#የመመሳሰል_ፀብ
የእኔና አንቺ ችግር፡-
አይደለም ቋንቋችን - በመዘባረቁ፣
አይደለም ጎጇችን - በማጨናነቁ፣
አይደለም ባህላችን- ልዩነት መፍጠሩ፣
'መለያየታችን' - አይደለም ችግሩ፡፡
የኔና አንቺ ችግር፡-
በብዙ ነገሮች “መመሳሰላችን
መደመጥን እንጂ፣
ማዳመጥ የማንወድ ሰዎች መሆናችን፡፡
የኔና አንቺ ችግር፡-
በጸባይ በምግባር - አንድ መሆናችን
ነገር እየበላን - እህል መራባችን፡፡
ያው እንደምታውቂው-
ፍቅር እየተራበ - ነገር ተመጋቢ - እያደር ይከሳል
በምላስ የቆመ - ጆሮ የሌለው ቤት - በጩኸት ይፈርሳል፡፡
በቀላል መፍትሔ - የተናጋውን ቤት - ሲቻለን ለማደስ
በተራ ምክንያት - ፍቅራችን አክትሞ -ቅጥራችን እንዳይፈርስ፤
አንዴ እንነጋገር፣
አንዴ እንደማመጥ - ግዴለሽም ፍቅሬ
ምንድን ነው ችግርሽ!?
ምንድን ነው ችግሬ!???
🔘ሙሉቀን ሰለሞን🔘
የእኔና አንቺ ችግር፡-
አይደለም ቋንቋችን - በመዘባረቁ፣
አይደለም ጎጇችን - በማጨናነቁ፣
አይደለም ባህላችን- ልዩነት መፍጠሩ፣
'መለያየታችን' - አይደለም ችግሩ፡፡
የኔና አንቺ ችግር፡-
በብዙ ነገሮች “መመሳሰላችን
መደመጥን እንጂ፣
ማዳመጥ የማንወድ ሰዎች መሆናችን፡፡
የኔና አንቺ ችግር፡-
በጸባይ በምግባር - አንድ መሆናችን
ነገር እየበላን - እህል መራባችን፡፡
ያው እንደምታውቂው-
ፍቅር እየተራበ - ነገር ተመጋቢ - እያደር ይከሳል
በምላስ የቆመ - ጆሮ የሌለው ቤት - በጩኸት ይፈርሳል፡፡
በቀላል መፍትሔ - የተናጋውን ቤት - ሲቻለን ለማደስ
በተራ ምክንያት - ፍቅራችን አክትሞ -ቅጥራችን እንዳይፈርስ፤
አንዴ እንነጋገር፣
አንዴ እንደማመጥ - ግዴለሽም ፍቅሬ
ምንድን ነው ችግርሽ!?
ምንድን ነው ችግሬ!???
🔘ሙሉቀን ሰለሞን🔘
🥰1
#እድሜ
የሰው ህይወት አጥር
የቁጥር ስብጥር፣
አንድ
ሁለት
ሶስት
አራት
.
.
.
ጠብ
ጠብ
ጠብ
ይላል በቁጥር፤
ከሰው ወደ ምድር
ከምድር ወደ ሰው፣
የእስትንፋስን ድንበር
የእስትንፋስን አጥር
በአንድ ጊዜ ሊያፈርሰው፡፡
.
የቁጥር ገበታ
የቁጥር ጠብታ፣
በቁጥር ተሞልቶ
ቁጥርን አንጠባጥቦ
ቁጥርን ባዶ ሊያስቀር
ጠብ
ጠብ
ጠብ
ይላል በቁጥር፡፡
ሲንጠባጠብ ኖሮ
ይደፋል በሙሉ ከሰው ወደ ምድር
ተምሶ ሊቀበር፡፡
🔘ሙሉቀን ሰለሞን🔘
የሰው ህይወት አጥር
የቁጥር ስብጥር፣
አንድ
ሁለት
ሶስት
አራት
.
.
.
ጠብ
ጠብ
ጠብ
ይላል በቁጥር፤
ከሰው ወደ ምድር
ከምድር ወደ ሰው፣
የእስትንፋስን ድንበር
የእስትንፋስን አጥር
በአንድ ጊዜ ሊያፈርሰው፡፡
.
