#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ፍፁም ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ
ቤዛዊት በተቀመጠችበት ቦታ በሀሳብ እሩቅ ተጉዛ ስለ ፍፁም መቅረት ትብከነከናለች
"ምን ሆኖ ቀረ?"
በአይምሮዋ የሚመላለስ ጥያቄ ነዉ።
ሀሳቧ ሁለት ፅንፍ ይዞ ይጋጫል
"ይመጣል አይቀርም"
የሚል የመፅናኛ እና የጤነኝነት ሀስብ በተቃራኒዉ
"አይመጣም ቀርቷል"
የሚል በህመም የገነነ ዉጥረት ባላቸዉ ጥያቄወች ተዉጣ በቀኝ እጇ አገጯን ደገፍ አርጋ
አይኖቿን አሁንም ፊት ለፊቷ አሻግራ ተስፋ ባለነቁረጥ የፍፁምን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ
ቆይታ አሉታዊዉ ሀሳቧ የፍፁምን መቅረት አሳምኗት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ዘላ ተነስታ እንደወታደራዊ አቋቋም በተጠንቀቅ ከቆመች በኋላ ለመራመድ መንቀሳቀስ ስትጀምር
በርቀት ሁኔታዋን ሲታዘቡት የነበሩት እማማ ስንቅነሽ ፈጠን እያሉ ተራምደዉ አስቆሟት
"የት ልትሄጂ ነዉ ልጄ?"
በእድሜ ብዛት የደከመ በሚመስል አሳዛኝ የእናትነት ድምፅ
የቤዛዊትን እጆች ለመያዝ እጃቸዉን እየሰደዱ
"ቀረ በቃ አይመጣም"
ቆጣ ብላ እጆቿን እያወናጨፈች ሊይዟት የቀረቡትን የእማማ ስንቅነሽን እጅ እየገፋች
"ማን ..."
ካሉ በኋላ እማማ ስቅነሽ ይመጣል እየጠበኩት ነው ያለቻቸዉን አስታዉሰዉ
"ፍፁምን ነዉ ምን አለ ትንሽ ብትጠብቂዉ ታድያ ልጄ ወዴት ልትሄጂ ነው የተነሳሽዉ.."
ከጎናቸዉ እንዳትርቅ እየፈለጉ ቤዛዊትን ማባበል ጀመሩ
የት እንደምትሄድ ያላረጋገጠችዉ ቤዛዊት ግን የእማማን ተማፅኖ ከቁብ ሳትቆጥር
ሂጂ ሂጂ የሚላትን ስሜት እየተከተለች እማማን
"እመለሳለሁ እመለሳለሁ እሺ"
እያለች በእርጅናና በህይወት የጎበጠ ትከሻቸዉን በእጇ ዳበስ አርጋ
እማማ ስንቅነሽን ወደ ኋላ ትታ እስዋ ወደ ፊት መራመድ ጀመረች።
ፍፁም ፍቃዱን አመልጣለሁ ብሎ ዘዉ ብሎ የገባበት ቤት መኖርያ ቤት መስሎት እየተሳቀቀ የያዝኩትን ክራንች ማነከሴንም አይተዉ ያዝኑልኛል ብሎ ሰተት እንዳለ
ቤቱ ዉስጥ በቁጥር የሚቆጠሩ ሰወች ሰብሰብ ብለዉ ስላየ በፍርሀት እና ተመልሼ ልዉጣ አልዉጣ እያለ በቆመበት
ሲያስብ አንዲት ደርባባ ሴትዮ ከቤቱ ዉስጠኛ ክፍል መጋረጃ ገልጣ ስትወጣ ፊት ለፊት ሲገጣጠሙ ፍፁም እንደምንም ብሎ
"ሰላም ዋልሽ"
አንገቱን ለሰላምታ ያክል ዝቅ እያረገ
ሴትየዋ ፊት ለፊቷ አይታዉ የማታዉቀዉ ሰዉ በማየቷ ጥቂት ተገርማ ክራንቹን አቋቋሙን ፊቱን በገረፍታ አይታዉ ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ
"እንዴ ምን አስቆመህ አረፍ በል እነጂ..."
በአይኖቿ ሰወቹ ከተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ክፍት ቦታ እያሳየችዉ መቀመጡን ስታይ ተመልሳ ወደ ጓዳዋ ፈጠን እያለች ገባች
ፍፁም የተቀመጡትን ሰወች ቃኛቸዉ የራሳቸዉ ጨዋታ ላይ ናቸዉ ሁሉም እግራቸዉ ስር ንኬል ተቀምጧል መሀል ላይ ጆግ ሙሉ ጠላ መኖሩን አስተዋለ ወድያዉ ሴትየዋ በጣሳ ዉሉ ጠላ ይዛ መጥታ ፊት ለፊቱ አስቀመጠች
ጠላ ቤት መግባቱ ስለገባዉ ፈገግ እያለ አመስግኖ ተቀብሎ መጠጣት ጀመረ።
ቤዛዊት የመንገዱን ጠርዝ ይዛ በለሆሳስ እያወራች ከንፈሮቿ እየተንቀሳቀሱ አንዴ ቆም
ብላ እያሰበች ሲላት ፈጠን ፈጠን እያለች እየተራመደች ነዉ
"ቀረ !!"
