ያመጡላት የአሳ ጥብስ ነው፡፡ዓሳ በአካባቢው በብዛት ከመመረቱ የተነሳ በቀላሉ የሚገኝ ዋነኛ ምግብ ነው፡፡ደግነቱ እሷም ዓሳ ትወድ ስለነበረ በደስታ ነው መመገብ የጀመረችው፡፡እውነትም ልጁ እንዳላት ከፊት ለፊቷ የሚገጥማትን ነገር ለመጋፈጥና ምን አልባት የማምለጥ እድሏን የምትሞክርበት የተሻለ አጋጣሚ ካገኘት በብቃት እና በጥንካሬ መፋለም እንድትችል የበለጠ ብርቱ መሆን እንዳለባት ከልቧ ስላመነች የተሰጣትን በአጠቃላይ ጥርግርግ አድርጋ በላችና በላዩ ላይ የቀረበላትን ውሀ ጠጣች፡፡ከዛ መጥተው እንሂድ ብለው ካለችበት የታፈነ ቤት እስኪወስዳት ድረስ ጋደም ብላ ዳግመኛ ከሀገሯ እና ከትናንቷ ጋር የሚያገናኛትን የትዝታ ሀዲድ ዘረጋችና ጭልጥ ያለ ትካዜ ውስጥ በመግባት ስለወንድሟ ማሰብ ጀመረች፡፡
ኢትዬጵያ/አዲስ አበባ
ትዝ ይላታል ከነበሩበት የማደጎ ቤት ወጥተው በረንደ መኖር ከጀመሩ ከአመት በኃላ ነው፡፡እለቱ የጥምቀት በዓል የሚከበርበት እለት ነበር፡፡ከተማው ከወቶሮዋ በተለይ መልኩ ከመኪና ፀድቶ በነጭ ለባሽ እና በዘነጡ ሰዎች ተሞልቷል ፡፡በጎዳናው ሞልቶ ሲርመሰመስ ይውል የነበረውን የመኪና ቁጥር በ75 ፐርሰንት ቀንሶ ሀገሩ ሁሉ እግረኛ ሆኗ ነበር፡፡መንገዶች ሁሉ በባንዲራና በባነር አሸብርቀው አገሪቱ ልጇን ድራ ሰርግ ላይ ያለች ነው የሚመስለው፡፡ እንደሚታወቀው ጥምቀት ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚከበር በባህላዊ ኩነቶች የደመቀ በአዳባባይ የሚከበር ሀይማኖታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡ከእነዚህ ሶስት ቀኖች ደግሞ ዋናው ማለት ጥር 11 ኑሀሚ እና የናኦል የልደት ቀናቸው ነው፡፡ ይህቺን ምድር የተቀላቀሉባት የልደት ቀናቸው በተመሳሳይ ደግሞ እናትና አባታቸውን በሞት ያጡበት የሀዘን ቀን ነው ፡፡በወቅቱ የ11 አመት ዕድሜ ያላቸው ኑሀሚ እና ናኦል ከምልአተ ህዝቡ በተቃራኒ ሁሉም ወደጇል ሜዳ ሲተም እነሱ ከከተማው ግርግር ተገልለው የተለየ ቦታ ነበር የሄድት ፡፡ ትዝ ይላታል በእጃቸው አንድ አንድ ሻማ ይዘው ዮሴፍ ቤተክርስቲያ እናትና አባታቸው መቃብርን መሀከል ከንፈራቸውን በኩርፊያ ጣጥለው ቁጭ ብለዋል፡፡
በወቅቱ እዛ መቃብር ስፍራ የተገኙት አመት በዓል ስለሆነ እና በአሉን ደግሞ የሚያደምቁላቸው ወላጆቻቸው በህይወት ስለሌሉ ብቻ አልነበረም፡፡እርግጥም አንደኛው ምክንያት ያ ነው… ግን ደግሞ ሌላም ተጨማሪ ምክንያት ነበራቸው፡፡በእለቱ የሁለቱም ልደት ነው፡፡እርግጥ ናኦል ከልጅነቱ ጀምሮ ልደትን ስለማክበር ብዙም ግድ የለውም ኑሀሚ ግን እንደዛ አይደለችም፡፡ኑሀሚ እና ናኦል ልክ ጥር 11 እናታቸው የሰፈራቸውን ታቦት ከጃልሜዳ ጀምራ አጅባ አስገብታ ወደቤት ከተመለሰች በኋላ ደከመኝ ብላ አረፍ እንዳለች ነበር አስር ሰዓት አካባቢ ምጧ ተፋፍሞ አካባቢው ወደአለ ጤና ጣቢያ የተወሰደችው፡፡ከዛ 11 ሰዓት መጀመሪያ ናኦል ከ10 ደቂቃ ቆይታ በኃላ ደግሞ ኑሀሚ ተወለደች፡፡
በወቅቱ ያሉበትን የተገሳቆለ ሁኔታ ለሚመለከታቸው ሰው ግን ሁለቱም እንኳን የልደት በዓል ሊያከብሩ ልደትም ያላቸው አይመስሉም ነበር፡፡ እሷም ሆነች ወንድሟም የለበሱት ልብስ እላያቸው ላይ ተቀዳዶ እርቃን ለመሆን ትንሽ የቀረው ነበር ፡፡ከመራቋታቸውም በተጨማሪ የሰውነታቸው አጥንት በቀላሉ አንድ ሁለት ተብሏ የሚቆጠር እና ፊታቸው በአቧራና በቆሻሻ ተሸፍኖ ገፅታቸውን በግልጽ መለየት የማይቻልበት የጉስቁልና ደረጃ ላይ ነበር የሚገኙት፡፡ቢሆንም ግን ሰው ናቸውና..እስትንፋስም በውስጣቸው እየተፈራገጠች ነውና አንዳቸው የአንዳቸውን ልደት እያከበሩ ወላጆቻቸውን ሊያስታውሱ በቀኑና በትክክለኛው ቦታ ተገኝተዋል፡፡ሁለቱም ትናንት ቀኑን ሙሉ ለምነው ባጠራቁሙት ብር አንድ አንድ ሻማ ገዝተዋል፡፡ እሷ ሻማውን የገዛችው ለወላጆቹ ሙት አመት መታሰቢያ ለማብራት ሲሆን ወንድሟ ናኦል ደግሞ ሻማውን የገዛው የእሷ የልደት ክብረበዓልን ለማክበር ነበር፡፡
‹‹ኑሀሚ…እማዬ ነች ወይስ አባዬ ነው በጣም የናፈቀሽ?››ብሎ ነበር የጠየቃት፡፡
ያ ጥያቄ ከምትወደው ወንድሟ አንደበት ሲወጣ ምን አይነት ጥልቅ ሀዘን ተሰምቷት እንደነበር ዛሬም ድረስ ስሜቱ ልቧ ላይ አለ…በወቅቱ ለጥያቄው መልስ ከመስጠቷ በፊት እንባ ባቀረዘዙ አይኖቾን ለረጅም ደቂቃዎች ነበር ወንድሟን አትኩራ ያየችው፣ከዛ ቅዝዝ ብላ‹‹ሁለቱም ናቸው የናፈቁኝ፡፡እማዬና አባዬ ብቻ ሳይሆኑ የድሮ ቤታችንም ጭምር ናፍቆኛል፡፡ የድሮ አንተም ናፈቀኸኛል፡፡››ብላ ነበር የመለሰችለት፡፡
እሱም በአንደኛው ጉንጩ ብቻ እንባው እያረገፈ…‹‹እኔም ሁሌ እንዲህ ልብስሽ ተቀዳዶ እና ቆሽሾ ሳይሽ አዝናለሁ፡፡….እነአባዬ እያሉ ትለብሻቸው የነበሩ ልብሶች ትዝ ይሉኛል፡፡ፀጉርሽን ተሰርተሸ ቆንጆ ጫማ አድርገሽ አስብሽና በጣም ትናፍቂኛለች፡፡ሁሌ በህልሜ አንቺን ሳይ እንደዛ ቆንጆ ሆነሽ ነው የማይሽ..፡፡››ነበር ያላት፡፡ያ ንግግሩ ደግሞ ይበልጥ ስሜቷ እንዲደፈራርስና አምርራ እንድታለቅስ ነበር ያደረጋት፡፡ከዛ እንደምንም ለመረጋጋት ከሞከረች በኃላ ‹‹ናኦሌ፡፡››ስትል ጠራችው፡
‹‹ወዬ››
‹‹አሁን እንዲህ ልብሴ ስለተቀዳደደ እና ስለቆሸሽኩ አትወደኝም እንዴ?››ብላ የቆረቆራትን ጉዳይ እንደጠየቀችው ትዝ ይላታል፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ኢትዬጵያ/አዲስ አበባ
ትዝ ይላታል ከነበሩበት የማደጎ ቤት ወጥተው በረንደ መኖር ከጀመሩ ከአመት በኃላ ነው፡፡እለቱ የጥምቀት በዓል የሚከበርበት እለት ነበር፡፡ከተማው ከወቶሮዋ በተለይ መልኩ ከመኪና ፀድቶ በነጭ ለባሽ እና በዘነጡ ሰዎች ተሞልቷል ፡፡በጎዳናው ሞልቶ ሲርመሰመስ ይውል የነበረውን የመኪና ቁጥር በ75 ፐርሰንት ቀንሶ ሀገሩ ሁሉ እግረኛ ሆኗ ነበር፡፡መንገዶች ሁሉ በባንዲራና በባነር አሸብርቀው አገሪቱ ልጇን ድራ ሰርግ ላይ ያለች ነው የሚመስለው፡፡ እንደሚታወቀው ጥምቀት ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚከበር በባህላዊ ኩነቶች የደመቀ በአዳባባይ የሚከበር ሀይማኖታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡ከእነዚህ ሶስት ቀኖች ደግሞ ዋናው ማለት ጥር 11 ኑሀሚ እና የናኦል የልደት ቀናቸው ነው፡፡ ይህቺን ምድር የተቀላቀሉባት የልደት ቀናቸው በተመሳሳይ ደግሞ እናትና አባታቸውን በሞት ያጡበት የሀዘን ቀን ነው ፡፡በወቅቱ የ11 አመት ዕድሜ ያላቸው ኑሀሚ እና ናኦል ከምልአተ ህዝቡ በተቃራኒ ሁሉም ወደጇል ሜዳ ሲተም እነሱ ከከተማው ግርግር ተገልለው የተለየ ቦታ ነበር የሄድት ፡፡ ትዝ ይላታል በእጃቸው አንድ አንድ ሻማ ይዘው ዮሴፍ ቤተክርስቲያ እናትና አባታቸው መቃብርን መሀከል ከንፈራቸውን በኩርፊያ ጣጥለው ቁጭ ብለዋል፡፡
በወቅቱ እዛ መቃብር ስፍራ የተገኙት አመት በዓል ስለሆነ እና በአሉን ደግሞ የሚያደምቁላቸው ወላጆቻቸው በህይወት ስለሌሉ ብቻ አልነበረም፡፡እርግጥም አንደኛው ምክንያት ያ ነው… ግን ደግሞ ሌላም ተጨማሪ ምክንያት ነበራቸው፡፡በእለቱ የሁለቱም ልደት ነው፡፡እርግጥ ናኦል ከልጅነቱ ጀምሮ ልደትን ስለማክበር ብዙም ግድ የለውም ኑሀሚ ግን እንደዛ አይደለችም፡፡ኑሀሚ እና ናኦል ልክ ጥር 11 እናታቸው የሰፈራቸውን ታቦት ከጃልሜዳ ጀምራ አጅባ አስገብታ ወደቤት ከተመለሰች በኋላ ደከመኝ ብላ አረፍ እንዳለች ነበር አስር ሰዓት አካባቢ ምጧ ተፋፍሞ አካባቢው ወደአለ ጤና ጣቢያ የተወሰደችው፡፡ከዛ 11 ሰዓት መጀመሪያ ናኦል ከ10 ደቂቃ ቆይታ በኃላ ደግሞ ኑሀሚ ተወለደች፡፡
በወቅቱ ያሉበትን የተገሳቆለ ሁኔታ ለሚመለከታቸው ሰው ግን ሁለቱም እንኳን የልደት በዓል ሊያከብሩ ልደትም ያላቸው አይመስሉም ነበር፡፡ እሷም ሆነች ወንድሟም የለበሱት ልብስ እላያቸው ላይ ተቀዳዶ እርቃን ለመሆን ትንሽ የቀረው ነበር ፡፡ከመራቋታቸውም በተጨማሪ የሰውነታቸው አጥንት በቀላሉ አንድ ሁለት ተብሏ የሚቆጠር እና ፊታቸው በአቧራና በቆሻሻ ተሸፍኖ ገፅታቸውን በግልጽ መለየት የማይቻልበት የጉስቁልና ደረጃ ላይ ነበር የሚገኙት፡፡ቢሆንም ግን ሰው ናቸውና..እስትንፋስም በውስጣቸው እየተፈራገጠች ነውና አንዳቸው የአንዳቸውን ልደት እያከበሩ ወላጆቻቸውን ሊያስታውሱ በቀኑና በትክክለኛው ቦታ ተገኝተዋል፡፡ሁለቱም ትናንት ቀኑን ሙሉ ለምነው ባጠራቁሙት ብር አንድ አንድ ሻማ ገዝተዋል፡፡ እሷ ሻማውን የገዛችው ለወላጆቹ ሙት አመት መታሰቢያ ለማብራት ሲሆን ወንድሟ ናኦል ደግሞ ሻማውን የገዛው የእሷ የልደት ክብረበዓልን ለማክበር ነበር፡፡
‹‹ኑሀሚ…እማዬ ነች ወይስ አባዬ ነው በጣም የናፈቀሽ?››ብሎ ነበር የጠየቃት፡፡
ያ ጥያቄ ከምትወደው ወንድሟ አንደበት ሲወጣ ምን አይነት ጥልቅ ሀዘን ተሰምቷት እንደነበር ዛሬም ድረስ ስሜቱ ልቧ ላይ አለ…በወቅቱ ለጥያቄው መልስ ከመስጠቷ በፊት እንባ ባቀረዘዙ አይኖቾን ለረጅም ደቂቃዎች ነበር ወንድሟን አትኩራ ያየችው፣ከዛ ቅዝዝ ብላ‹‹ሁለቱም ናቸው የናፈቁኝ፡፡እማዬና አባዬ ብቻ ሳይሆኑ የድሮ ቤታችንም ጭምር ናፍቆኛል፡፡ የድሮ አንተም ናፈቀኸኛል፡፡››ብላ ነበር የመለሰችለት፡፡
እሱም በአንደኛው ጉንጩ ብቻ እንባው እያረገፈ…‹‹እኔም ሁሌ እንዲህ ልብስሽ ተቀዳዶ እና ቆሽሾ ሳይሽ አዝናለሁ፡፡….እነአባዬ እያሉ ትለብሻቸው የነበሩ ልብሶች ትዝ ይሉኛል፡፡ፀጉርሽን ተሰርተሸ ቆንጆ ጫማ አድርገሽ አስብሽና በጣም ትናፍቂኛለች፡፡ሁሌ በህልሜ አንቺን ሳይ እንደዛ ቆንጆ ሆነሽ ነው የማይሽ..፡፡››ነበር ያላት፡፡ያ ንግግሩ ደግሞ ይበልጥ ስሜቷ እንዲደፈራርስና አምርራ እንድታለቅስ ነበር ያደረጋት፡፡ከዛ እንደምንም ለመረጋጋት ከሞከረች በኃላ ‹‹ናኦሌ፡፡››ስትል ጠራችው፡
‹‹ወዬ››
‹‹አሁን እንዲህ ልብሴ ስለተቀዳደደ እና ስለቆሸሽኩ አትወደኝም እንዴ?››ብላ የቆረቆራትን ጉዳይ እንደጠየቀችው ትዝ ይላታል፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍50❤45👏4😱4😁1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ጥያቄዋ እሱን በጣም ነበረ ያሳቀቀው ፤ ወዲያው ነበር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ወደእሷ የተጠጋው፡፡ከዛ ከጎኗ ተቀመጠና ወደራሱ ስቦ አቀፋት..በዛ ልስልስና ጣፋጭ አንደበቱ‹‹እንደውም በጣም የምወድሽማ አሁን ነው፡፡በጣም እኮ ነው የምታሳዝኚኝ፡፡አንቺ ብቻ ነሽ እኮ ያለሺን፡፡እንዴት አንቺን ላለመወደድ እችላለሁ?ከአንቺ ውጭ እኮ ምንም ነገር የለኝም፡፡››ብሎ በመረረና በጠነከረ ንግግር ስለፍቅሩ ጥልቀት አስረዳት፡፡
በጣም ነበር ያሳዘናት‹‹አንተም እነአባቢን ተከትለህ ጥለኸኝ ሄደህ ቢሆን ኖሮ ምን እሆን ነበር….?››አለችው ፡፡ያንን ስትለው መላ ሰውነቷ በፍራቻ እየተንቀጠቀጠባት እንደነበረ ትዝ ይላታል፡፡ናኦል ከገቡበት ከጨላማ ውስጥ ከሚመዘዝ የትዝታ ጉዞ በከፊልም ቢሆን እንዲወጡ ፈለገና የጫወታቸውን ርዕስ ቀየረ፡፡‹‹በቃ አሁን ልደሽን እናክብር….››አላት
‹‹ልደቱ የእኔ ብቻ ነው እንዴ…?የሁለታችንም እኮ ነው፡፡››
‹‹ታውቂያለሽ እኔ ልደቴን ማክበር እንደማልወድ››
‹‹እንዳልክ እሺ… ግን መጀመሪያ የእኔን ሻማ እንለኩስና የእነአባቢን የሙት አመት መታሰቢያ እናክብር››ብላ መለሰችለት፡፡
እሱ ግን‹‹አይ ልደቱም ሀዘኑም የእኛው አይደል ..ሁለቱንም ሻማዎች አንድ ላይ እንለኩሳቸው››አላት
አልተከራከረችውም‹‹ ክብሪቱን የት አደረከው?››
ከኪሱ ውስጥ ፈልጎ አወጣና ሰጣት ..ጫረችና የመጀመሪያውን የራሷን ሻማ በመለኮስ አባቷ መቃብር ላይ በማንጠባጠብ እረሱን ችሎ እንዲቆም አደረገች፡፡ከዛ ሌለናውን ሻማ ከወንድሟ እጅ ተቀበለችና ለኩሳ ወደግራዋ ዞራ እናቷ መቃብር ላይ በተመሳሳይ መልኩ አስቀመጠች፡፡በመቀጠል የራሷን የተቀዳደደ የጃኬት ኪስ ፈተሸችና ሁለት ብስኩት አወጣች፡፡ወደ ወንድሟ በስስት እያየች‹‹ወንድሜ ለልደቴ ሻማ ስለለኮስክልኝ አመሰግናለው .. ለእንተም መልካም ልደት ይሁንልህ..ለእኔ ስትል አብረኸኝ ስለተወለድክ አመሰግናለው፡፡››አለችውና ከኪሷ ያወጣችውን ብስኩት እጁ ላይ አደረገች፡፡
ትዝ ይላታል በጣም ነበር ደስ ያለው፡፡ያንን ብስኩት መያዟን አያውቅም ነበር፡፡ሳንቲሙን ከየት አግኝታ? መቼ ገዝታ? እንዴት ከእሱ ደብቃ ይዛ እንደመጣች አያውቅም፡፡እሱም ግን ሊያስደምማት ለሳምንት ሲያስብበት ነበረ፡፡እጁን ወደኪሱ ሰደደና አንድ ቸኮሌትና አንድ ጦር ማስቲካ በማውጣት .‹‹እህቴ እንኳን ተወለድሽ..ደግሞ ልደቱን የሚያከብር ሰው ስጦታ ይቀበላል እንጂ ስጦታ አይሰጥም›› ብሎ እጆ ላይ አስቀመጠላት፡፡
ኑሀሚ ቸኮሌትና መስቲካውን በጣም እንደምትወደው ያውቃል፡፡ ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ እናትዬው የመስቲካ ሱሰኛ አባትዬው ደግሞ የቸኮሌት ሱሰኛ አድርገዋት ነበር፡፡ያኔ በሰላሙ ጊዜ በቀን ሁለቴ ወይም ሶስቴ ሰበብ እየፈጠረች ታለቅስ ነበር፡፡ለቅሶዋን ምታቆመው ደግሞ ወይ ቸኮሌት ወይም ደግሞ መስቲካ ሲሰጣት ብቻ ነበር፡፡ይሄም በደንብ ስለሚታወቅ ቀደም ተብሎ ይገዛና ተደብቆ ይቀመጥላታል፡፡ …..እና በወቅቱ የወንድሟ ስጦታ እናትና አባቷን በአንድ ላይ በጥልቀት እንድታስታውስ ነበር ያደረጋት፡፡ መልካቸው ብቻ ሳይሆን ጠረናቸውም ነበር ትዝ ያላት፡፡
‹‹ወንድሜ በጣም ነው ያስደሰትከኝ፡፡አንተ ስላለህልኝ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹እህቴ ስናድግ የቸኮሌት ፋብሪካ ይኖረኛል፡፡እና ያንን ፋብሪካ ላንቺ ስል ነው የምከፍተው፡፡ሁል ጊዜ የፈለግሽውን ያህል ቸኮሌት መብላት እንድትቺይ እፈልጋለሁ፡፡››ሲል ከጥልቅ ልቡ የመነጨውን ምኞቱን በፍቅር እና በስስት አይን አይኗን እያየ ነበር ቃል የገባላት፡፡ወደእዚህ አሁን ወዳለችበት ደቡብ አሜሪካ ከመምጣቷ በፊት ወንድሟ የዛን ጊዜ በልጅነታቸው ቃል የገባላትን ቸኮሌት ፋብሪካ ለመገንባት ማሽኑ የሚተከልበትን ዌርሀውስ ማስገንባት ጀምሮ ነበር፡፡ምን አልባት እስከአሁን አጠናቆትም ሊሆን ይችላል፡፡በጣም የሚያሳዝነውና መራሩ ሀቅ ግን ቸኮሌት ፋብሪካው ተተክሎ ማምረት ቢጀምር እንኳን እህቱን ማብላት አይችልም፡፡እህቱን በሰው ሀገር ምድር ላይ በሞት መነጠቋን ካወቀ ፋብሪካውን ያቃጥለዋል፡፡በዛ እርግጠኛ ነች፡፡
በወቅቱ በዛ የልጅነት ጊዜያቸው በወላጆቻቸው መቃብር ስር ስለቸኮሌት ፋብሪካው ቃል ሲገበላት‹‹ወንድሜ ቸኮሌት ፋብሪካ ለመክፈት እኮ ብዙ ብር ነው የሚያስፈልገው…ሀብታም መሆን አለብህ..ያ እንዴት ሊሆን ይችላል? ፡፡››ብላ ነበር የጠየቀችው፡፡
ወንድሟ እጆቹን ዘርግቶ ግራና ቀኝ ትከሻዋን በመያዝ ትኩር ብሎ አይኖቹን አይኖቾ ላይ ተክሎ‹‹አዎ ሀብታም መሆን አለብኝ፡፡እኔ ብቻ ሳልሆን አንቺም ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡ለእኛ ሀብታም መሆን የግድ ነው፡፡እኔ ላንቺ ስል ሀብታምና ብዙ ብር ያለው ሰው መሆን እፈልጋለሁ፡፡አንቺም ለእኔ ስትይ እንደዛው ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡››ነበር ያላት
‹‹እንዴት ግን..?ትምህርታችንን ከሶስተኛ ክፍል እንዳቋረጥን ነው፡፡ሳንማር እንዴት ነው ሀብታም ልንሆን የምንችለው?››
‹‹እንችላለን፡፡ማለቴ ሳይማሩ ሀብታም መሆን የሚቻል ይመስለኛል፡፡ያለበለዚያ ቡዙ የተማሩ ሆነው ምንም ብር የሌለቸውና አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች ደግሞ ሀብታሞች ሆነው አናገኝም ነበር፡፡አዎ እንዴት እንደሆነ ለጊዜው ባላውቅም ሳይማሩም ሀብታም መሆን እንደሚቻል እርግጠኛ ነኝ፡፡››አላት፡፡
አዎ..የወደፊት ህልማቸውን በተመለከተ ወንድሟ የሚያወራው ነገር በጣም መሳጭ እና አጓጊ ሆኖ ነበር ያገኘችው፡፡ቢሆንም ግን እንዴት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል በወቅቱ ምንም ፍንጭ አልታያትም፡፡ግን ደግሞ የወንድሟን ንግግር የሞኝ ቅዠት አድርጋም አልወሰደችውም፡፡ ወንድሟን አይደለም በዛን ጊዜ አሁንም ታምነዋለች፡፡ከፍቅር የመነጨ እምነት፡፡
እርግጥ እሷም ከእሱ ጋር ተቀራራቢ የሆነ ሀሳብ ሁሌ በውስጧ ታሰላስል ነበር፡፡ስታድግ የተወለዱበትንና ያደጉበትን የወላጆቾን ቤት መልሳ መግዛት የዘወትር ምኞቷ ነበር፡፡አዎ በወቅቱ እቤቱን የአባታቸው የልብ ጓደኛው በነበረ ሰው ባለቤትነት ተይዟል፡፡ ወላጆቻቸው ሞተው ወር እንኳን ሳይሞላው ነበር ከመሟቱ በፊት ለስራ ብሎ ብዙ ሚሊዬን ብር ተበድሮኛል ብሎ የተናገረው፡፡ብዙም ሳይቆይ የተናገረውን የሚያረጋግጥለት ሰንድ አቀረበ፡፡ከዛ በቀላሉ በፍርድ ቤት ከሶ ወላጆቻቸው ሞተው በተቀበሩ በሶስተኛው ወር እቤቱን ተረክበ፡፡ለእነሱ ቀርቦ የሚከራከርላቸውም ሆነ ወስዶ የሚያሳድጋቸው አንድም ዘመድ መቅረብ ስላልቻለ …ሰውዬው ጎዳና ጣላቸው የሚለውን የሰው አፍ ብቻ በመፍራት ወስዶ ለማደጎ ቤት አስረከባቸው፡፡ኑሀሚ በዛ ጮርቃ እድሜዋ ላይ ሆና እንኳን ያ ሁሉ የተወሳሰበ ቲያትር መሰል አሻጥር ፈፅሞ አይዋጥላትም ነበር፡፡ያንን ቤት በጣም ትወደዋለች፡፡ልጅነቷ ያለው እዛ ቤት ውስጥ ነው፡፡ሳቅና ደስታዋ እዛ ቤት የሆነ ቁምሳጥን ወይም የኮመዲኖ ኪስ ውስጥ የተቆመለፈበት ነበር የሚመስላት፡፡እና አንድ ቀን ተሳክቶላት ያንን ቤት ማስመለስና የራሳቸው ማድረግ ብትችል እናትና አባቷንም በከፊልም ቢሆን ከሞት አለም ማስመለስ እንደሆነ አድርጋ ነበር የምትቆጥረው ፡፡ዘወትር ትንሽ በከፋት ቁጥር የሚተኙበትን መኝታ ቤት ትዝ ይላታል፤እናቷ ምግብ የምታበስልበት ኪችን ሙሉ ስዕሉ በአእምሮዋ ይመላለስባት ነበር፡፡አባቷ በእረፍት ቀኑ ቢጃማ ለብሶ በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ሲያነብ …እሷ ድክ ድክ እያለች ከሳሎን መጥታ ታፋው ላይ በመቀመጥ ከኪሱ ስልኩን አውጥታ ጌም ስትጫወት….
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ጥያቄዋ እሱን በጣም ነበረ ያሳቀቀው ፤ ወዲያው ነበር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ወደእሷ የተጠጋው፡፡ከዛ ከጎኗ ተቀመጠና ወደራሱ ስቦ አቀፋት..በዛ ልስልስና ጣፋጭ አንደበቱ‹‹እንደውም በጣም የምወድሽማ አሁን ነው፡፡በጣም እኮ ነው የምታሳዝኚኝ፡፡አንቺ ብቻ ነሽ እኮ ያለሺን፡፡እንዴት አንቺን ላለመወደድ እችላለሁ?ከአንቺ ውጭ እኮ ምንም ነገር የለኝም፡፡››ብሎ በመረረና በጠነከረ ንግግር ስለፍቅሩ ጥልቀት አስረዳት፡፡
በጣም ነበር ያሳዘናት‹‹አንተም እነአባቢን ተከትለህ ጥለኸኝ ሄደህ ቢሆን ኖሮ ምን እሆን ነበር….?››አለችው ፡፡ያንን ስትለው መላ ሰውነቷ በፍራቻ እየተንቀጠቀጠባት እንደነበረ ትዝ ይላታል፡፡ናኦል ከገቡበት ከጨላማ ውስጥ ከሚመዘዝ የትዝታ ጉዞ በከፊልም ቢሆን እንዲወጡ ፈለገና የጫወታቸውን ርዕስ ቀየረ፡፡‹‹በቃ አሁን ልደሽን እናክብር….››አላት
‹‹ልደቱ የእኔ ብቻ ነው እንዴ…?የሁለታችንም እኮ ነው፡፡››
‹‹ታውቂያለሽ እኔ ልደቴን ማክበር እንደማልወድ››
‹‹እንዳልክ እሺ… ግን መጀመሪያ የእኔን ሻማ እንለኩስና የእነአባቢን የሙት አመት መታሰቢያ እናክብር››ብላ መለሰችለት፡፡
እሱ ግን‹‹አይ ልደቱም ሀዘኑም የእኛው አይደል ..ሁለቱንም ሻማዎች አንድ ላይ እንለኩሳቸው››አላት
አልተከራከረችውም‹‹ ክብሪቱን የት አደረከው?››
ከኪሱ ውስጥ ፈልጎ አወጣና ሰጣት ..ጫረችና የመጀመሪያውን የራሷን ሻማ በመለኮስ አባቷ መቃብር ላይ በማንጠባጠብ እረሱን ችሎ እንዲቆም አደረገች፡፡ከዛ ሌለናውን ሻማ ከወንድሟ እጅ ተቀበለችና ለኩሳ ወደግራዋ ዞራ እናቷ መቃብር ላይ በተመሳሳይ መልኩ አስቀመጠች፡፡በመቀጠል የራሷን የተቀዳደደ የጃኬት ኪስ ፈተሸችና ሁለት ብስኩት አወጣች፡፡ወደ ወንድሟ በስስት እያየች‹‹ወንድሜ ለልደቴ ሻማ ስለለኮስክልኝ አመሰግናለው .. ለእንተም መልካም ልደት ይሁንልህ..ለእኔ ስትል አብረኸኝ ስለተወለድክ አመሰግናለው፡፡››አለችውና ከኪሷ ያወጣችውን ብስኩት እጁ ላይ አደረገች፡፡
ትዝ ይላታል በጣም ነበር ደስ ያለው፡፡ያንን ብስኩት መያዟን አያውቅም ነበር፡፡ሳንቲሙን ከየት አግኝታ? መቼ ገዝታ? እንዴት ከእሱ ደብቃ ይዛ እንደመጣች አያውቅም፡፡እሱም ግን ሊያስደምማት ለሳምንት ሲያስብበት ነበረ፡፡እጁን ወደኪሱ ሰደደና አንድ ቸኮሌትና አንድ ጦር ማስቲካ በማውጣት .‹‹እህቴ እንኳን ተወለድሽ..ደግሞ ልደቱን የሚያከብር ሰው ስጦታ ይቀበላል እንጂ ስጦታ አይሰጥም›› ብሎ እጆ ላይ አስቀመጠላት፡፡
ኑሀሚ ቸኮሌትና መስቲካውን በጣም እንደምትወደው ያውቃል፡፡ ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ እናትዬው የመስቲካ ሱሰኛ አባትዬው ደግሞ የቸኮሌት ሱሰኛ አድርገዋት ነበር፡፡ያኔ በሰላሙ ጊዜ በቀን ሁለቴ ወይም ሶስቴ ሰበብ እየፈጠረች ታለቅስ ነበር፡፡ለቅሶዋን ምታቆመው ደግሞ ወይ ቸኮሌት ወይም ደግሞ መስቲካ ሲሰጣት ብቻ ነበር፡፡ይሄም በደንብ ስለሚታወቅ ቀደም ተብሎ ይገዛና ተደብቆ ይቀመጥላታል፡፡ …..እና በወቅቱ የወንድሟ ስጦታ እናትና አባቷን በአንድ ላይ በጥልቀት እንድታስታውስ ነበር ያደረጋት፡፡ መልካቸው ብቻ ሳይሆን ጠረናቸውም ነበር ትዝ ያላት፡፡
‹‹ወንድሜ በጣም ነው ያስደሰትከኝ፡፡አንተ ስላለህልኝ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹እህቴ ስናድግ የቸኮሌት ፋብሪካ ይኖረኛል፡፡እና ያንን ፋብሪካ ላንቺ ስል ነው የምከፍተው፡፡ሁል ጊዜ የፈለግሽውን ያህል ቸኮሌት መብላት እንድትቺይ እፈልጋለሁ፡፡››ሲል ከጥልቅ ልቡ የመነጨውን ምኞቱን በፍቅር እና በስስት አይን አይኗን እያየ ነበር ቃል የገባላት፡፡ወደእዚህ አሁን ወዳለችበት ደቡብ አሜሪካ ከመምጣቷ በፊት ወንድሟ የዛን ጊዜ በልጅነታቸው ቃል የገባላትን ቸኮሌት ፋብሪካ ለመገንባት ማሽኑ የሚተከልበትን ዌርሀውስ ማስገንባት ጀምሮ ነበር፡፡ምን አልባት እስከአሁን አጠናቆትም ሊሆን ይችላል፡፡በጣም የሚያሳዝነውና መራሩ ሀቅ ግን ቸኮሌት ፋብሪካው ተተክሎ ማምረት ቢጀምር እንኳን እህቱን ማብላት አይችልም፡፡እህቱን በሰው ሀገር ምድር ላይ በሞት መነጠቋን ካወቀ ፋብሪካውን ያቃጥለዋል፡፡በዛ እርግጠኛ ነች፡፡
በወቅቱ በዛ የልጅነት ጊዜያቸው በወላጆቻቸው መቃብር ስር ስለቸኮሌት ፋብሪካው ቃል ሲገበላት‹‹ወንድሜ ቸኮሌት ፋብሪካ ለመክፈት እኮ ብዙ ብር ነው የሚያስፈልገው…ሀብታም መሆን አለብህ..ያ እንዴት ሊሆን ይችላል? ፡፡››ብላ ነበር የጠየቀችው፡፡
ወንድሟ እጆቹን ዘርግቶ ግራና ቀኝ ትከሻዋን በመያዝ ትኩር ብሎ አይኖቹን አይኖቾ ላይ ተክሎ‹‹አዎ ሀብታም መሆን አለብኝ፡፡እኔ ብቻ ሳልሆን አንቺም ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡ለእኛ ሀብታም መሆን የግድ ነው፡፡እኔ ላንቺ ስል ሀብታምና ብዙ ብር ያለው ሰው መሆን እፈልጋለሁ፡፡አንቺም ለእኔ ስትይ እንደዛው ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡››ነበር ያላት
‹‹እንዴት ግን..?ትምህርታችንን ከሶስተኛ ክፍል እንዳቋረጥን ነው፡፡ሳንማር እንዴት ነው ሀብታም ልንሆን የምንችለው?››
‹‹እንችላለን፡፡ማለቴ ሳይማሩ ሀብታም መሆን የሚቻል ይመስለኛል፡፡ያለበለዚያ ቡዙ የተማሩ ሆነው ምንም ብር የሌለቸውና አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች ደግሞ ሀብታሞች ሆነው አናገኝም ነበር፡፡አዎ እንዴት እንደሆነ ለጊዜው ባላውቅም ሳይማሩም ሀብታም መሆን እንደሚቻል እርግጠኛ ነኝ፡፡››አላት፡፡
አዎ..የወደፊት ህልማቸውን በተመለከተ ወንድሟ የሚያወራው ነገር በጣም መሳጭ እና አጓጊ ሆኖ ነበር ያገኘችው፡፡ቢሆንም ግን እንዴት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል በወቅቱ ምንም ፍንጭ አልታያትም፡፡ግን ደግሞ የወንድሟን ንግግር የሞኝ ቅዠት አድርጋም አልወሰደችውም፡፡ ወንድሟን አይደለም በዛን ጊዜ አሁንም ታምነዋለች፡፡ከፍቅር የመነጨ እምነት፡፡
እርግጥ እሷም ከእሱ ጋር ተቀራራቢ የሆነ ሀሳብ ሁሌ በውስጧ ታሰላስል ነበር፡፡ስታድግ የተወለዱበትንና ያደጉበትን የወላጆቾን ቤት መልሳ መግዛት የዘወትር ምኞቷ ነበር፡፡አዎ በወቅቱ እቤቱን የአባታቸው የልብ ጓደኛው በነበረ ሰው ባለቤትነት ተይዟል፡፡ ወላጆቻቸው ሞተው ወር እንኳን ሳይሞላው ነበር ከመሟቱ በፊት ለስራ ብሎ ብዙ ሚሊዬን ብር ተበድሮኛል ብሎ የተናገረው፡፡ብዙም ሳይቆይ የተናገረውን የሚያረጋግጥለት ሰንድ አቀረበ፡፡ከዛ በቀላሉ በፍርድ ቤት ከሶ ወላጆቻቸው ሞተው በተቀበሩ በሶስተኛው ወር እቤቱን ተረክበ፡፡ለእነሱ ቀርቦ የሚከራከርላቸውም ሆነ ወስዶ የሚያሳድጋቸው አንድም ዘመድ መቅረብ ስላልቻለ …ሰውዬው ጎዳና ጣላቸው የሚለውን የሰው አፍ ብቻ በመፍራት ወስዶ ለማደጎ ቤት አስረከባቸው፡፡ኑሀሚ በዛ ጮርቃ እድሜዋ ላይ ሆና እንኳን ያ ሁሉ የተወሳሰበ ቲያትር መሰል አሻጥር ፈፅሞ አይዋጥላትም ነበር፡፡ያንን ቤት በጣም ትወደዋለች፡፡ልጅነቷ ያለው እዛ ቤት ውስጥ ነው፡፡ሳቅና ደስታዋ እዛ ቤት የሆነ ቁምሳጥን ወይም የኮመዲኖ ኪስ ውስጥ የተቆመለፈበት ነበር የሚመስላት፡፡እና አንድ ቀን ተሳክቶላት ያንን ቤት ማስመለስና የራሳቸው ማድረግ ብትችል እናትና አባቷንም በከፊልም ቢሆን ከሞት አለም ማስመለስ እንደሆነ አድርጋ ነበር የምትቆጥረው ፡፡ዘወትር ትንሽ በከፋት ቁጥር የሚተኙበትን መኝታ ቤት ትዝ ይላታል፤እናቷ ምግብ የምታበስልበት ኪችን ሙሉ ስዕሉ በአእምሮዋ ይመላለስባት ነበር፡፡አባቷ በእረፍት ቀኑ ቢጃማ ለብሶ በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ሲያነብ …እሷ ድክ ድክ እያለች ከሳሎን መጥታ ታፋው ላይ በመቀመጥ ከኪሱ ስልኩን አውጥታ ጌም ስትጫወት….
