ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ዐውደ ምሕረት
Photo
#የአምላካችሁን_የእግዚአብሔርን_ቃል_ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት።”
#ኢያሱ 3፥3
ዐውደ ምሕረት
Photo
#አስተርዮ_ማርያም
______

ያቢሎስን ሥራ ያፈርስ ዘንድ #የእግዚአብሔር_ልጅ የተገለጠባት ምክንያተ ድኂን #ወላዲተ_አምላክ_ቅድስት_ድንግል_ማርያም 1 ዮሐ 3÷8-9

" #ቃል_ከአብ ያለ ድካም ወጣ #ከድንግልም ያለ ሕማም ተወለደ"
_ #ቅዱስ_ኤፍሬም ሶሪያዊ __
#የአድዋ_ተራሮች ትዝብት
_____

ቲሺ ምናለ ከዚህ ንበር ትንሽ ቀቅ ብዬ በተፈጠርኩ ካድማሱ ባሻገር እንደ ሰንሰለት ከተያያዙት ከአድዋ ተራሮች በመጠኑ ተለቅ የሚለው የአንዱ ተራራ የምሬት ንግግር ነበር

#እንዴ ይህ እኮ እኛ የተፈጠርንበትን የነጻነት ጀንበር የተፈነጠቀበት የኢትዮጱያ መሬት ነው ይህን መሬት ስንቱ ተራራ ሊፈጠርበት እንደሚመኝ እረስተህው ነው ።

ሌላኛው ከግራ ያለው ተራራ ቀበል አርጎ የዓለምና የአፍሪካ ስመ ጥር ተራሮች ኤቨረስትና ኪሊማንጃሮ እራሳቸው ረጃጅሞች ስመ ጥር ተራራሮች ሆነው ከሚታወቁ ይልቅ እዚህ ቦታ ተፈጥረው የጥቁር ሕዝብ ድልን የሰውልጅ እኩልነት የነጻነት ቀንዲል መለኮሰን ዕብሪተኝነት አንገት ሲደፈ ጨዋነት ሲረታ ቢያዮና የጀግኞች የዐይን መስክር ቢሆኑ የበለጠ ደስተኛ ይሆኑ ነበር። አንተ እዚህ በመፈጠረህ ታማርራለህ

#ግዙፉ ተራራ ከመካከላቸው ሆኖ ዐይ የልጅ ነገር እሱ መቼ ጠፋኝ " ለቀባሪው አረዱት አሉ " እናንተ በዚህች ምድር ከመፈጠራችሁ በፊት እኔ ቀድሜ ነበርኩ አድዋ ጦርነት እራሱ ከእናንተ የተሻለ ቁመናና ርዝመት ያለኝ በመሆኔ ከናንተ በተሻለ የጦርነቱን ሙሉ እንቅስቃሴ ለማየት ታድያለው የአባ ነብሶ ድፍረት መድፉን ለብቻ ሲያጓራው ፣የገበየው ደረት ደልብጦ መግባት ፣የጣይቱ ብልሐት፣ የምኒልክ ጽናት የሰማዕቱ እርዳታ ሁለም እንደ ትላንትና ሆኖ በሐይኔ ሕሊናዬ ተሰሎ ተቀምጧል መቼም ልረሳው አልችልም ያቺ የኃላ ደጀን የነበረች አዝማሪ ጻድቄ እራሱ ሳትቀር ከነ ግጥሞቿና ከነ አበረታች መሰንቆዋ የዕለት ለዕለት ትዝታዬ ነች እንዲያውም አንድ ጊዜ ጠላት በአድዋ ሥላሴ በኩል ገፍቶ ሲያይል "የአድዋን ሥላሴ ጠላት አረከሰው ገበየው በሞቴ ግባና ቀድሰው " ብላ ገጥማ ነበር።
ታድያ ይህን ያክል የምታስታውሰው ከሆነ ምን ቢመር ነው ከዚህች የነጻነት ድንበር ውጪ መፈጠርን የፈለክ? ሆ ሰው እንዴት ሰው አልኩ እንዴ ተራራ እንዴት በተመረጠ መሬት በነፃነት ሀገር ተፈጥሮ ሲያበቃ ለምን በዚህ የነፃነት ሀገር ተፈጠርኩ ብሎእንዴት በከንቱ ያማርራል?
#በከንቱ_አይደለም ማማረሬ እውነት ይዤ እንጂ ። በግራና በቀኝ ያሉት በመጠናቸው አነስ የሚሉት ተራሮች በተመሳሳይ ሰዓትና ቃል ማለት አልገባንም? አሉ።