አንገቷን ከግራ ወደ ቀኝ እያንቀሳቀሰች
"ቤቱ ለምን አልሄድም እንደዉም እሄዳለሁ"
እጇን ከንፈሯ ላይ ጣል አርጋ ትንፋሽ እየሳበች አሰበች
"ይሄኔ ከእህቴ ጋር ይሆናል"
ንዴቷ እየጨመረ ሄዶ እጆቿን ለቡጢ በሚመስል አኩዋሀን ጨበጠቻቸዉ
ወደ ፍፁም ቤት ሄዳ ፍፁም እና እህቷን አብረዉ ሆነዉ ስታገኛቸዉ ምን ልታረግ እንደምትችል እያሰበች
"ኪኪኪኪኪ ኪኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
እየተንከተከተች ስትስቅ መንገደኛ ሰዉ አይቷት እጆቹን ለማማተብ አንዴ ግንባሩን ቀጥሎ ወደ ሆዱ በስተመጨረሻ ሁለቱን ትከሻወቹን አስነክቶ እየዞረ እያያት ሲያልፍ ሳቋን አቁማ ኮስተር ለማለት እየሞከረች ወደ ፍፁም ቤት አመራች።
ፍቃዱ በንዴት ብዛት ተበሳጭቷ ባዶ ሜዳ ላይ ቆሞ ይዉረገረጋል
"እንዴት ይሄ ያመልጠኛል የት ሊገባ ይችላል"
እያለ በቆመጠት ዙርያዉን ይቃኛል ነገር ግን ፍፁምን ማየት ስላልቻለ እና ፀሀይዋም አቅም አሳጥታዉ ስለደከመዉ ለመመለስ እያሰበ ጥቂት ወደ ኋላ ሲራመድ
አንድ ጎልማሳ ሰዉዬ የጣሳ ምልክት ከተሰቀለበት ቤት በመጠኑ ገድገድ እያለ ሲወጣ ተመልክቶ ቆመ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ፍፁም ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ
ቤዛዊት በተቀመጠችበት ቦታ በሀሳብ እሩቅ ተጉዛ ስለ ፍፁም መቅረት ትብከነከናለች
"ምን ሆኖ ቀረ?"
በአይምሮዋ የሚመላለስ ጥያቄ ነዉ።
ሀሳቧ ሁለት ፅንፍ ይዞ ይጋጫል
"ይመጣል አይቀርም"
የሚል የመፅናኛ እና የጤነኝነት ሀስብ በተቃራኒዉ
"አይመጣም ቀርቷል"
የሚል በህመም የገነነ ዉጥረት ባላቸዉ ጥያቄወች ተዉጣ በቀኝ እጇ አገጯን ደገፍ አርጋ
አይኖቿን አሁንም ፊት ለፊቷ አሻግራ ተስፋ ባለነቁረጥ የፍፁምን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ
ቆይታ አሉታዊዉ ሀሳቧ የፍፁምን መቅረት አሳምኗት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ዘላ ተነስታ እንደወታደራዊ አቋቋም በተጠንቀቅ ከቆመች በኋላ ለመራመድ መንቀሳቀስ ስትጀምር
በርቀት ሁኔታዋን ሲታዘቡት የነበሩት እማማ ስንቅነሽ ፈጠን እያሉ ተራምደዉ አስቆሟት
"የት ልትሄጂ ነዉ ልጄ?"
በእድሜ ብዛት የደከመ በሚመስል አሳዛኝ የእናትነት ድምፅ
የቤዛዊትን እጆች ለመያዝ እጃቸዉን እየሰደዱ
"ቀረ በቃ አይመጣም"
ቆጣ ብላ እጆቿን እያወናጨፈች ሊይዟት የቀረቡትን የእማማ ስንቅነሽን እጅ እየገፋች
"ማን ..."
ካሉ በኋላ እማማ ስቅነሽ ይመጣል እየጠበኩት ነው ያለቻቸዉን አስታዉሰዉ
"ፍፁምን ነዉ ምን አለ ትንሽ ብትጠብቂዉ ታድያ ልጄ ወዴት ልትሄጂ ነው የተነሳሽዉ.."
