#ብሌን 🇪🇹
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በዮርዳኖስ
ያለሁበትን ቦታ በውል ባላውቀውም ግን ኢትየጵያ ወስጥ እንዳለሁ እርግጠኛ ነኝ።ሆኖም ስፍራወን እስካሁን በትክክል አላወኩትም።አከባቢው በአስፈሪ ጨለማ ተከቧል የጫካ ድባብ አለው ግን ጫካ አይደለም።ከደቂቃዎች በፊት ስለነበረው ነገር ብዙ ማስታውሰው የለም ራሴን ስቼ ነበር እናም አሁን ያለሁበትንም እንጃ።የነብሳት ድምፅ ከየምሽጋቸው ሲያስተጋባ ይሰማኛል።ውስጤ በፍራቻ ሲርድ ድንጋጤ በያንዳንዷ የደም ስሬ ሲሰራጭ ይታወቀኛል ሰውነቴ የኔ አልመስልሽ እስኪለኝ ድረስ በድን ሆኗል።በርግጥ ብቻዬን አይደለሁም በግምት ወደ አስር እንሆናለን ማናቸውንም ባላወቃቸውም ግን ከኔው እድሜ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ወንድና ጥቂት ሴቶች ወጣቶች ዙሪያዬን ልክ እንደኔው ግራ ሲጋቡና ሲያለቅሱ ይታያሉ።የት እንዳለን የምናውቀው ነገር የለም ሁሉም ግራ ተጋብቷል።እኔም እዚ እንዴት እንደተገኘው የማውቀው ነገር የለም እጆቼ ወደ ኋላ ተጠፍረው እንደታሰሩ ከህመሙ ተረድቻለው።ሌሎች አብረውኝ ያሉ ልጆችም እንደዛው አንዳንድ አፋቸውን የታሰሩ ሴቶችም ይታዩኛል ሆኖም ይጮሀሉ።ነብስ ተጨንቃ አይን ባያለቅስ አንደበት እንዴት ዝም ሊል ያስችል? ሌላው እንደኔ በድንጋጤ ደርቆ ግራ መጋባቱ ብቻ ከፊቱ ይነበባል የቀረው ያለቅሳል።ሁሉንም ከቃኘው ቡኋላ አንጋጥጬ ወደላይ ተመለከትኩ ከከበቡን ዛፎች ባሻገር ጥቁር ሰማይ ብቻውን ካላንዳች ኳክብትና ጨረቃ ጨልሞ ይታያል።ከአምላክ ጋር ፊትለፊት እማወራ ይመስል "የት ነኝ አንትስ ወዴት ነህ?" በውስጤ አነበነብኩ።ከንፋሱ ጋር አብሮ ከሚመጣው ሽውታ ጋር አንዳች ድምፅ የሰማው መሰለኝ ጆሮዬን ሰጠው አበረውኝ ካሉ ልጆች ለቅሶና ድምፆች ማለፍ አልቻለም።አይኖቼን ጨፍኜ የነበርኩበትን ለማስታወስ ሞከርኩ ።ምንም። አይምሮዬ ባዶ የሆነ መሰለኝ።መልሼ ወደ አከባቢው ትኩረቴን አደረኩ በድጋሚ ድምፅ ሰማሁ።ልክ ነበርኩ ድንገት ካለንበት ራቅ ካለ ስፍራ የባትሪ ና የእሳት ብርሀን ጭላንጭል ወደኛ ሲቀርብ አስከትሎም በዛ ያሉ ሰዎች ድምፅ በግልፅ ለሁሉም ተሰማ።ብርሀኑ ሲቀርብ ያለንበት ጫካ የመሰለው ቦታ በግልፅ ታየን ዙሪያውን በቀንጭብ የታጠረና በዛፎች የተሞለ ሰፊ ግቢ ነው።ሰዎቹ ሲቃረቡ ጫጫታ ተጀመረ ሁሉም ተደናገጠ ፈራን ግማሹ ያለቅሳል ሌላው ለእረዳታ የድረሱልን ጩኸቱን ይጮሀል የቀረው አለቀልን ሲል ሌላው እባካቹ ብሎ ይማፀናል።እኔ ብቻ ሳለሆን አልቀርም የደነዘዝኩት።ድንገት ኬት መጣ ያላልኩት እጅ ፀጉሬን ጨምድዶ ወደ ላይ ሲጎትት የደመ ነብሴን ተንደርድሬ ተነሳው ሌሎቹንም ልጆች እንደዛው ሰዎቹ ገና በአንደኛው የቅንጭብ መግቢያ እየገቡ ነበር ስለዚ ሲጠብቁን የነበሩ ሌሎች ሰዎች እዚው ባቅራቢያችን ነበሩ ማለት ነው።አየገፈታተሩ ና ሲከፋም በምት ጭምር እየተመራን እዛው አከባቢ ወዳለ የከብት ጋጣ ወደሚመስል ቤት አስገቡን።እርስ በእርሳቸው ቢያወሩም ግን ቋንቋቸው ሊገባኝ አልቻለም እነማን ይሁን? ምን ይሁኑ? ለምን ይያዙን? የሚያውቅ እንደሌለ ግልፅ ነው አብረወኝ ያሉ ልጆች እነማን ይሁኑ የማውቀው ነገር የለም።እዚ ስንደርስ ጠመንጃ የያዙ ሰዎች ቀደመው እየጠበቁን ነበር።እናም ለእያንዳንዳቸው ተሰጣቸው ጫጫታው ባሰ።አንዱ ሰውዬ ለየት ብሎ ከመካከላቸው
ወቶ ባላወቅነው ቋንቋ አየጮኸ ፊት ለፊታችን ቆሞ አፈ ሙዙን ወደኛ አስተካከለ።አሁን ነገሩ የገባኝ መሰለኝ በእርግጥ ምን ብሔር ይሁኑ እኛም ኬትኛው ብሔር ተወክለን እንደመጣን ባይገባኝም ግን ከዚ ቤት ማናችንም በሕይወት እንደማንወጣ ከፊታቸው ገፅታና ቁጣ ተረዳው።እኔ ብቻም ሳለሆን ሁሉም ወጣቶች ፊት ላይ ይሄ ተስፋ መቁረጥ ተነበበ።ሰውየው ቁልቁል እየተመለከተን ይለፈልፋል ሁሉም በአስፈሪ ፀጥታ ሚሆነውን ይጠብቃል። ያላዘዝኩት እንባዬ ቁልቁል በጉንጮቼ ላይ ሲወርድ ታወቀኝ ድንጋጤ በድን አካሌን ያፈረካከሰው መሰለኝ።ስቅስቀታ ያጀበው ፀጥታ ና የሚያነቡ አይኖች ሁሉም ሞቱን ሊገናኝ ሕይወትን እየተሰናበተ ይመስላል ።ሁሉንም ካየው ቡኋላ እሱ ጋር ስደርስ አንገቱን እየወዘወዘ በፈዘዘ አይን እያየኝ ነበር ከመጀመሪያው ጀምሮ እንደኔ ረጅም ዝምታ ውስጥ የነበረ ወጣት የማውቀው መሰለኝ ።አው አውቀዋለው አንድ ግቢ ነው የምንማረው አስተወስኩት "አልቆለናል ብሩክቲ"አለኝ በደከመ ድምፅ እንባው አየወረደ።የመጀመሪያው ጥይት በሱ ላይ ሲያርፍ ቤቱን እንደገና ጩኸት ሞላው። ያኔ ደንግጬ ነቃሁ።
:
:
💫 ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንደሁም ማስተካከል ያለባትን ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በዮርዳኖስ
ያለሁበትን ቦታ በውል ባላውቀውም ግን ኢትየጵያ ወስጥ እንዳለሁ እርግጠኛ ነኝ።ሆኖም ስፍራወን እስካሁን በትክክል አላወኩትም።አከባቢው በአስፈሪ ጨለማ ተከቧል የጫካ ድባብ አለው ግን ጫካ አይደለም።ከደቂቃዎች በፊት ስለነበረው ነገር ብዙ ማስታውሰው የለም ራሴን ስቼ ነበር እናም አሁን ያለሁበትንም እንጃ።የነብሳት ድምፅ ከየምሽጋቸው ሲያስተጋባ ይሰማኛል።ውስጤ በፍራቻ ሲርድ ድንጋጤ በያንዳንዷ የደም ስሬ ሲሰራጭ ይታወቀኛል ሰውነቴ የኔ አልመስልሽ እስኪለኝ ድረስ በድን ሆኗል።በርግጥ ብቻዬን አይደለሁም በግምት ወደ አስር እንሆናለን ማናቸውንም ባላወቃቸውም ግን ከኔው እድሜ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ወንድና ጥቂት ሴቶች ወጣቶች ዙሪያዬን ልክ እንደኔው ግራ ሲጋቡና ሲያለቅሱ ይታያሉ።የት እንዳለን የምናውቀው ነገር የለም ሁሉም ግራ ተጋብቷል።እኔም እዚ እንዴት እንደተገኘው የማውቀው ነገር የለም እጆቼ ወደ ኋላ ተጠፍረው እንደታሰሩ ከህመሙ ተረድቻለው።ሌሎች አብረውኝ ያሉ ልጆችም እንደዛው አንዳንድ አፋቸውን የታሰሩ ሴቶችም ይታዩኛል ሆኖም ይጮሀሉ።ነብስ ተጨንቃ አይን ባያለቅስ አንደበት እንዴት ዝም ሊል ያስችል? ሌላው እንደኔ በድንጋጤ ደርቆ ግራ መጋባቱ ብቻ ከፊቱ ይነበባል የቀረው ያለቅሳል።ሁሉንም ከቃኘው ቡኋላ አንጋጥጬ ወደላይ ተመለከትኩ ከከበቡን ዛፎች ባሻገር ጥቁር ሰማይ ብቻውን ካላንዳች ኳክብትና ጨረቃ ጨልሞ ይታያል።ከአምላክ ጋር ፊትለፊት እማወራ ይመስል "የት ነኝ አንትስ ወዴት ነህ?" በውስጤ አነበነብኩ።ከንፋሱ ጋር አብሮ ከሚመጣው ሽውታ ጋር አንዳች ድምፅ የሰማው መሰለኝ ጆሮዬን ሰጠው አበረውኝ ካሉ ልጆች ለቅሶና ድምፆች ማለፍ አልቻለም።አይኖቼን ጨፍኜ የነበርኩበትን ለማስታወስ ሞከርኩ ።ምንም። አይምሮዬ ባዶ የሆነ መሰለኝ።መልሼ ወደ አከባቢው ትኩረቴን አደረኩ በድጋሚ ድምፅ ሰማሁ።ልክ ነበርኩ ድንገት ካለንበት ራቅ ካለ ስፍራ የባትሪ ና የእሳት ብርሀን ጭላንጭል ወደኛ ሲቀርብ አስከትሎም በዛ ያሉ ሰዎች ድምፅ በግልፅ ለሁሉም ተሰማ።ብርሀኑ ሲቀርብ ያለንበት ጫካ የመሰለው ቦታ በግልፅ ታየን ዙሪያውን በቀንጭብ የታጠረና በዛፎች የተሞለ ሰፊ ግቢ ነው።ሰዎቹ ሲቃረቡ ጫጫታ ተጀመረ ሁሉም ተደናገጠ ፈራን ግማሹ ያለቅሳል ሌላው ለእረዳታ የድረሱልን ጩኸቱን ይጮሀል የቀረው አለቀልን ሲል ሌላው እባካቹ ብሎ ይማፀናል።እኔ ብቻ ሳለሆን አልቀርም የደነዘዝኩት።ድንገት ኬት መጣ ያላልኩት እጅ ፀጉሬን ጨምድዶ ወደ ላይ ሲጎትት የደመ ነብሴን ተንደርድሬ ተነሳው ሌሎቹንም ልጆች እንደዛው ሰዎቹ ገና በአንደኛው የቅንጭብ መግቢያ እየገቡ ነበር ስለዚ ሲጠብቁን የነበሩ ሌሎች ሰዎች እዚው ባቅራቢያችን ነበሩ ማለት ነው።አየገፈታተሩ ና ሲከፋም በምት ጭምር እየተመራን እዛው አከባቢ ወዳለ የከብት ጋጣ ወደሚመስል ቤት አስገቡን።እርስ በእርሳቸው ቢያወሩም ግን ቋንቋቸው ሊገባኝ አልቻለም እነማን ይሁን? ምን ይሁኑ? ለምን ይያዙን? የሚያውቅ እንደሌለ ግልፅ ነው አብረወኝ ያሉ ልጆች እነማን ይሁኑ የማውቀው ነገር የለም።እዚ ስንደርስ ጠመንጃ የያዙ ሰዎች ቀደመው እየጠበቁን ነበር።እናም ለእያንዳንዳቸው ተሰጣቸው ጫጫታው ባሰ።አንዱ ሰውዬ ለየት ብሎ ከመካከላቸው
ወቶ ባላወቅነው ቋንቋ አየጮኸ ፊት ለፊታችን ቆሞ አፈ ሙዙን ወደኛ አስተካከለ።አሁን ነገሩ የገባኝ መሰለኝ በእርግጥ ምን ብሔር ይሁኑ እኛም ኬትኛው ብሔር ተወክለን እንደመጣን ባይገባኝም ግን ከዚ ቤት ማናችንም በሕይወት እንደማንወጣ ከፊታቸው ገፅታና ቁጣ ተረዳው።እኔ ብቻም ሳለሆን ሁሉም ወጣቶች ፊት ላይ ይሄ ተስፋ መቁረጥ ተነበበ።ሰውየው ቁልቁል እየተመለከተን ይለፈልፋል ሁሉም በአስፈሪ ፀጥታ ሚሆነውን ይጠብቃል። ያላዘዝኩት እንባዬ ቁልቁል በጉንጮቼ ላይ ሲወርድ ታወቀኝ ድንጋጤ በድን አካሌን ያፈረካከሰው መሰለኝ።ስቅስቀታ ያጀበው ፀጥታ ና የሚያነቡ አይኖች ሁሉም ሞቱን ሊገናኝ ሕይወትን እየተሰናበተ ይመስላል ።ሁሉንም ካየው ቡኋላ እሱ ጋር ስደርስ አንገቱን እየወዘወዘ በፈዘዘ አይን እያየኝ ነበር ከመጀመሪያው ጀምሮ እንደኔ ረጅም ዝምታ ውስጥ የነበረ ወጣት የማውቀው መሰለኝ ።አው አውቀዋለው አንድ ግቢ ነው የምንማረው አስተወስኩት "አልቆለናል ብሩክቲ"አለኝ በደከመ ድምፅ እንባው አየወረደ።የመጀመሪያው ጥይት በሱ ላይ ሲያርፍ ቤቱን እንደገና ጩኸት ሞላው። ያኔ ደንግጬ ነቃሁ።
:
:
💫 ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንደሁም ማስተካከል ያለባትን ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
👍3
#ዳግም
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
"ሮምዬ...ብዙ ሰዐት ዝም አልሽ እኮ ...!..ጨነቀኝ...አንድ ነገር በይኝ እንጂ .." አላት፣ የደፈረሰ ፊቷን ሁለት እጆቿ ውስጥ ቀብራ በተቀመጠችበት ወደ ፊትና ወደ ኋላ ስትወዛወዝ እያየ። የምትሆነውን አላቆመችም። መልስም አልሰጠችውም። ጭንቀቱ ሳይለቀው፣ ፊት ለፊቱ ጠረፔዛ ላይ የተቀመጠውን ጀምሮት የነበረውን የብርጭቆ ውሃ፣ በአንድ ትንፋሽ ግጥም አድርጎ ጠጣና መልሶ አያት።
የተለወጠ ነገር የለም።
"ሮሚ..." አለና ትከሻዋን ነካት።
መወዝወዟን አቁማ፣ ፊቷን ከእጆቿ አውጥታ ከፊቷ እኩል በደፈረሱ ቁጡ ዐይኖቿ ዐየችው።
"በእናትሽ ለእኔም እዘኚልኝ እንጂ... ወድጄ እኮ አደለም...ያው ማወቅ አለብሽ ብዬ ነው..."
ምንም ሳትናገር ከተቀመጠችበት ተነሳችና የሳሎኑን በር ከፍታ ወጣች። ግራ በመጋባት ዐያትና ትንሽ ቆይቶ ተከተላት።
የበረንዳው መቀመጫ ላይ ኩምትር ብላ ተቀምጣለች።
አጠገቧ ተቀመጠ።
"ሮሚ..." አላት ወደ ጎን እያያት
"ወይ..."
"ባልነግርሽ ይሻል ነበር...? እ?"
"አሁን ሂድ...ብቻዬን መሆን እፈልጋለው ስምኦን...ነገ እደውልልሃለው..."
በመስማማትም፣ በአለሁልሽም፣ ትከሻዋን መታ መታ አድርጎ ተነሳና መራመድ ጀመረ።
የውጭው በር ጋር ደርሶ ከከፈተ በኋላ፣ ዞር ብሎ ዐያት። በተቀመጠችበት እያለቀሰች ነው። ተመልሶ ማፅናናት ትእዛዟን መጣስ፣ ዝም ብሎ መሄድ ደግሞ ጭካኔ ሆኖበት ግራ ተጋብቶ ዐያት። የሚያደርገውን መወሰን አቅቶት እንደቆመ ብድግ አለችና ወደ ቤት ገባች።
"ምስኪን ሮሚ" አለ ለራሱ። ምስኪን።
=========================
"አንቺ በቃ ይሄን ለቅሶ አልተውም አልሽ አይደል?" አለች ሳባ፣ በቁጣ። ስሞኦን ከሄደ ከረዥም ሰዐት በኋላ ሮማን ረጅሙ ሶፋ ላይ ጋቢዋን ለብሳ ስትንፋረቅ አግኝታት ነው።
"ተይኝ በናትሽ አንቺ ደሞ..." አለች፣ አፍንጫዋን በጋቢዋ ጫፍ እየጠረገች።
"ለምንድን ነው የምተውሽ? የምትወጅው ሰው የሞቸብሽ አንቺ ብቻ ነሽ እንዴ? ለእኔም ወንድሜ ነው...ያንን ደግ ሰው በሰላም እንዳያርፍ አታድርጊው። ይልቅ...ተነሽ አሁን ፊትሽን ታጠቢ..." አለች ሳባ ጮክ ብላ።
ሳባ የሮማን ታላቅ ብትሆንም፣ ዲበኩሉ ከሞተ ወዲህ እንደ ታላቅ ትቆጣታለች። እንደ ታላቅ ትወቅሳታለች። በሐዘን ተሽመድምዳ ለቁም ነገር መብቃት ያቃታት ሮማንም የታላቅነት ቦታዋን አምና ስለተቀበለችው እምቢ አትላትም። እህቷ ናትና፣ እንዲህ የሚያደርጋት ፍቅር ነውና በጄ ብላ ትታዘዝላታለች። ባሏን፣ ሁለተናዋን ካታች ደቂቃ ጀምሮ ለሦስት ወር ከመጣው ሰው ጋር ሁሉ ስትንፈራቅ፣ ሌሊት ተነስታ ዐይኖ እስኪጠፋ ስታለቅስ፣ በንዴት ጸጉሯን ስትነጭ፣ ከሰው አልገናኝም ብላ ሐያዥ ለገናዥ ስታስቸግር፣ ነጋ ጠባ የዲበ መቃብር ጋር እየሄደቸ፣ "ልጅ እንኳን ሳልወልድልህ አመለጥከኝ" ብላ ስታነባ፣ "በልክ አድርጊው.... በቃ" እያለች ወደ ሰውነት ልትመልሳት የምትታገለውን ታናሽ እህቷን፣ እሺ ትል ነበር። ዛሬ ግን አልቻለችም።
"ተነሽ እንጂ...ግቢና ታጠቢ!" አለች ሳባ፣ እጇን ይዛ ልታነሳት እየጎተተቻት።
"ውይ ሳባ ደግሞ! ተይኝ አልኩሽ እኮ!" አለች፣ እሷም ጮክ ብላ። "ለመሆኑ ምን ተፈጥሮ ነው ዛሬ ደሞ ደህና የነበርሽው ልጅ እንዲህ ሆነሽ የጠበቅሽኝ?" አለች ሳባ፣ ከሷፋው አልነሳም ብላ ያስቸገረቻትን ሮማን እጆቿን ለቃ እያየቻት።
"ምንም...."
