‹‹እኔ ይሄኛው ትክክለኛ፤ ያኛው ደግሞ በስህተት የተሞላ ነው ልልህ አልችልም፡፡ ሀይማኖት የምርምር ሳይሆን የእምነት ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ማስተርስህን የሠራኸው በፍልስፍና እንደመሆኑ መጠን የአብዛኞቹን ሃይማኖቶች ፍልስፍናዊ ፅንሰ ሀሳባቸውን የመመርመር ዕድሉ እንደነበረህ እገምታለሁ፤ ስለዚህ ከዛ በመነሳት አንዱን መምረጥ የሚያቅትህ አይመስለኝም፡፡››
ሁሴን ፊቱ የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ በማንሳት አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨለት በኃላ መልስ መስጠት ቀጠለ፡፡...
✨ይቀጥላል✨
እንደገና ጭቅጭቄን ልጀምር ነው እሱ ምንድነው #የዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ #አድርጉ #የሚል #ነው ለማድረግ የሚጠይቀው ውስጣዊ ቅንነትን፣ለሰዎች መልካም ማሰብን፣ደግነትን ብቻ ነው።
አሁን #ዩቲዩቡ 119 subscribers አሉት ይሄ ቻናል ከ100,000 በላይ አባላት አሉት ከነዚህ ውስጥ 10 ሰው subscribe ያደርጋል ብዬ እጠብቃለው በጣም ትንሽ ነው ማድረግ ትችላላችሁ በቅድምያ
ስለመልካምነታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ሁሴን ፊቱ የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ በማንሳት አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨለት በኃላ መልስ መስጠት ቀጠለ፡፡...
✨ይቀጥላል✨
እንደገና ጭቅጭቄን ልጀምር ነው እሱ ምንድነው #የዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ #አድርጉ #የሚል #ነው ለማድረግ የሚጠይቀው ውስጣዊ ቅንነትን፣ለሰዎች መልካም ማሰብን፣ደግነትን ብቻ ነው።
አሁን #ዩቲዩቡ 119 subscribers አሉት ይሄ ቻናል ከ100,000 በላይ አባላት አሉት ከነዚህ ውስጥ 10 ሰው subscribe ያደርጋል ብዬ እጠብቃለው በጣም ትንሽ ነው ማድረግ ትችላላችሁ በቅድምያ
ስለመልካምነታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍103❤15😁6👏1
<<የሠው ፍላጎት እንዴት ነው የተዘበራረቀው? ይህቺን የመሠለች ውብና አፍቃሪ ሴት ገፍቶ እንዴት የማያውቃትን ሴት አፍቅሬያለሁ ብሎ ይሄን ያህል ይሠቃያል?እዚህ አጠገቤ ያለችው ኤደን ምን ይጎላታል? መልክ አላት፣ ፀባይ አላት፣ ብር አላት ... ከዚህ በላይ ምን ማሟላት ይጠበቅባታል?››ከወራት በፊት ስለዚህ ጉዳይ ሁሴንን ጠይቆት የመለሠለት መልስ ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡
‹‹ወረት ነው አይደል እንዲህ የሚያንቀዠቅዠህ? አጠገብህ በጣም የሚያፈቅሩህ ሴቶች እያሉልህ አንተ ሌላ የማታውቃትን አየር የሆነች ልጅ ፍለጋ ምትሠቃየው?›› የሚል ጥያቄ ነበር ያቀረበለት፡፡
‹‹ትክክለኛ ሄዋኔን ፍለጋ ላይ ነኝ፡፡›› ብሎ መለሠለት፡፡
‹‹ታዲያ እነሱስ ሄዋንህ መሆን አይችሉም?››
‹‹አይመስለኝም፡፡ አየህ የሠው ልጅ አፈጣጠርን መለስ ብለን ስንመለከት
እግዚአብሔር መልኩን ወይም መሠሉን ማየት
ፈለገና ጭቃ አድቦልቡሎ እስትንፋሱን እፍ አለበትና አዳምን ፈጠረው፡፡ ልብ በልልኝ ለአዳም መፈጠር ዋናው ምክንያት እግዚአብሔር በአዳም ውስጥ የራሱን መልክ
ለማየት ስለፈለገ ነበር፡፡በሌላ አነጋገር አዳም
የእግዚያብሄር መስታወት ነው ማለት ትችላለህ፡፡ ቆየት አለና አዳም ደበረው፤ በብቸኝነቱ አጉረመረመ፤
እግዚአብሔርም ሠማው፤ እንቅልፍ ጣለበትና ከግራ ጎኑ አንድ አጥንት መዘዘና ሄዋንን አበረከተለት፡፡ የሄዋን የመፈጠር ምክንያት ደግሞ ምንድነው ?ብትለኝ የአዳም ድብርት ውስጥ መግባት ነው፡፡ አዳም ባይደብረው
እግዚአብሔር ሄዋንን ለመፍጠር ሀሳብ አይመጣለትም ነበር፡፡ወደ ነጥቤ ልመልስህና
በእያንዳንዱ አዳም የግራ ጎን ከእኔ እና ከአንተም ጭምር እግዚአብሔር አንድ አንድ አጥንት ወስዶ አንድ አንድ ሴት ፈጥሮልናል፡፡
ፍቅር የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ
?ያለ ፍቃድህ ከግራ ጎንህ በእግዚአብሔር የተወሠደብህን የራስህን አጥንት ለማስመለስ
የምታደርገው ውጣ ውረድ ነው፡፡ ታዲያ ብዙውን ጊዜ ፍቅር እንከን የተሞላ የሚሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ?ክህደት፣ ውስልትና፣ፍቺ የመሳሰሉት ለምን እንደሚከሰቱስ
ይገባሀል? አንዷን በአጋጣሚ ትቀርባታለህ፤ ይህቺ ከእራሴው አጥንት
የተሠራች ነች ብለህ ትወስናለህ ፡፡አፈቀርኩሽ
ትላታለህ…ታገባታለህ፡፡ አሁን ሙሉ ሠው ነኝ፤
ሙሉ አካልም አለኝ የተወሠደብኝን የግራ ጎኔን
መልሻለሁ ብለህ ትኩራራለህ፡፡ ጥቂት ቆይቶ
ግን ያ አጥንት ካንተ ጎን የተወሠደ ሳይሆን ከሌላ አዳም ጎን የተወሠደ ሆኖ ይገኛል፡፡ ያ ማለት አጥንቱ አንተ ላይ በትክክል ገብቶ
አይገጥምም ማለት ነው፡፡ ወይ ይሠፋል አሊያም ይጠባል፤ወይ ያጥራል ወይ ደግሞ ይረዝምብሀል፡፡ ያ ደግሞ ምቾትህን ይነሳሀል፡፡ በሽተኛ ያደርግሀል፣ ይቆረቁርሀል፣ይጎረብጥሀል፤ በመጨረሻ ስቃዩ ሲበዛብህ ያ ቦታ እንደድሮ ባዶ ቢሆን ይሻለኛል ብለህ ትወስናለህ፡፡ አውጥተህ አሽቀንጥረህ ትጥለዋለህ ሌላ ያንተኑ ትክክለኛ ግጣምህን ፍለጋ ዳግመኛ አንድ ብለህ መኳተን ትጀምራለህ፡፡….እና
ማጠቃለያዬ ምን መሠለህ ፤የራሴውን አጥንት እንዳገኘሁ እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ተረጋግቼ መቀመጥ አልፈልግም፡፡ ካለበለዚያ ያ ያንተ ዕጣ ነው የሚደርሠኝ፡፡›› በማለት ነበር ያስረዳው፡፡ በትውስታው ፈገግ ብሎ ወደ ሌላ ትካዜ ሊሸጋገር ሲል የኤደን ጥያቄ መለሠው፡፡
‹‹ልጆችህ ደህና ናቸው?››
‹‹ደህና ናቸው፤ እግዜር ይመስገን፡፡››
‹‹የውብዳርስ?››
‹‹እኔ እንጃላት፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃላት ... ?ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ? ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሟን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ከአፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም? ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው>>
‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፤ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናስተዳድርለት ነው፤ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡›› ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡...
✨ይቀጥላል✨
#ድርሰቱ ለምንድን ነው ቶሎ ቶሎ የማይለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ይመጣሉ ጥሩ ጥያቄ ነው ቶሎ ቶሎ መለቀቅም አለበት ነገር ግን ይሄን ጥያቄ ከምጠይቁት መሀል ምን ያህሎቻቹ #የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ አድርጋችኋል ሁሉም ሰው #ሰብስክራይብ ያድርግ አደለም ነገር ግን ድርሰቱን ከሚያነበው መሀል Post ሲደረግ ቢያንስ አምስት ሰው እንዴት ይጠፋል ከ 100000 ምናምን ሺ ሰው መሀል ማለት ነው እስቲ አሁንም በቅንነት እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ እኛም ሞራል አግኝተን ቶሎ ቶሎ እንልቀቅ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ወረት ነው አይደል እንዲህ የሚያንቀዠቅዠህ? አጠገብህ በጣም የሚያፈቅሩህ ሴቶች እያሉልህ አንተ ሌላ የማታውቃትን አየር የሆነች ልጅ ፍለጋ ምትሠቃየው?›› የሚል ጥያቄ ነበር ያቀረበለት፡፡
