<<የሠው ፍላጎት እንዴት ነው የተዘበራረቀው? ይህቺን የመሠለች ውብና አፍቃሪ ሴት ገፍቶ እንዴት የማያውቃትን ሴት አፍቅሬያለሁ ብሎ ይሄን ያህል ይሠቃያል?እዚህ አጠገቤ ያለችው ኤደን ምን ይጎላታል? መልክ አላት፣ ፀባይ አላት፣ ብር አላት ... ከዚህ በላይ ምን ማሟላት ይጠበቅባታል?››ከወራት በፊት ስለዚህ ጉዳይ ሁሴንን ጠይቆት የመለሠለት መልስ ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡
‹‹ወረት ነው አይደል እንዲህ የሚያንቀዠቅዠህ? አጠገብህ በጣም የሚያፈቅሩህ ሴቶች እያሉልህ አንተ ሌላ የማታውቃትን አየር የሆነች ልጅ ፍለጋ ምትሠቃየው?›› የሚል ጥያቄ ነበር ያቀረበለት፡፡
‹‹ትክክለኛ ሄዋኔን ፍለጋ ላይ ነኝ፡፡›› ብሎ መለሠለት፡፡
‹‹ታዲያ እነሱስ ሄዋንህ መሆን አይችሉም?››
‹‹አይመስለኝም፡፡ አየህ የሠው ልጅ አፈጣጠርን መለስ ብለን ስንመለከት
እግዚአብሔር መልኩን ወይም መሠሉን ማየት
ፈለገና ጭቃ አድቦልቡሎ እስትንፋሱን እፍ አለበትና አዳምን ፈጠረው፡፡ ልብ በልልኝ ለአዳም መፈጠር ዋናው ምክንያት እግዚአብሔር በአዳም ውስጥ የራሱን መልክ
ለማየት ስለፈለገ ነበር፡፡በሌላ አነጋገር አዳም
የእግዚያብሄር መስታወት ነው ማለት ትችላለህ፡፡ ቆየት አለና አዳም ደበረው፤ በብቸኝነቱ አጉረመረመ፤
እግዚአብሔርም ሠማው፤ እንቅልፍ ጣለበትና ከግራ ጎኑ አንድ አጥንት መዘዘና ሄዋንን አበረከተለት፡፡ የሄዋን የመፈጠር ምክንያት ደግሞ ምንድነው ?ብትለኝ የአዳም ድብርት ውስጥ መግባት ነው፡፡ አዳም ባይደብረው
እግዚአብሔር ሄዋንን ለመፍጠር ሀሳብ አይመጣለትም ነበር፡፡ወደ ነጥቤ ልመልስህና
በእያንዳንዱ አዳም የግራ ጎን ከእኔ እና ከአንተም ጭምር እግዚአብሔር አንድ አንድ አጥንት ወስዶ አንድ አንድ ሴት ፈጥሮልናል፡፡
ፍቅር የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ
?ያለ ፍቃድህ ከግራ ጎንህ በእግዚአብሔር የተወሠደብህን የራስህን አጥንት ለማስመለስ
የምታደርገው ውጣ ውረድ ነው፡፡ ታዲያ ብዙውን ጊዜ ፍቅር እንከን የተሞላ የሚሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ?ክህደት፣ ውስልትና፣ፍቺ የመሳሰሉት ለምን እንደሚከሰቱስ
ይገባሀል? አንዷን በአጋጣሚ ትቀርባታለህ፤ ይህቺ ከእራሴው አጥንት
የተሠራች ነች ብለህ ትወስናለህ ፡፡አፈቀርኩሽ
ትላታለህ…ታገባታለህ፡፡ አሁን ሙሉ ሠው ነኝ፤
ሙሉ አካልም አለኝ የተወሠደብኝን የግራ ጎኔን
መልሻለሁ ብለህ ትኩራራለህ፡፡ ጥቂት ቆይቶ
ግን ያ አጥንት ካንተ ጎን የተወሠደ ሳይሆን ከሌላ አዳም ጎን የተወሠደ ሆኖ ይገኛል፡፡ ያ ማለት አጥንቱ አንተ ላይ በትክክል ገብቶ
አይገጥምም ማለት ነው፡፡ ወይ ይሠፋል አሊያም ይጠባል፤ወይ ያጥራል ወይ ደግሞ ይረዝምብሀል፡፡ ያ ደግሞ ምቾትህን ይነሳሀል፡፡ በሽተኛ ያደርግሀል፣ ይቆረቁርሀል፣ይጎረብጥሀል፤ በመጨረሻ ስቃዩ ሲበዛብህ ያ ቦታ እንደድሮ ባዶ ቢሆን ይሻለኛል ብለህ ትወስናለህ፡፡ አውጥተህ አሽቀንጥረህ ትጥለዋለህ ሌላ ያንተኑ ትክክለኛ ግጣምህን ፍለጋ ዳግመኛ አንድ ብለህ መኳተን ትጀምራለህ፡፡….እና
ማጠቃለያዬ ምን መሠለህ ፤የራሴውን አጥንት እንዳገኘሁ እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ተረጋግቼ መቀመጥ አልፈልግም፡፡ ካለበለዚያ ያ ያንተ ዕጣ ነው የሚደርሠኝ፡፡›› በማለት ነበር ያስረዳው፡፡ በትውስታው ፈገግ ብሎ ወደ ሌላ ትካዜ ሊሸጋገር ሲል የኤደን ጥያቄ መለሠው፡፡
‹‹ልጆችህ ደህና ናቸው?››
‹‹ደህና ናቸው፤ እግዜር ይመስገን፡፡››
‹‹የውብዳርስ?››
‹‹እኔ እንጃላት፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃላት ... ?ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ? ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሟን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ከአፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም? ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው>>
‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፤ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናስተዳድርለት ነው፤ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡›› ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡...
✨ይቀጥላል✨
#ድርሰቱ ለምንድን ነው ቶሎ ቶሎ የማይለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ይመጣሉ ጥሩ ጥያቄ ነው ቶሎ ቶሎ መለቀቅም አለበት ነገር ግን ይሄን ጥያቄ ከምጠይቁት መሀል ምን ያህሎቻቹ #የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ አድርጋችኋል ሁሉም ሰው #ሰብስክራይብ ያድርግ አደለም ነገር ግን ድርሰቱን ከሚያነበው መሀል Post ሲደረግ ቢያንስ አምስት ሰው እንዴት ይጠፋል ከ 100000 ምናምን ሺ ሰው መሀል ማለት ነው እስቲ አሁንም በቅንነት እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ እኛም ሞራል አግኝተን ቶሎ ቶሎ እንልቀቅ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ወረት ነው አይደል እንዲህ የሚያንቀዠቅዠህ? አጠገብህ በጣም የሚያፈቅሩህ ሴቶች እያሉልህ አንተ ሌላ የማታውቃትን አየር የሆነች ልጅ ፍለጋ ምትሠቃየው?›› የሚል ጥያቄ ነበር ያቀረበለት፡፡
‹‹ትክክለኛ ሄዋኔን ፍለጋ ላይ ነኝ፡፡›› ብሎ መለሠለት፡፡
‹‹ታዲያ እነሱስ ሄዋንህ መሆን አይችሉም?››
‹‹አይመስለኝም፡፡ አየህ የሠው ልጅ አፈጣጠርን መለስ ብለን ስንመለከት
እግዚአብሔር መልኩን ወይም መሠሉን ማየት
ፈለገና ጭቃ አድቦልቡሎ እስትንፋሱን እፍ አለበትና አዳምን ፈጠረው፡፡ ልብ በልልኝ ለአዳም መፈጠር ዋናው ምክንያት እግዚአብሔር በአዳም ውስጥ የራሱን መልክ
ለማየት ስለፈለገ ነበር፡፡በሌላ አነጋገር አዳም
የእግዚያብሄር መስታወት ነው ማለት ትችላለህ፡፡ ቆየት አለና አዳም ደበረው፤ በብቸኝነቱ አጉረመረመ፤
እግዚአብሔርም ሠማው፤ እንቅልፍ ጣለበትና ከግራ ጎኑ አንድ አጥንት መዘዘና ሄዋንን አበረከተለት፡፡ የሄዋን የመፈጠር ምክንያት ደግሞ ምንድነው ?ብትለኝ የአዳም ድብርት ውስጥ መግባት ነው፡፡ አዳም ባይደብረው
እግዚአብሔር ሄዋንን ለመፍጠር ሀሳብ አይመጣለትም ነበር፡፡ወደ ነጥቤ ልመልስህና
በእያንዳንዱ አዳም የግራ ጎን ከእኔ እና ከአንተም ጭምር እግዚአብሔር አንድ አንድ አጥንት ወስዶ አንድ አንድ ሴት ፈጥሮልናል፡፡
ፍቅር የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ
?ያለ ፍቃድህ ከግራ ጎንህ በእግዚአብሔር የተወሠደብህን የራስህን አጥንት ለማስመለስ
የምታደርገው ውጣ ውረድ ነው፡፡ ታዲያ ብዙውን ጊዜ ፍቅር እንከን የተሞላ የሚሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ?ክህደት፣ ውስልትና፣ፍቺ የመሳሰሉት ለምን እንደሚከሰቱስ
ይገባሀል? አንዷን በአጋጣሚ ትቀርባታለህ፤ ይህቺ ከእራሴው አጥንት
የተሠራች ነች ብለህ ትወስናለህ ፡፡አፈቀርኩሽ
ትላታለህ…ታገባታለህ፡፡ አሁን ሙሉ ሠው ነኝ፤
ሙሉ አካልም አለኝ የተወሠደብኝን የግራ ጎኔን
መልሻለሁ ብለህ ትኩራራለህ፡፡ ጥቂት ቆይቶ
ግን ያ አጥንት ካንተ ጎን የተወሠደ ሳይሆን ከሌላ አዳም ጎን የተወሠደ ሆኖ ይገኛል፡፡ ያ ማለት አጥንቱ አንተ ላይ በትክክል ገብቶ
