ለምን አልሰለምኩም?
3K subscribers
52 photos
10 videos
42 files
187 links
ይህ ቻነል ቅዱሱ የአምላካችን ቃል በ1ኛ ጴጥ 3:15 ላይ ባዘዘን መሠረት ሙስሊም ወገኖቻችን በክርስትና ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች እና ትችቶች ምላሽ የምንሰጥበት፣ ጥያቄዎቻቸውን ከነመልሳቸው በየጊዜው እያዘጋጀን የምንለጥፍበት፣ ለምን እንዳልሰለምን ፣ እንደማንሰልምም የምንገልጥበት ፣ የኢስላምን የጨለማ መንገድነት በእውነት ብርሀን የሚገልጡ ፅሁፎችን የምናስነብብበት መድረክ ነው።
Download Telegram
👀ከሀፊዘሎች መካከል ሁለት ሰዎችን(👨‍👦) እንመልከት ዛይድ ቢን ሳቢትና አቡ ሙሳ አሻሪ፡-👀

እነዚህም አስተማማኝ መጠበቂያዎች አልነበሩም፡፡ እስኪ አቡ ሙሳ የተናገረውን እንመልከት፡-

📚 (ሳሂህ ሙስሊም 5 ፡ 2282-2286)

የነቢዩ ሙሐመድ ተከታይ የሆነው አቡ ሙሳ አሻሪ እንደ ዘገበው፣ በአንቀጾቹ ብዛትና በቅደም ተከተሉ ከአል-ተውባህ ጋር የሚመሳሰል ሱራ እንቀራ ነበር፡፡ ነገር ግን #እረስቸዋለሁ፤ አሁን ከእርሱ #የማስታውሰው #ይህንን #አንቀጽ #ብቻ #ነው፡፡🤷‍♀🤷‍♂🤷‍♀…….. ሌላው እንቀራው የነበረው ሱራ ደግሞ ከሙሳቢሃት ሱራዎች እንደ አንዱ የሚሆን አንቀጾች ያለውና የሚመሳሰል ነው፡፡ ነገር ግን #እረስቸዋለሁ፤ ከዛ አሁን #የማስታውሰው #ይህንን #አንቀጽ #ብቻ #ነው፡፡…………. 🤷‍♂🤷‍♀🤷‍♂

👵ዛይድ ቢን ሳቢት👵፡-
📚 (ሳሂህ አል-ቡኻሪ 60 ፡ 201 ቅጽ 6)

……. ከማንኛውም ሰው ማግኘት ያልቻልኳቸውን የሱራ አል-ተውባህ ሁለት ቁጥሮችን ከኹዜይማ አገኘሁ፤ እነርሱም ቁጥር 128-129 ነበሩ፡፡
ግራንቪል ሻርፕ በ ቲቶ 2:13

የ ሙሓመዳውያን ኡሥታዞች ከ ስላሴ ትምህርት ተቃዋሚያን ፅሁፍ በሚቃርሙት የተሳሳተ መረጃና እጅጉን አሳፋሪ በሆነ አለመረዳትና አለማወቅ የክርስቶስን አምላክነት ለመቃወም በ ፅሁፎቻቸው እራሳችውን ማዋረድና ማውረድ ከጀመሩ ሰንብቷል። ከነኚህ ትችህቶች ውስጥ ዛሬ የምናየው ቲቶ 2:13 ላይ የተነሱትን ይሆናል።

" ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም #የታላቁን #የአምላካችንንና #የመድኃኒታችንን #የኢየሱስ #ክርስቶስን ክብር #መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤"
(ወደ ቲቶ 2:12-13)
προσδεχόμενοι τὴν μακαρίαν ἐλπίδα καὶ ἐπιφάνειαν τῆς δόξης τοῦ μεγάλου #θεοῦ καὶ #σωτῆρος ἡμῶν #Χριστοῦ #Ἰησοῦ,

while we wait for the blessed hope—the appearing of the glory of our great #God and #Savior, #Jesus Christ ( tou megaluo #Theou kai #Soteros hemon Christou 'Iesou)