‹‹ትክክለኛ ሄዋኔን ፍለጋ ላይ ነኝ፡፡›› ብሎ መለሠለት፡፡
‹‹ታዲያ እነሱስ ሄዋንህ መሆን አይችሉም?››
‹‹አይመስለኝም፡፡ አየህ የሠው ልጅ አፈጣጠርን መለስ ብለን ስንመለከት
እግዚአብሔር መልኩን ወይም መሠሉን ማየት
ፈለገና ጭቃ አድቦልቡሎ እስትንፋሱን እፍ አለበትና አዳምን ፈጠረው፡፡ ልብ በልልኝ ለአዳም መፈጠር ዋናው ምክንያት እግዚአብሔር በአዳም ውስጥ የራሱን መልክ
ለማየት ስለፈለገ ነበር፡፡በሌላ አነጋገር አዳም
የእግዚያብሄር መስታወት ነው ማለት ትችላለህ፡፡ ቆየት አለና አዳም ደበረው፤ በብቸኝነቱ አጉረመረመ፤
እግዚአብሔርም ሠማው፤ እንቅልፍ ጣለበትና ከግራ ጎኑ አንድ አጥንት መዘዘና ሄዋንን አበረከተለት፡፡ የሄዋን የመፈጠር ምክንያት ደግሞ ምንድነው ?ብትለኝ የአዳም ድብርት ውስጥ መግባት ነው፡፡ አዳም ባይደብረው
እግዚአብሔር ሄዋንን ለመፍጠር ሀሳብ አይመጣለትም ነበር፡፡ወደ ነጥቤ ልመልስህና
በእያንዳንዱ አዳም የግራ ጎን ከእኔ እና ከአንተም ጭምር እግዚአብሔር አንድ አንድ አጥንት ወስዶ አንድ አንድ ሴት ፈጥሮልናል፡፡
ፍቅር የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ
?ያለ ፍቃድህ ከግራ ጎንህ በእግዚአብሔር የተወሠደብህን የራስህን አጥንት ለማስመለስ
የምታደርገው ውጣ ውረድ ነው፡፡ ታዲያ ብዙውን ጊዜ ፍቅር እንከን የተሞላ የሚሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃለህ?ክህደት፣ ውስልትና፣ፍቺ የመሳሰሉት ለምን እንደሚከሰቱስ
ይገባሀል? አንዷን በአጋጣሚ ትቀርባታለህ፤ ይህቺ ከእራሴው አጥንት
የተሠራች ነች ብለህ ትወስናለህ ፡፡አፈቀርኩሽ
ትላታለህ…ታገባታለህ፡፡ አሁን ሙሉ ሠው ነኝ፤
ሙሉ አካልም አለኝ የተወሠደብኝን የግራ ጎኔን
መልሻለሁ ብለህ ትኩራራለህ፡፡ ጥቂት ቆይቶ
ግን ያ አጥንት ካንተ ጎን የተወሠደ ሳይሆን ከሌላ አዳም ጎን የተወሠደ ሆኖ ይገኛል፡፡ ያ ማለት አጥንቱ አንተ ላይ በትክክል ገብቶ
አይገጥምም ማለት ነው፡፡ ወይ ይሠፋል አሊያም ይጠባል፤ወይ ያጥራል ወይ ደግሞ ይረዝምብሀል፡፡ ያ ደግሞ ምቾትህን ይነሳሀል፡፡ በሽተኛ ያደርግሀል፣ ይቆረቁርሀል፣ይጎረብጥሀል፤ በመጨረሻ ስቃዩ ሲበዛብህ ያ ቦታ እንደድሮ ባዶ ቢሆን ይሻለኛል ብለህ ትወስናለህ፡፡ አውጥተህ አሽቀንጥረህ ትጥለዋለህ ሌላ ያንተኑ ትክክለኛ ግጣምህን ፍለጋ ዳግመኛ አንድ ብለህ መኳተን ትጀምራለህ፡፡….እና
ማጠቃለያዬ ምን መሠለህ ፤የራሴውን አጥንት እንዳገኘሁ እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ተረጋግቼ መቀመጥ አልፈልግም፡፡ ካለበለዚያ ያ ያንተ ዕጣ ነው የሚደርሠኝ፡፡›› በማለት ነበር ያስረዳው፡፡ በትውስታው ፈገግ ብሎ ወደ ሌላ ትካዜ ሊሸጋገር ሲል የኤደን ጥያቄ መለሠው፡፡
‹‹ልጆችህ ደህና ናቸው?››
‹‹ደህና ናቸው፤ እግዜር ይመስገን፡፡››
‹‹የውብዳርስ?››
‹‹እኔ እንጃላት፡፡››
‹‹እንዴት እኔ እንጃላት ... ?ወንዶች ስትባሉ በቃ ሁላችሁም አንድ አይነት ናችሁ? ሴትን ልጅ ቀምሳችሁ... ልሳችሁ ጣዕሟን ከጨረሳችሁ በኋላ ተፍታችሁ ከአፈር ስትደባልቁ ጥቂት እንኳን ፀፀት አይሠማችሁም? ግርም የሚለኝ እግኢአብሔር ለምን እናንተን እንደፈጠራችሁ ነው>>
‹‹የፈጠረንማ አንደኛ አቶ ሁሴን እንደሚለው መልኩን በእኛ በኩል ለማየት ነው፤ምክንያቱም እኛ እሱን እንመስላለን፡፡ ሁለተኛው ምድርን እንድናስተዳድርለት ነው፤ሦስተኛው እንድናመሰግነው ይመስለኛል፡፡ እንደ እኔ ሦስተኛው ብዙም የተሳካ አይመስለኝም፡፡ እናንተን ከፈጠረ በኋላ አይናችንን ወደ ፈጣሪ እንዳናነሳ እንቅፋት እንደሆናችሁን ነው የምረዳው፡፡›› ሁለቱም ምግቡን ስላቆሙ አስተናጋጅ መጥቶ መአዱን አነሳና ጠረጴዛውን አፀዳዳው፡፡...