አይገጥምም ማለት ነው፡፡ ወይ ይሠፋል አሊያም ይጠባል፤ወይ ያጥራል ወይ ደግሞ ይረዝምብሀል፡፡ ያ ደግሞ ምቾትህን ይነሳሀል፡፡ በሽተኛ ያደርግሀል፣ ይቆረቁርሀል፣ይጎረብጥሀል፤ በመጨረሻ ስቃዩ ሲበዛብህ ያ ቦታ እንደድሮ ባዶ ቢሆን ይሻለኛል ብለህ ትወስናለህ፡፡ አውጥተህ አሽቀንጥረህ ትጥለዋለህ ሌላ ያንተኑ ትክክለኛ ግጣምህን ፍለጋ ዳግመኛ አንድ ብለህ መኳተን ትጀምራለህ፡፡….እና
ማጠቃለያዬ ምን መሠለህ ፤የራሴውን አጥንት እንዳገኘሁ እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ተረጋግቼ መቀመጥ አልፈልግም፡፡ ካለበለዚያ ያ ያንተ ዕጣ ነው የሚደርሠኝ፡፡›› በማለት ነበር ያስረዳው፡፡ በትውስታው ፈገግ ብሎ ወደ ሌላ ትካዜ ሊሸጋገር ሲል የኤደን ጥያቄ መለሠው፡፡
‹‹ልጆችህ ደህና ናቸው?››
‹‹ደህና ናቸው፤ እግዜር ይመስገን፡፡››
‹‹የውብዳርስ?››
‹‹እኔ እንጃላት፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃላት ... ?ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ? ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሟን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ከአፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም? ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው>>
‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፤ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናስተዳድርለት ነው፤ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡›› ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡...
✨ይቀጥላል✨
#ድርሰቱ ለምንድን ነው ቶሎ ቶሎ የማይለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ይመጣሉ ጥሩ ጥያቄ ነው ቶሎ ቶሎ መለቀቅም አለበት ነገር ግን ይሄን ጥያቄ ከምጠይቁት መሀል ምን ያህሎቻቹ #የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ አድርጋችኋል ሁሉም ሰው #ሰብስክራይብ ያድርግ አደለም ነገር ግን ድርሰቱን ከሚያነበው መሀል Post ሲደረግ ቢያንስ አምስት ሰው እንዴት ይጠፋል ከ 100000 ምናምን ሺ ሰው መሀል ማለት ነው እስቲ አሁንም በቅንነት እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ እኛም ሞራል አግኝተን ቶሎ ቶሎ እንልቀቅ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍113❤13👎5👏1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹዋቤ
የውብዳርስ?››
‹‹እኔ እንጃላት፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃላት ... ?ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ? ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሟን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ከአፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም? ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው>>
‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፤ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናስተዳድርለት ነው፤ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡›› ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡...