"ምንም አትበይኝ....ማን መጥቶ ነበር?"
"ማንም....ማንም አልመጣም..."
"ሠራተኛውን ጠይቄ ማወቅ እችላለሁ እኮ ሮሚ...ለምን አትነግሪኝም?"
ሮማን ዝም ብላ ቆማ የምታያትን ሳባን ሽቅብ ማየት ጀመረች።
"ማነው የመጣው ሮሚ?"
"ስምኦን...ስምኦን ነው የመጣው ሳባዬ.."
ሮማን ማልቀስ ጀመረች። ሳባ ቶሎ ብላ አጠገቧ ተቀመጠችና።
"እንዴ...ታድያ ስምኦን ከለቅሶው ጀምሮ ከዚህ ቤት ጠፍቶ ያውቃል እንዴ? ምን ተፈጥሮ ነው ዛሬ እንዲህ የሆንሽው?"
አለች።
"ሳብዬ...ስምኦን የሆነ ነገር ነገረኝ..."
"ምን? ምን ነገረሽ?
"ምን ብዬ ልንጠርሽ..."
"ውይ ሮሚ በናትሽ አታስጨንቂኝ..."
"ዲበ.......ዲበ ልጅ አለው..."
"ም....ን?" አለች ሳባ፣ ፍንጥር ብላ እየተነሳች። ሶፋው አንጥሮ ያጎናት ነበር የምትመስለው።
"ዲበ ልጅ አለው..." ሮማን ደገመችላት።
"የት...? ከማን...? መቼ....? ማለቴ እንዴት...? ሳባ በቆመችበት ቅደም ተከተል የሌላቸው ጥያቄዎች አዘነበችባት
"የመስርያ ቤት ልጅ ናት አለኝ..."
"ማን ነው እንዲህ ያለሽ ?"
"ውይ አንቺ ደግሞ ስምኦን ነዋ!"
"እ....ስምኦን...ቆይ ልቀመጥ... አዞረኝ አኮ በናትሽ..." ሳባ ተመልሳ ሮማን አጠገብ ተቀመጠች።
"እና...ማለቴ እርግጠኛ ነው? እንዴት ዐወቀ እሱ..."
"ቤስት ፍሬንዱ አይደል...ነግሮት ነዋ..."
ሳባ እራሷን በታላቅ መገረም ወደቀኝ እና ወደ ግራ ስትወዘውዝ ቆየችና...
"ቆይ...ቆይ ይሄ...ማለቴ ልጁ...ካንቺ በፊት የወለደው ነው አይደል...? ማለቴ የስንት ዓመት ልጅ ነው?"
ሮማን ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ ማልቀስ ጀመረች።
"ሮሚ....ካንቺ በፊት ነው አይደል?"
ሮማን ማልቀሷን ሳታቋርጥ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።
"ወይ ጉድ! ወይ ጉድ! ወይ ጉድ! ወይ ሰው! አለች ሳባ፣ እጆቿን በማጨብጨብ እያማታች።
"ለመሆኑ...የስንት ዓመት ልጅ ነው ያለው አለሽ...? አለች የሮማንን፣ ለቅሶ ለማስቋም ሳትቋጣ።
"ሦስት ዓመቱ ነው አለኝ..."
"ወንድ ልጅ ነው?"
"አዎ..."
"ወይ ጉድ! እኔ መቼስ ማመን አቅቶኛል... ውሸት መሆን አለበት...ዲበ ባንቺ ላይ? ሌላ ሴት? አይመስለኝም...."
"ህም...ሳቢዬ...እኔም ማመን አቅቶኛል ግን..."
"ግን...ምን?"
"ተቆራጭ ሲያደርግላት እንደነበር ነግሮኛል...እሱ ከሞተም ለሦስት ወር ስምኦን ሲከፍላት ነበር...."
"ወይ ጉድ...!"
"የት ነው የምትኖረው? እዚሁ አዲስአባ?"
"አይደለም..."
"እና የት ናት..."
"ናዝሬት"
"ናዝሬት?"
"አዎ....ናዝሬት..."
"እና ቆይ...ቅምጥ ነገር ናት ማለት ነው?"
"አይ...ሳቢ እኔ ምኑን አውቄው...? ስምኦን ግን ሲምል ሲገዘት ነበር..."
"ምን ብሎ?"
"የአንድ ቀን ስህተት ነው....ከዚህ ወዲህ ለልጁ ነው እንጂ እንኳን በፍቅር በሥርአትም አግኝቷት አያውቅ እያለ ሲምልልኝ ነበር....."
"ወይ ጉድ!"
በዚህ ሁኔታ ወሬው በ 'ወይ ጉድ' ታጅቦ፣ ባለማመን ታጅሎ ለሰዓታት ለሰአታት ቆየ። የመኝታ ሰዓት ደርሶ ለስሙ አልጋዋ ውስጥ የገባችው ሮማን ግን ነገር ማውጠንጠን ቀጠለች።
ዲበ? የኔ ዲበ ከሌላ ሴት ጋር ተኛ? እሺ ፊልድ ላይ ነው...እሺ ጠጥቶ ነው...እሺ ተሳስቶ ነው... የኔ ደግ፣ ካለኔ ዓይኑ የማይገለጠው፣ ካለኔ አንደበቱ የማይከፈተው ባል ከሌላ ሴት ተኝቶ ዘር ፈጠረ? ልጅ ሠራ?
የስህተት ልጅ ሰርቶስ አራት ዓመት ሙሉ ባልና ሚስት ሆነን፣ አፍ ለአፍ ገጥመን እያወራን፣ ከጣራ በላይ እየሳቅን፣ ፍቅር እነሰራን፣ ሙዚቃ እየሰማን፣ እስክስታ እየወረድን፣ ሻይ እያፈላን፣ ቡና እየጠጣን፣ ፍርፍር እየበላን፣ ሥራ እየሄድን፣ በመንገድ ጭንቅንቅ እየተነጫነጭን፣ መኪና እየነዳን፣ በኪራይ ቤት እየተማረርን፣ ቤት እየገነባን፣ በአሁኑ እንውለድ ወይስ ቤታችን እስቂያልቅ እንቆይ እየተከራከርን.... ይህን ሁሉ እየሆንን አስችሎት ዋሸኝ? አንጀቱ እሺ ብሎት ደበቀኝ? እኮ የኔ ዲበ....መንገድ ወጥቶ የቀረው
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
"ሮምዬ...ብዙ ሰዐት ዝም አልሽ እኮ ...!..ጨነቀኝ...አንድ ነገር በይኝ እንጂ .." አላት፣ የደፈረሰ ፊቷን ሁለት እጆቿ ውስጥ ቀብራ በተቀመጠችበት ወደ ፊትና ወደ ኋላ ስትወዛወዝ እያየ። የምትሆነውን አላቆመችም። መልስም አልሰጠችውም። ጭንቀቱ ሳይለቀው፣ ፊት ለፊቱ ጠረፔዛ ላይ የተቀመጠውን ጀምሮት የነበረውን የብርጭቆ ውሃ፣ በአንድ ትንፋሽ ግጥም አድርጎ ጠጣና መልሶ አያት።
የተለወጠ ነገር የለም።
"ሮሚ..." አለና ትከሻዋን ነካት።
መወዝወዟን አቁማ፣ ፊቷን ከእጆቿ አውጥታ ከፊቷ እኩል በደፈረሱ ቁጡ ዐይኖቿ ዐየችው።
"በእናትሽ ለእኔም እዘኚልኝ እንጂ... ወድጄ እኮ አደለም...ያው ማወቅ አለብሽ ብዬ ነው..."
ምንም ሳትናገር ከተቀመጠችበት ተነሳችና የሳሎኑን በር ከፍታ ወጣች። ግራ በመጋባት ዐያትና ትንሽ ቆይቶ ተከተላት።
የበረንዳው መቀመጫ ላይ ኩምትር ብላ ተቀምጣለች።
አጠገቧ ተቀመጠ።
"ሮሚ..." አላት ወደ ጎን እያያት
"ወይ..."
"ባልነግርሽ ይሻል ነበር...? እ?"
"አሁን ሂድ...ብቻዬን መሆን እፈልጋለው ስምኦን...ነገ እደውልልሃለው..."
በመስማማትም፣ በአለሁልሽም፣ ትከሻዋን መታ መታ አድርጎ ተነሳና መራመድ ጀመረ።
የውጭው በር ጋር ደርሶ ከከፈተ በኋላ፣ ዞር ብሎ ዐያት። በተቀመጠችበት እያለቀሰች ነው። ተመልሶ ማፅናናት ትእዛዟን መጣስ፣ ዝም ብሎ መሄድ ደግሞ ጭካኔ ሆኖበት ግራ ተጋብቶ ዐያት። የሚያደርገውን መወሰን አቅቶት እንደቆመ ብድግ አለችና ወደ ቤት ገባች።
"ምስኪን ሮሚ" አለ ለራሱ። ምስኪን።
=========================
"አንቺ በቃ ይሄን ለቅሶ አልተውም አልሽ አይደል?" አለች ሳባ፣ በቁጣ። ስሞኦን ከሄደ ከረዥም ሰዐት በኋላ ሮማን ረጅሙ ሶፋ ላይ ጋቢዋን ለብሳ ስትንፋረቅ አግኝታት ነው።
"ተይኝ በናትሽ አንቺ ደሞ..." አለች፣ አፍንጫዋን በጋቢዋ ጫፍ እየጠረገች።
"ለምንድን ነው የምተውሽ? የምትወጅው ሰው የሞቸብሽ አንቺ ብቻ ነሽ እንዴ? ለእኔም ወንድሜ ነው...ያንን ደግ ሰው በሰላም እንዳያርፍ አታድርጊው። ይልቅ...ተነሽ አሁን ፊትሽን ታጠቢ..." አለች ሳባ ጮክ ብላ።
ሳባ የሮማን ታላቅ ብትሆንም፣ ዲበኩሉ ከሞተ ወዲህ እንደ ታላቅ ትቆጣታለች። እንደ ታላቅ ትወቅሳታለች። በሐዘን ተሽመድምዳ ለቁም ነገር መብቃት ያቃታት ሮማንም የታላቅነት ቦታዋን አምና ስለተቀበለችው እምቢ አትላትም። እህቷ ናትና፣ እንዲህ የሚያደርጋት ፍቅር ነውና በጄ ብላ ትታዘዝላታለች። ባሏን፣ ሁለተናዋን ካታች ደቂቃ ጀምሮ ለሦስት ወር ከመጣው ሰው ጋር ሁሉ ስትንፈራቅ፣ ሌሊት ተነስታ ዐይኖ እስኪጠፋ ስታለቅስ፣ በንዴት ጸጉሯን ስትነጭ፣ ከሰው አልገናኝም ብላ ሐያዥ ለገናዥ ስታስቸግር፣ ነጋ ጠባ የዲበ መቃብር ጋር እየሄደቸ፣ "ልጅ እንኳን ሳልወልድልህ አመለጥከኝ" ብላ ስታነባ፣ "በልክ አድርጊው.... በቃ" እያለች ወደ ሰውነት ልትመልሳት የምትታገለውን ታናሽ እህቷን፣ እሺ ትል ነበር። ዛሬ ግን አልቻለችም።
"ተነሽ እንጂ...ግቢና ታጠቢ!" አለች ሳባ፣ እጇን ይዛ ልታነሳት እየጎተተቻት።
"ውይ ሳባ ደግሞ! ተይኝ አልኩሽ እኮ!" አለች፣ እሷም ጮክ ብላ። "ለመሆኑ ምን ተፈጥሮ ነው ዛሬ ደሞ ደህና የነበርሽው ልጅ እንዲህ ሆነሽ የጠበቅሽኝ?" አለች ሳባ፣ ከሷፋው አልነሳም ብላ ያስቸገረቻትን ሮማን እጆቿን ለቃ እያየቻት።
"ምንም...."
"ምንም አትበይኝ....ማን መጥቶ ነበር?"
"ማንም....ማንም አልመጣም..."
"ሠራተኛውን ጠይቄ ማወቅ እችላለሁ እኮ ሮሚ...ለምን አትነግሪኝም?"
ሮማን ዝም ብላ ቆማ የምታያትን ሳባን ሽቅብ ማየት ጀመረች።
"ማነው የመጣው ሮሚ?"
"ስምኦን...ስምኦን ነው የመጣው ሳባዬ.."
ሮማን ማልቀስ ጀመረች። ሳባ ቶሎ ብላ አጠገቧ ተቀመጠችና።
"እንዴ...ታድያ ስምኦን ከለቅሶው ጀምሮ ከዚህ ቤት ጠፍቶ ያውቃል እንዴ? ምን ተፈጥሮ ነው ዛሬ እንዲህ የሆንሽው?"
አለች።
"ሳብዬ...ስምኦን የሆነ ነገር ነገረኝ..."
"ምን? ምን ነገረሽ?
"ምን ብዬ ልንጠርሽ..."
"ውይ ሮሚ በናትሽ አታስጨንቂኝ..."
"ዲበ.......ዲበ ልጅ አለው..."
"ም....ን?" አለች ሳባ፣ ፍንጥር ብላ እየተነሳች። ሶፋው አንጥሮ ያጎናት ነበር የምትመስለው።
"ዲበ ልጅ አለው..." ሮማን ደገመችላት።
"የት...? ከማን...? መቼ....? ማለቴ እንዴት...? ሳባ በቆመችበት ቅደም ተከተል የሌላቸው ጥያቄዎች አዘነበችባት
"የመስርያ ቤት ልጅ ናት አለኝ..."
"ማን ነው እንዲህ ያለሽ ?"
"ውይ አንቺ ደግሞ ስምኦን ነዋ!"
"እ....ስምኦን...ቆይ ልቀመጥ... አዞረኝ አኮ በናትሽ..." ሳባ ተመልሳ ሮማን አጠገብ ተቀመጠች።
"እና...ማለቴ እርግጠኛ ነው? እንዴት ዐወቀ እሱ..."
"ቤስት ፍሬንዱ አይደል...ነግሮት ነዋ..."
ሳባ እራሷን በታላቅ መገረም ወደቀኝ እና ወደ ግራ ስትወዘውዝ ቆየችና...
"ቆይ...ቆይ ይሄ...ማለቴ ልጁ...ካንቺ በፊት የወለደው ነው አይደል...? ማለቴ የስንት ዓመት ልጅ ነው?"
ሮማን ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ ማልቀስ ጀመረች።
"ሮሚ....ካንቺ በፊት ነው አይደል?"
ሮማን ማልቀሷን ሳታቋርጥ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።
"ወይ ጉድ! ወይ ጉድ! ወይ ጉድ! ወይ ሰው! አለች ሳባ፣ እጆቿን በማጨብጨብ እያማታች።
"ለመሆኑ...የስንት ዓመት ልጅ ነው ያለው አለሽ...? አለች የሮማንን፣ ለቅሶ ለማስቋም ሳትቋጣ።
"ሦስት ዓመቱ ነው አለኝ..."
"ወንድ ልጅ ነው?"
"አዎ..."
"ወይ ጉድ! እኔ መቼስ ማመን አቅቶኛል... ውሸት መሆን አለበት...ዲበ ባንቺ ላይ? ሌላ ሴት? አይመስለኝም...."
"ህም...ሳቢዬ...እኔም ማመን አቅቶኛል ግን..."
"ግን...ምን?"
"ተቆራጭ ሲያደርግላት እንደነበር ነግሮኛል...እሱ ከሞተም ለሦስት ወር ስምኦን ሲከፍላት ነበር...."
"ወይ ጉድ...!"
"የት ነው የምትኖረው? እዚሁ አዲስአባ?"
"አይደለም..."
"እና የት ናት..."
"ናዝሬት"
"ናዝሬት?"
"አዎ....ናዝሬት..."
"እና ቆይ...ቅምጥ ነገር ናት ማለት ነው?"
"አይ...ሳቢ እኔ ምኑን አውቄው...? ስምኦን ግን ሲምል ሲገዘት ነበር..."
"ምን ብሎ?"
"የአንድ ቀን ስህተት ነው....ከዚህ ወዲህ ለልጁ ነው እንጂ እንኳን በፍቅር በሥርአትም አግኝቷት አያውቅ እያለ ሲምልልኝ ነበር....."
"ወይ ጉድ!"
በዚህ ሁኔታ ወሬው በ 'ወይ ጉድ' ታጅቦ፣ ባለማመን ታጅሎ ለሰዓታት ለሰአታት ቆየ። የመኝታ ሰዓት ደርሶ ለስሙ አልጋዋ ውስጥ የገባችው ሮማን ግን ነገር ማውጠንጠን ቀጠለች።
ዲበ? የኔ ዲበ ከሌላ ሴት ጋር ተኛ? እሺ ፊልድ ላይ ነው...እሺ ጠጥቶ ነው...እሺ ተሳስቶ ነው... የኔ ደግ፣ ካለኔ ዓይኑ የማይገለጠው፣ ካለኔ አንደበቱ የማይከፈተው ባል ከሌላ ሴት ተኝቶ ዘር ፈጠረ? ልጅ ሠራ?
የስህተት ልጅ ሰርቶስ አራት ዓመት ሙሉ ባልና ሚስት ሆነን፣ አፍ ለአፍ ገጥመን እያወራን፣ ከጣራ በላይ እየሳቅን፣ ፍቅር እነሰራን፣ ሙዚቃ እየሰማን፣ እስክስታ እየወረድን፣ ሻይ እያፈላን፣ ቡና እየጠጣን፣ ፍርፍር እየበላን፣ ሥራ እየሄድን፣ በመንገድ ጭንቅንቅ እየተነጫነጭን፣ መኪና እየነዳን፣ በኪራይ ቤት እየተማረርን፣ ቤት እየገነባን፣ በአሁኑ እንውለድ ወይስ ቤታችን እስቂያልቅ እንቆይ እየተከራከርን.... ይህን ሁሉ እየሆንን አስችሎት ዋሸኝ? አንጀቱ እሺ ብሎት ደበቀኝ? እኮ የኔ ዲበ....መንገድ ወጥቶ የቀረው
👍4🤔1
ፍቅሬ፣ አንጀቴን አስሬ አፈር ያስገባሁት ግማሽ አካሌ... ያ ገራገር ልቡ እሺ ብሎት ይሄን ሁሉ ግዜ አታለለኝ? አታለለኝ ወይ?
💫ነገ እንጨርሰው....💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
💫ነገ እንጨርሰው....💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ዳግም (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
==========
"ሳቢ ቅድስትን ነገ ላገኛት ነው..." አለች ሮማን፣ ሳባን ሳይሆን፣ በመብላት ፋንታ በዳቦ አንቃ ሰሃኑ ላይ ወዲህ ወድያ የምታንገላታውን እንቁላል ፍርፍር እያየች።
ሳባ ሻይ ትጠጣበት የነበረውን ወፍራም ብርጭቆ ጠረጴዛው ላይ በኀይል ጓ! አድርጋ አስቀመጠችና፣
"አንቺ ግን ጤና የለሽም በቃ? ደሞ ምን ልሁን ብለሽ ነው የምታገኛት?" አለች።
"ስንቴ ልንገርሽ...አንቺ አይገባሽም..." አለች ሮማን በፍርሃት ካቀረቀረችበት ቀና ብላ እያየቻት።
"ምኑ ነው የሚገባኝ? ባልሽ እላይሽ ላይ ሌላ ሴት ጋር መሄድ ሳያንስ፣ ልጅ መውለዱ ሳያንስ ሄጄ ላገኛቸው ስትይ ምኑ ነው የሚገባኝ!" ሳብ በንዴት መለሰች።
"ሳቢ...እንደሱ አይደለም... ሁለት ሳምንት ተናደድኩ...አለቀስኩ... አሁን ግን ረጋ ቡዬ ሳስበው በሞተ ሰው ለይ መናደድ ድንጋይ መንከስ ምናምን የሚሉት ገባኝ.... ማለት እሱ የለም...ስምኦን ደግሞ ደጋግሞ ነግሮኛል... ስህተት ነበር..."ሳባ አላስጨረሰቻትም።
"ስህተት ቢሆንስ? አንቺ የእሱን ዲቃላ ማሳደግ አለብሽ?" "ሳቢ... እንደሱ አይባልም...ደሞ እኔ ላሳድግ አልኩኝ?" "እና ታድያ ምን ልትሆኚ ነው የምታገኛት?