የቁጥር ገበታ
የቁጥር ጠብታ፣
በቁጥር ተሞልቶ
ቁጥርን አንጠባጥቦ
ቁጥርን ባዶ ሊያስቀር
ጠብ
ጠብ
ጠብ
ይላል በቁጥር፡፡
ሲንጠባጠብ ኖሮ
ይደፋል በሙሉ ከሰው ወደ ምድር
ተምሶ ሊቀበር፡፡
🔘ሙሉቀን ሰለሞን🔘
#ጨረሬን
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እማማ ሞቱ !!
ትላንት ልክ ፀሐይ ስትጠልቅ፤ እማማ ይችን ዓለም ተሰናበቱ !
ዘጠኝ ዓመት ሙሉ ከአልጋ ወርደው የማያውቁት ሚስኪን ሴት፣ የሰፈሩን ሰው ሁሉ እንዳኮረፉ ሞቱ። ዘጠኝ ዓመት አስታመን፣ እንደ እናት ተንከባክበን፣ ባለቀ ሰዓት ረግመውን ሞቱ” እያለ የሰፈሩ ሰው በሙሉ አዘነ: አፍ አውጥተው አይናገሩት እንጅ ያስረገምከን አንተ ነህ” የሚል ወቀሳቸውን ከእያንዳንዳቸው ዓይን ላይ እይቻለሁ፡፡እኔም ምነው በቀረብኝ ብዬ በውስጤ ስብሰለሰል ሳምንት አለፈኝ፡፡ የሆነ ሆኖ እማማ
ላይመለሱ ከነኩርፊያቸው አሸለቡ፡፡ ለነገሩ ኩርፊያ ይሁን ሐዘን ማንም አልገባውም:
በኩርፊያና በሐዘን መሃል ያለው ልዩነት ምንድነው? ምንስ ነው በቁጣና የኩርፊያ
መካከል ያለው መስመር? …መዝገበ ቃላት ቃላትን እንጅ ስሜትን አይፈታም፡፡ እማማ፡
በምናውቃቸው ቃላት የገለፅነው የማናውቀው ስሜት ውስጥ የነበሩ ይመስለኛል፡፡ የሕይወት ታሪካቸው ሲነበብ በደፈናው “የሁላችንም እናት ነበሩ” ከሚል የወል ምስጋና ውጭ እምብዛም የተዘረዘረ ነገር አልነበረም:: አስክሬናቸው በአራት የሰፈራችን ወንዶች ትስሻ ላይ ተቀምጦ በቀባሪው አጀብ በቀስታ ወደ መቃብር ቤቱ ጓሮ ሲጓዝ እእምሮዬ ወደትዝታው የኋሊት ነጎደ ፡፡
የዛሬን አያድርገውና ከሊቅ እስከ ደቂቅ መዋያችን እማማ ቤት ነበር፡፡ የእማማ ቤት እንደው ቤት ሆነ እንጅ ነገረስራው ድድ ማስጫ የሚሉት ዓይነት ነበር፣ ሕፃናቱ እማማ ቤት በር ላይ እቃቃቸውን ሲደረድሩና ሲያፈርሱ፣ የእቃቃ ሰርግ ሲደግሱና
ሲጋቡ፡ወጣቶቹ ተሰብስበን ካርታና ዳማ ስንጫዎት፡ ስለሴት ስናወራና ስናውካካ እንውላለን እሁድ እሁድ የሰፈሩ እድር ዳኞች እና የዕቁብ ገንዘብ ሰብሳቢዎች እዚያው እማማ ቤት ተሰብስበው ሲነታረኩ ያረፍዳሉ፤ ያ አንድ ክፍል የቀበሌ ቤት ሁል ጊዜ ከጧት እስከ ማታ በሩ ክፍት ነበር።
በዛ ዕድሜ እንደ እማማ ዓይነት ረዥም እና ቆንጆ ሴት አይቸ አላውቅም፤ በድህነት ተጎሳቁለው እንኳን ጥርት ያለ ጠይም ቆዳቸውና ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት ፀጉራቸው አንዳች ሞገስ ነበረው ስለ ረዥም ቁመት ሲወራ ምሳሌ ነበሩ እንደ እማማ ዠርጋዳ ይባላል፡፡ ዠርጋዳ ነበሩ፤ ሲራመዱ የሚንሳፈፉ የሚመስሉ፡፡ በስተኋላ ዘመናቸው እርጅና ተጭኗቸው፣ ትንሽ ከወገባቸው ጎበጥ ብለው እንኳ በቁመት የሚስተካከላቸው
እልነበረም፡፡ ባልም ልጅም አልነበራቸውም፡፡ መተዳደሪያችው ሰርግና ድግስ ሲኖር ወጥ
በመስራት ነበር፤ ታዲያ ወጥ ሳይቀምሱ በሽታው የሚያውቁ ባለሙያ ናቸው ይባላል።
ሴት ልጅ የወጥ ማማስያ ከላሰች ምኑን ሴት ሆነች ኤዲያ !?” ይላሉ፤ውጥ ሲቀመስ ሲያዩ
እይወዱም:
እማማ ለምን ባል አያገቡም? ስንላችው፣
“በልኬ ወንድ አጣሁ፤ ጨርሶ ኩርፋድ አጎንብሸ ላግባ እንዴ…? ይሉና ይስቃሉ፤ ጨዋታ
እዋቂ ናቸው :
ፀ
ታዲያ ዓመቱን ሙሉ ማድቤት ለማድቤት ከርመው ለጥምቀት ጽዓል ፀጉራቸውን ተሰርተው፣ሰፊ ባለባንዲራ፣ ጥለቱ ጉልበታቸው የሚደርስ ያበሻ ቀሚሳቸውን ይለብሱና፣ በወገባቸዉ ላይ ሶስት አራት ዙር ተጠምጥሞ ጫፉ ወደታች የሚንዘረፈፍ መቀነታቸውን ሸብ አድርገው፣ ክብ ሰርተው የሚጨፍሩ (እሳቸው “የአገሬ ሰዎች የሚሏቸው) ወንዶች መኻል ገብተው ምንጃርኛ የሚባል ዘፈን እያወራረዱ ጭፈራቸውን ያስነኩታል:እማማን ለማየት የማይመጣ ሰው የለም እማማ መጡ ክፈቱላቸውም ይባላል … ክቡ የሰው ቀለበት በመጡበት በኩል ተከፍቶ ይገባሉ… የታወቁ ናቸው !
ቸብ ቸብ ቸብ ሲዴረግ እማማ እጃቸውን ከፍ አድርገው …
“የምንጃር ልጅ …ሽቅርቅር ብለሺ ነይ ነይ ዙረሺ
ይላሉ፣
የከበበው ህዝብ ይቀበላቸዋል፤ ሕዝቡ ድንገት ለጥምቀት የተሰበሰበ ሳይሆን አብሮ ግጥምና ዜማ ሲያጠና የከረመ ነበር የሚመስለው!
ኢሄ የጀግናው አገር
.
እዛው ምንጃር …
ወረዶች ሸንኮራ …
ስንዴ ልትበላ፣
ወረደች ምንጃር ….
የጤፍ አገር፤
ተይ አብሪው ኩራዙን …
ሳትፈጅው ጎዙን፤
“ያዝ እንግዲህ!” ብለው በዛ ቁመት ድንገት ወደላይ እየዘለሉ ሲመለሱ በፀጉራቸው
የግዜርን ዘርፋፋ ቀሚስ ነክተው የሚመለሱ ነበር የሚመስሉት! ጭብጨባው፣ ጩኸቱ፣ሳቁ ይደምቃል ጎን ለጎን የተደረደሩ ጨፋሪዎች በከበበው ሰው ጭብጨባ ፊትም ልክ
በአንድ ላይ ሸብረክ ሸብረክ… ሸብረክ እያሉ ወደፊት ወደኋላ እተራመዱ ሲጨፍሩ
የተለየ ስሜት ነበረው፡፡
እዛ ማዶ፣
አሃ
ከተራራው!"
አሃ.!
ዓይኑ ነው ወይ፤
እሃ፣
የሚያበራው፧ - የሰሌን ባርኔጣ በቀኝ እጃቸው የያዙ ጨፋሪ ወንዶች በአንድ ላይ ባርኔጣቸውን ከፍና ዝቅ እያደረጉ ሲጨፍሩ አቧራው ይጨሳል …እማማ እንደዛ ነበሩ፡፡
በሰፈሩ ሰው ዘንድ እማማ የሚለው ቃል የወል ስምነቱ ቀርቶ የዚቹ ሴትዮ መጠሪያ ከሆነ ዘመን የለውም፡፡ ሰፈራችን ውስጥ የሚኖሩ ሰዕድሜ የገፉ ባልቴቶች ሁሉ እማማ ከሚለው ቀጥሎ ስማቸው ይጠራል፡፡ እማማ ተዋሱ ፡እማማ ዮሃና፣ እማማ ብርነሽ እማማ ግን እማማ ብቻ! የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ታዲያ ለማኅበር ድፎ ደፍተው ማድቤት ጉድ ጉድ ሲሉ ራሳቸውን ስተው እሳት ላይ ወደቁ፣ እሳቱ ግራ ክንዳቸውና በግራ
በኩል ያለ የራሳቸው ፀጉር ክፉኛ ተቃጠለ የግራ ጆሯቸውም በከፊል በእሳቱ ተጎድቶ ነበር፡፡ ያ የተረገመ አደገ የእማማ ጠይም ፊት ላይ በግራ በኩል ለማየት የሚያስፈራ የእሳት ጠባሳ ትቶባቸው አለፈ። ይሄም ባልከፋ ነበር፤ከአደጋው በኋላ ሁለት እግሮቻቸውና የቀኝ እጃቸው አልታዘዝ አላቸው… የግራ እጃቸው ብቻ ነበር የሚሰራው፡፡
በቃ እልጋ ላይ ዋሉ ሰው ደግፎ ካላነሳቸው በስተቀር ከአልጋቸውም መነሳት አይችሉም
ነበር፡፡
የሰፈሩ ሰው ደግ ነው እየተቀያየረ እማማን ለዘጠኝ ዓመታት አስታመመ፡፡ ቤታቸው
ሰው አይጠፋም፣ ከጧት እስከማታ የእማማ ቤት አደባባይ ነበር፤ መንደርተኛው ከልጅ እስከአዋቂ እማማን እየረዳ እግረመንገዱን ቤታቸውን መዋያ መቀጣጠሪያው አደረገው፡፡እማማ ትራሳቸውን ደገፍ ብለው ወጣቶቹ ሲጫወቱ እያዩ፣ አዋቂዎቹ ሲያጫውቷቸው እየተጫወቱ (እንደዛም ሆነው ጨዋታቸው ለጉድ ነበር ) ዘጠኝ ዓመታት አለፉ ።
እንድ ቅዳሜ ቀን ከሰዓት አምስት የምንሆን የሰፈር ልጆች ሰብሰብ ብለን እማማ ቤት ካርታ እንጫዎታለን ፡፡ ድንገት ዓይኔ እማማ ላይ ሲያርፍ የቤቱ ጣራ ላይ ባለች ሽንቁር የገባች ጨረር የብርሃን ዘነጓን ዘርግታ እማማ ጠይም ቆዳ ላይ የቀኝ ግማሽ ከንፈራቸውና የአፍንጫቸውን ጫፍ ያካለለች የብርሃን እንጎቻ ሰርታ ተመለከትኩ፡፡ አንዴ የጣራውን ሽንቁር አንዴ እማማ ፊት ላይ ያረፈውን ክብ ጨረር እያየሁ “ይሄ ሽንቁር ዝናብ ሲዘንብ
አልጋቸው ላይ ውሃ ያንጠባጥብባቸው ይሆን? ብዬ አሰብኩ፤ ጣራውን በሙሉ ስመለከተው ጥላሸት ሸፍኖታል፡፡ የጣራ ከዳኑ ቆርቆሮ እዚያና እዚህ ተበሳስቶ ጥቃቅን የብርሃን ነጠብጣቦቹ ጥቁር ሰማይ ላይ የተዘሩ ከዋከብት መስለዋል ።
ጓደኞቼ ጋር ተያይዘን ስንወጣ “ ለምን የእማማን ጣራ አናድሰላቸውም - አይታችሁታል? ጨረር ሁሉ ያስገባባቸዋልኮ” አልኳቸው… እኔም ሳስብ ነበር… እኔም… እያሉ በየአፋቸው ተንጫጩ፡፡ እንዲህ ነበር የተጀመረው፡፡ ለአንድ ሳምንት ቤት ለቤት እየዞርን ብር አሰባሰብን፤ ጎረቤቱ ሁሉ ደስ እያለው ካሰብነው በላይ ብር አዋጣ፡፡ እንደውም
አንዳንዶቹ ለራሳቸው ጉዳይ ገዝተውት ከተረፋቸው ማገርና ኣውራጅ እየቀነሱ ውሰዱ
አሉን ፡ ግርማቸው የሰፈራችን እናፂ ስራውን በነፃ ሊሰራ ቃል ገባልን ደግሞ ለማማ ብር ልቀበል እንዴ!?” ብሎ ::
በሳምንቱ እማማን ለማስደነቅ በማሰብ ሳንነግራቸው ቤታቸውን ለማደስ ወሰንንና አልፎ
አልፎ እንደምናደርገው አንድ ሁለት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እማማ ሞቱ !!
