥና ጠንካራ ሴት ነበረች:: ወደ ትውልድ አገርዋ የመመለስ አሳብ ነበራት፡፡ ምናልባት እዚያ ከሄደን
ድንገት የሚያውቃት ሰው ይኖርና ሥራ ይሰጠኝ ይሆናል የሚል እምነት አድሮባታል፡፡ ነገር ግን የፈጸመችውን ስህተት መደበቅ ስለነበረባት ልብዋ በሀዘን ቢቆስልም ሀሳብዋን ለመፈጸም ቆረጠች፡፡ በሃያ ሁለት ዓመት
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አንዳንዴ ኃላፊነትን ከመሸከም አሳልፎ መስጠት
በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፓሪስ አጠገብ ከሚገኘው ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንድ አነስተኛ ሆቴል ቤት ነበር፡፡ ዛሬ ግን የለም:: ሆቴል ቤቱ፡ ዘቴናድዬስ የተባሉ ባልና ሚስት ንብረት ሲሆን የሚገኘው በላንገር ከተባለ ቀጭን መንገድ ላይ ነበር፡፡ ከቤቱ በራፍ ላይ ስዕል
ተንጠልጥለአል:: ስዕለ ላይ ሜዳሊያ የተሰካላትና በደም ተበክሎ የተቦጫጨቀ የጄኔራል ልብስ የለበሰ ሰው ሸክም ተሸክሞ ነው የሚታየው::በተጨማሪም ከምስሉ ባዶ ሥፍራ ላይ ጭስ በብዛት አለ:: የሚያመለክተው
የጦር ሜዳን ሳይሆን አይቀርም:: ከምስሉ ስር «የዋተርሉ ጦር ሜዳ
ጀግና የሃምሳ አለቃ» የሚል ጽሑፍ ተጽፎበታል:: ከዚህ ሆቴል ቤት በራፍ ጋሪ ቆሞ ማየት አዲስ ነገር አልነበረም:: ሆኖም «ከዋተርሉ የጦር ሜዳ ጀግናው የሃምሳ አለቃ» ሆቴል ቤት በራፍ
የተሰባበረ ጋሪ መንገድ ዘግቶ ሲቆም ዘወትር የሚታይ ትርኢት አይደለም::ጊዜው የፀደይ ወራት ሲሆን ዓመተ ምህረቱ 1818 ዓ.ም ነው፡፡ የጋሪው መንገድ ዘግቶ መቆም ፤ ያን የመሰለ ስዕል ከዚያ ቤት በራፍ መሰቀል በዚያ
ያለፈ የማንኛውም ሰዓሊ ዓይን የሚማርክ ትርዒት ነበር::
ጋሪው ትላልቅ ግንዲላዎችን ጭኖአል፡፡ ታዲያ ይህ ጋሪ ከዚህ ስፍራ ምን ይሠራ ነበር የሚል ጥያቄ ቢነሳ «ከዚያ የተገተረውማ መንገድ ለመዝጋትና የትጉህ ሠራተኞችን ተግባር ለማደናቀፍ ነው» የሚል ትርጉም
ሊያሰጥ ይችላል፡፡
ከጋሪው የእቃ መጫኛ ሥር የተንጠለጠለው ወፍራም ሰንሰለት መሬት ሊነካ ምንም አልቀረው:: አንዲት ሁለት ዓመት ተመንፈቅ የሚሆናት ልጅ ሌላ ዓመት ከስድስት ወር የሚሆናትን ሕፃን ጭንዋ ላይ አሳርፋ
ከሰንሰለቱ ላይ ተቀምጣለች:: ልጆቹ ጅዋጅዌ ላይ እንደወጡ ደስ ብሎአቸዋል፡፡ አንዲት ሴት አቀማመጣቸውን አይታ «ልጆቼ መጫወቻ አገኘ» በማለት ደስ እንደሚላት ማንኛዋም እናት በማተኮር ታያቸዋለች::አተኩሮ ለተመለከታት አንጀት የምትበላ፧ አንዴ እንኳን ለማየት የምትቀፍና
ኑሮ እጅግ ያጎሳቆላት ሌላ ሴት ከበራፉ አጠገብ ተቀምጣለች፡፡ ልጆቹ ደስ ብሏቸው ሲጫወቱ «ምናልባት ፈረሱ ደምብሮ ይጐዳቸው ይሆን» እያለች
የመጀመሪያዋ ሴት አሁንም እንደማንኛውም እናት ማሰብዋ ኣልቀረም::ሰንሰለቱ በተነቃነቀ ቁጥር ሲጥጥ እያለ ይጮሃል:: ድምፁ ሕፃናቱን አልረሸሻቸወም:: የማታ ጨረር ከልጆቹ ላይ በማረፉ ልብ ብሉ ለተመለከታቸው ዓይንን ይማርካለ::
የልጆቹ እናት በድንገት ድምፅ ትሰማለች:: «እሜቴ ደስ የሚሉ
ልጆች ነው ያሉዎት!»
ከምግብ ቤቱ በራፍ የተቀመጠችው ሌላዋ ሴትም ልጅ ታቅፋ ነበር::ከባድ የሚመስል እቃ በጀርባዋ አዝላለች:: እርስዋም የታቀፈቻት ልጅ ሁለት ወይም ሦስት ዓመት ቢሆናት ነው:: በአለባበስ ከሁለቱ ልጆች
ምንም ያህል አትለይም:: ሻሽ መሳይ ጨርቅ አስራለች:: የተቦጫጨቀ ቀሚስዋ ቀዳዳው እስከጭንዋ ሊደርስ ምንም አልቀረ:: ሆኖም ጤነኛ ነበረች:: መልክዋ ድምቡሽቡሽ ያለ ስለሆነ ንከሰኝ፣ ንከሰኝ ትላለች፡፡ዓይኖችዋ ትላልቅ ስለነበሩ እንቅልፍ ቢወስዳትም ሙሉ ለመሉ
አልተከደነም:: ለስለስ ካለው የእናትዋ ክንድ ላይ ተመችቶአት ስለተኛች እንቅልፍ ሳይጠግብ ሲቀሰቅሱት እንደማይስማው እንደማንኛውም ሕፃን
እርስዋም ቢቀሰቅሱዋት እንኳ አትሰማም::እናትየዋ ሲያዩዋት የተከፋች ምስኪንና ከተማ ስራ ፍለጋ የመጣች የገጠር ሴት ለመሆንዋ ታስታውቃለች:: በእድሜ ልጅ ናት:: ተፈጥሮ
ውበት ቢቸራትም በዚያ ሁኔታዋ ውበትዋ ጎላ ብሎ አይታይም ፀጉርዋ ዞማ እንደሆነ ቢያስታውቅም ተንጨባሮአል:: የተቀዳደደ ሻሽዋ ተፈትቶ
ሊወድቅ ብሎ ከወደኋላዋ ተንጠልጥሎአል፡፡ የደላው ሲስቅ ነጭ ጥርሱን ያሳያል እንጂ የተከፋ ስለማይስቅ ስለጥርሶችዋ ለመናገር አይቻልም:: ለረጅም
ጊዜ ለማልቀስዋ ዓይኖችዋ ይመሰክራለ:: ገርጥታለች፤ ሰውነትዋ በመዛሉ የደከማት ለመሆነ ያስታውቃል፡፡ ምናልባትም ሳትታመም አልቀረችም::ጭንዋ ላይ የተኛችዋን ልጅ አትኩራ በፍቅር ዓይን ትመለከታታለች፡፡ ልጅዋን ደግፋ የያዘችበት እጅ ሲታይ በሥራ ብዛት ለመሻከሩ ጉልህ ነው::
ጠቅላላ ሀናቴዋ ሲታይ ሩህሩህ ልብ ያላቸው ሁሉ የማያልፍዋት
ዓይነት ስለነበረች አንጀት ትበላለች:: በይበልጥ የሚያሳዝነው ግን ማን
ትሁን፤ ከየት ትምጣ ማንም አለማወቁ ነው:: እርስዋም ራስዋ ብትሆን አባትዋና እናትዋ እነማን እንደሆኑ ማለት ማን እንደወለዳት አታውቅም፡፡ስምዋ ፋንቲን ይባላል፡፡ ቤተሰብ ስላልነበራት የአባት ስም የላትም:: የክርስትና
ስምም አልወጣላትም፡፡ ምክንያቱም በዚያ አካባቢ ቤተክርስቲያን ምን እንደሆነ
አይታወቅም:: ፋንቲን ብሎ ስም ያወጣላት በዚያ ሲያልፍ ያገኛት መንገደኛ ነው ይባላል፡፡ ይህ ሰው ይህችን ሕፃን መንገድ ወድቃ ዝናብ ሲዘንብባት ነው ፋንቲን የሚል ስም ያወጣላት:: «ፋንቲን» ማለት ውሃ ወይም ምንጭ
እንደማለት ነው::
ስለዚህች ሴተ ታሪክ ከዚህ ይበልጥ የሚያውቅ ስለሌላ ስላለፈው ታሪክዋ ከዚህ ይበልጥ መናገር አይቻልም:: ሆኖም ፋንቲን ወደዚህች ዓለም ለስቃይ የመጣች በዚህ ዓይነት ነበር ብሎ ለማጠቃለል ይቻላል፡፡ ወደኋላ
እንደተደረሰበት ደግሞ አሥር ዓመት ገደማ ሲሆናት ከከተማ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ መንደር ሥራ ፍለጋ ትሄዳለች:: አሥራ አምስት ዓመትዋ አሁንም ሥራ ፍለጋ ወደ ፓሪስ ከተማ ትመጣለች::
በመጨረሻ ጥርሶችዋ ታዩ ፧ እንደወተት የነጡ ነበሩ፡፡ ሌላ ቢጠፋ የእንጨት መፋቂያ አላጣችም ማለት ነው:: ስታገባ የተሰጣት ሳይሆን አይቀርም የሚያማምሩ ጌጣጌጦች አንገትዋ ላይ አስራለች:: ወይም ደግሞ ሥራ ብጤ አግኝታ ትንሽ ከሠራች በኋላ ፤ የገዛቻቸው ይሆናሉ፡፡ ሴት ናትና ማጌጥ አይቀርም:: እርስዋም እንደ ዓቅምዋ ለመኖር ፈልጋ ሥራ
ይዛ ነበር ማለት ነው:: ለመኖር ሆድ እንጀራ እንደሚርበው ሁሉ ልብም ፍቅር ይርበዋልና ልጅዋን እንደዚያ የምታያት የፍቅር ረሃብዋን ለማርካት ነበር፡፡
ያ ስሜት ለሕፃንዋ የእናት ፍቅር ሲሆን ለእናትዮዋ ግን የስሜት
መገንፈል ነበር፡፡ እናትና ልጅ ከተቀመጡበት አቅራቢያ የሚተላለፉ መንገደኞችና ተማሪዎች ቁጥር እጅግ ብዙ ነበር፡፡ ሕፃን ሆና ሕፃን
የታቀፈችዋን ሴት ሁሉም አይቶ አለፋት እንጂ ከመጤፍ የቆጠራት
አልነበረም::
የሕፃንዋ አባት ልጅቱ፡ እንደተወለደች ሚስቱንና ልጁን ጥሎ ከአገር ይጠፋል፡፡ አባት አንዴ ቤተሰቡን ጥሎ። ከሄደ መመለሱ ያጠራጥራል፡፡
ይህም በመሆኑ ልጅትዋ በብቸኝነት ዓለም ውስጥ እየዋዠቀች ስለነበር ተስፋ ከሚፈጥረው ደስታ ርቃለች:: በአንድ ወቅት ተሳሳተች እንጂ
በአፈጣጠርዋ ገራምና ትምክህት የተለያት ለመሆኑ ገፅታዋ ይመሰክራል በፊትዋ ገጽታ ላይ የሚነበብ ገራምነትዋ ብቻ አልነበረም፡፡ ተስፋ
መቁረጥዋን! ቀባሪና ጧሪ የሌላት መሆኑንና ከባድ ችግር ውስጥ
መዘፈቅዋንም ያሳያል፡፡ ሆኖም ፋንቲን ቆራጥና ጠንካራ ሴት ነበረች:: ወደ ትውልድ አገርዋ የመመለስ አሳብ ነበራት፡፡ ምናልባት እዚያ ከሄደን
ድንገት የሚያውቃት ሰው ይኖርና ሥራ ይሰጠኝ ይሆናል የሚል እምነት አድሮባታል፡፡ ነገር ግን የፈጸመችውን ስህተት መደበቅ ስለነበረባት ልብዋ በሀዘን ቢቆስልም ሀሳብዋን ለመፈጸም ቆረጠች፡፡ በሃያ ሁለት ዓመት
👍21❤1
ሕፃን ልጅ አዝላ ከፓሪስ ከተማ ወጣች፡፡ የእናትና ልጅን ሁናቴ ከዛ
ተቀምጠው ለተመለከተ እጅግ ያሳዝናሉ፡፡ እናት በዚህች ዓለም ውስጥ ከልጅዋ በስተቀር ሌላ ሀብት አልነበራትም፡፡ ሕፃንዋም ከእናትዋ ሌላ ምንም ነገር የላትም:: ፋንቲን በደከመ አቅምዋ ለልጅዋ በማዘን መንገድ ሲሄዱ
ታዝላታለች ፤ ሲቀመጡ ትታቀፋታለች፡፡ በሽታዋ ሲጠናባት ኣልፎ አልፎ ያስላታል::
ተስያት ላይ የፀሐይ ግለትን ለማሳለፍ ጥቂት ካረፉ በኋላ ጉዞቸውን ይቀጥላሉ:: ፀሐይ ቆልቆል ስትል አሁን ከነበሩት በመድረሳቸውና በጣም
ስለደክማቸው ነበር ከዚያ ያረፉት::
እነዚያ ሁለት ልጆች ከጋሪው ወፍራም ሰንሰለት ላይ ቁጭ ብለው ደስ ብሎአቸው ሲጫወቱ በማየትዋ ፋንቲን አሳብ ባህር ወስጥ ትዘፈቃላች
ልጆቹ ፊት ላይ ደስታ ይነበባል:: ይህም ያ የተባረከና የተቀደሰ
ሥፍራ እንደሆነ አሳመናት:: ሆቴል ቤቱም በረከት ያልተለየውና መንፈስ ቅዱስ የቀረበው ለመሆኑ ከልጆቹ ሁኔታ ገመተች:: ሁለቱ ልጆች በእርግጥ ተደሳቾች ነበሩ:: ልጆቹ ላይ አፈጠጠች ፧ አደነቀቻቸው:: ስለዚህ ነው ቀይ
ብለን እንደገለጽነው «ደስ የሚሉ ልጆች ነው ያለዎት እሜቴ» በማለት ለመናገር የደፈረችው::
የሁለቱ ልጆች እናት ቀና ብላ ካየቻት በኋላ ስለሰጠችው አስተያ
ታመሰግናታለች:: ልጅ የታቀፈችው ልጅ ከሴትዮዋ ምግብ ቤት
ስለነበር የተቀመጠችው ሁለቱ ሴቶች ጨዋታ ይጀምራሉ፡፡
«መዳም ተናድዬ እባላለሁ» አለች የሁለቱ ሴቶች ልጆች እናት፡፡
ሆቴል ቤቱ የባለቤቴና የእኔ ነው፡፡»
መዳም ቴናድዬ ሸበት ጣል ጣል ያደረገባትና እንደ ወታደር ሚስት
እንገትዋን የደፋች ስትሆን ጠባየ ብልሹ ሴት ትመስላለች፡፡ ወንዳወንድ ብጤ ሆና ሰውነትዋ ደልዳላ ነው:: ለረጅም ጊዜ ሆቴል ቤት ውስጥ ከገባና ከወጣ ሰው ጋር መጫጫሁና ከወዲያ ወዲህ መሯሯጥ ይህን የመሰለ
ባህርይ ሊያሰጥ ይችላል፡፡ ሽበት ቢወራትም በእድሜ እስከዚህም የገፋች አልነበረችም፡፡ ከሰላሣ ዓመት ብዙም አታልፍም:: ሕፃን ልጅ ታቅፋ ኩምሽሽ
ብላ ከተቀመጠችው እናት አጠገብ የቆመችውና እንደ ነጋዴ የፈረጠመና ደልዳላ ሰውነት ያላት ቴናድዬ ቀና ብለው ሲያዩዋት ትከብዳለች፡፡ ቁጭ
ያለችዋ ሴት «እኔና እርስዎ አሁን እኩል ቆመን እንሄዳለን› ብላ ሳታስብ አልቀረችም::
አንዱ ቁጭ ብሎ ሌላው ከአጠገብ ቆሞ ቁልቁል እያየ ሲያፈጥ ትንሽ ማስፈራቱ አይቀርም! ያውም ግዙፍና ጠንካራ ብጤ ስው ሲሆን፡፡ ለማንኛውም መንገደኛዋ ሴት ታሪኳ ውስጥ ትንሽ ቅመም እየጨመረች አወራቻት፡፡
በታሪክዋም ሥራ እንደነበራትና ባልዋ እንደሞተባት ተናገረች:: ፓሪስ ከተማ ውስጥ ስራ ልታገኝ ስላልቻለች ትውልድ አገርዋ ውስጥ እድልዋን ለመሞከር እየሄደች መሆንዋን ገለጸች:: ከፓሪስ ከተማ ልጅዋን አዝላ
የተነሳችው ገና ጎሕ ሲቀድ በእግር ጉዞ መሆኑንና አሁን በጣም ስለደከማት ለማረፍ ከበረንዳው ጥላ ሥር ቁጭ ማለትዋን፧ መንገድ ላይ ድካሙ ሲጠናባት ልጅዋ በእግርዋ ጥቂት መጓዝዋን ግን እጅግ በጣም ለአጭር
ርቀት መሆነን ካአስረዳች በኋላ ይህም በመሆኑ ሕፃንዋ በጣም ስለደከማት እንቅልፍ እንደወሰዳት ተናገረች::
እናት ይህን እንደተናገረች የልጅዋን ጉንጭ ምጥጥ አድርጋ ትስማለች፡፡በዚህ ጊዜ ሕፃንዋ ስለተቀሰቀሰች እነዚያ የሚያምሩ ዓይኖችዋን ገለጠች::
ዓይንዋን ስትገልጥ ምን ኣየች? ምንም:: የሁለት ዓመት ሕፃን ምንስ ታያለች? ግን እኮ አንዳንዴ ኮስተር፣ አንዳንዴም ቆጣ በማለት ሕፃናት የማያዩት ነገር የለም:: ያ ምስጢሩ ያልታወቀ ዓይን አይደለም ገሪምነታቸውን
የሚያሳየው! ምናልባት እኮ እነሱ መልአክ፡ እኛ ግን ሰዎች እንደሆንን ይታያቸው ይሆናል፡፡
እናትዮዋ ብትቆጣ" ህፃንዋ መሳቅዋን ቀጠለች:: ከእናትዮዋ ክንድ አምልጣ መሬት ወረደች:: ወዲያው ከጋሪው ስር ይጫወቱ ወደነበሩት ሁለት ልጆች ሮጠች:: ምን እንዳለች ሳይታወቅ ብቻ በመንተባተብ አንድ ነገር ተናገረች::
መዳም ቴናድዬ «አብራችሁ ተጫወቱ» አለች፡፡
በዚያ ዕድሜ መተዋወቅና መግባባት በጣም ቀላል ነው፡፡ የማዳም ቴናድዬ ልጆች አፈር እየፈጩና ጉድጓድ እየቆፈሩ በመሙላት ከአዲስ መጤዋ ሕፃን ጋር ደስ ብሎአቸው ይጫወቱ ጀመር፡፡
አዲሷ ሕፃንም ተጨዋችና ተገባቢ ልጅ ነበረች የእናትዋ ደግነት በሕፃንዋ ላይ ተንፀባርቋል፡፡ ስንጥር አንስታ ለዝንብ መቅበሪያ የሚሆን ጉድጓድ መቆፈር ጀመረች፡፡ የመቃብር ቆፋሪን ሥራ ሕፃናት ሲሠሩት ደስ ይላል፡፡
ሁለቱ ሴቶች ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡
«ልጅሽን ማን ብለሽ ነው የምትጠሪያት?»
«ኮሴት::»
«ስንት ዓመት ሆናት?»
«ወደ ሦስት እየተጠጋች ነው::»
«ከትልቅዋ ልጄ ጋር እኩል ናት ማለት ነዋ!»
ሦስቱ ልጆች ደስ ብሉአቸው አብረው ሲጫወቱ አንድ አስደናቂ ነገር ይሆናል፡፡ ትልቅ ትል ከሚቆፍሩት ጉድጓድ ውስጥ ወጣ፡፡ ልጆቹ በጣም
ደነገጡ፡፡ በፍርሃት ቀና ሲሉ የሦስቱም ግምባር ተጋጨ፡፡
ጭንቅላታቸውን ሳያላቅቁ ዝም ብለው ትሉን በመገረም ተመለከቱ::
«እናንተ ልጆች ምን ሆናችሁ?» ብላ መዳም ቴናድዬ ጠየቀች
«ልጆች እኮ ሲተዋወቁ ጊዜ አይወስድባቸውም፧ እያቸው እስቲ! ሦስቱም ከአንድ እናት አንጀት የወጡ አይመስሉም» በማለት መዳም ቴናድዬ ቀጥታ
ተናገረች::
የሴትዮዋ አነጋገር በተጠንቀቅ ላይ የነበረው የሌላይቱ እናት አሳብ መዘርገፍ ምክንያት ሆነ፡፡ ፋንቲን የመዳም ቴናድዬን እጅ ያዘች::
«ልጄን ያሳድጉልኛል?»
«ምን አልሽ!»
«ልጄን ያሳድጉልኛል?»
«ትንሽ ነገሩን ማብላላት አያስፈልግ ብለሽ!»
«በወር ስድስት ፍራንክ እከፍልዎታለሁ::»
ከቤት ውስጥ ጉርነን ያለ የወንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
«ከሰባተ ፍራንክ በታች አይሆንም፤ ደግሞም የስድስት ወር ክፍያ በቅድማያ ነው የሚከፈለው:: ስድስት ጊዜ ሰባት አርባ ሁለት ፍራንክ መሆኑ ነው::
‹‹እከፍላለሀ•» አለች የኮዚት እናት::
«አንዳንድ ነገሮችን ለማሟላት አንድ አሥራ አምስት ፍራንክ
በተጨማሪ ያስፈልጋል» አለ ቀጠለና ሰውዬው::
«እንግዲህ በድምሩ አምሳ ሰባት ፍራንክ መሆን ነው» አለች መዳም
ቴናድዬ::
እከፍላለሁ›› አለች ድሃዋ እናት:: «አሁን በእጁ ያለው ሰማንያ
ፍራንክ ነው:: ቀሪው ገንዘብ እንደምንም ብሎ አገሬ ያስገባኛል፡፡ ከዚያ ደግሞ ሥራ አላጣም:: ወዲያው ትንሽ ገንዘብ እንዳፈራሁ ተመልሼ መጥቼ
ልጄን እወስዳታለሁ::»
የሰውዬው ድምፅ እንደገና ተሰማ፡፡
«ለመሆነ የሌሊት ልብስ አላት?»
