አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ሦስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...የጠዋት ፀሐይ ከመቼውም ይልቅ ፏ ብላ ወጥታለች ።
"እኔንም አንዳንዴ አስታውሱኝ ፤ ስለእኔ ውበት ድምቀትና ሙቀት ተወያዩ ” የምትል ትመስላለች ሆኖም ቀና ብሎ የሚያደንቃት ወይም ከልቡ ሆኖ የሚሞቃት ተማሪ አልነበረም ። ሁሉም በየፊናው ይሯሯጣል ። ዛሬ የጠዋት እንቅልፍ የሚያሸንፈው ተማሪ የለም ፡

ማዕበሉ በግቢው ውስጥ ተነሥቷል ። ተማሪው ከግፊቱ ለመዳን ይተራመሳል " ድምፅ የለሽ ትርምስ ይተራመሳል ።
ወደ ፈተና ሲገቡ የሚያኾ ትጥቅን ለማሟላት ! እርሳስ ላጲስ ማስምሪያ

አንዳንዱ ሶባኤ ገብቶ የከረመ ይመስል ሞግጓል ።ጾም ጸሎት እንደ ጎዳው ሁሉ ትንፋሽ አጥሮታል « አጎንብሶ በአንገት ሰላምታ እየተለዋወጡ መተላለፍ ብቻ የሁሉም ልብ የፍርህት ደወል ይደውላል በጭንቀት ተወጥሮ ይነጥራል ።

የመፈተኛ አዳራሾቹ እንደ መቃብር አፋቸውን ከፍተው ይጠብቃሉ ቀድሞ የሚገባባቸው ተማሪ የለም ።ሁሉ ዙሪያውን ከብቦ የመጨረሻዋን ደወል ይጠባበቃል ።አንዳንዱ የሰዓቱንና የልቡን ትርታ ያነጻጽራል "እነዚህን የሚውጠው ትልቁ ደወል እስኪደወል ድረስ ! ...

የመፈተኛው እዳራሾች አቅራቢያ የሚገኙት ሽንት ቤቶች በወረፋ ተጨናንቀዋል ። የገባው ቶሎ አይወጣም
የሌለውን በግድ ያምጣል ። ከብዙ ምጥ በኋላ ትንሽ ጭርር አርጎ ይወጣል ። ከውጭ ያለው ያልጐመማል ። ይሳደባል ግን እሱም ሲገባ ያው ነው የፈተና ምጥ !

ቤተልሔም እንደ ልማዷ ሽንት ቤቱን አንቃ ይዛለች። በወረፋ ያገኘችውን መጸዳጃ ቤት በቀላሉ ልትለቀው አልፈለገችም ። ባለ በሌለ ኃይሏ እያማጠች ወስጧን ፈተሸችው ።ጠብ ያለ ነገር አልነበረም” ። በሸቀች ። ምናልባት ድንገተኛ አደጋ ተፈጥሮ እንደሆን ለማረጋገጥ የውስጥ ሱሪዋን መረመረች ቀይ ነገር የለም ።

እንግኒህ ታቃለህ ኢየሱስዬ ! ” አለች የውስጥ ሱሪዋን ታጥቃ ቀሚሷን ቁልቁል እየለቀቀች ።

በሩን ከፍታ ስትወጣ የወረፋ ጠባቂቹን ልጃገረዶች ዐይን ማየት አፍራ አንገቷን ሰብራ ያለፈቻቸው ። ከዚያ ቀጥሉ የታያት የማርታ ዘለፋ ነው። ፀባይዋ እንደሆነ ብታውቅም ሳትለክፋት አታልፍም ። “ .
ያንቺ ሽንት ደግሞ ለምን ፖፖ ይዘሽ አትዞሪም ? ወይም የፕላስቲክ ከረጢት
ብታጠልቂ ይሻላል ።

ዛሬሳ አልለክፈቻትም ። ዝም አለቻት ። ልዩ የምጥ ቀን በመሆኑና ችግሩ በእሷም ላይ ስለሚታይ ከትዕግሥት ጋር ውጪ ቆመው እየጠበቋት ነበር።

ይሄ ሁሉ ትጥቅ ምን ይሠራልሻል ? ” አለቻት ትዕግሥት ቤተልሔምን ፡ ይዛላት የቆየችውን የጽሕፈት መሳርያ ስትመለከት

ማን ያውቃል? ለክፉም ለደጉም" አለችና ቤተልሄም እየሣቀች ተቀበለቻት።

ትጥቋ ብዙ ነው ሁለት እርሳሰና አንድ ብዕር ሁለት ላጲስ ፥ አንድ ቀይ አንድ ጥቁር : ሁለት እስክሪፕቶ አንድ የፕላስቲክና አንድ የእንጨት ፥ ሁለት አጫጭር ማስመሪያ . . . ማን ያውቃል ጭንቅላት እምቢ ያለውን ትጥቁ ይመልሰው እንደሆን?

አንቺ የዛሬት ፈተና ተሰርቆ ወጥቶአል ሲባል ሰማው“ኮ” አለች ማርታ የቤተልሔምን ዐይን ዐይን እያየች

"የማን? የእናንተ ወይስ የእኛ? ” አለች ቤተልሔም ብዙም ባልተደነቀ ስሜት
“ ኧረ የኛ ? ”
“ ማን ነገረሽ ? ?

“ እሁን አንቺ ሽንት ቤት እንደ ገባሽ አንዲት ልጅ ስታወራ ሰማሁ ። ”

"ውሸት ነው እባክሽ ፈተና በወጣ ቁጥር
የሚወራ ወሬ ነው አለች ቤተልሔም።

“አረ እባክሽ ማን ያውቃል ? ሊሰረቅ ወይም በዘመድ አዝማድ ሊወጣ ይችላል ” አለች ማርታ ከጥርጣሬ ይልቅ እምነት በሞላበት ስሜት ።

“ እንሒድ እባክሽ ማርታ ” ስትል ትዕግሥት አቋረጠቻቸው። እሷና ማርታ የሚፈተኑበት ክፍል ቤተልሄም ከምትፈተንበት ራቅ ይል ነበር።

"ገና ኮ ነው"

“ አምስት ደቂቃ ነው፡ የቀረው ብንሔድ ይሻላል ” አለችና ትእግስት በቆራጥ ስሜት ተነቃነቀች።

“ መልካም ዕድል ! ” እየተባባሉ ተለያዩ ።

ትዕግሥት ከቤተልያም መለየት የፈለገችው በአቅራቢያዋ ያሉት ወንዶች ሲጠቋቁሙባት አይታ ነው። ምክንያቱ ምን እንደሆነ ይገባታል። አቤል አማኑኤል ሆስፒቲል ደርሶ ከተመለሰ ወዲህ የግቢው ወሬ ስለ እሶ እና ስለ እሱ ሆኗል ል ። “ ጎበዙዙን ተማሪ ያሳበደችው ኝ ” ትዕግሥትን" ትእግስትን ለማየት የማይጓጓ ተማሪ አልነበረም። እሷም በአንድ በኩል ይኸንኑ ፈርታ ፥ በሌላ ደግሞ የጥናት ሰሞን በመሆኑ ፥ መኝታ
ክፍሏ ውስጥ መሽጋ ነው የከረመችው ። የግድ ነውና አሁን ብትወጣ የተማሪው ሹክሹክታ የመንፈስ ዕረፍት ነሳት።

ቤተልሄም ከትዕግሥት እንደ ተለየች ሳምሶን ጉልቤውን አገኘችው የመፈተኛ ክፍሉን ለማወቅ አንደ ተጣደፈ ነበር።

“ ወዴት ነው ሩጫው ?” አለችው ። ልብ ብሎ አልተመለከታትም ነበር ። ድምጿን ሲሰማ ልቡ ተረጋጋ ።

“ መፈተኛ ክፍላችንን አይተሻል ? ” አላት ፡ ከቁጣ ባልተለየ ኃያል ድምፅ።

“ አዎ እዚህ 104 ውስጥ ነው ” አለችና በጣቷ አመለከተችው ።

ወደዚያው ቀረብ እንበላ !”

“ እሺ ቆይ መጣሁ” ብላው ባለችበት ቆመች ። “ ሁለተኛው አምላክ” ወደ እሷ ሲመጣ ተመልክታው ነበር ። ።በዛሬው ዕለት በቁም የምትፈልገው ሰው ነው ። እሱን ሳትሳለም ወደ ፈተና አትገባም ። እሱም ምልምሎቹን እየተዟዟረ በማጽናናት ተዋክቧል ።

“ እንደምን አደርክ ? ” አለችው ' አጠገቧ ሲደርስ
“ እግዚአብሔር ይመስገን፡ ደኅና ነኝ ። ”
እንግዲህ ወደ ፈተና መግባቴ ነው ።

“ አይዞሽ ፡ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ይሁን ብሏት ሄደ።

እሷም ይኽንኑ እንዲላት ነበር የፈለገችው የግዜርን የራሱን ድምፅ የሰማች ያህል ተጽናናች ። የፈተና ሰሞን ሁሉ አምላኳ ነው ።በተጠየቀችው ሐይማኖት ሁሉ እሺ
ነው ። ከጀህባውም ፡ ከጴንጤውም፥ ከባሀዪም ከሁሉም ጋር የግዜርን ቃል” ትሰማለች ። አንዱ ካንዱ ጋር ሲያያት
ዐይኑ እንደሚቀላ አልተገነዘበችም ። በእሷ ቤት ለሦስት ኣምልኮት መቆሟን ብልጠትና ዘዴ አርጋዋለች ። አንዱ አምላክ ቢስት ሌላው አይስትም ነው ጥበቧ ። በዚያ ላይ ደግሞ ስድስት ኮርስ ነው የምትፈተነው ። አንዱን ኮርስ በለማ
ላይ ጥላዋለች ። የተቀሩትን አምስት ኮርሶች በአንድ አምላክ ላይ መጣሉ ይከብዳል ። እና ሦስቱ “ አምላኮች”
ተከፋፍለው ቢሸከሙት ? መልማዮቿ ልቧን ከፍተው እንዳያዩባት እንጂ ጥሩ ዘዴ ነው ።

አቤልና እስክንድርም ከአንድ ጥግ ስፍራ ሆነው የመግቢያው ደውል እስኪደወል ድረስ ትርምሱን ይታዘባሉ ለፈተና ጊዜ የሚያደረገው ግርግርና ሽብር በተለይ እስክንድርን ሁልጊዜም ያበሽቀዋል ። ፈተና እንዲህ ተማሪውን የሚያርበደብድ ነገር ከሆነ የዕውቀት መለኪያነቱ ያጠራጥራል እያለ ለብቻው ውስጥ ውስጡን ያሰላስላል ።

አቤል የተማሪውን ዐይን ለመሸሽ የሚገባበት ጉድጓድ እጥቷል ። ተማሪዉ እሱ ላይ ሲጠቋቆቻምበትና ሲንሾካሾኩበት ይመለከታል ከትዕግሥትም ላይ እንዲሁ የማያውቁት ተማሪዎች አቤል ማለት የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ነበር የሚጠቋቆሙት አቤልን ያስገረመው ግን በፊት የሚያውቁትም ተማሪዎች እንደ እንግዳ ሆነው እየሰረቁ
መመልከታቸው ነው "

“ፊቴ ላይ ምን ለውጥ ለማየት ፈልገው ነው ? ወይስ ግንባሬ ላይ የሚያነቡት ነገር አለ ?” ሲል እሰበ ። በተማሪዉ
አስተያየት በሽቅ ።

የተማሪው ሹክሹክታና የስርቆት እይታ ራሱ ሳያብዱ ያሳብዳል ። “ጥናት ቢወጥረው " ምን ፈተና ቢያስጨንቀው
እንዲህ ዐይነቱን ወሬ ማነፍነፉ አይቀርም የስነ ልቦና ጥናት በስሎ አቶ ቢልልኝና የመሃበራዊ ሥራ ባልደረቦች ከአቤል ጋር በቀጥታም ሆና በተዘዋዋሪ ግኑኝነት አላቸው ብለው የገመቷቸውን ተማሪዎች
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።

ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።

እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።

የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።

“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"

“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?

አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።

“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።

« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”

ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።

“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።

ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።

ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።

“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-

ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።

“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣

እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "

ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።

“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።

“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።

ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።

አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?

“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው

ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።

“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ

“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።

አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።

“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር

“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።

“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”

" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”

በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።

እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል

እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።

ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።

"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ

“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።

ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...“ እንዲያው ምን ምን ይላት ይሆን?እኔ እሱ ለሴት ልጅ የሚያወራውን ነገር ለመስማት እጓጓለሁ " ግን አንተ ባል
ከው ዐይነት አገጣጥሞኝ አያውቅም ። ”

“አጅሬ ምኑ ሞኝ ነው ላንተ የሚታየው ?!እሷን ሲያገኛት ቦታው ጭር የሚልበትን ጊዜ ጠብቆ ነው ።

“ ወይ ጉድ ! መቼም ፍቅር የማያሸንፈው ልብ የለም ”አለ እስክንድር በልቡ ። ስለ ድብርት የበለጠ ለማወቅ ጓጉቶ ነበር ። ሆኖም ጨዋታው በተዘዋዋሪም ቢሆን አንዳንድ የአቤልን ድርጊቶች እንደሚንካ ስለ ገመተ አርዕስቱን ለመለወጥ ፈለገ ሳምሶንም ይህንን ሁሉ ልብ ሳይል እንደ መጣለት ነበር የሚጫወተው ። እስክንድር ግን የአቤል ስሜት
እየተለዋወጠ እንደ መጣ በሥርቆት ከገጽታው ላይ አንብቦአል ድብርት የሴት ጓደኛውን ለማግኘት ጭር ያለ ጊዜ
መጠበቁ የአቤልን ስሜት ክፉኛ ነክቶታል እሱም ትዕግሥትን ለማየት የሚጠቀምባቸውን ጊዜያቶች ያውቃል ።

ስማኝ ላምሶን ! ግን ለምንድነው አንተ ብዙ ጊዜ ድብርትን የምትለክፈው ? ” በማለት እስክንድር አርዕስቱን አሸጋገረው
“ ለተንኮል አይደለም ። ግን የሚነፋነፍ ሰው መልከፍ እንዲሁ ደስ ይለኛል ። እንዴት ብዬ ላስረዳህ ? ለምሳሌ
ቀርቦ መናከስ የማይደፍር ውሻ በሩቁ እያፈገፈገ ሲጮህብህ እልሁን ለማስጨራረስ በዱላ እንደምትተናኮለው ዐይነት ነው ። ብቻ እንዲሁ ስለክፈው ደስ ይለኛል እንጂ ለድብርት መጥፎ አመለካከት የለኝም ለየት ያለ ተፈጥሮ ስላለው ያስገርመኛል ” አለና አሳላፊዋን ለመጥራት ጠረጴዛውን ጠበጠበ።

“ አቤት ! ምን ልታዘዝ? ” እያለች አንገቷ በንቅሳት የተዥጎረጎረ ሴት ከፊታቸው መጥታ ቆመች ።

“ ቢራ ድገሚን ሦስት ቢራ ! ” አላት ሳምሶን በዚያው ቁጡ ድምፁ

“ እኔ ይብቃኝ ! ” አለ አቤል "

“ አትቀልድ እባክህ ። አንቺ እኔ የማዝሽን አምጪ!” አለና ሳምሶን አሳላፊዋ ላይ ጮኸባት ።

"ጥርስሽን እንዳያወልቅ ” አለና እስክንድር በልቡ ሳቀ ።

“ እኔኮ ያንተም ተፈጥሮ ያስገርመኛል ” አለው እስክንድር ሳምሶንን
“ እንዴት ?”
“ አሁን ሚስተር ሆርስ ከአቤል ጋር ከታረቀ በኋላ ለምን ትዝትበታለህ ?”

“ አዎ ! የማታውቀው ነገር አለ እስክንድር እየዛትክ የምትተው ከሆነ ዛቻው ሲደጋገም ሰው ይንቅሃል ።ወንድ ከሆንክ አንዴ ማቅመስ አለብህ ። እንዲያውም አንተን ብዬ ነው እንጂ እሱን ልጅ አንድቀን ብሰብረው ደስይለኛል ። ከፈለገ የገዛ ጥርሱን ከመሬት አሰለቅመዋለሁ ።

“ጡንቻህን ፈትነኝ እያለ ያስቸግሃል መሰለኝ” አለና እስክንድር እየሣቀ ከእሱ መልስ ሳይጠብቅ ፡ “ ብቻ ያለንበትንም ጊዜ አትዘንጋ : ሀያኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነን ” አለው ።

“ እና ? ” የብሽቀት ድምፅ ነበር ።

“ እናማ ስፖርተኝነትህን እወድልሃለሁ ። ይህችን በጡንቻ መመካትህን ግን ...

“ እንግዲህ አትልከፈኝ ፡ ልጠጣበት ! ” አለና ቢራውን ተጎነጨ

ሳምሶን ሌላ ሰው እንዲህ ቢናገረውም ካልተደባደበ በዋዛ እይላቀቁም ነበር ። ለእስክንድር ያለው ክብር ግን ብዙ ዓመት ከቆየ የልጅነት የአስተሳሰብ ተጽዕኖ የመጣ ነው ። የሠፈር ልጆች እንደ መሆናቸው መጠን ሳምሶን ስለ እስክንድር ብዙ ነገር ያውቃል ። እሱ ገና ልጅነቱን ሳይጨርስ እስክንድር በሠፈራቸው ውስጥ ስመ ጥር ጎረምሳ
ነበር ። እንዲህ እንዳሁኑ ከመስከኑ በፊት እናቱ በእስክንድር ያላዩት አበሳ የለም ። ከለውጡ በፊት ጸብ አሽትቶ ነበር
የሚፈልገው ። እስር ቤትን ቤቱ አድርጎት ነበር ። አንዴ ጸበኞቹ በቡድን ሆነው ከደበደቡት በኋላ ሆዱ ላይ በጩቤ
ወግተውት ለጥቂት ነው ከምት የተረፈው ከለውጡ በኋላ ደግሞ በወቅቱ በተፈጠሩት የፖለቲካ ድርጅቶች ሳቢያ
ያልቀመሰው፡ አበሳ የለም ። ችኩል ነበር ። ሰው አይገራውም ፣ ያየሁት አይለፈኝ የሚል ስሜት ያሸንፈዋል ።
የጀብደኝነት ስሜት ያጠቃዋል ። ትኩስ ኃያልነቱ፡ መንፈሱን ያቅበጠብጠዋል ። አሁን ግን በዕድሜም በብስለትም ሰክኖ
እንኳን ለራሰ ሌሎችንም ይመክራል ። ከአፍላነት ቅብጥብጥነት ጊዜው ይዞ የመጣውና አሁንም ያልተወው ነገር ቢኖር
የሲጋራ ሱስ ብቻ ነው። ይህ ሁሉ ሁኔታ በሳምሶን ላይ የሚኖረው ተጽእኖ ቀላል አይደለም። በፀጉሩ ኪንኪነት እየለከፈው ከእስክንድር ጋር መቃለድ የጀመረው እንኳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው።

አቤል እባክህ ተጫወት ይሄንን ተወው
አለ ሳምሶን እስክንድርን በመንቀፍ አይነት

“ እየሰማኋችሁ “ኮ ነው ? ” አለ አቤል በጨዋታቸው ውስጥ የቆየ ለመምሰል ጥርሱን በውሸት ብልጭ አደረገ።

ሐሳቡ በከፌል ወደ እነ ትእግስት ዘምቶ ነበረ። ፈተና ከጨረሰች በኋሳ ወዴት ትሔድ ይሆን ? አርፎ መተኛት ወይስ
ዙረት መውጣት ? እያለ ሲያሰላስል ነው የቆየው።ሁለተኛውን ጠርሙስ ቢራ ግማሽ አድርሶታል ። ከቻቻታው ጋር
ቢራው ሞቅ አድርጎት ውስጥ ውስጡን እየሰከረ መምጣቱ ይሰማው ነበር። የመጠጣት ልምድ ስለሌለው ጭንቅላቱ ቶሎ መረታት ጀምሯል ። ድፍረትም ተሰማው ማንንም ያለመፍራት ሃይነት ስሜት !

