ዐውደ ምሕረት
3.66K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
https://youtu.be/G9pLnjHKh5I

ልዩ የዓውደ ዓመት አበባዮሽ መዝሙር በአዲሱ የዓውደ ምሕረት ቻናል ላይ እነሆ ብለናል። ሰብስክራይብ በማድረግ ይቀላቀሉንና የተለያዩ ትምህርቶችንና ያሬዳዊ መዝሙሮችን ያግኙ።
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (toolkit)
ዘመኑን ዋጁ.mp3
1.2 MB
#ዓውደ ስብከት

"ዘመኑን ዋጁ" ኤፌ 5:16

በወንድማችን #ዲያቆን #እስጢፋኖስ ደሳለኝ


👇👇👇👇👇👇
👉 @AwediMeherit 👈
👉 @AwediMeherit 👈
👉 @AwediMeherit 👈
👆👆👆👆👆👆
https://m.youtube.com/watch?v=grgYCSU1zQ8

ሳምንታዊ የቀጥታ መርኃ ግብር በዓውደ ምሕረት ዩቲዩብ ቻናል። ሰብስክራይብ በማድረግ አብረን እንማር።
"፤ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል። " ማቴ 2÷13

የቅዱሳን ዝክር በማሰብ በመናገር እና በመተግበር ሊከበር ይችላል::ተዘከሩ ለመኳንንቲክሙ ዘነገረክሙ ቃለ እግዚአብሔር ::የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን #አስቡ ዕብ13÷7
አስቡ ማለቱ በዕሊናቸው ስራቸውን እፁብ እፁብ በሉ ማለቱ ነው ወረድ ብሎም በማሰብ ብቻ ሳይሆን እነርሱ በኑሯቸው የሰሩትን እናንተም በማየት በተግባር ተግብራችሁ ምሰሏቸው ይለናል ::የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው" እንዲል ከየት አግኝተን እንምሰላቸው ቢሉ ስለ እነርሱ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን በመጠየቅ ቅዱሳን መጻሕፍት በማገላበ እናገኛቸዋለን::"፤ ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፥ ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ፤። " ኢሳ 5÷2 እነ አብርሃምን ከወዴት አግኝተው ይመልከቱ ቢሉ የነ አብርሃምን ታሪክ ጠይቀው መጻሕፍት ጠቅሰው ይወቁ ሲል ነው እንጂ በዘመን ተዳርሰው አይደለም
በቅድስና ሕይወት ከተመላለሱ በዕሊና በማሰብ በአንደበት በመናገር በተግባር ከመዘከር ከሚታወሱ ቅዱሳን መካከል ሰማዕታት አንደኖቹ ናቸው::
ቅድስት አርሴማ አትናስያ የምትባል እናት ነበራት ልጅ በማጣት ለረጅም ዘመን ታዝን
ታለቅስ ነበር በኃላም እግዚአብሔር ልመናዋን ሰማት ይህችን ክብርት ቅድስት
ልጅንም ሰጣት፤ቅድስት አርሴማ ጥር 6 ነው የተወለደችው፤15 ዓመት ሲሆናት
ሊያጋቡአት አሰቡ እርሷ ግን ይህን አልወደደችም፤ በደናግል ገዳም ገብታ
በተጋድሎ መኖር ጀመረች። ከዚህ በኃላ እንዲህ ሆነ ከሃዲው ንጉስ ዲዮቅልጥያኖስ ሊያገባት ወደደ ቅድስት አርሴማ ግን ከደናግሉ ጋር ሸሽታ ወደ አርማንያ ሄደች በዚያም በበርሃ ለጥቂት ቀናት ተቀመጠች በኃላ ላይ ድርጣድስ የሚባል አገር ገዢ በበርሃ እንደሚኖሩ ሰማ ወታደሮችንም ልኮ
አስመጣቸው፤ የቅድስት አርሴማን መልክ በተመለከተ ጊዜ ፈዞ ደንዝዞ ቀረ የፊቷ ውበት እጹብ ድንቅ፤ ግርማዋ የሚያስደነግጥ ልብ የሚያርድ ነበርና፤ስለዚህም ሊያሰቃያት አልደፈረም በእንክብካቤ በሰገነት ላይ አኖራት፤ ሌሎቹን ግን ለጣአት እንዲሰግዱ ገረፋቸው፤ ቅድስት አርሴማ እኔንም አሰቃዩኝ እያለች አምርራ ታለቀስ ነበር። ድርጣድስ ብዙ ጊዜ ሊሸነግላት ሞከረ እርሷ ግን ትዘልፈው ጣኦታቱንም ትረግም ነበር፤ እርሷ ጸንታ ደናግሉን ታጸና ነበር ትመክራቸው ታረጋጋቸው ነበር፤ ድርጣድስ ሽንገላው እንደማያዋጠው
በአወቀ ጊዜ ማሰቃየት ጀመረ፤ በመጨረሻም ከብዙ ስቃይ በኃላ መስከረም
29 ቀን አንገቷን በሰይፍ ተከላ ሰማዕትነትን ተቀበለች:: ይህችን ቅድስት ሰማዕትን ታድያ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዕሊና ታስባታለች በትምህርቷ(በንግግሯ)ታነሳታለች በተግባሯ አርያ ታደርጋታለች::


