ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.82K subscribers
534 photos
68 videos
81 files
389 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
አንድ ሰባኪ " ኢየሱስ የተሰቀለው ከማርያም #በነሳው #ስጋ ነውና የኢየሱስ #ስጋ የማርያም #ስጋ ነው" እያለ ሰብኮ ካጠናቀቀ ቡሀላ ወደ መቀመጫው ይመለስና ከአንድ ሊቅ አጠገብ ይቀመጣል። ሊቁም ሰባኪውን ቆነጠጡት። በዚህ ጊዜ ሰባኪው "ምነው አባታችን? ምን አጠፋሁ?" ይላቸዋል። እርሳቸውም፣ " #አሁን ይህ ቁንጥጫ #አንተን ነው ወይስ #እናትህን ነው የተሰማት?" አሉት። ይባላል።
.
.
.
.
.
ሊቁ ለሰባኪው ያስተላለፉት መልእክት ግልጽ ነበር። ከማርያም ቢወለድም የኢየሱስ ስጋ፣ የኢየሱስ ስጋ እንጂ የማርያም ስጋ ተብሎ የሚጠራበት አንድም ምክንያት አይኖርም(ማቲ 27፥58 ፣ ማር 15፥43 ፣ ሉቃ 23፥52 ፣ 24፥3 ፣ ዩሀ 19፤ 38-40 ፣ 20፥12)

ምንጭ--- " ነገረ ድኅነት በአሚነ አበው " ገጽ 99
በዲያቆን አግዛቸው ተፈራ

@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
Photo


#ስለዚህም ይህ " #መናፍቅ #የጨመሩት ነው" የሚለው ንግግር ሆን ብሎ ሰውን ለማሳሳት #የተፈጠረ መላምት ነው ከማለት ያለፈ ሊባል የሚቻለው ሌላ ነገር የለም። ይህ ራሱ #የአንዳንዶች #የማታለያ #ዘዴ ብቻ ነው እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቃሉ #እውነት እንደሆነ #ከጥንትም እንደነበረ ራሳቸውም ማመናቸው ተራጋግጧል።
ለምሳሌ፦
#ማኅበረ ቅዱሳን #ለተሐድሶ መልስ እሰጥበታለሁ ብሎ በለቀቀው ድምፅ ወምስል (ቪሲዲ) ላይ " #ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ" ይህን ጥቅስ በተመለከተ ‹‹ #ስለ እኛ #የሚማልደው የሚለው ቃሉ አለ፤ #ከጥንቱም #ከግሪኩ አለ›› የሚል #አስተያየታቸውን መስጠታቸውን መመልከት ይቻላል፡፡
(ማኅበረ ቅዱሳን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እናድሳለን ብለው የተነሡ ፕሮቴስታንቶች በሚያነሧቸው ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መልስ 2ኛው ድምፅ ወምስል፣ (መስከረም 2010)፣ 8፡11-8፡15 ደቂቃ፡፡)