ባለቤቴ ነው» አለች ማዳም ቴናድዬ::
«በሚገባ፤ ደግሞ ለእርስዋ ያልሆንኩ፡፡ ባለቤትዎ እንደሆኑ እኔም ጠርጥሬአለሁ:: እኔው ፈትዬ ያሠራሁላት ወፍራም ልብስ አላት:: የሌሊት ብቻ ሳይሆን ቀን ቀን የምትለብሰውም ከለበሰችው ሌላ ሁለት ቀሚስ አላት::
«እንግዲያው ልብሶችዋን ትተሽ ነው የምትሄጂው» አሉ ሰውዬው::
«ይዤውማ አልሄድም» አለች እናት:: «ልጄን ራቁትዋን ጥያት
ብሄድ ሰው ጉድ አይልም::»
ሰውዬው ከነበረበት ወደ ውጭ ብቅ አለ፡፡
«ይሄ ጥሩ ነው» ሲል ተናገረ ዝቅ ባለ ድምፅ::
በዚህ ተስማሙ:: የኮዜት እናት ያን እለት እዚያው አደረች:: ገንዘቡን
ከፈለች:: የልጅትዋንም ልብስ ሰጠች፡፡ በማግስቱ የቀራትን ጨርቅ ቋጥራና በቶሎ እንደምትመለስ ቃል ገብታ የእግር ጉዞዋን ቀጠለች፡፡ ምንም እንኳን
በጥሞና የተፈጸመ ስምምነት ቢሆንም የወለደቻትን ልጅ ጥላ ለምትሄድ እናት ቀላል ውሳኔ አልነበረም:: አንጀትን ከሁለት የሚከፍል ዓይነት ውሳኔ
ነው::
ተቀምጠው ለተመለከተ እጅግ ያሳዝናሉ፡፡ እናት በዚህች ዓለም ውስጥ ከልጅዋ በስተቀር ሌላ ሀብት አልነበራትም፡፡ ሕፃንዋም ከእናትዋ ሌላ ምንም ነገር የላትም:: ፋንቲን በደከመ አቅምዋ ለልጅዋ በማዘን መንገድ ሲሄዱ
ታዝላታለች ፤ ሲቀመጡ ትታቀፋታለች፡፡ በሽታዋ ሲጠናባት ኣልፎ አልፎ ያስላታል::
ተስያት ላይ የፀሐይ ግለትን ለማሳለፍ ጥቂት ካረፉ በኋላ ጉዞቸውን ይቀጥላሉ:: ፀሐይ ቆልቆል ስትል አሁን ከነበሩት በመድረሳቸውና በጣም
ስለደክማቸው ነበር ከዚያ ያረፉት::
እነዚያ ሁለት ልጆች ከጋሪው ወፍራም ሰንሰለት ላይ ቁጭ ብለው ደስ ብሎአቸው ሲጫወቱ በማየትዋ ፋንቲን አሳብ ባህር ወስጥ ትዘፈቃላች
ልጆቹ ፊት ላይ ደስታ ይነበባል:: ይህም ያ የተባረከና የተቀደሰ
ሥፍራ እንደሆነ አሳመናት:: ሆቴል ቤቱም በረከት ያልተለየውና መንፈስ ቅዱስ የቀረበው ለመሆኑ ከልጆቹ ሁኔታ ገመተች:: ሁለቱ ልጆች በእርግጥ ተደሳቾች ነበሩ:: ልጆቹ ላይ አፈጠጠች ፧ አደነቀቻቸው:: ስለዚህ ነው ቀይ
ብለን እንደገለጽነው «ደስ የሚሉ ልጆች ነው ያለዎት እሜቴ» በማለት ለመናገር የደፈረችው::
የሁለቱ ልጆች እናት ቀና ብላ ካየቻት በኋላ ስለሰጠችው አስተያ
ታመሰግናታለች:: ልጅ የታቀፈችው ልጅ ከሴትዮዋ ምግብ ቤት
ስለነበር የተቀመጠችው ሁለቱ ሴቶች ጨዋታ ይጀምራሉ፡፡
«መዳም ተናድዬ እባላለሁ» አለች የሁለቱ ሴቶች ልጆች እናት፡፡
ሆቴል ቤቱ የባለቤቴና የእኔ ነው፡፡»
መዳም ቴናድዬ ሸበት ጣል ጣል ያደረገባትና እንደ ወታደር ሚስት
እንገትዋን የደፋች ስትሆን ጠባየ ብልሹ ሴት ትመስላለች፡፡ ወንዳወንድ ብጤ ሆና ሰውነትዋ ደልዳላ ነው:: ለረጅም ጊዜ ሆቴል ቤት ውስጥ ከገባና ከወጣ ሰው ጋር መጫጫሁና ከወዲያ ወዲህ መሯሯጥ ይህን የመሰለ
ባህርይ ሊያሰጥ ይችላል፡፡ ሽበት ቢወራትም በእድሜ እስከዚህም የገፋች አልነበረችም፡፡ ከሰላሣ ዓመት ብዙም አታልፍም:: ሕፃን ልጅ ታቅፋ ኩምሽሽ
ብላ ከተቀመጠችው እናት አጠገብ የቆመችውና እንደ ነጋዴ የፈረጠመና ደልዳላ ሰውነት ያላት ቴናድዬ ቀና ብለው ሲያዩዋት ትከብዳለች፡፡ ቁጭ
ያለችዋ ሴት «እኔና እርስዎ አሁን እኩል ቆመን እንሄዳለን› ብላ ሳታስብ አልቀረችም::
አንዱ ቁጭ ብሎ ሌላው ከአጠገብ ቆሞ ቁልቁል እያየ ሲያፈጥ ትንሽ ማስፈራቱ አይቀርም! ያውም ግዙፍና ጠንካራ ብጤ ስው ሲሆን፡፡ ለማንኛውም መንገደኛዋ ሴት ታሪኳ ውስጥ ትንሽ ቅመም እየጨመረች አወራቻት፡፡
በታሪክዋም ሥራ እንደነበራትና ባልዋ እንደሞተባት ተናገረች:: ፓሪስ ከተማ ውስጥ ስራ ልታገኝ ስላልቻለች ትውልድ አገርዋ ውስጥ እድልዋን ለመሞከር እየሄደች መሆንዋን ገለጸች:: ከፓሪስ ከተማ ልጅዋን አዝላ
የተነሳችው ገና ጎሕ ሲቀድ በእግር ጉዞ መሆኑንና አሁን በጣም ስለደከማት ለማረፍ ከበረንዳው ጥላ ሥር ቁጭ ማለትዋን፧ መንገድ ላይ ድካሙ ሲጠናባት ልጅዋ በእግርዋ ጥቂት መጓዝዋን ግን እጅግ በጣም ለአጭር
ርቀት መሆነን ካአስረዳች በኋላ ይህም በመሆኑ ሕፃንዋ በጣም ስለደከማት እንቅልፍ እንደወሰዳት ተናገረች::
እናት ይህን እንደተናገረች የልጅዋን ጉንጭ ምጥጥ አድርጋ ትስማለች፡፡በዚህ ጊዜ ሕፃንዋ ስለተቀሰቀሰች እነዚያ የሚያምሩ ዓይኖችዋን ገለጠች::
ዓይንዋን ስትገልጥ ምን ኣየች? ምንም:: የሁለት ዓመት ሕፃን ምንስ ታያለች? ግን እኮ አንዳንዴ ኮስተር፣ አንዳንዴም ቆጣ በማለት ሕፃናት የማያዩት ነገር የለም:: ያ ምስጢሩ ያልታወቀ ዓይን አይደለም ገሪምነታቸውን
የሚያሳየው! ምናልባት እኮ እነሱ መልአክ፡ እኛ ግን ሰዎች እንደሆንን ይታያቸው ይሆናል፡፡
እናትዮዋ ብትቆጣ" ህፃንዋ መሳቅዋን ቀጠለች:: ከእናትዮዋ ክንድ አምልጣ መሬት ወረደች:: ወዲያው ከጋሪው ስር ይጫወቱ ወደነበሩት ሁለት ልጆች ሮጠች:: ምን እንዳለች ሳይታወቅ ብቻ በመንተባተብ አንድ ነገር ተናገረች::
መዳም ቴናድዬ «አብራችሁ ተጫወቱ» አለች፡፡
በዚያ ዕድሜ መተዋወቅና መግባባት በጣም ቀላል ነው፡፡ የማዳም ቴናድዬ ልጆች አፈር እየፈጩና ጉድጓድ እየቆፈሩ በመሙላት ከአዲስ መጤዋ ሕፃን ጋር ደስ ብሎአቸው ይጫወቱ ጀመር፡፡
አዲሷ ሕፃንም ተጨዋችና ተገባቢ ልጅ ነበረች የእናትዋ ደግነት በሕፃንዋ ላይ ተንፀባርቋል፡፡ ስንጥር አንስታ ለዝንብ መቅበሪያ የሚሆን ጉድጓድ መቆፈር ጀመረች፡፡ የመቃብር ቆፋሪን ሥራ ሕፃናት ሲሠሩት ደስ ይላል፡፡
ሁለቱ ሴቶች ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡
«ልጅሽን ማን ብለሽ ነው የምትጠሪያት?»
«ኮሴት::»
«ስንት ዓመት ሆናት?»
«ወደ ሦስት እየተጠጋች ነው::»
«ከትልቅዋ ልጄ ጋር እኩል ናት ማለት ነዋ!»
ሦስቱ ልጆች ደስ ብሉአቸው አብረው ሲጫወቱ አንድ አስደናቂ ነገር ይሆናል፡፡ ትልቅ ትል ከሚቆፍሩት ጉድጓድ ውስጥ ወጣ፡፡ ልጆቹ በጣም
ደነገጡ፡፡ በፍርሃት ቀና ሲሉ የሦስቱም ግምባር ተጋጨ፡፡
ጭንቅላታቸውን ሳያላቅቁ ዝም ብለው ትሉን በመገረም ተመለከቱ::
«እናንተ ልጆች ምን ሆናችሁ?» ብላ መዳም ቴናድዬ ጠየቀች
«ልጆች እኮ ሲተዋወቁ ጊዜ አይወስድባቸውም፧ እያቸው እስቲ! ሦስቱም ከአንድ እናት አንጀት የወጡ አይመስሉም» በማለት መዳም ቴናድዬ ቀጥታ
ተናገረች::
የሴትዮዋ አነጋገር በተጠንቀቅ ላይ የነበረው የሌላይቱ እናት አሳብ መዘርገፍ ምክንያት ሆነ፡፡ ፋንቲን የመዳም ቴናድዬን እጅ ያዘች::
«ልጄን ያሳድጉልኛል?»
«ምን አልሽ!»
«ልጄን ያሳድጉልኛል?»
«ትንሽ ነገሩን ማብላላት አያስፈልግ ብለሽ!»
«በወር ስድስት ፍራንክ እከፍልዎታለሁ::»
ከቤት ውስጥ ጉርነን ያለ የወንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
«ከሰባተ ፍራንክ በታች አይሆንም፤ ደግሞም የስድስት ወር ክፍያ በቅድማያ ነው የሚከፈለው:: ስድስት ጊዜ ሰባት አርባ ሁለት ፍራንክ መሆኑ ነው::
‹‹እከፍላለሀ•» አለች የኮዚት እናት::
«አንዳንድ ነገሮችን ለማሟላት አንድ አሥራ አምስት ፍራንክ
በተጨማሪ ያስፈልጋል» አለ ቀጠለና ሰውዬው::
«እንግዲህ በድምሩ አምሳ ሰባት ፍራንክ መሆን ነው» አለች መዳም
ቴናድዬ::
እከፍላለሁ›› አለች ድሃዋ እናት:: «አሁን በእጁ ያለው ሰማንያ
ፍራንክ ነው:: ቀሪው ገንዘብ እንደምንም ብሎ አገሬ ያስገባኛል፡፡ ከዚያ ደግሞ ሥራ አላጣም:: ወዲያው ትንሽ ገንዘብ እንዳፈራሁ ተመልሼ መጥቼ
ልጄን እወስዳታለሁ::»
የሰውዬው ድምፅ እንደገና ተሰማ፡፡
«ለመሆነ የሌሊት ልብስ አላት?»
ባለቤቴ ነው» አለች ማዳም ቴናድዬ::
«በሚገባ፤ ደግሞ ለእርስዋ ያልሆንኩ፡፡ ባለቤትዎ እንደሆኑ እኔም ጠርጥሬአለሁ:: እኔው ፈትዬ ያሠራሁላት ወፍራም ልብስ አላት:: የሌሊት ብቻ ሳይሆን ቀን ቀን የምትለብሰውም ከለበሰችው ሌላ ሁለት ቀሚስ አላት::
«እንግዲያው ልብሶችዋን ትተሽ ነው የምትሄጂው» አሉ ሰውዬው::
«ይዤውማ አልሄድም» አለች እናት:: «ልጄን ራቁትዋን ጥያት
ብሄድ ሰው ጉድ አይልም::»
ሰውዬው ከነበረበት ወደ ውጭ ብቅ አለ፡፡
«ይሄ ጥሩ ነው» ሲል ተናገረ ዝቅ ባለ ድምፅ::
በዚህ ተስማሙ:: የኮዜት እናት ያን እለት እዚያው አደረች:: ገንዘቡን
ከፈለች:: የልጅትዋንም ልብስ ሰጠች፡፡ በማግስቱ የቀራትን ጨርቅ ቋጥራና በቶሎ እንደምትመለስ ቃል ገብታ የእግር ጉዞዋን ቀጠለች፡፡ ምንም እንኳን
በጥሞና የተፈጸመ ስምምነት ቢሆንም የወለደቻትን ልጅ ጥላ ለምትሄድ እናት ቀላል ውሳኔ አልነበረም:: አንጀትን ከሁለት የሚከፍል ዓይነት ውሳኔ
ነው::
👍18
የእነማዳም ቴናድዬ ጎረቤት ፋንቲንን መንገድ ታያታለች:: ሴትዮዋ
«እንዴት አደራችሁ» ለማለት ከእነቴናድዬ ቤት ጎራ ትላለች::
«ይገርማችኋል ፤ አሁን አንዲት ሴት መንገድ አይቼ ነው የመጣሁት::
ሴትዮዋ ስታሳዝን! በልቅሶ ብዛት ልብዋ የፈረጠ እስኪመስል ነው እያለቀሰች የሄደችው::»
የኮዜት እናት እንደ ሄደች ባል ሚስቱን እንዲህ አላት::
«ይሄ ገንዘብ እኮ ከሰማይ እንደወረደ ነው የሚቆጠረው፡፡ ነገ
ለማዘጋጃ ቤት 110 ፍራንክ እንድንከፍል የታዘዘበት የመጨረሻው ቀን ስለሆነ ለዚያ ማሟያ ይሆነናል:: '50 ፍራንክ ጎደለብኝ፤ ከየት አባቴ
አመጣለሁ' እያልኩ ስጨነቅ ነበር፡፡ በልጆቹ ሰበብ ደህና ይህችን ሴት አጠመድሽልኝ፡፡»
«ያውም ሳይታወቅብኝ» አለች ሴትዮዋ፡፡...
💫ይቀጥላል💫
«እንዴት አደራችሁ» ለማለት ከእነቴናድዬ ቤት ጎራ ትላለች::
«ይገርማችኋል ፤ አሁን አንዲት ሴት መንገድ አይቼ ነው የመጣሁት::
ሴትዮዋ ስታሳዝን! በልቅሶ ብዛት ልብዋ የፈረጠ እስኪመስል ነው እያለቀሰች የሄደችው::»
የኮዜት እናት እንደ ሄደች ባል ሚስቱን እንዲህ አላት::
«ይሄ ገንዘብ እኮ ከሰማይ እንደወረደ ነው የሚቆጠረው፡፡ ነገ
ለማዘጋጃ ቤት 110 ፍራንክ እንድንከፍል የታዘዘበት የመጨረሻው ቀን ስለሆነ ለዚያ ማሟያ ይሆነናል:: '50 ፍራንክ ጎደለብኝ፤ ከየት አባቴ
አመጣለሁ' እያልኩ ስጨነቅ ነበር፡፡ በልጆቹ ሰበብ ደህና ይህችን ሴት አጠመድሽልኝ፡፡»
«ያውም ሳይታወቅብኝ» አለች ሴትዮዋ፡፡...
💫ይቀጥላል💫
👍10❤7
#የታረሙ_ነፍሶች
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እጅጋየሁ ማታ ሦስት ሰዓት ላይ በቤታችን ስልክ ደወለች ማዘር ጋር አስራ አምስት ደቂቃ የሚሆን ሲያወሩ ቆዩና ጥግብ ሲሉ ማዘር እንዲህ አለች፣ “አብርሽ ስልኩ ያንተ ነው ና አናግራት…ቶሎ በል እንዳይቆጥርባት እጅግዬ ናት፡፡”
እጅጋየሁ ሰባትና ስምንተኛ ክፍል አብረን የተማርን ጓደኛዬ ናት፡፡ ይሄው እስካሁንም እንኳን ከኔ
ጋር፣ ከቤተሰብ ጋርም ጥብቅ ወዳጅ ሆና ቀጥላለች፡፡ በተለይ ማዘር ጋር በከፉ በደጉ ይጠያየቃሉ፤እንደውም እውነቱን ለመናገር እጅጋየሁ ከእኔ ይልቅ የእናቴ ጓደኛ ነው የምትመስለኝ፡፡ ከልቧ ጥሩ ልጅ ናት፡፡ የታመመ አሳዳ የምትጠይቅ፣ ሃዘን ካለ ከሃዘንተኛው ሳትለይ የምታፅናና (ጊዜው እንዴት ይለቃታል?) ሰርግም ካለ የጥሪ ካርድ ከማዘጋጀቱ ጀምሮ እስከቤተሰብ ቅልቅል ጎንበስ ቀና ብላ የምታዳድር ሌሎችን የማገልገል ፀጋ ያትረፈረፈላት ልጅ ናት፡፡ እች ናት እጅጋየሁ !
እኔ ታዲያ ወሬዋ ይሰለቸኛል፡፡ ይንዛዛል፡፡ ማቋረጫ የለውም (ስለእጅጋየሁ ወሬ ለእናቴ ስነግራት ግን 'ይንዛዛል አልልም፣ የምለው “ትንሽ ወሬዋ ዘለግ ይላል” ነው፡፡ እናቴ ታዲያ እንዲህ
አሳምሬም ነግሬያት ትበሳጭብኛለች፣ ሂድ እባክህ ወሬኛ ! ዝም ብለህ ወረቴ አለቃ አትልም…ዘለግ አጠር !! ሆዷ ክፋት የለውም፤ ውስጧ ያለውን ሁሉ ስለምታወራ ነው፣ እንደሌሎቹ ነገር በሆዷ የምታብላላ “ማሽንከ' አይደለችም፡፡”
እንግዲህ “ሌሎቹ” እና “ማሽንክ” የሚሉት ቃላት ዝምተኛዋንና የአሁኗን ፍቅረኛዬን 'ቤዛን ኢላማ ያደረጉ የእናቴ ጥይቶች ናቸው፤ እናቴ ቤዛን አትወዳትም፡፡ ከእጅጋየሁ ጋር እንድንገባ
ነበር ፍላጎቷ፡፡ ምን ያደርጋል፣ እጅጋየሁም አይታኝ አይታኝ አገባች፡፡ (ኧረ እንዲያውም የዛሬ
ስድስት ወር አካባቢ 'ወለድኩ ብላ ማዘር ሄዳ አይታታለች፡፡) እኔም ከቤዛ ጋር ፍቅር ጀመርኩ፡፡
ከስምንተኛ ክፍል ወደ ዘጠኝ አልፌ ወደ ሌላ ትምህርት ቤት ስዘዋወር እጅጋየሁ ደገመችና
እዛው ስምንተኛ ከፍል የተማርንበት ትምህርት ቤት ቀረች፡፡ ታዲያ ልክ መስከረም ገብቶ ትምህርት ስንጀምር ደብዳቤ ፃፈችልኝ፡፡ ደብዳቤዋ ላይ መቼም የማልረሳው ግጥም ነበር፡፡
የባህርዳር ቅጠል ዳርዳሩ ለስላሳ፣
ተለያየን ብለህ እንዳንረሳሳ፡፡
እኔም ያለሁ አዲስ አበባ እሷም ያለች አዲስ አበባ፣ “ባህርዳር ድረስ ሄዶ ቅጠል የሚያስበጥስ፣
ሙሾ የሚያስወርድ ምን ጉድ ተፈጠረ?” አልኩና ተገረምኩ፡፡ እጅጋየሁ ነገረ ስራዋ ሁሉ የትልቅ
ሰው ነበር ፤ ያኔ ትልቅ ሰው ማለት ዛሬ ላይ አካባጅ የሚለውን ቃል ይተካል፡፡
ይሄው ዛሬ ደግሞ ደወለች፡፡ መቼም የደወለችበት ምክንያት ወይ የታመመ አልያም የሞተ
ሰው ቢኖር ነው፡፡ ሁለቱም ግምቶቼ ልክ ካልሆኑ ግን የሚያገባ ጓደኛችን አለ ማለት ነው፡፡
“አንተ…ወይ የሰው ነገር፡፡ በቃ እንዲህ በዋል ፈሰስ ሆነህ ቀረህ ? ምን ይሻልሃል ? ወለድኩ
ብዬ አፍ አውጥቼ ተናግሬ 'ማሪያም ትማርሽ? ማንን ገደለ ?”
“አይ…ኧ…” አፍሬ ነበር፡፡
.
“ተወው ተወው… ደህና ነህ ግን ? ስራ ጥሩ ነው ? ቤዚዬስ እንዴት ናት ? ባለፈው መንገድ ላይ አግኝቻት ጉንፋን ያዘኝ ብላ፣ ተሸላት ? ውይ የሷ ነገር በሽታ አትችልም እኮ ሂሂሂሂ የትኛውን ልመልስ ? ትቀጥላለች፡፡ “አብርሽ ልጄ አለቀሰችብኝ፣ ቶሎ ጉዳዩን ልንገርህ.…ቲቸር በለጠ እኮ ሞቱ.."
“ምን?”
“ይሄውልህ ዛሬ ከረፉ፡፡ ነገ ሥላሴ ነው ቀብራቸው፣ ልንገርህ ብዬ ነው፣ ከተመቸህ ብቅ በል
አብርሽ ...እባክህ ከሰው አትለይ…"
“ትቀልጃለሽ በዚህማ አይቀለድም፡፡ ለቲቸር በለጠ ቀብር ….ሞት አልቀርም ለምን ሺ ስራ ጥንቅር አይልም" አልኩ፡፡
“ግን ምን አገኛቸው በናትሽ.…?”