በወንጌል አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው።
ደቀ መዛሙርቱም ይህ ጥፋት ምንድነው ሽቶ ተሽጦ ለድሆች በተቸረ ነበር አሉ

እርሱ ግን ድሆችስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር አሉ አላቸው: ቀጥሎም :"፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል። " (የማቴዎስ ወንጌል 26: 13) ይህች ሴት ዘመኗን ሙሉ ስትዘሙት የነበረች ሴት ነች ተፀፅታ ንስሐ ገብታ ባፈሰሰችሁ እንባና ሽቶ ይህ ቃል ኪዳን ከተሰጣት በክርስቶስ ፍቅር ልቦናቸው ተቃጥሎ እንደ ሴቲቱ ሽቶ ሳይሁን የከበረ ደማቸውን ያፈሰሱ ሰማዕታት ምን ያክል ቃል ኪዳኑ ይጸናላቸው ይሁን?

አዘጋጅ #ተርቢኖስ_ሰብስቤ


ከሰማዕቷ ረድኤት በረከት ይከፈለን አሜን!

📢📢📢📢📢📢📢📢📢
📢 @AwediMeherit 📢
📢 @AwediMeherit 📢
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
#እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ #እንደ_ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ18፥3

"ቃል ይቀትል ትርጓሜ ያድን"
"ቃል ይገላል ትርጓሜ ግን ያድናል"

#መታሰቢያነቱ :- ትርጓሜ ለምኔ ለሚሉ ወንድሞች ይሁን !
ውድ የዓውደ ምሕረት የቴሌግራም ተከታታዮቻችን ዓውደ ምሕረት በተለያዩ መንፈሳዊ ትምሕርቶች ስናስተላልፍ መቆየታችን ይታወቃል አሁንም በማሰስተላለፍ ላይ እንገኛለን ሆኖም ግን በእናንተው በመጣልን አስተያየትና በያዝነው ዕቅድ መሰረት ዓውደ ምሕረት በዩቱብ ቻናል መጥተናልና ሰብስክራይብ ላይክ ሸር በማድረግ ከዓውደ ምሕረት ጋር እንዲሆኑ በአክብሮት እንጠይቃለን
እግዚአብሔር ያክብርልን፡፡
https://youtu.be/grgYCSU1zQ8
#ስለ ሆሳዕና ከተማ የሆነ ነገር በሉ እንጂ?


“ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ?”
ሐዋ9፥4
ክርስቲያኖችን ማሳደድ ክርቶስን ማሳደድ ነው !። ይህ ደግሞ የመውጊያውን ብረት እንደመቃወም የሚብስ ነው።
# ክርቶሳዊያን በሆሳዕና ሲከለከሉ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም ያኜ በክርስቶስ ዘመን የተጀመረ ነው::
# ወደ_ደብረ ዘይት ቍልቍለትም አሁን በቀረበ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ሁላቸው ደስ እያላቸው ተአምራትን ሁሉ ስላዩ በታላቅ ድምፅ # እግዚአብሔርን ሊያመሰግኑ ጀምረው ነበር። "በጌታ ስም የሚመጣ ንጉሥ የተባረከ ነው፤ በሰማይ ሰላም በአርያምም ክብር" አሉ ። ይህን ጊዜ ከሕዝብም መካከል #ከፈሪሳውያን_አንዳንዱ፦መምህር ሆይ፥ደቀመዛሙርትህን ዝም እንዲሉ ገሥጻቸው አሉት። # እርሱም መልሶ፦እላችኋለሁ፥ እነዚህ ዝም ቢሉ እንኳ ድንጋዮች ይጮኻሉ አላቸው። ሉቃ19÷37-40