ከመካከላቸው መሆኑ እንደፈለጉ ጥያቄ እየጠየቁ እንደ ገና ዳቦ በጥያቄ ሊጠብሱት የተዘጋጁ አስመስሏቸዋል። ከዛ አንደኛው ተራራ ከአድመኝነት መንፈስ ወጣ ለማለት ብሎ ሀሳቡን ለመረዳት ትንሽ ፋታ ከወሰደ በኋላ እስቲ በል ንገረን ምንድነው ይህን ያክል ቁጭት አሳድሮ የተፈጠርክበትን የነፃነት ምድር ለመጸየፍ ያበቃህ? ሲል በእርጋታ ጠየቀው
እሳት አመድ ወልዶ ሳይ እንዴት የቁጭት ቆፈን አይውረሰኝ? በዕድሜ አንጋፈ አዛውንት የሚመስለው ተራራ ሳግ እየተናነቀው እንዳይታወቅበት ጉረሮውን እያጸዳ ቀስ ብሎ ቁጭቱን ሊያስረዳቸው ጀመር።
#በዚህ ቦታ በኖርኩበት በእስኳሁኑ ዕድሜ እንዲህ ዐይነት ውርደትና መሸማቀቅ ደርሶብኝ አያውቅም ። ጥንት ኢትዮጵያዊያን አርበኞች ጠላትን በዚህ ሥፈራ ድል ሲነሱ ለ ሀገር ለድንበር ለሃይማኖት ለአንድነት ለአንድ ሕዝብ ብለው ዋጋ ፍለው ደም አፍስሰው ሥጋ ቆርሰው አጥንት ገብረው ባለፉበት በዚሁ ሥፍራ በገደሉበት ሥፍራ ሲገዳደሉ ነጻ በወጡበት ሰፈር ምርኮ ሲገቡ ድል በነሱበት ሀገር ድል ሲነሳሱ ከማየት ሌላ ምን ውርደት አለ? የዘንድሮስ አድዋ ፋሽሽት ኢጣሊያንን ወይስ የእናት ልጅ ወንድምን ድን የነሳንበት በዓል ነው ብለው ሊያከብሩት ነው ?

የጀግኖች ደም ዋጋ ቢስ ሲሆን ከማየት ሌላ ምን አስቆጪ ነገርስ ይኖራል ? እነሱስ አንዴ ለሀገር ለድንበር ለነፃነትና ለሃይማኖት የሚገባቸውን ዋጋ ከፍለው በክብር አርፈዋል ይብላኝ እንጂ ለኔ ሞት ወስዶ ለማይገላግለኝ ግዑዝ ነው ይሉኛል ምንም የማይሰማኝ ንግግሬን ማድመጥ ያልቻሉ እነሱ መሆናቸው ማን በነሱ ቋንቋ በነገረልኝ

#ያኔ ቋንቋ ብሔር ዘር ሳይለያቸው እንደ አንድ ልብ መካሪ አንደ አንድ ቃል ተናጋረ ሆነው ጠላትን ያስጨነቁ ዛሬ ብሔሬ ቋንቋዬ ተባብለው ሲተላለቁ በዚሁ ሥፍራ ሳይ ለምን አልበግን

ደሞኮ ቋንቋውም ቢሆን በቅጡ የአባቶቻቸውን ቋንቋ አቀላጥፈው አያውቁትም ሁሉም ባለ ቋንቋ ነኝ ባይ ከእንግሊዘኛ ሳያዳቅል ማን በቅጡ የሚናገራቸው አለ እስቲ ቆንጆ ኦሮምኛ ተናጋሪ አምጡልኝ እስቲ ንጹሑ አማርኛ አንደበት ያለው ፈልጉልኝ እስቲ ትግርኛን አቀላጥፎ የሚያወራ የሰሜን ሰው ፈልጉልን የለም አታገኙም ። ለመጠፋፋትና ለመገዳደል ሲሆን ግን ብሔሬ ቋንቋዬ ይባልልኛል አስቀድመህ በቅጡ ውረስወ እስቲ ።

#ሁለቱ ተራሮች ምንም ሊመልሱለት አልቻሉም ከልብ ያልኖረ እውነት ከየት ይገለጣል።

እሱማ እውነትህን ነው በሚል በተጸጸተ አስተያየት ከግራም ከቀኝም ተመለከቱት

የላሊበላ መቅደስ ሰሪዎች እናንተ አይደላችሁም ቢሆንማ ኖሮ ሌላም አስደማሚ የኪነ ሕንጻ አብዝታችሁ ሰርታችሁ ከድኅነት አረንቋ በወጣችሁ ነበር የሚሉን የቀደመ ሥልጣኔያችንን ሊያስክዱን የሚዳዱ የነጭ እባቦች ከንፈር አደዋም የናንተ የኢትዮጵያዊያዊያን ድል አይደለም ቢሆንማ ዛሬ አንድነታችሁን ምን ፈታው መተባበራችሁን ማን ወሰደው ቢሉን ምን እንመልስ ይሆን?
በዚህ የመበላላት መንፈስ ውስጥ ሆነን የአፍሪካዊያን የነፃነት ቀንዲል የተለኮሰው ከዚህ ሀገር በነዚህ ተራሮች ሥር ነው ቢባል ማን ያምናል?