“ሚስታቸው…አንገብግባ ገደለቻቸው፡፡”
“አትቀልጅ ባክሽ”
“እመቤቴን ! በስተርጅና እንዲት እሳት አግብተው፣ ቀን ምድረ ውሪ ጋር ሲዳረቁ ውለው ሲገቡ
እሷ ደግሞ ማታ ከቤት በምላሷ ትጠብሳቸዋለች፡፡ በቃ ሳይደላቸው ድፍት አሉትና አረፉ
ከንፈሯን መጠጠች፡፡
“የሚስት ምላስ ቢደፋ ኖሮ ቢኒ ገና ድሮ…" ቢኒ ባሏ ነው፡፡
“አትሞጣሞጥ አንተ! እኔይቱ ልጅት!” ሳቋ ይቀድማታል፡፡ ነገ መምህር በለጠ ቀብር ላይ ልንናኝ
ተቀጣጥረን ተለያየን፡፡
ምንጊዜም የአማርኛ ክፍለጊዜ ሊጠናቀቅ ሲል አሮጌ የሸራ ቦርሳቸውን ከፍተው በስርዓት ከተሰደሩ ወረቀቶች መሐል አንድ በካኪ ወረቀት የተሸፈነ ትልቅ መፅሐፍ የሚያወጡ፣ ከወገባቸው በመጠኑ ጎበጥ ያሉና ትንሽ ዘርፈፍ ያለ ቅጠልማ ሹራብ የሚለብሱ እድሜያቸው ወደ ሃምሳ ዓመት
የሚሆን ሰው - መምህር በለጠ !!
ተማሪዎቻቸው መልስ ስንመልስ ትናንሽ ዓይኖቻቸውን ጠበብ አድርገው በጥሞና ሲመለከቱን
በዓይናቸው የሚያዳምጡን ይመስለን ነበር፡፡ መምህር በለጠ !! በመምህር በለጠ ከፍላ ጊዚ ደስታችን ፊታችን ላይ ይንበለበላል፡፡ የማይወዳቸው ተማሪ አልነበረም፡፡ መስፍን እንኳን
አምስት 'ፔሬድ ዘግቶ' እሳቸው ክፍለ ጊዜ ቢሞት አይቀርም፡፡
እንደውም አንድ ቀን በቲቸር በለጠ ክፍለ ጊዜ ለመታደም በአጥር ዘሎ ሲገባ ተይዞ ወላጅ ጠራ፤ የመስፍን አባት፣ “ይሄ የልጄን የትምህርት ፍቅር ነው የሚያሳየው፣ ዘሎ ሲወጣ አልተያዘም ዘሎ ሲገባ እንጂ" አሉ፡፡ መስፍን ከግቢ ውጭ የበላው ፓስቲ የዘይት መሃተሙን ከንፈሩ ላይ እንዳተመበት በቲቸር በለጠ ክፍለ ጊዜ ከተፍ ይላል ያውም ፊት ወንበር ላይ ! በሒሳብ
ከፍለ ጊዜ መስፍን ፊት ወንበር ሂድ!” ከሚባል ሞያሌ ድረስ በባዶ እግሩ ቢሄድ ይሻለዋል፡፡
...በካኪ ወረቀት የተሸፈነው መጸሐፍ ይከፈታል፣ “ፍቅር እስከ መቃብር” ነው ! በመምህር በለጠ ሊተረክ ተከፈተ፡፡ ምድረ ማቲ ከይናችን፣ አፋችን አብሮ ተከፈተ፡፡ ፍቅር እስከ መቃብር ተነስቶ መምህር በለጠን አለማንሳት፣ ከመጸሐፉ ላይ በዛብህን ከመርሳት አይተናነስም፣
እንደውም ፍቅር እስከ መቃብር ገለጥ ገለጥ ቢደረግ፣ በዛብህ ሰብለ ወንጌል..ጉዱ ካሳ.መምህር
በለጠና…ፊታውራሪ መሸሻ እኩል የመጸሐፉ ገፀ-ባህሪያት ሆነው የሚገኙ ይመስለኛል፡፡
በሚያምር ድምፃቸው ትረካውን ይጀምራሉ፡፡ ከዝምታችን ብዛት የልብሳችን ቱማታ ይሰማል
ጭጭ..መምህር በለጠ በትረካቸው መሐል የግል አስተያየታቸውን ይጨምራሉ፡፡ አንዳንዴ አስተያየቱን ጣል የሚያደርጉት በሚተርኩበት ድምፅና ፍጥነት ስለሆነ አስተያየቱን ከታሪክት መለየት ያዳግተናል ፤ ቢሆንም አስተያየቱን የታሪኩ ያህል እንወድደዋለን፡፡
አንደ ፊታውራሪ እየጎደሩ፣ እንደ በዛብህ እየተቅለሰለሱ፣ እንደ ሰብለ ረጋ ብለው፡ እንደ ጉዱ
ካሳ እያፌዙ እና እያሸሞሩ፣ እንደ ሃብትሽ ይመር እየተቆናጠሩ፣ እንደ ቄስ ሞገሴ እየተሽቆጠቆጡ
በግርምት አስጥመውን..እያለ ኪሊሊሊሊሊሊሊሊ ይላል ከፍለ ጊዜው ማብቃቱን የሚያረዳው
ደወል፡፡ ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ…ኤጭጭ! በየአፋችን እንጋጫለን፡፡
ቲቸር መጻሐፉን ደጋግመው ደጋግመው ስላነበቡት የሚበልጠውን በቃላቸው ነበር የሚወጡት፤
እያነበቡ ድንገት በመሐል አንዱን ወይም አንዷን ተማሪ ይጠራሉ፣
"ሃና"
እቤት ቲቸር!” ድንገት በመጠራቷ ደንግጣ ታፈጣለች፡፡ የከፍላችን ጎበዝ ተማሪ ናት ሃና…
“የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎት ምንድን ነው ?” ይጠይቋታል፡፡
“ምግብ…ልብስ…መጠለያ..” መለሰችው እንላለን እኛ በሹክሹክታ፡፡ ገና ትላንት ነው አካባቢ ሳይንስ መምህርታችን ያስተማረችን፡፡
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እጅጋየሁ ማታ ሦስት ሰዓት ላይ በቤታችን ስልክ ደወለች ማዘር ጋር አስራ አምስት ደቂቃ የሚሆን ሲያወሩ ቆዩና ጥግብ ሲሉ ማዘር እንዲህ አለች፣ “አብርሽ ስልኩ ያንተ ነው ና አናግራት…ቶሎ በል እንዳይቆጥርባት እጅግዬ ናት፡፡”
እጅጋየሁ ሰባትና ስምንተኛ ክፍል አብረን የተማርን ጓደኛዬ ናት፡፡ ይሄው እስካሁንም እንኳን ከኔ
ጋር፣ ከቤተሰብ ጋርም ጥብቅ ወዳጅ ሆና ቀጥላለች፡፡ በተለይ ማዘር ጋር በከፉ በደጉ ይጠያየቃሉ፤እንደውም እውነቱን ለመናገር እጅጋየሁ ከእኔ ይልቅ የእናቴ ጓደኛ ነው የምትመስለኝ፡፡ ከልቧ ጥሩ ልጅ ናት፡፡ የታመመ አሳዳ የምትጠይቅ፣ ሃዘን ካለ ከሃዘንተኛው ሳትለይ የምታፅናና (ጊዜው እንዴት ይለቃታል?) ሰርግም ካለ የጥሪ ካርድ ከማዘጋጀቱ ጀምሮ እስከቤተሰብ ቅልቅል ጎንበስ ቀና ብላ የምታዳድር ሌሎችን የማገልገል ፀጋ ያትረፈረፈላት ልጅ ናት፡፡ እች ናት እጅጋየሁ !
እኔ ታዲያ ወሬዋ ይሰለቸኛል፡፡ ይንዛዛል፡፡ ማቋረጫ የለውም (ስለእጅጋየሁ ወሬ ለእናቴ ስነግራት ግን 'ይንዛዛል አልልም፣ የምለው “ትንሽ ወሬዋ ዘለግ ይላል” ነው፡፡ እናቴ ታዲያ እንዲህ
አሳምሬም ነግሬያት ትበሳጭብኛለች፣ ሂድ እባክህ ወሬኛ ! ዝም ብለህ ወረቴ አለቃ አትልም…ዘለግ አጠር !! ሆዷ ክፋት የለውም፤ ውስጧ ያለውን ሁሉ ስለምታወራ ነው፣ እንደሌሎቹ ነገር በሆዷ የምታብላላ “ማሽንከ' አይደለችም፡፡”
እንግዲህ “ሌሎቹ” እና “ማሽንክ” የሚሉት ቃላት ዝምተኛዋንና የአሁኗን ፍቅረኛዬን 'ቤዛን ኢላማ ያደረጉ የእናቴ ጥይቶች ናቸው፤ እናቴ ቤዛን አትወዳትም፡፡ ከእጅጋየሁ ጋር እንድንገባ
ነበር ፍላጎቷ፡፡ ምን ያደርጋል፣ እጅጋየሁም አይታኝ አይታኝ አገባች፡፡ (ኧረ እንዲያውም የዛሬ
ስድስት ወር አካባቢ 'ወለድኩ ብላ ማዘር ሄዳ አይታታለች፡፡) እኔም ከቤዛ ጋር ፍቅር ጀመርኩ፡፡
ከስምንተኛ ክፍል ወደ ዘጠኝ አልፌ ወደ ሌላ ትምህርት ቤት ስዘዋወር እጅጋየሁ ደገመችና
እዛው ስምንተኛ ከፍል የተማርንበት ትምህርት ቤት ቀረች፡፡ ታዲያ ልክ መስከረም ገብቶ ትምህርት ስንጀምር ደብዳቤ ፃፈችልኝ፡፡ ደብዳቤዋ ላይ መቼም የማልረሳው ግጥም ነበር፡፡
የባህርዳር ቅጠል ዳርዳሩ ለስላሳ፣
ተለያየን ብለህ እንዳንረሳሳ፡፡
እኔም ያለሁ አዲስ አበባ እሷም ያለች አዲስ አበባ፣ “ባህርዳር ድረስ ሄዶ ቅጠል የሚያስበጥስ፣
ሙሾ የሚያስወርድ ምን ጉድ ተፈጠረ?” አልኩና ተገረምኩ፡፡ እጅጋየሁ ነገረ ስራዋ ሁሉ የትልቅ
ሰው ነበር ፤ ያኔ ትልቅ ሰው ማለት ዛሬ ላይ አካባጅ የሚለውን ቃል ይተካል፡፡
ይሄው ዛሬ ደግሞ ደወለች፡፡ መቼም የደወለችበት ምክንያት ወይ የታመመ አልያም የሞተ
ሰው ቢኖር ነው፡፡ ሁለቱም ግምቶቼ ልክ ካልሆኑ ግን የሚያገባ ጓደኛችን አለ ማለት ነው፡፡
“አንተ…ወይ የሰው ነገር፡፡ በቃ እንዲህ በዋል ፈሰስ ሆነህ ቀረህ ? ምን ይሻልሃል ? ወለድኩ
ብዬ አፍ አውጥቼ ተናግሬ 'ማሪያም ትማርሽ? ማንን ገደለ ?”
“አይ…ኧ…” አፍሬ ነበር፡፡
.
“ተወው ተወው… ደህና ነህ ግን ? ስራ ጥሩ ነው ? ቤዚዬስ እንዴት ናት ? ባለፈው መንገድ ላይ አግኝቻት ጉንፋን ያዘኝ ብላ፣ ተሸላት ? ውይ የሷ ነገር በሽታ አትችልም እኮ ሂሂሂሂ የትኛውን ልመልስ ? ትቀጥላለች፡፡ “አብርሽ ልጄ አለቀሰችብኝ፣ ቶሎ ጉዳዩን ልንገርህ.…ቲቸር በለጠ እኮ ሞቱ.."
“ምን?”
“ይሄውልህ ዛሬ ከረፉ፡፡ ነገ ሥላሴ ነው ቀብራቸው፣ ልንገርህ ብዬ ነው፣ ከተመቸህ ብቅ በል
አብርሽ ...እባክህ ከሰው አትለይ…"
“ትቀልጃለሽ በዚህማ አይቀለድም፡፡ ለቲቸር በለጠ ቀብር ….ሞት አልቀርም ለምን ሺ ስራ ጥንቅር አይልም" አልኩ፡፡
“ግን ምን አገኛቸው በናትሽ.…?”
“ሚስታቸው…አንገብግባ ገደለቻቸው፡፡”
“አትቀልጅ ባክሽ”
“እመቤቴን ! በስተርጅና እንዲት እሳት አግብተው፣ ቀን ምድረ ውሪ ጋር ሲዳረቁ ውለው ሲገቡ
እሷ ደግሞ ማታ ከቤት በምላሷ ትጠብሳቸዋለች፡፡ በቃ ሳይደላቸው ድፍት አሉትና አረፉ
ከንፈሯን መጠጠች፡፡
“የሚስት ምላስ ቢደፋ ኖሮ ቢኒ ገና ድሮ…" ቢኒ ባሏ ነው፡፡
“አትሞጣሞጥ አንተ! እኔይቱ ልጅት!” ሳቋ ይቀድማታል፡፡ ነገ መምህር በለጠ ቀብር ላይ ልንናኝ
ተቀጣጥረን ተለያየን፡፡
ምንጊዜም የአማርኛ ክፍለጊዜ ሊጠናቀቅ ሲል አሮጌ የሸራ ቦርሳቸውን ከፍተው በስርዓት ከተሰደሩ ወረቀቶች መሐል አንድ በካኪ ወረቀት የተሸፈነ ትልቅ መፅሐፍ የሚያወጡ፣ ከወገባቸው በመጠኑ ጎበጥ ያሉና ትንሽ ዘርፈፍ ያለ ቅጠልማ ሹራብ የሚለብሱ እድሜያቸው ወደ ሃምሳ ዓመት
የሚሆን ሰው - መምህር በለጠ !!
ተማሪዎቻቸው መልስ ስንመልስ ትናንሽ ዓይኖቻቸውን ጠበብ አድርገው በጥሞና ሲመለከቱን
በዓይናቸው የሚያዳምጡን ይመስለን ነበር፡፡ መምህር በለጠ !! በመምህር በለጠ ከፍላ ጊዚ ደስታችን ፊታችን ላይ ይንበለበላል፡፡ የማይወዳቸው ተማሪ አልነበረም፡፡ መስፍን እንኳን
አምስት 'ፔሬድ ዘግቶ' እሳቸው ክፍለ ጊዜ ቢሞት አይቀርም፡፡
እንደውም አንድ ቀን በቲቸር በለጠ ክፍለ ጊዜ ለመታደም በአጥር ዘሎ ሲገባ ተይዞ ወላጅ ጠራ፤ የመስፍን አባት፣ “ይሄ የልጄን የትምህርት ፍቅር ነው የሚያሳየው፣ ዘሎ ሲወጣ አልተያዘም ዘሎ ሲገባ እንጂ" አሉ፡፡ መስፍን ከግቢ ውጭ የበላው ፓስቲ የዘይት መሃተሙን ከንፈሩ ላይ እንዳተመበት በቲቸር በለጠ ክፍለ ጊዜ ከተፍ ይላል ያውም ፊት ወንበር ላይ ! በሒሳብ
ከፍለ ጊዜ መስፍን ፊት ወንበር ሂድ!” ከሚባል ሞያሌ ድረስ በባዶ እግሩ ቢሄድ ይሻለዋል፡፡
...በካኪ ወረቀት የተሸፈነው መጸሐፍ ይከፈታል፣ “ፍቅር እስከ መቃብር” ነው ! በመምህር በለጠ ሊተረክ ተከፈተ፡፡ ምድረ ማቲ ከይናችን፣ አፋችን አብሮ ተከፈተ፡፡ ፍቅር እስከ መቃብር ተነስቶ መምህር በለጠን አለማንሳት፣ ከመጸሐፉ ላይ በዛብህን ከመርሳት አይተናነስም፣
እንደውም ፍቅር እስከ መቃብር ገለጥ ገለጥ ቢደረግ፣ በዛብህ ሰብለ ወንጌል..ጉዱ ካሳ.መምህር
በለጠና…ፊታውራሪ መሸሻ እኩል የመጸሐፉ ገፀ-ባህሪያት ሆነው የሚገኙ ይመስለኛል፡፡
በሚያምር ድምፃቸው ትረካውን ይጀምራሉ፡፡ ከዝምታችን ብዛት የልብሳችን ቱማታ ይሰማል
ጭጭ..መምህር በለጠ በትረካቸው መሐል የግል አስተያየታቸውን ይጨምራሉ፡፡ አንዳንዴ አስተያየቱን ጣል የሚያደርጉት በሚተርኩበት ድምፅና ፍጥነት ስለሆነ አስተያየቱን ከታሪክት መለየት ያዳግተናል ፤ ቢሆንም አስተያየቱን የታሪኩ ያህል እንወድደዋለን፡፡
አንደ ፊታውራሪ እየጎደሩ፣ እንደ በዛብህ እየተቅለሰለሱ፣ እንደ ሰብለ ረጋ ብለው፡ እንደ ጉዱ
ካሳ እያፌዙ እና እያሸሞሩ፣ እንደ ሃብትሽ ይመር እየተቆናጠሩ፣ እንደ ቄስ ሞገሴ እየተሽቆጠቆጡ
በግርምት አስጥመውን..እያለ ኪሊሊሊሊሊሊሊሊ ይላል ከፍለ ጊዜው ማብቃቱን የሚያረዳው
ደወል፡፡ ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ…ኤጭጭ! በየአፋችን እንጋጫለን፡፡
ቲቸር መጻሐፉን ደጋግመው ደጋግመው ስላነበቡት የሚበልጠውን በቃላቸው ነበር የሚወጡት፤
እያነበቡ ድንገት በመሐል አንዱን ወይም አንዷን ተማሪ ይጠራሉ፣
"ሃና"
እቤት ቲቸር!” ድንገት በመጠራቷ ደንግጣ ታፈጣለች፡፡ የከፍላችን ጎበዝ ተማሪ ናት ሃና…
“የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎት ምንድን ነው ?” ይጠይቋታል፡፡
“ምግብ…ልብስ…መጠለያ..” መለሰችው እንላለን እኛ በሹክሹክታ፡፡ ገና ትላንት ነው አካባቢ ሳይንስ መምህርታችን ያስተማረችን፡፡
👍22
“አይደለም ! በጭራሽ አይደለም ! ሳይንሱ እውነታውን ጋርዶብናል፡፡ እንጀራን ማን ህሊና ውስጥ ቦታ ሰጠው ? 'የምድር ፍሬ፣ የወንዝ ውሃ ይሙላህ የተባለን ሆድ ማነው የሰው መሰረት
ያደረገው? የለም! በየጫካው በየዱሩ ርቃናቸውን የሚኖሩ ወገኖቻችን ርቃናቸው ጌጣቸው ነው፤ ቤትስ ቢሆን - የሰው ልጅ ተንኮሉን ሊከልል፣ ማካፈሉን ሊጋርድ ግድግዳ አቆመና ስስታም
እንዳይባል 'ቤት መሰረታዊ ፍላጎት ነው አለ ለግርዶሹ ስም አወጣ፡፡ ልጆች ልብ በሉ…የሰው መሰረታዊ ፍላጎት አንድ ነው፣ እሱም ፍቅር ነው:: ካለፍቅር ሰው የቁም ሙት ነው፡፡ ሰው ሰውን ሲያፈቅር፣ ሰው አምላኩን ሲያፈቅር፣ ሰው አገሩን ሲያፈቅር፣ ሰው እውነትን ሲያፈቅር፣ሰው ነፃነትን ሲያፈቅር ነው ህያው የሚሆነው:: ሰው ነገውን ሲወድ፣ ነገውን ሲያፈቅር ነው ነገ ለሚፈጠር ትውልድ ፍቅር የሚያወርሰው እስትንፋሱ የሚቀጥለው:፡ በሉ መልሱልኝ፣
“በዛብህ እንጀራ አጣ?” ይጠይቁናል፡፡
“አላጣም!” በአንድ ላይ እንመልሳለን፡፡
“ልብስ እጣ?”
“አላጣም”
“ቤትስ”
“አላጣም"
“አያችሁ! ፍቅርን ብሎ፣ ፍቅርን ተርቦ፣ ፍቅርን ተራቁቶ ሲንከራተት ኣባይ በረሃ የሽፍታ ሲሳይ ሆኖ ቀረ” እዝን ብለው በመስኮት ወደ ውጭ እየተመለከቱ ከቆዩ በኋላ፣ “ፍቅር ነው የሰው መሐሉ” ይሉና ሁላችንንም ያዩናል.
መምህር በለጠ ይሄው ሞቱ ! እጅጋየሁ እንዳለችው በሚስታቸው ብስጭት ሞተው ከሆነ የሰበኩትን ፍቅር አጥተው ሞቱ !!
ሃና የክፍላችን ጎበዝ ተማሪ ታዲያ ያሏትን ለቀም አደረገችና የአካባቢ ሳይንስ ፈትና ላይ የሰው
መሰረታዊ ፍላጎት 'ፍቅር' ነው ብላ በመመለሷ ኤክስ' ገባባት፡፡
ቲቸር በለጠ ይሄን ሰምተው ሳቅ አሉ፤ ከዛም ረጋ ብለው መከሩን፣
“ልጆች! በሉ የተባልነውን ስንላችሁ ብቻ ነው ትምህርት ተማራችሁ የሚባለው፡፡ የነፍስ ሃቅ ትምህርት መስሏችሁ ተቀብላችሁ አትሩጡ! ነፍስ ያመነው እና ወረቀት የሚያምነው የተለያየ ነው፡፡ ይሄን አትርሱ፡፡ የነፍስን እምነት የሚሸከም ትከሻ ያለው ወረቀት እምብዛም ነው፡፡ ስንቱ ነብሱ ሹክ ያለውን ለወረቀት ሹክ ብሎ እንጦሮጦስ ወርዷል !!” ብለው በዝምታ ከዳር እስከ ዳር የተኮለኮልነውን ተማሪዎች ይቃኙንና ድንገት፣
“ሃና !” ብለው ይጣራሉ፣
“አቤት ቲቸር!”
“..አስተማሪሽ ነፍስሽን ማረም አትችልም፣ ለዛ ነው ኤክስ' የገባብሽ” ካሉ በኋላ የሃናን አማርኛ ደብተር ወስደው በቀይ እስክርቢቶ ፈረሙበት፡፡ “አማርኛ ፈተና ላይ ሁለት ነጥብ ጉርሻ
ሰጥቼሻለሁ፡፡” የሃና ነፍስ ታረመ !! (ሃኒን ከብዙ ዓመት በኋላ አንድ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ላይ በጦርነት ስለሚጎዱ ህፃናትና እናቶች የምርምር ወረቀት አቅርባ በቴሌቪዥን አየኋት፡፡
ያቀረበችውን ወረቀት አፈላልጌ አነበብኩት፡፡ እውነትም ሃኒ ነፍሷ ታርሟል፡፡)
መምህር በለጠ…ትረካቸውን ቀጥለው እንደፈዘዝን…ድንገት፣
“አንተ እሳት ትውልድ ዝሙትና ፍቅር የየቅል ነው:: ሰብለ ዝሙት ብትሻ እንደ ውሻ እግሯን
የሚከተል መኳንንት ነበረላት፡፡ ልብ በሉ ትዳር አያስጨፍርም:: 'ብቻዬን ከመውደቅ ሁለት ሆኜ ልውደቅ' የሚሉም ጅሎች ናቸው ፤ አብሮ መሆን እና አንድ መሆን የየቅል ነው፡፡ ትዳር አንድ መሆን ነው !! በጥቅም በሰከረ ትዳርና በፍቅር በሰከረች ሰብለ መሐል አንድ የሰከረ እርምጃ ሲቀር ፍቅር በመሐል ገባ፡፡
በላይ ዘለቀ ከነተከታዮቹ ቤልጅግ ይዞ የናኘበትን ጫካ ሰብለ ፍቅር ታጥቃ ብቻዋን ዘመተችበት፡፡ በላይም ለአገሩ ፍቅር፣ ሰብለም ለበዛብህ ፍቅር አያችሁ ... የአባይን በረሃ የሚያሻግር ድልድይ ምንድን ነው ፍቅር ! ያልተበረዘ ያልተከለለ ሃቅን ወደ ትውልድ ማስተላለፊያው መንገድ ምንድን ነው ? ፍቅር! ሰብለ አንበሳና ነብሩን ፊት ለፊት ተጋፈጠች ..."