“ ለምን ሙዚቃውን አይቀይሩልንም ? ” ሲል ድምፁን አሰማ ። የእንግሊዝኛ ሙዚቃ ነበር አዳራሹን የሚነቀንቀው፤“ ማስቀየር እንችላለን ። የማን ክር ይደረግ ? ” አሉ እስክንድርና ሳምሶን በአንድ ድምፅ አቤል ከዝምታ ወደ
ተሳትፎ መምጣቱ ደስ አሰኝቶአቸው ነበር

•የ... የመልካሙ ተበጀ ክር ቢሆን
ይሻላል” አለ አቤል በተሰባበረ ድምፅ

እስክንድርም ሆነ ሳምሶን በፍጥነት የጠረጠሩት ነገር አልነበረም ። አሳላፊዋን ጠርተው ክሩ እንዲቀየር አዘዟዋት።

ባለቤትየዋ እሷ የመረጠችው ዘፈን ካልሆን እሺ አትልም ግን ልሞክርላችሁ ” አለች አሳላፊዋ ።

“ ንገሪያት ! ለምን እሺ አትልም ? ” አለና ሳምሶን አፈጠጠበት እሷ ዘፈኑን ልታዝዝ ስትሔድ አቤል ቀድሞ በልቡ
ያንጐራጉር ጀመር።

አረ መላ ምቱ ወዳጅ ዘመዶቼ
ዐይናፋር ሆኛለሁ ፡ ዐይናፋር አይቼ
ሰሳምታ አልሰጠኋት አላነጋገርኳት
በዐይን ብቻ እያየሁ አንድ ዓመት ወደድኳት።

ልቡ ይህን እያዜመ፥ ጆሮው የሚሰማው ግን ሌላ ሙዚቃ ነበር ቢጠብቅ ፥ ቢጠብቅ የተለወጠ ነገር የለም ጥቂት
ቆይታ አሳላፊዋ ተመልሳ መጣች።

የመልካሙ ክር የለም ብላለች ባለቤትየዋ ! ”

አቤል በሽቆ “ ገደል ግቢ በያት ! ” ከማለቱ ዐይኑ እንባ አቀረረ ። የሰው ስሜት የማይጠበቅበት ዓለም ! ባለቡና ቤቶች ፍቅረኛውን የሚያስታውስበትን ዘፈን አይከፍቱለትም "መምህራን ትምህርት ምን ያህል እንዳስጠላው አይረዱለትም ። ወላጆቹ ልጃቸው ከድህነት ቀንበር እንዲያላቅቃቸው
ይመኛሉ እንጂ እሱ ያለበትን ችግር አያውቁለትም ። ጓደኞቹ ብቸኝነቱን አይፈቅዱለትም ።

“ እሷ ከሙዚቃዋ ጋር ገደል ትግባ ! አንቺ ቢራ ድግሚን ” አላት ሳምሶን በሽቆ ።

“ኧረ ይብቃን ! ሰዓቱም መሽቷል የካምፓስ ፖሊሶች አያስገቡንም ” አለ እንክንርድ ኪሱን እየዳበሰ ።

አምጪልን እባክሽ እንጠጣው ዛሬ ካምፓስ ማን ይገባል? ” አለ ሳምሶን በሞቅታ ስሜት ።

“በይ እንግዲያው አንቺንም እንጋብዝሽ የምትጠጪውን ነገር ይዘሽ ነይ ” አላትና እስክንድር ፡ ወደ ሳምሶን ዘወር ብሎ ፥ “ ከጠጣን አይቀር መሐላችን አንዲት አንስታይ ስትኖር ይሻላል” አለው ። ከሳምሶን ሁኔታ ገንዘብ እንደያዘ
ገምቶ ነበር "

እቤል ምንም አስተያየት አልሰጠም ። የያዘውን ቢራም አልጨረሰም ። ከዚያ በላይ መጠጣት አልፈለገም ። ሆኖም
አልተከላከለም ። ሕይወትን የመሰልቸት ዐይነት ነበር የሚሰማው ። ለምንም ነገር ያለመጨነቅ ። ስካር ማለት ይሄ ይሆን እንዴ?
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
;
;
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


እስክንድር በምልክት አሳየው ። በዚያ ሁሉ ጠጪ መሐል ሁለት እጁን እኪሱ አድርጎ ፡ ሁሉንም በንቀት ዐይን እየተመለከተ ነበር ወደ ሽንት ቤቱ የሔደው ።

“ ቢራዋ ሥራዋን እየሠራች ነው ” አለ እስክንድር የአቤል አረማመድ እያየ ።

“ ግን ምን ይሻለዋል ?” አለ ሳምሶን " በአቤል ሁኔታ በማዘን ' “ አሁን በማዕረግ የሚመረቅ ይመስልሃል ? ” እስክንድር ገርሞት ሣቀ ። የሳምሶን ጥያቄ ግን ከቅን
መንፈስ የመነጨ ነበር ። አቤል የሚወደውም የሚያከብረውም በማዕረግ ተማሪነቱ ነው ። የአቤል የማዕረግ ተማሪነት በዩኒቨርስቲው ውስጥ በብዙ ተማሪዎች ዘንድ ይታወቃል
እንደ እስክንድር ጠጋ ብለው የማያውቁት አሁንም የዓመቱ የፕሬዚዳንት የከፍተኛ የማዕረግ ሽልማት ከአቤል እጅ አይወጣም የሚል ግምት አላቸው ። ሳምሶንም የመኝታ ክፍል ጓደኛው ቢሆንም ቅሉ በትምህርት ያን ያህል መድከሙን አያውቅም ነበር ።

“ እውነቴን ኮ ነው ። ምን ያሥቅሃል ?”

ማዕረጉ ቀርቶ በዚህ ዓመት መመረቁ ራሱ ነው እኔን የሚያጠራጥረኝ” አለው እስክንድር " በኀዘን ስሜት ፊቱ
ተለዋውጦ።

“ ያሳዝናል ! ግን ምን ታረገዋለህ! ” አለና ሳምሶን "ቢራውን ከጠርሙሱ ውስጥ እየጨለጠ ፥ “ በነገራችን ላይ መውደቂያችንን እናዘጋጅ እንጂ ! መቼም ዛሬ ወደ ካምፓስ አንገባም” አለው ።

እስክንድር የሳምሶን ሐሳብ ገባሁ ፤አንድ ሴሚስተር ሙሉ ታፍኖ የቆየ ስሜቴ ተነሣ ነገር ግን ኪሱ አስተ ማማኝ አልነበረም ።

“ እኔጋ በቂ ገንዘብ የለማ ! ” አለው ልመና በተቀላቀለበት ድምፅ ከልብ ተዝናንቶ ።

አቤልም እሺ የሚል አይመስለኝም ። ከአሁን በፊት ውጭ እድሮ አያውቅም ።
“ ምን ትቀልዳለህ ? ጭራሽ ? እምልህ ...”
“ አዎ ፡ ከእኔ ጋር ስንተዋወቅ ይኸው አራት ዓመት አለን አንድ ቀንም ኣድርጎት አያውቅም ።

እንግዲያው ዛሬ ድንግሉን ማስወሰድ አለብን ? ”አለ ሳምሶን ተንኮልም የፍቅር ስሜትም እየተሰማው ።

“ እዩዬ ! ተው እባክህ ! ” አለ እስክንድር ' በተዘበራረቀ ስሜት ።

“ ምናለበት ? አንተ ደሞ ! እንዲያውም ሴት ከቀመሰ የዐይኑ ፍቅር ይለቀው ይሆናል ። ገንዘብ እንደሆን እኔ ይዣለሁ ብዬሃለሁ ።

እስክንድር የሳምሶን ሁኔታ ራሱ እንግዳ ሆነበት ። ሳምሶን አብዛኛውን ጊዜ በኪሱ በርካታ ገንዘብ ይይዛል ። ወላጆቹ ደኅና ገቢ አላቸው ። አባቱ በአንድ ኢንተርናሽናል ድርጅት ውስጥ በጥሩ ደመወዝ ይሠራሉ ። በእናቱ ስም ደግሞ
መስጊድ አካባቢ የሰዓት መሸጫ ሱቅ አላቸው ። ወላጆቹ ለሳምሰን በወር ተቆራጭ ካደረጉለት ሃምሳ ብር ሌላ
ሊጠይቃቸው ብቅ ባለ ቁጥር አንድ ወይም ሁለት ባለ አሥር ኖት ሳያሽጉት አይመለስም ። ታዲያ ሳምሶን ይህን ሁሉ ገንዘብ ሲይዝ " ለመጠጥ ማጥፋት አይወድም። የሱ ገንዘብ የሚያልቀው በምግብ ነው ። መብላት ፡ ስፖርት መሥራት ግንባታ ብቻ ! በዩኒቨርስቲው አቅራቢያ ካሉት ምግብ ቤት ባለቤቶች ውስጥ እሱን የማያዉቅ የለም ። ዛሬ ገንዘቡን ለመጠጥና ለሴት ለማውጣት መዘጋጀቱ ነው እስክንድርን ያስገረመ።

“ እንዴት ነው ? ዛሬ ግንባታው ቀርቶ ለማፍረስ ነው መሰል የታጠቅከው ” አለው እስክንድር እየሣቀ ።

“አንዳንዴ ያስፈልጋል እባክህ ! ”
አሳላፊዋ አራት ጠርሙስ ቢራ ይዛ መጣች አንዱ ለራስዋ መሆኑ ነው ።

ቢራ እዚሁ ጓዳ መጥመቅ ጀመራችሁ እንዴ ? "
አላት እስክንድር ፡ ከታዘዘች መዘግየቷን ለመጠቆም ።

“ ቆየሁ እንዴ?አንድ ሰካራም ይዞ ሲነተርከኝ ነው” አለች ፥ ቢራውን እየከፈተች ።

“ አንቺው መጠጥ አቅርበሽለት አንቺው፡ሰካራም ትይዋለሽ ? በይ ነይ በይ ” አለና ሳምሶን ፡ ዳሌዋ ላይ ቸብ አደረጋት ቸብታው ጠንከር ያለ ስለ ነበር ዳሌዋን ለበለባት።

“ እንደዬ ! ታዲያ ዱላው ምንድነው ? ” አለች ተቆጥታ ዳሌዋን በእጅዋ እያሻሸች

ዝም በይና ቁጭ በይ ! ከፈለግኩ ጥርስሽን ነው የማረግፈው አላት ሳምሶን እንደ ልማዱ ።

እስክንድር ነገሩ ማየሉን ሲያይ ተደናገጠ

“ ኧረ እባክህ ! የማነህ ሒድና የሚስትህን ጥርስ አውልቅ " የእኔን የብርቅነሽን አይደለም። ስለ ቢራው እንደሆን ኬረዳሽ ! ” ብላው የከፈተችውን ቢራ ጥላ ተነሣች ብርቅነሽ አምርራ ልትሔድ ስትል'እስክንድር እጅዋን
ይዞ አባብሎ አስቀመጣት ።

“ አንቺ ደሞ እረፊ እንግዲህ ። እሱ ለጠዋታ ያህል ነው የነካሽ
እየተመናቀረች ከሳምሶን ርቃ እስክንድር ጎን ተቀምጠች ። ሳምሶንም ጥርሱን እያንቀጫቀጨባት ነበር ። በማይ
ረባ ነገር ተለካክፈው የጎሪጥ መተያየታቸው እስክንድርን
አስገረመው ።

“ ሁለታችሁም ዕረፉ ፡ ይሄ ቡና ቤት ነው በሰላም ጠጥተን መጫወት ነው የምንፈልገው ”አላቸው : ከግንባሩ ኮስተር ብሎ ፥ ግን በሆዱ እየሣቀ ።

የእስክንድር ሐሳብ እነሱጋ ረግቶ አልቆየም ። በድንገት አንድ ሐሳብ አእምሮውን ወጋው ።አቤል ወደ ሽንት
ቤት ከሔደ ቆይቷል ፤ግን አልተመለሰም ። እስክንድር ልቡ መጥፎ ነገር ጠረጠረና ድንገት ከተቀመጠበት ተነሣ ።

