#ስለ_ታቦቲቱ የባዕዳኑ ምልከታ !
______________________________
( The sign and the seal /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ )
ግራሃም ሐንኰክ
ታላቁ የመጻሕፍ ቅዱስ ምሥጢር
________________________ ገጽ 3-4
#በዘመነ ኦሪት እስራኤልላዊያን የቃል ኪዳኑን ታቦት የእግዚአብሔር ማደሪያ በመሆኑ የሚያመልኩትና በምድር ላይ ያኖረው ምልክቱንና ማኀተሙን እንዲሁም የኃይሉ መገለጫ ነው ብለው ያምኑ ነበር።
አሥርቱ ቃላት የተፃፉባቸው ሁለት ክንድ ርዝማኔ አንድ ክንድ ተኩል ቁመትና ወርድ ያለው በውስጥና በውጭ በወርቅ የተለበጠ ነው ከተቀጠቀጠ ንፁህ ወርቅ የተሠሩ ሁለት ኪሩቤል አንዱ ኪሩብ በአንድ ወገን ሁለተኛው ኪሩብ በሌላ ወገን ክንፎቻቸውን ወደ ላይ ዘርግተው ወደ መክደኛው በትይዮ ሲመለከቱ የሚያሳይ ነው ።
#መጽሐፍ_ቅዱስና ሌሎችም ጥንታውያን መዛግብት እንደሚሉት ታቦተ ሕጉ በሚንቀለቀል ብርሃኑና እሳቱ በነቀርሳ በእባጭ ና በለምጽ የመምታት የማቃጠል ተራራዎችን ወደ ሜዳማነት የመለወጥ ፣ ወንዞችን የማድረቅ ታላላቅ ሠራዊትን የመደምሰስ ፣ከተማዎችን የማፈራረስ ኃይል አለው።
እነዚሁ ምንጮች አክለውም ታቦተ ሕጉ የአይሁዶች የእምነት መሠረት እንደሆነ ና ንጉሥ ሰሎሞንንም የመጀመሪያውን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም ያሠራው ይህንኑ ታቦት በክብር ለማኖር አስቦ መሆኑን ይገልጻሉ።
#ይሁንና_ከክርስቶስ_ልደት በፊት በአንድ ሺህና ስድስት መቶ ዓመታት መካከል በገበረው ጊዜ ይህ እጅግ ድንቅና ተአምራዊ ታቦት የትና ወዴት እንደሄደ ሳይታወቅ በመሠወሩ ጉዳዩ ለብዙ ሺህ ዓመታት እንቆቅልሽ ሆኖ ቆይቷል ማስረጃው እንደሚጠቁመው በ587ዓመቸ ዓለም የናቡ ከደ ነጾር ሠራዊት ኢየሩሳሌምን ባቃጠለ ጊዜ ታቦቱ በቦታው አልነበረም ።
በጦርነቱ የተማረኩት እስራኤላውያን ከባቢሎን ወደ ሀገራቸው ኢየሩሳሌም በ538ዓመተ ዓለም ተመልሰው ሁለተኛውን ቤተ መቅደስ በሠሩበት ወቅትም ታቦቱ በዚያ አልነበረም ። ይህም ቀደም ሲልታቦቱ በባቢሎናዊያን አለመዘረፉን ያረጋግጣል።
#በካሊፎርኒያ ዮኒቨርስቲ ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሪቻርድ ኤሊየት ፍሬድማን በ1987ይህን ጉዳይ አስመልክተው ሲጽፋ "የታቦቱ መጥፋት ከመጽሐፍ ቅዱስ አስደናቂው ምሥጢሮቾ እንደ አንዱ ይቆጠራል"ብለዋል።
ብሉይ ኪዳን መጻሕፍ ውስጥ እስከ ንጉሥ ሰሎሞን ዘመነ መንግሥት (970-931 ቅድመ ልደተ ክርስቶስ) ድረስ ከሁለት መቶ ጊዜ በላይ ስለ ታቦቱ ተጠቅሷል። ከዚህ ብልህና አስተዋይ መሪ ዘመነ መንግሥት በኋላ ግን ታሪኩ አንድም ጊዜ እንኳን ተነስቶ አያውቅም። ይህን የመሰለ ክቡርና ውድ ቅርስ በተለይም ደግሞ ሃይማኖታዊ ከበሬታ ያለው በብሉይ ኪዳን የኋለኞቹ መጻሕፍት ጨርሶ አለመወሳቱ የሚያስገርም ነው።