‹‹ግን እውነት ደህና ነች?›› ጠየቀችው
‹‹እኔም እውነቴን እኮ ነው ..አላውቅም፡፡››
‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹ተፋተናል፡፡››
‹‹ምን?›› በድንጋጤ አፏን በእጇ ሸፍና ከመቀመጫዋ ተነሳችና መልሳ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አዋ አራት ወር አለፈን፡፡››
‹‹እንዴት ሳልሰማ? ምን አለበት ደውለህ እንኳ ብትነግረኝ?››
‹‹ምን የሚነገር ነገር አለው? ለሰርጉም ጠርቼሽ ለፍቺውም ጠርቼሽ እችላለሁ... ? ድግስና ጥሪ ለጋብቻ ብቻ ነው ብዬ ነው፡፡››
‹‹ለምን የለውም? የዛሬን አያድርገውና ስንት ጥሩና መጥፎውን ነገር አብረን አሳልፈናል እኮ …ቆይ እናንተን ሀይ የሚላችሁ ሠውም የለ እንዴ? ዳሩ ከእብድ ጋር የሚውል ምን ጤና ይኖረዋል?ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር...> እንደሚባለው ቢጤ እኮ ነው፡፡››
‹‹እንደምታስቢው እኔ ጠልቻት ወይም ሌላ አፍቅሬ እንዳይመስልሽ፡፡››
‹‹እና እንዴት ሆኖ ነው?››
‹‹ሠለቸኋት ... ድብብቆሽ ጨዋታ ውስጥ ገባች...እጅ ከፍንጅ ያዝኳት .. በቃ ይሄው ነው፡፡››
‹‹እኔ አላምንም ... የውብዳር ከሌላ ወንድ ጋር... ምቀኛ በመሀከላችሁ ገብቶ እንዳይሆን?››
‹‹አመንሽም አላመንሽም በወሬ ወይ በጥርጣሬ እንዳይመስልሽ፤እራሷም ባመነችበት አሳማኝ ማስረጃ ነው፡፡››
‹‹ወይ ጉድ!›› አለች ኤደን ግራ ገብቷት፡፡
ሠሎሞን ብርጭቆውን አነሳና ውስጥ ያለውን ጅው አድርጎ በመጨለጥ ጠርሙሱ ውስጥ የነበረውን ለሁለቱም ቀድቶ ሌላ እንዲጨምርላቸው ለአስተናጋጁ በምልክት ትዕዛዝ በማስተላለፍ ንግግሩን ቀጠለ፡፡ ‹‹አየሽ ኤደን ምን አልባት አንቺ ነገሮችን ከራስሽ አንፃር ስትገመግሚያቸው በወንድ በደል ደርሶብኛል ወይም ተገፍቼያለሁ ብለሽ ስለምታስቢ ጠቅላላ ወንዶች ላይ ያለሽ ግንዛቤ አሉታዊ ጎኑ ስለሚያመዝን ወንዶች ሁሉ በዳይ ሴቶች ደግሞ ተበዳይ ሆነው ሊታዩሽ ይችላሉ፡፡ ሀቁ ግን እንደዛ አይደለም ስንት መሠሪና አለሌ ሴቶችም አሉ ፡፡ እና ምን መሠለሽ ...››ንግግሩን የስልኩ መጮህ አቋረጠው፡፡ ከኪሱ አወጣና ደዋዩ ማን እንደሆነ አየው፡፡ ሁሴን ነበር፡፡ አነሳው፡፡
‹‹እሺ ጌታው፡፡››
<አለሁ ባክህ ... ሰርጉ እንዴት ነበር?>>ሁሴን
‹‹አሪፍ ነው፡፡ አሁን ወጥቼያለሁ፡፡ ፍንድቅድቅ ያልክ ትመስላለህ ደግሞ ምን አገኘህ?››
<ደወለች እባክህ::››
<<ማን?>>
ሁሴን ተበሳጨ ‹‹ማን ትላለህ እንዴ? ማን እንድልህ ትፈልጋለህ?››
‹‹ይቅርታ እሺ ደራሲዋ?››
ኤደን ሁሴን እንደደወለ አወቀች፡፡ ሌላ ነገር የምታስብ መስላ ከወይኑ እየተጎነጨች በጽሞና ቃለ ምልልሳቸውን እያዳመጠች ነው፡፡
‹‹ትክክል ነህ፤እሷን ለማግኘት ማድረግ የሚገባኝን ነገረችኝ፡፡››
‹‹አትለኝም ምን አለችህ?››
<<አግባኝ>>
‹‹በተሠቀለው ንጉስ አግባኝ? የምሯን ነው!››