ከላይ እንዳነበባችሁት ክፍሉ እየሱስን # θεοῦ God ወይም #እግዚያብሔር ብሎ እየጠራ እንደሆነ ግልፅ ነው። ነገር ግን አንዳንድ ከንቱ ተቺዎች "θεοῦ" የሚለው ለ እየሱስ ሳይሆን #ለአብ ነው ብሎ ሙግት አቅርቧል። ሙግቱም አንድ የ ግሪክ ቋንቋ ምሁር (Scholar)፣ ስሙም "ግራንቪል ሻርፕ" የተባለ ሰው ባስቀመጠው የ ሰዋሰው ሕግ ላይ የተመሰረተ ነው። ይሁን እንጂ ይህንን ሙግት ያቀረበው 'ተቺ'፥ ሕጉንና ቲቶ 2:13'ን  አንድ ላይ ቢያጠና ኖሮ፣ ክፍሉ እንዲያውም የ ክርስቶስን አምላክነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ስለሚረዳ አፉን ይዞ ቁጭ ይል ነበር። የሚገርመው ግራምቪል እራሱ ሕጉን ተጠቅሞ ቲቶ 2:13 እየሱስ አምላክ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ፅፏል።

1ኛው የ ግራንቪል ሕግ ምን ይላል??

“When the copulative kai connects two nouns of the same case, [viz. nouns (either substantive or adjective, or participles) of personal description, respecting office, dignity, affinity, or connexion, and attributes, properties, or qualities, good or ill], if the article ho, or any of its cases, precedes the first of the said nouns or participles, and is not repeated before the second noun or participle, the latter always relates to the same person that is expressed or described by the first noun or participle”

καὶ(kai, 'እና') የተሰኘች መስተፃምር ሁለት ተመሳሳይ ሙያ ያላቸውን ስሞች ለማያያዝ ስትገባና ከመጀመሪያው ስም በፊት ho ወይም τοῦ ("The") የሚለው definite article ከገባ  ግን ሁለተኛው ስም(noun) በፊት ሳይገባ ከቀረ እነኚህ ሁለቱ ስሞች የሚናገሩት(የሚገልፁት) ስለ አንድ ሰው ነው።
(Remarks on the Uses of the Definitive Article, 3)
(ይህንን ካላሟላ ግን ሁለት የተለያዩ አካላትን ለመግለፅ ነው የሚለው ሙግት ከዚህ የመጣ ነው፤ሁል ግዜ ትክክል ባይሆንም)

ይሁን እንጂ ይሄ ሕግ ከላይ የተገለፀውን የ አርፍተ ነገር አወቃቀር ለሚያሟሉ  ሁሉ ይሰራል ማለት #አይደለም። ሕጉ የሚሰራው ቀጥለን ይምንዘረዝራቸውን ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟሉ #ብቻ ነው።

1. ስሞቹ ሕልውና ላላቸው (ለሰው, ለ አምላክ) ብቸ የተጠቀሙ መሆን አለባቸው (they must refer to a person;not a thing)

2. የተፀውኦ ስም (Proper name) መሆን #የለባቸውም

3. ተመሳሳይ ሙያ መሆን አለባቸው (The same case)

4. ነጠላ መሆን አለባቸው (singular in number)

ዋቢ መፅሓፍት

ሀ. A Reexamination of the Granville Sharp rule by Daniel B.Wallace, Ph.D. Associate professor of New Testament Studies;

ለ. Wallace, Greek Grammar, 280-290

ሐ. Robertson, Grammar, 785-90

ስለዚህ በዚህ ሕግ መሰረት ቲቶ 2:13 "እየሱስ አምላክ ነው" ይላል?? መልሱን የምንሰጠው ክፍሉ የ ግራንቪልን ሕግ ሙሉ ለሙሉ ማሟላቱን ነጥብ በ ነጥብ እያየን ይሆናል።