👍71❤8👎2👏2
‹‹ናሆሚ እስኪ ድምፁን ቀንሺ ላንብብበት..›› እያለ ሲቆጣት ሁሌ ነበር ድምጹ የሚሰማት……አዎ ስለዛ ቤት ብዙ ብዙ ነገር ትዝ ይላታል፡፡ትዝታ ደግሞ የሰው ልጅ ትልቁ ሀብቱ ነው፡፡የሰው ልጅ ህልውናው የሚረጋገጠው እኮ በሚታየው ስጋና አጥንቱ ብቻ አይደለም…በእስትንፋሱም አይደለም፤እነሱ ለብቻቸው ልክ እንደአንድ እንስሳ እንጂ እንደሰው እንዲታይ አያደርጉትም፡፡ዋናው ሰው መሆንን የሚያጎናፅፈን ያለፈ ህይወታችንን በትዝታ ቋት በማከማቸትና በምናብ መንኮራኩር ጊዜና ቦታ ሳይገድበን ወደነገ በመመንጠቅ ችሎታችን ነው፡፡ አንድ ሰው ትዝታው ከተደመሰሰና በምናብ ወደነገ የመጓዝ ችሎታው ከተዳከመ ምን እንደሚሆን አስብቱ..በቃ የለም ማለት እኮ ነው፡፡እከሌ በቁም ሞቷል ሚባለው እኮ እንደዚህ አይነት ጉዳይ ሲያጋጥመው ነው፡፡ትዝታው ሲዛባበትና ምናብ ሲከስምበት፡፡
በዛን የመከራ ጊዜቸው አንዳንዴ ወንድሟን ለምና ወደድሮ ሰፈራቸው ይዛው ትሄድና በሩቅ ሆነው ግቢውን ይዞሩት ነበር፡፡በስተመጨረሻ ግን በቁጭት ቆስለውና በንዴት በግነው እየተላቀሱ እና አንደኛው ሌላውን እያፅናኑ ሰፈሩን ለቀው ይመለሳሉ፡፡
ናኦል እሷ እያስገደደችው እንጂ እዛ ሰፈር መሄድ አይወድም ነበር፡፡ጭራሽ ስለእዛ ቤትም ማሰብ አይፈልግም….፡፡እሱ ያንን ቤት ወደፊት መልሼ ገዝቼ የእኛ አደረግዋለሁ የሚል ምኞት አልነበረም ያለው፡፡የእሱ እቅድ አንድ ቀን እንደምንም ሁለት- ሶስት ፈንጅ አግኝቼ ውስጡ እስከአሉት ሰዎች ማፈንዳትና አመድ ማድረግ በቻልኩ ብሎ ነበር የሚያስበው፡፡ስለቤታቸው ሲያስብ እልክ ፣ንዴትና የመዘረፍ ስሜት ነበር የሚያሰቃየው፡፡የተዘረፉት ንብረት ብቻ እንዳልሆነ ያውቃል፡፡እናትና አባታቸውንም ጭምር ተዘርፈዋል፡፡ ነገሩን ከእህቱ ጋ አንስቶ አያውራበት እንጂ የወላጆቹ ሞት ላይም ከፍተኛ ጥርጣሬ አለው፡፡ እራሳቸውን አጠፉ ነው የተባለው፡፡የገዛ መኝታቸው ላይ ማታ በተኙበት ጥዋት ደርቀው ነው የተገኙት ፡፡ከመጠን በላይ መድሀኒት በመውሰድዳቸው ለመሞታቸው ዋናው ምክንያት እንደሆነ በሀኪም ተረጋግጧል፡፡እርግጥ የዛን ሰሞን ጉንፋን መሰል በሽታ እንደወረርሺኝ ገብቶና እነሱም ታመው ስለነበረ…በተከታታይ የሚወስዱት መድሀኒት ነበር፡፡ግን እንዴት ለሞት እስኪዳርጋቸው ድረስ ከመጠን በላይ መድሀኒቱን ሊወስዱ ቻሉ…?ይሄ ናኦልን ብቻ ሳይሆን ብዙ ትላልቅ ሰዎች የማይመስል ነገር ነው ሲሉ ሰምቷል፡፡
ከወላጆቹ ግድያ ጀርባ ያለውን እውነት ለማጣራት ከፍተኛ ፍላጎት አለው፡፡ያንን ለማድረግ ደግሞ ኃይል ያለው፤ የተናገረው የሚደመጥለት፤ ያዘዘው የሚከወንለት፤ ቆፍጠን ያለ ሰው መሆን እንዳለበት ቀድሞ ነበር እየገባው ፡፡ኃይል ከስልጣን ወይ ከገንዘብ ነው የሚገኘው፡፡ያንን የጎዳና ህይወት ባሳለፋቸው ጊዜያቶች የተማረውና የገባው ነገር ነበር፡፡ለዛ ነው በወቅቱ ለገንዘብ ከፍተኛ ፍቅርና ፍላጎት ያደረበት፡፡
‹‹እህቴ ስሚኝ…እንማራለን፡፡ደግሞ እንዳልኩሽ ባንማርም በሆነ መንገድ ብቻ ሀብታም መሆን አለብን፡፡ግን ዋናው ሁሌ አብረን መሆናችን ነው ፡፡ መተሳሰብና መረዳዳት አለብን፡፡ሁለታችን ከተጋገዝን ያልኩሽን እናሳካለን፡፡›› ነበር ያላት
‹‹እሺ እንዳልክ፡፡››አለችና በድጋሚ ተንጠራርታ ጉንጮን ሳመችው፡፡ ..የሰጣትን ቸኮሌት ሽፋን ላጠችና ግማሹን ቆርሳ አቀበለችው፡፡
‹‹ኸረ እኔ ጣፋጭ እንደማልወድ አታውቂም፡፡ብስኩቱን ነው የምበላው፡፡›› በማለት የብስኩቱን ላስቲክ በጥርሶች መካከል አስገብቶ መቅደድ ጀመረ፡፡
‹‹ወንድሜ ደግሞ …ቸኮሌት አሁን እምቢ ይባላል?››
‹‹ላንቺ ነዋ እምቢ ማይባለው፡፡ለእኔ ይባላል፡፡.››እንደማኩረፍ አለችና ከቸኮሌቱ እየቆረሰች አፏ ውስጥ በመክተት ጣእሙን በፍቅር እና በጥሞና እያጣጣመች ትውጥ ጀመረ፡፡
እዛ ሲያወሩና ሲጫወቱ ዋሉና ፀሀዩ በረድ ማለት ሲጀምር ‹‹‹አሁን እነአባዬን ተሰናብተን እንሂድ..››አላት፡፡
ሁለቱም እናትና አባታቸው መቃብር መሀከል እንደተቀመጡ እጆቻቸውን እንደመስቀል ዘረጉ ..አንደኛውን መዳፋቸውን እናታቸው መቃብር ላይ ሌለኛውን ደግሞ አባታቸውን መቃብረ ላይ አደረጉ…ናኦል ነበር ቀድሞ ማውራት የጀመረው
‹‹እማ አባ..እኛ በጣም ሰላም ነን..እንዴት እየኖሩ ነው? ብላችሁ ስለእኛ አትጨነቁ፡፡እኔና አህቴ ጎበዞች ሆነናል፡፡ወደፊት ትልቅ ስንሆን ይሄንን የመቃብራችሁን ስፍራ በእብነበረድ የሚያምር አድርገን እናሰራላችኋለን፡፡ደግሞ እየመጣን እንጠይቃችኋለን፡፡››
ኑሀሚ ተቀበለችው
‹‹አዎ ወንድሜ እንዳለው..ስትናፍቁን እየመጣን እንጠይቃችኋለን፡፡ያው ቶሎ ቶሎ የማንመጣው እናንተም ሁለት ስለሆናችሁ እርስ በርስ እንደእኔ እና ወንድሜ እንደምታወሩና እንደምትጫወቱ ስለምናምን እና እንደማይደብራሁችሁ ስለምናውቅ ነው፡፡…በሉ መልካም ልደት ስላላችሁን ደስ ብሎናል፡፡ እንወዳችኃላን..አልፎ አልፎ ስትናፍቁን እየመጣን እንጠይቃችኋለን፡፡›› ንግግሯን አጠናቀቀችና የወንድሟን እጅ በመያዝ ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ቀስ እያሉ መቃብሩን ስፍራ ለቀው በዝግታ እርምጃ ማዝገም ጀመሩ፡፡
በትዝታው ወደኃላ ተመልሳ ጥልቅ ሀዘን ውስጥ በመግባት እንባዋን እያዘራች ባለችበት መጥፎ ሰዓት በርካታ የእግር ኮቴ፤የመሳሪያ ቅጭልጭልታ ወዲያው ደግሞ የበራፍ መከፈት ሰማች… በፍጥነት ጋደም ካለችበት ተነሳችና ተቀመጠች፡፡አንዱ ግማሽ ፊቱ በማረሻ የታረሰ ሚመስል አስፈሪ ፍጡር ገባና በእጁ እንድትነሳ ምልክት እየሰጣት በማይገባት ቋንቋ ለፈለፈ፡፡ቀልጠፍ ብላ ተነስታ ቆመች፡፡ወደእሷ ተራመደና ክንዷን ጨምድዶ በመያዝ ወደራሱ ጎተታት፡፡ደነገጠችም.. ተገረመችም፡፡እጁ በጣም ያማል፡፡እጁ ብቻ አይደለም ቁጣውና መኮሳተሩ እራሱ ያማል፡፡አንጠልጥሎ ከጎጆ አወጣትና ወረወራት፡፡ብዥ አለባት፡፡ከአስራ አምስት የሚበልጡ ፀጉራቸው የተንጨፈረረ..ጡንቻቸው የደደረና ፊታቸው የጨለመ ሰዎች ልክ የሆነ ክፍለ ጦር ለመዋጋት ዝግጁ ሆኖ እንደሚጓዝ አማፂ ብድን በሰልፍ ተሰልፈው ለጉዞ ዝግጁ ሆነዋል፡፡
በፊት ከምታውቃቸው ሌላ ቢያንስ 6 ተጫማሪ ገዳዬች ወደስብስቡ ተጨምረዋል፡፡ከደቂቃዎች በፊት የማምለጥ እድል ሊኖረኝ ይችላል በሚል ስታብሰለስለው የነበረው ዘዴና ውጥን ሁሉ እንደጉም በኖ ሲጠፋ ለራሷ ታወቃት፡፡እውነትም ያ ቅድም ምግብ ያቀረበላት ልጅ ጥሩ የሚባል የወዳጅ ምክር እንደመከራት አመነች፡፡ጥቂት እንኳን የማምለጥ ሙከራ ብትሞክር እንደፋሲካ ዶሮ አስራሁለት ቦታ እንደሚገነጣጥሎት እርግጠኛ ሆነችና ሽምቅቅ አለች፡፡ ምግብ አቅርቦላት የነበረው ወጣት ወደእሷ ቀረበና በቀደመ ጉዞቸው እንዳደረገው እጇ ላይ ታስሮ ስትጎትተው የነበረውን ሰንሰለት አነሳና ከራሱ እጅ ጋር አቆራኝቶ እንደድሮ ባሪያ እየጎተተ በመውሰድ ከሰልፉ መሀከል አስገባትና ከኃላዋ ሆነ ፡፡
ከጀርባ ያለ አንድ ድምፅ በማታውቀው ቋንቋ የሆኑ አረፍተ ነገሮችን ተናገረ፡፡ሁሉም መሳሪያቸውን ለመተኮስ በሚመስል መንገድ አስተካከሉ፡፡ ሊያደበላልቁት ነው ብላ ስትጠብቅ በዝግታ ፊት ያለው ሰው እርምጃውን ቀጠለ ከዛ እያንዳንዱ ሰልፉን እየጠበቀ መንቀሳቀስ ጀመረ..እሷም ልክ እንደሌሎቹ ፊት ያለውን በመመልከትና የእርምጃዋን ልክ በማስተካከል መጓዝ ጀመረች፡፡ጉዞው በጣም ፈታኝና አስቸጋሪ ነበር፡፡ከላይ ዝናብ ይዘንባል..ዝናቡ ቀጥታ ወርዶ መሬት አይነካም፡፡ እያዳንዱ ግዙፍ የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ያርፋል…፡፡ከዛ ኃይሉን እየቀነሰ ወደታች ይረግፍና ሰውነታቸውን ያርሳቸዋል፡፡አብዛኛው ልምድ ስላለው ለቦታው የሚገባ አለባበስ ነው የለበሱት፡፡እሷ ግን ወደኤርፖርት ልትሄድ በለበሰችው የተለመደ አይነት አለባበስ ነበረች፡፡ሰውነቷ ውስጥ አጥንት የሚሰረስር
በዛን የመከራ ጊዜቸው አንዳንዴ ወንድሟን ለምና ወደድሮ ሰፈራቸው ይዛው ትሄድና በሩቅ ሆነው ግቢውን ይዞሩት ነበር፡፡በስተመጨረሻ ግን በቁጭት ቆስለውና በንዴት በግነው እየተላቀሱ እና አንደኛው ሌላውን እያፅናኑ ሰፈሩን ለቀው ይመለሳሉ፡፡
ናኦል እሷ እያስገደደችው እንጂ እዛ ሰፈር መሄድ አይወድም ነበር፡፡ጭራሽ ስለእዛ ቤትም ማሰብ አይፈልግም….፡፡እሱ ያንን ቤት ወደፊት መልሼ ገዝቼ የእኛ አደረግዋለሁ የሚል ምኞት አልነበረም ያለው፡፡የእሱ እቅድ አንድ ቀን እንደምንም ሁለት- ሶስት ፈንጅ አግኝቼ ውስጡ እስከአሉት ሰዎች ማፈንዳትና አመድ ማድረግ በቻልኩ ብሎ ነበር የሚያስበው፡፡ስለቤታቸው ሲያስብ እልክ ፣ንዴትና የመዘረፍ ስሜት ነበር የሚያሰቃየው፡፡የተዘረፉት ንብረት ብቻ እንዳልሆነ ያውቃል፡፡እናትና አባታቸውንም ጭምር ተዘርፈዋል፡፡ ነገሩን ከእህቱ ጋ አንስቶ አያውራበት እንጂ የወላጆቹ ሞት ላይም ከፍተኛ ጥርጣሬ አለው፡፡ እራሳቸውን አጠፉ ነው የተባለው፡፡የገዛ መኝታቸው ላይ ማታ በተኙበት ጥዋት ደርቀው ነው የተገኙት ፡፡ከመጠን በላይ መድሀኒት በመውሰድዳቸው ለመሞታቸው ዋናው ምክንያት እንደሆነ በሀኪም ተረጋግጧል፡፡እርግጥ የዛን ሰሞን ጉንፋን መሰል በሽታ እንደወረርሺኝ ገብቶና እነሱም ታመው ስለነበረ…በተከታታይ የሚወስዱት መድሀኒት ነበር፡፡ግን እንዴት ለሞት እስኪዳርጋቸው ድረስ ከመጠን በላይ መድሀኒቱን ሊወስዱ ቻሉ…?ይሄ ናኦልን ብቻ ሳይሆን ብዙ ትላልቅ ሰዎች የማይመስል ነገር ነው ሲሉ ሰምቷል፡፡
ከወላጆቹ ግድያ ጀርባ ያለውን እውነት ለማጣራት ከፍተኛ ፍላጎት አለው፡፡ያንን ለማድረግ ደግሞ ኃይል ያለው፤ የተናገረው የሚደመጥለት፤ ያዘዘው የሚከወንለት፤ ቆፍጠን ያለ ሰው መሆን እንዳለበት ቀድሞ ነበር እየገባው ፡፡ኃይል ከስልጣን ወይ ከገንዘብ ነው የሚገኘው፡፡ያንን የጎዳና ህይወት ባሳለፋቸው ጊዜያቶች የተማረውና የገባው ነገር ነበር፡፡ለዛ ነው በወቅቱ ለገንዘብ ከፍተኛ ፍቅርና ፍላጎት ያደረበት፡፡
‹‹እህቴ ስሚኝ…እንማራለን፡፡ደግሞ እንዳልኩሽ ባንማርም በሆነ መንገድ ብቻ ሀብታም መሆን አለብን፡፡ግን ዋናው ሁሌ አብረን መሆናችን ነው ፡፡ መተሳሰብና መረዳዳት አለብን፡፡ሁለታችን ከተጋገዝን ያልኩሽን እናሳካለን፡፡›› ነበር ያላት
‹‹እሺ እንዳልክ፡፡››አለችና በድጋሚ ተንጠራርታ ጉንጮን ሳመችው፡፡ ..የሰጣትን ቸኮሌት ሽፋን ላጠችና ግማሹን ቆርሳ አቀበለችው፡፡
‹‹ኸረ እኔ ጣፋጭ እንደማልወድ አታውቂም፡፡ብስኩቱን ነው የምበላው፡፡›› በማለት የብስኩቱን ላስቲክ በጥርሶች መካከል አስገብቶ መቅደድ ጀመረ፡፡
‹‹ወንድሜ ደግሞ …ቸኮሌት አሁን እምቢ ይባላል?››
‹‹ላንቺ ነዋ እምቢ ማይባለው፡፡ለእኔ ይባላል፡፡.››እንደማኩረፍ አለችና ከቸኮሌቱ እየቆረሰች አፏ ውስጥ በመክተት ጣእሙን በፍቅር እና በጥሞና እያጣጣመች ትውጥ ጀመረ፡፡
እዛ ሲያወሩና ሲጫወቱ ዋሉና ፀሀዩ በረድ ማለት ሲጀምር ‹‹‹አሁን እነአባዬን ተሰናብተን እንሂድ..››አላት፡፡
ሁለቱም እናትና አባታቸው መቃብር መሀከል እንደተቀመጡ እጆቻቸውን እንደመስቀል ዘረጉ ..አንደኛውን መዳፋቸውን እናታቸው መቃብር ላይ ሌለኛውን ደግሞ አባታቸውን መቃብረ ላይ አደረጉ…ናኦል ነበር ቀድሞ ማውራት የጀመረው
‹‹እማ አባ..እኛ በጣም ሰላም ነን..እንዴት እየኖሩ ነው? ብላችሁ ስለእኛ አትጨነቁ፡፡እኔና አህቴ ጎበዞች ሆነናል፡፡ወደፊት ትልቅ ስንሆን ይሄንን የመቃብራችሁን ስፍራ በእብነበረድ የሚያምር አድርገን እናሰራላችኋለን፡፡ደግሞ እየመጣን እንጠይቃችኋለን፡፡››
ኑሀሚ ተቀበለችው
‹‹አዎ ወንድሜ እንዳለው..ስትናፍቁን እየመጣን እንጠይቃችኋለን፡፡ያው ቶሎ ቶሎ የማንመጣው እናንተም ሁለት ስለሆናችሁ እርስ በርስ እንደእኔ እና ወንድሜ እንደምታወሩና እንደምትጫወቱ ስለምናምን እና እንደማይደብራሁችሁ ስለምናውቅ ነው፡፡…በሉ መልካም ልደት ስላላችሁን ደስ ብሎናል፡፡ እንወዳችኃላን..አልፎ አልፎ ስትናፍቁን እየመጣን እንጠይቃችኋለን፡፡›› ንግግሯን አጠናቀቀችና የወንድሟን እጅ በመያዝ ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ቀስ እያሉ መቃብሩን ስፍራ ለቀው በዝግታ እርምጃ ማዝገም ጀመሩ፡፡
በትዝታው ወደኃላ ተመልሳ ጥልቅ ሀዘን ውስጥ በመግባት እንባዋን እያዘራች ባለችበት መጥፎ ሰዓት በርካታ የእግር ኮቴ፤የመሳሪያ ቅጭልጭልታ ወዲያው ደግሞ የበራፍ መከፈት ሰማች… በፍጥነት ጋደም ካለችበት ተነሳችና ተቀመጠች፡፡አንዱ ግማሽ ፊቱ በማረሻ የታረሰ ሚመስል አስፈሪ ፍጡር ገባና በእጁ እንድትነሳ ምልክት እየሰጣት በማይገባት ቋንቋ ለፈለፈ፡፡ቀልጠፍ ብላ ተነስታ ቆመች፡፡ወደእሷ ተራመደና ክንዷን ጨምድዶ በመያዝ ወደራሱ ጎተታት፡፡ደነገጠችም.. ተገረመችም፡፡እጁ በጣም ያማል፡፡እጁ ብቻ አይደለም ቁጣውና መኮሳተሩ እራሱ ያማል፡፡አንጠልጥሎ ከጎጆ አወጣትና ወረወራት፡፡ብዥ አለባት፡፡ከአስራ አምስት የሚበልጡ ፀጉራቸው የተንጨፈረረ..ጡንቻቸው የደደረና ፊታቸው የጨለመ ሰዎች ልክ የሆነ ክፍለ ጦር ለመዋጋት ዝግጁ ሆኖ እንደሚጓዝ አማፂ ብድን በሰልፍ ተሰልፈው ለጉዞ ዝግጁ ሆነዋል፡፡
በፊት ከምታውቃቸው ሌላ ቢያንስ 6 ተጫማሪ ገዳዬች ወደስብስቡ ተጨምረዋል፡፡ከደቂቃዎች በፊት የማምለጥ እድል ሊኖረኝ ይችላል በሚል ስታብሰለስለው የነበረው ዘዴና ውጥን ሁሉ እንደጉም በኖ ሲጠፋ ለራሷ ታወቃት፡፡እውነትም ያ ቅድም ምግብ ያቀረበላት ልጅ ጥሩ የሚባል የወዳጅ ምክር እንደመከራት አመነች፡፡ጥቂት እንኳን የማምለጥ ሙከራ ብትሞክር እንደፋሲካ ዶሮ አስራሁለት ቦታ እንደሚገነጣጥሎት እርግጠኛ ሆነችና ሽምቅቅ አለች፡፡ ምግብ አቅርቦላት የነበረው ወጣት ወደእሷ ቀረበና በቀደመ ጉዞቸው እንዳደረገው እጇ ላይ ታስሮ ስትጎትተው የነበረውን ሰንሰለት አነሳና ከራሱ እጅ ጋር አቆራኝቶ እንደድሮ ባሪያ እየጎተተ በመውሰድ ከሰልፉ መሀከል አስገባትና ከኃላዋ ሆነ ፡፡
ከጀርባ ያለ አንድ ድምፅ በማታውቀው ቋንቋ የሆኑ አረፍተ ነገሮችን ተናገረ፡፡ሁሉም መሳሪያቸውን ለመተኮስ በሚመስል መንገድ አስተካከሉ፡፡ ሊያደበላልቁት ነው ብላ ስትጠብቅ በዝግታ ፊት ያለው ሰው እርምጃውን ቀጠለ ከዛ እያንዳንዱ ሰልፉን እየጠበቀ መንቀሳቀስ ጀመረ..እሷም ልክ እንደሌሎቹ ፊት ያለውን በመመልከትና የእርምጃዋን ልክ በማስተካከል መጓዝ ጀመረች፡፡ጉዞው በጣም ፈታኝና አስቸጋሪ ነበር፡፡ከላይ ዝናብ ይዘንባል..ዝናቡ ቀጥታ ወርዶ መሬት አይነካም፡፡ እያዳንዱ ግዙፍ የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ያርፋል…፡፡ከዛ ኃይሉን እየቀነሰ ወደታች ይረግፍና ሰውነታቸውን ያርሳቸዋል፡፡አብዛኛው ልምድ ስላለው ለቦታው የሚገባ አለባበስ ነው የለበሱት፡፡እሷ ግን ወደኤርፖርት ልትሄድ በለበሰችው የተለመደ አይነት አለባበስ ነበረች፡፡ሰውነቷ ውስጥ አጥንት የሚሰረስር
👍70❤10🔥3🥰1👏1😱1
ጥዝጣዜ እየተሰማት ነው፡፡ግን ደግሞ ነፍስን የሚያቀዘቅዝም ፍርሀት ውስጧን እየቆራረጣት ስለሆነ ቅድሚያ የሰጠችው ስለምቾቶ ለማሰብ ሳይሆን ህይወቷን ስለማትረፍ ነው፡፡እግዜር ይስጠው አብሯት የተቆራኘው ወጣት ቆም አለና ትከሻው ላይ ካንጠለጠለው ቦርሳ ውስጥ አንድ ወፈር ያለ የጥጥ ገበር ያለው ባለ ኮፍያ ጀኬት አወጣና ሰጣት፡፡በፈገግታ አመሰገነችውና እርምጃዋና ሳታቆም ለበሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍56🥰8❤4
ህፃን ሄቨን ላይ የተደረገውን ድርጊት ለመናገር ሁሉ ያሸማቅቃል
ምን አይነት የጭካኔ ዘመን ውስጥ እንደደረስን የሚያሳይ ቆ ሻሻ የሆነ ግፍ😢ለቤተሰቦቿ ጥንካሬውን ያድላቸው ።
ይህው እናትም የልጄን ፍትህ አሰጡኝ እያለች የኢትዮጵያ ህዝብ እየለመነች ትገኛለች።
ለዚች እናትስ ምን ቃላት ያፅናናት ይሆን ?😪
ለህፃን ሄቨን ፍትህ ይገኝ ዘንድ ጫና ለመፍጠር እየተሰበሰበ ያለውን petition እንቀላቀል፣ ሼርም እናድርግ።
https://chng.it/rrSzFxp7PW
ድምፅ ሁኑ 🙏
ብላቴናዋ ሚጣ
ምን አይነት የጭካኔ ዘመን ውስጥ እንደደረስን የሚያሳይ ቆ ሻሻ የሆነ ግፍ😢ለቤተሰቦቿ ጥንካሬውን ያድላቸው ።
ይህው እናትም የልጄን ፍትህ አሰጡኝ እያለች የኢትዮጵያ ህዝብ እየለመነች ትገኛለች።
ለዚች እናትስ ምን ቃላት ያፅናናት ይሆን ?😪
ለህፃን ሄቨን ፍትህ ይገኝ ዘንድ ጫና ለመፍጠር እየተሰበሰበ ያለውን petition እንቀላቀል፣ ሼርም እናድርግ።
https://chng.it/rrSzFxp7PW
ድምፅ ሁኑ 🙏
ብላቴናዋ ሚጣ
😢69👍17🤔5
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ባለ ኮፍያ ጀኬት አወጣና ሰጣት፡፡በፈገግታ አመሰገነችውና እርምጃዋና ሳታቆም ለበሰች፡፡
ፊት ለፊታቸውም ያሉት እራቅ ብለዋል ኋላም ያሉት ቢያንስ በ20 እርምጃ ወደኃላ ቀርተዋል፡፡፡ስለዚህ በምቾት ታወራው ጀመረ፡፡
‹‹ቁራኛዬ..ስለመልካምነትህ አመሰግናለሁ››አለችው፡፡
‹‹ቁራኛዬ ማለት ምን ማለት ነው?››ጠየቃት፡፡
‹‹በሀገራችን የጥንት ጊዜ ቁራኛዬ የሚባል ባህላዊ የፍርድ ስርዓት ነበር፡፡ በዳይና ተበዳይ፤ሰራቂና ተሰራቂ ፤ገዳይና የተገደለበት ፍርድ የሚሰጥበት ቦታ እስኪደርሱ ድረስ እንዲህ እንደእኔና እንደአንተ በአካባቢው ሽማግሌ ሸማቸውን አንድ ላይ ይቋጥርሩትና እርስ በርስ አቆራኝተው ይልኳቸዋል፡፡በጉዞቸው ታዲያ አንድ ሌላውን በመንከባከብ..ከአደጋ በመጠበቅ ፍርድ እስከሚያገኙበት ቦታ ድረስ በሰላም የመድረስ ግዴታ አለባቸው፡፡ከዛ ተከራክረውና ማስረጃቸውና አቅርበው የተወሰነው ከተወሰነ በኃላ ነገሩ ይደመደማል ፡፡
‹‹የሚገርም ባህል ነው፡፡››
‹‹አዎ ነው..ለመሆኑ ትክክለኛ ስምህ ማን ነው?፡፡››
‹‹ካርሎስ››
‹‹የእኔ ኑሀሚ ነው ..ኢትዬጵያዊ ነኝ፡፡››
‹‹ኢትዬጵያ የት ነች..?ኢስያ አህጉር ውስጥ ነች?››
‹‹አይ አፍሪካ ነች….ምስራቅ አፍሪካ፡፡››
‹‹እ አዎ አስታወስኩ…ታዲያ እዚህ እንዴት ተገኘሽ?››
‹‹በናንተ ተጠለፍኩ እንጂ… የተባበሩት ድርጅት የተፈጥሮ ጥበቃ ፅ/ቤት ባዘጋጀው አለምአቀፍ ሴሚናር ላይ ለመካፈል ነበር አመጣጤ፡፡››
‹‹እ የተፈጥሮ ጥበቃ ላይ ነው የምትሰሪው?››በአድናቆት ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ …ነበር፡፡››
‹‹እድለኛ ነሽ…የተፈጥሮ ጥበቃ ወታደር መሆን ከምንም በላይ የሚያኮራ ስራ ነው፡፡በአሁኑ ጊዜ የሰው ልጅ በከፍተኛ ትጋትና ጥረት ምድርን ለማውደም እየሰራ ነው….ያ በጣም አሳሳቢ እና አደገኛ ጉዳይ ነው..ግን ደግሞ ተስፋ እንዳንቆርጥ የሚያደርገን እንደአንቺ አይነት ጀግኖች ያንን ጥፋት ለማክሰም ሲለፉና ሲጥሩ ስለምናይ ነው፡፡ ››
እሷ ለተፈጥሮ ጥበቃና እንክብካቤ እሱ በሚያስበው ልክ ቁርጠኝነቱ ሆነ ፍላጎቱ እንደሌላት ብታውቅም ያንን በግልፅ ልትነግረው አልፈለገችም፡፡ስለእሷ አሁን እየተሰማው ባለው አድናቆትና ክብር እንዲቀጥል ፈልጋለች..ምን አልባት በሆነ አጋጣሚ ሊጠቅማት አንደሚችል አሰበች፡፡
‹‹ተፈጥሮ ላይ ያለህ ፍላጎት ጥልቅ ይመስላል?፡፡››
‹‹አዎ እዚህ በምታይው መልኩ ለመኖሬ ምክንያቴ ለተፈጥሮ ካለኝ ቀናኢነት የተነሳ ነው፡፡ከአማዞን ጫካም ሆነ ከአማዞን ወንዝ ፍቅር ይዞኛል፡፡ይሄው እዚህ ከገባሁ አምስት አመት አለፈኝ…በተቻለኝ አቅምና ዕውቀት የዚህ ደን ውስጠ ሚስጥሩን በርብሬ እያጠናሁ ነው፡፡እስከአሁን ሁለት መፅሀፍ አሳትሜያለሁ….አሁን ደግሞ ሶስተኛውን እየሰራው ነው፡፡››ብሎ አስደመማት፡፡
‹‹የእውነትህን ነው የምታወራኝ?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እስኪ ስለአማዞን ጥቂት ንገረኝ፡፡››አለችው
‹‹ምን ልንገርሽ…?››
‹‹ስለአጠቃላይና መሰረታዊ ነገሮች፡፡››
‹‹እሺ …አማዞን የአለማችን ትልቁ ደን ሲሆን 40 በመቶ በሚሆኑት የደቡብ አሜሪካ ሃገራት ላይ አርፏል፡፡ የአማዞን ጥቅጥቅ ደን 9 ሀገራት ላይ የረፈ በዓለም ላይ ትልቁ ሞቃታማ ደን ሲሆን የሚያካትታቸው ሀገሮችም ብራዚልን 60% ፣ ፔሩ 13% የደን ሽፋን ፣ ኮሎምቢያ 10% እና ቀሪው 17% ቬንዙዌላ ፣ ኢኳዶር ፣ ቦሊቪያ ፣ ጉያና ፣ ሱሪናሜ እና የፈረንሳይ ጓያና የአማዞን ደን የጋራ ባለቤቶች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአማዞን ስፋት የህንድን ሁለት እጥፍ ያክላል፡፡ያ ማለት አማዞን አንድ ላይ ተካሎ እራሱን የቻለ አንድ ሀገር ይሁን ቢባል ከ30ሚሊዮን በላይ ዜጎች ያሉት የአለማችን 9ኛው ትልቁ ሃገር ይሆን ነበር ማለት ነው፡፡››
‹‹ይገርማል፡፡››ብላ አድናቆቷን ገለፀችለት፡፡
በዛ ተበረታቶ ማብራሪያውን ቀጠለ‹‹ሌላው በአማዞን ደን ከ350 በላይ ነበር ጎሳዎች በውስጡ ተበታትነው ሲኖሩበት ከእነዛ ጎሳዎች መካከል ከ75 በላይ የሚሆኑት ጎሳዎች እርስ በእርስ ተገናኝተው የማያውቁ እራሳቸውን ከሌላው ማህበረሰብ፤ከመንግስትም ሆነ ከማንኛውም ቴክኖሎጂ ያራቁ ናቸው፡፡ ስለእንስሳቱ ንገረኝ ካልሺኝ ደግሞ አማዞን በአለማችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አጥቢ አንስሳት፤አዕዋፋት እና በደረት የሚሳቡ ፍጡራን የሚገኙበት ደን ነው፡፡በዛ ጥቅጥቅ ደን 400 ቢሊዮን ዛፎች፤40 ሺህ የእጽዋት እና 1300 የአዕዋፍ ዝርያዎች በውስጡ ይገኛሉ፡፡››
በገለፃው የእውነት ከልቧ ተደምማበት‹‹እውነትም ከዚህ ደን ጥልቅ የሆነ ፍቅር ይዞሀል››የሚል አስተያየት ሰጠችው፡፡
‹‹አዎ…በትክክል ገልጸሸዋል፡፡››
ንግግሩን ያቋረጠው ከኃላቸው የፉጨት ድምፅ ሲሰማ ነው፡፡ፈጠን አለና ክንዷን ጨምድዶ እየሄድበት ካለው ጠባብ መንገድ ዞር አድርጎ በመውሰድ አንድ ግዙፍ ዛፍ ጋር አጣብቋት በሰውነቱ ጋርዷትና ቆመ ፡፡እሷን በግንዱና በራስ መካከል አድርጎ ስላቆማት ትንፋሽ አጠራት፡፡ቢሆንም እንደምንም ችላው ‹‹ምን ተፈጥሮ ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
በእጅ ላይ ያለውን ሽጉጥ እንዳቀባበለ ወደፊት ደቅኖ የሚሆነውን እየጠበቀ ነው….እጁን አፉ ላይ በመጫን ዝም እንድትልና ድምፅ እንዳታሰማ ጠየቃት ፡፡ወዲያው ሰቅጣጭ የሚያጎራ አይነት የሰው ድምፅ ተሰማ …እሱን ተከትሎ…ሶስት ተከታታይ ፉጨት ተሰማ፡፡
የሆነ አደጋ ተፈጥሮል፡፡እርዳታ እየጠየቁ ነው፡፡ከጀርባዬ ተከልለሽ በጥንቃቄ ተከተይኝ አለና ወደፊት መንቀሳቀስ ጀመረ…በአንድ እጇ ትከሻውን ይዛ ከወጋቧ ወደታች አጎንብሳ ልክ እንደእሱ እየተሹለከለከች ወደኃላ መጎዝ ጀመሩ፡፡ ከሶስት ደቂቃ በኃላ ተፈላጊው ቦታ ሲደርሱ የሚዘገንን ነገር ገጠማቸው…የሆነ ኩሬ መሳይ እረግረግ ቦታ ላይ ስድስት ሚሆኑት አጋቾቾ ክብ ሰርተው መሳሪያቸውን አቀባብለውና ደቅነው እንተኩስ አትኩሱ እየተባባሉ ይጨቃጨቃሉ፡፡መሀከል ላይ ያ ሲነሱ ከቤት ክንዷን ጨምድዶ ያወጣት አውሬ መሳየ ሰው ተዘርሯል፡፡ እሱ መሆኑን ያወቀችው በተንጨፈረረ ፀጉሩ እና በለበሰው ጃኬት ነው፡፡በሙሉ ሰውነቱ አንኮንዳ ዘንዶ ልክ እንደጥምዝ ቀለበት ተጠምጥሞበት ወደረግረጉ ጉድጓድ እያሰመጠው ነው፡፡እዲህ አይነት ነገር እንኳን በአካል በፊልም አንኳን አይታ አታውቅም፡፡ዝግንን አላት፡፡አረ በፈጣሪ የሆነ ነገር አድርጉና አድኑት››ጮኸች፡፡
