ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ባለፈው ጊዜ ረዓብ ወይም ራኬብ ስለምትባል ደገኛ ሴት ታሪክ አቅረበንላችሁ ነበር

#ማጠቃለያ ሀሳብ ለመስጠት ያክል ረዓብ/ራኬብ ሦስት ነገር የተገኛባት ሴት ነበረች በነዚህም ነገሮች ለመዳን ችላለች።



1)ደግነት ፦ ወደ ቤቷ ሸሽተው የገቡትን ሰዎች ማናችሁ ?ምንድናችሁ ?ሳትል ዘር ፣ጎሳ ፣ መልክ ሳታይ በደግነት ዝም ብላ ተባረው ሰለመጡ ብቻ አዝና ተቀበለቻቸው።
2)እምነት፦ ከተማዋን ሲወርሱና ሲቆጣጠሩ ሊያድኟት እንደሚችሉ ሲነግሯት በቅንነነት ተቀብላቸው መልክት አድርጋ እንድታውለበልበው የነገሯትን ቀይ በፍታ በመስኮታ ላይ አድርጋ የእምነት ማዕተሟን ጠብቃ ኖራለች።
3)ጥበብ፦ 3.1ተሳደው ወደ ቤቷ ያስገባቻቸውን ሰዎች ሰገነቱ ላይ አውጥታቸው ነበር በዚያም በረበረበችው በተልባ እግር ውስጥ ሸሽጋቸው ነበር
3.2 ሌላው ጥበቧ አሳዳጃቸው መጥተው ወደ ቤትሽ የገቡ ሰላዮች አሉ አስወጫቸው ሲሏት አረ አልገቡም ብላ አልካደችም አዎ ገብተው ነበር ግን በዚህ በኩል ወጡ ማለቷ ብልኀተኛ መሆኟን ያሳያል እንደውም በትርጓሜ ላይ መግባታቸውን ስላመነችላቸው ተመልሰው መውጣታቸውን ስትነግራቸው አመኑላት ብሎ ጥበቧን ይገልጣል።

የኢያሪኮ ቅጥር ሰባት ቀን ከዞሩበት በኋላ በእምነት ወደቀ። "ጋለሞታይቱ ረዓብ ሰላዮችን በሰላም ስለ ተቀበለቻቸው ከማይታዘዙ ጋር በእምነት አልጠፋችም።ዕብ11÷30-31

ረዓብ/ራኬብ ከዚህ ክብሯ ባለፈ ከጌታችን ቅድመ አያቶች መካከልም ገብታ ለመቆጠር ችላለች።



“የወንድማማች መዋደድ ይኑር። #እንግዶችን_መቀበል_አትርሱ፤ በዚህ አንዳንዶች ሳያውቁ #መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” ዕብ 13፥1-2
#ኃበ_ብዙኃን_አባታችን_አብርሃም ደግሶ ያበላቸው ዘንድ እንደ ወትሮው ይጠብቅ የነበረው ብዙ ሰዎችን ነበር።
ጸላዬ ሰናያት የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ዲያቢሎስ ግን ከመንገድ ቆሞ እራሱን በምትአት ገምሶ ደሙን አፍስሶ እያንጠባጠበ ወደ አብርሃም የሚመጡትን እንግዶች የድሮ አብርሃም ያለ መስሏችሁ ወደ አብርሃም አትሂዱ አብርሃም የድሮ ደግነቱን ትቷል።
#ይህው_እኔም እንደ ወትሮው መስሎኝ ያበላኛል ያጠጣኛል ብዬ ወደ እርሱ ብሄድ እራሴን ገምሶ ደሜን አፍሶ መለሰኝ ይላቸው ጀመር ። ሕዝቡም መቼም ደግ ሰው አይበረክትም እያሉ እያዘኑ ተመለሱ።
#ምስኪኑ_አብርሃም ግን እነርሱ መጥተው ሳይበሉማ እኔ አልበላም ብሎ ሳይበላ ፣ሳይጠጣ ከነገ ዛሬ ይመጣሉ እያለ ሦስት ቀን በተስፋ ጠበቃቸው ማንም ግን ዝር አላለም።
በሦስተኛው ቀን በቀትር ሰዓት ከድንኳኑ በር ቁጭ ብሎ ሳለ ከመምሬ የአድባር ዛፍ ሥር ሦስት ሽማግሌ ሰዎችን ተመለከተ ሰው የተራቡ አይኞቹም በደስታ ተሞሉ ሰው መቀበል የለመዱ እጆቹ ተዘረጉ እግሮቹም ወደ ፊት ሮጡ። በቀረባቸውም ጊዜ ስለ ግርማቸው ከፊታቸው ተምበርክኮ ሰገደላቸው።
#ጥቂት_ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና ። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።
አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።
#አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። የዛሬ ዓመትም ልጅ በመስጠት ወደእርሱ በረድኤት እንደሚመጡ ቃል ገብተውለት ተሰናብተውት ሄዱ ።

ሰው ብቀህ ሰው ቀርቶብ ብዙ ጊዜ ሐዝነህ ታውቅ ይሆናል ነገር ግን ሁል ጊዜ ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣልና ሰው በቀረብህ ጊዜ ደስ ይበልህ! ሰው በዲያቢሎስ የሐሰት ወሬና ምክር ከመንገድ ሊቀር ይችላል ሰው ቀረ ብለህ ግን የቀደመ ልማድህን አትተው ሳትበላ የምጠብቃቸው ከሆነ ቢመጡም ቢቀሩም ሳትበላ ጠብቃቸው እነርሱ ቢቀሩ ሥላሴ አይቀሩምና! ግን ወዳጄ ሥላሴ ሲመጡ እኔ ሥላሴ ነኝ እያሉ ላይመጡ ይችላሉ ።