‹‹አዎ ከምሯ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ ምን ችግር አለው እሺ በላታ፤ከዛም አግኛትና ካልተመቸችህ ቃልህን ታጥፋለህ፤ቃል ማጠፍ እንደሆነ ላንተ የሚከብድ አይመስለኝም››
የኤደን ስሜት ይበልጥ እየተነቃቃ ውስጧ በቁጣና በቅናት እየነደደ መጣ፡፡ ትቼዋለሁ ወጥቶልኛል ብላ ከሁሴን አጠገብ ከራቀችና እሱን ማግኘት ከተወች ስድስት ወር ቢያልፋትም ውስጧ ግን ዛሬም ይራበዋል፡፡ መሸነፍ ልቧን ያቆስለዋል፡፡
ንግግራቸው ቀጥሏል፡-‹‹ባክህ የዋዛ እንዳትመስልህ የእውነት ከወደድከኝ ቆማጣም ሆንኩ ሸፋፋ የማትተወኝ ከሆነ እና ልታገባኝ ከወሠንክ በመጀመሪያ ሠርግ ደግስ ለምታውቃቸው ሠዎች ሁሉ የሠርግ ጥሪ በትን ከዛ በሠርጉ ቀን ሽማግሌዎችህን ሚዜዎችህንና አጃቢዎችህን አዘጋጅ ልክ
በሠዓቱ እደውልልሀለሁ ያለሁበት ትመጣና ይዘኸኝ ትሄዳለህ፡፡››አለችኝ፡፡
‹‹እንዲህ ነችና ... ልጅቷ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ፊልም እየሠራች ነው እንዴ ...? እኔ ይሄንን ጉዳይ ከዚህ በላይ በስልክ ማውራት አልፈልግም ነገ ጥዋት እቢሮ እመጣለሁ፤ ታወራኛለህ፡፡››
እጠብቅካለው....ለማኝማውም ሚዜ ለመሆን ተዘጋጅ፡፡››
‹‹እሱን እናያለን .. ለማንኛውም አሁን ከኤደን ጋር ነኝ፡፡ሰርግ ቤት ተገናኘን፡፡ ሠላም እያለችህ ነው፡፡››
ኤደን በተቃውሞ ፊቷን አኮሳተረች፡፡
‹‹ተመችቶኃላ .. ላናግራት›› አለ ሁሴን ሠሎሞን ሞባይሉን ዘረጋላት .. ፍቃደኛ አልሆነችም፡፡ ‹‹በል ቻው፡፡ በአየር ላይ ሠላም ብላሀለች፡፡›› በማለት ስልኩን ዘጋው፡፡
‹‹በቃ አሁንም ስለዛች ደራሲ የቀን ህልም እያለመ ነው?››
‹‹ባክሽ እኔም ግራ ገብቶኛል፡፡››
‹‹እኔ እኮ የሚገርመኝ ቆይ ማን ትሆን እንዲህ የምትጫወትበት?››
‹‹እሱ አይደል እንቆቅልሹ፡፡ አሁን እኮ የሚለኝ ልታየኝ ከፈለክ ድግስ ደግስና አግባኝ አለችኝ ነው >>
‹‹በቃ በቃ እኔ እንዲህ አይነት ቅራቅንቦ መስማት አልፈልግም፡፡ እንደውም መጠጣት ሁሉን መርሳት እፈልጋለሁ፤ ሞቅ ያለ ቤት ውሠደኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹ኧረ እስማማለሁ፡፡›› በማለት ሂሳቡን ከፍሎ ቀጫጭን የእጆቿን ጣቶች በፈርጣማው ጣቶቹ አቆላልፎ በመያዝ ወደ ጭፈራ ቤት ይዟት ለመሄድ መኪናው ውስጥ ይዟት ገባ፡፡ መኪናውን ከማንቀሳቀሱ በፊት ግን የሞባይል ስልኩን ካስቀመጠበት ኪሱ አውጥቶ የጹሁፍ መልክት ለሁሴን ላከ ‹‹ኤደን ጭፈራ ቤት ውሠደኝ እያለችኝ ነው፡፡ ባንተ የተበሳጨች ይመስለኛል፡፡ ስሰክር ማስተዋሌ እንደሚቀንስ ታውቃለህ፡፡ ምን አልባት አንተን የማያስደስት ነገር በእኔና በእሷ መሀከል ይፈጠር ይሆን? ብዬ ፈራሁ፡፡ ምን ትመክረኛለህ?››መልዕክቱን ላከና የመኪናውን ሞተር አስነስቶ መንዳት ጀመረ፡፡ ወዴት እንደሚሄዱ አያውቅም፡፡ ከሁሴን መልስ እስኪመጣለት ጊዜ ለማግኘት እየጣረ ነው ፡፡ ሠዓቱ 3፡45 ሆኗል፡፡ ከዚህ ሠዓት በኋላ ለብታን ወደ ስካር ለማሸጋገር፤ ለዛውም ከሴት ጋር ጭፈራ ቤት መግባት መጨረሻውን መገመት አዳጋች ነው፡፡ ሞባይሉ ምልክት አሳየው፡፡ መኪናውን ጥግ ይዞ አቆመና የመጣለትን መልስ ከፍቶ ማንበብ ጀመረ፡፡