ሁሉም ዞር ዞር እያሉ አዮት››መናገሯን እንጂ ምን እንዳለች የገባው የለም፡፡››ለካ ያወራችው በአማርኛ ነው፡፡ሁል ጊዜ ከልክ በላይ ስትደነግጥና ስትናደድ ከአማርኛ ቋንቋ ውጭ በአንደበቷ ለምን ሌላ ቋንቋ እንደማይገባ ሁሌ እንደገረማት ነው፡፡ትዝ ሲላት ወዲያው ስህተቷን አረመችና በእንግሊዘኛ ደገመችላቸው፡፡እነሱ በእስፓኒሽ ተነጋገሩና መተኮስ ጀመሩ …ደም እየተንኮለለ መፍሰስ ጀመረ ..የሰውዬው ይሁን የአናኮንዳው አላወቀችም፡፡ሁለቱም ኩሬ መሳይ እረግረግ ውሀ ውስጥ ሰመጡና ከእይታቸው ተሰወሩ፡፡ከተወሰነ ደቂቃዎች መደናገጥ እና ቁዘማ በኃላ ሁሉም እንደቀድሟቸው በሰልፍ ገብተው መንገዳቸውን ቀጠሉ፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ባለ ኮፍያ ጀኬት አወጣና ሰጣት፡፡በፈገግታ አመሰገነችውና እርምጃዋና ሳታቆም ለበሰች፡፡
ፊት ለፊታቸውም ያሉት እራቅ ብለዋል ኋላም ያሉት ቢያንስ በ20 እርምጃ ወደኃላ ቀርተዋል፡፡፡ስለዚህ በምቾት ታወራው ጀመረ፡፡
‹‹ቁራኛዬ..ስለመልካምነትህ አመሰግናለሁ››አለችው፡፡
‹‹ቁራኛዬ ማለት ምን ማለት ነው?››ጠየቃት፡፡
‹‹በሀገራችን የጥንት ጊዜ ቁራኛዬ የሚባል ባህላዊ የፍርድ ስርዓት ነበር፡፡ በዳይና ተበዳይ፤ሰራቂና ተሰራቂ ፤ገዳይና የተገደለበት ፍርድ የሚሰጥበት ቦታ እስኪደርሱ ድረስ እንዲህ እንደእኔና እንደአንተ በአካባቢው ሽማግሌ ሸማቸውን አንድ ላይ ይቋጥርሩትና እርስ በርስ አቆራኝተው ይልኳቸዋል፡፡በጉዞቸው ታዲያ አንድ ሌላውን በመንከባከብ..ከአደጋ በመጠበቅ ፍርድ እስከሚያገኙበት ቦታ ድረስ በሰላም የመድረስ ግዴታ አለባቸው፡፡ከዛ ተከራክረውና ማስረጃቸውና አቅርበው የተወሰነው ከተወሰነ በኃላ ነገሩ ይደመደማል ፡፡
‹‹የሚገርም ባህል ነው፡፡››
‹‹አዎ ነው..ለመሆኑ ትክክለኛ ስምህ ማን ነው?፡፡››
‹‹ካርሎስ››
‹‹የእኔ ኑሀሚ ነው ..ኢትዬጵያዊ ነኝ፡፡››
‹‹ኢትዬጵያ የት ነች..?ኢስያ አህጉር ውስጥ ነች?››
‹‹አይ አፍሪካ ነች….ምስራቅ አፍሪካ፡፡››
‹‹እ አዎ አስታወስኩ…ታዲያ እዚህ እንዴት ተገኘሽ?››
‹‹በናንተ ተጠለፍኩ እንጂ… የተባበሩት ድርጅት የተፈጥሮ ጥበቃ ፅ/ቤት ባዘጋጀው አለምአቀፍ ሴሚናር ላይ ለመካፈል ነበር አመጣጤ፡፡››
‹‹እ የተፈጥሮ ጥበቃ ላይ ነው የምትሰሪው?››በአድናቆት ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ …ነበር፡፡››
‹‹እድለኛ ነሽ…የተፈጥሮ ጥበቃ ወታደር መሆን ከምንም በላይ የሚያኮራ ስራ ነው፡፡በአሁኑ ጊዜ የሰው ልጅ በከፍተኛ ትጋትና ጥረት ምድርን ለማውደም እየሰራ ነው….ያ በጣም አሳሳቢ እና አደገኛ ጉዳይ ነው..ግን ደግሞ ተስፋ እንዳንቆርጥ የሚያደርገን እንደአንቺ አይነት ጀግኖች ያንን ጥፋት ለማክሰም ሲለፉና ሲጥሩ ስለምናይ ነው፡፡ ››
እሷ ለተፈጥሮ ጥበቃና እንክብካቤ እሱ በሚያስበው ልክ ቁርጠኝነቱ ሆነ ፍላጎቱ እንደሌላት ብታውቅም ያንን በግልፅ ልትነግረው አልፈለገችም፡፡ስለእሷ አሁን እየተሰማው ባለው አድናቆትና ክብር እንዲቀጥል ፈልጋለች..ምን አልባት በሆነ አጋጣሚ ሊጠቅማት አንደሚችል አሰበች፡፡
‹‹ተፈጥሮ ላይ ያለህ ፍላጎት ጥልቅ ይመስላል?፡፡››
‹‹አዎ እዚህ በምታይው መልኩ ለመኖሬ ምክንያቴ ለተፈጥሮ ካለኝ ቀናኢነት የተነሳ ነው፡፡ከአማዞን ጫካም ሆነ ከአማዞን ወንዝ ፍቅር ይዞኛል፡፡ይሄው እዚህ ከገባሁ አምስት አመት አለፈኝ…በተቻለኝ አቅምና ዕውቀት የዚህ ደን ውስጠ ሚስጥሩን በርብሬ እያጠናሁ ነው፡፡እስከአሁን ሁለት መፅሀፍ አሳትሜያለሁ….አሁን ደግሞ ሶስተኛውን እየሰራው ነው፡፡››ብሎ አስደመማት፡፡
‹‹የእውነትህን ነው የምታወራኝ?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እስኪ ስለአማዞን ጥቂት ንገረኝ፡፡››አለችው
‹‹ምን ልንገርሽ…?››
‹‹ስለአጠቃላይና መሰረታዊ ነገሮች፡፡››
‹‹እሺ …አማዞን የአለማችን ትልቁ ደን ሲሆን 40 በመቶ በሚሆኑት የደቡብ አሜሪካ ሃገራት ላይ አርፏል፡፡ የአማዞን ጥቅጥቅ ደን 9 ሀገራት ላይ የረፈ በዓለም ላይ ትልቁ ሞቃታማ ደን ሲሆን የሚያካትታቸው ሀገሮችም ብራዚልን 60% ፣ ፔሩ 13% የደን ሽፋን ፣ ኮሎምቢያ 10% እና ቀሪው 17% ቬንዙዌላ ፣ ኢኳዶር ፣ ቦሊቪያ ፣ ጉያና ፣ ሱሪናሜ እና የፈረንሳይ ጓያና የአማዞን ደን የጋራ ባለቤቶች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአማዞን ስፋት የህንድን ሁለት እጥፍ ያክላል፡፡ያ ማለት አማዞን አንድ ላይ ተካሎ እራሱን የቻለ አንድ ሀገር ይሁን ቢባል ከ30ሚሊዮን በላይ ዜጎች ያሉት የአለማችን 9ኛው ትልቁ ሃገር ይሆን ነበር ማለት ነው፡፡››
‹‹ይገርማል፡፡››ብላ አድናቆቷን ገለፀችለት፡፡
በዛ ተበረታቶ ማብራሪያውን ቀጠለ‹‹ሌላው በአማዞን ደን ከ350 በላይ ነበር ጎሳዎች በውስጡ ተበታትነው ሲኖሩበት ከእነዛ ጎሳዎች መካከል ከ75 በላይ የሚሆኑት ጎሳዎች እርስ በእርስ ተገናኝተው የማያውቁ እራሳቸውን ከሌላው ማህበረሰብ፤ከመንግስትም ሆነ ከማንኛውም ቴክኖሎጂ ያራቁ ናቸው፡፡ ስለእንስሳቱ ንገረኝ ካልሺኝ ደግሞ አማዞን በአለማችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አጥቢ አንስሳት፤አዕዋፋት እና በደረት የሚሳቡ ፍጡራን የሚገኙበት ደን ነው፡፡በዛ ጥቅጥቅ ደን 400 ቢሊዮን ዛፎች፤40 ሺህ የእጽዋት እና 1300 የአዕዋፍ ዝርያዎች በውስጡ ይገኛሉ፡፡››
በገለፃው የእውነት ከልቧ ተደምማበት‹‹እውነትም ከዚህ ደን ጥልቅ የሆነ ፍቅር ይዞሀል››የሚል አስተያየት ሰጠችው፡፡
‹‹አዎ…በትክክል ገልጸሸዋል፡፡››
ንግግሩን ያቋረጠው ከኃላቸው የፉጨት ድምፅ ሲሰማ ነው፡፡ፈጠን አለና ክንዷን ጨምድዶ እየሄድበት ካለው ጠባብ መንገድ ዞር አድርጎ በመውሰድ አንድ ግዙፍ ዛፍ ጋር አጣብቋት በሰውነቱ ጋርዷትና ቆመ ፡፡እሷን በግንዱና በራስ መካከል አድርጎ ስላቆማት ትንፋሽ አጠራት፡፡ቢሆንም እንደምንም ችላው ‹‹ምን ተፈጥሮ ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
በእጅ ላይ ያለውን ሽጉጥ እንዳቀባበለ ወደፊት ደቅኖ የሚሆነውን እየጠበቀ ነው….እጁን አፉ ላይ በመጫን ዝም እንድትልና ድምፅ እንዳታሰማ ጠየቃት ፡፡ወዲያው ሰቅጣጭ የሚያጎራ አይነት የሰው ድምፅ ተሰማ …እሱን ተከትሎ…ሶስት ተከታታይ ፉጨት ተሰማ፡፡
የሆነ አደጋ ተፈጥሮል፡፡እርዳታ እየጠየቁ ነው፡፡ከጀርባዬ ተከልለሽ በጥንቃቄ ተከተይኝ አለና ወደፊት መንቀሳቀስ ጀመረ…በአንድ እጇ ትከሻውን ይዛ ከወጋቧ ወደታች አጎንብሳ ልክ እንደእሱ እየተሹለከለከች ወደኃላ መጎዝ ጀመሩ፡፡ ከሶስት ደቂቃ በኃላ ተፈላጊው ቦታ ሲደርሱ የሚዘገንን ነገር ገጠማቸው…የሆነ ኩሬ መሳይ እረግረግ ቦታ ላይ ስድስት ሚሆኑት አጋቾቾ ክብ ሰርተው መሳሪያቸውን አቀባብለውና ደቅነው እንተኩስ አትኩሱ እየተባባሉ ይጨቃጨቃሉ፡፡መሀከል ላይ ያ ሲነሱ ከቤት ክንዷን ጨምድዶ ያወጣት አውሬ መሳየ ሰው ተዘርሯል፡፡ እሱ መሆኑን ያወቀችው በተንጨፈረረ ፀጉሩ እና በለበሰው ጃኬት ነው፡፡በሙሉ ሰውነቱ አንኮንዳ ዘንዶ ልክ እንደጥምዝ ቀለበት ተጠምጥሞበት ወደረግረጉ ጉድጓድ እያሰመጠው ነው፡፡እዲህ አይነት ነገር እንኳን በአካል በፊልም አንኳን አይታ አታውቅም፡፡ዝግንን አላት፡፡አረ በፈጣሪ የሆነ ነገር አድርጉና አድኑት››ጮኸች፡፡
ሁሉም ዞር ዞር እያሉ አዮት››መናገሯን እንጂ ምን እንዳለች የገባው የለም፡፡››ለካ ያወራችው በአማርኛ ነው፡፡ሁል ጊዜ ከልክ በላይ ስትደነግጥና ስትናደድ ከአማርኛ ቋንቋ ውጭ በአንደበቷ ለምን ሌላ ቋንቋ እንደማይገባ ሁሌ እንደገረማት ነው፡፡ትዝ ሲላት ወዲያው ስህተቷን አረመችና በእንግሊዘኛ ደገመችላቸው፡፡እነሱ በእስፓኒሽ ተነጋገሩና መተኮስ ጀመሩ …ደም እየተንኮለለ መፍሰስ ጀመረ ..የሰውዬው ይሁን የአናኮንዳው አላወቀችም፡፡ሁለቱም ኩሬ መሳይ እረግረግ ውሀ ውስጥ ሰመጡና ከእይታቸው ተሰወሩ፡፡ከተወሰነ ደቂቃዎች መደናገጥ እና ቁዘማ በኃላ ሁሉም እንደቀድሟቸው በሰልፍ ገብተው መንገዳቸውን ቀጠሉ፡፡
👍68❤4👎1😢1
የወቀሳ ቅላፄ ባለው ድምፀት ‹‹በቃ ህይወት ለእናንተ እንዲህ ቀልድ ነው››ስትል ካርሎስን ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን ታደርጊዋለሽ እንግዲህ ..ህይወት በአማዞን ደን እንዲህ ነች…ሞትን በእጅ መዳፍሽ ይዘሽ ነው የምትዞሪው፡፡››
‹‹በጣም ይገርማል ..ይሄ ዘንዶ ግን ምን አይነት አስፈሪ ፍጡር ነው?››
‹‹ዘንዶ አይደለም አናኮንዳ ይባላል፡፡አናኮንዳ በአልም በክብደት በጣም ግዙፉ የእባብ ዝርያ ሲሆን በርዝመት ደግሞ ፓይቶን በተባለው ዝርያ ብቻ ነው የሚበለጠው ፡፡ አናኮንዳ እስከ 550 ፓውንድ ወይም ከዚያ በላይ ሊመዝን እና እስከ 25 ጫማ ሊያድግ ይችላል ፡፡አናኮንዳ መርዛም ከሚባሉት የእባብ ዝርያዎች ውስጥ የሚመደብ አይደለም፡፡ግን ደግሞ እንደምታይው አደገኛ አዳኝና ገዳይ ነው፡፡አናኮንዳ ከሌሎች እባቦች የተለየበት ትልቁ ባህሪው ድንቅ ዋናተኛ መሆኑና ከቀን ይልቅ በለሌት የተሻለ የማደን ብቃትና ቅልጥፍና አቅም ባለቤት በመሆኑ ነው፡፡የአናኮንዳ ዋነኛ ታዳኞች ዓሦዎችን ፣ ኤሊዎችን ፣ አሳማዎችን ፣ ካይማኖችን ፣ ጃጓሮችን ፣ አጋዘን የመሳሰሉት እንስሳቶች ናቸው፡፡አናኮንዳ በቅልጥፍና ሚፈልገውን እንስሳት በጅራቱ ይጠልፍና ወደውሀ ውስጥ ይዞት ይሰምጥና በአንድ ጊዜ ይውጠዋል፡፡ከደቂቃዎች በፊት እንዳየሸው አልፎ አልፎ እድል ከቀናው ሰውንም አይምርም፡፡
‹‹ዘግናኝ ነው..እኔስ በእሱ ከምዋጥ እናንተው በፍጥነት አሁነኑ ብትገድሉኝ ይሻለኛል››አለችው፡፡
ምንም አልመለሰላትም፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ምን ታደርጊዋለሽ እንግዲህ ..ህይወት በአማዞን ደን እንዲህ ነች…ሞትን በእጅ መዳፍሽ ይዘሽ ነው የምትዞሪው፡፡››
‹‹በጣም ይገርማል ..ይሄ ዘንዶ ግን ምን አይነት አስፈሪ ፍጡር ነው?››
‹‹ዘንዶ አይደለም አናኮንዳ ይባላል፡፡አናኮንዳ በአልም በክብደት በጣም ግዙፉ የእባብ ዝርያ ሲሆን በርዝመት ደግሞ ፓይቶን በተባለው ዝርያ ብቻ ነው የሚበለጠው ፡፡ አናኮንዳ እስከ 550 ፓውንድ ወይም ከዚያ በላይ ሊመዝን እና እስከ 25 ጫማ ሊያድግ ይችላል ፡፡አናኮንዳ መርዛም ከሚባሉት የእባብ ዝርያዎች ውስጥ የሚመደብ አይደለም፡፡ግን ደግሞ እንደምታይው አደገኛ አዳኝና ገዳይ ነው፡፡አናኮንዳ ከሌሎች እባቦች የተለየበት ትልቁ ባህሪው ድንቅ ዋናተኛ መሆኑና ከቀን ይልቅ በለሌት የተሻለ የማደን ብቃትና ቅልጥፍና አቅም ባለቤት በመሆኑ ነው፡፡የአናኮንዳ ዋነኛ ታዳኞች ዓሦዎችን ፣ ኤሊዎችን ፣ አሳማዎችን ፣ ካይማኖችን ፣ ጃጓሮችን ፣ አጋዘን የመሳሰሉት እንስሳቶች ናቸው፡፡አናኮንዳ በቅልጥፍና ሚፈልገውን እንስሳት በጅራቱ ይጠልፍና ወደውሀ ውስጥ ይዞት ይሰምጥና በአንድ ጊዜ ይውጠዋል፡፡ከደቂቃዎች በፊት እንዳየሸው አልፎ አልፎ እድል ከቀናው ሰውንም አይምርም፡፡
‹‹ዘግናኝ ነው..እኔስ በእሱ ከምዋጥ እናንተው በፍጥነት አሁነኑ ብትገድሉኝ ይሻለኛል››አለችው፡፡
ምንም አልመለሰላትም፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍64😢6❤4😱1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ናኦል የእህቱን ድምፅ ከሰማ አራት ቀናት አልፎታል፡፡ይሄ ያልተለመደና ሊታሰብ የማይችል ነገር ነው፡፡እህቱ ቢዚ ብትሆን እንኳን አራት ቀን ሙሉ ቢያንስ ሚሴጅ ትልክለታለች ወይም ኢሜል ትልክለታለች እንጂ እንዲሁ ዝም ልትለው አትችልም፡፡እንዲህ አይነት ነገር አላስለመደችውም፡፡በተለይ የመጨረሻ ጊዜ ስትደውልለት በመጥፎ አየር ፀባይ ወደብራዚል መድረስ አቅቷቸው ያልሆነ ከተማ አርፋ አልጋ ክፍል ሆና ነበር የደወለችለት፡፡የአየር ፀባዩ ከተስተካከለ በማግስቱ ወደብራዚል በረራውን እንደምትቀጥልም ነግራው እሱም አምኗት ነበር፡፡በማግስቱ ትደውልልኛለች ብሎ ጠብቆ ነበር፡፡ማህበራዊ ሚዲያ ላይም ደጋግሞ ሊያገኛት ሞክሯል ፡፡፡ግን ምንም አይነት እንቀስቃሴ የለም፡፡ሚሲጅም ላከላት.. ኢሚልም ደጋግሞ ፃፈላት፡፡መልስ የለም፡፡መስራቤቷ ሄዶ አመለከተ..የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተፈጥሮ ጥበቃ መስሪያ ቤት ጋር ተፃፅፈው የሚያገኙትን አዲስ መረጃ ከለ ወዲያውኑ እንደሚያሳውቁት ነገረው ሸኑት፡፡የሄደችበትን ድርጅት ድህረ-ገፅ ፈልጎ መረጃ ማሰስ ጀመረ…በአራተኛው ቀን ማታ እቤቱ ቁጭ ብሎ በትካዜ ላይ ሳለ ሰውነት የሚያርድ ልብ የሚያቆም ዜና ከድህረ ገፅ ላይ አነበበ፡፡
‹‹ለተግባራዊ ስልጠና ከፔሩ ወደብራዚል ስትሄድ በአየር ፀባይ መበላሸት ምክንያት ፔሩ ኢኩዩቶስ ከተማ አርፋ የነበረችው ኢትዬጴያዊቷ የተፈጥሮ ጥበቃ ባለሞያ ኑሀሚ በቀለ የገባችበት ጠፋ፡፡ወጣቷ የተፈጥሮ ጥበቃ ኢኬስፐርት አንድ ሆቴል ውስጥ ከአንድ ግለሰብ ጋር አብራ ያደረችና ጥዋትም በታክሲ ተሳፍራ ወደኤርፖርት ጉዞ እንደጀመረች ከሆቴሉ ሰራተኞች ማጣራት ቢቻልም ከዛ በኃላ ግን ኤርፖርት እንዳልደረሰች ታውቋል፡፡ምን አልባትም ወደሀገሯ መመለስ ስላልፈገች እራሷን ሰውራ ሊሆን እንደሚችል የአካባቢው ፖሊሶች ግምታቸውን የተናገሩ ሲሆን ፍለጋው ግን መቀጠሉን ታውቋል›› ይላል፡፡
ጮኸ…ኡ..ኡ ብሎ ጨኸ፡፡ግድግዳው ላይ የተንጠለጠለውን መስታወት በቦክስ ነረተው፡፡መስታወቱ ተፈረካክሶ ወለሉን ሞላው፡፡እጁን ሁለት ቦታ ሸረከተውና በደም ታጠበ…ሰራተኛዋ በርግጋ በውስጥ ልብሷ ብቻ መኝታዋን ለቃ መጥታ ፊቱ እስክትቆም ድርስ እራሱን እንደመሳት አድረጎት ነበር…በሶስት መቶ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቤታቸው የተኙ ጎሮቤቶች ከእንቅልፋቸው ባነው ግራ እስኪጋቡ ድረስ ነው የጮኸው፡፡
‹‹እህቴ የደሀዋ ኢትዬጵያ ዜጋ ልትሆን ትችላለች..ግን ደግሞ የእኔ እህት ነች…..እኔን ትታ ገነትም ቢሆን መቅረት አትፈልግም…እህቴ አንድ ነገር ሆናለች፡፡እህቴ ታፋናለች፡፡››
‹‹ምንድነው …..ምን ሆነህ ነው…..?ኑሀሚ ምን ሆነች?››ሰራተኛዋ ነች የምትጠይቀው፡፡
‹‹በሄደችበት ሀገር ጠፋች ነው የሚሉት..ሰው እንዴት ዝም ብሎ ይጠፋል….?እህቴን ወንጀለኞች አፍነዋት ነው፡፡››
ከእጁ እየተንጠባጠበ ያለውን ደም በጨርቅ እያሰረችለት‹‹ተረጋጋ እስኪ…የሰው ሀገር አይደለች ያለችው ..ምን አልባት መንገድ ጠፍቷት ያልሆነ ስፍራ ገብታ ያልሆኑ ሰዎች እጅ ወድቃ ሊሆን ይችላል ፡፡››ስትል
…ልታፅናናው ሞከረች፡፡
‹‹አንቺ ደግሞ ከፊቴ ጥፊ …መንገድ የሚጠፋት እንደአንቺ ደንባራ ነገር አደረግሻት እንዴ?፡፡›› አበሳጨችው፡፡
‹‹ያው ማንኛውም ሰው በሰው ሀገር ሲሆን መደናበሩ ይቀራል?››
ከተቀመጠበት ተነሳና ጀኬቱን ከሶፋው ላይ አነሳ …ወደመኝታ ቤቱ ሄደና የመሳቢያውን ኪስ ከፍቶ የሆነ ያህል ብር በማውጣት በኪሱ ጨመረ …ከሌለኛው መሳቢያ ሽጉጥ አወጣና በጀርባው ሽጦ ወጣ ፡፡ሰራተኛዋ ሳሎኑ መሀከል ተገትራ ግራ በመጋባት እየጠበቀችው ነበር፡፡ቀጥታ ወደሳሎኑ በራፍ ሄዶ መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹እንዴ ብቻህን በውድቅት ለሊት ወዴት ነው…?በዛ ላይ ቆስለሀል…ልብስ ልልበስና አብሬህ ልምጣ›››አለችው፡፡
‹‹ወዴት ነው የምትመጪው?››
‹‹ወዴት ማለት ምን ማለት ነው…?ለእኔም እኮ እህቴ ነች …ልፈልጋት ነዋ፡፡››
‹‹አሀ ልትፈልጌት ..ደቡብ አሜሪካ?››
‹‹የትስ ቢሆን እንኳን ሰው ከብትም ጠፍቶ ዝም ተብሎ መቀመጥ ይቻላል እንዴ?፡፡››
እንግዲያው ደቡብ አሜሪካ ትንሽ እራቅ ስለሚል ወፈር ያለ ልብስ ልበሺ ደግሞም የእግር መንገድ ስላለው ደህና ጫማ አድርጊ››አላት፡፡
‹‹ደግ…መጣሁ ቆየኝ ››አለችና ተንደርድራ ወደመኝታ ቤቷ ሄደች፡፡ይንን ንግግር በሰላሙ ጊዜ ሰምቶት ቢሆን ኖሮ ሆዱን ይዞ እስኪያመው ይስቅ ነበር፡፡ዛሬ ግን አይችልም፡፡
‹‹አለማወቅ ደጉ ››አለና ሳሎኑን ከፍቶ ወጣና ዘግቶ ቀጥታ ወደውጨኛው የአጥር በራፍ ሔደ..ወለል አድርጎ ከፈተውና ፒካፕ መኪናውን አስነስቶ ግቢውንም አካባቢውን ለቆ ወጣ፡፡
አስራአምስት ደቂቃ ከነዳ በኃላ ስልኩን አንስቶ አንድ አእምሮ ውስጥ በስውር የተቀመጠ ቁጥር አስታወሰና‹‹አስቸኳይ›› ብሎ ፃፈበትና ላከው፡፡እዚህ ቁጥር ላይ ሲፅፍ ከሶስት አመት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜው ነው፡፡የሞትና የሽረት ጉዳይ ካልሆነ እንዳይደውል ተነግሮታል፡፡እና ሁል ጊዜ መደወል ወይም መልዕክት መላክ ይፈልግና ግን ደግሞ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ እንደቀልድ ችላ ማለት ስለማይችል ውጦ ስሜቱን ያዳፍነዋል፡፡ያም ቢሆን ግን ስለጤንነቷና ስለለችበት ሁኔታ በተዘዋዋሪም ቢሆን በየጊዜው ያረጋግጣል፡፡ ግን አሁን ጊዜው ደርሷል…ለእሱ ከእህቱ መጥፋት በበለጠ የህይወት እና የሞት ሽረት ጉዳይ የለም...ለዛ ነው ይሄን መልዕክት በድፍረት የላከላት፡፡
መልዕክቱ የተላከው ምስራቅ የምትባል በእሱም ሆነ በእህቱ ህይወት ላይ ከፍተኛ ድርሻ እና ተፅዕኖ ያላት የደህንነት ሰው ስልክ ላይ ነው፡፡አሁን ካጋጠመው ችግር መፍትሄ ልታስገኝለት የምትችል በምድር ላይ አንድ ትክክለኛ ሰው ብትኖር እሷ ነች፡፡እሷ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከአለም አቀፍ የዲፕሎማሲው ማህብረሰብ ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ስላላት የሆነ ነገር ልታደርግለት እንደምትችል እርግጠኛ ነው፡፡
ቀጥታ ወደ እስታዲዬም ነው የነዳው፡፡መስቀል አደባባይ ሲደርስ መኪናውን አቆመና ወደ መቀመጫወቹ በመሄድ ኩርምት ብሎ ተቀመጠ፡፡በዛ በውድቅት ለሊት በሰባት ሰዓት አልፎ አልፎ ውር ውር ከሚሉ መኪኖች ውጭ አካባቢው ጭር እንዳለ ነው፡፡ብርዱ ግን ያንሰፈስፋል፡፡የጃኬቱን ዚፕ አንሸራተተና ወደላይ ቆለፈው፡፡ይሄንን ብርድ እና ስቃይ ያውቀዋል ፡፡ሰውነቱ ውስጥ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ ውስጥም ጭምር ነው ያለው፡፡ በርካታ አመታት በዛ በጮርቃ እድሜው ከአንዲቷና ከተወዳጅ እህቱ ጋር በረንዳ ኖሮ ያውቀዋል፡፡አሁን መልዕክት ልኮላት እስክትመልስለት ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ በብርድ እየተጠበሰ የሚጠብቃት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዴት እንዳገኘቻቸው በትዝታ አመታትን ወደኃላ ተመልሷ ማመንዠግ ጀመረ ፡፡የ12 አመት ጮርቃ ታዳጊ እያሉ እንደተለመደው 22 በሚገኝ በረንዳቸው ላይ በተለመደው መልኩ ተኝተው ነበር፡፡ሰዓቱ ልክ አሁን ባለበት ተመሳሳይ ሰዓት ላይ ነው ፡፡ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ፡፡እሱና እህቱ እርስ በርስ ተቃቅፈው አሮጌ ብርድልብስና ከላይ ጆንያ ደርበውበት ጋደም ብለው ወጪ ወራጁን በማየት ላይ ነበሩ፡፡
‹‹ምነው ወንድሜ እንቅልፍ እምቢ አለህ እንዴ?››ስትል ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እህቴ…ያቺን ሴትዬ አየሻት?››
‹‹የቷን?››
‹‹ያቺ ከስልክ ፖሉ አጠገብ ያለችው ልጅ፡፡››
ከትከሻዋ ቀና አለችና አየቻት‹‹አዲሷን ልጅ እያልከኝ ነው?››
‹‹አዎ…አዲሷን ልጅ…፡፡››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ናኦል የእህቱን ድምፅ ከሰማ አራት ቀናት አልፎታል፡፡ይሄ ያልተለመደና ሊታሰብ የማይችል ነገር ነው፡፡እህቱ ቢዚ ብትሆን እንኳን አራት ቀን ሙሉ ቢያንስ ሚሴጅ ትልክለታለች ወይም ኢሜል ትልክለታለች እንጂ እንዲሁ ዝም ልትለው አትችልም፡፡እንዲህ አይነት ነገር አላስለመደችውም፡፡በተለይ የመጨረሻ ጊዜ ስትደውልለት በመጥፎ አየር ፀባይ ወደብራዚል መድረስ አቅቷቸው ያልሆነ ከተማ አርፋ አልጋ ክፍል ሆና ነበር የደወለችለት፡፡የአየር ፀባዩ ከተስተካከለ በማግስቱ ወደብራዚል በረራውን እንደምትቀጥልም ነግራው እሱም አምኗት ነበር፡፡በማግስቱ ትደውልልኛለች ብሎ ጠብቆ ነበር፡፡ማህበራዊ ሚዲያ ላይም ደጋግሞ ሊያገኛት ሞክሯል ፡፡፡ግን ምንም አይነት እንቀስቃሴ የለም፡፡ሚሲጅም ላከላት.. ኢሚልም ደጋግሞ ፃፈላት፡፡መልስ የለም፡፡መስራቤቷ ሄዶ አመለከተ..የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተፈጥሮ ጥበቃ መስሪያ ቤት ጋር ተፃፅፈው የሚያገኙትን አዲስ መረጃ ከለ ወዲያውኑ እንደሚያሳውቁት ነገረው ሸኑት፡፡የሄደችበትን ድርጅት ድህረ-ገፅ ፈልጎ መረጃ ማሰስ ጀመረ…በአራተኛው ቀን ማታ እቤቱ ቁጭ ብሎ በትካዜ ላይ ሳለ ሰውነት የሚያርድ ልብ የሚያቆም ዜና ከድህረ ገፅ ላይ አነበበ፡፡
‹‹ለተግባራዊ ስልጠና ከፔሩ ወደብራዚል ስትሄድ በአየር ፀባይ መበላሸት ምክንያት ፔሩ ኢኩዩቶስ ከተማ አርፋ የነበረችው ኢትዬጴያዊቷ የተፈጥሮ ጥበቃ ባለሞያ ኑሀሚ በቀለ የገባችበት ጠፋ፡፡ወጣቷ የተፈጥሮ ጥበቃ ኢኬስፐርት አንድ ሆቴል ውስጥ ከአንድ ግለሰብ ጋር አብራ ያደረችና ጥዋትም በታክሲ ተሳፍራ ወደኤርፖርት ጉዞ እንደጀመረች ከሆቴሉ ሰራተኞች ማጣራት ቢቻልም ከዛ በኃላ ግን ኤርፖርት እንዳልደረሰች ታውቋል፡፡ምን አልባትም ወደሀገሯ መመለስ ስላልፈገች እራሷን ሰውራ ሊሆን እንደሚችል የአካባቢው ፖሊሶች ግምታቸውን የተናገሩ ሲሆን ፍለጋው ግን መቀጠሉን ታውቋል›› ይላል፡፡
ጮኸ…ኡ..ኡ ብሎ ጨኸ፡፡ግድግዳው ላይ የተንጠለጠለውን መስታወት በቦክስ ነረተው፡፡መስታወቱ ተፈረካክሶ ወለሉን ሞላው፡፡እጁን ሁለት ቦታ ሸረከተውና በደም ታጠበ…ሰራተኛዋ በርግጋ በውስጥ ልብሷ ብቻ መኝታዋን ለቃ መጥታ ፊቱ እስክትቆም ድርስ እራሱን እንደመሳት አድረጎት ነበር…በሶስት መቶ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቤታቸው የተኙ ጎሮቤቶች ከእንቅልፋቸው ባነው ግራ እስኪጋቡ ድረስ ነው የጮኸው፡፡
‹‹እህቴ የደሀዋ ኢትዬጵያ ዜጋ ልትሆን ትችላለች..ግን ደግሞ የእኔ እህት ነች…..እኔን ትታ ገነትም ቢሆን መቅረት አትፈልግም…እህቴ አንድ ነገር ሆናለች፡፡እህቴ ታፋናለች፡፡››
‹‹ምንድነው …..ምን ሆነህ ነው…..?ኑሀሚ ምን ሆነች?››ሰራተኛዋ ነች የምትጠይቀው፡፡
‹‹በሄደችበት ሀገር ጠፋች ነው የሚሉት..ሰው እንዴት ዝም ብሎ ይጠፋል….?እህቴን ወንጀለኞች አፍነዋት ነው፡፡››
ከእጁ እየተንጠባጠበ ያለውን ደም በጨርቅ እያሰረችለት‹‹ተረጋጋ እስኪ…የሰው ሀገር አይደለች ያለችው ..ምን አልባት መንገድ ጠፍቷት ያልሆነ ስፍራ ገብታ ያልሆኑ ሰዎች እጅ ወድቃ ሊሆን ይችላል ፡፡››ስትል
…ልታፅናናው ሞከረች፡፡
‹‹አንቺ ደግሞ ከፊቴ ጥፊ …መንገድ የሚጠፋት እንደአንቺ ደንባራ ነገር አደረግሻት እንዴ?፡፡›› አበሳጨችው፡፡
‹‹ያው ማንኛውም ሰው በሰው ሀገር ሲሆን መደናበሩ ይቀራል?››