ዞሮ ዞሮ ይህም የሆነው #እውነትን ደብቆ #መቀመጥ ስለማይቻል ብቻ ነው። ከዚህም በተጨማሪ #አባቶቼ እያሉ የሚጠሯቸው ፣ #መታሰቢያም የሰሩላቸው #አባቶች ይህን ቃል የተረዱት የዛሬዎቹ አንዳንድ መምህር ተብዬዎች ከሚያስቡት በተቃራኒ ነው።
@ ለምሳሌ፦
#ዮሐንስ አፈወርቅን ብንመለከት #የሮሜ መልእክትን በተረጎመበት
/" #ድርሳን 15" ይህን ቃል #እንደወረደ ተጠቅሞታል።
እንዲህ ብሏል ፦
<< #ቅዱስ ጳውሎስ " #ስለ እኛ #የሚማልደው"ብሎ #ለሥጋ እንደሚገባ አድርጎ የተናገረው #ፍቅሩን #ይገልጽ ዘንድ #በታላቅ #ትህትና የገለጸው ነው>>
ብሎ ጽፏል።
#አስተውሉ #ዮሐንስ #አፈወርቅ #የጳውሎስ ጹሕፍ ምን እንደነበረ
#ሲገልጽ እነመለከታለን።
#ጳውሎስ " #የሚማልደው"ብሎ እንደጻፈ ይህም የክርስቶስን #ትሕትና እና #በሥጋው ወይም #በሰውነቱ #አንጻር #የተነገረ እነደሆነ እና #ጌታ ለእኛ ያለውን #ፍቅር #ለሚያስረዳት የተጻፈ #መሆኑን ገልጿል።
አስተውሉ!!
#ዮሐንስ አፈወርቅ #መናፍቅ ነበር እንዴ? ነው ወይስ
#የመናፍቃንን #መጽሐፍ ቅዱስ
ነው የተረጎመው? ነው ወይስ
#እናንተ #አባታችን ከምትሉት #ዮሐንስ አፈወርቅ #ትበልጣላችሁ? ነው ወይስ
#ተሳስቶ ነበር? ምንድን ነው #የምትመልሱት?
*
#ይህም ብቻ አይደለም የክርስቶስ #አማላጅነት #ከአብ #ያንሳል ማለት እንዳልሆነ
፣እኛን ለመርዳት አቅም ስለሌለው #መለመን አስፈልጎት እንዳልሆነ ነገር ግን
ለእኛ ያለውን #ፍቅር ለማሳየት እንደሆነ ገልጿል።
#ይህን ቢገልጽም #የጳውሎስን
#ቃል #መናፍቃን #የጨመሩት ነው አላለም።
ነገር ግን ከጳውሎስ #የሰማውን ቃል #እርሱም ተቀበሎ እየደጋገመ ይናገረዋል ።
ለምሳሌ ፦

<< #ክርስቶስ አሁን #በክብሩ #የሚታይ ቢሆንም #ርኅራኄውን ከእኛ #አላራቀም #ስለእኛ
#ይማልዳል #እንጅ>>


<< #እንግዲህ #መንፈስቅዱስ ራሱ #በማይነገር #መቃተት #የሚማልድልን ከሆነ #ኢየሱስም #ሞቶ #የሚያማልደን ከሆነ #አብም #ለአንተ ሲባል #ለልጁ #ካልራራለት #አንተን #ከመረጠህ #ካጸደቀህ ከዚህ ሌላ በምን #ትፈራለህ?>>


<< #እግዚአብሔር #ዘውዱን አቀዳጅቶናል። #የሚኮንነንስ #ማነው? #ክርስቶስ #ሞቶልናል #መሞት ብቻ አይደለም ከዚህም በኋላ #ለእኛ #ስለሚማልድ ማን
#ይኮንነናል? >>
📖/፤ ሐመረ መጽሄት ሐምሌ 2007 ገጽ 10
በማለት ያብራራዋል።
#ለመሆኑ > #ዮሐንስ #አፈወርቅ< እንዲህ እየገለጸው እያለ
#መናፍቃን #የጨመሩት ነው #የምትሉት ከየት አምጥታቹ ነው? እናንተ #ሰዎች ሆይ #ከስህተታችሁ ታረሙ።
#ይህ " #ዮሐንስ #አፈወርቅ" ዕብራውያን 7:25ን በተረጎመበት ድርሳን 13 ላይ
የሮሜን መልእክት ለማስረጃ ጠቅሶታል።
ሮሜ8:34 ላይ የተጻፈውና ዕብ7:25 ላይ የተጻፈው ቃል #ተመሳሳይ እንደሆነ ያስረዳል። ይህ ዮሐንስ አፈወርቅ
#የክርስቶስን #አማላጅነት #ከፍቅር #አንጻር ይመለከተዋል ለምሳሌ፦
ዮሐ17:9-21
ያለውን #የጌታን #ምልጃ እንዲህ ገልጾታል ፦
*
<< "I pray not that You should take them out of the world, but
that You should keep them from the evil."
Again He simplifies His language; again He renders it more
clear; which is the act of one showing, by making entreaty
for them with exactness, nothing else but this, that He has a
very tender care for them. Yet He Himself had told them,
that the Father would do all things whatsoever they should
ask. How then does He here pray for them? As I said, for
no other purpose than to show His love .>>
በማለት የጸለየው የፍቅር መገለጫ መሆኑን በድርሳን 82 ገልጾታል ።
ራሱን ያለምስክር የማይተው ጌታ በእነዚህ ሰዎች ሞስክር አአስቀምጧል ።