ምነው ?” አለው ሳምሶንም ፡ በሁኔታው ተደናግጦ ።

“ ምንም አይደለም ፥ መጣሁ ” ብሎ እስክንድር ወደ ሽንት ቤቱ ሄደ ። አቅለሽልሾት ይሆናል በሚል ግምት ሳምሶን ነገሩን ቸል አለው ።

እስክንድር ከመጸዳጃ ቤቱ አጠገብ ሲደርስ አቤል እጁን በኪሱ እንዳደረገ ግድግዳ ተደግፎ ቆሞ ነፋስ ሲቀበል አገኘው። ዐይኑ በርበሬ መስሏል ።አላፊ አግዳሚውን በንቀት ዐይን ነው የሚመለከተው።

ቴክሱ ምነው ? ”አለው እስክንድር ፥ ደህና መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ"

“ ወረፋ ሆኖብኝ ነው እባክህ ! ”

“ የሽንት ወረፋ ? በል እንግዲህ ጠብቅ ። ምን ታረገዋለህ ? ” ብሎት እስንድርን ወደ መጣበት ተመለሰ ።አቤል አንድ አደጋ ደርሶቀታል የሚል ሥጋት ስለ ነበር፡ በሰላም በማግኘቱ ልቡ ተረጋጋ ። ምንጊዜም አያምነውም አንድ ቀን በራሱ ላይ የሞት ቅጣት ይፈርዳል የሚል ፍራቻ አለው።

ወደ መቀመጫው ሲምለስ ብርቅነሽና ሳምሶን ተስማተው ጎን ለጎን ተቀምጠው ሲያወሩ አገኛቸው ።

ታረቃችሁ እንዴ ? ”

“ ዱሮስ መች ተጣላን ? አንተ ደሞ ” አለችና ብርቅነሽ ጠየቀችው፡ ፡

ቀድሞውንም ጸበኞች የሚገባበዙት መሐላቸው ገላጋይ ሲኖር ነው ። ብቻቸውን ሲሆኑ አንደኛው ዐቅሙን
ዐውቆ ወይም ጥቅሙን ከጉዳቱ አመዛዝኖ ጸባዩን ያሳምራል ? አለ እስክንድር በልቡ ።

“ ያንን ነገር “ኮ ለብርቅነሽ ነገርኳት” አለው ሳምሶን' ዓይኑን እስክንድር ላይ ተክሎ "

የቱን ነግር ? ”

የአቤልን ነዋ ! በቃ እሷ ይዛው ትደር ።

ሳምሶን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መሆናቸውን አጫውቷት ከዚያው ቡና ቤት መኝታ እንድትይዝ ገንዘብም
ሰጥቷታል ።

“ አንተ ዛሬ የልጁን ድንግል ለማስወሰድ ታጥቀህ ተነሥተሃል ማለት ነው? ” አለ እስክንድር ጉጉቱ አስገርሞት እየሣቀ ።

“መሆን አለበት ብዬሃለሁ ። አድቬንቸር ነው
“ አንቺስ ? በነገሩ ተስማማሽ ? ” አላት እስክንድር ፊቱን ወደ ብርቅነሽ መልሶ።

ውይ በደስታ ነዋ ! እንዲያም ድንግል ወንድ ደርሶኝ አያውቅም ። ዕድሌ ሆኖ የተፈተነ ብቻ ነው የሚደርሰኝ።

ስትናገር ሣቅ ሃቅ ስለምትል የቀልዷን ይመስላል እንጂ ብርቅነሽ የምትናገረው የልቧን ነበር ። ወሲብ ጀማሪ ደርሷት
አያውቅም ። የልጅነት ባሏም ቢሆን ሁለተኛ ሚስቱ ነበረች ።ቡና ቤቱ ውስጥ የሥራ ጓደኞቾ፥ “ ዛሬ የአንዱን ጀማሪ ድንግል ወሰድን ” እያሉ ሲያወሩ ትቀናለች በዚህ ወሬ የተካነችው የቡና ቤቱ ባለቤት ነች የጥንት ዝናዋን ስታወራ ይሄ አርዕስት
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።

“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?

"አራት ዓመት!”

"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "

“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።

“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”

“ሒድ'ደረቅ ! ”

ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !

"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።

የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።

“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”

ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””

“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ

“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።

“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።

«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።

“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።

“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!

እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !

“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።

ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::

ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።

ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”

ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።

“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «

“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች

“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”

ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "

እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....በማግሥቱ ጠዋት ከቀጠሮው ሰዓት ቀድሞ ጆሊ ባር የተገኘው እስክንድር ነበር። ያደረበት ቤት ስላልተስማማው
በሌሊት ነበር ሾልኮ የወጣው ። የቤቱ አለ መስማማት ብቻ ሳይሆን የሰው ዐይን ፍራቻም ነው “ አላሁ አክብር” ሳይል ያስወጣው ። የገዛ ኅሊናው ዐይን ሲያለቅስ እንባውን አድርቆ ሲልከሰከስ እያደረ ' የሌሎችን ዐይን ለምን እንደ
ሚፈራ ሁሌም ይገርመዋል ። ባደረበት ቤት አንግቶ፡ ተዝናንቶ ቆይቶ አያውቅም ።

ይህን ልምድ ከየት ይሆን የቀዳነው ? ” ሲል አሰበ በዩኒቨርስቲው ውስጥ በትምህርት ወራት ቀለም ላይ ተደፍቶ
መክረም ፡ በዕረፍት ሳምንታት ደግሞ ኪስ እስከ ተቻለ ድረስ በአልኮል ማበድና በየበረንዳው ማደር ፈሊጥ እየሆነ መምጣቱ ነበር ያሳሰበው ። በዛሬው ዕለት እንኳ እንደ እሱው የሰው ዐይን እየፈሩ ከያደሩበት በረንዳ በሌሊት እየተሾለኩ " ጸጉራቸው እንደ ተንጨፈረረ ወደ ካምፓስ ቢሮ ያያቸው ተማሪዎች ቁጥር ትንሽ አልነበረም ።

ሁኔታው በትምህርት ተጨንቆ የከረመን አዕምሮ የማዝናናት አዝማሚያ ይመስላል” ሲል ሐሳቡን ቀጠለ
“ ታዲያ ከሰው ዐይንም ; ከዛ ኅሊናም የማይሸሹበት ሌላ መዝናኛ መፍጠር አይቻልም ወይ ? ተማሪው ከተባበረ ከፈተና በኋላ ባለው የዕረፍት ጊዜ ውስጥ እንደየዓቅሙ ገንዘብ አዋጥቶ ' የሙዚቃና ሌሎች የተለያዩ ትርኢቶችን እንዲሁም አዝናኝና አነቃቂ ውድድሮችን ማዘጋጀት፥ በቡድን ሆኖ ከከተማ ወጣ እያሉ ብርቅና ድንቅ ቦታዎችን መጐብኘትና የመሳሰሉት ልምዶች ቢዳብሩ ጤናማ መዝናኛ ይሆኑ
ነበር ። ታዲያ ይህን በጐ ተግባር ለማስተባበር የግንባሩን ቦታ ማን ይውሰድ ? ?

በራሱ ሣቀና ሲጋራ ለመፈለግ ኪሱን ይደባብስ ጀምር ትላንት ማታ ሌላ፡ ዛሬ ጠዋት ሌላ መሆኑ ነው ያሣቀውም
የአንድ ሰው ሁለት ልክ ? አለ በልቡ።

ሣቁ ከፊቱ ላይ ሳይጠፋ ሳምሶን ጉልቤው ደረሰ። ፊቱን ጭፍግግ አድርጐታል • እሱነቱ አስጠልቶት ራሱን የሚጥልበት ቦታ ያጣ ሰው ይመስላል "

“ ታድያስ ? ” አለው እስክንድር ፈገግ እያል ።

ሳምሶን አፉ መናገር እንዳቃተው ሁሉ “ መቼም አልሞትኩም ! ” በማለት ዐይነት አፍንጫውን አጣሞ አንገቱን ወደ ግራ አዘነበለ እጆቹን ኪሶቹ ውስጥ እንደ
ከተተ ሊቀመጥ ሲል ሱሪው የመተርተር ድምፅ አሰማ።

“ እናትክን ! ” አለው ሱሪውን ።

ጥርሳም እንዳትለው ሱሪው ጥርስ የለው አለና እስክንድር ቀለደበት ።

ሳምሶን ፈገግም አላለም "ቢኮረኩሩትም የሚሥቅ አይመስልም

“ ምነው ደበረህ ?” አለው እስክንድር ሣቁን እየዋጠ ።
“ ምን እባክህ ነጭ ናጫ ሴት ነች የገጠመችኝ፡እንዲሁ ስንበጣበጥ ነው ያደርነው "

አይዞህ አንድ ነን ። እኔም ቀዝቃዛ አሮጌት ይዤ ነው ያደርኩት መጠጥ ምን የማይሠራው አለ? ብቻ አትፍረድባቸው ። የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባቸው ነው እንጂ ሰልችቶቸዋል "

“ ጥርሳሞች ! ” አላቸው ሳምሶን በልቡ ። ከእስክንድር ጋር መከራከርም መጫወትም አልፈለገም ። መላ ሰውነቱ
ደክሞአል " ለመፍታታት ያህል እንኳ የጠዋት ስፖርት አልሠራም። ሕይወትን የመሰላቸት ስሜት ተሰማው ፡ ፊቱን
በመስታወት ባያየውም በስሜቱ ጠውልጎ ታየው ። የጠጣበትን ቡና ቤት ያጠጣውን ገንዘብና አብሯት ያደረችውን ሴት በልቡ እየረገመ ጠረጴዛውን በቡጢ ደበደበ "

“አቤት!ምን ልታዘዝ?” ሲልአሳላፊው ከተፍ አለ ።
"አንድ ጠርውስ ቀዝቃዛ አምቦ ውሃ ”
“ አዎ ጎሽ ፡ የተቃጠለ አንጀት ለማራስ” አለ እስክንድር ተደርቦ ።

አምቦ ውሃው ቀርቦላቸው እየጠጡ በመጫወት ላይ ሳሉ አቤልን በውጭው መስተዋት በኩል አዩት። ከኋላው
የሚያባርሩትን ያህል በፍጥነት ነበር ወደ እነሱ የሚገሰግሰው ። የእስክንድርና የሳምሶን የተደበረ ስሜት አቤልን
ሲያዩ ተነቃቃ ። ወሬውን ለመስማት አጠገባቸው እስኪደርስ ተቻኮሉ። እሱም ከውጭ ሲያያቸው ዐይናቸውን አፍሮ
በሆዱ አቀርቅሮ ነበር የተጠጋቸው» ማታ በቅዠት መልክ የሰማውን “ ብር አምባር ሰበረልዎ ” አሁን ለቱ ሰበውን የሚሉት መሰስው ።