ሮማን በዝምታ ማሰብ ጀመረች። ለምንድን ነው ቅድስትን የምታገኛት? ራሷ ዐይታ ለማረጋገጥ? የአራት ዓመት ባሏ የተሳሳተባትን ሴት በዐይኗ ለመመልከት ልጁን ዐይታ እሺ ብትለው ኖሮና ቢወልዱ ኖሮ ምን የሚመስሉ ልጆቹን ይኖሯት እንደነበር ለመገመት? አታውቅም። ግን ልታገኛት ፈልጋለች።
"መልሺልኝ እንጂ!" ሳባ በጩኸት ጠየቀች።
"አላውቅም ሳቢ ግን ላገኛት ይገባል... ይቆርጥልኛል...." "ተይ ባክሽ ያንቺ ጅል አንጀት ምንም ቢያደርጉት አይቆርጥም. የራስሽ ጉድይ!" ሳባ ከወንበሯ ተነሳችና ወደ መታጠብያ ቤት መሄድ ጀመረች።
ከሳሎን ልትወጣ ጥቂት እርምጃ ሲቀራት ግን የበላችበት እጇን አንከርፍፋ ዞር አለችና፣
"ልጁን ይዛ ነው የምትመጣው ?" አለቻት።
"እ?"
"ልጇን ታመጣዋለቸሸ ወይ ?"
"እኔ እኮ ነው የምሄደው.... ናዝሬት ነው የምሄደው...."
"ምን....?"
"እሷ ልጅ ይዛ እዚህ ድረስ ከምትመጣ እኔ ብሄድ አይሻልም?"
"አንቺ ለይቶልሻል.... የራስሸ ጉዳይ...!"
ሳባ ምንቅርቅር እያለች ከሳሎን ወጣች።
=============
ሮማን የተቀጣጠሩበት ባለ ሰፊ የአትክልት ቦታ ሆቴል ቀድማ ደርሳ እየጠበቀች ነው። ያዘዘችውን ሚሪንዳ አሁንም አሁንም እየተጎነጨች በትግስት እየጠበቀች ነው። ለሚያያት የናፈቀችውን ፍቅረኛ እንጂ ባላንጣዋንና የባሏን ሕገ-ወጥ ልጅ የምትጠብቅ አትመስልም። ሕገ-ወጥ ልጅ - ሕገ- ወጥ ሰው አለ? ዐሥር ደቂቃ እንዳለፈ ሙሉ ቀይ ቱታ ለብሳ፣ ከእሷ እኩል ለመራመድ የሚታገል ትንሽ ልጅ እጅ ይዛ፣ ወደ ግቢው የምትገባ አጠርና ደልደል ያለች ሴት ዐየች።
ሚሪንዳዋን አንስታ ተጎነጨች። በረጅሙ ተኘፈሰች። እነሱ መሆን አለባቸው።
ሴትየዋ በረንዳው ላይ የተቀመጡ ሰዎችን ሰው በሚፈልግ ሰው ዓይነት ከቃኘች በኋላ ወደ እሷ መምጣት ጀመረች።
ሮማን በተቀመጠችበት ተንቆራጠጠች።
ሊያልቅ አንድ ጉንጭ የቀረውን ሚሪንዳዋን ተጎነጨች። ሴትየዋ ከነልጇ አጠገቧ ደረሰች።
"ይቅርታ...ሮማን ነሽ?" አለቻት ወድያው።
"አዎ...ቅድስት? " አለች ሮማን፣ ከተቀመጠችበት ተነስታ እጇን ለሰላምታ እየዘረጋች - አንዴ አጠገቧ ስትደርስ ከቅድሙ በጣም ያጠረችባትን ሴት፣ አንዴ ደግሞ ድምቡሽቡሹን ትንሽዬ ልጇን አፈራርቃ እያየች።
ቅድስት የልጅ መንቀዥቀዥ የሌለበትን ልጇን አቅፋ ቸቀመጠች። ከምንና በምን ወሬ እንጀምትጀምር ግራ የተጋባችው ሮማን፣ የሳባን ምክር ሰምታ መቅረት እንደነበረባት ማሰብ ጀመረች። ምን ልትላት ነው? ለምን ከባሌ ጋር ተኛሽ? ለምን ከእኔ ሳይወልድ ከእሱ ወለድሽ? ሞቱ እንደኔ ጎዳሽ ወይ?
"ምን ይምጣላችሁ አለች?" በዚህ ሁሉ ፋንታ።
ቅድስት ለራሷ ኮካ ኮላ፣ ለልጇ ደሞ ፋንታ አዘዘች። ሮማን ደግሞ ሌላ ሚሪንዳ ጠየቀች። እንደገና ምቾት የማይሰጥ ዝምታ ሰፈነ። አሁን ደግሞ ለብቻው ወንበር ላይ የተቀመጠው ልጅ በትልቅ ሰው ወግ በስነ- ስርአት ተቀምጦ እናቱ የምታጠጣውን ፋንታ በዝምታ፣ አንዳንዴ በፈገግታ ይጠጣል። እርጋታው ደስ ከማለት ይልቅ ምቾት ይኘሳል።
"በረታችሁ....?" አለች ቅድስት፣ እየሰፋ የመጣውን የዝምታ ክፍተት ለመሙላት በመመኘት።
"እግዜር ይመስገን...ቋሚ ምን ይሆናል... በርትተናል..." አለች ሮማን። "አንቺስ በረታሽ?" ብዬ ልጠይቃት ወይስ ዝም ልበል ፣ በሚል ሐሳብ ተይዛ። "የዲበ ነገር መቼም የሚያሳዝን ነው... እግዜር ነፍሱን ይማር..." አለች ቅድስት።
"እህ... አሜን..." ሮማን መለሰች....
"እኔ ምለው..." አለች ወዲያው መልሳ።
"አንቺ የምትይው..." ቅድስት መለሰች።
"ለቅሶ መጥተሽ ነበር እንዴ?"
ቅድስት ከብዙ ምርጫዎች ውስጥ መልሷን ለመምረጥ እንደፈለገች ሁሉ አሰበችና፤ "እንዴት አልመጣም....ቀብር መጥቼ ነበር....ቤት ግን መረበሽ ስላልፈለግኩ አልመጣሁም..." አለች።
"መረበሽ ማለት? " ሮማን ቶሎ ብላ ጠየቀች። "አይ...እንዳልነገረሽ ስለማውቅ በዚያ ሰዐት ሌላ ነገር...ጭንቀት መጨመር አልፈለግኩም...."
ሮማን በገባኝ ራሷን ነቅንቃ ዝም አለችና ወደ ልጁ ዞር ብላ ዐየችው። አሁንም በትልቅ ሰው ወግ ፈገግ አለላት።
"ዲበን ይመስላል ልበል?" አለች ሳታስበው።
"እ?" ቅድስት በድንጋጤ መለሰች።
"ልጅሽ አይኑ ጋር...ዲበን ይመስላል...."
"ነው ብለሽ ነው...? እንጃ አይመስለኝም... ሰው ሁሉ የእኔን አባት ነው ይመስላል የሚለው...."
"አይ...ዐይኑ ጋር ወደሱ የሚሄድ ነገር አለው..."
ሮማን ሳታስበው ዐይኖቿ በእንባ ተሞሉ።
"ማነው ስሙ?"
"ስሙ?"
"እ...ማነው ስሙ?"
"ዳግም..."
"ዳግም ዲበኩሉ?"
"አዎ..."
"አንቺ ነሽ ያወጣሽለት ወይስ ዲበ ነው?"
"አይ... እኔ ነኝ...."
ዳግም ወሬው እንደከበደው ሁሉ ከወንበሩ ተንሸራቶ ወረደና ወደ አትክልት ቦታው እየተደረደረ መሄድ ጀመረ። እናቱ በዐይኗ እንጂ ተነስታ አልተከተለችውም።
"ኮንዶም አልተጠቀማችሁም ነበር?" ሮማን አሁንም ሳታስበው ጠየቀች።
"ምን?" አለች ቅድስት በድንጋጤ ዐይኖቿን እየተንገዳገደ ከሚሄደው ልጅ ወደ ሮማን መልሳ...
"ማለቴ...መስከራችሁን ስምኦን ነግሮኛል...ግን ኮንደም አልተጠቀማችሁም?"
ይህንን ጥያቄ በዚህ ሰዐት ለምን እንደጠየቀች አታውቅም። ምናልባት የተሳሳተው ባሏ በስካርና በስህተት ሰዐት እንኳን የወትሮው ጠንቃቃነቱ አብሮት ነበር ብላ ለማመን ፈልጋ ይሆናል.... ምናልባት በሽታ ይዞኝ ሚስቴንንም አሲዛለሁ ብሎ ሰግቶ፣ አዝኖልኝ ይሆናል ብላ ልታምን ፈልጋ ይሆናል።
"ወይዘሮ ሮማን... ለምን ልታገኚኝ እንደፈለግሽ አልገባኝም...ግን እሺ ያልኩሽ ለዲበ ብዬ ነው... ጥሩ ሰው ነበር.... ለእሱ ብዬ...ስሞኦንንም አንቺንም አክብሬ ነው...ግን እንዲህ አይነት ጥያቄ...."
"ይቅርታ ቅድስት....."
"እ?"
"ይቅርታ.... እንዲህ አይነት ነገር መጠየቅ አልነበረብኝም....ግራ ገብቶኝ ኘው...."
ቅድስት ምንም ሳትመልስላት ብድግ ብላ ወደ ልጇ ሄደች። ሮማን በተቀመጠችበት ሆና አትክልት ስፍራው ውስጥ የውሸት ስታባርረው ፣ ሲፈነድቅ፣ እፍስፍስ አድርጋ አንስተረ ሁለመናውን ስትስመው ዐየች።
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
==========
"ሳቢ ቅድስትን ነገ ላገኛት ነው..." አለች ሮማን፣ ሳባን ሳይሆን፣ በመብላት ፋንታ በዳቦ አንቃ ሰሃኑ ላይ ወዲህ ወድያ የምታንገላታውን እንቁላል ፍርፍር እያየች።
ሳባ ሻይ ትጠጣበት የነበረውን ወፍራም ብርጭቆ ጠረጴዛው ላይ በኀይል ጓ! አድርጋ አስቀመጠችና፣
"አንቺ ግን ጤና የለሽም በቃ? ደሞ ምን ልሁን ብለሽ ነው የምታገኛት?" አለች።
"ስንቴ ልንገርሽ...አንቺ አይገባሽም..." አለች ሮማን በፍርሃት ካቀረቀረችበት ቀና ብላ እያየቻት።
"ምኑ ነው የሚገባኝ? ባልሽ እላይሽ ላይ ሌላ ሴት ጋር መሄድ ሳያንስ፣ ልጅ መውለዱ ሳያንስ ሄጄ ላገኛቸው ስትይ ምኑ ነው የሚገባኝ!" ሳብ በንዴት መለሰች።
"ሳቢ...እንደሱ አይደለም... ሁለት ሳምንት ተናደድኩ...አለቀስኩ... አሁን ግን ረጋ ቡዬ ሳስበው በሞተ ሰው ለይ መናደድ ድንጋይ መንከስ ምናምን የሚሉት ገባኝ.... ማለት እሱ የለም...ስምኦን ደግሞ ደጋግሞ ነግሮኛል... ስህተት ነበር..."ሳባ አላስጨረሰቻትም።
"ስህተት ቢሆንስ? አንቺ የእሱን ዲቃላ ማሳደግ አለብሽ?" "ሳቢ... እንደሱ አይባልም...ደሞ እኔ ላሳድግ አልኩኝ?" "እና ታድያ ምን ልትሆኚ ነው የምታገኛት?
ሮማን በዝምታ ማሰብ ጀመረች። ለምንድን ነው ቅድስትን የምታገኛት? ራሷ ዐይታ ለማረጋገጥ? የአራት ዓመት ባሏ የተሳሳተባትን ሴት በዐይኗ ለመመልከት ልጁን ዐይታ እሺ ብትለው ኖሮና ቢወልዱ ኖሮ ምን የሚመስሉ ልጆቹን ይኖሯት እንደነበር ለመገመት? አታውቅም። ግን ልታገኛት ፈልጋለች።
"መልሺልኝ እንጂ!" ሳባ በጩኸት ጠየቀች።
"አላውቅም ሳቢ ግን ላገኛት ይገባል... ይቆርጥልኛል...." "ተይ ባክሽ ያንቺ ጅል አንጀት ምንም ቢያደርጉት አይቆርጥም. የራስሽ ጉድይ!" ሳባ ከወንበሯ ተነሳችና ወደ መታጠብያ ቤት መሄድ ጀመረች።
ከሳሎን ልትወጣ ጥቂት እርምጃ ሲቀራት ግን የበላችበት እጇን አንከርፍፋ ዞር አለችና፣
"ልጁን ይዛ ነው የምትመጣው ?" አለቻት።
"እ?"
"ልጇን ታመጣዋለቸሸ ወይ ?"
"እኔ እኮ ነው የምሄደው.... ናዝሬት ነው የምሄደው...."
"ምን....?"
"እሷ ልጅ ይዛ እዚህ ድረስ ከምትመጣ እኔ ብሄድ አይሻልም?"
"አንቺ ለይቶልሻል.... የራስሸ ጉዳይ...!"
ሳባ ምንቅርቅር እያለች ከሳሎን ወጣች።
=============
ሮማን የተቀጣጠሩበት ባለ ሰፊ የአትክልት ቦታ ሆቴል ቀድማ ደርሳ እየጠበቀች ነው። ያዘዘችውን ሚሪንዳ አሁንም አሁንም እየተጎነጨች በትግስት እየጠበቀች ነው። ለሚያያት የናፈቀችውን ፍቅረኛ እንጂ ባላንጣዋንና የባሏን ሕገ-ወጥ ልጅ የምትጠብቅ አትመስልም። ሕገ-ወጥ ልጅ - ሕገ- ወጥ ሰው አለ? ዐሥር ደቂቃ እንዳለፈ ሙሉ ቀይ ቱታ ለብሳ፣ ከእሷ እኩል ለመራመድ የሚታገል ትንሽ ልጅ እጅ ይዛ፣ ወደ ግቢው የምትገባ አጠርና ደልደል ያለች ሴት ዐየች።
ሚሪንዳዋን አንስታ ተጎነጨች። በረጅሙ ተኘፈሰች። እነሱ መሆን አለባቸው።
ሴትየዋ በረንዳው ላይ የተቀመጡ ሰዎችን ሰው በሚፈልግ ሰው ዓይነት ከቃኘች በኋላ ወደ እሷ መምጣት ጀመረች።
ሮማን በተቀመጠችበት ተንቆራጠጠች።
ሊያልቅ አንድ ጉንጭ የቀረውን ሚሪንዳዋን ተጎነጨች። ሴትየዋ ከነልጇ አጠገቧ ደረሰች።
"ይቅርታ...ሮማን ነሽ?" አለቻት ወድያው።
"አዎ...ቅድስት? " አለች ሮማን፣ ከተቀመጠችበት ተነስታ እጇን ለሰላምታ እየዘረጋች - አንዴ አጠገቧ ስትደርስ ከቅድሙ በጣም ያጠረችባትን ሴት፣ አንዴ ደግሞ ድምቡሽቡሹን ትንሽዬ ልጇን አፈራርቃ እያየች።
ቅድስት የልጅ መንቀዥቀዥ የሌለበትን ልጇን አቅፋ ቸቀመጠች። ከምንና በምን ወሬ እንጀምትጀምር ግራ የተጋባችው ሮማን፣ የሳባን ምክር ሰምታ መቅረት እንደነበረባት ማሰብ ጀመረች። ምን ልትላት ነው? ለምን ከባሌ ጋር ተኛሽ? ለምን ከእኔ ሳይወልድ ከእሱ ወለድሽ? ሞቱ እንደኔ ጎዳሽ ወይ?
"ምን ይምጣላችሁ አለች?" በዚህ ሁሉ ፋንታ።
ቅድስት ለራሷ ኮካ ኮላ፣ ለልጇ ደሞ ፋንታ አዘዘች። ሮማን ደግሞ ሌላ ሚሪንዳ ጠየቀች። እንደገና ምቾት የማይሰጥ ዝምታ ሰፈነ። አሁን ደግሞ ለብቻው ወንበር ላይ የተቀመጠው ልጅ በትልቅ ሰው ወግ በስነ- ስርአት ተቀምጦ እናቱ የምታጠጣውን ፋንታ በዝምታ፣ አንዳንዴ በፈገግታ ይጠጣል። እርጋታው ደስ ከማለት ይልቅ ምቾት ይኘሳል።
"በረታችሁ....?" አለች ቅድስት፣ እየሰፋ የመጣውን የዝምታ ክፍተት ለመሙላት በመመኘት።
"እግዜር ይመስገን...ቋሚ ምን ይሆናል... በርትተናል..." አለች ሮማን። "አንቺስ በረታሽ?" ብዬ ልጠይቃት ወይስ ዝም ልበል ፣ በሚል ሐሳብ ተይዛ። "የዲበ ነገር መቼም የሚያሳዝን ነው... እግዜር ነፍሱን ይማር..." አለች ቅድስት።
"እህ... አሜን..." ሮማን መለሰች....
"እኔ ምለው..." አለች ወዲያው መልሳ።
"አንቺ የምትይው..." ቅድስት መለሰች።
"ለቅሶ መጥተሽ ነበር እንዴ?"
ቅድስት ከብዙ ምርጫዎች ውስጥ መልሷን ለመምረጥ እንደፈለገች ሁሉ አሰበችና፤ "እንዴት አልመጣም....ቀብር መጥቼ ነበር....ቤት ግን መረበሽ ስላልፈለግኩ አልመጣሁም..." አለች።
"መረበሽ ማለት? " ሮማን ቶሎ ብላ ጠየቀች። "አይ...እንዳልነገረሽ ስለማውቅ በዚያ ሰዐት ሌላ ነገር...ጭንቀት መጨመር አልፈለግኩም...."
ሮማን በገባኝ ራሷን ነቅንቃ ዝም አለችና ወደ ልጁ ዞር ብላ ዐየችው። አሁንም በትልቅ ሰው ወግ ፈገግ አለላት።
"ዲበን ይመስላል ልበል?" አለች ሳታስበው።
"እ?" ቅድስት በድንጋጤ መለሰች።
"ልጅሽ አይኑ ጋር...ዲበን ይመስላል...."
"ነው ብለሽ ነው...? እንጃ አይመስለኝም... ሰው ሁሉ የእኔን አባት ነው ይመስላል የሚለው...."
"አይ...ዐይኑ ጋር ወደሱ የሚሄድ ነገር አለው..."
ሮማን ሳታስበው ዐይኖቿ በእንባ ተሞሉ።
"ማነው ስሙ?"
"ስሙ?"
"እ...ማነው ስሙ?"
"ዳግም..."
"ዳግም ዲበኩሉ?"
"አዎ..."
"አንቺ ነሽ ያወጣሽለት ወይስ ዲበ ነው?"
"አይ... እኔ ነኝ...."
ዳግም ወሬው እንደከበደው ሁሉ ከወንበሩ ተንሸራቶ ወረደና ወደ አትክልት ቦታው እየተደረደረ መሄድ ጀመረ። እናቱ በዐይኗ እንጂ ተነስታ አልተከተለችውም።
"ኮንዶም አልተጠቀማችሁም ነበር?" ሮማን አሁንም ሳታስበው ጠየቀች።
"ምን?" አለች ቅድስት በድንጋጤ ዐይኖቿን እየተንገዳገደ ከሚሄደው ልጅ ወደ ሮማን መልሳ...
"ማለቴ...መስከራችሁን ስምኦን ነግሮኛል...ግን ኮንደም አልተጠቀማችሁም?"