#ገዢዎቻችን ባልሰማ ዝም ቢሉም እንኳ #በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ እርሱ የተባረከ ነው እያለች ሆሳዕና ዛሬም ትጮሃለች !
የዛሬው ባለ ታሪክ ደግሞ ሌንጌኖስ ይባላል
ዘመነ መስቀልን በማገናዘብ የተመረጠ ወቅታዊ ታሪክ ነው።


#ከዮናናውያን ወገን ሲሆን የሮማ ወታደር ነው፡፡ ጲላጦስ ጌታችንን እንዲሰቅሉት ለአይሁድ አሳልፎ ሲሰጠው ይህ ለንጊኖስ ከጲላጦስ ጭፍሮች ውስጥ አንዱ ስለነበር የጌታችንን ሥቃይ አይቶ በክፉ ግብራቸው ላለመተባበር ብሎ ከአካባቢው ሸሽቶ ሄደ፡፡ በዕለተ አርብ ግን ሮማውያን በጌታችን መከራ ያልተባበረውን ሁሉ እንደ ንጉሥ ጠላት ስላዩት መድኃኔዓለም ክርስቶስ በመጨረሻዋ ሰዓት ‹‹ተፈጸመ›› ካለ በኋላ ለንጊኖስ ወደ ቀራንዮ ተራራ ወጣ፡፡ በሁለት ወንበዴዎች መካከልም ተገርፎ የተሰቀለውን አይቶ ልቡ በአዘን ተመላ በሀገራቸው የተገረፈ እንደማይሰቀል የሚሰቀልም እንደማይገረፍ ያውቅ ነበርና የክርቶስን የተሰቀለ ገላ ሲያይ የግርፋቱን ሰንበር አስተዋለ ያለ ሕግም በግፍ ገርፈው እንደሰቀሉት አወቀ ። ሮማውያኑም የሁለቱን ሽፍቶች አጥንቶች ሲሰብሩ ሌንጌሎስም አልተባበረንም ብለው ይቃወሙኛል ንጽህ እንደሆነና በግፍ እንደተሰቀለ ባውቅም እኔም አንዳች ነገር ማድረግ አለብኝ ብሎ ሀሰበ አስቦም አልቀረ ለንጊኖስ ያላመነበትን ነገር አደረገ ደግሞ ከሞተ መቼም አልጎዳውም ብሎ አስቦ የጌታችንን በጦር ጎኑን ወጋው፡፡ በዚያም ጊዜ አንድ ዐይኑ ዕውር ነበርና ከጌታችን ከግራ ጎኑ ውኃና ደም ሲወጣ የታወረች ዐይኑን ቢነካው ዐይኑ በራችለት፡፡ ሆኖም ግን ዐይነ ልቡናው በሰራው ሥራ በተራዋ በጸጸት ታወረችበት ።


#ውድ የመርሐ ግብር ታዳሚዎቻችን እርሶ ሮማዊውን ወታደር ሌንጌኖስን ቢሆኑ ምን ያደርጉ ነበር?
👉እኔ ሥራዬ ነው የሰራሁት ጥፋት የለብኝም ይላሉ? ወይስ
👉ንጽሕናው ከገባኝ ሥራዬን እንኳ እለቅ ነበር ይላሉ? ወይስ ደግሞ
👉ከሰዎች ከምለይ ሰዎችም ከሚያገሉኝ የማላምንበትንም ነገር ቢሆን ሰርቼ ጌታዬን እወጋዋለው ይላሉ?

👩‍🚀ሮማዊው ወታደር ምክሮቻችሁን ይጠብቃል👨‍🚀

እርሶ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE

ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit