አትሮኖስ
277K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
448 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#እናቴን_ተመኘኋት


#ክፍል_ሁለት (የመጨረሻ ክፍል)

:
#በሜሪ_ፈለቀ

#ያኔ.......

በህፃን ልቤ ከተሸከምኳት፣ ባደገች ልቤ ካገዘፍኳት ከኔ በቀር መንደርተኛው ሁሉ ጤንነቷን የማይቀበል ብዙ ጊዜ ብቻዋን
የምታወራ ነበረች።

"ዞር በልልኝ ከዚህ! አንተም እንደመንደሩ ሰው እብድ መሰልኩህ? ዞር በል ብዬሃለሁ።ምን በሀጢያት ተወልጄ?
ሀጢያትን ሳቦካ ብኖር ልጄን የምተኛ ሸርሙጣ ታደርገኛለህ?" ያለችኝ......

ያኔ በሀያ አምስት ዓመቴ በረንዳዋ ላይ እሷ ተቀምጣ በገዛሁላት መስታወት የፊቷ ገፅታ ላይ ይሁን የፊቷ ማድያት ላይ የተሳለ ያለፈ ህይወቷ ላይ አፍጥጣ፣ በእንጨት ማበጠሪያ ረዥሙን እና ሽበት ጣል ጣል የጀመረውን ፀጉሯን እያበጠርኩላት 'ላግባሽ?' ስላት ነበር፡፡

"አንተ ባለጌ!! እናትህ መሆኔ ጠፋህና ለብልግናህ ተመኘኸኝ?"
ብላኝ ነበር እንደልጅነቴ ባለማወቄ ያለመሆኑን ስታውቅ፡፡እየተወራጨች ቢሆንም የምታወራኝ ለዓመታት አመሻሽ ላይ የማበጥርላትን ፀጉሯን ማበጠር እንዳቆም የፈለገች አትመስልም።

"ድንች ሸጩ ባጠራቀምኩት ብር ሰርግ እደግስልሻለሁ፡፡ በወግ ማዕረግ አገባሻለሁ። ባልሽ እሆናለሁ::" አልኳት የዛን ዕለት።

የመቀየም ይሁን የማዘን ያልገባኝን መተራመስ ፊቷ ላይ አሳይታኝ በቀስታ እጄን ከፀጉሮቿ ላይ አንስታ ተነሳች።
አንዳንድ ጊዜ እናቴ የሚያስመስላትን ፊቷን አመጣችው አንዳንዴ እንደሚሆነው የሌላ ሰው ከባድ ሰውነት የተሸከመ
ይመስል እግሯ እየተጎተተ ወደ ቤቷ ገባች። እንደነዚህ አይነት
አንዳንድ ቀኖቿ ላይ እንደማደርገው ተከተልኳት፡፡ ኩርምት ብላ መደቧ ላይ ተኛች፡፡ ትዩዩ ያለው ጠባብ መደብ ላይ ተቀምጬ አያታለሁ። ዓይኖቿ እንባ አቀረሩ።

#ያኔ.......

እቤት ስጠፋ ብቅ ይል የነበረው ያሳደገኝ ብቸኛው ዘመዴ አያቴም ስለሞተ እቤቷ ከኔ ውጪ ማንም አይገባም፡፡ የቀረው
ልጇም ሊዘርፋት የሚችለው ገንዘብ ስላልነበራት መኖሪያውን ከሷ አርቋል፡፡

#ያኔ.......

ነፍስ ያለው ሳቋ ብቸኛ ምንጭ የሆኑት ጤንነቷን በሚጠራጠሩ የመንደራችን ቤተሰቦች በተደጋጋሚ የሚቀጡት ህፃናት እንኳን ሲርባቸው እንዳልበሉ፣ ሲታረዙ በኪሮሿ ሹራብ ሰርታ እንዳላለበሰቻቸው፣ እናታቸው እንዳልነበረች ሁሉ ከቤቷ ቀሩ።

#ያኔ.......

“መካሪ ስለሌለው'፣ “እሱም እንደሷ እብድ ነው'፣ “አሳዳጊ የበደለው ሌላ ብዙ የምባለው እኔ ብቻ በጎጆዋ ነበርኩ፡፡

“የሙሽራ ልብሴን አልብሰኝ፡፡ ቀለበቱን እሰርልኝ፡፡ ወግ ማዕረግ አይታ ሞተች ልባል።" ያለችኝ

#አሁን.....