ትላንት ልክ ፀሐይ ስትጠልቅ፤ እማማ ይችን ዓለም ተሰናበቱ !
ዘጠኝ ዓመት ሙሉ ከአልጋ ወርደው የማያውቁት ሚስኪን ሴት፣ የሰፈሩን ሰው ሁሉ እንዳኮረፉ ሞቱ። ዘጠኝ ዓመት አስታመን፣ እንደ እናት ተንከባክበን፣ ባለቀ ሰዓት ረግመውን ሞቱ” እያለ የሰፈሩ ሰው በሙሉ አዘነ: አፍ አውጥተው አይናገሩት እንጅ ያስረገምከን አንተ ነህ” የሚል ወቀሳቸውን ከእያንዳንዳቸው ዓይን ላይ እይቻለሁ፡፡እኔም ምነው በቀረብኝ ብዬ በውስጤ ስብሰለሰል ሳምንት አለፈኝ፡፡ የሆነ ሆኖ እማማ
ላይመለሱ ከነኩርፊያቸው አሸለቡ፡፡ ለነገሩ ኩርፊያ ይሁን ሐዘን ማንም አልገባውም:
በኩርፊያና በሐዘን መሃል ያለው ልዩነት ምንድነው? ምንስ ነው በቁጣና የኩርፊያ
መካከል ያለው መስመር? …መዝገበ ቃላት ቃላትን እንጅ ስሜትን አይፈታም፡፡ እማማ፡
በምናውቃቸው ቃላት የገለፅነው የማናውቀው ስሜት ውስጥ የነበሩ ይመስለኛል፡፡ የሕይወት ታሪካቸው ሲነበብ በደፈናው “የሁላችንም እናት ነበሩ” ከሚል የወል ምስጋና ውጭ እምብዛም የተዘረዘረ ነገር አልነበረም:: አስክሬናቸው በአራት የሰፈራችን ወንዶች ትስሻ ላይ ተቀምጦ በቀባሪው አጀብ በቀስታ ወደ መቃብር ቤቱ ጓሮ ሲጓዝ እእምሮዬ ወደትዝታው የኋሊት ነጎደ ፡፡
የዛሬን አያድርገውና ከሊቅ እስከ ደቂቅ መዋያችን እማማ ቤት ነበር፡፡ የእማማ ቤት እንደው ቤት ሆነ እንጅ ነገረስራው ድድ ማስጫ የሚሉት ዓይነት ነበር፣ ሕፃናቱ እማማ ቤት በር ላይ እቃቃቸውን ሲደረድሩና ሲያፈርሱ፣ የእቃቃ ሰርግ ሲደግሱና
ሲጋቡ፡ወጣቶቹ ተሰብስበን ካርታና ዳማ ስንጫዎት፡ ስለሴት ስናወራና ስናውካካ እንውላለን እሁድ እሁድ የሰፈሩ እድር ዳኞች እና የዕቁብ ገንዘብ ሰብሳቢዎች እዚያው እማማ ቤት ተሰብስበው ሲነታረኩ ያረፍዳሉ፤ ያ አንድ ክፍል የቀበሌ ቤት ሁል ጊዜ ከጧት እስከ ማታ በሩ ክፍት ነበር።
በዛ ዕድሜ እንደ እማማ ዓይነት ረዥም እና ቆንጆ ሴት አይቸ አላውቅም፤ በድህነት ተጎሳቁለው እንኳን ጥርት ያለ ጠይም ቆዳቸውና ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት ፀጉራቸው አንዳች ሞገስ ነበረው ስለ ረዥም ቁመት ሲወራ ምሳሌ ነበሩ እንደ እማማ ዠርጋዳ ይባላል፡፡ ዠርጋዳ ነበሩ፤ ሲራመዱ የሚንሳፈፉ የሚመስሉ፡፡ በስተኋላ ዘመናቸው እርጅና ተጭኗቸው፣ ትንሽ ከወገባቸው ጎበጥ ብለው እንኳ በቁመት የሚስተካከላቸው
እልነበረም፡፡ ባልም ልጅም አልነበራቸውም፡፡ መተዳደሪያችው ሰርግና ድግስ ሲኖር ወጥ
በመስራት ነበር፤ ታዲያ ወጥ ሳይቀምሱ በሽታው የሚያውቁ ባለሙያ ናቸው ይባላል።
ሴት ልጅ የወጥ ማማስያ ከላሰች ምኑን ሴት ሆነች ኤዲያ !?” ይላሉ፤ውጥ ሲቀመስ ሲያዩ
እይወዱም:
እማማ ለምን ባል አያገቡም? ስንላችው፣
“በልኬ ወንድ አጣሁ፤ ጨርሶ ኩርፋድ አጎንብሸ ላግባ እንዴ…? ይሉና ይስቃሉ፤ ጨዋታ
እዋቂ ናቸው :
ፀ
ታዲያ ዓመቱን ሙሉ ማድቤት ለማድቤት ከርመው ለጥምቀት ጽዓል ፀጉራቸውን ተሰርተው፣ሰፊ ባለባንዲራ፣ ጥለቱ ጉልበታቸው የሚደርስ ያበሻ ቀሚሳቸውን ይለብሱና፣ በወገባቸዉ ላይ ሶስት አራት ዙር ተጠምጥሞ ጫፉ ወደታች የሚንዘረፈፍ መቀነታቸውን ሸብ አድርገው፣ ክብ ሰርተው የሚጨፍሩ (እሳቸው “የአገሬ ሰዎች የሚሏቸው) ወንዶች መኻል ገብተው ምንጃርኛ የሚባል ዘፈን እያወራረዱ ጭፈራቸውን ያስነኩታል:እማማን ለማየት የማይመጣ ሰው የለም እማማ መጡ ክፈቱላቸውም ይባላል … ክቡ የሰው ቀለበት በመጡበት በኩል ተከፍቶ ይገባሉ… የታወቁ ናቸው !
ቸብ ቸብ ቸብ ሲዴረግ እማማ እጃቸውን ከፍ አድርገው …
“የምንጃር ልጅ …ሽቅርቅር ብለሺ ነይ ነይ ዙረሺ
ይላሉ፣
የከበበው ህዝብ ይቀበላቸዋል፤ ሕዝቡ ድንገት ለጥምቀት የተሰበሰበ ሳይሆን አብሮ ግጥምና ዜማ ሲያጠና የከረመ ነበር የሚመስለው!
ኢሄ የጀግናው አገር
.
እዛው ምንጃር …
ወረዶች ሸንኮራ …
ስንዴ ልትበላ፣
ወረደች ምንጃር ….
የጤፍ አገር፤
ተይ አብሪው ኩራዙን …
ሳትፈጅው ጎዙን፤
“ያዝ እንግዲህ!” ብለው በዛ ቁመት ድንገት ወደላይ እየዘለሉ ሲመለሱ በፀጉራቸው
የግዜርን ዘርፋፋ ቀሚስ ነክተው የሚመለሱ ነበር የሚመስሉት! ጭብጨባው፣ ጩኸቱ፣ሳቁ ይደምቃል ጎን ለጎን የተደረደሩ ጨፋሪዎች በከበበው ሰው ጭብጨባ ፊትም ልክ
በአንድ ላይ ሸብረክ ሸብረክ… ሸብረክ እያሉ ወደፊት ወደኋላ እተራመዱ ሲጨፍሩ
የተለየ ስሜት ነበረው፡፡
እዛ ማዶ፣
አሃ
ከተራራው!"
አሃ.!