“መስፍን"
"አቤት ቲቸር?"
አንተ ዱርዬ ፓስቲ ቤት ለፓስቲ ቤት ልጃገረድ ይዞ መዞር ፍቅር አይደለም. የከፍሉ ልጅ
በሳቅ ያውካካል፡፡ መስፍን ሁልጊዜም ከሴቶች ጋር ሻይ ቤት መታየቱ የታወቀ ነው፡፡
"አበባ!"
"አቤት!"
(ወደ አበባ በመጸሐፉ እየጠቆሙ) "ከማንም ጎረምሳ ጋር ሲገቡና ሲወጡ መላፋትና መጓተት
ፍቅር አይደለም፡፡ ፍቅር ራስን ያስከፍላል፡፡ ፍቅር ብታገኘውም ያስከፍልሃል፣ ብታጣውም
ያስከፍላል .. ክፍያው የየቅል ቢሆንም !!
መምህር በለጠ በአማርኛ ክፍለ ጊዜ የፍቅር ሰዋሰው የሚያስተምሩ፣ የነፍሳችን ስንኝ ከፍቅር ስንኝ ጋር ቤት እንዲመታ የገለፁን መምህር ይሄው እንደተባለው ከሆነ ፍቅር ተርበው' ሞቱ !
እሳት ትውልድ ንቃ፣ ዘመኑ የእነ ቄስ ሞገሴ ዘመን ነው:: ተመሳስሎ፣ ተለጥፎ የመኖር
ዘመንና። ሆድን አናት ላይ አስቀምጦ እዩኝ ማለት፡፡ ፊት ለፊት ለምን?” ከማለት ፊት እያዩ፣
ፊትን የመምሰል እስስትነት አዋቂ የሚያስብልበት ዘመን ነው:: እባብነት ዝና የሆነበት፡፡ እነጉዱ
ካሳን የማውገዘ ዘመን..” ይላሉ ሲናገሩ አንዳንድ ከተረከዛቸው ብጅግ ብለዉት በጥፍራቸው
እየቆሙ መፅሐፉን በአመልካች ጣታቸው እልባትነት ከፍለው ይዘው ከፍ ዝቅ እያደረጉ ስለሆነ፣
የሙዚቃ ኦርኬስትራ መሪ ይመስሉ ነበር፡፡
ሞቱ መምህሩ !
አንድ ቀን አበበ በሶ በላ ብለው ፃፉና፣ " አበበ አንተ ነህ፣ አበበ እኔ ነኝ፣ ከበበ በዛብህ ... አበበ
ሰብለ ናት፡፡ አበባ ጉዱ ካሳ፣ አበበ ቄስ ሞገሴ፣ አበበ ፊታውራሪ መሸሻ .. አበበ ወዛደሩ፣
አበበ ምሁሩ፡፡ እነጋገራቸው ስብከት ይመስል ነበር፡፡
... አበበ ሰብለ ስትሆን፣ በሶው .. የታሰርክበትን የባህል ሰንሰለት በፍቅር ቢላዋ መበጣጠስ
የጥቅም ጣኦትህን አሽቀንጥረህ የፍቅር ፅላትህን ማንገስ ነው፡፡ አበበ በዛብህ ቢሆን፡ በሶው መርገምትና ማስፈራሪያን የናቀ ፍቅር ነው፡፡ ሌሎች በራሳቸው ደስታ የጫኑብህን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስእለት ማሽቀንጠር ነው::ላልተሳልከው ስእለት ህይወትህን አለመስጠት አበበ ፊታውራሪ መሸሻ ሲሆን በሶው ቅራሪ ርዝራዥ የዘር ማንዘር ክብር ነው... በዘር መኮፈስ .. ትዕቢት፡፡ አበበ ጉዱ ካሳ ሲሆን፣ በሶው በጨለመ ዘመን በእብደት ደመና የተሸፈነ መብረቃዊ መግለጥ ነው…” እሉና ኮስተር ብለው ቃኙን፡፡
ይሄው 'ቲቸር በሰጠ፥ ሞቱ !
የቲቸር በለጠን አስክሬን ከተሸከሙት ሰዎች መካከል እንዱ እኔ ነበርኩ፡፡ ከፊቴ መስፍን አለ፤
አስክሬኑ ከበደኝ፡፡ የተሽከምኩት የመምህሬን ኮስማና አካል መሆኑን እስክጠራጠር አስክሬኑ
ከበደኝ.. !!
ከአብረቅራቂ ልብስ ተሸፍኖ በእሳት ትውልድ ታጅቦ ወደ መቃብር የሚጣደፈው አስከሬን ጋር..ሰብለ …በዛብህ ..ጉዱ ካሳ … ፊታውራሪ መሸሻ የኢትዮጵያ ስነ ጽሁፍ ..ታላላቆቹ የጥበብ
ሰዎች ..ፍቅር ራሱ አብረው ወደ መቃብር እየተወሰዱ መሰለኝ፡ ካለነገሩ አልከበደኝም ይሄ
አስክሬን !! እህሳ ....ማን ተረፈ፣ እና ቄስ ሞገሴ አልቃሽ ሆነው፣ ቀብር ቆፋሪ ሆነው፣ አጃቢ
ሆነው ምድርን ሞልተው
አበበ መምህር በለጠ ሲሆን፣ በሰው ነፍሱ የታረመ ትውልድ ነበር!!
ይሄን ያለ ግን አልነበረም፡፡ ሁሉም ሰው የሚያወራው ስለሚስታቸው አቃጣይነት ብቻ ነበር፤ ከሟቹ ይልቅ የሞቱ ምክንያት መግነኑ የሞተን ሰው ሥራ ህያው ከማድረግ ይልቅ የቋሚን መቆም
በምክንያት መዝለፍ ስለሚቀል ይሄንኑ ተራ መንገድ የመከተል አምልኮ መሰለኝ፡፡
✨አለቀ✨
ያደረገው? የለም! በየጫካው በየዱሩ ርቃናቸውን የሚኖሩ ወገኖቻችን ርቃናቸው ጌጣቸው ነው፤ ቤትስ ቢሆን - የሰው ልጅ ተንኮሉን ሊከልል፣ ማካፈሉን ሊጋርድ ግድግዳ አቆመና ስስታም
እንዳይባል 'ቤት መሰረታዊ ፍላጎት ነው አለ ለግርዶሹ ስም አወጣ፡፡ ልጆች ልብ በሉ…የሰው መሰረታዊ ፍላጎት አንድ ነው፣ እሱም ፍቅር ነው:: ካለፍቅር ሰው የቁም ሙት ነው፡፡ ሰው ሰውን ሲያፈቅር፣ ሰው አምላኩን ሲያፈቅር፣ ሰው አገሩን ሲያፈቅር፣ ሰው እውነትን ሲያፈቅር፣ሰው ነፃነትን ሲያፈቅር ነው ህያው የሚሆነው:: ሰው ነገውን ሲወድ፣ ነገውን ሲያፈቅር ነው ነገ ለሚፈጠር ትውልድ ፍቅር የሚያወርሰው እስትንፋሱ የሚቀጥለው:፡ በሉ መልሱልኝ፣
“በዛብህ እንጀራ አጣ?” ይጠይቁናል፡፡
“አላጣም!” በአንድ ላይ እንመልሳለን፡፡
“ልብስ እጣ?”
“አላጣም”
“ቤትስ”
“አላጣም"
“አያችሁ! ፍቅርን ብሎ፣ ፍቅርን ተርቦ፣ ፍቅርን ተራቁቶ ሲንከራተት ኣባይ በረሃ የሽፍታ ሲሳይ ሆኖ ቀረ” እዝን ብለው በመስኮት ወደ ውጭ እየተመለከቱ ከቆዩ በኋላ፣ “ፍቅር ነው የሰው መሐሉ” ይሉና ሁላችንንም ያዩናል.
መምህር በለጠ ይሄው ሞቱ ! እጅጋየሁ እንዳለችው በሚስታቸው ብስጭት ሞተው ከሆነ የሰበኩትን ፍቅር አጥተው ሞቱ !!
ሃና የክፍላችን ጎበዝ ተማሪ ታዲያ ያሏትን ለቀም አደረገችና የአካባቢ ሳይንስ ፈትና ላይ የሰው
መሰረታዊ ፍላጎት 'ፍቅር' ነው ብላ በመመለሷ ኤክስ' ገባባት፡፡
ቲቸር በለጠ ይሄን ሰምተው ሳቅ አሉ፤ ከዛም ረጋ ብለው መከሩን፣
“ልጆች! በሉ የተባልነውን ስንላችሁ ብቻ ነው ትምህርት ተማራችሁ የሚባለው፡፡ የነፍስ ሃቅ ትምህርት መስሏችሁ ተቀብላችሁ አትሩጡ! ነፍስ ያመነው እና ወረቀት የሚያምነው የተለያየ ነው፡፡ ይሄን አትርሱ፡፡ የነፍስን እምነት የሚሸከም ትከሻ ያለው ወረቀት እምብዛም ነው፡፡ ስንቱ ነብሱ ሹክ ያለውን ለወረቀት ሹክ ብሎ እንጦሮጦስ ወርዷል !!” ብለው በዝምታ ከዳር እስከ ዳር የተኮለኮልነውን ተማሪዎች ይቃኙንና ድንገት፣
“ሃና !” ብለው ይጣራሉ፣
“አቤት ቲቸር!”
“..አስተማሪሽ ነፍስሽን ማረም አትችልም፣ ለዛ ነው ኤክስ' የገባብሽ” ካሉ በኋላ የሃናን አማርኛ ደብተር ወስደው በቀይ እስክርቢቶ ፈረሙበት፡፡ “አማርኛ ፈተና ላይ ሁለት ነጥብ ጉርሻ
ሰጥቼሻለሁ፡፡” የሃና ነፍስ ታረመ !! (ሃኒን ከብዙ ዓመት በኋላ አንድ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ላይ በጦርነት ስለሚጎዱ ህፃናትና እናቶች የምርምር ወረቀት አቅርባ በቴሌቪዥን አየኋት፡፡
ያቀረበችውን ወረቀት አፈላልጌ አነበብኩት፡፡ እውነትም ሃኒ ነፍሷ ታርሟል፡፡)
መምህር በለጠ…ትረካቸውን ቀጥለው እንደፈዘዝን…ድንገት፣
“አንተ እሳት ትውልድ ዝሙትና ፍቅር የየቅል ነው:: ሰብለ ዝሙት ብትሻ እንደ ውሻ እግሯን
የሚከተል መኳንንት ነበረላት፡፡ ልብ በሉ ትዳር አያስጨፍርም:: 'ብቻዬን ከመውደቅ ሁለት ሆኜ ልውደቅ' የሚሉም ጅሎች ናቸው ፤ አብሮ መሆን እና አንድ መሆን የየቅል ነው፡፡ ትዳር አንድ መሆን ነው !! በጥቅም በሰከረ ትዳርና በፍቅር በሰከረች ሰብለ መሐል አንድ የሰከረ እርምጃ ሲቀር ፍቅር በመሐል ገባ፡፡
በላይ ዘለቀ ከነተከታዮቹ ቤልጅግ ይዞ የናኘበትን ጫካ ሰብለ ፍቅር ታጥቃ ብቻዋን ዘመተችበት፡፡ በላይም ለአገሩ ፍቅር፣ ሰብለም ለበዛብህ ፍቅር አያችሁ ... የአባይን በረሃ የሚያሻግር ድልድይ ምንድን ነው ፍቅር ! ያልተበረዘ ያልተከለለ ሃቅን ወደ ትውልድ ማስተላለፊያው መንገድ ምንድን ነው ? ፍቅር! ሰብለ አንበሳና ነብሩን ፊት ለፊት ተጋፈጠች ..."
“መስፍን"
"አቤት ቲቸር?"
አንተ ዱርዬ ፓስቲ ቤት ለፓስቲ ቤት ልጃገረድ ይዞ መዞር ፍቅር አይደለም. የከፍሉ ልጅ
በሳቅ ያውካካል፡፡ መስፍን ሁልጊዜም ከሴቶች ጋር ሻይ ቤት መታየቱ የታወቀ ነው፡፡
"አበባ!"
"አቤት!"
(ወደ አበባ በመጸሐፉ እየጠቆሙ) "ከማንም ጎረምሳ ጋር ሲገቡና ሲወጡ መላፋትና መጓተት
ፍቅር አይደለም፡፡ ፍቅር ራስን ያስከፍላል፡፡ ፍቅር ብታገኘውም ያስከፍልሃል፣ ብታጣውም
ያስከፍላል .. ክፍያው የየቅል ቢሆንም !!
መምህር በለጠ በአማርኛ ክፍለ ጊዜ የፍቅር ሰዋሰው የሚያስተምሩ፣ የነፍሳችን ስንኝ ከፍቅር ስንኝ ጋር ቤት እንዲመታ የገለፁን መምህር ይሄው እንደተባለው ከሆነ ፍቅር ተርበው' ሞቱ !
እሳት ትውልድ ንቃ፣ ዘመኑ የእነ ቄስ ሞገሴ ዘመን ነው:: ተመሳስሎ፣ ተለጥፎ የመኖር
ዘመንና። ሆድን አናት ላይ አስቀምጦ እዩኝ ማለት፡፡ ፊት ለፊት ለምን?” ከማለት ፊት እያዩ፣
ፊትን የመምሰል እስስትነት አዋቂ የሚያስብልበት ዘመን ነው:: እባብነት ዝና የሆነበት፡፡ እነጉዱ
ካሳን የማውገዘ ዘመን..” ይላሉ ሲናገሩ አንዳንድ ከተረከዛቸው ብጅግ ብለዉት በጥፍራቸው
እየቆሙ መፅሐፉን በአመልካች ጣታቸው እልባትነት ከፍለው ይዘው ከፍ ዝቅ እያደረጉ ስለሆነ፣
የሙዚቃ ኦርኬስትራ መሪ ይመስሉ ነበር፡፡
ሞቱ መምህሩ !
አንድ ቀን አበበ በሶ በላ ብለው ፃፉና፣ " አበበ አንተ ነህ፣ አበበ እኔ ነኝ፣ ከበበ በዛብህ ... አበበ
ሰብለ ናት፡፡ አበባ ጉዱ ካሳ፣ አበበ ቄስ ሞገሴ፣ አበበ ፊታውራሪ መሸሻ .. አበበ ወዛደሩ፣
አበበ ምሁሩ፡፡ እነጋገራቸው ስብከት ይመስል ነበር፡፡
... አበበ ሰብለ ስትሆን፣ በሶው .. የታሰርክበትን የባህል ሰንሰለት በፍቅር ቢላዋ መበጣጠስ
የጥቅም ጣኦትህን አሽቀንጥረህ የፍቅር ፅላትህን ማንገስ ነው፡፡ አበበ በዛብህ ቢሆን፡ በሶው መርገምትና ማስፈራሪያን የናቀ ፍቅር ነው፡፡ ሌሎች በራሳቸው ደስታ የጫኑብህን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስእለት ማሽቀንጠር ነው::ላልተሳልከው ስእለት ህይወትህን አለመስጠት አበበ ፊታውራሪ መሸሻ ሲሆን በሶው ቅራሪ ርዝራዥ የዘር ማንዘር ክብር ነው... በዘር መኮፈስ .. ትዕቢት፡፡ አበበ ጉዱ ካሳ ሲሆን፣ በሶው በጨለመ ዘመን በእብደት ደመና የተሸፈነ መብረቃዊ መግለጥ ነው…” እሉና ኮስተር ብለው ቃኙን፡፡
ይሄው 'ቲቸር በሰጠ፥ ሞቱ !
የቲቸር በለጠን አስክሬን ከተሸከሙት ሰዎች መካከል እንዱ እኔ ነበርኩ፡፡ ከፊቴ መስፍን አለ፤
አስክሬኑ ከበደኝ፡፡ የተሽከምኩት የመምህሬን ኮስማና አካል መሆኑን እስክጠራጠር አስክሬኑ
ከበደኝ.. !!
ከአብረቅራቂ ልብስ ተሸፍኖ በእሳት ትውልድ ታጅቦ ወደ መቃብር የሚጣደፈው አስከሬን ጋር..ሰብለ …በዛብህ ..ጉዱ ካሳ … ፊታውራሪ መሸሻ የኢትዮጵያ ስነ ጽሁፍ ..ታላላቆቹ የጥበብ
ሰዎች ..ፍቅር ራሱ አብረው ወደ መቃብር እየተወሰዱ መሰለኝ፡ ካለነገሩ አልከበደኝም ይሄ
አስክሬን !! እህሳ ....ማን ተረፈ፣ እና ቄስ ሞገሴ አልቃሽ ሆነው፣ ቀብር ቆፋሪ ሆነው፣ አጃቢ
ሆነው ምድርን ሞልተው
አበበ መምህር በለጠ ሲሆን፣ በሰው ነፍሱ የታረመ ትውልድ ነበር!!
ይሄን ያለ ግን አልነበረም፡፡ ሁሉም ሰው የሚያወራው ስለሚስታቸው አቃጣይነት ብቻ ነበር፤ ከሟቹ ይልቅ የሞቱ ምክንያት መግነኑ የሞተን ሰው ሥራ ህያው ከማድረግ ይልቅ የቋሚን መቆም
በምክንያት መዝለፍ ስለሚቀል ይሄንኑ ተራ መንገድ የመከተል አምልኮ መሰለኝ፡፡
✨አለቀ✨
👍34❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ወጥመድ ውስጥ የገባ አይጥ ማምለጫ አጥቶ ይቅበዘበዛል፡፡ ከድመት ጥፍር ውስጥ የገባ ፍጡር ግን ይበልጥ ይጨነቃል፡፡
ማዳምና ሚስተር ቴናድዬ ምን ዓይነት ሰዎች ይሆኑ?
ምድባቸው እውቀት ኖሯቸው ግን ጊዜ ከጣላቸው ሳይሆን የተናቁ
ሆነው ጊዜ ካነሳቸው ሰዎች ውስጥ ነበር፡፡ ጊዜ ያነሳቸው ሰዎች ጥፋት ቢፈጽሙ የሠርቶ አደሩ ትጋት ወይም የቡርዣው ክብር የተጐናጸፉ ባይሆነም ስህተታቸው ጊዜ ከጣላቸው ሰዎች ላይ ተደፍድፎ እነርሱ
ከጥፋቱ ነፃ ይሆናሉ፡፡
ይህም በመሆነ ባልና ሚስት መደባቸው ከተናቁ ሰዎች መካከል
ቢሆንም ጊዜ ስለሰጣቸው ብቻ እንደ ትልልቅ ሰዎች ይከበራሉ:: ሴትዮዋ ጨካኝ፣ ሰውዬው በዋል ፈሰስ ዓይነት ሰዎች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ትንሽ ቀዳዳ ካገኙ ተንኮል ከመሥራት አይቆጠቡም:: እንደ ትል ከብርሃን ወደ ጨለማ፤
እንደ አባያ በሬ ወደፊት ከመራመድ ወደኋላ ማፈግፈግ፤ እንደ እባብ ከቀና አስተሳሰብ ተንኮል ወደ መሽረብ፤ ከሰፊው ጠባብ መንገድን የሚመርጡ
ዓይነት ሰዎች ናቸው::
የሚገርመው ግን ክፋት፧ ተንኮልና ምቀኝነት ለኑሮ መሳካት ዋስትና
ሊሆን ስለማይችል እነዚህ ሰዎች በሆቴል ቤታቸው ብዙም አልተጠቀሙም።
ፋንቲንን ያመስግኑና ሳያስቡት በድንገት ሃምሣ ሰባት ፍራንክ
አግኝተዋል፡፡ ይህን ገንዘብ በማግኘታቸው ሆቴል ቤታቸው ከመታሸግ ዳነ፡፡ግን አሁንም ቢሆን በሚቀጥለው ወር ተጨማሪ ገንዘብ ያስፈልጋቸው ስለነበር ሴትዮዋ የኮዜትን ጋቢና ቀሚሶች ወደ ገበያ ወስዳ ስልሣ ፍራንክ
ሽጠቻቸው፡፡ ገንዘቡ ሲያልቅ ኮዜትን ለነፍሳችን ብለው ያስጠግዋት እንጂ ጥቅም እንዳገኙባት ረስተው በጣም ጨከኑባት፡፡ የራስዋ የሆኑ ልብሶች
ተሽጠው የተቦጫጨቁትን የልጆቻቸው ውራጅ ኣለበስዋት:: ለውሻ እንደሚሰጥም አጥንት ከበላተኛ የወዳደቀ ትርፍራፊ አበልዋት:: ምድብዋ በር
ላይ ተኝቶ ዓይን ዓይን ከሚያይ ውሻና ከተመጋቢ እግር ስር ድምፅ እያሰማ ከሚሄድ ድመት ጋር ሆነ፡፡ ምግብ እንደ ውሻና ድመት በገበቴ መሣይ ነገር መሬት ተጣለላት::
እናትዋ አገርዋ ከገባች በኋላ ከእዚህ ግባ የማይባል ሥራ አገኘች፡፡በየወሩ ደብዳቤ ለእነሚስተር ቴናድዬ ጻፈችላቸው:: በደብዳቤዋ ከልጅዋ
ደኅንነት በስተቀር ሌላ የምትጠይቀው ነገር አልነበራትም፡፡ ባልና ሚስት
የመልስ ደብዳቤ ሲልኩ ኮዜት ተመችቶአት እንደምትኖርና ጤናዋም ደህና መሆኑን ገልጸው ነበር የሚጽፉላት::
ኣንዳንድ ልቦች በአንድ ጎናቸው ጥላቻን ካላቀፉ ፍቅር ብቻውን
መንተራስ የማይችሉ አሉ፡፡ መዳም ቴናድዬ የራስዋን ልጆች በጣም
ትወዳለች:: የልጆችዋ ፍቅር አዲስዋን ልጅ እጅግ እንድትጠላ አደረጋት፡፡ኮዜት ያለ አግባብ ስትነቀፍ፤ ስትገረፍ፤ ስትሰደብ፧ ስትመናጨቅና ስትጠላ
እኩዮችዋ የሆነ ሌሎቹ ሁለት ልጆች ሲታቀፉ፤ እሽሩሩ ሲባሉ፤
የማይገባቸውን ምስጋና ሲያገኙ በማየትዋ ነገሩ ሊገባት አልቻለም:: የሰው ልጅ ጭካኔ፤ የዚህ ዓለም ውጣ ውረድ፤ የእግዚኣብሔር ሽረትና ምህረት
ምን እንደሆነ ለማወቅ እድሜዋ አልፈቀደላትም::
ሴትዮዋ ትጨክንባታለች:: ኢፓኒንና አዜልማም ይጨክኑባታል፡፡ምናልባት የጭካኔው መጠን ይለያይ ይሆናል እንጂ በዚያ እድሜ ልጆች
ቤተሰቦቻቸው የሚፈጽሙትን ነው የሚከተሉት፡፡
ዓመት አለፈ፤ ሌላውም ተደገመ::
የሰፈር ሰዎች ምን ብለው ያወሩ ጀመር፧ «እነመዳም ቴናድዬ ምን
ዓይነት ርህሩህና ደግ ቢሆኑ ነው እባካችሁ:: እነርሱ ለራሳቸው ምስኪኖች ሆነው መጠጊያ የሌላትንና እናትዋ የጣለቻትን ልጅ ያሳድጋሉ::»
የዜት እናት ልጅዋን የረሳች መሰላቸው::
ዓመት እስከ ዓመት ቁመትዋ እየጨመረ ሲሄድ መከራዋና
ስቃይዋም እንዲሁ ጨመረ::
ኮዜት ሕፃን ሆና ሳለ የሁለቱ ልጆች ጥፋት ማስተባበያ ነበረች::
እያደገች ስትሄድ ማለት አምስት ዓመት ሳይሞላት የቤቱ አሽከር ሆነች::
ኮዜት ትላላካለች ፤ ቤት ትጠርጋለች፤ ግቢ ታጸዳለች ፤ እቃ
ታጥባለች ፤ ከባድ ነገር ትሸከማለች:: እናትዋ በየወሩ የምትከፍለውን ገንዘብ ባጓደለች ቁጥር ልጅትዋ የምትሸከመው ሸክም እየከበደ ይሄዳል::
እናትዋ የጥቂት ወሮችን ክፍያ አልላከችም::
እናት ከሦስት ዓመት በኋላ ወደ ሞንትፌርሜ ከተማ ብትመለስና
ልጅዋን ብታያት አታውቃትም፡፡ ያኔ ጥላት ስትሄድ ድምቡሽቡሽ ብላ
ንከሱኝ፣ ግመጡኝ ትል የነበረችው ልጅ በቁራና መንምና አጥንትዋ .