#በዚህ የተነሳ በዘመኑ የነበሩ ጸሐፍትና ቀሳውስት የዚህን ቅዱስ ቅርስ የመሰወር ምሥጢር ላለማሳወቅ ከፍተኛ የሆነ የመሸፋፈን ጥረት ያደረጉ አስመስሎባቸዋል። የተሰወሩ ቅርሳ ቅርሶችን የሚያስሱ ወገኖች የዚህን ታላቅ ቅርስት መሰወር አውቀው በርካታ ዘመቻዎችን ቢያካሂዱም አንዳቸውም አልተሳካላቸውም።
በ1981/የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/( #Raiders_of_the_Lost_Ark ) በሚል ርእስ ሐሪሰን ፎርድ እንደኢንዲያና ጆንሰ ሆና የተወነችበት የሆሊውድፊልም ውስጥ በአሜሪካና በአውሮፓ ለዕይታ ቀርቦ ነበር። እኔም 1983 ናይሮቢ ውስጥ ይህንኑ ፊልም የማየት ዕድሉ አጋጥሞኝ ነበር።
#ፊልሙን ካየው በኋላ የታቦቱን ዱካ አነፍንፌ የለማግኘት ሀሳብ አደረብኝ።ከጥቂት ወራት በኋላም ሀሳቤን ለመተግበሮ ወደ ኢትዮጵያ አመራሁኝ። ጉዞዬንም ወደ ትግራይ አቅንቼ የኢትዮጵያውያን ቅድስት ከተማ የምትባለውን አክሱምን ጎበኘሁ። በዚህ ጊዜ ነበር ጠባቂውን መነኩሴ ያገኘኋቸው።
( The sign and the seal /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ)
በግራሃም ሐንኰክ
............... #ይቀጥላል ..........
በቀጣይ
#ታቦቲቱ በኦሪቱ_ምልከታ
#ታቦቲቱ በአዲሳት ምልከታ
#ታቦቲቱ_በኢትዮጵያውያን እምነትና መልከታ
______________________________
( The sign and the seal /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ )
ግራሃም ሐንኰክ
ታላቁ የመጻሕፍ ቅዱስ ምሥጢር
________________________ ገጽ 3-4
#በዘመነ ኦሪት እስራኤልላዊያን የቃል ኪዳኑን ታቦት የእግዚአብሔር ማደሪያ በመሆኑ የሚያመልኩትና በምድር ላይ ያኖረው ምልክቱንና ማኀተሙን እንዲሁም የኃይሉ መገለጫ ነው ብለው ያምኑ ነበር።
አሥርቱ ቃላት የተፃፉባቸው ሁለት ክንድ ርዝማኔ አንድ ክንድ ተኩል ቁመትና ወርድ ያለው በውስጥና በውጭ በወርቅ የተለበጠ ነው ከተቀጠቀጠ ንፁህ ወርቅ የተሠሩ ሁለት ኪሩቤል አንዱ ኪሩብ በአንድ ወገን ሁለተኛው ኪሩብ በሌላ ወገን ክንፎቻቸውን ወደ ላይ ዘርግተው ወደ መክደኛው በትይዮ ሲመለከቱ የሚያሳይ ነው ።
#መጽሐፍ_ቅዱስና ሌሎችም ጥንታውያን መዛግብት እንደሚሉት ታቦተ ሕጉ በሚንቀለቀል ብርሃኑና እሳቱ በነቀርሳ በእባጭ ና በለምጽ የመምታት የማቃጠል ተራራዎችን ወደ ሜዳማነት የመለወጥ ፣ ወንዞችን የማድረቅ ታላላቅ ሠራዊትን የመደምሰስ ፣ከተማዎችን የማፈራረስ ኃይል አለው።
እነዚሁ ምንጮች አክለውም ታቦተ ሕጉ የአይሁዶች የእምነት መሠረት እንደሆነ ና ንጉሥ ሰሎሞንንም የመጀመሪያውን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም ያሠራው ይህንኑ ታቦት በክብር ለማኖር አስቦ መሆኑን ይገልጻሉ።