በጉልምስናዬ በበሽታ እና በሃዘን የደቀቀ ሰውነቷን መደቧ ላይ አሳርፋ፣ በመስታወቷ ልታየው የማትፈልገውን የፊቷን ገፅታ በእጆቿ ሸፍና፣ ከሚቆራረጥ ትንፋሿ እየታገለ በሚወጣ ቀሰስተኛ ድምፅዋ ነበር።

“ልጇን ያገባች ባለጌ ናት እንዲሉኝ አልፈልግም፡፡ ወግ ማዕረግ
ሳታይ ሞተች እንዲሉኝም አልፈልግም። ሊቀብሩኝ ሲመጡ ሙሽራ ሆኜ ያግኙኝ፡፡" አለችኝ፡፡ ግድግዳው ላይ በላስቲክ
ተሸፍኖ የተሰቀለውን ከአዲስ አበባ የገዛሁላትን የሙሽራ ቀሚስ ለመገለጥ በደከማቸው ዓይኖቿ እያየች።

በዚህ ቅፅበት የምላት ስላልነበረኝ ምንም አላልኳትም፡፡ ለገላዋ የወዘፍኩትን ውሃ በርዤ ገላዋን አጠብኳት። የታመመች ሰሞን ታደርግ እንደነበረው ሰውነቷን እንዳላይ አቅሙ ኖሯት አትከለክለኝም።

በአበባነት ዘመኗ እንደምታደርገው ሰውነቷን ውብ ጠረን ባለው ቅባት አሸሁላት፡፡ የሙሽራ ቀሚሷን አለበስኳት፣ ነጩን ጫማ አጠለቅኩላት፣ በሽበት የተወረረ ተነቃቅሎ ያለቀ ፀጉሯን አበጥሬ
በልጅነቴ ስታደርግ እንዳየኋት ጠቅልዬ በክር አስያዝኩላት፣ስታደርግ እንዳየኋት ዓይኗን በኩል ከንፈሯን በቀለም
አሳመርኩላት፣ ጣቷ ላይ ቀለበት አጠለቅኩላት። እንደቆነጀች
መደቧ ላይ አስተኝቻት በልጅነቴ የማውቀውን አሁን እያማጠች
የምትፈግገውን ነፍስ ያለው ፈገግታ አያለሁ፡፡ ከልጅነት እስከ ጉርምስና፣ ከወጣትነት እስከ ጉልምስና
የኖርኩለት ህልሜ እሷ ነበረች።ህልሜ በበሽታ ደቃ ልትሞት እጄ ላይ እያጣጣረች ነው። ከዚህ ወዲያ የምኖረው ለምን ይሆን? ለማንስ ይሆን?

#አሁን......

ላግባሽ ብዬ ስማፀናት “አሻፈረኝ ልጄ ነህ' ያለችኝ ወይንሽት በሞቷ አፋፍ ላይ ቀለበት እንዳደርግላት ጠየቀችኝ፡፡

#አሁን.....

ህልምና ዓለሜ የሷ ባል መሆን ብቻ የነበረው እኔ ህልሜ አብሯት ሊሞት እጄ ላይ ነው። ዓለሜም ሊጨልም እየተንደረደረ ነው።

#አሁን...

ባሏ ልሆን ማደጌን፣ ምኞቷን ልሞላላት መጎርመሴን፣ ማዕረጓን እንድታገኝ መጎልመሴን እንጂ እሷ ሚስቴ እንድትሆን ይሁን እናቴ እንድትሆን የምፈልግ የተዘባረቀብኝ እኔ አንዴ እናቴ ሌላ ጊዜ ወይንሽት የምትሆንብኝ ዓለሜ ልትሞት ነው፡፡ ሞታ ልትገድለኝ ነው።

#አሁን......

የወለደቻቸው፣ ያሳደገቻቸው፣ ያበላቻቸው፣ ያለበሰቻቸው፣ ያባበለቻቸው፣ የመከረቻቸው፣ በፍቅር ጉያዋ የተጠለሉ ህፃናት ሁላ አድገዋል። አይፈልጓትም። ሌላ የሚጠለሉበት ጉያ
ተሸሽገዋል።መሀን አድርገዋታል። ሊያለቅሱላት ግን ይመጣሉ።
እናታችን ነበረች ሊሉ።

#አሁን......

አግብተዋት ባሏ ያልነበሩ፣ በባልና በመሽማ ስም የተጣቧት፣
በውበቷ ፍሰሃ ያገኙ፣ ባለፈው እሷነቷ ውስጥ የነበሩ፣ የልቧን ዙፋን
የተቀራመቱ፣ በሴትነቷ የሰለጠኑ.... እነሱም አይፈልጓትም።ስግብግብ ምኞታቸውን አሟልተውባታል።
አሁን የሚቦጠቡጡት ጥቅም እሷጋ የለም። እነዚህም በእድሜና
ምቾት የሰባ ስጋቸውን አስቀድመው እና ፀጉር አልባ ራሳቸውን እየነካኩ ይመጣሉ። ሊያለቅሱላት፡፡ ወዳጃችን ነበረች፣ ፍቅራችን ነበረች፣ እያሉ ሊያለቅሱላት።

#አሁን......

ባሏ እንዳልሆን በልጅነቴ የሰለጠኑባት ባል መሳዮች ሲያበግኑኝ በጉርምስናዬ በግድ ያለፍላጎቷ አግብቻት እንዳለፉት ባሎቿ እንዳልመዘብራት ፈርቼ፣ በወጣትነቴ ፍላጎቷን አክብሬ፣ በዙፋኗ
ልትሾመኝ እንዳላመነችኝ ገብቶኝ ታግሼ፣ በጉልምስናዬ ደግሞ ባሏ ሆኖ ሙቀቷን ከመጋራት እና እናቴ ሆና ከምጠብቃት
የትኛውን እንደምመርጥ ግራ እየገባኝ ህልሜ፣ ዓለሜ......የመኖሬ ምክንያት የሞቷ አፋፍ ላይ ናት፡፡

አለቅስላታለሁ፡፡ እናቴ ሞተች ብዬ የልጆቿን ሁሉ አለቅስላታለሁ። ሚስቴ ሞተች ብዬ የሰውነቷን ጥፍጥና
የቀመሱትን ለቅሶ ሁሉ አለቅስላታለሁ። እኔ ህልሜ ሞተች ብዬ የራሴን አለቅስላታለሁ።እንደባል የሰለጠኑባትም እንደ ልጅ የተጠለሉባትም የተዋት
መታመሟ ያላመማቸው የሁሉም የነበረች እሷ በሞቷ ዋዜማ እጄ ላይ ናት።የእኔ እጅ ብቻ ላይ ሙሽራዬ!!!

አ...ለ...ቀ

በዚህስ ድርሰት ላይ ምን ውስጣቹ ተብላላ? አሳውቁኝ።

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
#ህያብ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_በኤርሚ



#ከጊዜያት_በኋላ

"ንገሪኝ እስኪ ህያብ ሀኪም እንዲያይሽ ባትፈልጊም ህመምሽን ለኔ ንገሪኝ ዝምምም ብዬ እሰማሻለሁ። ስለ ልጅሽ ስለ ዮኒ ስለተፈጠረው ሁሉንም ንገሪኝ" ሶስት ወራትን በዝምታ ስለዚህ ነገር ሳያነሳብኝ ሳላወራው በየጊዜው የአእምሮ ህመሜ እየተነሳ ከኔው እኩል ሲሰቃይ አሳልፈናል። ትዕግስቱ እንክብካቤው ፍቅሩ ድሮ ከማውቀው የበለጠ ተወዳጅ ሆኖ ነው ያገኘሁት። ግን ምን ዋጋ አለው ፍቅር አንዳንዴ ፍትሀዊ አይደለም ቢሆንማ ኖሮ የማፈቅረው ዮኒን ሳይሆን ቢኒን ነበር። ወደ መኝታ ቤት ሄድኩ... ተከተለኝ... በሩን ከፍቼ ገባሁና ቤቴ ሄደን ካመጣናቸው እቃዎች መሀል አነስተኛውን ሻንጣዬን አወረድኩት... ከፈትኩት... ውስጡ ያለው ሁሉም የልጄ ማስታወሻ ነው። ለአዲስ አመት የሳለችልኝን አበባ አገኘሁት... እሱን አቅፌ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ

"የኔ ልጅ... የኔ እንቁ... ናፈቅሽኝ እኮ" ቢኒ አጠገቤ ብርክክ ብሎ ትከሻዬን ያዘኝ ከዛም ወደራሱ አስጠግቶ አቀፈኝ። ህመሜ ሳይነሳ ለመጀመሪያ ጊዜ ራሴን አረጋጋሁና ከእቅፉ ወጥቼ ከመፅሀፍ መሀል አጣጥፌ ያስቀመጥኩትን ደብዳቤ አወጣሁት... ከባዱን መርዶ ያረዳኝን... መራራውን እውነታ የጋተኝን ደብዳቤ አወጣሁና ለቢኒ ሰጠሁት። ግራ በተጋባ ፊት ካየኝ በኋላ ከፈተው... ደጋግሜ ከማንበቤ የተነሳ እያንዳንዱን ቃል እንደ ውዳሴ ማርያም የሸመደድኩትን ደብዳቤ እሱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊያነበው ከፈተው... እንዲህ ነው የሚለው...

"ማሚ ከበደል ሁሉ የቱ እንደሚከፋ ታውቂያለሽ... አባቴ የምትይው ሰው በስሜት ጦዞ ጭንሽን ሊከፍት ሲታገል ማየቱ...... ማም እውነቱ ይገልሻል አውቃለሁ ...ግን እንደዛ ጠንካራ ስነ ልቦና እንዲኖራት አድርገሽ ያሳደግሻት ልጅሽ ለምን ራሷን አጠፋች? የሚለው ጥያቄም ይገልሻል። ማም እውነቱን እወቂው..... መጀመሪያ የውሸት ቆይቶ ደግሞ የእውነት አባት የሆነኝ ዮኒ የውሸት አባቴ እያለ አንዴ ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ ደፍሮኛል። ታስታውሻለሽ ያኔ ፔሬድ አሞኝ ነው ብዬሽ የተኛሁ ጊዜ... ለመጀመሪያ ጊዜ የደፈረኝ ቀን ነበር። አንቺ ውስጥ እያለሽ ሊጠይቀኝ ሲመጣ ፊቴን አዙሬበት ነበር አይደል? ከዛ አንቺ ወጣሽ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ 'በሶስተኛው ቀን መድገም አለብን ካላዛ ተደፍነሽ ትቀሪያለሽ' አለኝ። እናም በሶስተኛው ቀን መኝታ ቤቴ ድረስ መጣ... መከላከል ደከመኝ እና በዝምታ አየሁት ሳይራራልኝ እላዬ ላይ ጨፍሮ ሄደ... ያንኑ ድርጊቱን የአባትነት እውነታው እስከሚታወቅ ድረስ ደጋገመው። በተለይ ፊልድ መውጣትሽ ለሱ ምቹ ሁኔታ ለኔ ደግሞ ስቃይን ፈጠረ

ካንቺ ፊት ላይ የየሁትን ደስታ እኔ ጋር ፈልጌ አጣሁት። ማም እንዴት ልደሰት... አባቴን አገኘሁ ብዬ እንዴት ደስ ይበለኝ...? አባትነቱን እኮ ጭኔ መሀል ቆፍሮ ቀብሮታል። እናም አባቴ አይደለም ሊሆንም አይችልም ብዬ በዝምታ ተሸብቤ ቁጭ ብዬ እያለ ሌላ ክስተት ተፈጠረ። በየጊዜው እየመጣ ይቅርታ ብሎኝ 'አደራ ለናትሽ እንዳትነግሪያት' ከሚለኝ ከህሊናቢሱ አባቴ የስምንት ሳምንት ነብሰ ጡር እንደሆንኩ ሆስፒታል አረጋገጥኩ። ያኔ በራሴ ላይ ወሰንኩ... ታሪክ ራሱን አይደግምም... ማም አንቺ አባት እንደሌለኝ እያሰብሽ ወልደሽ እሳደግሺኝ... የኔ ልጅ አባት ግን አባቴ ነው... እናም በራሴ ላይ እና ባልወለድኩት የአባቴ ልጅ ላይ የሞት ፍርድ ወሰንኩ።

ማሚዬ ለኔ ስትይ ጠንክረሽ ኑሪ እወድሻለሁ።
እድለቢሷ ልጅሽ"

ደብዳቤውን አንብቦ ከጨረሰ ቢቆይም እንባ ከአይኖቹ እየወረደ ፍዝዝ ብሎ ተቀምጧል።

"ይህን ደብዳቤ ሳገኘው ቢኒ ጊዜው ረፍዷል... የልጄ ገዳይ አጠገቤ አልነበረም... ትቶኝ ሄዶ ነበር... ፈለኩት በየሆስፒታሉ በየሆቴሉ ግን አጣሁት... ባገኘው በአደባባይ ስጋውም ዘልዝዬ ለአሞራ እሰጠው ነበር"። እያለቀሰ መጥቶ አቀፈኝ ረጅም ሰአት ተቃቅፈን ተላቀስን...።

"እባክሽ አንድ ነገር እሺ በይኝ የስነልቦና ሀኪም ይይሽ እባክሽ ለኔ ስትይ" ለብዙ ጊዜ ደጋግሞ ቢጨቀጭቀኝም እምቢ ነበር መልሴ

"እሺ ደስ ያለህ ሀኪም ጋ ውሰደኝ"

።።።።። ።።።።። ።።።። ።።።።። ።።።

የስነ ልቦና ህክምናዬን ከጀመርኩ አንድ ሳምንት ቢያልፈኝም ለዶክተሬ ምንም የነገርኩት ነገር አልነበረም። የሆነ ቀን ግን ልክ ከዚህ በፊት ያለውን ታሪክ እንደሚያውቀው ሁሉ

"ዮኒን ብቻ ጥፋተኛ አድርጌ እንዳልፈርድ የሚያደርገኝ እንደዚህ ያሳመመኝ ብዙ ፀፀት ውስጤ አለ። ብዙ ቢሆን ኖሮ.... ብዙ.... ብዙ....

•ከመጀመሪያው ታሪኬን ነግሬው ቢሆን ኖሮ

•ስራ ስራ ማለቴን ትቼ ለልጄ ጊዜ ሰጥቻት ቢሆን ኖሮ

•እንደዛ ሆና እያየኋት ትንሽ እንኳን ለምን አልተጠራጠርኩም... አሁን እኔ ዶክተር እባላለሁ...

ከሁሉም በላይ ፀፀቱ በልቶ ጨረሰኝ... መገጣጠሚያ አጥንቴ እስከሚታይ ከሳሁ... ጠቆርኩ... ታመምኩ... አበድኩ ...ግን ትርጉም አልነበረውም... እኝህ ሁሉ የኔን እንቁ አይመልሱልኝም ባዶ... አንተስ የኔን እንቁ ትመልስልኛለህ? አየህ እዚህ መጥቼ መፋጠጣችንም ትርጉም የለውም ባዶ..." አልኩት። ዝምምም ብሎ ካየኝ በኋላ ከወንበሩ ተነስቶ መጥቶ ፊት ለፊቴ ሶፋ ላይ ተቀመጠ

ከስድስት ወራት ያላሰለሰ የህክምና ክትትል በኋላ ወደራሴ ተመለስኩ ወደ ስራየም ጭምር። ከቢኒ ጋር ደስ የሚል የፍቅር ግንኙነት ጀመርኩ... ህይወት ድጋሚ ቀጠለች። ያለፈው ባይረሳም ህመሙ ቀንሷል... የልቤ በልቤ ተቀብሮ መሳቅ ቻልኩ።

ከቢኒ ጋ ልንጋባ ነው ማለትም ከሁለት ወር በኋላ እንጋባለን። ለፊርማው እንጂ የምንኖረው አንድ ቤት የምንተኛው አንድ አልጋ ላይ ከተጋባን ቆይተናል ለማለት ነው። ልንጋባ መሆኑን ያወቀው ሀብታሙ ካለበት ሀገረ አሜሪካ የሚያምር ቬሎና ሱፍ ልኮልናል። ለቢኒ ሚዜ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ።

የሆነኛው ሌሊት ላይ ተኝቼ ልጄን በህልሜ አየኋት... ብቻዋን አይደለም ዮኒ ሲደፍራት "ድረሽልኝ" እያለች ስትጮህ... ጮኬ ከእንቅልፌ ነቃሁ... አጠገቤ የተኛው ቢኒ ጩኸቴ አስደንግጦት

"ምንድነው ፍቅር አይዞሽ ቅዠት ነው" አለና እቅፉ ውስት ከተተኝ... እኔ ግን የበቀል ጥሜ ድጋሚ አንሰራራ... እፈልገዋለሁ እናም እገለዋለሁ... እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ።

ለቀናት በሀሳብ ተብሰከሰኩ እናም ወሰንኩ ይህን ነገር ከስሩ መንግዬ መጣል ይኖርብኛል። ተቆርጦ ባቆጠቆጠ ቁጥር ህመሙ እየባሰ ነው የሚሄደው ስለዚህ እ ገ ለ ዋ ለ ው

#አሁን

ትቼው ልሄድ ነው። በቃ ልሄድ ነው የመጨረሻ ውሳኔዬን ወስኛለሁ የምሄደው እንደ ሌላው ጊዜ ጥላቻንና ክህደትን ሽሽት አይደለም... ፍቅርን እንጂ።
እናም በሀሳብ እየዋዠኩ ደብዳቤ ልፅፍለት ወሰንኩ ቢያንስ ምክንያቴን ማሳወቅ አለብኝ አይደል... ደግሞ ጠፋች ብሎ ሀገር ምድሩን ነው የሚያምሰው...

መፃፍ ጀመርኩ

"አንዳንዴ ልቋቋመው ከምችለው በላይ ይሆንብኛል። ፍቅርህ፣ ስስትህ፣ እንክብካቤህ፣ አንተን ትተህ ለኔ ደስታ መድከምህ፣ ከቃላት ጋጋታ ይልቅ በተግባር የምታሳየኝ መውደድህ በአጠቃላይ ሁሉም ነገርህን መቋቋም ያቅተኛል።