#አንዱ ወጣት እግር የሆነ ተራራ ይህማ አይሆንም እኔ አንደበት አውጥቼ እንደ ቢታንያ ድንጋይ አድዋ የኢትዮጵያዊያን ድል ነው ስል ጮክ ብዬ እመሰክራለዋ ሲል ሌላላው ቀበል አርጎ አዎ እኔም ዝም አልልም አድዋ ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ የጥቁር ሕዝበ ሁሉ ድል ነው ሲል አሳቡን ተጋራው
አንጋፈው ተራራ ግን ከሰማይ ደመናትን ሰብስቦ እንደ ጋቢ ተከናንቦ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል በሽሙጥ ተከናነበ ቀጠል አርጎም አንድነቱና ህብረቱ እንዲመጣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ካልጣረ እመሆኝ ወደፊት እኔ እንዳልኳችሁ ሳይሆን አይቀርም በርግጥ ሁሉም ነገር ከትምህት ቤት መማር አይቻልም የዕድሜ ባለ ፀጋ ሲነግራችሁ ግን እህ ብላችሁ ብሰሙ መልካም ነው ዕድሜ እዚህች ዮኒቨርስ ላይ ያልተገነባና የማይገነባ ትልቅ ዮኒቨርስቲ ነው ።

እናንተ ይህ ትላላችሁ አክሱም፣ ጀጎል፣ አባይ ፣ጣና ሁሉ ሳይቀር ከሀገር ሊወጡ ሲሉ አገኘዋቸውና ስለምን ይህችን ምድር ለቃችሁ ትወጣላችሁ ስል ሞገትኳቸው ሲሉ የነበሩ ኢትዮጵያ አብጠርጥረው ያውቋታል የሚባሉ ለምድ የከበዱ ሰዎች እንኳ ሳይቀሩ ዛሬ መሀመድ ግራኝ ወራሪአይደለም ሲሉ እየተደመጡ ነው ተደምጠዋል ምን ያርጉ ሥልጣን ወደ ሐሰት ዘወረቻቸው ። ታድያ ግራኝ ወራሪ ካልሆነ አርበኛ ነውንን? አምባ ሳደር ነውን? ወይ ብሔራዊ ጀግናችን ነው? በዚህ ዓይነትኮ ወደፊት ዐውልት ይቁምለት መንገድ ይሰየምለት መባሉ አይቀሬ ነው ። በዕድሜ የምታንሱኝ ልጆቼና ወንድሞቼ ይህ አበክራችሁ ስሙኝ በልባችሁም ጽላት ጽፋችሁ አኑሩት እውነት ሁል ጊዜም እውነት ነች ለማቻቻልና ሚዛን ለመጠበቅ አልያም ዲሞክራት ለመሆን ብለህ ልትሸፉፍናት መልኳን አጥፍተህ ልታጠይማት አትችልም ። መሀመድ ግራኝ ሀገር ያፈረሰ ሃይማኖት ያጠፈ ወራሪ ነው። ግራኝ ወራሪ አይደለም ካልን 11 ሚሊየን አይሁዳዊያንን በዘራቸው ምክንያት የጨፈጨፋቸው ኢትለር ቅዱስ ነው ሀገሩም ከደጋጎቹ ሀገር ከመንግሥተ ሠማይ ነው ማለት ነው
#ይህን ጊዜ ታናናሾቹ ተራሮች ቡፍ ቡፍ እያሉ እጆቻቸውን በአቸው ላይ ጭነው ያመለጣቸውን ሳቅ ለማፈን ሲሞክሩ አንጋፈው ተራራ ተፈነጣጣ የምራቅ ቅንጣቶችን እንዳይለቁበት በመስጋት ከቀድሞ ይበልጥ አብልጦ ፊቱን በደመና ጋቢ ተከናነበ ። ሳቃቸው የሚጋባ ሳቅ ቢሆንም ከራሱ ቁጭት አልወጣም ነበርና ሳቃቸው በራስ እንደማሾፍ ቆጠረው

ጠላትን ድል በነሳንበት ሀገር እርስ በእርስ ድል ስንነሳሳ ለከረምን ለኛ ትልቅ ውርደት እንደሆነ ባወቃችሁ ጥርሳችሁን በዘነዘና ትነቀሱት ነበር። ለነገሩ የእሳት ልጅ አመድ ነው እናንተም የዚህ ትውልድ አብራክ አይደላችሁምን? አለና በስላቅ አብሯቸው ሳቅ አለ በልቡ ግን ግን ወይ መፍለስን ወይ መፍረስን ይመኝ ነበር ሰማይና ምድር ያልፋሉ ያለውንም እያሰበ አብዝቶ ያቺን ቀን ናፈቃት ።
_ይኩን ሠላም ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ___
ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 23/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
ዜና እረፍት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አራተኛ ፓትርያሪክ ብፅእ አቡነ መርቆሪዎስ ከዚ አለም ድካም አረፉ።