✨ይቀጥላል✨
#ድርሰቱ ለምንድን ነው ቶሎ ቶሎ የማይለቀቀው የሚሉ ጥያቄዎች ይመጣሉ ጥሩ ጥያቄ ነው ቶሎ ቶሎ መለቀቅም አለበት ነገር ግን ይሄን ጥያቄ ከምጠይቁት መሀል ምን ያህሎቻቹ #የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ አድርጋችኋል ሁሉም ሰው #ሰብስክራይብ ያድርግ አደለም ነገር ግን ድርሰቱን ከሚያነበው መሀል Post ሲደረግ ቢያንስ አምስት ሰው እንዴት ይጠፋል ከ 100000 ምናምን ሺ ሰው መሀል ማለት ነው እስቲ አሁንም በቅንነት እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ እኛም ሞራል አግኝተን ቶሎ ቶሎ እንልቀቅ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍113❤13👎5👏1
‹‹ምን ችግር አለው፡፡ አንድ ከተማዋን የሚያውቃት ጓደኛ ፈልጋ፡፡ አየህ ይሄንን የመሠለ አጓጊ ጨዋታ በአዲስ አበባ ግርግር ውስጥ መጫወት አልፈልግም፡፡በደብረዘይት ፀጥታና ውበት እየተደመምኩ ቢሆን እመርጣለሁ፡፡››
‹‹እሺ ይሁን ለጊዜው ከጓደኞቼ መሀከል ከተማዋን ማን እንደሚያውቃት ትዝ አይለኝም፡፡ ካልሆነ አንድ ሰው እቀጥራለሁ፡፡››
‹‹የግድ እኮ ወንድ ጓደኛህ መሆን የለበትም፤ሴትም ጓደኛህ ልትሆን ትችላለች...የመጨረሻ አንድ ማሳሰቢያ ሞባይል ስልኬን በመከታተል ጊዜ እዳታጠፋ...የተመዘገበው በእኔ ስም ሳይሆን እኔም በማላውቀው በሌላ ሰው ስም ነው፡፡አረብ አገር በሄደ ሰው ስም፡፡ለማንኛውም ቻው፡፡ ዝርዝር ህጎችን ቀኑን ስትወስን እንነጋገራለን፡፡ >> ሰልኩ ተዘጋ፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ ቤተሰቦች ዛሬም አንድ 10 ሰው እጠብቃለው👍 አሁንም እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ ያሰብነው ከሞላ ነገ እንገናኝ ይሆናል።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹እሺ ይሁን ለጊዜው ከጓደኞቼ መሀከል ከተማዋን ማን እንደሚያውቃት ትዝ አይለኝም፡፡ ካልሆነ አንድ ሰው እቀጥራለሁ፡፡››
‹‹የግድ እኮ ወንድ ጓደኛህ መሆን የለበትም፤ሴትም ጓደኛህ ልትሆን ትችላለች...የመጨረሻ አንድ ማሳሰቢያ ሞባይል ስልኬን በመከታተል ጊዜ እዳታጠፋ...የተመዘገበው በእኔ ስም ሳይሆን እኔም በማላውቀው በሌላ ሰው ስም ነው፡፡አረብ አገር በሄደ ሰው ስም፡፡ለማንኛውም ቻው፡፡ ዝርዝር ህጎችን ቀኑን ስትወስን እንነጋገራለን፡፡ >> ሰልኩ ተዘጋ፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ ቤተሰቦች ዛሬም አንድ 10 ሰው እጠብቃለው👍 አሁንም እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ ያሰብነው ከሞላ ነገ እንገናኝ ይሆናል።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍56😁7🔥3
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹በጊዜ ነበር እኮ መምጣት የፈለኩት ለሆነች ጉዳይ ከአንድ መስሪያ ቤት ወደ ሌላው ስሯሯጥ መሸብኝ›› ሠሎሞን ነው፡፡
‹‹ምንም አይደል ዋናው መምጣትህ ነው›› ፎዚያ መለሠችለት ከፍሪጅ ያወጣችውን ቀዝቃዛ ቢራ ከፍታ ፊት ለፊቱ እያስቀመጠች፡፡
‹‹ወድጄ መሠለሽ ፤ ያ እብድ ሳታያት እንዳታድር ብሎ ስላስገደደኝ ነው የመጣሁት፡፡››
‹‹ሁሴን እያት ባይልህ አትመጣም ነበር ማለት ነው?›› አለችው ትንሽ እንደማኩረፍ ብላ፡፡
‹‹አይደለም፤ እንዲሁ ነገፀሩን አልኩ እንጂ መምጣቱንማ እኔም እፈልገው ነበር ምነው ቆመሽ ቀረሽ አንቺም ያዥና ቁጭ በያ ::
ፍሪጁን ከፍታ ሚሪንዳ አውጥታ ከፍታ ፊት ለፊቱ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አይ ይሄማ አይሆንም.ቢራ ከሌለ ወጣ ብዬ ገዝቼ እመጣለሁ ካለበለዚያ ግን እኔን አልኮል እየጋትሽ አንቺ ለስላሳ እንዳትከፍቺ››
‹‹እንዴ! አረ እኔ አልጠጣም ።.››
‹‹ይቅርታ እንደዛ ፓጋን መስለሺኝ ነው፡፡
‹‹እዚህ ጋር ወራጅ አለ…እኔ ፊት እሱን መተቸት ክልክል ነው፡፡.››
‹‹ተቀብያለሁ...ለመሆኑ ዛሬ ደውሎልሻል?››
‹‹አልደወለልኝም ትናንት ነው የደወለልኝ ፣እንደውልለት እንዴ?››
‹‹አይ ተይው አሁን ከሀያ ደቂቃ በፊት አናግሬዋለሁ፡፡.››
‹‹እንዴት ነው ተሳካለት?›› በጉጉት ጠየቀችው፡፡
‹‹አልተሳካለትም፡፡ዛሬማ ሊያብድ ደርሷል፡፡እኔ በበኩሌ ምን እንደሚሻለው ግራ ግብት ብሎኛል፡፡.››
‹‹ምን አንተ ብቻ ኧረ እኔም የማደርገው ጠፍቶኝ እንዴት እንደተጨነቅኩ ብታይ! ወይኔ ወንድሜን ምን አይነት ምትሀተኛ ልጅ ገጠመው?