“ እህሳ ? ሌሊቱ እንዴት ነበር ? ” አለው ሳምሶን' ቀድሞ ሊጨብጠው እጁን እየዘረጋ።

ጥሩ ነበር” አለ አቤል ሁለቱንም ከጨበጣቸው በኋላ ጠርሙሱ ውስጥ የተረፈውን አምቦ ውሃ በብርጭቆ
እየቀዳ ። ጠጥቶ እንደ ጨረሰ በእርካታ ተንፍሶ፡ “እንሒድ እባካችሁ ” አላቸው ።

"ቁጭ በልና ተጫወት እንጂ ” አለው ሳምሶን ለወሬው ጓጉቶ ። አቤል ግን መቀመጥ አልፈለገም ። ወደ ካምፓስ ለመሔድ ቸኩሎአል ። በዩኒቨርስቲም ግቢ ውስጥ አንዳች ነገር ጥሎ ያደረ ይመስል ልቡ ተሰቅሎአል ። እስክንድርም ይህን ስሜቱን ስለ ተረዳለት ለመሔድ ተነሣ።

ወደ ስድስት ኪሎ ሲጓዙም ሳምሶን ከእቤል የመስማት “ጥማቱ እንደ ቀጠለ ነበር ። በዝምታ ትንሽ እንደ ተራመዱ "

“ ታዲያስ ፡ እንዴት ነበር ? ” ሲል ይጠይቀዋል የሴት ተግባሩን አስጐልጉሎ ለማናዘዝ በሚጥር ጥልቅ ስሜት ።

“ ደኅና ነበር ይላል አቤል ነገሩን ቸል ብሎ ለማሳጠር በሚጥር ስሜት ። ሳምሶን በዚህ መልስ አይረካም

"ብርቅነሽ እንዴት ነች ? ” ሲል ደግሞ ሊያወጣጣ ይሞክራል ።

“ ብርቅነሽ ጥሩ ሴት ነች” ሲል አቤል ነገሩን በአጭሩ ይደመድመዋል ።

አቤል ከብርቅነሽ ጋር ምን ዐይነት የመጀመሪያ ሌሊት እንዳሳለፈ ለመስማት ሳምሶን ብቻ ሳይሆን እስክንድርም
ጓጉቶ ነበር ። የብርቅነሽ ጥሬነት ፡ ግልጽነትና ጣፋጭነት ሳያስቡት በሁሉም ልብ ውስጥ ግልጽ ያልሆነ የፍቅር
ስሜት አሳድሮባቸው ነበር። ያም ሆነ ይህ፡ አቤል እንደ ጠበቁት በሰፊው የሚያወራላቸው አልሆነም ። ጓደኛሞች እንዲህ ዐይነት ሌሊት አሳልፈው ጠዋት ሲገናኙ ስለ አዳራቸው ሁኔታ ወይም አብረዋት ስላደሩት ሴት ማውራት
የተለመደ ቢሆንም ፥ ለአቤል እንግዳ ነገር ነበር ። ስለ አዳሩ እንዳይናዘዝ የፍረትና የቁጥብነት ስሜት ኅሊናውን
ጨምድዶ ያዘው ።

ብርቅነሽ የትዕግሥትን ቦታ ባትወስድም በአቤል ልብ ውስጥ የተወሰነ ዳርቻ ይዛ ነው ያደረችው ። ለወሲብ የመጀመሪያ ሴቱ በመሆንዋ ብቻም አይደለም ። እስዋም ራስዋ ሁኔታውን በማየትና ሳምሶን የነገራትን በማገናዘብ
ለአቤል ቀና ስሜት ስለ ነበራት በባነነ ቁጥር አብራው ስትባንን ነው ያደረችው ። የልቧን አጫውታው የልቡን ምስጢር ወስዳለች ። ግልጽነቷና ፍቅራዊ መስተንግዶዋ አስገድዶት አቤልም ስለ ትዕግሥት ሲያጫውታት ነው ያደረው።
የትዕግሥትን ጉዳይ ለብርቅነሽ ግልጽ ማውጣቴ የቆረቆረው ጠዋት ከተለያት በኋላ ነው ። በግትርነት ተወጥሮ የነበረው መንፈሱ እየላላ መምጣቱ ለራሱም ተሰማው ። ምስጥሬ ብሎ ደብቆ የያዘውን የትዕግሥትን ነገር በመጀመሪያ ለሐኪሙ ፡ በትላንቱ ምሽት በመጠጥ ኃይል ለእስክንድር ሌሊቱን ደግሞ ለብርቅነሽ መናዘዙን ሲያስታውስ የመንፈሱ መላላት ታወቀው ።

ሳምሶንም ሆነ እስክንድር የጓጉትን ያህል ሳያወራቸው ከዩኒቨርስቲው በር ደረሱ ። ግቢው ጭር ብሎአል ።ለወትሮው ቢሆን ይህ ሰዓት ወደ ትምህርት ክፍል መግቢያ ጊዜ በመሆኑ መራወጥ ይታይበት ነበር።ዛሬ ግን ገና ከእንቅልፉ ያልተነሣም ኘለ ። የሚነቃነቅ ተማሪ አይታይም ።

እነ አቤል ግቢ ውስጥ ከገቡ በኋላ፥ወደ መኝታ ቤታቹኑ የሚወስደውን ጠምዛዛ መንገድ ሲይዙ አራት ልጃገረዶች
ከሩቅ ተመለከቱ ። ልጃገረዶቹ ሻንጣ ሻንጣቸውን ይዘው ከግቢው በመውጣት ላይ ነበሩ ። ሦስቱ፡ ልጃገረዶች እነማን
እንደሆኑ ሦስቱም ወንዶች ከመቅጽበት ለዩኣቸው ትዕግሥት፡ ማርታና ቤተልሔም ነበሩ ። ሁሉም ያላወቋት አንዷ ልጃገረድ የቤቴልሔም የመኝታ ክፍል ጓደኛ ነበረች
አቤል ደነገጠ
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

ጊዜ መደፊት አይገፈትርም።ጊዜ ለሰው ጭንቀትም ሆነ ደስታ ደንታ የለውም።
የራሱን ሥርዓት ጠብቆ የሚጓዘው፤ያለፈ ጊዜ አይመለስም ፤የወደፊቱ ደግሞ እንደ
ፈለግጉት ፈጥኖ አይመጣም። ሰው በጊዜ ቁጥጥር ሥር ነው እንጂ ጊዜ በሰው ቁጥጥር ስር አይደሉም ሰዓት ሰው ሠራሽ ነገር ነው ፤ ሞላውን በማዞር ካለበት ሰዓት ወይም ደቂቃ ማስቀደም ይቻላል ። የቀን መቁጠሪያም ሰው ሠራሽ
ነገር ነው ፤አንዱን ወር አልፎ ሌላውን ወር ማየት ይቻላል ።ቀንን ገፍቶ ማስመሸት፣ ወይም ምሽት ጎፍቶ ማንጋት ግን
የማይቻል ነው ።

አቤል ቢቸግረው እንዲህ አይነት የጊዜ ምርምር ውስጥ ገባ ። ችግሩ ነው ምርምሩን የጋበዘው ቀኑ አልመሽልህ "
ሌሊቱ አልነጋልህ እያለው ተቸገረ ለሌላው ተማሪ የዕረፍት ጊዜ ለእሱ ግን የመጨረሻው ደረጃ የጭንቀት ጊዜ
ሆኖበታል ። ቀንም ይተኛል ፡ ማታም ይታኛል ። ነገር ግን እንቅልፍ አይወስደውም ። እንዲሁ አልጋው ላይ እየተገላበጠ በሐሳብ መብከንከን ሆነ ። ጊዚ ከመቼውም ይልቅ የኋሊት እየተጎተተ የሚያቃስት መስለው ።

ሳምሶን ለዕረፍቱ ወደ ቤቱ ስለ ሔደ መኝታ ክፍላቸው ውስጥ የቀሩት አቤል ፡ እስክንድርና "ድብርት ” ብቻ ነበሩ ። “ ድብርት ” ፈተና ካለቀ በኋላ ያሳየው ለውጥ ቢኖር አልጋ ማንጠፉ ብቻ ነው ። በተረፈ እንደ ጥንቱ “ድብርት ጥናቱም ቢቀር ያው አልጋውን በጋቢ ጋርዶ በራሱ ሕልም ውስጥ መኖሩን አልተወም ። ወደ ውጭ ቢወጣ ብቻውን ነው ።

እስክንድር የዕረፍት ጊዜ ጓደኛው መጽሐፍ ነው ።የአማርኛና የእንግሊዝኛ ልብወለድ መጽሐፎችን እየተዋሰ
ሲያነብ ስለሚውል፥ ቀኑ በፍጥነት ነው የሚገሰግስለት ማንበብ ስልቸት ሲለው፡ወደ መዝናኛው ክበብ እየሔደ ቼዝ
ይጫወታል ። መቼም ከሱ ቦታ ሰው ቢጠፋ ሚስተር ሆርስ አይጠፋም ።

እስክንድር በዚህ ሁኔታ የዕረፍቱን ጊዜ ቢያሳልፍም ከአቤል ጋር አብሮ መጨነቁ አልቀረለትም ። ዐቅሙ በሚፈቅደው መጠን አቤልን ለማዝናናት የማያደርገው ሙከራ የለም ። ከአነበባቸው መጽሐፎች ውስጥ ጥሩ የሚላቸውን መርጦ ይሰጠዋል ። አቤል ግን ነጻ ኣዕምሮ ስለሌለው፥ አንዱንም ከነጣዕሙ አንብቦት አያውቅም ። ጀምሮ ሳይጨርሰው ይቀራል ። ወይም በግል ሐሳቡ ውስጥ እየዋዠቀ ገጹን
በመቁጠር ብቻ ይጨርሰዋል ። እስክንድር ወደ ቼዝ መጫወቻው ቦታ ሲሔድ አቤል አብሮት እንዲሔድ ለማድረግ ቢሞክርም እሺ አላለውም ፡ ከሚስተር ሆርስ ጋር ከተጣላ ወዲህ የመዝናኛ ክበቡን ረግጦት አያውቅም ።
አቤል ወደ ውጭ ብቅ እያለ ከሰዎች ቢቀላቀል ፡ ጊዜውን መዝናኛ ቦታዎች እየሔደ ቢያሳልፍና በአንዳንድ እን
ቅስቃሴዎች ቢሳተፍ፡ ጭንቀቱ እንደሚቀልለት እስክንድር
ቢረዳም ፡ ይህን ለማድረግ ሁኔታዎች አልተመቻቹለትም አብዛኛው መዝናኛ ገንዘብ ይጠይቃል ። ይህን ማሟላት
አይችሉም ። ገንዘብ በማይጠይቅበት መዝናኛ ቦታ ለመዋል ደግሞ የአቤል ሙሉ ፈቃደኝነት አይገኝም ። ሌላ ቀርቶ
ከእስክንድር ጋር ከሚያወራበት ጊዜ ይልቅ፡ ብቻውን ተደብሮ ውስጥ ውስጡን ነገር ሲያብሰለስል የሚውልበት ጊዜ
ይበልጣል ።