ከተቀመጠበት ተነሳና ጀኬቱን ከሶፋው ላይ አነሳ …ወደመኝታ ቤቱ ሄደና የመሳቢያውን ኪስ ከፍቶ የሆነ ያህል ብር በማውጣት በኪሱ ጨመረ …ከሌለኛው መሳቢያ ሽጉጥ አወጣና በጀርባው ሽጦ ወጣ ፡፡ሰራተኛዋ ሳሎኑ መሀከል ተገትራ ግራ በመጋባት እየጠበቀችው ነበር፡፡ቀጥታ ወደሳሎኑ በራፍ ሄዶ መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹እንዴ ብቻህን በውድቅት ለሊት ወዴት ነው…?በዛ ላይ ቆስለሀል…ልብስ ልልበስና አብሬህ ልምጣ›››አለችው፡፡
‹‹ወዴት ነው የምትመጪው?››
‹‹ወዴት ማለት ምን ማለት ነው…?ለእኔም እኮ እህቴ ነች …ልፈልጋት ነዋ፡፡››
‹‹አሀ ልትፈልጌት ..ደቡብ አሜሪካ?››
‹‹የትስ ቢሆን እንኳን ሰው ከብትም ጠፍቶ ዝም ተብሎ መቀመጥ ይቻላል እንዴ?፡፡››
እንግዲያው ደቡብ አሜሪካ ትንሽ እራቅ ስለሚል ወፈር ያለ ልብስ ልበሺ ደግሞም የእግር መንገድ ስላለው ደህና ጫማ አድርጊ››አላት፡፡
‹‹ደግ…መጣሁ ቆየኝ ››አለችና ተንደርድራ ወደመኝታ ቤቷ ሄደች፡፡ይንን ንግግር በሰላሙ ጊዜ ሰምቶት ቢሆን ኖሮ ሆዱን ይዞ እስኪያመው ይስቅ ነበር፡፡ዛሬ ግን አይችልም፡፡
‹‹አለማወቅ ደጉ ››አለና ሳሎኑን ከፍቶ ወጣና ዘግቶ ቀጥታ ወደውጨኛው የአጥር በራፍ ሔደ..ወለል አድርጎ ከፈተውና ፒካፕ መኪናውን አስነስቶ ግቢውንም አካባቢውን ለቆ ወጣ፡፡
አስራአምስት ደቂቃ ከነዳ በኃላ ስልኩን አንስቶ አንድ አእምሮ ውስጥ በስውር የተቀመጠ ቁጥር አስታወሰና‹‹አስቸኳይ›› ብሎ ፃፈበትና ላከው፡፡እዚህ ቁጥር ላይ ሲፅፍ ከሶስት አመት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜው ነው፡፡የሞትና የሽረት ጉዳይ ካልሆነ እንዳይደውል ተነግሮታል፡፡እና ሁል ጊዜ መደወል ወይም መልዕክት መላክ ይፈልግና ግን ደግሞ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ እንደቀልድ ችላ ማለት ስለማይችል ውጦ ስሜቱን ያዳፍነዋል፡፡ያም ቢሆን ግን ስለጤንነቷና ስለለችበት ሁኔታ በተዘዋዋሪም ቢሆን በየጊዜው ያረጋግጣል፡፡ ግን አሁን ጊዜው ደርሷል…ለእሱ ከእህቱ መጥፋት በበለጠ የህይወት እና የሞት ሽረት ጉዳይ የለም...ለዛ ነው ይሄን መልዕክት በድፍረት የላከላት፡፡
መልዕክቱ የተላከው ምስራቅ የምትባል በእሱም ሆነ በእህቱ ህይወት ላይ ከፍተኛ ድርሻ እና ተፅዕኖ ያላት የደህንነት ሰው ስልክ ላይ ነው፡፡አሁን ካጋጠመው ችግር መፍትሄ ልታስገኝለት የምትችል በምድር ላይ አንድ ትክክለኛ ሰው ብትኖር እሷ ነች፡፡እሷ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከአለም አቀፍ የዲፕሎማሲው ማህብረሰብ ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ስላላት የሆነ ነገር ልታደርግለት እንደምትችል እርግጠኛ ነው፡፡
ቀጥታ ወደ እስታዲዬም ነው የነዳው፡፡መስቀል አደባባይ ሲደርስ መኪናውን አቆመና ወደ መቀመጫወቹ በመሄድ ኩርምት ብሎ ተቀመጠ፡፡በዛ በውድቅት ለሊት በሰባት ሰዓት አልፎ አልፎ ውር ውር ከሚሉ መኪኖች ውጭ አካባቢው ጭር እንዳለ ነው፡፡ብርዱ ግን ያንሰፈስፋል፡፡የጃኬቱን ዚፕ አንሸራተተና ወደላይ ቆለፈው፡፡ይሄንን ብርድ እና ስቃይ ያውቀዋል ፡፡ሰውነቱ ውስጥ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ ውስጥም ጭምር ነው ያለው፡፡ በርካታ አመታት በዛ በጮርቃ እድሜው ከአንዲቷና ከተወዳጅ እህቱ ጋር በረንዳ ኖሮ ያውቀዋል፡፡አሁን መልዕክት ልኮላት እስክትመልስለት ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ በብርድ እየተጠበሰ የሚጠብቃት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዴት እንዳገኘቻቸው በትዝታ አመታትን ወደኃላ ተመልሷ ማመንዠግ ጀመረ ፡፡የ12 አመት ጮርቃ ታዳጊ እያሉ እንደተለመደው 22 በሚገኝ በረንዳቸው ላይ በተለመደው መልኩ ተኝተው ነበር፡፡ሰዓቱ ልክ አሁን ባለበት ተመሳሳይ ሰዓት ላይ ነው ፡፡ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ፡፡እሱና እህቱ እርስ በርስ ተቃቅፈው አሮጌ ብርድልብስና ከላይ ጆንያ ደርበውበት ጋደም ብለው ወጪ ወራጁን በማየት ላይ ነበሩ፡፡
‹‹ምነው ወንድሜ እንቅልፍ እምቢ አለህ እንዴ?››ስትል ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እህቴ…ያቺን ሴትዬ አየሻት?››
‹‹የቷን?››
‹‹ያቺ ከስልክ ፖሉ አጠገብ ያለችው ልጅ፡፡››
ከትከሻዋ ቀና አለችና አየቻት‹‹አዲሷን ልጅ እያልከኝ ነው?››
‹‹አዎ…አዲሷን ልጅ…፡፡››
👍73❤10🥰1
‹‹እና ምን ሆነች….ምነው ልብስ ሳላለበሰች ይበርዳታል ብለህ ሰጋህ እንዴ?››
‹‹አይ ብርድ እንደማይገድላት አውቃለው፡፡››
‹‹እና ታዲያ…?››
‹‹ቾንቤ ቅድም ሲያወራ ሰምቼው ነው፡፡ዛሬ ወሰድ ወሰድ አድርጌ ልምጣና ይህቺን አዲስ ልጅ እከካታለው ሲል ነበር፡፡››ብሎ ለእህቱ ነገራት፡፡
‹‹ታዲያ ይከካታ ..ምን ችግር አለው?፡፡››
በወቅቱ እንዲህ አይነት ነገር በየቀኑ የሚያዩትና የሚታዘዙት ነገር ስለነበር የወንድሟ የስጋት ምንጭ አልጋባትም ነበር፡፡
‹‹አልገባሽም እንዴ..?ሊጠጣ ነው የሄደው፡፡ደግሞ ታውቂያለሽ ከጠጣ ዊድ ስቦ ነው የሚመጣው፡፡እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሁሉ ነገሩ ነው የሚቀየረው፡፡እምቢ ብላ ከታገለችው….እንደዛች ልጅ ይገድላታል፡፡››
ዝግንን አላት፡፡የወንድሟ ስጋት ወዲያው ነበር የገባት፡፡ከዛ ገጠመኛቸው ከ3 ወር በፊት ከለሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ አንድ አዲስ ጓዳና የወጣች ልጅ አብሬሽ ልተኛ ሲላት እሷ አይሆንም ብላ ስትታገለው ግንባሯን ብሎ ሲገድላት ሁለቱም በተኙበት ሆነው እያጨነቆሩ ተመልክተውታል፡፡ከዛ ከጓደኞቹ ጋር ተሸከመው ይዘዋት በመሄድ ሬሳዋን የሆነ ቦታ እንደቀበሩት ያውቃሉ፡፡
‹‹አንተ እውነትን ነው ምን እናድርግ?››ወዲያው ነበር ስጋቱ የተጋባባት፡፡
‹‹እኔ እንጃ ግን ባትሞት ደስ ይለኛል…..፡፡››ብሎ ነበር የመለሰላት፡፡
እሱ ሰው ጠል እንደሆነ ታውቃለች..በወቅቱ እንደዛ አይነት ግራ መጋባት የታየባት ይህቺ ሴት እንዴት እንደሳዘነችው ግራ በመጋባቷ ምክንያት ነው፡፡
‹‹ወንድሜ.. ለሰው ማዘን ጀመርክ አይደል?››
‹‹አይ በፍፅም …ሰዎች መቼም ቢሆን መቼም ሊታዘንላቸው አይገባም፡፡እርስ በርስ ቢጫረሱም ደስ ይለኛል፡፡››
የተናገረው ነገር የእውነት እንዳልሆነ ሁለቱም ያውቃሉ…ናኦል መቼም በሌላ ሰው ላይ ጨክኖ አይጨክንም….ሁል ጊዜ ጥንከር ያለ አንደበትና ልስልስ ያለ ልብ ያለው ልጅ ነው፡፡ጭካኔና ቆራጥነት የእህቱ የኑሀሚ መገለጫ ነው፡፡‹‹እና ታዲያ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹እኔ እንጃ እኔ በሆነ ምክንያት ተለይቼሽ ብቻሽን እንዲህ ቁርምድ ብለሽ…የሆኑ ጉልቤ ወንዶች ሊተናኮሉሽ….ብቻ እንደዛ አስቤ ነው ሙዴ የተከነተው…እህቴ ብትሆንስ ብዬ አስቤ ነው?››
‹‹እኔ ምን አልኩ …ለሰው እኮ እንዲህ ነው የሚታዘነው..ቆይ መጣሁ፡፡››አሮጌውን ብርድ ልብስና ጆንያ ከላዮ ገፋ ተነሳች…፡፡
‹‹ምን እየሰራሽ ነው…?››
‹‹እንድትባንን ኢንፎ ልስጣታ››
‹‹ኸረ ካወቀ ይተናኮለናል፡፡››
‹‹ግድየለህም..አያውቅም››አለችና ሄደች፡፡በዛን ወቅትም ሆነ አሁን ትልቅ ሆነውም ጭምር ከእሱ ይልቅ እህቱ ደፋርና የድርጊት ሰው ነች፡፡አስባ ሳትጨርስ ለማድረግ ትንደረደራለች..እሱ ደግሞ በተቃራኒው በማሰብ ረጅም ጊዜ ይወስዳል፡፡
ኑሀሚ ወደልጅቷ ቀርባ ባየቻት ጊዜ ..የምትገርም ሴት ሆና ነበር ያገኘቻት፡፡የእብድ ገፀ-ባህሪ ለመጫወት የተዘጃጀች አማተር ተዋናይ እንጂ የጎዳና ቋሚ ኑዋሪ አትመስልም፡፡የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደ ቢሆንም ግን ለክፉ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ፀጉሯ ጭፍርር ብሎ እንደ አንፑሎ ወደላይ ተጠቅልሎ በቀይ ጨርቅ ታስሮ ነበር ፡፡አይኖቾ ተቁለጭላጭና ንቁ ነበሩ፡፡ቀጭን ብትሆንም ሰውነቷ ግን የተጎዳ አይነት ሆኖ አላገኘችውም …››
‹‹ሲስቱ እንዴት ነሽ?››በሚል ንግግር ነበር የጀመረችው፡፡
‹‹አለው ጩጬዋ..››
‹‹አዲስ ነሽ?››
‹‹አዎ ምነው? ግብር ልትቀፍይኝ ነው እንዴ የመጣሽው?፡፡ አለቻት፡፡
‹‹አይ እዛ ጋር አብሮኝ የተኛው ወንድሜ ነው….መንታ ወንድሜ ..አሳዝነሽው ነው››
‹‹የበረደኝ መሰለው ወይስ ተከየፈብኝ?››
‹‹አረ አይደለም…››ስሯ ተቀመጠችና በሹክሹክታ ‹‹ለእኛ እንደ ሀለቃ የሚታይ ጉልቤና ሰይጣን የሆነ ቾንቢ የሚባል ልጅ አለ፡፡አሁን ሊጠጣ ሄዷል ..ዊድም ያቦናል፡፡አሁን መምጫው ነው..››
‹‹እና?››
‹‹ወንድሜ ሲዶልት ሰምቶታል››
‹‹ማለት? ስለምንድነው የዶለተው.?››
‹‹አንቺን ሊከካሽ ፈልጓል መሰለኝ….››
ኑሀሚ ልጅቷ ፊቷ ላይ ድንጋጤና ፍራቻ አያለሁ ብላ ጠብቃ ነበር፡፡ግን በፈገግታ የታጀበ ሹፈት ነበር ያሳየቻት፡፡
‹‹ምነው ስታይኝ ባቄላ መስላለሁ እንዴ? ….ለማንኛውም ..ወንድምሽን አመሰግናለሁ ለእኔ ብዙም አትጨነቅ ብላሀለች በይልኝ፡፡››
‹‹እና ሳይመጣ ዞር በያ …እዛ ቅያሱ ጋር ፖሊስ ጣቢያ አለ ..እዛ አካባቢ መደቀሻ ብትፈልጊ ይሻላል፡፡››የተሻለ ነው ያለችውን ምክር ለገሰቻት፡፡
‹‹አይ አታስቢ እዚሁ ተመችቶኛል…ቾንቤ ያልሺውን አያሳስብሽ፡፡ ሊታናኮለኝ ከፈለገ በቁንጥጫ አስተካክለዋልው›››
ሳቀችባት..‹‹ቾምቤ ማለት እኮ የእኛ እኩያ አይደለም ..የ30 አመት ግብዳ ጎረምሳ ነው…፡፡››
‹‹ገባኝ፡፡››
‹‹አይ እሱ እንኳን የገባሽ አይመስለኝም፡፡ለማንኛውም የራስሽ ጉዳይ… አላስጠነቀቁኝም እንዳትይ፡፡እርግጥ ከቤት ተጣልተሸ ተስፋ ቆርጠሸ እራስሽን ስለማጥፋት እያሰብሽ ከሆነ..ትክክል ነሽ.. መጥቶ ሲከመርብሽ ትንሽ ብቻ መታገል ነው ሚጠበቅብሽ፡፡ከዛ እሱ ይተባበርሻል..የሬሳሽም ደብዛው አይገኝም፡፡››
‹‹እሺ እንዳልሺኝ አደርጋለሁ….ትንሽ መታገል አይከብደኝም፡፡››
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹አይ ብርድ እንደማይገድላት አውቃለው፡፡››
‹‹እና ታዲያ…?››
‹‹ቾንቤ ቅድም ሲያወራ ሰምቼው ነው፡፡ዛሬ ወሰድ ወሰድ አድርጌ ልምጣና ይህቺን አዲስ ልጅ እከካታለው ሲል ነበር፡፡››ብሎ ለእህቱ ነገራት፡፡
‹‹ታዲያ ይከካታ ..ምን ችግር አለው?፡፡››
በወቅቱ እንዲህ አይነት ነገር በየቀኑ የሚያዩትና የሚታዘዙት ነገር ስለነበር የወንድሟ የስጋት ምንጭ አልጋባትም ነበር፡፡
‹‹አልገባሽም እንዴ..?ሊጠጣ ነው የሄደው፡፡ደግሞ ታውቂያለሽ ከጠጣ ዊድ ስቦ ነው የሚመጣው፡፡እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሁሉ ነገሩ ነው የሚቀየረው፡፡እምቢ ብላ ከታገለችው….እንደዛች ልጅ ይገድላታል፡፡››
ዝግንን አላት፡፡የወንድሟ ስጋት ወዲያው ነበር የገባት፡፡ከዛ ገጠመኛቸው ከ3 ወር በፊት ከለሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ አንድ አዲስ ጓዳና የወጣች ልጅ አብሬሽ ልተኛ ሲላት እሷ አይሆንም ብላ ስትታገለው ግንባሯን ብሎ ሲገድላት ሁለቱም በተኙበት ሆነው እያጨነቆሩ ተመልክተውታል፡፡ከዛ ከጓደኞቹ ጋር ተሸከመው ይዘዋት በመሄድ ሬሳዋን የሆነ ቦታ እንደቀበሩት ያውቃሉ፡፡
‹‹አንተ እውነትን ነው ምን እናድርግ?››ወዲያው ነበር ስጋቱ የተጋባባት፡፡
‹‹እኔ እንጃ ግን ባትሞት ደስ ይለኛል…..፡፡››ብሎ ነበር የመለሰላት፡፡
እሱ ሰው ጠል እንደሆነ ታውቃለች..በወቅቱ እንደዛ አይነት ግራ መጋባት የታየባት ይህቺ ሴት እንዴት እንደሳዘነችው ግራ በመጋባቷ ምክንያት ነው፡፡
‹‹ወንድሜ.. ለሰው ማዘን ጀመርክ አይደል?››
‹‹አይ በፍፅም …ሰዎች መቼም ቢሆን መቼም ሊታዘንላቸው አይገባም፡፡እርስ በርስ ቢጫረሱም ደስ ይለኛል፡፡››
የተናገረው ነገር የእውነት እንዳልሆነ ሁለቱም ያውቃሉ…ናኦል መቼም በሌላ ሰው ላይ ጨክኖ አይጨክንም….ሁል ጊዜ ጥንከር ያለ አንደበትና ልስልስ ያለ ልብ ያለው ልጅ ነው፡፡ጭካኔና ቆራጥነት የእህቱ የኑሀሚ መገለጫ ነው፡፡‹‹እና ታዲያ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹እኔ እንጃ እኔ በሆነ ምክንያት ተለይቼሽ ብቻሽን እንዲህ ቁርምድ ብለሽ…የሆኑ ጉልቤ ወንዶች ሊተናኮሉሽ….ብቻ እንደዛ አስቤ ነው ሙዴ የተከነተው…እህቴ ብትሆንስ ብዬ አስቤ ነው?››
‹‹እኔ ምን አልኩ …ለሰው እኮ እንዲህ ነው የሚታዘነው..ቆይ መጣሁ፡፡››አሮጌውን ብርድ ልብስና ጆንያ ከላዮ ገፋ ተነሳች…፡፡
‹‹ምን እየሰራሽ ነው…?››
‹‹እንድትባንን ኢንፎ ልስጣታ››
‹‹ኸረ ካወቀ ይተናኮለናል፡፡››
‹‹ግድየለህም..አያውቅም››አለችና ሄደች፡፡በዛን ወቅትም ሆነ አሁን ትልቅ ሆነውም ጭምር ከእሱ ይልቅ እህቱ ደፋርና የድርጊት ሰው ነች፡፡አስባ ሳትጨርስ ለማድረግ ትንደረደራለች..እሱ ደግሞ በተቃራኒው በማሰብ ረጅም ጊዜ ይወስዳል፡፡
ኑሀሚ ወደልጅቷ ቀርባ ባየቻት ጊዜ ..የምትገርም ሴት ሆና ነበር ያገኘቻት፡፡የእብድ ገፀ-ባህሪ ለመጫወት የተዘጃጀች አማተር ተዋናይ እንጂ የጎዳና ቋሚ ኑዋሪ አትመስልም፡፡የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደ ቢሆንም ግን ለክፉ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ፀጉሯ ጭፍርር ብሎ እንደ አንፑሎ ወደላይ ተጠቅልሎ በቀይ ጨርቅ ታስሮ ነበር ፡፡አይኖቾ ተቁለጭላጭና ንቁ ነበሩ፡፡ቀጭን ብትሆንም ሰውነቷ ግን የተጎዳ አይነት ሆኖ አላገኘችውም …››
‹‹ሲስቱ እንዴት ነሽ?››በሚል ንግግር ነበር የጀመረችው፡፡
‹‹አለው ጩጬዋ..››
‹‹አዲስ ነሽ?››
‹‹አዎ ምነው? ግብር ልትቀፍይኝ ነው እንዴ የመጣሽው?፡፡ አለቻት፡፡
‹‹አይ እዛ ጋር አብሮኝ የተኛው ወንድሜ ነው….መንታ ወንድሜ ..አሳዝነሽው ነው››
‹‹የበረደኝ መሰለው ወይስ ተከየፈብኝ?››
‹‹አረ አይደለም…››ስሯ ተቀመጠችና በሹክሹክታ ‹‹ለእኛ እንደ ሀለቃ የሚታይ ጉልቤና ሰይጣን የሆነ ቾንቢ የሚባል ልጅ አለ፡፡አሁን ሊጠጣ ሄዷል ..ዊድም ያቦናል፡፡አሁን መምጫው ነው..››
‹‹እና?››
‹‹ወንድሜ ሲዶልት ሰምቶታል››
‹‹ማለት? ስለምንድነው የዶለተው.?››
‹‹አንቺን ሊከካሽ ፈልጓል መሰለኝ….››
ኑሀሚ ልጅቷ ፊቷ ላይ ድንጋጤና ፍራቻ አያለሁ ብላ ጠብቃ ነበር፡፡ግን በፈገግታ የታጀበ ሹፈት ነበር ያሳየቻት፡፡
‹‹ምነው ስታይኝ ባቄላ መስላለሁ እንዴ? ….ለማንኛውም ..ወንድምሽን አመሰግናለሁ ለእኔ ብዙም አትጨነቅ ብላሀለች በይልኝ፡፡››
‹‹እና ሳይመጣ ዞር በያ …እዛ ቅያሱ ጋር ፖሊስ ጣቢያ አለ ..እዛ አካባቢ መደቀሻ ብትፈልጊ ይሻላል፡፡››የተሻለ ነው ያለችውን ምክር ለገሰቻት፡፡
‹‹አይ አታስቢ እዚሁ ተመችቶኛል…ቾንቤ ያልሺውን አያሳስብሽ፡፡ ሊታናኮለኝ ከፈለገ በቁንጥጫ አስተካክለዋልው›››
ሳቀችባት..‹‹ቾምቤ ማለት እኮ የእኛ እኩያ አይደለም ..የ30 አመት ግብዳ ጎረምሳ ነው…፡፡››
‹‹ገባኝ፡፡››
‹‹አይ እሱ እንኳን የገባሽ አይመስለኝም፡፡ለማንኛውም የራስሽ ጉዳይ… አላስጠነቀቁኝም እንዳትይ፡፡እርግጥ ከቤት ተጣልተሸ ተስፋ ቆርጠሸ እራስሽን ስለማጥፋት እያሰብሽ ከሆነ..ትክክል ነሽ.. መጥቶ ሲከመርብሽ ትንሽ ብቻ መታገል ነው ሚጠበቅብሽ፡፡ከዛ እሱ ይተባበርሻል..የሬሳሽም ደብዛው አይገኝም፡፡››
‹‹እሺ እንዳልሺኝ አደርጋለሁ….ትንሽ መታገል አይከብደኝም፡፡››
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍77❤14🔥3
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከዛ በኃላ ኑሀሚ በመገረም እንደተዋጠች ፊቷን አዙራ ወደወንድሟ ነበር የተመለሰችው፡፡ እንደደረሰች ጆንያውንና አሮጌ ብርድልብሱን ገለጠችና ወንድሟ እቅፍ ውስጥ ገባች፡፡
‹‹ምነው አኮረፍሽ?››
‹‹አረ ይህቺ ደነዝ ነች…ጭራሽ ታሾፋለች፡፡››
‹‹ይገልሻል አላልሻትም?››
‹‹አይገባትም አልኩህ እኮ …የጨለለች ሳትሆን አትቀርም ፡፡››
ወዲያው ንግግራቸውን ሳያገባድዱ ነበር የቾንቤ ድምፅ የተሰማው .. እያጓራና እየለፈለፈ ወደእነሱ እየቀረበ ነበር…‹‹ተሸፋፈኚ ..ተሸፋፈኚ….››ናኦል እህቱን አስጠነቀቀ፡፡ሁለቱም ተሸፋፈኑና አይኖቻቸውን በብርድልብሱ ቀዳዳ አጨንቁረው የሚሆነውን ለመመልከት ዝግጁ ሆኑ፡፡እንደጠበቁት ቾንቤ እየለፈለፈና እየፎከረ ቀጥታ ወደልጅቷ ነበር የሄደው፡፡ዘና ብላ ከተቀመጠችበት ነቅነቅ ሳትል እየጠበቀችው ነበር፡፡
‹‹ወንድሜ አለቀላት..ስታሳዝን››ኑሀሚ በቀጣይ የሚሆነውን እየገመተች ተሸማቀቀች፡፡
ቾንቤ ደረሰባትና ዘፍ ብሎ ስሯ ቁጭ አለ፡፡ያ ሁሉ ሲሆን ከልጅቷ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እየታያቸው አልነበረም ፡፡
‹‹ምንም እየተንቀሳቀሰች እኮ አይደለም፡፡››
‹‹አዎ መሞት እንደምትፈልግ ነግራኛለች…እንዲገድላት ነው የምትፈልገው፡፡›› ከልጅቷ ጋር ባደረገችው ንግግር የገባት የመሰላትን ለወንድሟ አብራራችለት፡፡
ቾምቤ ሲያቅፋት ተመለከቱ…ወደኃላ ሊያስተኛት እየሞከረ ነበር፡፡ከዛ እጇን አዙራ ስታቅፈው አዩ…..‹‹እንዴ ልጅቷ እራሷ መከካት ፈልጋለች መሰለኝ?›› ናኦል ነበር ተናጋሪው፡፡
ቀስ ብላ ወደኃላ አስተኛችውና እሷ ተነስታ ቆመች፡፡ከዛ ልብሷን ረገፍ ረገፍ አደረገችና ስሯ የነበረውን አንድ ጥቁር ፔስታል ይዛ ሁለት ሜትር ያህል ከእሱ ራቅ አለችና ተቀመጠች..ቾምቤ እንደተዘረረ ነው..እየተንቀሳቀሰ አይደለም፡፡››
‹‹ወይኔ አይንቀሳቀስም እኮ፡፡››
‹‹ምን አደረገችው?››
‹‹እኔ እንጃ…ሁለቱም ከተሸፋፈኑበት ገልጠው ወጡ፡፡አስር ደቂቃ ያህል ጠበቁ….፡፡ምንም የተለየ ነገር እየታያቸው አልነበረም…፡፡እንደውም ልጅቷ ከፔስታሏ ውስጥ ሻርፕ ነገር አውጥታ ፊቷን ተሸፋፈነችና ሸርተት ብላ ግንቡን ተደግፋ እንደመተኛት አለች፡፡
‹‹እንዴ ገደላት ስንል ገደለችው እንዴ….?››እሱ የለበሰውን ከላዩ ገፎ ተነሳ
‹‹ወዴት ነው?››ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹ …ሄጄ ላጣራ?›››
‹‹ቆይ አብረን እንሂድ ፡፡››አለችና እሷም ተነሳች፡፡ፈራ ተባ እያሉ ተጠጉ፡፡ ደረሱ…. ቾምቤ እጥፍጥፍ ብሎ እንደተኛ ነበር፡፡
‹‹እ ጩጬዎቹ ምንነው?››
‹‹ደየመብሽ እንዴ?››ናኦል ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹ጎንበስ ብለህ እየው…..እኔ እንዲተኛ ብቻ ነው ያደረኩት፡፡ሞቶም ከሆነ የእኔ የእጅ የለበትም፡፡››
‹‹ካራቲስት ነገር ነሽ እንዴ..?እንዴት አድርገሽ ቆለፍሽው?››
ናኦል ጎንበስ አለና ትንፋሹን አዳመጠው፡፡እውነትም አልሞተም፡፡ ትንፋሹ በደንብ ይሰማል፡፡
‹‹አይ ሰላም ነው፡፡››
‹‹ኑ እስቲ ከጎኔ ተቀመጡ፡፡››
ሁለቱ ታዳጊዎች እርስበርስ ተያዩ፡፡ የዚህችን እንግዳ ሴት ግብዣ እንቀበል ወይስ ይቅርብን ሚለውን በአይን እየተነጋገሩ ይመስል ነበር፡፡ከዛ እንደተግባባ ሰው ወደእሷ ቀረቡና እሱ በቀኟ እሷ ደግሞ በግራዋ በኩል ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ቆያችሁ…ማለቴ በርንዳ ላይ?››ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹አዎ አንድ አመት ሊሞላን ነው፡፡››
‹‹ታዲያ አይተናኮሏችሁም…በተለይ አንቺን፡፡››
‹‹አይ እንደመጣን ሰሞን ያስቸግሩን ነበር..ግን እዛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሰራ ፓሊስ አባታችንን በደንብ ያውቀው ነበር..እና እዚህ ሰፈር ላሉት ጉልቤዎች በጠቅላላ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡አንድ ሰው እኛን ቢያጠቃ ሁሉንም እንደሚያጠፋችው ስለነገራቸው አይነኩንም፡፡››በሰላም እየኖሩ ያሉበትን ምክንያት በግልፅ አብራሩላት፡፡
‹‹ለጊዜው ጥሩ ነው..ግን እዚህ ጎዳና ላይ እስከኖራችሁ ድረስ በሌላ ሰው ላይ ተማምናችሁ እስከመጨረሻው ከጥቃት ተጠብቃችሁ መኖር አትችሉም፡፡ያላችሁት ፖሊስ አዛዥ የመንግስት ቅጥረኛ ነው፡፡መንግስት ደግሞ ነገ ተነስቶ ሌላ ወረዳ ወይም ሌላ ከተማ ሊመድበው ይችላል፡፡የዛን ጊዜስ ምን ትሆናላችሁ?››በውድቅት ለሊት ቀን እንኳን ቢሆን መመለስ ሚከብድ ጥያቄ ነበር የጠየቀቻቸው፡፡፡
‹‹እውነትሽን ነው..ይሄ ጉዳይ ሁሌ ያስጨንቀኛል….ለእኔ ሳይሆን ለእህቴ?››የሚል መልስ እንደሰጣት ያስታውሳል፡፡
‹‹እንዴ እንዲህ እንደምታስብ እኮ አንድም ቀን ነግረኸኝ አታውቅም…?›› ኑሀሚ በጭለማው ውስጥ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ብዬሽ እንድትፈሪ አደርጋለሁ?››
ልጅቷ ቦርሳዋን በረበረችና ትንሽ የመጠጥ ብልቃጥ በማውጣት ክዳኑን አሽከርክራ ከፈተችና ተጎነጨችለትና መልሳ በመክደን ከፊት ለፊቷ አስቀመጠች፡፡
‹‹የት ነበርሽ..?ማለቴ እዚህ ሰፈር እንዴት ልትመጪ ቻልሽ?››
‹‹እንዲሁ በዚህ ሳልፍ ሰፈሩ ደስ አለኝና እዚሁ አረፍ አልኩ፡፡››
‹‹እና ነገ ትሄጂያለሽ ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ… ሂጂ ሂጂ ካለኝ እሄዳለሁ፡፡››
ናኦል‹‹ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡እንደዛ ያላት ልጅቷ በእድሜ በጣም ታላቁ ብትሆንም ገና እንዳያት በጣም ስለወደዳት ነበር…የዛን ጊዜ ስለእሷ የተሰማው ስሜት ዛሬም ድረስ በልቡ ላይ ተቋጥሮ እንደቆረቆረው ነው፡፡
ዞር ብላ አየችውና እጆቾን ዘርግታ ፀጉሩን እያሻሸች‹‹ጎረምሳው…ተከየፍክብኝ እንዴ?››ነበር ያለችው፡፡
እንደማፈር አለና …አቀርቅሮ ዝም አላት፡፡በወቅቱ ብዙ ነገር ሊመልስላት ፈልጎ ነበር፡፡ግን ከንፈሮቹ ተነቃንቀው ቃላት ከአንደበቱ ማውጣት አልቻሉም፡፡
‹‹አይዞኝ ስቀልድ ነው፡፡ለማንኛውም አሁን ሂዱና ተኙ፡፡.ነገ እናወራለን፡፡››
‹‹እሺ›› አሉና ሁላቱም ከግራና ከቀኞ ተነስተው ባዶ መሬት ላይ ዘና ብሎ በመዘረጋጋት ተኝቶ እያንኳራፋ ያለውን ቾንቤን በጎሪጥ እያዩ በስሩ አልፈው ወደመኝታቸው ሄዱ፡፡ኑሀሚና ናኦል ጥዋት ተነስተው አካባቢውን ሲቃኙ የለሊቷ ልጅ ተነስታ ልክ እንደደላው የቤት ልጅ ስፖርት እየሰራች ነበር ያገኞት፡፡…ሳንቾ በአካባቢው የለም፡፡ሌሎች ጓደኞቻቸው የተወሰኑት ተኝታዋል…የተቀሩትም ወደሚሄድበት ሄደዋል፡፡ለብሳው ያደሩትን አሮጌ ብርድልብስ እና ጆንያ ከስር የሚያነጥፉትን ካርቶን ስብስበውና አጣጥፈው ወደጥግ በማድረግ ዘወትር እንደሚያደርጉት በላዩ ላይ ድንጋይ ጭኑበት እና ወደልጅቷ ሄዱ ፡፡
‹‹እ ጩጬዎች ..ተነሳችሁ፡፡››በሚል ጥያቄ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡
‹‹አዎ…ቡሌ ፍለጋ ልንሄድ ነው… ትመጪያለሽ?››
‹‹አዎ…››አለችና እስፖርቷን አቋርጣ ..ፔስታሏን ያዘችና ተከተለቻቸው፡፡
‹‹እ የት ነው ምንበላው?