በረከታቸው ይደርብን
ዐውደ ምሕረት
Photo
#ኑ-ዝምታን-እንተርጉም
---------------------------------

"አቤቱ ለአፌ ጠባቂን አኑርለት
የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ"

አጥብቆ ቢደግማት የዳዊትን መዝሙር
ተቀጥሮለት መሰል ጠባቂ ከናፍር
እንጂማ
ጆሮ አልባ በሆነች ባናጋሪ ዓለም
አስችሎት ዝም የሚል ትግስተኛ የለም

እኔስ ይመስለኛል የአባቴ ዝምታ
ቃል ያለማውጣቱ የጸትታው ፋታ
በጆሮ አልባ ሀገር
በደንቆሮ መንደር
ሰሚ በሌለበት
ፊደል ማባከኑ ቃላት ማበላሸት
መረበሽ ነው እንጂ መግባባት የለበት
ብሎ ይመስለኛል

እኔስ ይመስለኛል የአባቴ አርምሞ
በማይሰሙ ሰዎች ነብሰ ሥጋው ታሞ
ሰልችቶት ይሆናል አርሞ አርሞ
እንጂማ
እንዲያ ባይሆን ኖሮ
ባልሸሸ ነበረ ካደገበት ጓሮ

እኔስ ይመስለኛል ያባቴ አርሞሞ
ለአንድ መንጋ አንድ እረኛ
ይበቃዋል ካለ እውነተኛ
ከዛ ውጪ ነው ምንደኛ
ብሎ አስቦ በትትና
እራሱን ዝቅ አረገና
ከሰማይ ቤት ደጅ ጠና
የይህን ዓለም ንቋልና

እኔስ ይመስለኛ ያባቴ ዝምታ

አንድም ቢደርስ ነው ከቅዱሳን ተርታ
የበቃ ቢሆን ነው ምግባሩ የበረታ

ግን.... ግን
በሚንጫጫ ዓለም በማይሰማ ቅዬ
እንዴት አስችሏቸው ዝም አሉ አቡዬ?
ለፍላፊ ሳይሰሙት
ኸኸ ባይ ሳይነግሩት
ጆሮ በጠፋበት
ምላስ ሰንበር በዝቶ
ሲገድፍ የሚውል አንደበት ጾም ትቶ
ድንጋዮን ያልጣለው ከአፉ አውጥቶ
እንደምን ተጠራ ዳግማዊው አጋቶ ን ???

#ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 25 /2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" #ካለ_ፈጣሪ_አሟጠሽ ጋግሪ"
______________________
ስስት ንፍገት ፣ሆዳምነትን፣ ኑሮዬ ይበቃኛል አለማለትን እንዲሁም አልጠግብ ባይነትን የሚገልጽ ግሥ ነው ። (የመ.ቅዱስ መዝገበ ቃላት/ ገጽ ፹ ፭ ) በዘመናች ቋንቋ "ቋጣሪነት" ልንለው እንችላለን። በንባባችን ላይ ቋጣሪነት ወይም ስስታምነት ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ የመጣ ነገር እንጂ በሰው ተፈጥሮ ውስጥ "ስስት" ወይም "ንፍገት" የሚባል ነገር የለም ። የስስት ተቃራኒ ቸርነት ነው ። ቸር ደግሞ #እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሌሎች ቸር ቢሆኑ #ከእግዚአብሔር የተቀበሉን በመስጠት ነው እንጂ የእራሳቸው አንዳች የላቸውም ቸርነትን ለሌላው ቢያደርጉ በሥጋ የሕሊና ሰላም ፣በሃይማኖት ደግሞ ጽድቅን ፈልገውበት ነው ።

#እግዚአብሔር ቸር ቢሆን ግን እጸድቅበት አይል ነገር ጻድቅ ነው እከብርበት አይል ነገርም ክቡር ነው ስለዚህ ቸርነት ማንም ያልሰጠው ማንምም የማይነጥቀው የእግዚአብሔር የባሕሪው ገንዘቡ ነው:: “ #ከአንዱ_ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።” ሉቃ ፲ ፰ ፥፲ ፱

ይህን ያልተገነዘበው ዲያቢሎስ እሩቅ ብዕሲ (ተራ ሰው) መስሎት አርባ ቀን በገዳመ ቆሮንቶስ ጾሞ ሲወጣ መራቡን ዐይቶ ቸሩ መድኃኔዓለምን በስስት ሊፈትነው ቀረበ ። በኮሮጆም ትኩስ የሚሸት ዳቦ ይዞ "የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ ይህን ድንጋይ ዳቦ እንዲሆን እዘዝ " አለው :: #ማቴ ፬÷፫