1. 'tou' 'The' የሚለውን definite article የተጠቀመው በ መጀመሪየ ስም ላይ ብቻ ነውን?
መልስ- #አዎ
#tou megaluo #Theou kai #Soteros hemon Christou 'Iesou (ቲቶ 2:13)
θεοῦ(Theou, አምላክ, God) የሚለው የመጀመሪያ ስም ሲሆን σωτῆρος(Soteros, አዳኝ ወይም መድሃኒት, saviour) ሁለተኛ ስም ነው። tou' የሚለው የገባው በ θεοῦ ፊትለፊት ብቻ ነው።

2. ስሞቹ የተጠቀሙት(Theou እና Soteros) "ህልውና ላለው( personal) ነውን??
መልስ፦አዎ። ምክንኒያቱም ሁለቱም እየሱስን ለመግለፅ ነው የገቡት።
"..የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን #የኢየሱስ #ክርስቶስን.."

3. θεοῦ እና σωτῆρος ሁለቱም የተፀውኦ ስም (Proper name) #አይደሉም። ስለዚህ አሁንም ክፍሉ 2ኛውን  ቅድመ ሁኔታ ያሟላል ማለት ነው።

4. θεοῦ እና σωτῆρος ተመሳሳይ ሙያ ናቸውንህ??

θεοῦ=Noun #Genetive masculine singular
σωτῆρος=Noun #Genetive masculine Singular
ስለዚህ መልሱ "አዎ! ሁለቱም ተመሳሳይ ሙያ ናቸው።"

5. θεοῦ እና σωτῆρος ሁለቱም #ነጠላ (singular) ናቸው። ስለዚህ የመጨረሻውንም ቅድመ ሁኔታ ያሟላል።

ስለዚህ፤ ቲቶ 2:13 ሁሉንም የ ግራንቪል የ ሰዋሰው ሕግ ያሟላል። ማለትም θεοῦ እና σωτῆρος ( God and saviour, አምላካችንና መድሓኒታችን) ብሎ የተቀመጠው ሁለቱም #እየሱስን ለመግለፅ ነው ማለት ነው። ስለዚህ እየሱስ 'አምላክ" እና "መድሃኒት" ነው ማለት ነው።

ሙስሊሙ 'ተቺ"ይህንን ክፍል ለማክሸፍ የተጠቀማቸው ጥቅሶች ሁለት ናቸው።

1. ማቴ 21:12 ኢየሱስም ወደ መቅደስ ገባና በመቅደስ *የሚሸጡትን* እና *የሚገዙትን* ሁሉ አወጣ። "እነኚህ ሁለቱ ስሞች የተለያዩ ሰዎችን ይገልፃሉ" ብሎ ፅፏል።

ይሄ ክፍል በ አረፍተ ነገር አወቃቀሩ ቲቶ 2:13ን ቢመስልም (τοὺς πωλοῦντας καὶ ἀγοράζοντας*Those selling and buying) ግን ቅድመሁኔታዎችን ስለማያሟላ ውድቅ ነው። ምክኒያቱም "የሚሸጡትን* እና *የሚገዙትን" የሚሉ ሁለቱም ቃላት #ነጠላ አይደሉም።የ ግራምቪልን ሕግ አያሟሉም። ስለዚህ ክፍሉን እንደማስረጃ ማቅረብ በራሱ አሳፋሪ ነው።

2. ኤፌሶን 2:20 *በሐዋርያት* እና *በነቢያት* መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥

አሁንም በዚህ ክፍል "በሐዋርያት* እና *በነቢያት"  የተባሉት ሁለቱም ብዛትን የሚያሳዩ እንጂ ነጠላ አይደሉም። ስለዚህ አሁንም ማስረጃው የ ግራንቪልን ሕግ ስለማያሟላ  ውድቅ ይሆናል
@Jesuscrucified
የ አይሻ ቤት ወይስ የ አይሸ ቀሚስ?