‹‹ቀሽም አትሁን…ምንም ቅር የሚያሰኝ ነገር የለም፡፡ ግን አደራ በቦርጭህ ሙሉ ተከምረህባት እንዳታፈነዳት፡፡ በል ይመቻችሁ፡፡ በጥዋት ቢሮ ና፡፡ ባይሆን የአልጋ መውረጃ ደህና ቁርስ ጋብዝሀለሁ፡፡››ይላል፡፡አንብቦ ሲጨርስ ፈገግ አለና መኪናውን አስነስቶ ተፈተለከ .....ወደ ጭፈራ ቤት፡፡ እሷ ግን በዝምታዋ ውስጥ እንደሰመጠች ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
የዛሬው ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ የማድረግ እንቅስቃሴ ጥሩ ነው ይልመድባችሁ👍 አሁንም እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #እያደረጋቹ ቤተሰቦች
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹዋቤ
የውብዳርስ?››
‹‹እኔ እንጃላት፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃላት ... ?ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ? ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሟን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ከአፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም? ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው>>
‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፤ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናስተዳድርለት ነው፤ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡›› ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡...
‹‹ግን እውነት ደህና ነች?›› ጠየቀችው
‹‹እኔም እውነቴን እኮ ነው ..አላውቅም፡፡››
‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹ተፋተናል፡፡››
‹‹ምን?›› በድንጋጤ አፏን በእጇ ሸፍና ከመቀመጫዋ ተነሳችና መልሳ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አዋ አራት ወር አለፈን፡፡››
‹‹እንዴት ሳልሰማ? ምን አለበት ደውለህ እንኳ ብትነግረኝ?››
‹‹ምን የሚነገር ነገር አለው? ለሰርጉም ጠርቼሽ ለፍቺውም ጠርቼሽ እችላለሁ... ? ድግስና ጥሪ ለጋብቻ ብቻ ነው ብዬ ነው፡፡››
‹‹ለምን የለውም? የዛሬን አያድርገውና ስንት ጥሩና መጥፎውን ነገር አብረን አሳልፈናል እኮ …ቆይ እናንተን ሀይ የሚላችሁ ሠውም የለ እንዴ? ዳሩ ከእብድ ጋር የሚውል ምን ጤና ይኖረዋል?ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር...> እንደሚባለው ቢጤ እኮ ነው፡፡››