ገጥጦ ፣ ፊትዋ ገርጥቶ ሌላ ልጅ መስላለች፡፡ «እደለ ቢስ፣ ገዳፋ» እያሉ ነው ባልና ሚስት የሚጠርዋት::
እድልዋ ዝምተኛ እንድትሆን ፧ ችግርዋ ፉንጋ እንድትመስል
አድርጓአታል። ዓይኖችዋ ቢጎደጉዱም ከቦታቸው አልጠፉም፣ ሲያይዋቸው
ያስፈራሉ፡፡ ስቃይ እንዳንገበገባቸው ያስታውቃሉ፡፡ ትላልቅ ስለነበሩ ያዘሉትም የስቃይ መጠን ትልቅ ነበር::
ዓይኖችዋ እንባ አቅርረው፣ በክረምት ቡትቶ ለብሳ አፈር ላይ
ስትተኛና በበጋ ደባደቦ ለብሳ በጠራራ ፀሐይ ከቁመትዋ የሚበልጥ መጥረጊያ ይዛ ደጃፍ ስትጥርግ ማየት ልብ ላለው የሚዘገንን ትርኢት ነበር፡፡ ሆኖም
ሰዎች «እድለቢስ... ገዳፉ... እበይ» እያሉ ነበር የሚጠርዋት::
ጠዋት ጠዋት እየተባችና እየፈራች ሰውነትዋ ተንቀጥቅጦ በቅጡ
ሳይነጋ ነበር የምትነሳው:: ከሰፈር የምታመጣው ነገር ካለ የሰፈር ሰው ሳይነሳ ትሄድና እስኪነሱ ትጠብቃለች፡፡ከገበያም የምትገዛው እቃ ካላ
ገበያተኞች እቃቸውን ሳያወጡ እርስዋ ቀድማ ትገኛለች::
ደጉ ሰው
የዚያች ምስኪን ልጅ እናት ምን ሆነች? ሞንትፐርሜ ውስጥ ይኖሩ
የነበሩ ሰዎች ልጅዋን ከድታ እንደጠፋች ሲናገሩ ሰምተናል:: የት ነው ያለችው? ምን እየሠራች ነው?
ኮዜትን ከነማዳም ቴናድዩ ቤት ትታ ከሄደች በኋላ ትውልድ አገርዋ
በደህና ደርሳለች:: ከአሁን በፊት እንደተጠቀሰው IIመነ 1818 ዓ.ም. ነበር፡፡ፋንቲን ወደ ትውልድ አገርዋ የተመለሰችው አገሩን ለቅቃ በወጣች በአሥራ
ሁለተኛ ዓመትዋ ነበር፡፡ አገሩ በጣም ተለዋውጦ ነው ያገኘችው:: የእርስዋ ኑሮ እያቆለቆለ ሲሄድ የትውልድ አገርዋ ከተማ በጣም እያደገና እየተሻሻለ ሄድዋል፡፡ በመጨረሻዎቹ ሁለት ዓመታት በተለይ ትልቅ መሻሻል ተገኝቶ
አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ተቋቁመዋል፡
በዚያ አገር ፋብሪካ ውስጥ ተመርተው የሚወጡ ዕቃዎች ዋጋ እጅግ የናረ ነበር፡፡ ነገር ግን ፋንቲን ወደ አገርዋ ስትመለስ ያ ሁናቴ ተለውጦ ነው የደረሰችው:: አንድ ያልታወቀ ሰው በ1815 ዓ.ም. መጨረሻ ገደማ
መጥቶ አስደናቂ የሆነ የፈጠራ ሥራ በመሥራቱ የፋብሪካ ውጤቶች ዋጋ ዝቅ ይላል::
ሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሰውዬው ከመጠን በላይ ሀብታም
ይሆናል፡፡ ፋብሪካው ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ሰዎች ደግሞ ጥሩ ደመወዝ ስለተከፈላቸው እነሱም የተሻሻለ ኑሮ መኖር ቻሉ፡፡ ሰውዬው ማን እንደሆነና
ከየት እንደመጣ ግን ማንም አያውቅም:: ወደ ከተማው ሲመጣ ምንም ገንዘብ ይዞ እንዳልመጣ ሁሉም የሚያውቀው ፥ነው:: ግን እርሱ በወጠነው
የፈጠራ አሳብ እርሱ ብቻ ሳይሆን አገሩ ሁሉ ከበረበት:: ወደዚያ ሲመጣ አለባበሱም ሆነ አነጋገሩ የጭቁን ሰው ነበር፡፡ በታኅሣሥ ወር ለዓይን ያዝ ሲያደርግ ወደ ከተማው ሲገባ የለበሰው ልብስ የተቦጫጨቀ እግሩና እጁ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ወጥመድ ውስጥ የገባ አይጥ ማምለጫ አጥቶ ይቅበዘበዛል፡፡ ከድመት ጥፍር ውስጥ የገባ ፍጡር ግን ይበልጥ ይጨነቃል፡፡
ማዳምና ሚስተር ቴናድዬ ምን ዓይነት ሰዎች ይሆኑ?
ምድባቸው እውቀት ኖሯቸው ግን ጊዜ ከጣላቸው ሳይሆን የተናቁ
ሆነው ጊዜ ካነሳቸው ሰዎች ውስጥ ነበር፡፡ ጊዜ ያነሳቸው ሰዎች ጥፋት ቢፈጽሙ የሠርቶ አደሩ ትጋት ወይም የቡርዣው ክብር የተጐናጸፉ ባይሆነም ስህተታቸው ጊዜ ከጣላቸው ሰዎች ላይ ተደፍድፎ እነርሱ
ከጥፋቱ ነፃ ይሆናሉ፡፡
ይህም በመሆነ ባልና ሚስት መደባቸው ከተናቁ ሰዎች መካከል
ቢሆንም ጊዜ ስለሰጣቸው ብቻ እንደ ትልልቅ ሰዎች ይከበራሉ:: ሴትዮዋ ጨካኝ፣ ሰውዬው በዋል ፈሰስ ዓይነት ሰዎች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ትንሽ ቀዳዳ ካገኙ ተንኮል ከመሥራት አይቆጠቡም:: እንደ ትል ከብርሃን ወደ ጨለማ፤
እንደ አባያ በሬ ወደፊት ከመራመድ ወደኋላ ማፈግፈግ፤ እንደ እባብ ከቀና አስተሳሰብ ተንኮል ወደ መሽረብ፤ ከሰፊው ጠባብ መንገድን የሚመርጡ
ዓይነት ሰዎች ናቸው::
የሚገርመው ግን ክፋት፧ ተንኮልና ምቀኝነት ለኑሮ መሳካት ዋስትና
ሊሆን ስለማይችል እነዚህ ሰዎች በሆቴል ቤታቸው ብዙም አልተጠቀሙም።
ፋንቲንን ያመስግኑና ሳያስቡት በድንገት ሃምሣ ሰባት ፍራንክ
አግኝተዋል፡፡ ይህን ገንዘብ በማግኘታቸው ሆቴል ቤታቸው ከመታሸግ ዳነ፡፡ግን አሁንም ቢሆን በሚቀጥለው ወር ተጨማሪ ገንዘብ ያስፈልጋቸው ስለነበር ሴትዮዋ የኮዜትን ጋቢና ቀሚሶች ወደ ገበያ ወስዳ ስልሣ ፍራንክ
ሽጠቻቸው፡፡ ገንዘቡ ሲያልቅ ኮዜትን ለነፍሳችን ብለው ያስጠግዋት እንጂ ጥቅም እንዳገኙባት ረስተው በጣም ጨከኑባት፡፡ የራስዋ የሆኑ ልብሶች
ተሽጠው የተቦጫጨቁትን የልጆቻቸው ውራጅ ኣለበስዋት:: ለውሻ እንደሚሰጥም አጥንት ከበላተኛ የወዳደቀ ትርፍራፊ አበልዋት:: ምድብዋ በር
ላይ ተኝቶ ዓይን ዓይን ከሚያይ ውሻና ከተመጋቢ እግር ስር ድምፅ እያሰማ ከሚሄድ ድመት ጋር ሆነ፡፡ ምግብ እንደ ውሻና ድመት በገበቴ መሣይ ነገር መሬት ተጣለላት::
እናትዋ አገርዋ ከገባች በኋላ ከእዚህ ግባ የማይባል ሥራ አገኘች፡፡በየወሩ ደብዳቤ ለእነሚስተር ቴናድዬ ጻፈችላቸው:: በደብዳቤዋ ከልጅዋ
ደኅንነት በስተቀር ሌላ የምትጠይቀው ነገር አልነበራትም፡፡ ባልና ሚስት
የመልስ ደብዳቤ ሲልኩ ኮዜት ተመችቶአት እንደምትኖርና ጤናዋም ደህና መሆኑን ገልጸው ነበር የሚጽፉላት::
ኣንዳንድ ልቦች በአንድ ጎናቸው ጥላቻን ካላቀፉ ፍቅር ብቻውን
መንተራስ የማይችሉ አሉ፡፡ መዳም ቴናድዬ የራስዋን ልጆች በጣም
ትወዳለች:: የልጆችዋ ፍቅር አዲስዋን ልጅ እጅግ እንድትጠላ አደረጋት፡፡ኮዜት ያለ አግባብ ስትነቀፍ፤ ስትገረፍ፤ ስትሰደብ፧ ስትመናጨቅና ስትጠላ
እኩዮችዋ የሆነ ሌሎቹ ሁለት ልጆች ሲታቀፉ፤ እሽሩሩ ሲባሉ፤
የማይገባቸውን ምስጋና ሲያገኙ በማየትዋ ነገሩ ሊገባት አልቻለም:: የሰው ልጅ ጭካኔ፤ የዚህ ዓለም ውጣ ውረድ፤ የእግዚኣብሔር ሽረትና ምህረት
ምን እንደሆነ ለማወቅ እድሜዋ አልፈቀደላትም::
ሴትዮዋ ትጨክንባታለች:: ኢፓኒንና አዜልማም ይጨክኑባታል፡፡ምናልባት የጭካኔው መጠን ይለያይ ይሆናል እንጂ በዚያ እድሜ ልጆች
ቤተሰቦቻቸው የሚፈጽሙትን ነው የሚከተሉት፡፡
ዓመት አለፈ፤ ሌላውም ተደገመ::
የሰፈር ሰዎች ምን ብለው ያወሩ ጀመር፧ «እነመዳም ቴናድዬ ምን
ዓይነት ርህሩህና ደግ ቢሆኑ ነው እባካችሁ:: እነርሱ ለራሳቸው ምስኪኖች ሆነው መጠጊያ የሌላትንና እናትዋ የጣለቻትን ልጅ ያሳድጋሉ::»
የዜት እናት ልጅዋን የረሳች መሰላቸው::
ዓመት እስከ ዓመት ቁመትዋ እየጨመረ ሲሄድ መከራዋና
ስቃይዋም እንዲሁ ጨመረ::
ኮዜት ሕፃን ሆና ሳለ የሁለቱ ልጆች ጥፋት ማስተባበያ ነበረች::
እያደገች ስትሄድ ማለት አምስት ዓመት ሳይሞላት የቤቱ አሽከር ሆነች::
ኮዜት ትላላካለች ፤ ቤት ትጠርጋለች፤ ግቢ ታጸዳለች ፤ እቃ
ታጥባለች ፤ ከባድ ነገር ትሸከማለች:: እናትዋ በየወሩ የምትከፍለውን ገንዘብ ባጓደለች ቁጥር ልጅትዋ የምትሸከመው ሸክም እየከበደ ይሄዳል::
እናትዋ የጥቂት ወሮችን ክፍያ አልላከችም::
እናት ከሦስት ዓመት በኋላ ወደ ሞንትፌርሜ ከተማ ብትመለስና
ልጅዋን ብታያት አታውቃትም፡፡ ያኔ ጥላት ስትሄድ ድምቡሽቡሽ ብላ
ንከሱኝ፣ ግመጡኝ ትል የነበረችው ልጅ በቁራና መንምና አጥንትዋ .
ገጥጦ ፣ ፊትዋ ገርጥቶ ሌላ ልጅ መስላለች፡፡ «እደለ ቢስ፣ ገዳፋ» እያሉ ነው ባልና ሚስት የሚጠርዋት::
እድልዋ ዝምተኛ እንድትሆን ፧ ችግርዋ ፉንጋ እንድትመስል
አድርጓአታል። ዓይኖችዋ ቢጎደጉዱም ከቦታቸው አልጠፉም፣ ሲያይዋቸው
ያስፈራሉ፡፡ ስቃይ እንዳንገበገባቸው ያስታውቃሉ፡፡ ትላልቅ ስለነበሩ ያዘሉትም የስቃይ መጠን ትልቅ ነበር::
ዓይኖችዋ እንባ አቅርረው፣ በክረምት ቡትቶ ለብሳ አፈር ላይ
ስትተኛና በበጋ ደባደቦ ለብሳ በጠራራ ፀሐይ ከቁመትዋ የሚበልጥ መጥረጊያ ይዛ ደጃፍ ስትጥርግ ማየት ልብ ላለው የሚዘገንን ትርኢት ነበር፡፡ ሆኖም
ሰዎች «እድለቢስ... ገዳፉ... እበይ» እያሉ ነበር የሚጠርዋት::
ጠዋት ጠዋት እየተባችና እየፈራች ሰውነትዋ ተንቀጥቅጦ በቅጡ
ሳይነጋ ነበር የምትነሳው:: ከሰፈር የምታመጣው ነገር ካለ የሰፈር ሰው ሳይነሳ ትሄድና እስኪነሱ ትጠብቃለች፡፡ከገበያም የምትገዛው እቃ ካላ
ገበያተኞች እቃቸውን ሳያወጡ እርስዋ ቀድማ ትገኛለች::
ደጉ ሰው
የዚያች ምስኪን ልጅ እናት ምን ሆነች? ሞንትፐርሜ ውስጥ ይኖሩ
የነበሩ ሰዎች ልጅዋን ከድታ እንደጠፋች ሲናገሩ ሰምተናል:: የት ነው ያለችው? ምን እየሠራች ነው?
ኮዜትን ከነማዳም ቴናድዩ ቤት ትታ ከሄደች በኋላ ትውልድ አገርዋ
በደህና ደርሳለች:: ከአሁን በፊት እንደተጠቀሰው IIመነ 1818 ዓ.ም. ነበር፡፡ፋንቲን ወደ ትውልድ አገርዋ የተመለሰችው አገሩን ለቅቃ በወጣች በአሥራ
ሁለተኛ ዓመትዋ ነበር፡፡ አገሩ በጣም ተለዋውጦ ነው ያገኘችው:: የእርስዋ ኑሮ እያቆለቆለ ሲሄድ የትውልድ አገርዋ ከተማ በጣም እያደገና እየተሻሻለ ሄድዋል፡፡ በመጨረሻዎቹ ሁለት ዓመታት በተለይ ትልቅ መሻሻል ተገኝቶ
አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ተቋቁመዋል፡
በዚያ አገር ፋብሪካ ውስጥ ተመርተው የሚወጡ ዕቃዎች ዋጋ እጅግ የናረ ነበር፡፡ ነገር ግን ፋንቲን ወደ አገርዋ ስትመለስ ያ ሁናቴ ተለውጦ ነው የደረሰችው:: አንድ ያልታወቀ ሰው በ1815 ዓ.ም. መጨረሻ ገደማ
መጥቶ አስደናቂ የሆነ የፈጠራ ሥራ በመሥራቱ የፋብሪካ ውጤቶች ዋጋ ዝቅ ይላል::
ሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሰውዬው ከመጠን በላይ ሀብታም
ይሆናል፡፡ ፋብሪካው ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ሰዎች ደግሞ ጥሩ ደመወዝ ስለተከፈላቸው እነሱም የተሻሻለ ኑሮ መኖር ቻሉ፡፡ ሰውዬው ማን እንደሆነና
ከየት እንደመጣ ግን ማንም አያውቅም:: ወደ ከተማው ሲመጣ ምንም ገንዘብ ይዞ እንዳልመጣ ሁሉም የሚያውቀው ፥ነው:: ግን እርሱ በወጠነው
የፈጠራ አሳብ እርሱ ብቻ ሳይሆን አገሩ ሁሉ ከበረበት:: ወደዚያ ሲመጣ አለባበሱም ሆነ አነጋገሩ የጭቁን ሰው ነበር፡፡ በታኅሣሥ ወር ለዓይን ያዝ ሲያደርግ ወደ ከተማው ሲገባ የለበሰው ልብስ የተቦጫጨቀ እግሩና እጁ
👍17❤1
በሥራ ብዛት የሻከረ ሲሆን በአንድ እጁ ምርኩዝ መሳይ ነገር ይዞ፧ በሌላ እጁ በጨርቅ የተጠቀለለ ነገር አንጠልጥሎ ነበር፡፡ በእለቱ እርሱ ወደ ከተማው ሲገባ ሰፈር ውስጥ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ስለነበር ሰውዬው በቀጥታ ወደ እሳት ቃጠሎው ይሄዳል፡፡ ልክ እርሱ ሲደርስ ሁለት ትንንሽ
ልጆች በእሳቱ ተከብበው ያያል፡፡ ክልሉ ገብቶ ይዞአቸው ይወጣል፡፡ ልጆቹ የባለሥልጣን ልጆች ነበሩ፡፡ በዚያ ግርግር የከተማው ሹሞች የመታወቂያ ወረቀት ሳይጠይቁት ከሕዝብ ጋር አብሮ ይቀላቀላል፡፡ እንኳን የመታወቂያ ወረቀት ሊጠየቅ ስለፈጸመው በጎ ተግባር ሰው ሁሉ ከብቦ ያመሰግነዋል፡፡
ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ሁሉም ሰው «አባባ ደጉ ማንደላይን» እያለ ጠራው::
ዕድሜው በግምት ሃምሳ ይሆናል:: አሳብ ስለሚያጠቃው ዘወትር ትክዝ ከማለቱ በስተቀር ስለዚህ ሰው ከዚህ ይበልጥ በአሁኑ ሰዓት ማውራት
አይቻልም፡፡ ብቻ እርሱ በፈጠረው ጥበብ ሳቢያ በብዛት ተሠርቶ ለሚወጣው የፋብሪካ ውጤት ምስጋና ይግባውና የብዙ ሰው ሕይወት ተሻሻለ፡፡ ከተማዋ
የነጋዴዎች መናኸሪያ ሆነች:: እቃው ከአገር ውጭ ወደ እስፓኝ በብዛት ተወሰደ:: የእቃው ዓይነት እንግሊዝና ጀርመን አገር ተመርተው ከሚወጡት
ተመሳሳይነት ካላቸው እቃዎች የተሻለ ሆኖ በመገኘቱ ተወዳጅነትን አተረፈ፡፡
ስለዚህ ገበያው ደራ! የሚገኘውም ጥቅም እጅግ ብዙ ስለሆነ አባባ ማንደላደን
በሁለተኛው ዓመት ሌላ መጠነኛ ፋብሪካ ከፈተ:: ፋብሪካው ውስጥ አንደኛው ክፍል ውስጥ ሴቶች ብቻ የተሰማሩበት ነበር፡፡ ከእዚያ ከተማ ስራ ያጣ ሁሉ ከእነዚህ ሁለት ፋብሪካዎች ውስጥ በደህና ደመወዝ ሥራ በቀላሉ ማግኘት ቻለ፡፡ አባባ ማንደላይን ከመምጣቱ በፊት ብዙ ሰው ሥራ
ስላልነበረው ከተማይቱ ውስጥ ብዙም እንቅስቃሴ አልነበረም:: አሁን ግን ሁሉም በየፊናው መፍጨርጨሪያ መንገድ ስለተከፈተለት ከተማው
ተንቀሳቀሰ፡፡ የኢኮኖሚ መንቀሳቀስ የተፈለገው ነገር ሁሉ የትም አስገኘ፡፡ሥራ መፍታትና ችግር ከከተማው ተወገዱ፡፡ እያንዳንዱ ነዋሪ መጠነኛ
የሆነ ገቢ ስለኣገኘ ሁለም እንደአቅሙ፣ በደረጃው ደስ ብሎት ይኖር ጀመር፡፡
ነገር ግን አባባ ማንደላይን ለሁሉም ሥራ ቢያስገኝም ሥራ ለሰጠው ሁሉ «ታማኝና እውነተኛ ሰው መሆን አለባችሁ» እያለ ያስጠነቅቅ ነበር።
ተደጋግሞ እንደተገለጸው በዚህ አጋጣሚ የአባባ ማንደላይን ሀብት ተትረፈረፈ፡፡ የሚገርመው ግን ይህ ሰው ለሀብት ይህን ያህል ደንታ አልነበረውም፡፡ ከሀብቱ ይልቅ ስለሌሎች ሰዎች ደኅንነት እጅግ ያስባል፤ ይጨነቃል፡፡ ስለራሉ ግን ብዙም ግድ አልነበረውም፡፡ በ1920 ዓ.ም. ባንኪ ውስጥ ስድስት መቶ ሰላሣ ሺህ ፍራንክ ነበረው:: በዚያው ዓመት ደግሞ
ለከተማው እድገትና ለተቸገረ ድሃ ያወጣው ገንዘብ ወደ አንድ ሚሊዮን ፍራንክ ገደማ ነበር፡፡
ከተማው ውስጥ የነበረው ሆስፒታል የተሟላ ክፍልና አልጋ
ስላልነበረው የሕሙማን ማስተኛ አሥር ተጨማሪ አልጋዎች እንዲገዙ አደረገ፡፡ ከተማው የላይኛውና የታችኛው ተብሎ ከሁለት የተከፈለ ሲሆን
እርሱ ይኖርበት የነበረው የታችኛው ከተማ ብዙ የጎደለው ነገር ነበር::አንድ ትምህርት ቤት ብቻ ነበር ያለው፡፡ እርሱም ቢሆን ሊፈርስ ምንም ያህል አልቀረው:: ስለዚህ ሁለት አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን አሠራ አንደኛው ትምህርት ቤት ለሴቶች ሌላው ለወንዶች ተመደበ፡፡ ከግሉ ወጪ
አራት አዳዲስ አስተማሪዎችን ቀጥሮ መንግሥት ከሚከፍለው የአስተማሪ ደመወዝ እጥፍ ከፈላቸው፡፡ ይህን ያየ ጎረቤቱ ስለሠራው ሥራ አድንቆ ሲናገር «ነርስና እስተማሪ እኮ ምርጥ የአገር ገንቢዎች ናቸው» አለ ይባላል።ፈረንሣይ አገር እጅግ የታወቀ ጠዋሪና ደጋፊ ለሌላቸው የሚሆን ትልቅ ቤትም እሠራ:: ፋብሪካው መሃል ከተማ ውስጥ ስለነበር በፋብሪካው ጭስ
ሰበብ የሰፈሩ ነዋሪዎች ስለተጎዱ በነፃ መድኃኒት የሚወስዱበት የመድኃኒት ቤት ከፈተላቸው::
በ1817 ዓ.ም. ይህ ሰው የሠራው በጎ ምግባር በመላ ፈረንሣይ
በመሰማቱ በዚያን ጊዜ የነበረው ንጉሥ አባባ ማንደላይንን የከተማው ከንቲባ አድርጎ ሊሾመው ነው ተብሎ ተወራ፡፡ ወሬው አሉባልታ ሆኖ አልቀረም፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የአባባ ማንደላይን መሾም በጋዜጣ ታትሞ ወጣ፡፡ አባባ ማንደላይን ግን ሹመቱን የማይበቀለው መሆኑን አስታወቀ፡፡
ወደ ከተማው በገባ በአምስተኛው ዓመት ማለት በ1820 ዓ.ም. ደጉ
ሰው ለሕዝብ ጥቅም ብሎ ያሠራው ነገር እጅግ በጣም የገነነ በመሆኑ የከተማው ነዋሪ ሁሉ እርሱ የከተማው ከንቲባ እንዲሆን ጥቆማው አስተጋባ፡፡ ንጉሡ እንደገና ሾሙት፡፡ አሁንም ሹመቱን አልቀበልም አለ፡፡ ግን የከተማው
ፖሊስ አዛዥ ‹ሹመቱን እንዲቀበል በግድ መታዘዝ አለበት» ሲል አስታወቀ፡፡ የከተማው ታላላቅ መኳንንትም ከቤቱ ድረስ ተሰብስበው መጥተው ሹመቱን
መቀበል አለብህ» አሉት:: የወዝ አደሮችም እሳብ ከዚህ የተለየ አልነበረም።ሰው ሁሉ ሹመቱን እንዲቀበል ስለወተወተው በመጨረሻ እሺ ብሉ የከተማው ሹም ሆነ፡፡
ሰው ሁሉ ሹመቱን እንዲቀበል የገፋፋው አንዲት የኑሮ ደረጃዋ
ዝቅተኛ የሆነ አሮጊት ከሰፈር ሰፈር እየዞረች በቁጣ «ጥሩ ከንቲባ ማግኘት እኮ ጥሩ ነገር ነው ! ደግ ሥራ የሚሠራ ሰው አይወድላችሁም?» እያለች
ሕዝቡን በመቀስቀስዋ ነበር፡፡ ብዙ ሕዝብ ካልበዛበት ከተማ ወሬ ስለማይደበቅ ይህች ሴት የምትለው ነገር በአጭር ጊዜ ከተማው ውስጥ ተሰራጨ፡፡ ጊዜ
እያለፈ ሲሄድ ግን ቁጥሩ አነስተኛ ቢሆንም የሚቃወም አልጠፋም፡፡
መቼም የሕይወት እውነታ ነው፤ በራሳቸው ጥረትና ችሎታ ወይም
በሌሎች ደግነት ሥልጣን ላይ የወጡ ሰዎች ተቃዋሚ አያጡም:: መሴይ ማንደላይንም ቢሆን ከዚህ ሊርቅ አይችልም:: ግን ተቃውሞው ብዙ ጊዜ
አልቆየም። እንዲያውም የሚገርመው ከተሾመ በኋላ በሕዝቡ ዘንድ ያለው አድናቆትና አክብሮት እየጨመረ ሄደ፡፡ የተጣላን ያስታርቃል፤ የታመመን
ይጠይቃል፤ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየውን ይቀብራል፡፡ ሰውም በራሱ ፈቃድ ዳኛ አደረገው:: የዓለም ሕግ ልቡ ላይ የተጻፈ ይመስል የሚሰጠው ፍርድ የተወላገደ፤ የሚሰጠው ምክር የተጣመመ አልነበረም:: የነገርን ፊት ለፊት እንጂ ወደኋላ አያውቅም፡፡ በዚህም የተነሣ ከስድስትና ሰባት ዓመት
በኋላ ስሙ በነበረበት ክፍለ ሀገር ብቻ ሳይሆን በመላ ፈረንሣይ እጅግ ገነነ።
ነገር ግን በአንድ ሰው ብቻ ተጠምዶ ይያዛል፡፡ ይህ ሰው አባባ
ማንደላይን የሚያደርገውን ሁሉ ይቃወማል:: ሁልጊዜም ይጠራጠረዋል፡፡ስሜቱ ብቻ ሳይሆን መላ ሰውነቱ ማንደላይንን አይቀበልም::ዘወትር መሴይ ማንደላይን በመንገድ ባለፈ ቁጥር ሰው ሁሉ በፍቅር ዓይን
ሲያየው ይህ ቀጠን ብሉ ከቁመቱ ዘለግ ያለና የወታደር ልብስ
የሚለብሰው ሰው በዓይነ ቁራኛ ይከተለዋል:: ከዓይኑ እስከተሰወረ ድረስ አተኩሮ ከመመልከትና መሴይ ማንደላይንን ከማጤን አይቆጠብም:: ግምባሩንም እየቋጠረ «ይሄ ሰው ማነው?» በእርግጥ ከአሁን በፊት .
