አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
461 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ህያብ


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_ኤርሚ

ከቤት ስወጣ ማንም ያየኝ የለም ለነገሩ ማን ሊያየኝ ይችላል... እንደሚሰበር እንቁላል የሚንከባከቡኝን ሁሉ አጥቻለው..... እየሄድኩ ነው....መነሻዬን አስታውሳለሁ መድረሻዬን ግን እንጃ.....

ማሰብና ማስታወስ ቢደክመኝም አይምሮዬ ወደማልፈልገው ጊዜ ሽምጥ ጋለበ.... ወደዛ የሁሉም ነገር ጅማሬ የመከራዬ ሀ ወደሆነው ጊዜ....

በአንድ አነስተኛ የገጠር ከተማ ውስጥ ከእናቴ ጋር ነበር የምኖረው። አባቴን ገና በልጅነቴ ነው በካንሰር በሽታ ያጣሁት። የልጅነት ጊዜዬን እንደማንኛውም ልጅ በጨዋታ እና በሳቅ ነው ያሳለፍኩት። ምንም እንኳን በቤታችን ብዙ የጎደሉ ነገሮች ቢኖሩም እናቴ ለኔ ደስታ አብዝታ ትደክማለች።

ፓስቲ እና ጠላ በመሸጥ ለኔም ሆነ ለሷ የሚያስፈልጉንን ነገሮች ታሟላለች። ሁል ጊዜም ባይሆንም ችግር እና ረሀብ አልፎ አልፎ ቤታችንን ያንኳኳል፤
እናቴን ሲያማት.....
.....
በዛን ሰዓት ምን እንደሆነ ባይገባኝም እናቴን አልፎ አልፎ ከበድ ባለ ሁኔታ ያማት ነበር። አንዴ አሟት ከተኛች ሳምንት እና ከዛ በላይ ያስተኛታል። ሀኪም ቤት እንድትሄድ ደጋግሜ ብጨቀጭቃትም የሁል ጊዜም መልሷ አይሆንም ነው፤ ብያት ብያት እምቢ ስትለኝ በሚያማት ሰዓት ከአጠገቧ ሳልለይ እንከባከባት ነበር።
....
ከእለታት በአንዱ ቀን ከትምህርት ቤት ስመለስ በራችንን ተዘግቶ አገኘሁት.... እናቴ በዚህ ሰዓት የጠላ ጣሳዎቿን ደርድራ ፓስቲዋን በርንዳ ላይ እየጠበሰች መገኘት ነበረባት....
.....
በሩን ከፍቼ ወደ ውስጥ ስገባ የሽቦ አልጋዋ ላይ እጥፍጥፍ ብላ ተኝታ አገኘኋት

"እማ ምን ሆነሽ ነው አመመሽ እንዴ?' እጄን ግንባሯ ላይ አድርጌ ትኩሳቷን አየሁ.... በጣም ግላለች

'እማዬ አተኩሶሻል እኮ እባክሽ ዛሬ እምቢ አትበይኝ ሆስፒታል እንሂድ' ከወገቧ ቀና ለማለት ስትሞክር አገዝኳትና ትራሱን ከጀርባዋ አስደገፍኳት....
.....
"አይሆንም ልጄ.... ደግሞ ልሂድ ብልስ በምን ገንዘብ .... ይልቅ መድሀኒት አልቆብኛል ሂጂና ግዢልኝ፤ ይህን ወረቀት ስታሳያቸው ይሰጡሻል...." የሆነች ትንሽዬ ወረቀት ከእጅ ቦርሳዋ ውስጥ አውጥታ ከብር ጋር ሰጠችኝ....
......
..
" በይ ታዲያ መጀመሪያ መክሰስሽን ብይና ነው የምትሄጂው" እሺ ብያት ዩኒፎርሜን ቀይሬ ምግብ አቀረብኩና እምቢ ብትለኝም በግድ እያጎረስኳት ትንሽ አብራኝ በላች።
....
....
ከተማችን ያለው አንድ የመንግስት ፋርማሲ ብቻ ነው። እሱም ለሰፈራችን ራቅ ስለሚል በሩጫ መሄድ ይጠበቅብኛል። የእናቴን ጉንጭ ስሜና ቶሎ እንደምመለስ ነግሪያት እየሮጥኩ ከቤት ወጣሁ
....
....
ነፋሻማው አየር ቀሚሴን ወደላይ እያነሳው እኔም እንዳይገልጠኝ ለመከላከል እየሞከርኩ እየሮጥኩ እያለ አንድ ሰው ስሜን የጠራኝ መሰለኝ። ድጋሚ
" ሚጣ" አለኝ ማነው የጠራኝ ብዬ ዞር ስል ሸክም ከአጠገቡ ያስቀመጠ ጎረምሳ ልጅ እጁን አውለበለበልኝ። አቅጣጫዬን ቀይሬ በፍጥነት አጠገቡ ደረስኩና
' አቤት የሚያሸክምህ አጥተህ ነው አልኩት' ከሁኔታው ሳየው ምኑም የኛን ከተማ ሰው አይመስልም ምናልባት ከሌላ ቦታ ለስራ መጥቶ ይሆናል ብዬ መላ ምቴን አስቀመጥኩ።
...
...
ያልገባኝን ፈገግታ ከለገሰኝ በኋላ "አዎ ሚጣዬ እስኪ አሸክሚኝ" አለኝ።
'የምችለው አይመስለኝም ግን እሺ ልሞክር' አልኩትና ጎነበስ ብዬ ሸክሙን ያዝ አደርኩና ቀና ብዬ አየሁት የማይገባኝን አስተያዬት እያየኝ ነው።
'ምነው መሸከም አትፈልግም እኔ እቸኩላለሁ ለእናቴ መድኃኒቱን መግዛት አለብኝ' አልኩት ቆጣ ብዬ

"አይ እንደዛ አይደለም ይሄን አንቺም ለማሸከም ይከብድሻል እኔም እንጃ የምችለው አይመስለኝም... ውስጥ አነስ ያለ ሌላ ሸክም አለ እንደውም እሱን አሸክሚኝ አይዞሽ አትቆይም" ምላሼን ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ በጭቃ እየተሰራ ወዳለ ጅምር ቤት ገባ። ዘግዬት ብዬ ተከተልኩትና ወደ ውስጥ ስገባ ዘሎ በጥፊ ደረገመብኝ። ተንደርድሬ መሬቱ ላይ ተደፋሁ.... ለመጮህ አፌን እንደከፈትኩ ፀጉሬን ይዞ አፌ ውስጥ ጨርቅ ጠቀጠቀብኝ።
.....
በመንፈራገጥ እና በድብደባ በዛለ ሰውነቴ ላይ ከላዬ ሆኖ በስሜት ይጨፍራል....
......
ከባድ የሆነ የህመም ስሜት ይሰማኛል........
ቀስ በቀስ በእንባ የራሰው አይኔ መከደን ጀመረ......
ከላዬ ላይ ያለው ሰው ምስል ወደ ብዙ ሰውነት ተቀየረ.......
ከዛ ደግሞ ድብዝዝ እያለ መጣ...... በስተመጨረሻም ድርግም ብሎ ጠፋ...

ጨለማ

ከምን ያክል ሰዓት በኋላ እንደሆነ አላውቅም.... ራሴን እዛ ጅምር የጭቃ ቤት ውስጥ ተኝቼ አገኘሁት። እንደምንም እየተንገዳገድኩ ከቤቱ ውስጥ ወጣሁ... ልብሴ በደም ተነክሯል፣ የሚሰማኝ የህመም ጥዝጣዜ ራሴን ሊያስተኝ ደርሷል ግን እንደምንም ተቋቁሜ ለመራመድ ሞከርኩ።
.....
ብርሀን ለጨለማ ቦታዋን ብታስረክብም ደማቋ የምሽት ጨረቃ አካባቢውን በብርሀን ሞልታዋለች....

በቀስታ እየተራመድኩ ወደ መንገዱ ወጣሁ። አሁንም ደሜ አልቆመም በቀስታ ከጭኔ ላይ ሲወርድ ይሰማኛል። ከሩቅ ነጠላ ለብሶ የሚመጣ ሰው አየሁ አንደበቴን ከፍቼ ለመጣራት መከርኩ ግን በምጥ የወጡት ቃላቶች እንኳን ለሌላ ለኔም የሚሰሙ አልነበሩም።

ያለኝ አማራጭ ወደሚመጣበት አቅጣጫ ተራምጄ እንዲያየኝ ማድረግ ነው። እየቀረብኩት ስመጣ ቄስ እንደሆኑ ተረዳሁ.... አጠገባቸው ለመድረስ ትንሽ ሲቀረኝ ጉልበቴ ተብረከረከ፣ አቅሜ ተሟጠጠ፣ አጠገቤ መጥተው ያዙኝና

" ምነው የኔ ልጅ ችግር አለ ምን ሆነሽ ነው?" ድምፃቸው ከሩቅ የሆነ ያክል ይሰማኛል ። ልቤን ስልብ የሚያደርግ ህመም ተሰማኝ ከዛ በኋላ አላስታውስም
......
"ልጄ የኔ ስስት.... ምን አድርገውብኝ ነው? እባክሽ ተነሽ ሚጣዬ ተነሽልኝ..... የኔ ብቸኛ ልጅ... ያላንቺ ማን አለኝ.... ትተሽኝ እንዳትሄጂ.... ተስፋዬ.... ነገን የማይብሽ.... " አይኔን ሳልገልጥ የሰማኋቸው የእናቴ በሳግና በለቅሶ የታጀቡ ቃላቶች ናቸው... ከዛ ከባዱ ጨለማ ይውጠኛል።
ትንሽ ትንሽ ዙሪያዬ እየተፈጠረ ያለውን ነገር ባውቅም አይኔን ለመክፈት ወሰድ መለስ የሚያደርገኝን ጨለማ እና የተጫነኝ ከባድ ነገር መታገል ግድ ሆኖብኛል።
.....
"አሁንስ አልነቃችም አይደል" አለ የሆነ ጎርናና ድምፅ

" አልነቃችም ኢንስፔክተር ልጄን እንደዚህ ያደረገውን ሰው አገኛችሁት?" እማዬ ናት

" አይ... ወይዘሮ ወይንሸት አላገኘነውም እሱን ለመያዝ የልጆት ቃል ያስፈልገናል" የበር መዘጋት ድምፅ ተሰማኝ እኔም ወደዛው ጨለማ የሄድኩ መሰለኝ.... እንቅልፍ
....

ዛሬ የተሻለ ጥንካሬ ይሰማኛል። ልክ አይኔን ስግልጥ እናቴን አጠገቤ አየኋት የአልጋውን ጠርዝ ተደግፋ እንቅልፍ ወስዷታል። እጄን አንቀሳቅሼ ፊቷን ስዳስሳት ተነሳች... ወዲያው እልልታዋን አቀለጠችው።

"ልጄ ነቃሽልኝ የኔ ስስት.... ተመስገን ልጄ ነቃች" ዶክተሩ ምርመራ እስከሚያደርግልኝ ውጪ እንድትቆይና ነገራትና አንዳንድ ህክምናዎች ካደረገልኝ በኋላ

"ፖሊስ መጥቶ ቃልሽን ይወስዳል... እንደዚ ያደረገሽ አውሬ እንዲያዝ ከፈለግሽ ምንም ሳትፈሪ ሁሉንም ለመናገር ሞክሪ.... ደግሞ አይዞሽ በሚያስፈልግሽ ሁሉ ከአጠገብሽ አለን..." ብሎኝ ክፍሉን ለቆ እንደወጣ ሁለት ፖሊሶች ተከታትለው ገቡ።
....
ከ አንድ ወር በኋላ
የሰፈር ሰው ሰምቶ ስለነበር ግማሹ ሲያዝን ግማሹ ደግሞ የራሱን መላምት ማስቀመጥ ጀመረ።
"ፈልጋ ነው እንጂ ሳትፈልግ ማን ሊነካት..." በነገር የምትታወቀው ብርቄ
👍736👎2😢2🤔1
#ህያብ


#ክፍል_ሁለት


#ድርሰት_ኤርሚ

"አቤት ህያብ" አለኝ ዶክተሩ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ካየኝ በኋላ

'ማስወረድ እፈልጋለሁ' አልኩት

"ምን" የሚል ድምፅ ሰምቼ ስዞር እናቴ ከኋላዬ ቆማለች።

"ምንድነው የምታወሪው እ... ማን ፈቅዶልሽ ነው የምታስወርጂው.... ምን ስልጣንስ ኖሮሽ ነው የእግዜርን ፍጡር የምትገይው......" ወደኔ የበለጠ እየተጠጋች የቁጣ ናዳ አወረደችብኝ። እናቴ በአካባቢው እያለች ከአንደበቴ ይህንን ቃል ማውጣት አልነበረብኝም።
.......
ከውርጃ ጋር ተያይዞ በጣም መጥፎ ትዝታ አለባት። ልጅ እያለሁ ትርሲት የምትባል የዘመዳችን ልጅ አብራን ትኖር ነበር። ታናሽም ታላቅም ስለሌለኝ እንደ እህቴ ነበር የማያት እሷም ሲበዛ ታቀብጠኝ ነበር። በትምህርቷ በጣም ጎበዝ ነበረች። ታዲያ ከጊዜ በኋላ ውጤቷ እያሽቆለቆለ መጣ። መምህሮቿ ቤታችን ድረስ መጥተው እናቴን አናገሯት እማዬ ደነገጠች..... ትርሱ ከሄደችበት ስትመለስ ቁጭ አድርጋ አወራቻት መከረቻት ግን ለውጥ አልነበረውም የባሰ ትምህርት ቤት እያለች ሌላ ቦታ እንደምትውል ተደረሰባት.... እናቴ ይህን ስትሰማ በጣም ተቆጣቻት።
......
የሆነኛው ቀን ላይ መልዕክተኛ መጥቶ ትርሲት ታማ ሆስፒታል መግባቷን ነገሩን እናቴ እየሮጠች ሄደች። ወደቤት ይዛ የተመለሰችው ግን አስከሬን ነበር።
.......
ትንሽ ካደኩ በኋላ እናቴን ጠይቄ እንደተረዳሁት ከሆነ ትርሲት ከአንድ የከተማችን ነጋዴ ጋር የፍቅር ግንኙነት ትጀምራለች። ሁሉ ነገሯን ትታ ነበር ክንፍ ያለችለት .... ግንኙነታቸው በሱ ጎትጓችነት ወደ አልጋ ላይ ጨዋታ ይሸጋገራል.... በዚህ መሀልም ትርሲት አረገዘች። ማርገዟን ስታውቅ ሁሉንም ነገር ዘርዝራ ለጓደኛዋ ከነገረቻት በኋላ ምክሯን ጠየቀቻት
"ስለሚወድሽ ያገባሻል እንዳረገዝሽለት ንገሪው" አለቻት።

በማግስቱ ወደ ፊት የሚኖራቸውን የደስታ ህይወት እያሰበች በፈገግታ የደመቀ ፊቷን ይዛ ወደ ነጋዴው ፍቅረኛዋ ጋ ሄደች። እንዳረገዘችለት ስትነግረው

" ከማናባሽ አርግዘሽ መጥተሽ ነው አረገዝኩልህ የምትይው" አላት።
ከሱ ውጪ ወንድ እንደማታውቅ ያውቃል ግን ሊሰማት አልፈለገም። ትርሲት ለሱ የሆነ ሰዓት ላይ ተጠቅሞባት እንደሚጥላት እቃ ነበረች።
አይንሽን ማዬት አልፈልግም ከነ ዲቃላሽ ገደል ግቢ ብሎ አባረራት..... ለሳምንታት ተስፋ ሳይቆርጡ እሷም ጓደኛዋም ለመኑት.... ጭራሽ አይኑን ወደ ጓደኛዋ ማዞር ጀመረ ነገሩ ሲገባቸው እሱን እርግፍ አድርገው ትተው ሌላ መፍትሄ መፈለግ ጀመሩ እናም ማስወረድ በሚለው ተስማሙ። የትርሲት ጓደኛ ቤተሰቦቿ ወደገጠሩ ስለሚርቁ ቤት ተከራይተውላት ነው ትምህርቷን የምትማረው.... እናም ለእቅዳቸው ተስማሚ የሷ ቤት ስለሆነ ትርሲት እማዬን ለፈተና ለማጥናት ጓደኛዬ ጋር ልደር ብላ አስፈቀደቻት። እማዬም ምናልባት አብረው ሲያጠኑ ውጤቷ ይሻሻላል ብላ ስላሰበች አልተቃወመቻትም።
.......
ጓደኛዋ ቤተሰቦቿ ካሉበት ገጠር ለውርጃ ይጠቀሙታል ያለችውን መድኃኒት ሰጠቻት እናም ግጥም አድርጋ ጠጣችው። ለትንሽ ጊዜ ሁሉም ሰላም ነበር ሌሊት ላይ ግን ከበድ ባለ ሁኔታ ደም ይፈሳት ጀመር። ልጁ እየወረደ ነው ብለው ስላሰቡ የሚሆነውን በዝምታ ጠበቁ..... ከሰአታት በኋላ ግን ትርሲት እየደከመች መጣች። ጓደኛዋ የአከራዮቿን ቤት አንኳኩታ እርዳታ ጠየቀች እናም ወደ ሆስፒታል ተወሰደች ግን አርፍደው ነበር። ትርሲት ብዙም ሳትቆይ አሸለበች ።

አይደለም እኔ ልጇ ማንም ላሶርድ ቢላት ኡ ኡ እንደምትል አላጣሁትም ግን.......

"እማዬ በዘመናዊ መንገድ እኮ ነው በሀኪም" አልኳት

"አይሆንም ብያለሁ አይሆንም..." ጮኸችብኝ.... ንግግራችንን ሲሰማ የነበረው ዶክተር ተነስቶ አጠገባችን መጣና አረጋግቶ ወንበር ላይ ካስቀመጠን በኋላ

"ህያብ ከማስወረድ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም ብለሽ ታስቢያለሽ" አለኝ።

"አዎ ዶክተር መማር እፈልጋለሁ በዛ ላይ የሰው መሳቂያ ነው የምሆነው.... ማንም ተደፍራ ወለደች የሚለኝ የለም...." ንግግሬን ሳግ አቋረጠኝ

"እርሶስ ወይዘሮ ወይንሸት ምን ይላሉ"

"እኔ ቆሜ እያለሁ ልጄን ለሞት አሳልፌ አልሰጣትም በፍፁም አይሆንም" እርግጠኝነት በተሞላበት መንፈስ ተናገረች።
......
"እኔም የእናንተን ሀሳብ ልስማ ብዬ እንጂ ፅንሱ ሶስት ወር አልፎታል በዛ ላይ ልጅ ነሽ ከማስወረዱ ብትወልጂው ይሻላል ለሱም ቢሆን እድሜሽ ገና ስለሆነ ያላቋረጠ የህክምና ድጋፍ ያስፈልግሻል......" ይሄን እና የመሳሰሉትን ሲያወራ እናቴ 'እህ' እያለች አንገቷን እየነቀነቀች ትሰማዋለች።

ትቻቸው በሀሳብ ነጎድኩ ከዛስ አልኩ ለራሴ...... ከዛስ ትምህርቴ ሊቀር..... የሰፈር ሰው መጠቋቆሚያ ልሆን...... ከዛስ እ...... የወደፊት እጣ ፋንታዬስ.... እዚሁ የተወለድኩበት ሀገር በናቴ እግር ተተክቼ ፓስቲ እና ጠላ ስሸጥ ልጄን ለማሳደግ ደፋ ቀና ስል በህሊናዬ ሳልኩ።
....
"አይሆንም" አልኩ ቃል አውጥቼ.... ያልኩት መልሶ አስደነገጠኝ

"ምኑ ነው የማይሆነው ሚጣዬ.... ዶክተር ያለውን ሰምተሻል አይደል እንደዛ እናደርጋ...." ዶክተር! ዶክተር ምንድነው ያለው?...... ምንም ይበል ምን አገባኝ። ዶክተር እኮ ህልሙ ይሁንም አይሁንም ዶክተር ሆኗል አይደል.... ደግሞ እሱ ምን አለበት በሰው ቁስል ላይ እንጨት መስደድ ለሱ ቀላል ነው.... "ውለጂው" አለ አይደል? መውለዴ የሚያሳጣኝ ነገር ግን ግድም አይሰጠው.... ይቺ የአስራ ሶስት አመት ልጅ ከምታስወርድ ትውለድ ሲል ይቺ የአስራ ሶስት አመቷ ህያብ ህልሟን ትቅበረው ማለቱ እንደሆነ አልገባውም።

''ወለድኩ ማለት ህልሜ ሁላ ይቀበራል" አልኩት የመጨረሻ እድሌን ልሞክር ብዬ

"አንቺ ከምትቀበሪ ህልምሽ ቢቀበር አይሻልም" አለችኝ እናቴ.... ምንም ሳልናገር ቢሮውን ለቅቄ ወጣሁና ወደቤት መንገድ ጀመርኩ እማዬ ከኋላዬ ደረሰችብኝ። ምንም ሳንነጋገር ጎን ለጎን ትንሽ ከሄድን በኋላ

"እስኪ ሚጣዬ ሆድሽን ሸፈን አድርጊው" ብላ የለበስኩትን ፎጣ ስባ ሆዴን አለበሰችው.....
..........
እና ሁሉም ነገር እንደዚህ ሊቀጥል ነው? አይሆንም! እናቴም እኔም አንገታችንን ከምንደፋ የሆነ ሀሳብ በውስጤ መጣልኝ። እንደማደርገው እርግጠኛ ሆንኩ.....

ይቀጥላል
👍567👎3🥰2
#ህያበ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_ኤርሚ

"እሱን እንዳታስቢው ወይም ራስሽ ፈልገሽ አግኝው... ደግሞ አታገኝውም" አማራጭ የለኝም ሻንጣዬን ይዤ ወደኋላ ተመለስኩ።

"እሺ ውሰደኝ አሁን ውሰደኝ"

"አይ አይሆንም ነገ ነው የምንሄደው" በእሽታ አንገቴን ነቀነኩለት።

ወደቀኝ ገልመጥ ብዬ ሳይ የሰርግ ቬሎዬ ተሰቅሏል። ለራሴ ወደኋላ የለም አልኩ...

"አንደርስም እንዴ ደግሞ እኮ አይኔን በጨርቅ አስረህዋል። የት ነው የምንሄደው ራቀብኝ? ያ ውሻ የት ነው ያለው?"

"አይንሽን ከገለጥሽ ከኔ ጋ ትጣያለሽ ማርያምን የምሬን ነው። ታገሽ ትንሽ ነው የቀረን ደርሰናል" ጥቂት ደቂቃ ከተጓዘ በኋላ መኪናውን አቆመው

"አሁን ጨርቁን ማንሳት ትችያለሽ" ቶሎ ብዬ ፈታሁት... ሰው የሌለበት ቦታ ነው።

"ምንድነው ቢኒ እየቀለድክብኝ ነው" ፊቴን አዙሬ በንዴት አየሁት

"ውረጂ.,. ያውልሽ እዛጋ ይታይሻል...( በወዳደቁ ነገሮች የተሰራች ቤት) እዛ ውስጥ አለልሽ ውረጂና የፈለግሽውን አድርጊው" ሳላቅማማ ወረድኩ። በእልህና ንዴት እየተራመድኩ ወደቤቱ ተጠጋሁ ልገባ ስል

"እባቷ ነኝ ባሏ. ... ሀ ሀ ሀ... ንገሩኝ እስኪ እናቷን አግብቶ ልጁን ያስረገዘ አባት ታውቃላችሁ... አታውቁም? ሙትቻ ለምንድነው የምታፈጡብኝ... መልሱልኝ... ኧረ ተውኝ ኡ ኡ ኡ..." ጩኸቱ አስደንግጦኝ ወደኋላ ተመለስኩ። ትንሽ ተራምጄ ቆምኩና ልጄን አሰብኳት "እገለዋለሁ" ወደ ቤቷ ተመለስኩና ከፍቼ ጎንበስ ብዬ ገባሁ። የቤቱ ጠረን ይገፈትራል ሰው የመጣም አልመሰለው ዝምም ብሎ ልፍለፋውን ቀጥሏል። የማላውቃቸውን ብዙ የሴት ስሞች ይጠራል... ያለቅሳል፣ ይስቃል፣ ይራገማል፣ ድንገት ደግሞ አስደንጋጭ ጩኸቱን ይለቀዋል። ለደቂቃዎች ዝምምም ብዬ ሰማሁት... በብዙው የቤቱ ቀዳዳ በሚገባ ብርሀን አየሁት ከድምፁ ውጪ ምኑም እሱን አይመስልም። ልብሱ ተቀዳዷል፣ ፊቱ ጠቁሮ ከሰል መስሏል፣ ፀጉሩ ተንጨባሯል፣ እላዩ ላይ ተፀዳድቶ መሬቱ ጭምር በሽንትና ሰገራ ተበክሏል። ዮኒ እኔ ልሰጠው ካሰብኩት ሞት በላይ በቁሙ ሞቷል... ልቤን ሽው የሚል የሀዘኔታ ጦር ወጋኝ። ወዲያው ደግሞ ልጄን የከዳኋት መሰለኝ... እየሮጥኩ ከቤቱ ወጣሁ... ልፍለፋው ከኋላዬ ይሰማኛል... እያለቀስኩ መኪናውን ከፍቼ ስገባ

"አደረግሺው ህያብ ገደልሽው" አለኝ

"ሞቷል እኮ ቢኒ የሞተን ሰው ድጋሚ እንዴት እገለዋለሁ" ድፍት ብዬ ተንሰቀሰቅሁ

"ቢኒ እባክህ ምንም ሰላም ሊሰማኝ አልቻለም ዮኒን ሆስፒታል እንውሰደው" ደረቱ ላይ ተኝቼ ለቀናት ከራሴ ጋ ስከራከርበት የነበረውን ሀሳብ ነገርኩት

"እኔ የማውቃትም የምወዳትም ህያብ ይቺ ናት ለጠላቷ ሳይቀር የምትራራ። አታስቢ የኔ ቆንጆ ዛሬውኑ እናደርገዋለን" እዛው ቦታ ተመልን ሄድን። ወደዛች ቤት ገባን አጠገቡ ዳቦ ቁጭ ብሏል። ለነፍሱ ያደረ ሰው እንደሚመግበው ገባኝ። መለፍለፉን አላቆመም እንጂ ተዳክሟል... ይዘናቸው የሄድነው ባለሞያዎች በግድ አንስተው ስትሬቸር ላይ አደረጉት... ከኪሱ የተጣጠፈ ወረቀት ወደቀ፤ ቀልጠፍ ብዬ አነሳሁትና ዞር ብዬ ከፈትኩት በትልቁ ርዕስ "ፀፀት" ይላል። ከስሩ ደግሞ "ለማታዩኝ እኔ ግን በየቀኑ ለማያችሁ ለበደልኳችሁ ሁሉ" ይላል... ትርጉም ያለው ነገር ሊሆን ቢችልም ማንበብ አልፈለኩም... ሌላ ሸክም መሸከም አልፈልግም... እጄ ላይ ያለውን ሶስት ገፅ ወረቀት ቀዳድጄ ዱቄት አደረኩትና ለነፋስ ሰጠሁት ብትትንን... አምቡላንስ ውስጥ አስገብተው ይዘውት ሄዱ። ሰላም ተሰማኝ

አዳራሹ በእንግዶች ጢም ብሎ ተሞልቷል። ቃል የሚያገባቡን ቄስ ቦታቸውን ይዘው ተቀምጠዋል።

"በሀዘን በደስታዋ በህመም በጤናዋ..." ቢኒ ቃል ገባ እሱ ያለውን መልሰው እኔንም አስባሉኝ።

የጋብቻ ቀለበት ጣቴ ላይ አደረገልኝ እኔም እንደዛው አደረኩለት.....
ገና ወደሰውነት ቅርፅ ያልተቀየረው የአምስት ሳምንት ልጄ ደስ ብሏት/ብሎት ይሆን ሆዴን ዳበስኩት። የልጄ አባት ቢኒ ፈገግ ብሎ አየኝ

"ተመስገን" አልኩ በልቤ የማያልፉ የመሰሉኝ ሁሉ አለፉ... ዛሬ ደስተኛ ነኝ... ነገን አምላክ ያውቃል።

ተ ፈ ፀ መ
👍11249👏2