ሁለቱም አፍጥጠው አዮት‹‹እንዴ ገና ሆቴል ሄደን ተመላሽ ጠይቀን ነዋ››ኑሀሚ ነበረች በመኮሳተር የመለሰችላት፡፡
‹‹አይ ብር አለኝ ..ለምን ገዝተን አንበላም…፡፡››
ሁለቱም በደስታ ፈገግ አሉ…‹‹ስንት አለሽ..?››ናኦል ነበር ጠያቂው፡፡
‹‹ጅንስ ሱሪ ኪሷ ውስጥ እጇን ሰደደችና ሁለት መቶ ብር መዛ አወጣች…››
‹‹አይበቃም…››
‹‹አረ ይበቃል..ነይ ዝናሽ ጋር እንሂድ፡፡››
‹‹ዝናሽ ማነች…?››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከዛ በኃላ ኑሀሚ በመገረም እንደተዋጠች ፊቷን አዙራ ወደወንድሟ ነበር የተመለሰችው፡፡ እንደደረሰች ጆንያውንና አሮጌ ብርድልብሱን ገለጠችና ወንድሟ እቅፍ ውስጥ ገባች፡፡
‹‹ምነው አኮረፍሽ?››
‹‹አረ ይህቺ ደነዝ ነች…ጭራሽ ታሾፋለች፡፡››
‹‹ይገልሻል አላልሻትም?››
‹‹አይገባትም አልኩህ እኮ …የጨለለች ሳትሆን አትቀርም ፡፡››
ወዲያው ንግግራቸውን ሳያገባድዱ ነበር የቾንቤ ድምፅ የተሰማው .. እያጓራና እየለፈለፈ ወደእነሱ እየቀረበ ነበር…‹‹ተሸፋፈኚ ..ተሸፋፈኚ….››ናኦል እህቱን አስጠነቀቀ፡፡ሁለቱም ተሸፋፈኑና አይኖቻቸውን በብርድልብሱ ቀዳዳ አጨንቁረው የሚሆነውን ለመመልከት ዝግጁ ሆኑ፡፡እንደጠበቁት ቾንቤ እየለፈለፈና እየፎከረ ቀጥታ ወደልጅቷ ነበር የሄደው፡፡ዘና ብላ ከተቀመጠችበት ነቅነቅ ሳትል እየጠበቀችው ነበር፡፡
‹‹ወንድሜ አለቀላት..ስታሳዝን››ኑሀሚ በቀጣይ የሚሆነውን እየገመተች ተሸማቀቀች፡፡
ቾንቤ ደረሰባትና ዘፍ ብሎ ስሯ ቁጭ አለ፡፡ያ ሁሉ ሲሆን ከልጅቷ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እየታያቸው አልነበረም ፡፡
‹‹ምንም እየተንቀሳቀሰች እኮ አይደለም፡፡››
‹‹አዎ መሞት እንደምትፈልግ ነግራኛለች…እንዲገድላት ነው የምትፈልገው፡፡›› ከልጅቷ ጋር ባደረገችው ንግግር የገባት የመሰላትን ለወንድሟ አብራራችለት፡፡
ቾምቤ ሲያቅፋት ተመለከቱ…ወደኃላ ሊያስተኛት እየሞከረ ነበር፡፡ከዛ እጇን አዙራ ስታቅፈው አዩ…..‹‹እንዴ ልጅቷ እራሷ መከካት ፈልጋለች መሰለኝ?›› ናኦል ነበር ተናጋሪው፡፡
ቀስ ብላ ወደኃላ አስተኛችውና እሷ ተነስታ ቆመች፡፡ከዛ ልብሷን ረገፍ ረገፍ አደረገችና ስሯ የነበረውን አንድ ጥቁር ፔስታል ይዛ ሁለት ሜትር ያህል ከእሱ ራቅ አለችና ተቀመጠች..ቾምቤ እንደተዘረረ ነው..እየተንቀሳቀሰ አይደለም፡፡››
‹‹ወይኔ አይንቀሳቀስም እኮ፡፡››
‹‹ምን አደረገችው?››
‹‹እኔ እንጃ…ሁለቱም ከተሸፋፈኑበት ገልጠው ወጡ፡፡አስር ደቂቃ ያህል ጠበቁ….፡፡ምንም የተለየ ነገር እየታያቸው አልነበረም…፡፡እንደውም ልጅቷ ከፔስታሏ ውስጥ ሻርፕ ነገር አውጥታ ፊቷን ተሸፋፈነችና ሸርተት ብላ ግንቡን ተደግፋ እንደመተኛት አለች፡፡
‹‹እንዴ ገደላት ስንል ገደለችው እንዴ….?››እሱ የለበሰውን ከላዩ ገፎ ተነሳ
‹‹ወዴት ነው?››ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹ …ሄጄ ላጣራ?›››
‹‹ቆይ አብረን እንሂድ ፡፡››አለችና እሷም ተነሳች፡፡ፈራ ተባ እያሉ ተጠጉ፡፡ ደረሱ…. ቾምቤ እጥፍጥፍ ብሎ እንደተኛ ነበር፡፡
‹‹እ ጩጬዎቹ ምንነው?››
‹‹ደየመብሽ እንዴ?››ናኦል ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹ጎንበስ ብለህ እየው…..እኔ እንዲተኛ ብቻ ነው ያደረኩት፡፡ሞቶም ከሆነ የእኔ የእጅ የለበትም፡፡››
‹‹ካራቲስት ነገር ነሽ እንዴ..?እንዴት አድርገሽ ቆለፍሽው?››
ናኦል ጎንበስ አለና ትንፋሹን አዳመጠው፡፡እውነትም አልሞተም፡፡ ትንፋሹ በደንብ ይሰማል፡፡
‹‹አይ ሰላም ነው፡፡››
‹‹ኑ እስቲ ከጎኔ ተቀመጡ፡፡››
ሁለቱ ታዳጊዎች እርስበርስ ተያዩ፡፡ የዚህችን እንግዳ ሴት ግብዣ እንቀበል ወይስ ይቅርብን ሚለውን በአይን እየተነጋገሩ ይመስል ነበር፡፡ከዛ እንደተግባባ ሰው ወደእሷ ቀረቡና እሱ በቀኟ እሷ ደግሞ በግራዋ በኩል ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ቆያችሁ…ማለቴ በርንዳ ላይ?››ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹አዎ አንድ አመት ሊሞላን ነው፡፡››
‹‹ታዲያ አይተናኮሏችሁም…በተለይ አንቺን፡፡››
‹‹አይ እንደመጣን ሰሞን ያስቸግሩን ነበር..ግን እዛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሰራ ፓሊስ አባታችንን በደንብ ያውቀው ነበር..እና እዚህ ሰፈር ላሉት ጉልቤዎች በጠቅላላ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡አንድ ሰው እኛን ቢያጠቃ ሁሉንም እንደሚያጠፋችው ስለነገራቸው አይነኩንም፡፡››በሰላም እየኖሩ ያሉበትን ምክንያት በግልፅ አብራሩላት፡፡
‹‹ለጊዜው ጥሩ ነው..ግን እዚህ ጎዳና ላይ እስከኖራችሁ ድረስ በሌላ ሰው ላይ ተማምናችሁ እስከመጨረሻው ከጥቃት ተጠብቃችሁ መኖር አትችሉም፡፡ያላችሁት ፖሊስ አዛዥ የመንግስት ቅጥረኛ ነው፡፡መንግስት ደግሞ ነገ ተነስቶ ሌላ ወረዳ ወይም ሌላ ከተማ ሊመድበው ይችላል፡፡የዛን ጊዜስ ምን ትሆናላችሁ?››በውድቅት ለሊት ቀን እንኳን ቢሆን መመለስ ሚከብድ ጥያቄ ነበር የጠየቀቻቸው፡፡፡
‹‹እውነትሽን ነው..ይሄ ጉዳይ ሁሌ ያስጨንቀኛል….ለእኔ ሳይሆን ለእህቴ?››የሚል መልስ እንደሰጣት ያስታውሳል፡፡
‹‹እንዴ እንዲህ እንደምታስብ እኮ አንድም ቀን ነግረኸኝ አታውቅም…?›› ኑሀሚ በጭለማው ውስጥ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ብዬሽ እንድትፈሪ አደርጋለሁ?››
ልጅቷ ቦርሳዋን በረበረችና ትንሽ የመጠጥ ብልቃጥ በማውጣት ክዳኑን አሽከርክራ ከፈተችና ተጎነጨችለትና መልሳ በመክደን ከፊት ለፊቷ አስቀመጠች፡፡
‹‹የት ነበርሽ..?ማለቴ እዚህ ሰፈር እንዴት ልትመጪ ቻልሽ?››
‹‹እንዲሁ በዚህ ሳልፍ ሰፈሩ ደስ አለኝና እዚሁ አረፍ አልኩ፡፡››
‹‹እና ነገ ትሄጂያለሽ ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ… ሂጂ ሂጂ ካለኝ እሄዳለሁ፡፡››
ናኦል‹‹ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡እንደዛ ያላት ልጅቷ በእድሜ በጣም ታላቁ ብትሆንም ገና እንዳያት በጣም ስለወደዳት ነበር…የዛን ጊዜ ስለእሷ የተሰማው ስሜት ዛሬም ድረስ በልቡ ላይ ተቋጥሮ እንደቆረቆረው ነው፡፡
ዞር ብላ አየችውና እጆቾን ዘርግታ ፀጉሩን እያሻሸች‹‹ጎረምሳው…ተከየፍክብኝ እንዴ?››ነበር ያለችው፡፡
እንደማፈር አለና …አቀርቅሮ ዝም አላት፡፡በወቅቱ ብዙ ነገር ሊመልስላት ፈልጎ ነበር፡፡ግን ከንፈሮቹ ተነቃንቀው ቃላት ከአንደበቱ ማውጣት አልቻሉም፡፡
‹‹አይዞኝ ስቀልድ ነው፡፡ለማንኛውም አሁን ሂዱና ተኙ፡፡.ነገ እናወራለን፡፡››
‹‹እሺ›› አሉና ሁላቱም ከግራና ከቀኞ ተነስተው ባዶ መሬት ላይ ዘና ብሎ በመዘረጋጋት ተኝቶ እያንኳራፋ ያለውን ቾንቤን በጎሪጥ እያዩ በስሩ አልፈው ወደመኝታቸው ሄዱ፡፡ኑሀሚና ናኦል ጥዋት ተነስተው አካባቢውን ሲቃኙ የለሊቷ ልጅ ተነስታ ልክ እንደደላው የቤት ልጅ ስፖርት እየሰራች ነበር ያገኞት፡፡…ሳንቾ በአካባቢው የለም፡፡ሌሎች ጓደኞቻቸው የተወሰኑት ተኝታዋል…የተቀሩትም ወደሚሄድበት ሄደዋል፡፡ለብሳው ያደሩትን አሮጌ ብርድልብስ እና ጆንያ ከስር የሚያነጥፉትን ካርቶን ስብስበውና አጣጥፈው ወደጥግ በማድረግ ዘወትር እንደሚያደርጉት በላዩ ላይ ድንጋይ ጭኑበት እና ወደልጅቷ ሄዱ ፡፡
‹‹እ ጩጬዎች ..ተነሳችሁ፡፡››በሚል ጥያቄ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡
‹‹አዎ…ቡሌ ፍለጋ ልንሄድ ነው… ትመጪያለሽ?››
‹‹አዎ…››አለችና እስፖርቷን አቋርጣ ..ፔስታሏን ያዘችና ተከተለቻቸው፡፡
‹‹እ የት ነው ምንበላው?
ሁለቱም አፍጥጠው አዮት‹‹እንዴ ገና ሆቴል ሄደን ተመላሽ ጠይቀን ነዋ››ኑሀሚ ነበረች በመኮሳተር የመለሰችላት፡፡
‹‹አይ ብር አለኝ ..ለምን ገዝተን አንበላም…፡፡››
ሁለቱም በደስታ ፈገግ አሉ…‹‹ስንት አለሽ..?››ናኦል ነበር ጠያቂው፡፡
‹‹ጅንስ ሱሪ ኪሷ ውስጥ እጇን ሰደደችና ሁለት መቶ ብር መዛ አወጣች…››
‹‹አይበቃም…››
‹‹አረ ይበቃል..ነይ ዝናሽ ጋር እንሂድ፡፡››
‹‹ዝናሽ ማነች…?››
👍67❤8👎1
‹‹እዛ ነዳጅ ማደያው ጎን ዳስ ውስጥ ቆቆር ፤አሳምብሳና ሻይ ምናምን ምትሸጥ ጀለሳችን ነች፡፡ሳንቲም ሲኖረን እሷ ጋር ነው የሚንሄደው፡፡ጥሩ ልጅ ነች፡፡ ሳንቲም ሲጎድለን ሁሌ ትሞላልናለች፡፡››ናኦል አብራራላት፡፡
‹‹ጥሩ ነዋ በቃ እንሂድ ››ተስማሙና ወደእዛ ሄዱ፡፡ ሶስቱም በደንብ እስኪጠግቡ ቁርሳቸውን በሉ፡፡ እንደወጡ…‹‹በሉ ደህና ዋሉ፡፡›› ብላ ነበር የስንብት ቃል ያሰማቻቸው፡፡
ሁለቱም ያልጠበቁት ነገር ስለነበር ደነገጡ…‹‹ምነው ልትሄጂ ነው?››ናኦል በቅሬታ ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ ምነው?››
‹‹አይ ጥሩ ልጅ ነበርሽ….ባትሄጂ ደስ ይለን ነበር››
ፈገግ እያለች‹‹እሺ አንተ ደስ ካለህ ተመልሼ መጣለሁ፡፡››አለችው
‹‹በእውነት?››
‹‹አዎ የሆነ ቦታ ደርሼ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ እመጣለሁ፡፡››
‹‹እሺ ቸው.. እንዳትቀሪ››
‹‹እሺ በሉ ደህና ሁኑ፡፡›› ፊቷን አዙራ በተቃራኒው አቅጣጫ ነበር መጓዝ ጀመረች፡፡እንሱም ፊት ለፊታቸውን ይዘው ሶስት የሚሆኑ እርምጃዎች ከተራመዱ በኃላ ናኦል ድንገት ዞር አለና
‹‹እህቴ›› ሲል ተጣራ…ዞር አለች፡፡‹‹እ ምነው?››
‹‹ስምሽን እኮ አልነገርሽንም፡፡››
‹‹ምስራቅ እባላለሁ፡፡››ስሟ ከአንደበቷ ተስፈንጥሮ ሲወጣ ወዲያው ነበር ልቡ ላይ አርፎ ቅልጥልጥ በማለት ከመላ ሰውነቱ የተዋሀደው …..‹‹ምስራቅ…አንፀባራቂና በብርሀን የተሞላ ስም››ይላል ሁል ጊዜ፡፡ከዛ ‹‹የእኔ ደግሞ ናኦል ነው …የእህቴ ደግሞ ኑሀሚ፡፡››ብሎ ነበራት፡፡
‹‹እሺ ቸው ናኦል››ፊቷን አዞረችና እርምጃዋን ቀጠለች… ጎኑ ያለችው እህቱ በክርኗ ጎሰመችው
‹‹እንዴ ምን እየሆንሽ ነው…?ምን አደረኩ?››ግራ ተጋብቶ ጠየቃት፡፡
‹‹እህቴ አልካት እኮ፡፡››
‹‹እና ምን ችግር አለው?››
‹‹አንተ እኔን በምትጠራበት ስም ሌላ ትናንት ያወቅካትን ሴት ትጠራለህ…?ሆዳም ነገር ነህ፡፡ አሳንቡሳ ስለጋበዘችህ ነው አይደል?፡፡››የቅናት ወቀሳ ወቀሰችው፡፡
‹‹አይ አይደለም..ቆንጆ ስለሆነች ነው፡፡››አላት
‹‹ቆንጆ ብትሆንም እኮ ትልቅ ልጅ ነች… ሰላሳ አመት ይሆናታል፡፡››
‹‹አትዋሺ 25 ቢሆናት ነው፡፡››
‹‹ሀያ አምስት ቢሆናትም እኮ ትልቅ ነች ማለት ነው… አንተ እኮ ገና 11 አመትህ ነው…ታምራለች ትላለህ እንዴ?››አሾፈችበት፡፡
‹‹አሁን ስራ እስኪደርስ የት እንሂድ?››
በወቅቱ ሁለቱም በቀን ሰላሳ ብር የሚያስገኝላቸው ቋሚ ስራ ነበራቸው፡፡ስራው እዛው ሰፈር ካለ ጫት ቤት ጫትና መሰል ዕቃዎችን ደንበኛ ለሆኑ አምስት ሚሆኑ ሰዎች እንዳንዴም ቁጥራቸው እስከአስር ይሄዳል…ከ6-8 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በየቤታቸው ማድረስ ነበር፡፡ሁሉም ቤት የሚሄዱት አብረው ነው፡፡ከዛ የእለቱን ስራቸውን ሲያጠናቅቁ የጫት ቤቱ ልጅ 30 ብር ይሰጣቸዋል፡፡ታዲያ ብቸኛ ገቢያቸው ያ ብቻ አልነበረም..የሚወሰዱላቸውም ሰዎች አምስትም አስርም ብር ይሰጧቸው ስለነበር..በየቀኑ 50 ስልሳ ብር አካባቢ አንዳንዴም ከዛ በላይ ያገኛሉ፡፡
እዛ መስቀል አደባባይ በቀዘቀዘ ድንጋይ ላይ ተጎልቶ የሚያመነዥገውን ትዝታ ሳይጨርስ የስልኩ ጥሪ አባነነው፡፡የማያውቀው ስልክ ነው፡፡በዛ ውድቅት ለሊት ከሷ ውጭ ሌላ ሰው እንደማይሆን እርግጠኛ ነው ፡በፍጥነት አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ 22 ጎላጎል ህንፃ ፊት ለፊት ከ30 ደቂቃ በኃላ.. ትችላለህ?
‹‹አዎእችለለሁ፡› ስልኩተጠረቀመ፡
ድንግርግር አለው፡፡ናፍቀዋለች፡፡ብዙ የመግቢያ ሰላምታና የናፍቆት ንግግር ጠብቆ ነበር፡፡ምን አይነት ችግር አጋጥሞህ ነው? ብላ እንድትጠይቀውም ፈልጎ ነበር..ግን ከምኞቱ አንዱንም አላሞላችለትም፡፡‹‹ዋና መደወሏ ነው›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡እግሩን መንቀሳቀስ ግን በቀላሉ አልቻም፡፡ድንዝዝ ነበር ያለው..እንደምንም ለማፍታታትና ለመራመድ ከሁለት ደቂቃ በላይ አስፈልጎት ነበር፡፡መኪና ውስጥ ገባና ወደተባለው አቅጣጫ መንዳት ጀመረ፡፡በለሊት በአዲስአበባ ጎዳና መንዳት እንዴት ደስ ይላል?››ሲል አሰባ፡፡ከፊት የሚደነቀር መኪና የለ ፤በየደቂቃው ፍሬን እምቅ አድር መያዝ የለ፤ ከኃላ ሚያንባርቅ የመኪና ጥሩንባ የለ ››በማለት በነፃነት በመንዳቱ እተደነቀ የተባለበት ቦታ ከተባለበት ሰዓት ቀድሞ ደርሶ መኪናዋና ራቅ አድርጎ በማቆም ይጠብቅ ጀመር፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ አንድ ጥቁር መርቼዲስ ከወደ ቦሌ አቅጣጫ መጣችና አደባባዩን መዞር ጀመረች፡፡የመኪናውን የፊት መብራት ቦግ ብልጭ አድርጎ በማብራት ምልክት ሰጠ..እሷ ከሆነች ይገባታል፡፡ለረጅም ጊዜ አብረው የስለላ ስራ ይሰሩ በነበረበት ወቅት ከሚጠቀሙባቸው በርካታ የመግባቢያ ኮዶች መካከል አንዱን ነው የተጠቀመው፡፡መርቸዲሶ ቀጥታ ወደእሱ በመምጣት ዞራ ከእሱ ኃላ ቆመች፡፡ቀስ ብሎ ወረደና ወደ እሷ ሄደ፡፡ገቢናው ተከፈተለት፡፡ገባና ዘጋው፡፡ከቅድሙ የስልክ ልውውጥ በመነሳት ኮስተር ያለ ነገር ነበር የጠበቀው፡፡
በተቀመጠችበት ሆና ሁለት እጆቾን ዘረጋችና አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡ፊቱን አንገቷ ሰር ደፈቀው…ከገላዋ የሚወጣው ጠረን አፍንጫው ውስጥ ተመሰገ.. ወደውስጥ በጥልቀት ሳበው፡፡እየቃተተ በሚመስል የሰለለ ድምፅ‹‹በጣም ናፍቀሺኝ ነበር››አላት፡፡
ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ አይቶ እንደደነገጠባት የ12 ዓመት ልጅ አይደለም አሁን ጉርምስናውና በማጠናቀቅ ላይ ያለ የ27 አመት ሙሉ ወጣት ነው፤እሷ ደግሞ የ43 ዓመት ጎልማሳ፡፡አሁን ስለእሷ የሚሰማው የፍቅር ስቃይ አካላዊም ስነልቦናዊም ጭምር ነው፡፡ልቡም ነፍሱ ናቸው በእኩል የሚንሰፈሰፉላት፡፡ከእቅፎ አወጣችውና ጉንጩን ሳመችው፡፡እሱም በተመሳሳይ ሳማት፡፡
‹‹አርጅተሀል እኮ…ምነው አገባህ እንዴ?››
‹‹እንዴት ላገባ ችላለሁ?››አላት፡፡
‹‹እኔ እንጃ ጅርግፍግፍ ስትል ምን አልባት ሰርግ ሳትጠራኝ አግብተህ እንደሆነ ብዬ ነዋ፡፡ ››
‹‹እህቴ እንደዛ አይደለም ባክሽ …ችግር ላይ ነች፡፡››
‹‹እሱንማ መልዕክት ስትልክልኝ ነው ችግር ላይ መሆንህን ያወቅኩት ….ለመሆኑ ምን አይነት ወንጀል ውስጥ ገብተህ ነው?››የጠረጠረችውን ጠየቀችው፡፡በእሷ ሀሳብ ያው እንደልማዱ ከሆኑ ወንጀለኛ ብድኖች ጋር ተቀላቅሎ የሆነ ስራ ውስጥ በመግባት አሁን መውጫ መንገድ አጥቶ ወይ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ እሷ ከማጥ እንድታወጣው ፈልጎ እንደሆነ እርግጠኛ ሆና ነው ልትረዳወው የመጣችው፡፡ከዚህ በፊትም ከተመሳሳይ ማጥ ሶስት አራት ጊዜ አድነዋለች..አሁንም ከእሷ አቅም በላይ አይሁን እንጂ ታደርገዋለች፡፡ለእሷ እሱን መርዳትና ማገዝ እንደምርጫ ሳይሆን እንደግዴታ ነው፡፡
‹‹እህቴ በለፈው እኮ ቃል ገብቼልሻለሁ…አንቺን ችግር ውስጥ የሚያስገባ ምን አይነት መጥፎ ነገረ እንዳማልሰራ ነግሬሽ ነበር… ያንንም እስከቻልኩት ድረስ ቃሌን ጠብቄ መቀጠል ነው የምፈልገው፡፡››
እና ታዲያ በዚህ ውድቅት ለሊት መልዕክት የላክልኝ እንዳቅፍህና ጉንጮችህን እያገላበጥኩ እንድስምህ ነው እንዴ…?.እንደዛ ከሆነ ችግር ውስጥ ነህ፡፡››ብስጩዋ ሴት ከውስጦ ብቅ አለች፡፡
‹‹አረ አይደለም ..እህቴ ..ኑሀሚ ችግር ላይ ነች፡፡››
‹‹ምን ….ከሀገር ውጭ ያለች መስሎኝ ፣መቼ መጥታ መቼ ችግር ውስጥ ገባች?››
‹‹አይ እዛው ነች…››ብሎ የሆነውን ሁሉ በርዝር ነገራት፡፡ከእሱ ባልተናነሰ ሁኔታ አዘነች፡፡ሲነጋ ከብራዚል አምባሳደር ሆነ ከሌሎች የውጭ ጉዳይ ሰዎች ጋር በመነጋገር የሆነ ነገር እንደምታደርግ ቃል ገብታለት…የኑሀሚ ጉዳይ እልባት እስኪያገኝ ቀጥታ የሚደውልላትን ቁጥር ሰጥታው ከአንድ ሰዓት የአብሮንት ቆይታ በኃላ ተለየችውና እንደአመጣጧ ተመልሳ ሄደች ፡፡እሱም ሌላ ወዴት እንደሚሄድ ግራ ስለገባው ወደቤቱ ነዳው፡፡
✨ይቀጥላል✨
‹‹ጥሩ ነዋ በቃ እንሂድ ››ተስማሙና ወደእዛ ሄዱ፡፡ ሶስቱም በደንብ እስኪጠግቡ ቁርሳቸውን በሉ፡፡ እንደወጡ…‹‹በሉ ደህና ዋሉ፡፡›› ብላ ነበር የስንብት ቃል ያሰማቻቸው፡፡
ሁለቱም ያልጠበቁት ነገር ስለነበር ደነገጡ…‹‹ምነው ልትሄጂ ነው?››ናኦል በቅሬታ ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ ምነው?››
‹‹አይ ጥሩ ልጅ ነበርሽ….ባትሄጂ ደስ ይለን ነበር››
ፈገግ እያለች‹‹እሺ አንተ ደስ ካለህ ተመልሼ መጣለሁ፡፡››አለችው
‹‹በእውነት?››
‹‹አዎ የሆነ ቦታ ደርሼ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ እመጣለሁ፡፡››
‹‹እሺ ቸው.. እንዳትቀሪ››
‹‹እሺ በሉ ደህና ሁኑ፡፡›› ፊቷን አዙራ በተቃራኒው አቅጣጫ ነበር መጓዝ ጀመረች፡፡እንሱም ፊት ለፊታቸውን ይዘው ሶስት የሚሆኑ እርምጃዎች ከተራመዱ በኃላ ናኦል ድንገት ዞር አለና
‹‹እህቴ›› ሲል ተጣራ…ዞር አለች፡፡‹‹እ ምነው?››
‹‹ስምሽን እኮ አልነገርሽንም፡፡››
‹‹ምስራቅ እባላለሁ፡፡››ስሟ ከአንደበቷ ተስፈንጥሮ ሲወጣ ወዲያው ነበር ልቡ ላይ አርፎ ቅልጥልጥ በማለት ከመላ ሰውነቱ የተዋሀደው …..‹‹ምስራቅ…አንፀባራቂና በብርሀን የተሞላ ስም››ይላል ሁል ጊዜ፡፡ከዛ ‹‹የእኔ ደግሞ ናኦል ነው …የእህቴ ደግሞ ኑሀሚ፡፡››ብሎ ነበራት፡፡
‹‹እሺ ቸው ናኦል››ፊቷን አዞረችና እርምጃዋን ቀጠለች… ጎኑ ያለችው እህቱ በክርኗ ጎሰመችው
‹‹እንዴ ምን እየሆንሽ ነው…?ምን አደረኩ?››ግራ ተጋብቶ ጠየቃት፡፡
‹‹እህቴ አልካት እኮ፡፡››
‹‹እና ምን ችግር አለው?››
‹‹አንተ እኔን በምትጠራበት ስም ሌላ ትናንት ያወቅካትን ሴት ትጠራለህ…?ሆዳም ነገር ነህ፡፡ አሳንቡሳ ስለጋበዘችህ ነው አይደል?፡፡››የቅናት ወቀሳ ወቀሰችው፡፡
‹‹አይ አይደለም..ቆንጆ ስለሆነች ነው፡፡››አላት
‹‹ቆንጆ ብትሆንም እኮ ትልቅ ልጅ ነች… ሰላሳ አመት ይሆናታል፡፡››
‹‹አትዋሺ 25 ቢሆናት ነው፡፡››
‹‹ሀያ አምስት ቢሆናትም እኮ ትልቅ ነች ማለት ነው… አንተ እኮ ገና 11 አመትህ ነው…ታምራለች ትላለህ እንዴ?››አሾፈችበት፡፡
‹‹አሁን ስራ እስኪደርስ የት እንሂድ?››
በወቅቱ ሁለቱም በቀን ሰላሳ ብር የሚያስገኝላቸው ቋሚ ስራ ነበራቸው፡፡ስራው እዛው ሰፈር ካለ ጫት ቤት ጫትና መሰል ዕቃዎችን ደንበኛ ለሆኑ አምስት ሚሆኑ ሰዎች እንዳንዴም ቁጥራቸው እስከአስር ይሄዳል…ከ6-8 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በየቤታቸው ማድረስ ነበር፡፡ሁሉም ቤት የሚሄዱት አብረው ነው፡፡ከዛ የእለቱን ስራቸውን ሲያጠናቅቁ የጫት ቤቱ ልጅ 30 ብር ይሰጣቸዋል፡፡ታዲያ ብቸኛ ገቢያቸው ያ ብቻ አልነበረም..የሚወሰዱላቸውም ሰዎች አምስትም አስርም ብር ይሰጧቸው ስለነበር..በየቀኑ 50 ስልሳ ብር አካባቢ አንዳንዴም ከዛ በላይ ያገኛሉ፡፡
እዛ መስቀል አደባባይ በቀዘቀዘ ድንጋይ ላይ ተጎልቶ የሚያመነዥገውን ትዝታ ሳይጨርስ የስልኩ ጥሪ አባነነው፡፡የማያውቀው ስልክ ነው፡፡በዛ ውድቅት ለሊት ከሷ ውጭ ሌላ ሰው እንደማይሆን እርግጠኛ ነው ፡በፍጥነት አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ 22 ጎላጎል ህንፃ ፊት ለፊት ከ30 ደቂቃ በኃላ.. ትችላለህ?