ከጎናቸዉ እንዳትርቅ እየፈለጉ ቤዛዊትን ማባበል ጀመሩ
የት እንደምትሄድ ያላረጋገጠችዉ ቤዛዊት ግን የእማማን ተማፅኖ ከቁብ ሳትቆጥር
ሂጂ ሂጂ የሚላትን ስሜት እየተከተለች እማማን
"እመለሳለሁ እመለሳለሁ እሺ"
እያለች በእርጅናና በህይወት የጎበጠ ትከሻቸዉን በእጇ ዳበስ አርጋ
እማማ ስንቅነሽን ወደ ኋላ ትታ እስዋ ወደ ፊት መራመድ ጀመረች።
ፍፁም ፍቃዱን አመልጣለሁ ብሎ ዘዉ ብሎ የገባበት ቤት መኖርያ ቤት መስሎት እየተሳቀቀ የያዝኩትን ክራንች ማነከሴንም አይተዉ ያዝኑልኛል ብሎ ሰተት እንዳለ
ቤቱ ዉስጥ በቁጥር የሚቆጠሩ ሰወች ሰብሰብ ብለዉ ስላየ በፍርሀት እና ተመልሼ ልዉጣ አልዉጣ እያለ በቆመበት
ሲያስብ አንዲት ደርባባ ሴትዮ ከቤቱ ዉስጠኛ ክፍል መጋረጃ ገልጣ ስትወጣ ፊት ለፊት ሲገጣጠሙ ፍፁም እንደምንም ብሎ
"ሰላም ዋልሽ"
አንገቱን ለሰላምታ ያክል ዝቅ እያረገ
ሴትየዋ ፊት ለፊቷ አይታዉ የማታዉቀዉ ሰዉ በማየቷ ጥቂት ተገርማ ክራንቹን አቋቋሙን ፊቱን በገረፍታ አይታዉ ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ
"እንዴ ምን አስቆመህ አረፍ በል እነጂ..."
በአይኖቿ ሰወቹ ከተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ክፍት ቦታ እያሳየችዉ መቀመጡን ስታይ ተመልሳ ወደ ጓዳዋ ፈጠን እያለች ገባች
ፍፁም የተቀመጡትን ሰወች ቃኛቸዉ የራሳቸዉ ጨዋታ ላይ ናቸዉ ሁሉም እግራቸዉ ስር ንኬል ተቀምጧል መሀል ላይ ጆግ ሙሉ ጠላ መኖሩን አስተዋለ ወድያዉ ሴትየዋ በጣሳ ዉሉ ጠላ ይዛ መጥታ ፊት ለፊቱ አስቀመጠች
ጠላ ቤት መግባቱ ስለገባዉ ፈገግ እያለ አመስግኖ ተቀብሎ መጠጣት ጀመረ።
ቤዛዊት የመንገዱን ጠርዝ ይዛ በለሆሳስ እያወራች ከንፈሮቿ እየተንቀሳቀሱ አንዴ ቆም
ብላ እያሰበች ሲላት ፈጠን ፈጠን እያለች እየተራመደች ነዉ
"ቀረ !!"
አንገቷን ከግራ ወደ ቀኝ እያንቀሳቀሰች
"ቤቱ ለምን አልሄድም እንደዉም እሄዳለሁ"
እጇን ከንፈሯ ላይ ጣል አርጋ ትንፋሽ እየሳበች አሰበች
"ይሄኔ ከእህቴ ጋር ይሆናል"
ንዴቷ እየጨመረ ሄዶ እጆቿን ለቡጢ በሚመስል አኩዋሀን ጨበጠቻቸዉ
ወደ ፍፁም ቤት ሄዳ ፍፁም እና እህቷን አብረዉ ሆነዉ ስታገኛቸዉ ምን ልታረግ እንደምትችል እያሰበች
"ኪኪኪኪኪ ኪኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
እየተንከተከተች ስትስቅ መንገደኛ ሰዉ አይቷት እጆቹን ለማማተብ አንዴ ግንባሩን ቀጥሎ ወደ ሆዱ በስተመጨረሻ ሁለቱን ትከሻወቹን አስነክቶ እየዞረ እያያት ሲያልፍ ሳቋን አቁማ ኮስተር ለማለት እየሞከረች ወደ ፍፁም ቤት አመራች።
ፍቃዱ በንዴት ብዛት ተበሳጭቷ ባዶ ሜዳ ላይ ቆሞ ይዉረገረጋል
"እንዴት ይሄ ያመልጠኛል የት ሊገባ ይችላል"
እያለ በቆመጠት ዙርያዉን ይቃኛል ነገር ግን ፍፁምን ማየት ስላልቻለ እና ፀሀይዋም አቅም አሳጥታዉ ስለደከመዉ ለመመለስ እያሰበ ጥቂት ወደ ኋላ ሲራመድ
አንድ ጎልማሳ ሰዉዬ የጣሳ ምልክት ከተሰቀለበት ቤት በመጠኑ ገድገድ እያለ ሲወጣ ተመልክቶ ቆመ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።
ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።
እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።
የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።
“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"
“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?
አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።
“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።
« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”
ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።
“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።
ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።
ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።
“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-
ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።
“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣
እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "
ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።
“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።
“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።
ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።
አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?
“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው
ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።
“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ
“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።
አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።
“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር
“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።
“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”
" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”
በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።
እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል
እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።
ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።
"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ
“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።
ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።
ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።
እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።
የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።
“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"
“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?
አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።
“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።
« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”
ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።
“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።
ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።
ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።
“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-
ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።
“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣
እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "
ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።
“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።
“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።
ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።
አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?
“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው
ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።
“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ
“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።
አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።
“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር
“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።
“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”
" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”
በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።
እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል
እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።
ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።
"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ
“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።
ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ
...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡
ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡
“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡
ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....
ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡
ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡
እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡
በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ
...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡
ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡
“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡
ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....
ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡
ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡
እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡
በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
👍3
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....እንደ ድንጋይ ከተጫናት ሰመመን ውስጥ ቀስ በቀስ እየወጣች ስትመጣ… እላይዋ ላይ ተጭኖ የያዛት ድቅድቅ ጨለማ እንደ ጭስ እየሳሳ እየበነነ ለቋት ሲጠፋ በመጀመሪያ የተቀበላት በእግሮቿ መሃል የሚነዝራት የደነዘዘ ስቃይ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ እየጠራ ሲመጣም አይኖቿን ለመክፈት አልደፈረችም፡፡ ሌላ ዱላ፣ ሌላ ስቃይ ሌላ የጋለ ሽቦ የሚችል
አካል አልነበራትም። በክፍሉ ውስጥ ብቻዋን ትሁን አትሁን እርግጠኛ
አልነበረችም፡፡ አይኖቿን ለመክፈት ግን አልደፈረችም፡፡
እጆቿ ግራና ቀኝ ተወጥረው ከታሰሩሰት ተፈተው በድን እንደሆኑ ሁሉ በግራና በቀኝ ተዘርረዋል፡፡ በተኛችበት ልብስ ደርበውላታል፡፡ እግሮቿ ግን አሁንም ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ተወጥረው እንደታሰሩ ናቸው፡፡ ቁስሏን ለማዳመጥ ሞከረች፡፡ በጭኖቿ መሃል የሚሰማትን ስቃይ ለማዳመጥ ዝም አለች የተዳፈነ... የደነዘ… የደበዘዘ ስቃይ፡፡ ግራ ክንዷ ላይ ህመም ተሰማት:: ለመነቃነቅ ግን አልደፈረችም፡፡ በአይነ ህሊናዋ ሁኔታውን
ለመቅረፅ ሞከረች። መቼ ነበር በጋለ ሽቦ ጭኖቿ መሃል ሰውነቷን ያቃጠሏት? ዛሬ? ትላንት? ዛሬ ምንድነው? ቀን ነው ሌሊት? ሰዓታትና ቀናት ትርጉም ካጡባት ቆይተዋል፡፡
ድምፅ የሰማች መስላት። ዓይኖቿን እንደከደነች ጆሮዎቿን ኣስልታ ተጠባበቀች፡፡ የበር ድምፅ ተሰማት… የሚከፈት የበር የሚያሰማው ድምፅ..
“አልተነሳችም፡፡” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ፡፡
“ኮለኔል” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ “ዙርያውን አጥረነዋል።በርም ላይ አንድ ሰው አቁመን እየተጠባበቅን ነው::”
“መጣሁ” ሲል ተሰማት ማርቆስ፡፡
ሁለት የእግር ኮቴዎች በግራና በቀኟ ተስሟት…በስተቀኝ ኣንድ መዳፍ ግንባሯ ላይ አረፈ::
“ከነቃች የመርፌ ማደንዘዣውን ስጣትስቃይ ሊኖርባት ይችላል።” የማርቆስ ድምፅ ነበር።
“ካስቸገረችኝስ ልምታት?” አለ በስተግራዋ የቆመ ሌላ ሰው፡፡
“ረጋ ብለህ አባብለህ ውጋት። ለምን ትመታታለህ? ደግሞ አታስቸግርህም.. ከተወራጨችብህ ግን ግሉኮሱን ንቀልላት፡፡” አለ እጁን ግንባሯ ላይ የጫነው ማርቆስ በጣቶቹ ፀጉሯን ወደኋላ እያበጠረ፡፡ “ጠዋት እቀየርልሃለሁ፡፡”