ይህንን ጥያቄ በዚህ ሰዐት ለምን እንደጠየቀች አታውቅም። ምናልባት የተሳሳተው ባሏ በስካርና በስህተት ሰዐት እንኳን የወትሮው ጠንቃቃነቱ አብሮት ነበር ብላ ለማመን ፈልጋ ይሆናል.... ምናልባት በሽታ ይዞኝ ሚስቴንንም አሲዛለሁ ብሎ ሰግቶ፣ አዝኖልኝ ይሆናል ብላ ልታምን ፈልጋ ይሆናል።
"ወይዘሮ ሮማን... ለምን ልታገኚኝ እንደፈለግሽ አልገባኝም...ግን እሺ ያልኩሽ ለዲበ ብዬ ነው... ጥሩ ሰው ነበር.... ለእሱ ብዬ...ስሞኦንንም አንቺንም አክብሬ ነው...ግን እንዲህ አይነት ጥያቄ...."
"ይቅርታ ቅድስት....."
"እ?"
"ይቅርታ.... እንዲህ አይነት ነገር መጠየቅ አልነበረብኝም....ግራ ገብቶኝ ኘው...."
ቅድስት ምንም ሳትመልስላት ብድግ ብላ ወደ ልጇ ሄደች። ሮማን በተቀመጠችበት ሆና አትክልት ስፍራው ውስጥ የውሸት ስታባርረው ፣ ሲፈነድቅ፣ እፍስፍስ አድርጋ አንስተረ ሁለመናውን ስትስመው ዐየች።
ዲበኩሉ እንውለድ ባላት ቁጥር ቆይ የቤቱ ጣራ ይመታ፣ ቆይ በርና መስኮት ይግባ ፣ ቆይ የባኞ ቤት እቃ ገብቶ ይለቅ...ሴራሚክስ ስራው እንዳለቀ አረግዝና ቤታችን እወልዳለሁ እያለች ለመሐፀኖም ፣ ለእሱም የሰጠችው የዓራት አመት ቀጠሮን እያሰበች በአንዲት ሌሊት ስህተት ዘሩን አስቀርታ የዲበን ልጅ የምትስመውን ሴት እያየች ሳታስበው አነባች።
በእናቱ እቅፍ ውስጥ የሚቦርቀው ዳግም የክህደት ምልክት መሆኑ ቀርቶ፣የዲበ ብቸኛ ማስታወሻ ሃውልት ሆኖ ታያት።
ቦታ ሳትለይ ልጇን የምትስመው አጭር ሴት ባላንጣነቷ ቀርቶ ዕድለኝነቷ ጎልቶ ታሰባት።
እንባዋን አበሰችና በረጅሙ ተነፈሰች።
በማለቅ ላይ ያለ ሁለተኛ ሚሪንዳዋን ተጎነጨች።
ቅድስትና ዳግም ተመለሱ።
"ምንድን ነው የምትሠሪው አሁን?" አለቻት ሮማን ዳግምን ትኩር ብላ እያየቻት።
"እ....ስምኦን አልነገረሽም? "
"የእናንተ 'ፊልድ ኦፊስ' እንደተዘጋና ከስራ እንደተቀነሽ ነግሮኛል....ሌላ ስራ አላገኘሽም?"
"አላገኘሁም....የማገኘው ስራ ሁሉ ሌላ አገር ነው...ማለቴ አሶሳ ምናምን አግኝቼ ነበር ግን ልጄን ትቼ አልሄድ ነገር....."
ሮማን አሁንም በገባኝ ራሷን ነቀነቀችና፣
"የዲበ ልጅ ነው...ተቆራጩን አላቋርጥብሽም...."
"እ?"
"በየወሩ ይልክልሽ የነበረውን ብር እልክልሻለዉ....ስለሱ እንዳታስቢ..."
የቅድስት ድንጋጤ ከልክ አልፎ ነበር።
"ምነው ደነገጥሽ?"
"አይ....እኔ እንዲህ ታደርጊያለሽ ብዬ አልጠበኩም ነበር...."
"ለምን....?"
"እንዴ...ማን እንዲህ ያደርጋል?"
"የዲበ ልጅ ተቸግሮ ማደግ የለበትም....በሕይወት ቢኖር እንደዛ አይሆንም....እሱ ስለሌለ...."
"እሱማ ገባኝ..."
"ለልጁ ኀላፊነት የሚሰማው ሰው እንደነበር ዐውቃለሁ..."
"በጣም...መልካም ሰው ነበር...ምንም ጎሎብኝ አያውቅም...."
"አሁንም አይጎልብሽም....መሄድ አለብኝ አሁን...ልሳመው ይሄን ጎረምሳ?"
ቅድስት ከድንጋጤዋ ሳትወጣ ራሷን በአወንታ ነቀኘቀች። ሮማን ዳግምን አንስታ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችውና ወፍራም ጉንጮቹን አፈራርቃ ሳመቻቸው። ዲበን ያቀፈች፣ ዲበን የሳመች እስኪመስላት እንባ በዐይኖቿ ሞልቶ አቀፈችው። ሳመችው።
ልጁን ለእናቱ አስረክባ ከአትክልት ስፍራው ጀርባ ወደ አቆመችው መኪናዋ መንገድ ጀመረችና ዞር ብላ፣
"የማደርሳችሁ ቦታ አለ?" አለች።
"አይ.... የለም....ሂጂ....ቅርብ ነን እኛ..." አለች ቅድስት ቃላቱን አነባብራ። መረበሽዋ በመቅለል ፈንታ ብሷል።
ሮማን መንገዷን ቀጠለች።
የሮማን መኪና ግባውን ለቅቆ ሲወጣ የምታነው ቅድስት ዳግምን ጥብቅ አድርጋ አቀፈችና ለራሷ ብቻ በሚሰማ ድምፅ እንዲህ ብላ አጉተመተመች።
"አምላኬ ሆይ....መጀመርያ ያንን ደግ ሰው....አሁን ደግሞ ይህችን መልአክ ስላታለልኩ ይቅር በለኝ....ምናባቴ ላድርግ? ልጄን ያለ ገቢ እንዴት ብዬ ለሳድግ? ይቅር በለኝ።
💫ጨርሰናል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
በእናቱ እቅፍ ውስጥ የሚቦርቀው ዳግም የክህደት ምልክት መሆኑ ቀርቶ፣የዲበ ብቸኛ ማስታወሻ ሃውልት ሆኖ ታያት።
ቦታ ሳትለይ ልጇን የምትስመው አጭር ሴት ባላንጣነቷ ቀርቶ ዕድለኝነቷ ጎልቶ ታሰባት።
እንባዋን አበሰችና በረጅሙ ተነፈሰች።
በማለቅ ላይ ያለ ሁለተኛ ሚሪንዳዋን ተጎነጨች።
ቅድስትና ዳግም ተመለሱ።
"ምንድን ነው የምትሠሪው አሁን?" አለቻት ሮማን ዳግምን ትኩር ብላ እያየቻት።
"እ....ስምኦን አልነገረሽም? "
"የእናንተ 'ፊልድ ኦፊስ' እንደተዘጋና ከስራ እንደተቀነሽ ነግሮኛል....ሌላ ስራ አላገኘሽም?"
"አላገኘሁም....የማገኘው ስራ ሁሉ ሌላ አገር ነው...ማለቴ አሶሳ ምናምን አግኝቼ ነበር ግን ልጄን ትቼ አልሄድ ነገር....."
ሮማን አሁንም በገባኝ ራሷን ነቀነቀችና፣
"የዲበ ልጅ ነው...ተቆራጩን አላቋርጥብሽም...."
"እ?"
"በየወሩ ይልክልሽ የነበረውን ብር እልክልሻለዉ....ስለሱ እንዳታስቢ..."
የቅድስት ድንጋጤ ከልክ አልፎ ነበር።
"ምነው ደነገጥሽ?"
"አይ....እኔ እንዲህ ታደርጊያለሽ ብዬ አልጠበኩም ነበር...."
"ለምን....?"
"እንዴ...ማን እንዲህ ያደርጋል?"
"የዲበ ልጅ ተቸግሮ ማደግ የለበትም....በሕይወት ቢኖር እንደዛ አይሆንም....እሱ ስለሌለ...."
"እሱማ ገባኝ..."
"ለልጁ ኀላፊነት የሚሰማው ሰው እንደነበር ዐውቃለሁ..."
"በጣም...መልካም ሰው ነበር...ምንም ጎሎብኝ አያውቅም...."
"አሁንም አይጎልብሽም....መሄድ አለብኝ አሁን...ልሳመው ይሄን ጎረምሳ?"
ቅድስት ከድንጋጤዋ ሳትወጣ ራሷን በአወንታ ነቀኘቀች። ሮማን ዳግምን አንስታ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችውና ወፍራም ጉንጮቹን አፈራርቃ ሳመቻቸው። ዲበን ያቀፈች፣ ዲበን የሳመች እስኪመስላት እንባ በዐይኖቿ ሞልቶ አቀፈችው። ሳመችው።
ልጁን ለእናቱ አስረክባ ከአትክልት ስፍራው ጀርባ ወደ አቆመችው መኪናዋ መንገድ ጀመረችና ዞር ብላ፣
"የማደርሳችሁ ቦታ አለ?" አለች።
"አይ.... የለም....ሂጂ....ቅርብ ነን እኛ..." አለች ቅድስት ቃላቱን አነባብራ። መረበሽዋ በመቅለል ፈንታ ብሷል።
ሮማን መንገዷን ቀጠለች።
የሮማን መኪና ግባውን ለቅቆ ሲወጣ የምታነው ቅድስት ዳግምን ጥብቅ አድርጋ አቀፈችና ለራሷ ብቻ በሚሰማ ድምፅ እንዲህ ብላ አጉተመተመች።
"አምላኬ ሆይ....መጀመርያ ያንን ደግ ሰው....አሁን ደግሞ ይህችን መልአክ ስላታለልኩ ይቅር በለኝ....ምናባቴ ላድርግ? ልጄን ያለ ገቢ እንዴት ብዬ ለሳድግ? ይቅር በለኝ።
💫ጨርሰናል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ብሌን 🇪🇹
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
ከሌሊቱ 10:52 አይኖቼን ስገልጥ ከክፍሌ ጨለማ ጋር ተፋጠጥኩ በዳበሳ መብራቴን አብርቼ በፍጥነት አከባቢዬን ቃኘው።አስማት ወይንም ተዓምር ሊመስል ይችላል ግን አሁን እቤቴ ነኝ።ትንፋሼ ይቆራረጣል።ከፍተኛ ሙቀት ስለተሰማኝ ከብርድልብሴ ወጣው ላብ ጥምቅ አድርጉኛል። ልቤ ክፉኛ ይመታል በፍጥነት ተነስቼ ወደ በሩ አመራው።ነብሴ ስለ ተጨነቀች እንጂ የትም ልሔድ አልነበረም።ተመልሼ አልጋዬ ጫፍ ተቀመጥኩ ቀን ማስበውንና ምፈራው ትውስታ ነው ሌሊት በህልሜ ሳይ እና ስቃዥ የማድረው።
ለሊቱ በሀይለኛ ፀጥታ ተውጧል ምንም ድምፅ የለም።ወደ መስኮቴ በቀስታ ሄጄ ከፈትኩት ሊነጋ ማቅላላት ጀምሯል ካልተሳሳትኩ ከደቂቃዎች ቡሗላ የመስጊድ አዛን መሰማት ይጀምራል።ፍፁም እርጋታ አና ፀጥታ የተሞላው ሌሊት ደስ በሚል እና ሰላምን በሚያስተጋባ ቀዝቃዛ ንፍስ ታጅቧል ። ይሄንን በነፈሰበት አብረውት እኩል በነፃነት ከሚደንሱት ዛፎች ውጪ የሚያስተውለውም ሆነ የሚያጣጥመው ግን ያለ አይመስልም። እንዳለመታደል ሆኖ ግን እኔም እንኳን እንዲ እያስተዋልኩት ልደሰትበትም ሆነ ላጣጣመው አልቻልኩም። ምክንያቱም ደግሞ ከእርጋታውና ፀጥታው ይልቅ ውስጤ ያለው ጩኸት እና ጫጫታ ይበልጡኑ ስለሚሰማኝ እና ስለሚበረታ ነው።ተመልሼ ወደ አልጋዬ አመራው ግን እንቅልፌን ፈራሁት።ቀሪዎቹን ሰዓታት ማሳለፊያ ነገር መፈለግ ሰይኖርብኝ አይቀርም።
ከሌሊቱ11:20 እንቅልፍ የሚባል ባይኔ ዝር አላለም።ሴከንዶች ደቂቃን ደቂቃዎች ሰዓታትን እየተኩ ይሄዳል። ለኔ ግን የቆመ ነው የሚመስለው ።
በማያቋርጥ ቅዠት የተሞላ ቀን እና ለሊቶችን ማሳለፍ ከጀመርኩ ሰነባበትኩ።ሰው ያላወቀውን ህመም ከታመምኩ ቆየ፣ሊነግሩት በማይቻል ሰው በማይረዳውእና ሊገለፅ በማይቻል ጥለቅ ፍርሀት ውስጥ መዋልና ማደር ከጀመርኩ ሳምንታት አልፈው ወር አስቆጠረዋል።ራሴን ማውራት ወስጤን ማድመጥ እፈራለው ሆኖም ግን ውስጤን ዝም ማሰኘት አልችልም ያለማቋረጥ ይጮሀል።ንዴት፤ቁጭትና ፀፀት፤ቂም፤ተስፋ መቁረጥ ይሁን እልህ በትኛውም ቃል በትክክል ልገልፀው ያልቻልኩት ስሜት ውስጤን አጨልሞታል።
ምናልባት አንዳንዴ ያለሁበትን እረሳለው ስለነበረውም እንደዛው አይምሮዬን ስቼ እቆይና ስመለስ ደግሞ ላመልጠው ካልቻልኩት መጥፎ ትውስታ ውስጥ ራሴን አገኘዋለው።እንደገና ያንንም ልረሳው እና ባዶ ልሆንም እችላለው።ብቻ በዚ ሁኔታ ቀናትን አሳልፍያለው ወደ ራሴ ለመመለስ የሚወስድብኝ ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ ባላውቅም ግን ይሄ ስቃዬ እንዲያበቃና ከዚ ቅዠት መውጣት እፈልጋለው።
ስሜን እንዳላስተዋውቃቹ ልረሳው ስለምችልና በውል ስለማላስታውሰው ይቆያቹ።ግን....ብሩክቲ ነኝ ይሆን እንዴ....? እንጃ።
ከሌሊተለ 11:40 የምፈልገውን አላውቀም ግን የሆነ ነግር ፈልግያለው ያጣሁትን ባላውቅም ግን አንዳች ያጣሁት ነገሮ አለ ግን አይምሮዬ ጥያቄውን ብቻ እንጂ መልሱን አይነግረኝም።
ለደቂቄዎች በወረቀት ላይ ለመፃፍ ሞኩርኩ ግን ምን ልፅፍ አልቻልኩም ከባዶ ነጭ ወረቀቴ ጋር ተፋጠጥኩ ግን የምፅፈው ነገር የለኝም ወይም የምፅፈውን አላውቅም።የነበርኩበት የት ነው አንዴትስ መጣው ማን አመጣኝ ኬትስ ነው የመጣሁት ሌሎቹስ ታድያ...??? መልስ የሚሰጠኝ የለም ግን አይምሮዬ የሚያሰማኝ ያንን ስቃይ የተሞላበትን ቅዠቴን የው።ለምንድነው በደንብ ማስታወስ ማልችለው?እንጃ ቢያምም ግን የግድ ማስታወስ እፈልጋለው ደሞም አለብኝ።
ለሊቱ ነግቶም ከክፍሌ ንቅንቅ አላልኩም አሁንም ከባዶ ወረቀቴ ጋር እይደተፋጠጥኩ ነው ምክንያቱም መመለስ አለብኝ። ስሚ....ስሚ...."ሔዋን ሔዋን "የክፍሌ በር ተንኳኳ።አው ስሜ በትክክል ሔዋን ነው ሔዋን በድሉ እናም የሚጠራኝ አባቴ ነው እቤቴ ነኝ የምማረው እና የነበርኩት ግን university ነው የ3ኛ ዓመት ህክምና ተማሪ።ግን የት? እንጃ።
"ሔዋን" አባቴ ነው "አቤት አባ ግባ"አልኩት።"ሰላም አደርሽ ልጄ" አለኝ።ጥያቄውን እንዲሁ በዘልማድ መመለስ ስላልፈለኩ ትንሽ አሰብ አድርጌ አንገቴን ነቅንቄ "አይ ሲያቃዠኝ ነው ያደረኩት"
"ያስታወሽው ነገር አለ እንዴ?"ፀጉሬን አየዳበሰ ጠየቀኝ አሁንም አሰብ አረኩና "ማስታወስ የማልፈልገው ነዋ...."አልኩት እንባ ሊተናነቀኝ እያለ.....
፡
፡
፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየታቹ እንዲሁም ማስተካከል ያለባትን ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
ከሌሊቱ 10:52 አይኖቼን ስገልጥ ከክፍሌ ጨለማ ጋር ተፋጠጥኩ በዳበሳ መብራቴን አብርቼ በፍጥነት አከባቢዬን ቃኘው።አስማት ወይንም ተዓምር ሊመስል ይችላል ግን አሁን እቤቴ ነኝ።ትንፋሼ ይቆራረጣል።ከፍተኛ ሙቀት ስለተሰማኝ ከብርድልብሴ ወጣው ላብ ጥምቅ አድርጉኛል። ልቤ ክፉኛ ይመታል በፍጥነት ተነስቼ ወደ በሩ አመራው።ነብሴ ስለ ተጨነቀች እንጂ የትም ልሔድ አልነበረም።ተመልሼ አልጋዬ ጫፍ ተቀመጥኩ ቀን ማስበውንና ምፈራው ትውስታ ነው ሌሊት በህልሜ ሳይ እና ስቃዥ የማድረው።
ለሊቱ በሀይለኛ ፀጥታ ተውጧል ምንም ድምፅ የለም።ወደ መስኮቴ በቀስታ ሄጄ ከፈትኩት ሊነጋ ማቅላላት ጀምሯል ካልተሳሳትኩ ከደቂቃዎች ቡሗላ የመስጊድ አዛን መሰማት ይጀምራል።ፍፁም እርጋታ አና ፀጥታ የተሞላው ሌሊት ደስ በሚል እና ሰላምን በሚያስተጋባ ቀዝቃዛ ንፍስ ታጅቧል ። ይሄንን በነፈሰበት አብረውት እኩል በነፃነት ከሚደንሱት ዛፎች ውጪ የሚያስተውለውም ሆነ የሚያጣጥመው ግን ያለ አይመስልም። እንዳለመታደል ሆኖ ግን እኔም እንኳን እንዲ እያስተዋልኩት ልደሰትበትም ሆነ ላጣጣመው አልቻልኩም። ምክንያቱም ደግሞ ከእርጋታውና ፀጥታው ይልቅ ውስጤ ያለው ጩኸት እና ጫጫታ ይበልጡኑ ስለሚሰማኝ እና ስለሚበረታ ነው።ተመልሼ ወደ አልጋዬ አመራው ግን እንቅልፌን ፈራሁት።ቀሪዎቹን ሰዓታት ማሳለፊያ ነገር መፈለግ ሰይኖርብኝ አይቀርም።
ከሌሊቱ11:20 እንቅልፍ የሚባል ባይኔ ዝር አላለም።ሴከንዶች ደቂቃን ደቂቃዎች ሰዓታትን እየተኩ ይሄዳል። ለኔ ግን የቆመ ነው የሚመስለው ።
በማያቋርጥ ቅዠት የተሞላ ቀን እና ለሊቶችን ማሳለፍ ከጀመርኩ ሰነባበትኩ።ሰው ያላወቀውን ህመም ከታመምኩ ቆየ፣ሊነግሩት በማይቻል ሰው በማይረዳውእና ሊገለፅ በማይቻል ጥለቅ ፍርሀት ውስጥ መዋልና ማደር ከጀመርኩ ሳምንታት አልፈው ወር አስቆጠረዋል።ራሴን ማውራት ወስጤን ማድመጥ እፈራለው ሆኖም ግን ውስጤን ዝም ማሰኘት አልችልም ያለማቋረጥ ይጮሀል።ንዴት፤ቁጭትና ፀፀት፤ቂም፤ተስፋ መቁረጥ ይሁን እልህ በትኛውም ቃል በትክክል ልገልፀው ያልቻልኩት ስሜት ውስጤን አጨልሞታል።
ምናልባት አንዳንዴ ያለሁበትን እረሳለው ስለነበረውም እንደዛው አይምሮዬን ስቼ እቆይና ስመለስ ደግሞ ላመልጠው ካልቻልኩት መጥፎ ትውስታ ውስጥ ራሴን አገኘዋለው።እንደገና ያንንም ልረሳው እና ባዶ ልሆንም እችላለው።ብቻ በዚ ሁኔታ ቀናትን አሳልፍያለው ወደ ራሴ ለመመለስ የሚወስድብኝ ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ ባላውቅም ግን ይሄ ስቃዬ እንዲያበቃና ከዚ ቅዠት መውጣት እፈልጋለው።
ስሜን እንዳላስተዋውቃቹ ልረሳው ስለምችልና በውል ስለማላስታውሰው ይቆያቹ።ግን....ብሩክቲ ነኝ ይሆን እንዴ....? እንጃ።
ከሌሊተለ 11:40 የምፈልገውን አላውቀም ግን የሆነ ነግር ፈልግያለው ያጣሁትን ባላውቅም ግን አንዳች ያጣሁት ነገሮ አለ ግን አይምሮዬ ጥያቄውን ብቻ እንጂ መልሱን አይነግረኝም።
ለደቂቄዎች በወረቀት ላይ ለመፃፍ ሞኩርኩ ግን ምን ልፅፍ አልቻልኩም ከባዶ ነጭ ወረቀቴ ጋር ተፋጠጥኩ ግን የምፅፈው ነገር የለኝም ወይም የምፅፈውን አላውቅም።የነበርኩበት የት ነው አንዴትስ መጣው ማን አመጣኝ ኬትስ ነው የመጣሁት ሌሎቹስ ታድያ...??? መልስ የሚሰጠኝ የለም ግን አይምሮዬ የሚያሰማኝ ያንን ስቃይ የተሞላበትን ቅዠቴን የው።ለምንድነው በደንብ ማስታወስ ማልችለው?እንጃ ቢያምም ግን የግድ ማስታወስ እፈልጋለው ደሞም አለብኝ።
ለሊቱ ነግቶም ከክፍሌ ንቅንቅ አላልኩም አሁንም ከባዶ ወረቀቴ ጋር እይደተፋጠጥኩ ነው ምክንያቱም መመለስ አለብኝ። ስሚ....ስሚ...."ሔዋን ሔዋን "የክፍሌ በር ተንኳኳ።አው ስሜ በትክክል ሔዋን ነው ሔዋን በድሉ እናም የሚጠራኝ አባቴ ነው እቤቴ ነኝ የምማረው እና የነበርኩት ግን university ነው የ3ኛ ዓመት ህክምና ተማሪ።ግን የት? እንጃ።
"ሔዋን" አባቴ ነው "አቤት አባ ግባ"አልኩት።"ሰላም አደርሽ ልጄ" አለኝ።ጥያቄውን እንዲሁ በዘልማድ መመለስ ስላልፈለኩ ትንሽ አሰብ አድርጌ አንገቴን ነቅንቄ "አይ ሲያቃዠኝ ነው ያደረኩት"
"ያስታወሽው ነገር አለ እንዴ?"ፀጉሬን አየዳበሰ ጠየቀኝ አሁንም አሰብ አረኩና "ማስታወስ የማልፈልገው ነዋ...."አልኩት እንባ ሊተናነቀኝ እያለ.....