ትዕግሥት በተለያየ መልክ በሕልሙ እየመጣች ትታየዋለች ። አንዴ ይጣላሉ ፤አንዴ ጥላው በመሔዷ የተሰማውን ቅሬታ ይገልጽላታል ፤ አንዳንዴ ደግሞ ደብረ ዘይት ድረስ ሔዶ ሲገናኛት ያድራል ቀን ያሰበውን ማታ በሕልሙ ይደግመዋል አንዳንዴ በቅዠት ይወራጫል ።
ከትዕግሥት ናፍቆት ጋር ተደርቦ የወላጆቹ በተለይም የእናቱ ሁኔታ ፊቱ ላይ እየተደቀነበት መጨነቁ አልቀረም ።
ያስብ ያስብና ሁሉም ነገር ፍቺ የሌለው እንቆቅልሽ ይሆንበታል ። ሆኖም እንቆቅልሽ ነው ብሎ አይተወውም ።

ተመልሶ በዚያው ሐሳብ ዙሪያ ይሽከረከራል ፡ በሐሳብ ከመብከንከኑ ጋር የምግብ ፍላጎቱም እየቀነሰ ስለመጣ
በጣም ከስቶ ነበር ። ግን ለዚህ ደንታ አልነበረውም ። አካሉ መንምኖ ነፍሱ ብቻ ከውስጥ ሚን ሚን እስክትል ይጠብቃታል

ብርቅነሽ ትዝ ስትለው የደስታ ብርሃን ትፈነጥቃለች ።ስለ እሷ ማሰብ ደስ ይለዋል። አብሯት ካደረ ጀምሮ የመውደድ ስሜት ተቀርጾበታል ። የፍቅሩን ዐይነት ግን በግል ለይቶ ማወቅ አልቻለም ። ትዕግሥትን ይወዳታል ፡ ብርቅነሽን ይወዳታል ። የመወደዱ ዐይነት ይለያያል ሲያስቡት ደስ የሚልና ሲያስቡት የሚያስቃይ ፍቅር ! ስለ ብርቅነሽ ማሰብ ያስደስተዋል ፤ አያሠቃየውም ፤ ጭንቅላቱን አይበጠብጠውም ። ስለ ትዕግሥት ማሰብ ግን ያሰቃየዋል፥
ይበጠብጠዋል ፤ ያስለቅሰዋል ። እንዲያም ሆኖ ፍቅሩ ለምታሠቃየው ለትዕግሥት ያደላል ። ሙሉ ልቡን ያሳረፈው በትዕግሥት ላይ ነው ። ቀርቦ ምስጢሩን ካካፈላት ፥ ገላዋን ካቀፈውና ትኩሳቷን ሲቀበል ካደራት ሴት ይልቅ ከዐይኑ ላላለፈች ሴት ፍቅሩ ማመዘኑ ለምን እንደያነ ሊገባው አልቻለም ። “ የፍቅር ምስጢሩ ምንድነው ? ሲል አሰበ "
ፍቅር የሚወደው ሥቃይን ይሆን እንዴ ? ?

አንድ ቀን ብርቅነሽን ሲያስታውስ ከውስጡ “ሔደህ እያት ” የሚል አንዳች ግፊት መጣበት። ለእስክንድር ሳያማክረው ተደብቆ ብቻውን ሔደ ። ለምን እንደሚሔድና ቢያገኛት ምን እንደሚላት አላሰበበትም ። ገብቶ ለመጫወትም ቢሆን ፥ የሚጠጣ! ለማዘዝ በኪሱ ገንዘብ የለም ። እናም ቡና ቤቱ አጠገብ ሲደርስ ቀጥ ብሎ ቆመ።

የቡና ቤቱ በር ክፍት ነው ። ነገር ግን ድምፅ አይሰማበትም። እንደዚያ ዕለቱ ምሽት ሙዚቃና የሰው ቻቻታ የለበትም ። ከዝንቦች እምታ በቀር ጸጥ ረጭ ብሏል ።
መግባት አልደፈረም ። እየተንጎራደደ ሰው ብቅ እስኪል ይጠብቅ ጀመር ። ጥቂት እንደ ቆየ ፥ አንዲት ሴት የከሰል
ምድጃ ይዛ ከውስጥ ብቅ አለች ። አለባበሷ ግድ የለሽ ነው ።
ሻሿን የገርዳሳ አስራለች ።

አቤል ሲያያት ክው አለ ። የዋህነቷንና ጥሬነቷን አይታ የቡና ቤቷ ባለቤት ማታ ማታ እንደ አሻሻጭ ቀን ደግሞ እንደ ገረድ ነው የምትጠቀምባት ፡ ከሰሉ እንዲቀጣጠልላት ምድጃውን ወደ ንፋስ አድርጋ ቀና ስትል አየችው ቶሎ አልለየችም። ያው እንደ መንገደኛ ነበር የተመለከተችው ። ስታየው ተደናግጦ ጀርባውን ሰጥቷት ወደ ኋላው ሊመለስ ፈልጎ ነበር ። ግን ዐይኑን ከማሸሹ በፊት የምታውቀው ወንድ መሆኑን ለይታ ጥርሷን ብልጭ አረገችለት እሷን ፍለጋ ያልመጣ ለመምሰል እጁን ኪሱ ከትቶ በግዴለሽ አረማመድ ተጠጋት ስሜቱን ለመሸፈን በከንቱ ደከመ እንጂ በድንጋጤ ፊቱ ቀልቶ ግንባሩን አልቦት ነበር።

ውይ ! አንተ ነህ እንዴ ? በሞትኩት ! ምነው ጠፋህ ? ” አለች ከልብ በሆነ አነጋግር ።

ምንም ሳይመልስላት ስሜቱን በፈግግታ ብልጭታ ለመሸፈን እየሞከረ ጨበጣት

ሙት እውነቴን እኮ ነው ጠፋህ ? ቆይ እስኪ ስንት ቀን ሆነን አዎ ሳምንት አልፎሃል ። እኔ ከዛሬ ነገ ትመጣለህህ እያልኩ በልቤ ሳስብህ ነበር አለችው።

“ እነቷን ይሆን እንዴ ? ” ሲል አሰበ ግን አሁንም ከመቅለስለስና ራሰን ከማከክ ሌላ ምንም አልመለሰም ። ድምጿ የእውነት ቅላጼ ነበረው የተናገረችው የልቧን ነው ፤ ለአቤል አንድ ጥሩ የሆነ ስሜት አድሮበታል ። ሴት ያልለመደ መሆኑና የተማረ መሆኑ ፥ በስሜቷ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጎታል እናም እንዳለችው አብራው ካደረችበት ሌሊት በኋላ ዐልፎ ዐልፎ በልቧ ታስበው ነበር ። የተሰማራችበት ሙያ ሆነና በወሲብ ተገናኙ እንጂ ፥ እሷ ለሱ ያደረባት ስሜት ሐሳቧንና ችግሯን እንደምታዋየው
እሱም በዕውቀቱ እንደሚረዳት የቅርብ ዘመዷ ወይም ታናሽ ወንድሟ ዐይነት ነበር

“ በል እሺ ግባ ! በር ላይ አትቁም አለችው ከእሱ አንዳችም ቃል ባለመስማቷ እያዘነች ።

“አአይ ልሒድ ፤ድንገት ሳልፍ'ኮ ነው
👍2
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


የዕረፍቱ ጊዜ ለአቤል ብቻ ሳይህን ለአብዛኛው ተማሪ ረዥም ነበር " በጥናት መወጠር የለምደ አእምሮ ሥራ ሲፈታ ደቂቃዋም ትረገማለች ። የአዲስ አበባም ተማሪዎች እንኳ አብዛኛዎቹ ወደየ ዘመዶቻቸው መጥተው ሰንብተዋል። ከየክፍለ ሀገሩ የመጡ ተማሪዎች ግን መሄጃም ሆነ ጊዜ ማሳለፊያ በማጣት ቦዝነው ነው የሰነበቱት ቀን ቀን ሁሌም ተደብረው ይውላሉ " ጫዋታና ቀልድ የሚኖረው ማታ ማታ በየመኝታቸው ሲሰፍሩ ነው " በአብዛኛው መኝታ ክፍል ተደጋጋሚ የጨዋታ አርዕስቶች ሆነው የሚቀርቡት የአቤልና የትዕግሥት የዐይን ፍቅር • የለማና የቤተልሔም ጉዳይ ፡ ወይም ሌሎችን የተደረሰባቸው አዲስ
ፍቅረኞችን ማጋለጥ የመሳሰሉት ናቸው ።

የግቢውን የፍቅር ታሪክ መሰለልን መዝናኛችው አድርገው የያዙ አንዳንድ ተማሪዎች አሉ ። ወሬአቸውን የሚያደምቁት የፍቅረኞቹ ጓደኛ በመምሰል ቀርበው ምስጢራቸውን እየሰረሰሩ ነው ። በዚሁ ተግባራቸው፡“ ሳተላይት”” “ ሮይተር” ፡ “ ቢቢሲ” የሚል የቅጽል ስም የወጣላቸው ተማሪዎች ነበሩ ። ወሬ አጠናቅረው መጥተው በግቢው ያሰራጫሉ ። ምሽት ላይ እነሱ ሲመጡ! ሁሉም ወሬ ለመስማት ከተኛበት ብድግ ብድግ ይላል ።

“ ያልሰማህ ስማ ! የሰማህ ላልሰማ አሰማ ! አዲስ ዜና በዚህ በዝግ ጊዜ ውስጥ አንድ መምህር ከአንዲት ተማሪው ጋር በዋቢ ሸበሌ ሆቴል የዳንስ ምሽት ላይ መታየቱ፥ ከታመኑ የዜና ምንጮች ደርሶናል።

• ደሞ ማን ይሆን ? ” እያለ ተሜ ከመኝታው ውስጥ በአንሶላው ብቻ እየወጣ ' በጆሮው ሳይሆን በመላ ሰውነቱ
የሚያዳምጥ ይመስል' ወሬው ወደ ነፈሰበት ይጠጋል ምን ጊዜም የሚሞቀው « እነ “ ሮይተር ” እነ “ ሳተላይት” ያሉበት መኝታ ክፍል ነው ። ብዙ ተማሪ ክፍሉን ትቶ እነሱ ያሉበት ድረስ እየመጣ ያመሻል ።

« ማነው እሱ በናትህ፣"

"ለማን ታውቁታላችሁ ? ሁለተኛ ዓመቶችን የሚያስተምር ራሰ በራ ሰውዬ።

“ እ" ዐወኩት ። ከማን ጋር ነው የታየው ? ” ይላል " የሚያውቀው።

ለማን የማያውቀው ደግሞ ፣ በእዝነ
ልቦናው ለማን ፍለጋ ይጓዛል።

"በተልሔም ከምትባል ቀይ ወፍራም የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ጋር ፡ ..".