‹‹እንደምታስቢው እኔ ጠልቻት ወይም ሌላ አፍቅሬ እንዳይመስልሽ፡፡››
‹‹እና እንዴት ሆኖ ነው?››
‹‹ሠለቸኋት ... ድብብቆሽ ጨዋታ ውስጥ ገባች...እጅ ከፍንጅ ያዝኳት .. በቃ ይሄው ነው፡፡››
‹‹እኔ አላምንም ... የውብዳር ከሌላ ወንድ ጋር... ምቀኛ በመሀከላችሁ ገብቶ እንዳይሆን?››
‹‹አመንሽም አላመንሽም በወሬ ወይ በጥርጣሬ እንዳይመስልሽ፤እራሷም ባመነችበት አሳማኝ ማስረጃ ነው፡፡››
‹‹ወይ ጉድ!›› አለች ኤደን ግራ ገብቷት፡፡
ሠሎሞን ብርጭቆውን አነሳና ውስጥ ያለውን ጅው አድርጎ በመጨለጥ ጠርሙሱ ውስጥ የነበረውን ለሁለቱም ቀድቶ ሌላ እንዲጨምርላቸው ለአስተናጋጁ በምልክት ትዕዛዝ በማስተላለፍ ንግግሩን ቀጠለ፡፡ ‹‹አየሽ ኤደን ምን አልባት አንቺ ነገሮችን ከራስሽ አንፃር ስትገመግሚያቸው በወንድ በደል ደርሶብኛል ወይም ተገፍቼያለሁ ብለሽ ስለምታስቢ ጠቅላላ ወንዶች ላይ ያለሽ ግንዛቤ አሉታዊ ጎኑ ስለሚያመዝን ወንዶች ሁሉ በዳይ ሴቶች ደግሞ ተበዳይ ሆነው ሊታዩሽ ይችላሉ፡፡ ሀቁ ግን እንደዛ አይደለም ስንት መሠሪና አለሌ ሴቶችም አሉ ፡፡ እና ምን መሠለሽ ...››ንግግሩን የስልኩ መጮህ አቋረጠው፡፡ ከኪሱ አወጣና ደዋዩ ማን እንደሆነ አየው፡፡ ሁሴን ነበር፡፡ አነሳው፡፡
‹‹እሺ ጌታው፡፡››
<አለሁ ባክህ ... ሰርጉ እንዴት ነበር?>>ሁሴን
‹‹አሪፍ ነው፡፡ አሁን ወጥቼያለሁ፡፡ ፍንድቅድቅ ያልክ ትመስላለህ ደግሞ ምን አገኘህ?››
<ደወለች እባክህ::››
<<ማን?>>
ሁሴን ተበሳጨ ‹‹ማን ትላለህ እንዴ? ማን እንድልህ ትፈልጋለህ?››
‹‹ይቅርታ እሺ ደራሲዋ?››
ኤደን ሁሴን እንደደወለ አወቀች፡፡ ሌላ ነገር የምታስብ መስላ ከወይኑ እየተጎነጨች በጽሞና ቃለ ምልልሳቸውን እያዳመጠች ነው፡፡
‹‹ትክክል ነህ፤እሷን ለማግኘት ማድረግ የሚገባኝን ነገረችኝ፡፡››
‹‹አትለኝም ምን አለችህ?››
<<አግባኝ>>
‹‹በተሠቀለው ንጉስ አግባኝ? የምሯን ነው!››
‹‹አዎ ከምሯ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ ምን ችግር አለው እሺ በላታ፤ከዛም አግኛትና ካልተመቸችህ ቃልህን ታጥፋለህ፤ቃል ማጠፍ እንደሆነ ላንተ የሚከብድ አይመስለኝም››
የኤደን ስሜት ይበልጥ እየተነቃቃ ውስጧ በቁጣና በቅናት እየነደደ መጣ፡፡ ትቼዋለሁ ወጥቶልኛል ብላ ከሁሴን አጠገብ ከራቀችና እሱን ማግኘት ከተወች ስድስት ወር ቢያልፋትም ውስጧ ግን ዛሬም ይራበዋል፡፡ መሸነፍ ልቧን ያቆስለዋል፡፡
ንግግራቸው ቀጥሏል፡-‹‹ባክህ የዋዛ እንዳትመስልህ የእውነት ከወደድከኝ ቆማጣም ሆንኩ ሸፋፋ የማትተወኝ ከሆነ እና ልታገባኝ ከወሠንክ በመጀመሪያ ሠርግ ደግስ ለምታውቃቸው ሠዎች ሁሉ የሠርግ ጥሪ በትን ከዛ በሠርጉ ቀን ሽማግሌዎችህን ሚዜዎችህንና አጃቢዎችህን አዘጋጅ ልክ
በሠዓቱ እደውልልሀለሁ ያለሁበት ትመጣና ይዘኸኝ ትሄዳለህ፡፡››አለችኝ፡፡
‹‹እንዲህ ነችና ... ልጅቷ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ፊልም እየሠራች ነው እንዴ ...? እኔ ይሄንን ጉዳይ ከዚህ በላይ በስልክ ማውራት አልፈልግም ነገ ጥዋት እቢሮ እመጣለሁ፤ ታወራኛለህ፡፡››