#ቸሩ_መድኃኔ_ዓለምም ማንነቴን ላሳየው፤ ሁሉን ቻይነቴን ይወቅልኝ ሳይል ዲያቢሎስ እንዳለው ድንጋዮን ዳቦ ሳያደርግ "ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም " ተብሎ ተጽፏል ብሎ " #በትዕግስት" ድል ነሳው። #ማቴ ፬÷፬

በበርሃ የሚኖሩ መነኮሳት ፆራቸው ስስት ነው ፤ በፈለጉ ጊዜ ምግባቸውን አያገኙምና ‹‹ ያለችን ብንመፀውት ሰውን ብናበላ ያለችን ታልቅብናለች ከዚያ ምን እንበላለን›› እያሉ በስስት ብዙውን ይፈተናሉ፡፡ ስለዚህ ቸሩ ፈጣሪያቸን ይህን የስስት ፈተና እንዴት በትዕግሥት ድል ማድረግ እንደሚችሉ ሲያስተምራቸው በመነኮሳት ቦታ በበርሃ ተገኝቶ ዲያቢሎስን በትዕግስ "ሰው በእጀራ ብቻ አይኖርም" ብሎ ድል አደረገው፡፡

#በስስት የመጣብንን ፈተና በትግሥትና በቸርነት ለንሻገረው ያስፈልጋል ያ ሲባል ግን ቁጠባንና ባህሉን ለመሸርሸር ሳይሆን የመቀበል ግልብጥ ስሌት መስጠት እንደሆነ ጭምር ለማስታወስ ነው ። ሁለት ነገር ያለው ሰው ሌላ ሦስተኛ ነገር ከፈጣሪው ከፈለገ ከያዘው ሁለት ነገር ቢያንስ አንዱን እንኳ ምንም ለሌለው መስጠት ይገባዋል :: ለመቀበልምኮ መስጠት ያስፈልጋል! ሰው ሁለት እጅ የተሰጠው በአንዱ ተቀብሎ በሌላኛው እንዲያቀብል ነው እንዲሉ አበው።


“ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።” #ምሳሌ ፲ ፱ ፥፲ ፯ “ኀጥእ ቀኑን ሁሉ ምኞትን ይመኛል፤ ጻድቅ ግን ይሰጣል፥ አይሰስትም።” #ምሳሌ ፳ ፩ ፥ ፳ ፮ ስለዚህም በክርስቶስ እኖራለሁ የሚል ክርስቶስ ደግሞ እንደተመላለስ ይመላለስ ! ጸሎቱም ሁል ጊዜ “ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን።” የሚል ይሁን ! #መዝ ፻ ፲ ፰ (፻ ፲ ፱) ፥ ፴ ፮
......... ይቆየን..........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
#እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ”
________________________________
#ያዕ ፬ ፥ ፮
#፩ጴጥ ፭ ÷ ፭

ትዕቢት ከሦስቱ (አርስተ/ ርዕሰ ኃጥዐው) መካከል አንዱ ነው:: ሦስቱ ርዕሰ ኃጥዐው የሚባሉት ስስት ፣ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ ናቸው።

#ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ነዋይ የኃጢያት ሁሉ እራሶች ፣ አለቆች ና አውራዎች መባላቸው ኃጢያት ሁሉ ከእነዚህ ስለሚመነጭ ነው።

ዲያቢሎስ መንፈሳዊ ሰውን የሚፈትነው በሦስቱ የፈተና ዐይነቶች ነው በስስት፣ በትዕቢትና በፍቅረ ነዋይ ፤ ሌሎች የኃጢያት ዐይነቶች የነዚህ የሦስቱ ጭፍሮች ወይም ተከታዮች ናቸው።

#ለምሳሌ የትዕቢት መንፈስ የተጠናወተው አንድ ሰው እኔ ከማን አንሳለሁ የሚል የበታችነት ስሜት ውስጥ በመግባት ለግድያ ፣ለስርቆት፣ ብሎም ለዝሙት ኃጢያቶች ተጋላጭ ይሆናል።
ትዕቢት የዲያቢሎስ ልዮ መገለጫው ነው ስለሆነም ዲያቢሎስ ስለ ግብሩ ( ስለ ሥራው) ትዕቢተኛ ብቻ ሳይሆን እራሱ ትዕቢት እየተባለ ይጠራል። ለዚህ ነው ሐዋርያው እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል" ካለ በኋላ " እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ " ሲል ትዕቢተኞች ብሎ በተውላጠ ስም የጠራቸውን ዲያቢሎስና ጭፍሮቹን አስከትሎ ደግሞ "ዲያቢሎስን" ብሎ በግልጥ የተናገረው #ያዕ ፬÷፮ - ፯
#ለዚህ ትልቁ ማሳያ የገዳመ ቆሮንቶስ ሁለተኛ ፈተና ትዕቢት የተሞላበት መሆኑ ነው "ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና (ወሰደው ሲል በፍቃዱ ሄደለት ለማለት እንጂ ለዲያቢሎስስ ታዛዢ ሆኖ አይደለም) እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው። “ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል" ብሎ የትዕቢትን ፈተና በትሕትና ድል ነሳው ። የካህናት ፆራቸው ትዕቢት ነው ፤‹ ‹ እኛ አእምሮአችን ረቂቅ ማዕረጋችን ምጡቅ ›› እያሉ በትዕቢት ይፈተናሉ፡፡ ዲያብሎስ በካህናት ቦታ በቤተመቅደስ በትዕቢት ቢመጣበት በትህትና ድል አድርጎላቸዋል፡፡ #የትዕቢትን ፈተና ማሸነፍ የሚቻለው በትሕትና ብቻ ነው! #ማቴ ፬÷ ፭- ፰ .

“ከእኔም_ተማሩ_እኔ_የዋህ_በልቤም_ትሑት_ነኝና"
#ማቴ ፲ ፩ ፥ ፳ ፱

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፬ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ !"
________________________________
#ማቴ ፬÷፱
#ንግግሩ_ብዙ_ጊዜ ዲያቢሎስና የግብር ልጆቹ ሰዎችን በፍቅረ ነዋይ ሊጥሉ
ከሃይማኖትም መንገድ ሊያስወጡ ሲፈልጉ የሚናገሩት የተንኮል ንግግር ነው። የሚሰጥ
መስፈርት ወይም ቅድመ ሆኔታ አያስቀምጥም ዝም ብሎ በፍቅር ይሰጣል ተንኮለኞች ግን
ለተንኮል ይሰጣሉ ። #እግዚአብሔር ቸር ሰጪ ነው ሲሰጥም የሰገደልኝ ያልሰገደልኝ
ያመነኝ ያላመነኝ አይልም ያመነው ይበልጡኑ ያተርፍበታል ያላመነው በሥራው ይከሥርበታል
እንጂ አያስገድደውም ።“ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና
በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” #ማቴ ፭ ፥ ፵፬-፵ ፭
ከፍቅረ ነዋይ የተነሳ ብዙዎች " ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ" ለሚላቸው አካል ልቡናቸው ክፍት
ነው። ዲያቢሎስም ይህን ስለሚያውቅ በብዙ ይፈትናቸዋል ስለዚህ እግሮቻቸውን " ይህን
ሁሉ እሰጥሃለሁ " ወደሚል ወደ ጠንቋይ ቤት ያነሳሉ በእውነቱ ግን ጠንቋይ ሁሉን
ሊሰጣቸው ቀርቶ ያላቸውንም አራቁቶ ባዶ ያስቀራቸዋል። ጠንቋይ ማለት ጠንቀ ነዋይ
ማለት ነውና። የንጽሕ ገንዘብ ምንጭ አይደለም ሰርቶ ባለ ፀጋ መሆን ይቻላል!
አያስኮንንም። ሰርቆ መክበር ግን ያዋርዳል።
ብዙ ጊዜ ባለ ጸጎች # ከእግዚአብሔር መንግሥ የራቁ ናቸው። ለዚህም ነው " ለባለ ጸጋ
መንግሥተ ሰማያት መግባት ጭንቅ ይሆንበታል፤ ባለ ጸጋ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ
ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይቀላል "ተብሎ የተነገረው #ማቴ ፲ ፱÷፳ ፫
ዲያቢሎስ በጠንቋይ እያደረ " ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ" ያለንን ሁሉ ያሳጣናል በዚህ የፍቅረ
ነዋይ ፈተና #እግዚአብሔር ሁሉ ሳይቀር ይህን "ሁሉ እሰጥሀለሁ " ብሎ ለመፈተን
ሞክሯል። ግን አልተሳካለትም # እግዚአብሔር ሰጪ እንጂ ተቀባይ አይደለምና በዚህም
ፈተና ተፈተነ ሲባል ሰይጣን የእግዚአብሔር የሚፈትነው ሆኖ አይደለም ወደ ፊት ለሚነሱ
ጾሚ ተአራሚዎች እንዴት ድል እንደሚያደርጉት ድል ማድረጌያውን ሊያስተምራቸው ወዶ
ነው እንጂ።
# እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም
አሳይቶ ብትሰግድልኝ እጅ ብትነሣኝም ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ " አለው፡፡” #ማቴ ፬ ÷ ፰
ወሰደው ”ሲባል፡- ሰይጣን ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚወስድ
የሚያመጣው ሆኖ ሳይሆን ‹‹ ነገሥታቱን ድል በምንነሣበት በተራራ ቢሆን መች ድል ይነሳኝ
ነበር›› ብሎ አስቧልና ነው ፡፡ (ነገሥታት በተራራ ቤተ መንግስታቸውን ይሠራሉና) አሁንም
ምክንያት ለማሳጣት ከረጅም ተራራ በራሱ ፍቃድ ወጥቷልና “ወሰደው ” ተባለ፡፡ ሰይጣን
ሳያፍርና ሳይፈራ “ብትሰግድልኝ እጅም ብትነሣኝ ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ” ብሎ ብዙዎችን
ድል ባረገበት በፍቅረ ነዋይ የመጨረሻ ፈተናውን አቀረበ፡፡
በእውነቱ ከሆነ ዛሬ በዚህ ፈተና ያልተሸነፈ የለም፡፡ በዓለም ላይ ያሉ ሁሉም ጦርነቶች
ሌላምክንያት ቢሰጣቸውም ዋናው ምክንያታቸው የኢኮኖሚ ፉክክር ፣የከበርቴነት ውድድር
ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡ዘፈኑ፤ዝሙቱ፤ሥርቆቱም ምንጫቸው ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡
ባለ ሽቶዋ ማርያም የአልባስጥሮሽ ሽቶ ይዛ መታ የጌታዋን እግር በትቀባ ገንዘብ ወዳዱ
ይሁዳ አልተዋጠለትም "ይህ ሦስት መቶ ዲናር የሚያወጣ ውድ ሽቶ ነው ተሽጦ ለድሆች
በተሰጠ ይሻል ነበር ብሎ ተናገረ፤ ሽቶው ከተሸጠ ከሦስቱ አስር አስር እጅ ማለትም ሰላሳ
የሚጠዱ ዲናሮችን በቀረጥ መልክ ይሰበስብ ነበርና ነው እንጂ ለድሆችሽ ተጨንቆላቸው
አልነበረም እንዲያውም መጻሕፍ " ሌባ "ስለ ነበር ነው ብሎ ይገልጠዋል። ጌታችን
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቀጥሎ ሽቶ ስለቀባችኝ ይህችን ሴት ስለምን
ታደክሟታላችሁ? ድሆችስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ናቸው ባሻችሁ ጊዜ መልካም
ልታደርጉላቸው ትችላላችሁ አለ።
# ይሁዳ ሠላሳዋን ብር ስላጣ ተቆጨ በዚህም ሰይጣን በልቡ ገባበት ሠላሳውንም ብር
ጌታውን ሽጦ ያገኛት ዘንድ ሰይጣን ልቡን አጸናው ። በመጨረሻም በገንዘብ ፍቅር ታውሮ
ነበርና ወደር ስለማይገኝለት ፍቅሩ ክህደትን ከፈለው ። የሚገርመው ይሁዳን ገንዘብ
መውደደ የሚያውቅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ ሌባ ነው ሳይል የሐዋርያት ገንዘብ ያዢ