‹‹አዎእችለለሁ፡› ስልኩተጠረቀመ፡
ድንግርግር አለው፡፡ናፍቀዋለች፡፡ብዙ የመግቢያ ሰላምታና የናፍቆት ንግግር ጠብቆ ነበር፡፡ምን አይነት ችግር አጋጥሞህ ነው? ብላ እንድትጠይቀውም ፈልጎ ነበር..ግን ከምኞቱ አንዱንም አላሞላችለትም፡፡‹‹ዋና መደወሏ ነው›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡እግሩን መንቀሳቀስ ግን በቀላሉ አልቻም፡፡ድንዝዝ ነበር ያለው..እንደምንም ለማፍታታትና ለመራመድ ከሁለት ደቂቃ በላይ አስፈልጎት ነበር፡፡መኪና ውስጥ ገባና ወደተባለው አቅጣጫ መንዳት ጀመረ፡፡በለሊት በአዲስአበባ ጎዳና መንዳት እንዴት ደስ ይላል?››ሲል አሰባ፡፡ከፊት የሚደነቀር መኪና የለ ፤በየደቂቃው ፍሬን እምቅ አድር መያዝ የለ፤ ከኃላ ሚያንባርቅ የመኪና ጥሩንባ የለ ››በማለት በነፃነት በመንዳቱ እተደነቀ የተባለበት ቦታ ከተባለበት ሰዓት ቀድሞ ደርሶ መኪናዋና ራቅ አድርጎ በማቆም ይጠብቅ ጀመር፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ አንድ ጥቁር መርቼዲስ ከወደ ቦሌ አቅጣጫ መጣችና አደባባዩን መዞር ጀመረች፡፡የመኪናውን የፊት መብራት ቦግ ብልጭ አድርጎ በማብራት ምልክት ሰጠ..እሷ ከሆነች ይገባታል፡፡ለረጅም ጊዜ አብረው የስለላ ስራ ይሰሩ በነበረበት ወቅት ከሚጠቀሙባቸው በርካታ የመግባቢያ ኮዶች መካከል አንዱን ነው የተጠቀመው፡፡መርቸዲሶ ቀጥታ ወደእሱ በመምጣት ዞራ ከእሱ ኃላ ቆመች፡፡ቀስ ብሎ ወረደና ወደ እሷ ሄደ፡፡ገቢናው ተከፈተለት፡፡ገባና ዘጋው፡፡ከቅድሙ የስልክ ልውውጥ በመነሳት ኮስተር ያለ ነገር ነበር የጠበቀው፡፡
በተቀመጠችበት ሆና ሁለት እጆቾን ዘረጋችና አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡ፊቱን አንገቷ ሰር ደፈቀው…ከገላዋ የሚወጣው ጠረን አፍንጫው ውስጥ ተመሰገ.. ወደውስጥ በጥልቀት ሳበው፡፡እየቃተተ በሚመስል የሰለለ ድምፅ‹‹በጣም ናፍቀሺኝ ነበር››አላት፡፡
ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ አይቶ እንደደነገጠባት የ12 ዓመት ልጅ አይደለም አሁን ጉርምስናውና በማጠናቀቅ ላይ ያለ የ27 አመት ሙሉ ወጣት ነው፤እሷ ደግሞ የ43 ዓመት ጎልማሳ፡፡አሁን ስለእሷ የሚሰማው የፍቅር ስቃይ አካላዊም ስነልቦናዊም ጭምር ነው፡፡ልቡም ነፍሱ ናቸው በእኩል የሚንሰፈሰፉላት፡፡ከእቅፎ አወጣችውና ጉንጩን ሳመችው፡፡እሱም በተመሳሳይ ሳማት፡፡
‹‹አርጅተሀል እኮ…ምነው አገባህ እንዴ?››
‹‹እንዴት ላገባ ችላለሁ?››አላት፡፡
‹‹እኔ እንጃ ጅርግፍግፍ ስትል ምን አልባት ሰርግ ሳትጠራኝ አግብተህ እንደሆነ ብዬ ነዋ፡፡ ››
‹‹እህቴ እንደዛ አይደለም ባክሽ …ችግር ላይ ነች፡፡››
‹‹እሱንማ መልዕክት ስትልክልኝ ነው ችግር ላይ መሆንህን ያወቅኩት ….ለመሆኑ ምን አይነት ወንጀል ውስጥ ገብተህ ነው?››የጠረጠረችውን ጠየቀችው፡፡በእሷ ሀሳብ ያው እንደልማዱ ከሆኑ ወንጀለኛ ብድኖች ጋር ተቀላቅሎ የሆነ ስራ ውስጥ በመግባት አሁን መውጫ መንገድ አጥቶ ወይ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ እሷ ከማጥ እንድታወጣው ፈልጎ እንደሆነ እርግጠኛ ሆና ነው ልትረዳወው የመጣችው፡፡ከዚህ በፊትም ከተመሳሳይ ማጥ ሶስት አራት ጊዜ አድነዋለች..አሁንም ከእሷ አቅም በላይ አይሁን እንጂ ታደርገዋለች፡፡ለእሷ እሱን መርዳትና ማገዝ እንደምርጫ ሳይሆን እንደግዴታ ነው፡፡
‹‹እህቴ በለፈው እኮ ቃል ገብቼልሻለሁ…አንቺን ችግር ውስጥ የሚያስገባ ምን አይነት መጥፎ ነገረ እንዳማልሰራ ነግሬሽ ነበር… ያንንም እስከቻልኩት ድረስ ቃሌን ጠብቄ መቀጠል ነው የምፈልገው፡፡››
እና ታዲያ በዚህ ውድቅት ለሊት መልዕክት የላክልኝ እንዳቅፍህና ጉንጮችህን እያገላበጥኩ እንድስምህ ነው እንዴ…?.እንደዛ ከሆነ ችግር ውስጥ ነህ፡፡››ብስጩዋ ሴት ከውስጦ ብቅ አለች፡፡
‹‹አረ አይደለም ..እህቴ ..ኑሀሚ ችግር ላይ ነች፡፡››
‹‹ምን ….ከሀገር ውጭ ያለች መስሎኝ ፣መቼ መጥታ መቼ ችግር ውስጥ ገባች?››
‹‹አይ እዛው ነች…››ብሎ የሆነውን ሁሉ በርዝር ነገራት፡፡ከእሱ ባልተናነሰ ሁኔታ አዘነች፡፡ሲነጋ ከብራዚል አምባሳደር ሆነ ከሌሎች የውጭ ጉዳይ ሰዎች ጋር በመነጋገር የሆነ ነገር እንደምታደርግ ቃል ገብታለት…የኑሀሚ ጉዳይ እልባት እስኪያገኝ ቀጥታ የሚደውልላትን ቁጥር ሰጥታው ከአንድ ሰዓት የአብሮንት ቆይታ በኃላ ተለየችውና እንደአመጣጧ ተመልሳ ሄደች ፡፡እሱም ሌላ ወዴት እንደሚሄድ ግራ ስለገባው ወደቤቱ ነዳው፡፡
✨ይቀጥላል✨
👍93❤8😁1
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍9
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
አማዞን ደን ኮሎንቢያ ግዛት
ጫካውን እየሰነጠቁ ከአውሬውና ከነፋሳት ጋር እየተጋፉ መጓዝ በጀመሩ አራት ቀን ሆኗቸዋል፡
በጉዞቸው ከዛፍ ዛፍ ሲንጠለጠል አንድ ገራሚ እንስሳ አየች፡፡ትንሽ ነው፡፡ ድመት ነው የሚመስለው፡፡ ግን ጸጉር የለበሰ በመሆኑ ከመጠኑ ገዝፎ እንዲታይ እረድቶታል፡፡ ዝንጀሮም አንበሳም ይመስላል፡፡ከዚህ በፊት በምስል ላይ ፎቶውን እንኳን አይታ አታውቅም፡፡
‹‹ምንድነው ይሄ እንስሳት?››ቁራኛዋን ካርሎስን ጠየቀችው፡፡
‹‹እ ታማሪን ወይም ሮሳሊያ ይባላል፡፡ወይም በቀላሉ ወርቃማው አንበሳ ይሉታል፡፡››
‹‹አዎ እውነትም ወርቃማው አንበሳ፡፡ፀጉሩ እኮ ወርቅ መሳይና አብረቅራቂ ነው…ትክክለኛ ስሙ ይሄኛው ነው፡፡››
‹‹አዎ ዝርያው የዝንጀሮ ቢሆንም እንደምታይው ግን አንበሳ ነው የሚመስለው፡፡የዚህ ፕሪሜት ልዩ ቀለም ምናልባትም በጠንካራ የፀሐይ ብርሃን ጥምረት እና በአመጋገቡ ውስጥ በሚገኙ የካሮቲኖይዶች ብዛት ላይ የተመሠረተ ነው የሚል መላምት አለ።እንደምታይው አስደናቂ ገጽታ አለው: ወፍራም፤ ለስላሳ፤ ደማቅ ቀይ ፀጉር፤እንዲሁም ጥቁር ፊት እና ትልቅ ቡናማ አይኖች ያሉት አስደማሚ ፍጡር ነው››
‹‹ስላየሁት ደስ ብሎኛል፡፡የማልሞት ቢሆን ኖሮ እዚህ መጥቼ ስላየሁት እያንዳንዳንዱ ድንቅ እና አስደሳች ነገር… ስለእንስሳቱና ስለጥቅጥቁ ዳን… ስለሚንዠቀዠቀው የአማዞን ወንዝ ለወንድሜም ለጓደኞቼም በደስታ እንግራቸው ነበር..ግን ምን ዋጋ አለው….››ከገባችበት ጊዜያዊ የደስታ ስሜት ወጣችና ሀዘን ውስጥ ገባች፡፡
‹‹አይዞሽ …እሰክአሁን በህይወት አለሽ ..ለጊዜው ያ በቂ ነው፡፡››አላት፡፡
‹‹እንዳልክ ይሁንልህ››አለችውና ዝምታ ውስጥ ገባች፡፡
እኩለ ቀን ላይ ኣማዞን ወንዝን ታካ የተመሰረተች የደቡብ ኮለምቢያ የጠረፍ ከተማ ከሆነችውና 35 ሺ ኑዋሪዎች ከሚኖሩባት ላቲሲያ ከተማ ደረሱ፡፡ይህቺ ከታማ ሶስት ሀገሮች ማለት ፔሩ ኮሎቢያን ብራዚል የሚገናኙባት ነጥብ ከሆነችው ትሬስ ፎረንቴራስ ትንሽ ወደላይ ፈቅ ብላ ምትገኝ በዓሳ ምርቷ የታወቀች እጥር ምጥን ያለች ከተማ ነች፡፡የኮሎምቢያ መንግስት ግዙፍ የሆነ የዓሳ ምርቱን ከአካባቢው እየሰበሰበ በጀልባ በመጫን ወደ ማአከላዊ የሀገሪቱ ስፋራዎች የሚጫንባት ወሳኝ ከተማ ነች፡፡ከታማዋን በሩቅ ሲያዮት እና ጉዞቸውንም በዛ አቅጣጫ ሲያቀና ቀጥታ ወደከታማው ዘልቀው ሚገቡ መስሏት ተደስታ ነበር፡፡የዛም ምክንያቱ ህዝብ ያለበትና የመንግስት ተቋማት ሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ላይ ከደረሰች በተቻላት መጠን ለማምለጠ ትሞክራለች፤ያ ከሆነ ደግሞ ጥረቷ የመሳካት እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ ስሌቱን ስለሰራች ነው፡፡ይሁን እንጂ አጋቾቻ
የገመተቻቸውን ያህል ጥንቃቄ አልባ አልነበሩም፤በዛም ምክንያት ወደከታማዋ አልገቡም፡፡ይልቅስ ከተማዋን በቅርብ ርቀት ታካ አማዞን ጉያ ውስጥ ተወሽቃ ከምትገኝ ነባር ጎሳዎች ወደሚኖሩባት ወደአንድ መንደር ነው ጎራ ያሉት፡፡
‹‹እርግጠኛ ነኝ ይሄ የመጨረሻ የጉዞ መዳረሻችን ነው፡፡››ካርሎስን ነው የምትጠይቀው፡፡
‹‹አይመስለኝም..ግን የተወሰኑ ቀናትን እዚህ የምናርፍ ይመስለኛል››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹በሩቅ ወደምትታየው ከተማ ምንገባ መስሎኝ ነበር››
‹‹እ..ወደ ላቲሲያ ማለትሽ ነው..ወደእዛ አለመግባታችን ጥሩ ነው…ለአንቺ ምንም ሚጠቅም ነገር አይገኝበትም…ከኑዋሪዎቹ ከግማሽ በላይ የእኛ ሰውዬ ሰዎች ናቸው››
ተስፋ ቆረጠችና… ዝም አለች፡፡..የቡድኑ ሰዎችን ለመቀበል ሶስት የሆኑ የመንደሩ ሰዎች መጡና አወሯቸው፡፡ ከተወሰኑት ጋር የሞቀ ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ አንድ ወለሉ በአየር ላይ የተንጠለለ በስሩ ውሀ የሞላበት በጣውላ እርብራብ የተሰራ የሳር ክዳን ቤት ከፊት ለፊታቸው ይታያል፡፡ወደዛው መጓዝ ጀመሩ፡፡ቤቱ ሰፋ ያለ ግን ደግሞ እቃ አልባ ነበር፡፡ቁራኛዋ ሰንሰለቱን ከላዩ ላይ አላቀቀና ለብቻዋ ተወላት፡፡ሁሉም በተርታ መቀመጫ ይዘው ተቀመጡ…ምግብ ቀረበላቸው፡፡ ሁሉም ተርበው ስለነበር የምግብ አይነቱ ሳያስጨንቃቸው በፍቅር በሉ ፡፡የሚጠጣ ነገር ቀረበላቸው…ጠንከር ያለ የአልኮል መጠጥ ነው፡፡እሷ መጠጣት አልፈቀደችም፡፡፡ውሀ ቀረበላት፤እሱን ጠጣች፡፡የምግብ ስርአቱ ካለቀ በኃላ እሷን እዛው ቤት ውስጥ ተዋትና ከውጭ ቆልፈውባት ወጥተው ሄዱ፡፡
ቤቱን ክፍት ትተውት ቢሄዱም ወደምትሄድበት ቦታ የላትም፡፡መቼስ በቃ ተመልሰሽ ሂጂ ቢሏት እንኳን የአራት ቀን መንገድ በእንደዛ አይነት ጥቅጥቅ የአማዞን ደን ከጇጓርና ከአናኮንዳ ጋር እየታገለች…አረንጎዴ መርዛማ እንቁራሪቶችና ሰውነት ላይ ከተጣበቁ ማይላቀቁ ጉንዳኖችን ተቋቁማ ወደኃላ ተመልሳ ፔሩ ገባለው የሚል ግምት የላትም፡፡እርግጥ ወደፊት ቀጥላ በአምስት ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ ከምትታየው ላቲሲያ ከተማ ልትሄድ ትችላለች፡፡ግን ሙሉ ከተማው የራሳቸው የጋንግስተሮቹ ግዛት እንደሆነ ካርሎስ በግልፅ ነግሯታል...ምክሩን ችላ ብላ ብትሄድና ምንም አይነት የመንግስት ተቋም ሆነ የሚታደጋት ተቋም በቦታው ባይኖርስ…?፡፡ጠቅለል አድርጋ ስታስበው ከዚህ አሁን ካለችበት ስፍራ አምልጦ ነፃ መውጣት የማይተገበር ምኞት ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡
ደክሞት ስለነበረ እቤቱ ውስጥ ያለች አንድ መተኛ ፍራሽ ነገር ላይ ሄዳ ጋደም አለች፡፡፡ሰውነቷን በቀላሉ እንዳሳረፈችው አእምሮዋን ልታሳርፍ አልቻለችም፡፡ በእነዚህ ሰዎች እጅ ከገባች ቀን ጀምሮ እንዲህ ለብቻዋ በመሆን ጥቂት ሳዕታትን ባገኘች ቁጥር ወዲያውኑ ሀሳቧ በሮ ወንድሟ ጋ ነው የሚሄደው፡፡የትናንት ትዝታዋ ጋር ነው የሚለጠፈው፡፡ናኦል ይሄኔ ለአራት ቀን ድምፆ ሲጠፈበት እና ስልኳም አልሰራ ሲለው የሚያደርገው ጠፍቶት መስሪያ ቤቷ ሄዶ እህቴን ውለዱ እያለ እያስጨነቃቸው አንደሚሆን ገመተች..ብቻ በዛ ችኩል ባህሪው የሆነ ሰውን ውለዷት ብሎ አፍንጫ እንዳይሰብር ነው የሰጋችው፡፡ምን አልባትም ምስራቅ ጋር ሊሄድ እንደሚችል ገመተች፡፡እንዲህ አይነት ጭንቅ ውስጥ ሲገባ ከምስራቅ ቀድሞ ወደአእምሮ የሚመጣ ሌላ የተሻለ የሚቀርባቸውና የሚረዳቸው ሰው እንደሌለ ታውቃለች፡፡እሷም በእሱ ቦታ ብትሆን እንደዛ ነው የምታደርገው፡፡
ከምስራቅ ጋር በወዳጅነት መቀራረብ ብቻ ሳይሆን የስራ ባለደረባም ሆነው እንደሀለቃና ምንዝር ለረጅም አመት ሰርተዋል፡፡ለዛውም በሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት፡፡እርግጥ እሷም ሆነች ወንድሟ ቀጥታ የደህንነት መስሪያ ቤቱ ተወዳድረው አይደለም የተቀጠሩት፡፡በወቅቱ ለእዛ የሚያበቃ እድሜ ላይም ሆነ ሁኔታ ላይ አልነበሩም፡፡ ..የእዛ መስሪያ ቤት አባል የሆኑት በእሷ በኩል ተመልምለው ..በእሷ ጥረት ወደስልጠና እንዲገቡ ተደርገው…በእሷ በኩል ተልዕኮ እየተሰጣቸው ነው፡፡ከዛ ብዙ ብዙ የሚባል ተልዕኮዎችን ተወጥተዋል…ለሀገር የሚጠቅሙ አንዳንዴም የተሳሳቱ ሰራዎችን ሰርተዋል፡፡ ያኔ እዛ በረንዳ ላይ ረዳት አልባ በነበሩበት ጊዜ ካገኘቻቸው በኋላ እንዴት እንደመለመለቻቸው ትዝ አላት፡፡
ኢትዬጵያ/አዲስ አበባ
አንድ ቀን አስራሁለተኛ አመታቸው ላይ ከምስራቅ ጋር በተዋወቁ በሁለተኛው ቀን በየእለቱ ለደምበኞች ጫት የማመላለስ ስራ ሰርተው ከጨረሱ በኃላ ምስራቅ እመጣለሁ ብላቸው ስለነበረች ቦታቸው ላይ ቁጭ ብለው እየጠበቋት ነበር፡፡ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ላይ ምስራቅ እንዳለችው መጣች፡፡ ከመቀመጫቸው ተነስተው በፈገግታ ተቀበሏት፡፡ይዛ የሄደችው አንድ ፔስታል ቢሆንም አሁን ግን ሌላ አንድ ጥብሰቅ ያለ እቃ የታጨቀበት ፔስታል ይዛ መጥታለች፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
አማዞን ደን ኮሎንቢያ ግዛት
ጫካውን እየሰነጠቁ ከአውሬውና ከነፋሳት ጋር እየተጋፉ መጓዝ በጀመሩ አራት ቀን ሆኗቸዋል፡
በጉዞቸው ከዛፍ ዛፍ ሲንጠለጠል አንድ ገራሚ እንስሳ አየች፡፡ትንሽ ነው፡፡ ድመት ነው የሚመስለው፡፡ ግን ጸጉር የለበሰ በመሆኑ ከመጠኑ ገዝፎ እንዲታይ እረድቶታል፡፡ ዝንጀሮም አንበሳም ይመስላል፡፡ከዚህ በፊት በምስል ላይ ፎቶውን እንኳን አይታ አታውቅም፡፡
‹‹ምንድነው ይሄ እንስሳት?››ቁራኛዋን ካርሎስን ጠየቀችው፡፡
‹‹እ ታማሪን ወይም ሮሳሊያ ይባላል፡፡ወይም በቀላሉ ወርቃማው አንበሳ ይሉታል፡፡››
‹‹አዎ እውነትም ወርቃማው አንበሳ፡፡ፀጉሩ እኮ ወርቅ መሳይና አብረቅራቂ ነው…ትክክለኛ ስሙ ይሄኛው ነው፡፡››
‹‹አዎ ዝርያው የዝንጀሮ ቢሆንም እንደምታይው ግን አንበሳ ነው የሚመስለው፡፡የዚህ ፕሪሜት ልዩ ቀለም ምናልባትም በጠንካራ የፀሐይ ብርሃን ጥምረት እና በአመጋገቡ ውስጥ በሚገኙ የካሮቲኖይዶች ብዛት ላይ የተመሠረተ ነው የሚል መላምት አለ።እንደምታይው አስደናቂ ገጽታ አለው: ወፍራም፤ ለስላሳ፤ ደማቅ ቀይ ፀጉር፤እንዲሁም ጥቁር ፊት እና ትልቅ ቡናማ አይኖች ያሉት አስደማሚ ፍጡር ነው››
‹‹ስላየሁት ደስ ብሎኛል፡፡የማልሞት ቢሆን ኖሮ እዚህ መጥቼ ስላየሁት እያንዳንዳንዱ ድንቅ እና አስደሳች ነገር… ስለእንስሳቱና ስለጥቅጥቁ ዳን… ስለሚንዠቀዠቀው የአማዞን ወንዝ ለወንድሜም ለጓደኞቼም በደስታ እንግራቸው ነበር..ግን ምን ዋጋ አለው….››ከገባችበት ጊዜያዊ የደስታ ስሜት ወጣችና ሀዘን ውስጥ ገባች፡፡
‹‹አይዞሽ …እሰክአሁን በህይወት አለሽ ..ለጊዜው ያ በቂ ነው፡፡››አላት፡፡
‹‹እንዳልክ ይሁንልህ››አለችውና ዝምታ ውስጥ ገባች፡፡
እኩለ ቀን ላይ ኣማዞን ወንዝን ታካ የተመሰረተች የደቡብ ኮለምቢያ የጠረፍ ከተማ ከሆነችውና 35 ሺ ኑዋሪዎች ከሚኖሩባት ላቲሲያ ከተማ ደረሱ፡፡ይህቺ ከታማ ሶስት ሀገሮች ማለት ፔሩ ኮሎቢያን ብራዚል የሚገናኙባት ነጥብ ከሆነችው ትሬስ ፎረንቴራስ ትንሽ ወደላይ ፈቅ ብላ ምትገኝ በዓሳ ምርቷ የታወቀች እጥር ምጥን ያለች ከተማ ነች፡፡የኮሎምቢያ መንግስት ግዙፍ የሆነ የዓሳ ምርቱን ከአካባቢው እየሰበሰበ በጀልባ በመጫን ወደ ማአከላዊ የሀገሪቱ ስፋራዎች የሚጫንባት ወሳኝ ከተማ ነች፡፡ከታማዋን በሩቅ ሲያዮት እና ጉዞቸውንም በዛ አቅጣጫ ሲያቀና ቀጥታ ወደከታማው ዘልቀው ሚገቡ መስሏት ተደስታ ነበር፡፡የዛም ምክንያቱ ህዝብ ያለበትና የመንግስት ተቋማት ሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ላይ ከደረሰች በተቻላት መጠን ለማምለጠ ትሞክራለች፤ያ ከሆነ ደግሞ ጥረቷ የመሳካት እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ ስሌቱን ስለሰራች ነው፡፡ይሁን እንጂ አጋቾቻ
የገመተቻቸውን ያህል ጥንቃቄ አልባ አልነበሩም፤በዛም ምክንያት ወደከታማዋ አልገቡም፡፡ይልቅስ ከተማዋን በቅርብ ርቀት ታካ አማዞን ጉያ ውስጥ ተወሽቃ ከምትገኝ ነባር ጎሳዎች ወደሚኖሩባት ወደአንድ መንደር ነው ጎራ ያሉት፡፡
‹‹እርግጠኛ ነኝ ይሄ የመጨረሻ የጉዞ መዳረሻችን ነው፡፡››ካርሎስን ነው የምትጠይቀው፡፡
‹‹አይመስለኝም..ግን የተወሰኑ ቀናትን እዚህ የምናርፍ ይመስለኛል››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹በሩቅ ወደምትታየው ከተማ ምንገባ መስሎኝ ነበር››
‹‹እ..ወደ ላቲሲያ ማለትሽ ነው..ወደእዛ አለመግባታችን ጥሩ ነው…ለአንቺ ምንም ሚጠቅም ነገር አይገኝበትም…ከኑዋሪዎቹ ከግማሽ በላይ የእኛ ሰውዬ ሰዎች ናቸው››
ተስፋ ቆረጠችና… ዝም አለች፡፡..የቡድኑ ሰዎችን ለመቀበል ሶስት የሆኑ የመንደሩ ሰዎች መጡና አወሯቸው፡፡ ከተወሰኑት ጋር የሞቀ ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ አንድ ወለሉ በአየር ላይ የተንጠለለ በስሩ ውሀ የሞላበት በጣውላ እርብራብ የተሰራ የሳር ክዳን ቤት ከፊት ለፊታቸው ይታያል፡፡ወደዛው መጓዝ ጀመሩ፡፡ቤቱ ሰፋ ያለ ግን ደግሞ እቃ አልባ ነበር፡፡ቁራኛዋ ሰንሰለቱን ከላዩ ላይ አላቀቀና ለብቻዋ ተወላት፡፡ሁሉም በተርታ መቀመጫ ይዘው ተቀመጡ…ምግብ ቀረበላቸው፡፡ ሁሉም ተርበው ስለነበር የምግብ አይነቱ ሳያስጨንቃቸው በፍቅር በሉ ፡፡የሚጠጣ ነገር ቀረበላቸው…ጠንከር ያለ የአልኮል መጠጥ ነው፡፡እሷ መጠጣት አልፈቀደችም፡፡፡ውሀ ቀረበላት፤እሱን ጠጣች፡፡የምግብ ስርአቱ ካለቀ በኃላ እሷን እዛው ቤት ውስጥ ተዋትና ከውጭ ቆልፈውባት ወጥተው ሄዱ፡፡
ቤቱን ክፍት ትተውት ቢሄዱም ወደምትሄድበት ቦታ የላትም፡፡መቼስ በቃ ተመልሰሽ ሂጂ ቢሏት እንኳን የአራት ቀን መንገድ በእንደዛ አይነት ጥቅጥቅ የአማዞን ደን ከጇጓርና ከአናኮንዳ ጋር እየታገለች…አረንጎዴ መርዛማ እንቁራሪቶችና ሰውነት ላይ ከተጣበቁ ማይላቀቁ ጉንዳኖችን ተቋቁማ ወደኃላ ተመልሳ ፔሩ ገባለው የሚል ግምት የላትም፡፡እርግጥ ወደፊት ቀጥላ በአምስት ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ ከምትታየው ላቲሲያ ከተማ ልትሄድ ትችላለች፡፡ግን ሙሉ ከተማው የራሳቸው የጋንግስተሮቹ ግዛት እንደሆነ ካርሎስ በግልፅ ነግሯታል...ምክሩን ችላ ብላ ብትሄድና ምንም አይነት የመንግስት ተቋም ሆነ የሚታደጋት ተቋም በቦታው ባይኖርስ…?፡፡ጠቅለል አድርጋ ስታስበው ከዚህ አሁን ካለችበት ስፍራ አምልጦ ነፃ መውጣት የማይተገበር ምኞት ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡
ደክሞት ስለነበረ እቤቱ ውስጥ ያለች አንድ መተኛ ፍራሽ ነገር ላይ ሄዳ ጋደም አለች፡፡፡ሰውነቷን በቀላሉ እንዳሳረፈችው አእምሮዋን ልታሳርፍ አልቻለችም፡፡ በእነዚህ ሰዎች እጅ ከገባች ቀን ጀምሮ እንዲህ ለብቻዋ በመሆን ጥቂት ሳዕታትን ባገኘች ቁጥር ወዲያውኑ ሀሳቧ በሮ ወንድሟ ጋ ነው የሚሄደው፡፡የትናንት ትዝታዋ ጋር ነው የሚለጠፈው፡፡ናኦል ይሄኔ ለአራት ቀን ድምፆ ሲጠፈበት እና ስልኳም አልሰራ ሲለው የሚያደርገው ጠፍቶት መስሪያ ቤቷ ሄዶ እህቴን ውለዱ እያለ እያስጨነቃቸው አንደሚሆን ገመተች..ብቻ በዛ ችኩል ባህሪው የሆነ ሰውን ውለዷት ብሎ አፍንጫ እንዳይሰብር ነው የሰጋችው፡፡ምን አልባትም ምስራቅ ጋር ሊሄድ እንደሚችል ገመተች፡፡እንዲህ አይነት ጭንቅ ውስጥ ሲገባ ከምስራቅ ቀድሞ ወደአእምሮ የሚመጣ ሌላ የተሻለ የሚቀርባቸውና የሚረዳቸው ሰው እንደሌለ ታውቃለች፡፡እሷም በእሱ ቦታ ብትሆን እንደዛ ነው የምታደርገው፡፡
ከምስራቅ ጋር በወዳጅነት መቀራረብ ብቻ ሳይሆን የስራ ባለደረባም ሆነው እንደሀለቃና ምንዝር ለረጅም አመት ሰርተዋል፡፡ለዛውም በሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት፡፡እርግጥ እሷም ሆነች ወንድሟ ቀጥታ የደህንነት መስሪያ ቤቱ ተወዳድረው አይደለም የተቀጠሩት፡፡በወቅቱ ለእዛ የሚያበቃ እድሜ ላይም ሆነ ሁኔታ ላይ አልነበሩም፡፡ ..የእዛ መስሪያ ቤት አባል የሆኑት በእሷ በኩል ተመልምለው ..በእሷ ጥረት ወደስልጠና እንዲገቡ ተደርገው…በእሷ በኩል ተልዕኮ እየተሰጣቸው ነው፡፡ከዛ ብዙ ብዙ የሚባል ተልዕኮዎችን ተወጥተዋል…ለሀገር የሚጠቅሙ አንዳንዴም የተሳሳቱ ሰራዎችን ሰርተዋል፡፡ ያኔ እዛ በረንዳ ላይ ረዳት አልባ በነበሩበት ጊዜ ካገኘቻቸው በኋላ እንዴት እንደመለመለቻቸው ትዝ አላት፡፡
ኢትዬጵያ/አዲስ አበባ
አንድ ቀን አስራሁለተኛ አመታቸው ላይ ከምስራቅ ጋር በተዋወቁ በሁለተኛው ቀን በየእለቱ ለደምበኞች ጫት የማመላለስ ስራ ሰርተው ከጨረሱ በኃላ ምስራቅ እመጣለሁ ብላቸው ስለነበረች ቦታቸው ላይ ቁጭ ብለው እየጠበቋት ነበር፡፡ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ላይ ምስራቅ እንዳለችው መጣች፡፡ ከመቀመጫቸው ተነስተው በፈገግታ ተቀበሏት፡፡ይዛ የሄደችው አንድ ፔስታል ቢሆንም አሁን ግን ሌላ አንድ ጥብሰቅ ያለ እቃ የታጨቀበት ፔስታል ይዛ መጥታለች፡፡
👍61❤13
‹‹ጩጬዎቹ አላቹሁ?›› አለችና ግንቡን ተጠግቶ ያለ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ቁጭ አለች፡፡ እነሱም ሌላ ድንጋይ በግራና በቀኝ አስጠጉና መሀከል አድርገዋት ተቀመጡ ፡፡
‹‹ከሁለታችሁ ማነው ታላቅ?››ያልጠበቁትን ጥያቄ ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹እኔ ነኝ…10 ደቂቃ ቀድማታለው››አለ ናኦል፡፡
‹‹እንዴ መንታ ናችሁ እንዴ…?ለነገሩ ጠርጥሬ ነበር…እኩል እድሜ ላይ እንደምትገኙ እንዲሁ በእይታ ታስታውቃላችሁ፡፡››
‹‹አዎ መንትዬዎች ነን፡፡››አረጋገጡላት፡፡ፔስታሉን ከፈተችና እጇን ወደውስጥ ላከች፡፡ ሰማያዊ ሮዝ ቀለም ያለው ሁለት ሙሉ ቢጃማ ከነአላባሹ አወጣችና‹‹ በስምምነት አንድአንድ ተካፈሉ፡፡›› አለቻቸው፡፡
ሁለቱም ፈዘው ይመለከቷት ጀመር፡፡እሷ እራሷ የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደና መቀየር የሚገባው ነው…ታዲያ ለምን ለእነሱ?››በወቅቱ ግልፅ አልሆነላቸውም ነበር፡፡
‹‹ምነው? ያልኩት አልገባችሁም እንዴ?እነዚህን ቢጃማዎችን የገዛሁት ለእናንተ ነው፡፡እ… ጎረምሳው የትኛው ይሁንልህ?››
‹‹እህቴ ሮዝ ቀለም ትወዳለች..ሮዙ ለእሷ ይሁን፡፡››
‹‹አንተስ ሰማያዊው ይመችሀል?››
‹‹የእኔ ችግር የለውም..እህቴ ደስ ካላት ደስ ይለኛል፡፡ግን ለምን ለራስሽ ሳትገዢ ለእኛ ገዛሽ??››
‹‹ገዝታ አይመስለኝም…ፖሽራ ነው››ኑሀሚ ግምቷን ተናገረች፡፡
‹‹ተይ እህቴ.. ለምን እንደዛ ትያለሽ….?ብትፖሽረውም እኮ ደግነቷን ነው የሚያሳየው፡፡ለእኛ ከመስጠት ሁለቱን ሸጣ አንድ ለእሷ ሚሆን ልብስ ልትገዛበት ትችል ነበር፡፡››
‹‹ እኔም ያልገባኝ እኮ በደንብ ሳታውቀን ለምን ብዬ ነው…?ምን አስባ ነው?››
በወቅቱ የጎዳና ህይወት ልምዳቸው በጣም ተጠራጣሪ አድርጓቸው ነበር፡፡በዛ ምክንያት ነበር እሷን ዘንግተው እርስ በርሳቸው ክርክር ውስጥ የገቡት፡፡
‹‹ኸረ እህቴ አመሰግናለሁ ነው የሚባለው፡፡››
‹‹ናኦሌ ደግሞ… እዚህ ጓደና ላይ ስንት የማጭበርበር ታሪክ እደሚሰራ አታውቂምናነው.?ለሆነ ነገር እያመቻችንስ ቢሆን…?እኔ ይሄንን ልብስ አልፈልግም፡፡አንተም እንድትቀበላት አልፈቅድልህም…፡፡››
ምስራቅ እጇን ወደ ፔስታሉ ሰዳ ሌላ ነገር አወጣች፡፡በስስ ፔስታል የተጠቀለለ ምግብ ነው፡፡ፊት ለፊቷ መሬት አስቀመጠችና ፈታችው፡፡የሚያስጎመዣ አጥንት ያለው የቅቅል ፍትፍት ነው፡፡እጇን ሰደደችና አንዴ ጠቅለል አደረገችና ጎረሰች፡፡ከፔስታሉ ውስጥ የቀረውን ሁለት ሊትር ውሀ አወጣችና ምግቡ ጎን አስቀምጣ…‹‹አንቺ ነብር የሆንሽ ልጅ…ምግቡ ላይም መርዝ አድርገሽበታል እንዳትይ ነው የቀመስኩልሽ፡፡››በማለት ከተቀመጠችበት ተነሳችና ትናንትም ይዛት የነበረውን ፔስታል አንጠልጥላ በመጣችበት መንገድ ተመልሳ መጓዝ ጀመረች፡፡
‹‹ምስራቅ ወዴት ነው…?እህቴ እኮ ሁሉን ነገር የምትጠራጠረው ለእኔ ስለምትጨነቅ ነው፡፡››
‹‹ችግር የለውም..የምሄድበት ቦታ ስላለ ነው፡፡››
‹‹እና ተመልሰሽ ትመጪያለሽ?››
‹‹ይመስለኛል፡፡››ብላ ሄደች፡፡
መንትዬቹ ተፋጠው ተያዩ‹‹እህቴ ለምን አስቀየምሻት?››
‹‹አላስቀየምኳትም…ስለማናውቃት ተጠራጥሬያት ነው፡፡››
‹‹እሺ በቃ …እስኪ ለኪው፡፡›› ብሎ ሮዝ ቀለም ያለውን ቢጃማ አቀበላት፡፡፡ተቀበለችውና ያደረገችውን ነጠላ ጫማ አውልቃ ሱሪውን በቀሚሷን ከፍ አድርጋ አጠለቀችው
‹‹ከስር ካኔቴራ አድርገሽ የለ ቀሚሱን አውልቂው፡፡››
አወለቀችውና ጀኬቱን ከላይ ለበሰችበት..ወደእሷ ተጠጋና ዚፑን ዘጋላት፡፡እና ከእሷ ራቅ ብሎ አያት፡፡
‹‹ውይ አህቴ ..በጣም ነው ፏ-ፈሽ ያልሽው፡፡አቤት ፀጉርሽ ባይንጨፈረር…፡፡››
‹‹እስቲ የራስህን ልበሰውና እንየው››
‹‹አይ የእኔ ይደርሳል…መጀመሪያ ቡሌውን እንጥለፍ፡፡ሽታው ሆዴን አገለባበጠው፡፡››
‹‹እሺ እንብላ›› አለችና ምግብን አመቻችተው ተቀመጡ፡፡በጣም ጣፋጭ ምግብ ነበር፡፡ሆዳቸው እስኪወጠር ድረስ ነበር የበሉት፡፡እንደጨረሱ ናኦልም ለእሱ የመጣለትን ቢጃማ ለበሰ…..