‹‹ያን ያህል ትወጂዋለሽ ማለት ነው?››
‹‹ምን አይነት ጥያቄ ነው የምትጠይቀኝ? እሱ እኮ ለእኔ ወንድሜም፣አባቴም፣ መላ ቤተሠቤ ማለት ነው፡፡መውደድ የሚለው ቃል ብቻ ይገልፀዋል፡፡.››>
ሠሎሞን በስሜት እየተንዘረዘረ ስታወራው በአንክሮ እየተመለከታት ውስጡ ቅናት ነገር ብልጭ አለበት‹‹እኔን ይሄን ያህል ከልብ የሚወደኝ ሠው ይኖር ይሆን? >> ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ቢያስብ ቢያስብ ከልጆቹ በስተቀር ማንም ትዝ ሊለው አልቻለም፡፡ የቀረውን ቢራ
ጨለጠና እርሱ ተነስቶ ፍሪጁን ከፍቶ ድጋሚ ቢራ አውጥቶ ከፈተው፡፡
‹‹እኔ የሚገርመኝ ምን እንደሆነ ታውቃለህ?›› ፎዚያ ነች ንግግሯን የጀመረችው፡፡
‹‹ካልነገርሽኝ አላውቅም፡፡››
‹‹የትንግርት ነገር!››
‹‹የእሷ ነገር ስትይ?››
‹‹አብራው መንከራተቷ ነዋ፡፡ ምንም ቢሆን መቼስ አንሶላ መጋፈፋቸው አልቀረ፡፡ ያፈቀርኳትን ሴት አፋልጊኝ ሲላት እሺ ብላው አብራ መሄዷ፡፡
‹‹ምን ታድርግ! መቼስ የሚያፈቅሩት ሠው ሲያብድ ወይ በሠንሠለት አስሮ ህክምና መውሠድ አልያም ደግሞ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በሄደበት እየሄዱ ባደረበት እያደሩ ደህንነቱን መከታተል ነው.…እሷም እያረገች ያለችው እንደዚሁ ነው፡፡››
‹‹በፊት ለእሷ ያለኝ ስሜት የቀዘቀዘ ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን እየወደድኳት መጣሁ፡፡››
‹‹በደንብ ውስጧን ብታውቂ ደግሞ ይበልጥ ታፈቅሪያታለሽ፡፡ ልዩ ሠው ነች፡፡ ምን እንዳደረገባት አላውቅም እንጂ እኔ እሱን ብሆን ዓይኔ ከእሷ ውጭ ሌላ ሠው አያይም ነበር፡፡ በስብዕናዋ፣በጥበብ አፍቃሪነቷ፣ በአስደሳች ገፅታዋ፣በምሁራዊ ምልከታዋ፣የሕይወትን ውስጠ ምሥጢር አብጠርጥራ በማወቋ በቃ በሁሉም ነገሯ ለእሱ የምትገባ ሴት ነበረች፡፡እንዴ! ትንግርት ማለት እኮ አንድ ሴት ሳትሆን አስር ሴት ነች፡፡››
‹‹ኤደንስ?››
‹‹የእሷ ትንሽ የተለየ ነው፡፡››
‹‹የተለየ ስትል?››
‹‹አየሽ ኤደን ስርዓቷም ሆነ አስተዳደጓ ለሁሴን የሚሆን አይደለም፡፡ ኤደን ማለት የተለመደች አይነት ሴት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፣ ሃይማኖተኛ ነች፣ባህል አክባሪ ነች፣ አብዛኛው ህብረተሠብ በመኖር ላይ ያለውን ኑሮ መኖር የምትፈልግ ሴት ነች፡፡ ጋብቻ፣ ሠርግ፣ እቁብ፣ ዕድር፣ አራስ-ጥሪ፣ ክርስትና፣ ለቅሶ ... የመሳሠሉትን ማህበራዊ ሠንሠለቶችን ሳታዛንፍ መከወን የምትፈልግ ሴት ነች፡፡ ሁሴንን ተመልከተችው ከህብረተሠቡ ጋር ያለው ግንኙነት የላላ፣ ከባህሉ ጋር ያለው መስተጋብር የረገበ፣ እንዲሁም የግሌ ሃይማኖት አለኝ ብሎ የሚፈላሠፍ ግለሠብ ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ በሁለት ጽንፍ ያሉ ግለሠቦች እንዴት ይጣመራሉ? መጀመሪያ እንደውም ለምን አታገባትም ብዬ እጨቀጭቀው ነበር፤ አሁን በደንብ ቀርቤ ሳያትና ልዩነታቸውን ስገነዘብ የእሱ ውሳኔ ትክክል እንደነበር ነው የገባኝ፡፡ እሷ ባይሆን ለእንደኔ አይነቱ ተመራጭ ነች፡፡›› በፈገግታ ንግግሩን አጠናቀቀና ቢራውን አንስቶ ተጎነጨ፡፡
‹‹ለእንደኔ አይነቱ ስትል?››
‹‹አየሽ እኔም እንደ እሷ የተለመደ አይነት ኑሮ ነው የሚመቸኝ፡፡ ፍልስፍና ቅብጥርሴ ያን ያህል አይደለሁም፡፡ አብዛኛው እሷን የሚመቿት ነገሮች እኔንም ይመቹኛል፡፡ በዛ ላይ ቆንጆ ነች፡፡ ገንዘብ አባካኝ አይደለችም፣ እንደውም ጠንካራ ሠራተኛ ነች፣ ታማኝ ነች፣ እነዚህ ነገሮች ደግሞ እኔ በጣም እምፈልጋቸው ናቸው››
ከመጠጡ ጋር ወደ ውስጡ የዋጠውን ንግግሩን ስታላምጠው የሆነ ነገር ጫረባት፡፡ ‹‹ያፈቅራት ይሆን እንዴ?›› ስትል አሠበችና ማረጋገጥ ፈለገች፡፡
‹‹መጀመሪያ የሁሴን ፍቅረኛ ባትሆን ኖሮ እሷን ማግባት ትፈልግ ነበር?››
