አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
እርግጠኝነት በጎደለውና በቀዘቀዘ መንፈስ "አዎ" አለዋለሁ

ሁለቴም ሳወራው ዮኒ ሰምቶኝ የጥላችን ምክንያት ሆኖ ነበር። ቢኒ የሚባል ስም ቤት ውስጥ በተለይ ከኔ አፍ መስማት አይፈልግም።

።።።።
ከቀናት በአንዱ አዳር ስራ ገብቼ ደክሞኝ ቤት ስደርስ ከእንቁ መኝታ ቤት የለቅሶ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝና ደንግጬ ሄጄ በሯን ስከፍት አልጋ ላይ ኩርምት ብላ ተኝታ ታለቅሳለች።

"እንቁዬ ምንድነው የኔ ልጅ ምን ሆንሽ" ድንግጥ ብላ ተነሳችና እንባዋን እየጠራረገች

"ምንም አልሆንኩም ማሚ"

"ምንድነው ፊትሽ ገርጥቷል እኮ አይንሽም አብጧል አሞሻል እንዴ" እጄን ግንባሯ ላይ አድርጌ ትኩሳቷን ለካሁት ግላለች

"አይ ትንሽ ሆዴን አሞኝ ነው። ማለቴ ፔሬድ ስለመጣብኝ ቁርጠቱን አልቻልኩትም" ፔሬድ ሲመጣ እንደሚያማት ባውቅም እንደዚ በህመም ስታለቅስ አይቻት አላውቅም ነበር። ማስታገሻ ኪኒን እንድትውጥ ካደረኳት በኋላ ተመልሳ ጥቅልል ብላ ተኛች።

መኝታ ቤት ገብቼ ልብሴን ቀይሬ ልተኛ ስል ስልኬ ላይ መልዕክት ገባልኝ።

"ባልሽን አሳርፊው ልንማር እንጂ ልንሸረሙጥ አልመጣንም ቴሌግራም ላይ ሙሉ መረጃውን ታገኛለሽ" ይላል። እየተጠራጠርኩ ቴሌግራም ከፈትኩ ፊት ለፊት የመጣልኝን መልዕክት ስከፍተው
ፎቶ እና አጭር ቪድዮ.....  ዮኒ ከሌላ ሴት ጋር....

ይቀጥላል
👍6914😱6🔥3😁2
🎈💰የእናቴ ልጅ💰🎈
💰🎈ክፍል ሠላሳ🎈💰
🔮🎈🔮🎈🔮🎈🔮
ሁሉም ነገር አላፊ ነው !አነሰም ከበደም ኸደ አንተ የመጣው ነገር እንደተጫነህ አይቀርም ፡ በቃ አልቆልኛል ከእንግዲማ ምንም ነገር አይስተካከልም፣ ይህንንማ ልወጣው አልችልም፣ ብሞት ይሻለኛል፣ ወይም ብን ብዬ አገር ለቅቄ ልጥፋ ፣ የምትልበት አጋጣሚ  ይመጣል ። አንተ የዚች ዓለም ነገር ቀድሞ ከገባህ እረጋ ሰከን ብለህ ነገሮችን ለማሳለፍ መሞከር አለብ  ፣ነገሮችህን ሁሉ ለፈጣሪህ እየነገርክ በፀሎት  መትጋት እናም እየሄድክበት የነበረውን መንገድ በድጋሚ ማጤን እና ለነገሮች መፍትሔ መስጠት ነው ። ከዛ ሁሉም ነገር ጊዜ ጠብቆ እንደ አመጣጡ ይሄዳል ። ይሄን በራሴ አይቼዋለው ።
  እናቴ ለኔ የነበራት ጥላቻ የተሳሳተ መሆኑን በጊዜ ሂደት ተረድታለች ፡ የጠፋው አባቴ ተገኝቷል ፡ አቤል ሁሉንም ነገር በኔ የማመካኘቱ ጉዳይ እስከመጨረሻው ተነቅቶበታል ፡  ለገንዘብና ለሀብት ያን ያክል ጉጉ ባልሆንም ፡ ቤተሰቦቼ ተስማምተው ባለንብረት አድርገውኛል ፡   እናም ከምወዳት ልጅ ጋር  ቃልኪዳን አስረናል ይህ ሁሉ የሆነው የመጣብኝን ነገር ፊትለፊት በመጋፈጤ እና በመቻሌም ጭምር ነው ፡
🎈አቤል ከቀጠርልኝ ነብሰ ገዳይ ጋር  አባታችን በቀላቀለው ጊዜ ፡የገዛ ተባባሪው ላይ ጉዳት ማድረሱን ሰማው ፡ ነገርግን ቤተሰቦቼ ስህተት የሰሩ መሰለኝ  ። አቤል እውነቱን ስላወጣበት ልጁን ደብድቦ እንዳልነበር ቢያደርገውም ።አባቴ ግን ልጁን እንዳየው ። አፋፍሶ ወደ እክምና መስጫ ጥሎት መምጣቱን ነገሩኝ በጣም ነበር የደበረኝ ።ስለ አቤል ስጠይቅ  በእናቴ ውሳኔ መሰረት  በረራው ሳይስተጓጎል በበንጋታው ወደ ስዊዲን እንዲሄድ መደረጉን ነገሩኝ ። ማመን አቃተኝ የእናቴ ውሳኔ ።ለጊዜው አሳመመኝ እንዴት እንዲ ታደርጋለች ብዬ ተበሳጨው ። ልጁስ ድኖ ሲወጣ ምን ሊፈጠር ነው መቼም ጠላት መግዛታችን አይቀርም ።አቤል ከሚሄድ ይልቅ ቢታሰር ነበር የምመርጠው ።እናቴን ለማነጋገር ብሞክርም አልቻልኩም ....


ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍473🥰1😁1🤔1
🔴🍑የእናቴ ልጅ🍑🔴
🍀ክፍል ሠላሳ አንድ🍀
🌺🍀🌺🍀🌺🍀🌺
ከባባድ የሚባሉ ጉዳዮችን አለፌለው ነገሮችን ሲናገሩት እንደሚቀሉ ሆነው አታገኛቸውም ፡በውስጡ ማለፍ እንደመናገር ላይሆን ይችላል ፡ ነገር ግን ምን አማራጭ አለህ ፡ አልችልም አልቻልኩም ካልክ ፡ አይምሮህ በራሱ ጠላት ነው የሚሆንብህ ።
አልቻልኩም ስትለው አዎ አትችልም የሚለውን አሳብ ወስዶ ይደጋግመዋል ፡ ይበልጥ እንዳትችል ያደርግሃል። ለራስህ መንገር ያለብህ ይሄ ጉዳይ ከባድ ነው ነገርግን ፡ እወጣዋለው !በየቀኑ የመጣብኝን ችግር ለመቅረፍ አእሰራለው እታገላለው ፡ እናም ደሞ ቀስ በቀስ አሸንፈዋለው ማለት መቻል አለብህ።
    እውነት ለመናገር አልችልም አይሆንልኝም ብትልስ ቁጭብለህ አደጋዎችን ከማስተናገድ ውጪ ምን ታመጣለህ ?ምንም ! ከዛ ይልቅ እየተንቀሳቀስክ እየታገልክ በሕይወት ጎዳና ላይ  ወደፊት ብትራመድ አይሻልም።  በነገራችን ላይ ፈጣሪም በኑሮህ በግንኙነቶችህ ላይ ለውጥ እንዲመጣ እየጣርክ ስትፀልይ ነው የሚሰማህ ።
🍀ከነገሮች ማለፍ በዋላ ዛሬ ሁላችንም እንደ ቤተሰብ ተሰብስበናል ።ቤተሰቦቼ ተሟልተዋል ማለት ይቻላል ፡እናትና አባቴ ፣አክስቴ ደግነሽ እና ፡ በችግሬ ወቅት ያገኘዋት የእናት ያህል የማያት ባዩሽ ፣  ትንሿ  ማማ ፣ሁሉም ተሰብስበው ቡና እየተፈላ ምግብ ቀርቦ እየበላን ንፁ የሆነ ጨዋታ እየተጫወትን ቅዳሜን ቀን በጥሩ መንፈስ ጀምረነዋል ፡ እንዲ አይነት የተረጋጋ ቤተሰባዊ ግንኙነት መፍጠር ቀላል አይደለም ፡ ሰላም እና ጤና ያለው ደስተኛ ቤተሰብ  ያለው ሰው እሱን መቼም እንዳይበረዝ መንከባከብ አለበት ፡ ምክንያቱም  የአገር ሰላም እራሱ የሚጀምረው ከቤት ነው ፡ ቤት የተሰራነገር ነው አንዳንዴ  ወደውጭ ወጥቶ ፡ ማህበረሰቡን ብሎም አገርን የሚረብሸው ።
እናም ለቤተሰብህ የምትሰጠውን ትኩረት ከልብህ አድርገው  እልሃለው
አቤልን በሰው ሀገር ሕይወት የራሷን ምክር ትስጠው ብለን ትተነዋል  ።እናም የማማን እናት ጭምር እናቴ እያፈላለገቻት ነው ።እናቴ እሷም ወዳ አይደለም ልጇን እኛላይ እንድትጥል የሆነችው ።አቤል ነው አላፊነቱን መውሰድ ያለበት የሚል አሳብ አምጥታለች ።እኔም ብሆን ነገሩን በተረጋጋ መንፈስ ሳስበው ልክ ናት ፡ ለዚሁሉ ጥፋት መነሻ አቤል ነው ። እሱው ነው መቀጣት ያለበት ያቺ ሴት ከልጇ ጋር የሚገባትን ቦታ እንሰጣታለን ብዬ እኔም በእናቴ ውሳኔ ተስማማው.....


ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍67👏3
🍀🔴የእናቴ ልጅ🔴🍀
🍑ክፍል ሠላሳ ሁለት🍑
👁👁የመጨረሻ👁👁
💫💫💫🌏💫💫💫
ቀን ቀንን እየተካ በሄደ ቁጥር በወንድሜ ላይ የነበረኝ የመረረ ጥላቻ እና ቂም እየደበዘዘ ሲመጣ ይታወቀኛል  ይህን ስሜት ወደድኩት ምክንያቱም እኔ ቂመኝነት በውስጤ ሰርፆ ቤቱን እንዲሰራብኝ የምፈልግ ሰው አይደለውም ። መጥፎ እና ልክ ያልሆኑ ጉዳዮች ጭንቅላቴ ውስጥ ጊዜ ወስደው በቁዩ ቁጥር እታመማለው ፡መረጋጋት አልችልም ። ያንን ስሜት ለማስታገስ ስል ነውጠኛ ነው የምሆነው ፡ከዚበፊት የእናቴን ጥላቻ እና የሰፈሬን ሰው ግልምጫ ለመወጣት ስል ንዴቴን ካገኘውት ሰው ጋር ሁሉ ነገር ፈልጌ እጣላ ነበር ። አሁን ላይ ከጉርምስናውም እየወጣው ነው እና ያ ስሜት እንዲቆጣጠረኝ አልፈልግም ። ስለዚ በወንድሜላይ ያለኝ ብስጭት እየቀነሰልኝ ሲመጣ ተጠቃሚ ነኝና ደስታ እየተሰማኝ ነው ። እሱ በሰው አገር ላይ ምን እያሳለፈ እንዳለ የምናውቀው ነገር የለም ። ሲዊዲን መድረሱን ከተቀባዮቹ ጋር ሆኖ ለእናቴ ደውሎ ከነገራት በዋላ ።ድጋሚ ደውሎም አያውቅም ። እናቴም ብትሆን ጨከን ብላበታለች ። 'ከአሁን በዋላ ቤተሰብ አለኝ ብለህ ወደእኛ እንዳታስብ 'ብላ እንደተናገረቸው አባቴ ነግሮኛል ። በእርግጥ ምንእንደሚሰማት  እሷው ነው የምታውቀው ።የእናት አንጀት እንዲ በቀላሉ ይቆርጣል ማለት ዘበት ነው ። አባታችንም ቢሆን ስሙን ለማንሳት ድፍረቱ ባይኖረውም አንዳንዴ በጨዋታችን መሃል ተክዞ ተክዞ በረጅሙ ሲተነፍስ አጋጥሞኛል ።ምን አልባት ስለ አቤል እያሰበ ይሆናል ብዬ እጠረጥራለው  ።
እኔ እራሱ ሳስበው ለአቤል እንዲመሆን ጥፋተኛው ማነው ? ብዬ አስባለው ። ያለ አባት አድገናል ፣እናታችን የሌለ አቅርባው አቅብጣውም ነበር ። የራሱስ አስተዋፆ ? እኔስ ብሆን ጥፋቶቹን በኔ ሲያላክክ የረዘመ ዝምታ አሳይቼስ አልነበረ ? ብቻ አንዳንዴ ሳስበው አቤል እንዲ እንዲሆን ትንሽ አስተዋፅዖ ሳይኖረን አይቀርም እላለው !!!!
🍑እሁድ ቀን  ተሰብስበን እንደተለመደው እየተጨዋወትን ፡ ቤቱን ሞቅ ደመቅ አድርገነዋል ፣ አባታችን እናቴን እየቀለደባት ያስቀናል ማማ በእናቴ ዙሪያ እየዞረች ባልገባት ነገር ትፈነድቃለች የኛ ሳቅ ሳይጋባባት አይቀርም ፣ እናቴ  ስለተሳቀባት አልከፋትም በጣም ደስተኛ ትመስላለች በባሏ ጎኗ መሆን ሙሉነት ሳይሰማት አይቀርም ልዩ ሆናለች ፡ በዛላይ ትላንትና የማማን እናት በማግኘቷ እፎይታ ተሰምቷታል ፡ የአቤልን ትልቅ ስህተት እንዳረመች ሳይሰማት አይቀርም ፡ የማማን እናት ይዛት መጥታ በማንኛውም ሰአት ልጇን የማየት መብት እንዳላት ነግራ ፡ ነገር ግን እፃኗ ከኛጋር መኖር እንዳለባት አስረግጣ አስረድታታለች እሷም ብትሆን ለልጇ ያን ያክል የምትጓጓ መስላ አልታየችም ።እንዲ መሆኑን የፈለገች ነው የምትመስለው ይሄ በራሱ ለኔም እንደ ግልግል ነው ።በአራስነቷ የተረከብኳትን ስንት ነገር ያየውባትን ልጅ ልውሰድ ብትል ምን እንደሚሰማኝ አላውቅም ።  ማማ ለኔ ትምህርት ቤቴ ናት በሷ የተነሳ እራሴን ገዝቻለው  ስለ ዓለም ክፋት ደግነት አይቻለው  ማጣት ምን ያክል እንደሚፈትን ገብቶኛል ። ብቻ ብዙ ብዙ ,,,,,
ዛሬ ላይ ግን በዛ ሂደት ውስጥ ስንት የምወዳቸውን ሰው አውቄ አለው ።ለየት ባለ መልኩ ባዩሽን የክፉ ቀኔ ። ብሌኔን ፍቅሬን የወደፊት ሚስቴ የአይኔን ማረፊያ ፡የልብ ምቴ የሕይወቴ ቅመም ማጣፈጫዬን ፡ ብሌኔ ውዴን ብሌኔ ብሌኔ ፡ስሟን እንኳ ስጠራው የሆነ መሃዛ ከአፌ ወጥቶ አብሮ ያውደኛል  ብሌኔ ብሌኔ ......
እረፋዱ ላይ አንዳችን በአንዳች እየሳቅን ጨወታችን ደርቶ ፡  ሳለ የእናቴ ስልክ ጮኽች ።እናቴ እንደሌላው ጊዜ አልፈጠነችም ታነሳዋለች ብለን ስንጠብቅ ፡ወደኛ ማየት ሆነ ። ስትዘገይብኝ ስልኳን አንስቼ ቁጥሩን አየውት የውጪ ለጠ ር ነው ደንገጥ አልኩ ። እናቴ በፍርሃት ስታየኝ
"የውጪ ስልክ ነው አንሺው አልኳት "
"አንተአንሳው "አለች እንደፈራች ስለገባኝ ፡ እኔው አነሳሁት
"ሄሎ "
"ሄሎ የወይዘሮ ዘውድነሽ ስልክ አይደለም "አለኝ የሴት ድምፅ ድንጋጤዬ ጨመረ አቤል ምን ሆኖ ነው
"ነው ማን ልበል አንቺን"አልኳት
"ዲና እባላለው እእ ከሲዊዲን ነው የምደውለው "አለች
"እሺ ምምን የየተፈጠረ ችግር አለ ወንድሜ ምን ሆኖ ነው "አልኳት እየተርበተበትኩ ።እናቴ ስታቃስት ሰማው ዞሬ ሳይ ዕንባዋ ቀድሟል ።
"ኧረ ተረጋጋ እሱ ምንም አልሆነም እኔ ፍቅረኛው ነኝ ያው ብቻ ስለ እናንተ ብዙጊዜ ያወራኛል እና ዛሬ አበረታትቼው አብረን እናወራቸዋለን ብዬ ነው በስንት መከራ የደወልኩት "አለች ፈጠን ፈጠን ብላ
"ድምፁን መስማት እንችላለን "አልኳት
"አዎ እባክህ አንተ ወንድሙ ከሆንክ በጣም ተፀፅቷል እና ይቅር በለው  "አለች
"ችግር የለም ይቅር ብዬዋለው አጠገብሽ ካለ ስልኩን ለሱ ስጪው እናቱን ያናግራት "አልኳት
"እሺ "ብላ ስታስተላልፍ እኔም ስልኩን ለእናቴ ሰጠዋት ።እናቴ ልትደብቀው የማትችለው የልጇ ፍቅር ገንፍሎ ወጣ ፡ በቃ ከአቤል ጋር በናፍቆት አወሩ በተደጋጋሚ ይቅር በይኝ ሲላት ይሰማል ልቡ የተሰበረ ይመስላል ፡ ከአባታችንም ጋር አወራ ፡አባታችንም አለቀሰ ፡ብዙ ነገር ተናገረው እንደዚ አይነት ክፋት ከገዛ ልጁ ስላልጠበቀ እስካሁንም ድረስ እየተሰቃየ እንደሆነ ነገረው አቤል ስቅስቅ ብሎ ሲያለቅስ ይሰማል ፡ጓደኛው ነኝ ያለችው ሴት ታባብለዋለች ፡ላውድ አድርገነው ስለሆነ የምናዳምጠው ፡አክስቴ ደግነሽም ባዩሽም ማልቀሳቸው አልቀረም ፡ አክስቴ ደግነሽ ወደኔ እያየች "ይቅር በለው ልጅነት ነው አውሬ ያደረገው "አለችኝ ሆደባሻነቷ አይሎ ፡  እኔ ውስጤ ተረጋግቷል ሞተ የምባል መስሎኝ ስለነበር ክፉ ነገር ስላልሰማው ሰላም ሰፍኖብኛል ። ዓለም እንግዴ እንደዚ ናት እንደ ዥዋዥዌ ነው ነገሯ ወደዚ ወደዚያ ፣ እንደ ፈለገች አንተ ጠንክረ ገመዷን ይዘህ እየተቆጣጠርክ ካልተጫወጥክ ፈንግላ ልትጥልህ ትችላለች ፡ እራስህን ከማንም ጋር ሳታወዳድር የማንንም ንዋይ ሳትመኝ የሕይወት መንገድህን በራስህ በንፁ ሕሊናህ ታግዘህ አስምር መስመሩ ሲበላሽ በትህግስት እያስተካከልክ  ወደፊት ቀጥል ። ለሌሎች የደስታ የሰላም ምንጭ እንጂ ፣የስቃይ የመከራ ምንጭ አትሁን ፣ አንተ ደስተኛ የምትሆነው በዙሪያህ ደስተኞች ሲኖሩነው ፡ 'ብቻህን በሚያለቅሱ ሰዎች መሃል ብትስቅ እብድ ነው የምትባለው'
             ,
                  👁ተፈፀመ👁
ደራሲ Unknown

    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍12236👎2😁1
አሮሯ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _አንድ
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
🚲🚲🚲
አሮራ  ውብ ነች ከማለት ይልቅ ጣኦት ትመስላለች ማለት ይበልጥ ይገልፃታል።ብዙውን ጊዜ የውበት መስፈሪያውን ወይም መለኪያውን በተመለከተ አጨቃጫቂ የሆነ ክርክር አለ።አንድ ማህበረሰብ ጋር ደልደል እና ደርፎጭ ያለች ሴት ውብ ስትባል በሌላው ማህበረሰብ ደግሞ ሰበር-ቅንጥስ የምትል ሴት ውብ ነች ይባላል።በግለሠብ ደረጃም እያንዳንድ ሰው የራሱ የሆነ ቴስት አለው። አሮራ ግን ለማንም ሰው አስማሚ የውበት ሚዛን ነች።ሴቶች በቅናት ወንዶች በመጎምዠት  እኩል የሚያደንቋት ሴይጣንም መላዕክም እኩል የሚስማማባትና ሳይጨቃጨቅ የሚመርጣት የውበት ጣኦት ነች።የወንዶችን  የፍቅር ስሜታቸውንና የወሲብ ረሀባቸውን በአንድ ቅፅበታዊ እይታ የማናጋት ልዩ ኃይል ያላት አደገኛ ሴት ነች፤በዛ ላይ ተስረቅራቂና ተንሳፋፊ ድምፅ ያላት ታዋቂ ወጣት ድምፃዊ ነች።
አሮራ እድሜዋ 21 ነው።የምትኖረው ኑሮ ከላይ በድፍኑ ሲታይ እጅግ የቅምጥልና  ፍፅም የምቾት ነው።አባቷ ከተማዋን  ከሚዘውሩ ጥቂት  ቱጃሮች መካከል አንደኛውና ዋነኛው ነው።በዛ ላይ በእሷ ህይወት ውስጥ ፍፁም አድራጊ ፈጣሪ ከመሆኑም በላይ ማናጀሯ  ነው።በእሱ በኩል ካልሆነ ማንም ሰው ወደዚህቺ አማላይና ፅፀ-ወሲብ ወደ ሆነች ልጅ  መጠጋት አይችልም።ለሠላምታ እንኳን እሱ መፍቀድ አለበት።
አሮሯ አሁን የገዛ መኝታ ቤቷ አልጋዋ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብላለች።ፊት ለፊቷ የልቧ ሰው የሆነው ተወዳጅ አጎቷ እዝራ ቁጭ ብሎ እያጫወታት ነው።እዝራ አጎቷ ብቻ አይደለም ከ20 ዓመት በላይ የእድሜ ልዩነት በመሀከላቸው ቢኖርም ብቸኛውና ተወዳጅ ጓደኛዋም ጭምር ነው።ለሰው የሚነገር ሆኖ ለእሱ የማትነግረውና ከእሱ ጋር ማትማከርበት አንድም ጉዳይ የለም።ክፋቱ ከእሷ ነገሮች አብዛኞቹ ለማንም መነገር የማይችሉ አሰቃቂ ጨለማ ምስጢሮች በመሆናቸው እሱም ቢሆን እንኳን ስለእሷ የማያውቃቸው ነገሮች ከግማሸ ይበልጣሉ።
እዝራ አባቷ ካለምንም ገደብና ክልከላ እንደፈለገች እንድትገናኘው የሚፈቅድላት ብቸኛው ሰው ነው።ምን አልባት በጣም የሚወደው ብቸኛ ታናሽ ወንድሙ ስለሆነ ሊሆን ይችላል?ምን አልባትም ነገረ-አለሙን እርግፍ አድርጎ በህይወት ተስፋ የቆረጠ ጉዳት- አልባና ጥቅም-አልባ ሰው አድርጎ ስለሚያስበውም ሊሆን ይችላል።

"ሮሪ ስምሽን አሮራ ብሎ ማን እንዳወጣልሽ ታውቂያለሽ?"ሲል ጠየቃት።
"አጎቴ አውቃለሁ አንተ ነህ።"
"ከመልክሽ በላይ አንፀባራቂ ስም ነው ያወጣሁልሽ።አሮራ ጥልቀት ያለው ብርሀናማ  ስም ነው።ቀለል አድርገሽ ስትተረጉሚው  በማለዳ  ከእንቅልፍሽ  ተነስተሽ ከነቢጃማሽ በረንዳ ላይ ቁጭ እንዳልሽ ለመጀመሪያ ጊዜ ብልጭ ስትል የምታያት ልብ ሰንጣቂ  የፀሀይ ብርሀን ማለት ነው።በሌላ ጎኑም ማታ ለመጨረሻ ጊዜ ውስጥሽ በፍራቻ እየተሸበረ እያየች ግን ደግሞ ተሠናብታሽ የምትጠልቀው የመጨረሻዋ የፀሀይ ፍንጣቂ  ማለት ነው።"
"አጎቴ ስሜ ብዙ ትርጉም ያለው ነው..አውቃለሁ ደጋግመህ ነግረኸኛል።"
"አዎ ነግሬሻለሁ።የፀሀይ አካል የሆኑ የኤሌክትሪክ ቻርጆች (ፓርቲክሎች) በምድር አካባቢ  ከሚገኙ ናይትሮጂን እና ኦክስጅንን ከመሰሉ ጋዞች ጋር  ሲዋሀድ   የሚፈጠርና  በምድር  ከፍታ(ሰማይ) ላይ በሚፈጠር በአረንጓዴ ፣ቢጫ፣ ቀይና ነጭ ቀለም የሚገለፅ የተፈጥሮ ክስተት ማለትም ነው።ሌላውጨደቡብ እና ሰሜን ዋልታ ጫፍ ላይ ያለች ውብና ተወዳጅ የፀሀይ ብርሀንም ብለሽ ብትተረጉሚው ትክክል ነሽ።"
"አጎቴ ይሄንን ስም ለእኔ መሰየም የለብህም ነበር።ዝብርቅርቅ ትርጉም ያለው ስም ሰጥተኸኝ ዝብርቅርቋ የወጣ ልጅ ሆኜ ቀረሁ።" አለችው።
"ወድጄ ይመስልሻል ይሄን ስም የሰጠሁሽ?እንዲህ አሁን ባለሽበት አፍላ እድሜ ላይ ጣሊያን እያለሁ  ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ ልቤን የከፈትኩትና በእንብርክኬ እስክሄድ ያፈቀርኩት አሮራ የተባለች  ስፔናዊት ልጅን ነበር...."
ንግግሩን አቆመና ኪሱን በረበረ...የሮዝማን ሲጋራ ፓኮውንና ላይተሩን ከኪሱ አወጣና  አንድን ከውስጡ መዞ በመለኮስ የሲጋራውን ፓኮና ላይተሩን ፊት ለፊት ጠረጴዛው ላይ ጣል አድርጎ  የለኮሰውን ማብነን ጀመረ...እዝራ ይሄንን ታሪክ ለአሮራ ሲነግራት   ምን አልባት ለአስር ሺኛ ጊዜ ሊሆን ይችላል ።እሱም ስለፍቅረኛው አሮሯ  አውርቶ አይደክመውም እሷም አይ ይሄኛውን ታሪክን ከመቶ ጊዜ በላይ ነግረሀኛል አሁን ሰለቸኝ መስማት አልፈልግም ብላው አታውቅም።እንደዛ የማትለው ደግሞ እሱን ማስቀየምና ማስከፋት ስለማትፈልግ ብቻ አይደለም በእሱ የማፍቀር መጠንና ጥልቀት ስለምትቀናም ጭምር  ነው።በእሱ መጠን አፍቅሮ በእሱ መጠን መሠቃየት ስለሚያምራት ነው።እንደዚህ እንዴት ልታስብ እንደቻለች ለራሷም ይገርማታል።እንደእሱ ለይቶላት ህይወቷን ሙሉ በሙሉ እርግፍ አድርጋ በመተው የሙሉ ጊዜ እብድ አትሁን እንጂ ከእሱ የበለጠ የውስጥ ህመም፤ ከእሱ የበለጠ የልብ መሠባበርና የስሜት መፈረካከስ ያጋጠማትና በዛም የተነሳ የማይድን በሽታ ታቅፋ የምትኖር ልጅ  ነች፣ለዛውም በዚህ ጨቅላ ዕድሜዎ። እሱ ግን ስለዛ መራር የስደት አለም የፍቅር ታሪኩ ለእሷም ሆነ ለሚያዳምጠው ለማንኛውም ሰው ሲያወራና በናፍቆት እንባ በጉንጮቹ እያንጠባጠበ በኩራት ሲተርክ ደስታውንም ሆነ ሀዘኑን ከሌላው ሲያጋራ ይኖራል ።በዛም እራሱን ያክማል።እሷ ግን እንደዛ አይነት እድል የላትም።ስለፍቅር ታሪኳ ለራሷም የማውራቱ ሞራልም ሆነ ድፍረቱ የላትም።ስሜቷን አዳፍና ህመሞን በውስጧ ቀብራ እህህ ማለት ብቻ ነው ያላት እድል።እስከአሁን ግን እንዴት እንደእሱ እንዳለየላትና እንዳላበደች ይገርማታል...አንድ ቀን ግን የእሱ እጣ እንደማይቀርላት እርግጠኛ ነች።ከአንድ ቤት ሁለት እብድ።

እዝራ ሲጋራውን ግማሽ ድረስ ከማገ በኃላ ወሬውን ካቆመበት ቀጠለ"አሮራ ልክ እንደአንቺ ውብ ነበረች.. ጥርት ያለ ድምፅ፣ልስልስ ቆዳ፣ ስስ ልብ...ሰው ሳይሆን ከሰማያዊው መንደር ጠፍታ በስህተት በምድር እየኖረች ያለች መላአክ ስለምትመስለኝ አብዝቼ እሳሳላት ነበር...ስስማት እንኳን ከንፈሯን አሳምማት ይሆን ?እያልኩ እጨነቅ ነበር።በሆነ ንግግሬ ግንባሯን ከቋጠረችማ በቃ  ክፍሌ ገባና በራፌን ዘግቼ በጉልበቴ ተንበርክኬ ለሠራሁት ሀጥያት እግዜር ይቅር እንዲለኝ እፀልይ ነበር።በእሷ ምክንያት የድሮ ነገሬን ሁሉ ረስቼ ነበር።ከኢትዬጰያ መሄዴን ረሳሁ።ዘመዶች እንዳሉኝ እረሳሁ።ጥቁር መሆኔንም እረሳሁ።..በቃ እኔ የአሮራ ፍቅር ብቻ ሆንኩ።ለመጋባት ወሰንን፣ እቤት ገዛን ፣ሁሉ ነገር ተዘጋጀን ...ግን ለሰርጋችን አንድ ወይም ሁለት ቀን  ሲቀረን እሷ ከጎደኞቾ ጋር እቃ ለመግዛት የሆነ ሱፐርማርኬት እንደገባች አጋጣሚ ሆኖ  የሆኑ ዘራፊዎች በቦታው ተከሰቱ፤ ፓሊስ በአካባቢው ስለነበረ መታኳስ ጀመሩ ፤ከአንድ አስጠሊታ ሽጉጥ የወጣች አስጠሊታ ጥይት የእኔ መልአክ  ጉሮሮ ውስጥ ተሠነቀረች።ከዛ አሮራ የምትጠልቀው ፀሀይ ሆነች....ከዛ በኃላ እንደምታውቂው  ሁለ ነገሬ ፈራረሰ ..መስራትም መማርም አልቻልኩም። ከአስር አመት ቆይታ  በኃላ ሳልወድ  በግድ  ግማሽ ልቤና ግማሽ ነፍሴ ታሞ ወደሀገሬ ተመለስኩ።ስመለስ ወንድሜ እንዳገባ እንኳን ሳላቅ አንቺን የመሰለች ፀሀይ ልጅ ወልዶ ጠበቀኝ ።በወቅቱ አምስት አመትሽ ነበር ።በጣም ነው የወደድኩሽ ...ሰው ሁሉ ቢያስጠላኝም አንቺን ግን ወደድኩሽ። ከዛ አንቺም የምታንፀባርቂ ፀሀይ ስለሆንሽ እግረመንገድም ለፍቅሬ መታወሻ ለማድረግ...ማለቴ በየቀኑ ደጋግሜ  ስሟን ለመጥራት እድሉን ለማግኘት ስል  አሮራ የሚል ስም
👍10213👏3🔥1😁1
አወጣሁልሽ...እና ሮሪ ሁሉ ነገር እንደዛ ነው የሆነው።"አለና የመጨረሻውን የሲጋራ ቁራጭ መጠጠና ጫፍን  ወለሉ ላይ በመጣል በእግሩ በማሸት እሳቱን አጠፋው።
"እና እኔስ ብጠፍ...ልክ እንደፍቅረኛህ የምትጠልቀው የማታ  ፀሀይ ብሆንስ?"ስትል ጠየቀችው።
"በፍፁም እንደዛ አይሆንም።  አንቺ  በሰማይ ላይ ዘወትር የምታንፀባርቂው ፀሀይ ነሽ።ተመልከች ገና 21 አመትሽ ነው።በጣም ስኬታማና ታዋቂ ድምፃዊ ነሽ።በዚህ ዕድሜሽ በርካት ሽልማቶችን የግልሽ አድርገሻል።ግን ይሄ በቂ አይደለም አለማቀፍ ብርሀን እንድትሆኚ ነው የምፈልገው።ከዚህ መቶ ጊዜ እጥፍ እንድታንፀባርቂ.."
"አጎቴ እኔ ግን ውስጤ በጨለማ ድቅድቅ ተውጦ የአለም ብርሀን መሆን ፈልጋለሁ እያልኩ እራሴን ማታለል ነው የሠለቸኝ ...እኔ ማንም የማያውቀኝ ተራ ግን ደግሞ ደስተኛ ሴት መሆን ነበር የምፈልገው።"
"እንደዛ ከሆነ ከእናትሽ ሞት ጋር የተያያዘ ህመምሽን ታክሞ ለመዳን ሞክሪ ፣የተሠበርሽበት ቦታ ፈራርሰሽ አትቅሪ "
"አንተ ከአሮራ ሞት ጋር የተያያዘውን ቁስልህን መርሳት ችለኸል? እኔስ የእናቴ ሞት ገና አራት አመት አልሆነውም አንተ ግን 15 አመት ሙሉ እራስህን ማከም አልቻልክም..ዛሬም ቁስልህ አዲስ ነው።"
ምን ታደርጊዎለሽ... አንዳንድ ቁስሎችን ጊዜ በቀላሉ አይፈውሳቸውም...አንቺ ግን ማድረግ ያለብሽ ቢያንስ ከእኔ ከእብድ አጎትሽ  የከሸፈ ህይወት መማር ነው... አሁን መጠጥ አማረኝ "ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ።
"አጎቴ ደግሞ...እዚሁ ምትፈልገውን መጠጥ ያምጡልህ "
"አይ የዚህ ቤት መጠጥ ውስኪ.. ቢራ ምናምን ነው ..እኔ ምፈልገው ካቲካላ ነው።"አላት።

.

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍6113😁1😱1
#ህያብ


#ክፍል_አስር


#ድርሰት_በኤርሚ


"ባልሽን አሳርፊው ልንማር እንጂ ልንሸረሙጥ አልመጣንም ቴሌግራም ላይ ሙሉ መረጃውን ታገኛለሽ" ይላል። እየተጠራጠርኩ ቴሌግራም ከፈትኩ ፊት ለፊት የመጣልኝን መልዕክት ስከፍተው
ፎቶ እና አጭር ቪድዮ.....  ዮኒ ከሌላ ሴት ጋር....

እየሰሙ አለማመን ያለም የሚጠበቅም ነው። እያዩ አለማመን ግን ምን ይባላል። በአካል መጥተው ዮኒ ከእከሊት ጋር ማገጠብሽ ቢሉኝ አይደለም እሱን ልጠራጠር ከነገረኝ ሰው ጋር ልጣላ እችላለሁ። አሁን ግን እውነታ ነው ቁጭ ያለልኝ... ከምወደው ባሌ ጋር እርቃን ገላዋን አብራው የምታብድ ሴት እያየሁ ነው። የአንዷ አልበቃ ብሎ ከሌላ ሴት ጋር ደግሞ ከንፈሯ ላይ ተጣብቆ ያለ ፎቶ እያየሁ ነው... ግን አንድ ነገር ብቻ ነው የምለው። "የኔ ዮኒ አያደርገውም" አድርጎታል እኮ ...ግን ይህንን ማመን ያልፈለገ ውስጥ አለኝ... እናም እውነታውን እያየ ግግም ብሎ አላምን አለኝ። አንደኛው ውስጤ ደግሞ ፍቅርን ሳይቀር ወደጎን ብሎ በቀልን ፈለገ። ቢችል አሁን ያለበት ሄዶ ስጋውን ቢዘለዝለው ተመኘ። የማያምነው ውስጤ ገኖ ወጣና
"ዮኒ አያደርገውም" በጩኸት ቤቱን አደበላለኩት። ሰራተኛዬ እልፍነሽ መኝታ ቤቴን ከፈት አደረገችና

"ሰላም ነው ህያብ" አለችኝ

"ሰላም ነው እልፌ ወደ ስራሽ ተመለሽ" በሩን ዘግታ ተመለሰች። ረጅም ደቂቃ ዝምምም ብዬ ስልኬ ላይ አፈጠጥኩ

ሀሳቡ አደከመኝ ያየሁት እውነት አራደኝ በዛ ላይ ሰሞኑን የተለየ ኬዝ ስለነበረ ያለ እንቅልፍ ሆስፒታል ነበርኩ። ስልኬን ዘግቼ ያስቀመጥኩት መሰለኝ... ከዛ ወደ አልጋዬ ተራመድኩ.... አንድ.... ሁለት..... ጭልም አለብኝ።

"እናት ኧረ ንቂ የኔ ፍቅር" ይሄን ጥሪ ከሰማሁት ስንት አመት ሆነኝ.... ሁለት.... ሶስት... ብቻ በዛ መሀል... አሁንስ ለምንድነው እየሰማሁት ያለሁት... ሁሉም ነገር ከረፈደ... ካለፈበት በኋላ ለምን?... አይኔን ሳልገልጥ እንቅስቃሴውን እየተከታተልኩ ነው።

"ንገሪኝ እስኪ እናት ማነው ጥፋተኛ እኔ ወይስ አንቺ? በእርግጥ የኔ ጥፋት ሚዛን ይደፋል... ምክንያቱም ካየሽው ውጭ እንኳን ብዙ ጥፋቶችን ሰርቻለሁ ግን ባንቺ ጥፋት ላይ ተመርኩዤ ነው። ታውቂያለሽ ከቢኒ ጋር ድሮም እጠረጥርሽ ነበር እና ጥርጣሬዬን የሚያረጋግጥልኝ ነገር ሳገኝ እውነት አይደለም ብዬ ማመን አቃተኝ። ልታስረጅኝ ስትሞክሪ ውሸቷን ነው ብዬ አልሰማም አልኩሽ እናም ከዛን ጊዜ ጀምሮ ያለማቋረጥ ማገጥኩብሽ... ግን እናት ያሁኑ በደሌ በዛ..... (ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ እና ትንሽ ዝም ካለ በኋላ ቀጠለ) ከስንት ጊዜ በኋላ በአንዲት ልጅ ምክንያት ራሴን አዳመጥኩት። አብረሽኝ ካልተኛሽ ውጤትሽን አበላሸዋለሁ ብዬ አስፈራራኋት.... ብዙ ለመነችኝ... ልመናው አልሰራ ሲላት ግን ያንቺን አድራሻ ፈልጋ ሆስፒታል መጣችና አየችሽ። ስለትዳራችን ሳይቀር ብዙ መረጃ ሰበሰበች ከረፈደ ቢሆንም  ንግግሯ ከእንቅልፌ አነቃችኝ... ትልቁን በደሌን የሰራሁ እለት ከእንቅልፌ ነቃሁ

'ሚስትህ ነፍሷን ሳትሰስት ትሰጥሀለች... አንተ ማመን ባልፈለከው ውሸት ውስጥ ተደብቀህ በሀጢያት ተጨማልቀሀል... ለሷ አትገባትም ምክንያቱም ንፁህ ናት... ግን እግዜር ይቅር የማይለው የለም አምላክህንም ሚስትህንም ይቅርታ ጠይቀህ ወደራስህ ተመለስ። ለውጤቴ ስል አብሬህ ላድር አልፈልግም በተለይ ያቺ ሚስኪ ላይ ይሄን ላደርግ አልችልም። ከፈለግህ ኤፍ አድርገው ህሊናዬን አላቆሽሽም'  ብላኝ ስላንቺ እንዴት እንዳወቀች ሁሉንም ነገር አብራራችልን እና ለአመታት ከተኛሁበት እንቅልፍ ዛሬ ቀስቅሳኝ ሄደች። ያሰብኩት ለሀያ ደቂቃ ብቻ ነው። ወደራሴ ተመለስኩ... እውነታውን ማየት ቻልኩ... በንግግሮቼም ሆነ በተግባር ብዙ እንደገፋሁሽ አወቅሁ... በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን እንዴት እንደምትጠነቀቂልኝ... ምን ያክል እንደምትወጂኝ ተረዳሁ። ወደዚህ ለመምጣት እየተጣደፍኩ ስወጣ ቢሮ በር ላይ ከዚህ በፊት በውጤት አስፈራርቻት አብሪያት የተኛሁትን ልጅ አገኘኋት እናም ቪዲዮና ምስል ላንቺ እንደላከችልሽ ነገረችኝ። ምንም ሳልል ወደዚሁ መጣሁ ወድቀሽ አገኘሁሽ።
ህያቤቴ እየሰማሽኝ እንደሆነ አውቃለሁ። ይቅር በይኝ አልልሽም በተለይ በአንድ ጉዳይ ያንቺ ይቅርታ አይገባኝም... ብቻ አይንሽን ግለጪና የፈለግሺውን ቅጪኝ" አይኔን ገለጥኩ ከወገቤ ቀና አልኩና ትራስ ተደግፌ ቁጭ አልኩ። ለረጅም ደቂቃ በዝምታ አፈጠጥኩበት

"ደስ ያለሽን አድርጊኝ የፈለግሺውን ቅጪኝ " አንደበቴ ሊናገር ቢፈልግ እንኳን ውስጤ ዝምምምም ብሏል የሚያስፈራ ዝምታ

"ደግሞ አሁን እሰማሻለሁ ከቢኒ ጋር ያደረጋችሁትን ንገሪኝ እኔ እንደተናዘዝኩ ተናዘዢልኝ.... ይቅር ተባብለን  አብረን ባንቀጥልም ጥያቄዎቼን እንድትመልሽልኝ እፈልጋለሁ... የምናሴ አባት ማነው። ህያብ አንቺም እኮ ድብቅ ነሽ ከኔ የደበቅሺው ብዙ ሚስጥር አለሽ" ዝምምምም

"እንቁን አሟት ነበር ልያት" ከመኝታ ቤታችን ወጥቼ ወደሷ ስሄድ

"እወቂ ለዚህ ሁሉ ነገር ያንቺም እጅ አለበት....ወይኔ አምላኬ ምንድነው ያደረኩት" ሰማሁት ግን ባልሰማ ወደ ልጄ ክፍል ሄድኩ

በሩን ከፈት አድርጌ ሳያት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝታለች ወደ ውስጥ ገባሁና ቀስ አድርጌ ዘጋሁት። የአልጋዋ ጫፍ ላይ ቁጭ ብዬ የትኛችውን እንቁዬን አየኋት ግንባሯ ላይ ቸፈፍ ያለ ላብ አለ። ፎጣ አንስቼ ስጠርግላት እጄን ለቀም አድርጋ ወረወረችውና

"እባክህ አትንካኝ እባክህ" ከእንቅልፏ ደንግጣ ነቃች

"ምንድነው ልጄ ማንን ነው አትንካኝ የምትይው"

"አይይ እእ....እ

"የምን እእ ነው ምንድነው ንገሪኝ" ለአመታት ስቃዥ የነበረው ትዝ አለኝ... አይ አይሆንም

"በህልሜ የሚያስፈራ ሰው ገደል ውስጥ ሊከተኝ ሲል አየሁ" ኡፍፍፍፍ.... እኔ ደግሞ ስንቱን አሰብኩት

"አሁን እንዴት ነው ቁርጠቱ ተሻለሽ" ዮኒ በሩን ከፍቶ ገባ

"ምን ሆነሽ ነው ምናሴ ብዙ አመመሽ እንዴ ጠዋት እኮ ረፍዶብኝ ሳላይሽ ሄድኩ" የቅድሙን የተፀፀተ ፊት ሳይሆን ፍም እሳት የሚተፋ አይኑን አየሁት... እንቁ ፊቷን አዙራ ተኛች

"ምንድነው አንቺ ባለጌ ለአባትሽ መልስ ስጪው እንጂ" ፊቷን እንዳዞረች

"ደና ነኝ ተሽሎኛል" አለችው። ተነሳሁና ትቻቸው ወጣሁ። ሳሎን ሶፋ ላይ ቁጭ ብዬ ቲቪው ላይ አፈጠጥኩ..... ሀሳቤ ግን ሩቅ ሄዶ ነበር። መች ነው ይሄን ክፍተት የፈጠርኩት... ለራሴ ደግሜ ልነግረው አልፈልግም የምለውን ያን የመደፈር ታሪኬን ከመደበቅ... አዎ ከዛ ነው የጀመርኩት... ከዛ  የአዲስ አበባ ልጅ ነኝ አልኩት... ከዛ... ከዛ... ከቢኒ ጋር እንኳን ምንም ግንኙነት የለንም... እሱም እንዳስረዳው እድሉን አልሰጠኝም።

ቢዘገይም ነገሮችን አጥርቼ መሄድ እንዳለብኝ ተሰማኝ እና ታሪኬን ከአንድ ጀምሬ እነግረዋለሁ ብዬ ወሰንኩ... ግን አሁን አይደለም።

ህያብን ምን ይጨንቃታል ብትሉ ሰውን ተጣልቶ ማኩረፍ እላችኋለሁ። በህይወቴ እንደመኮራረፍ የምጠላው ነገር የለም አኩርፌ ማደርም አልችልም... በቃ ከሰው ጋ ተጋጨሁ አይደል ወይ እዛው ጋ ችግሩን እነግረዋለሁ ወይም ዝም ብዬ አልፈዋለሁ... ብቻ ያስከፋኝም ላስከፋውም ድጋሚ ሳገኘው ያንን ሰው አዋራዋለሁ። ከዮኒጋ በአንድ ጣራ ስር... አንድ አልጋ ላይ እየተኛን በየቀኑ እያየሁት ለማኩረፍ ሞከርኩ ግን አልተሳካልኝም በደሉን ባልረሳውም ሳላስበው አዋራሁት።
👍606
"መነጋገር ያለብን አይመስልሽም" አለኝ። ወደ ስራ ለመሄድ እየተጣደፍኩ እያለ   "አስቤበታለሁ ማውራት አለብን ግን አሁን አይደለም... ሆስፒታላችን የልምድ ልውውጥ ሌላ ከተማ ሊልከኝ ነው። ከአስራ አምስት ቀን በኋላ እመለሳለሁ ያኔ እናወራለን" መኪናዬን አስነስቼ ወጣሁ

ሳሎን ቁጭ ብለን ከታሪኬ ሀ ጀመርኩለት
"የአስራ ሶስት አመት ልጅ እያለሁ ነው........." ሁሉንም አንድ በአንድ ዘርዝሬ ነገርኩት ከሱ ግን ያላሰብኩትን ነገር ሰማሁ

"እና ያኔ የደፈርኩት አንቺን ነበር"

"ምን? ምንድነው የምታወራው?"

"ብርቄን ታውቂያታለሽ? ጎረቤታችሁ ናት መሰለኝ"

"አዎ ብርቄን ከነ ነገሯ የማያውቅ አለ እንዴ... ግን አንተ እንዴት?"

"የዩንቨርስቲ ተማሪ እያለሁ እናቴ የማልወዳት አክስቴ ጋ መልዕክት ይዘህ ሂድ ብላ ላከችኝ... እረፍት ስለነበርንም እየተነጫነጭኩ ብርቄ ጋ መጣሁ።
በዛውም ከአክስቴ ጎረቤት ልጅ ዘመናይ ጋር ተዋወቅሁ። በሁለት ቀን ውስጥ ተዋደን ሴክስ አደረግን( አውቃታለሁ አገር ያወቃት ወንድ አሳዳጅ ናት አልገረመኝም ) የዛን እለት ግን እዛ የጭቃ ቤት ውስጥ እያለን ወደኛ የሚመጣ ሰው ድምፅ ሰማን እና እሷ ቶሎ ብላ ወጥታ ሄደች እኔ ግን እዛው ቀረሁ። በወሲብ ስሜት ጦዤ ስወጣ አንቺን ከሩቅ አየሁሽ እና ጠራሁሽ.... ያ ሁሉ ነገር ተፈጠረ" ከነገረኝ ታሪክ ውስጥ አንድ አስደሳች ነገር አገኘሁ... የእንቁን እውነተኛ አባት

"አክስቴ እኔ እንደደፈርኩሽ ስታውቅ... ማንም ሳያየኝ በሌሊት ሀገሩን ለቅቄ እንድሄድ ድጋሚም እንዳልመለስ አስጠንቅቃ ወደ እናቴ ላከችኝ። በሶስት ቀን ቆይታዬ ብዙ ታሪክ ፈጥሬ ተመለስኩ"
' ሳትፈልግ ማን ሊነካት' እያለች ስታወራ የነበረችውን ብርቄን አሰብኳትና ተገረምኩ ወዲያው ደግሞ ደስ የሚለውን ሁኔታ አሰብኩት

"ደስ ሲል" ሳላስበው ቃል ከአፌ ወጣ

"ምኑ ነው ደስ የሚለው የኔ አንቺን መበደል ድሮ እንደጀመረ ማወቅሽ ነው" ግራ ግብት ብሎት ያየኛል

"እንቁ እውነተኛ አባቷን ማግኘቷ"

"ማለት...? ምን እያልሽን ነው? ምናሴ የኔ ልጅ... አይ አይሆንም... ማለት ተደፍረሽ ነው የወለድሻት...? አይ ውሸትሺን ነው።"

መልስ ሳልሰጠው እየሮጥኩ እንቁ መኝታ ቤት ገባሁ ቁጭ ብላ እያነበበች ነው። ስገባ ቀና ብላ አየችኝ

" ምን ተገኘ ማሚ ፊትሽ እኮ በፈገግታ ሊፈነዳ ነው"

"የተገኘውማ አባትሽ ነው"

"የእውነት...(እንባዋ ኮለል ብሎ ወረደ ሰፍ ብላ አፍ አፌን አየችኝ) የት ነው ያለው ማሚ... የኔ አባት የት ነው?( ሳግ አነቃት) ማሚ በተለይ በዚህ ሰዓት አባቴን በጣም እፈልገዋለሁ... እማ ንገሪኛ..."

"ዮኒ እውነተኛ አባትሽ ነው" አንገቷን ወደኔ አስግጋ ሁለመናዋ ጆሮ ሆኖ በአይኗ ሳይቀር ስትማፀነኝ የነበረችው ልጄ ከኣካሏ እኩል ስብር ስትል አየኋት

"እሱ አባቴ አይደለም... ትክክለኛ አባቴን የአብራኩ ክፋይ የሆንኩትን ሰው ነው የምፈልገው" አለችኝ እንዳቀረቀረች

"አዎ የኔ እንቁ አንቺ የዮኒ የአብራኩ ክፋይ ነሽ ታሪኩን እነግርሻለሁ። የአስራ ሶስት አመት ልጅ እያለሁ..." ዝምምም ብላ ሰማችኝ... ምንም አይነት እንቅስቃሴም ሆነ ንግግር አላደረገችም... ዝምምምም.... አውርቼ ስጨርስ

"ደስ አይልም የኔ እንቁ" አልኳት እንባዋ ገደቡን ጥሶ ወረደ 'ምንድነው እንቁ ለምንድነው የምታለቅሺው'

"ደስ ብሎኝ ነው እማ... የደስታ እምባ ነው። ነይ እቀፊኝ" ተቃቀፍንና

"በቃ ይሄን ቀን ፏ አድርገን እናከብረዋለን ነይ ተነሺ" እጇን ይዤ አስነሳኋትና ወደ ሳሎን ሄድን ዮኒ የለም... መኝታ ቤት አየሁት የለም... ቤት ውስጥ የለም... ለአንድ ቀን ብቻ ሳይሆን ለሳምንታት የለም...

የሆነኛው ቀን ሌሊት ላይ ስልክ ተደውሎልኝ ዮኒ ያለበትን ቦታ ነገሩኝ... ጭፈራ ቤት ነው። ስሄድ ከሁለት ሴቶች ጋ አብሮ እያበደ ነው... ምንም ሳልል ወደቤቴ ተመለስኩ... ለራሴ ግን አንድ ውሳኔ ወስኜ ነበር 'ተመልሶ እዚህ ቤት አይረግጥም'። ብቸኝነት ተሰማኝ... ቅዝቃዜው አንዘፈዘፈኝ.. እናም ብቸኛዋ እንቁዬ ጋ ልሸሸግ ወደሷ መኝታ ቤት ሄድኩ። በሩን ከፍቼ ስገባ ግን የኔ እንቁ መሬት ላይ ተዘርራ አየኋት ጮኩ። እልፍነሽ ስትሮጥ መጣች... ከመሬት አንስተን አልጋ ላይ ካደረግናት በኋላ የልብ ምቷን አየሁት... ቆሟል... አፏን አሸተትኩት ገዳይ መርዝ ጠጥታለች። ሰውነቷን ነካሁት ከበረዶ ቀዝቅዛለች...
የኔ እንቁ የለችም... ትታኝ ሄዳለች...

ይቀጥላል
👍84😢31🤔87😱7👏1
አሮሯ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _ሁለት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
🚲🚲🚲🚲
መንግስቱ ዛሬ ከሶስት አመት የእስር ቆይታ በኃላ ከእስር  የሚወጣበት የነፃነቱ ቀን ነው።ለዛም እየተዘጋጀ ነው ።ለብሶት ያደረውን ቢጃማ አወለቀ። ከወገብ በላይ እራቁቱን ሆኖ ከአሮጌ ሻንጣው ውስጥ የተሻለ ያለውን ልብስ እየመረጠ ነው።መንግስቱ እስር ቤት ከመግባቱም በፊት ዘለግ ያለ ቁመትና ፈርጠም ያለ ሰውነት ያለው የ31 ዓመት ወጣት ሲሆን እስር ቤት ከገባ በኃላም ያንን ሰውነት በእስፓርት ፈርጣማና በጡንቻ የዳበረ እንዲሆን አድርጓታል።በዛ የደረጀ ሰውነቱ ላይ ደረቱ አካባቢ ወደ ግራ ልብ ዘንበል ያለ የሴት  ምስል ተነቅሶበታል ።ከጀርባው ደግሞ ከመቶ ሜትር ርቀት በሚነበብ ድምቀትና መጠን "አሮራ ፍቅር"የሚል ሌላ ንቅሳት አለበት።ይህቺ አሮሯ የልብ ሰው ነች።ክፍኛ ያፈቀራት የውስጥ እሳቱና የልብ ትኩሳት  ነች።ሶስት አመት የታሰረላት ሴት ። ልብሱን ለብሶ ሲጨርስ ሻንጣውን መልሶ ዘጋጋና ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
መቼስ ለማንም ሰው ቢሆን ከእስር  መለቀቅ የተለየ አይነት ስሜት መጫሩ የሚጠበቅ ነው። ግን  ሶስት አመት በእስር ቆይቶ ከሚለቀቅ ሰው ይልቅ ሶስት ሳምንት ታስሮ ሊፈታ ያለ ሰው የበለጠ  እንደሚደሠትና በመፈታቱ ፈንጠዝያ ተሰምቶት አምላኩን እንደሚያመሠግን  ብዙ ሰው አያውቅም።አንድ ሰው ሶስት ሳምንት እስር ቤት ቢያሳልፍ እስር ሳይሆን እረፍት ነው ሚሆንለት።አዲስ ልምድ ያገኝበታል ፣ጥቂት ማሰቢያ ጊዜ... የተወሰነ መረጋጊያ ስፋራ  አግኝቶ  ከነበረበት የህይወት  ግርግር ገለል በማለት ከራሱ ጋር ስብሰባ እንደተቀመጠ ነው የሚቆጠረው እና ከዛ  ሲለቀቅ ከሞላ ጎደል ሁሉን ነገር በተወበት ቦታ  እንደነበረው ነው የሚጠብቀው።።እንዲህ እንደ መንግስቱ ሶስት አመት የታሰረ  ሰው ግን ትፈታለህ ሲባል ጭው የሚያደርግ ብዠታ ውስጥ ነው የሚገባው። "ተፈትቼስ እንዴት ነው የምሆነው?ምን ሰርቼስ እኖራለሁ?"ሲል ይጠይቃል።አዎ  አሁን  መንግስቱ ደጋግሞ በአእምሮ እያመላለሳት ያለውን ጥያቄ ብዙዎቹ የእሱ ቢጤ ከረጅም እስር በኃላ የሚፈቱ ታራሚዎች ሁሉ ይጠይቁታል።
መንግስቱ  ሶስት አመት በእስር በማሳለፉ ምክንያት ከስራ ተፈናቅሏል።አሁን ከእስር እንደወጣ የድሮ መስሪያ ቤቱ ሄዶ ወደስራዬ መልሱኝ ብሎ ቢጠይቅ ከመልሳቸው ቀድሞ ሳቃቸው እንደሚያመልጣቸው እርግጠኛ ነው።ለአመታት ባንክ ደብተሩ ላይ አጠራቅሞት የነበረውን ብርም አንድ ሁለት እያለ አውጥቶ ጨርስታል።በተለይ በተከሰሰበት ወንጀል ከ10-15 አመት  እንዲቀጣ ትግል ያደረግበት የነበረውን በአሮራ አባት የተቀጠረው የከሳሽ ጠበቃን  በመፋለም ከተራዘመ አሰልቺ ክርክር  በኃላ ወደ አምስት አመት እስር ዝቅ አስደርጎ ለማስወሰን በአመክሮም በሶስት አመት ለመውጣት  ላስቻለው  ጠበቃው ከፍተኛ የሚባል ገንዘብ  ከፍሏል።

አሁን  ይህን ሁሉ እያሰበ ያለው እስር ቤት ግቢ ውስጥ  ሆኖ ሻንጣውን  በቀኝ ጎኑ አስቀምጦ በእጅ ላይ ያለውን የአሮሯን ፎቶ እያሻሸና  በአትኩሮትና በናፍቆት እያየ" ፓሊሶቹ ናና ውጣ" እስኪሉት በመጠበቅ ላይ እያለ ነው።ይህን ፎቶ ለአንድ ሚሊዬን ጊዜ  ነው  እያየው ያለው ።አሮሯ የጥቁር ፈርጥ ዕንቁ መልክ ያላት ዝነኛ እና ቆንጆ ልጅ ነች። ብዙ ጊዜ ኮስታራ ግን ደግሞ ከቀናቶች አንድ ቀን እንደው ተሳስታ ፈገግ ስትል የጥርሶቾ ንጣት ከፊቷ ጥቁረት ጋር  እና ከአይኖቾ ፍካት ጋር ያለቸው ህብራዊ ስምምነት እንደው ልብን ድንዝዝ ወይም ፍስስ የሚያደርግ ልዩና አጠቃላይ ሁለንተናውን  የማቅለጥ ኃይል ያላት አስማት የሆነች ወጣት ነች።
ይሄን ሁሉ ስለእሷ መልክና ቁመና ያጠናው ፍቅረኛው አድርጎ ቀርቦትና  እርቃን እሷነቷን እያገላበጠ ስላየ   አይደለም። በርቁ ስለሚያፈቅራት ነው።ባታስበውም ያለማቋረጥ ስለሚናፍቃት ነው።የለሊት ህልሙና የመላ ህይወቱ እቅድ ስለሆነች ቀኑንም ሆነ ሌቱን በአእምሮ እየተገለባበጠች ስለምታሳልፍ ነው።

አሁን በኪሱ ጥቂት ገንዘብ አለው።ይሄን ገንዘብ  እዚሁ ወህኒ ቤት የእንጨት ስራ በመስራት ካገኘው ገንዘብ የቆጠበው ነው።ይሄንን ሞያ እዚሁ እስር ቤት የተማረው ነው።ሲወጣም ምን አልባት እራሱን ሊያኖርበት የሚችለው   የተሻለው ተስፋው ይሄ ሞያ ነው። ዘመዶቹም ጓደኞቹም ከታሰረ በኃላ ለስድስት ወር ያህል እንደነገሩ በተንጠባጠበ ሁኔታ ከጠየቁት በኃላ ቀስ በቀስ እግራቸውን ሰብሰብ አድርገው ጠፍተዋል።እናም እረስተውታል። እናትና አባቱም ከረጅም ጊዜ በፊት ነው የሞቱት።በዚህም የተነሳ  አሁን የሚያስታውሰውና እየናፈቀ ያስቸገረው አንድም ሰው በምናብ የለም።ከአሮሯ በስተቀር ሁሉንም ረስቷቸዋል።አዎ አሮሯ ህመሙ ነች።አሮሯ ናፎቆቱ ነች።አሮሯ ረሀብ ነች።አሮሯ በህይወቱ የሆነ ጎኑ እንዲበሰብስበት ያደረገች ..የሆነ ገኑን ደግሞ  ሻማ ለኩሳ የሚንቦገቦግ ብርሀን በውስጡ እንዲረጭ ያደረገች  ሴት ነች..አሮራ።እና ከዚህ እስር ቤት በመውጣቱ ደስ የሚሰኝበት አንድና ብቸኛ ምክንያት  ለመጨረሻ ጊዜ የዛሬ ከሶስት አመት ከመታሰሩ በፊት አይቷት የነበረውን አሮሯን  ዳግመኛ ለማየት ብቻ ነው።እርግጥ እሷ ባለችበት አካባቢ 500 ሜትር በላይ እንዳይቀርባት  በፍርድ ቤት  የተጣለበትን  ገደብ አሁንም አልተነሳለትም።ቢሆንም ከዚህ ይውጣ እንጂ   ለዛ የሆነ መፍትሄ ያበጅለታል።"አሁን ምን ያህል አድጋ  ?ምን ያህልስ ወፍራ ወይም ከስታ ይሆን?"ሲል እራሱን ጠየቀና ፈገግ አለ።

"መንግስቱ ኃይሉ ...መንግስቱ ኃይሉ..."የሚል የፓሊስ የጥሪ ድምፅ  ከትካዜው አባነነው።
"አቤት"
"ዕቃህን  ያዝና ተከተለኝ...ልትወጣ ነው።"ሲል ማይቀረውንና አስፈሪውን የምስራች አበሰረው።ቶሎ አለና ፎቶውን ደረት ኪሱ በመክት ሻንጣውን ይዞ የስር ቤት ጓደኞቹን በየተራ እያቀፈ ለመጨረሻ ጊዜ ተሠናብቶ  ሻንጣውን በመያዝ ፓሊሱን ተከትሎ ወጣ። ወደአስተዳደር ቢሮ ነው ያመሩት።ከእስር ነፃ መለቀቁን የሚገልፅ ደብዳቤ ተቀበለና ከግቢው እንዲወጣ ተደረገ።
አሁን እዚህ ቦታ ሄዳለሁ የሚለው የተለየ ስፍራ የለውም። ወደድሮ ሰፈሩም የሚሄድበት ምንም ምክንያት እየታየው አይደለም። ከወላጇቹ የወረሰውንም እቤት ከመታሰሩ በፊት ነው በረጅም ጊዜ ኮንትራት ያከራየው።ስለዚህ ለጊዜው የእሱ አይደለም። አሁን ማድረግ የሚችለው ባገኘው በመጀመሪያው ታክሲ ወይም ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ይሄን ሰፈር መልቀቅ ፤ከዛ ታክሲው በሚቆምበት የመጀመሪያው ወይም ሁለተኛ ፌርማታ ላይ መውረድና በአካባቢው ዞር ዞር ብሎ ኪሱን የሚመጥን ቤርጎ ፈልጎ መከራየት ...ከዛ አንድ ሁለት ቀን አርፎ መረጋጋት፣አሮሯን አፈላልጎ በሩቁም ቢሆን ማየት ... ከዛ ስራ ፈልጎ መቀጠር...እንደዛ እንደዛ እያለ ቀስ በቀስ ህይወቱን በአዲስ መልክ  ማስተካከል ...አዎ እቅድ እንደዛ ነው።

ከማረሚያ ቤቱ ቅፅር ግቢ መቶ ሜትር ተጓዘና ታክሲዎች እና  ባጃጆች የሚራኮቱበት ስፍራ ደረሰ።ወደ ታክሲ  ልግባ ፈይስ ወደ ባጃጅ ?እያለ ከራሱ ጋር ሙግት ገጥሞ ባለበት ሰዓት ከወደቀኝ በኩል  ደመቅ ያለ የመኪና ክላክስ  ጥሪ ሰማ።ሳያስበው ዞር ብሎ እይታውን ወደዛ ሲልክ  በመቶ ሜትር ርቀት አጥር ታካ የቆመች የተወለወለች አዲስ አይጥማ ከሮላ መኪና ተመለከተ።በመኪናው የኃላ ገቢና የተቀመጠች አንድ ብስል ቀይ ሴት  አንገቷን በመስኮት አስግጋ በማውጣት  እጆቾን ወደእሱ እያርገበገበች ወደ መኪናዋ  እንዲመጣ ምልክት እያሳየችው ነው።ግራ ገባው።ወደጀርባው ዞር ዞር  አለና ሌላ ሰው ይሆን እንዴ የምትጠራው? የሚለውን ጥርጣሬ ለማረጋገጥ ሞከረ።ማንም ከጀርባው
👍656🔥2👏1😁1
የለም።መልሶ ፊቱን ወደሴትዬዎ አዞረ።አሁንም ጥሪዋን አላቋረጠችም... እጆቹን አንከረፈፈና ጣቶቹን ወደደረቱ  በመጠቆም "እኔን ነው?"የሚል   ምልክት አሳያት።
እሱን እንደሆነ ግንባሯን በመነቅነቅ አረጋገጠችላት።መልኳ በግልፅ እየታየው ስላልሆነ ማንነቷን ፈፅሞ ማወቅ አልቻለም።
እግሩን አንቀሳቀሰ ።... ፈራ ተባ በሆነ እርምጃ ወደ መኪናዋ ማዝገም ጀመረ።


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍409👏1
#ህያብ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_በኤርሚ



#ከጊዜያት_በኋላ

"ንገሪኝ እስኪ ህያብ ሀኪም እንዲያይሽ ባትፈልጊም ህመምሽን ለኔ ንገሪኝ ዝምምም ብዬ እሰማሻለሁ። ስለ ልጅሽ ስለ ዮኒ ስለተፈጠረው ሁሉንም ንገሪኝ" ሶስት ወራትን በዝምታ ስለዚህ ነገር ሳያነሳብኝ ሳላወራው በየጊዜው የአእምሮ ህመሜ እየተነሳ ከኔው እኩል ሲሰቃይ አሳልፈናል። ትዕግስቱ እንክብካቤው ፍቅሩ ድሮ ከማውቀው የበለጠ ተወዳጅ ሆኖ ነው ያገኘሁት። ግን ምን ዋጋ አለው ፍቅር አንዳንዴ ፍትሀዊ አይደለም ቢሆንማ ኖሮ የማፈቅረው ዮኒን ሳይሆን ቢኒን ነበር። ወደ መኝታ ቤት ሄድኩ... ተከተለኝ... በሩን ከፍቼ ገባሁና ቤቴ ሄደን ካመጣናቸው እቃዎች መሀል አነስተኛውን ሻንጣዬን አወረድኩት... ከፈትኩት... ውስጡ ያለው ሁሉም የልጄ ማስታወሻ ነው። ለአዲስ አመት የሳለችልኝን አበባ አገኘሁት... እሱን አቅፌ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ

"የኔ ልጅ... የኔ እንቁ... ናፈቅሽኝ እኮ" ቢኒ አጠገቤ ብርክክ ብሎ ትከሻዬን ያዘኝ ከዛም ወደራሱ አስጠግቶ አቀፈኝ። ህመሜ ሳይነሳ ለመጀመሪያ ጊዜ ራሴን አረጋጋሁና ከእቅፉ ወጥቼ ከመፅሀፍ መሀል አጣጥፌ ያስቀመጥኩትን ደብዳቤ አወጣሁት... ከባዱን መርዶ ያረዳኝን... መራራውን እውነታ የጋተኝን ደብዳቤ አወጣሁና ለቢኒ ሰጠሁት። ግራ በተጋባ ፊት ካየኝ በኋላ ከፈተው... ደጋግሜ ከማንበቤ የተነሳ እያንዳንዱን ቃል እንደ ውዳሴ ማርያም የሸመደድኩትን ደብዳቤ እሱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊያነበው ከፈተው... እንዲህ ነው የሚለው...

"ማሚ ከበደል ሁሉ የቱ እንደሚከፋ ታውቂያለሽ... አባቴ የምትይው ሰው በስሜት ጦዞ ጭንሽን ሊከፍት ሲታገል ማየቱ...... ማም እውነቱ ይገልሻል አውቃለሁ ...ግን እንደዛ ጠንካራ ስነ ልቦና እንዲኖራት አድርገሽ ያሳደግሻት ልጅሽ ለምን ራሷን አጠፋች? የሚለው ጥያቄም ይገልሻል። ማም እውነቱን እወቂው..... መጀመሪያ የውሸት ቆይቶ ደግሞ የእውነት አባት የሆነኝ ዮኒ የውሸት አባቴ እያለ አንዴ ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ ደፍሮኛል። ታስታውሻለሽ ያኔ ፔሬድ አሞኝ ነው ብዬሽ የተኛሁ ጊዜ... ለመጀመሪያ ጊዜ የደፈረኝ ቀን ነበር። አንቺ ውስጥ እያለሽ ሊጠይቀኝ ሲመጣ ፊቴን አዙሬበት ነበር አይደል? ከዛ አንቺ ወጣሽ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ 'በሶስተኛው ቀን መድገም አለብን ካላዛ ተደፍነሽ ትቀሪያለሽ' አለኝ። እናም በሶስተኛው ቀን መኝታ ቤቴ ድረስ መጣ... መከላከል ደከመኝ እና በዝምታ አየሁት ሳይራራልኝ እላዬ ላይ ጨፍሮ ሄደ... ያንኑ ድርጊቱን የአባትነት እውነታው እስከሚታወቅ ድረስ ደጋገመው። በተለይ ፊልድ መውጣትሽ ለሱ ምቹ ሁኔታ ለኔ ደግሞ ስቃይን ፈጠረ

ካንቺ ፊት ላይ የየሁትን ደስታ እኔ ጋር ፈልጌ አጣሁት። ማም እንዴት ልደሰት... አባቴን አገኘሁ ብዬ እንዴት ደስ ይበለኝ...? አባትነቱን እኮ ጭኔ መሀል ቆፍሮ ቀብሮታል። እናም አባቴ አይደለም ሊሆንም አይችልም ብዬ በዝምታ ተሸብቤ ቁጭ ብዬ እያለ ሌላ ክስተት ተፈጠረ። በየጊዜው እየመጣ ይቅርታ ብሎኝ 'አደራ ለናትሽ እንዳትነግሪያት' ከሚለኝ ከህሊናቢሱ አባቴ የስምንት ሳምንት ነብሰ ጡር እንደሆንኩ ሆስፒታል አረጋገጥኩ። ያኔ በራሴ ላይ ወሰንኩ... ታሪክ ራሱን አይደግምም... ማም አንቺ አባት እንደሌለኝ እያሰብሽ ወልደሽ እሳደግሺኝ... የኔ ልጅ አባት ግን አባቴ ነው... እናም በራሴ ላይ እና ባልወለድኩት የአባቴ ልጅ ላይ የሞት ፍርድ ወሰንኩ።

ማሚዬ ለኔ ስትይ ጠንክረሽ ኑሪ እወድሻለሁ።
እድለቢሷ ልጅሽ"

ደብዳቤውን አንብቦ ከጨረሰ ቢቆይም እንባ ከአይኖቹ እየወረደ ፍዝዝ ብሎ ተቀምጧል።

"ይህን ደብዳቤ ሳገኘው ቢኒ ጊዜው ረፍዷል... የልጄ ገዳይ አጠገቤ አልነበረም... ትቶኝ ሄዶ ነበር... ፈለኩት በየሆስፒታሉ በየሆቴሉ ግን አጣሁት... ባገኘው በአደባባይ ስጋውም ዘልዝዬ ለአሞራ እሰጠው ነበር"። እያለቀሰ መጥቶ አቀፈኝ ረጅም ሰአት ተቃቅፈን ተላቀስን...።

"እባክሽ አንድ ነገር እሺ በይኝ የስነልቦና ሀኪም ይይሽ እባክሽ ለኔ ስትይ" ለብዙ ጊዜ ደጋግሞ ቢጨቀጭቀኝም እምቢ ነበር መልሴ

"እሺ ደስ ያለህ ሀኪም ጋ ውሰደኝ"

።።።።። ።።።።። ።።።። ።።።።። ።።።

የስነ ልቦና ህክምናዬን ከጀመርኩ አንድ ሳምንት ቢያልፈኝም ለዶክተሬ ምንም የነገርኩት ነገር አልነበረም። የሆነ ቀን ግን ልክ ከዚህ በፊት ያለውን ታሪክ እንደሚያውቀው ሁሉ

"ዮኒን ብቻ ጥፋተኛ አድርጌ እንዳልፈርድ የሚያደርገኝ እንደዚህ ያሳመመኝ ብዙ ፀፀት ውስጤ አለ። ብዙ ቢሆን ኖሮ.... ብዙ.... ብዙ....

•ከመጀመሪያው ታሪኬን ነግሬው ቢሆን ኖሮ

•ስራ ስራ ማለቴን ትቼ ለልጄ ጊዜ ሰጥቻት ቢሆን ኖሮ

•እንደዛ ሆና እያየኋት ትንሽ እንኳን ለምን አልተጠራጠርኩም... አሁን እኔ ዶክተር እባላለሁ...

ከሁሉም በላይ ፀፀቱ በልቶ ጨረሰኝ... መገጣጠሚያ አጥንቴ እስከሚታይ ከሳሁ... ጠቆርኩ... ታመምኩ... አበድኩ ...ግን ትርጉም አልነበረውም... እኝህ ሁሉ የኔን እንቁ አይመልሱልኝም ባዶ... አንተስ የኔን እንቁ ትመልስልኛለህ? አየህ እዚህ መጥቼ መፋጠጣችንም ትርጉም የለውም ባዶ..." አልኩት። ዝምምም ብሎ ካየኝ በኋላ ከወንበሩ ተነስቶ መጥቶ ፊት ለፊቴ ሶፋ ላይ ተቀመጠ

ከስድስት ወራት ያላሰለሰ የህክምና ክትትል በኋላ ወደራሴ ተመለስኩ ወደ ስራየም ጭምር። ከቢኒ ጋር ደስ የሚል የፍቅር ግንኙነት ጀመርኩ... ህይወት ድጋሚ ቀጠለች። ያለፈው ባይረሳም ህመሙ ቀንሷል... የልቤ በልቤ ተቀብሮ መሳቅ ቻልኩ።

ከቢኒ ጋ ልንጋባ ነው ማለትም ከሁለት ወር በኋላ እንጋባለን። ለፊርማው እንጂ የምንኖረው አንድ ቤት የምንተኛው አንድ አልጋ ላይ ከተጋባን ቆይተናል ለማለት ነው። ልንጋባ መሆኑን ያወቀው ሀብታሙ ካለበት ሀገረ አሜሪካ የሚያምር ቬሎና ሱፍ ልኮልናል። ለቢኒ ሚዜ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ።

የሆነኛው ሌሊት ላይ ተኝቼ ልጄን በህልሜ አየኋት... ብቻዋን አይደለም ዮኒ ሲደፍራት "ድረሽልኝ" እያለች ስትጮህ... ጮኬ ከእንቅልፌ ነቃሁ... አጠገቤ የተኛው ቢኒ ጩኸቴ አስደንግጦት

"ምንድነው ፍቅር አይዞሽ ቅዠት ነው" አለና እቅፉ ውስት ከተተኝ... እኔ ግን የበቀል ጥሜ ድጋሚ አንሰራራ... እፈልገዋለሁ እናም እገለዋለሁ... እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ።

ለቀናት በሀሳብ ተብሰከሰኩ እናም ወሰንኩ ይህን ነገር ከስሩ መንግዬ መጣል ይኖርብኛል። ተቆርጦ ባቆጠቆጠ ቁጥር ህመሙ እየባሰ ነው የሚሄደው ስለዚህ እ ገ ለ ዋ ለ ው

#አሁን

ትቼው ልሄድ ነው። በቃ ልሄድ ነው የመጨረሻ ውሳኔዬን ወስኛለሁ የምሄደው እንደ ሌላው ጊዜ ጥላቻንና ክህደትን ሽሽት አይደለም... ፍቅርን እንጂ።
እናም በሀሳብ እየዋዠኩ ደብዳቤ ልፅፍለት ወሰንኩ ቢያንስ ምክንያቴን ማሳወቅ አለብኝ አይደል... ደግሞ ጠፋች ብሎ ሀገር ምድሩን ነው የሚያምሰው...

መፃፍ ጀመርኩ

"አንዳንዴ ልቋቋመው ከምችለው በላይ ይሆንብኛል። ፍቅርህ፣ ስስትህ፣ እንክብካቤህ፣ አንተን ትተህ ለኔ ደስታ መድከምህ፣ ከቃላት ጋጋታ ይልቅ በተግባር የምታሳየኝ መውደድህ በአጠቃላይ ሁሉም ነገርህን መቋቋም ያቅተኛል።
👍7414🔥2😁1
ሰው እንዴት ይህን ያክል ሰውን ሊወድ ይችላል እንዴትስ ሁሉ ነገሩ ፍቅር ብቻ ይሆናል ፍቅር... ፍቅር... አሁንም ፍቅር.... አንተጋ ያለው ፍቅር ብቻ ነው እኔጋ ደግሞ ላንተ ያለኝን ፍቅር ሊፈታተን የሚችል የበቀል ጥም አለ። ያንተ ፍቅር እና የኔ በቀል ጥም ተጣጥመው ሊሄዱ አይችሉም ስለሆነም ጥሜን ልቆርጠው ፍቅርህን መሸሽ መርጫለሁ። ያጣሁት ልጄን... ማያዬን... እንቁዬን... ሁሉ ነገሬን ነው። ገዳይዋን ሳልገድል እረፍት እይሰማኝም። አዝናለሁ ቢኒ...

አፈቅርሀለሁ ግን ልሄድ ነው። ትቼህ ልሄድ ነው... ጠንካራ ነህ ትወጣዋለህ።

ደህና ሁን
ህያብ"

ደብዳቤውን ፅፌ ከጨረስኩ በኋላ አጥፌ ፊት ለፊት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጥኩትና ሻወር ልወስድ ገባሁ። ቢኒ ቶሎ እንደማይመጣ ስለማውቅ ዘና ብያለሁ... ታጥቤ ፎጣዬን እንዳሸረጥኩ ስወጣ ቢኒን አልጋ ላይ ቁጭ ብሎ አገኘሁት በእጁ የፃፍኩትን ደብዳቤ ይዟል።

"ምንድነው ፍቅር? ድጋሚ ወደኋላ... ለምን እኔንስ ታደክሚኛለሽ አላሳዝንሽም" አለኝ አጠገቤ መጥቶ አይን አይኔን እያየኝ

"ልጄን በህልሜ አየኋት ቢኒ... አድኚኝ እያለች ስትጮህ አየኋት... ልጄ ከመሬት ስር ተቀብራ...(ሳግ አነቀኝ) አፈር ተጭኖባት እሱ ግን እየተነፈሰ ነው። እፈልገዋለሁ እናም በእጄ እገለዋለሁ" እልሄ ልኩን አለፈ... ፎጣዬን ጥዬ ልብሴን ለባበስኩና ሻንጣዬን ይዤ ልወጣ ስል።

"ዮኒን አግኝቼዋለሁ" አለኝ። ባለሁበት ቀጥ ብዬ ቆምኩ

"ምን?"

"ይሄን በቀል የተውሽ መስሎኝ ነበር ግን ከፈለግሽ አብሬሽ እሄዳለሁ ያለበትንም አሳይሻለሁ ስትገይውም ቆሜ አይሻለሁ።"

"የት ነው ያለው ቦታውን ብቻ ንገረኝ ብቻዬን እሄዳለሁ"

"እሱን እንዳታስቢው ወይም ራስሽ ፈልገሽ አግኝው... ደግሞ አታገኝውም" አማራጭ የለኝም ሻንጣዬን ይዤ ወደኋላ ተመለስኩ።

"እሺ ውሰደኝ አሁን ውሰደኝ"

"አይ አይሆንም ነገ ነው የምንሄደው" በእሽታ አንገቴን ነቀነኩለት።

ወደቀኝ ገልመጥ ብዬ ሳይ የሰርግ ቬሎዬ ተሰቅሏል። ለራሴ ወደኋላ የለም አልኩ...

ይቀጥላል
👍7710👎3🤔3😢3😁2🔥1
አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _3
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ሊሄድ በመነሳቱ ቅር ብሏት"አጎቴ ደግሞ...እዚሁ ምትፈልገውን መጠጥ ያምጡልህ "አለችው።
አልተስማማም"አይ የዚህ ቤት መጠጥ ውስኪ.. ቢራ ምናምን ነው ..እኔ ምፈልገው ካቲካላ ነው።"አላት።
"እሺ ግን በልክ ጠጣ ...አብዝተህ ጠጥተህ ብኃላ  ቢያምህ በጣም እበሳጭብሀለሁ።"
"እቪ ሮሪ "አለና እንደልማድ ቦርሳዋን በመክፈት ...የተወሰኑ ብሮችን መዘዝ አደረገና ኪሱ ከቶ...ግንባሯን ስሞ ወጥቶ ሄደ።እሷም በተቀመጠችበት ቦታ ሆነ በስስት አይኗ ሸኘችው።ከዛ ጠረጴዛው ላይ ትቶት የሄደውን ሲጋራ አነሳችና አንድ መዛ ለኮሰች...ከዛ ማጨስ ጀመረች...የረሳ መስሎ አውቆ ለእሷ ሲል ትቶላት እንደሄደ ታውቃለች።ሁሌ እንደዛ ነው የሚያደርገው።የእሷ ተወዳጅ የልብ አውቃ አጎት።

ከምታጨሰው ሲጋራ ጭስ እየትጎለጎለ ሄዶ በአየር ላይ ሲበተን ማየት ያስደስታታል።እሷም የውስጥ ህመሟና የልብ ሀዘኗ አንድ ቀን እንዲህ ከውስጧ ተመዘ ወጥቶ በአየር ላይ ተበትኖላት ነፃና ደስተኛ ሆነ ለአንድ ወር እንኳን ሰላማዊ ህይወት ኖራ ሰላማዊ ሞት ብትሞት ደስ ይላታል።በውስጧ የተዳፈነው ሚስጥር ውስጧን በልቶ ሊጨርሳት ነው።
ሁል ጊዜ በልባችን አርቀን የቀበርነው ምስጢር ከሌላ ከማንም ሰው ጋር አንስተን ልንነጋገርበት  የማንችለው ስውር ገበናችን እያንዳንዶን ቀን በውስጣችን  የሚኖረው እኛኑ እየበላ ነው።ልባችንን ይቀረጣጥፋታል ነፍሳችንን በስለታም ጥርሱ ያደቃታል...አዎ ሄዶ ሄዶ መፍትሄ ማናገኝለት ከሆነ ሙሉ በሙሉ ይውጠናል።ምናችንንም አያስቀር ነፍሳችንንም ስጋችንንም ሰልቅጦ በመዋጥ ከህልውና መዝገብ ላይ ያጠፋናል።

እናም አሮራ ይሄ በደንብ ይታወቃታል የገዛ ምስጢሯ ማንም እንዳያስተውለው ማንም እንዳይረዳው እታች ጥልቅ ንብርብር ልቧ ውስጥ እንደቀበረችው ብታውቅም ከዛ አፈንግጦ በመውጣት ከአንጀቷ ሙዳ ስጋ ዘንጥሎ ወደቦታው ሲመለስ በደንብ ይታወቃታል በሌላ ቀን ደግሞ ወደጨጓራዋ ሄዶ የላይ ንብርብርና ሻካራ ክፍሉን ሞዣልቆ ሲያነሳውና ሲሠለቅጠው በደንብ ይሰማታል።ድንዛዜውና ቀጠሎ  መፈጠሯን እስክጠላ ያሰቃያታል።ብቻ በአጠቃላይ በውስጧ አውሬ እያሳደገች ነው።እሷን እየተመገበ በማደግ ላይ ያለ አውሬ።እሷ እንዲህ የተሠቃየች አባቷስ እንዴት ነው መኖር የቻለው?ሁል ጊዜ በውስጧ የሚላወስ ጥያቄ ነው።እንደሷ ሲያዝንና ሲተክዝ እንኳን አይታው አታውቅም።ሁል ጊዜ እንደሮጠ ሁል ጊዜ የሆነ ገንዘብ ለማግኘት...የሆነ ኃይል ለመጨበጥ...የሆነ ተልኮ ለማሳካት እንደባከነ ና እንደተዋከበ ነው።ስለውስጥ ህመሙና ስለልብ ስቃዩ ማሰቢያ ጊዜም ያለው አይመስላትም።አረ መታመሙን ራሱ እርግጠኛ ሆና መናገር አትችልም። ከተቀመጠችበት ክፍል ወጣችና ኮሪደሩን አልፋ ታናሽ እህቷ መኝታ ክፍል ሄደች።አንኳኳችን ገፋ አድርጋ ስትገባ እህቷ አልጋዋ ላይ ቁጭ ብላ  የስዕል መሳያ ደብተሯን ዘርግታ የተለያዩ ከለሮችን እየቀባች ነበረ...መጀመሪያ ሞግዚቷ የመጣች መስሎት ቀና አላለችም ነበር
"የእኔ ፅጌረዳ ምን እየሠራሽ ነው?"የሚለውን የእህቷን ድምፅ ስትሰማ ግን እጇ ላይ ያሉትን ከለሮች በትና ደብተሯንም ጥላ ከአልጋዋ ተስፈንጥራ ወረደችን አላዬ ላይ ተጠመጠመችባት።
አሮራም እንጠልጥላ እንዳቀፈቻት ወደአልጋው ወሰደቻትና እሷን አስቀምጣት ከጎኗ ተቀመጠች።

ታናሽ   እህቷ ሳሮን ገና ሰባት አመት ለመድፈን ሁለት ወር ይቀራታል።እናቷ ገና የሁለት አመት ጨቅላ እያለች ነው የሞተችው።በዚህ የተነሳ አሮሯ እንደእህቷ ብቻ ሳይሆን ልክ እንደራሷ ልጅ ነው የምታያት..ከሞግዚቶቹ ጋር በመተጋገዝ በምቾት እንድታድግ የተቻላትን አድርጋለች
ቢያንስ የእናቷ የሙት መንፈስ በእሷ ላይ ያለውን ቅሬታ ሊያለዝብ የሚችልበት አንድ ብቸኛ  የሠራችው ጥሩ ተግባር   ይሄ ታናሽ እህቷን ለማሳደግ የምታደርገው  እንክብካቤ ነው።
ከእህቷ ጋር ብዙ ነገር ከተጫወቱ በኃላ በመሀል የልጠበቀችው አስደንጋጭ ነገር  አንደበቷ ወጣ።
በተኮላተፈ አንደበት"እኔም እንደአንቺ ቶሎ ባድግ ደስ ይለኛል"አለቻት።
አሮሯ ደነገጠችና"የእኔ ውድ ለምንድነው ፈጥነሽ ማደግ የፈለግሽው...?ብዙ ትላልቅ ሰዎች እኮ እንደውም ተመልሰው ልጅ መሆን ነው የሚፈልጉት።"
"እንዴ !!!ልጅ መሆን ምን ሊያደርግላቸው?"
"ትልቅ ስትሆኚ ህይወት እየጠቆረችና እየቆሸሸች ትሄዳለች።ስታድጊ ደስታሽ እየደበዘዘ ሳቅሽ እየፈዘዘ ይመጣል።ትልቅ ስትሆኚ  ሀሳብሽ  በተንኮል የተሞላ ምኞትሽም በራስ ወዳድነት የተሰላ እየሆነብሽ ይሄዳል።"
ትንሽ እህቷ አሮራ ካተናገረቻቸው ነገሮች መካከል አንድም አልገባትም።
"እህቴ ምንድነው ምትይኝ?"
"የተናገርኩትን እርሺው...ለመሆኑ አንቺ እንደእኔ ቶሎ ማደግ የፈለግሽው ለምንድነው?"ስትል መልሳ ጠየቀቻት...የሠማችው መልስ ግን ጭንቅላት የሚያዞር እና ፈፅሞ ያልጠበቀችው ነበር።"አባዬ እንደአንቺ እንዲወደኝ"ነበር ያለቻት።
ይህን ቃል ስትሰማ በአእምሮዋ ደማሚት ነገር ነው የፈነዳው...በጦር ጎንን የመወጋት አይነት  ስቃይ ያለው ስሜት።
ብዙም እርግጠኝነት በማይገለፅበት የድምፅ ቅላፄ "እንዴ ?አባዬ እኳ አንቺን ነው ከእኔ በላይ የሚወድሽ "አለቻት።
"አይ አይደለም...ግን እንደአንቺ ባድግ ካንቺ እኩል ይወደኛል... አብሬው እንድተኛም ይፈቅድልኛል።"ስትላት
ሽምቅቅ አለች።ኩምትርትር አድርጎ ውስጥን የሚቆራርጥና የሚሸረካክት መሠነጣጠቅ።
ትንሽዬ ተወዳጅ እህቷን...የእናቷን አደራ የተሰጠቻት እህቷን ወደራሷ ስባ አቀፈቻት።የእኔ ውድ በደንብ እንድትስሚኝ እፈልጋለሀ
"..እኔ  የራሴ መኝታ ቤት የሌለኝ እና አባቴ መኝታ ክፍል የምተኛው አባቴ ከአንቺ በላይ ስለሚወደኝ ሳይሆን እኔ ስለሚያመኝና ለሊት ተነስቼ መድሀኒት መውስድ ስላለብኝ ሰዓቱን ጠብቄ እንድነሳ አባቴ ስለሚያግዘኝ ነው።እንጂ እንደውም እኔ እንደአንቺ የግሌ የሆነ የሚያምር መኝታ ክፍል   ቢኖረኝ በጣም ደስተኛ እሆን ነበር"አለቻት።አዎ ልትነግራት የምትችለው ይሄንን ብቻ ነው።ይሄንን ምክንያት የኮረጀችው ከአባቷ ነው።ብዙውን ጊዜ እቤቱ ውስጥ ላሉ ሰዎች ደጋግሞ ይሄንን የመድሀኒት ታሪክ ሲያወራ ሰምታለች።እናም እሷም ያንን ምክንያት ደግማ ማውራት ከጀመረች ቆይታለች።እርግጥ ከልብ በሽተዋ ጋር ተያይዞ ብዙውን ጊዜ በተከታታይ የምትወስደው መድሀኒት አላት።ግን አንደኛ መድሀኒቱን ከመተኛቷ በፊት መወሰድ የሚትችለው  ነው።እንደው ለሊት የሚወሰድ ቢሆንም እንኳን አሮራ በፈለገችው ሰዓት በመነሳት የፈለገችውን ነገር የማድረግ ችግር የለባትም።እሱም እንደሚያወራው በዚህ ጉዳይም ረድቷት አያውቅም።
ታናሽ እህቷም መጨናነቋል አውቃ"በቃ ገብቶኛል..ግን አንዳንዴ እኔ ጋር ብተኚ ለሊት ቀስቅሼሽ መድሀኒትሽን አውጥሻለሁ"አለቻት።
"የእኔ ውድ አውቃለሁ..እንዳልሺውም አልፎ አልፎ አብረን የምንተኛበት ሁኔታ እናመቻቻለን... አሁን  ተነሽ ወደሳሎን እንሂድና እራታችንን እንብላ"አለቻት።እየተሳሳቁ ተያይዘው ወደሳሎን ሄድ

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍7813😁3👎1🤔1
#ህያበ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_ኤርሚ

"እሱን እንዳታስቢው ወይም ራስሽ ፈልገሽ አግኝው... ደግሞ አታገኝውም" አማራጭ የለኝም ሻንጣዬን ይዤ ወደኋላ ተመለስኩ።

"እሺ ውሰደኝ አሁን ውሰደኝ"

"አይ አይሆንም ነገ ነው የምንሄደው" በእሽታ አንገቴን ነቀነኩለት።

ወደቀኝ ገልመጥ ብዬ ሳይ የሰርግ ቬሎዬ ተሰቅሏል። ለራሴ ወደኋላ የለም አልኩ...

"አንደርስም እንዴ ደግሞ እኮ አይኔን በጨርቅ አስረህዋል። የት ነው የምንሄደው ራቀብኝ? ያ ውሻ የት ነው ያለው?"

"አይንሽን ከገለጥሽ ከኔ ጋ ትጣያለሽ ማርያምን የምሬን ነው። ታገሽ ትንሽ ነው የቀረን ደርሰናል" ጥቂት ደቂቃ ከተጓዘ በኋላ መኪናውን አቆመው

"አሁን ጨርቁን ማንሳት ትችያለሽ" ቶሎ ብዬ ፈታሁት... ሰው የሌለበት ቦታ ነው።

"ምንድነው ቢኒ እየቀለድክብኝ ነው" ፊቴን አዙሬ በንዴት አየሁት

"ውረጂ.,. ያውልሽ እዛጋ ይታይሻል...( በወዳደቁ ነገሮች የተሰራች ቤት) እዛ ውስጥ አለልሽ ውረጂና የፈለግሽውን አድርጊው" ሳላቅማማ ወረድኩ። በእልህና ንዴት እየተራመድኩ ወደቤቱ ተጠጋሁ ልገባ ስል

"እባቷ ነኝ ባሏ. ... ሀ ሀ ሀ... ንገሩኝ እስኪ እናቷን አግብቶ ልጁን ያስረገዘ አባት ታውቃላችሁ... አታውቁም? ሙትቻ ለምንድነው የምታፈጡብኝ... መልሱልኝ... ኧረ ተውኝ ኡ ኡ ኡ..." ጩኸቱ አስደንግጦኝ ወደኋላ ተመለስኩ። ትንሽ ተራምጄ ቆምኩና ልጄን አሰብኳት "እገለዋለሁ" ወደ ቤቷ ተመለስኩና ከፍቼ ጎንበስ ብዬ ገባሁ። የቤቱ ጠረን ይገፈትራል ሰው የመጣም አልመሰለው ዝምም ብሎ ልፍለፋውን ቀጥሏል። የማላውቃቸውን ብዙ የሴት ስሞች ይጠራል... ያለቅሳል፣ ይስቃል፣ ይራገማል፣ ድንገት ደግሞ አስደንጋጭ ጩኸቱን ይለቀዋል። ለደቂቃዎች ዝምምም ብዬ ሰማሁት... በብዙው የቤቱ ቀዳዳ በሚገባ ብርሀን አየሁት ከድምፁ ውጪ ምኑም እሱን አይመስልም። ልብሱ ተቀዳዷል፣ ፊቱ ጠቁሮ ከሰል መስሏል፣ ፀጉሩ ተንጨባሯል፣ እላዩ ላይ ተፀዳድቶ መሬቱ ጭምር በሽንትና ሰገራ ተበክሏል። ዮኒ እኔ ልሰጠው ካሰብኩት ሞት በላይ በቁሙ ሞቷል... ልቤን ሽው የሚል የሀዘኔታ ጦር ወጋኝ። ወዲያው ደግሞ ልጄን የከዳኋት መሰለኝ... እየሮጥኩ ከቤቱ ወጣሁ... ልፍለፋው ከኋላዬ ይሰማኛል... እያለቀስኩ መኪናውን ከፍቼ ስገባ

"አደረግሺው ህያብ ገደልሽው" አለኝ

"ሞቷል እኮ ቢኒ የሞተን ሰው ድጋሚ እንዴት እገለዋለሁ" ድፍት ብዬ ተንሰቀሰቅሁ

"ቢኒ እባክህ ምንም ሰላም ሊሰማኝ አልቻለም ዮኒን ሆስፒታል እንውሰደው" ደረቱ ላይ ተኝቼ ለቀናት ከራሴ ጋ ስከራከርበት የነበረውን ሀሳብ ነገርኩት

"እኔ የማውቃትም የምወዳትም ህያብ ይቺ ናት ለጠላቷ ሳይቀር የምትራራ። አታስቢ የኔ ቆንጆ ዛሬውኑ እናደርገዋለን" እዛው ቦታ ተመልን ሄድን። ወደዛች ቤት ገባን አጠገቡ ዳቦ ቁጭ ብሏል። ለነፍሱ ያደረ ሰው እንደሚመግበው ገባኝ። መለፍለፉን አላቆመም እንጂ ተዳክሟል... ይዘናቸው የሄድነው ባለሞያዎች በግድ አንስተው ስትሬቸር ላይ አደረጉት... ከኪሱ የተጣጠፈ ወረቀት ወደቀ፤ ቀልጠፍ ብዬ አነሳሁትና ዞር ብዬ ከፈትኩት በትልቁ ርዕስ "ፀፀት" ይላል። ከስሩ ደግሞ "ለማታዩኝ እኔ ግን በየቀኑ ለማያችሁ ለበደልኳችሁ ሁሉ" ይላል... ትርጉም ያለው ነገር ሊሆን ቢችልም ማንበብ አልፈለኩም... ሌላ ሸክም መሸከም አልፈልግም... እጄ ላይ ያለውን ሶስት ገፅ ወረቀት ቀዳድጄ ዱቄት አደረኩትና ለነፋስ ሰጠሁት ብትትንን... አምቡላንስ ውስጥ አስገብተው ይዘውት ሄዱ። ሰላም ተሰማኝ

አዳራሹ በእንግዶች ጢም ብሎ ተሞልቷል። ቃል የሚያገባቡን ቄስ ቦታቸውን ይዘው ተቀምጠዋል።

"በሀዘን በደስታዋ በህመም በጤናዋ..." ቢኒ ቃል ገባ እሱ ያለውን መልሰው እኔንም አስባሉኝ።

የጋብቻ ቀለበት ጣቴ ላይ አደረገልኝ እኔም እንደዛው አደረኩለት.....
ገና ወደሰውነት ቅርፅ ያልተቀየረው የአምስት ሳምንት ልጄ ደስ ብሏት/ብሎት ይሆን ሆዴን ዳበስኩት። የልጄ አባት ቢኒ ፈገግ ብሎ አየኝ

"ተመስገን" አልኩ በልቤ የማያልፉ የመሰሉኝ ሁሉ አለፉ... ዛሬ ደስተኛ ነኝ... ነገን አምላክ ያውቃል።

ተ ፈ ፀ መ
👍11249👏2
አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _4
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
///
መንግስቱ እግሩን አንቀሰቀሰና ወደ መኪናዋ ፈራ ተባ  በሚል እርምጃ ማዝገም ጀመረ….ከመድረሱ በፊት ገቢናው ተከፈተና አንድ ሰው ከውስጥ ተመዞ ወጣ፡፡እንደእሱ ግዙፍና ፈርጣማ ነው፡፡ፈገግ እያለ ወደእሱ መራመድ ጀመረ….ፈፅሞ አይደለም ከእስር ቤት በወጣ በመጀመሪያው ቀን ይቅርና እድሜ ልክም ዳግመኛ አየዋለሁ ብሎ ያልጠበቀው ሰው ነው፡፡አጎቱ፡፡፡የአባቱ  ታናሽ ወንድም።

"በፈጣሪ ይሄ ሰይጣን ሰውዬ ከየት መጣ?››ብሎ  በውስጡ አጉረመረመ፡፡

አጎቱ ወደእሱ መጓዝ ጀምሯል ...መሀከል መንገድ ላይ ተገናኙ ….እላዩ ላይ ተጠመጠበት።በመንሰፍሰፍ እንደናፈቀው የገዛ ልጁ እያገላበጠ ጉንጮቹን ሳመው፡፡ያለምንም ተቃውሞ እንዳደረገው ሆነለት፡፡እንደዛ መሆን ፈልጎ ሳይሆን እየሆነ ያለው ነገር ፈፅሞ ያልጠበቀውና ያልተዘጋጀበት ስለሆነ ምንም አይነት የተቃውሞም ሆነ የትብብር እንቅስቃሴ ማድረግ አልቻለም።….

"አንተ በጣም ትልቅ ሰው ሆነህ የለ እንዴ?እንዴ…. ይገርማል..ለማንኛውም ስለተፈታህ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡"አለና እጅን  ትከሻው  ላይ ጣል አድርጎ  አቅፎት ወደ መኪናው ይዞት ሄደ፡፡ወደመኪናው ሲጠጋ ቀድማ እጆቾን በመኪናው መስታወት አውጥታ እያውለበለበች ስትጠራው የነበረች ሴት መኪናውን ለቃ ወረደች፡፡

"ተዋወቃት ባለቤቴ ነች፡፡"

ለስላሳ እጆን ዘርግታ አይኖቾን እላዩ  ላይ  እያንከባለለች፡፡" ውቢት  እባላለሁ፡፡›"አለችው ።ጨበጣትና "መንግስቱ " አላት፡፡
አጎቱ ሻንጣውን ተቀበለና ከኃላውን በራፍ ከፍቶ ከስቀመጠ በኃላ" በሉ ግቡ እንሂድ"አላቸው።
መንግስቱ  የኃላውን በር ሲከፍት‹‹እስኪ ገቢና ከጎኔ ሁን ››አለው፡፡ሚስቱ ወደነበረችበት የኃላ ወንበር ተመልሳ ስትገባ እሱ አጎቱ እንዳለው ዞረና ፊትለፊት ገቢና ገባ ፡፡መኪናዋ ተንቀሳቀሰች፡፡

"ሶስት አመት ስታሰር አንድ ቀን ታሳስቶ እንኳን ያልጠየቀኝ ዛሬ እንዴት ፈለገኝ..?የመፈቻ ቀኔንስ እንዴት አወቀው…..?ወዴት ነው እየወሰደኝ ያለው?፡፡››በውስጡ የተተረማመሱ ካሉ ጥያቄዎች መካከል ጥቂቶቹ ነበሩ…..።ትንሽም የተረጋጋው ሚስቴ ነች ያላት ሴት አብራው ስላላች እንጂ ብቻውን መጥቶ ቢሆን ኖሮ ከዚህ የከፋ ጥርጣሬ በውስጡ ይፈጠር ነገር "ሊያስገድለው ቢሆንስ?"ገንዘብ በጣም እንደሚወድ ያውቃል…ሀብታ ለመሆን የማይፈነቅለው ድንጋይ እንደሌለ ከዚህ በፊት ደጋግሞ አሳይቶታል።የገዛ አባቱ ላይ ብዙ ብዙ ግፍ ሰርቶበታል…..።መአት ብር ከድቶታል….።በዚህም ምክንያት አባቱ ህመምተኛ እንዲሆን ምክንያት ሆኖል ….ህመሙ ደግሞ ወደሞቱ ሸኘቶታል፡፡ያ ማለት በተዘዋዋሪ ይሄ ከጎኑ የተቀመጠው አጎት ተብዬው ሰው የአባቱ ገዳይ ነው፡፡፡እና ዛሬም የሆነ ጥቅም የሚያስገኝለት ከሆነ እሱንም ከማስገደል ወደኃላ እንደማይል እርግጠኛ ነው፡፡፡"ግን እኔን ቢያስገድል ምን ይጠቀማል;?"ብሎ እራሱን ጠየቀ፡፡ከወላጆቹ የወረሰውን ቤት፡፡አዎ ወደደውም ጠላውም…ቀረቤታ ኖረቻውም አልኖራቸውም በአሁኑ ዘንድ በዝምድና ሰንሰለት ለእሱ ከዚህ ከጎኑ ከተቀመጠው ሰውዬ የሚቀርበው ሰው የለም፡፡ስለዚህ እሱ አንድ ነገር ቢሆን   ከወላጀቹ የወረሰውን ቤት ይገባኛል ብለው ከፊት ከሚሰለፉ ሰዎች ዋነኛው ምንአልባትም ብቸኛው ይሄ ሰው ነው፡፡

"ምነው ሀሳብ ውስጥ ገባህሳ…?.አሁን እኮ ሁሉ ነገር አልፏል….መከራዎቹን ሁሉ ከኃላ ጥለሀቸው ወጥተሀል….ይሄንን የነጻነት አየር ተንፍስ››አለው፡፡

"ለጊዜው ምንም አይነት የነፃነት አይር ወደ ውስጤ እየገባ አይደለም….እንደውም መታፈን ነው እየተሰማኝ ያለው።››ሲል መለሠለት።
አይዞኝ ….እስክትለምደው ነው…..ከአንድ ሁለት ቀን በኃላ ሁሉን ነገር አሪፍ ይሆንልህና ማጣጣም ትጀምራለህ… እኔ አጎትህ እንደዛ አይነት የመታፈን ስሜት አንዲሰማህ አላደርግም..እርግጥ በውስጥህ ብዙ ጥያቄዎች እንዳሉ አውቃለሁ….ግን አታስብ ቀስ በቀስ ጥያቄዎችህን ሁሉ እመልስልሀለው….አሁን እቤት ደርሰናል፡፡ቤተሰቡ ሁላ እየጠበቁህ ነው፡፡ልጀቼን አጎታችሁ ከመቀሌ እየመጣ ነው ነው ያልኮቸው።››ሲል ያልጠበቀውን ሌላ ነገር ነገረው።

"ለምን ዋሸሀቸው?››

‹‹ልጆቼ ከእስር ቤት ነው የወጣው ብላቸው….ብዙ ብዙ ጥያቄ ይጠይቁሀል…ምን አልባት እነዛን ጥያቄዎች ለመመለስ አትፈልግም ይሆናል ብዬ አሰብኩ..እናም ለዛ ነው እውነቱን ያልነገርኳቸው።››

"ምን …አንተም ሴት ደፍሮ ነወ የታሰረው ብለህ ታስባለህ እንዴ?"

"አረ በፍፁም….ግን ያው ሆነም ቀረም በሴት ጉዳይ አይደል የታሰርከው፡፡"

"በሴት ጉዳይ አይደለም…በአሮራ ጉዳይ ነው……አሮራ ፍቅሬ ነች ..አሮራ ህይወቴ ነች….ለእሷ ደጋግሜ እታሰርላታለሁ፡፡አባቶ ከእሷ ሊያርቀኝ ሲፈልግ ብሩን ተጠቅሞ የፈጣራ ወንጀል አዘጋጀና ልጄን ሊደፍራት ብሎ ዘብጥያ አስወረወረኝ…..እኔ ግን አሮራን የምደፍርበት ምንም ምክንያት የለኝም….አሮራ እኮ የእኔ ነች..ማለት ውስጤ ነች ፣ልቤውስጥና  ሰርጋ ከነፍሴ ጭምር ተዳብላለች..እራሴን  ሆናለች…ሰው ቢፈልግስ እራሱን እንዴት ሊደፍር ይችላል….?"

"ይቅርታ በወቅቱ ልደርስልህና ከጎንህ ቆሜ ልታገልልህ ባለመቻሌ በጣም ነው የሚቆጨኝ..ግን ሀገር ውስጥ አልነበርኩም ከመጣሁ በኃላ እራሱ  ሁሉ ነገር ከረፈደ በኃላ ነው ስለተፈጠረው ነገር የሰማሁት ..አይዞኝ እክስሀለው፡፡"

"ችግር የለም….በሆነው ነገር ምንም ቅሬታ የለኝም….ግን ከመቀሌ እንደመጣሁ ለምን ነገርካቸው..ማለቴ ከጎንደር ወይም ከሀዋሳ ለምን አላልካቸውም?››ሲል የገረመውን ነገር ጠየቀው፡፡

"አይ  ዩኒቨርሲት የተማርከው መቀሌ ስለሆነ ስለከተማዋ በጣም ታውቃለህ..ምንም ነገር ቢጠይቁህ ሳትጨናነቅ ታስረዳቸዋለህ ...ለዛ ብዬ ነው መቀሌ ያልኳቸው፡፡"

"ጥሩ ነው…..ስለእኔ ይሄን ያህል ማወቅህ አስገርሞኛል።››አለው በዚህን ጊዜ የመኪናዋ የቤታቸው የውጭ አጥር ጋር ደርሳ ክላክስ እያስጮኸች ነበር፡፡

ዘበኛው በራፉን ሲከፍት የቤቱ በረንዳ ሁሉ በሰው ተሞልቶ ነበር…ሁለት መንታ የሚመስሉ ዕድሜያቸው በ15 እና በ16 መካከል ያለ የሚመስል ሴቶች እያተንደረደሩ መጥተው ተጠመጠሙበት..እንዷ ግራ ጉንጪን ስትስም ሌላዋ ቀኝ ጉንጩን ትስመው ነበር….

ምን እየተካሄደ እንዳለ በትክክል መረዳት አልቻለም….ይሄ ሰውዬ የፊልም ዳሬክተር ሆኖ ይሆን እንዴ…?.የሆነ ሪያሊቲ ሾ እየሰራ ያለ ነው የመሰለው፡፡እነዚህን ልጆች አምሰት ወይም ስድስት አመታቸው ላይ አንድ ሁለቴ  እንሱ ቤት መጥተው  ስለነበረ  ትንሽ ትንሽ ትዝ ይሉታል…..ጭራሽ ሳያያቸው ግን አስር አመታት አልፎታል፡፡እነሱ ደግሞ በዛን ወቅት ህፃን ስለነበሩ ሊያስታውሱት እንደማይችሉ እርግጠኛ ነው..ታዲያ ይሄ ሁሉ የናፍቆት የሚመስል የደመቀ አቀባበል ከየት የመጣ ነው?፡፡ደግሞም ምኑም አርቴፊሻል አይመስልም
"እነዚህ ልጆች የዘመድ ረሀብ አለባቸው ይሆን እንዴ?"ሲል በውስጡ አጉረመረመ።

አጎትዬው ሻንጣውን በእጁ አንጠልጥሎ ወደእሱ በመምጣት ከልጆቹ አላቀቀውና…"ልጆች አጎታችሁ ከረጅም ጉዞ ስለመጣ ደክሞታል…ወደክፍሉ ይግባና ሻወር ወስዶ ልብስ ቀያይሮ ተመልሶ ይመጣል..እስከዛ ለምሳ  ዝግጅ እየሆናችሁ ጠብቁት"አለና እጁን ይዞ ወደውስጥ ይዞት ገባ..ሳሎን ሰንጥቀው ከላፉ በሃላ ከኃላ ያሉ ብዙ ክፍሎችን እያለፍ በመሄድ  አንድ የተዘጋ ክፍል ከፍቶ " ግባ ..."እያለው ቀድሞት ገባ፡፡ገዘፍ ያለ የራሱ የሆነ ሻወር ቤት ያለው መኝታ  ክፍል ነው፡፡ ሻንጣውን ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠለትና…". እንግዲህ 30 ደቂቃ እንሰጥሀለን፡፡ሻወር ውሰድ...
👍705👎4👏1
ትንሽ አረፍ በልና ስድስት ሰዓት ወደሳሎን ና ….ሁሉም አንተን ነው ሚጠብቁት፡፡ "አለውና ወጥቶ ሊሄድ በራፍ አካባቢ ከደረሰ በኃላ ወደኃላ ዞር በማለት"ስትመጣ እዛ ቀይ ፔስታል ውስጥ ያለውን ዕቃ ይዘሀው ና..ለልጆቹ ስጦታ ነው።እንዲህ አይነት ነገር ስለለመድ ትሠጣቸዋለህ…ላንተ ልብስ ቁም ሳጥኑ ውስጥ አለልህ…ሳይዝህን በትክክል ስለማላውቅ በግምት ነው የተገዛው..ግን ከውስጡ የሚሆንህ አይጠፋም ብዬ እስባለሁ…በል እንጠብቅሀለን" ብሎት ክፉሉን ሙሉ በሙሉ ለቆ ወጣና ከውጭ ዘግቶለት ሄደ፡፡መንግስቱ የግራ መጋባቱ መጠን በጣም ከፍተኛ ስለነበረ ድክምክም አለው።አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለና መኝታ ቤትህ  ነው የተባለውን   ክፍል እንደ አዲስ አይኖቹን እያዘዋወረ መቃኘት ጀመረ፡፡


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍672
አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _5
"""
አሮራ ከአባቷ ከአቶ ግርማ  ደረት ላይ ተንሸራታ ተነሳችና ከአልጋው ወረደች።እርቃኗን ነች...መለመላዋን  ከአልጋው አንድ ሜትር እራቅ ብላ ቆመችና ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ያለውን  አባቷን በትኩረት አየችው ።ይሄን ሰው አባቷ ነው ።ቢያንስ ለ17 ዓመት እናቷ እስክትሞት ድረስ የአለም ምርጡ (የእንጀራ አባቷ)ነበር..ከዛ በኃላ በተለይ ባለፉት 5 አመታት ነገሮች መስመር ስተው  ድብልቃቸው ወጥቷል።አዎ ይሄን ሰው በጣም  ትወደዋለች ...ይሄን ሰው አምርራ ትጠላዋለች።ቀስ ብላ ወደ ኮመዲኖ ሄደችና አንድን የመሳቢያ ኪስ ሳበች ።የተወሰኑ ሰነዶችና አንድ ሽጉጥ አለ ..ማታ ከጎኑ  አውጥቶ ሲያስቀምጥ አይታ ነው ።አነሳችው...።አስተካክላ ያዘችና ወደእሱ ተጠጋች ። በልብ ትክክል ደቀነች። መጠበቂያውን አላቀቀችና ለመተኮስ ተዘጋጀች።ገድላው መሞት አሰኛት።
"ከዛ ተያይዘን ሲኦል እንሄዳለን..አዋ መቃጠል ለሁለታችንም ይገባናል...ለሁለታችንም መቅለጥ የገባናል"አለች።
ቃታውን ልሳብ አልሳብ እያለች ከነፍሷ ጋር ሙግት ገጥማ እያለ አይኑን ገለጠ...ወደላይ አንጋጦ አያት  ..ምንም አልደነገጠም ..አልገረመውም ።ሁል ጊዜ ልትገለው  እንደምትፈልግ ያውቃል።ያላስደነገጠው ሞቱን የምትመኘውን ያህል በህይወት መቆየቱንም በጣም እንደምትፈልግ እርግጠኛ ስለሆነ ነው።
"ልቤ ላይ ከምትደቅኚ ግንባሬ ላይ አይሻልሽም።ልቤ ውስጥ ውቅያኖስ የሆነ ያንቺ ፍቅር አለ..ቀጥታ ልቤ ላይ ከተኮሽ ማዕበል ታስነሺያለሽ።ማዕበሉ ደግሞ ሁለታችንንም ከህይወት ሰልፍ ጠራርጎ የማስወገድ አቅም ይኖረዋል"አላት።
ሽጉጥ የደቀነውን እጇን ሰበሰበችና ሽጉጡን ወደቦታው መልሳ ወደ ቁምሳጥኗ ሄደች..ከፓንት ጀምራ ልብሷን መልበስ ጀመረች።እሱም በተኛበት በአድናቆትና በፍዘት ሲመለከታት ከቆየ በኃላ "ምነው በጥዋት ተነሳሽ ?"ሲል ጠየቃት ።
"ወጣ ብዬ ዕቃ መገዛዛት  ፈልጋለሁ፤እቤት ውስጥ ታፍኜ መዋል ሰልችቶኛል...በዛ ላይ ዛሬ ሀሙስ ነው ማታ ናይት ክለብ ፕሮግራም አለኝ።"
"ጥሩ....  ጋርዶችሽን  ሶስት አድርጌያቸዋለሁ"
"ምን ተፈጠረ ደግሞ..?አይደለም ሶስት ሆነው ሁለቱንም መቋቋም አልቻልኩም...ያፍኑኛል...ነፃነተቴን እንደተዘረፍኩ ነው ሚሰማኝ።"
"እንግዲህ ያንን ከጠላሽ ከቤት አለመውጣት ..ተሠብስቦ መቀመጥ ነው። ሁሉንም ማደርገው ለአንቺው ብዬ ነው"
ከት ብላ ሳቀች
"ምን ያስቅሻል?"
"ምነው ስንተዋወቅ..ግን እማዬ በህይወት እያለች እንዲህ መፈናፈኛ አሳጥተህ  ከማንም እንዳትገናኝ ቁም ስቅሏን ታሳያት ነበር?"
"እሷን እንደዛ አድርጌ እንደማላውቅ ታውቂያለሽ...እናትሽ እንደአንቺ ዝነኛና የሰው አይን ሁሉ የሚንከራተትባት አብሪ ኮኮብ አልነበረችም...አንቺ እኮ የወንዶችም የሴቶችም አይን እኩል የሚሸረሙጥብሽ  አፍዛሽ    ጣኦት ነሽ።"
"ቆይ ለምን ለአንድ ድረኸኝ አትገላገልም"
"የትኛው ሞኝ ነው በየቀኑ የወርቅ እንቁላል የምትጥልለትን ተወዳጅ ዶሮውን አርዶ የሚበላው።"
"አሁን አንድ  መጥቶ የዚህች ልጅ እውነተኛ አባት እኔ ነኝ።አራስ ሆና እናቷ ይዛብኝ ጠፋታ መጥታ አንተን አገባች።ከፈለክ ዲኤን ኤ ማሰራት እንችላለ።አንተ ያሳደካት እንጂ ወላጅ አባቷ አይደለህም..ይሄንን አንተም በልብህ ታውቃለህ።ስለዚህ ልጄን ስጠኝ ቢልህ ..ምን ታደርጋለህ?"

"ምንም ..ተንደርድሬ አቅፈውና አገላብጬ ስመዋለሁ..ወደቤት ይዤው ገባና የሚቀመጥበት ወንበር አቀርብለታለው..ከዛ አንድ ብርጭቆ ውሀ እሰጠዋለሁ ...እሱን አንስቶ እየጠጣ ሳለ በግንባሩ ሶስት ጥይት እለቅበታለው።ከዛ እጅ ላይ ያለው ብርጭቆ አምልጦት ወለል ላይ ይወድቅና ስብርብሩ ይወጣል..ከዛ አንድ እጅን ይዤ ወደሻወር ቤትእየጎተትኩ ወስደውና እጅን ቆርጣሁ..እግሮቹን ቆራርጣለሁ....."
ዝግንን አላት "በቃ በቃ...እንዲህ እንድታደርግ የሚያደርግህ  ለእኔ ያለህ የአባትነት ፍቅርህ ነው ?ወይስ ይሄኛው ለእኔ ያለህ ቆሻሻው ስሜትህ ነው?"
"አንቺ ለእኔ በህይወቴ የተሠጠሽኝ ሁሉን የምታሟይ ሙሉ ፓኬጄ ነሽ...ይሄ ከዚህ ብዬ አልመርጥም...አንቺ እስከህይወት ፍፃሜሽ የእኔ ነሽ ይሄንን መቼም እንዳትረሺ"
"ትንሿ እህቴ በቀደም ምን እንዳለቺኝ ታውቃለህ እኔም እንዳንቺ አድጌ አባዬ ካንቺ እኩል እንዲወደኝና ከእሱ ጋር አብሬ እንድተኛ እንዲፈቅድልኝ እፈለጋለሁ አለቺኝ...እንዴት እንደሚሰቀጥጥ አየኸው?አንድ የቤተሠብ አባል ይሄንን ጉዳችንን ያወቀ ቀን ምን ይውጠናል..?"
"እንደዛ እንዳይሆን መጠንቀቅ ነው...ከሆነም በጊዜው እናስብበታለን።ለማንኛውም ስትወጪ ጠንቀቅ በይ ..ያ መንግስቱ የተባለው ወጠጤሽ  ተፈቷል።"
"ወይ ተፈታ...መቼ?"አለች በሰማችው ዜና ተደስታ።
"ምነ? በመፈታቱ  በጣም ደስ ያለሽ ትመስያለሽ"
"አዎ ለምን ደስ አይለኝም...በፊትም ባልሰራው ስራ ነው ያሳሰርከው...ገና ለገና ትኩር ብሎ አየሽ ብለህ ነው የልጅን ህይወት የበጠበጥከው ።"
"ነግሬሻለሁ ...አሁንም ሊያገኝሽና በዙሪያሽ ሊያንዣብብ ቢሞክር በቀላል እስር አላልፈውም.. ወደአለመኖር ነው የማሸጋግረው..በውስጥሽ ጥቂት እንኳን ለእሱ ፍቅር ቢጤ ካለሽ ይቅርብሽ ...በኃላ ታዝኚያለሽ...አንቺ ስታዝኚ ደግሞ ዞሮ ዞሮ አኔው ነኝ የማዝነው"
"..አንተ አባቴ በህይወት እያለህ እኔ ማንንም የማፍቀር ሆነ በማንም የመፈቀር መብት እንደሌላኝ አውቃለሁ"አለችው

"በቃ እንግዲህ..አንቺ ከሰሙሽ ቀኑን ሙሉ ስትነዛነዢ ነው የምትውይው"አለና ከአልጋው ወርዶ እራቀቱን  ወደ እሷ ተጠጋና ጎትቶ ጎኑ ሸጎጣት  ...ከንፈሯን ለደቂቃዎች መጠጣቸው...አቅመቢስ ሆና ልፍስፍስ አለችና  ከሰውነቱ ተለጠፈች።