እንደአማረበት ‹‹የእኔን ትላለህ እንጂ አንተም በጣም አምሮብሀል፡፡››ስትል ነበር ያረጋገጠችለት፡፡
‹‹አይደል…?አሁን የት አግኝተን እናመስግናት?››
‹‹እመጣለሁ ብላለች እኮ !ታገስ፡፡››
‹‹እህቴ ስትመጣ ግን እንደቅድሙ ያልሆኑ ያልሆኑ ነገሮች እንዳትናገሪያት፡፡››
‹‹እሞክራለሁ..፡፡ግን ይህቺ ሴት ምኗም አልጣመኝም፡፡ምን ነካህ ወንድሜ ስለእሷ ምንም አናውቅም አኮ!››
‹‹እኮ እንጠይቃታለና….ስንግባባ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን፡፡››
በዛን ቀን እስከ እኩለ ለሊት ቢጠብቋትም ምስራቅ ተመልሳ አልመጣችም ነበር፡፡ናኦል በጣም ቅር ቢለውም ኑሀሚ ግን ብዙም አልከፋትም፡፡እንደውም የወንድሟን ትኩረት ስለተሻማቻት እያበሳጨቻት ነበር፡፡በማግስቱ ጥዋት አንድ ሰዓት ከመሆኑ በፊት ግን ከእንቅልፋቸው ወዝውዛ የቀሰቀሰቻቸው እሷ ነበረች፡፡ናኦል አይኑን ገልጦ እሷ መሆኗን ሲያውቅ በደስታ ዘሎ ተጠመጠመባትና ጉንጫን ሳማት‹‹ማትመለሺ መስሎኝ ደንግጬ ነበር፡፡››
‹‹ምን ያስደነግጥሀል..?እስከዛሬ ከእሷ ጋር የኖርክ አስመሰልከው፡፡››ኑሀሚ በብስጭት መለሰችለት፡፡
‹‹እህቴ ቃል ገብተሸልኝ ነበር አይደል?››
‹‹እሺ..እንዳልክ፡፡››
‹‹እሺ በእኔ መጨቃጨቁን አቁሙና ተነሱ…ጥሩ ጨላ የሚያስገኝ ስራ ትሰራላችሁ፡፡››
‹‹ምንድነው ?ወንጀል እንዳይሆን?››
‹‹ጎዳና እየኖራችሁ ወንጀል ምናምን ትላላችሁ እንዴ…?ወንጀለኛ እናንተ ሳትሆኑ እናንተን እዚህ ጓዳና ላይ የጣላችሁ ስርአት ነው፡፡ ወንጀለኛ እናንተን ትራፊ እየለቃቀማችሁ እንድትኖሩ አይቶ እንዳላ የሚያልፋችሁ ማህበረሰቡ ነው፤እንጂ እናንተ ለመኖርና ህይወታችሁን ለማቆየት ስትሉ የምትሰሩት ነገር በምንም አይንት ወንጀል ሊባል አይችልም፡፡››
‹‹ትክክል ልትሆኚ ትችያለሽ፡፡ግን ዛፓዎች እጅ ከፍንጅ ሲይዙን እንደዛ ብለው አያልፉንም፡፡ስንሰርቅ ከያዙን ሌባ ፤ ስንገድል ካገኙን ገዳይ ብለው ማሰራቸው አይቀርም፡፡››
‹‹አ…እንግዲያው አለመያዝ ነዋ፡፡አሁን በምትሰሩት ስራ የምታገኙት ለእያንዳንዳችሁ አንድ አንድ ሺ ብር ነው፡፡ትሰራላችሁ ወይስ አትሰሩም…፡፡?›› በወቅቱ ያንን የስራ ግብዣ ከአንደበቷ ሲሰሙ ሁለቱም ጆሮቸውን ነበር ማመን ያቃታቸው፡፡
‹‹እውነትሽን ነው እህቴ?››ናኦል በጉጉት ጠየቃት ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እህቴ እንሳራለን አይደል…?ሁለት ሺ ብር እኮ ብዙ ነው፡፡ብዙ ምግብ ቡዙ ልብስ ይገዛልናል፡፡››
ኑሀሚ ዝም ነበረ ያለችው ..ዝም ስላለች ደግሞ ናኦል አልከፋውም…..ዝም ካለች ወደመስማማቱ እያዘነበለች ነው ሲል ነበር ያሰበው‹‹ተስማምተናል..ስራው ምንድነው?፡፡››
ከኪሷ ጠፍጣፋ የእጅ ሰዓት ምታክል ነገር አወጣችና..‹‹ኩማደር ከዲርን ታውቁታላችሁ…?››
‹‹አዎ እዚህ ሰፈር እሱን የማያውቅ አለ እንዴ..?የእኛ ሰፈር የፖሊስ አዛዥ ነው…፡፡››
‹‹ጥሩ ወደእሱ ቢሮ ትሄዱና የሆነ አሳማኝ ምከንያት ፈጥራችሁ ቢሮው በመግባት ይሄንን ጠረጴዛው ስር ማንም እንዳያየው አድርጋችሁ በማይገኝበት ቦታ ታስቀምጣላችሁ…፡፡››
‹‹እንዴ ምንድነው?ፈንጅ ነው እንዴ?››ኑሀሚ አልፎ አልፎ በፊልም የምታያቸው የአሸባሪዎች የጥቃት አይነቶች ትዝ አላት፡፡
‹‹አረ አይደለም…ይህ ድምፅ መቅጃ ነው፡፡የሚያወራውንና ቢሮ ቁጭ ብሎ ሚሰራውን ስራ ማወቅ ፈልጋለሁ?››
ገራ ገባቸው‹‹ምነው ….ስራውን አትፈልጉም?››
‹‹አይ እሱማ እንፈልጋለን..አንቺ ግን ምን ያደርግልሻል…?››ናኦል እንደማባበል ብሎ ጠየቃት፡፡
‹‹ወንድሜ ከመጀመሪያውም እኮ ይህቺን ልጅ እንዳላመንኳት ነግሬህ ነበር… ምኗም እኮ ቦርኮ አይመስልም፡፡››
‹‹ከሁለታችሁ ማነው ታላቅ?››ያልጠበቁትን ጥያቄ ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹እኔ ነኝ…10 ደቂቃ ቀድማታለው››አለ ናኦል፡፡
‹‹እንዴ መንታ ናችሁ እንዴ…?ለነገሩ ጠርጥሬ ነበር…እኩል እድሜ ላይ እንደምትገኙ እንዲሁ በእይታ ታስታውቃላችሁ፡፡››
‹‹አዎ መንትዬዎች ነን፡፡››አረጋገጡላት፡፡ፔስታሉን ከፈተችና እጇን ወደውስጥ ላከች፡፡ ሰማያዊ ሮዝ ቀለም ያለው ሁለት ሙሉ ቢጃማ ከነአላባሹ አወጣችና‹‹ በስምምነት አንድአንድ ተካፈሉ፡፡›› አለቻቸው፡፡
ሁለቱም ፈዘው ይመለከቷት ጀመር፡፡እሷ እራሷ የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደና መቀየር የሚገባው ነው…ታዲያ ለምን ለእነሱ?››በወቅቱ ግልፅ አልሆነላቸውም ነበር፡፡
‹‹ምነው? ያልኩት አልገባችሁም እንዴ?እነዚህን ቢጃማዎችን የገዛሁት ለእናንተ ነው፡፡እ… ጎረምሳው የትኛው ይሁንልህ?››
‹‹እህቴ ሮዝ ቀለም ትወዳለች..ሮዙ ለእሷ ይሁን፡፡››
‹‹አንተስ ሰማያዊው ይመችሀል?››
‹‹የእኔ ችግር የለውም..እህቴ ደስ ካላት ደስ ይለኛል፡፡ግን ለምን ለራስሽ ሳትገዢ ለእኛ ገዛሽ??››
‹‹ገዝታ አይመስለኝም…ፖሽራ ነው››ኑሀሚ ግምቷን ተናገረች፡፡
‹‹ተይ እህቴ.. ለምን እንደዛ ትያለሽ….?ብትፖሽረውም እኮ ደግነቷን ነው የሚያሳየው፡፡ለእኛ ከመስጠት ሁለቱን ሸጣ አንድ ለእሷ ሚሆን ልብስ ልትገዛበት ትችል ነበር፡፡››
‹‹ እኔም ያልገባኝ እኮ በደንብ ሳታውቀን ለምን ብዬ ነው…?ምን አስባ ነው?››
በወቅቱ የጎዳና ህይወት ልምዳቸው በጣም ተጠራጣሪ አድርጓቸው ነበር፡፡በዛ ምክንያት ነበር እሷን ዘንግተው እርስ በርሳቸው ክርክር ውስጥ የገቡት፡፡
‹‹ኸረ እህቴ አመሰግናለሁ ነው የሚባለው፡፡››
‹‹ናኦሌ ደግሞ… እዚህ ጓደና ላይ ስንት የማጭበርበር ታሪክ እደሚሰራ አታውቂምናነው.?ለሆነ ነገር እያመቻችንስ ቢሆን…?እኔ ይሄንን ልብስ አልፈልግም፡፡አንተም እንድትቀበላት አልፈቅድልህም…፡፡››
ምስራቅ እጇን ወደ ፔስታሉ ሰዳ ሌላ ነገር አወጣች፡፡በስስ ፔስታል የተጠቀለለ ምግብ ነው፡፡ፊት ለፊቷ መሬት አስቀመጠችና ፈታችው፡፡የሚያስጎመዣ አጥንት ያለው የቅቅል ፍትፍት ነው፡፡እጇን ሰደደችና አንዴ ጠቅለል አደረገችና ጎረሰች፡፡ከፔስታሉ ውስጥ የቀረውን ሁለት ሊትር ውሀ አወጣችና ምግቡ ጎን አስቀምጣ…‹‹አንቺ ነብር የሆንሽ ልጅ…ምግቡ ላይም መርዝ አድርገሽበታል እንዳትይ ነው የቀመስኩልሽ፡፡››በማለት ከተቀመጠችበት ተነሳችና ትናንትም ይዛት የነበረውን ፔስታል አንጠልጥላ በመጣችበት መንገድ ተመልሳ መጓዝ ጀመረች፡፡
‹‹ምስራቅ ወዴት ነው…?እህቴ እኮ ሁሉን ነገር የምትጠራጠረው ለእኔ ስለምትጨነቅ ነው፡፡››
‹‹ችግር የለውም..የምሄድበት ቦታ ስላለ ነው፡፡››
‹‹እና ተመልሰሽ ትመጪያለሽ?››
‹‹ይመስለኛል፡፡››ብላ ሄደች፡፡
መንትዬቹ ተፋጠው ተያዩ‹‹እህቴ ለምን አስቀየምሻት?››
‹‹አላስቀየምኳትም…ስለማናውቃት ተጠራጥሬያት ነው፡፡››
‹‹እሺ በቃ …እስኪ ለኪው፡፡›› ብሎ ሮዝ ቀለም ያለውን ቢጃማ አቀበላት፡፡፡ተቀበለችውና ያደረገችውን ነጠላ ጫማ አውልቃ ሱሪውን በቀሚሷን ከፍ አድርጋ አጠለቀችው
‹‹ከስር ካኔቴራ አድርገሽ የለ ቀሚሱን አውልቂው፡፡››
አወለቀችውና ጀኬቱን ከላይ ለበሰችበት..ወደእሷ ተጠጋና ዚፑን ዘጋላት፡፡እና ከእሷ ራቅ ብሎ አያት፡፡
‹‹ውይ አህቴ ..በጣም ነው ፏ-ፈሽ ያልሽው፡፡አቤት ፀጉርሽ ባይንጨፈረር…፡፡››
‹‹እስቲ የራስህን ልበሰውና እንየው››
‹‹አይ የእኔ ይደርሳል…መጀመሪያ ቡሌውን እንጥለፍ፡፡ሽታው ሆዴን አገለባበጠው፡፡››
‹‹እሺ እንብላ›› አለችና ምግብን አመቻችተው ተቀመጡ፡፡በጣም ጣፋጭ ምግብ ነበር፡፡ሆዳቸው እስኪወጠር ድረስ ነበር የበሉት፡፡እንደጨረሱ ናኦልም ለእሱ የመጣለትን ቢጃማ ለበሰ…..
እንደአማረበት ‹‹የእኔን ትላለህ እንጂ አንተም በጣም አምሮብሀል፡፡››ስትል ነበር ያረጋገጠችለት፡፡
‹‹አይደል…?አሁን የት አግኝተን እናመስግናት?››
‹‹እመጣለሁ ብላለች እኮ !ታገስ፡፡››
‹‹እህቴ ስትመጣ ግን እንደቅድሙ ያልሆኑ ያልሆኑ ነገሮች እንዳትናገሪያት፡፡››
‹‹እሞክራለሁ..፡፡ግን ይህቺ ሴት ምኗም አልጣመኝም፡፡ምን ነካህ ወንድሜ ስለእሷ ምንም አናውቅም አኮ!››
‹‹እኮ እንጠይቃታለና….ስንግባባ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን፡፡››
በዛን ቀን እስከ እኩለ ለሊት ቢጠብቋትም ምስራቅ ተመልሳ አልመጣችም ነበር፡፡ናኦል በጣም ቅር ቢለውም ኑሀሚ ግን ብዙም አልከፋትም፡፡እንደውም የወንድሟን ትኩረት ስለተሻማቻት እያበሳጨቻት ነበር፡፡በማግስቱ ጥዋት አንድ ሰዓት ከመሆኑ በፊት ግን ከእንቅልፋቸው ወዝውዛ የቀሰቀሰቻቸው እሷ ነበረች፡፡ናኦል አይኑን ገልጦ እሷ መሆኗን ሲያውቅ በደስታ ዘሎ ተጠመጠመባትና ጉንጫን ሳማት‹‹ማትመለሺ መስሎኝ ደንግጬ ነበር፡፡››
‹‹ምን ያስደነግጥሀል..?እስከዛሬ ከእሷ ጋር የኖርክ አስመሰልከው፡፡››ኑሀሚ በብስጭት መለሰችለት፡፡
‹‹እህቴ ቃል ገብተሸልኝ ነበር አይደል?››
‹‹እሺ..እንዳልክ፡፡››
‹‹እሺ በእኔ መጨቃጨቁን አቁሙና ተነሱ…ጥሩ ጨላ የሚያስገኝ ስራ ትሰራላችሁ፡፡››
‹‹ምንድነው ?ወንጀል እንዳይሆን?››
‹‹ጎዳና እየኖራችሁ ወንጀል ምናምን ትላላችሁ እንዴ…?ወንጀለኛ እናንተ ሳትሆኑ እናንተን እዚህ ጓዳና ላይ የጣላችሁ ስርአት ነው፡፡ ወንጀለኛ እናንተን ትራፊ እየለቃቀማችሁ እንድትኖሩ አይቶ እንዳላ የሚያልፋችሁ ማህበረሰቡ ነው፤እንጂ እናንተ ለመኖርና ህይወታችሁን ለማቆየት ስትሉ የምትሰሩት ነገር በምንም አይንት ወንጀል ሊባል አይችልም፡፡››
‹‹ትክክል ልትሆኚ ትችያለሽ፡፡ግን ዛፓዎች እጅ ከፍንጅ ሲይዙን እንደዛ ብለው አያልፉንም፡፡ስንሰርቅ ከያዙን ሌባ ፤ ስንገድል ካገኙን ገዳይ ብለው ማሰራቸው አይቀርም፡፡››
‹‹አ…እንግዲያው አለመያዝ ነዋ፡፡አሁን በምትሰሩት ስራ የምታገኙት ለእያንዳንዳችሁ አንድ አንድ ሺ ብር ነው፡፡ትሰራላችሁ ወይስ አትሰሩም…፡፡?›› በወቅቱ ያንን የስራ ግብዣ ከአንደበቷ ሲሰሙ ሁለቱም ጆሮቸውን ነበር ማመን ያቃታቸው፡፡
‹‹እውነትሽን ነው እህቴ?››ናኦል በጉጉት ጠየቃት ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እህቴ እንሳራለን አይደል…?ሁለት ሺ ብር እኮ ብዙ ነው፡፡ብዙ ምግብ ቡዙ ልብስ ይገዛልናል፡፡››
ኑሀሚ ዝም ነበረ ያለችው ..ዝም ስላለች ደግሞ ናኦል አልከፋውም…..ዝም ካለች ወደመስማማቱ እያዘነበለች ነው ሲል ነበር ያሰበው‹‹ተስማምተናል..ስራው ምንድነው?፡፡››
ከኪሷ ጠፍጣፋ የእጅ ሰዓት ምታክል ነገር አወጣችና..‹‹ኩማደር ከዲርን ታውቁታላችሁ…?››
‹‹አዎ እዚህ ሰፈር እሱን የማያውቅ አለ እንዴ..?የእኛ ሰፈር የፖሊስ አዛዥ ነው…፡፡››
‹‹ጥሩ ወደእሱ ቢሮ ትሄዱና የሆነ አሳማኝ ምከንያት ፈጥራችሁ ቢሮው በመግባት ይሄንን ጠረጴዛው ስር ማንም እንዳያየው አድርጋችሁ በማይገኝበት ቦታ ታስቀምጣላችሁ…፡፡››
‹‹እንዴ ምንድነው?ፈንጅ ነው እንዴ?››ኑሀሚ አልፎ አልፎ በፊልም የምታያቸው የአሸባሪዎች የጥቃት አይነቶች ትዝ አላት፡፡
‹‹አረ አይደለም…ይህ ድምፅ መቅጃ ነው፡፡የሚያወራውንና ቢሮ ቁጭ ብሎ ሚሰራውን ስራ ማወቅ ፈልጋለሁ?››
ገራ ገባቸው‹‹ምነው ….ስራውን አትፈልጉም?››
‹‹አይ እሱማ እንፈልጋለን..አንቺ ግን ምን ያደርግልሻል…?››ናኦል እንደማባበል ብሎ ጠየቃት፡፡
‹‹ወንድሜ ከመጀመሪያውም እኮ ይህቺን ልጅ እንዳላመንኳት ነግሬህ ነበር… ምኗም እኮ ቦርኮ አይመስልም፡፡››
👍55❤5🥰2
ምስራቅ የኑሀሚን ንጭንጭ ችላ ብላ ስለጉዳዩ ማስረዳቷን ቀጠለችበት ‹‹ኮማንደሩ ወንድሜን ሌባ ነው ብሎ አሳስሮብኛል፡፡የሆነ ህገወጥ ነገር ሲሰራ ወይ ጉቦ ሊቀበል ሲደራደር የሚያሳይ የድምፅ መረጃ ባገኝ በዛ አስፈራርቼ ወንድሜን ላስፈታ ችላለሁ፡፡.››
ኑሀሚ ማውራት ጀመረች‹‹እሺ እንሳረለን….ግን….?››
‹‹ግን ምን እህቴ?››ናኦል እህቱ ነገሩን አወሳስባ እንዳታሰነካክለው ሰጋ፡፡
‹‹ስራው ከባድ ነው…ዛፓዎችን ስናጭበርበር ከተያዝን አደጋው ከባድ ነው..››
‹‹በእኔ ይሁንብሽ እህቴ… አንያዝም፡፡እንደውም እኔ ለብቻዬ አደርገዋለው፡፡››
ኑሀሚን ኮስተር ብላ‹‹አይ እንደዛ አይሆንም.. ምናደርግ ከሆነ አብረን ነው የምናደርገው፡፡ የምትከፍይን ገንዘብ ግን ከስራው አንፃር በቂ አይደለም፡፡ለእያንዳንዳችን ሁለት ሁለት ሺ ብር በጠቅላላው አራት ሺብር ትክፍይናለሽ፡፡››አለቻት
ናኦል ደነገጠ‹‹እህቴ ምን ነካሽ…?ያን ሁሉ ብር ከየት ታመጣለች….? ደግሞ ያን ሁሉ ነገር አድርጋልን..ልብስ አልብሳን…አረ ሁለት ሺ ብሩ ይበቃናል…አታያትም እንዴት…››
ምስራቅ ፈገግ አለች…ወደናኦል ተራመደችና ጭንቅላቱን ደባበሰችውና ‹‹ጓረምሳው ስለሰብክልኝ አመሰግናለው፡፡እህትህ እውነቷን ነው፡፡ከስራው አንፃር ክፍያው አንሷል››አለችና እጆን ወደኪሷ ሰዳ የታሰረ ብር መዥርጣ በማውጣት የተወሰነውን ቆጥራ ከውስጡ መዘዘችና‹‹‹ይሄው ሁለት ሺ ብር ነው…ስራውን ስታጠናቅቁ ደግሞ ቀሪው ሁለት ሺ ብር ሰጣችኋለው፡፡ነብሯ ብሩን ተቀበይ..እንደማየው ሀለቃዋ አንቺ ነሽ፡፡››አለቻትና ብሩን እጇ ላይ አሰቀመጠችላት፡፡
ኑሀሜ ኮስተር እንዳለች ብሩን ተቀበለቻትና ቆጠረችው…ሁለት ሺ ብር መሆኑን ካረጋጠች በኃላ ኪሷ ከተተች…፡፡
‹‹በሉ ማታ ተመልሼ እመጣለሁ፡፡››ብላቸው ጥላቸው ሄደች፡፡
መንትዬችም እንዴት አድርገው ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገቡ፤ እንዴት አድረገው የኮማንደሩ በሮ ዘልቀው መግባትና የተሰጣቸውን ሚስጥራዊ ድምፅ መቅረጫ ትክክለኛ ቦታ ማስቀመጥ እንደሚችሉ ለአንድ ሰዓት ያህል ከተማከሩና በመጨረሻ በእቅዳቸው ላይ ሙሉ በሙሉ ከተስማሙ በኃላ ተያይዘው ወደፖሊስ ጣበያው ሄዱ፡፡
ምስራቅ መንትያዎቹ ለአንድ ሰዓት ያን ሁሉ ሲከራከሩ በሆነ ነገር ሲሳማሙ በሌላው ደግሞ ሲጨቃጨቁና የመጨረሻውን እቅዳቸው ላይ ሲስማሙ ሁሉ ካፌ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ በሞባይሏ እየተከታተለቻቸው ነበር፡፡ጥዋት ለሁለቱም ገዝታ የሰጠቻቸው ቢጃማ ውስጥ የተቀበረ ረቂቅ ድምፅና መስል ጭምር በመቅረፅ በስልኳ ሚያስተላልፍ መሳሪያ ነበር፡፡ዝግጅታቸውን ጨርሰው የመጨረሻ ተልዕኳቸውን ወደሚፈፅሙበት ፓሊስ ጣቢያ ሲያመሩ …መከታተሏን ሳታቋርጥ እጇን ወደፔስታሏ በመላክ አንድ ሌላ አነስተኛ ሞባይል በማውጣት ደወለች፡፡
‹‹ሄሎ ኩማንደር?››
‹‹ሄሎ ሀለቃ እንዴት ነሽ?››
‹‹አለው ሚዳቆዎቹ ወደአንተ እየመጡ ነው››
‹‹እሺ ..እስቲ ይወጡት እንደሆነ እንያ፡፡››
‹‹እሺ በቃ ቸቸው… ወደፖሊስ ጣቢያው ግቢ እየገቡ ነው….››ዘጋችውና ትኩረቷን ሰብስባ እነሱን መከታተሉ ላይ አተኮረች፡፡ቀጥታ ተጋብዘው እንደሚሄዱ ነገር ፊት ለፊት ለጉዳይ ግቢ ውስጥ ያሉትንና ወዲህ ወዲያ በሚተረማመሱት ሰዎች መካከል እየተሸለኮለኩ በማለፍ አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው የኩማደሩ ቢሮ እየሄዱ ነው፡፡የአንደኛ ፎቅ ወለል ግራውንድ ላይ እንዳለው በሰው የተጨናነቀ እና ትርምስ ያለበት አልነበረም፡፡ቢሆንም ግን ወንበር ላይ ቁጭ ብለው ተራቸውን የሚጠብቁ 5 የሚሆኑ ባለጉዳዬች ነበሩ፡፡መንትዬዎችም ቀጥታ ክፍት ወዳለው ወንበር ሄዱና በስነስርአት ተቀምጠው አካባቢውን መቃኘት ጀመሩ፡፡ያለምንም ንግግር አስር ደቂቃ አለፈ፡፡በትዕግስት እየጠበቁ ነው፡፡በራፉ ሲከፈት ወዲያው ኑሀሚ በእጇ የያዘችውን ፍሬ ነገር ወደአፏ ወረወረችና ዋጠችው፡፡ውስጥ ያለው ባለጉዳይ ሲወጣ..‹‹‹ልቀቀኝ ..አድኑኝ ልቀቀኝ…እያለች.ወደተከፈተው በራፍ መንደርደር ጀመረች፡፡አካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ሁሉ በድንጋጤ ከተቀመጡበት ብድግ ብድግ አሉ፡፡በተከፈተው በራፍ ተንደርድራ ወደውስጥ ስትገባ ናኦል..‹‹እህቴን ..እህቴ ምን ነካሽ..?እህቴ ተረጋጊ.. ያምሻል…?››እያለ ተከትሏት ገባ፡፡ግዙፉና ባለቦርጫሙ ኮማንደር በተቀመጠበት አይኖቹን አፍጥጦ በትኩረት እየተካሔደ ያለውን ነገር እየተመለከተ ነው፡፡ክፍት የሆነው በራፉ ግማሽ ደርዘን በሆኑ ሰዎች ታጥሯል፡፡ከዛ ኑሀሚ ድንገት ተዝለፍልፋ ወደቀች፡፡ተንቀጠቀጠችና በአፏ አረፋ ደፈቀች፡፡በራፉ ላይ የተኮለኮሉት ወደውስጥ ተንደረደሩ፡፡ ኮማንደሩ የክብር ወንበሩን ለቆ እነሱ ወዳሉበት ሮጠ፡፡አረፋ እየደፈቀች ያለችው ኑሀሚ ሊይዟት ስራ የደረፈሱትን ሰዎች እየገፈተረች.. ተስባ ጠረጴዛ ስር ገባች፡፡ናኦል..‹‹እህቴን አድኑልኝ እህቴን..››እያለ ተከትሎት ጠረጴዛው ስር ገባ፡፡በአንድ እጁ እሷን እየጎተተ በሌላው እጁ የያዘውን ስውር መሳሪያ ከውሰጠኛው የጠረጳዛው ኮርነር ላይ አጣበቀው..ግማሹ እግሯን ግማሹ እጇን ይዘው ስበው አወጣት..እሱም ተከትሎት ወጣ፡፡
‹‹.የሚጥል በሽታ ነው ያለባት፡፡ስትበሳጭ ይነሳበታል…››ክብሪት ተባለ…ተፈልጎ መጣና እየጫሩ ሰለፈሩን እንድታሸት አደረጉ፡፡ውሀ በማምጣት ግንባሯን እና ልቧ አካባቢ በማፍሰስ እንድትራጋጋ ተሞከረ ፡፡ከእንቅልፍ አንደባነነ ሰው እንደመንቃት አለችና ዙሪያውን በድንጋጤ ተመለከተች››በቃ ዞር በሉላት…ውጡ ከቢሮ…››ኮማንዳሩ በአስፈሪ ድምፅ ከልጆቹ በስተቀር ቢሮ የገቡትን ሰዎች አስወጣና ወንበር ስቦ እንዲቀመጡ በማድረግ ወደቦታው ሔዶ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ ፡፡ለ5 ደቂቃ በመገረምና በአድናቆት ሲያያቸው ከቆየ በኃላ..
‹‹እሺ አሁን ተሻለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ ኮማንደር..ይቅርታ ቢሮህን ረበሽን አይደል?››
‹‹አይ ምንም አይደለል…ግን ምን ሆነሽ ነው?››
‹‹ኮምንደር እህቴ ስትበሳጭ ሁሌ ነው የሚያማት…››ናአል ቀድሞ መልስ ሰጠላት፡፡.
‹‹ምን አበሳጫት…››
‹‹እዚህ እንምጣ ስትለኝ እምቢ ስላልኳት በእኔ ተበሳጭታ ነው፡፡››
‹‹ለምንድነበር እኔ ጋር መምጣት የፈለጋችሁት?››
‹‹ሮንድ የሚዞሩ የሰፈር ሰዎች አንዳንዴ የተኛንበት ቦታ ድረስ መጥተው ይረብሹናል..ሌባ እያሉ ይሰድቡናል፤ከተኛንበትም ያስነሱናል፡፡እና እኛ የት እንሂድ…?አትንኳቸው እንሱ ሌባ አይደሉም እንድትሉልን ነው፡፡››ኑሀሚ አስረዳች፡፡
‹‹ታዲያ አንተ እንዳትመጣ ለምን ፈለክ?››
‹‹አይ ሮንዶቹን የሚልኮቸው ፖሊሶች ናቸው ..ብንከሳቸውም እንደውም በእልክ ከሰፈሩ ሙሉ በሙሉ ያባርሩናል ብዬ ፈርቼ ነው፡፡››
‹‹እና አንተ ፖሊስ ፍትህ ያስከብራል ብለህ አታምንም?››
‹‹አይ.. ብር ላላቸው ሰዎችማ ያስከብራል…፡፡››
ኮማንደሩ በፍፅም መደነቅ ከት ብሎ ሳቀ….ስልኩን አነሳና ደወለ‹‹ሄሎ ሳጄን አንዴ ቢሮ ና፡፡››
ከ2 ደቂቃ በኃላ የተጠራው ሳጂን መጣ
‹‹ሳጂን እነዚህን ልጆች ታውቃቸዋለህ….?››
ሳጂኑ ልጆቹን እያፈራረቀ ትኩር ብሎ አያቸው…ፀዳ ቢሉበትም ያውቃቸዋል… ‹‹አዎ አውቃቸዋለው፡፡›› መለሰ፡፡
‹‹ሮንድ የሚዞሩ የሰፈር ሰዎች እያንገላቱን ነው የሚል ክስ አላቸው፡፡››
ኑሀሚ ማውራት ጀመረች‹‹እሺ እንሳረለን….ግን….?››
‹‹ግን ምን እህቴ?››ናኦል እህቱ ነገሩን አወሳስባ እንዳታሰነካክለው ሰጋ፡፡
‹‹ስራው ከባድ ነው…ዛፓዎችን ስናጭበርበር ከተያዝን አደጋው ከባድ ነው..››
‹‹በእኔ ይሁንብሽ እህቴ… አንያዝም፡፡እንደውም እኔ ለብቻዬ አደርገዋለው፡፡››
ኑሀሚን ኮስተር ብላ‹‹አይ እንደዛ አይሆንም.. ምናደርግ ከሆነ አብረን ነው የምናደርገው፡፡ የምትከፍይን ገንዘብ ግን ከስራው አንፃር በቂ አይደለም፡፡ለእያንዳንዳችን ሁለት ሁለት ሺ ብር በጠቅላላው አራት ሺብር ትክፍይናለሽ፡፡››አለቻት
ናኦል ደነገጠ‹‹እህቴ ምን ነካሽ…?ያን ሁሉ ብር ከየት ታመጣለች….? ደግሞ ያን ሁሉ ነገር አድርጋልን..ልብስ አልብሳን…አረ ሁለት ሺ ብሩ ይበቃናል…አታያትም እንዴት…››
ምስራቅ ፈገግ አለች…ወደናኦል ተራመደችና ጭንቅላቱን ደባበሰችውና ‹‹ጓረምሳው ስለሰብክልኝ አመሰግናለው፡፡እህትህ እውነቷን ነው፡፡ከስራው አንፃር ክፍያው አንሷል››አለችና እጆን ወደኪሷ ሰዳ የታሰረ ብር መዥርጣ በማውጣት የተወሰነውን ቆጥራ ከውስጡ መዘዘችና‹‹‹ይሄው ሁለት ሺ ብር ነው…ስራውን ስታጠናቅቁ ደግሞ ቀሪው ሁለት ሺ ብር ሰጣችኋለው፡፡ነብሯ ብሩን ተቀበይ..እንደማየው ሀለቃዋ አንቺ ነሽ፡፡››አለቻትና ብሩን እጇ ላይ አሰቀመጠችላት፡፡
ኑሀሜ ኮስተር እንዳለች ብሩን ተቀበለቻትና ቆጠረችው…ሁለት ሺ ብር መሆኑን ካረጋጠች በኃላ ኪሷ ከተተች…፡፡
‹‹በሉ ማታ ተመልሼ እመጣለሁ፡፡››ብላቸው ጥላቸው ሄደች፡፡
መንትዬችም እንዴት አድርገው ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገቡ፤ እንዴት አድረገው የኮማንደሩ በሮ ዘልቀው መግባትና የተሰጣቸውን ሚስጥራዊ ድምፅ መቅረጫ ትክክለኛ ቦታ ማስቀመጥ እንደሚችሉ ለአንድ ሰዓት ያህል ከተማከሩና በመጨረሻ በእቅዳቸው ላይ ሙሉ በሙሉ ከተስማሙ በኃላ ተያይዘው ወደፖሊስ ጣበያው ሄዱ፡፡
ምስራቅ መንትያዎቹ ለአንድ ሰዓት ያን ሁሉ ሲከራከሩ በሆነ ነገር ሲሳማሙ በሌላው ደግሞ ሲጨቃጨቁና የመጨረሻውን እቅዳቸው ላይ ሲስማሙ ሁሉ ካፌ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ በሞባይሏ እየተከታተለቻቸው ነበር፡፡ጥዋት ለሁለቱም ገዝታ የሰጠቻቸው ቢጃማ ውስጥ የተቀበረ ረቂቅ ድምፅና መስል ጭምር በመቅረፅ በስልኳ ሚያስተላልፍ መሳሪያ ነበር፡፡ዝግጅታቸውን ጨርሰው የመጨረሻ ተልዕኳቸውን ወደሚፈፅሙበት ፓሊስ ጣቢያ ሲያመሩ …መከታተሏን ሳታቋርጥ እጇን ወደፔስታሏ በመላክ አንድ ሌላ አነስተኛ ሞባይል በማውጣት ደወለች፡፡
‹‹ሄሎ ኩማንደር?››
‹‹ሄሎ ሀለቃ እንዴት ነሽ?››
‹‹አለው ሚዳቆዎቹ ወደአንተ እየመጡ ነው››
‹‹እሺ ..እስቲ ይወጡት እንደሆነ እንያ፡፡››
‹‹እሺ በቃ ቸቸው… ወደፖሊስ ጣቢያው ግቢ እየገቡ ነው….››ዘጋችውና ትኩረቷን ሰብስባ እነሱን መከታተሉ ላይ አተኮረች፡፡ቀጥታ ተጋብዘው እንደሚሄዱ ነገር ፊት ለፊት ለጉዳይ ግቢ ውስጥ ያሉትንና ወዲህ ወዲያ በሚተረማመሱት ሰዎች መካከል እየተሸለኮለኩ በማለፍ አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው የኩማደሩ ቢሮ እየሄዱ ነው፡፡የአንደኛ ፎቅ ወለል ግራውንድ ላይ እንዳለው በሰው የተጨናነቀ እና ትርምስ ያለበት አልነበረም፡፡ቢሆንም ግን ወንበር ላይ ቁጭ ብለው ተራቸውን የሚጠብቁ 5 የሚሆኑ ባለጉዳዬች ነበሩ፡፡መንትዬዎችም ቀጥታ ክፍት ወዳለው ወንበር ሄዱና በስነስርአት ተቀምጠው አካባቢውን መቃኘት ጀመሩ፡፡ያለምንም ንግግር አስር ደቂቃ አለፈ፡፡በትዕግስት እየጠበቁ ነው፡፡በራፉ ሲከፈት ወዲያው ኑሀሚ በእጇ የያዘችውን ፍሬ ነገር ወደአፏ ወረወረችና ዋጠችው፡፡ውስጥ ያለው ባለጉዳይ ሲወጣ..‹‹‹ልቀቀኝ ..አድኑኝ ልቀቀኝ…እያለች.ወደተከፈተው በራፍ መንደርደር ጀመረች፡፡አካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ሁሉ በድንጋጤ ከተቀመጡበት ብድግ ብድግ አሉ፡፡በተከፈተው በራፍ ተንደርድራ ወደውስጥ ስትገባ ናኦል..‹‹እህቴን ..እህቴ ምን ነካሽ..?እህቴ ተረጋጊ.. ያምሻል…?››እያለ ተከትሏት ገባ፡፡ግዙፉና ባለቦርጫሙ ኮማንደር በተቀመጠበት አይኖቹን አፍጥጦ በትኩረት እየተካሔደ ያለውን ነገር እየተመለከተ ነው፡፡ክፍት የሆነው በራፉ ግማሽ ደርዘን በሆኑ ሰዎች ታጥሯል፡፡ከዛ ኑሀሚ ድንገት ተዝለፍልፋ ወደቀች፡፡ተንቀጠቀጠችና በአፏ አረፋ ደፈቀች፡፡በራፉ ላይ የተኮለኮሉት ወደውስጥ ተንደረደሩ፡፡ ኮማንደሩ የክብር ወንበሩን ለቆ እነሱ ወዳሉበት ሮጠ፡፡አረፋ እየደፈቀች ያለችው ኑሀሚ ሊይዟት ስራ የደረፈሱትን ሰዎች እየገፈተረች.. ተስባ ጠረጴዛ ስር ገባች፡፡ናኦል..‹‹እህቴን አድኑልኝ እህቴን..››እያለ ተከትሎት ጠረጴዛው ስር ገባ፡፡በአንድ እጁ እሷን እየጎተተ በሌላው እጁ የያዘውን ስውር መሳሪያ ከውሰጠኛው የጠረጳዛው ኮርነር ላይ አጣበቀው..ግማሹ እግሯን ግማሹ እጇን ይዘው ስበው አወጣት..እሱም ተከትሎት ወጣ፡፡
‹‹.የሚጥል በሽታ ነው ያለባት፡፡ስትበሳጭ ይነሳበታል…››ክብሪት ተባለ…ተፈልጎ መጣና እየጫሩ ሰለፈሩን እንድታሸት አደረጉ፡፡ውሀ በማምጣት ግንባሯን እና ልቧ አካባቢ በማፍሰስ እንድትራጋጋ ተሞከረ ፡፡ከእንቅልፍ አንደባነነ ሰው እንደመንቃት አለችና ዙሪያውን በድንጋጤ ተመለከተች››በቃ ዞር በሉላት…ውጡ ከቢሮ…››ኮማንዳሩ በአስፈሪ ድምፅ ከልጆቹ በስተቀር ቢሮ የገቡትን ሰዎች አስወጣና ወንበር ስቦ እንዲቀመጡ በማድረግ ወደቦታው ሔዶ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ ፡፡ለ5 ደቂቃ በመገረምና በአድናቆት ሲያያቸው ከቆየ በኃላ..