፡
፡
፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየታቹ እንዲሁም ማስተካከል ያለባትን ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
👍2
#ብሌን 🇪🇹
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
"አይዞሽ የኔ ውድ ማድረግ የምትፈልጊው ነገር አለ? ለምሳሌ መውጣት ወይም ሌላ ነገር...?"
እንዲያው ለአመል ይጠይቀኝ እንጂ ባለፉት ቀናት ብዙ ነገር አንዳላደርግ ሲከለክለኝና ሲደብቀኝ እንደነበር አስተውያለው ለምሳሌ ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንዲሁም ሞባይል ኢንተርኔት አንዳላይ አድርጎኛል።ከቤት መውጣቱንም ቢሆን አብሮኝ ካልሆነ አያስወጣኝም።ለኔ ተጠንቅቆ እንደሆነ ቢገባኝ ግን ማወቅ እና ማየትን እፈለጋለው ከቤት መውጣትንም እንደዛው።ግን አባቴ ስጋት ያለበት ይመስላል ደግሞም ይገባዋል ምክንያቱም ለሱ ብቸኛ ልጁ ነኝ ሊያውም ካለናት ያሳደገኝ።ያ ማለት ግን ከናቴ ጋር ተጣልተዋል አልያም ሞታለች ማለት አይደለም ሚስጥሩ ሌላ ነው።ለጊዜው ግን እኔና አባቴ ከአንድ ሰራተኛችን ጋር ነው የምንኖረው።ሰራተኛ ለማለት ግን ይከብዳል እህና አብሮ አደጌ ብላት ይሻላል። ብርቱካን ትባላለች የዋህ እና ንፁ ኢትየጵያዊ ምርጥ እናትና ጠሩ እህት ነች በቃ ከዚ ሌላ መግለጫ የለኝም።
አባቴ ላቀረበልኝ ጥያቄ መልስ"ከስራ ልትቀር...?"አልኩት በዘዴ "አንቺ ከፈለግሽ ካንቺ አይበልጥም"አለኝ
"አይ ብቻዬን ነው መውጣት የምፈለገው ካለሆነ ይቅር"አልኩ።አባቴ በረጅሙ ተንፍሶ"በርግጥ አሁን ይበልጥ ትሻያለሽ ደና ነሽ ግን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወደራስሽ እስክትመለሽና የቅርብ ጊዜ ትውስታሽ እስኪመለስ መጠበቅ አለብሽ ካልሆነ ግን ትንሽ ከደገኛ አይመስለሽም ሔዊ?" መልሶ በጥያቄ መለስልኝ።
"አይ አይመስለኝ እንድረጋጋና ነገሮችን አንዳስታውስ ከፈለክ ነፃ ብታደርገኝ የሚሻል ነው የሚመስለኝ"። እንደማቅማማት አለና "እሺ ወደ ሳሎን ነይና ቁርስ እንብላ"አለኝ እንደ እሽታ ቆጥሬ"አባዬ ስለተረዳኸኝ አመሰግናለው "አቅፌ ሳምኩት።ግን የአባቴን ጥንቃቄ አይታችሁልኛል ምን እንዳስታወስኩ እንኳን ጠይቆ ሊያስታውሰኝ አልፈለገም ምክንያቱም ማስታወስ እንደማልፈልግ ነግሬዋለዋ።
ለወትሮው አባቴ እስካለና እቅፍ ውስጥ ስሆን ፈርቼ አላውቅም በአባቴ መሉ እምነት ና መተማመን ነበረኝ።ልክ በአምላኬ እቅፍ ውስጥ ያለው ያህል ደህንነትና ሰላም ይሰመኝ ነበር።ግን በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባቴ እቅፍ ወደማያስጥለኝ ወደማያድነኝ አስፈሪ ገፅታ ወዳለውእና ማለቂያ የሌለው የሚመስል ስቃይ ውስጥ ራሴን ካገኘው ቡሗላ ግን ፍፁም ቀድሞ የነበረኝ ሰላምን ሊሰጠኝም ሆነ እምነት ሊኖረኝና ፍራቻን ሊያስወግድልኝ አልቻለም።
ሳሎን ስንደርስ ቀርስ ቀርቦ ግሩም ቃና ባለው ሻይ ሽታ ታውዶ ነበር።"ደና ደርሽ ሔዊ"አለች ቡርቴ በዝግታ ሔጄ ሳምኳትና"ሽታው በጣም አያስራበኝ ነው ባለሞያ እኮ ነሽ!"አልኳት።"አሱን በደንብ ስትበዪ ነው ማምንሽ በደንብ አትቢና ግን ወይልሽ!"አለች የውሽት ቁጣ እየተቆጣች።
"እሺ እናመስግን"አለ አባዬ ፊቱ ላይ አንዳች ስሜት እየተነበበ እንደተረበሸ ያስታውቃል።
በፊተት ከምወደውና ደንነት እንዲሰማኝ ከሚያደርገኝ ሌላው ነገር የአባቴ ፀሎት ነው ልጅ እያለው እንደሱ ለመፀለይ አለማመድና አንደ አባታችን ፀሎት አደጋግመው ነበር።የሚፀልይበትን እረጋታ እና ድምፅ አወደዋለው በአይምሮዬ ጥሩ ዜማ እንዳለው ተወዳጅ ሙዚቃ ተቀርጿል።"አሜን"ስል የእውነትም አባቴ በሚለው ነገር በአምላኬ ተሰሚነትን አንደማገኝ ወስጤ እረግጠኛ ሆንና አምኜ ነው።እና ይሄንን የአባቴን ፀሎት አድጌም አልጠጎበውም።ደስ ይለኛል ምግብ ላይም ይሁን በምንም አጋጣሚ ሲፀልይ ሰላም ወስጤን ይሞላዋል ከእግዚአብሄር ጋር የምገናኝ የማወራው እና እሚመልስለኝ ነው የሚመስለኝ።
ይሄንን ሁሉ የምላቹ አባቴ ለቁርስ እየፀለየ ነው እኔና ቡርቴ በአሜንታ እየተከተልነው አመስግነን ጨረስን።
ቁርስ በልተን እስክንጨርስና አባዬ ወደ ስራ እስኪካሄድ መጠበቅ በጣም ረዝሞብኝ ነው ቢሆንም ጠበኩ።አባዬ በቅራኔ እንደተሞላ ለመውጣት ሲወጋጅ ድንገት የት እንደምሄድ ጠየቀኝ የት ነው የምሄደው...?
"ገበያ..."አልኩት ዝም ብዬ
ገበያ....??" አለኝ በጥያቄ አይን አያየኝ
" አው አታስብ ቡርቴ የምትገዛው እቃ ስላለ ከሷ ጋር ነው የምሄደው" አልኩት አፌ ላይ አንደመጣልኝ።
"እሺ እንደዛ ከሆነ ገንዘብ ያስፈለግሻል"ከዋሌቱ የተወሰኑ መቶ ብሮችን እያወጣ "ምንያህል ያስፈለግሻል?
"አይ አትቸገር ብዙም አይደል"እንደዛ ከሆነ ካፌ ነገር ብትገቡ ወይም ደስ ያላችሁን ብታደርጉ ጥሩ ነው ብቻ ሚያዝናናቹን" ሰጠኝ።
"ይሄ ደሞ ላንቺ ነው"ለቡርቴ እያቀበላት ገና ከጓዳ እየወጣች ነበር"ለምን....?"አለች ከመጀመሪያው ስላልሰማች"ገበያ ልንሄድ አይደል...!"አልኳት ካፏ ነጥቄ።
"በሉ እሺ ልጆች መልካም ቀን ታዲያ እየተጠነቀቃቹ"ብሎ ስሞን ወጣ ከቡርቴ ጋር መወጣቴ እንዳስደሰተው አና ምን ያህል እንደቀለለው ሳይ ደስ አለኝ።አባቴ አንዲ ነው ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ፍቅር መስጠት እና ሰውን መውደድ አይሰስትም አያልቅበትምም።ብዙዎች ሀብታሙ ፓስተር ይሉታል።በርግጥ የራሱ ስራ ያለውና ደሞዝተኛ ነው።ከዛ ውጪ ትጉህ አገልጋይ እና ታታሪ ሰራተኛ ነው።ብዙ ጊዜ በአንድ ቤተ/ያን መገደብ ስለማይወድና ከሁሉም ጋር ህብረት ስለሚያደርግ በዚ ሰዎች ይተቹታል ሆኖም አባቴን ግድ ሰቶት አያውቅም ምክንያቱም ሲበዛ በአንድነት የሚያምንና ልዮነትና ክፍፍል የሚባል ነገር ስለማይወድ ነው።በቤተ/ያን ብቻ አይደለም አባቴ ሲበዛ በኢትዮጵያዊነት አንድነት የሚያምን ነው።ለማንም ሰው ስለብሔሩም ሆነ ስለዘሩ ሲናገር አትሰሙትም።የማይታመን ይሆናል ግን ለኔ እንኳን "እንትን ዘር ነኝ ስለዚ አንቺም እንደዚ ነሽ "ብሎኝ አያውቅም ለዛ እኔም ስለብሔሬም ሆነ ስለዘር ግድ ሰቶኝ አያውቅም።ከአባቴ የተማርኩት ምንም ትርጉምም ሆነ ጥቅም የሌለው ነገር መሆኑን ነው።ግን አባቴ ስለሁሉም ሰው ቢጠየቅ መልሱ "ኢትየጵያዊ ብቻ" የሚል ነው የሚሆነው።እኔም ስለነዚ ነገሮች ለማወቅ ጉቱም ፍላጎቱም አድሮብኝ አያውቅም ደሞም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያስብ የሚገባወና ሊይዘው የሚገባው አመለካከት ነው።ግን እንዴትና ለምን አንደሆነ ባይገባኝ በምማርበት ግቢ በአንድ ብሔር ተሰይሜ እና ተወክዬ ስቀጣ ነበር።ግን እነማን ነበሩ...? በምንስ ወከሉኝ...? መልስ ያላገኘሁለት ጥያቄ ነው።እነማንን መጠንቀቅ ይኑርብኝ እነማንን ማመን ይኑርብኝ እንኳ አላውቅም
በዚ ምክንያት ነው እስካሁን በፍርሀት እንድኖር የተገደድኩት።
አባቴ እንደወጣ ምን እንደማደርግ ቀድሜ እያቀድኩ ክፍሌ ገባውና ቀለል ያለ አለባበስ ለብሼ በፍጥነት ወደ ቡርቴ ሄድኩ
"ጨርሻለው!" አልኳት
ዞራ በአግራሞት ከላይ እስከ ታች አየችኝ።እኔም ግራ ገብቶኝ እንደገና አለባበሴን አየሁት ጅንስ ሱሪ፣ፓካወት እና ሸሚዝ ብዙ ጊዜ የማዘወትረውን እና ሚመቸኝን አለባበስ ነው የለበስኩት።
"ያጠፋሁት ነገር አለ? አለባበሴ ምን ሆነብሽ?"አልኳት
"አይ...ቶሎ..ጨረሽ ብዬ ነው"
"ልጅት ምን ሆነሻል ልብስ ስለብስ ጊዜ ፈጅቶብኝ አያወቅም ሁሌም እንዲ ነበርኩ"አልኳት ፊቷ ላይ የማየውን ስሜት ለመረዳት በጥንቃቄ እያየሗት።
"አይ ሔዊ ግን እኮ እንደዚ መልበስ ካቆምሽ ቆይተሻል"አለች።አሁን ገባኝ በራፍ ላይ እንደቆምኩ ለሴኮንዶች እያሰብኩ አፈጠጥኩባት እና ተጠግቻት
"ቢያንስ ለምን ያሀል ጊዜ..?"ጠየኳት።
"እንጃ 1...3 ዓመት እና ከዛ በላይ ይሆናል"
"እሺ ቡርቴ አንዳስታውስ እንድትረጂኝ እፈለጋለው አትረጂኝም...?"እጆቿን የዤ ጠየኳት።"
ሔዊዬ አንቺ አስታውሽና ደና ሁኝልኝ እንጂ ለምን ብዬ ነው ማልረዳሽ"
"ምንም ነገር ቢሆን የጠየኩሽን ታደርጊያለሽ?"
"ደስ ያለሽን" "ግን አባዬ ሳያውቅ ነው"
"ማለት..? ግን ለምን
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
"አይዞሽ የኔ ውድ ማድረግ የምትፈልጊው ነገር አለ? ለምሳሌ መውጣት ወይም ሌላ ነገር...?"
እንዲያው ለአመል ይጠይቀኝ እንጂ ባለፉት ቀናት ብዙ ነገር አንዳላደርግ ሲከለክለኝና ሲደብቀኝ እንደነበር አስተውያለው ለምሳሌ ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንዲሁም ሞባይል ኢንተርኔት አንዳላይ አድርጎኛል።ከቤት መውጣቱንም ቢሆን አብሮኝ ካልሆነ አያስወጣኝም።ለኔ ተጠንቅቆ እንደሆነ ቢገባኝ ግን ማወቅ እና ማየትን እፈለጋለው ከቤት መውጣትንም እንደዛው።ግን አባቴ ስጋት ያለበት ይመስላል ደግሞም ይገባዋል ምክንያቱም ለሱ ብቸኛ ልጁ ነኝ ሊያውም ካለናት ያሳደገኝ።ያ ማለት ግን ከናቴ ጋር ተጣልተዋል አልያም ሞታለች ማለት አይደለም ሚስጥሩ ሌላ ነው።ለጊዜው ግን እኔና አባቴ ከአንድ ሰራተኛችን ጋር ነው የምንኖረው።ሰራተኛ ለማለት ግን ይከብዳል እህና አብሮ አደጌ ብላት ይሻላል። ብርቱካን ትባላለች የዋህ እና ንፁ ኢትየጵያዊ ምርጥ እናትና ጠሩ እህት ነች በቃ ከዚ ሌላ መግለጫ የለኝም።
አባቴ ላቀረበልኝ ጥያቄ መልስ"ከስራ ልትቀር...?"አልኩት በዘዴ "አንቺ ከፈለግሽ ካንቺ አይበልጥም"አለኝ
"አይ ብቻዬን ነው መውጣት የምፈለገው ካለሆነ ይቅር"አልኩ።አባቴ በረጅሙ ተንፍሶ"በርግጥ አሁን ይበልጥ ትሻያለሽ ደና ነሽ ግን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወደራስሽ እስክትመለሽና የቅርብ ጊዜ ትውስታሽ እስኪመለስ መጠበቅ አለብሽ ካልሆነ ግን ትንሽ ከደገኛ አይመስለሽም ሔዊ?" መልሶ በጥያቄ መለስልኝ።
"አይ አይመስለኝ እንድረጋጋና ነገሮችን አንዳስታውስ ከፈለክ ነፃ ብታደርገኝ የሚሻል ነው የሚመስለኝ"። እንደማቅማማት አለና "እሺ ወደ ሳሎን ነይና ቁርስ እንብላ"አለኝ እንደ እሽታ ቆጥሬ"አባዬ ስለተረዳኸኝ አመሰግናለው "አቅፌ ሳምኩት።ግን የአባቴን ጥንቃቄ አይታችሁልኛል ምን እንዳስታወስኩ እንኳን ጠይቆ ሊያስታውሰኝ አልፈለገም ምክንያቱም ማስታወስ እንደማልፈልግ ነግሬዋለዋ።
ለወትሮው አባቴ እስካለና እቅፍ ውስጥ ስሆን ፈርቼ አላውቅም በአባቴ መሉ እምነት ና መተማመን ነበረኝ።ልክ በአምላኬ እቅፍ ውስጥ ያለው ያህል ደህንነትና ሰላም ይሰመኝ ነበር።ግን በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባቴ እቅፍ ወደማያስጥለኝ ወደማያድነኝ አስፈሪ ገፅታ ወዳለውእና ማለቂያ የሌለው የሚመስል ስቃይ ውስጥ ራሴን ካገኘው ቡሗላ ግን ፍፁም ቀድሞ የነበረኝ ሰላምን ሊሰጠኝም ሆነ እምነት ሊኖረኝና ፍራቻን ሊያስወግድልኝ አልቻለም።
ሳሎን ስንደርስ ቀርስ ቀርቦ ግሩም ቃና ባለው ሻይ ሽታ ታውዶ ነበር።"ደና ደርሽ ሔዊ"አለች ቡርቴ በዝግታ ሔጄ ሳምኳትና"ሽታው በጣም አያስራበኝ ነው ባለሞያ እኮ ነሽ!"አልኳት።"አሱን በደንብ ስትበዪ ነው ማምንሽ በደንብ አትቢና ግን ወይልሽ!"አለች የውሽት ቁጣ እየተቆጣች።
"እሺ እናመስግን"አለ አባዬ ፊቱ ላይ አንዳች ስሜት እየተነበበ እንደተረበሸ ያስታውቃል።
በፊተት ከምወደውና ደንነት እንዲሰማኝ ከሚያደርገኝ ሌላው ነገር የአባቴ ፀሎት ነው ልጅ እያለው እንደሱ ለመፀለይ አለማመድና አንደ አባታችን ፀሎት አደጋግመው ነበር።የሚፀልይበትን እረጋታ እና ድምፅ አወደዋለው በአይምሮዬ ጥሩ ዜማ እንዳለው ተወዳጅ ሙዚቃ ተቀርጿል።"አሜን"ስል የእውነትም አባቴ በሚለው ነገር በአምላኬ ተሰሚነትን አንደማገኝ ወስጤ እረግጠኛ ሆንና አምኜ ነው።እና ይሄንን የአባቴን ፀሎት አድጌም አልጠጎበውም።ደስ ይለኛል ምግብ ላይም ይሁን በምንም አጋጣሚ ሲፀልይ ሰላም ወስጤን ይሞላዋል ከእግዚአብሄር ጋር የምገናኝ የማወራው እና እሚመልስለኝ ነው የሚመስለኝ።
ይሄንን ሁሉ የምላቹ አባቴ ለቁርስ እየፀለየ ነው እኔና ቡርቴ በአሜንታ እየተከተልነው አመስግነን ጨረስን።
ቁርስ በልተን እስክንጨርስና አባዬ ወደ ስራ እስኪካሄድ መጠበቅ በጣም ረዝሞብኝ ነው ቢሆንም ጠበኩ።አባዬ በቅራኔ እንደተሞላ ለመውጣት ሲወጋጅ ድንገት የት እንደምሄድ ጠየቀኝ የት ነው የምሄደው...?