ኮቴ ተሰማት፡፡ ተከታትለው ሲወጡ ሰማች። በሩ ሲዘጋ በክፍሉ ውስጥ ፀጥታ ሲነግስ ስትፈራ ስትቸር አይኖቿን ገለጠቻቸው::መኝታ ክፍሏ ውስጥ ብቻዋን አስተኝተዋታል፡፡ በቢጫው የብርድ ልብሷ ከአንገቷ እስከ
እግሯ ጫፍ ድረስ ሸፍነዋታል፡፡ በተንጋለለችበት ዙሪያዋን ተመለከተች፡፡
ግራ ክንዷ ላይ የሚሰማት ህመም ከራስጌዋ ከተንጠለጠለው የግሉኮስ
ከረጢት ጋር የተያያዘው መርፌ ክንዷን ጠልቆ የገባበት ላይ መሆኑን ተረዳች። የክፍሉ መጋረጃ ተዘግቷል፡፡ በጥግና ጥግ የታየው ሰማይ ጨልሟል... መሽቷል፡፡ ሰመነቃነቅ ስትሞክር ግራና ቀኝ የታሰሩት እግሮቿ መሃል የተዳፈነው ስቃይ እንደ ጦር ወጋት፡፡ ከስሱ የብርድ ልብስ በታች ያለው እራቁት ሰውነቷ ተንሰፈሰፈ፡፡
ድምፅ ተሰማት የመኝታ ቤቷ በር ተከፈተ፡፡ ቶሎ ዓይኖቿን ጨፈነቻቸው፡፡ : እንደነቃች ማወቅ የለባቸውም፡፡ ዝም ብላ መተኛት ነው ያለባት፡፡ መረበሽ የለባትም! አለበለዚያ ይመቷታል፡፡ ዝም ብላ መተኛት። በሩ ሲዘጋ ተሰማት: የእግር ኮቴ እየቀረባት መጣ. አንድ በላብ የረጠበ እጅ
እራቁት ትከሻዋ ላይ ሲያርፍ ተሰማት… ትንፋሼ እላይ እታች የሚል ትንፋሽ እላይዋ ላይ የነበረው ስስ የብርድልብስ ፡ ተገፈፈ፡ መረበሽ የለባትም… መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም... አለበለዚያ ድጋሚ
ያስቃይዋታል. , ትከሻዋ ላይ ያረፈው በላብ የራሰ መዳፍ ወደታች ወደ
ደረቷ ተንሸራተት…. እልተንቀሳቀሰችም ጡቶቿ ሲዳስሱ ተሰማት እላይ እታች የሚል ትንፋሽ… ፍርሃት ወረራ ግራ ክንዷ ላይ የተሰካውን መርፌ አስሮ የያዘው ፕላስተር ተላጠ.. ክንዷ ላይ የተሰካው መርፌ ተነቀለ መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም… አለበለዚያ ይመቷታል... እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ቀረባት፡፡ ብርድ ልብሷ ወደታች ተጎተተ ፍርሃቷ
እየጨመረ መጣ እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ወደ አንገቷ ስር ሲጠጋ ተሰማት.. ብርድ ልብሱ ከላይዋ ላይ ተንሸራቶ ወደ መሬት ወደቀ፡፡ ራሷን መቆጣጠር አቃታት… አይኖቿን ገለጠቻቸው፡፡
ጺማሙ ሰውዬ ነበር፡፡ እላይዋ ላይ እንዳንገርበበ ድንገት አይኖቿን ስትገልጥ ደንገጥ አለ፡፡ ወዲያው ፈገግ አለላት... የሸሚዙን ቁልፎች መፍታት ጀመረ… ፈገግ አለላት ድጋሚ… ሸሚዙን ከላዩ ላይ ወርውሮ ተጠጋት… እጆቹን ጡቶቿ ላይ ጫናቅው ድንገት ተወራጨች፡፡ ሙቅ
እርጥብ እጆቹን ከላይዋ ላይ ገፍትራ ተሸማቀቀች ፈገግ አለላት፡፡ አልጋዋ
ላይ የተንጋለለውን እራቁት ገላዋን ከላይ እስከታች በተራሱ ኣይኖቹ ዳሰሰው፡፡ ምራቁን ሲውጥ ትልቅ ማንቁርቱ እላይ እታች ሲመላለስ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡ ድንገት ዘሉ አፏን በመዳፉ ኣፈናት… ታገለችው…
እጆቿን እያፈራረቀች እንደብረት የደደሩ ሁለት ክንዶቹን ደበደበቻቸው
ቧጠጠቻቸው... ያለብዙ ችግር እፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሶ ለጎማት
ትንፍስ ትንፍስ እያለ ቁልቁል ተመለከታት፡፡ አይኖቹ የሚያርፉበት
ቦታ ያጠ ይመስላል፡፡ መላ ሰውነቷ ላይ ተንቀዠቀዡ።
ሱሪውን ማውለቅ ጀመሬ በተንጋለለችበት በምሬት… ጭንቅላቷን አወራጨችው… እንባዋ ደረሰላት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ቢሮው ትዕግስቱ አልቋል፡፡” አለ ከቴልአቪቭ የገባው ይሁዳ አሚ
የብርቱካን ጭማቂውን ተጎንጭቶ ብርጭቆውን ካስቀመጠ ሰኋላ ረጅም
ጺሙን እየዳሰሰ፡፡
የአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴልኝ የመዋኛ ስፍራ በስተቀኛቸው አድርገው ተቀምጠዋል፡፡ በርካታ እንግዶች በመዋኛ ልብሶቻቸው ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡ የተቀሩት በደረትና በጀርባቸው እየተገላበጡ ጭል ጭል የምትለውን ለስላሳ የጳጉሜ ፀሐይ ይሻማሉ፡፡
ይሁዳ አሚ በሆቴሉ ውስጥ ከያዘው የመኝታ ክፍል ወጥቶ ከቀጠሮኣቸው ስፍራ የደረሰው ልክ በሰዓቱ ነበር። ከቀጠሮው ሰዓት ቀደም ብሎ የደረሰው አሃሮን የእንግዳውን ፀባይ ስለሚያውቅ የብርቱካን ጭማቂ አዝዞ ከፊት ለፊቱ አስቀምጦ ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሚ የሌሊት ልብሱን ሳይቀይር በላዩ ላይ ወፍራም የጠዋት ልብሱን ደርቦ ወገቡ ላይ ቀበቶውን ሽብ አድርጎ ከጥጥ የተሰራ ወፍራም የእግር ሹራብና የቤት ነጠላ ጫማዐእንዳደረገ ወደ መዋኛው ስፍራ የሚወስደውን ደረጃ በእርጋታ ወርዶ ወደዐአሃሮን አመራ፡፡
“እንኳን ደህና መጣህ፡፡” አለ አሃሮን ተነስቶ እንደቆመ የአሚን እጅ
ጠበቅ አድርጎ እየጨበጠ፡፡
“እንኳን ደህና ጠበቅኸኝ።” አለ አሚ ነጫጭ ውብ ጥርሶቹን ለአንድ አፍታ ብልጭ አድርጎ የጓደኛውን እጅ እየወዘወዘ፡፡
አሚ “ ኪዶን” በሚል ስያሜ በሚታወቀው የሞሳድ ገዳይና አፋኝ
ክፍል ውስጥ ለአስራ ሰባት ዓመታት የሰራና አትግደል እና አትዋሽ
ከሚሉት ከሙሴ ትዕዛዛት በስተቀር በተቅሩት በስምንቱ ትዕዛዛት ላይ ፌዝ
የማያውቅ ጥብቅ ሃይማኖተኛ አይሁዳዊ ነው። በሌሊት ልብሱ ላይ የደረበው
ወፍራም የጠዋት ልብስና ቡፍ ካለ ጥጥ መሳይ የቤት ጫማው ጋር ሲያዩት
ጺማሙ ሰው በቤት ውስጥ ተቀምጦ የሳጠራ ዘንቢሉችን ሲሰራ የሚውል
የዋህ በሬ ይመስላል፡፡
“የብርቱካን ጭማቂ፡፡” አለ አሚ ፈገግ ብሉ ከጎኑ የቆመውን የሆቴሉን አስተናጋጅ እየተመለከተ፡፡
የአልኮል መጠጥ ፍጹም የማይቀምስና የአሳማ ስጋ አፉ የማይገባ ጥብቅ ሃይማኖተኛ የሆነው አሚ በመስከረም 5 1972 በሙኒክ ሃያኛው ኦሎምፒክ ዝግጅት ላይ የብላክ ሴፕቴምበር ቡድን የእሥራኤል ስፖርተኞችን ሰፈር በመውረር አስራ አንድ ተጨዋቾችን ከገደለ በኋላ የጠቅላይ ሚኒስትር ጎልዳሜይርን የብቀላ ትዕዛዝ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....እንደ ድንጋይ ከተጫናት ሰመመን ውስጥ ቀስ በቀስ እየወጣች ስትመጣ… እላይዋ ላይ ተጭኖ የያዛት ድቅድቅ ጨለማ እንደ ጭስ እየሳሳ እየበነነ ለቋት ሲጠፋ በመጀመሪያ የተቀበላት በእግሮቿ መሃል የሚነዝራት የደነዘዘ ስቃይ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ እየጠራ ሲመጣም አይኖቿን ለመክፈት አልደፈረችም፡፡ ሌላ ዱላ፣ ሌላ ስቃይ ሌላ የጋለ ሽቦ የሚችል
አካል አልነበራትም። በክፍሉ ውስጥ ብቻዋን ትሁን አትሁን እርግጠኛ
አልነበረችም፡፡ አይኖቿን ለመክፈት ግን አልደፈረችም፡፡
እጆቿ ግራና ቀኝ ተወጥረው ከታሰሩሰት ተፈተው በድን እንደሆኑ ሁሉ በግራና በቀኝ ተዘርረዋል፡፡ በተኛችበት ልብስ ደርበውላታል፡፡ እግሮቿ ግን አሁንም ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ተወጥረው እንደታሰሩ ናቸው፡፡ ቁስሏን ለማዳመጥ ሞከረች፡፡ በጭኖቿ መሃል የሚሰማትን ስቃይ ለማዳመጥ ዝም አለች የተዳፈነ... የደነዘ… የደበዘዘ ስቃይ፡፡ ግራ ክንዷ ላይ ህመም ተሰማት:: ለመነቃነቅ ግን አልደፈረችም፡፡ በአይነ ህሊናዋ ሁኔታውን
ለመቅረፅ ሞከረች። መቼ ነበር በጋለ ሽቦ ጭኖቿ መሃል ሰውነቷን ያቃጠሏት? ዛሬ? ትላንት? ዛሬ ምንድነው? ቀን ነው ሌሊት? ሰዓታትና ቀናት ትርጉም ካጡባት ቆይተዋል፡፡
ድምፅ የሰማች መስላት። ዓይኖቿን እንደከደነች ጆሮዎቿን ኣስልታ ተጠባበቀች፡፡ የበር ድምፅ ተሰማት… የሚከፈት የበር የሚያሰማው ድምፅ..
