ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
" #ደስታ_ተክለ_ሃይማኖት_ተወለደ"

#የሚገቡት
እንኳን ማርያም ማረችሽ ፣
አሜን!
እንኳን ማርያም ሁለት አረገችሽ
አሜን!
#የሚወጡት
ማርያም ጭንሽን ታሙቀው
አሜን!
ማርያም በሽልም ታውጣሽ.......ይሏታል
የእመጫቷ መልስ አሜን !አሜን! የሚል ብቻ ነው። ይህ የእግዚእኃረያ ቤት ነው። ባሏ ፀጋ ዘአብ ደስታውን መቋቋም አቅቶታል ቤቷ በወዳጆቻቸው እና በጠያቂዎቻቸው እንዲሁም ባለ መውለዳቸው እንደ ኃጢያተኛ ቆጥሮ ይጠቋቆሙባቸው በነበሩ ሰዎች ተጨናንቃለች መካን ሚስቱ ወንድ ልጅን ወልዳለችና ። ለሁሉም እንደ ማዕረጋቸው ምሳ አደረጉላቸው ማጋረጃ ገልጠው እናቲቱንና ልጇን ቅቤ እስኪቀቡ የቸኮሉ ሳይኖሩ አይቀሩም ሌላው ግን ስለ አወላለዷ ለመረዳት ሰሀናቸውን ይዘው የወላዲቱ አልጋ አጠገብ ጠጋ ብለው የተቀመጡም አልጠፋም ።

#እርሷም_የእግዚአብሔርን ቸርነት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየመሰከረች ከሞተለሚ ምርኮ እንዴት ባለ ተአምር እደዳነች እያወራች ከባሏ ከፀጋ ዘአብም ጋርም ወንድ ልጅ ስለ መውለዷ አስቀድመው ዕራይን እንዳዮ እየነገረቻቸው ቀኑን በደስታ አሳለፈች ደስታ የሆነ ልጅ ወልዳለችና ።

*ስሙንስ ማን አላችሁት ?
ፍስሐ ጽዮን ( የጽዮን ደስታዋ) ብለነዋል ። ነገር ግን መላእኩ እንደነገረን ስሙ ሌላ ነው ከእናንተም የተሰወረ በልበ ሥላሴ የተጻፈ አዲስ ስም ይወጣለታል ብሎናል። "ተክለ ሃይማኖት"! ሕጻናት እንደሚያለቅሱም አያለቅስም ነበር "ቅኖች ሰዎች ሁል ጊዜ ደስ ይላቸዋል" እንደሚል

"ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለእራስህ አዘጋጀህ " አንደተባለም ሕጻኑ ፍስሐ ጽዮን በተወለደ ገና በሦስተኛው ቀን ከእናቱ እቅፍ ወርዶ "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ ሥላሴን በአንድነት በሦስትነት አመስግነ:: መዝ 9÷2

#ልጆች_የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው የእግዚአብሔር ስጦታ ሁሉ ደግሞ ደስ ያሰኛል ። ይልቁኑ እግዚአብሔር በእነርሱ አድሮ ድንቅ ሥራውን ይሰራባቸው ዘንድ ያዘጋጃቸው የቅዱሳን ሰዎች ልደታቸው ብቻ ሳይሆን እነርሱ እራሳቸው ደስታ ናቸው :: " በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ተድላና ደስታም ይሆንልሃል" ዮሐ1፥14 ተብሎ እንደተጻፈ እውነት ነው በመወለዱ ብዙዎች ደስ ብሎናል በሉቃስ ወንጌል ላይ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል በመጥምቀ መለኮት በቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ እንደሚሰኙ አስረግጦ ነግሮናል።

እነሆ ዛሬ ደግሞ እንደ ዮሐንስ በድንግልና የኖረ እንደ መጥምቁ ካህን ያውም ሰማያዊ የሆነ እንደ አዋጅ ነጋሪው በምድረ ኢትየጵያን ሁሉ እየዞረ ወንጌልን የሰበከ ለእናትና ለአባቱ እንዲሁም ለብዝዎቻችን የደስታ ምንጭ የሆነ የጽዮን ደስታዋ የተባለ ፍስሐ ጽዮን ተወለደ እነሆ እኛም እንደ ተስፋው ቃል ዳግማዊው ዮሐንስ ተወልዶልናልና ደስ አለን::
#መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰለሞን" ጻድቃን በበዙ ቁጥር ሕዝብ ደስ ይለዋል" እንዳለ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በተወለዱ ሰዓት ክርስቲያኖች ደስ ብሏቸዋል ምክንያቱም ጻድቁ ሕሙማነ ነፍስን በትምህርታቸው ሕሙማነ ሥጋን በተአምራታቸው እያዳኑና እየፈወሱ ለሕዝብ ደስታ ምንጭ ሆነዋል ያን ጊዜ ብቻም ሳይሆን ዛሬም በአፀደ ነፍስ ሳሉ ለኛ ለክርስቲያኖች የደስታችን ምንጭ ናቸው " የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለችና " ስለኛ የጽድቅ ሕይወት የሰላም እጦት የሃይማኖት ጉለት የምግባር ዝቅጠት ዕለት ዕለት ወደ ፈጣሪ እየጸለዮ ያማልዱናልና ነው #ያዕቆ 5÷16

በጻድቃን መወለድ ሕዝብ ደስ የሚለው በተወለዱበት ዘመን እና ወር ብቻ አይደለም አንዴ ጻድቃን ከተወለዱ በኃላ ሕዝብ ለዘለአለሙ ደስ ይለዋል ጻድቃን በአፀደ ሥጋም በአፀደ ነፍስም በምልጃቸው ደስ ያሰኛሉና ..... .. ልክ እንደዛሬው......

" #እኔ ግን ለዘለዓለሙ ደስ ይለኛል
ለያዕቆብ( #ለተክለ_ሃይማኖት )
አምላክም ዝማሬን አቀርባለው" #መዝ76÷9
...........ይቆየን........

የጻድቁ አባታችን የተክለ ሃይማኖት እረድኤትና በረከት በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ሁሉ ለዘለዓለሙ ቀንቶ ይኑር ....!!!

ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
በድጋሚ የተለጠፈ ጥንተ ጽሕፈቱ
ታህሳስ 22/2013ዓ/ም
#ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ ስለ ጠላትህ፥ ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት።”(መዝ 8፥2)

#ፍስሐ #ጽዮን የተባለ #ተክለሃይማኖት በተወለደ በሦስተኛው ቀን "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ እግዚአብሔርን አመሰገነ።

#ነቢየ #እግዚአብሔር #ኤርምያስ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።” (ኤር 1፥5)እንደተባለ ቅዱስ #ተክለሃይማኖት ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ነቢይ ሆኖ ለእግዚአብሔር ተለየ።


#መልአከ #ብርሃን ቅዱስ #ገብርኤል ስለ ቅዱስ #ዮሐንስ መጥምቅ“በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤”( ሉቃስ 1፥15) እንዳለ #ተክለሃይማኖት ጻድቅ ከዓለምና ከምኞቷ ሁሉ የተለየ ፤ በጌታም ፊት ታላቅ የተባለ ፤ መንፈስ ቅዱስም የሞላበት ነው።ዳግመኛም መልአክ “ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”(ሉቃ 1፥14) እንዳለ በፍስሐ ጽዮን (በጽዮን ደስታ) በ #ተክለሃይማኖት መወለድ ለጊዜው አባቱ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና እናቱ ቅድስት #እግዚእ ኃረያ ተደስተዋል ፤ ለፍጻሜው ግን ጽዮን የተባለች ቅድስት #ቤተክርስቲያን ተደስታለች።

#ቅዱስ #ጳውሎስም ስለ ራሱ “ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም”(ገላ1፥15-16) እንዳለ አባታችን #ተክለሃይማኖት በጸጋ #መንፈስ #ቅዱስ ለስብከተ ወንጌል ገና በማኅፀን ተጠራ።

#ጌታም በወንጌል ስለ እነ #ተክለሃይማኖት እንዲህ አለ “በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ”(ማቴ 19፥12)

#እንኳን አደረሳችሁ!!!

#ታኅሣሥ 26 /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
" |አዳም ከመሬት ተወለደ፤ ሔዋን ከአዳም ጎን ተወለደች፤ ቃየል ከአዳምና ሔዋን ተወለደ። ሦስቱ አልጠቀሙኝም። #እኔ_የተጠቀምኩት_ክርስቶስ_ከድንግል_በመወለዱ ነው። "

#አባ_ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ |(1357-1417)
#መልካም ገና /ጌና

ታኅሳስ 28/2017 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
#ሁለተኛውን_ልደቱን_አስደናቂ_አደረገው!

📍እግዚአብሔር እልፍ ድንቅ ነገሮችን ትላንት አድርጓል፣ ዛሬም እያደረገ ነው ለወደፊትም ያደርጋል። ከድንቆች በላይ ግን ምንድነው ከተባለ ይህ ነው።

 አምላክ ሰው የሆነበት፣ ሰውም አምላክን የሆነበት፣ ረቂቁ
ግዙፍ የሆነበት፣ ልዑሉ ትሑት የሆነበት ይህ ሁለተኛው ልደቱ
እጅግ ይደንቃል።

 ታላቅነቱን በታናሽነት፣ ኃያልነቱን በደካማ ሥጋ ሰውሮ
መምጣቱ በጣሙን ይገርማል።

 ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላክ በማኅፀነ ማርያም መወሰኑ
እጅግ ያስደንቃል።

 ሰማይ ዙፋኑ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆነችለት አምላክ የዕለት
ጽንስ ሆኖ በማኅፀነ ማርያም ማደሩ በጣሙን ያስደንቃል።

 የአስራ አምስት ዓመት ብላቴና እንድትሸከመው መፍቀዱ እጅግ ያስደንቃል።

 የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ተብሎ መጠራቱ እጅግ
ያስደንቃል።

 እኛን ወደሰማይ ሊያወጣ እርሱ ወደመሬት መውረዱ በጣም
ያስደንቃል።

 እኛን ከክብር ዙፋን ላይ ሊያስቀምጥ እርሱ በውርደት በረት
መጣሉ እጅጉን ያስደንቃል።

 እኛ ከመላእክት ጋራ እንድንዘምር እርሱ ከእንስሳት ጋራ በበረት
ማደሩ ያስደንቃል።

 ባለዙፋን ባለበረት ሲሆን ማየት እጅግ ያስደንቃል።

 ኃያል አምላክ ሕጻን ሆኖ መወለዱ ያስደንቃል። (ኢሳይያስ ሕጻን ተወለደልን አለ ማቴዎስ ደግሞ የተወለደው ንጉሥ ነው ይለናል። ሰብአ ሰገል ለዚህ ዘውዳቸውን አንሥተው ለሕጻኑ ሰግደዋል። በሚታይ ዕድሜ ቢሆን ኖሮ አይታሰብም አይሞከርም ነበር።)

#በሚታይ ሕጻንነቱ ግን ዘለዓለማዊ አባትነት አለው፣
#በሚታይ ሕጻንነት ዘለዓለማዊ ንግሥና አለው፣
#በሚታይ ሕጻንነት ዘለዓለማዊ አምላክነት ስላለው ዘውዳቸውን አንሥተው ለሕጻኑ ሰገዱለት።

 ኃያል አምላክ ሕጻን ሆኖ መወለዱ እጅግ ያስደንቃል።

 የዘለዓለም አባት "አንድ" ተብሎ ዘመን ሲቆጠርለት አረ
በጣሙን ያስደንቃል።

 ከአንዲት ታናሽ ብላቴና ምግብ ሲለምን ማየት በጣም
ያስደንቃል።

 ከአንዲት ታናሽ ብላቴና ምግብን ፈልጎ ማልቀሱ እጅግ
ያስደንቃል። እግዚአብሔርም አለቀሰ ሲባል እጅግ ያስደንቃል።

 የእርሱ ማልቀስ የእርሷ እሹሩሩ ብሎ ማባበል እጅግ በጣም
ያስደንቃል።
.
.
.
.

አባ ጊዮርጊስ "የመጀመሪያውን ልደቱን (ከአብ ያለ እናት) ረቂቅ አደረገው። ሁለተኛውን ልደቱን (ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት) አስደናቂ አደረገው።" ብሎ እንደተናገረ በእውነት ይህ ሁለተኛ ልደቱ እጅጉን ድንቅ ነው!!

ምድር እስከ ተዘረጋችበት ውኃም እስከፈሰሰበት ድረስ ያላችሁ በክርስቶስ ክርስቶሳውያን የሆናችሁ ሁሉ እንኳን ለልደቱ ለእግዚእነ አደረሳችሁ።
መልካም በዓል!!🤲🤲



©️ከ ስምዓ ጽድቅ አርአያ የፌስ ቡክ ገጽ የተወሰደ
#ኖላዊ ወበግዕ#(እረኛም በግም)

#ትጉህ #እረኛችን #አማኑኤል ከድንግል #ማርያም ተወልዶ በበረት ተኛ።ቅዱስ ዳዊት “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”(መዝ 121፥4) ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ በበረት ውስጥ ተኛ።(ሉቃ 2:7)

#እረኛ ሲሆን በግ ፣ በግ ሲሆን እረኛ ነው።መልአኩም በጎቹን (ምዕመናንን) ተግቶ የሚጠብቅ የጌታን ልደት ያበሠረው መንጎቻቸውን ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች ነው።በእረኛነቱ ይጠብቀናል ፤ በበግነቱም በመስቀል ላይ ተሠውቶልናል (ዮሐ 1:29)።

#የጌታችን እረኛነት ግን ልዩ ነው።እረኛ በጎቹን አስብቶ ኋላ ይበላቸዋል ወይም ሽጧቸው ጥቅም ያገኛል።ይህ እረኛችን ግን ስለ ራሱ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
(ዮሐ 10፥11) ሲል ተናግሯል።

#እርሱ ከሚገኝባት የበጎች በረት (ከቤተክርስቲያን) ያልሆኑ ሌሎች በጎችን አስመልክቶ ሩኅሩኅ እረኛ #መድኃኔዓለም እንዲህ ይላል “ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”(ዮሐ 10፥16)

#በዓሉን አከባበራችን ሁሉ የተዘክሮተ #እግዚአብሔር ሊሆን ይገባዋል።ስንበላ እውነተኛ መብላችን ክርስቶስ መወለዱን ፤ ስንጠጣም እውነተኛ መጠጣችን አምላካችን መወለዱን ፤ ስንለብስ ስናጌጥም እውነተኛ ልብሳችን ክርሰቶስ መወለዱን ልናስብ ይገባናል።ይህ ካልሆነ ግን ጌታ ለእኛ ያደረገውን ውለታ የዘነጋን ውለተ ቢሶች እንሆናለን።
በዓሉን በዓል የሚያደርገውም የጌታን የፈቃድ ተዋርዶውንና ውለታውን እያሰብን ካመሰገንን ብቻ ነው ፤ እንጂ የምግብና መጠጡ ጉዳይ አይደለም።ይህን #የጌታችን ውለታ ከሚያረሳሱ የቴሌቪዥን መርኃግብሮችን ሁሉ ልንጠነቀቅም ይገባናል!!!

#በዓለ #ልደቱን በተዘክሮ እግዚአብሔር እንድናከብር አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን!!!

#በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ
#ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ!!!

ልደተ #እግዚእ / 2017 ዓ.ም
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው

በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
#ዛሬ #እግዚአብሔር “ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።” (ዘፍ 11፥7) ብሎ ለራሱ በብዙ ቁጥር ተናግሮ ሦስትነቱን ገልጧል።ስለዚህም ቅድስት #ሥላሴ ብለን እናከብራለን።ቅድስት #ሥላሴ ማለትም ልዩ ሦስትነት ማለት ነው።

#እግዚአብሔር ያንጻል #እግዚአብሔር ያፈርሳል

#“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።”( ዘፍ1፥1) በሚለው ቃል የእግዚአብሔርን አናፂነቱን ተረዳን ፤“እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተው።"ዘፍ 11፥8) በሚለው ቃልም የእግዚአብሔር አፍራሽነቱን ዐወቅን።የሰናዖርን ግንብ የገነቡ ሰዎች ዓላማቸው እግዚአብሔርን ከንግሥና ዙፋኑ አውርዶ ለመንገሥ ነበር።

#እነዚህም ቅዱስ #ዳዊት"የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜ በቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል።"(መዝ 2:2-5) ብሎ የተናገረላቸው ዓይነት ሰዎች ናቸው።ዓላማቸውም #የእግዚአብሔር አምላክነቱን (ገዢነቱን) ከላያቸው ላይ መጣል ነው።ነገሩ ግን አስቂኝ ነው።ሰው የማይሆንለትን ነገር ሲሞክር ቂልነቱ ያስቃል።

#የሰው ፍላጎት በአጭሩ #እግዚአብሔርን መሆን ነው።የአዳም ምኞት ፣ የባቢሎን ሰዎች ፍላጎት፣ የአላውያን ነገሥታት ጉጉት ፣ አሁን ያለን ሰዎች ፍላጎትም አምላክ መሆን ነው።አምላክ የመሆን ፍላጎታችን ማሳያዎችም አሉ።መውሰድ #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንሰርቃለን ፤ መግደል #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንገድላለን ፤ መፍረድ #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንፈርዳለን።

#ቅድስት #ሥላሴ በዛሬው ዕለት የባቢሎንን ግንብ እንዳፈረሰ የእኛንም የትዕቢትና የኃጢአት ግንብ በቸርነቱ አፍርሶ ፤ ሰውነታችንን ለእርሱ ማደሪያነት ያንጽልን።

#ጥር #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
#ከሕግ በላይ ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ንጽሕት ነሽ።ከአንቺ በቀር መርገመ አዳም ወሔዋን የቀረለት የለምና።
#ከሕግ በላይ ጌታን በድንግልና ፀንሰሽ በድንግልና ወለድሽ።ድንግልም እናትም ሆንሽ፤ያውም ወላዲተ አምላክ
#ከሕግም ውጪ መርገም ሳያገኝሽ ኃጢአት ሳይኖርብሽ ሞትን ቀመስሽ።ሞት የኃጢአት ውጤት ነውና!!!
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ #ለማርያም የዐፅብ ለኩሉ"
"ሞትስ ለሟች ይገባል ፤ #የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል"

#ኃጢአትን ሳይሠሩ ሞትን መቅመስ(ሞተ ሥጋም ቢሆን በቀደመው በደል የመጣ ነውና) ፤ ደግሞ ኃጢአትን ሠርቶ #በእመቤታችን የዕረፍት ቃልኪዳን ተማምኖ ዝክር አድርጎ ከዳግም ሞት መዳን!!!
#የእግዚአብሔር ፍርዱ ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!

#የእመቤታችን በረከቷ ይደርብን፤ፍቅሯ አይለየን!!!

#አስተርእዮ #ማርያም / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው

በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