እውቀት አልባውን ሙስሊም ሰብስቦ ሲያስጨፍር የሚውል አንድ 'ጥንጥ' ጭንቅላት የተሸከመ ሕይወቱን ሙሉ ሲንከራተት ያሳለፈና ምን ማመን እንዳለበት እንኳን የማያውቅ አንድ 'ኡስታዝ ነውም ይሉታል'፣ አለ። ልክ በራሱ አጥንቶ እንዳመጣ ሰው፣ ነብዩ ሙሓመድ 'የ አይሻ #ቀሚስ ውስጥ ካልሆነኩ ወሒ(መገለጥ) አይመጣልኝም' ብሎ የተናገሩትን፣ "የ አይሻ #ቤት" ማለት ነው ብሎ ሙግቱን አቅርቧል።ክርስቲያኖችም ይህንን መረዳት ያልቻሉበት ምክኒያት ከ ጎግል ስለሚጎረግሩት እንጂ እውቀት ስላላቸው እንዳልሆነ ተናግሯል። የሚገርመው ነገር ግን ይህ ሰው ሙግቱን ቃል በ ቃል 'Answering Christianity' ከተሰኘ ድሕረ ገፅ  በ 'ኦሳማ አብዱላህ' ከተፃፈው አርቲክል እና 'አቡአልራብ' የሚባል ሰው ከፃፈው አርቲክል ኮፒ ፔስት ማድረጉ እጅጉን ፈገግ የሚያደርግ ነው። "ሌባ እናት ልጇን አታምንም" ይሉ ይለ?

ሳሂህ አል ቡኻሪ መፅሓፍ 51 ሓዲሥ 16

ነብዩ እንዲህ ብሏል "...ወሒ(መገለጥ) በ አይሻ ቀሚስ(ሠውብ 'ثوب') ውስጥ(في) ካለሆነ በ ሌሎች ሴቶች ቀሚስ ውስጥ አይመጣልኝም።"
فدار إليها فكلمته فقال لها ‏ ‏لا تؤذيني في ‏ ‏عائشة ‏ ‏فإن الوحي لم يأتني وأنا في ثوب امرأة إلا ‏ ‏عائشة.

ሳሂህ ሙስሊም መፅሓፍ 31 ሓዲዝ 5907

زَوْجَ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم وَعُثْمَانَ حَدَّثَاهُ أَنَّ أَبَا بَكْرٍ اسْتَأْذَنَ عَلَى رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم وَهُوَ مُضْطَجِعٌ عَلَى ِرَاشِهِ لاَبِسٌ ِرْطَ عَائِشَةَ
Abu Bakr requested permission from the prophet to enter when the prophet was lying down on Aisha’s #bed wearing her #garment (mirt)
"አቡ በከር ነብዩ ወዳሉበት ክፍል ለመግባት ፍቃድ ጠየቀ። ነብዩም በ አይሻ #ፍራሽ ላይ የሷን #ቀሚስ(mirt) ለብሶ ጋደም ብሎ ነበር።"

ነብዩ በ እርግጥ የሴት ልብስ እንደሚለብሱና መገለጥም በሱ ውስጥ እንደሚመጣላቸው መናገራቸው ግልፅ ነው። እነኚህ የሙሃመድ "ጠባቂያን" ግን ይህንን የሚያክል አሳፋሪ ድርጊት ለመሸፈን የማይቆፍሩት ጉድጓድ የለም።

የ ሙስሊም ነኝ ባዩ ሙግት እንዲህ የሚል ነው፦

"ሠውብ” ثَوْب የሚለው ቃል በብዙ ይመጣል፦
“ሂጃብ” حِجَاب “መጋረጃ”፣“ፊራሽ” فِرَٰش ምንጣፍ”፣“ሊሃፍ” لِحَاف “ፍራሽ”“በይት” بَيْت “ቤት”
“ሊባሥ” لِبَاس “ልብስ......ይህንን ካየን ነብያችን”ﷺ”፦ “ከማናቸውም ሴቶች ልብስ ውስጥ ወህይ አይመጣልኝም ከዓኢሻ”ረ.ዓ.” ልብስ በስተቀር” ሲሉ ከዓኢሻ”ረ.ዓ.” #ፍራሽ ወይም #ቤት ማለታቸው እንደሆነ እሙንና ቅቡል ነው..."