"ገበያ..."አልኩት ዝም ብዬ
ገበያ....??" አለኝ በጥያቄ አይን አያየኝ
" አው አታስብ ቡርቴ የምትገዛው እቃ ስላለ ከሷ ጋር ነው የምሄደው" አልኩት አፌ ላይ አንደመጣልኝ።
"እሺ እንደዛ ከሆነ ገንዘብ ያስፈለግሻል"ከዋሌቱ የተወሰኑ መቶ ብሮችን እያወጣ "ምንያህል ያስፈለግሻል?
"አይ አትቸገር ብዙም አይደል"እንደዛ ከሆነ ካፌ ነገር ብትገቡ ወይም ደስ ያላችሁን ብታደርጉ ጥሩ ነው ብቻ ሚያዝናናቹን" ሰጠኝ።
"ይሄ ደሞ ላንቺ ነው"ለቡርቴ እያቀበላት ገና ከጓዳ እየወጣች ነበር"ለምን....?"አለች ከመጀመሪያው ስላልሰማች"ገበያ ልንሄድ አይደል...!"አልኳት ካፏ ነጥቄ።
"በሉ እሺ ልጆች መልካም ቀን ታዲያ እየተጠነቀቃቹ"ብሎ ስሞን ወጣ ከቡርቴ ጋር መወጣቴ እንዳስደሰተው አና ምን ያህል እንደቀለለው ሳይ ደስ አለኝ።አባቴ አንዲ ነው ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ፍቅር መስጠት እና ሰውን መውደድ አይሰስትም አያልቅበትምም።ብዙዎች ሀብታሙ ፓስተር ይሉታል።በርግጥ የራሱ ስራ ያለውና ደሞዝተኛ ነው።ከዛ ውጪ ትጉህ አገልጋይ እና ታታሪ ሰራተኛ ነው።ብዙ ጊዜ በአንድ ቤተ/ያን መገደብ ስለማይወድና ከሁሉም ጋር ህብረት ስለሚያደርግ በዚ ሰዎች ይተቹታል ሆኖም አባቴን ግድ ሰቶት አያውቅም ምክንያቱም ሲበዛ በአንድነት የሚያምንና ልዮነትና ክፍፍል የሚባል ነገር ስለማይወድ ነው።በቤተ/ያን ብቻ አይደለም አባቴ ሲበዛ በኢትዮጵያዊነት አንድነት የሚያምን ነው።ለማንም ሰው ስለብሔሩም ሆነ ስለዘሩ ሲናገር አትሰሙትም።የማይታመን ይሆናል ግን ለኔ እንኳን "እንትን ዘር ነኝ ስለዚ አንቺም እንደዚ ነሽ "ብሎኝ አያውቅም ለዛ እኔም ስለብሔሬም ሆነ ስለዘር ግድ ሰቶኝ አያውቅም።ከአባቴ የተማርኩት ምንም ትርጉምም ሆነ ጥቅም የሌለው ነገር መሆኑን ነው።ግን አባቴ ስለሁሉም ሰው ቢጠየቅ መልሱ "ኢትየጵያዊ ብቻ" የሚል ነው የሚሆነው።እኔም ስለነዚ ነገሮች ለማወቅ ጉቱም ፍላጎቱም አድሮብኝ አያውቅም ደሞም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያስብ የሚገባወና ሊይዘው የሚገባው አመለካከት ነው።ግን እንዴትና ለምን አንደሆነ ባይገባኝ በምማርበት ግቢ በአንድ ብሔር ተሰይሜ እና ተወክዬ ስቀጣ ነበር።ግን እነማን ነበሩ...? በምንስ ወከሉኝ...? መልስ ያላገኘሁለት ጥያቄ ነው።እነማንን መጠንቀቅ ይኑርብኝ እነማንን ማመን ይኑርብኝ እንኳ አላውቅም
በዚ ምክንያት ነው እስካሁን በፍርሀት እንድኖር የተገደድኩት።
አባቴ እንደወጣ ምን እንደማደርግ ቀድሜ እያቀድኩ ክፍሌ ገባውና ቀለል ያለ አለባበስ ለብሼ በፍጥነት ወደ ቡርቴ ሄድኩ
"ጨርሻለው!" አልኳት
ዞራ በአግራሞት ከላይ እስከ ታች አየችኝ።እኔም ግራ ገብቶኝ እንደገና አለባበሴን አየሁት ጅንስ ሱሪ፣ፓካወት እና ሸሚዝ ብዙ ጊዜ የማዘወትረውን እና ሚመቸኝን አለባበስ ነው የለበስኩት።
"ያጠፋሁት ነገር አለ? አለባበሴ ምን ሆነብሽ?"አልኳት
"አይ...ቶሎ..ጨረሽ ብዬ ነው"
"ልጅት ምን ሆነሻል ልብስ ስለብስ ጊዜ ፈጅቶብኝ አያወቅም ሁሌም እንዲ ነበርኩ"አልኳት ፊቷ ላይ የማየውን ስሜት ለመረዳት በጥንቃቄ እያየሗት።
"አይ ሔዊ ግን እኮ እንደዚ መልበስ ካቆምሽ ቆይተሻል"አለች።አሁን ገባኝ በራፍ ላይ እንደቆምኩ ለሴኮንዶች እያሰብኩ አፈጠጥኩባት እና ተጠግቻት
"ቢያንስ ለምን ያሀል ጊዜ..?"ጠየኳት።
"እንጃ 1...3 ዓመት እና ከዛ በላይ ይሆናል"
"እሺ ቡርቴ አንዳስታውስ እንድትረጂኝ እፈለጋለው አትረጂኝም...?"እጆቿን የዤ ጠየኳት።"
ሔዊዬ አንቺ አስታውሽና ደና ሁኝልኝ እንጂ ለምን ብዬ ነው ማልረዳሽ"
"ምንም ነገር ቢሆን የጠየኩሽን ታደርጊያለሽ?"
"ደስ ያለሽን" "ግን አባዬ ሳያውቅ ነው"
"ማለት..? ግን ለምን
👍5❤1
.?"አለች ፊቷን አኮሳትራ
"አይዞሽ መጥፎ ነገር አይደለም"ተያይዘን ወጣን።
ጠዋቱ ደመናማና ቀዝቃዛ ነው።በግምት 3 ሰዓት ይሆናል የነጌሌ ገበያ በብዛት ከዚን ሰዓት ቡሗላ ነው የሚደራው።
ነገሌ ቦረና ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 600 ኬ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኝና በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ስር ከሚተዳደሩ ከተሞች አንዷ ስትሆን በአሁኑ ወቅት የጉጂ ዞን ዋና ከተማም ነች።ከዛ በተረፈ ግን የትንሿ ኢትዮጵያ ምሳሌ ነች ኬትኛውም ብሔረሰብ የመጡ ሰዎች በእኩል አና በአንድነት የሚኖሩባት ሁሉንም በአንድ አቅፋ የያዘች ከተማ ናት።
በአባ ገዳ ስረዓት ከሚተተዳደሩትም ውስጥ አንዷ ነች በከተማዋ ውስጥ ከሚገኙ ሀውልቶችም ትለቁና የሚታወቀውም የአባ ገዳ አባት ሀውልት ነው።
የከተማዋ አየር ሞቃት የሚባል አይነት ሲሆን ብዙ ነገራ ከአዳማ ናዝሬት ጋር አንደሚያመሳስላትም ይነገርላታል።በአመት ሁለት ጊዜ ዝናብ ምታገኝ ቢሆንም ግን በነዚ የፀደይ ወቅት ላይ አልፎ አልፎ ደመናና ወቀቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊያገኛት ይችላል።
በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎችም በእርሻ ስራና በንግድ ስራ የተሰማሩ ሲሆን በከብት ቀንድ ሀብትም የታደለች ናት።ሱማሌ ጠረፍ እና ድንበር መሆና ደሞ በመጠኑ ለንግድ ስራ አመቺ አድርጓታል።
ለማንኛውም ተወለጄ ያደኩት እዚው ትንሿ ኢትዮጵያ ነገሌ ቦረና
ውስጥ ነው።
የጠዋቱን አየር አያጣጣምን ከቡርቴ ጋር መንገድ እንደጀመርን
"ቡርቴ...?" አልኳት ጠይቂኝ ባለችው መሰረት ጥያቄን መርጬ
"ለምንድነው እዚ ያለሁት ከት/ት አንዴትና ለምን መቼ መጣው?"
"ይሄንን እኮ ሁለት ቀን በፊት ጠይቀሽኝ ነግሬሻለው በርግጥ ዶክተሩ አንዲ ሊሆን እንደሚችል ነግሮን ነበር። ይኸውልሽ አሁን ሀገሩ ላይ ያለው
ሁኔታ በተለይም በዮንቨርሲቲዎች አከባቢ ግጭትና አለመረጋጋት ስላለ አብዛኛውን ተማሪ ወደ ቤቱ ተመልሶ ቁጭ ብሏል።እና አንቺም እንደምትመጪ ነገርሽን አና ግን መጣለው ባልሽበት ቀን አልመጣሽም ከዛ ቡሗላ ብንጠብቅም አልመጣሽም ነበር በስለክሽም ልናገኝሽ አልቻልንም ጓደኞችሽ እዛ እንደሌለሽ ነበር የነገሩን።ግን መጣለው ካልሽበት ከአንድ ሁለት ሳምንት ና ከዛበላይ ከቆየሽ ቡሗላ ነው የመጣሽው አና ምንም አታስታውሺም ነበር እንደዚ ሆነሽና ታመሽም ነበር"
"ማን አመጣኝ ታዲያ...?"
"እንጃ ጋሼ ነው ይዘውሽ ወደቤት የመጡት ስለክም ልብስም አልያሽም ነበር እና አንድ የማናውቀው ሰው ይመስለኛል እስከዚ ያመጣሽ እና ጋሼም በሰው በሰው መሰለኝ ያገኘሽ በደንብ አልነገረኝ።"
"ኬት ነበር የመጣሁት??" "እንጃ ብንጠይቅም መልስ ስላጣን ዶክተር ጋር ነበር የወሰድንሽ እናም ለማገገም ጊዜ እንደሚያስፈለግሽ ተረዳን።" "ዶ/ሩ ምን አለ..?"
"ጭንቀትና የአይምሮ መታወክ ነው ብሎ ነው የገመተው ግን እሱን ማረጋገጥ ሚቻለው አንቺን ጠይቆ ስትመልሺ ብቻ ነው ሆኖም ለጊዜው መጨናነቅና መረበሽ ስለሌብሽ ጋሼም ሆነ ዶ/ሩ ማንኛቸውም እንዳይጠይቁሽ ሆኗል"
"የት እንደነበር ወይም ምን ሆኜ አንደነበር ትንሽም አንኳን ምንም አታውቁም...?" በአሉታ አንገቷን ነቀነቀችልኝ።
"አይ አይመስለኝም ይሄማኮ ግልፅና ለመገመት እንኳን በጣም ቀላል ነው ቡርቴ !!!"እንደመጮኽ አልኩባትና ትቻት ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ።አባቴ በትክክልም የሆንኩትን ያውቃል እኔን መጣለት ሰውንም በትክክል። ለዛ ነው ምን አስታወሽ ብሎ እንኳን ያልጠየቀኝ መስማት ስለሚፈራ ወይም ስላልፈለገ ነው።ዜናስ እንዳልሰማ የተደረኩበት ምክንያትስ..?የአባቴ ስጋትና ጥንቃቄስ...?ምናልባት እንዳላስታወስ ተፈልጎና ሆን ተብሎ ቢሆን....?
ሁለቱይ ሳምንት የት ነበርኩ...?ማስታወስ አለመቻሌ ንዴት እየጫሰብኝ የመጣ መሰለኝ..
፡
፡
፡
💫 ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንዲሁም ማስተካከል ያለባት ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
"አይዞሽ መጥፎ ነገር አይደለም"ተያይዘን ወጣን።
ጠዋቱ ደመናማና ቀዝቃዛ ነው።በግምት 3 ሰዓት ይሆናል የነጌሌ ገበያ በብዛት ከዚን ሰዓት ቡሗላ ነው የሚደራው።
ነገሌ ቦረና ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 600 ኬ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኝና በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ስር ከሚተዳደሩ ከተሞች አንዷ ስትሆን በአሁኑ ወቅት የጉጂ ዞን ዋና ከተማም ነች።ከዛ በተረፈ ግን የትንሿ ኢትዮጵያ ምሳሌ ነች ኬትኛውም ብሔረሰብ የመጡ ሰዎች በእኩል አና በአንድነት የሚኖሩባት ሁሉንም በአንድ አቅፋ የያዘች ከተማ ናት።
በአባ ገዳ ስረዓት ከሚተተዳደሩትም ውስጥ አንዷ ነች በከተማዋ ውስጥ ከሚገኙ ሀውልቶችም ትለቁና የሚታወቀውም የአባ ገዳ አባት ሀውልት ነው።
የከተማዋ አየር ሞቃት የሚባል አይነት ሲሆን ብዙ ነገራ ከአዳማ ናዝሬት ጋር አንደሚያመሳስላትም ይነገርላታል።በአመት ሁለት ጊዜ ዝናብ ምታገኝ ቢሆንም ግን በነዚ የፀደይ ወቅት ላይ አልፎ አልፎ ደመናና ወቀቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊያገኛት ይችላል።
በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎችም በእርሻ ስራና በንግድ ስራ የተሰማሩ ሲሆን በከብት ቀንድ ሀብትም የታደለች ናት።ሱማሌ ጠረፍ እና ድንበር መሆና ደሞ በመጠኑ ለንግድ ስራ አመቺ አድርጓታል።
ለማንኛውም ተወለጄ ያደኩት እዚው ትንሿ ኢትዮጵያ ነገሌ ቦረና
ውስጥ ነው።
የጠዋቱን አየር አያጣጣምን ከቡርቴ ጋር መንገድ እንደጀመርን
"ቡርቴ...?" አልኳት ጠይቂኝ ባለችው መሰረት ጥያቄን መርጬ
"ለምንድነው እዚ ያለሁት ከት/ት አንዴትና ለምን መቼ መጣው?"
"ይሄንን እኮ ሁለት ቀን በፊት ጠይቀሽኝ ነግሬሻለው በርግጥ ዶክተሩ አንዲ ሊሆን እንደሚችል ነግሮን ነበር። ይኸውልሽ አሁን ሀገሩ ላይ ያለው
ሁኔታ በተለይም በዮንቨርሲቲዎች አከባቢ ግጭትና አለመረጋጋት ስላለ አብዛኛውን ተማሪ ወደ ቤቱ ተመልሶ ቁጭ ብሏል።እና አንቺም እንደምትመጪ ነገርሽን አና ግን መጣለው ባልሽበት ቀን አልመጣሽም ከዛ ቡሗላ ብንጠብቅም አልመጣሽም ነበር በስለክሽም ልናገኝሽ አልቻልንም ጓደኞችሽ እዛ እንደሌለሽ ነበር የነገሩን።ግን መጣለው ካልሽበት ከአንድ ሁለት ሳምንት ና ከዛበላይ ከቆየሽ ቡሗላ ነው የመጣሽው አና ምንም አታስታውሺም ነበር እንደዚ ሆነሽና ታመሽም ነበር"
"ማን አመጣኝ ታዲያ...?"
"እንጃ ጋሼ ነው ይዘውሽ ወደቤት የመጡት ስለክም ልብስም አልያሽም ነበር እና አንድ የማናውቀው ሰው ይመስለኛል እስከዚ ያመጣሽ እና ጋሼም በሰው በሰው መሰለኝ ያገኘሽ በደንብ አልነገረኝ።"
"ኬት ነበር የመጣሁት??" "እንጃ ብንጠይቅም መልስ ስላጣን ዶክተር ጋር ነበር የወሰድንሽ እናም ለማገገም ጊዜ እንደሚያስፈለግሽ ተረዳን።" "ዶ/ሩ ምን አለ..?"
"ጭንቀትና የአይምሮ መታወክ ነው ብሎ ነው የገመተው ግን እሱን ማረጋገጥ ሚቻለው አንቺን ጠይቆ ስትመልሺ ብቻ ነው ሆኖም ለጊዜው መጨናነቅና መረበሽ ስለሌብሽ ጋሼም ሆነ ዶ/ሩ ማንኛቸውም እንዳይጠይቁሽ ሆኗል"
"የት እንደነበር ወይም ምን ሆኜ አንደነበር ትንሽም አንኳን ምንም አታውቁም...?" በአሉታ አንገቷን ነቀነቀችልኝ።
"አይ አይመስለኝም ይሄማኮ ግልፅና ለመገመት እንኳን በጣም ቀላል ነው ቡርቴ !!!"እንደመጮኽ አልኩባትና ትቻት ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ።አባቴ በትክክልም የሆንኩትን ያውቃል እኔን መጣለት ሰውንም በትክክል። ለዛ ነው ምን አስታወሽ ብሎ እንኳን ያልጠየቀኝ መስማት ስለሚፈራ ወይም ስላልፈለገ ነው።ዜናስ እንዳልሰማ የተደረኩበት ምክንያትስ..?የአባቴ ስጋትና ጥንቃቄስ...?ምናልባት እንዳላስታወስ ተፈልጎና ሆን ተብሎ ቢሆን....?
ሁለቱይ ሳምንት የት ነበርኩ...?ማስታወስ አለመቻሌ ንዴት እየጫሰብኝ የመጣ መሰለኝ..
፡
፡
፡
💫 ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንዲሁም ማስተካከል ያለባት ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
👍2
#ቄስ_ቫላንቲ_ሆይ……
እንዴት ሰንብተዋል ኑሮዎት እንዴት ነዉ
ይሄዉ ተገናኘን መሰንበት ደግ ነዉ
እኔ ብቻየን ነኝ ዛሬም ልክ እንዳምናዉ
የክህደት ባንዴራ ህይወታችን መሀል
ከፍ ብሎ ሲሰቀል
ጥንድ መሆን ህመም ብቻነት ይበጃል
የኔን ነገር ተዉት ይቅር አይነሳ
ግን እንደዉ ግንሳ….