‹‹እሺ አሁን ተሻለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ ኮማንደር..ይቅርታ ቢሮህን ረበሽን አይደል?››
‹‹አይ ምንም አይደለል…ግን ምን ሆነሽ ነው?››
‹‹ኮምንደር እህቴ ስትበሳጭ ሁሌ ነው የሚያማት…››ናአል ቀድሞ መልስ ሰጠላት፡፡.
‹‹ምን አበሳጫት…››
‹‹እዚህ እንምጣ ስትለኝ እምቢ ስላልኳት በእኔ ተበሳጭታ ነው፡፡››
‹‹ለምንድነበር እኔ ጋር መምጣት የፈለጋችሁት?››
‹‹ሮንድ የሚዞሩ የሰፈር ሰዎች አንዳንዴ የተኛንበት ቦታ ድረስ መጥተው ይረብሹናል..ሌባ እያሉ ይሰድቡናል፤ከተኛንበትም ያስነሱናል፡፡እና እኛ የት እንሂድ…?አትንኳቸው እንሱ ሌባ አይደሉም እንድትሉልን ነው፡፡››ኑሀሚ አስረዳች፡፡
‹‹ታዲያ አንተ እንዳትመጣ ለምን ፈለክ?››
‹‹አይ ሮንዶቹን የሚልኮቸው ፖሊሶች ናቸው ..ብንከሳቸውም እንደውም በእልክ ከሰፈሩ ሙሉ በሙሉ ያባርሩናል ብዬ ፈርቼ ነው፡፡››
‹‹እና አንተ ፖሊስ ፍትህ ያስከብራል ብለህ አታምንም?››
‹‹አይ.. ብር ላላቸው ሰዎችማ ያስከብራል…፡፡››
ኮማንደሩ በፍፅም መደነቅ ከት ብሎ ሳቀ….ስልኩን አነሳና ደወለ‹‹ሄሎ ሳጄን አንዴ ቢሮ ና፡፡››
ከ2 ደቂቃ በኃላ የተጠራው ሳጂን መጣ
‹‹ሳጂን እነዚህን ልጆች ታውቃቸዋለህ….?››
ሳጂኑ ልጆቹን እያፈራረቀ ትኩር ብሎ አያቸው…ፀዳ ቢሉበትም ያውቃቸዋል… ‹‹አዎ አውቃቸዋለው፡፡›› መለሰ፡፡
‹‹ሮንድ የሚዞሩ የሰፈር ሰዎች እያንገላቱን ነው የሚል ክስ አላቸው፡፡››
👍43❤8
‹‹እያንገላቱን..እነማን ናቸው?››
‹‹እኛ በስም አናውቃቸውም..ሮንድ መሆናቸውን ብቻ ነው የምናውቀው፡፡›› ኑሀሚ ነች ተናጋሪዋ፡፡
‹‹በቃ ሳጆን ሮንድ ለሚያሰማሩ የቀበሌ ሰዎች ንገራቸው፡፡በተለይ እነዚህን ሁለት ልጆች እንዳይነኳቸው፡፡እናንተም ከአሁን ወዲህ ምንም አይነት ችግር ካጋጠማችሁ…ማለቴ ሮንድም ሆነ ሌላ ማንም ሰው ሊተናኮላችሁ ከሞከረ መጥታችው ቀጥታ ለሳጅን ንገሩት..እሱ ሁሉን ነገር ያስተካክልላችኋል ..አይደል ሳጅን?››
‹‹በትክክል ኮማንደር››ብሎ ትዕዛዙን ተቀብሎ ወታደራዊ ሰላምታውን ሰጥቶ ወጥቶ ሄደ፡፡
…‹‹በሉ አሁን መሄድ ትችላላቸሁ፡፡››
‹‹ኮማንደር እናመሰግናለን..እግዜር ይስጥልን፡፡››ብለው ተያይዘው ወጡ፡፡ኮማንደር ሌላ ባለጉዳይ እንዳይገባ ቶሎ ብሎ ቢሮውን ከውስጥ ቀረቀረና ወለል ላይ ተንበርክኮ ጠረጴዛ ስር ገባ፡፡ፈለገ አገኘው፡፡ በስነስርአት ትክክለኛው ቦታ ላይ ተቀምጧል፡፡ አነሳው..እና ወጣ፡፡ስልኩን አንሰቶ ደወለ
‹‹ሀለቃ፡፡››
‹‹እሺ እየተመለከትኳችሁ ነበረ እኮ፡፡››
‹‹ልጆቹ መአተኞች ናቸው፡፡እያወቅኩ እራሱ እኮ አሳመኑኝ፡፡ በምን አይንሽ አየሻቸው?…ይገርማል፡፡››
‹‹አንድ ወር ሙሉ የቀንና ሌት ውሎቸውን ተከታትዬለሁ፡፡ሁሉንም መስፈርቶቼን የሚያማሉ እንደሆነ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይሄው የመጨረሻ ፈተናውን አልፈዋል፡፡ እግዲህ እነዚህን ለአንድ ስድስት ወር ሲሰለጥኑ ምን አይነት እሳት የላሱ ሰላዬች እንደሚወጣቸው መገመት ቀላል ነው፡፡››የሚል አስተያየት ነበር የሰጠችው፡፡
‹‹በዛ ጥርጥር የለኝም…››
‹‹ኩማንደር በፈተናው ስለተባበርከኝ አመሰገናለሁ፡፡››
‹‹ሀለቃ….ለእንደዚህ አይነት ለሀገር ወሳኝ ለሆነ ሰራ የራሴን የሆነ ጥቂትም ቢሆን አስተዋፅኦ እንዳበረክት እድሉን ስላገኘው እኔ ነኝ ክብር የሚሰማኝ፡፡››
‹‹እሺቸው፡› ስልኩተዘጋ፡
ይሄ ለስለላ ተግባር ብቁ እንዲሆኑ ያስቻላቸው የመጀመሪያ የተግባር ፈተናቸው ነበር፡፡
ከዚህ ሁሉ ረጅም የልጅነት የመከራ ወቅት ትዝታዋን ስታመነዥግ ለሳዕታት ስላሳለፍች አእምሮዋንም ደከማትና አይኖቾን ከደነች…ወዲያው እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹እኛ በስም አናውቃቸውም..ሮንድ መሆናቸውን ብቻ ነው የምናውቀው፡፡›› ኑሀሚ ነች ተናጋሪዋ፡፡
‹‹በቃ ሳጆን ሮንድ ለሚያሰማሩ የቀበሌ ሰዎች ንገራቸው፡፡በተለይ እነዚህን ሁለት ልጆች እንዳይነኳቸው፡፡እናንተም ከአሁን ወዲህ ምንም አይነት ችግር ካጋጠማችሁ…ማለቴ ሮንድም ሆነ ሌላ ማንም ሰው ሊተናኮላችሁ ከሞከረ መጥታችው ቀጥታ ለሳጅን ንገሩት..እሱ ሁሉን ነገር ያስተካክልላችኋል ..አይደል ሳጅን?››
‹‹በትክክል ኮማንደር››ብሎ ትዕዛዙን ተቀብሎ ወታደራዊ ሰላምታውን ሰጥቶ ወጥቶ ሄደ፡፡
…‹‹በሉ አሁን መሄድ ትችላላቸሁ፡፡››
‹‹ኮማንደር እናመሰግናለን..እግዜር ይስጥልን፡፡››ብለው ተያይዘው ወጡ፡፡ኮማንደር ሌላ ባለጉዳይ እንዳይገባ ቶሎ ብሎ ቢሮውን ከውስጥ ቀረቀረና ወለል ላይ ተንበርክኮ ጠረጴዛ ስር ገባ፡፡ፈለገ አገኘው፡፡ በስነስርአት ትክክለኛው ቦታ ላይ ተቀምጧል፡፡ አነሳው..እና ወጣ፡፡ስልኩን አንሰቶ ደወለ
‹‹ሀለቃ፡፡››
‹‹እሺ እየተመለከትኳችሁ ነበረ እኮ፡፡››
‹‹ልጆቹ መአተኞች ናቸው፡፡እያወቅኩ እራሱ እኮ አሳመኑኝ፡፡ በምን አይንሽ አየሻቸው?…ይገርማል፡፡››
‹‹አንድ ወር ሙሉ የቀንና ሌት ውሎቸውን ተከታትዬለሁ፡፡ሁሉንም መስፈርቶቼን የሚያማሉ እንደሆነ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይሄው የመጨረሻ ፈተናውን አልፈዋል፡፡ እግዲህ እነዚህን ለአንድ ስድስት ወር ሲሰለጥኑ ምን አይነት እሳት የላሱ ሰላዬች እንደሚወጣቸው መገመት ቀላል ነው፡፡››የሚል አስተያየት ነበር የሰጠችው፡፡
‹‹በዛ ጥርጥር የለኝም…››
‹‹ኩማንደር በፈተናው ስለተባበርከኝ አመሰገናለሁ፡፡››
‹‹ሀለቃ….ለእንደዚህ አይነት ለሀገር ወሳኝ ለሆነ ሰራ የራሴን የሆነ ጥቂትም ቢሆን አስተዋፅኦ እንዳበረክት እድሉን ስላገኘው እኔ ነኝ ክብር የሚሰማኝ፡፡››
‹‹እሺቸው፡› ስልኩተዘጋ፡
ይሄ ለስለላ ተግባር ብቁ እንዲሆኑ ያስቻላቸው የመጀመሪያ የተግባር ፈተናቸው ነበር፡፡
ከዚህ ሁሉ ረጅም የልጅነት የመከራ ወቅት ትዝታዋን ስታመነዥግ ለሳዕታት ስላሳለፍች አእምሮዋንም ደከማትና አይኖቾን ከደነች…ወዲያው እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍61🥰8👏7🔥6❤5👎2
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፔሩ/አማዞን ወንዝ ላይ
ዳግላስ ሚስቱ የሰጠችውን መድሀኒት ወስዶ ከተኛ ከሁለት ሰዓት በኃላ ነቃ፡፡አይኑን ሲገልጥ የቅንጡ ጀልባዋ መኝታ ቤት ውስጥ ብቻዋን ነው ያለው፡፡ ከነቃም በኃላ አይኑን ብቻ ገልጦ ዙሪያ ገባውን እየቃኘ ባለበት ሆኖ 15 ደቂቃ አሳለፈ፡፡፡ከዛ ተነሳና በራፉን ከፍቶ ‹‹ማሪያ…ማሪያ እያ ተጣራ››ስሙ ሳያስበው ነው አፉ ውስጥ የገባለት፡፡ ሚስቱ ተንደርድራ መጣችን ፊቱ ቆመች፡፡ ወደራሱ ጎትቶ አቀፋትና ደረቱ ላይ ለጥፎ ከንፈሯን ለረጅም ደቂቃ መጠጣት፡፡እሷም እጆቾን ዘርግታ በአንገቷ ዙሪያ አሽከርክራ አቀፈችውና እላዩ ላይ ተንጠለጠለችበት፡፡
‹‹ማሪያ የእኔ ውድ ..አንጀሊናስ?››
‹‹ከእነ ሳንዲያጎ ጋር ነች፡፡እጇን ይዞ እየጎተተ ወደጀልባዋ በረንዳ ወጣ፡፡ሲደርስ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ አስፈሪ ጠባቂዎች ከየተቀመጡበት በድንጋጤ ተነሱና ቀጥ ብለው ቆሙ….አንጀሊና አባቷን ስታይ ወደእሱ ተንደረደረች…በአየር ላይ ቀለባትና ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ አሽከረከራት፡፡ መርከቡ ላይ ያሉት ሁሉ ደስ አላቸው፡፡አሁን እራሱን ዳግላስን ሆኖል ማለት ነው፡፡ከልጁ ና ከሚስቱ ጋር ሀያ ለሚሆኑ ደቂቃዎች በማሳለፍ በመጠኑ ናፍቆቱን ከተወጣ በኃላ እነሱን ወደውስጥ ገብተው እንዲጠብቁት አዞ …ቀጥታ መርከቡ ላይ ካሉት 5 ታጣቂዎች ጋር ስብሰባ ተቀመጠ፡፡
‹‹እሺ እየሰማዋችሁ ነው፡፡››
የታጣቂዎች ሀለቃ የሚመስለው ግዝፍ ሰው አንገቱን እንደደፋ መናገር ጀመረ‹‹ሀለቃ በተፈጠረው ነገር በጣም እናዝናለን፡፡በእውነቱ ችግሩ እንደተፈጠረ ስንሰማ ወዲያው ነበር እርምጃ የወሰድነው››
‹‹እኮ ምን አደረጋችሁ?››
‹‹ያው ብራዚሊያ አየር ማረፊያ ገብታችሁ ነበር… አንተ ወደፕሌኑ ማለፍ ብትችልም አብሮህ የነበረው ፓብሎ ግን በፖሊስ እጅ ወደቀ፡፡አንተን ማሳለፍ ቢችልም እሱ እራሱን ግን ከፖሊሶች እጅ ማስመለጥ አልቻለም፡፡እና ምንም ልንረዳው ባለመቻላችን…ጠበቀ ያለ ምርመራ ሲደረግበት ስለአንተ የሆነ ሚስጥር ሊያወጣ ይችላል ብለን ስለሰጋን እዛው የገባበት እስር ቤት እርምጃ እንዲወሰድበት አድርገናል፡፡
አንተን ወደ ብራዚሊያ ይዛ የሚበረው አውሮፕላን በአየር ፀባይ ምክንያት ኢኩዩቶስ እንደረፈ ስንሰማ እኔ እራሴ ነኝ አንድ ቡድን እየመራሁ በቻርተር አውሮፕላን ወደዛ ያመራሁት፡፡ከዛ ምን አልባት የመንግስት ሰዎች ሆኑ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች እጅ እንዳትገባ ተጠንቅቀን ከሆቴል ስትወጣ አፈነንህ ከኢኩዬቶስ አስወጣንህ፡፡
‹‹ጥሩ ስራ ነው….እርግጠኛ ነኝ ምንም ያዝረከረካችሁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አረ የለም..ሁሉን ነገር በጥንቃቄ ነው የተከወነው…ግን….››
‹‹‹ግን ምን?››
‹‹አንድ የአንተን ውሳኔ የሚጠብቅ ጉዳይ አለን፡፡››
‹‹ምንድ ነው?››
‹‹ልጅቷን ምን እናድረጋት …?ምን አልባት የምትለው ነገር ይኖራል ብለን..ወደ ዋናው ሳንቺዋሪ እየወሰድናት ነው፡፡አሁን ላቲሲያ ደርሰዋል፡፡ለሁለት ቀን እዛ ቆይተው…ወደሳንቹዋሪ ይዘዋት ይመጣሉ፡፡
‹‹ምንድነው የምታወራው ..?የቷ ልጅ?››
ሰውዬው አንዴ ዳግላስን አንዴ ደግሞ ወደመርከቡ የውስጠኛ በራፍ እያየ ለመናገር ጊዜ ወሰደ‹‹እየጠየቅኩህ እኮ ነው..የምን ልጅ?››
ድምፁን ቀነሰና …‹‹ሆቴል ስናገኝህ ከሆነች አፍሪካዊት ልጅ ጋር ነበርክ….፡፡ ከኤርፖርት አብራችሁ ወጥታችሁ ሆቴልም አንድ ክፍል ነው ያደራችሁት፡፡››ለምን ድምፁ ቀንሶ እንደሚያወራ አሁን ገባው፡፡ከሴት ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ማደሩን ሚስቱ ሰምታ ግርግር እንዳትፈጥር ነው፡፡አሱ ግን ያ ብዙ አላስጨነቀውም፡፡
‹‹እርግጠኛ ነህ..እንደዛ አድርጌለሁ?››
‹‹አዎ እርግጠኛ ነኝ…ምን አልባት ስለአንተ ማንነት ያወቀችው ነገር ይኖር ይሆናል ብለን ስለሰጋን ልንለቃት አልፈለግንም፡፡››
‹‹እና አሁን ወደሴንቸዋሪ ከሚጓዘው ቡዱን ጋር እየወሰድናት ነው እያልከኝ ነው፡፡››
‹‹አዎ፡፡››
‹‹ሽጉጥህን ስጠኝ ፡፡››ኮሰተር ያለ ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ሁሉም በያለበት ሽምቅቅ አሉ፡፡ዳግላስ ሽጉጥ ስጠኝ ካለ የሆነ ችግር ሊፈጠር እንደሆነ ሁሉም ያውቃሉ፡፡ሽጉጥ እጁ ከገባ ይተኩሳል፡፡ሲተኩስ ደግሞ አየር ላይ አይደለም..ወይ አንዱ ደረት ላይ ወይ ደግሞ ጭንቅላት ላይ ነው የሚያሳርፈው፡፡በሚንቀጠቀጡ እጆቹ ሽጉጡን ከጎኑ መዞ ሰጠው…ግንባሩ ላይ ደቀነበት፡፡
‹‹እንዴት አንድ ምንነቷን የማታውቃትን መንገደኛ ሴት እየነዱ ወደግዛቴ ይዘዋት እንዲመጡ ትዕዛዝ ታስተላልፋለህ….?ምን ተልዕኮ እንዳላት ታውቃለህ…?ማን እንዳሰማራትስ?››
‹‹ጌታዬ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርገናል…ሙሉ እቃዋን ሆነ ጠቅላላ ሰውነቷን አብጠርጥረን ፈትሸናል፡፡ አታስፈልግም ካልከን አሁን ባለችበት እንዲያስወግዶት ማድረግ እችላለሁ፡፡››በፍርሀት በራደና በሚንቀጠቀት ድምፅ ሊያስረዳው ሞከረ፡፡
‹‹አይ መጀመሪያ አንተን አስወግድህና ትዕዛዙን እራሴ አስተላላፋለሁ፡፡››የሽጉጡን መጠበቂያ አላቀቀ….እጠቱን ምላጩ ላይ አሳረፈ…በዚህ ቅፅበት ልጁ‹‹አባዬ…አባዬ›› እያለች የጀልባውን በራፉ ከፍታ ወደእሱ ተንደረደረች….ቶሎ ብሎ የደቀነውን ሽጉጥ ከሰውዬው ግንባር ላይ አላቀቀና ጠረጴዛ ላይ ወርውሮ ከተቀመጠበት በመነሳት ወደ ልጅ ተንደረደረ፡፡አቃፋትና አባበላት፡፡ዝም ስትል ወደ ታጣቂዎች ዞረና ትዕዛዙን አሰስተላለፈ‹‹ በሉ አሁን ጉዞ እንቀጥል፡፡ እስከአሁን ያባከነው ሰዓት ይበቃል ፡፡ዛሬ ካምፕ ገብተን ማደር አለብን፡፡››
‹‹እሺ ጌታዬ ..ልጅቷን በተመለከተ ትዛዙን ላስተላልፍ?፡፡››
እንደማሰብ አለና‹‹..አይ ያንን ዕድልማ አጥተኸዋል…አሁን እራሴ የሚሆነውን አደርጋለው፡፡››ብሎ ወደውስጥ ገባ…..ጀልባዋም ተንቀሳቀሰችና ጉዞ ጀመረች፡፡
ወዲያው ነበር እጃቸው ላይ ያለችውን ሴት ገድለው ማንም እንዳያገኛት አድርገው እንዲቀብሯት ላቲሲያ ለሚገኙት ገዳዬቹ ትዕዛዝ የስተላለፈው፡፡
ኮለምቢያ
/ላቲሲ(አማዞን ወንዝን ታካ የተመሰረተች በአሳ ምርቶ የምትጣወቅ ከተማ) ካርሎስ ከገዳይ አጋሮቹ ፈንጠር ብሎ አንድ ግዙፍ ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ በማስታወሻ ደብተሩ ላይ የቀን ውሎውንና ገጠመኞቹን በምጥን ቃላት እያሰፈረ ሳለ በቡድኑ ሀለቃ ተጠራ፡፡ማስተወሻ ደብተሩን አጣጥፎ ጎኑ ያለው የጉዞ ቦርሳው ውስጥ ከተተና መሳሪያውን በአንድ ተከሻው አንጠልጥሎ ቦርሳውን በእጁ ይዞ ወደተጠራበት ቦታ ሄደ፡፡
ቀጥታ ‹‹ግባና ግደላት፡፡››የሚል ትዕዛዝ ነበር የሰጠው፡፡
‹‹ምን ?››ካርሎስ ሀላቀውን በድንጋጤ ጠየቀ፡፡
‹‹ትልቁ ሀለቃችን ትገደል ብሏል…ግባና ግደላት፡፡››ኮስተር ብሎ በድጋሚ ትዕዛዙን አስተላለፈ፡፡
‹‹እርግጠኛ ናችሁ ትገደል ብሏል?››
‹‹ሰውዬ ያምሀል እንዴ? እኔ የተሳሳተ ትዕዛዝ ሳስተላልፈ አይተሀኝ ታቃለህ..?ነው ወይስ ፈራህ?ከፈራህ ግድ የለም ሌላ ሰው በደስታ ያድርገዋል፡፡እኔ እኮ ስለምትወዳት በፍቅር እንድትገድላት እድሉን ልስጥህ ብዬ ነው እንጂ ሌሎች በደስታ የሚፈፅሙት ትዕዛዝ መሆኑን አጥቼው አይደለም …ምንም ቢሆን እሷን እዚህ ድረስ በማጓጓዙ ከአንተ እኩል የለፋ የለም፡፡››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፔሩ/አማዞን ወንዝ ላይ
ዳግላስ ሚስቱ የሰጠችውን መድሀኒት ወስዶ ከተኛ ከሁለት ሰዓት በኃላ ነቃ፡፡አይኑን ሲገልጥ የቅንጡ ጀልባዋ መኝታ ቤት ውስጥ ብቻዋን ነው ያለው፡፡ ከነቃም በኃላ አይኑን ብቻ ገልጦ ዙሪያ ገባውን እየቃኘ ባለበት ሆኖ 15 ደቂቃ አሳለፈ፡፡፡ከዛ ተነሳና በራፉን ከፍቶ ‹‹ማሪያ…ማሪያ እያ ተጣራ››ስሙ ሳያስበው ነው አፉ ውስጥ የገባለት፡፡ ሚስቱ ተንደርድራ መጣችን ፊቱ ቆመች፡፡ ወደራሱ ጎትቶ አቀፋትና ደረቱ ላይ ለጥፎ ከንፈሯን ለረጅም ደቂቃ መጠጣት፡፡እሷም እጆቾን ዘርግታ በአንገቷ ዙሪያ አሽከርክራ አቀፈችውና እላዩ ላይ ተንጠለጠለችበት፡፡
‹‹ማሪያ የእኔ ውድ ..አንጀሊናስ?››
‹‹ከእነ ሳንዲያጎ ጋር ነች፡፡እጇን ይዞ እየጎተተ ወደጀልባዋ በረንዳ ወጣ፡፡ሲደርስ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ አስፈሪ ጠባቂዎች ከየተቀመጡበት በድንጋጤ ተነሱና ቀጥ ብለው ቆሙ….አንጀሊና አባቷን ስታይ ወደእሱ ተንደረደረች…በአየር ላይ ቀለባትና ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ አሽከረከራት፡፡ መርከቡ ላይ ያሉት ሁሉ ደስ አላቸው፡፡አሁን እራሱን ዳግላስን ሆኖል ማለት ነው፡፡ከልጁ ና ከሚስቱ ጋር ሀያ ለሚሆኑ ደቂቃዎች በማሳለፍ በመጠኑ ናፍቆቱን ከተወጣ በኃላ እነሱን ወደውስጥ ገብተው እንዲጠብቁት አዞ …ቀጥታ መርከቡ ላይ ካሉት 5 ታጣቂዎች ጋር ስብሰባ ተቀመጠ፡፡
‹‹እሺ እየሰማዋችሁ ነው፡፡››
የታጣቂዎች ሀለቃ የሚመስለው ግዝፍ ሰው አንገቱን እንደደፋ መናገር ጀመረ‹‹ሀለቃ በተፈጠረው ነገር በጣም እናዝናለን፡፡በእውነቱ ችግሩ እንደተፈጠረ ስንሰማ ወዲያው ነበር እርምጃ የወሰድነው››
‹‹እኮ ምን አደረጋችሁ?››
‹‹ያው ብራዚሊያ አየር ማረፊያ ገብታችሁ ነበር… አንተ ወደፕሌኑ ማለፍ ብትችልም አብሮህ የነበረው ፓብሎ ግን በፖሊስ እጅ ወደቀ፡፡አንተን ማሳለፍ ቢችልም እሱ እራሱን ግን ከፖሊሶች እጅ ማስመለጥ አልቻለም፡፡እና ምንም ልንረዳው ባለመቻላችን…ጠበቀ ያለ ምርመራ ሲደረግበት ስለአንተ የሆነ ሚስጥር ሊያወጣ ይችላል ብለን ስለሰጋን እዛው የገባበት እስር ቤት እርምጃ እንዲወሰድበት አድርገናል፡፡
አንተን ወደ ብራዚሊያ ይዛ የሚበረው አውሮፕላን በአየር ፀባይ ምክንያት ኢኩዩቶስ እንደረፈ ስንሰማ እኔ እራሴ ነኝ አንድ ቡድን እየመራሁ በቻርተር አውሮፕላን ወደዛ ያመራሁት፡፡ከዛ ምን አልባት የመንግስት ሰዎች ሆኑ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች እጅ እንዳትገባ ተጠንቅቀን ከሆቴል ስትወጣ አፈነንህ ከኢኩዬቶስ አስወጣንህ፡፡
‹‹ጥሩ ስራ ነው….እርግጠኛ ነኝ ምንም ያዝረከረካችሁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አረ የለም..ሁሉን ነገር በጥንቃቄ ነው የተከወነው…ግን….››
‹‹‹ግን ምን?››
‹‹አንድ የአንተን ውሳኔ የሚጠብቅ ጉዳይ አለን፡፡››
‹‹ምንድ ነው?››
‹‹ልጅቷን ምን እናድረጋት …?ምን አልባት የምትለው ነገር ይኖራል ብለን..ወደ ዋናው ሳንቺዋሪ እየወሰድናት ነው፡፡አሁን ላቲሲያ ደርሰዋል፡፡ለሁለት ቀን እዛ ቆይተው…ወደሳንቹዋሪ ይዘዋት ይመጣሉ፡፡
‹‹ምንድነው የምታወራው ..?የቷ ልጅ?››
ሰውዬው አንዴ ዳግላስን አንዴ ደግሞ ወደመርከቡ የውስጠኛ በራፍ እያየ ለመናገር ጊዜ ወሰደ‹‹እየጠየቅኩህ እኮ ነው..የምን ልጅ?››
ድምፁን ቀነሰና …‹‹ሆቴል ስናገኝህ ከሆነች አፍሪካዊት ልጅ ጋር ነበርክ….፡፡ ከኤርፖርት አብራችሁ ወጥታችሁ ሆቴልም አንድ ክፍል ነው ያደራችሁት፡፡››ለምን ድምፁ ቀንሶ እንደሚያወራ አሁን ገባው፡፡ከሴት ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ማደሩን ሚስቱ ሰምታ ግርግር እንዳትፈጥር ነው፡፡አሱ ግን ያ ብዙ አላስጨነቀውም፡፡
‹‹እርግጠኛ ነህ..እንደዛ አድርጌለሁ?››
‹‹አዎ እርግጠኛ ነኝ…ምን አልባት ስለአንተ ማንነት ያወቀችው ነገር ይኖር ይሆናል ብለን ስለሰጋን ልንለቃት አልፈለግንም፡፡››
‹‹እና አሁን ወደሴንቸዋሪ ከሚጓዘው ቡዱን ጋር እየወሰድናት ነው እያልከኝ ነው፡፡››
‹‹አዎ፡፡››
‹‹ሽጉጥህን ስጠኝ ፡፡››ኮሰተር ያለ ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ሁሉም በያለበት ሽምቅቅ አሉ፡፡ዳግላስ ሽጉጥ ስጠኝ ካለ የሆነ ችግር ሊፈጠር እንደሆነ ሁሉም ያውቃሉ፡፡ሽጉጥ እጁ ከገባ ይተኩሳል፡፡ሲተኩስ ደግሞ አየር ላይ አይደለም..ወይ አንዱ ደረት ላይ ወይ ደግሞ ጭንቅላት ላይ ነው የሚያሳርፈው፡፡በሚንቀጠቀጡ እጆቹ ሽጉጡን ከጎኑ መዞ ሰጠው…ግንባሩ ላይ ደቀነበት፡፡
‹‹እንዴት አንድ ምንነቷን የማታውቃትን መንገደኛ ሴት እየነዱ ወደግዛቴ ይዘዋት እንዲመጡ ትዕዛዝ ታስተላልፋለህ….?ምን ተልዕኮ እንዳላት ታውቃለህ…?ማን እንዳሰማራትስ?››
‹‹ጌታዬ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርገናል…ሙሉ እቃዋን ሆነ ጠቅላላ ሰውነቷን አብጠርጥረን ፈትሸናል፡፡ አታስፈልግም ካልከን አሁን ባለችበት እንዲያስወግዶት ማድረግ እችላለሁ፡፡››በፍርሀት በራደና በሚንቀጠቀት ድምፅ ሊያስረዳው ሞከረ፡፡
‹‹አይ መጀመሪያ አንተን አስወግድህና ትዕዛዙን እራሴ አስተላላፋለሁ፡፡››የሽጉጡን መጠበቂያ አላቀቀ….እጠቱን ምላጩ ላይ አሳረፈ…በዚህ ቅፅበት ልጁ‹‹አባዬ…አባዬ›› እያለች የጀልባውን በራፉ ከፍታ ወደእሱ ተንደረደረች….ቶሎ ብሎ የደቀነውን ሽጉጥ ከሰውዬው ግንባር ላይ አላቀቀና ጠረጴዛ ላይ ወርውሮ ከተቀመጠበት በመነሳት ወደ ልጅ ተንደረደረ፡፡አቃፋትና አባበላት፡፡ዝም ስትል ወደ ታጣቂዎች ዞረና ትዕዛዙን አሰስተላለፈ‹‹ በሉ አሁን ጉዞ እንቀጥል፡፡ እስከአሁን ያባከነው ሰዓት ይበቃል ፡፡ዛሬ ካምፕ ገብተን ማደር አለብን፡፡››
‹‹እሺ ጌታዬ ..ልጅቷን በተመለከተ ትዛዙን ላስተላልፍ?፡፡››
እንደማሰብ አለና‹‹..አይ ያንን ዕድልማ አጥተኸዋል…አሁን እራሴ የሚሆነውን አደርጋለው፡፡››ብሎ ወደውስጥ ገባ…..ጀልባዋም ተንቀሳቀሰችና ጉዞ ጀመረች፡፡
ወዲያው ነበር እጃቸው ላይ ያለችውን ሴት ገድለው ማንም እንዳያገኛት አድርገው እንዲቀብሯት ላቲሲያ ለሚገኙት ገዳዬቹ ትዕዛዝ የስተላለፈው፡፡
ኮለምቢያ
/ላቲሲ(አማዞን ወንዝን ታካ የተመሰረተች በአሳ ምርቶ የምትጣወቅ ከተማ) ካርሎስ ከገዳይ አጋሮቹ ፈንጠር ብሎ አንድ ግዙፍ ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ በማስታወሻ ደብተሩ ላይ የቀን ውሎውንና ገጠመኞቹን በምጥን ቃላት እያሰፈረ ሳለ በቡድኑ ሀለቃ ተጠራ፡፡ማስተወሻ ደብተሩን አጣጥፎ ጎኑ ያለው የጉዞ ቦርሳው ውስጥ ከተተና መሳሪያውን በአንድ ተከሻው አንጠልጥሎ ቦርሳውን በእጁ ይዞ ወደተጠራበት ቦታ ሄደ፡፡
ቀጥታ ‹‹ግባና ግደላት፡፡››የሚል ትዕዛዝ ነበር የሰጠው፡፡
‹‹ምን ?››ካርሎስ ሀላቀውን በድንጋጤ ጠየቀ፡፡
‹‹ትልቁ ሀለቃችን ትገደል ብሏል…ግባና ግደላት፡፡››ኮስተር ብሎ በድጋሚ ትዕዛዙን አስተላለፈ፡፡
‹‹እርግጠኛ ናችሁ ትገደል ብሏል?››
‹‹ሰውዬ ያምሀል እንዴ? እኔ የተሳሳተ ትዕዛዝ ሳስተላልፈ አይተሀኝ ታቃለህ..?ነው ወይስ ፈራህ?ከፈራህ ግድ የለም ሌላ ሰው በደስታ ያድርገዋል፡፡እኔ እኮ ስለምትወዳት በፍቅር እንድትገድላት እድሉን ልስጥህ ብዬ ነው እንጂ ሌሎች በደስታ የሚፈፅሙት ትዕዛዝ መሆኑን አጥቼው አይደለም …ምንም ቢሆን እሷን እዚህ ድረስ በማጓጓዙ ከአንተ እኩል የለፋ የለም፡፡››
👍61❤7😢6