ይሄ ሙግት በጣም የወረደ መሆኑን ላስነብባቹ።

1. ነብዩ "ለበሱ" የተባለው " ሠውብ" ብቻ አይደለም። "ሚርት" ተብሏል።ትርጉሞቹን እንመልከት

ሠውብ፦ ከ ዲክሺነሪ
ثَوْب
apparel
- clothes worn on a special occasion
(ልዩ የሆነ ቀን ላይ የሚለበስ ልብስ)
- clothes; dress(ልብስ፣ቀሚስ)

2. "ሚርት"
 እውነት ሓዲዙ የሚነግረን ነብዩ መገለጥ ይመጣልኛል ያሉት የ አይሻ #ቤት ወይም #ፍራሽ ላይ እንጂ የሷ ቀሚስ ውስጥ አይደለምን?

ከ ላይ እንዳነበብነው፣ ሳሂህ ሙስሊም 5907 እንዲህ ይላል፦
"አቡ በከር ነብዩ ወዳሉበት ክፍል ለመግባት ፍቃድ ጠየቀ። ነብዩም በ አይሻ #ፍራሽ فِرَاشِهِ ላይ የሷን #ቀሚስ(ሚርት) ለብሶ ጋደም ብሎ ነበር።"

ልብ በሉ፣ በዚህ ሓዲዝ ላይ በ ግልፅ "ፍራሽ" እና "ልብስ" ሁለት የተለያዩ ቃላቶች ሆኖ ተቀምጧል።
A. ነብዩ ምን ላይ ነው የተኙት? መልሱ፦ የ አይሻ ፍራሽ
B. ነብዩ ምን ለብሶ ነበር?፦ የ አይሻ ቀሚስ

ስለዚህ በ ሌሎች ሓዲሣት ውስጥ ነብዩ "በ አይሻ ቤት ውስጥ እንጂ በሌሎች ሶቶች ቤት ውስጥ መገለጥ አይመጣልኝም (ሙስነድ አህመድ መጽሐፍ 6 ሐዲስ 293") ብለው እንደተናገሩ ተደረጎ የተፃፉ፣ ነብዩ የ አይሻ ልብስ አይለብሱም ማለት አይደለም። ይልቁንስ ከላይ ባነበብነው ሓዲሥ መሠረት "በ አይሻ ቤት ውስጥ የሷን ቀሚስ ለብሶ" ማለት ነው እንጂ።

በተጨማሪም "ሚርት" የሚለበሰው በ ሴቶች #ብቻ መሆኑን የ ሙስሊሞች መፃሕፍት መስክሯል። ምሳሌ፦

ፈትሁል ባሪ፣ የ ሳሂህ አልቡካሪ ማብራሪያ (ኢማም ኢብን ሓጀር አል አስቀላኒ) ቅጽ 2፤
Volume 2፦ The Book of Prayer Times; Chapter of Dawn Prayer

"..'ሚርት' ተብሎ የሚጠራ ልብስ በ ሴቶች #ብቻ የሚለበስ ነው" ይላል።

#የሴት_ልብስ_መልበስ_በ_ሓዲሣት_ህግ

ሱናን አቡ ዳውድ 4098
Narrated AbuHurayrah:

The Messenger of Allah (ﷺ) cursed the man who dressed like a woman and the woman who dressed like a man. (Sahih)
حَدَّثَنَا زُهَيْرُ بْنُ حَرْبٍ، حَدَّثَنَا أَبُو عَامِرٍ، عَنْ سُلَيْمَانَ بْنِ بِلاَلٍ، عَنْ سُهَيْلٍ، عَنْ أَبِيهِ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ لَعَنَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الرَّجُلَ يَلْبَسُ لِبْسَةَ الْمَرْأَةِ وَالْمَرْأَةَ تَلْبَسُ لِبْسَةَ الرَّجُلِ ‏.‏
:  (  صحيح   (الألباني)
"ነብዩ እንዲህ ብሏል፦ 'የ ሴት ልብስ(እንደሴት) የሚለብስ  ወንድ ወይም የ ወንድ ልብስ የምትለብስ ሴት #የተረገመ/ች ነው/ናት"

መደምደሚያ:

ነብዩ የሴት ልብስ ይለብሱ ስለ ነበረ እራሳቸው በተናገሩት ንግግር መሠረት #የተረገሙ ናቸው ማለት ነው!! አከተመ።

ነብዩ ለ እርግማናቸው የሞተውን ክርስቶስ ለመቀበል ሁለተኛ እድል አይሰጣቸውም። ይህን ፅሁፍ የምታነብ ሙስሊም ግን ማምለጥ ትችላለህ። የሞተልህን ክርስቶስ ተቀበል!!!