መልስ ሳይሠጣት ለደቂቃዎች በአትኩሮት ተመለከታትና መናገር ጀመረ<<አዋ እሺ ካለችኝ ለሁለተኛ ጊዜ ላገባ የምፈልገው እሷን ነው፡፡ ደግሞም እሺ የምትለኝ ይመስለኛል›
ደነገጠች፡፡ የሠከረም መሠላት ‹‹ስለ ኤደን እኮ ነው የምናወራው››
«አዎ ምነው?>
‹‹አገባታለሁ ስትል ምን ማለትህ ነው? የሁሴን ፍቅረኛ እኮ ነበረች፡፡››
‹‹ነበረች፤ አሁን ግን አይደለችም፡፡ ከተለያዩ አመት ሊደፍን ነው›
‹‹ቢሆንም የሁሴንን አምቧረቀችበት፡፡
ፈገግ አለና ‹‹ባክሽ አታካብጂ .. በመጀመሪያ ሀሳቡን ያቀረበው እርሱ ነው፡፡ ሁሴን ማን እንደሆነ አታውቂም መሠለኝ›
‹‹ይሄንን ነገር እኔ አላምንም ደግሞም ያው እሱ እብድ ነው ሊልህ ይችላል፡፡ እሷ ግን በፍፁም እሽ አትልህም፡፡››
‹‹በተወሠነ መልኩ ትክክል ነሽ፡፡ እስከ አሁን አገባሀለሁ ብላ ቃሏን አልሠጠችኝም፤ግን
የተወሠነ መንገድ ተጉዘናል፡፡››
‹‹ምን ዓይነት መንገድ?››
የሁለት ወር ጉዞ፡፡ እርግጥ የመጀመሪያ ቀን አብረን ስናድር አቅደን አይደለም፤ በተለይ እሷ በአዕምሮዋም አልነበረም፡፡
እኔ ግን ሁሴን ከፈለክ ቀጥል ካለኝ በኃላ የተወሠነ ፍላጎት በውስጤ ተጭሮ ነበር፤እናም የዛን ቀን እሷ በእሱ ተናዳ፣ እኔ በሚስቴ ተንገብግቤ ተገናኘን ጠጣን እስክንበሠብስ ሠከርን፣ አብረን አደርን፤ ማደር መቼም ምን ማለት እንደሆነ ይገባሻል፡፡
‹‹ቆይ ጥዋት በንፁህ አዕምሮዋ ስታስበው ምን አለች?››
‹‹ተቆጣች፣ አለቀሰች፣ ብዙ ተፀፀተች፣ ለአንድ ሳምንት አኮረፈችኝ ፣ ግን ቀስ በቀስ ለቀቀ እያለች መጣች ደጋግመን ማደር ጀመርን››
‹‹ታዲያ እዚህ ደረጃ ከደረሳችሁ መጋባቱም ቀላል ነው በለኛ!››
‹‹እሱ ላይ እንኳን ትንሽ ችግር አለ፣ ሁሴን አግብቶ ያየሁ ቀን በማግስቱም ቢሆን አገባለሁ ብላኛለች
‹‹የሚገርም ጉድ ነው፤ ታዲያ ይቅናው ብለህ
አትፀልይም?››
‹‹ኧረ ምን ፀሎት ብቻ አዲስ አበባ ለሚገኙት ታቦቶች በጠቅላላ ተስያለሁ››
✨ይቀጥላል✨
ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ ቤተሰቦች ዛሬም አንድ 10 ሰው እጠብቃለው👍 አሁንም እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹በጊዜ ነበር እኮ መምጣት የፈለኩት ለሆነች ጉዳይ ከአንድ መስሪያ ቤት ወደ ሌላው ስሯሯጥ መሸብኝ›› ሠሎሞን ነው፡፡
‹‹ምንም አይደል ዋናው መምጣትህ ነው›› ፎዚያ መለሠችለት ከፍሪጅ ያወጣችውን ቀዝቃዛ ቢራ ከፍታ ፊት ለፊቱ እያስቀመጠች፡፡
‹‹ወድጄ መሠለሽ ፤ ያ እብድ ሳታያት እንዳታድር ብሎ ስላስገደደኝ ነው የመጣሁት፡፡››
‹‹ሁሴን እያት ባይልህ አትመጣም ነበር ማለት ነው?›› አለችው ትንሽ እንደማኩረፍ ብላ፡፡
‹‹አይደለም፤ እንዲሁ ነገፀሩን አልኩ እንጂ መምጣቱንማ እኔም እፈልገው ነበር ምነው ቆመሽ ቀረሽ አንቺም ያዥና ቁጭ በያ ::
ፍሪጁን ከፍታ ሚሪንዳ አውጥታ ከፍታ ፊት ለፊቱ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አይ ይሄማ አይሆንም.ቢራ ከሌለ ወጣ ብዬ ገዝቼ እመጣለሁ ካለበለዚያ ግን እኔን አልኮል እየጋትሽ አንቺ ለስላሳ እንዳትከፍቺ››
‹‹እንዴ! አረ እኔ አልጠጣም ።.››
‹‹ይቅርታ እንደዛ ፓጋን መስለሺኝ ነው፡፡
‹‹እዚህ ጋር ወራጅ አለ…እኔ ፊት እሱን መተቸት ክልክል ነው፡፡.››
‹‹ተቀብያለሁ...ለመሆኑ ዛሬ ደውሎልሻል?››
‹‹አልደወለልኝም ትናንት ነው የደወለልኝ ፣እንደውልለት እንዴ?››
‹‹አይ ተይው አሁን ከሀያ ደቂቃ በፊት አናግሬዋለሁ፡፡.››
‹‹እንዴት ነው ተሳካለት?›› በጉጉት ጠየቀችው፡፡
‹‹አልተሳካለትም፡፡ዛሬማ ሊያብድ ደርሷል፡፡እኔ በበኩሌ ምን እንደሚሻለው ግራ ግብት ብሎኛል፡፡.››
‹‹ምን አንተ ብቻ ኧረ እኔም የማደርገው ጠፍቶኝ እንዴት እንደተጨነቅኩ ብታይ! ወይኔ ወንድሜን ምን አይነት ምትሀተኛ ልጅ ገጠመው?