#ይሁንና_ከክርስቶስ_ልደት በፊት በአንድ ሺህና ስድስት መቶ ዓመታት መካከል በገበረው ጊዜ ይህ እጅግ ድንቅና ተአምራዊ ታቦት የትና ወዴት እንደሄደ ሳይታወቅ በመሠወሩ ጉዳዩ ለብዙ ሺህ ዓመታት እንቆቅልሽ ሆኖ ቆይቷል ማስረጃው እንደሚጠቁመው በ587ዓመቸ ዓለም የናቡ ከደ ነጾር ሠራዊት ኢየሩሳሌምን ባቃጠለ ጊዜ ታቦቱ በቦታው አልነበረም ።
በጦርነቱ የተማረኩት እስራኤላውያን ከባቢሎን ወደ ሀገራቸው ኢየሩሳሌም በ538ዓመተ ዓለም ተመልሰው ሁለተኛውን ቤተ መቅደስ በሠሩበት ወቅትም ታቦቱ በዚያ አልነበረም ። ይህም ቀደም ሲልታቦቱ በባቢሎናዊያን አለመዘረፉን ያረጋግጣል።
#በካሊፎርኒያ ዮኒቨርስቲ ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሪቻርድ ኤሊየት ፍሬድማን በ1987ይህን ጉዳይ አስመልክተው ሲጽፋ "የታቦቱ መጥፋት ከመጽሐፍ ቅዱስ አስደናቂው ምሥጢሮቾ እንደ አንዱ ይቆጠራል"ብለዋል።
ብሉይ ኪዳን መጻሕፍ ውስጥ እስከ ንጉሥ ሰሎሞን ዘመነ መንግሥት (970-931 ቅድመ ልደተ ክርስቶስ) ድረስ ከሁለት መቶ ጊዜ በላይ ስለ ታቦቱ ተጠቅሷል። ከዚህ ብልህና አስተዋይ መሪ ዘመነ መንግሥት በኋላ ግን ታሪኩ አንድም ጊዜ እንኳን ተነስቶ አያውቅም። ይህን የመሰለ ክቡርና ውድ ቅርስ በተለይም ደግሞ ሃይማኖታዊ ከበሬታ ያለው በብሉይ ኪዳን የኋለኞቹ መጻሕፍት ጨርሶ አለመወሳቱ የሚያስገርም ነው።
#በዚህ የተነሳ በዘመኑ የነበሩ ጸሐፍትና ቀሳውስት የዚህን ቅዱስ ቅርስ የመሰወር ምሥጢር ላለማሳወቅ ከፍተኛ የሆነ የመሸፋፈን ጥረት ያደረጉ አስመስሎባቸዋል። የተሰወሩ ቅርሳ ቅርሶችን የሚያስሱ ወገኖች የዚህን ታላቅ ቅርስት መሰወር አውቀው በርካታ ዘመቻዎችን ቢያካሂዱም አንዳቸውም አልተሳካላቸውም።
በ1981/የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/( #Raiders_of_the_Lost_Ark ) በሚል ርእስ ሐሪሰን ፎርድ እንደኢንዲያና ጆንሰ ሆና የተወነችበት የሆሊውድፊልም ውስጥ በአሜሪካና በአውሮፓ ለዕይታ ቀርቦ ነበር። እኔም 1983 ናይሮቢ ውስጥ ይህንኑ ፊልም የማየት ዕድሉ አጋጥሞኝ ነበር።
#ፊልሙን ካየው በኋላ የታቦቱን ዱካ አነፍንፌ የለማግኘት ሀሳብ አደረብኝ።ከጥቂት ወራት በኋላም ሀሳቤን ለመተግበሮ ወደ ኢትዮጵያ አመራሁኝ። ጉዞዬንም ወደ ትግራይ አቅንቼ የኢትዮጵያውያን ቅድስት ከተማ የምትባለውን አክሱምን ጎበኘሁ። በዚህ ጊዜ ነበር ጠባቂውን መነኩሴ ያገኘኋቸው።
( The sign and the seal /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ)
በግራሃም ሐንኰክ
............... #ይቀጥላል ..........
በቀጣይ
#ታቦቲቱ በኦሪቱ_ምልከታ
#ታቦቲቱ በአዲሳት ምልከታ
#ታቦቲቱ_በኢትዮጵያውያን እምነትና መልከታ
ስለ ታቦቲቱ የባዕዳኑ መልከታ
...... #ካለፈው የቀጠለ.....
#ጀምስ_ብሩስ /james bruce/
____________________________
#የዓባይን ምንጭ ወይስ #ታቦቲቱን ፍለጋ ???