#የተቀዳደደ ልብስ ለብሰው ጎልዳፉ አንደበት ይዘው አንድ ወይም ሦስት ሆነው ሊመጡ ይችላሉ ያን ጊዜ በእነርሱ ደስ ብሎህ ለሌላው የምታደርገውን ሳታጓድል አድርገህ ደስ አሰኝተህ ላካቸው እንጂ እኔ የጠራሁት ነጭ ለባሽ የመጣብኝ ብጣሽ ለባሻ ብለት ከመቀበል ወደ ኋላ አትበል። "ተርቤ አላበላህኝም፥ ተጠምቼ አላጠጣህኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበልከኝምና " ትባለለህና #ማቴ 24÷42

“ የወንድማማች መዋደድ ይኑር። #እንግዶችን_መቀበል አትርሱ፤ #በዚህ_አንዳንዶች_ሳያውቁ_መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” #ዕብ 13፥1-2
" ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣል! "
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክ ኤል ኃ ማርያም
ሐምሌ ፯/ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ኃበ_ብዙኃን_አባታችን_አብርሃም ደግሶ ያበላቸው ዘንድ እንደ ወትሮው ይጠብቅ የነበረው ብዙ ሰዎችን ነበር።
ጸላዬ ሰናያት የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ዲያቢሎስ ግን ከመንገድ ቆሞ እራሱን በምትአት ገምሶ ደሙን አፍስሶ እያንጠባጠበ ወደ አብርሃም የሚመጡትን እንግዶች የድሮ አብርሃም ያለ መስሏችሁ ወደ አብርሃም አትሂዱ አብርሃም የድሮ ደግነቱን ትቷል።
#ይህው_እኔም እንደ ወትሮው መስሎኝ ያበላኛል ያጠጣኛል ብዬ ወደ እርሱ ብሄድ እራሴን ገምሶ ደሜን አፍሶ መለሰኝ ይላቸው ጀመር ። ሕዝቡም መቼም ደግ ሰው አይበረክትም እያሉ እያዘኑ ተመለሱ።
#ምስኪኑ_አብርሃም ግን እነርሱ መጥተው ሳይበሉማ እኔ አልበላም ብሎ ሳይበላ ፣ሳይጠጣ ከነገ ዛሬ ይመጣሉ እያለ ሦስት ቀን በተስፋ ጠበቃቸው ማንም ግን ዝር አላለም።
በሦስተኛው ቀን በቀትር ሰዓት ከድንኳኑ በር ቁጭ ብሎ ሳለ ከመምሬ የአድባር ዛፍ ሥር ሦስት ሽማግሌ ሰዎችን ተመለከተ ሰው የተራቡ አይኞቹም በደስታ ተሞሉ ሰው መቀበል የለመዱ እጆቹ ተዘረጉ እግሮቹም ወደ ፊት ሮጡ። በቀረባቸውም ጊዜ ስለ ግርማቸው ከፊታቸው ተምበርክኮ ሰገደላቸው።
#ጥቂት_ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና ። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።
አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።
#አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። የዛሬ ዓመትም ልጅ በመስጠት ወደእርሱ በረድኤት እንደሚመጡ ቃል ገብተውለት ተሰናብተውት ሄዱ ።

ሰው ብቀህ ሰው ቀርቶብ ብዙ ጊዜ ሐዝነህ ታውቅ ይሆናል ነገር ግን ሁል ጊዜ ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣልና ሰው በቀረብህ ጊዜ ደስ ይበልህ! ሰው በዲያቢሎስ የሐሰት ወሬና ምክር ከመንገድ ሊቀር ይችላል ሰው ቀረ ብለህ ግን የቀደመ ልማድህን አትተው ሳትበላ የምጠብቃቸው ከሆነ ቢመጡም ቢቀሩም ሳትበላ ጠብቃቸው እነርሱ ቢቀሩ ሥላሴ አይቀሩምና! ግን ወዳጄ ሥላሴ ሲመጡ እኔ ሥላሴ ነኝ እያሉ ላይመጡ ይችላሉ ።

#የተቀዳደደ ልብስ ለብሰው ጎልዳፉ አንደበት ይዘው አንድ ወይም ሦስት ሆነው ሊመጡ ይችላሉ ያን ጊዜ በእነርሱ ደስ ብሎህ ለሌላው የምታደርገውን ሳታጓድል አድርገህ ደስ አሰኝተህ ላካቸው እንጂ እኔ የጠራሁት ነጭ ለባሽ የመጣብኝ ብጣሽ ለባሻ ብለት ከመቀበል ወደ ኋላ አትበል። "ተርቤ አላበላህኝም፥ ተጠምቼ አላጠጣህኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበልከኝምና " ትባለለህና #ማቴ 24÷42

“ የወንድማማች መዋደድ ይኑር። #እንግዶችን_መቀበል አትርሱ፤ #በዚህ_አንዳንዶች_ሳያውቁ_መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” #ዕብ 13፥1-2
" ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣል! "
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክ ኤል ኃ ማርያም
ሐምሌ ፯/ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም