ሳራ ክፍሉ ውስጥ ወደ ነበረችው ሰራተኛ ዞረችና "እባክሽ በሩን ዝጊው።
››አለቻት፡፡ሰራተኛዋ በሩን ዘጋችና ትታቸው ሄደች ፡፡ አለም እንድትቀመጥ ባሳየቻት ቦታ ተቀመጠች፡፡
"ስለጋበዝሽ አመሰግናለሁ። በጣም ጥሩ ሀሳብ ነበር።"
"ትናንት ማታ ስለተናገርኩሽ ነገር ይቅርታ መጠየቄ ግዴታ ነበር።"
" ግድ የለም.. አሁን እሱን እንርሳው።"
በሩ ተከፈተና ሰራተኛው ሻይ የያዘ ፔርሙዝና ኩኪሶች ያየዘ አንድ ሰሀን አምጥታ በመሀከላቸው በሚገኝ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠችና እንደአመጣጧ ወጥታ ሔደች፡፡
ሳራ ፌርሙዙን አነሳችና ሻዩን የሁለቱም ብርጭቆ ላይ ከቀዳች በኋላ..‹‹ስኳር ስንት ማንኪያ ላድርግልሽ?"በማለት ጠየቀቻት፡፡
‹‹እባክሽ..ሁለት ይበቃኛል;;››አለም መለሰች፡፡
"አመሰግናለሁ።"
ሳንድዊች አንስታ እየጎረሰች ሻዬን ጠጣችና እና መልሳ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች፡፡
ሳራ ቀጥታ ወደጉዳዮ ገባች
"ከፍሰሀ እና ጁኒየር በስተቀር የቀረኝ ቤተሰብ የለኝም።በልጅነቴ ከጀማይካ ወደእዚህ ይዘውኝ የመጡት እናትና አባቴ ነበሩ.. አሁን ሁለቱም ሞተዋል…በስመ ጀማይካዊ ካልሆነ በስተቀር እዚህ ኢትዬጵያ ውስጥ የቅርብ ዘመድ የለኝም፡፡››
‹‹ይሄን በመስማቴ አዝናለው…ያው እንደምታውቂው ዘመድን በተመለከተ እኔም ካንቺ ብዙ አልሻልም›› ስትል መለሰችላት፡፡
"ምን መሰለሽ …ሙታን በተቀበሩበት በሰላም እንዲያርፉ መፍቀድ የተሻለ እንደሆነ እየነገርኩሽ ነው፡፡››
አለም የሳራ የንግግሯ አቅጣጫ እየገባት ነው ፡፡
"ስለእናቴን ነው የምትናገሪው?"
"በትክክል ….ይህ የአንቺ ምርመራ መላ ቤተሰቤን ሰላም እየነሳ ነው›፡፡››
"ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እጠይቃለሁ፣ ነገር ግን በእኔ እቅድ ላይ ምንም የሚደረግ ለውጥ የለም።"ስትል መለሰችላት፡፡
"ወንበዴዎች ንብረቴን አወደሙት፣ ዛሬ የእንስሳቱን ህይወት አደጋ ላይ ከጣሉ ነገ ደግሞ ባሌን ወይም ልጄን ለማጥቃት ከማድባት ወደኃላ አይሉም፡፡ ››
አለም "ይህ አሳዛኝ ክስተት ነበር ። በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንዳዘንኩ ልነግርሽ አልችልም" በማለት ሴትየዋን እንድትረዳ ተማፀነች፡፡
ሳራ ጆ በረጅሙ ተነፈሰች። "እናትሽ ከጁኒየር እና ገመዶ ጋር ስለነበራት ግንኙነት ምን ያህል ታውቂያለሽ?"
"አያቴ የነገረችኝን ብቻ፣ እዚህ ሻሸመኔ ከመጣው በኃላ ካነጋገርኳቸው የተለየያዩ ሰዎች የሰበሰብኩት የተወሰነ መረጃም አለ።"
"እንደ መንትያ ወፎች አይነት ነበሩ… ለራሳቸው ትንሽ ቡድን ፈጥረው ነበር. ጁኒየር ከእነሱ ጋር እንዲገናኝ አልፈልግም ነበር….ገመዶ በሁሉም ነገር የሰከረ የከተማ ልጅ ነበር። እና እናትሽም እንደዛው ...ከእነሱ ጋር እንዲጣመር የማልፈልግበት ብዙ ምክንያቶች ነበሩ።"
"አንድን ጥቀሺልኝ."
"በዋነኛነት በእሷ እና በገመዶ መካከል ስላለው ሁኔታ ጁኒየር ሁል ጊዜ ሁለተኛ ምርጫዋ እንደሆነ አውቅ ነበር። የተሻለው የቱ እንደሆነ እንኳን መለየት የማትችል ከንቱ ነበረች፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ለጁኒየር ላስረዳውና ላስጠነቅቀው ብሞክርም ስለሚወዳት ሊሰማኝ አልፈቀደም። እንደፈራሁት አፍቅሯት ነበር።" በድንገት ዓይኖቿ በአለም ላይ አተኩሩ።የሳራ አይኖች በክፋት ጠበቡ።
"እናትሽ ተንኮለኛ ነበረች።››
"እስከዚህ ነጥብ ድረስ አለም ምላሷን በጥንቃቄ ተቆጣጥራ ነበር። ነገር ግን ጋባዦ በሟች እናቷ ላይ ምትሰነዝረውን ልቅ ንግግር መታገስ አልቻለችም፡፡
"ከዚያ የስም ማጥፋት የተለየ አስተያየት አለኝ ወይዘሮ ሳራ።››
ሳራ ግድ የለሽ በሆነ ሁኔታ እጆን አወናጨፈችን " ግድ አይሰጠኝም…የተናገርኩት እውነቴን ነው፤እሷን ባገኘኋት ጊዜ ቆንጆ ነበረች፣ በጋለ ስሜት ነበር የምታወራው። የሚወደድ አይኖች ነበሯት ። ጮክ ብላ ነበር የምትስቀው፣ ተጫወች ነበረች፣ ስትጠጣ በጣም ስሜታዊ ስለምትሆን እራሷን መቆጣጠር አትችልም ነበር፡፡ በጣም ሐቀኛ ትመስላለች ግን አልነበረችም፡- ስትናገር በኩራት ነው፡ ‹‹ሰዎች የሚሰማቸውን በግልጽ ቢናገሩ ዓለም የተሻለ ሊሆን ይችል ነበር›› ብላ የምትጎርር አይነት ሴት ነች።ወንዶች ሁሉ ያለ ልዩነት ይፈልጓት ነበር፡፡ ያገኘችውን ወንዷች ሁሉ በፍቅር እንዲወድቁላት በማድረግ እርካታ የሚሰማት አይነት አደገኛ ሴት ነበረች፡፡ ››
"እራሷን ለመከላከል የማትችልን ሴት ከዚህ በላይ እንድታጣጥያት አልፈቅድልሽም. ንግግርሽ ከስርዓት ያፈነገጠ ነው ወ.ሮ ሳራ፡፡››
ስትገባ እንደ ግሪንሃውስ ንፁህ አየር የሞላው የነበረ ክፍል አሁን የታፈነ ይመስላል። ለቃ መውጣት ፈለገች፡፡
"መሄዴ ነው"አለቻት፡፡
"ገና አልጨረስንም.እናትሽ ከራሷ በላይ ኩማንደሩን ትወደው ነበር።"
"ታዲያ ይሄ ጉዳይ አንቺን እንዴት ሊያሳስብሽ ቻለ?"
"ምክንያቱም ጁኒየርን በዚህ ጉዳይ ውስጥ ስላስገባችው ነው የሚያሳስበኝ ..አያትሽ ያቺ ደደብ ሴት በልጆቻችን መካከል መግባቷን ስላወቀች በጣም ተናደደች:: ጁኒየር ሰሎሜን እንዲያገባ የፈቀድኩኝ አስመስላ መንቀሳቀስ ጀመረች" ስትል ተሳለቀች::
‹‹አልገባኝም››
"አያትሽ አንድ ጊዜ ደውላልኝ የወደፊት አማቶች እንደመሆናችን መጠን በደንብ እንድንተዋወቅ ሀሳብ አቀረበችልኝ፣ በእግዚአብሔር ስም.. በዛኑ ጊዜ መሞት ነበር የፈለኩት
›› አለችና .. በንቀት ሳቀች።
‹‹ከዛ ምን አልሻት?››አለም በንዴት እየተንተከተከች ጠየቀች፡፡
"አለም ምራቴ የምትሆንበት ምንም አይነት እድል አልነበረም። ይህንንም ለአያትሽ በግልፅ ነበር የነገርኳት።እና ምን ለማለት ፈልጌ መሰለሽ …ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ እሱ ስለ አንቺ ብቻ ነው የሚያስበው፤ ልክ ከእናትሽ ጋር እንደነበረው."
"ወ.ሮ ሳራ አትስጊ…በመካከላችን የፍቅር መጠላለፍ በፍፁም ሊኖር አይችልም። ምናልባት ይህ ምርመራ ከተፈታ በኋላ ጓደኛሞች ልንሆን እንችል ይሆናል።››
ሳራ "እናትሽም እንደዚሁ ነበር የምትለው…በኋላ ግን ጓደኝነታቸውን አላግባብ ተጠቀመችበት ፡፡ምክንያቱም ጓደኝነታቸው ወደጋብቻ ያድጋል የሚል ስውር ተስፋ ነበራት፡፡
አንቺም እንደ እናትሽ ምርመራውን እንደሰበብ አድርገሽ ከእሱ ለመቀራረብ እና ልቡን ለመስረቅ እየተጠቀምሺበት ነው።››አለቻት
"ይህ በበፍጹም እውነት አይደለም."
"እውነት ካልሆነ ለምን ወደዚህ መምጣት አስፈለገሽ?"ሳራ በመንገሽገሽ ጠየቀች፡፡
"የመጣሁበት አላማማ ግልፅ ነው…እናቴ ለምን እንደተገደለች እና ማን እንደገደላት ለማወቅ እፈልጋለሁ."
ጣቷን በቀጥታ ወደ አለም ልብ እየጠቆመች"እናትሽ የተገደለችበት ምክንያቱማ አንቺ ነሽ!" አለቻት ። አለም ይህንን ንግግር ከዚህ በፊት ከገዛ አያቷም አንደበት ሰምታ ነበር …አሁን ከወ.ሮ ሳራ ለሁለተኛ ጊዜ ስትሰማው የመሬት መንቀጥቀ የተነሳ ያህል ነው መላ አካሏን የነዘራት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው?››
"አንቺ የሰሎሜ ዲቃላ ልጅ ነሽ ››
አለም ስለታም ብረት በሆዷ ውስጥ እንደተሻጠ አይነት ህመም ተሰማት፡፡
‹‹አልገባኝም›› "
የምናገረው ግልፅ እኮ ነው…ከጋብቻ ውጭ የተወለድሽ ህገ ወጥ ልጅ ነበርሽ"
"ይህ ውሸት ነው" አለም ትንፋሿን ካደት። "እናቴ ከጎበና ጋር ተጋብታ ነበር። የሰማንያ ወረቀታቸው አይቻለው ።"ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመች፡፡
››አለቻት፡፡ሰራተኛዋ በሩን ዘጋችና ትታቸው ሄደች ፡፡ አለም እንድትቀመጥ ባሳየቻት ቦታ ተቀመጠች፡፡
"ስለጋበዝሽ አመሰግናለሁ። በጣም ጥሩ ሀሳብ ነበር።"
"ትናንት ማታ ስለተናገርኩሽ ነገር ይቅርታ መጠየቄ ግዴታ ነበር።"
" ግድ የለም.. አሁን እሱን እንርሳው።"
በሩ ተከፈተና ሰራተኛው ሻይ የያዘ ፔርሙዝና ኩኪሶች ያየዘ አንድ ሰሀን አምጥታ በመሀከላቸው በሚገኝ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠችና እንደአመጣጧ ወጥታ ሔደች፡፡
ሳራ ፌርሙዙን አነሳችና ሻዩን የሁለቱም ብርጭቆ ላይ ከቀዳች በኋላ..‹‹ስኳር ስንት ማንኪያ ላድርግልሽ?"በማለት ጠየቀቻት፡፡
‹‹እባክሽ..ሁለት ይበቃኛል;;››አለም መለሰች፡፡
"አመሰግናለሁ።"
ሳንድዊች አንስታ እየጎረሰች ሻዬን ጠጣችና እና መልሳ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች፡፡
ሳራ ቀጥታ ወደጉዳዮ ገባች
"ከፍሰሀ እና ጁኒየር በስተቀር የቀረኝ ቤተሰብ የለኝም።በልጅነቴ ከጀማይካ ወደእዚህ ይዘውኝ የመጡት እናትና አባቴ ነበሩ.. አሁን ሁለቱም ሞተዋል…በስመ ጀማይካዊ ካልሆነ በስተቀር እዚህ ኢትዬጵያ ውስጥ የቅርብ ዘመድ የለኝም፡፡››
‹‹ይሄን በመስማቴ አዝናለው…ያው እንደምታውቂው ዘመድን በተመለከተ እኔም ካንቺ ብዙ አልሻልም›› ስትል መለሰችላት፡፡
"ምን መሰለሽ …ሙታን በተቀበሩበት በሰላም እንዲያርፉ መፍቀድ የተሻለ እንደሆነ እየነገርኩሽ ነው፡፡››
አለም የሳራ የንግግሯ አቅጣጫ እየገባት ነው ፡፡
"ስለእናቴን ነው የምትናገሪው?"
"በትክክል ….ይህ የአንቺ ምርመራ መላ ቤተሰቤን ሰላም እየነሳ ነው›፡፡››
"ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እጠይቃለሁ፣ ነገር ግን በእኔ እቅድ ላይ ምንም የሚደረግ ለውጥ የለም።"ስትል መለሰችላት፡፡
"ወንበዴዎች ንብረቴን አወደሙት፣ ዛሬ የእንስሳቱን ህይወት አደጋ ላይ ከጣሉ ነገ ደግሞ ባሌን ወይም ልጄን ለማጥቃት ከማድባት ወደኃላ አይሉም፡፡ ››
አለም "ይህ አሳዛኝ ክስተት ነበር ። በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንዳዘንኩ ልነግርሽ አልችልም" በማለት ሴትየዋን እንድትረዳ ተማፀነች፡፡
ሳራ ጆ በረጅሙ ተነፈሰች። "እናትሽ ከጁኒየር እና ገመዶ ጋር ስለነበራት ግንኙነት ምን ያህል ታውቂያለሽ?"
"አያቴ የነገረችኝን ብቻ፣ እዚህ ሻሸመኔ ከመጣው በኃላ ካነጋገርኳቸው የተለየያዩ ሰዎች የሰበሰብኩት የተወሰነ መረጃም አለ።"
"እንደ መንትያ ወፎች አይነት ነበሩ… ለራሳቸው ትንሽ ቡድን ፈጥረው ነበር. ጁኒየር ከእነሱ ጋር እንዲገናኝ አልፈልግም ነበር….ገመዶ በሁሉም ነገር የሰከረ የከተማ ልጅ ነበር። እና እናትሽም እንደዛው ...ከእነሱ ጋር እንዲጣመር የማልፈልግበት ብዙ ምክንያቶች ነበሩ።"
"አንድን ጥቀሺልኝ."
"በዋነኛነት በእሷ እና በገመዶ መካከል ስላለው ሁኔታ ጁኒየር ሁል ጊዜ ሁለተኛ ምርጫዋ እንደሆነ አውቅ ነበር። የተሻለው የቱ እንደሆነ እንኳን መለየት የማትችል ከንቱ ነበረች፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ለጁኒየር ላስረዳውና ላስጠነቅቀው ብሞክርም ስለሚወዳት ሊሰማኝ አልፈቀደም። እንደፈራሁት አፍቅሯት ነበር።" በድንገት ዓይኖቿ በአለም ላይ አተኩሩ።የሳራ አይኖች በክፋት ጠበቡ።
"እናትሽ ተንኮለኛ ነበረች።››
"እስከዚህ ነጥብ ድረስ አለም ምላሷን በጥንቃቄ ተቆጣጥራ ነበር። ነገር ግን ጋባዦ በሟች እናቷ ላይ ምትሰነዝረውን ልቅ ንግግር መታገስ አልቻለችም፡፡
"ከዚያ የስም ማጥፋት የተለየ አስተያየት አለኝ ወይዘሮ ሳራ።››
ሳራ ግድ የለሽ በሆነ ሁኔታ እጆን አወናጨፈችን " ግድ አይሰጠኝም…የተናገርኩት እውነቴን ነው፤እሷን ባገኘኋት ጊዜ ቆንጆ ነበረች፣ በጋለ ስሜት ነበር የምታወራው። የሚወደድ አይኖች ነበሯት ። ጮክ ብላ ነበር የምትስቀው፣ ተጫወች ነበረች፣ ስትጠጣ በጣም ስሜታዊ ስለምትሆን እራሷን መቆጣጠር አትችልም ነበር፡፡ በጣም ሐቀኛ ትመስላለች ግን አልነበረችም፡- ስትናገር በኩራት ነው፡ ‹‹ሰዎች የሚሰማቸውን በግልጽ ቢናገሩ ዓለም የተሻለ ሊሆን ይችል ነበር›› ብላ የምትጎርር አይነት ሴት ነች።ወንዶች ሁሉ ያለ ልዩነት ይፈልጓት ነበር፡፡ ያገኘችውን ወንዷች ሁሉ በፍቅር እንዲወድቁላት በማድረግ እርካታ የሚሰማት አይነት አደገኛ ሴት ነበረች፡፡ ››
"እራሷን ለመከላከል የማትችልን ሴት ከዚህ በላይ እንድታጣጥያት አልፈቅድልሽም. ንግግርሽ ከስርዓት ያፈነገጠ ነው ወ.ሮ ሳራ፡፡››
ስትገባ እንደ ግሪንሃውስ ንፁህ አየር የሞላው የነበረ ክፍል አሁን የታፈነ ይመስላል። ለቃ መውጣት ፈለገች፡፡
"መሄዴ ነው"አለቻት፡፡
"ገና አልጨረስንም.እናትሽ ከራሷ በላይ ኩማንደሩን ትወደው ነበር።"
"ታዲያ ይሄ ጉዳይ አንቺን እንዴት ሊያሳስብሽ ቻለ?"
"ምክንያቱም ጁኒየርን በዚህ ጉዳይ ውስጥ ስላስገባችው ነው የሚያሳስበኝ ..አያትሽ ያቺ ደደብ ሴት በልጆቻችን መካከል መግባቷን ስላወቀች በጣም ተናደደች:: ጁኒየር ሰሎሜን እንዲያገባ የፈቀድኩኝ አስመስላ መንቀሳቀስ ጀመረች" ስትል ተሳለቀች::
‹‹አልገባኝም››
"አያትሽ አንድ ጊዜ ደውላልኝ የወደፊት አማቶች እንደመሆናችን መጠን በደንብ እንድንተዋወቅ ሀሳብ አቀረበችልኝ፣ በእግዚአብሔር ስም.. በዛኑ ጊዜ መሞት ነበር የፈለኩት
›› አለችና .. በንቀት ሳቀች።
‹‹ከዛ ምን አልሻት?››አለም በንዴት እየተንተከተከች ጠየቀች፡፡
"አለም ምራቴ የምትሆንበት ምንም አይነት እድል አልነበረም። ይህንንም ለአያትሽ በግልፅ ነበር የነገርኳት።እና ምን ለማለት ፈልጌ መሰለሽ …ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ እሱ ስለ አንቺ ብቻ ነው የሚያስበው፤ ልክ ከእናትሽ ጋር እንደነበረው."
"ወ.ሮ ሳራ አትስጊ…በመካከላችን የፍቅር መጠላለፍ በፍፁም ሊኖር አይችልም። ምናልባት ይህ ምርመራ ከተፈታ በኋላ ጓደኛሞች ልንሆን እንችል ይሆናል።››
ሳራ "እናትሽም እንደዚሁ ነበር የምትለው…በኋላ ግን ጓደኝነታቸውን አላግባብ ተጠቀመችበት ፡፡ምክንያቱም ጓደኝነታቸው ወደጋብቻ ያድጋል የሚል ስውር ተስፋ ነበራት፡፡
አንቺም እንደ እናትሽ ምርመራውን እንደሰበብ አድርገሽ ከእሱ ለመቀራረብ እና ልቡን ለመስረቅ እየተጠቀምሺበት ነው።››አለቻት
"ይህ በበፍጹም እውነት አይደለም."
"እውነት ካልሆነ ለምን ወደዚህ መምጣት አስፈለገሽ?"ሳራ በመንገሽገሽ ጠየቀች፡፡
"የመጣሁበት አላማማ ግልፅ ነው…እናቴ ለምን እንደተገደለች እና ማን እንደገደላት ለማወቅ እፈልጋለሁ."
ጣቷን በቀጥታ ወደ አለም ልብ እየጠቆመች"እናትሽ የተገደለችበት ምክንያቱማ አንቺ ነሽ!" አለቻት ። አለም ይህንን ንግግር ከዚህ በፊት ከገዛ አያቷም አንደበት ሰምታ ነበር …አሁን ከወ.ሮ ሳራ ለሁለተኛ ጊዜ ስትሰማው የመሬት መንቀጥቀ የተነሳ ያህል ነው መላ አካሏን የነዘራት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው?››
"አንቺ የሰሎሜ ዲቃላ ልጅ ነሽ ››
አለም ስለታም ብረት በሆዷ ውስጥ እንደተሻጠ አይነት ህመም ተሰማት፡፡
‹‹አልገባኝም›› "
የምናገረው ግልፅ እኮ ነው…ከጋብቻ ውጭ የተወለድሽ ህገ ወጥ ልጅ ነበርሽ"
"ይህ ውሸት ነው" አለም ትንፋሿን ካደት። "እናቴ ከጎበና ጋር ተጋብታ ነበር። የሰማንያ ወረቀታቸው አይቻለው ።"ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመች፡፡
❤41👍1
"አይደለም…..ክርምት ቤተሰቦቼን ልጠይቅ ብላ ኮፈሌ ሄዳ ነበር….ግን ስትንዘላዘል አንቺን ፀንሳ ተመለሰች….አላወቀችም ነበረና ሀገር ሳላም ነው ብላ ከገመዶም ሆነ ከልጄ ጋር ያላትን ግንኙነት ቀጥላበት ነበር….በኃላ ግን ማርገዟን አወቀች….ማስወረድም አልቻለችም መሰለኝ መልሳ ወደኮፈሌ ተመልሳ ጠፋች….ዘመዶቾ ልጁን አስገድደው እንዲያገባት አደረጉ
…ግን ሰማንያውን ፈረመ እንጂ አንድ ቤት እንኳን አልገቡም ነበር…ከዛሬ ነገ እቤት ተከራይቶ እና እቃ አሞልቷ ይጠቀልለኛል ብላ ስትጠብቅ እሱ ሹልክ ብሎ ውትድርና ተቀጠረና ሄደ… እሷም የተቀበተተ ሆዷን እና የሰማንያ ወረቀቷን ይዛ አይኗን በጨው አጥባ ወደእዚህ ተመለሰች….ደጋግሜ እንደነገርኩሽ ሁሉንም ወንዶች የሚያደነዝዝ አዚም ስላለባት ሁለቱም ቢበሳጩባትም ከህይወታቸው ሊያስወግዷት አልፈቀዱም…..እስከነ ዲቃላዋ ይንከባከቦት ጀመረ…. ከዛ አንቺም ተወለድሽ.. ዲቃላ ያስታቀፋትም እዛው ወታደር ቤት እንደገባ መሞቱን መርዶ መጣላት፡
"ውሸትሽን ነው!" አለም እንዳትወድቅ ስለፈራች የወንበሩን እጄታ ያዘች።
"ለምን እዋሻኛለሁ?ቤተሰቦቼን ከአንቺ የበቀል ጥፋት ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነው። ፍሰሀ በአመታት ልፋት የገነባውን ሁሉ እንድታጠፊ አልፈቅድም። በቤተሰቤ ውስጥ አለመግባባት እንድትፈጥሪ አልፈቅድም። ከዚህ በፊት እናትሽ እንደዛ አድርጋ ነበር… አሁን.. ግን አልፈቅድም።
"ሴቶች… ሴቶች." ጁኒየር እየሳቀ ወደ ክፍሉ ገባ።‹‹ ይህ ጩኸት ምንድነው? ሸረሪት ተመለከታችሁ እንዴ?"
በመካከላቸው ያለውን ጥላቻ ሲታዘብ ቀልዱን አቆመና ግራ በመጋባት እያፈራረቀ ያያቸው ጀመር ። በአቅራቢያው መብረቅ የወረደ ይመስል አለም ደርቃና ገርጥታ ተመለከታ፡፡
"እናቴ? አሌክስ? ምን ተፈጠረ?"
አለም ምንም ሳትናገር ወንበሩ ላይ የተንጠለጠለውን ቦርሳዋን አነሳችና ከክፍሉ በፍጥነት ወጣች እና ሄደች ፡፡ጁኒየር አለምን ከኋላ ተከትሎ ከመግቢያው በር ጋር ደረሰባት ፡፡
"ምንድን ነው የተፈጠረው?"
አለም እንባዋን እንዳያይ ፊቷን በእጆቾ ሸፈነች።
"ምንም።"
" ሻይ ለመጠጣት እንደተቀጣጠራችሁ ስሰማ እኮ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር››
"ሻይ? ሃ!ሻይ እንድንጠጣ አይደለም የጋበዘችኝ››
‹‹እና ለምንድነው?››
እንባዋ እንዳይወርድ ለማድረግ ብላ ዓይኖቿን ብታሽም አልተሳካላትም "ለነገሩ ስለነገረችኝ ማመስገን አለብኝ ።"
"ምንድነው የነገረችሽ?" "እኔ ዲቃላ መሆኔን ."
የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
…ግን ሰማንያውን ፈረመ እንጂ አንድ ቤት እንኳን አልገቡም ነበር…ከዛሬ ነገ እቤት ተከራይቶ እና እቃ አሞልቷ ይጠቀልለኛል ብላ ስትጠብቅ እሱ ሹልክ ብሎ ውትድርና ተቀጠረና ሄደ… እሷም የተቀበተተ ሆዷን እና የሰማንያ ወረቀቷን ይዛ አይኗን በጨው አጥባ ወደእዚህ ተመለሰች….ደጋግሜ እንደነገርኩሽ ሁሉንም ወንዶች የሚያደነዝዝ አዚም ስላለባት ሁለቱም ቢበሳጩባትም ከህይወታቸው ሊያስወግዷት አልፈቀዱም…..እስከነ ዲቃላዋ ይንከባከቦት ጀመረ…. ከዛ አንቺም ተወለድሽ.. ዲቃላ ያስታቀፋትም እዛው ወታደር ቤት እንደገባ መሞቱን መርዶ መጣላት፡
"ውሸትሽን ነው!" አለም እንዳትወድቅ ስለፈራች የወንበሩን እጄታ ያዘች።
"ለምን እዋሻኛለሁ?ቤተሰቦቼን ከአንቺ የበቀል ጥፋት ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነው። ፍሰሀ በአመታት ልፋት የገነባውን ሁሉ እንድታጠፊ አልፈቅድም። በቤተሰቤ ውስጥ አለመግባባት እንድትፈጥሪ አልፈቅድም። ከዚህ በፊት እናትሽ እንደዛ አድርጋ ነበር… አሁን.. ግን አልፈቅድም።
"ሴቶች… ሴቶች." ጁኒየር እየሳቀ ወደ ክፍሉ ገባ።‹‹ ይህ ጩኸት ምንድነው? ሸረሪት ተመለከታችሁ እንዴ?"
በመካከላቸው ያለውን ጥላቻ ሲታዘብ ቀልዱን አቆመና ግራ በመጋባት እያፈራረቀ ያያቸው ጀመር ። በአቅራቢያው መብረቅ የወረደ ይመስል አለም ደርቃና ገርጥታ ተመለከታ፡፡
"እናቴ? አሌክስ? ምን ተፈጠረ?"
አለም ምንም ሳትናገር ወንበሩ ላይ የተንጠለጠለውን ቦርሳዋን አነሳችና ከክፍሉ በፍጥነት ወጣች እና ሄደች ፡፡ጁኒየር አለምን ከኋላ ተከትሎ ከመግቢያው በር ጋር ደረሰባት ፡፡
"ምንድን ነው የተፈጠረው?"
አለም እንባዋን እንዳያይ ፊቷን በእጆቾ ሸፈነች።
"ምንም።"
" ሻይ ለመጠጣት እንደተቀጣጠራችሁ ስሰማ እኮ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር››
"ሻይ? ሃ!ሻይ እንድንጠጣ አይደለም የጋበዘችኝ››
‹‹እና ለምንድነው?››
እንባዋ እንዳይወርድ ለማድረግ ብላ ዓይኖቿን ብታሽም አልተሳካላትም "ለነገሩ ስለነገረችኝ ማመስገን አለብኝ ።"
"ምንድነው የነገረችሽ?" "እኔ ዲቃላ መሆኔን ."
የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍44❤18😢1
🌼ውድ የቻናሉ ተከታዎችእንኳን ለ 2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሠላም በጤና አደረሳችሁ
❤️በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የደስታ እና የፍቅር አመት እንዲሆን ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !
🌼መልካም አዲስ ዓመት ለሁላችን🌼
@atronosee
❤️በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የደስታ እና የፍቅር አመት እንዲሆን ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !
🌼መልካም አዲስ ዓመት ለሁላችን🌼
@atronosee
❤5🥰2
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
"ምንድነው የነገረችሽ?"
"እኔ ዲቃላ መሆኔን ."
የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።
"እውነት ነው አይደል?"
ጁኒየር እጆቹን ዘረጋና እቅፉ ውስጥ አስገባት… እንባዋ በመጨረሻ የዐይን ሽፋኖቿን ሞልተው ያለከልካይ ፈሰሰ።
"ሰሎሜ ከኮፈሌ ተመልሳ መጣች። ከገመዶ ጋር ለመታረቅ ተዘጋጅታ ነበር።ፍቅራቸውን ለማደስ ተስማምተው ነበር …የመጋባት እድል ሁሉ ነበራቸው…በመሀል ግን ለማንኛችንም ሳትነግረን መልሳ ጠፋች….በኋላ ነው አንቺን ማረገዟን ስላወቀች እንደጠፋች ያወቅነው፡፡››ሲል አስረዳት፡፡
በእፍረት ፊቷን በእጆቿ ሸፈነች።
" ኦ አምላኬ በጣም ቢጠላኝ አይገርምም።››
ጁኒየር እጆቿን ከፊቷ ላይ አንስቶ በቅን ልቦና የሚወዳቸውን ጥቆቁር አይኖችን እየተመለከተ።
"ገመዶ አንቺን አይጠላሽም አሌክስ። ማናችንም ብንሆን አንጠላሽም…ያ ከአመታት በፊት ተጋፍጠን በይቅርታ ያለፍነው ጉዳይ ነው››
በንግግሩ በምሬት ሳቀች።‹‹ለምን አያቴ ሁሌ እኔ ላይ ጥብቅ እንደምትሆን እያሰብኩ እበሳጭ ነበር …በስንት ሰዓት ከቤት እንደወጣው? በስንት ሰዓት እንደተመለስኩ..?ከማን ጋር እንደነበርኩ ከአግባቡ ያለፈ ቁጥጥር ታደርግብኝ ነበር…ምክንያቷ አሁን ነው የገባኝ
…ለካ እናቴን ያጋጠማት ነገር እንዳያጋጥመኝ ፈርታ ነው፡፡አሁን ነው የገባኝ፡››
"ይሄ ከሃያ አምስት አመታት በፊት የሆነ ድርጊት ነው ፣ አሌክስ አሁን ስለዛ ማሰብ አቁሚ "
"አያቴ በእውነት እኔን ለምን እንደማትወደኝ የሚያብራራልኝ ታሪክ ነው… የሰሎሜን ህይወት አበላሽቻዋለሁ…እና ለዛ ፈጽሞ ይቅር ሳትለኝ ነው የሞተችው…. ሰሎሜ ገመዶን አጥታለች …ፍቅራቸው እንዳይሆን ሆኖ ተሰባብሯል … እና ሁሉም የሆነው በእኔ ምክንያት ነው››.
‹‹ኦህ፣በእግዚአብሔር !ተረጋጊ እንጂ!"
አለም ከእቅፉ ወጣችና ወደ መኪናዋ ሮጠች…መኪና ውስጥ በመግባት አስነሳችና አካባቢውን ለቀቀች።
."ምንድነው ነገሩ?" አለም ወደ መኪናዋ አቅጣጫ ስትሮጥ ያያት አቶ ፍሰሀ ጠየቀው።
"ሁለታችሁም እሷን ተዋት" ሳራ ከውስጥ እየወጣች ለባሏ መለሰች፡፡
ጁኒየር ወደ እናቱ ዞረና።
"እማዬ እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ? እንዴት ልጅቷን እንዲህ ትጎጂያታለሽ?"
"ልጎዳት አስቤ አይደለም የነገርኳት፡፡››
"ምን ነግራት ነው?" አቶ ፍሰሀ ጠየቀ ፡፡
ጁኒየር “በእርግጥ ጎድተሻታል። ደግሞ አቅደሽበት ነው ያደረግሽው… ለምን ነገርሻት?"
‹‹ምክንያቱም እሷ ማወቅ ስላለባት። አለምን የምትጎዳት እራሱ አለም ብቻ ነች። ሸቅዠቷን እያሳደደች ነው። የምትፈልጋት አይነት ቅድስት የሆነች እናት በሰሎሜ ውስጥ አልነበረችም። ሰሎሜ ምትባል ድንቅ እናት እንደነበረቻት በማይረባ ጭንቅላቷ ደምድማለች። እናቷ ምን ያህል ተንኮለኛ እና ሀጥያተኛ እንደሆነች ልጅቷ ማወቅ አለባት.. እናቷ ስትማግጥ እሷን ዲቃላ እንዳረገዘቻት የማወቅ መብት አላት››
" አንቺ እኮ ጤነኛ አይደለሽም!" አቶ ፍሰሀ ተበሳጨባት፡፡
…
አቶ ፍሰሀ በጸጥታ ወደ መኝታ ቤት ገባና ከኋላው በሩን ዘጋው፡፡ሳራ በአልጋዋ ላይ ያሉትን ትራስ ደራርባ ተደግፋ መፅሃፏን እያነበበች ነበር…እሱን ስታይ መፅሀፉን ከደነችና አጠገቧ ያለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠች ።
ወደአልጋው ቀረበና " ላናግርሸ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"ስለ ምን?"
‹‹ዛሬ ከሰአት በኋላ ስለተፈጠረው ነገር።››
"ራስ ምታት እየፈለጠኝ ነው…ለእራት ወደታች ያልመጣሁትም ለዛ ነው"
‹‹የሆነ መድሀኒት አልወሰድሺበትም?"
"አዎ ወስጄለሁ…አሁን በመጠኑ እየተሻለኝ ነው ።"የሳራ የራስ ምታት በትዳራቸው ልክ አብሯት የቆየ ህመም ስለሆነ የተለመደ ነው፡፡
በአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠ እና አቀርቅሮ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡
" ምንድነው ፍሰሀ ?አሁንም የሚያሰጋን ችግር አለ እንዴ?››ጠየቀች፡፡
"አይ..ሁሉም ነገር ሰላም ነው።"
"ታዲያ ለምን ታስባለህ…?እግዚአብሔር ይመስገን ብቸኛው የሞተው ፈረስ የገመዶ ነው
።››
አቶ ፍሰሀ ምንም አስተያየት መስጠት አልፈለገም ። ሳራ ጆ ለገመዶ ያላት ስሜት ፈጽሞ አይለወጥም፤በዚህ ጉዳይ ከእሷ ጋር መነጋገር ጥቅም አልባ እንደሆነ እርግጠኛ ነው፡፡ከእሷ ጋር ሊወያይ የመጣው ስስ ስለሆነ ጉዳይ ነው። ቃላቱን በጥንቃቄ ለመምረጥ ትንሽ ጊዜ ወሰደበት.
"ሳራ ዛሬ ከሰአት በኋላ -……" "በጣም ተበሳጭቼ ነበር" አለችው፣ ፡፡
" ተበሳጭተሽ ነበር?" ፍሰሀ ትዕግሥተኛ ሆኖ ጠየቃት፡፡ወደ ድምዳሜው ከመዝለሉ በፊት ከእሷ ወገን ያለውን የታሪኩን ገጽታ መስማት ፍልጓል።
"የአለምን ስሜትስ የጎዳሽ አይመስልሽም…?"
"ዲቃላ መሆኗን ስላወቀች ብቻ አይደለም የተናደደችው….እሷ በተፈጥሮዋም ብስጩ ነች:: "
"እኔ በእሷ ቦታ ብሆን አይገርመኝም… ወላጆቼ የጋብቻ ሰርተፊኬት እንዳላቸው በጭራሽ አጣርቼ አላውቅም.., እና ባይኖራቸውም ምንም አይመስለኝም ነበር.››
" ሁሉም ሰው ለነገሮች ያለው ምላሽ የተለያየ ነው››
‹‹ አለም ግን ስሜታዊነት የሚያጠቃት ወጣት ሴት ነች።"
"እሷ ይሄን ታሪክ ለመቀበል የሚያስችል ጥንካሬ እንዳላት አምናለው."ስትል መለሰችለት
"በእርግጥ የምትይውን ያህል ጥንካሬ እንዳላት እርግጠኛ አይደለሁም።በረንዳ ላይ ቆሜ እያየችኝ እኔን እንኳን ሀሳትሰናበተኝ ነው ገፍትራኝ ሮጣ የሄደችው፡፡››
የሳራ ፈገግታ ተሰበረ። "ስለነገርኳት ትወቅሰኛለህ? ስህተት የሰራው ይመስልሃል?"ስትል ጠየቀችው፡፡
በዛ ልብን በሚሰረስር የግሏ የሆነ ልዩ እይታ ስታየው፣ ልቡ ቀለጠ። ሁል ጊዜም የዚህ አይነት አስተያየት ስታየው የሚሆነው እንደዚሁ ነው። ፍሰሀ በስሱ ይዳብሳት ጀመር፡፡
‹‹ውዴ ስለነገርሻት አልወቅስሽም። ግን የነገርሽበት መንገድ እንደዚህ ባይሆን ጥሩ ነበር፡፡ እንደዛ ከማድረግሽ በፊት ከጁኒዬር እና ከእኔ ጋር መመካከር ነበረብሽ…በህይወቷ ሙሉ ባታውቀው የሚሻል ታሪክ ነበር፡፡››
"አልስማማም" ስትል ሳራ ተከራከረች።
አቶ ፍሰሀም "እናቷ እና አባቷ አብረው ከተኙ በኃላ አለመጋባታቸው ወይ መጋባታቸው በእሷ ልጅነት ላይ አሁን ምን ለውጥ ያመጣል? ይህ በቡዙ ወጣት ሴቶች ህይወት ላይ የሚያጋጥም በጣም የተለመደ ነገር ነው..››አላት፡፡
"ልጅቷ ስለ ሰሎሜ ያላት አመለካከት ላይ ግን ለውጥ ያመጣል። ››
‹‹እንዴት?››
‹‹ሰሎሜ ልጅቷ የምታስባትን አይነት ቅድስት ሴት አይደለችም…ይሄን ማወቋ የእሷን የግድያ ጉዳይ ለማወቅ የምታደርገውን ልፋትና ጥረት ቆም ብላ እንድታይ ያግዛት ይሆናል….ይልቅ ከአሁን በኃላ ሁላችሁም ከአለም ጋር መገናኘቱን እና መወያየቱን ማቆም አለባችሁ፡፡››
"ለምን?"ግራ ገብቶት ጠየቀው፡፡
"ለምን? ምክንያቱም እሷ እኛን ለማጥፋት እየሞከረች ነው…ለዚህ ነው. እሷን ለመፋለም የወሰንኩ…. ያለኝን ጥይት ነው የተጠቀምኩት….አንተን እና ጁኒየርን ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነበር."
በእውነቱ፣ ፍሰሀ እንደ አለም ያለ በራስ መተማመን የነበራትን ሴትን ለመጋፈጥ ለሣራ ትልቅ ድፍረት እንደሆነ አሰበ። ያደረገችው ስህተት ቢሆንም ሳራ ያደረገችውን ነገር ያደረገችው ቤተሰቧን ልትጠብቅ እንደሆነ ተረድቷታል። የጀግንነት ጥረቷ ከትችት የተሻለ ነገር ይገባዋል ብሎ አሰበ እና ጎንበስ ብሎ ግንባሯን ሳመ።
ለስለስ ባለ ንግግር" የትግል መንፈስሽን አደንቃለሁ… ግን ማናችንም ያንቺን ጥበቃ አንፈልግም ።"አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
"ምንድነው የነገረችሽ?"
"እኔ ዲቃላ መሆኔን ."
የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።
"እውነት ነው አይደል?"
ጁኒየር እጆቹን ዘረጋና እቅፉ ውስጥ አስገባት… እንባዋ በመጨረሻ የዐይን ሽፋኖቿን ሞልተው ያለከልካይ ፈሰሰ።
"ሰሎሜ ከኮፈሌ ተመልሳ መጣች። ከገመዶ ጋር ለመታረቅ ተዘጋጅታ ነበር።ፍቅራቸውን ለማደስ ተስማምተው ነበር …የመጋባት እድል ሁሉ ነበራቸው…በመሀል ግን ለማንኛችንም ሳትነግረን መልሳ ጠፋች….በኋላ ነው አንቺን ማረገዟን ስላወቀች እንደጠፋች ያወቅነው፡፡››ሲል አስረዳት፡፡
በእፍረት ፊቷን በእጆቿ ሸፈነች።
" ኦ አምላኬ በጣም ቢጠላኝ አይገርምም።››
ጁኒየር እጆቿን ከፊቷ ላይ አንስቶ በቅን ልቦና የሚወዳቸውን ጥቆቁር አይኖችን እየተመለከተ።
"ገመዶ አንቺን አይጠላሽም አሌክስ። ማናችንም ብንሆን አንጠላሽም…ያ ከአመታት በፊት ተጋፍጠን በይቅርታ ያለፍነው ጉዳይ ነው››
በንግግሩ በምሬት ሳቀች።‹‹ለምን አያቴ ሁሌ እኔ ላይ ጥብቅ እንደምትሆን እያሰብኩ እበሳጭ ነበር …በስንት ሰዓት ከቤት እንደወጣው? በስንት ሰዓት እንደተመለስኩ..?ከማን ጋር እንደነበርኩ ከአግባቡ ያለፈ ቁጥጥር ታደርግብኝ ነበር…ምክንያቷ አሁን ነው የገባኝ
…ለካ እናቴን ያጋጠማት ነገር እንዳያጋጥመኝ ፈርታ ነው፡፡አሁን ነው የገባኝ፡››
"ይሄ ከሃያ አምስት አመታት በፊት የሆነ ድርጊት ነው ፣ አሌክስ አሁን ስለዛ ማሰብ አቁሚ "
"አያቴ በእውነት እኔን ለምን እንደማትወደኝ የሚያብራራልኝ ታሪክ ነው… የሰሎሜን ህይወት አበላሽቻዋለሁ…እና ለዛ ፈጽሞ ይቅር ሳትለኝ ነው የሞተችው…. ሰሎሜ ገመዶን አጥታለች …ፍቅራቸው እንዳይሆን ሆኖ ተሰባብሯል … እና ሁሉም የሆነው በእኔ ምክንያት ነው››.
‹‹ኦህ፣በእግዚአብሔር !ተረጋጊ እንጂ!"
አለም ከእቅፉ ወጣችና ወደ መኪናዋ ሮጠች…መኪና ውስጥ በመግባት አስነሳችና አካባቢውን ለቀቀች።
."ምንድነው ነገሩ?" አለም ወደ መኪናዋ አቅጣጫ ስትሮጥ ያያት አቶ ፍሰሀ ጠየቀው።
"ሁለታችሁም እሷን ተዋት" ሳራ ከውስጥ እየወጣች ለባሏ መለሰች፡፡
ጁኒየር ወደ እናቱ ዞረና።
"እማዬ እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ? እንዴት ልጅቷን እንዲህ ትጎጂያታለሽ?"
"ልጎዳት አስቤ አይደለም የነገርኳት፡፡››
"ምን ነግራት ነው?" አቶ ፍሰሀ ጠየቀ ፡፡
ጁኒየር “በእርግጥ ጎድተሻታል። ደግሞ አቅደሽበት ነው ያደረግሽው… ለምን ነገርሻት?"
‹‹ምክንያቱም እሷ ማወቅ ስላለባት። አለምን የምትጎዳት እራሱ አለም ብቻ ነች። ሸቅዠቷን እያሳደደች ነው። የምትፈልጋት አይነት ቅድስት የሆነች እናት በሰሎሜ ውስጥ አልነበረችም። ሰሎሜ ምትባል ድንቅ እናት እንደነበረቻት በማይረባ ጭንቅላቷ ደምድማለች። እናቷ ምን ያህል ተንኮለኛ እና ሀጥያተኛ እንደሆነች ልጅቷ ማወቅ አለባት.. እናቷ ስትማግጥ እሷን ዲቃላ እንዳረገዘቻት የማወቅ መብት አላት››
" አንቺ እኮ ጤነኛ አይደለሽም!" አቶ ፍሰሀ ተበሳጨባት፡፡
…
አቶ ፍሰሀ በጸጥታ ወደ መኝታ ቤት ገባና ከኋላው በሩን ዘጋው፡፡ሳራ በአልጋዋ ላይ ያሉትን ትራስ ደራርባ ተደግፋ መፅሃፏን እያነበበች ነበር…እሱን ስታይ መፅሀፉን ከደነችና አጠገቧ ያለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠች ።
ወደአልጋው ቀረበና " ላናግርሸ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"ስለ ምን?"
‹‹ዛሬ ከሰአት በኋላ ስለተፈጠረው ነገር።››
"ራስ ምታት እየፈለጠኝ ነው…ለእራት ወደታች ያልመጣሁትም ለዛ ነው"
‹‹የሆነ መድሀኒት አልወሰድሺበትም?"
"አዎ ወስጄለሁ…አሁን በመጠኑ እየተሻለኝ ነው ።"የሳራ የራስ ምታት በትዳራቸው ልክ አብሯት የቆየ ህመም ስለሆነ የተለመደ ነው፡፡
በአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠ እና አቀርቅሮ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡
" ምንድነው ፍሰሀ ?አሁንም የሚያሰጋን ችግር አለ እንዴ?››ጠየቀች፡፡
"አይ..ሁሉም ነገር ሰላም ነው።"
"ታዲያ ለምን ታስባለህ…?እግዚአብሔር ይመስገን ብቸኛው የሞተው ፈረስ የገመዶ ነው
።››
አቶ ፍሰሀ ምንም አስተያየት መስጠት አልፈለገም ። ሳራ ጆ ለገመዶ ያላት ስሜት ፈጽሞ አይለወጥም፤በዚህ ጉዳይ ከእሷ ጋር መነጋገር ጥቅም አልባ እንደሆነ እርግጠኛ ነው፡፡ከእሷ ጋር ሊወያይ የመጣው ስስ ስለሆነ ጉዳይ ነው። ቃላቱን በጥንቃቄ ለመምረጥ ትንሽ ጊዜ ወሰደበት.
"ሳራ ዛሬ ከሰአት በኋላ -……" "በጣም ተበሳጭቼ ነበር" አለችው፣ ፡፡
" ተበሳጭተሽ ነበር?" ፍሰሀ ትዕግሥተኛ ሆኖ ጠየቃት፡፡ወደ ድምዳሜው ከመዝለሉ በፊት ከእሷ ወገን ያለውን የታሪኩን ገጽታ መስማት ፍልጓል።
"የአለምን ስሜትስ የጎዳሽ አይመስልሽም…?"
"ዲቃላ መሆኗን ስላወቀች ብቻ አይደለም የተናደደችው….እሷ በተፈጥሮዋም ብስጩ ነች:: "
"እኔ በእሷ ቦታ ብሆን አይገርመኝም… ወላጆቼ የጋብቻ ሰርተፊኬት እንዳላቸው በጭራሽ አጣርቼ አላውቅም.., እና ባይኖራቸውም ምንም አይመስለኝም ነበር.››
" ሁሉም ሰው ለነገሮች ያለው ምላሽ የተለያየ ነው››
‹‹ አለም ግን ስሜታዊነት የሚያጠቃት ወጣት ሴት ነች።"
"እሷ ይሄን ታሪክ ለመቀበል የሚያስችል ጥንካሬ እንዳላት አምናለው."ስትል መለሰችለት
"በእርግጥ የምትይውን ያህል ጥንካሬ እንዳላት እርግጠኛ አይደለሁም።በረንዳ ላይ ቆሜ እያየችኝ እኔን እንኳን ሀሳትሰናበተኝ ነው ገፍትራኝ ሮጣ የሄደችው፡፡››
የሳራ ፈገግታ ተሰበረ። "ስለነገርኳት ትወቅሰኛለህ? ስህተት የሰራው ይመስልሃል?"ስትል ጠየቀችው፡፡
በዛ ልብን በሚሰረስር የግሏ የሆነ ልዩ እይታ ስታየው፣ ልቡ ቀለጠ። ሁል ጊዜም የዚህ አይነት አስተያየት ስታየው የሚሆነው እንደዚሁ ነው። ፍሰሀ በስሱ ይዳብሳት ጀመር፡፡
‹‹ውዴ ስለነገርሻት አልወቅስሽም። ግን የነገርሽበት መንገድ እንደዚህ ባይሆን ጥሩ ነበር፡፡ እንደዛ ከማድረግሽ በፊት ከጁኒዬር እና ከእኔ ጋር መመካከር ነበረብሽ…በህይወቷ ሙሉ ባታውቀው የሚሻል ታሪክ ነበር፡፡››
"አልስማማም" ስትል ሳራ ተከራከረች።
አቶ ፍሰሀም "እናቷ እና አባቷ አብረው ከተኙ በኃላ አለመጋባታቸው ወይ መጋባታቸው በእሷ ልጅነት ላይ አሁን ምን ለውጥ ያመጣል? ይህ በቡዙ ወጣት ሴቶች ህይወት ላይ የሚያጋጥም በጣም የተለመደ ነገር ነው..››አላት፡፡
"ልጅቷ ስለ ሰሎሜ ያላት አመለካከት ላይ ግን ለውጥ ያመጣል። ››
‹‹እንዴት?››
‹‹ሰሎሜ ልጅቷ የምታስባትን አይነት ቅድስት ሴት አይደለችም…ይሄን ማወቋ የእሷን የግድያ ጉዳይ ለማወቅ የምታደርገውን ልፋትና ጥረት ቆም ብላ እንድታይ ያግዛት ይሆናል….ይልቅ ከአሁን በኃላ ሁላችሁም ከአለም ጋር መገናኘቱን እና መወያየቱን ማቆም አለባችሁ፡፡››
"ለምን?"ግራ ገብቶት ጠየቀው፡፡
"ለምን? ምክንያቱም እሷ እኛን ለማጥፋት እየሞከረች ነው…ለዚህ ነው. እሷን ለመፋለም የወሰንኩ…. ያለኝን ጥይት ነው የተጠቀምኩት….አንተን እና ጁኒየርን ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነበር."
በእውነቱ፣ ፍሰሀ እንደ አለም ያለ በራስ መተማመን የነበራትን ሴትን ለመጋፈጥ ለሣራ ትልቅ ድፍረት እንደሆነ አሰበ። ያደረገችው ስህተት ቢሆንም ሳራ ያደረገችውን ነገር ያደረገችው ቤተሰቧን ልትጠብቅ እንደሆነ ተረድቷታል። የጀግንነት ጥረቷ ከትችት የተሻለ ነገር ይገባዋል ብሎ አሰበ እና ጎንበስ ብሎ ግንባሯን ሳመ።
ለስለስ ባለ ንግግር" የትግል መንፈስሽን አደንቃለሁ… ግን ማናችንም ያንቺን ጥበቃ አንፈልግም ።"አላት፡፡
❤46👍3
በሃሳቡ ሳቀች። "እንዴት እንደ አንቺ ያለች ደካማ ሴት ከመካከላችን ትልቅ እና የታጠቁ ወንዶችን ልትጠብቅ ትችላለች ለማለት ነው?አታስተውልም እንዴ ጁኒየር እኮ ከእሷ ጋር ፍቅር እየያዘው ነው."
"ታዲያ ቢይዘው ምን ችግር አለው ?" አለ በሚያብረቀርቅ ፈገግታ። ሳራ "እናቷ ልቡን ሰብራው ነበር ፣ ያ አያስጨንቅህም?"።
ፍሰሀ ፊቱን አኮሰታትሮ፣
"ያ ከረጅም ጊዜ በፊት የሆነ ነው። እና አለም እንደ እናቷ አይደለችም።"
"በዛ እርግጠኛ መሆን አልችልም." አለችና ሳራ ወደ ኮርኒሱ ተመለከተች።
"አለም እንደ ሰሎሜ ተለዋዋጭ እና ?ገራሚ ሴት አይደለችም….እንደውም እሷ በጣም ጎበዝ ሴት ነች ፣ ምናልባት ለጁኒየር የምታስፈልገው እንደእሷ አይነት ሴት ልትሆን ትችላለች
… እስከአሁን ብዙ ሴቶች ለማግባት ሞክሮ አንዱም ትዳር ሊሰምርለት አልቻለም፤እንደ እሷ ምን እንደሆነ የምትነግረው ሴት ይፈልጋል ።"
"በነገራችን ላይ አሁን የት ነው ያለው? አሁንም እንደተናደደብኝ ነው?" ብላ በጭንቀት ጠየቀች።
" ተበሳጨቷል … ነገር ግን እንደ ሁልጊዜውም በመስከር ብስጭቱን ሊረሳ ሄዷል ." ሁለቱም ተሳሳቁ።
" ተጠንቅቆ እንደሚነዳ ተስፋ አደርጋለሁ።"
‹‹ምን አልባት …ሌሊቱን እዛው የሚያሳልፍ ይመስለኛል ." "ወይ ተው እንጂ ?"
"እንደዛ ቢያደርግ …አይገርመኝም" አለ ፍሰሀ
"አለም እራሷን ለማስተካከል የተወሰነ ጊዜ ያስፈልጋታል። ዛሬ ማታ የሚፈልገውን መጽናኛ የምትሰጠውን ሌላ ሴት ያገኛል።››
የአቶ ፍሰሀ አይን ወደ ሚስቱ ዳሌ ዝቅ አለ፣ …እጁ ሰውነቷን ሲዳብሳት በድካም ቃተተች።
"እናንተ ወንዶች ! ስለእዛ ጉዳይ ብቻ ነው የምታስቡት? -"ተነጫነጨች "እንዲህ አይነት ቋንቋ አትጠቀሚ። ጭካኔ ነው።››
‹‹ ዛሬ ማታ ይህን ማድረግ አልፈልግም። ራስ ምታቴ እየተመለሰ ነው።››
የእሱ መሳም ተጨማሪ ተቃውሞዎችን አስነሳ. ። እሷ ሁል ጊዜ መቃወሟ የማይቀር ነው፡፡ ግን በጭራሽ አይቀበላትም። ከስሜታዊነት ይልቅ በግዴታ ስሜት ለእሱ ምላሽ መስጠቱ እሷን ከመፈለግ አግዶት አያውቅም። እንደውም በተቃራኒው ፍላጎቱን ከፍ ያደርግለት ይሆናል ። ፈጥኖ ልብሱን አውልቆ አንሶላውን ገልጦ ገባ ፡፡
ሳራ የሌሊት ልብሷን ጫፍ ወደላይ ሲሰበስባ እጁን ያዘችና ከለከለችው፡፡ አቶ ፍሰሀ ወደእሷ ተጠጋና ጉንጯን ሳመ እና አቀፋት። ለስላሳ እና፣ ጥሩ መዓዛ ያለው ቆዳዋን መዳበስ ክፉኛ ፈልጎ ነበር … ከእሷ ግር ፍቅር መስራት አምሮታል፡፡
"ፍሰሀ አሁን ተኛ … ይህን የጀመርኩትን ምዕራፍ መጨረስ እፈልጋለሁ" አለችው።
እንደ ፍቅሯ ደረቅ እና ህይወት የሌለውን ልቦለድዋን እንደገና ከፍታለች። ፍሰሀ ከማንበቢያዋ መብራት ርቆ ወደ ሌላኛው የአልጋው ጠርዝ ተጠጋና ፊቱን አዞሮ ተኛ ፡፡ እንደፍላጎቱ ስላልሆነችለት ተበሳጭቶ ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
"ታዲያ ቢይዘው ምን ችግር አለው ?" አለ በሚያብረቀርቅ ፈገግታ። ሳራ "እናቷ ልቡን ሰብራው ነበር ፣ ያ አያስጨንቅህም?"።
ፍሰሀ ፊቱን አኮሰታትሮ፣
"ያ ከረጅም ጊዜ በፊት የሆነ ነው። እና አለም እንደ እናቷ አይደለችም።"
"በዛ እርግጠኛ መሆን አልችልም." አለችና ሳራ ወደ ኮርኒሱ ተመለከተች።
"አለም እንደ ሰሎሜ ተለዋዋጭ እና ?ገራሚ ሴት አይደለችም….እንደውም እሷ በጣም ጎበዝ ሴት ነች ፣ ምናልባት ለጁኒየር የምታስፈልገው እንደእሷ አይነት ሴት ልትሆን ትችላለች
… እስከአሁን ብዙ ሴቶች ለማግባት ሞክሮ አንዱም ትዳር ሊሰምርለት አልቻለም፤እንደ እሷ ምን እንደሆነ የምትነግረው ሴት ይፈልጋል ።"
"በነገራችን ላይ አሁን የት ነው ያለው? አሁንም እንደተናደደብኝ ነው?" ብላ በጭንቀት ጠየቀች።
" ተበሳጨቷል … ነገር ግን እንደ ሁልጊዜውም በመስከር ብስጭቱን ሊረሳ ሄዷል ." ሁለቱም ተሳሳቁ።
" ተጠንቅቆ እንደሚነዳ ተስፋ አደርጋለሁ።"
‹‹ምን አልባት …ሌሊቱን እዛው የሚያሳልፍ ይመስለኛል ." "ወይ ተው እንጂ ?"
"እንደዛ ቢያደርግ …አይገርመኝም" አለ ፍሰሀ
"አለም እራሷን ለማስተካከል የተወሰነ ጊዜ ያስፈልጋታል። ዛሬ ማታ የሚፈልገውን መጽናኛ የምትሰጠውን ሌላ ሴት ያገኛል።››
የአቶ ፍሰሀ አይን ወደ ሚስቱ ዳሌ ዝቅ አለ፣ …እጁ ሰውነቷን ሲዳብሳት በድካም ቃተተች።
"እናንተ ወንዶች ! ስለእዛ ጉዳይ ብቻ ነው የምታስቡት? -"ተነጫነጨች "እንዲህ አይነት ቋንቋ አትጠቀሚ። ጭካኔ ነው።››
‹‹ ዛሬ ማታ ይህን ማድረግ አልፈልግም። ራስ ምታቴ እየተመለሰ ነው።››
የእሱ መሳም ተጨማሪ ተቃውሞዎችን አስነሳ. ። እሷ ሁል ጊዜ መቃወሟ የማይቀር ነው፡፡ ግን በጭራሽ አይቀበላትም። ከስሜታዊነት ይልቅ በግዴታ ስሜት ለእሱ ምላሽ መስጠቱ እሷን ከመፈለግ አግዶት አያውቅም። እንደውም በተቃራኒው ፍላጎቱን ከፍ ያደርግለት ይሆናል ። ፈጥኖ ልብሱን አውልቆ አንሶላውን ገልጦ ገባ ፡፡
ሳራ የሌሊት ልብሷን ጫፍ ወደላይ ሲሰበስባ እጁን ያዘችና ከለከለችው፡፡ አቶ ፍሰሀ ወደእሷ ተጠጋና ጉንጯን ሳመ እና አቀፋት። ለስላሳ እና፣ ጥሩ መዓዛ ያለው ቆዳዋን መዳበስ ክፉኛ ፈልጎ ነበር … ከእሷ ግር ፍቅር መስራት አምሮታል፡፡
"ፍሰሀ አሁን ተኛ … ይህን የጀመርኩትን ምዕራፍ መጨረስ እፈልጋለሁ" አለችው።
እንደ ፍቅሯ ደረቅ እና ህይወት የሌለውን ልቦለድዋን እንደገና ከፍታለች። ፍሰሀ ከማንበቢያዋ መብራት ርቆ ወደ ሌላኛው የአልጋው ጠርዝ ተጠጋና ፊቱን አዞሮ ተኛ ፡፡ እንደፍላጎቱ ስላልሆነችለት ተበሳጭቶ ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍32❤17
አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?
አሁንም ግፍ አይበቃሽም
ዘንድሮም ለምለም ትያለሽ
ካቀፍሽው ቅጠል ባለፈ
የለመለመ ምን አለሽ?
ካቻምናም አምናም መተሻል
አቅፈንሽ አጥነን ደግሰን
አመትሽ ውበቱ ላይቆይ
እያደር ሊያተራምሰን
አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?
አምና ተስፋ አስደረግሺኝ
ደክሜ ቤቴን ሰራሁኝ
አልቅሼ ልገባበት ስል
ይፈርሳል ሁሉ ሰማሁኝ
አሁንም ተስፋ አልቆረጥኩም
ቃልሽን ስመላልሰው
አመትህ ተባርኳል ብለሽ
የላክሺኝ እንደ ሞኝ ሰው
ስታገል ከማይሽር ህይወት
መቀመቅ ነፍሴን ሲውጣት
ወደፊት ፈቀቅ እያልኩኝ
ሞት ልቤን እንዳይለውጣት
"አበባ አየሆሽ" አትበዪኝ
አበባ አልቸገረኝም
ዘፈንሽ አንገሽግሾኛል
ጨዋታሽ አይሰማኝም
በያመት ደምቀሽ ስትመጪ
ህፃን ልጅ ለምትመስዪው
ግጥሙን በምነግርሽ ቃል
ስትዘፍኚ አስተካክዪው
"የሀገሬ ልጆች ውጡ በተራ
ቅስም ሰብሬ ሰው እስክሰራ
እንኳን ሰውና የለኝም እድል
ሁሌ መጣለው አመት ላጎድል
አመት አጉድዬ ስገባ ቤቴ
ደስታ ይሰማታል የእንጀራ እናቴ"
አደዪ
የሞት ጉዳዪ
"ኡኡ" በዪ
እንደዚህ ብለሽ ዝፈኚ
ግጥሙን አስተካክለሽው
በቃ አንቺም እንዳገሬ ሰው
ጊዜን ነው የተማመንሽው?
"ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ
ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ"
ሆሆሆሆ!
አታፍሪም ደግሞ
ልክ እንደ ንፁህ እንዳልበደለ
ተስፋሽ ምስኪኑን እየገደለ
ከዘመን ዘመን ማትለወጪ
ጉድ ያዘለ አመት አቅፈሽ ምትሰጪ
ሆ ብለሽ መጣሽ?
ሆ ብለሽ ውጪ!
ለተድላ ሳይሆን
ለሞት ዋዜማ ፡ እያስጨፈርሺኝ
በመጣሽ ቁጥር
ሆ የምልልሽ ፡ ሞኝ አደረግሺኝ?
አሁን ንገሪኝ
ስለ አመትሽ
ይብስብኛል ወይስ ድናለው?
ዘፈኑን ተዪ ፡ ያንቺን ስሞታ ለምጄዋለው
ባለእንጀሮችሽ በተራ ገቡ
አዝማች አባትሽ ሌላ አገቡ
እንጨቱን ሰብረሽ ቤት እስክትሰሪ
ለእንጀራ እናትሽ ሳትናገሪ
እድጅ አድረሻል ኮከብ ስትቆጥሪ
እኔ ምስኪኑ
ምን ያገባኛል ስላንቺ ኮከብ
ምን ያገባኛል የእንቅልፍሽ ማጠር
የኔ ችግር ነው ወሰን የሌለው
የኔ ስቃይ ነው የማይቆጠር
እህት አበባ ፡ እህት አበባ
እህት አበባ ስትልሽ ከርማ፤
ጥላሽ ብትሄድም በሀምሌ ጭለማ
እኔ ላይ "አዬዬ".. አትበዪብኝ፡
ለኔ አመቱ ነው የጨለመብኝ።
ተይ ባለጊዜ..
ተይ እንቁጣጣሽ..
ሀገር ጉድ አቅፈሽ ፥
ሁሌ እየመጣሽ፦
እንኩ አትበዪን፡
ሀዘን ቁስላችን ፡ ድኖ ሳይገግም፤
ካምናው የሚብስ
ሌላ አዲስ አመት ..አንፈልግም!
🔘ሚኪያስ ፈይሳ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?
አሁንም ግፍ አይበቃሽም
ዘንድሮም ለምለም ትያለሽ
ካቀፍሽው ቅጠል ባለፈ
የለመለመ ምን አለሽ?
ካቻምናም አምናም መተሻል
አቅፈንሽ አጥነን ደግሰን
አመትሽ ውበቱ ላይቆይ
እያደር ሊያተራምሰን
አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?
አምና ተስፋ አስደረግሺኝ
ደክሜ ቤቴን ሰራሁኝ
አልቅሼ ልገባበት ስል
ይፈርሳል ሁሉ ሰማሁኝ
አሁንም ተስፋ አልቆረጥኩም
ቃልሽን ስመላልሰው
አመትህ ተባርኳል ብለሽ
የላክሺኝ እንደ ሞኝ ሰው
ስታገል ከማይሽር ህይወት
መቀመቅ ነፍሴን ሲውጣት
ወደፊት ፈቀቅ እያልኩኝ
ሞት ልቤን እንዳይለውጣት
"አበባ አየሆሽ" አትበዪኝ
አበባ አልቸገረኝም
ዘፈንሽ አንገሽግሾኛል
ጨዋታሽ አይሰማኝም
በያመት ደምቀሽ ስትመጪ
ህፃን ልጅ ለምትመስዪው
ግጥሙን በምነግርሽ ቃል
ስትዘፍኚ አስተካክዪው
"የሀገሬ ልጆች ውጡ በተራ
ቅስም ሰብሬ ሰው እስክሰራ
እንኳን ሰውና የለኝም እድል
ሁሌ መጣለው አመት ላጎድል
አመት አጉድዬ ስገባ ቤቴ
ደስታ ይሰማታል የእንጀራ እናቴ"
አደዪ
የሞት ጉዳዪ
"ኡኡ" በዪ
እንደዚህ ብለሽ ዝፈኚ
ግጥሙን አስተካክለሽው
በቃ አንቺም እንዳገሬ ሰው
ጊዜን ነው የተማመንሽው?
"ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ
ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ"
ሆሆሆሆ!
አታፍሪም ደግሞ
ልክ እንደ ንፁህ እንዳልበደለ
ተስፋሽ ምስኪኑን እየገደለ
ከዘመን ዘመን ማትለወጪ
ጉድ ያዘለ አመት አቅፈሽ ምትሰጪ
ሆ ብለሽ መጣሽ?
ሆ ብለሽ ውጪ!
ለተድላ ሳይሆን
ለሞት ዋዜማ ፡ እያስጨፈርሺኝ
በመጣሽ ቁጥር
ሆ የምልልሽ ፡ ሞኝ አደረግሺኝ?
አሁን ንገሪኝ
ስለ አመትሽ
ይብስብኛል ወይስ ድናለው?
ዘፈኑን ተዪ ፡ ያንቺን ስሞታ ለምጄዋለው
ባለእንጀሮችሽ በተራ ገቡ
አዝማች አባትሽ ሌላ አገቡ
እንጨቱን ሰብረሽ ቤት እስክትሰሪ
ለእንጀራ እናትሽ ሳትናገሪ
እድጅ አድረሻል ኮከብ ስትቆጥሪ
እኔ ምስኪኑ
ምን ያገባኛል ስላንቺ ኮከብ
ምን ያገባኛል የእንቅልፍሽ ማጠር
የኔ ችግር ነው ወሰን የሌለው
የኔ ስቃይ ነው የማይቆጠር
እህት አበባ ፡ እህት አበባ
እህት አበባ ስትልሽ ከርማ፤
ጥላሽ ብትሄድም በሀምሌ ጭለማ
እኔ ላይ "አዬዬ".. አትበዪብኝ፡
ለኔ አመቱ ነው የጨለመብኝ።
ተይ ባለጊዜ..
ተይ እንቁጣጣሽ..
ሀገር ጉድ አቅፈሽ ፥
ሁሌ እየመጣሽ፦
እንኩ አትበዪን፡
ሀዘን ቁስላችን ፡ ድኖ ሳይገግም፤
ካምናው የሚብስ
ሌላ አዲስ አመት ..አንፈልግም!
🔘ሚኪያስ ፈይሳ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
Telegram
አትሮኖስ
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
😢12❤8👏3
መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም አፄ ኃይለሥላሴ ከዙፋናቸው የወረዱት 48ተኛ ዓመት!
#ጃንሆይ_ያቺን_ሰዓት!
=============================
መስከረም 2, 1967 ዓ.ም የደርግ አባላት 13 ሆነው ወደ ቤተ-መንግሥት ሄዱና ጃንሆይ የአገዛዝ ዘመናቸው ማብቃቱን አረዷቸው፡፡ የደርግ አባላት ቤተ-መንግሥት ደርሰው ንጉሱን አስጠሯቸው፡፡
ንጉሱም በዝግታ ከፎቅ ላይ ወርደው በዙፋናቸው ላይ ሲቀመጡ የደርግ አባላት ደነገጡ፡፡ ሻምበል ደበላ ዲንሳ ደርግ የወሰነውን የውሳኔ ሃሳብ አነበቡ …
"ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲባል በዛሬው ዕለት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከስልጣን ወርደዋል፤ ለደህንነትዎ ሲባልም አስተባባሪው ኮሚቴ ወዳዘጋጀልዎ ቦታ እንዲሄዱ ተወስኗል …" የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ አነበቡ፡፡
ሻምበል ደበላ ውሳኔውን አንበበው ሲጨርሱ ንባባቸውን ሲጀምሩ የሰጡትን ወታደራዊ ሰላምታ ደገሙ፡፡ ንጉሱም ዝም ብለው ቆዩና መናገር ጀመሩ፡፡
"ያነበባችሁትን ሰምተናል፤ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ስንሆን ስም ብቻ አይደለም፡፡ ቢሆንም በየጊዜው የሚለዋወጠው ነገር ደግሞ ላገር የሚጠቅም ነገር እስካለበት…
የኢትዮጵያን ታሪክ ጠብቃችሁ ማልማት ከቻላችሁ የእኛ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃል፤ ካልቻላችሁ የእናንተ ታሪክ ያበቃና የእኛ ይቀጥላል ፤ አገራችንንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ እድል የእኛን መወገድ የሚጠይቅ ከሆነ ስራችንን አቁመን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነን፤ ‹አሁን ተራው የእኛ ነው› ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ›› በማለት ተናገሩ፡፡
… ከዚያም ንጉሱ ውብ በሆነችው ሮልስ ሮይስ መኪናቸው ሳይሆን ባረጀች ሰማያዊ ቮልስ ዋገን መኪና ተጭነው ወደ አራተኛ ክፍለ ጦር ግቢ ተወሰዱ፡፡
"ወደ ዋገን ወርደው ሲተኩ በሌላ" እንዲል ቴዲ አፍሮ ሰላም ዋሉ!!
#ጃንሆይ_ያቺን_ሰዓት!
=============================
መስከረም 2, 1967 ዓ.ም የደርግ አባላት 13 ሆነው ወደ ቤተ-መንግሥት ሄዱና ጃንሆይ የአገዛዝ ዘመናቸው ማብቃቱን አረዷቸው፡፡ የደርግ አባላት ቤተ-መንግሥት ደርሰው ንጉሱን አስጠሯቸው፡፡
ንጉሱም በዝግታ ከፎቅ ላይ ወርደው በዙፋናቸው ላይ ሲቀመጡ የደርግ አባላት ደነገጡ፡፡ ሻምበል ደበላ ዲንሳ ደርግ የወሰነውን የውሳኔ ሃሳብ አነበቡ …
"ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲባል በዛሬው ዕለት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከስልጣን ወርደዋል፤ ለደህንነትዎ ሲባልም አስተባባሪው ኮሚቴ ወዳዘጋጀልዎ ቦታ እንዲሄዱ ተወስኗል …" የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ አነበቡ፡፡
ሻምበል ደበላ ውሳኔውን አንበበው ሲጨርሱ ንባባቸውን ሲጀምሩ የሰጡትን ወታደራዊ ሰላምታ ደገሙ፡፡ ንጉሱም ዝም ብለው ቆዩና መናገር ጀመሩ፡፡
"ያነበባችሁትን ሰምተናል፤ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ስንሆን ስም ብቻ አይደለም፡፡ ቢሆንም በየጊዜው የሚለዋወጠው ነገር ደግሞ ላገር የሚጠቅም ነገር እስካለበት…
የኢትዮጵያን ታሪክ ጠብቃችሁ ማልማት ከቻላችሁ የእኛ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃል፤ ካልቻላችሁ የእናንተ ታሪክ ያበቃና የእኛ ይቀጥላል ፤ አገራችንንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ እድል የእኛን መወገድ የሚጠይቅ ከሆነ ስራችንን አቁመን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነን፤ ‹አሁን ተራው የእኛ ነው› ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ›› በማለት ተናገሩ፡፡
… ከዚያም ንጉሱ ውብ በሆነችው ሮልስ ሮይስ መኪናቸው ሳይሆን ባረጀች ሰማያዊ ቮልስ ዋገን መኪና ተጭነው ወደ አራተኛ ክፍለ ጦር ግቢ ተወሰዱ፡፡
"ወደ ዋገን ወርደው ሲተኩ በሌላ" እንዲል ቴዲ አፍሮ ሰላም ዋሉ!!
❤12😢6😱2
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ስርጉት እኩለ ለሊት ቢያልፍም ኪችን ውስጥ ስራ እየሰራች ስለነበር አልተኛችም..ድንገት ግን የውጭ በራፍ ሲንጎጎ ስትሰማ እጇ ላይ የነበረውን የሸክላ ሰሀን ለቀቀችውን ወለል ላይ አርፎ ፍርክስክስ ብሎ ተሰበረባት፡፡የበሩ መንኳኳት እንደቀጠለ ነው..ቶሎ ብላ ኪችኑን ለቃ ወጣችና ወደሳሎን ሄደች ...
" በፈጣሪ ማን ነው ?" ጠየቀች፡፡
"ስርጉት… እኔ ነኝ ..ክፈቺ."
የሰማችውን ድምፅ ልታምን አልቻለችም ….ለማሰብ ጥቂት ሰከንድ እንኳን ሳታቅማማ
ተንደርድራ ወደበሩ ሄደችና ከፈተችው፡፡
በረንዳው ላይ ተገትሯል…ለደቂቃዎች በራፉን አንደያዘች በትኩረት ተመለከተች፣
‹‹በሰላም ነው ጁኒዬር?››
‹‹ሰላም ነው››መለሰላት፡፡
‹‹ግባ …››አለችና ከበራፉ ዞር አለችለት..ሰተት ብሎ ገባ፡፡
"እዚህ ምን እየሰራህ ነው?"
"አንቺ ጋር መጥቼ ነዋ…ክብር ዳኛ ተኝቶ እንደሚሆን እገምታለው››
"አዎ አባዬ በጊዜ ነው የተኛው።››
የቀድሞ ባለቤቷ በዚህ እኩለ ለሊት እሷን ብሎ የሚመጣበት አንድም አሳማኝ ምክንያት ሊመጣላት አልቻለም፡፡ ቢሆንም ግን….ግድ አልነበራትም። እዚህ መገኘቱ በቂ ነበር። አባቷ ካገመሰው ቦድካ በብርጭቆ ቀዳችና ሰጠችው፡፡ተቀበላትና በቆመበት አንዴ ተጎነጨለት፡፡
"ይህ የሌሊቱ የመጀመሪያ መጠጥህ አይደለም አይደል?"
"አይ..አይደለም." ድምፁን ዝቅ አድርጎ መለሰላት ፡፡
"ወደእኔ እንድትመጣ ለወራት ስጠብቅ ነበር ። ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ አሁን ወደእኔ ስትመጣ ደግሞ ለምን የሚል ጥያቄ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ነው፡፡››አለችው፡፡
" ፈልጌ ነበር." አላት፡፡
ለጁኒየር አእምሮ ያ በቂ ምክንያት እንደሆነ ታውቃለች። ሶፋው ላይ ተቀመጠና ጎትቶ ከጎኑ አስቀመጣት።ከበርካታ ደቂቃ ፀጥታ በኋላ " በእርባታ ድርጅቱ ውስጥ ስለተፈጠረው ችግር ሰምቻለሁ" አለችው.
"አሁን ሁሉ ነገር ሰላም ሆኗል….እሳቱ በጊዜው ነው የተደረሰበት…በጣም የከፋ ሊሆን ይችል ነበር."
እያመነታች እጇን እጁ ላይ አሳረፈች፡፡
‹‹አንተ ግን ራስህን ጠብቅ…ንብረታችሁን ለማቃጠል የደፈረ ጠላት በእናንተም ላይ ቀጥታ ጥቃት ከመፈፀም ወደኃላ ላይል ይችላል፡፡››
"አሁንም ለደህንነቴ ትጨነቂያለሽ?"
"ሁልጊዜ።"አለችው፡፡
‹‹ሰሎሜ እንዳንቺ ጣፋጭ ሆኖልኝ አታውቅም። ››
"የደከመህ እና የተቸገርክ ትመስላለህ?።"
"አዎ ደክሞኛል!!።"
ሶፋው ላይ ሙሉ በሙሉ ወጣና ትራሱን ተንተርሶ አረፈ። "በሰሎሜ ግድያ ላይ ያለው ውዥንብር እየበጠበጠን ነው።ሁሉም ነገር እንደ ገሃነም ተስፋ አስቆራጭ ነው።››አላት፡፡ከትራሱ ቀና አለና እሷ ትከሻ ላይ ተንተራሰ"እህ…ጥሩ መዓዛ አለሽ…ይህ ሽታ ናፍቆኝ ነበር. በጣም ንጹህ. ነው፡፡
"ስለዚህ ምርመራ በጣም የሚያስጨንቅህ ምንድን ነው?"
"ምንም የተለየ ነገር የለም። አለም ነች ። እሷ እና እናቴ ዛሬ ተፋጠው ነበር። እናቴ ስለሰሎሜ አንዳንድ መጥፎ ነገሮችን ነገረቻትና በጣም እንድታዝን አደረገቻት… ያ ጥሩ ትእይንት አልነበረም።››
ክንዱ በወገቧ ዙሪያ ላከውና አቀፋት ..እጇን አነሳች እና ጭንቅላቱ ላይ አሳርፋ እንደህፃን ልጅ ታሻሸው ጀመር፡፡
"ዋሻተኋታል እንዴ?"
"የማጣት ፍርሀት የወለደው ውሸት"ጁኒየር ፍላጎት በማጣት አጉተመተመ።
"እናቷ በተገደለችበት ቀን በረንዳ ላይ እንደነበርኩ አልነገርኳትም።ለምን እንደዛ አደረክ ?"
" በተከታታይ ጥያቄዎች እንድታጣድፈኝ አልፈለኩም።አንዳንድ መመለስ የማልችላቸውን ጥያቄዎች ብትጠይቀኝ እንዴት አደርጋለው?›››
‹‹ ጁኒየር ዳግመኛ ችግር ስለፈጠረችብህ ጠላኋት።"
"አለም ሁኔታውን ልትረዳ አትችልም….ያም የእሷ ጥፋት አይደለም.››
ጁኒየር ስለ ሶለሜ ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነገር ተናግሮ ነበር። የቱንም ያህል ብታበሳጨውም ስለእሷ ጠንከር ያለ ቃል ተናግሮ አያውቅም።ስርጉት በሹክሹክታ
‹‹ይህችን የሰሎሜን ልጅ ልክ እንደእናቷ በጣም እጠላታለሁ››ስትል አንሾካሾከች፡፡
"አሁን ስለዛ አታስቢ። ይህ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ አያደርግም" አላት፡
እጁን አነሳና እርጥበታማ ከንፈሯ ላይ አሳርፉ ዳበሳት …ከለበሰችው ጋወን ያፈነገጡ ጡቶቾን ተመለከተ።እጁን ከከንፈሯ አነሳና ጡቷ ላይ አስቀመጠ…
‹‹እንደዚህ ሳደርግ ሁል ጊዜ ደስ ይልሽ ነበር ።››
"አሁንም አድርገው።››
‹‹እውነት? ››
"ጡቷን ወደ አፉ አቀረበችለት…ጎረሰው…. እጁን በጭኖቿ መካከል ሰነቀረው፡፡እርጥበት ያለውን ፀጉር እየዳበሰ ወደውስጥ መጓዙን ቀጠለ … ስሙን እየጠራች አቃሰተች።
‹‹ካልፈለግሽ ይገባኛል››አላት
"አይ" አለች በፍጥነት "እፈልጋለው እባክህ።›››ተማፀነችው፡፡፡
"ስርጉቴ ያንቺ በርህራሄ የበለጸገ ፍቅራዊ እንክብካቤ ዛሬ ማታ ያስፈልገኛል። ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ሁልጊዜም በአንቺ ልተማመንብሽ እችላለሁ።››ሲል ተናዘዘላት፡፡
ጎንበስ አለችና ከንፈሩን ሳመችው፡፡
"ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት እንዴሰማኝ እንደጣርሽ ነው…አይደል እንዴ?" ብሎ ጠየቃት፡፡
"አዎ ።"አለችና አጎንብሳ ተመለከተችው። ልክ እንደ መልአክ ፈገግ አለላት ። እንደዚያ ሲያያት ምንም ልትከለክለው አቅም አይኖራትም በጭራሽ።
///
"ወ/ሪት አለም…ወ.ሪት አለም?አለሽ እንዴ?››
አለም ድክምክም ብላ ተኝታ ነበር። ጥገና የተደረገላት በሯን በተደጋጋሚ ሲንኳኳ ነው ከእንቅልፎ የነቃችው፡፡ ስትነቃ… ደንዛዛ እና ቀዝቃዛ ነበር።ከመተኟቷ በፊት ለረጅም ሰዓት ከማልቀሷ የተነሳ ዓይኖቿ አብጠው ነበር።
"ምን ፈለክ?" ድምጿ ለጩኸት የቀረበ ነበር።
" ክፈቺልኝ እትዬ…መልዕክት አለሽ?።"
እንደምንም ከአልጋው ወረደችና ጋወኗን ለብሳ ወደሳሎን በመሄድ በራፉን ከፈተች፡፡የተከራየችበት አፓርታማ ዘበኛ ነው
"እትዬ ስልክሽ ከአገልግሎት መስጫ ውጭ ነው ይላል?"
"አዎ…ዝግ ነው….ለምን ፈለከኝ?" ግራ በመጋባት ጠየቀችው፡፡
‹‹እኔ አይደለውም…አቶ ግርማ የሚባሉ ሰውዬ መጥተው ነበር›› ደነገጠች‹‹የት ነው..?አሁን አለ?››
‹‹አይ ሄደዋል …መልዕክት ንገርልኝ ብለዋል….ነገ ጥቃት ዝዋይ ስብሰባ ስላለ እንድትገኚ ብለዋል››
‹‹ዝዋይ..?የምን ስብሰባ?››
‹‹አላውቅም እትዬ …ሰውዬው ናቸው ያሉት››
‹‹ማለት ተሳስተህ እንዳይሆን?››
‹‹አይ ይሄው ማስታወሻ ላይ አስፍሬዋለው…››ብሎ በተወለጋገደ ፅሁፍ የተፃፈውን ማስታወሻ አሳያት፡፡
‹‹እሺ በቃ አመሰግናው››ብላ ሸኘችውና ወደ መኝታ ቤቷ ተመለሰች፡፡ከዛ ስልኳን ፈለግችና አበራችው…ዋናው አቃቢ ህጉ ጋር ደወለች….ስልኩ አይሰራም፡፡፡ስልኳን አስቀመጠችና ጋወኗን አውልቃ ቢጃማ መልበስ ጀመረች፡፡እንደጨረሰች ከእንደገና ስልኳን አነሳችና ደወለች፡፡
"ፖሊስ መምሪያ ነው…ምን እንርዳዎት?."
"እባክህ ኩማንደር ገመዶን ፈልጌ ነበር፡፡"
"እሱ የለም። ሌላ የሚረዳሽ ሰው ጋር እናገናኝሽ?"
"አይ፣ አመሰግናለሁ፣ በቀጥታ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብኝ…ምክትል አቃቢ ህግ አለም ጎበና ነኝ።"
‹‹ክብርት አቃቢ ህግ እንዴት ነሽ….አሁን የት ነሽ?፧"
"እቤቴ ነኝ …ለምን ጠየቅከኝ?"
"ኩማንደር ወደአንቺ እየመጣ ነው….እስከአሁን ይደርሳል››
‹‹ምነው በሰላም…..?››መልሱን ሳይመልስላት በራፏ ሲንኳኳ ሰማች‹‹ እሺ …በል ደህና ሁን…ደርሶል መሰለኝ ››አለችና ስልኩን በመዝጋት ወደሳሎን ሄዳ በራፉን ከፈተችለት፡፡
‹‹እሺ ኩማንደር ?››
‹‹ዞር በይልኝ እንጂ ልግባ።››
‹‹መግባትህ አስፈላጊ ነው?››እያለች በራፉን ለቀቀችለት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ስርጉት እኩለ ለሊት ቢያልፍም ኪችን ውስጥ ስራ እየሰራች ስለነበር አልተኛችም..ድንገት ግን የውጭ በራፍ ሲንጎጎ ስትሰማ እጇ ላይ የነበረውን የሸክላ ሰሀን ለቀቀችውን ወለል ላይ አርፎ ፍርክስክስ ብሎ ተሰበረባት፡፡የበሩ መንኳኳት እንደቀጠለ ነው..ቶሎ ብላ ኪችኑን ለቃ ወጣችና ወደሳሎን ሄደች ...
" በፈጣሪ ማን ነው ?" ጠየቀች፡፡
"ስርጉት… እኔ ነኝ ..ክፈቺ."
የሰማችውን ድምፅ ልታምን አልቻለችም ….ለማሰብ ጥቂት ሰከንድ እንኳን ሳታቅማማ
ተንደርድራ ወደበሩ ሄደችና ከፈተችው፡፡
በረንዳው ላይ ተገትሯል…ለደቂቃዎች በራፉን አንደያዘች በትኩረት ተመለከተች፣
‹‹በሰላም ነው ጁኒዬር?››
‹‹ሰላም ነው››መለሰላት፡፡
‹‹ግባ …››አለችና ከበራፉ ዞር አለችለት..ሰተት ብሎ ገባ፡፡
"እዚህ ምን እየሰራህ ነው?"
"አንቺ ጋር መጥቼ ነዋ…ክብር ዳኛ ተኝቶ እንደሚሆን እገምታለው››
"አዎ አባዬ በጊዜ ነው የተኛው።››
የቀድሞ ባለቤቷ በዚህ እኩለ ለሊት እሷን ብሎ የሚመጣበት አንድም አሳማኝ ምክንያት ሊመጣላት አልቻለም፡፡ ቢሆንም ግን….ግድ አልነበራትም። እዚህ መገኘቱ በቂ ነበር። አባቷ ካገመሰው ቦድካ በብርጭቆ ቀዳችና ሰጠችው፡፡ተቀበላትና በቆመበት አንዴ ተጎነጨለት፡፡
"ይህ የሌሊቱ የመጀመሪያ መጠጥህ አይደለም አይደል?"
"አይ..አይደለም." ድምፁን ዝቅ አድርጎ መለሰላት ፡፡
"ወደእኔ እንድትመጣ ለወራት ስጠብቅ ነበር ። ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ አሁን ወደእኔ ስትመጣ ደግሞ ለምን የሚል ጥያቄ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ነው፡፡››አለችው፡፡
" ፈልጌ ነበር." አላት፡፡
ለጁኒየር አእምሮ ያ በቂ ምክንያት እንደሆነ ታውቃለች። ሶፋው ላይ ተቀመጠና ጎትቶ ከጎኑ አስቀመጣት።ከበርካታ ደቂቃ ፀጥታ በኋላ " በእርባታ ድርጅቱ ውስጥ ስለተፈጠረው ችግር ሰምቻለሁ" አለችው.
"አሁን ሁሉ ነገር ሰላም ሆኗል….እሳቱ በጊዜው ነው የተደረሰበት…በጣም የከፋ ሊሆን ይችል ነበር."
እያመነታች እጇን እጁ ላይ አሳረፈች፡፡
‹‹አንተ ግን ራስህን ጠብቅ…ንብረታችሁን ለማቃጠል የደፈረ ጠላት በእናንተም ላይ ቀጥታ ጥቃት ከመፈፀም ወደኃላ ላይል ይችላል፡፡››
"አሁንም ለደህንነቴ ትጨነቂያለሽ?"
"ሁልጊዜ።"አለችው፡፡
‹‹ሰሎሜ እንዳንቺ ጣፋጭ ሆኖልኝ አታውቅም። ››
"የደከመህ እና የተቸገርክ ትመስላለህ?።"
"አዎ ደክሞኛል!!።"
ሶፋው ላይ ሙሉ በሙሉ ወጣና ትራሱን ተንተርሶ አረፈ። "በሰሎሜ ግድያ ላይ ያለው ውዥንብር እየበጠበጠን ነው።ሁሉም ነገር እንደ ገሃነም ተስፋ አስቆራጭ ነው።››አላት፡፡ከትራሱ ቀና አለና እሷ ትከሻ ላይ ተንተራሰ"እህ…ጥሩ መዓዛ አለሽ…ይህ ሽታ ናፍቆኝ ነበር. በጣም ንጹህ. ነው፡፡
"ስለዚህ ምርመራ በጣም የሚያስጨንቅህ ምንድን ነው?"
"ምንም የተለየ ነገር የለም። አለም ነች ። እሷ እና እናቴ ዛሬ ተፋጠው ነበር። እናቴ ስለሰሎሜ አንዳንድ መጥፎ ነገሮችን ነገረቻትና በጣም እንድታዝን አደረገቻት… ያ ጥሩ ትእይንት አልነበረም።››
ክንዱ በወገቧ ዙሪያ ላከውና አቀፋት ..እጇን አነሳች እና ጭንቅላቱ ላይ አሳርፋ እንደህፃን ልጅ ታሻሸው ጀመር፡፡
"ዋሻተኋታል እንዴ?"
"የማጣት ፍርሀት የወለደው ውሸት"ጁኒየር ፍላጎት በማጣት አጉተመተመ።
"እናቷ በተገደለችበት ቀን በረንዳ ላይ እንደነበርኩ አልነገርኳትም።ለምን እንደዛ አደረክ ?"
" በተከታታይ ጥያቄዎች እንድታጣድፈኝ አልፈለኩም።አንዳንድ መመለስ የማልችላቸውን ጥያቄዎች ብትጠይቀኝ እንዴት አደርጋለው?›››
‹‹ ጁኒየር ዳግመኛ ችግር ስለፈጠረችብህ ጠላኋት።"
"አለም ሁኔታውን ልትረዳ አትችልም….ያም የእሷ ጥፋት አይደለም.››
ጁኒየር ስለ ሶለሜ ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነገር ተናግሮ ነበር። የቱንም ያህል ብታበሳጨውም ስለእሷ ጠንከር ያለ ቃል ተናግሮ አያውቅም።ስርጉት በሹክሹክታ
‹‹ይህችን የሰሎሜን ልጅ ልክ እንደእናቷ በጣም እጠላታለሁ››ስትል አንሾካሾከች፡፡
"አሁን ስለዛ አታስቢ። ይህ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ አያደርግም" አላት፡
እጁን አነሳና እርጥበታማ ከንፈሯ ላይ አሳርፉ ዳበሳት …ከለበሰችው ጋወን ያፈነገጡ ጡቶቾን ተመለከተ።እጁን ከከንፈሯ አነሳና ጡቷ ላይ አስቀመጠ…
‹‹እንደዚህ ሳደርግ ሁል ጊዜ ደስ ይልሽ ነበር ።››
"አሁንም አድርገው።››
‹‹እውነት? ››
"ጡቷን ወደ አፉ አቀረበችለት…ጎረሰው…. እጁን በጭኖቿ መካከል ሰነቀረው፡፡እርጥበት ያለውን ፀጉር እየዳበሰ ወደውስጥ መጓዙን ቀጠለ … ስሙን እየጠራች አቃሰተች።
‹‹ካልፈለግሽ ይገባኛል››አላት
"አይ" አለች በፍጥነት "እፈልጋለው እባክህ።›››ተማፀነችው፡፡፡
"ስርጉቴ ያንቺ በርህራሄ የበለጸገ ፍቅራዊ እንክብካቤ ዛሬ ማታ ያስፈልገኛል። ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ሁልጊዜም በአንቺ ልተማመንብሽ እችላለሁ።››ሲል ተናዘዘላት፡፡
ጎንበስ አለችና ከንፈሩን ሳመችው፡፡
"ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት እንዴሰማኝ እንደጣርሽ ነው…አይደል እንዴ?" ብሎ ጠየቃት፡፡
"አዎ ።"አለችና አጎንብሳ ተመለከተችው። ልክ እንደ መልአክ ፈገግ አለላት ። እንደዚያ ሲያያት ምንም ልትከለክለው አቅም አይኖራትም በጭራሽ።
///
"ወ/ሪት አለም…ወ.ሪት አለም?አለሽ እንዴ?››
አለም ድክምክም ብላ ተኝታ ነበር። ጥገና የተደረገላት በሯን በተደጋጋሚ ሲንኳኳ ነው ከእንቅልፎ የነቃችው፡፡ ስትነቃ… ደንዛዛ እና ቀዝቃዛ ነበር።ከመተኟቷ በፊት ለረጅም ሰዓት ከማልቀሷ የተነሳ ዓይኖቿ አብጠው ነበር።
"ምን ፈለክ?" ድምጿ ለጩኸት የቀረበ ነበር።
" ክፈቺልኝ እትዬ…መልዕክት አለሽ?።"
እንደምንም ከአልጋው ወረደችና ጋወኗን ለብሳ ወደሳሎን በመሄድ በራፉን ከፈተች፡፡የተከራየችበት አፓርታማ ዘበኛ ነው
"እትዬ ስልክሽ ከአገልግሎት መስጫ ውጭ ነው ይላል?"
"አዎ…ዝግ ነው….ለምን ፈለከኝ?" ግራ በመጋባት ጠየቀችው፡፡
‹‹እኔ አይደለውም…አቶ ግርማ የሚባሉ ሰውዬ መጥተው ነበር›› ደነገጠች‹‹የት ነው..?አሁን አለ?››
‹‹አይ ሄደዋል …መልዕክት ንገርልኝ ብለዋል….ነገ ጥቃት ዝዋይ ስብሰባ ስላለ እንድትገኚ ብለዋል››
‹‹ዝዋይ..?የምን ስብሰባ?››
‹‹አላውቅም እትዬ …ሰውዬው ናቸው ያሉት››
‹‹ማለት ተሳስተህ እንዳይሆን?››
‹‹አይ ይሄው ማስታወሻ ላይ አስፍሬዋለው…››ብሎ በተወለጋገደ ፅሁፍ የተፃፈውን ማስታወሻ አሳያት፡፡
‹‹እሺ በቃ አመሰግናው››ብላ ሸኘችውና ወደ መኝታ ቤቷ ተመለሰች፡፡ከዛ ስልኳን ፈለግችና አበራችው…ዋናው አቃቢ ህጉ ጋር ደወለች….ስልኩ አይሰራም፡፡፡ስልኳን አስቀመጠችና ጋወኗን አውልቃ ቢጃማ መልበስ ጀመረች፡፡እንደጨረሰች ከእንደገና ስልኳን አነሳችና ደወለች፡፡
"ፖሊስ መምሪያ ነው…ምን እንርዳዎት?."
"እባክህ ኩማንደር ገመዶን ፈልጌ ነበር፡፡"
"እሱ የለም። ሌላ የሚረዳሽ ሰው ጋር እናገናኝሽ?"
"አይ፣ አመሰግናለሁ፣ በቀጥታ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብኝ…ምክትል አቃቢ ህግ አለም ጎበና ነኝ።"
‹‹ክብርት አቃቢ ህግ እንዴት ነሽ….አሁን የት ነሽ?፧"
"እቤቴ ነኝ …ለምን ጠየቅከኝ?"
"ኩማንደር ወደአንቺ እየመጣ ነው….እስከአሁን ይደርሳል››
‹‹ምነው በሰላም…..?››መልሱን ሳይመልስላት በራፏ ሲንኳኳ ሰማች‹‹ እሺ …በል ደህና ሁን…ደርሶል መሰለኝ ››አለችና ስልኩን በመዝጋት ወደሳሎን ሄዳ በራፉን ከፈተችለት፡፡
‹‹እሺ ኩማንደር ?››
‹‹ዞር በይልኝ እንጂ ልግባ።››
‹‹መግባትህ አስፈላጊ ነው?››እያለች በራፉን ለቀቀችለት፡፡
❤82👍15
#ሲያጋጥም
ልቤ በግኖ ነዶ ራሴን በፎከትኩት
ሌላኛ ጠላቴን ቅማሌን ገደልኩት፡፡
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ልቤ በግኖ ነዶ ራሴን በፎከትኩት
ሌላኛ ጠላቴን ቅማሌን ገደልኩት፡፡
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😁8👍3😢1
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ከሰፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
የዝዋዩን ስብሰባ ተሳትፈው በተመለሱ በማግስት ዋና አቃቢ ህጉና አለም በቢሮቸው ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡
እሱ እጁ ላይ አንድ ደብዳቤ በትኩረት እየተመለከተ ትካዜ ውስጥ ገብቷል …
‹‹ክብሩ አቃቢ ህግ…ምነው ችግር አለ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ወደስራ ስትመጪ ከተማው ውስጥ የታዘብሽው ነገር የለም?››
‹‹ምንን በተመለከተ…?››
‹‹የምታሳድጃቸውን ሰዎች በተመለከተ፡፡››
‹‹እ..የጁኒዬር ፍሰሀ ምስል የያዘ የምርጫ ቅስቀሳ ፖስተር ከተማውን ሞልቶታል፡፡ገዢውን ፓርቲ ወክሎ ለተወካዬች ምክር ቤት መወዳደሩ እርግጥ ሆኗል….ያንን ነው የታዘብኩት›››
‹‹አዎ…የዚህ ትርጉም ገብቶሻል ብዬ አስባለው….ጠላቶችሽ ከቀን ወደቀን የማይነኩ አይነት ኃያል እየሆኑ ነው፡፡››
"ምንም ሆነ ምንም …እኔ የጀመርኩትን ወደፊት ከመቀጠል አያስቆመኝም››
‹‹አይ የግድ ለማቆም ትገደጂያለሽ…..››
‹‹ለምን ተብሎ››
እጁ ላይ ያለውን ደብዳቤ ወረወረላት፤ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ ተቀበችውና አነበበች..ማመን ነው ያቃታት….ከመቀመጫዋ ተነሳች…ተወራጨች…
‹‹ምንድነው ይሄ…››
‹‹ታላቅ እድል ነው….እንደኦሮሚያ ይህንን እድል ካገኙ ሁለት የህግ ባለሞያዎች መከካል አንዷ አንቺ ነሽ…ቀጣዩን ስድስት ወር ቻይና ሄደሽ ይህንን ስልጠና ትወስጂያለሽ…ከዛ ስትመለሺ እርግጠኛ ነኝ….ወይ እዛው ክልል ዋናው ቢሮ ካለበለዚያም ሌላ ዞን በዋና አቃቢ ህግነት ትመደቢያለሽ››
‹‹እኔ መች ፈለኩና…?በምን መስፈርት ነው እኔ የተመረጥኩት….?››
‹‹እሱን እኔ አላውቅም..››
‹‹አወቅክም አላወቅክም ..ይህ እኔን ከእዚህ ገለል ለማድረግ የተሸረበ ሴራ ነው..ለስድስት ወር ከሀገር ወጣሁ ማለት… እስከዛ ጁኒዬር ምርጫውን አሸንፎ ምክርቤት ይገባል…ስመለስም ወደእዚህ ከተማ ስለማይልኩኝ የእናቴ ገዳይ ነፃ እንደሆነ ይቀጥላል ማለት ነው…ይህን መቀበል አልችልም፡፡››
‹‹መቀበልማ የግድ ነው….በዚህ ስራ ላይ ለመቆየት ያለሽ እድል ከ15ቀን አይበልጥም……እሱም ምን አልባት ነው፡፡ደብዳቤውን አንብበሻል አይደል?ይሄ ደብዳቤ ከደረሰት ቀን አንስቶ እጇት ላይ ያለውን ስራና የመንግስት ንብረት ለተተኪው ሰው አስረክበው ለጉዞው ይዘጋጁ ነው የሚለው፡፡››
በንዴት ተንዘረዘረች‹‹አየህ የሰዎቹን ተንኮል….ይህንን ያቀናጁት አቶ ፍሰሀ እና ገመዶ እናም ዳኛው እንደሆኑ እርግጠኛ ነኝ…በዘዴ እኔን ለማስወገድ የሄዱበትን ርቀት የማይታመን ነው››
‹‹አይ የእነሱ እጅ የለበትም ብዬ ልከራከርሽ አልፈልግም….እንደውም ሁኔታውን በደንብ አንድትረጂ ነው የምፈልገው…የሰዎች አቅምና ኃይል ክልል እና ፌዴራል ድረስ ምን ያህል የተዘረጋ እና ስር የሰደደ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡አንቺ በማትጎጂበት መንገድ ከጀመርሽው መንገድ ዞር ለማድረግ የቀየሱት ጥበብ የተሞላበት ዘዴ ነው፡፡ያ ማለት እኔ እፈራው እንደነበር ቀጥታ አንቺ ላይ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሊያደርሱብሽ ፍላጎቱም ሆነ እቅዱ የላቸውም ማለት ነው….ይሄንን በማወቄ አፎይታ ተሰምቶኛል፡፡››
"አንተም እንድሄድ ነው የምትፈልገው?"
"አዎ፣ ሳስበው ለአንቺም የሚበጅሽ እንደዛ ማድረጉ ነው።" በለሆሳስ መለሰላት፡፡
ዋና አቃቢ ህጉ ለእሷ ከአለቃ ይልቅ እንደ ጓደኛ ነው። ስለዚህ እሷ ደህነንት ያሳስበዋል፡፡ " እንደምንም አንድ ወር በስራዬ ላይ እንድቆይ አድርግ"ተማፀነችው፡፡
" እንደዛማድረግ አልችልም.. አልፈልግም."
‹‹እባክህ››
"አንድ ሳምንት አለሽ…ልክ የዛሬ ሳምንት የቢሮሽን ቁልፍ አስረክበሽ ወደ አዲስ አበባሽ ጉዞ ትጀምሪያለሽ።"
" አታስበው…የመጣሁበትን ከግብ ሳላደርስ ከዚህች ከተማ ንቅንቅ አልልም››
‹‹እንዳዛ ከሆነ ስራሽን ታጪያለሽ››
‹‹ስራውን በስራነቱ እንደማልፈልገው ታውቃለህ….የእናቴን ገዳይ እንዳገኝ ካረዳኝ ስራው ምን ያደርግልኛል?››
‹‹የውጭ እድሉም ይቃጥልብሻል››
‹‹አልፈልገውም …ለሌላ ሰው ስጡት፡፡››
‹‹ይሄንን ስራ ከለቀቅሽ…በራስሽ ብቻሽን ነው የምትቆሚው…የቢሮው እገዛና ጥበቃ አይኖርሽም::እንደአንድ ተራ ግለሰብ እነሱን መጋፈጥ እትችይም….››
‹‹ያንን ስሞክር ነው የማውቀው››
"በእግዚያብሄር ስም …ምን አይነት ግትር ሴት ነሽ?"
‹‹ይህ ግትርነት አይደለም…እዚ ከተማ ስመጣ አሁን እናቴን ገድለዋት ይሆናሉ ብዬ የምጠረጥራቸው ሶስት ሰዎች ነበሩ ..ወደዚህ መጥቼ ምርመራዬን ከጀመርኩ በኃላ ተጠርጣሪዎች ወደአምስት አድገዋል፡፡››
‹‹ጭራሽ ተጠርጣሪዎችሽን ቁጥር እያጠበብሽ መሄድ ሲገባሽ እያንዛዛሽው መጣሽ ማለት ነው…ለመሆኑ እነማን ናቸው የተካተቱበት?››
‹‹የአቶ ፍሰሀ ባለቤት ሳራ እና የጁኒዬር የቀድሞ ባለቤት ስርጉት››
ሲጋራውን ከፓኮው አወጣና ለኮሰ ፣ አንዴ ማገና ጭሱን በአየሩ ላይ በተነው ‹‹እንሱ ደግሞ ለምን ብለው ነው እናትሽን የሚገድሏት?››ሲል ከመገረም ውስጥ ሳይወጣ ጠየቃት፡፡
እንደውም ከወንዶቹ በተሻለ እናቴን ለመግደል በቂ ምክንያት እና ጥላቻ ያላቸው ሴቶቹ ናቸው፡፡ወ.ሮ ሳራ ልጇ ጁኒዬር እናቴን እዳያገባ ስትጥር ነበር ቆየችው....በዚህ ጉዳይ ከአያቴ ጋር ሁሉ እንተጨቃጨቁ በገዛ አንደበቷ ነው የነገረቺኝ፡፡በእሷ እምነት እናቴ በሁሉም መስፈርት ለአንድዬና ብቸኛ ልጇ ሚስት ለመሆን እንደማትመጥን ነው የምታስበው፡፡እና ልጇም ተመሳሳዪን እንዲያስብ ብዙ ጊዜ ሞክራ እንዳልተሳካላት ነግራኛለች..ይታይህ ታዲያ ድንገት እኔን ወልዳ አራስ የሆነችውን እናቴን ሊያገባ እየተዘጋጀ ነው ብለው ሲነግሯት እሷን አስወግዳ ልጇን ነፃ ለማውጣት ብትሞክር ምን ይገርማል…?በሌላ በኩል የዳኛው ልጅ የሆነችው ስርጉት ደግሞ ጁኒዬርን ለአመታት ስታፈቅረው እና የራሷ እንዲሆን ስትመኘው የነበረ ሰው ነው….እሱን የራሷ እንዳታደርገው እንቅፋት የሆነቻት እናቴ ነች..ይባስ ብሎ ከአንድ ዲቃላ ልጇ ጋር ሊያገባት እንደሆነ ስትሰማ ምንድነው የሚሰማት….?ደግሞ እናቴን እንዴት አምርራ ትጠላት እንደነበረና መሞቷን እንደግልግል እንደወሰደችው እዛ ድግስ ላይ
የተገናኘን ቀን ምንም ሳትደብቅ ነግራኛለች፡፡እና በአጠቃላይ ከእናቴ ሞት ይበልጥ ተጠቃሚ የሆነው ማን ነው? ብለን ሰንጠይቅ ለጊዜው ሁለቱ ሴቶች የሚል መልስ ነው ምናገኘው…ሳራም ልጇ የማትፈልጋትን ሴት ከማግባት ተገላገለ..ስርጉትም እናቴ ሞታ ብዙም ሳይቆይ ለአመታት ስታፈቅረው የነበረውን ሰው አሳምና ማግባት ቻለች….ምንም እንኳን ጋብቻው ረጅም እድሜ መቆየት ባይችልም ለጊዜው ግን ተጠቃሚ ነበረች፡፡››
በጥሞና ሲያዳምጣት የቆየው አቃቢ ህግ ጭንቅላቱን እየነቀነቀ‹‹ጥሩ መላ ምት ነው››አላት
፡፡
"በዚህ ጉዳይ እኔን የገረመኝን አንድ ነገር ታውቃለህ? ዳኛው። የእናቴን ግድያ በተመለከተ ተጠርጣሪዎች በጠቅላላ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ከእሱ ጋር ትስስር ያላቸው ናቸው..ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው ትክክለኛውን ፍርድ ሊፈርድ የሚችለው?።"
በማግስቱ የአለም የመጀመሪ ስራ የዋና አቃቢ ህጉን ቢሮ ማንኳኳት ነበር፡፡ ባልተሟሸ የጥዋት ሻካራ ድምፅ፡፡‹‹ይግቡ››አላት፡፡
በራፉን ገፋ አድርጋ ገባች
‹‹የመጀመሪያ ባለጉዳይ አንቺ ትሆኜያለሽ ብዬ አልጠበቅኩም ነበር››
ለቀልዱ ምንም መልስ ለመስጠት ፍላጎት አልነበራትም…ጠረጴዛውን ተጠጋች እና ከቦርሰዋ ውስጥ አንድ ወረቀት አውጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት፡፡ጠቅላላ አቃቢ ህጉ በሁኔታዋ ግራ ተጋብቶ‹‹ምንድነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ስራ መልቀቂያ ነው››
‹‹ማለት ?አልገባኝም››
፡
፡
#ከሰፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
የዝዋዩን ስብሰባ ተሳትፈው በተመለሱ በማግስት ዋና አቃቢ ህጉና አለም በቢሮቸው ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡
እሱ እጁ ላይ አንድ ደብዳቤ በትኩረት እየተመለከተ ትካዜ ውስጥ ገብቷል …
‹‹ክብሩ አቃቢ ህግ…ምነው ችግር አለ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ወደስራ ስትመጪ ከተማው ውስጥ የታዘብሽው ነገር የለም?››
‹‹ምንን በተመለከተ…?››
‹‹የምታሳድጃቸውን ሰዎች በተመለከተ፡፡››
‹‹እ..የጁኒዬር ፍሰሀ ምስል የያዘ የምርጫ ቅስቀሳ ፖስተር ከተማውን ሞልቶታል፡፡ገዢውን ፓርቲ ወክሎ ለተወካዬች ምክር ቤት መወዳደሩ እርግጥ ሆኗል….ያንን ነው የታዘብኩት›››
‹‹አዎ…የዚህ ትርጉም ገብቶሻል ብዬ አስባለው….ጠላቶችሽ ከቀን ወደቀን የማይነኩ አይነት ኃያል እየሆኑ ነው፡፡››
"ምንም ሆነ ምንም …እኔ የጀመርኩትን ወደፊት ከመቀጠል አያስቆመኝም››
‹‹አይ የግድ ለማቆም ትገደጂያለሽ…..››
‹‹ለምን ተብሎ››
እጁ ላይ ያለውን ደብዳቤ ወረወረላት፤ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ ተቀበችውና አነበበች..ማመን ነው ያቃታት….ከመቀመጫዋ ተነሳች…ተወራጨች…
‹‹ምንድነው ይሄ…››
‹‹ታላቅ እድል ነው….እንደኦሮሚያ ይህንን እድል ካገኙ ሁለት የህግ ባለሞያዎች መከካል አንዷ አንቺ ነሽ…ቀጣዩን ስድስት ወር ቻይና ሄደሽ ይህንን ስልጠና ትወስጂያለሽ…ከዛ ስትመለሺ እርግጠኛ ነኝ….ወይ እዛው ክልል ዋናው ቢሮ ካለበለዚያም ሌላ ዞን በዋና አቃቢ ህግነት ትመደቢያለሽ››
‹‹እኔ መች ፈለኩና…?በምን መስፈርት ነው እኔ የተመረጥኩት….?››
‹‹እሱን እኔ አላውቅም..››
‹‹አወቅክም አላወቅክም ..ይህ እኔን ከእዚህ ገለል ለማድረግ የተሸረበ ሴራ ነው..ለስድስት ወር ከሀገር ወጣሁ ማለት… እስከዛ ጁኒዬር ምርጫውን አሸንፎ ምክርቤት ይገባል…ስመለስም ወደእዚህ ከተማ ስለማይልኩኝ የእናቴ ገዳይ ነፃ እንደሆነ ይቀጥላል ማለት ነው…ይህን መቀበል አልችልም፡፡››
‹‹መቀበልማ የግድ ነው….በዚህ ስራ ላይ ለመቆየት ያለሽ እድል ከ15ቀን አይበልጥም……እሱም ምን አልባት ነው፡፡ደብዳቤውን አንብበሻል አይደል?ይሄ ደብዳቤ ከደረሰት ቀን አንስቶ እጇት ላይ ያለውን ስራና የመንግስት ንብረት ለተተኪው ሰው አስረክበው ለጉዞው ይዘጋጁ ነው የሚለው፡፡››
በንዴት ተንዘረዘረች‹‹አየህ የሰዎቹን ተንኮል….ይህንን ያቀናጁት አቶ ፍሰሀ እና ገመዶ እናም ዳኛው እንደሆኑ እርግጠኛ ነኝ…በዘዴ እኔን ለማስወገድ የሄዱበትን ርቀት የማይታመን ነው››
‹‹አይ የእነሱ እጅ የለበትም ብዬ ልከራከርሽ አልፈልግም….እንደውም ሁኔታውን በደንብ አንድትረጂ ነው የምፈልገው…የሰዎች አቅምና ኃይል ክልል እና ፌዴራል ድረስ ምን ያህል የተዘረጋ እና ስር የሰደደ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡አንቺ በማትጎጂበት መንገድ ከጀመርሽው መንገድ ዞር ለማድረግ የቀየሱት ጥበብ የተሞላበት ዘዴ ነው፡፡ያ ማለት እኔ እፈራው እንደነበር ቀጥታ አንቺ ላይ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሊያደርሱብሽ ፍላጎቱም ሆነ እቅዱ የላቸውም ማለት ነው….ይሄንን በማወቄ አፎይታ ተሰምቶኛል፡፡››
"አንተም እንድሄድ ነው የምትፈልገው?"
"አዎ፣ ሳስበው ለአንቺም የሚበጅሽ እንደዛ ማድረጉ ነው።" በለሆሳስ መለሰላት፡፡
ዋና አቃቢ ህጉ ለእሷ ከአለቃ ይልቅ እንደ ጓደኛ ነው። ስለዚህ እሷ ደህነንት ያሳስበዋል፡፡ " እንደምንም አንድ ወር በስራዬ ላይ እንድቆይ አድርግ"ተማፀነችው፡፡
" እንደዛማድረግ አልችልም.. አልፈልግም."
‹‹እባክህ››
"አንድ ሳምንት አለሽ…ልክ የዛሬ ሳምንት የቢሮሽን ቁልፍ አስረክበሽ ወደ አዲስ አበባሽ ጉዞ ትጀምሪያለሽ።"
" አታስበው…የመጣሁበትን ከግብ ሳላደርስ ከዚህች ከተማ ንቅንቅ አልልም››
‹‹እንዳዛ ከሆነ ስራሽን ታጪያለሽ››
‹‹ስራውን በስራነቱ እንደማልፈልገው ታውቃለህ….የእናቴን ገዳይ እንዳገኝ ካረዳኝ ስራው ምን ያደርግልኛል?››
‹‹የውጭ እድሉም ይቃጥልብሻል››
‹‹አልፈልገውም …ለሌላ ሰው ስጡት፡፡››
‹‹ይሄንን ስራ ከለቀቅሽ…በራስሽ ብቻሽን ነው የምትቆሚው…የቢሮው እገዛና ጥበቃ አይኖርሽም::እንደአንድ ተራ ግለሰብ እነሱን መጋፈጥ እትችይም….››
‹‹ያንን ስሞክር ነው የማውቀው››
"በእግዚያብሄር ስም …ምን አይነት ግትር ሴት ነሽ?"
‹‹ይህ ግትርነት አይደለም…እዚ ከተማ ስመጣ አሁን እናቴን ገድለዋት ይሆናሉ ብዬ የምጠረጥራቸው ሶስት ሰዎች ነበሩ ..ወደዚህ መጥቼ ምርመራዬን ከጀመርኩ በኃላ ተጠርጣሪዎች ወደአምስት አድገዋል፡፡››
‹‹ጭራሽ ተጠርጣሪዎችሽን ቁጥር እያጠበብሽ መሄድ ሲገባሽ እያንዛዛሽው መጣሽ ማለት ነው…ለመሆኑ እነማን ናቸው የተካተቱበት?››
‹‹የአቶ ፍሰሀ ባለቤት ሳራ እና የጁኒዬር የቀድሞ ባለቤት ስርጉት››
ሲጋራውን ከፓኮው አወጣና ለኮሰ ፣ አንዴ ማገና ጭሱን በአየሩ ላይ በተነው ‹‹እንሱ ደግሞ ለምን ብለው ነው እናትሽን የሚገድሏት?››ሲል ከመገረም ውስጥ ሳይወጣ ጠየቃት፡፡
እንደውም ከወንዶቹ በተሻለ እናቴን ለመግደል በቂ ምክንያት እና ጥላቻ ያላቸው ሴቶቹ ናቸው፡፡ወ.ሮ ሳራ ልጇ ጁኒዬር እናቴን እዳያገባ ስትጥር ነበር ቆየችው....በዚህ ጉዳይ ከአያቴ ጋር ሁሉ እንተጨቃጨቁ በገዛ አንደበቷ ነው የነገረቺኝ፡፡በእሷ እምነት እናቴ በሁሉም መስፈርት ለአንድዬና ብቸኛ ልጇ ሚስት ለመሆን እንደማትመጥን ነው የምታስበው፡፡እና ልጇም ተመሳሳዪን እንዲያስብ ብዙ ጊዜ ሞክራ እንዳልተሳካላት ነግራኛለች..ይታይህ ታዲያ ድንገት እኔን ወልዳ አራስ የሆነችውን እናቴን ሊያገባ እየተዘጋጀ ነው ብለው ሲነግሯት እሷን አስወግዳ ልጇን ነፃ ለማውጣት ብትሞክር ምን ይገርማል…?በሌላ በኩል የዳኛው ልጅ የሆነችው ስርጉት ደግሞ ጁኒዬርን ለአመታት ስታፈቅረው እና የራሷ እንዲሆን ስትመኘው የነበረ ሰው ነው….እሱን የራሷ እንዳታደርገው እንቅፋት የሆነቻት እናቴ ነች..ይባስ ብሎ ከአንድ ዲቃላ ልጇ ጋር ሊያገባት እንደሆነ ስትሰማ ምንድነው የሚሰማት….?ደግሞ እናቴን እንዴት አምርራ ትጠላት እንደነበረና መሞቷን እንደግልግል እንደወሰደችው እዛ ድግስ ላይ
የተገናኘን ቀን ምንም ሳትደብቅ ነግራኛለች፡፡እና በአጠቃላይ ከእናቴ ሞት ይበልጥ ተጠቃሚ የሆነው ማን ነው? ብለን ሰንጠይቅ ለጊዜው ሁለቱ ሴቶች የሚል መልስ ነው ምናገኘው…ሳራም ልጇ የማትፈልጋትን ሴት ከማግባት ተገላገለ..ስርጉትም እናቴ ሞታ ብዙም ሳይቆይ ለአመታት ስታፈቅረው የነበረውን ሰው አሳምና ማግባት ቻለች….ምንም እንኳን ጋብቻው ረጅም እድሜ መቆየት ባይችልም ለጊዜው ግን ተጠቃሚ ነበረች፡፡››
በጥሞና ሲያዳምጣት የቆየው አቃቢ ህግ ጭንቅላቱን እየነቀነቀ‹‹ጥሩ መላ ምት ነው››አላት
፡፡
"በዚህ ጉዳይ እኔን የገረመኝን አንድ ነገር ታውቃለህ? ዳኛው። የእናቴን ግድያ በተመለከተ ተጠርጣሪዎች በጠቅላላ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ከእሱ ጋር ትስስር ያላቸው ናቸው..ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው ትክክለኛውን ፍርድ ሊፈርድ የሚችለው?።"
በማግስቱ የአለም የመጀመሪ ስራ የዋና አቃቢ ህጉን ቢሮ ማንኳኳት ነበር፡፡ ባልተሟሸ የጥዋት ሻካራ ድምፅ፡፡‹‹ይግቡ››አላት፡፡
በራፉን ገፋ አድርጋ ገባች
‹‹የመጀመሪያ ባለጉዳይ አንቺ ትሆኜያለሽ ብዬ አልጠበቅኩም ነበር››
ለቀልዱ ምንም መልስ ለመስጠት ፍላጎት አልነበራትም…ጠረጴዛውን ተጠጋች እና ከቦርሰዋ ውስጥ አንድ ወረቀት አውጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት፡፡ጠቅላላ አቃቢ ህጉ በሁኔታዋ ግራ ተጋብቶ‹‹ምንድነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ስራ መልቀቂያ ነው››
‹‹ማለት ?አልገባኝም››
❤44👍6👎1👏1
‹‹ማለትማ ፣ስራችሁን አልፈልግም፡፡››
‹‹እስቲ ቁጭ በይ›› ቁጭ አለች፡፡
‹‹ምን እያደረግሽ ነው…?ስራውን ለቀሽስ…?››
‹‹እነሱ ማንኛውንም ዘዴ ተጠቅመው እኔን ሊያስወግዱኝ ነው አይደለ እየሞከሩ ያሉት?..እኔም ስራዬን ለቅቄ በነፃነት በማንኛውም ነገር እፋለማቸዋለው››
‹‹በማንኛውም ነገር ማለት?››
‹‹በማንኛውም ነገር ማለትማ በማንኛውም ነገር ነው››
‹‹እኔ እንደታናሽ እህቴ ነው የማይሽ…ስትጎጂ ማየት አልፈልግም…እነሱን በወንጀለኝነት ሚያስጠይቅ ምንም አይነት ተጨባጭ ማስረጃ አታገኚም…ብታገኚ እንኳን ፍርድ ቤት አቅርበሽ ፍትህ ከማስገኘትሽ በፊት መረጃውን በሆነ መንገድ ያጠፉታል!!››
‹‹አይ አሁን እነሱን ለፍትህ ማቅረብ አይደለም የምፈልገው….መበቀል ነው…እኔን ለማስወገድ እንደሞከሩት እኔም አስወግዳቸዋለው…..ስማቸውንም፤ሀብታቸውንም ኃይላቸውንም እንዲያጡ ነው የማደርገው፡፡
‹‹እንዴት አድርገሽ?››
‹‹ዝርዝሩን አልነግርህም››
‹‹ምነው እኔንም ከእነሱ እንደአንዱ አድርገሽ እያየሺኝ ነው እንዴ?››
‹‹አይ እንደዛ አላልኩም..ግን ለጊዜው እቅዴን ለማንም የመናገር ፍላጎት የለኝም››
‹‹ጥሩ …ግን ሌላ እርምጃ እንዲወስዱብሽና እንደእናትሽ አንዲያጠፉሽ ምክንያት አትስጪያቸው››
‹‹ለማንኛውም ለምክርህ አመሰግናለው…..ቢሮዬ ገብቼ የግል እቃዎቼን ልሰብስብ››
‹‹አረ እስኪ ተረጋጊ…መልቀቂያሽን እኮ ገና አልተቀበልኩም››
‹‹‹ተቀበልክም አልተቀበልክም…ሀሳቤን አታስቀይረኝም….ምን አልባት ካላሰርከኝ በስተቀር
›› አፉን እንደከፈተ ቢሮውን ለቃ ወጣች፡፡
///
አለም ድንገት ነው የገመዶ ቤት የተገኘችው፡፡እየመጣሁ ነው ብላ ስትደውልለት በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ ነበር የጠበቃት፤፡፡መቆጣቷን እና ማኩረፏን ለማወቅ የእሷን ገፅታ ማየት አላስፈለገውም። እሷ ፍጹም ኩስትርትር ብላ ከረሜላ የከለከሏት ህፃን መስላለች ፡፡ ፊት ለፊቱ ኩርሲ አስቀመጠና እንድትቀመጥ ጋበዛት ፡፡እየጠለቀች ያለችው ጀንበር የምትረጨው ጨረር በፀጉሯ ላይ አርፎ የሚያበራ ደማቅ ነበልባል ፈንጥቆ ይታያል ።
"ዛሬ ጥዋት ስራ ገብተሸ ወዲያው እንደወጣሽና …ተመልሰሽ እንዳልገባሽ ነገሩኝ … ምን ሆና ይሆን ብዬ እያሰብኩ ነበር፡፡በሰላም ነው ?››አላት፡፡
"አንተ ውሸታም ፣ አታላይ ፣ ምናልባትም ነፍሰ ገዳይ ነህ።"
"ከመጀመሪያው ጀምሮ በእኔ ላይ ያለሽ አስተያየት ይህ ነበር…. የማላውቀውን አንድ አዲስ ነገር ንገሪኝ.››
ቆይ የሶሌ ኢንተርፕርይዝ 30 ፐርሰንት ድርሻ ያንተ እንደሆነ ለምን ሳትነግረኝ?››
ያልጠበቀው ወቀሳ ነው የገጠመው" ለምን ብዬ ነግርሻለሁ…..አግብቼሽ ንብረት ሳልቆጥርልሽ ያታለልኩሽ እኮ ነው ያስመሰልሽው?።"
‹‹ነገሩን አታደባብሰው…እዛ እንስሳት እራባታ ውስጥ ጥቂት ፈረሶች እንዳሉህ አይነት እድርገህ ነበር የነገርከኝ….ግን አንተ የጠገበ ሚሊዬነር ነህ፡፡››
‹‹እና ምነው ?ከፋሽ?››
‹‹ደሞዝህ 15 ሺ ብር አይሞላም…ይሄንን ሁሉ ብር ከየት አገኘህ?››
‹‹እንዴ ምርመራሽን ከግድያ ወንጀል ወደሙስና ልታዞሪው አሰብሽ እንዴ?…በንግድ ስራዬ ውስጥ ጣልቃ ለመግባት ምንም መብት የለሽም። ይህ ከአንቺ የግድያ ጉዳይ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም።"
"ይህን ምርመራ ወደ ውጤት ያደርሰኛል ብዬ ባመንኩበት ባሻኝ መንገድ የማስኬድ ሙሉ መብት አለኝ."
‹‹ወደሌሎች ነገሮች ጠልቀሽ ለመግባት በሞከርሽ መጠን የበለጠ ወደአደጋ እየቀረብሽ መሆኑን ልንግርሽ እፈልጋለው፡፡››
‹‹በዚህ መልኩ ስታስፈራራኝ ይሄ የመጀመሪያ ቀንህ አይደለም…ይህን ምርመራ እንዳይሳካልኝ በየደረጃው እንቅፋት ስታስቀምጥብኝ ነበር። ባጅህን ተጠቅመህ ገዳዩን ማንም ይሁን ማን እንዳላገኘው እየተከላከልክ ነው… ምክንያቱም የትኛውም የእናንተ ክበብ ውስጥ ባለ ሰው ላይ ክስ ቢመሰረት የሶሌን ኢንተርፕራይዝ የአክሲዬን ድርሻ ሆነ የገበያ ተቀባይነት ገደል ይገባል፡፡
‹‹እንዴት ማለት?፡፡››
‹‹የሶሌ ኢንተርፕራይዝ 10 ፐርሰንቱ የስርጉት ድርሻ ነው….ጁኒዬር የ15 ፐርሰንት አለው፣ እናቱ ሳራ 10 ፐርሰንት አላት…አቶ ፍሰሀ 35 ፐርሰንት ሲኖረው አንተ ደግሞ 30 ፐርሰንት አለህ፡፡››
ውስጡ በንዴት ሲንቀለቀል ታወቀው….ግን እንዲህ ተበሳጭቶባት እንኳን ዘለህ እነቃት የሚል ስሜት ሳይሆን እየተናነቀው ያለው ዘለህ ከንፈሯ ላይ ተጣበቅ የሚል ስሜት ነው፡፡ ግን እንደምንም እራሱን ተቆጣጥሮ
‹‹ለመሆኑ ይሄንን መረጃ ከየት አገኘሽው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ዋናው መረጃው ትክክል መሆኑ ነው ፡፡ምንጮቼንማ ለምን ብዬ አጋልጬ እሰጣለው፡፡››
‹‹ይሄ እኮ ምንም ሚስጥር የለውም…››
ከት ብላ ሳቀች…….
‹‹ምን ያስቅሻል?››
‹‹አለው እንጂ….ተመልከት….በምንም አይነት ስሌት አንተ እና ስርጉት የዚህ ኢንተርፕራይዝ የአክሲዬን ድርሻ ባለቤቶች ትሆናላችሁ ብዬ አስቤ አላውቅም..እርግጥ አንተ ከቤተሰቡ ጋር ባለህ ቤተሰባዊ ግንኙነት አንዳንድ ነገሮችን እየሰራህ ጠቀም ያለ ገንዘብ እንደምትቀበላቸው ግምቱ ነበረኝ…..ግን ተመልከት ከአቶ ፍሰሀ ቀጥሎ ሁለተኛው ትልቁ
አክሲዬን የማን ነው…?ያንተ፡፡ 30 ፐርሰንት…. ከልጁ ጁኒዬር በእጥፍ የሚበልጥ የአክሲዬን ድርሻ አለህ››
‹‹ምኑ ይገርማል….ጁኒዬር እኮ እድሜ ልኩን በየመዝናኛ ቦታው እየትሽከረከረ ሲዝናና እና ከሴቶች ጋር አለሙን ሲቀጭ የኖረ ሰው ነው….እኔ ደግሞ ድህነት ስፀየፍ የኖርኩና ያንንም ለማሸነፍ ቀን ከሌት የምለፋና የምጥር ሰው ነኝ…..የእኔ ከእሱ እጥፍ የአክሲዬን ባለድርሻ መሆኔን ነው የሚገርምሽ? በአባቱ ባይሆን አይደለም 15 ፐርሰንት አንድ ፐርሰንትም አይኖረውም ነበር››፡፡
‹‹እሺ ስርጉትስ?››
‹‹ስርጉት ምን ሆነች?››
‹‹ድርሻው በእሷ ስም ይሁን እንጂ ንብረትነቱ የዳኛው ነው አይደል?››
‹‹ያምሻል እንዴ…የራሷ ነው…የጁኒዬር ሚስት እኮ ነበረች፡፡››
‹‹አይ የአክሲዬን ባለድርሻ የሆነችው አናቴ በሞተች ከ15ተኛ ቀን በኋላ ሲሆን ሁለት ወር ቆይቶ ደግሞ ጁኒየርን አገባች፡፡››
‹‹እሱን አላውቅም››
‹‹አይ በደንብ ታውቃለህ….ከማግባቱ ከወር ከአስራአምስት ቀን በፊት የመቶ ሚሊዬን ብር ዋጋ ያለው የአክሲዬን ድረሻ በጥሎሽ መልክ የሚሰጥ ሰው በምድር ላይ የለም፡፡››
‹‹እንግዲህ ስለዚህ ጉዳይ እራሳቸውን ጠይቂያቸው››
‹‹ጠይቃቸዋለው….በደንብ ነው የምጠይቃቸው….እሺ አንተስ?››
‹‹እኔስ ምን?፡፡››
‹‹እናቴ ከመሞቷ በፊት ድርጅቱ ውስጥ ያለህ ድርሻ 10 ፐርሰንት ነበር…ግን ልክ እንደስርጉት ሁሉ እናቴ ከሞተች ከ15 ቀን በኃላ 20ፐርሰንት ተጨምሮ ከአቶ ፍሰሀ ቀጥሎ የድርጅቱን ትልቅ ድርሻ ባለቤት ሆንክ፡፡››
‹‹እና ?››
‹‹እናማ ሁሉ ነገር ግልፅ ምስል እየሰጠኝ ነው…ከእናቴ ሞት ማግስት ለሞቷ ምክንያት ናቸው ብዬ የምጠረጥራቸው ሰዎች ሁሉ በህይወት ውስጥ ከፍተኛ ትርምስ ተከስቷል….ግማሹ ከስሯል ግማሾቻችሁ ደግሞ በልፅጋችሃኃላ…….በእናቴ ሞት ሰበብ የሚፍልገውን ያገኘ አለ…ያለውንም ያጣም አለ….እና ምንድነው ሚስጥሩ?››
በሚሰረስሩ ደማቅ ጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ አፈጠጠባት፡፡እይታው ውስጧን አሸበራት፡፡ጡቶቿ ከሹራብዋ ስር ሲንቀጠቀጡ ተሰማት…. ባልተስተካከለ የተቆራረጠ ትንፋሽ‹‹ከመካከላችሁ ማን ነው የገደላት?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አላውቅም››
‹‹እስቲ ቁጭ በይ›› ቁጭ አለች፡፡
‹‹ምን እያደረግሽ ነው…?ስራውን ለቀሽስ…?››
‹‹እነሱ ማንኛውንም ዘዴ ተጠቅመው እኔን ሊያስወግዱኝ ነው አይደለ እየሞከሩ ያሉት?..እኔም ስራዬን ለቅቄ በነፃነት በማንኛውም ነገር እፋለማቸዋለው››
‹‹በማንኛውም ነገር ማለት?››
‹‹በማንኛውም ነገር ማለትማ በማንኛውም ነገር ነው››
‹‹እኔ እንደታናሽ እህቴ ነው የማይሽ…ስትጎጂ ማየት አልፈልግም…እነሱን በወንጀለኝነት ሚያስጠይቅ ምንም አይነት ተጨባጭ ማስረጃ አታገኚም…ብታገኚ እንኳን ፍርድ ቤት አቅርበሽ ፍትህ ከማስገኘትሽ በፊት መረጃውን በሆነ መንገድ ያጠፉታል!!››
‹‹አይ አሁን እነሱን ለፍትህ ማቅረብ አይደለም የምፈልገው….መበቀል ነው…እኔን ለማስወገድ እንደሞከሩት እኔም አስወግዳቸዋለው…..ስማቸውንም፤ሀብታቸውንም ኃይላቸውንም እንዲያጡ ነው የማደርገው፡፡
‹‹እንዴት አድርገሽ?››
‹‹ዝርዝሩን አልነግርህም››
‹‹ምነው እኔንም ከእነሱ እንደአንዱ አድርገሽ እያየሺኝ ነው እንዴ?››
‹‹አይ እንደዛ አላልኩም..ግን ለጊዜው እቅዴን ለማንም የመናገር ፍላጎት የለኝም››
‹‹ጥሩ …ግን ሌላ እርምጃ እንዲወስዱብሽና እንደእናትሽ አንዲያጠፉሽ ምክንያት አትስጪያቸው››
‹‹ለማንኛውም ለምክርህ አመሰግናለው…..ቢሮዬ ገብቼ የግል እቃዎቼን ልሰብስብ››
‹‹አረ እስኪ ተረጋጊ…መልቀቂያሽን እኮ ገና አልተቀበልኩም››
‹‹‹ተቀበልክም አልተቀበልክም…ሀሳቤን አታስቀይረኝም….ምን አልባት ካላሰርከኝ በስተቀር
›› አፉን እንደከፈተ ቢሮውን ለቃ ወጣች፡፡
///
አለም ድንገት ነው የገመዶ ቤት የተገኘችው፡፡እየመጣሁ ነው ብላ ስትደውልለት በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ ነበር የጠበቃት፤፡፡መቆጣቷን እና ማኩረፏን ለማወቅ የእሷን ገፅታ ማየት አላስፈለገውም። እሷ ፍጹም ኩስትርትር ብላ ከረሜላ የከለከሏት ህፃን መስላለች ፡፡ ፊት ለፊቱ ኩርሲ አስቀመጠና እንድትቀመጥ ጋበዛት ፡፡እየጠለቀች ያለችው ጀንበር የምትረጨው ጨረር በፀጉሯ ላይ አርፎ የሚያበራ ደማቅ ነበልባል ፈንጥቆ ይታያል ።
"ዛሬ ጥዋት ስራ ገብተሸ ወዲያው እንደወጣሽና …ተመልሰሽ እንዳልገባሽ ነገሩኝ … ምን ሆና ይሆን ብዬ እያሰብኩ ነበር፡፡በሰላም ነው ?››አላት፡፡
"አንተ ውሸታም ፣ አታላይ ፣ ምናልባትም ነፍሰ ገዳይ ነህ።"
"ከመጀመሪያው ጀምሮ በእኔ ላይ ያለሽ አስተያየት ይህ ነበር…. የማላውቀውን አንድ አዲስ ነገር ንገሪኝ.››
ቆይ የሶሌ ኢንተርፕርይዝ 30 ፐርሰንት ድርሻ ያንተ እንደሆነ ለምን ሳትነግረኝ?››
ያልጠበቀው ወቀሳ ነው የገጠመው" ለምን ብዬ ነግርሻለሁ…..አግብቼሽ ንብረት ሳልቆጥርልሽ ያታለልኩሽ እኮ ነው ያስመሰልሽው?።"
‹‹ነገሩን አታደባብሰው…እዛ እንስሳት እራባታ ውስጥ ጥቂት ፈረሶች እንዳሉህ አይነት እድርገህ ነበር የነገርከኝ….ግን አንተ የጠገበ ሚሊዬነር ነህ፡፡››
‹‹እና ምነው ?ከፋሽ?››
‹‹ደሞዝህ 15 ሺ ብር አይሞላም…ይሄንን ሁሉ ብር ከየት አገኘህ?››
‹‹እንዴ ምርመራሽን ከግድያ ወንጀል ወደሙስና ልታዞሪው አሰብሽ እንዴ?…በንግድ ስራዬ ውስጥ ጣልቃ ለመግባት ምንም መብት የለሽም። ይህ ከአንቺ የግድያ ጉዳይ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም።"
"ይህን ምርመራ ወደ ውጤት ያደርሰኛል ብዬ ባመንኩበት ባሻኝ መንገድ የማስኬድ ሙሉ መብት አለኝ."
‹‹ወደሌሎች ነገሮች ጠልቀሽ ለመግባት በሞከርሽ መጠን የበለጠ ወደአደጋ እየቀረብሽ መሆኑን ልንግርሽ እፈልጋለው፡፡››
‹‹በዚህ መልኩ ስታስፈራራኝ ይሄ የመጀመሪያ ቀንህ አይደለም…ይህን ምርመራ እንዳይሳካልኝ በየደረጃው እንቅፋት ስታስቀምጥብኝ ነበር። ባጅህን ተጠቅመህ ገዳዩን ማንም ይሁን ማን እንዳላገኘው እየተከላከልክ ነው… ምክንያቱም የትኛውም የእናንተ ክበብ ውስጥ ባለ ሰው ላይ ክስ ቢመሰረት የሶሌን ኢንተርፕራይዝ የአክሲዬን ድርሻ ሆነ የገበያ ተቀባይነት ገደል ይገባል፡፡
‹‹እንዴት ማለት?፡፡››
‹‹የሶሌ ኢንተርፕራይዝ 10 ፐርሰንቱ የስርጉት ድርሻ ነው….ጁኒዬር የ15 ፐርሰንት አለው፣ እናቱ ሳራ 10 ፐርሰንት አላት…አቶ ፍሰሀ 35 ፐርሰንት ሲኖረው አንተ ደግሞ 30 ፐርሰንት አለህ፡፡››
ውስጡ በንዴት ሲንቀለቀል ታወቀው….ግን እንዲህ ተበሳጭቶባት እንኳን ዘለህ እነቃት የሚል ስሜት ሳይሆን እየተናነቀው ያለው ዘለህ ከንፈሯ ላይ ተጣበቅ የሚል ስሜት ነው፡፡ ግን እንደምንም እራሱን ተቆጣጥሮ
‹‹ለመሆኑ ይሄንን መረጃ ከየት አገኘሽው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ዋናው መረጃው ትክክል መሆኑ ነው ፡፡ምንጮቼንማ ለምን ብዬ አጋልጬ እሰጣለው፡፡››
‹‹ይሄ እኮ ምንም ሚስጥር የለውም…››
ከት ብላ ሳቀች…….
‹‹ምን ያስቅሻል?››
‹‹አለው እንጂ….ተመልከት….በምንም አይነት ስሌት አንተ እና ስርጉት የዚህ ኢንተርፕራይዝ የአክሲዬን ድርሻ ባለቤቶች ትሆናላችሁ ብዬ አስቤ አላውቅም..እርግጥ አንተ ከቤተሰቡ ጋር ባለህ ቤተሰባዊ ግንኙነት አንዳንድ ነገሮችን እየሰራህ ጠቀም ያለ ገንዘብ እንደምትቀበላቸው ግምቱ ነበረኝ…..ግን ተመልከት ከአቶ ፍሰሀ ቀጥሎ ሁለተኛው ትልቁ
አክሲዬን የማን ነው…?ያንተ፡፡ 30 ፐርሰንት…. ከልጁ ጁኒዬር በእጥፍ የሚበልጥ የአክሲዬን ድርሻ አለህ››
‹‹ምኑ ይገርማል….ጁኒዬር እኮ እድሜ ልኩን በየመዝናኛ ቦታው እየትሽከረከረ ሲዝናና እና ከሴቶች ጋር አለሙን ሲቀጭ የኖረ ሰው ነው….እኔ ደግሞ ድህነት ስፀየፍ የኖርኩና ያንንም ለማሸነፍ ቀን ከሌት የምለፋና የምጥር ሰው ነኝ…..የእኔ ከእሱ እጥፍ የአክሲዬን ባለድርሻ መሆኔን ነው የሚገርምሽ? በአባቱ ባይሆን አይደለም 15 ፐርሰንት አንድ ፐርሰንትም አይኖረውም ነበር››፡፡
‹‹እሺ ስርጉትስ?››
‹‹ስርጉት ምን ሆነች?››
‹‹ድርሻው በእሷ ስም ይሁን እንጂ ንብረትነቱ የዳኛው ነው አይደል?››
‹‹ያምሻል እንዴ…የራሷ ነው…የጁኒዬር ሚስት እኮ ነበረች፡፡››
‹‹አይ የአክሲዬን ባለድርሻ የሆነችው አናቴ በሞተች ከ15ተኛ ቀን በኋላ ሲሆን ሁለት ወር ቆይቶ ደግሞ ጁኒየርን አገባች፡፡››
‹‹እሱን አላውቅም››
‹‹አይ በደንብ ታውቃለህ….ከማግባቱ ከወር ከአስራአምስት ቀን በፊት የመቶ ሚሊዬን ብር ዋጋ ያለው የአክሲዬን ድረሻ በጥሎሽ መልክ የሚሰጥ ሰው በምድር ላይ የለም፡፡››
‹‹እንግዲህ ስለዚህ ጉዳይ እራሳቸውን ጠይቂያቸው››
‹‹ጠይቃቸዋለው….በደንብ ነው የምጠይቃቸው….እሺ አንተስ?››
‹‹እኔስ ምን?፡፡››
‹‹እናቴ ከመሞቷ በፊት ድርጅቱ ውስጥ ያለህ ድርሻ 10 ፐርሰንት ነበር…ግን ልክ እንደስርጉት ሁሉ እናቴ ከሞተች ከ15 ቀን በኃላ 20ፐርሰንት ተጨምሮ ከአቶ ፍሰሀ ቀጥሎ የድርጅቱን ትልቅ ድርሻ ባለቤት ሆንክ፡፡››
‹‹እና ?››
‹‹እናማ ሁሉ ነገር ግልፅ ምስል እየሰጠኝ ነው…ከእናቴ ሞት ማግስት ለሞቷ ምክንያት ናቸው ብዬ የምጠረጥራቸው ሰዎች ሁሉ በህይወት ውስጥ ከፍተኛ ትርምስ ተከስቷል….ግማሹ ከስሯል ግማሾቻችሁ ደግሞ በልፅጋችሃኃላ…….በእናቴ ሞት ሰበብ የሚፍልገውን ያገኘ አለ…ያለውንም ያጣም አለ….እና ምንድነው ሚስጥሩ?››
በሚሰረስሩ ደማቅ ጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ አፈጠጠባት፡፡እይታው ውስጧን አሸበራት፡፡ጡቶቿ ከሹራብዋ ስር ሲንቀጠቀጡ ተሰማት…. ባልተስተካከለ የተቆራረጠ ትንፋሽ‹‹ከመካከላችሁ ማን ነው የገደላት?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አላውቅም››
❤38👍6
"ሰሎሜ አንተን ሁለቴ ከድታሀለች ..ከማንም አስበልጣ ብታፈቅርህም ልብህን ግን ደጋግማ ሰብራዋለች። ከእኔ መወለድ በፊትም ሆነ ከእኔ መወለድ በኋላ ያደረገችብህን ነገር ቂም በሆድህ ቆጥርህ ነበር፡፡ያንን ይቅር ማለት እና መርሳት አልቻልክም፣ ጁኒየር ግን እንደአንተ ስላልሆነ እሷን በደስታ ነው የተቀበላት ፡፡ ቀስ በቀስም ትኩረቷን ማግኘት ጀመረ እና ጥረቶቹ ውጤት አስገኙለት… አንተን ረስታ ከእሱ ጋር ፍቅር እንደያዛት ስታስተዋል ከነከነህ፣ይባስ ብለው ሊጋቡ እንደሆነ ደረስክበት ….ከዛ ምን አደረክ ቀጥታ ገድለሀት ከእነሱ አንዳቸው እንደገደሏት እንዲያስቡ አደረክ ወይስ ምን አይነት የበቀል ዘዴ ነው የተጠቀምከው…..?ምን አልባት እናቴን ብቻ ሳይሆን ጁኒዬርንም ተበቅለኸው ይሆናል…?››
"በጣም ጥሩ አቃቢ ህግ ነሽ።በእውነት አድናቂሽ ነኝ…. ግን በዚያ መላ ምትሽ ትልቅ አመክንዬ ጥሰት አለበት፡፡››አለና የተቀመጠበትን ኩርሲ ወደእሷ አስጠጋ ….ምን ሊያደርግ ነው በሚል ስጋት በትኩረት ተመለከተችው፡፡
"አንቺ ..በብዙ ግምቶች እየተወዛገብሽ ነው…አንዱንም ማረጋገጥ አትችይም…በእኔ ላይ ምንም መረጃ የለሽም…ስለዚህ, ለምን የሁላችንንም ህይወትን ቀላል አታደርጊልንም ››አለና እጆቹን ትከሻዋ ላይ ጭነ… ወደራሱ ጎተተና ጉንጮን ሳማት፡፡
"ምክንያቱም አልችልም።›› ከንግግሯ በስተጀርባ ያለውን የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰማ እና እሷን ለመስበር ከግማሽ በላይ መንገድ ላይ እንደደረሰ አወቀ።
"ለምን አትችይም?" ጠየቃት፡፡
‹‹ምክንያቱም እናቴን የገደላትን፤መገደሏን አውቆ ገዳዩን ለመታደግ የተባበረውን በጠቅላላ መቅጣት እፈልጋለሁ።››
እጁን ከትከሻዋ ላይ አነሳና …አይን አይኗል በትኩረት እያየ….."ይህን ለሰሎሜ ብለሽ አይደለም እያደረግሽ ያለሽው… ለራስሽ ነው የምታደርጊው"አላት፡፡
"ያ እውነት አይደለም!"
" አያትሽ በጭንቅላትሽ ውስጥ የፈጠረችብሽ የማይሆን ሀሳብ አለ ፡፡እናም በእናትሽ ህይወት ውስጥ በተሳሳተ ጊዜ በመምጣትሽ እና ኑሮዋን በማበላሸትሽ ራስህሽ ይቅር ማለት አልቻልሽም።"
"በፈጣሪ አንተው ነህ ስለ ስነ ልቦና ግጭት ለእኔ የምታወራው?" ብላ በቁጣ ጠየቀችው። ቀጠለችናም "ገመዶ ራስ ወዳድ መሆንህን ለማወቅ ስለአንተ በቂ እውቀት አለኝ። ሌላ ሰው እንደግል ንብረትህ ስለምትቆጥር ሲነኩብህ ትበሳጫለህ ።››
"አገላለጿ ፈታኝ ነበር። ››
"ገመዶ ፣እናቴን ይቅር ለማለት በጣም የከበደህ ነገር ለምንድን ነው? እሷ ከሌላ ወንድ ጋር ስለተኛች ነው? ወይስ እድሉ እያለህ እሷን ባለማግባትህ ራስህን ይቅር ማለት አልቻልክም?"
ገላዋን በእጁ ነቀነቀ፣ ከዚያም እስኪነካኩ ድረስ ወደ ፊት አዘነበለ። "አንድ ጊዜ አስጠንቅቄሻለሁ ….እናትሽ ከጁኒየር ጋር የነበራትን ግንኙነት ለማስቀጠል እና ለምን እንደዛ እሷን ሊያፈቅራት እንደቻለ ለማወቅ ያለሽን የማወቅ ጉጉት ማርካት እየጣርሽ ነው"
"አይ ..ያ እውነት አይደለም" ብላ በቁጣ ካደች
" አይመስለኝም።"
‹‹ አንተ ታመሃል…?"አለችው፡፡
አንገቱን ጎንበስ አድርጎ ሳማት። በዝምታ ተቀበለችው….ከንፈሮቹን ወደከንፈሯ አስጠጋት…
…ባለችበት ሳትነቃነቅ ጠበቀችው፡፡ ከንፈሮቾን በስሱ ይመጣቸው ጀመር … ከንፈሯቾ እርጥብ እና ሙቀት የሚረጩ ከመሆናቸውም በላይ ጣፋጭ ነበሩ፣ ቀኝ እጁን አንቀሳቀሰና
በለበሰችው ሹራብ ውስጥ ሰቅስቆ ጡቷን በእጁ ጨመቀ። የጡቷን ጫፎች በሁለት ጣቶቹ ማፍተልተል ጀመረ… ጩኸት የተቀላቀለበት የጣር ድምፅ ከጉሮሮዋ ወጣ።አንገቱን ቀና አደረገና ቁልቁል ፊቷን ተመለከተ። በእጁ መዳፍ ውስጥ ተፈጥርቃ እንደተያዘች ትንሽ የዱር ፍጡር ልቧን ሲንፈራገጥ ይሰማዋል። አይኖቿ ተጨፍነው ነበር። መልሶ ከንፈሯን ጎረሰ…ምላሱን ወደውስጥ ከተተ…ከተቀመጠችበት ኩርሲ ተንሸራተተችና ደረቱ ላይ ተለጠፈችበት….ከተቀመጠበት ተነስቶ ልክ እንደህጻን ልጅ አቅፎ ወደቤቱ ውስጥ ይዞት ሄዶ አልጋው ላይ ሊዘርራትና ያለምንም ገደብ ሙሉ በሙሉ ከእሷ ጋር ለመቅለጥ እና ከእሷ ጋር ለመጥፋት ከፍተኛ ፍላጎት ጉሮሮዋ ስር ተሰነቀረበት…..እንደዚህ ካደረገ ወደኃላ መመለስ እንደማይችል እና ምንም ነገር እስከአሁን እንደነበረው እንዳማይሆን ያውቃል፡፡ምን ያድርግ…ልቡና አእምሮው ከፍተኛ ፊልሚያ ላይ ገቡበት፡፡ በመጨረሻ አእምሮው በልቡ ተሸንፎ እሷን ወደውስጥ ተሸክሞ ሊገባ ሲንቀሳቀስ የውጭ በራፍ በሀይል ሲንኳኳ ሰማ….ሁለቱም ከገቡበት መደንዘዝ እኩል ነቁ…..የበራፉ መንኳኳት ቀጠለ….ገመዶና አለም ተላቀቁ….ከተቀመጡበት የተዘበራረቀ ልብሷንና የተጎሳቆለ ፀጉሯን ማስተካከል ጀመረች….እሷ ሙሉ በመሉ እራሷን እንዳስተካከለች እርግጠኛ ከሆነ በኃላ በንዴት ሄዶ በራፉን ከፈተው..አቶ ፍሰሀ ነበር፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
"በጣም ጥሩ አቃቢ ህግ ነሽ።በእውነት አድናቂሽ ነኝ…. ግን በዚያ መላ ምትሽ ትልቅ አመክንዬ ጥሰት አለበት፡፡››አለና የተቀመጠበትን ኩርሲ ወደእሷ አስጠጋ ….ምን ሊያደርግ ነው በሚል ስጋት በትኩረት ተመለከተችው፡፡
"አንቺ ..በብዙ ግምቶች እየተወዛገብሽ ነው…አንዱንም ማረጋገጥ አትችይም…በእኔ ላይ ምንም መረጃ የለሽም…ስለዚህ, ለምን የሁላችንንም ህይወትን ቀላል አታደርጊልንም ››አለና እጆቹን ትከሻዋ ላይ ጭነ… ወደራሱ ጎተተና ጉንጮን ሳማት፡፡
"ምክንያቱም አልችልም።›› ከንግግሯ በስተጀርባ ያለውን የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰማ እና እሷን ለመስበር ከግማሽ በላይ መንገድ ላይ እንደደረሰ አወቀ።
"ለምን አትችይም?" ጠየቃት፡፡
‹‹ምክንያቱም እናቴን የገደላትን፤መገደሏን አውቆ ገዳዩን ለመታደግ የተባበረውን በጠቅላላ መቅጣት እፈልጋለሁ።››
እጁን ከትከሻዋ ላይ አነሳና …አይን አይኗል በትኩረት እያየ….."ይህን ለሰሎሜ ብለሽ አይደለም እያደረግሽ ያለሽው… ለራስሽ ነው የምታደርጊው"አላት፡፡
"ያ እውነት አይደለም!"
" አያትሽ በጭንቅላትሽ ውስጥ የፈጠረችብሽ የማይሆን ሀሳብ አለ ፡፡እናም በእናትሽ ህይወት ውስጥ በተሳሳተ ጊዜ በመምጣትሽ እና ኑሮዋን በማበላሸትሽ ራስህሽ ይቅር ማለት አልቻልሽም።"
"በፈጣሪ አንተው ነህ ስለ ስነ ልቦና ግጭት ለእኔ የምታወራው?" ብላ በቁጣ ጠየቀችው። ቀጠለችናም "ገመዶ ራስ ወዳድ መሆንህን ለማወቅ ስለአንተ በቂ እውቀት አለኝ። ሌላ ሰው እንደግል ንብረትህ ስለምትቆጥር ሲነኩብህ ትበሳጫለህ ።››
"አገላለጿ ፈታኝ ነበር። ››
"ገመዶ ፣እናቴን ይቅር ለማለት በጣም የከበደህ ነገር ለምንድን ነው? እሷ ከሌላ ወንድ ጋር ስለተኛች ነው? ወይስ እድሉ እያለህ እሷን ባለማግባትህ ራስህን ይቅር ማለት አልቻልክም?"
ገላዋን በእጁ ነቀነቀ፣ ከዚያም እስኪነካኩ ድረስ ወደ ፊት አዘነበለ። "አንድ ጊዜ አስጠንቅቄሻለሁ ….እናትሽ ከጁኒየር ጋር የነበራትን ግንኙነት ለማስቀጠል እና ለምን እንደዛ እሷን ሊያፈቅራት እንደቻለ ለማወቅ ያለሽን የማወቅ ጉጉት ማርካት እየጣርሽ ነው"
"አይ ..ያ እውነት አይደለም" ብላ በቁጣ ካደች
" አይመስለኝም።"
‹‹ አንተ ታመሃል…?"አለችው፡፡
አንገቱን ጎንበስ አድርጎ ሳማት። በዝምታ ተቀበለችው….ከንፈሮቹን ወደከንፈሯ አስጠጋት…
…ባለችበት ሳትነቃነቅ ጠበቀችው፡፡ ከንፈሮቾን በስሱ ይመጣቸው ጀመር … ከንፈሯቾ እርጥብ እና ሙቀት የሚረጩ ከመሆናቸውም በላይ ጣፋጭ ነበሩ፣ ቀኝ እጁን አንቀሳቀሰና
በለበሰችው ሹራብ ውስጥ ሰቅስቆ ጡቷን በእጁ ጨመቀ። የጡቷን ጫፎች በሁለት ጣቶቹ ማፍተልተል ጀመረ… ጩኸት የተቀላቀለበት የጣር ድምፅ ከጉሮሮዋ ወጣ።አንገቱን ቀና አደረገና ቁልቁል ፊቷን ተመለከተ። በእጁ መዳፍ ውስጥ ተፈጥርቃ እንደተያዘች ትንሽ የዱር ፍጡር ልቧን ሲንፈራገጥ ይሰማዋል። አይኖቿ ተጨፍነው ነበር። መልሶ ከንፈሯን ጎረሰ…ምላሱን ወደውስጥ ከተተ…ከተቀመጠችበት ኩርሲ ተንሸራተተችና ደረቱ ላይ ተለጠፈችበት….ከተቀመጠበት ተነስቶ ልክ እንደህጻን ልጅ አቅፎ ወደቤቱ ውስጥ ይዞት ሄዶ አልጋው ላይ ሊዘርራትና ያለምንም ገደብ ሙሉ በሙሉ ከእሷ ጋር ለመቅለጥ እና ከእሷ ጋር ለመጥፋት ከፍተኛ ፍላጎት ጉሮሮዋ ስር ተሰነቀረበት…..እንደዚህ ካደረገ ወደኃላ መመለስ እንደማይችል እና ምንም ነገር እስከአሁን እንደነበረው እንዳማይሆን ያውቃል፡፡ምን ያድርግ…ልቡና አእምሮው ከፍተኛ ፊልሚያ ላይ ገቡበት፡፡ በመጨረሻ አእምሮው በልቡ ተሸንፎ እሷን ወደውስጥ ተሸክሞ ሊገባ ሲንቀሳቀስ የውጭ በራፍ በሀይል ሲንኳኳ ሰማ….ሁለቱም ከገቡበት መደንዘዝ እኩል ነቁ…..የበራፉ መንኳኳት ቀጠለ….ገመዶና አለም ተላቀቁ….ከተቀመጡበት የተዘበራረቀ ልብሷንና የተጎሳቆለ ፀጉሯን ማስተካከል ጀመረች….እሷ ሙሉ በመሉ እራሷን እንዳስተካከለች እርግጠኛ ከሆነ በኃላ በንዴት ሄዶ በራፉን ከፈተው..አቶ ፍሰሀ ነበር፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤58👍13🔥4👎1
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
እሱ በራፉን ለመክፈት ሲሄድ አለም ቶሎ ብላ ቦርሳዋ ውስጥ ገባች እና በጣም የሚያምር ውድና ጌጠኛ ብእር አወጣችና ወደቤቱ በራፉ ፊት ለፊት በመወርወር ወደፊት ራመድ ብላ እስኪመለሱ መጠበቅ ጀመረች፡፡
‹‹እ..ሰላም ነው..?ስልክህ አይነሳም፡፡››አቶ ፍሰሀ ነው ተናጋሪው፡፡
‹‹ውስጥ ቻርጅ ላይ እርጌው አላየሁትም…ግባ››ኩማንደሩ መለሰለት፡፡ ወደውስጥ ሲገባ አለምን ስላያት ነገሩ ገባው፡፡
‹‹እንዴት ነህ አቶ ፍሰሀ?››
‹‹ሰላም ነኝ…አንቺስ?››
‹‹አለሁ..››አላችና ‹‹በሉ እንግዲህ መሄዴ ነው››ስትል አከለችበት፡፡
‹‹ምነው ..እኔ ስመጣ ነው እንዴ ምትሄጂው?››
‹‹አይ መጀመሪያውኑም ለመሄድ ስል ነው የመጣሀው…ጉዳዬን ጨርሼለው..ተራውን ለአንተ ልልቀቅ፡፡››አለችና ሁለቱንም ተሰናብታ ወጣች፡፡
ገመዶ እና አቶ ፍሰሀን አስከትሎ ወደውስጥ ለመግባት ሲራመድ በራፉ ጋር ሲደርሱ አቶ ፍሰሀ ጎንበስ አለና አይኑ የገባውን ብዕር አነሳ፡፡
‹‹ይሄን የመሰለ ብዕር ትጥላልህ እንዴ?››ብሎ ወደ ኩማንደሩ ዘረጋለት፡፡ኩማንደሩ ተቀብሎ አገላብጦ ተመለከተውና‹‹ወይ የእኔ አይደለም…የአለም መሰለኝ›››አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለላት፡፡
‹‹ሄሎ››
‹‹ ምነው ከአሁኑ ናፈቅኩህ እንዴ?››
‹‹ባክሽ ሌላ ቦታ ጥዬዋለው ብለሽ እንዳትፈልጊ ነው…አንድ ብዕር ጥለሽ ሄደሻል..ካልራቅሽ ተመለሺና ውሰጂው››
‹‹ወይ እንዴት ጣልኩት…?ለማንኛውም በጣም ከምወደው ሰው የተሰጠኝ ስጦታ ነው…ከኪስህ እንዳይወጣ …ስንናኝ ትሰጠኛለህ››አለቸው፡፡
‹‹እሺ ቻው››አለና ስልኩን በመዝጋት ብእሩን ደረት ኪሱ ውስጥ ሻጠውና ከአቶ ፍሰሀ ጋር ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ….
‹‹ቢራ ልክፈትልህ››
‹‹በጣም ደስ ይለኛል››
ለሁለቱም ቢራ ከፈተና ፊት ለፊት ተቀመጠ፡፡
‹‹መጥፎ ሰዓት ነው እንዴ የመጣሁት?››አቶ ፍሰሐ ጠየቀ፡፡
‹‹አይ እንደውም በተቃራኒው ጥሩ ሰዓት ላይ ነው የመጣሀው..በጣም አደጋ ላይ ነን››
‹‹ማለት››
‹‹ይህቺ ልጅ ከጠበቅኳት በላይ አደገኛ ነች…ሳታጠፋን አርፋ አትቀመጥም….››
‹‹ማለት….አንተ እንዲህ ካልክ ነገሮች ከባድ ናቸው ማለት ነው››
‹‹አዎ…ስለእያንንድ የሶሌ ኢንተርፕራይዝ የአክሲዬን ድርሻ…ማን ስንት ፐርሰንት እንዳለው…አክሲዬኑ መቼ እንዳገኘነው….ዝርዝር መረጀ አላት፡፡››
አቶ ፍሰሀ ልብ ምቱ በደቂቃ ውስጥ ሲጨምር ታወቀው….
‹‹ምን እያልከኝ ነው?››
‹‹አዎ….የእናቴን ሞት ተከትሎ የአንዳችሁ አክሲዬን ተቀንሶ ለሌሎቻችሁ የተጨመረው ለምንድነው ብላ ጠየቀችኝ…?፡፡››
‹‹ይሄ እኮ ወደእውነት እየቀረበች መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡››
‹‹አዎ…አንድ ውሳኔ መወሰን አለብን፡፡››
አቶ ፍሰሀ ወዲያው ስልኩን አወጣ…መጀመሪያ ዳኛ ዋልልኝ ጋር ደወል…አሁኑኑ ወደቤት እንዲመጣ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ መልሶ ልጁ ጁኒዬር ጋር ደወለ..ቤት እንደሆነ ነገረው…ሳይወጣ እንዲጠብቀው ነግሮ ዘጋውና‹‹በል ተነስ እንሂድ….አሁኑኑ ተነጋግረን አንድ ነገር ማድረግ አለብን፡፡››
///
ከምሽቱ አራት ሰዓት አራቱ ሰዎች ምድር ቤት በሚገኘው የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ፊት ለፊት ተፋጠዋል…በጠረጴዛው መሀከል ሙሉ የውስኪ ጠርሙስ ሲኖር በመሀከላቸው ግማሽ ድረስ የተሞላ ብርጭቆ አለ….