‹‹ያን ያህል ትወጂዋለሽ ማለት ነው?››
‹‹ምን አይነት ጥያቄ ነው የምትጠይቀኝ? እሱ እኮ ለእኔ ወንድሜም፣አባቴም፣ መላ ቤተሠቤ ማለት ነው፡፡መውደድ የሚለው ቃል ብቻ ይገልፀዋል፡፡.››>
ሠሎሞን በስሜት እየተንዘረዘረ ስታወራው በአንክሮ እየተመለከታት ውስጡ ቅናት ነገር ብልጭ አለበት‹‹እኔን ይሄን ያህል ከልብ የሚወደኝ ሠው ይኖር ይሆን? >> ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ቢያስብ ቢያስብ ከልጆቹ በስተቀር ማንም ትዝ ሊለው አልቻለም፡፡ የቀረውን ቢራ
ጨለጠና እርሱ ተነስቶ ፍሪጁን ከፍቶ ድጋሚ ቢራ አውጥቶ ከፈተው፡፡
‹‹እኔ የሚገርመኝ ምን እንደሆነ ታውቃለህ?›› ፎዚያ ነች ንግግሯን የጀመረችው፡፡
‹‹ካልነገርሽኝ አላውቅም፡፡››
‹‹የትንግርት ነገር!››
‹‹የእሷ ነገር ስትይ?››
‹‹አብራው መንከራተቷ ነዋ፡፡ ምንም ቢሆን መቼስ አንሶላ መጋፈፋቸው አልቀረ፡፡ ያፈቀርኳትን ሴት አፋልጊኝ ሲላት እሺ ብላው አብራ መሄዷ፡፡
‹‹ምን ታድርግ! መቼስ የሚያፈቅሩት ሠው ሲያብድ ወይ በሠንሠለት አስሮ ህክምና መውሠድ አልያም ደግሞ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በሄደበት እየሄዱ ባደረበት እያደሩ ደህንነቱን መከታተል ነው.…እሷም እያረገች ያለችው እንደዚሁ ነው፡፡››
‹‹በፊት ለእሷ ያለኝ ስሜት የቀዘቀዘ ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን እየወደድኳት መጣሁ፡፡››
‹‹በደንብ ውስጧን ብታውቂ ደግሞ ይበልጥ ታፈቅሪያታለሽ፡፡ ልዩ ሠው ነች፡፡ ምን እንዳደረገባት አላውቅም እንጂ እኔ እሱን ብሆን ዓይኔ ከእሷ ውጭ ሌላ ሠው አያይም ነበር፡፡ በስብዕናዋ፣በጥበብ አፍቃሪነቷ፣ በአስደሳች ገፅታዋ፣በምሁራዊ ምልከታዋ፣የሕይወትን ውስጠ ምሥጢር አብጠርጥራ በማወቋ በቃ በሁሉም ነገሯ ለእሱ የምትገባ ሴት ነበረች፡፡እንዴ! ትንግርት ማለት እኮ አንድ ሴት ሳትሆን አስር ሴት ነች፡፡››
‹‹ኤደንስ?››
‹‹የእሷ ትንሽ የተለየ ነው፡፡››
‹‹የተለየ ስትል?››
‹‹አየሽ ኤደን ስርዓቷም ሆነ አስተዳደጓ ለሁሴን የሚሆን አይደለም፡፡ ኤደን ማለት የተለመደች አይነት ሴት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፣ ሃይማኖተኛ ነች፣ባህል አክባሪ ነች፣ አብዛኛው ህብረተሠብ በመኖር ላይ ያለውን ኑሮ መኖር የምትፈልግ ሴት ነች፡፡ ጋብቻ፣ ሠርግ፣ እቁብ፣ ዕድር፣ አራስ-ጥሪ፣ ክርስትና፣ ለቅሶ ... የመሳሠሉትን ማህበራዊ ሠንሠለቶችን ሳታዛንፍ መከወን የምትፈልግ ሴት ነች፡፡ ሁሴንን ተመልከተችው ከህብረተሠቡ ጋር ያለው ግንኙነት የላላ፣ ከባህሉ ጋር ያለው መስተጋብር የረገበ፣ እንዲሁም የግሌ ሃይማኖት አለኝ ብሎ የሚፈላሠፍ ግለሠብ ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ በሁለት ጽንፍ ያሉ ግለሠቦች እንዴት ይጣመራሉ? መጀመሪያ እንደውም ለምን አታገባትም ብዬ እጨቀጭቀው ነበር፤ አሁን በደንብ ቀርቤ ሳያትና ልዩነታቸውን ስገነዘብ የእሱ ውሳኔ ትክክል እንደነበር ነው የገባኝ፡፡ እሷ ባይሆን ለእንደኔ አይነቱ ተመራጭ ነች፡፡›› በፈገግታ ንግግሩን አጠናቀቀና ቢራውን አንስቶ ተጎነጨ፡፡