“አልተነሳችም፡፡” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ፡፡
“ኮለኔል” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ “ዙርያውን አጥረነዋል።በርም ላይ አንድ ሰው አቁመን እየተጠባበቅን ነው::”
“መጣሁ” ሲል ተሰማት ማርቆስ፡፡
ሁለት የእግር ኮቴዎች በግራና በቀኟ ተስሟት…በስተቀኝ ኣንድ መዳፍ ግንባሯ ላይ አረፈ::
“ከነቃች የመርፌ ማደንዘዣውን ስጣትስቃይ ሊኖርባት ይችላል።” የማርቆስ ድምፅ ነበር።
“ካስቸገረችኝስ ልምታት?” አለ በስተግራዋ የቆመ ሌላ ሰው፡፡
“ረጋ ብለህ አባብለህ ውጋት። ለምን ትመታታለህ? ደግሞ አታስቸግርህም.. ከተወራጨችብህ ግን ግሉኮሱን ንቀልላት፡፡” አለ እጁን ግንባሯ ላይ የጫነው ማርቆስ በጣቶቹ ፀጉሯን ወደኋላ እያበጠረ፡፡ “ጠዋት እቀየርልሃለሁ፡፡”
ኮቴ ተሰማት፡፡ ተከታትለው ሲወጡ ሰማች። በሩ ሲዘጋ በክፍሉ ውስጥ ፀጥታ ሲነግስ ስትፈራ ስትቸር አይኖቿን ገለጠቻቸው::መኝታ ክፍሏ ውስጥ ብቻዋን አስተኝተዋታል፡፡ በቢጫው የብርድ ልብሷ ከአንገቷ እስከ
እግሯ ጫፍ ድረስ ሸፍነዋታል፡፡ በተንጋለለችበት ዙሪያዋን ተመለከተች፡፡
ግራ ክንዷ ላይ የሚሰማት ህመም ከራስጌዋ ከተንጠለጠለው የግሉኮስ
ከረጢት ጋር የተያያዘው መርፌ ክንዷን ጠልቆ የገባበት ላይ መሆኑን ተረዳች። የክፍሉ መጋረጃ ተዘግቷል፡፡ በጥግና ጥግ የታየው ሰማይ ጨልሟል... መሽቷል፡፡ ሰመነቃነቅ ስትሞክር ግራና ቀኝ የታሰሩት እግሮቿ መሃል የተዳፈነው ስቃይ እንደ ጦር ወጋት፡፡ ከስሱ የብርድ ልብስ በታች ያለው እራቁት ሰውነቷ ተንሰፈሰፈ፡፡
ድምፅ ተሰማት የመኝታ ቤቷ በር ተከፈተ፡፡ ቶሎ ዓይኖቿን ጨፈነቻቸው፡፡ : እንደነቃች ማወቅ የለባቸውም፡፡ ዝም ብላ መተኛት ነው ያለባት፡፡ መረበሽ የለባትም! አለበለዚያ ይመቷታል፡፡ ዝም ብላ መተኛት። በሩ ሲዘጋ ተሰማት: የእግር ኮቴ እየቀረባት መጣ. አንድ በላብ የረጠበ እጅ
እራቁት ትከሻዋ ላይ ሲያርፍ ተሰማት… ትንፋሼ እላይ እታች የሚል ትንፋሽ እላይዋ ላይ የነበረው ስስ የብርድልብስ ፡ ተገፈፈ፡ መረበሽ የለባትም… መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም... አለበለዚያ ድጋሚ
ያስቃይዋታል. , ትከሻዋ ላይ ያረፈው በላብ የራሰ መዳፍ ወደታች ወደ
ደረቷ ተንሸራተት…. እልተንቀሳቀሰችም ጡቶቿ ሲዳስሱ ተሰማት እላይ እታች የሚል ትንፋሽ… ፍርሃት ወረራ ግራ ክንዷ ላይ የተሰካውን መርፌ አስሮ የያዘው ፕላስተር ተላጠ.. ክንዷ ላይ የተሰካው መርፌ ተነቀለ መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም… አለበለዚያ ይመቷታል... እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ቀረባት፡፡ ብርድ ልብሷ ወደታች ተጎተተ ፍርሃቷ
እየጨመረ መጣ እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ወደ አንገቷ ስር ሲጠጋ ተሰማት.. ብርድ ልብሱ ከላይዋ ላይ ተንሸራቶ ወደ መሬት ወደቀ፡፡ ራሷን መቆጣጠር አቃታት… አይኖቿን ገለጠቻቸው፡፡
ጺማሙ ሰውዬ ነበር፡፡ እላይዋ ላይ እንዳንገርበበ ድንገት አይኖቿን ስትገልጥ ደንገጥ አለ፡፡ ወዲያው ፈገግ አለላት... የሸሚዙን ቁልፎች መፍታት ጀመረ… ፈገግ አለላት ድጋሚ… ሸሚዙን ከላዩ ላይ ወርውሮ ተጠጋት… እጆቹን ጡቶቿ ላይ ጫናቅው ድንገት ተወራጨች፡፡ ሙቅ