እጠብቅካለው....ለማኝማውም ሚዜ ለመሆን ተዘጋጅ፡፡››
‹‹እሱን እናያለን .. ለማንኛውም አሁን ከኤደን ጋር ነኝ፡፡ሰርግ ቤት ተገናኘን፡፡ ሠላም እያለችህ ነው፡፡››
ኤደን በተቃውሞ ፊቷን አኮሳተረች፡፡
‹‹ተመችቶኃላ .. ላናግራት›› አለ ሁሴን ሠሎሞን ሞባይሉን ዘረጋላት .. ፍቃደኛ አልሆነችም፡፡ ‹‹በል ቻው፡፡ በአየር ላይ ሠላም ብላሀለች፡፡›› በማለት ስልኩን ዘጋው፡፡
‹‹በቃ አሁንም ስለዛች ደራሲ የቀን ህልም እያለመ ነው?››
‹‹ባክሽ እኔም ግራ ገብቶኛል፡፡››
‹‹እኔ እኮ የሚገርመኝ ቆይ ማን ትሆን እንዲህ የምትጫወትበት?››
‹‹እሱ አይደል እንቆቅልሹ፡፡ አሁን እኮ የሚለኝ ልታየኝ ከፈለክ ድግስ ደግስና አግባኝ አለችኝ ነው >>
‹‹በቃ በቃ እኔ እንዲህ አይነት ቅራቅንቦ መስማት አልፈልግም፡፡ እንደውም መጠጣት ሁሉን መርሳት እፈልጋለሁ፤ ሞቅ ያለ ቤት ውሠደኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹ኧረ እስማማለሁ፡፡›› በማለት ሂሳቡን ከፍሎ ቀጫጭን የእጆቿን ጣቶች በፈርጣማው ጣቶቹ አቆላልፎ በመያዝ ወደ ጭፈራ ቤት ይዟት ለመሄድ መኪናው ውስጥ ይዟት ገባ፡፡ መኪናውን ከማንቀሳቀሱ በፊት ግን የሞባይል ስልኩን ካስቀመጠበት ኪሱ አውጥቶ የጹሁፍ መልክት ለሁሴን ላከ ‹‹ኤደን ጭፈራ ቤት ውሠደኝ እያለችኝ ነው፡፡ ባንተ የተበሳጨች ይመስለኛል፡፡ ስሰክር ማስተዋሌ እንደሚቀንስ ታውቃለህ፡፡ ምን አልባት አንተን የማያስደስት ነገር በእኔና በእሷ መሀከል ይፈጠር ይሆን? ብዬ ፈራሁ፡፡ ምን ትመክረኛለህ?››መልዕክቱን ላከና የመኪናውን ሞተር አስነስቶ መንዳት ጀመረ፡፡ ወዴት እንደሚሄዱ አያውቅም፡፡ ከሁሴን መልስ እስኪመጣለት ጊዜ ለማግኘት እየጣረ ነው ፡፡ ሠዓቱ 3፡45 ሆኗል፡፡ ከዚህ ሠዓት በኋላ ለብታን ወደ ስካር ለማሸጋገር፤ ለዛውም ከሴት ጋር ጭፈራ ቤት መግባት መጨረሻውን መገመት አዳጋች ነው፡፡ ሞባይሉ ምልክት አሳየው፡፡ መኪናውን ጥግ ይዞ አቆመና የመጣለትን መልስ ከፍቶ ማንበብ ጀመረ፡፡
‹‹ቀሽም አትሁን…ምንም ቅር የሚያሰኝ ነገር የለም፡፡ ግን አደራ በቦርጭህ ሙሉ ተከምረህባት እንዳታፈነዳት፡፡ በል ይመቻችሁ፡፡ በጥዋት ቢሮ ና፡፡ ባይሆን የአልጋ መውረጃ ደህና ቁርስ ጋብዝሀለሁ፡፡››ይላል፡፡አንብቦ ሲጨርስ ፈገግ አለና መኪናውን አስነስቶ ተፈተለከ .....ወደ ጭፈራ ቤት፡፡ እሷ ግን በዝምታዋ ውስጥ እንደሰመጠች ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
የዛሬው ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ የማድረግ እንቅስቃሴ ጥሩ ነው ይልመድባችሁ👍 አሁንም እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #እያደረጋቹ ቤተሰቦች
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍124❤13🥰2😁2