‹‹ለእንደኔ አይነቱ ስትል?››
‹‹አየሽ እኔም እንደ እሷ የተለመደ አይነት ኑሮ ነው የሚመቸኝ፡፡ ፍልስፍና ቅብጥርሴ ያን ያህል አይደለሁም፡፡ አብዛኛው እሷን የሚመቿት ነገሮች እኔንም ይመቹኛል፡፡ በዛ ላይ ቆንጆ ነች፡፡ ገንዘብ አባካኝ አይደለችም፣ እንደውም ጠንካራ ሠራተኛ ነች፣ ታማኝ ነች፣ እነዚህ ነገሮች ደግሞ እኔ በጣም እምፈልጋቸው ናቸው››
ከመጠጡ ጋር ወደ ውስጡ የዋጠውን ንግግሩን ስታላምጠው የሆነ ነገር ጫረባት፡፡ ‹‹ያፈቅራት ይሆን እንዴ?›› ስትል አሠበችና ማረጋገጥ ፈለገች፡፡
‹‹መጀመሪያ የሁሴን ፍቅረኛ ባትሆን ኖሮ እሷን ማግባት ትፈልግ ነበር?››
መልስ ሳይሠጣት ለደቂቃዎች በአትኩሮት ተመለከታትና መናገር ጀመረ<<አዋ እሺ ካለችኝ ለሁለተኛ ጊዜ ላገባ የምፈልገው እሷን ነው፡፡ ደግሞም እሺ የምትለኝ ይመስለኛል›
ደነገጠች፡፡ የሠከረም መሠላት ‹‹ስለ ኤደን እኮ ነው የምናወራው››
«አዎ ምነው?>
‹‹አገባታለሁ ስትል ምን ማለትህ ነው? የሁሴን ፍቅረኛ እኮ ነበረች፡፡››
‹‹ነበረች፤ አሁን ግን አይደለችም፡፡ ከተለያዩ አመት ሊደፍን ነው›
‹‹ቢሆንም የሁሴንን አምቧረቀችበት፡፡
ፈገግ አለና ‹‹ባክሽ አታካብጂ .. በመጀመሪያ ሀሳቡን ያቀረበው እርሱ ነው፡፡ ሁሴን ማን እንደሆነ አታውቂም መሠለኝ›
‹‹ይሄንን ነገር እኔ አላምንም ደግሞም ያው እሱ እብድ ነው ሊልህ ይችላል፡፡ እሷ ግን በፍፁም እሽ አትልህም፡፡››
‹‹በተወሠነ መልኩ ትክክል ነሽ፡፡ እስከ አሁን አገባሀለሁ ብላ ቃሏን አልሠጠችኝም፤ግን
የተወሠነ መንገድ ተጉዘናል፡፡››
‹‹ምን ዓይነት መንገድ?››
የሁለት ወር ጉዞ፡፡ እርግጥ የመጀመሪያ ቀን አብረን ስናድር አቅደን አይደለም፤ በተለይ እሷ በአዕምሮዋም አልነበረም፡፡
እኔ ግን ሁሴን ከፈለክ ቀጥል ካለኝ በኃላ የተወሠነ ፍላጎት በውስጤ ተጭሮ ነበር፤እናም የዛን ቀን እሷ በእሱ ተናዳ፣ እኔ በሚስቴ ተንገብግቤ ተገናኘን ጠጣን እስክንበሠብስ ሠከርን፣ አብረን አደርን፤ ማደር መቼም ምን ማለት እንደሆነ ይገባሻል፡፡
‹‹ቆይ ጥዋት በንፁህ አዕምሮዋ ስታስበው ምን አለች?››
‹‹ተቆጣች፣ አለቀሰች፣ ብዙ ተፀፀተች፣ ለአንድ ሳምንት አኮረፈችኝ ፣ ግን ቀስ በቀስ ለቀቀ እያለች መጣች ደጋግመን ማደር ጀመርን››
‹‹ታዲያ እዚህ ደረጃ ከደረሳችሁ መጋባቱም ቀላል ነው በለኛ!››
‹‹እሱ ላይ እንኳን ትንሽ ችግር አለ፣ ሁሴን አግብቶ ያየሁ ቀን በማግስቱም ቢሆን አገባለሁ ብላኛለች
‹‹የሚገርም ጉድ ነው፤ ታዲያ ይቅናው ብለህ
አትፀልይም?››
‹‹ኧረ ምን ፀሎት ብቻ አዲስ አበባ ለሚገኙት ታቦቶች በጠቅላላ ተስያለሁ››
✨ይቀጥላል✨
ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ ቤተሰቦች ዛሬም አንድ 10 ሰው እጠብቃለው👍 አሁንም እየገባችሁ #ሰብስክራይብ #አድርጉ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍129😁16❤14👎3