“ውይ እሷንማ ሲያወጣት ቆይቶ የለም እንዴ? " ይላል ከአሁን በፊት ቀድሞ ወሬውን የሰማ።

"ሒ.....ድ?" ይላል ለወሬው እንግዳ የሆነ ሁሉ በአድናቆት

“ ኧረ እንዲያውም ሊጋቡ ነው ” ሲል ቤተልሔም ጣት ላይ የጌጥ ቀለበት ያየው ደግም ነገሩን ያጋንናል ።

“ ስጥ እንዲህ ! ” ይላሉ ፡ ውሸቱ አልዋጥ ያላቸው።

“ ተወው እስኪ ያውራ ፡ እጅሬ መቼም መስጠት ልማዱ ነው።

ውሸት ፈጥረው የወሬ ማጣፈጫ እያደረጉ በማቅረብ የተካኑ ተማሪዎች አሉ ። “ ስጥ እንግዲህ ” የጨዋታቸው»
አርዕስት ሲሆን እነሱ ደግሞ “ አባ መስጠት ” በመባል ይታወቃሉ ።

ውሸቱ ከፍ ያለ እንደህነ "ርግጫ ” ይባላል ። ዋሻዎቹ “ ረጋጮች” ሲባሉ፥ የፕሮግራማቸው ስም ደግሞ

“ረግጣ” ነው ። ማኅበራዊ ኑሮን የሚጠሉ ጥቂት መሠሪዎች ካልሆኑ በስተቀር ። የአብዛኛው ተማሪ የሮይተሩም የረጋጩም - ተግባር የዩኒቨርስቲውን የዕረፍት ጊዚ ሕይወት ለማጣፈጥ ነው። »

“ እባካችሁ ጨዋታውን ወደ ቀልድ እትቀይሩት ይላል ለወሬው የጓጓ ፥ አምርሮ ።

"በቃ " ይኸው ነው ለማ ቤተልሔምን እወጣት

“ “A” ያለምንም መጨነቅ በእጅዋ ገባ ማለት ነው ።ከቻለ ደግሞ ከራሱ ትምህርት ዐልፎ ሌሎቹም ጓደኞቹ እንዲረዷት ይለምንላታል ፡

“ እናታቸውን ! እነዚህ ሴቶች ጨረሱን ” ኮ ! ጭንቅላት ሲያጡ በወሲብ ዩኒቨርስቲን ሊወጡ ! ” ሲል ፥ ሁሉም
በብሽቀት ጥርሱን እያንቀጫቀዉ በጅምላ ሴቶቹን ይራገማል።

“ ለካ ለዚህ ነው ” ይላል " እርዕስቱ እንዳይቋረጥ የሚፈልገህ ለአርዕስቱ እንደገና ሕይወት ለመስጠት ቅመም እያዘጋጀ

“ ምኑ ? ብዙ ጆሮዎች ሰልተው ይቆማሉ "

"ሰሞኑን ለማ ከሚስተር ራህማን ጋር ግንባር ፈጥሮት የሚታየው !!

"ራህማን ? ”

"ሚስተር ራህማን እኝያ ህንዳዊው ። ”

“ እ ! እ ! ” ሞቅ ያለ ሣቅ ።

“ ለማ የቅርብ ጓደኞቸ ሆኗል ። ለሻይ ሲወጡም አንድ ላይ ነው።

“ የዓላማ አንድነት ነዋ ያስተሳሰራችው ።

“ እሳቸው”ኮ ሐኪም ሳያይዝላቸው አይቀርም ። በሴት ቀልድ አያውቁም ፤ በተለይ ወፍራም ሴት ሲወዱ ! ”

“ ብቻ አንድ ቀን ሴት ጭን ውስጥ ትንፋሻቸው ቆሞ እንዳይገኙ ” ይላል የበሸቀው ክፍል እያፈዘ »

ጨዋታው ይቀጥልና ከመምህራን ተመልሶ ወድ ግል መበሻሸቅ ያመራል ። እርስ በርስ መጋለጥ ይመጣል ። አንዱ
የሌላውን ምስጢር ለመጎልጎል በነገር ጎሸም ያረጋል "ነገሩ የሚነካው ቁስለኛ ካለ በወዲሁ ማኩረፍ ይጀምራል ።
ሆኖም እነ “ ሮይተር ” የማንም ኩርፊያ አያግዳቸውም ።

“ ነገርን ነገር ያነሣዋል ” ሲሉ ይጀምራሉ

“ ደሞ ምን ልታመጡ ነው ? ”

የቤተልሔምን ጓደኛ ሊያወጣ የሞከረም ከመሃከላችንም አይጠፋም ኮ ! ”

ማንን ? ያቺን ማርታን እንዳይሆን ? ! ”
“ እህህሳ ! ማርታ ዐይኗ ስለማያርፍ ሳይሆን አይቀርም ፤ ብዙ ተማሪዎች ዐይናቸውን ጥለውባታል ፡ በግቢው ውስጥ ከብዙ ሴቶች መሃል ተለይታ ትታወቃለች ። ጠይቀው ሊያወጧት የሞከሩ ወይም የሚፈልጓት ከእስክንድር ሌላ ብዙ ናቸው በአለባበሷ ደምቃ ከመታየቷ ሌላ ምን ጊዜም ዐይኗ አያርፍም ። ስትበላ የአዳራሹን ወንድ እየቃኘች ነው ። ስታጠናም መጻሕፍት ቤት የተቀመጠ ፍጥረት አይቀራትም ። ወንዶችን ብቻ ሳይሆን ሴቶችንም ሥራዬ ብላ ነው የምታየው ፡ ሴቶችን የምታየው ግን በጤናማ ዐይን አይደለም ። ዘወር ብላ እንደ ሽንኩርት ትልጣቸዋለች ። በተለይ ደመቅ ያለች ሴት ማርታ ዐይን ውስጥ ከገባች አለቀላት !
ውሸት ፈጥራ ስሟን ታጠፋለች ። !

“ ውይ ! ያቺን ሞጥሟጣ ነው እንዴ ?” ሲል ቁስል ያለበት ማጥላላት ይጀምራል
“ሞጥሟጣነቷን በምን ዐወቅክ ? ” በማለት ፡ ሳታላይቶቹ ያፈጣሉ "

“ደሞ ምን ልታመጡ ነው ? እዚያው በጸበላችሁ ! ”
ቁስለኞ ማኩረፍ ይጀምራል ።

“ አንተ ምን አስኮረፈህ ? አንድ ቀን ብቻ ነው የጠየቅካት እና “F” ኮመኩህ ተመለስክ ። ይሄ ደሞ አያሳፍርም ።"

ጠይቆ ሲሳካ “A” እንደማግኘት ሲቆጠር ፡ ሳይሳካ ሲቀር ደግሞ "F" መኮምኮም ይባላል ።

“ አይ አጅሬ ! መኮምኮም አይሰለቸው ! ” በማለት ከፊሉ ያደንቃል "

“ ስጡ እንግዲህ ! አባ መስጠቶች መስጠት አይሰለቻችሁ።

“ ምኑ ላይ ነው ውሸቱ ?”

“ መዋሽት ብቻ ነዉ እንዴ ደኅና አርጎ መርገጥ ነው እንጂ ። ምን ታረጉ ? ! ዝም ብለው የሚረገጡላችሁ እገኛችሁ ርግጡዋቸው !”

አስረጅ ! ” በማለት ከመሐል ነገሩን አጠናካሪ ይናገራል።

"ደም አንተ ምን ልትል ነው ? ”

“ አጅሬ አንድ ቀን" እነማርታ የሚያጠኑበት ኣካባቢ ያለ ሥራው ሲያንዣብብ አግኝቼዋለሁ ፡ ”
አጥቂ ሲበዛበት ቁስለኛው የሚያመልጥበትን ዘዴ ያሰላሰላል ኩርፊያ አያዋጣም ። ቁጣም አያዋጣም ። የዚህ
ዐይነት አዝማሚያ ከታየ ተማሪዎቹ የባሰ ያሳብዳሉ ። ያለው ምርጫ ቀስ ብሎ ቀዘዴ አርዕስት ማስለወጥ ነው ።

“ ይልቅ የሚገርመው የዚያች የእነ ማርታ ጓደኛ ነገር ነው " ያ የአራተኛ ዓመት የማዕረግ ተማሪ የሚወዳት ! ”
ሲል እንደ ምንም ወደ ሌላ አርዕስት ይሸጋገራል ።

የቤተልሔም እና የማርታ ነገር ከተነሣ የትዕግሥትም አይቀርም » ብዙ ጊዜ አብረው ስለሚታዩ ነው ። አቤል ከሚስተር ሆርስ ጋር ተጣልቶ የአዕምሮ መታከሚያ ሆስፒታል ከተወሰደ ጊዜ ጀምሮ እነ “ ሮይተር ” ስለዚህ ጉዳይ
👍21
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


....እስክንድር በግቢው ውስጥ በሚካሔዱት የመዝናኛ ቀልዶች ተረቦችና ጨዋታዎች በተሳተፈ ቁጥር አንድ
የሚገርመው ነገር አለ ። አብዛኛው ወሬ ስለ ሴትና ወንድ ግንኙነት ወይም ስለ ፍቅር ነው ። “ ሌላ ወሬ አጥተን ነው
ወይስ ዕድሜአችን ነው በዚህ አርዕስት ዙሪያ የሚያሽከረክረን ? ወይስ ደግሞ የጋራ ስሜታችንን የሚነካ ጉዳይ ይህ
ብቻ ሆኖ ነው ?” ሲል ያስባል ። ነገር ግን ከአቻው ጋር በተገናኘ ቁጥር ዞሮ ዞሮ አመርቂ አርዕስት ሴት ሆናለች ፤ እና
የዕድሜን ኃይል ግለት ይታዘባል ትኩስ 'አፍላ የሚያቅበጠብጥ ዕድሜ።

የዕረፍቱ የጨዋታ ምሽቶች ከፍቅር እልፍ ያሉ እንደ ሆን በግቢው ውስጥ ከሚታዩት ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያርፋሉ የፍቅር ጉድጓድ እንደሚሰረስሩት “ሮይተሮች ” ሁሉ በዩኒቨርስቲው ውስጥ ፀረ መጤ ሃይማኖት አቋም ይዘው እያንዳንዷን እንቅስቃሴ እየተከታተሉ የሚ
ተርቡም አሉ ። በየዕለቱ በየትኛው ድርጅት ውስጥ ማን እንደ ተመለመለ ወሬው አያመልጣቸውም ሌላው ቀርቶ
የትኛው የሃይማኖት ድርጅት በግቢው ውስጥ የአባላት ብዛት እንዳለው የሚያውቁና በአሀዝ የሚያቀርቡ አሉ ።