እንግዲህ መጀመሪያ #በግሪክ የጻፈው #ሐዋርያ ስለእኛ #የሚማልደው ካለ አባቶቻችንም ይህንን #እውነት ካጸኑልን ታድያ ይህንን #በመንፈስ ቅዱስ በተሰጠ #ሐዋርያዊ ስልጣን የተጻፈን ቃል #የመለወጥ ስልጣን ያለው አለን? #ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን #እንመን? #ወይስ #እነርሱን?
አስቡበት!!

#ይህም ብቻ ሳይሆን ‹ #ስለ እኛ #ይፈርዳል› ተብሎ የተተረጐመው ቃል #ስሕተት የሆነው ንባቡ በመተርጎሙ ብቻ ሳይሆን፤ #በሕገ #ሰዋስው መሠረት ሲታይ ሐረጉ #በዐረፍተ ነገሩ ውስጥ እንዲገልጽ #የተፈለገውን ሐሳብ ስለማይገልጽና ሌላ #ትርጕም ስለሚሰጥም #ጭምር ነው እንጂ፡፡ በዐማርኛ ሰዋስው ‹ #ስለ እኛ ይፈርዳል› የሚል ንባብ " #ለእኛ ይፈርዳል› ወይም " #በእኛ ይፈርዳል" የሚል #ትርጕም ሊሰጥ አይችልም፡፡ የሚሰጠው #ፍቺ በእኛ ምትክ፣ #እኛን #ወክሎ #ይፈርዳል የሚል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ቃሉን የለወጡት ሰዎች ቃሉ እንዲናገርላቸው የፈለጉትን ‹ #ለእኛ ይፈርዳል› ወይም " #በእኛ ይፈርዳል" የሚለውን #ሐሳብ አይጠራላቸውም፡፡ እንዲያውም ያልጠበቁትን #ትርጕም ይሰጥባቸዋል፡፡ የተፈለገውን #ትርጕም ይሰጥ ዘንድ ‹ #ስለ› የሚለው መስተዋድድ #ይፈርዳል ከሚለው ግስ ጋር ሳይሆን #ይማልዳል ወይም #ይከራከራል ከሚለው #ግሥ ጋር ነው ሊሄድ የሚችለው››፡፡

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
አንድ ሰባኪ " ኢየሱስ የተሰቀለው ከማርያም #በነሳው #ስጋ ነውና የኢየሱስ #ስጋ የማርያም #ስጋ ነው" እያለ ሰብኮ ካጠናቀቀ ቡሀላ ወደ መቀመጫው ይመለስና ከአንድ ሊቅ አጠገብ ይቀመጣል። ሊቁም ሰባኪውን ቆነጠጡት። በዚህ ጊዜ ሰባኪው "ምነው አባታችን? ምን አጠፋሁ?" ይላቸዋል። እርሳቸውም፣ " #አሁን ይህ ቁንጥጫ #አንተን ነው ወይስ #እናትህን ነው የተሰማት?" አሉት። ይባላል።
.
.
.
.
.
ሊቁ ለሰባኪው ያስተላለፉት መልእክት ግልጽ ነበር። ከማርያም ቢወለድም የኢየሱስ ስጋ፣ የኢየሱስ ስጋ እንጂ የማርያም ስጋ ተብሎ የሚጠራበት አንድም ምክንያት አይኖርም(ማቲ 27፥58 ፣ ማር 15፥43 ፣ ሉቃ 23፥52 ፣ 24፥3 ፣ ዩሀ 19፤ 38-40 ፣ 20፥12)

ምንጭ--- " ነገረ ድኅነት በአሚነ አበው " ገጽ 99
በዲያቆን አግዛቸው ተፈራ

@gedlatnadersanat @teeod