አድርጎ ሁሉ ሾሞት ነበር ። ይህ ሁሉ ግን የይሁዳን ድንጋይ ልብ ሊሰብረው አልቻለም።
ፍቅረ ነዋይ እንዲህ ነው!
ብዙዎቻች በዚህ ፈተና ውስጥ እንገኛለን ገንዘብ ከመውደዳችን የተነሳ አስራቱን በአግባቡ
ባለማውጣት ከእግዚአብሔር እንኳን ሳይቀር ሰርቀናል “ሰው # እግዚአብሔርን ይሰርቃልን?
እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል።
በአሥራትና በበኵራት ነው።” # ሚልክያስ ፫፥፰
# ጌታችን_አምላካችን_መድኀኒታችን_ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ይሄን ሁሉን ተንኮሉን
ያውቃልና “ብትሰግድልኝ ይሄን ሁሉ እሰጥሃለሁ” ብሎ በፍቅረ ነዋይ የፈተነውን ሰይጣን
“አንተ ሰይጣን ከአጠገቤ ሒድ ፤ ለጌታ ለእግዚአብሔር ስገድ እርሱን ብቻ አምልክ ተብሎ
ተፅፏልና ” ብሎ በጸሊአ ነዋይድል አድርጎታል፡፡
.“አንተ ሠይጣን ከአጠገቤ ሒድ”፡- ሲለው እግዚአብሔር አምላክ የሌለበት ቦታ ኖሮ
ወደዚያ ሂድ ያለው አይደለም፡፡ይልቁንም “ ከእኔ በኃላ ከሚነሱ ከኦርቶዶክሳዊያን ልቦና
ሒድ ሲለው” እንጂ # ማቴ. ፲፮፥፳፫፡፡ በእውነት በፍቅረ ነዋይ የሚፈታተነንን ሰይጣን
ዲያቢሎስን ከልቦናችን አርቆ ያስቀርልን “ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ባርያ ማንም
የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላልና ሁለተኛውንም ይወዳል፥ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል
ሁለተኛውንም ይንቃል። # ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።” ተብሏልና
ገዘብን ከመውደድ እግዚአብሔር መውደድን አብዝቶ ያድለን ገንዘብን መውደድ (ፍቅረ
ነዋይን) እንዴት መተው እንችላለን ቢሉ አላፊነቱን፣ ከእግዚአብሔር መንግስት መለየቱንና
የጥፋት ሁሉ ሥር መሆኑን ዕለት ዕለት በማሰብ ጸላሄ ነዋይ መሆን ይቻላል ይህ ለመንፈሳዊ
ሰው ቀላል ነው በገዳመ ቆሮንቶስ ያስተማረን ይህንኑ ነው!
ለሀገራችንና ለዓለማችንም ሠላሙን ይስጥልን # ሉቃስ ፲ ፮ ፥ ፲ ፫
.......ይቆየን.......
ግብሐት:- መጻሕፍ ቅዱስ
ወንጌል ትርጓሜ
መቅረዘ ተዋሕዶ
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፯ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" #ዕለት_ሳበችው_ምሕረትም_ጠቀሰችው"
_______________________________
#አባታችን_ሁልጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር። ‹‹የሚጣፍጥ ምግብን መውደድ ኃጢአትን
ያመጣል፣ሞትን ያስከትላል፡፡ ክንፍ ያላቸው የሰማይ ወፎች እንኳን በመብል ምክንያት
ይጠመዳሉ፣ ምግብ በመሻት ከምድር ላይ ይወድቃሉ በወጥመድም ይያዛሉ፡፡የሰው ልጅም
ምግብን በመውደድ በኃጢአት ይወድቃልና እኔስ ለሰውነቴ ምግብ መጠጥን
አልፈልግም፤ልብስም አልሻም ዕራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን እንደወጣሁ እንዲሁ ዕረቁቴን ወደ
መቃብር እመለሳለሁ እንጂ፡፡ከዚህ ከኃላፊው ዓለም በሞት በተለየሁ ጊዜ መብል
መጠጥንና ልብስን ማን ያስከትልልኛል?›› አሉ። ዳግመኛም‹‹ሰው:ሊደርስበ
ማይችልበት:በረሃ:እኖራለሁ፣ ነጣቂ ተኩላዎችና አራዊቶች ባሉበት እነርሱ እንዲበሉኝ
ሥጋዬን እጥላለሁ፤ ዳዊት በመዝሙር ‹የጻድቃን ሥጋቸው ለዱር አራዊት ነው› እንዳለ እኔ
ክፉ አውሬዎች፣ ተናዳፊ እባቦችና ዘንዶዎች ወዳሉበት እገባለሁ ምግብም እሆናቸው ዘንድ
እወዳለሁ››በማለት አባታችን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጡ ነበር ነገር ግን አራዊቱ
ሁሉ እየሰገዱላቸው ይገዙላቸው ከእግራቸውም በታች ይተኙ ነበር፡፡ እንደሚታዘዝ ደቀ
መዝሙርም ይታዙላቸው ነበር፤ለጸሎትም በሚቆሙበት ጊዜ አብረዋቸው ይቆማሉ፡፡
በፊታቸውም ይጫወታሉ፡፡
#በመጨረሻም ዕለት ሳበችሁ ምሕረትም ጠቀሰችሁ ለሞትም የሚያበቃ ጽኑ ሕማም
ታመመ የሚጠጋበት የዛፍ ጥላ በሌለበት እንደ አንበሳ በበርሃ ወደቀ ለጸሎት ከቆመበት
ጊዜ አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ እጆቹን በትምህርተ መስቀል እንዳማተበ ነበር ። ብዙ
ግሁሳንም ወደ እርሱ መጡ #እግዚአብሔር አምላክም ብዙ የብዙ ብዙ መላእክትን
አስከትሎ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምን አስቀድሞ ዳዊትንም በገና አስይዞ ተገለጠና
ነብሱን አክብሮ ተቀበላት፣ሳማት፣ ደስታውንም መላት መላእክትም ከዳዊት ጋር "ክቡር ሞቱ
ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ
በአንድነት ዘመሩለት #መዝ ፻ ፲ ፭ {፻ ፲ ፮ }÷፲ ፭
#እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ
እናውቃለን።”
#ሮሜ ፰ ፥፳ ፰
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፭ ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
"እኔስ #እግዚአብሔር ባልኩኝ ጊዜ #አብ-ወልድ-መንፈስ-ቅዱስ ማለት ነው"
---- #ቅዱስ ባስልዮስ ዘቄሳርያ-----