የባለፈዉ ለታ የቫላንቲኖ ቀን
ህዝቤ ያረገዉን መቸም አይረሱትም
ከሰሜን ደቡብ ጫፍ ከምራብ ምስራቅም
ተፋቀርን ያሉ ጥንዶች ባደባባይ
ቀይ አበባ ይዘዉ…
ቀይ ወይን ተጎንጭተዉ…
ጉዋዳ ጎዳናዉን በቀይ አስሸብርቀዉ
ቀይ ጠረጴዛ ቀይ ስጋጃ ላይ
በጥንዶች ተሞልቶ አለም ቀልቶ ሲታይ
እዉነት እንዳይመስሎት ቄስ ቫላንቲኖ ሆይ
እዉነት እዉነት እዉነት
አለም ቀልቶ አይደለም ቀንቶ ነዉ እዉነቱ
እሽ አሁን የት አሉ አምና የቀሉቱ
ቀንተዉ ነዉ በሰዉ ቀይ አበባ ይዘዉ
ሲሉ ሰምታን ሰምተዉ ያለ ሀቁ ናዉዘዉ
ሲነጋ የጠፉት ቀዩን ካርድ መዝዘዉ
በእዉነት ቫላንቲኖ
እርስዎ ደክመዋል እርስዎ ለፍተዋል
ለፍቅረኞች ሲሉ ህይወት ሰዉተዋል
ግና ባደባባይ እዩኝ ያለ ፍቅር
እዩኝ ያለ ህይወት
መሰረት ከሌለዉ
በረከት ከሌለዉ ንፋስ ሽዉ ያለ ለት
ፍጻሜዉ ቀይ ነዉ ቢጫም አይገባበት
ቫላንቲኖ አባቴ….
ግዜዉ ተለዉጡዋል ዘመን ለዛዉ ከፍቱዋል
ታሪክ ተቀይሩዋል
በእርግጥ በእርሶ ዘመን
ንጉስ ወጣቶቹን እንዳይጋቡ አዙዋል
ይህም ክፉ ትዛዝ እርሶን አስከፍቱዋል
አሁን በኛ ግዜ
ወጣቱ ይጋባል ግን ወድያዉ ይፋታል
ለምን?
የተሸበረ ልብ የፈራ ሰዉነት
ትዳርን አይደለም የራሰንም ህይወት
መሸከም ይፈራል
በእዉነት ቫላንቲኖ አለም ተሸብሯል
ቀይ ሲያይ…. ሹፌሩ ይቆማል
ቀይ ሲያይ….ኩዋሰኛዉ ይወጣል
ቀይ ሲያይ….ቀይ ሲያይ
የከፋዉ ሀገሬዉ ልቡ ይሸበራል
ባክዎን አባቴ
ባክዎን አባቴ
የሚቀጥለዉን ዳግመኛ ሲመጡ
ቀይ አበባ ጥለዉ…
እንደ ኖህ እርግብ ከሳር ከቀንበጡ
አረንጉዋዴ ቅጠል ጨፌ ይዘዉ ይምጡ
⚪️በሰለሞን ሰሃለ⚫️
እንዴት ሰንብተዋል ኑሮዎት እንዴት ነዉ
ይሄዉ ተገናኘን መሰንበት ደግ ነዉ
እኔ ብቻየን ነኝ ዛሬም ልክ እንዳምናዉ
የክህደት ባንዴራ ህይወታችን መሀል
ከፍ ብሎ ሲሰቀል
ጥንድ መሆን ህመም ብቻነት ይበጃል
የኔን ነገር ተዉት ይቅር አይነሳ
ግን እንደዉ ግንሳ….
የባለፈዉ ለታ የቫላንቲኖ ቀን
ህዝቤ ያረገዉን መቸም አይረሱትም
ከሰሜን ደቡብ ጫፍ ከምራብ ምስራቅም
ተፋቀርን ያሉ ጥንዶች ባደባባይ
ቀይ አበባ ይዘዉ…
ቀይ ወይን ተጎንጭተዉ…
ጉዋዳ ጎዳናዉን በቀይ አስሸብርቀዉ
ቀይ ጠረጴዛ ቀይ ስጋጃ ላይ
በጥንዶች ተሞልቶ አለም ቀልቶ ሲታይ
እዉነት እንዳይመስሎት ቄስ ቫላንቲኖ ሆይ
እዉነት እዉነት እዉነት
አለም ቀልቶ አይደለም ቀንቶ ነዉ እዉነቱ
እሽ አሁን የት አሉ አምና የቀሉቱ
ቀንተዉ ነዉ በሰዉ ቀይ አበባ ይዘዉ
ሲሉ ሰምታን ሰምተዉ ያለ ሀቁ ናዉዘዉ
ሲነጋ የጠፉት ቀዩን ካርድ መዝዘዉ
በእዉነት ቫላንቲኖ
እርስዎ ደክመዋል እርስዎ ለፍተዋል
ለፍቅረኞች ሲሉ ህይወት ሰዉተዋል
ግና ባደባባይ እዩኝ ያለ ፍቅር
እዩኝ ያለ ህይወት
መሰረት ከሌለዉ
በረከት ከሌለዉ ንፋስ ሽዉ ያለ ለት
ፍጻሜዉ ቀይ ነዉ ቢጫም አይገባበት
ቫላንቲኖ አባቴ….
ግዜዉ ተለዉጡዋል ዘመን ለዛዉ ከፍቱዋል
ታሪክ ተቀይሩዋል
በእርግጥ በእርሶ ዘመን
ንጉስ ወጣቶቹን እንዳይጋቡ አዙዋል
ይህም ክፉ ትዛዝ እርሶን አስከፍቱዋል
አሁን በኛ ግዜ
ወጣቱ ይጋባል ግን ወድያዉ ይፋታል
ለምን?
የተሸበረ ልብ የፈራ ሰዉነት
ትዳርን አይደለም የራሰንም ህይወት
መሸከም ይፈራል
በእዉነት ቫላንቲኖ አለም ተሸብሯል
ቀይ ሲያይ…. ሹፌሩ ይቆማል
ቀይ ሲያይ….ኩዋሰኛዉ ይወጣል
ቀይ ሲያይ….ቀይ ሲያይ
የከፋዉ ሀገሬዉ ልቡ ይሸበራል
ባክዎን አባቴ
ባክዎን አባቴ
የሚቀጥለዉን ዳግመኛ ሲመጡ
ቀይ አበባ ጥለዉ…
እንደ ኖህ እርግብ ከሳር ከቀንበጡ
አረንጉዋዴ ቅጠል ጨፌ ይዘዉ ይምጡ
⚪️በሰለሞን ሰሃለ⚫️
❤1
#የቤት_እመቤት_በመሆን_ውስጥ_እመቤትነት #አለ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
በአንድ ወቅት፣ ያገኘኋቸውን ወንዶች በሙሉ አንድ ጥያቄ ስጠይቅ ነበር፤ "የቤት እመቤት ማለት ምን ማለት ነው?" ከአንድ ወይም ሁለት መልሶች ውጪ የተሰጡኝ ፍቺዎች በሚከተሉት ሐረጎች ሊጠቃለል ይችላል።
"የማትሰራ ሴት"
"ሥራ የሌላት ሴት"
"ገቢ የሌላት ሴት"
"ሥራ አጥ ሴት"
"ሥራ ፈት ሴት"
እነዚህ መልሶች የሰጡኝን ወንዶች መልሼ ይሄንን ጥያቄ ጠየኳቸው።
ነጋ ጠባ አልጋ ማንጠፍ፣ ቆሻሻ ልብስ ማጠብ፣ የታጠበ ልብስ ማጠፍ፣ የታጠፈ ልብስ በየቦታው ማስቀመጥ፤ ከሻይ ማንኪያ እስከ በርሜል ሙልጭ አድርጎ ማጠብ ፣ የታጠበውን እቃ ማድረቅ ከሻይ ማንኪያ እስከ በርሜል ሙልጭ ተደርጎ የታጠበና የደረቀ እቃን በየቦታው ማስቀመጥ፣ ሥራ አይደለም?
በየቀኑ ከኩሽና እስከ ሳሎን ፤ ከሽንት ቤት እስከ ግቢ መጥረግና መወልወል፤
ከሳሎን ጠረጴዛ እስከ ቁም ሳጥን ጀርባ እና አልጋ ሥር ድረስ መጥረግና መወልወል፤
የቤቱን ሁሉ የተጠረገና የተወለወለ ቆሻሻን ሰብስቦ መጣልስ ፤ ሥራ አይደለም ?
ቀን ቆጥሮ አንሶላ ፤ ትራስ ልብስና አልጋ ልብስ መቀየር ፤ ጊዜን አስልቶ የኩሽና እቃ ግልብጥ አድርጎ አውጥቶ ማጽዳት፤ ጊዜን ወስኖ የመስኮትና የበር መስታወትን በጋዜጣ ሲያፀዱ እና ሲያስውቡ መዋል ፤ የአደፈ መጋረጃን መሐወጥ፤ ሥራ አይደለም?
"ምን አለቀ?" ብሎ ቀለብ መሸመት ፤ የተሸመተውን አመጣጥኖ ማዘጋጀት፤ የተዘጋጀውን ማቅረብና ቤተሰብ መመጠብ፤ ሥራ አይደለም? ደግሞ ከሁሉ በላይ፤
ልጅ ማርገዝ፤
ልጅ አምጦ መውለድ፤
ልጅ አጥብቶ ማሳደግ፤
ልጅ ማነጽ፤
ልጅን ለወግ ማብቃት ፤ ሥራ አይደለም?
እናም ወንድሞቼ...
አገልግሎትና ምርታማነት በጥሬ ገንዘብ በሚተመን የኢኮኖሚ ሥርአት ውስጥ በመኖራችን ብቻ ፤
በቀጥታ የገንዘብ ክፍያ የማያስገኝ ሥራ እንደ ሥራ በማይቆጠርበት ዓለም በመኖራችን ብቻ ፤ ይሄንና ሌላም ልዘረዝረው ብል መጽሀፍ የማይበቃውን ሥራ ሁሉ የምትሰራን ሴት "ሥራ የላትም" አትበለኝ።
ይልቅስ፣ በእኛ ሀገር የቤት እመቤት መሆን ፤ ከእመቤትነቱ ሸክሙ ይበልጣልና ፤ ሚዛናችሁን አስተካክላችሁ የቤት እመቤት ማለት ፤ "በዓለም ላይ ከባዱን ፤ ግን ክፍያ የሌለውን ሥራ የምትሰራ ሴት ማለት ናት" በሉኝ።
💫ጨረስን💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
በአንድ ወቅት፣ ያገኘኋቸውን ወንዶች በሙሉ አንድ ጥያቄ ስጠይቅ ነበር፤ "የቤት እመቤት ማለት ምን ማለት ነው?" ከአንድ ወይም ሁለት መልሶች ውጪ የተሰጡኝ ፍቺዎች በሚከተሉት ሐረጎች ሊጠቃለል ይችላል።
"የማትሰራ ሴት"
"ሥራ የሌላት ሴት"
"ገቢ የሌላት ሴት"
"ሥራ አጥ ሴት"
"ሥራ ፈት ሴት"
እነዚህ መልሶች የሰጡኝን ወንዶች መልሼ ይሄንን ጥያቄ ጠየኳቸው።
ነጋ ጠባ አልጋ ማንጠፍ፣ ቆሻሻ ልብስ ማጠብ፣ የታጠበ ልብስ ማጠፍ፣ የታጠፈ ልብስ በየቦታው ማስቀመጥ፤ ከሻይ ማንኪያ እስከ በርሜል ሙልጭ አድርጎ ማጠብ ፣ የታጠበውን እቃ ማድረቅ ከሻይ ማንኪያ እስከ በርሜል ሙልጭ ተደርጎ የታጠበና የደረቀ እቃን በየቦታው ማስቀመጥ፣ ሥራ አይደለም?
በየቀኑ ከኩሽና እስከ ሳሎን ፤ ከሽንት ቤት እስከ ግቢ መጥረግና መወልወል፤
ከሳሎን ጠረጴዛ እስከ ቁም ሳጥን ጀርባ እና አልጋ ሥር ድረስ መጥረግና መወልወል፤
የቤቱን ሁሉ የተጠረገና የተወለወለ ቆሻሻን ሰብስቦ መጣልስ ፤ ሥራ አይደለም ?
ቀን ቆጥሮ አንሶላ ፤ ትራስ ልብስና አልጋ ልብስ መቀየር ፤ ጊዜን አስልቶ የኩሽና እቃ ግልብጥ አድርጎ አውጥቶ ማጽዳት፤ ጊዜን ወስኖ የመስኮትና የበር መስታወትን በጋዜጣ ሲያፀዱ እና ሲያስውቡ መዋል ፤ የአደፈ መጋረጃን መሐወጥ፤ ሥራ አይደለም?
"ምን አለቀ?" ብሎ ቀለብ መሸመት ፤ የተሸመተውን አመጣጥኖ ማዘጋጀት፤ የተዘጋጀውን ማቅረብና ቤተሰብ መመጠብ፤ ሥራ አይደለም? ደግሞ ከሁሉ በላይ፤
ልጅ ማርገዝ፤
ልጅ አምጦ መውለድ፤
ልጅ አጥብቶ ማሳደግ፤
ልጅ ማነጽ፤
ልጅን ለወግ ማብቃት ፤ ሥራ አይደለም?
እናም ወንድሞቼ...
አገልግሎትና ምርታማነት በጥሬ ገንዘብ በሚተመን የኢኮኖሚ ሥርአት ውስጥ በመኖራችን ብቻ ፤
በቀጥታ የገንዘብ ክፍያ የማያስገኝ ሥራ እንደ ሥራ በማይቆጠርበት ዓለም በመኖራችን ብቻ ፤ ይሄንና ሌላም ልዘረዝረው ብል መጽሀፍ የማይበቃውን ሥራ ሁሉ የምትሰራን ሴት "ሥራ የላትም" አትበለኝ።
ይልቅስ፣ በእኛ ሀገር የቤት እመቤት መሆን ፤ ከእመቤትነቱ ሸክሙ ይበልጣልና ፤ ሚዛናችሁን አስተካክላችሁ የቤት እመቤት ማለት ፤ "በዓለም ላይ ከባዱን ፤ ግን ክፍያ የሌለውን ሥራ የምትሰራ ሴት ማለት ናት" በሉኝ።
💫ጨረስን💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1
#ብሌን 🇪🇹
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
"እና መጀመሪያ ምንድነው ምንገዛው?" አለችኝ።ገበያ ደርሰን ነበር ገበያው ያን ያህል አልደራም ቢሆንም በቂ ሱቆች ተከፍተዋል።"አንቺ የፈለግሽውን" አልኳት
"እንደዛ ከሆነ ነይ በዚ እንቁላል እና ወተት አንግዛ"
በአትክልት ተራው አልፈን ወደ እህል ተራ በሚወስደው መንገድ ስንደርስ በአንደኛው መታጠፊያ ይዛኝ ገባች።ወደ ትልቁ የገበያ አዳራሽ ማዕክል እና የቤት እቃዎች በመሸጫዎች መሀል አቋርጠን እዛው ወዳለው ወደ ወተት ተራው ገባን።"ደንበኛዬ አልመጣችም በዛ ላይ ሀይላንድ ያስፈልገኛል መጣው እዚሁ ጠብቂኝ"ብላኝ ሔደች ትኩረቴ እሷ ጋር ስላልነበረ ግድ አልሰጠኝም ነበር።ግራና ቀኙን መቃኘት ጀመርኩ አንዳንድ እቃው ባለሱቆች ገና ከፍተው እቃ በማውጣጣት ላይ ሲሆኑ አብዛኛው ጨርሶ ቁጭ ብሏል።የማውቀውን ሰው ፍለጋ ይመስል ሁሉንም እያስተዋልኩ አያለው።
"ኧረ እማ እንሒድ በቃ ለኔኮ ጫማ አልገዛንም..."
"አይ የልጅ ነገር በቃ ከራስህ ውጪ አታስብም አይደል መጀመሪያ የምንበላውን ልገዛ እስኪ" እናትና ልጅ ትኩረቴን ስለሳቡኝ እሰማቸው ጀመር።
"ገና እኮ ጠዋት ነው ማሙሽ ሱቁም በደንብ ይከፈት እናትህን አታስቸግራት እንጂ" ሌላኛዋ ሴት እንቁላል ለእናትየው እያቀበለቻት የእንቁላል ነጋዴ ነች።
"እሺ እዛጋ ያንን"ህፃኑ ለናቱ እየጠቆማት እድሜው በግምት ወደ ሰባትና ስምንት የሚጠጋ ይመስላል።
"ምን የቱ ጋር?" አለች እናቱ።እኔም ጥቆማውን ተከትዬ አይኔን ጣልኩ
"ምንድ ነው እሱ አትናገርም እንዴ?" እናትየው የታያት አይመስልም እኔ ግን በትክክል አይቼዋለው የልጁ እሳቤ ቀድም የነገረኝ ይመስል ተረድቼዋለው።በቀስታ ወዳየሁት ነገር መራመድ ጀመርኩ።
"ያውና ሰው የሚታረድበት ነገር እኮ ነው!!"
"ምን.... ?በስመአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ!!"
እናትየው እንቁላሉን ስትለቅ ይሰማኛል።እግሬ አየተንቀጠቀጠ ቀረብኩ በቁጥር በዛ ያሉ ስለታቸወና አዲስነታቸው ከሩቅ የሚያብለጨልጭ ባንጋዎች ናቸው ሰውነቴን አየሰቀጠጠኝ አጠገቡ ቆሜ ወደታች አየውት።
"ደሞ ኬት አመጣኸው ይሄንን? ሁለተኛ አንደዚ እንዳትል እሺ አባቴ ሁለተኛ!! ና ከዚ እንሒድ"የናትየው ድንጋጤ ከድምጿ ቃና ይታወቀኛል።የሷ ብቻ አይደለም እኔም ፍርሀቴ ሲጀምረኝ እና ወደነዛ ቀናት በትውስታ የተመለስኩ ሲመስለኝ ይተወቀኛል። ህፃኑ ያለው በአይምሮዬ ተስሎ ታየኝ።
ይሄ ነው እንግዲ የማንነት የትውልድ ኪሳራ፣ ይሄ ነው እንግዲ አዲሱ ለትውልድ የምናስተላልፈው ታሪክ እና ገድላችን ፣ይሄ ነው እንግዲ ሰውነት ከእንስሳነትም ከእቃነትም ተራ አልፎ የረከሰበትና የቀለለበት ዘመንና ትውልድ ፤ይሄ ነው የማንነት ክስረት። ይሄንን የማንነት ውደቀታችን ነው በታናናሾቻችንና በልጆቻችን አይምሮ እየሞላንና እየቀረፅን ያለነው።
"ጉድ እኮ ነው አንቺ ይሄ ህፃን እንኳ እንዲ ይናገር....አጃኢብ!!!
"ሰማሽ አይደል ለነገሩ ምን ያድርግ በሱም አይፈረድም።እነሱስ ቢሆኑ ሰው እንደዚ በተጨካከነበትና በሚጨራረስበት ወቅት እንደዚ በሰፊው ይሄን መነገዳቸው ምን ማለታቸው ነው? እንዲያው ሲያዮት እንኳ አንዴት ይዘገንናል!"።
"ሔዊ ምነው" ደንዝዤ ከቆምኩበት የቡርቴ ጥሪ ከኋላዬ ተሰማኝ።"እንዴ እያለቀሽ ነው እንዴ ሔዋን ምነው የኔ ወድ?"
የተናነቀኝን እንባ እያየች።ግን የድንጋጤ እና የፍረሀት ወይም
የሀዘን እንባ አልነበረም ቁጭትና እልህ እና ንዴት እንጂ።
"የኔ ጥፋት ነው ይዤሽ መውጣትም ሆነ ብቻሽን መተው አልነበረብኝም"እንባዬን አየጠረገች።
"ቡርቴ..?"አልኳት"ሁለቱን ሳምንት ታግቼ ነበር አይደል? ለነገሩ እሱ በጣም ግልፅ ነው ደሞም ይሄንን አባቴም ሆነ አንቺም በደንብ ታውቃላቹ!!