‹‹እኔ ከመጀመሪያውም ነግሬችሁ ነበር..ይህቺን ሴት አንድ ነገር አድርጓት ስላችሁ ነበር››ዳኛው በንዴት ደነፉ፡፡
‹‹አሁን ያለፈውን ገር እያነሳን ልንወቃቀስ አይደለም የተገናኘው…አሁን እንዴት አድርገን እናሳቁማት የሚለው ነው ወሳኙ ነገር፡፡››
‹‹ለምን ሁችንም ባለንበት አግኝተናት ይሄንን ጉዳይ እንድታቆም ለመጨረሻ ጊዜ አናሳጠነቅቃትም››አለ ጁኒዬር፡፡
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ….መቼስ ልጅቷን ግትርነት ከአንተ በላይ የሚያውቅ ያለ አይመስለኝም፡፡ እኔ በበክሌ እዚህ እግሯ ከረገጠበት ቀን አንስቶ በሰላምም በማስፈራራትም ይህንን ጉዳይ እንዳታቆም ያልጠየቅኳት ቀን የለም…አንድም ቀን ሽብርክ ስትል አልሰማዋትም…ዛሬም የነገረችኝ ጉዳዩን ከማቆም መሞትን እንደምትመርጥ ነው፡፡››ሲል አስተያየቱን ያቀረበው ኩማንደሩ ነበር፡፡
‹‹እሱማ ትክክል ነህ …እኔም ያልሞከርኩበት ቀን የለም…›አለ ጁኒዬር፡፡
‹‹አዎ…ይሄ ጉዳይ አይሰራም፡፡››
ዳኛው ትእግስት አልባ በሆነ ንግግራቸው‹‹በቃ በንግግር ማስቆሙ ካልሰራ …አስወግዷታ
…መቼስ ይሄንን ስታደርጉ የመጀመሪያችሁ አይደለም››አለ ፡፡
በገመዶና በጂኒዬር ላይ የተከሰተው ድንጋጤ የተለየ ነበር…..እርስ በእርስ ተያዩ….ከዛ ሁለቱም በእኩል ጊዜ ወደአቶ ፍሰሀ ዞሩ….አቶ ፍሰሀ አይናቸው ተጉረጥርጧል…ለመናገር እየፈለጉ እየተናነቃቸው ነው፡፡ከአንደበታቸው ቃል ማውጣት የከበዳቸው መሆኑን ያስታውቃል…ከዛ እንደምንም አሉና መናገር ጀመሩ፡፡
‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው…ለሁላችሁም….እዚህች ልጅ ላይ የመግደል ሀሳብ አይደለም አንዲት ፀጉሯን ለመንቀል ብታስቡ ቀጥታ ፀባችሁ ከእኔ ጋር ነው፡፡ማንም እጣቱን በእሷ ላይ ሊያነሳ አይችልም፡፡››
ዳኛው አይናቸውን አጉረጠረጡ‹‹ለምን ተብሎ..ለአንድ ዲቃላ ልጅ ሲባል የእኛ ህይወት መመሰቃቀል አለበት፡፡.እናንተ ማድረግ ካልፈለጋችሁ እኔ አደርገዋለው፡፡››
አቶ ፍሰሀ ልክ እንደጎረምሳ ከተቀመጡበት ተስፈንጥረው ተነሳና ከወገቡ ያለውን ሽጉጥ መዞ ሽማግሌው ዳኛ መላጣ ጭንቅላት ላይ ደቀነው፡፡
ገመዶና ጁኒዬር በርግገው ከተቀመጡበት ተነሱ‹‹እንዴ አባዬ ….!ምን እያደረክ ነው?››
‹‹አንተ ፈርሳም ሽማግሌ….ከዛሬ ጀምሮ እንደውም ለልጅቷ ጠባቂ ቀጥረህ እንቅፋት እንኳን እንዳይነካት ብታስጠብቃት ይሻልሀል….በማንም ሆነ በማን አንድ ነገር ገጠማት ሲባል ብሰማ ይሄንን ምላጭ በአንተ ጭንቅላት ላይ ለመሳብ ለሰከንድ እንኳን አላቅማማም፡፡››
‹‹ጋሼ በቃ…..ወደመቀመጫህ ተመለስ..ተረጋጋ…››አለ ገመዶ፡፡
አቶ ፍሰሀ የደቀነውን ሽጉጥ መልሶ ወደ ወገብ ሻጠው እና መደመቀመጫው ተመለሰ
…..ሁሉም በፀጥታ ማሰላሰል ውስጥ ገባ…ገመዶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደመስኮቱ ተጠግቶ ሲጋራውን ለኮሰና እያጬሰ ማሰብ ጀመረ፡፡ሲጋራውን እንደጨረሰ ወደመቀመጫው ተመለሰና ከውስኪው አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨ በኃላ ‹‹እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ››ሲል የሁሉንም ቀልብ ሳበ፡፡
‹‹ምንድነው እንስማው››ሁሉም ተነቃቁና ኩማንደሩ የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ሆነ፡፡
‹‹የሚቀጥሉት ስድስት ወራት ወሳኝ ጊዜዎች ናቸው..ማለቴ ከጂኒዬር የምርጫ ጉዳይ ጋር ተያይዞ ይሄ የክስ ጉዳይ ወደፊት ከገፋና እንዲህ አይነት ወሬዎች ህዝቡና ሚዲያው ጆሮ መግባት ከጀመሩ ነገሮች ድብልቅልቃቸው ነው ሚወጣው፡፡እንደእኔ ለተወሰነ ጊዜ ወደሆነ ቦት ዞር አድርገን ብናስቀምጣት፡፡››
‹‹ዞር አድርገን ስትል….?ግልፅ አድርገው?፡፡››
‹‹በቃ ከሰው እያታ ውጭ የሆነ ቤት ወሰድን እዛ ሁሉ ነገር እንዲሞላላት እድርገን ግን ደግሞ ከማንም የማትገናኝበትን ሁኔታ ብናመቻች ጥሩ ይመስለኛል፡፡››
‹‹ጥሩ…እኔም እስከዛ ጡረታ ወጣና ከዚህ ከተማ ዞር እላለሁ››በማለት ዳኛው ቅድሚያ ተስማማ፡፡
አቶ ፍሰሀ ‹‹ጥሩ ሀሳብ ይመስላል….እንደውም ይርጋ ጨፌ የቡና እርሻችን ያለበት ቦታ ብንወስዳት ማንም ሊያገኛት አይችልም……እዛ ሁሉን ነገር እናሟላላታለን…እኛም በየተራ እየሄድን እንጠይቃታለን..መጥፎ ሰዎች እንዳልሆን እንድታምን እናደርጋለን፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
እሱ በራፉን ለመክፈት ሲሄድ አለም ቶሎ ብላ ቦርሳዋ ውስጥ ገባች እና በጣም የሚያምር ውድና ጌጠኛ ብእር አወጣችና ወደቤቱ በራፉ ፊት ለፊት በመወርወር ወደፊት ራመድ ብላ እስኪመለሱ መጠበቅ ጀመረች፡፡
‹‹እ..ሰላም ነው..?ስልክህ አይነሳም፡፡››አቶ ፍሰሀ ነው ተናጋሪው፡፡
‹‹ውስጥ ቻርጅ ላይ እርጌው አላየሁትም…ግባ››ኩማንደሩ መለሰለት፡፡ ወደውስጥ ሲገባ አለምን ስላያት ነገሩ ገባው፡፡
‹‹እንዴት ነህ አቶ ፍሰሀ?››
‹‹ሰላም ነኝ…አንቺስ?››
‹‹አለሁ..››አላችና ‹‹በሉ እንግዲህ መሄዴ ነው››ስትል አከለችበት፡፡
‹‹ምነው ..እኔ ስመጣ ነው እንዴ ምትሄጂው?››
‹‹አይ መጀመሪያውኑም ለመሄድ ስል ነው የመጣሀው…ጉዳዬን ጨርሼለው..ተራውን ለአንተ ልልቀቅ፡፡››አለችና ሁለቱንም ተሰናብታ ወጣች፡፡
ገመዶ እና አቶ ፍሰሀን አስከትሎ ወደውስጥ ለመግባት ሲራመድ በራፉ ጋር ሲደርሱ አቶ ፍሰሀ ጎንበስ አለና አይኑ የገባውን ብዕር አነሳ፡፡
‹‹ይሄን የመሰለ ብዕር ትጥላልህ እንዴ?››ብሎ ወደ ኩማንደሩ ዘረጋለት፡፡ኩማንደሩ ተቀብሎ አገላብጦ ተመለከተውና‹‹ወይ የእኔ አይደለም…የአለም መሰለኝ›››አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለላት፡፡
‹‹ሄሎ››
‹‹ ምነው ከአሁኑ ናፈቅኩህ እንዴ?››
‹‹ባክሽ ሌላ ቦታ ጥዬዋለው ብለሽ እንዳትፈልጊ ነው…አንድ ብዕር ጥለሽ ሄደሻል..ካልራቅሽ ተመለሺና ውሰጂው››
‹‹ወይ እንዴት ጣልኩት…?ለማንኛውም በጣም ከምወደው ሰው የተሰጠኝ ስጦታ ነው…ከኪስህ እንዳይወጣ …ስንናኝ ትሰጠኛለህ››አለቸው፡፡
‹‹እሺ ቻው››አለና ስልኩን በመዝጋት ብእሩን ደረት ኪሱ ውስጥ ሻጠውና ከአቶ ፍሰሀ ጋር ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ….
‹‹ቢራ ልክፈትልህ››
‹‹በጣም ደስ ይለኛል››
ለሁለቱም ቢራ ከፈተና ፊት ለፊት ተቀመጠ፡፡
‹‹መጥፎ ሰዓት ነው እንዴ የመጣሁት?››አቶ ፍሰሐ ጠየቀ፡፡
‹‹አይ እንደውም በተቃራኒው ጥሩ ሰዓት ላይ ነው የመጣሀው..በጣም አደጋ ላይ ነን››
‹‹ማለት››
‹‹ይህቺ ልጅ ከጠበቅኳት በላይ አደገኛ ነች…ሳታጠፋን አርፋ አትቀመጥም….››
‹‹ማለት….አንተ እንዲህ ካልክ ነገሮች ከባድ ናቸው ማለት ነው››
‹‹አዎ…ስለእያንንድ የሶሌ ኢንተርፕራይዝ የአክሲዬን ድርሻ…ማን ስንት ፐርሰንት እንዳለው…አክሲዬኑ መቼ እንዳገኘነው….ዝርዝር መረጀ አላት፡፡››
አቶ ፍሰሀ ልብ ምቱ በደቂቃ ውስጥ ሲጨምር ታወቀው….
‹‹ምን እያልከኝ ነው?››
‹‹አዎ….የእናቴን ሞት ተከትሎ የአንዳችሁ አክሲዬን ተቀንሶ ለሌሎቻችሁ የተጨመረው ለምንድነው ብላ ጠየቀችኝ…?፡፡››
‹‹ይሄ እኮ ወደእውነት እየቀረበች መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡››
‹‹አዎ…አንድ ውሳኔ መወሰን አለብን፡፡››
አቶ ፍሰሀ ወዲያው ስልኩን አወጣ…መጀመሪያ ዳኛ ዋልልኝ ጋር ደወል…አሁኑኑ ወደቤት እንዲመጣ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ መልሶ ልጁ ጁኒዬር ጋር ደወለ..ቤት እንደሆነ ነገረው…ሳይወጣ እንዲጠብቀው ነግሮ ዘጋውና‹‹በል ተነስ እንሂድ….አሁኑኑ ተነጋግረን አንድ ነገር ማድረግ አለብን፡፡››
///
ከምሽቱ አራት ሰዓት አራቱ ሰዎች ምድር ቤት በሚገኘው የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ፊት ለፊት ተፋጠዋል…በጠረጴዛው መሀከል ሙሉ የውስኪ ጠርሙስ ሲኖር በመሀከላቸው ግማሽ ድረስ የተሞላ ብርጭቆ አለ….
‹‹እኔ ከመጀመሪያውም ነግሬችሁ ነበር..ይህቺን ሴት አንድ ነገር አድርጓት ስላችሁ ነበር››ዳኛው በንዴት ደነፉ፡፡
‹‹አሁን ያለፈውን ገር እያነሳን ልንወቃቀስ አይደለም የተገናኘው…አሁን እንዴት አድርገን እናሳቁማት የሚለው ነው ወሳኙ ነገር፡፡››
‹‹ለምን ሁችንም ባለንበት አግኝተናት ይሄንን ጉዳይ እንድታቆም ለመጨረሻ ጊዜ አናሳጠነቅቃትም››አለ ጁኒዬር፡፡
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ….መቼስ ልጅቷን ግትርነት ከአንተ በላይ የሚያውቅ ያለ አይመስለኝም፡፡ እኔ በበክሌ እዚህ እግሯ ከረገጠበት ቀን አንስቶ በሰላምም በማስፈራራትም ይህንን ጉዳይ እንዳታቆም ያልጠየቅኳት ቀን የለም…አንድም ቀን ሽብርክ ስትል አልሰማዋትም…ዛሬም የነገረችኝ ጉዳዩን ከማቆም መሞትን እንደምትመርጥ ነው፡፡››ሲል አስተያየቱን ያቀረበው ኩማንደሩ ነበር፡፡
‹‹እሱማ ትክክል ነህ …እኔም ያልሞከርኩበት ቀን የለም…›አለ ጁኒዬር፡፡
‹‹አዎ…ይሄ ጉዳይ አይሰራም፡፡››
ዳኛው ትእግስት አልባ በሆነ ንግግራቸው‹‹በቃ በንግግር ማስቆሙ ካልሰራ …አስወግዷታ
…መቼስ ይሄንን ስታደርጉ የመጀመሪያችሁ አይደለም››አለ ፡፡
በገመዶና በጂኒዬር ላይ የተከሰተው ድንጋጤ የተለየ ነበር…..እርስ በእርስ ተያዩ….ከዛ ሁለቱም በእኩል ጊዜ ወደአቶ ፍሰሀ ዞሩ….አቶ ፍሰሀ አይናቸው ተጉረጥርጧል…ለመናገር እየፈለጉ እየተናነቃቸው ነው፡፡ከአንደበታቸው ቃል ማውጣት የከበዳቸው መሆኑን ያስታውቃል…ከዛ እንደምንም አሉና መናገር ጀመሩ፡፡
‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው…ለሁላችሁም….እዚህች ልጅ ላይ የመግደል ሀሳብ አይደለም አንዲት ፀጉሯን ለመንቀል ብታስቡ ቀጥታ ፀባችሁ ከእኔ ጋር ነው፡፡ማንም እጣቱን በእሷ ላይ ሊያነሳ አይችልም፡፡››
ዳኛው አይናቸውን አጉረጠረጡ‹‹ለምን ተብሎ..ለአንድ ዲቃላ ልጅ ሲባል የእኛ ህይወት መመሰቃቀል አለበት፡፡.እናንተ ማድረግ ካልፈለጋችሁ እኔ አደርገዋለው፡፡››
አቶ ፍሰሀ ልክ እንደጎረምሳ ከተቀመጡበት ተስፈንጥረው ተነሳና ከወገቡ ያለውን ሽጉጥ መዞ ሽማግሌው ዳኛ መላጣ ጭንቅላት ላይ ደቀነው፡፡
ገመዶና ጁኒዬር በርግገው ከተቀመጡበት ተነሱ‹‹እንዴ አባዬ ….!ምን እያደረክ ነው?››
‹‹አንተ ፈርሳም ሽማግሌ….ከዛሬ ጀምሮ እንደውም ለልጅቷ ጠባቂ ቀጥረህ እንቅፋት እንኳን እንዳይነካት ብታስጠብቃት ይሻልሀል….በማንም ሆነ በማን አንድ ነገር ገጠማት ሲባል ብሰማ ይሄንን ምላጭ በአንተ ጭንቅላት ላይ ለመሳብ ለሰከንድ እንኳን አላቅማማም፡፡››
‹‹ጋሼ በቃ…..ወደመቀመጫህ ተመለስ..ተረጋጋ…››አለ ገመዶ፡፡
አቶ ፍሰሀ የደቀነውን ሽጉጥ መልሶ ወደ ወገብ ሻጠው እና መደመቀመጫው ተመለሰ
…..ሁሉም በፀጥታ ማሰላሰል ውስጥ ገባ…ገመዶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደመስኮቱ ተጠግቶ ሲጋራውን ለኮሰና እያጬሰ ማሰብ ጀመረ፡፡ሲጋራውን እንደጨረሰ ወደመቀመጫው ተመለሰና ከውስኪው አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨ በኃላ ‹‹እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ››ሲል የሁሉንም ቀልብ ሳበ፡፡
‹‹ምንድነው እንስማው››ሁሉም ተነቃቁና ኩማንደሩ የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ሆነ፡፡
‹‹የሚቀጥሉት ስድስት ወራት ወሳኝ ጊዜዎች ናቸው..ማለቴ ከጂኒዬር የምርጫ ጉዳይ ጋር ተያይዞ ይሄ የክስ ጉዳይ ወደፊት ከገፋና እንዲህ አይነት ወሬዎች ህዝቡና ሚዲያው ጆሮ መግባት ከጀመሩ ነገሮች ድብልቅልቃቸው ነው ሚወጣው፡፡እንደእኔ ለተወሰነ ጊዜ ወደሆነ ቦት ዞር አድርገን ብናስቀምጣት፡፡››
‹‹ዞር አድርገን ስትል….?ግልፅ አድርገው?፡፡››
‹‹በቃ ከሰው እያታ ውጭ የሆነ ቤት ወሰድን እዛ ሁሉ ነገር እንዲሞላላት እድርገን ግን ደግሞ ከማንም የማትገናኝበትን ሁኔታ ብናመቻች ጥሩ ይመስለኛል፡፡››
‹‹ጥሩ…እኔም እስከዛ ጡረታ ወጣና ከዚህ ከተማ ዞር እላለሁ››በማለት ዳኛው ቅድሚያ ተስማማ፡፡
አቶ ፍሰሀ ‹‹ጥሩ ሀሳብ ይመስላል….እንደውም ይርጋ ጨፌ የቡና እርሻችን ያለበት ቦታ ብንወስዳት ማንም ሊያገኛት አይችልም……እዛ ሁሉን ነገር እናሟላላታለን…እኛም በየተራ እየሄድን እንጠይቃታለን..መጥፎ ሰዎች እንዳልሆን እንድታምን እናደርጋለን፡፡
❤51👍8😱2
‹‹እናንተ ሰዎች አብዳችኃል እንዴ…?ሴትዬዋ እኮ የዞኑ ምክትል አቃቢ ህግ ነች….ዝም ብላ ስትሰወር መንግስት ዝም የሚል ይመስላችኃል?፡፡››ጁኒዬር ነው ጠያቂው፡፡
‹‹ትክክል ነህ….ግን አሁን ልጅቷ ስራ ለቃለች፡፡››ኩማንደር መለሰ፡፡
‹‹ማለት..?ከመቼ ጀምሮ?››
ከዛሬ ወዲህ ወደስራ መግባት እንደማትፈልግ ታናግራ መለቀቂያዋን ለዋና አቃቢ ህጉ አስገብታለች…ስለዚህ ከነገ ጀምሮ ከተማ ውስጥ ባትታይ የሚገርም አይሆንም፡፡››
‹‹አዎ….እኔም መልቀቂያ እንዳስገባች ሰምቼለው››አሉ አቶ ፍሰሀ፡፡
‹‹ለምን ለቀቀች…?የደረሰባት መጥፎ ነገር አለ?፡፡››ጁኒዬር ነው በስጋት የጠየቀው፡፡
‹‹እኔና ኩማንደር ቀደም ብለን ተነጋግረን ከዚህ ምርመራዋ ዞር ለማድረግ በማሰብ እላይ ያሉ ወዳጆቻችንን አስቸግረን የውጭ እድል እንድታገኝና እዚህ ያለውን ስራ ለሌላ ሰው አስረክባ በሳምንት ውስጥ ከተማውን ለቃ እንድትወጣ አመቻችተን ነበር….እሷ ግን የውጭ እድሉን ውድቅ አድርጋ ስራዋና ለመልቀቅ በመወሰን እቅዳችንን ውድቅ እንዲሆን አድርጋለች፡፡››ሲሉ ስለሁኔታው ምንም መረጃ ለሌላቸውን ለዳኛውና ለልጃቸው አብራሩላቸው፡፡
‹‹እንዴ አባይ …?ይሄንን ሁሉ ስታደርጉ እኔ ጫፉን እንኳን ለምን ሳላውቅ?››ሲል ጁኒዬር በቅሬታ ጠየቀ፡፡
‹‹ልጄ ነገሩን እንድታውቀው ካላደረግን ለአንተ ጥቅም እንደሆነ ማወቅ አለብህ›› ጁኒዬር ግን በጣም ቅር እንዳለው ከፊቱ ላይ በግልፅ ማንበብ ይቻላል፡፡
አቶ ፍሰሀ ‹‹‹በቃ አሁን እሷን ከአካባቢው በጥንቃቄ ዞር ከማድረግ ውጭ የተሻለ መፍትሄ የለም… አሁን ስራ እንከፋፈል…ኩማንደር እና ጁኒዬር አንድ ላይ ሆናችሁ…እሷን በታማኝነት የሚጠብቁ አንድ አራት ሰዎች ምግብ የምታበስልላትና የምታወራት አንድ ሴት ፈልጋችሁ አዘጋጁ….ከዛ ውጭ የሚያስፈልጓትን እቃዎች ልብሶች ማንኛውንም ነገር አዘጋጁ..እኔ ነገ ለሊት ወደ ይርጋጨፌ ሄድና የቡና ጫካ ውስጥ ያለውን ማረፊያ ቤታችንን እንዲታደስና እንዲዘጋጅ አደርጋለው…ሁሉንም ነገር በ5 ቀን ውስጥ ማጠናቀቅ አለብን
….እና የዛሬ ሳምንት ኦፕሬሽኑን እናደርጋለን….ከተቻለ..ከሁለት አንዳችሁ አሳምኗትና ከከተማ ይዛችኃት ውጡ …››
‹‹እኔስ ምንድነው የማግዛችሁ?››ዳኛው በእፎይታ ጠየቀ፡፡
‹‹አንተ ባለመነጫነጭ እና አድበህ በመቀመጥ ተባበረን፡፡››ሲል አቶ ፍሰሀ በመሰላቸት መለሰለት፡፡
‹‹በቃ…..አሁን ወደ የቤታችን እንሂድ…ከነገ ጀምሮ ሚደረገውን እናደርጋለን፡፡››
‹‹ግን በዚህ አንድ ሳምንት ውስጥ የሆነ ነገር ብታደርግስ?፡፡››ዳኛው ናችው ጠያቂ፡፡
ኩማንደሩ‹‹እያንዳንዱን እንቅስቃሴዋን የሚከታተል ሰው መድቤለው…በጣም የሚያሰጋ ነገር ካለ ቀድመን እርምጃ እንወስዳለን››አለና ጃኬቱን ካተንጠለጠለበት አንስቶ ወደመውጫው መራመድ ጀመረ..ጁኒዬር ከኋላው ተከተለው፡፡
///
ሁሉም በተሰጠው ስራ መሰረት መደበኛ ስራቸውን ሳይቀር ሙሉ በሙሉ በመዘንጋት ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ሲሯሯጡ ነው የሚውሉት፣እንደዛም በመሆኑ አምስት ቀን ይፈጃል የተባለው አለም የምትኖርበትን ቤት የማዘጋጀትና የሚጠብቃት ሰዎችን የመመልመልና የመቅጠር ስራ በሶስት ቀን ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡
አሁን ኩማንደር ቢሮው ቁጭ ብሎ ስልኩን አነሳና ይርጋአለም ወደሚገኙት አቶ ፍሰሀ ጋር ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ጋሼ..እንዴት ነህ?››
‹‹ደህና ነኝ.. ይመስገነው፡፡››
‹‹የላክናቸው ጠባቂዎችና ሰራተኛዋ ደረሱ?››
‹‹ከተማ ገብተዋል… የሚቀበላቸው ሰው ልኬላው …ከአንድ ሰዓት በኋላ ቦታው ላይ ይደርሳሉ››
‹‹ጥሩ ነው….አንተጋስ ነገሮች እንዴት ናቸው?››
‹‹ሁሉ ነገር ፐርፌክት ነው፡፡ቤቱን ለእሷ እንዲመች አድርገን አሳምረነዋል …..ግቢው በዛፎችና በአበቦች የተሞላ ስለሆነ ገነት በለው…በጣም ነው የምትወደው….ፏፏቴ ሳይቀር ግቢ ውስጥ አለ….እኔ ራሴ እዚሁ ኑር እዚሁ ኑር ነው ያሰኘኝ፡፡››
‹‹ተረጋጋ..መጀመሪያ ከዚህ ችግር እንገላገል..ከዛ በሰላም ጡረታ ትወጣና..ስራህን ለልጅህ አስተላልፈህ እንዳልከው ማድረግ ትችላለህ››አለው፡፡
‹‹እንደዛ ማድረጌማ አይቀርም…ለማንኛውም ከጁኒዬር ጋር ተማከራችሁ?፡፡››
‹‹ምንን በተመለከተ?››
‹‹እንዴት ወደ እዚህ ይዛችኃት ልትመጡ እንዳሰባችሁ ነዋ?፡፡››
‹‹አዎ…..ነገ ማታ ጂኒዬር አሳምኖ ወደ ጭፈራ ቤት ይዞት ይወጣና በደንብ እንድትጠጣ እናደርጋለን…ከዛ ለረጅም ሰዓት የሚያስተኛ መድሀኒት እንሰጣትና እንድትተኛ እናደርጋለን …ለሊቱን ይዘናት እንመጣለን....እና ጥዋት ስትነቃ እራሷን አንተ ያዘጋጀህላት ገነት ውስጥ ታገኘዋለች፡፡››
‹‹ጥሩ ነው በቃ…ቻው…ተጠንቀቁ፡፡››
‹‹ችግር የለም..አንተም ተጠንቀቅ፡፡››
‹‹ስልኩን ተዘጋ..ፈገግ አለ…..አለም ነገ ማታ ለመዝናናት ዝንጥንጥ ብላ ከቤቷ ወጥታ በማግስቱ ከእንቅልፏ ስትነቃ እራሷን ጥቅጥቅ ያለ ደን ውስጥ በጠባቂዎች ተከባ ስታገኘው እንዴት እንደምትናደድና ምን አይነት እርግማን እንደምታዥጎደጉድባቸው በምናብ አሰበና ፈገግ አለ…ስልኩን ወደራሱ አስጠጋና ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ሳጅን….››
‹‹ደህና ነኝ ኩማንደር››
‹‹እሺ …ተጠርጣሪያችን ምን እየሰራች ነው?፡፡››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ኩማንደር ልደውልልህ ስል ነው የደወልክልኝ…ትናንትና ጥዋት ወደክፍሏ የገባች እስከአሁን አልወጣችም..በራፏም አልተከፈተም…››ሲል ያልጠበቀውን ዜና ነገረው፡፡፡
‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ…ለሊቱን ሲጠብቃት ያደረው ፖሊስ ያለኝ እንደዛ ነው…እኔም ከተረከብኩት በኋላ በቤቷ ዙሪያ ምን አይነት እንቅስቃሴ አላየሁም፡፡››
ኩማንደር የሆነ ደስ የማይል ስሜት ተሰማው….‹‹ቆይ ሳጅን….አንዴ ስልኩን ዝጋው….ልደውልላትና መልሼ ደውልልሀለው››
ስልኩ ተቋረጠ…ወዲያው የአለምን ቁጥር አወጣና ደወለ…ጥሪ አይቀበልም ነው የሚለው…ደገመ…ተመሳሰይ ነው፡፡ከተቀመጠበት ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳና ክፍሉ ውስጥ እየተሸከረከረ ማሰብ ጀመረ..መልሶ ሳጅኑ ጋር ደወለ‹‹ሳጅን ቀጥታ ወደቤቷ ሂድና አንኳኳ››የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡
‹‹ከከፈተችልኝስ?››
‹‹ጥሩ ነዋ…የምፈልገው ያንን አይደል?››
‹‹ማለቴ ምን እላታለው?››
‹‹ኩማደር በስልክ አገናኘኝ ብሎኝ ነው ብለህ ደውለህ ከእኔ ጋር ታገናኘናለህ››
‹‹እሺ በቃ ወደቤቷ እየቀረብኩ ነው፡፡››
ስልኩ ተቋረጠ…ኩማደሩ ከፊልድ ጃኬቱ ውስጥ ሲጋራ አወጣና ለኮሰ…..ወደ መስኮት ሄደና መስኮቱን ከፍቶ ውጭ የሚርመሰመሱትን መንገደኞች እየተመለከተ ሲጋራውን ማቡነንና መጥፎ መጥፎ ሀሳቦችን እየደራረበ ማሰቡን ቀጠለ፡፡ሲጋራውን አጭሶ ሳይጨርስ ስልኩ ተንጫረረ…ሳጅኑ ነው…አነሳውና የአለምን ድምጽ ለመስማት እየፀለየ ጆሮው ጋር አስጠጋ፡፡
‹‹አዝናለው ኩማንደር..ባንኳኳ ባንኳኳ ከውስጥ የሚመልስ ሰው የለም…..››
‹‹በቃ መጣው..እዛ በራፉ ጋር ሆነህ ጠብቀኝ››በማለት ግማሽ ሲጋራውን ወደ አሽትሬው ላይ ወረወረና ጃኬቱን ከወንበሩ ላይ አንጠልጥሎ ቢሮውን ለቆ ወጣ…ቀጥታ የመስሪያ ቤቱን ፒካፕ መኪና አስነስቶ ወደቤቷ መብረር ጀመረ፡፡ስልኩ መጥራት ጀመረ..ሲያየው ጁኒዬር ነው….በዚህ ሰዓት ከእሱ ጋር የማውራት አፒታይት የለውምና አላነሳም..ደግሞ ደወለ…..ልክ አለም ቤት ጋር ለመድረስ የሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ሲቀረው..ዳኛው ዋልልኝ ደወሉ…..‹‹ይሄማ በሰላም ሊሆን አይችልም አለና››የዳኛውን ስልክ ዘግቶ የመኪናውን ፍጥነት በመቀነስ ጁኒዬር ጋር ደወለለት…ወዲያው ነው የተነሳው፡፡
‹‹የት ነህ?››
‹‹ወደ አለም ቤት እየሄድኩነው››
‹‹አለች ግን?››
‹‹ትክክል ነህ….ግን አሁን ልጅቷ ስራ ለቃለች፡፡››ኩማንደር መለሰ፡፡
‹‹ማለት..?ከመቼ ጀምሮ?››
ከዛሬ ወዲህ ወደስራ መግባት እንደማትፈልግ ታናግራ መለቀቂያዋን ለዋና አቃቢ ህጉ አስገብታለች…ስለዚህ ከነገ ጀምሮ ከተማ ውስጥ ባትታይ የሚገርም አይሆንም፡፡››
‹‹አዎ….እኔም መልቀቂያ እንዳስገባች ሰምቼለው››አሉ አቶ ፍሰሀ፡፡
‹‹ለምን ለቀቀች…?የደረሰባት መጥፎ ነገር አለ?፡፡››ጁኒዬር ነው በስጋት የጠየቀው፡፡
‹‹እኔና ኩማንደር ቀደም ብለን ተነጋግረን ከዚህ ምርመራዋ ዞር ለማድረግ በማሰብ እላይ ያሉ ወዳጆቻችንን አስቸግረን የውጭ እድል እንድታገኝና እዚህ ያለውን ስራ ለሌላ ሰው አስረክባ በሳምንት ውስጥ ከተማውን ለቃ እንድትወጣ አመቻችተን ነበር….እሷ ግን የውጭ እድሉን ውድቅ አድርጋ ስራዋና ለመልቀቅ በመወሰን እቅዳችንን ውድቅ እንዲሆን አድርጋለች፡፡››ሲሉ ስለሁኔታው ምንም መረጃ ለሌላቸውን ለዳኛውና ለልጃቸው አብራሩላቸው፡፡
‹‹እንዴ አባይ …?ይሄንን ሁሉ ስታደርጉ እኔ ጫፉን እንኳን ለምን ሳላውቅ?››ሲል ጁኒዬር በቅሬታ ጠየቀ፡፡
‹‹ልጄ ነገሩን እንድታውቀው ካላደረግን ለአንተ ጥቅም እንደሆነ ማወቅ አለብህ›› ጁኒዬር ግን በጣም ቅር እንዳለው ከፊቱ ላይ በግልፅ ማንበብ ይቻላል፡፡
አቶ ፍሰሀ ‹‹‹በቃ አሁን እሷን ከአካባቢው በጥንቃቄ ዞር ከማድረግ ውጭ የተሻለ መፍትሄ የለም… አሁን ስራ እንከፋፈል…ኩማንደር እና ጁኒዬር አንድ ላይ ሆናችሁ…እሷን በታማኝነት የሚጠብቁ አንድ አራት ሰዎች ምግብ የምታበስልላትና የምታወራት አንድ ሴት ፈልጋችሁ አዘጋጁ….ከዛ ውጭ የሚያስፈልጓትን እቃዎች ልብሶች ማንኛውንም ነገር አዘጋጁ..እኔ ነገ ለሊት ወደ ይርጋጨፌ ሄድና የቡና ጫካ ውስጥ ያለውን ማረፊያ ቤታችንን እንዲታደስና እንዲዘጋጅ አደርጋለው…ሁሉንም ነገር በ5 ቀን ውስጥ ማጠናቀቅ አለብን
….እና የዛሬ ሳምንት ኦፕሬሽኑን እናደርጋለን….ከተቻለ..ከሁለት አንዳችሁ አሳምኗትና ከከተማ ይዛችኃት ውጡ …››
‹‹እኔስ ምንድነው የማግዛችሁ?››ዳኛው በእፎይታ ጠየቀ፡፡
‹‹አንተ ባለመነጫነጭ እና አድበህ በመቀመጥ ተባበረን፡፡››ሲል አቶ ፍሰሀ በመሰላቸት መለሰለት፡፡
‹‹በቃ…..አሁን ወደ የቤታችን እንሂድ…ከነገ ጀምሮ ሚደረገውን እናደርጋለን፡፡››
‹‹ግን በዚህ አንድ ሳምንት ውስጥ የሆነ ነገር ብታደርግስ?፡፡››ዳኛው ናችው ጠያቂ፡፡
ኩማንደሩ‹‹እያንዳንዱን እንቅስቃሴዋን የሚከታተል ሰው መድቤለው…በጣም የሚያሰጋ ነገር ካለ ቀድመን እርምጃ እንወስዳለን››አለና ጃኬቱን ካተንጠለጠለበት አንስቶ ወደመውጫው መራመድ ጀመረ..ጁኒዬር ከኋላው ተከተለው፡፡
///
ሁሉም በተሰጠው ስራ መሰረት መደበኛ ስራቸውን ሳይቀር ሙሉ በሙሉ በመዘንጋት ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ሲሯሯጡ ነው የሚውሉት፣እንደዛም በመሆኑ አምስት ቀን ይፈጃል የተባለው አለም የምትኖርበትን ቤት የማዘጋጀትና የሚጠብቃት ሰዎችን የመመልመልና የመቅጠር ስራ በሶስት ቀን ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡
አሁን ኩማንደር ቢሮው ቁጭ ብሎ ስልኩን አነሳና ይርጋአለም ወደሚገኙት አቶ ፍሰሀ ጋር ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ጋሼ..እንዴት ነህ?››
‹‹ደህና ነኝ.. ይመስገነው፡፡››
‹‹የላክናቸው ጠባቂዎችና ሰራተኛዋ ደረሱ?››
‹‹ከተማ ገብተዋል… የሚቀበላቸው ሰው ልኬላው …ከአንድ ሰዓት በኋላ ቦታው ላይ ይደርሳሉ››
‹‹ጥሩ ነው….አንተጋስ ነገሮች እንዴት ናቸው?››
‹‹ሁሉ ነገር ፐርፌክት ነው፡፡ቤቱን ለእሷ እንዲመች አድርገን አሳምረነዋል …..ግቢው በዛፎችና በአበቦች የተሞላ ስለሆነ ገነት በለው…በጣም ነው የምትወደው….ፏፏቴ ሳይቀር ግቢ ውስጥ አለ….እኔ ራሴ እዚሁ ኑር እዚሁ ኑር ነው ያሰኘኝ፡፡››
‹‹ተረጋጋ..መጀመሪያ ከዚህ ችግር እንገላገል..ከዛ በሰላም ጡረታ ትወጣና..ስራህን ለልጅህ አስተላልፈህ እንዳልከው ማድረግ ትችላለህ››አለው፡፡
‹‹እንደዛ ማድረጌማ አይቀርም…ለማንኛውም ከጁኒዬር ጋር ተማከራችሁ?፡፡››
‹‹ምንን በተመለከተ?››
‹‹እንዴት ወደ እዚህ ይዛችኃት ልትመጡ እንዳሰባችሁ ነዋ?፡፡››
‹‹አዎ…..ነገ ማታ ጂኒዬር አሳምኖ ወደ ጭፈራ ቤት ይዞት ይወጣና በደንብ እንድትጠጣ እናደርጋለን…ከዛ ለረጅም ሰዓት የሚያስተኛ መድሀኒት እንሰጣትና እንድትተኛ እናደርጋለን …ለሊቱን ይዘናት እንመጣለን....እና ጥዋት ስትነቃ እራሷን አንተ ያዘጋጀህላት ገነት ውስጥ ታገኘዋለች፡፡››
‹‹ጥሩ ነው በቃ…ቻው…ተጠንቀቁ፡፡››
‹‹ችግር የለም..አንተም ተጠንቀቅ፡፡››
‹‹ስልኩን ተዘጋ..ፈገግ አለ…..አለም ነገ ማታ ለመዝናናት ዝንጥንጥ ብላ ከቤቷ ወጥታ በማግስቱ ከእንቅልፏ ስትነቃ እራሷን ጥቅጥቅ ያለ ደን ውስጥ በጠባቂዎች ተከባ ስታገኘው እንዴት እንደምትናደድና ምን አይነት እርግማን እንደምታዥጎደጉድባቸው በምናብ አሰበና ፈገግ አለ…ስልኩን ወደራሱ አስጠጋና ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ሳጅን….››
‹‹ደህና ነኝ ኩማንደር››
‹‹እሺ …ተጠርጣሪያችን ምን እየሰራች ነው?፡፡››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ኩማንደር ልደውልልህ ስል ነው የደወልክልኝ…ትናንትና ጥዋት ወደክፍሏ የገባች እስከአሁን አልወጣችም..በራፏም አልተከፈተም…››ሲል ያልጠበቀውን ዜና ነገረው፡፡፡
‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ…ለሊቱን ሲጠብቃት ያደረው ፖሊስ ያለኝ እንደዛ ነው…እኔም ከተረከብኩት በኋላ በቤቷ ዙሪያ ምን አይነት እንቅስቃሴ አላየሁም፡፡››
ኩማንደር የሆነ ደስ የማይል ስሜት ተሰማው….‹‹ቆይ ሳጅን….አንዴ ስልኩን ዝጋው….ልደውልላትና መልሼ ደውልልሀለው››
ስልኩ ተቋረጠ…ወዲያው የአለምን ቁጥር አወጣና ደወለ…ጥሪ አይቀበልም ነው የሚለው…ደገመ…ተመሳሰይ ነው፡፡ከተቀመጠበት ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳና ክፍሉ ውስጥ እየተሸከረከረ ማሰብ ጀመረ..መልሶ ሳጅኑ ጋር ደወለ‹‹ሳጅን ቀጥታ ወደቤቷ ሂድና አንኳኳ››የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡
‹‹ከከፈተችልኝስ?››
‹‹ጥሩ ነዋ…የምፈልገው ያንን አይደል?››
‹‹ማለቴ ምን እላታለው?››
‹‹ኩማደር በስልክ አገናኘኝ ብሎኝ ነው ብለህ ደውለህ ከእኔ ጋር ታገናኘናለህ››
‹‹እሺ በቃ ወደቤቷ እየቀረብኩ ነው፡፡››
ስልኩ ተቋረጠ…ኩማደሩ ከፊልድ ጃኬቱ ውስጥ ሲጋራ አወጣና ለኮሰ…..ወደ መስኮት ሄደና መስኮቱን ከፍቶ ውጭ የሚርመሰመሱትን መንገደኞች እየተመለከተ ሲጋራውን ማቡነንና መጥፎ መጥፎ ሀሳቦችን እየደራረበ ማሰቡን ቀጠለ፡፡ሲጋራውን አጭሶ ሳይጨርስ ስልኩ ተንጫረረ…ሳጅኑ ነው…አነሳውና የአለምን ድምጽ ለመስማት እየፀለየ ጆሮው ጋር አስጠጋ፡፡
‹‹አዝናለው ኩማንደር..ባንኳኳ ባንኳኳ ከውስጥ የሚመልስ ሰው የለም…..››
‹‹በቃ መጣው..እዛ በራፉ ጋር ሆነህ ጠብቀኝ››በማለት ግማሽ ሲጋራውን ወደ አሽትሬው ላይ ወረወረና ጃኬቱን ከወንበሩ ላይ አንጠልጥሎ ቢሮውን ለቆ ወጣ…ቀጥታ የመስሪያ ቤቱን ፒካፕ መኪና አስነስቶ ወደቤቷ መብረር ጀመረ፡፡ስልኩ መጥራት ጀመረ..ሲያየው ጁኒዬር ነው….በዚህ ሰዓት ከእሱ ጋር የማውራት አፒታይት የለውምና አላነሳም..ደግሞ ደወለ…..ልክ አለም ቤት ጋር ለመድረስ የሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ሲቀረው..ዳኛው ዋልልኝ ደወሉ…..‹‹ይሄማ በሰላም ሊሆን አይችልም አለና››የዳኛውን ስልክ ዘግቶ የመኪናውን ፍጥነት በመቀነስ ጁኒዬር ጋር ደወለለት…ወዲያው ነው የተነሳው፡፡
‹‹የት ነህ?››
‹‹ወደ አለም ቤት እየሄድኩነው››
‹‹አለች ግን?››
❤39👍8
‹‹እኔ እንጃ …ትኑር አትኑር አይታወቅም..ሰው ልኬ ነበር… ሲያንኳኩ ከውስጥ የሚመልስ ሰው የለም አሉኝ…ግን ምንድነው? የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ?››
‹‹ገመዶ ይህቺ የሰሎሜ ልጅ በጣም አደገኛ ነች..ቀድማ ጥቃት ጀምራለች….ሳታጠፋን የምታቆም አይመስለኝም››
‹‹ምን ተፈጠረ››
‹‹ቴሌግራምህን ክፈት የተፈጠረውን ልኬልሀለው….ዛሬውኑ አፍነን ወደተዘጋጀላት ቦታ መውሰድ አለብን…ቤት ካለች እንዳትለቃት ..እስክመጣ አብረሀት ሁን››ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡
ገመዶ መኪናውን ዳር አሲይዞ አቆመና ቴሌግራሙን ከፈተ …ከጁኒዬር አንድ ቪዲዬ ተልኳለታል፡፡
‹‹የሻሸመኔ ከተማ ወክሎ ለምክር ቤት የሚወዳደረው እጩ ተወዳዳሪው ስለእናቴ ግድያ ያውቃል!!››ይላል ርዕሱ…በንዴት እየተንቀጠቀጠ ከፈተው፡፡ሙሉ የአለም ምስል በእስክሪኑ ሞላ….፡፡በእናቷ እና በጁኒዬር..በእናቷ እና በገመዶ መሀከል ያለውን የልጅነት ግንኑኙነት ትዘረዝርና…እሷ እስከተወለደችበት ጊዜ ያለውን ታሪክ ተናግራ…ቀጣዩን ከሶስት ቀን በኃላ በተመሳሳይ ሰዓት ይጠብቁ በሚል ይቋረጣል፡፡ቪዲዬ ከተለቀቀ ገና አንድ ሰዓት ቢሆነውም..8 ሺ እይታ አግኝቷል…ከአንድ ከሁለት ቀን በኃላ በመላው ሀገር እንደሚዳረስ እርግጠኛ ነው…..ስልኩን ወደኪሱ አስገባና መኪናዋን አንቀሳቀሰ…አለም ቤት ጋር ሲደርስ ሳጂኑ በታዘዘው መሰረት በረንዳው ላይ ቆሞ እየጠበቀው ነበር፡፡
‹‹እ ምንም ነገር የለም››
‹‹አይ ምንም ነገር የለም››መለሰለት፡፡ኩማንደሩ ወደ ጓሮ ዞረ…ሳጅኑ ተከተለው….የጓሮውን በር ገፋ ሲያደርገው ተከፈተለት..ተንደርድሮ ወደውስጥ ገባ፡፡ በየክፍሉ እየተዘዋወረ ፈለገ…የለችም…መኝታ ቤቷ ገባና ቁም ሳጥኗን ከፈተ ባዶ ነው…ልብሷ ..ሻንጣዋ…ላፕቶፖ የለም፡፡አንድ ብጣሽ ወረቀት ጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል፡፡አነሳና ተመለከተው፡፡በንዴት ወደሳጅኑ ዞረና፡፡‹‹ምንድነው ኦና ቤት ነበር እንዴ ስትጠብቁ የነበረው?››
‹‹ ሄዳለች ማለት ነው››ሳጅኑ በድንጋጤ እና ግራ በመጋባት መልሶ ጠየቀ፡፡
‹‹ብሽቅ ናችሁ….››አለና በንዴት የፊት ለፊቱን በር ከፍቶ ወደበረንዳ ሲወጣ ጁኒዬር እየተንደረደረ ሲመጣ ተገጣጠሙ፡፡
‹‹አገኘሀት…?የት አለች?››
‹‹የለችም?››
‹‹የለችም ማለት?››
ኩማንደሩ ለጁኒዬር ሌላ መልስ ከመመለሱ በፊት ወደ ሳጅኑ ዞረና ‹‹ሳጅን በቃ አሁን አታስፈልግም..እዚህ ያላችሁ ስራ ተጠናቋል መሄድ ትችላለህ›› በማለት አሰናበተው፡፡
‹‹ግን እኮ መኪናዋ እንደቆመች ነው፡፡››
ገመዶ ‹‹መኪናዋን ከተጠቀመችማ በቀላሉ እንደምንከታተላት ታውቃለች..ለዛ ነው ማንም ሳያያት በጓሮ በር ወጥታ የተሰወረችው፡፡እቅዳችንን በሆነ መንገድ ያወቀችብን ይመስለኛል››ሲል ጥርጣሬውን ተናገረ፡፡
‹‹እንዴት ልታውቅ ትችላለች…?.ማን ሊነግራት ይችላል?››
‹‹አላውቅም…ግን እቃዎቾን ጠቅልላ ማንም ሳያይ በጓሮ በራፍ ወጥታ ነው የተሰወረችው….እና መኝታ ቤቷ ይሄንን ወረቀት ጥላ ነው ሄደችው..››አለና አንድ ብጣሽ ወረቀት አቀበለው፡፡
ለገመዶ..ጁኒዬርና ለአቶፍሰሀ….
እኔን ከዚህ ጫወታ ገለል ማድረግ እንደዚህ ቀላል አይሆንላችሁም፡፡ከዛሬ ጀምሮ ከፍትህ ይልቅ በቀልን መርጫለው፡፡ አድናችሁ ካገኛችሁኝ ግደሉኝ….ግን ያንን ማድረግ ከመቻላችሁ በፊት በየቀኑ አንድ አንድ ክንፋችሁን....ቀጥሎ እጆቻችሁን …ከዛም እግራችሁን… ከዛም አይኖቻችሁን..እያልኩ አጠፋችኋላው…..፡፡በማንኛውም ሰዓት ከመሀከላችሁ(ማለት..ገመዶ፤ጁኒዬር፤ስርጉት፤አቶ ፍሰሀ፤ሳራ)ከአምስታችሁ እናቴን የገደለው ሰው ወንጀሉን አምኖ አጅን ለመንግስት ከሰጠ በቀሌን አቆማለው
….ካለበለዚያ ሁላችሁንም አጠፋችኋላው….የማስጀመሪያው ርችት ተተኩሷል …ሰዓቱ እየቆጠረ ነው…ለእኔም ለእናንተም መልካም እድል፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ገመዶ ይህቺ የሰሎሜ ልጅ በጣም አደገኛ ነች..ቀድማ ጥቃት ጀምራለች….ሳታጠፋን የምታቆም አይመስለኝም››
‹‹ምን ተፈጠረ››
‹‹ቴሌግራምህን ክፈት የተፈጠረውን ልኬልሀለው….ዛሬውኑ አፍነን ወደተዘጋጀላት ቦታ መውሰድ አለብን…ቤት ካለች እንዳትለቃት ..እስክመጣ አብረሀት ሁን››ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡
ገመዶ መኪናውን ዳር አሲይዞ አቆመና ቴሌግራሙን ከፈተ …ከጁኒዬር አንድ ቪዲዬ ተልኳለታል፡፡
‹‹የሻሸመኔ ከተማ ወክሎ ለምክር ቤት የሚወዳደረው እጩ ተወዳዳሪው ስለእናቴ ግድያ ያውቃል!!››ይላል ርዕሱ…በንዴት እየተንቀጠቀጠ ከፈተው፡፡ሙሉ የአለም ምስል በእስክሪኑ ሞላ….፡፡በእናቷ እና በጁኒዬር..በእናቷ እና በገመዶ መሀከል ያለውን የልጅነት ግንኑኙነት ትዘረዝርና…እሷ እስከተወለደችበት ጊዜ ያለውን ታሪክ ተናግራ…ቀጣዩን ከሶስት ቀን በኃላ በተመሳሳይ ሰዓት ይጠብቁ በሚል ይቋረጣል፡፡ቪዲዬ ከተለቀቀ ገና አንድ ሰዓት ቢሆነውም..8 ሺ እይታ አግኝቷል…ከአንድ ከሁለት ቀን በኃላ በመላው ሀገር እንደሚዳረስ እርግጠኛ ነው…..ስልኩን ወደኪሱ አስገባና መኪናዋን አንቀሳቀሰ…አለም ቤት ጋር ሲደርስ ሳጂኑ በታዘዘው መሰረት በረንዳው ላይ ቆሞ እየጠበቀው ነበር፡፡
‹‹እ ምንም ነገር የለም››
‹‹አይ ምንም ነገር የለም››መለሰለት፡፡ኩማንደሩ ወደ ጓሮ ዞረ…ሳጅኑ ተከተለው….የጓሮውን በር ገፋ ሲያደርገው ተከፈተለት..ተንደርድሮ ወደውስጥ ገባ፡፡ በየክፍሉ እየተዘዋወረ ፈለገ…የለችም…መኝታ ቤቷ ገባና ቁም ሳጥኗን ከፈተ ባዶ ነው…ልብሷ ..ሻንጣዋ…ላፕቶፖ የለም፡፡አንድ ብጣሽ ወረቀት ጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል፡፡አነሳና ተመለከተው፡፡በንዴት ወደሳጅኑ ዞረና፡፡‹‹ምንድነው ኦና ቤት ነበር እንዴ ስትጠብቁ የነበረው?››
‹‹ ሄዳለች ማለት ነው››ሳጅኑ በድንጋጤ እና ግራ በመጋባት መልሶ ጠየቀ፡፡
‹‹ብሽቅ ናችሁ….››አለና በንዴት የፊት ለፊቱን በር ከፍቶ ወደበረንዳ ሲወጣ ጁኒዬር እየተንደረደረ ሲመጣ ተገጣጠሙ፡፡
‹‹አገኘሀት…?የት አለች?››
‹‹የለችም?››
‹‹የለችም ማለት?››
ኩማንደሩ ለጁኒዬር ሌላ መልስ ከመመለሱ በፊት ወደ ሳጅኑ ዞረና ‹‹ሳጅን በቃ አሁን አታስፈልግም..እዚህ ያላችሁ ስራ ተጠናቋል መሄድ ትችላለህ›› በማለት አሰናበተው፡፡
‹‹ግን እኮ መኪናዋ እንደቆመች ነው፡፡››
ገመዶ ‹‹መኪናዋን ከተጠቀመችማ በቀላሉ እንደምንከታተላት ታውቃለች..ለዛ ነው ማንም ሳያያት በጓሮ በር ወጥታ የተሰወረችው፡፡እቅዳችንን በሆነ መንገድ ያወቀችብን ይመስለኛል››ሲል ጥርጣሬውን ተናገረ፡፡
‹‹እንዴት ልታውቅ ትችላለች…?.ማን ሊነግራት ይችላል?››
‹‹አላውቅም…ግን እቃዎቾን ጠቅልላ ማንም ሳያይ በጓሮ በራፍ ወጥታ ነው የተሰወረችው….እና መኝታ ቤቷ ይሄንን ወረቀት ጥላ ነው ሄደችው..››አለና አንድ ብጣሽ ወረቀት አቀበለው፡፡
ለገመዶ..ጁኒዬርና ለአቶፍሰሀ….
እኔን ከዚህ ጫወታ ገለል ማድረግ እንደዚህ ቀላል አይሆንላችሁም፡፡ከዛሬ ጀምሮ ከፍትህ ይልቅ በቀልን መርጫለው፡፡ አድናችሁ ካገኛችሁኝ ግደሉኝ….ግን ያንን ማድረግ ከመቻላችሁ በፊት በየቀኑ አንድ አንድ ክንፋችሁን....ቀጥሎ እጆቻችሁን …ከዛም እግራችሁን… ከዛም አይኖቻችሁን..እያልኩ አጠፋችኋላው…..፡፡በማንኛውም ሰዓት ከመሀከላችሁ(ማለት..ገመዶ፤ጁኒዬር፤ስርጉት፤አቶ ፍሰሀ፤ሳራ)ከአምስታችሁ እናቴን የገደለው ሰው ወንጀሉን አምኖ አጅን ለመንግስት ከሰጠ በቀሌን አቆማለው
….ካለበለዚያ ሁላችሁንም አጠፋችኋላው….የማስጀመሪያው ርችት ተተኩሷል …ሰዓቱ እየቆጠረ ነው…ለእኔም ለእናንተም መልካም እድል፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍42😱22❤18🔥1