_________________________________
ባለፈው ጽሑፋችን ግራሃም ሐንኰክ የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/#Raiders_of_the_Lost_Ark/ በሚል ርእስ የተሠራውን የሆሊውድ ፊልም በ 1983 ናይሮቢ ውስጥ ካየ በኋላ ታቦቲቱን ለማግኘት እንደተነሳሳ ዓይተን ነበር። አሁን ደግሞ ጀምስ ብሩስን በሽፋን ስም ታቦቲቱንና መገኛዋን ለማግኘት ያደረገውን ምሥጢራዊ ጥረት እንመለከታለን።
#ከክርስቶፈር ደጋማ ሞት በኋላ "የክርስቶስ ሠራዊት" ስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ የነበረው ጉጉት እየቀዘቀዘ ሲመጣ የስኮትላንዱ "ምሥጢራዊ የወንድማማቶች ማህበርም " ስለ ሰሎሞን ቤተ መቅደስና የቃል ኪዳኑ ታቦት የወረሳቸው አንዳንድ ምሥጢራዊ የሃይማኖት ሥርዓቶች ሲኖሩ በነዚህም ውስጥ ታቦቱ ጉልህ ሚና አለው።
በመሆኑም በዚህ ረገድ በድፍረቱና በቆራጥነቱ ስለሚታወቀውና ቴምፕላሮችን ካዳነው ከንጉስ ብሩስ ጋር የዘር ግንዱን ስለሚቆጠረውና ኢትዮጵያ በስፋት ስለጎበኘው የእስኮትላንዱ ተወላጅ ጀምስ ብሩስ መለመለ።
#ረጅሙና ግዙፉ ጀምስ ብሩስ ስኮትላንድ ውስጥ 1730 ተወለዶ ከፍተኛ ትምህርቱን በኤደን ብራ ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቀ ምሁር ነው። በትምህርቱ በኋላ ኢስት ኢንድያ በተባለ ድርጅት ተቀጥሮ ሠርቷል። ይሁንና በ1754 ባለ ቤቱ ስለሞተች በደረሰበት ብስጭት የተነሣ ከሀገር ወደ ሀገር መዘዋወር የጀመረ ሰው ነው።
የነበረው የቋንቋ ችሎታው በማጤንም በሰሜን አፍሪካ አልጀርስ ውስጥ የብሪቲሽ ቆንጽላ በመሆን እንዲሰራ ከመደረጉም ባሻገር ወደ ቅድስቲቱ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌምም ተጉዟል። በቋንቋ ረገድ አረብኛ፣ፖርቱጋልኛ እንዲሁም ጥንታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ቋንቋ (ግእዝን) ያውቅ ነበር።
#ጀምስ_ብሩስ በ1759 የግእዝ ቋንቋ ያጠናበት ዋነኛ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ላሰበው ጉዞ ዝግጅት ለማድረግ ሲሆን ከእርሱ በፊት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የነበሩ ሰዎችን የጻፏቸውንም በማንበብ በማጥናት ስለ ሀገሪቱ በቂ ዕውቀት ጨብጦ ነበር ዘዚያም 1768ወደ ካይሮ በመሄድ ታሪካዊ ጉዞዎን ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
ብሩስ ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ምን አነሳሳው? እርሱ እንደሚለው የዓባይን ወንዝ ምንጭ ለማግኘትከ1768-1773በተከታታይ የተደረጉ ጉዞዎች( Travels to Discover The Source of Nile in The Years 1768-1773 የሚል ባለ 3ሺህ ገጽ መጻሕፍ በ5 ተከታታይ ጥራዝ ጽፎል። ቢሆንም ግን ቅሉ የዓባይን ወንዝ ምንጭ በትክክል እንኳ አላወቀውም፤አልደረሰበትም የዓባይ ወንዝ ጣና እንደሆነ አስፎሯልና
#ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት ግን የዓባይ ምንጭ ግሽ ዓባይ ሰከላ እንደሆነ እና ዋነኛ ምንጩም ገነት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስን ዋቢ አድርገው ይገልጻሉ ፤ያምናሉ #ዘፍ 2÷10 -13 የሱ ዓላማ ታቦቲቱን ማግኘት እንጂ የዓባይን ምንጭ ማግኘት ስላልነበረ ነው ያን የሚያክል ባለ ብዙ ገጽ መጽሐፍ ጽፎ ከስተት የደረሰው ። በኢትዮጵያም ሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ ሦስት የመጽሐፈ ሄኖክ ቅጂዎችን ሰርቆ ኮብልሏል።
ኢትዮጵያ አ.አ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፯ / ፳ ፻ ፲ ፫
...... #ካለፈው የቀጠለ.....
#ጀምስ_ብሩስ /james bruce/
____________________________
#የዓባይን ምንጭ ወይስ #ታቦቲቱን ፍለጋ ???