"ምን...? ለምንድነው እንደዚ የምትይው ነይ ከዚ አንሂድ መዳኒትሽን መውሰድ አለብሽ..."እጄን ይዛ ጎተተችኝ።
"አይ አይሆንም ለቀቂኝ!"እጄን አስለቀኳት
"አቁሚ በጭራሽ አልሄድም አሁን ባልሺኝ መሰረት የምጠይቅሽን እሺ በማለት ታደረጊያለሽ!"ጥያቄ ሳይሆን ትዕዛዝ ነበር።
#ሕዳር 20/12 ቀን የታገቱ ተማሪዎች እስካሁን ድምፃቸው አልተሰማም።
ይላል ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ፔጁን ተቀላቀልኩ።
January 24
#ከ 35 ሺህ በላይ ተማሪዎች ቤታቸው ናቸው።በአንዳንድ የሀገሪቱ ዮኒቨርስቲዎች ውስጥ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት መደበኛ ት/ታቸውን አቋርጠው የተመለሱ ተማሪዎች ወደ ትም/ት ገበታቸው አልተመለሱም።
#የኢትዮጵያ የሳይንስና የከፍተኛ ት/ት ሚኒስተር በ22ቱ ዮኒቨርስቲዎች ባካሄደው ምርመራ እና ቅኝት በግማሽ መንፈቅ ዓመት ብቻ የ12 ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ ተገልጿል።
=> ታህሳስ 27
ሌሎች የታገቱ ተማሪዎች እንዳሉና ቁጥራቸውም 4 እንደሚደርስ የክልሉ ርዕሰ መስተዳዶር በጋዜጣዊ መግለጫ የገለፁበት ቀን
#በሕዳር 20/12 ስለታገቱ ተማሪዎች የጠቅላይ ሚንስተሩ ፅ/ቤት የፕሬስ ሴክሬተርያት በሰጡት መግለጫ፦አጠቃላይ 27 ተማሪዎች ታግተው እንደነበረና 21ዱ መለቀቃቸው 6ቱ ደግሞ ታግተው እንዳሉ ገልፀዋል።የሚልና ሌሎች ተመሳሳይ የወጡ ዜናዎችን በብዛት ካየሁ ቡሗላ
አሁን ሁሉም በግልፅ የገባኝ መሰለኝ።
የሰጠሗትን ትዕዛዝ ላለመቀበል ጋሼ ቢጠየቁኝስ ምን እላቸዋለው?"ነበር ያለችኝ እኔም
ቃል በገባሁላት መሰረት አባቴ ሳይመለስ ቀድሜ ቤት ለመገኘት ከሷ እንደተለየው ጊዜ ሳላባክን ወደ ኢንተርኔት ቤት ነበር ያመራሁት።እና የምፈልገውን ካየው ቡሗላ ቶሎ እሷ ጋር መሄድ ስለነበረብኝ ባጃጅ አስቁሜ ገባው ውስጤ ብዙ ሀሳብ ይመላለሳል ግን የትኛውን በትክክል መስማት እንዳለብኝ እንጃ። እስካሁን ምንም ባለማወቄ እና በዝምታዬ የተሞኘውም መሰለኝ
ሀገሪቱ ላይ የሚካሄደውና የሰው ሁኔታ ግን ግርምትን የሚያጭር ነው። ምንም እንዳልተፈጠረ መኖራችን አስገርሞኛል። ለምሳሌ ያለሁበት ባጃጅ ሹፌር ዕድሜው ከኔው ጋር ተመሳሳይ ነው። እርግጠኛ ነኝ በነዛ ወጣቶች ላይ የተፈጠረውን/ይቅርታ በኛ ላይ ልበል እንጂ ስለተፈጠረውና ስለተፈፀመው ድርጊት በሚገባ ሰምቷል።እና ናላ በሚያዞር ምንነቱ በማይገባ ዘፈን ባጃጁን መጓጓዣ ሳይሆን ክለብ አስመስሎ እስከቂጡ ከፍቶ ባጃጇን እንደ አየር ያከንፋታል። ተማሪዎች ከየት/ት ቤታቸው ተለቀው በተለያየ ዮኒፎርማቸው ሲተራመሱ ይታያሉ። ይሄን ሁሉ ጊዜ ቤት መጥቼ ቁጭ ስልም ሆነ ስወጣ ማንም ሰው ስለነዛ ልጆች ሲያወራ ና ሲያነሳ አጋጥሞኝ አለማወቁም የማይታመን ነው
ሚድያዎቻችንም ቢሆኑ
ከምንም በላይ ያስገረመኝ ግን የራሴው አባት ነው።ምንም ያሀል ልጁን የሚወድ አባት ሊሆን ይችላል ግን ደሞ ይሄ ትልቅ ራስ ወዳድነት ይመስለኛል።ስለኔ ብቻ ሳይሆን የሌሎቹም ነብስና መጨረሻ ሊያሳስበው ይገባ ነበር።
ለማንኛውም ግን ማወቄንም ሆነ ማስታወሴን በድብቅ ለመያዝ እና ለመቀጠል ወስኛለው ምክንያቱም ማንኛውም ወላጅ ቢሆን ለጁ እንዲያደርግ እማይፈልገውን ነገር ለማድረግ ስለወሰንኩ ነው።በርግጥ አንደማንኛውም ሰባዊ ሰው ሲታይ ልክ የሆነና ተገቢ ድርጊት ሊሆን ይችላል።እንደ ወላጅ ግን አይደለም!
" ደርሳሻል እናት"አለኝ ወጣቱ ባለባጃጅ ድምፁን ከፍ አድርጓ፤ እስኪ ምናለበት ከመጮህ ዘፈኑን ቢቀንሰው ያለኝን ብር ከፍዬ በፍጥነት ወደቤት ገባው።አባቴ ገና አልመምጣቱ ካረጋገጥኩ ቡሗላ ወደ ቡርቴ ሮጥኩ
"ውይ ተመስገን ለትንሽ ነው የደረሽው"አለችኝ
"ቡርቴ..?"
"እ...?"
"ብሌንስ...??"ውስጤ ሲመላለስ የነበረውን ጥያቄ ጠየኳት።
፡
፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንዲሁም ማስተካከል ያለባት ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
"እና መጀመሪያ ምንድነው ምንገዛው?" አለችኝ።ገበያ ደርሰን ነበር ገበያው ያን ያህል አልደራም ቢሆንም በቂ ሱቆች ተከፍተዋል።"አንቺ የፈለግሽውን" አልኳት
"እንደዛ ከሆነ ነይ በዚ እንቁላል እና ወተት አንግዛ"
በአትክልት ተራው አልፈን ወደ እህል ተራ በሚወስደው መንገድ ስንደርስ በአንደኛው መታጠፊያ ይዛኝ ገባች።ወደ ትልቁ የገበያ አዳራሽ ማዕክል እና የቤት እቃዎች በመሸጫዎች መሀል አቋርጠን እዛው ወዳለው ወደ ወተት ተራው ገባን።"ደንበኛዬ አልመጣችም በዛ ላይ ሀይላንድ ያስፈልገኛል መጣው እዚሁ ጠብቂኝ"ብላኝ ሔደች ትኩረቴ እሷ ጋር ስላልነበረ ግድ አልሰጠኝም ነበር።ግራና ቀኙን መቃኘት ጀመርኩ አንዳንድ እቃው ባለሱቆች ገና ከፍተው እቃ በማውጣጣት ላይ ሲሆኑ አብዛኛው ጨርሶ ቁጭ ብሏል።የማውቀውን ሰው ፍለጋ ይመስል ሁሉንም እያስተዋልኩ አያለው።
"ኧረ እማ እንሒድ በቃ ለኔኮ ጫማ አልገዛንም..."
"አይ የልጅ ነገር በቃ ከራስህ ውጪ አታስብም አይደል መጀመሪያ የምንበላውን ልገዛ እስኪ" እናትና ልጅ ትኩረቴን ስለሳቡኝ እሰማቸው ጀመር።
"ገና እኮ ጠዋት ነው ማሙሽ ሱቁም በደንብ ይከፈት እናትህን አታስቸግራት እንጂ" ሌላኛዋ ሴት እንቁላል ለእናትየው እያቀበለቻት የእንቁላል ነጋዴ ነች።
"እሺ እዛጋ ያንን"ህፃኑ ለናቱ እየጠቆማት እድሜው በግምት ወደ ሰባትና ስምንት የሚጠጋ ይመስላል።
"ምን የቱ ጋር?" አለች እናቱ።እኔም ጥቆማውን ተከትዬ አይኔን ጣልኩ
"ምንድ ነው እሱ አትናገርም እንዴ?" እናትየው የታያት አይመስልም እኔ ግን በትክክል አይቼዋለው የልጁ እሳቤ ቀድም የነገረኝ ይመስል ተረድቼዋለው።በቀስታ ወዳየሁት ነገር መራመድ ጀመርኩ።
"ያውና ሰው የሚታረድበት ነገር እኮ ነው!!"
"ምን.... ?በስመአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ!!"
እናትየው እንቁላሉን ስትለቅ ይሰማኛል።እግሬ አየተንቀጠቀጠ ቀረብኩ በቁጥር በዛ ያሉ ስለታቸወና አዲስነታቸው ከሩቅ የሚያብለጨልጭ ባንጋዎች ናቸው ሰውነቴን አየሰቀጠጠኝ አጠገቡ ቆሜ ወደታች አየውት።
"ደሞ ኬት አመጣኸው ይሄንን? ሁለተኛ አንደዚ እንዳትል እሺ አባቴ ሁለተኛ!! ና ከዚ እንሒድ"የናትየው ድንጋጤ ከድምጿ ቃና ይታወቀኛል።የሷ ብቻ አይደለም እኔም ፍርሀቴ ሲጀምረኝ እና ወደነዛ ቀናት በትውስታ የተመለስኩ ሲመስለኝ ይተወቀኛል። ህፃኑ ያለው በአይምሮዬ ተስሎ ታየኝ።
ይሄ ነው እንግዲ የማንነት የትውልድ ኪሳራ፣ ይሄ ነው እንግዲ አዲሱ ለትውልድ የምናስተላልፈው ታሪክ እና ገድላችን ፣ይሄ ነው እንግዲ ሰውነት ከእንስሳነትም ከእቃነትም ተራ አልፎ የረከሰበትና የቀለለበት ዘመንና ትውልድ ፤ይሄ ነው የማንነት ክስረት። ይሄንን የማንነት ውደቀታችን ነው በታናናሾቻችንና በልጆቻችን አይምሮ እየሞላንና እየቀረፅን ያለነው።
"ጉድ እኮ ነው አንቺ ይሄ ህፃን እንኳ እንዲ ይናገር....አጃኢብ!!!
"ሰማሽ አይደል ለነገሩ ምን ያድርግ በሱም አይፈረድም።እነሱስ ቢሆኑ ሰው እንደዚ በተጨካከነበትና በሚጨራረስበት ወቅት እንደዚ በሰፊው ይሄን መነገዳቸው ምን ማለታቸው ነው? እንዲያው ሲያዮት እንኳ አንዴት ይዘገንናል!"።
"ሔዊ ምነው" ደንዝዤ ከቆምኩበት የቡርቴ ጥሪ ከኋላዬ ተሰማኝ።"እንዴ እያለቀሽ ነው እንዴ ሔዋን ምነው የኔ ወድ?"
የተናነቀኝን እንባ እያየች።ግን የድንጋጤ እና የፍረሀት ወይም
የሀዘን እንባ አልነበረም ቁጭትና እልህ እና ንዴት እንጂ።
"የኔ ጥፋት ነው ይዤሽ መውጣትም ሆነ ብቻሽን መተው አልነበረብኝም"እንባዬን አየጠረገች።
"ቡርቴ..?"አልኳት"ሁለቱን ሳምንት ታግቼ ነበር አይደል? ለነገሩ እሱ በጣም ግልፅ ነው ደሞም ይሄንን አባቴም ሆነ አንቺም በደንብ ታውቃላቹ!!
"ምን...? ለምንድነው እንደዚ የምትይው ነይ ከዚ አንሂድ መዳኒትሽን መውሰድ አለብሽ..."እጄን ይዛ ጎተተችኝ።
"አይ አይሆንም ለቀቂኝ!"እጄን አስለቀኳት
"አቁሚ በጭራሽ አልሄድም አሁን ባልሺኝ መሰረት የምጠይቅሽን እሺ በማለት ታደረጊያለሽ!"ጥያቄ ሳይሆን ትዕዛዝ ነበር።
#ሕዳር 20/12 ቀን የታገቱ ተማሪዎች እስካሁን ድምፃቸው አልተሰማም።
ይላል ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ፔጁን ተቀላቀልኩ።
January 24
#ከ 35 ሺህ በላይ ተማሪዎች ቤታቸው ናቸው።በአንዳንድ የሀገሪቱ ዮኒቨርስቲዎች ውስጥ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት መደበኛ ት/ታቸውን አቋርጠው የተመለሱ ተማሪዎች ወደ ትም/ት ገበታቸው አልተመለሱም።
#የኢትዮጵያ የሳይንስና የከፍተኛ ት/ት ሚኒስተር በ22ቱ ዮኒቨርስቲዎች ባካሄደው ምርመራ እና ቅኝት በግማሽ መንፈቅ ዓመት ብቻ የ12 ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ ተገልጿል።
=> ታህሳስ 27
ሌሎች የታገቱ ተማሪዎች እንዳሉና ቁጥራቸውም 4 እንደሚደርስ የክልሉ ርዕሰ መስተዳዶር በጋዜጣዊ መግለጫ የገለፁበት ቀን
#በሕዳር 20/12 ስለታገቱ ተማሪዎች የጠቅላይ ሚንስተሩ ፅ/ቤት የፕሬስ ሴክሬተርያት በሰጡት መግለጫ፦አጠቃላይ 27 ተማሪዎች ታግተው እንደነበረና 21ዱ መለቀቃቸው 6ቱ ደግሞ ታግተው እንዳሉ ገልፀዋል።የሚልና ሌሎች ተመሳሳይ የወጡ ዜናዎችን በብዛት ካየሁ ቡሗላ
አሁን ሁሉም በግልፅ የገባኝ መሰለኝ።
የሰጠሗትን ትዕዛዝ ላለመቀበል ጋሼ ቢጠየቁኝስ ምን እላቸዋለው?"ነበር ያለችኝ እኔም
ቃል በገባሁላት መሰረት አባቴ ሳይመለስ ቀድሜ ቤት ለመገኘት ከሷ እንደተለየው ጊዜ ሳላባክን ወደ ኢንተርኔት ቤት ነበር ያመራሁት።እና የምፈልገውን ካየው ቡሗላ ቶሎ እሷ ጋር መሄድ ስለነበረብኝ ባጃጅ አስቁሜ ገባው ውስጤ ብዙ ሀሳብ ይመላለሳል ግን የትኛውን በትክክል መስማት እንዳለብኝ እንጃ። እስካሁን ምንም ባለማወቄ እና በዝምታዬ የተሞኘውም መሰለኝ
ሀገሪቱ ላይ የሚካሄደውና የሰው ሁኔታ ግን ግርምትን የሚያጭር ነው። ምንም እንዳልተፈጠረ መኖራችን አስገርሞኛል። ለምሳሌ ያለሁበት ባጃጅ ሹፌር ዕድሜው ከኔው ጋር ተመሳሳይ ነው። እርግጠኛ ነኝ በነዛ ወጣቶች ላይ የተፈጠረውን/ይቅርታ በኛ ላይ ልበል እንጂ ስለተፈጠረውና ስለተፈፀመው ድርጊት በሚገባ ሰምቷል።እና ናላ በሚያዞር ምንነቱ በማይገባ ዘፈን ባጃጁን መጓጓዣ ሳይሆን ክለብ አስመስሎ እስከቂጡ ከፍቶ ባጃጇን እንደ አየር ያከንፋታል። ተማሪዎች ከየት/ት ቤታቸው ተለቀው በተለያየ ዮኒፎርማቸው ሲተራመሱ ይታያሉ። ይሄን ሁሉ ጊዜ ቤት መጥቼ ቁጭ ስልም ሆነ ስወጣ ማንም ሰው ስለነዛ ልጆች ሲያወራ ና ሲያነሳ አጋጥሞኝ አለማወቁም የማይታመን ነው
ሚድያዎቻችንም ቢሆኑ
ከምንም በላይ ያስገረመኝ ግን የራሴው አባት ነው።ምንም ያሀል ልጁን የሚወድ አባት ሊሆን ይችላል ግን ደሞ ይሄ ትልቅ ራስ ወዳድነት ይመስለኛል።ስለኔ ብቻ ሳይሆን የሌሎቹም ነብስና መጨረሻ ሊያሳስበው ይገባ ነበር።
ለማንኛውም ግን ማወቄንም ሆነ ማስታወሴን በድብቅ ለመያዝ እና ለመቀጠል ወስኛለው ምክንያቱም ማንኛውም ወላጅ ቢሆን ለጁ እንዲያደርግ እማይፈልገውን ነገር ለማድረግ ስለወሰንኩ ነው።በርግጥ አንደማንኛውም ሰባዊ ሰው ሲታይ ልክ የሆነና ተገቢ ድርጊት ሊሆን ይችላል።እንደ ወላጅ ግን አይደለም!
" ደርሳሻል እናት"አለኝ ወጣቱ ባለባጃጅ ድምፁን ከፍ አድርጓ፤ እስኪ ምናለበት ከመጮህ ዘፈኑን ቢቀንሰው ያለኝን ብር ከፍዬ በፍጥነት ወደቤት ገባው።አባቴ ገና አልመምጣቱ ካረጋገጥኩ ቡሗላ ወደ ቡርቴ ሮጥኩ
"ውይ ተመስገን ለትንሽ ነው የደረሽው"አለችኝ
"ቡርቴ..?"
"እ...?"
"ብሌንስ...??"ውስጤ ሲመላለስ የነበረውን ጥያቄ ጠየኳት።
፡
፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንዲሁም ማስተካከል ያለባት ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
👍1
#ዝግመትሽ_እና_ፍጥነቴ
፡
፡
የፍቅሬን መጠን ነግሬሽ - ካደመጥሺኝ ቡኋላ
ላስብበት ብለሽ ሄድሽ - እንደቆምኩኝ ካውላላ
በብስለት ሁሉን መርምረሽ- ክፉና ደጉን መዝነሽ
ስለ እኔ ጀርባ አጥንተሽ - ጓደኛ ዘመድ አማክረሽ
ከወር በኋላ ብትመጪ- ልትነግሪኝ ፈቀድኩ ብለሽ
የጊዜ አጠቃቀመችን - ልዩነታችን ገረመኝ
ዝግመትሽ እና ፍጥነቴ - ሁለቱም አስደመመኝ
ቆየው እኮ ሌላ አፍቅሬ - ቀለበት አስሬአለሁ
በዚህ ግርግር መሃል - አንቺን እረስቼለሁ
ዛሬ ይሁን ስትይኝ - ምን መልስ እሰጥሻለሁ።
፡
፡
የፍቅሬን መጠን ነግሬሽ - ካደመጥሺኝ ቡኋላ
ላስብበት ብለሽ ሄድሽ - እንደቆምኩኝ ካውላላ
በብስለት ሁሉን መርምረሽ- ክፉና ደጉን መዝነሽ
ስለ እኔ ጀርባ አጥንተሽ - ጓደኛ ዘመድ አማክረሽ
ከወር በኋላ ብትመጪ- ልትነግሪኝ ፈቀድኩ ብለሽ
የጊዜ አጠቃቀመችን - ልዩነታችን ገረመኝ
ዝግመትሽ እና ፍጥነቴ - ሁለቱም አስደመመኝ
ቆየው እኮ ሌላ አፍቅሬ - ቀለበት አስሬአለሁ
በዚህ ግርግር መሃል - አንቺን እረስቼለሁ
ዛሬ ይሁን ስትይኝ - ምን መልስ እሰጥሻለሁ።
#ጫፍ_አልባ_ቁልቁለት
፡
፡
የያዙትን ይዞ ካልተጠላጠሉ
ወደ ላይ ካላሉ
ወ
ደ
ታ
ች
እ
ያ
ዩ
መውደቂያ ካሰሉ
ከውድቀት ዳርዳሩ ከተንደረደሩ
መውደቅ ከጀመሩ
ውድቀት ጫፍ የለውም
ሜዳዉ ቁልቁለት ነው ውድቀት ዳር የለውም
በውድቀት ላይ ውድቀት እየተያያዘ እየተዋዋለ
ከውድቀትም በታች ሌላ ውድቀት አለ።
፡
፡
የያዙትን ይዞ ካልተጠላጠሉ
ወደ ላይ ካላሉ
ወ
ደ
ታ
ች
እ
ያ
ዩ
መውደቂያ ካሰሉ
ከውድቀት ዳርዳሩ ከተንደረደሩ
መውደቅ ከጀመሩ
ውድቀት ጫፍ የለውም
ሜዳዉ ቁልቁለት ነው ውድቀት ዳር የለውም
በውድቀት ላይ ውድቀት እየተያያዘ እየተዋዋለ
ከውድቀትም በታች ሌላ ውድቀት አለ።
👍1