አይቼዋለሁ? የት ነው የማውቀው? ሰው ሁሉ ያደንቀዋል? ይወደዋል!
እኔ ግን እጠራጠረዋለሁ» የሚል ይመስል አጠገቡ ሰው ሳይኖር ከንፈሩን ያነቃንቃል፡፡ መሴይ ማንደላይንን ባየ ቁጥር ከሃሳብ ጋር ሙግት መግጠሙን
ያስታውቅበታል፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
ልጆች በእሳቱ ተከብበው ያያል፡፡ ክልሉ ገብቶ ይዞአቸው ይወጣል፡፡ ልጆቹ የባለሥልጣን ልጆች ነበሩ፡፡ በዚያ ግርግር የከተማው ሹሞች የመታወቂያ ወረቀት ሳይጠይቁት ከሕዝብ ጋር አብሮ ይቀላቀላል፡፡ እንኳን የመታወቂያ ወረቀት ሊጠየቅ ስለፈጸመው በጎ ተግባር ሰው ሁሉ ከብቦ ያመሰግነዋል፡፡
ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ሁሉም ሰው «አባባ ደጉ ማንደላይን» እያለ ጠራው::
ዕድሜው በግምት ሃምሳ ይሆናል:: አሳብ ስለሚያጠቃው ዘወትር ትክዝ ከማለቱ በስተቀር ስለዚህ ሰው ከዚህ ይበልጥ በአሁኑ ሰዓት ማውራት
አይቻልም፡፡ ብቻ እርሱ በፈጠረው ጥበብ ሳቢያ በብዛት ተሠርቶ ለሚወጣው የፋብሪካ ውጤት ምስጋና ይግባውና የብዙ ሰው ሕይወት ተሻሻለ፡፡ ከተማዋ
የነጋዴዎች መናኸሪያ ሆነች:: እቃው ከአገር ውጭ ወደ እስፓኝ በብዛት ተወሰደ:: የእቃው ዓይነት እንግሊዝና ጀርመን አገር ተመርተው ከሚወጡት
ተመሳሳይነት ካላቸው እቃዎች የተሻለ ሆኖ በመገኘቱ ተወዳጅነትን አተረፈ፡፡
ስለዚህ ገበያው ደራ! የሚገኘውም ጥቅም እጅግ ብዙ ስለሆነ አባባ ማንደላደን
በሁለተኛው ዓመት ሌላ መጠነኛ ፋብሪካ ከፈተ:: ፋብሪካው ውስጥ አንደኛው ክፍል ውስጥ ሴቶች ብቻ የተሰማሩበት ነበር፡፡ ከእዚያ ከተማ ስራ ያጣ ሁሉ ከእነዚህ ሁለት ፋብሪካዎች ውስጥ በደህና ደመወዝ ሥራ በቀላሉ ማግኘት ቻለ፡፡ አባባ ማንደላይን ከመምጣቱ በፊት ብዙ ሰው ሥራ
ስላልነበረው ከተማይቱ ውስጥ ብዙም እንቅስቃሴ አልነበረም:: አሁን ግን ሁሉም በየፊናው መፍጨርጨሪያ መንገድ ስለተከፈተለት ከተማው
ተንቀሳቀሰ፡፡ የኢኮኖሚ መንቀሳቀስ የተፈለገው ነገር ሁሉ የትም አስገኘ፡፡ሥራ መፍታትና ችግር ከከተማው ተወገዱ፡፡ እያንዳንዱ ነዋሪ መጠነኛ
የሆነ ገቢ ስለኣገኘ ሁለም እንደአቅሙ፣ በደረጃው ደስ ብሎት ይኖር ጀመር፡፡
ነገር ግን አባባ ማንደላይን ለሁሉም ሥራ ቢያስገኝም ሥራ ለሰጠው ሁሉ «ታማኝና እውነተኛ ሰው መሆን አለባችሁ» እያለ ያስጠነቅቅ ነበር።
ተደጋግሞ እንደተገለጸው በዚህ አጋጣሚ የአባባ ማንደላይን ሀብት ተትረፈረፈ፡፡ የሚገርመው ግን ይህ ሰው ለሀብት ይህን ያህል ደንታ አልነበረውም፡፡ ከሀብቱ ይልቅ ስለሌሎች ሰዎች ደኅንነት እጅግ ያስባል፤ ይጨነቃል፡፡ ስለራሉ ግን ብዙም ግድ አልነበረውም፡፡ በ1920 ዓ.ም. ባንኪ ውስጥ ስድስት መቶ ሰላሣ ሺህ ፍራንክ ነበረው:: በዚያው ዓመት ደግሞ
ለከተማው እድገትና ለተቸገረ ድሃ ያወጣው ገንዘብ ወደ አንድ ሚሊዮን ፍራንክ ገደማ ነበር፡፡
ከተማው ውስጥ የነበረው ሆስፒታል የተሟላ ክፍልና አልጋ
ስላልነበረው የሕሙማን ማስተኛ አሥር ተጨማሪ አልጋዎች እንዲገዙ አደረገ፡፡ ከተማው የላይኛውና የታችኛው ተብሎ ከሁለት የተከፈለ ሲሆን
እርሱ ይኖርበት የነበረው የታችኛው ከተማ ብዙ የጎደለው ነገር ነበር::አንድ ትምህርት ቤት ብቻ ነበር ያለው፡፡ እርሱም ቢሆን ሊፈርስ ምንም ያህል አልቀረው:: ስለዚህ ሁለት አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን አሠራ አንደኛው ትምህርት ቤት ለሴቶች ሌላው ለወንዶች ተመደበ፡፡ ከግሉ ወጪ
አራት አዳዲስ አስተማሪዎችን ቀጥሮ መንግሥት ከሚከፍለው የአስተማሪ ደመወዝ እጥፍ ከፈላቸው፡፡ ይህን ያየ ጎረቤቱ ስለሠራው ሥራ አድንቆ ሲናገር «ነርስና እስተማሪ እኮ ምርጥ የአገር ገንቢዎች ናቸው» አለ ይባላል።ፈረንሣይ አገር እጅግ የታወቀ ጠዋሪና ደጋፊ ለሌላቸው የሚሆን ትልቅ ቤትም እሠራ:: ፋብሪካው መሃል ከተማ ውስጥ ስለነበር በፋብሪካው ጭስ
ሰበብ የሰፈሩ ነዋሪዎች ስለተጎዱ በነፃ መድኃኒት የሚወስዱበት የመድኃኒት ቤት ከፈተላቸው::
በ1817 ዓ.ም. ይህ ሰው የሠራው በጎ ምግባር በመላ ፈረንሣይ
በመሰማቱ በዚያን ጊዜ የነበረው ንጉሥ አባባ ማንደላይንን የከተማው ከንቲባ አድርጎ ሊሾመው ነው ተብሎ ተወራ፡፡ ወሬው አሉባልታ ሆኖ አልቀረም፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የአባባ ማንደላይን መሾም በጋዜጣ ታትሞ ወጣ፡፡ አባባ ማንደላይን ግን ሹመቱን የማይበቀለው መሆኑን አስታወቀ፡፡
ወደ ከተማው በገባ በአምስተኛው ዓመት ማለት በ1820 ዓ.ም. ደጉ
ሰው ለሕዝብ ጥቅም ብሎ ያሠራው ነገር እጅግ በጣም የገነነ በመሆኑ የከተማው ነዋሪ ሁሉ እርሱ የከተማው ከንቲባ እንዲሆን ጥቆማው አስተጋባ፡፡ ንጉሡ እንደገና ሾሙት፡፡ አሁንም ሹመቱን አልቀበልም አለ፡፡ ግን የከተማው
ፖሊስ አዛዥ ‹ሹመቱን እንዲቀበል በግድ መታዘዝ አለበት» ሲል አስታወቀ፡፡ የከተማው ታላላቅ መኳንንትም ከቤቱ ድረስ ተሰብስበው መጥተው ሹመቱን
መቀበል አለብህ» አሉት:: የወዝ አደሮችም እሳብ ከዚህ የተለየ አልነበረም።ሰው ሁሉ ሹመቱን እንዲቀበል ስለወተወተው በመጨረሻ እሺ ብሉ የከተማው ሹም ሆነ፡፡
ሰው ሁሉ ሹመቱን እንዲቀበል የገፋፋው አንዲት የኑሮ ደረጃዋ
ዝቅተኛ የሆነ አሮጊት ከሰፈር ሰፈር እየዞረች በቁጣ «ጥሩ ከንቲባ ማግኘት እኮ ጥሩ ነገር ነው ! ደግ ሥራ የሚሠራ ሰው አይወድላችሁም?» እያለች
ሕዝቡን በመቀስቀስዋ ነበር፡፡ ብዙ ሕዝብ ካልበዛበት ከተማ ወሬ ስለማይደበቅ ይህች ሴት የምትለው ነገር በአጭር ጊዜ ከተማው ውስጥ ተሰራጨ፡፡ ጊዜ
እያለፈ ሲሄድ ግን ቁጥሩ አነስተኛ ቢሆንም የሚቃወም አልጠፋም፡፡
መቼም የሕይወት እውነታ ነው፤ በራሳቸው ጥረትና ችሎታ ወይም
በሌሎች ደግነት ሥልጣን ላይ የወጡ ሰዎች ተቃዋሚ አያጡም:: መሴይ ማንደላይንም ቢሆን ከዚህ ሊርቅ አይችልም:: ግን ተቃውሞው ብዙ ጊዜ
አልቆየም። እንዲያውም የሚገርመው ከተሾመ በኋላ በሕዝቡ ዘንድ ያለው አድናቆትና አክብሮት እየጨመረ ሄደ፡፡ የተጣላን ያስታርቃል፤ የታመመን
ይጠይቃል፤ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየውን ይቀብራል፡፡ ሰውም በራሱ ፈቃድ ዳኛ አደረገው:: የዓለም ሕግ ልቡ ላይ የተጻፈ ይመስል የሚሰጠው ፍርድ የተወላገደ፤ የሚሰጠው ምክር የተጣመመ አልነበረም:: የነገርን ፊት ለፊት እንጂ ወደኋላ አያውቅም፡፡ በዚህም የተነሣ ከስድስትና ሰባት ዓመት
በኋላ ስሙ በነበረበት ክፍለ ሀገር ብቻ ሳይሆን በመላ ፈረንሣይ እጅግ ገነነ።
ነገር ግን በአንድ ሰው ብቻ ተጠምዶ ይያዛል፡፡ ይህ ሰው አባባ
ማንደላይን የሚያደርገውን ሁሉ ይቃወማል:: ሁልጊዜም ይጠራጠረዋል፡፡ስሜቱ ብቻ ሳይሆን መላ ሰውነቱ ማንደላይንን አይቀበልም::ዘወትር መሴይ ማንደላይን በመንገድ ባለፈ ቁጥር ሰው ሁሉ በፍቅር ዓይን
ሲያየው ይህ ቀጠን ብሉ ከቁመቱ ዘለግ ያለና የወታደር ልብስ
የሚለብሰው ሰው በዓይነ ቁራኛ ይከተለዋል:: ከዓይኑ እስከተሰወረ ድረስ አተኩሮ ከመመልከትና መሴይ ማንደላይንን ከማጤን አይቆጠብም:: ግምባሩንም እየቋጠረ «ይሄ ሰው ማነው?» በእርግጥ ከአሁን በፊት .
አይቼዋለሁ? የት ነው የማውቀው? ሰው ሁሉ ያደንቀዋል? ይወደዋል!
እኔ ግን እጠራጠረዋለሁ» የሚል ይመስል አጠገቡ ሰው ሳይኖር ከንፈሩን ያነቃንቃል፡፡ መሴይ ማንደላይንን ባየ ቁጥር ከሃሳብ ጋር ሙግት መግጠሙን
ያስታውቅበታል፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
👍25
#የኔ_ዓለሞ!
አብረሽኝ እያለሽ...
አገኝሽ ነበረ ፤ እግሬ እንደቋመጠ፤
ስትለዬኝ ግና...
አካሌ በሙሉ ፣ ክንፍ አቆጠቆጠ፤
ለምን?
መብረር እንደሳተ አክናፍ
አንቺ ሆነሽብኝ ፣ የጉዚዬ አጽናፍ
ተፈጥሮን አወቀ ፤ የተሰጠን አክናፍ። -
(እንደታወረ ወፍ)
እከንፍልሻለሁ፤
እነፍስልሻለሁ፤
የቱ ጋር ቆመሻል? ልምጣልሽ እላለሁ።
ክንፍ ክንፍንፍ
ነፋስን መሰንጠቅ ፤ በመሄድ መደምደም፤
ቀሪ መንገድ ሕልሜን ፣ካንቺ ለመካደም።
አላውቀውምና፣
አይገባኝምና ፣ያንቺ መዳረሻስ፣
እኔ ልብ የለኝም
አጠገብሽ ቆሜሞ ፣ አጠገብሽ ልሆን
እነሳለሁ ጭራሽ።
(ለየልኝ ማለት ነው።)
ማለትም...
ማለት የምችለው...
የክንፋም ልብ ወዳጅ ፣ ነፋስን ማርገብገብ፤
በነፋስ መንገብገብ፤
ነፋስን መጠርጠር፤ ነፋስን መመገብ፤
ከንፋስ መጓተት ፤ ከነፋስ መሳሳብ፤
እሷ ነች አያሉ፣ ከነፋስ መሣሣም፤
እነፍስልሻለሁ!
ባየር ፣በብርሃን ፣በጨለማ መብረር፤
አንቺ ጋር እንደቆምኩ ፣ ክንፊን አጥፍ ጀመር።
ደረስኩኝ ማለት ነው!
ማለትም
የክንፋሞ ቀልብ ጦስ ፣ መርግፊያ ሞኝነት፣
መሄጃ ሰበብ ጋር ፣ በቶሎ መገኘት።
ዓለሜ...
መጓዝ ዳራ ኖሮት ፣ካስረገፈ ላባ፣
ማማር መርገም ሆኖ ፣ካስነቀለ አበባ፣
መድረስ ከመገኘት ፣ ከእቅፍሽ ቢያሞቀኝ፣
መፈለግ ደስታዬ ፣ ሳገኝሽ ራቀኝ።
መሄዴን ብውደው...
በቆይልኝ ብዬ ፣ ክንፊ መቼ ደክሞት፣
እጸልይ ጀመረ
ስቀርብሽ ሂጂልኝ ፣ ሳገኝሽ እንዳልሞት።
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
አብረሽኝ እያለሽ...
አገኝሽ ነበረ ፤ እግሬ እንደቋመጠ፤
ስትለዬኝ ግና...
አካሌ በሙሉ ፣ ክንፍ አቆጠቆጠ፤
ለምን?
መብረር እንደሳተ አክናፍ
አንቺ ሆነሽብኝ ፣ የጉዚዬ አጽናፍ
ተፈጥሮን አወቀ ፤ የተሰጠን አክናፍ። -
(እንደታወረ ወፍ)
እከንፍልሻለሁ፤
እነፍስልሻለሁ፤
የቱ ጋር ቆመሻል? ልምጣልሽ እላለሁ።
ክንፍ ክንፍንፍ
ነፋስን መሰንጠቅ ፤ በመሄድ መደምደም፤
ቀሪ መንገድ ሕልሜን ፣ካንቺ ለመካደም።
አላውቀውምና፣
አይገባኝምና ፣ያንቺ መዳረሻስ፣
እኔ ልብ የለኝም
አጠገብሽ ቆሜሞ ፣ አጠገብሽ ልሆን
እነሳለሁ ጭራሽ።
(ለየልኝ ማለት ነው።)
ማለትም...
ማለት የምችለው...
የክንፋም ልብ ወዳጅ ፣ ነፋስን ማርገብገብ፤
በነፋስ መንገብገብ፤
ነፋስን መጠርጠር፤ ነፋስን መመገብ፤
ከንፋስ መጓተት ፤ ከነፋስ መሳሳብ፤
እሷ ነች አያሉ፣ ከነፋስ መሣሣም፤
እነፍስልሻለሁ!
ባየር ፣በብርሃን ፣በጨለማ መብረር፤
አንቺ ጋር እንደቆምኩ ፣ ክንፊን አጥፍ ጀመር።
ደረስኩኝ ማለት ነው!
ማለትም
የክንፋሞ ቀልብ ጦስ ፣ መርግፊያ ሞኝነት፣
መሄጃ ሰበብ ጋር ፣ በቶሎ መገኘት።
ዓለሜ...
መጓዝ ዳራ ኖሮት ፣ካስረገፈ ላባ፣
ማማር መርገም ሆኖ ፣ካስነቀለ አበባ፣
መድረስ ከመገኘት ፣ ከእቅፍሽ ቢያሞቀኝ፣
መፈለግ ደስታዬ ፣ ሳገኝሽ ራቀኝ።
መሄዴን ብውደው...
በቆይልኝ ብዬ ፣ ክንፊ መቼ ደክሞት፣
እጸልይ ጀመረ
ስቀርብሽ ሂጂልኝ ፣ ሳገኝሽ እንዳልሞት።
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍13👏4
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መሴይ ማንደላይንን ባየ ቁጥር ከሃሳብ ጋር ሙግት መግጠሙን
ያስታውቅበታል፡፡.
ሰውዬው ኮስተርተር የሚል ዓይነት ስለነበር እንኳን በዓይነቁራኛ
ተከትሎ ለአንድ አፍታ ቢያይም «ይሄ ሰውዬ ከኔ ነገር አለው?» የሚያሰኝ ዓይነት ፊትና አመለካከት ያለው፧ ሳይወዱ በግድ ጭንቀትን ከልብ ውስጥ በማሳደር የሕሊና መረበሽን አንጎል ውስጥ የሚፈጥር ዓይነት ሰው ነበር::
ስሙ ዣቬር ይባላል፡፡ ፖሊስ ነው:: ተራ ፖሊስ ሳይሆን የከተማው
ፖሊስ አዛዥ ነው:: መሴይ ማንደላይን ወደ ከተማው ሲመጣ ከዚያ አልነበረም::
አንዳንድ የፖሊስ መኮንኖች የተለየ መልክ አላቸው:: አንዳንዴ
ደማቸው ውስጥ ከእልቅናቸው ጋር የተቆራኘ ክፋት ለመኖሩ ገጽታቸው ላይ ይታያል፡፡ ዣቬር የዚህ ዓይነት ገጽታ ቢኖረውም በውስጡ ግን ክፋት የተቀበረበት ዓይነት ሰው ነበር ለማለት አያስደፍርም:: እስር ቤት ነው
የተወለደው:: እናቱ ደግሞ ጠንቋይ ነበሩ፡፡ አባቱ የወህኒ ቤት ሠራተኛ ስለነበሩ ሁልጊዜም ሕብረተሰቡ የእነርሱን ቤተሰብ ከማኅበራዊ ኑሮ ያገለላ
ይመስላቸው ስለነበር ዣቬር ቀቢጸ ተስፋ ያዉቃዋል፡፡ የሰውን ልጅ ከሁለት ከፍሎ ነው የማያየው:: አንደኛው ወገን ሕብረተሰብን የሚያጠቃ ሲሆን
ሌላው ወገን ከዚህ ጥቃት የሚከላከልለት ክፍል ነው:: ዣቬር በሥነ ሥርዓትና በቅንነት በጣም ያምናል:: ጎሳውን ግን ይጠላል፡፡ ፖሊስ ለመሆን ፈልጎ ነው የፖሊስ ኃይል አባል የሆነው:: በሥራው ምስጉን ፖሊስ መሆን
ስለተረጋገጠ በአርባ ዓመቱ ከፍተኛ የማዕረግ እድገት አግኝቶ የክፍል አዛዥ ሆነ፡፡ በወጣትነት ዘመኑ ደቡብ ክፍለ ሀገራት ውስጥ ከሚገኝ ወህኒ
ቤት እንዲሠራ ይመደባል፡፡
አፍንጫው እንደ ቀትር እባብ ቀጥ ያለ ሲሆን ሪዘን ከግራና ከቀኝ
በጣም ኣሳድጎት ጉንጮቹን ሸፍኖበታል:: ዣቬር ድንገት የሳቀ እንደሆነ ስስ ከንፈሮቹ ተገልጠው ጥርሶቹን ብቻ ሳይሆን የሚያሳዩት ድዶቹንም ጭምር ነው:: ግን ብዙ ጊዜ መኮሳተርን እንጂ ሳቅ አያውቅም:: ከአፍንጫው ግራና
ቀኝ የተሸበሸበ ሥጋ ኣለው:: ይህም ሲቆጣ የአደን ውሻን፣ ሲስቅ ደግሞ ነብርን ያስመስለዋል፡፡ ከዚህ በተረፈ ጭንቅላቱ፡ ትንሽ፣ አገጩ ሰፊ፧ ፀጉሩን ወደፊት እያበጠረው ግምባሩ እስከ ቅንድቡ በፀጉር የተሸፈነ፤ ጨገጎ ፊት ያለው ፤ ፊቱ፡ የሚ.ያርበደብድና የኮስታራ አለቃ ሰውነት ያለው ሰው ነው።
ይህ ሰው በሁለት ዓይነት አመለካከቶች የተወጠረ ነበር፡፡ በመሠረቱ፡ሀሳቦቹ ምንም ዓይነት ስህተት የሌለባቸው ቀላል አመለካከቶች ሲሆን ዣቬር ግን በጣም ስላጋነናቸው እንደ ከባድ ነገር ነበር የሚያያቸው::
እነርሱም ባለሥልጣንን ማክበርና ሕግ የሚፃረሩትን መጥላት ናቸው:: በእርሱ አመለካከት ሌብነት፣ ግድያና ማንኛውም ወንጀል መፈጸም ማለት
ሕግን መፃረር ማለት ነው:: በማንኛውም የሥራ መስክ የተሰማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ማለት ከአገር መሪ ጀምሮ እስከ ተራ ወታደርና ተላላኪ. ድረስ የእርሱን እምነት መቀበል እንዳለባቸው ያምናል፡፡ በእርሱ
አመለካከት ሕግ የሚጥሱትን ሁሉ ተከታትሎ ማጥፋትና ማስወገድ ተገቢ እርምጃ ነው:: ሕግ የሚጥሱትን ከመጠን በላይ ያጠላል:: ማንንም ሳይለይ
ሕግን ማስከበር ለእርሱ ትልቅ ቁም ነገር ነው::
«በአንድ በኩል» ይላል ዣቬር፤ የመንግሥት ባለሥልጣንን ማታለል አይቻልም፧ ሕግ አስከባሪ ዳኛ ደግሞ ፈጽሞ አይሳሳትም:: በሌላ በኩል ደግሞ» ይላል፤ «መዳኛ ከሌለው አዘቅት ውስጥ ከተዘፈቁ ክፉ ሰዎች በጎ
ተግባር አይጠበቅም፡፡»
«ሰው የሠራው ሕግ መጣስ የለበትም» ብለው የሚያምኑ የአንዳንድ ወግ አጥባቂዎችን እምነት ይከተላል፡፡ ከተጠራጠረ እንደ ጦር የሚወጋውን ዓይነት ሰው ላይ እንዲተክል የማገፋፋው ይህ እምነቱ ነበር፡፡ ይህም
በመሆነ «ነቅቶ መጠበቅ› በሚል ፍልስፍና ሕይወቱን ያንፃል። በዚህም የተነሳ ሕሊናው ሕግን በማስከበር፧ እምነቱ የእለት ተግባሩን በመከታተል ላይ ያተኮረ ሲሆን ቄሶች ለቅዳሴ እንደሚራሯጡ ሁሉ እሱም ለስለላ ተግባር ይሯሯጣል፡፡
ይብላኝለት እርሱ መዳፍ ውስጥ ለሚወድቅ፡፡ አባቱ፡ ከእስር ቤት
ሲያመልጥ ቢያየው ሮጦ ሄዶ ያሲዘዋል:: እናቱ አንድ ጊዜ ቲኬት
ስታጭበረብር ስላገኛት አሳልፎ ሰጥቶአታል፡፡ ዣቬር ተመሳሳይ የሆነ ሥራ በሚሠራበት ጊዜ ትክክለኛ ነገር እንደፈጸመ ሰው መንፈሱ ይረካል::ሕይወቱ በብቸኝነትና በግላዊነት የተሞላ ሲሆን ከዓለማዊ ምቾት የራቀ
ነበር፡፡ የእርሱ ደስታ ወንጀለኞችን ተከታትሎ ማደን እንጂ ዳንኪራ መርገጥ ወይም መዚቃ ማዳመጥ አልነበረም::
ዣቬር ማለት ይህ ሲሆን አሁንም ዓይኑን ከመሴይ ማንደላይን
አላነሳም፤ በጣም ይጠራጠረዋል፡ግን የተጨበጠ ማስረጃ ሊያገኝ አልቻለም::በመጨረሻ በክፉ ዓይን እንደሚያየው መሴይ ማንደላይን ደረሰበት:: ሆኖም ከምንም አልቆጠረውም:: ዣቬር ማን እንደሆነ ለማወቅ ፈልጎ ጥያቄ
አልጠየቀውም:: ለማንኛውም ብዙም አላቀረበውም፤ ብዙም አልሸሸውም፡፡በየጊዜው ሲያፈጥበት እያየ እንዳላየ ሆኖ ያልፈዋል፡፡ ሌሎችን በሚያይበትና
ማንደላይን ሁናቴ ዣቬርን በይበልጥ ግራ አጋባው፡፡ ሆኖም አንድ ቀን የዣቬር ሁኔታ መሴይ ማንደላይንን ያስቆጣዋል:: ነገሩ እንዲህ ነበር፡፡
አንድ ቀን መሴይ ማንደላይን ከአንዲት መንደር ውስጥ ከወዲያ
ወዲህ እያለ ይንሸራሸራል፡፡ ጩኸት ሰምቶ ዞር ሲል ሰዎች ተሰብስበው ያያል፡፡ ወደ ሥፍራው ቢሄድ ደብተራ ፎሽለማ የተባሉ ሽማግሌ ወድቀው እቃ የጫነ ጋሪ ተጭኖአቸዋል፡፡ ፈረሱም ወድቆ እግሩ ስለተሰበረ መነቃነቅ
እንዳቃተው ሁሉ ሽማግሌውም ጋሪው ተጭኖአቸው ሊነቃነቁ አልቻሉም። ጋሪው ላይ መጠነኛ ጭነት ስለነበረ ሽማግሌው የጣር ያህል ነበር የተጨነቁት:: ሰዎች ተሰብስበው ጭነቱን ብድግ አድርገው ሊያላቅቋቸው
ቢሞክሩም አልሆነላቸውም:: ዋጋ የሌለው ሙከራ የአንዳንዱ አያያዝ
የአላዋቂ ሲሆን የአንዳንዱም አያያዝ ለማስመሰል ያህል ብቻ ነበር፡፡ ሽማግሌው ትንፋሽ አጥሯቸው ሊሞቱ ሆነ፡፡ መፍትሔው ከሥር ገብቶ ጋሪውን ብድ ማድረግ ነበር፡፡ ከጋሪው ላይ ወጥቶ የተጫነውን ጭነት ለማራገፍ ከሞከሩ የባሰውን ሊጫንዋቸው ሆነ፡፡ ከሥሩ ገብቶ በሸክም ብድግ ለማድረግ ለራስ
የሚያስፈራ ሆነ፡፡ ስለዚህ ሁሉም ተፋጠጡ፡፡ ዣቬር አደጋው እንደደረሰ መጥቶ ስለነበር የእቃ ማንሻ መሣሪያ እንዲመጣ ሰው ልኮአል::
መሴይ ማንደላይን ከሥፍራው ደረሰ፡፡ ሕዝቡ መንገድ ለቀቀለት
«እርዱኝ እባካችሁ» ብለው ሽማግሌው ጮኹ፡፡ «የማነው ሳምራዊ ይህን ሽማግሌ የሚያድን?» ሲል መሌይ ማንደላይን ጠየቀ፡፡
መሴይ ማንደላይን ዞር ዞር እያለ ተመለከተ፡፡
«የእቃ ማንሻ መሣሪያ ያለው የለም?»
«ሰዎች ሊያመጡ ሄደዋል» አለ አንድ ሰው::
«ቶሉ ይደርሳሉ?»
«ፍሉቮ ከተባለ ሥፍራ ወደሚገኝ አንጥረኛ ነው የሄዱት፡፡ መቼስ
ቢያንስ አንድ ሩብ ሰዓት ያህል ያቆያቸዋል፡፡›
«ሩብ ሰዓት!» ሲል ጮኸ፡፡
ሌሊቱን ሲዘንብ ስላደረ ኣካባቢው ጨቅይቶ ነበር፡፡ ፈረሰ ተንሸራትቶ
የወደቀበትም ሥፍራ እንደማጥ ዓይነት ስለነበር የጋሪው እግሮች በአንድ በኩል ከጭቃው ውስጥ እየዘለቁ ወደ ውስጥ ሰመጡ:: በዚህ ዓይነት በአምስት ደቂቃ ጊዜ ውስጥ የሽማግሌው ወገብ ሊቀነጠስ ሆነ፡፡
«ሩብ ሰዓት መቆየት አንችልም» አላቸው መሴይ ማንደላይን እዚያ
የተሰበሰቡትን ሁሉ እያየ::
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መሴይ ማንደላይንን ባየ ቁጥር ከሃሳብ ጋር ሙግት መግጠሙን
ያስታውቅበታል፡፡.
ሰውዬው ኮስተርተር የሚል ዓይነት ስለነበር እንኳን በዓይነቁራኛ
ተከትሎ ለአንድ አፍታ ቢያይም «ይሄ ሰውዬ ከኔ ነገር አለው?» የሚያሰኝ ዓይነት ፊትና አመለካከት ያለው፧ ሳይወዱ በግድ ጭንቀትን ከልብ ውስጥ በማሳደር የሕሊና መረበሽን አንጎል ውስጥ የሚፈጥር ዓይነት ሰው ነበር::
ስሙ ዣቬር ይባላል፡፡ ፖሊስ ነው:: ተራ ፖሊስ ሳይሆን የከተማው
ፖሊስ አዛዥ ነው:: መሴይ ማንደላይን ወደ ከተማው ሲመጣ ከዚያ አልነበረም::
አንዳንድ የፖሊስ መኮንኖች የተለየ መልክ አላቸው:: አንዳንዴ
ደማቸው ውስጥ ከእልቅናቸው ጋር የተቆራኘ ክፋት ለመኖሩ ገጽታቸው ላይ ይታያል፡፡ ዣቬር የዚህ ዓይነት ገጽታ ቢኖረውም በውስጡ ግን ክፋት የተቀበረበት ዓይነት ሰው ነበር ለማለት አያስደፍርም:: እስር ቤት ነው
የተወለደው:: እናቱ ደግሞ ጠንቋይ ነበሩ፡፡ አባቱ የወህኒ ቤት ሠራተኛ ስለነበሩ ሁልጊዜም ሕብረተሰቡ የእነርሱን ቤተሰብ ከማኅበራዊ ኑሮ ያገለላ
ይመስላቸው ስለነበር ዣቬር ቀቢጸ ተስፋ ያዉቃዋል፡፡ የሰውን ልጅ ከሁለት ከፍሎ ነው የማያየው:: አንደኛው ወገን ሕብረተሰብን የሚያጠቃ ሲሆን
ሌላው ወገን ከዚህ ጥቃት የሚከላከልለት ክፍል ነው:: ዣቬር በሥነ ሥርዓትና በቅንነት በጣም ያምናል:: ጎሳውን ግን ይጠላል፡፡ ፖሊስ ለመሆን ፈልጎ ነው የፖሊስ ኃይል አባል የሆነው:: በሥራው ምስጉን ፖሊስ መሆን
ስለተረጋገጠ በአርባ ዓመቱ ከፍተኛ የማዕረግ እድገት አግኝቶ የክፍል አዛዥ ሆነ፡፡ በወጣትነት ዘመኑ ደቡብ ክፍለ ሀገራት ውስጥ ከሚገኝ ወህኒ
ቤት እንዲሠራ ይመደባል፡፡
አፍንጫው እንደ ቀትር እባብ ቀጥ ያለ ሲሆን ሪዘን ከግራና ከቀኝ
በጣም ኣሳድጎት ጉንጮቹን ሸፍኖበታል:: ዣቬር ድንገት የሳቀ እንደሆነ ስስ ከንፈሮቹ ተገልጠው ጥርሶቹን ብቻ ሳይሆን የሚያሳዩት ድዶቹንም ጭምር ነው:: ግን ብዙ ጊዜ መኮሳተርን እንጂ ሳቅ አያውቅም:: ከአፍንጫው ግራና
ቀኝ የተሸበሸበ ሥጋ ኣለው:: ይህም ሲቆጣ የአደን ውሻን፣ ሲስቅ ደግሞ ነብርን ያስመስለዋል፡፡ ከዚህ በተረፈ ጭንቅላቱ፡ ትንሽ፣ አገጩ ሰፊ፧ ፀጉሩን ወደፊት እያበጠረው ግምባሩ እስከ ቅንድቡ በፀጉር የተሸፈነ፤ ጨገጎ ፊት ያለው ፤ ፊቱ፡ የሚ.ያርበደብድና የኮስታራ አለቃ ሰውነት ያለው ሰው ነው።
ይህ ሰው በሁለት ዓይነት አመለካከቶች የተወጠረ ነበር፡፡ በመሠረቱ፡ሀሳቦቹ ምንም ዓይነት ስህተት የሌለባቸው ቀላል አመለካከቶች ሲሆን ዣቬር ግን በጣም ስላጋነናቸው እንደ ከባድ ነገር ነበር የሚያያቸው::
እነርሱም ባለሥልጣንን ማክበርና ሕግ የሚፃረሩትን መጥላት ናቸው:: በእርሱ አመለካከት ሌብነት፣ ግድያና ማንኛውም ወንጀል መፈጸም ማለት
ሕግን መፃረር ማለት ነው:: በማንኛውም የሥራ መስክ የተሰማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ማለት ከአገር መሪ ጀምሮ እስከ ተራ ወታደርና ተላላኪ. ድረስ የእርሱን እምነት መቀበል እንዳለባቸው ያምናል፡፡ በእርሱ
አመለካከት ሕግ የሚጥሱትን ሁሉ ተከታትሎ ማጥፋትና ማስወገድ ተገቢ እርምጃ ነው:: ሕግ የሚጥሱትን ከመጠን በላይ ያጠላል:: ማንንም ሳይለይ
ሕግን ማስከበር ለእርሱ ትልቅ ቁም ነገር ነው::
«በአንድ በኩል» ይላል ዣቬር፤ የመንግሥት ባለሥልጣንን ማታለል አይቻልም፧ ሕግ አስከባሪ ዳኛ ደግሞ ፈጽሞ አይሳሳትም:: በሌላ በኩል ደግሞ» ይላል፤ «መዳኛ ከሌለው አዘቅት ውስጥ ከተዘፈቁ ክፉ ሰዎች በጎ
ተግባር አይጠበቅም፡፡»
«ሰው የሠራው ሕግ መጣስ የለበትም» ብለው የሚያምኑ የአንዳንድ ወግ አጥባቂዎችን እምነት ይከተላል፡፡ ከተጠራጠረ እንደ ጦር የሚወጋውን ዓይነት ሰው ላይ እንዲተክል የማገፋፋው ይህ እምነቱ ነበር፡፡ ይህም
በመሆነ «ነቅቶ መጠበቅ› በሚል ፍልስፍና ሕይወቱን ያንፃል። በዚህም የተነሳ ሕሊናው ሕግን በማስከበር፧ እምነቱ የእለት ተግባሩን በመከታተል ላይ ያተኮረ ሲሆን ቄሶች ለቅዳሴ እንደሚራሯጡ ሁሉ እሱም ለስለላ ተግባር ይሯሯጣል፡፡
ይብላኝለት እርሱ መዳፍ ውስጥ ለሚወድቅ፡፡ አባቱ፡ ከእስር ቤት
ሲያመልጥ ቢያየው ሮጦ ሄዶ ያሲዘዋል:: እናቱ አንድ ጊዜ ቲኬት
ስታጭበረብር ስላገኛት አሳልፎ ሰጥቶአታል፡፡ ዣቬር ተመሳሳይ የሆነ ሥራ በሚሠራበት ጊዜ ትክክለኛ ነገር እንደፈጸመ ሰው መንፈሱ ይረካል::ሕይወቱ በብቸኝነትና በግላዊነት የተሞላ ሲሆን ከዓለማዊ ምቾት የራቀ
ነበር፡፡ የእርሱ ደስታ ወንጀለኞችን ተከታትሎ ማደን እንጂ ዳንኪራ መርገጥ ወይም መዚቃ ማዳመጥ አልነበረም::
ዣቬር ማለት ይህ ሲሆን አሁንም ዓይኑን ከመሴይ ማንደላይን
አላነሳም፤ በጣም ይጠራጠረዋል፡ግን የተጨበጠ ማስረጃ ሊያገኝ አልቻለም::በመጨረሻ በክፉ ዓይን እንደሚያየው መሴይ ማንደላይን ደረሰበት:: ሆኖም ከምንም አልቆጠረውም:: ዣቬር ማን እንደሆነ ለማወቅ ፈልጎ ጥያቄ
አልጠየቀውም:: ለማንኛውም ብዙም አላቀረበውም፤ ብዙም አልሸሸውም፡፡በየጊዜው ሲያፈጥበት እያየ እንዳላየ ሆኖ ያልፈዋል፡፡ ሌሎችን በሚያይበትና
ማንደላይን ሁናቴ ዣቬርን በይበልጥ ግራ አጋባው፡፡ ሆኖም አንድ ቀን የዣቬር ሁኔታ መሴይ ማንደላይንን ያስቆጣዋል:: ነገሩ እንዲህ ነበር፡፡
አንድ ቀን መሴይ ማንደላይን ከአንዲት መንደር ውስጥ ከወዲያ
ወዲህ እያለ ይንሸራሸራል፡፡ ጩኸት ሰምቶ ዞር ሲል ሰዎች ተሰብስበው ያያል፡፡ ወደ ሥፍራው ቢሄድ ደብተራ ፎሽለማ የተባሉ ሽማግሌ ወድቀው እቃ የጫነ ጋሪ ተጭኖአቸዋል፡፡ ፈረሱም ወድቆ እግሩ ስለተሰበረ መነቃነቅ
እንዳቃተው ሁሉ ሽማግሌውም ጋሪው ተጭኖአቸው ሊነቃነቁ አልቻሉም። ጋሪው ላይ መጠነኛ ጭነት ስለነበረ ሽማግሌው የጣር ያህል ነበር የተጨነቁት:: ሰዎች ተሰብስበው ጭነቱን ብድግ አድርገው ሊያላቅቋቸው
ቢሞክሩም አልሆነላቸውም:: ዋጋ የሌለው ሙከራ የአንዳንዱ አያያዝ
የአላዋቂ ሲሆን የአንዳንዱም አያያዝ ለማስመሰል ያህል ብቻ ነበር፡፡ ሽማግሌው ትንፋሽ አጥሯቸው ሊሞቱ ሆነ፡፡ መፍትሔው ከሥር ገብቶ ጋሪውን ብድ ማድረግ ነበር፡፡ ከጋሪው ላይ ወጥቶ የተጫነውን ጭነት ለማራገፍ ከሞከሩ የባሰውን ሊጫንዋቸው ሆነ፡፡ ከሥሩ ገብቶ በሸክም ብድግ ለማድረግ ለራስ
የሚያስፈራ ሆነ፡፡ ስለዚህ ሁሉም ተፋጠጡ፡፡ ዣቬር አደጋው እንደደረሰ መጥቶ ስለነበር የእቃ ማንሻ መሣሪያ እንዲመጣ ሰው ልኮአል::
መሴይ ማንደላይን ከሥፍራው ደረሰ፡፡ ሕዝቡ መንገድ ለቀቀለት
«እርዱኝ እባካችሁ» ብለው ሽማግሌው ጮኹ፡፡ «የማነው ሳምራዊ ይህን ሽማግሌ የሚያድን?» ሲል መሌይ ማንደላይን ጠየቀ፡፡
መሴይ ማንደላይን ዞር ዞር እያለ ተመለከተ፡፡
«የእቃ ማንሻ መሣሪያ ያለው የለም?»