ሰሞኑን “ ሁለተኛው አምላክ ዘ" ታላቅ ኪሳራ ደርሶበታል ” ሲል አንዱ ይጀምራል

“ እንዴት ? ”

“ በፈተና ሰሞን የመለመላቸው አባላት አብዛኛዎቹ ፈተና ካለቀ በኋላ ርግፍ አርገው ትተውታል። ከመብላታቸው በፊት መጸለይ አቁመዋል ። አስረጅ ”

“ በዩኒቨርስቲው ውስጥ በሃይማኖት አባልነት የተመለመሉት የሚታወቁት፡ምግብ ኣዳራሽ ውስጥ ከመመገባቸው
በፊት አቀርቅረው ሲጸልዩ ነው ። ጸሎቱን ሲያቆሙ ኮንትራታቸውን መጨረሳቸው ይታወቃል

“ አትለኝም ማን ማን ተወ በናትህ ? ”

የሚታወቁትን በስም የማይታወቁትን በመልክ ጥቆማ ይካሔዳል ።

“ ምነው ውጤት እስኪቀበሉ እንኳ ቢቆዩ ፈተና ላይ “ የረዳቸው ” አምላክ የአራሚውንም መምህር እጅ በማሳሳት እንዲረዳቸው ። ”

"ቸኮሉዋ ! ምን ያርጉ በዕረፍት ጊዜያቸው በሃይማኖቱ ከቀጠሉበት ሴቶቹ መደነስ ወንዶቹም መጠጣት ሊያመልጣቸው ሆነ ለማን ጀቴ ብለው !”

“ አሥቂኝ ነው ” ይላል አንዱ ቀልደኛ ከመሐል።

“ እንዴት ?” ሲል ሁሉም ጆሮውን ይቀስራል ።

“ ከአምላካቸው ጋር ድብብቆሽ ጨዋታ ነው ” ኮ የተያያዙት ። ፈተና ሲደርስ ይሰግዱለታል ። ከፈተና ከወጡ በኋላ ይዘጉታል ። ዋ ብቻ አንድ ቀን ያመረረ ዕለት !”

ቀልዱ ሲኮረኩራቸው መሣቅ እየፈለጉ በልባቸው አፍነው የሚያሳልፉ አሉ። ሲሥቁበት አምላክ እንዳያያቸው
የፈሩ ይመስላሉ ። አንዳንዱ በዚህ አርዕስት ላይ ሲያሾፍ ፡ ሲቀልድ ፥ ሲተርክ አንዳንዱ ደግሞ ገለልተኛ ሆኖ መስማቱን ይመርጣል ። ጨዋታውን ማዳመጥ ይወዳል ፤ ግን በሃይማኖታዊ ድርጅቶችም ሆነ በአምላክ ላይ አንዳችም
ተቃርኖ አያነሣም ። “ ከአፍ የወጣ እንጂ በጆሮ የገባ አያረክስም” ከሚል ግምት ላይ የደረሰ ይመስላል ።አፌን በዳቦ
ነው ነገሩ ።

እንዲህ ዐይነቶቹ የጨዋታ ምሽቶች በብዙ ተማሪዎች አእምሮ ተቀርጸው የሚቆዩ ናቸው ። በሴቶችም መኝታ ክፍል ቢሆን ሐሜቱና ተረቡ ቢበዛ እንጅ አያንስም ። ወንዶችን በማብጠልጠል አስተማሪዎችን በመቦጨቅና ራስን በመካብ ሴቶቹን የሚያህል የለም ። “ እገሌ “ኮ እንድወጣለት ጠይቆኝ ዘጋሁት ያ ባላገር ” የብዙዎቹ የጋራ ፈሊጥ ይመስላል ። የሚገርመው ደግሞ ሴቶቹ ሲዋሹ እርስ
በርሳቸው ይቻቻላሉ ። እንደ ወንዶቹ “ረገጣ” እና “ስጥ እንግዲህ ” እየተባባሉ ቅስም አይሰባበሩም ።

ቀልድ እየፈጠሩና ወሬ እያጠናቀሩ ተማሪውን የሚያዝናኑትን ያህል በየአስተማሪው ቢሮ እየተሹለከለኩ የፈተና ውጤት ከመነገሩ በፊት መርዶ የሚያረዱ አንዳንድ ተማሪዎችም አሉ ። እነዚህን ማንም አይወዳቸውም የዩኒቨርስቲ ሕይወታቸው ዕድሜ የሚኖረው ለአስተማሪዎች ወሬ በማመላለስ ነው እየተባሉ ይታማሉ ። ማርክ ቀድም የመስማት ሱስ አለባቸው ። የራሳቸውን ሳይሆን የሌሎቹንም የመስማት ሱስ ነው የያዛቸው ። እወደድ ባይ ወይም ለተራ ወሬ ጆሮውን የሰጠ መምህር የሦስት ልጆችን ማርክ ይነግራቸዋል ።እነሱ ደግሞ አባዝተውት የሃምሳ ልጆችን ውጤት እንደ ሰሙ አርገው ወሬውን ይዘራሉ መምህሩ ወደቀ ካላቸው እነሱ “ ተሰበረ ” ብለው በግቢው ውስጥ ሽብር ይፈጥራሉ ።

ዘንድሮ ይህን ያህል ፍሬሽ ይባረራል ” ብለው በአፋቸው ሙሉ ሲናገሩ የሬጂስተራሩን ቢሮ የያዙት ይመስላሉ ።

“ የእንትን አስተማሪ ከዚያ ሁሉ ተማሪ መሐል ሁለት “A” ብቻ ነው የሰጠወ” ሲሉ የመምህሩ የቅርብ ጓደኛ ይመስቀሉ

ከመልካም ዜና ይልቅ የዝቅተኛና የውድቀት ማርክ ሽብር መፍጠር ነው የሚቀናቸው ። ሌላውን አስበርግጎ ወይ
እነሱ የወሬ ሱሳቸውን ካልተወጡ አይሆንላቸውም ።

እቅጩ የሚታወቀው ግን ጊዜው ደርሶ ማንኛውም ተማሪ የራሱ ውጤት በራሱ እጅ ከደረሰው በኋላ ነው፡አቤል ከሁሉም፦ ርቋል ጥሩውንም መጥፎውንም አይሰማም ። “ ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው” እንዲሉ በሱ ላይ የሚወራበትን አያውቅም። ነገር ግን ተማሪው ሁሉ በሽታወን ያወቀበት እየመሰለው ከሁሉም ሸሽቶአል ። ጓደኛው ብቸኝነቱ ነው » አጫዋቹ የቀን ቅዠቱ ፥ የሌሊት
ሕልሙ ነው ። ሌላው ክፍል ተማሪው ተሰብስቦ እያወራ እየቀለደና እየተጫወተ ሲሣሣቅ፥ አቤል ከብቸኝነቱ ጋር
ይሟገታል ። ትዕግሥትን ያልማል ፤ በል ሲለውም ይረግማታል ። የመልካሙ ተበጀን ዘፈን ያዜማል ። ብርቅነሽን ያስባል ከራሱ ጋር ይሥቃል ። ከራሱ ጋር እየተጣላ ያለቅሳል።

በዚህ ዓይነት የሚገፉ ዐሥራ አምስት የዕረፍት ቀናት የዐሥራ አምስት ዓመት ያህል ቢረዝሙም ማለቃቸው አይቀርም ያልቃሉ ። የሚጠበቀውም ቀን መድረሱ
አይቀርም ይደርሳል ።

ትዕግሥት የፈተና ውጤት ሊሰጥ እንድ ቀን ሲቀረው ከደብረ ዘይት አዲስ አበባ ገባች ። ወደ ዩኒቨርስቲዉ መኝታ ክፍሏ ስታመራ፥ አንዳች ነገር የኋሊት ይጎትታት ነበር። ከዘመዶቿ ጋር ከርማ መለያየቷ ተጫጭኖዋታል "በዚያ ላይ ማርታና ቤተልሔምገና ስላልመጡ ብቻዋን ነበረች።

አቤልን ለማየት ቆርጣ ነበር የመጣችው ። ተለይታው በከረመችበት የዕረፍት ጊዜ ውስጥ ሲናፍቃት ነበር ። ግን ለምን ? መናፈቁን ነው እሷ ያልወደደችው ። ትዕግሥትም እንደ አቤል ለፍቅር እንግዳ ናት ። በልጅነቷ ጭቃ እያቦካች
ጎጆ ሠርታ፡ “ባልናሚስት” የተጫወተችበትን ጊዜ ወይም
ከትምህርት ቤት ጓደኞቿ ጋር የተጫወተችባቸውን ጊዜያት ታስታውስ እንደሆን ነው እንጂ ሌላ የፍቅር ትዝታ የላትም፡ አሁን ዕድሜዋ ይገፋፋታል " የወንድ ልጅ ክንድ ተደግፋ
በነፋሻማ ስፍራዎች መወዝወዝ ያምራታል አፍ ለአፍ ገጥማ ምስጢር የምታወራው አቻ ወንድ ያምራታል የወንድ ልጅ ከንፈር ጣዕም መቅመስ የሚያሰኛት ዕድሜ ላይ
ነች። ነገር ግን በዚህ ፋንታ የመጀመሪያ ፍቅሯ ከዐይን የማያልፍ ሆነ ። አቤል ቀርቦ ምስጢሯን አይካፈላትም ።የፍቅር ትኩሳቷን አይጋራትም ፡ የደረቀ ከንፈሯን አያረጥብላትም ፡ ወንዶች ላይ ለሚቅበዘበዝ ዐይኗ ገደብ አይገዛላትም። እሷነቷን ቀርቦ አያውቅላትም ። በሩቅ እየተያዩ መነፋፈቅ ብቻ

ትዕግሥት ይህን ሁሉ አመዛዝና ነበር አቤልን ቀና ብላ ለማየት የወሰነችው ። ትርጉም የሌለው ፍቅር ሆነባት ።
ከመጐዳቱና ከማንገብገቡ በቀር ጥቅሙ አልታይ አላት ።እንዳሰበችው የመጣች ዕለት ጨክና ሳታየው ዋለች። ከደብረ
ዘይት ያመጣችው የአገልግል ምግብ ስለ ነበር ወደ ምግብ አዳራሽም ብቅ ሳትል ዋለች ። ሐሳቧ ሴሚስተሩን በሙሉ
ከእርሱ ርቃ ለመቀጠል ነበር ። ግን ያን ዕለቱኑ ወደ ምሽት ላይ ከቁጥጥሯ በላይ
👍1