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍8911😱8👎6🥰5
አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _6
መንግስቱ አሁን የተሰጠው ክፍል አይደለም ሶስት አመት ከቆየበት የታፈገ የእስር ቤት ክፍል ይቅርና ቀድሞም በሰላሙ ጊዜ የራሱ የሆነ የተከበረ ስራ እያለው ከሚኖርበት ክፍል በጣም የተሻለና በውበትም በምቾትም የደመቀ ነው፡፡የአልጋው ጥራት፤ጠረጳዛው፤ ወንበሮቹ…ቁምሳጥኑ አንድ ዘመናዊ ወንደላጤ ቢኖሩት የሚመኛቸው ነገሮች ሁሉ የተሞሉለት ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ወደ ሻወር ቤት አመራ፡፡ከፍቶ ገባ …ልዩ ነው፡፡ልብሱን አወላለቀና ወደመሀከል ተጠግቶ ውሀውን ከላይ ለቀቀው…..እስር ቤት ሻወር እንዴት እንደሚወስዱ ትዝ አለው…..መአት ወንዶች አንድ ላይ ይጠቀጠቁና ውሀው ከላይ ይለቀቃል… የአንዱ ጭቅቅት ተፈናጥሮ አንዱ ሰውነት ላይ እየተረጨ..አንዱ የሌላውን እርቃን ገላ እየጎበኛ ምቾት በሚነሳ መንገድ ይታጠባሉ፡፡
ያንንን እያሰበ ታጠበና  ፎጣ አገልድሞ ወደመኝታ ቤቱ ተመለሰ ፡፡ሰውነቱን አደራረቀና ልብስ ለመቀየር አሮጌ ሻንጣውን ከፈተ፡፡የተሻለ ያለውን ልብስ በመምረጥ ላይ ሳለ አጎቱ ቁም ሳጥኑ ውስጥ ልብስ አለልህ ያለው ትዝ አለው፡፡ሻንጣውን ባለበት ተወና እራቁቱን ወደ  ቁም ሳጥኑ አመራ፡ደረሰና ከፈተው፡፡መለስተኛ ቡቲክ ሊያስከፍት የሚችል ብዛትና ጥራት ያላቸው ልብሶች ተጠቅጥቀውበታል፡፡ሶስት የተለያየ ቀለም ያላቸው  ሙሉ ሱፎች ፤ከአምስት የሚበልጡ ጅንስ ሱሪዎች ሌሎች ሁለት ካኪ ሱሬዎች፤ ሸሚዞች፤ ፓክአውቶች ፤ፓንቶች እና ካልሲዎች ሳይቀሩ ተገዝተውለታል፡፡ቁም ሳጥኑ ጎን ያለው ወንበር ላይ ቁጭ አለ፡፡
‹‹ይሄ ሰውዬ ከእኔ ምንድነው የሚፈልገው…?››ሲል ጠየቀ፡፡አጎቱ ለእሱ ከፍተኛ እቅድ እንዳለው እርግጠኛ ነው፡፡ከለበለዚያ እንዲህ ድንገት ከተደበቀበትና ከተሸሸገበት ብቅ ብሎ ተወዳጅ አባት፤ ተናፋቂ ታላቅ ወንድም አይነት ገፀ ባህሪ ተላብሶ አይጫወትም ነበር…ዝም ብሎ አንድ ጅንስ ሱሪ አንድ ሸሚዝና አንድ ቀለል አያለ ጃኬት መረጠና ወደአልጋው ተመለሰ…፡፡ሁሉንም በየተራ ለበሰ፡፡ ወደሻወር ቤት ተመለሰና እራሱን በመስታወት ተመለከተ፡፡ የተወሰነ ቅባት እጅ ላይ አደረጋና ፀጉሩን እና ፊቱን  አባበሰ፡፡
‹‹አሁን እስኪ ወደ አዲሶቹ ተናፋቂ ዘመዶቼ ልሂድ ››አለና ወደውጭ መራመድ እንደጀመረ አጎቱ ለልጆቹ ምትሰጠው ስጦታ ነው ብሎ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠለትን የስጦታ እቃ ትዝ አለው..ወደኃላ ተመለሰና አነሳቸው፡፡
‹‹አጎቴ አንተ እኔ ላይ ቆንጆ እቅድ ሊኖርህ እንደሚችል ጠንካራ ጥርጣሬ አለኝ..ግን እንዳትሸወድ እኔም በቅርብ ቀን አስበህ እራሱ የማታውቀውን እቅድ አወጣልሀለሁ፡፡ከአመታት በፊት ከአባቴ የወሰድከውን ሀብት ፤ ሰላም እና ጤና በጠቅላላ ከነወለዱ እረከብሀለው፡፡››ይሄንን በውስጡ እያሰላሰለ ሳሎን ሲደርስ የሳሎኑ ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቶ ዙሪያውን በሰዎች ተከቦ  የእሱን መምጣት በናፍቆት ሲጠብቁ ደረሰ፡፡ከዛ ድግሱም ሆነ የአቀባበል ዝግጅቱ እስከምሽት የዘለቀና የተለየ ነበር፡፡
/////
በማግስቱ ጥዋት ከቁርስ በኃላ አጎቱ ይዞት ወጣ ፤ለሰላሳ ደቂቃ ዝምታ ያጠላበት ጉዞ ከተጓዙ በኃላ አንድ ግዙፍ ባለሶስት ወለል ገስትሀውስ ግቢ ውስጥ ይዞት ገባ፡፡መኪናዋን አቆሙና ግራውንድ ላይ ወዳለ አንድ ክፍል ይዞት ገባ….ለገስት ሀውሱ እንደቢሮ ሚያገለግል መሆኑን ክፍሉ ውስጥ ያሉትን እቃዎችን አይቶ መረዳት ይቻላል፡፡አጎትዬው የለበሰውን ጃኬት አወለቀና ማንጠልጠያው ላይ ሰቅሎ ጠረጴዛውን ዞሮ ግዙፉ ተሸከርካሪ ወንበር ላይ እየተቀመጠ እሱን ፊት ለፊት ያለ ወንበር ላይ እዲቀመጥ አዘዘው፡፡
‹‹እንግዲህ ይሄ የእኛ ገስት ሀውስ ነው፡፡በኃላ ልጀቹ ሁሉንም ክፍልም ሆነ  አጠቃላይ ግቢውን ያስጎበኙሀል....

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍1117😁6👏3
አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _7
‹‹እንግዲህ ይሄ የእኛ ገስት ሀውስ ነው፡፡በኃላ ልጀቹ ሁሉንም ክፍልም ሆነ  አጠቃይ ግቢውን እያዞሩ ያሳዩሀል…አሁን ግን እናውራ፡፡››
በሰማው ነገር ስለተደነቀ‹‹አሀ ያንተ ገስትሀውስ ነው ማለት ነው?››ሲል መልሶ ጠየቀው፡፡
‹‹አዎ እኛ ነው፡፡››
‹‹ጥሩ ..ግን አንተ ስለምትፈልግው ነገር ከማውራታችን በፊት እኔ እንዲመለሱልኝ የምፈልጋቸው መአት ጥያቄዎች አሉኝ፡፡ እስከአሁንም በውስጤ አፍኜ የያዝኳቸው አመቺውን ጊዜ ስጠብቅ ነበር፡፡››
‹‹ጥሩ ብዙ ጥያቄዎች እንደሚኖሩህ እኔም እጠብቃለሁ…ሁሉንም ጥያቄዎች ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡››
‹‹እሺ ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኃላ ያለሁበት ቦታ እንዴት መጣህ? ለዛውም በመፈቻ ቀኔ ላይ?፡፡››
‹‹ምንመ መሰለህ የዛሬ ሰባት አመት በፊት ከአባትህ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተለያየን …በወቅቱ ወንድሜ እናንተ አጠገብ እንድደርስ አይፈልገም ነበር፡፡ከዛ ከእናንተም ሆነ ከሌላው ቤተሰብ ተነጥዬ የራሴን ኑሮ መኖር ጀመርኩ፡፡››
‹‹እና ሲሞት ቀብሩ ላይ ሁሉ አልመጣህም…ምንም ብትቀያየሙ ብቸኛ ወንድምህ አይደል?››ሲል በጥንካሬ ሞገተው፡፡
‹‹አውቃለሁ..ግን በወቀቱ እኔ ሀገር ውስጥ አልነበርኩም፤፤ ወንድሜ ከሞተ ከሶስት አመት በኃላ ተመልሼ ስመጣ ነው መርዶውን የሰማሁት..በዛን ጊዜ  ስለአንተ እስርቤት መግባትህን ሰማሁ…ያው የነገሩኝ ደስ የማይል ነገር ስለበር ምንም ለማድረግ አልተደፋፈርኩም..››
‹‹ታዲያ አሁንስ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ልታገኘኝ ወሰንክ?››
‹‹እንደአጋጣሚ ጠበቃህ ከነበረ ሰው ጋር የሆነ ቦታ ተገናኘንና ስለአንተ ተነሳ….የተፈጠረውን ነገር አስረዳኝ፡፡ በእውነት በጣም ነው ያዘንኩትም በራሴም ያፈርኩት….የሰው ወሬ ሰምቼ ችላ ከምልህ ቀርቤ አንተኑ ስለሁኔታው ብጠይቅህ ጥሩ ነበር…በጊዜው ልደርስልህና ልሟገትልህ ይገባ ነበር፡፡ከእድሜህ ላይ ሶስት አመት ሲባክን ዝም ብዬ በማየቴ በጣም ይቅርታ..››
‹‹አረ ነገሩ እንጂ ችግር የለውም..ደግሞ ምንም የባከነ ጊዜ የለኝም…ሶስት አመት በእስር በማሳለፌ ምንም የምቆጭበት ነገር የለም…ብዙ ነገር ተምሬበታለሁ፤ ከብዙ ድንቅ ሰዎች ጋር ተዋውቄ ብዙ የህይወት ተሞክሮ ከእነሱ አግኝቼለሁ..አዲስ ሞያ ተምሬለሁ፤ትእግስትን ….መረጋጋትንና …ጥሞናን ..አረ ብዙ ብዙ..ደግሞም በእሷ ምክንያት ሌላ 30 አመት ያህል ብታሰር እንኳን ቅንጣት ቅሬታ አይሰማኝም…››
‹‹ያን  ያህል ታፈቅራታለህ ማለት ነው?››
‹‹መጠንና ወሰን በሌለው ሁኔታ አፈቅራታለሁ…ደፈራት ብለው ሲከሱኝ በጣም ነው ያስገረሙኝ፡፡ እሷ እኮ የእኔው ነች፡፡ ልቤ ውስጥም ነፍሴ ላይም ያለችው እሷ ነች..እሷ ፊት ላይ ምታርፍ አንድ ጥፊ እንኳን ልቤ ላይ ጠባሳ ትተዋለች፡፡እንዴት ሰው የገዛ ልቡን በቢላዋ ወግቶ ያደማል…?እኔ እሷን እንኳን ልደፍራታ የለፍቃዷ  እጇን አልጨብጥም፡፡››
ፈዞ በተመስጦ ሲያዳምጠው የነበረው አጎቱ‹‹እሷስ ግን …?ማለቴ ያንተን ያህል ታፈቅርሀለች?››
‹‹እሱን ለማወቅ አልችልም…..እኔ እርግጠኛ ምሆነው በእኔ ማፈቅር ነው…ደግሞ የእኔ ፍቅር ጥልቅና ስምጥ ስለሆነ ለእኔም ለእሷም ይበቃል….ብቻዬንም ቢሆን ለሁለታችን የሚሆነውን ፍቅር ማመንጨት እችላለሁ፡፡››


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍7517🥰8👏6🔥3😁1
አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _8

‹‹የሚገርም ነው…ይህቺን ልጅንማ ከመሄዴ በፊት ታስተዋውቀኛለህ?››
‹‹የት ነው የምትሄደው….?››
‹‹ይሄውልህ እዚህ ሀገር ውስጥ የምቆው ግፋ ቢል ለ15 ቀን ብቻ ነው፡፡ከዛ ወደካናዳ እሄዳለሁ፡፡››
‹‹ምነው ለእረፍት ነው?››
‹‹አይ ለስራ ነው….ከአንድ አለማ አቀፍ የመአድን አምራች ካምፓኒ ጋር የተለየ አይነት የስራ እድል አግኝቼያለሁ…የዚህ ድርጅት ዋና መቀመጫው ከናዳ ነው፡፡ግን ደቡብ አሜሪካ ሀገሮች ውስጥ ብዙ የማዕድን ማውጫ ቦታዎች አሉት….እኔ ከዛ ድርጅት ጋር ቢያንስ ለቀጣዬቹ 5 አመታት አብሬ ለመስራት ነው የምሄደው…ምን አልባትም በአመት ሁለቴ ወይም አንዴ ብቻ ነው መጥቼ ላያችሁ የምችለው፡፡ይሄ ስራ የሁላችንንም ህይወት ነው ከመሰረቱ የሚቀይረው..እና በዚህ የስኬት መንገድ ከጎኔ እንድትሆን እፈልጋለሁ››…
‹‹ቤተሰቦችህን ይዘህ ነው የምትሄደው?››
‹‹አይ ማለቴ ልጆቹ የተሻለ ትምህርት እንዲማሩ ሰለምፈልግ ከሶስት ወር በኃላ ተመልሼ መጥቼ ወስዳቸዋለሁ… በተረፈ ሁሉም ነገር እንዳለ ነው የሚቀጥለው፡፡እዚህ ያለውን ንብረቴንም ሆነ ቤተሰቤን እንድትቆጣጠርልኝ ፈልጋለሁ..ይሄ ገስት ሀውስ በወር እስክ አንድ ሚሊዬን ብር የተጣራ ገቢ ያስገባል….በተጨማሪ ሌሎች ተያያዥ ቢዝነሶች አሉ..እነዛን ሁሉ በአንተ ስር ይሆናሉ…ከአምስት አመት በኃላ ደግሞ ጠቅልዬ ስመለስ በጥናት ላይ የተመሰረተ አንድ ግዙፍ ከምፓኒ እንከፍትና በጋራ እናስተዳድራለን፡፡አንተ የወንድሜ ልጅ ነህ …ያ ማለት ደግሞ ልጄ ነህ ማለት ነው፡፡››
‹‹አጎቴ ሀሳብ ደስ የሚል ነው..ግን እኔ በህይወቴ ተቀጥሮ ከመስራት ወጭ የራሴን አንድ የሰፈር ሱቅ እንኳና ከፍቼ አስተዳድሬ አላውቅም …ስለገስት ሀውስም ሆነ ስለሌላ ቢዝነስ ምነም የማውቀው ነገር የለኝም››
‹‹አውቃለሁ…ያ ብዙም ሊያስጨንቅህ አይገባም…ሁሉን ነገር ያሚያስረዱህና በደንብ እስክትለምድ ድረስ እንደረዳት ሆኖ የምታግዝህ አንድ ጥሩ ልጅ አለች….አንተ በቃኝ ብለህ እስክታሰናብታት ድረስ ረዳትህ ሆና ትሰራለች፡፡ይሄ ደግሞ የትርፍና የኪሳራ ጉዳይ አይደለም…ቤተሰበን የመሰብሰብ ጉዳይ ነው….ይሄ የራስህ ንብረት ነው..ከሰርክም አተረፍክም የራስህው ነው. ምርጫ ስለሌለህ ፈጣን ተማሪ ለመሆን መጣር ብቻ ነው የሚያዋጣህ፡እስከምሄድ ደግሞ እኔም አለው ዋና ዋና ነገሮችን አሳይሀለው››
‹‹ግን አጎቴ ባለቤትህ ከአንተ ጋር የማትሄድ ከሆነ ለምን ሀላፊነቱን ለእሷ አትሰጥም ነበር..እሷስ ብትሆን ንብረቷ በሌላ ሰው ቁጥጥር ስር ሲተዳደር ደስ ይላት ይመስልሀል››
ስለእሷ ምንም አታስብ፡፡ ንብረቷ በሌላ ሰው ቁጥጥር ስር ሳይሆነ በወንድሜ ልጅ ቁጥጥር ስር ነው የገባው…በዚህ መስማማት ግዴታዋ ነው፡፡በነገራችን ላይ ይሄንን ገስት ሀውስ ላይም ሆነ ጠቅላላ ንብረቴ ላይ በዚህ ይግባ በዚህ ይውጠ ብህ እንደምትወስን ሁሉ እሷ ላይም ያለህ ስልጣን እንደዛው ነው ሚሆነው….አንተ ያልፈቀድክበት ቦታ መሄድ አትችልም፤ አንተ ማታውቀውን ነገር ማድረግ አትችለም…ይሄንን ከመሄዴ በፊት ሁለታችሁም ባላችሁበት እንግራችኋላው፡፡
የሰውዬው ሁኔታና ጠቅላላ እቅዱ ሊጨበጥለት እልቻለም…፡፡‹‹ምን ያህል እንደምጠላው….ለአባቴ ሞት ለአባቴ የአመታት ስቃይና ህመም እሱን ተጠያቂ ሳደርግና ስረግመው እንደኖርኩ ቢያውቅ እንዲህ በድፍረት ንብረቱንም ሚስቱንም አሳልፎ አይሰጠኝም ነበር››ሲል አሰበ ፡፡

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍715🔥2😁2🤔2