እርጥብ እጆቹን ከላይዋ ላይ ገፍትራ ተሸማቀቀች ፈገግ አለላት፡፡ አልጋዋ
ላይ የተንጋለለውን እራቁት ገላዋን ከላይ እስከታች በተራሱ ኣይኖቹ ዳሰሰው፡፡ ምራቁን ሲውጥ ትልቅ ማንቁርቱ እላይ እታች ሲመላለስ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡ ድንገት ዘሉ አፏን በመዳፉ ኣፈናት… ታገለችው…
እጆቿን እያፈራረቀች እንደብረት የደደሩ ሁለት ክንዶቹን ደበደበቻቸው
ቧጠጠቻቸው... ያለብዙ ችግር እፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሶ ለጎማት
ትንፍስ ትንፍስ እያለ ቁልቁል ተመለከታት፡፡ አይኖቹ የሚያርፉበት
ቦታ ያጠ ይመስላል፡፡ መላ ሰውነቷ ላይ ተንቀዠቀዡ።
ሱሪውን ማውለቅ ጀመሬ በተንጋለለችበት በምሬት… ጭንቅላቷን አወራጨችው… እንባዋ ደረሰላት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ቢሮው ትዕግስቱ አልቋል፡፡” አለ ከቴልአቪቭ የገባው ይሁዳ አሚ
የብርቱካን ጭማቂውን ተጎንጭቶ ብርጭቆውን ካስቀመጠ ሰኋላ ረጅም
ጺሙን እየዳሰሰ፡፡
የአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴልኝ የመዋኛ ስፍራ በስተቀኛቸው አድርገው ተቀምጠዋል፡፡ በርካታ እንግዶች በመዋኛ ልብሶቻቸው ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡ የተቀሩት በደረትና በጀርባቸው እየተገላበጡ ጭል ጭል የምትለውን ለስላሳ የጳጉሜ ፀሐይ ይሻማሉ፡፡
ይሁዳ አሚ በሆቴሉ ውስጥ ከያዘው የመኝታ ክፍል ወጥቶ ከቀጠሮኣቸው ስፍራ የደረሰው ልክ በሰዓቱ ነበር። ከቀጠሮው ሰዓት ቀደም ብሎ የደረሰው አሃሮን የእንግዳውን ፀባይ ስለሚያውቅ የብርቱካን ጭማቂ አዝዞ ከፊት ለፊቱ አስቀምጦ ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሚ የሌሊት ልብሱን ሳይቀይር በላዩ ላይ ወፍራም የጠዋት ልብሱን ደርቦ ወገቡ ላይ ቀበቶውን ሽብ አድርጎ ከጥጥ የተሰራ ወፍራም የእግር ሹራብና የቤት ነጠላ ጫማዐእንዳደረገ ወደ መዋኛው ስፍራ የሚወስደውን ደረጃ በእርጋታ ወርዶ ወደዐአሃሮን አመራ፡፡
“እንኳን ደህና መጣህ፡፡” አለ አሃሮን ተነስቶ እንደቆመ የአሚን እጅ
ጠበቅ አድርጎ እየጨበጠ፡፡
“እንኳን ደህና ጠበቅኸኝ።” አለ አሚ ነጫጭ ውብ ጥርሶቹን ለአንድ አፍታ ብልጭ አድርጎ የጓደኛውን እጅ እየወዘወዘ፡፡
አሚ “ ኪዶን” በሚል ስያሜ በሚታወቀው የሞሳድ ገዳይና አፋኝ
ክፍል ውስጥ ለአስራ ሰባት ዓመታት የሰራና አትግደል እና አትዋሽ
ከሚሉት ከሙሴ ትዕዛዛት በስተቀር በተቅሩት በስምንቱ ትዕዛዛት ላይ ፌዝ
የማያውቅ ጥብቅ ሃይማኖተኛ አይሁዳዊ ነው። በሌሊት ልብሱ ላይ የደረበው
ወፍራም የጠዋት ልብስና ቡፍ ካለ ጥጥ መሳይ የቤት ጫማው ጋር ሲያዩት
ጺማሙ ሰው በቤት ውስጥ ተቀምጦ የሳጠራ ዘንቢሉችን ሲሰራ የሚውል
የዋህ በሬ ይመስላል፡፡
“የብርቱካን ጭማቂ፡፡” አለ አሚ ፈገግ ብሉ ከጎኑ የቆመውን የሆቴሉን አስተናጋጅ እየተመለከተ፡፡
የአልኮል መጠጥ ፍጹም የማይቀምስና የአሳማ ስጋ አፉ የማይገባ ጥብቅ ሃይማኖተኛ የሆነው አሚ በመስከረም 5 1972 በሙኒክ ሃያኛው ኦሎምፒክ ዝግጅት ላይ የብላክ ሴፕቴምበር ቡድን የእሥራኤል ስፖርተኞችን ሰፈር በመውረር አስራ አንድ ተጨዋቾችን ከገደለ በኋላ የጠቅላይ ሚኒስትር ጎልዳሜይርን የብቀላ ትዕዛዝ
👍2