_________________________________
ባለፈው ጽሑፋችን ግራሃም ሐንኰክ የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/#Raiders_of_the_Lost_Ark/ በሚል ርእስ የተሠራውን የሆሊውድ ፊልም በ 1983 ናይሮቢ ውስጥ ካየ በኋላ ታቦቲቱን ለማግኘት እንደተነሳሳ ዓይተን ነበር። አሁን ደግሞ ጀምስ ብሩስን በሽፋን ስም ታቦቲቱንና መገኛዋን ለማግኘት ያደረገውን ምሥጢራዊ ጥረት እንመለከታለን።
#ከክርስቶፈር ደጋማ ሞት በኋላ "የክርስቶስ ሠራዊት" ስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ የነበረው ጉጉት እየቀዘቀዘ ሲመጣ የስኮትላንዱ "ምሥጢራዊ የወንድማማቶች ማህበርም " ስለ ሰሎሞን ቤተ መቅደስና የቃል ኪዳኑ ታቦት የወረሳቸው አንዳንድ ምሥጢራዊ የሃይማኖት ሥርዓቶች ሲኖሩ በነዚህም ውስጥ ታቦቱ ጉልህ ሚና አለው።
በመሆኑም በዚህ ረገድ በድፍረቱና በቆራጥነቱ ስለሚታወቀውና ቴምፕላሮችን ካዳነው ከንጉስ ብሩስ ጋር የዘር ግንዱን ስለሚቆጠረውና ኢትዮጵያ በስፋት ስለጎበኘው የእስኮትላንዱ ተወላጅ ጀምስ ብሩስ መለመለ።
#ረጅሙና ግዙፉ ጀምስ ብሩስ ስኮትላንድ ውስጥ 1730 ተወለዶ ከፍተኛ ትምህርቱን በኤደን ብራ ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቀ ምሁር ነው። በትምህርቱ በኋላ ኢስት ኢንድያ በተባለ ድርጅት ተቀጥሮ ሠርቷል። ይሁንና በ1754 ባለ ቤቱ ስለሞተች በደረሰበት ብስጭት የተነሣ ከሀገር ወደ ሀገር መዘዋወር የጀመረ ሰው ነው።
የነበረው የቋንቋ ችሎታው በማጤንም በሰሜን አፍሪካ አልጀርስ ውስጥ የብሪቲሽ ቆንጽላ በመሆን እንዲሰራ ከመደረጉም ባሻገር ወደ ቅድስቲቱ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌምም ተጉዟል። በቋንቋ ረገድ አረብኛ፣ፖርቱጋልኛ እንዲሁም ጥንታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ቋንቋ (ግእዝን) ያውቅ ነበር።
#ጀምስ_ብሩስ በ1759 የግእዝ ቋንቋ ያጠናበት ዋነኛ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ላሰበው ጉዞ ዝግጅት ለማድረግ ሲሆን ከእርሱ በፊት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የነበሩ ሰዎችን የጻፏቸውንም በማንበብ በማጥናት ስለ ሀገሪቱ በቂ ዕውቀት ጨብጦ ነበር ዘዚያም 1768ወደ ካይሮ በመሄድ ታሪካዊ ጉዞዎን ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
ብሩስ ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ምን አነሳሳው? እርሱ እንደሚለው የዓባይን ወንዝ ምንጭ ለማግኘትከ1768-1773በተከታታይ የተደረጉ ጉዞዎች( Travels to Discover The Source of Nile in The Years 1768-1773 የሚል ባለ 3ሺህ ገጽ መጻሕፍ በ5 ተከታታይ ጥራዝ ጽፎል። ቢሆንም ግን ቅሉ የዓባይን ወንዝ ምንጭ በትክክል እንኳ አላወቀውም፤አልደረሰበትም የዓባይ ወንዝ ጣና እንደሆነ አስፎሯልና
#ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት ግን የዓባይ ምንጭ ግሽ ዓባይ ሰከላ እንደሆነ እና ዋነኛ ምንጩም ገነት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስን ዋቢ አድርገው ይገልጻሉ ፤ያምናሉ #ዘፍ 2÷10 -13 የሱ ዓላማ ታቦቲቱን ማግኘት እንጂ የዓባይን ምንጭ ማግኘት ስላልነበረ ነው ያን የሚያክል ባለ ብዙ ገጽ መጽሐፍ ጽፎ ከስተት የደረሰው ። በኢትዮጵያም ሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ ሦስት የመጽሐፈ ሄኖክ ቅጂዎችን ሰርቆ ኮብልሏል።
ኢትዮጵያ አ.አ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፯ / ፳ ፻ ፲ ፫