 " እንግዲህ። በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ አልኋችሁ፤ እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና አላቸው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 8:24)
@Jesuscrucified
@Jesuscrucified
እንግዲህ ነገሩ እዚ ላይ ነው እሚጀምረው። እዚጋር ነው እንግዲህ ድሮም ቢሆን የእየሱስ ከአባቱ ከአብ ጋር ያለው የልጅና የአባትነት ሕብረት በሚገለጥበት ዘላለማዊ ፍፁም #መታዘዝ(በፈቃዱ) ያልገባቸው መሐመዳውያን😲 ግራ መጋባት የሚጀምሩት። እየሱስ ፈቃዱን በፍፁም መታዘዝ(#perfectobedience) የሚናገረውን የሚያደርገውንም ሁሉን ፈቃዱን #በራሱ ለአብ በማስገዛት የአብን እውቀትና ፈቃድ ይፈፅም ዘንድ ያለው። ይህ ነው እንግዲ የመጀመሪያው የሁለቱ ሕብረት። ይህ ማለት ግን ከአብ የመጣው እውቀት ልክ መልዐኩ ከእየሱስ ተቀብሎ ለሐዋርያው ዮሐንስ እንደሚገልጥ በሶስተኛ ሰውና እራሱን #እኔ እያለ ሳይጠራ እንደሚያቀብል ተራ የመልእክት ተዋረድ አካል ነው ማለት አይደለም‼️ይህም መፅሐፉን መጀመርያና መጨረሻ #ብቻ ሳይሆን #ከመጀመርያ እስከ መጨረሻ ላነበበ እየሱስ ራሱን ብቻና ብቻ የሚወክልን ንግግር ሲያደርግ ትዕይንት ሲከውን እንመለከታለን። ስለዚህም የአብን ፈቃድና እውቀት ሲፈፅምና ሲናገር በተመሳሳይ መልኩ አብ የልጁን ማንነት ልጁ በአባቱ ግልጠት እራሱ የሚያቀውን ይናገር ዘንድ ሰቶታል ማለት ነው።🔑 ይህንንም በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14፥21-24 ማበብ ጠቃሚ ነው። እየሱስ "የላከኝ የአብ ቃል ነው" እያለ፤ እዛው "ቃሌን" ብሎ ሲጀምር፤ የሚገልጠው የተሰጠውን የላከውን እንደሆነ እያወሳ #ራሴን እገልጥለታለሁ ሲል እናያለን። ይህ ማለት አብና ወልድ አንድ አካል ናቸው ማለት ሳይሆን #በምንነት #ሁለቱ #ከአንድ እንደሚቀዱ ያስተውላል።ይህንን ጠልቀን በየጥቅሱ እንተነትናለን።
እንደው ለመጠየቅ ያህል መሐመዳውያን ቁጥር አንድን ሲያነቡ "ለባሪያዎቹ...በመልአኩ ልኮ" የሚሉት ቃላት የሚያሳዩት #ባለቤት ማነው?
መቼም መልአክን የሚልክ ባርያም እንሆንለት ዘንድ የተገባው ማን እንደሆን ግልፅ ነው።🤔😁😁😁
ቁጥር ሁለትን በመዝለል መሮጥ🏃‍♂ የሁሌም ልማዳቸው ነው። ግና ሁለትን ቢያዮአት ኖሮ መፅሐፉ ስለምን እንደሚያወራ ይገባቸው ነበር።💡 በቁጥር ሁለት ላይ ለእግዚአብሄር ቃል፣ ለእየሱስም ምስክርነትና ላየው ሁሉ ነገር እንደተፃፈ በእርግጥ ያስረዳል❗️ ይህ ማለት ይህ መፅሐፍ ሦስት ነገሮችን ይዞል ማለት ነው 1⃣ የእግዚአብሄርን ቃል፣ 2⃣የእየሱስን ምስክርነትና 3⃣መልአኩ ያሳየውን። ስለዚህ እየሱስ ተራ መልዕክት አስተላላፊ ቢሆን ኖሮ እንዴት የራሱን ምስክርነት ያወራል?🤔 ግን ነገሩ እንደዛ ስላልሆነ አብን በማክበሩ አብ ደግሞ እርሱ በፊት በነበረ ክብሩ ያከብረው ዘንድ ይሁን ያለውን #የራሱን ምስክርነት ሲያቀርብ እናያለን። ለዚነው ተዋረዱ እነሱ እንዳሰቡት #አደለም ያልነው።
ቁጥር አራት የሚናገረው ስለሰላምታ ቢሆንም ግልፅ ያለ #የስላሴን አስተምሮ የሚያሳይ ለቀጣይም ቁጥሮች ማጣቀሻን #ፍንጭ የሚሰጥ ትልቅ ቁጥር ነው።
ሰላምታው ከአብ(ካለው ከነበረው ከሚመጣ)፣ ከሰባቱ መናፍስት(ከመንፈስ ቅዱስ፤ ይህን በ3፥1,4፥5,5፥6 ላይ መመልከት ይቻላል...ሰባት ብዛትን ሳይሆን ፍፅምናን የሚያሳይ ሲሆን ከነዚ ውጭ ያሉ ሰባት መልአክት ወዘተ የሚሉ ክፍሎች እስካልተፃፈ ድረስ ይህንን ሐረግ አይወክሉም)ና ከወልድ(ከእየሱስ) ነው የመጣው። #ፍንጩንም እንደሚከተለው አትታለሁ፦
ማነው የታመነ ምስክር? #እየሱስ
" ከሙታን በኩር? #እየሱስ....
" ኃጥያታችንን በደሙ ያጠበ? #እየሱስ
" ለአምላኩና ለአባቱ ካህናትያረገን? #እየሱስ
" ከደመና ጋር እሚመጣ? #እየሱስ
" የተወጋ የተወጋውም ውጉም ሲመጣ የሚታይ? #እየሱስ(ዮሐ19፥37) ...
ስለዚህ ይህንን ይዘን ታች ቁጥር 8 ላይ ስንደርስ ይኃው ሲገለፅ የነበረ ማንነት እኔ እንዲ ነኝ ብሎ ይናገራል፦ " ያለውና የሚመጣውም ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላክ #አልፋናዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል።"
🤔እናም "ማነው ይህን የሚለው?" #እየሱስ "ስለማ?" ከላይ ጀምሮ የተጠቀሰው ማንነት እርሱ ብቻ ስለሆነ #ስለራሱ ነዋ እሚለው።
"እንዴት ተልኮ ነው እንጂ ስለ ራሱማ አደለም!" ታድያ እኔ ብሎ ስለ አብ ብቻ ከሆነ እሚያወራው ለምን በቁጥር 18 ላይ "ሞቼ ነበርሁ..." እያለ ያወራል ወገንመችና የትነው አብ የሞተው እናስብ እንጂ‼️