«ሰዎች ሊያመጡ ሄደዋል» አለ አንድ ሰው::
«ቶሉ ይደርሳሉ?»
«ፍሉቮ ከተባለ ሥፍራ ወደሚገኝ አንጥረኛ ነው የሄዱት፡፡ መቼስ
ቢያንስ አንድ ሩብ ሰዓት ያህል ያቆያቸዋል፡፡›
«ሩብ ሰዓት!» ሲል ጮኸ፡፡
ሌሊቱን ሲዘንብ ስላደረ ኣካባቢው ጨቅይቶ ነበር፡፡ ፈረሰ ተንሸራትቶ
የወደቀበትም ሥፍራ እንደማጥ ዓይነት ስለነበር የጋሪው እግሮች በአንድ በኩል ከጭቃው ውስጥ እየዘለቁ ወደ ውስጥ ሰመጡ:: በዚህ ዓይነት በአምስት ደቂቃ ጊዜ ውስጥ የሽማግሌው ወገብ ሊቀነጠስ ሆነ፡፡
«ሩብ ሰዓት መቆየት አንችልም» አላቸው መሴይ ማንደላይን እዚያ
የተሰበሰቡትን ሁሉ እያየ::
👍23😁3
«ሌላ ምርጫ የለም::»
«ከሩብ ሰዓት በኋላማ ዋጋ የለውም:: ጋሪው እየሰመጠ መሆኑን አይታያችሁም እንዴ!»
«ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡»
«ስሙ» አለ መሴይ ማንደላይን፤ «አሁኑኑ ከሆነ ከእቃ መጫኛው
ሥር ራስን ለማስገባት የሚያስችል ቦታ አለ፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ግን ይህ አይቻልም::» ስለዚህ አሁን ጥቂት ሰዎች ተንፏቅቀው ገብተው በጀርባቸው ጋሪውን ብድግ ማድረግ አለባቸው:: ይህ ከሆነ ሰውዬው
በግማሽ ደቂቃ ውስጥ ይወጣሉ፡፡ ማነው እስቲ ጎበዝ ሰውዬውን የሚያድን? መቶ ፍራንክ ይከፈለዋል፡፡»
ሁሉም ዝም!
«ሁለት መቶ ፍራንክ» አለ መሴይ ማንደላይን፡፡
የተሰበሰበው ሰው መሬት መሬት ያይ ጀመር፡፡
«ከእዚያ ውስጥ ደፍሮ የሚገባ ሰው በጣም ጡንቸኛ መሆን አለበት፡፡
ግን እኮ ያ ሰው ከዚያ በኋላ እንዴት ይወጣል፣ እዚያው ተጨፍልቆ ይቀራል እንጂ» አለ አንድ ሰው በመካከሉ፡፡
«በሉ እባካችሁ! አራት መቶ ፍራንክ»
«አሁንም ዝም»
«ፈቃደኛነቱ እኮ አይደለም የጠፋው» አሉ አንድ ሰው::
መሴይ ማንደላይን ዞር ብሉ ሲያይ ዣቬርን አየው:: ከዚያ ለመኖሩ
አልተገነዘበም ነበር፡፡ ዣቬር ቀጠለ፡፡
«ኃይል ነው የሚያስፈልገው:: ከዚያ ውስጥ የሚገባ ሰው ደፋርና
እጅግ በጣም ጉልበተኛ መሆን ይኖርበታል:: ይህን የሚያህል የእቃ መጫኛ ጋሪ በጀርባው ተሸክሞ ለማንሳት የሚችል ምን ዓይነት ጉልበተኛ ነው?»
ከዚያ በኋላ ዣቬር መሴይ ማንደላይንን እንደልማዱ አፍጥጦ እያየው እያንዳንዱን ቃል ረገጥ አድርጎ የሚከተለውን ተናገረ::
«መሴይ ማንደላይን፣ አሁን እርስዎ የሚጠይቁትን ሥራ ለመፈጸም የሚችል አንድ ሰው ብቻ ነበር የማውቀው::
ማንደላይን ደነገጠ፡፡
ዣቬር ዓይኑን ከመሴይ ማንደላይን ሳያነሳ የአነጋገሩን ዘይቤ ለውጥ አድርጎ ቀጠለ፡፡
«ይህ ሰው ወንጀለኛ ነበር፡፡»
«እሱን ተወው እባክህ» እለ መሴይ ማንደላይን፡፡
«ቱለን ከተባለ ሥፍራ ታስሮ ነበር፡፡»
የማንደላይን ፊት አመድ መሰለ፡፡
«ወይኔ ተጨፈለቅሁ!» ሲሉ ሽማግሌው ጮኹ::
መሴይ ማንደላይን ቀና ብሎ ተመለከተ፡፡ ዣቬር አሁንም
እንዳፈጠጠበት መሆኑን ተገነዘበ፡፡ የተሰበሰበውን ሰው ቃኘ፡፡ የሃዘኔታ ፈገግታ እያሳየ:: ከዚያም ቃል ሳይተነፍስ በጉልበቱ ተንበረከከ፡፡ ወዲያው ከጋሪው እቃ መጫኛ ስር ከመቅጽበት ገባ፡፡
ሁሉም ተጨነቀ፡፡ ሰው ሁሉ ወሬ ለማየት ተርመሰመሰ፡፡ ለመቀመጥ ይችል እንደሆነ ከአንዴም ሁለቴ ሞከረ፡፡
«መሴይ ማንደላይን ከዚያ በቶሎ ብትወጣ ይሻላል» ሲል ሕዝቡ
ጮኸ፡፡ ሽማግሌውም ይህንኑ አሉ፡፡ «መሴይ ማንደላይን ከዚያ ቶሎ ብለህ ውጣ፡፡ እኔ ልሙት እንጂ አንተ ምን በወጣህ! ካልወጣህ አንተም
ትጨፈልቃለህ::»
ማንደላይን መልስ አልሰጠም፡፡ የተሰበሰበው ሕዝብ እንደገና ዝም
አለ፡፡ ጋሪው ሲነካካ ጊዜ የባሰውኑ ወደ ውስጥ ይሰምጥ ጀመር፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው መሴይ ማንደላይን ራሱን ማላቀቅ ተሳነው::ሰው ተጨነቀ፤ ግን ጭቃው ውስጥ ሰምጦ የነበረው እግር መነቃነቅ ጀምሮ ቀስ እያለ ወደላይ መጣ፡፡ «ከግራ ቀኝ ያዘ እንጂ» ሲል ማንደላይን
ጮኸ፡፡ በአለው ኃይል ለማንሳት ሞከረ፡፡ ሁሉም ለመያዝ የሚችለውን ያህል ያዘ፡፡ የአንድ ሰው ድፍረት ሁሉንም ሰው አነቃንቆ ጉልበት ሰጣቸው::
ሃያ ሰው ያህል ጋሪውን አነሳው፡፡ ሽማግሌው ከሞት ዳነ፡፡
መሴይ ማንደላይን ተነሳ፡፡ ፊቱ፡ በአንድ ጊዜ የገረጣ መሰለ፧ በኃይል አልቦት ነበር፡፡ ልብሱ በጭቃ ከመለወሱም በላይ አንዳንድ ቦታ ላይ ተቀድዷል:: ሰው ሁሉ አለቀሰ፡፡ ሽማግሌው የማንደላይንን ጉልበት ሳመ::
«ደጉ አምላክ» ሲሉ ጠሩት፡፡ ራሱም ቢሆን በጣም ደስ አለ:: በእርካታ ዓይን ዣቬርን አየው::: ዣቬር ግን አሁንም በዓይነ ቁራኛ ይጠብቀዋል።
ደብተራ ፎሽለማ መላላጥ እንጂ ስብራት ስላልደረሰባቸወ ቶሎ ዳኑ፡፡
ግን ጉልበታቸሁ አልነቃነቅ ብሎ አስቸገራቸው:: መሴይ ማንደላይን ከሲሮች ጋር ተነጋግሮ ሽማግሌው ፓሪስ ከተማ አጠገብ ከሚገኝ ገዳም በአትክልተኝነት እንዲሠሩ አስቀጠራቸው::
💫ይቀጥላል💫
«ከሩብ ሰዓት በኋላማ ዋጋ የለውም:: ጋሪው እየሰመጠ መሆኑን አይታያችሁም እንዴ!»
«ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡»
«ስሙ» አለ መሴይ ማንደላይን፤ «አሁኑኑ ከሆነ ከእቃ መጫኛው
ሥር ራስን ለማስገባት የሚያስችል ቦታ አለ፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ግን ይህ አይቻልም::» ስለዚህ አሁን ጥቂት ሰዎች ተንፏቅቀው ገብተው በጀርባቸው ጋሪውን ብድግ ማድረግ አለባቸው:: ይህ ከሆነ ሰውዬው
በግማሽ ደቂቃ ውስጥ ይወጣሉ፡፡ ማነው እስቲ ጎበዝ ሰውዬውን የሚያድን? መቶ ፍራንክ ይከፈለዋል፡፡»
ሁሉም ዝም!
«ሁለት መቶ ፍራንክ» አለ መሴይ ማንደላይን፡፡
የተሰበሰበው ሰው መሬት መሬት ያይ ጀመር፡፡
«ከእዚያ ውስጥ ደፍሮ የሚገባ ሰው በጣም ጡንቸኛ መሆን አለበት፡፡
ግን እኮ ያ ሰው ከዚያ በኋላ እንዴት ይወጣል፣ እዚያው ተጨፍልቆ ይቀራል እንጂ» አለ አንድ ሰው በመካከሉ፡፡
«በሉ እባካችሁ! አራት መቶ ፍራንክ»
«አሁንም ዝም»
«ፈቃደኛነቱ እኮ አይደለም የጠፋው» አሉ አንድ ሰው::
መሴይ ማንደላይን ዞር ብሉ ሲያይ ዣቬርን አየው:: ከዚያ ለመኖሩ
አልተገነዘበም ነበር፡፡ ዣቬር ቀጠለ፡፡
«ኃይል ነው የሚያስፈልገው:: ከዚያ ውስጥ የሚገባ ሰው ደፋርና
እጅግ በጣም ጉልበተኛ መሆን ይኖርበታል:: ይህን የሚያህል የእቃ መጫኛ ጋሪ በጀርባው ተሸክሞ ለማንሳት የሚችል ምን ዓይነት ጉልበተኛ ነው?»
ከዚያ በኋላ ዣቬር መሴይ ማንደላይንን እንደልማዱ አፍጥጦ እያየው እያንዳንዱን ቃል ረገጥ አድርጎ የሚከተለውን ተናገረ::
«መሴይ ማንደላይን፣ አሁን እርስዎ የሚጠይቁትን ሥራ ለመፈጸም የሚችል አንድ ሰው ብቻ ነበር የማውቀው::
ማንደላይን ደነገጠ፡፡
ዣቬር ዓይኑን ከመሴይ ማንደላይን ሳያነሳ የአነጋገሩን ዘይቤ ለውጥ አድርጎ ቀጠለ፡፡
«ይህ ሰው ወንጀለኛ ነበር፡፡»
«እሱን ተወው እባክህ» እለ መሴይ ማንደላይን፡፡
«ቱለን ከተባለ ሥፍራ ታስሮ ነበር፡፡»
የማንደላይን ፊት አመድ መሰለ፡፡
«ወይኔ ተጨፈለቅሁ!» ሲሉ ሽማግሌው ጮኹ::
መሴይ ማንደላይን ቀና ብሎ ተመለከተ፡፡ ዣቬር አሁንም
እንዳፈጠጠበት መሆኑን ተገነዘበ፡፡ የተሰበሰበውን ሰው ቃኘ፡፡ የሃዘኔታ ፈገግታ እያሳየ:: ከዚያም ቃል ሳይተነፍስ በጉልበቱ ተንበረከከ፡፡ ወዲያው ከጋሪው እቃ መጫኛ ስር ከመቅጽበት ገባ፡፡
ሁሉም ተጨነቀ፡፡ ሰው ሁሉ ወሬ ለማየት ተርመሰመሰ፡፡ ለመቀመጥ ይችል እንደሆነ ከአንዴም ሁለቴ ሞከረ፡፡
«መሴይ ማንደላይን ከዚያ በቶሎ ብትወጣ ይሻላል» ሲል ሕዝቡ
ጮኸ፡፡ ሽማግሌውም ይህንኑ አሉ፡፡ «መሴይ ማንደላይን ከዚያ ቶሎ ብለህ ውጣ፡፡ እኔ ልሙት እንጂ አንተ ምን በወጣህ! ካልወጣህ አንተም
ትጨፈልቃለህ::»
ማንደላይን መልስ አልሰጠም፡፡ የተሰበሰበው ሕዝብ እንደገና ዝም
አለ፡፡ ጋሪው ሲነካካ ጊዜ የባሰውኑ ወደ ውስጥ ይሰምጥ ጀመር፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው መሴይ ማንደላይን ራሱን ማላቀቅ ተሳነው::ሰው ተጨነቀ፤ ግን ጭቃው ውስጥ ሰምጦ የነበረው እግር መነቃነቅ ጀምሮ ቀስ እያለ ወደላይ መጣ፡፡ «ከግራ ቀኝ ያዘ እንጂ» ሲል ማንደላይን
ጮኸ፡፡ በአለው ኃይል ለማንሳት ሞከረ፡፡ ሁሉም ለመያዝ የሚችለውን ያህል ያዘ፡፡ የአንድ ሰው ድፍረት ሁሉንም ሰው አነቃንቆ ጉልበት ሰጣቸው::
ሃያ ሰው ያህል ጋሪውን አነሳው፡፡ ሽማግሌው ከሞት ዳነ፡፡
መሴይ ማንደላይን ተነሳ፡፡ ፊቱ፡ በአንድ ጊዜ የገረጣ መሰለ፧ በኃይል አልቦት ነበር፡፡ ልብሱ በጭቃ ከመለወሱም በላይ አንዳንድ ቦታ ላይ ተቀድዷል:: ሰው ሁሉ አለቀሰ፡፡ ሽማግሌው የማንደላይንን ጉልበት ሳመ::
«ደጉ አምላክ» ሲሉ ጠሩት፡፡ ራሱም ቢሆን በጣም ደስ አለ:: በእርካታ ዓይን ዣቬርን አየው::: ዣቬር ግን አሁንም በዓይነ ቁራኛ ይጠብቀዋል።
ደብተራ ፎሽለማ መላላጥ እንጂ ስብራት ስላልደረሰባቸወ ቶሎ ዳኑ፡፡
ግን ጉልበታቸሁ አልነቃነቅ ብሎ አስቸገራቸው:: መሴይ ማንደላይን ከሲሮች ጋር ተነጋግሮ ሽማግሌው ፓሪስ ከተማ አጠገብ ከሚገኝ ገዳም በአትክልተኝነት እንዲሠሩ አስቀጠራቸው::
💫ይቀጥላል💫
👍10❤7
#ችርስ...
አንጀታችን ቢርስ!
እኔና ፈጣሪን ፣ውድድር ሲቃጣን፣
ላለመስከር ማልን፤ወይን እየጠጣን፡፡
ወይን
እያጋጨን፤
ነገር
እየፈጨን፤
ጨዋታ…ጀመርን፤
(አቦ ተባባል)
ስለ ሙሴ ታቦት፤
ስለ ዳዊት መሞት፤
ስለ እየሱስ ታምር
ስለበተነው ፣ከንቱ ሠላሳ ብር፤
ስለ ቤተሳይዳ..
እግዜር ወይን ቀዳ!
ስለቤታሳይዳ፤
ስለብሽቅ ይሁዳ፤
ስለዘማዊት ሴት፤
ስለ ፍጥሞ ደሴት፤
አወጋኝ፤
ስለ ሰው ሰውነት፤
ስለድብብቆሽ ፣ ስለጉራንጉሩ፧
ደርቶ ክርክሩ፤
ከቁዘማ ድሪያ ፣ከሐዘን ተሪክቦ፣
በወይን ተከቦ።
ደገምን፤
ደጋገምን፣
ወይን ሌላ ቀዳን፤
ጨለጥን፤
ቀለጥን፤
በወይን ሮጥን።
ሰው ግን ፤ሞቅ እያለው፣
እግዜር ባለበት ነው።
"ሙላው” እስቲ ቢልም፣
ንቅንቅ እንኳ አይልም።
የሰውን ግፍ ሁሉ እየተረኩበት፣
ካላንገዳገደው ፣ ሁሉን ቻዩን ጉልበት፣
እውነትም ጽኑ ነው ፤ብርቱ ለዘላለሞ፤
አትስከሩ ያለው ፣ ቢሰክር አይደለም፤
እያልኩ..
እየበገንኩ፤
የቀረው ወይን ፣ ልቀዳ እያነሣው፣
ከራድዮን ስለው ፣ ጠርሙሱን አነሣው፤
ነደደ፤
እጁን ጨመደደ፤
ሃ ሃ ሃ ሃ
እግዜር ተናደደ።
በነገራችን ላይ (ከራድዮን! ማለት ለኔ
የዘላለም ስለት፤
የልቤ ሐቅ፤
የነፍሴ ሳቅ፤
እምነቴ፤
ክህደቴ፤
ክስተቴ፤
ክፍተቴ፤
ስሕተቴ፤
የአንድ ወቅት ሕይወቴ፤
የሁል ቀን ሞቴ፤
ናት...
እና...
“ከሪደዮን” ብዬ ፣ ልክ እንደቀጠልኩኝ፣
ሰውነቴ ጠፋ ፣ አምላኬን አከልኩኝ።
ስላንቺ ሳነሣ፣
አብሾው ተነሣ፤
ንዴትና ዕንባ ፣ ቀልቡን ቢያወያየው፣
እግዜር አለ "ወየው!"
“እምቢየው፧"
"አልፈልግም" አለ! በእጄ እንደያዝኩት
ወይኑን ፣ ወሬውን ፣ መልሼ ጠየኩት፤
ዝሞ አለ...ዐሰበ!
ኹለቱሞ ግሪ ነው ፤ አንቺን ስላሰበ።
እወድሽ ነበረ!
ነገርኩት...ዝም አለ፤
እስምሽ ነበረ!
አሁንሞ..ዝም አለ፤
መልክሽ ከስሞ በላይ፤
ስሞሽ ከቃል ሰማይ፤
ልቤ መረገጫሽ፤
የምወደው ሣቅሽ ፣ ወደምድር መሞጫሽ፤
የከንፈሯ ወዙ ፣ ስትስመኝ እንጃልኝ
እግዜር ተናደደ ..."አዚጋ ቅዳልኝ፤”
አለልኝ
ስላንቺ ብመክረው
ስላንቺ ብነክረው፣
ስላንቺ ብነግረው፣
ቅናት አሰከረው፤
እንግዲህ እግዚሐር.. እግዚሐር ይኸነው።
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
አንጀታችን ቢርስ!
እኔና ፈጣሪን ፣ውድድር ሲቃጣን፣
ላለመስከር ማልን፤ወይን እየጠጣን፡፡
ወይን
እያጋጨን፤
ነገር
እየፈጨን፤
ጨዋታ…ጀመርን፤
(አቦ ተባባል)
ስለ ሙሴ ታቦት፤
ስለ ዳዊት መሞት፤
ስለ እየሱስ ታምር
ስለበተነው ፣ከንቱ ሠላሳ ብር፤
ስለ ቤተሳይዳ..
እግዜር ወይን ቀዳ!
ስለቤታሳይዳ፤
ስለብሽቅ ይሁዳ፤
ስለዘማዊት ሴት፤
ስለ ፍጥሞ ደሴት፤
አወጋኝ፤
ስለ ሰው ሰውነት፤
ስለድብብቆሽ ፣ ስለጉራንጉሩ፧
ደርቶ ክርክሩ፤
ከቁዘማ ድሪያ ፣ከሐዘን ተሪክቦ፣
በወይን ተከቦ።
ደገምን፤
ደጋገምን፣
ወይን ሌላ ቀዳን፤
ጨለጥን፤
ቀለጥን፤
በወይን ሮጥን።
ሰው ግን ፤ሞቅ እያለው፣
እግዜር ባለበት ነው።
"ሙላው” እስቲ ቢልም፣
ንቅንቅ እንኳ አይልም።
የሰውን ግፍ ሁሉ እየተረኩበት፣
ካላንገዳገደው ፣ ሁሉን ቻዩን ጉልበት፣
እውነትም ጽኑ ነው ፤ብርቱ ለዘላለሞ፤
አትስከሩ ያለው ፣ ቢሰክር አይደለም፤
እያልኩ..
እየበገንኩ፤
የቀረው ወይን ፣ ልቀዳ እያነሣው፣
ከራድዮን ስለው ፣ ጠርሙሱን አነሣው፤
ነደደ፤
እጁን ጨመደደ፤
ሃ ሃ ሃ ሃ
እግዜር ተናደደ።
በነገራችን ላይ (ከራድዮን! ማለት ለኔ
የዘላለም ስለት፤
የልቤ ሐቅ፤
የነፍሴ ሳቅ፤
እምነቴ፤
ክህደቴ፤
ክስተቴ፤
ክፍተቴ፤
ስሕተቴ፤
የአንድ ወቅት ሕይወቴ፤
የሁል ቀን ሞቴ፤
ናት...
እና...
“ከሪደዮን” ብዬ ፣ ልክ እንደቀጠልኩኝ፣
ሰውነቴ ጠፋ ፣ አምላኬን አከልኩኝ።
ስላንቺ ሳነሣ፣
አብሾው ተነሣ፤
ንዴትና ዕንባ ፣ ቀልቡን ቢያወያየው፣
እግዜር አለ "ወየው!"
“እምቢየው፧"
"አልፈልግም" አለ! በእጄ እንደያዝኩት
ወይኑን ፣ ወሬውን ፣ መልሼ ጠየኩት፤
ዝሞ አለ...ዐሰበ!
ኹለቱሞ ግሪ ነው ፤ አንቺን ስላሰበ።
እወድሽ ነበረ!
ነገርኩት...ዝም አለ፤
እስምሽ ነበረ!
አሁንሞ..ዝም አለ፤
መልክሽ ከስሞ በላይ፤
ስሞሽ ከቃል ሰማይ፤
ልቤ መረገጫሽ፤
የምወደው ሣቅሽ ፣ ወደምድር መሞጫሽ፤
የከንፈሯ ወዙ ፣ ስትስመኝ እንጃልኝ
እግዜር ተናደደ ..."አዚጋ ቅዳልኝ፤”
አለልኝ
ስላንቺ ብመክረው
ስላንቺ ብነክረው፣
ስላንቺ ብነግረው፣
ቅናት አሰከረው፤
እንግዲህ እግዚሐር.. እግዚሐር ይኸነው።
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍15❤7🔥1👏1