ዓይኑ ነው ወይ፤
እሃ፣
የሚያበራው፧ - የሰሌን ባርኔጣ በቀኝ እጃቸው የያዙ ጨፋሪ ወንዶች በአንድ ላይ ባርኔጣቸውን ከፍና ዝቅ እያደረጉ ሲጨፍሩ አቧራው ይጨሳል …እማማ እንደዛ ነበሩ፡፡
በሰፈሩ ሰው ዘንድ እማማ የሚለው ቃል የወል ስምነቱ ቀርቶ የዚቹ ሴትዮ መጠሪያ ከሆነ ዘመን የለውም፡፡ ሰፈራችን ውስጥ የሚኖሩ ሰዕድሜ የገፉ ባልቴቶች ሁሉ እማማ ከሚለው ቀጥሎ ስማቸው ይጠራል፡፡ እማማ ተዋሱ ፡እማማ ዮሃና፣ እማማ ብርነሽ እማማ ግን እማማ ብቻ! የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ታዲያ ለማኅበር ድፎ ደፍተው ማድቤት ጉድ ጉድ ሲሉ ራሳቸውን ስተው እሳት ላይ ወደቁ፣ እሳቱ ግራ ክንዳቸውና በግራ
በኩል ያለ የራሳቸው ፀጉር ክፉኛ ተቃጠለ የግራ ጆሯቸውም በከፊል በእሳቱ ተጎድቶ ነበር፡፡ ያ የተረገመ አደገ የእማማ ጠይም ፊት ላይ በግራ በኩል ለማየት የሚያስፈራ የእሳት ጠባሳ ትቶባቸው አለፈ። ይሄም ባልከፋ ነበር፤ከአደጋው በኋላ ሁለት እግሮቻቸውና የቀኝ እጃቸው አልታዘዝ አላቸው… የግራ እጃቸው ብቻ ነበር የሚሰራው፡፡
በቃ እልጋ ላይ ዋሉ ሰው ደግፎ ካላነሳቸው በስተቀር ከአልጋቸውም መነሳት አይችሉም
ነበር፡፡
የሰፈሩ ሰው ደግ ነው እየተቀያየረ እማማን ለዘጠኝ ዓመታት አስታመመ፡፡ ቤታቸው
ሰው አይጠፋም፣ ከጧት እስከማታ የእማማ ቤት አደባባይ ነበር፤ መንደርተኛው ከልጅ እስከአዋቂ እማማን እየረዳ እግረመንገዱን ቤታቸውን መዋያ መቀጣጠሪያው አደረገው፡፡እማማ ትራሳቸውን ደገፍ ብለው ወጣቶቹ ሲጫወቱ እያዩ፣ አዋቂዎቹ ሲያጫውቷቸው እየተጫወቱ (እንደዛም ሆነው ጨዋታቸው ለጉድ ነበር ) ዘጠኝ ዓመታት አለፉ ።
እንድ ቅዳሜ ቀን ከሰዓት አምስት የምንሆን የሰፈር ልጆች ሰብሰብ ብለን እማማ ቤት ካርታ እንጫዎታለን ፡፡ ድንገት ዓይኔ እማማ ላይ ሲያርፍ የቤቱ ጣራ ላይ ባለች ሽንቁር የገባች ጨረር የብርሃን ዘነጓን ዘርግታ እማማ ጠይም ቆዳ ላይ የቀኝ ግማሽ ከንፈራቸውና የአፍንጫቸውን ጫፍ ያካለለች የብርሃን እንጎቻ ሰርታ ተመለከትኩ፡፡ አንዴ የጣራውን ሽንቁር አንዴ እማማ ፊት ላይ ያረፈውን ክብ ጨረር እያየሁ “ይሄ ሽንቁር ዝናብ ሲዘንብ
አልጋቸው ላይ ውሃ ያንጠባጥብባቸው ይሆን? ብዬ አሰብኩ፤ ጣራውን በሙሉ ስመለከተው ጥላሸት ሸፍኖታል፡፡ የጣራ ከዳኑ ቆርቆሮ እዚያና እዚህ ተበሳስቶ ጥቃቅን የብርሃን ነጠብጣቦቹ ጥቁር ሰማይ ላይ የተዘሩ ከዋከብት መስለዋል ።
ጓደኞቼ ጋር ተያይዘን ስንወጣ “ ለምን የእማማን ጣራ አናድሰላቸውም - አይታችሁታል? ጨረር ሁሉ ያስገባባቸዋልኮ” አልኳቸው… እኔም ሳስብ ነበር… እኔም… እያሉ በየአፋቸው ተንጫጩ፡፡ እንዲህ ነበር የተጀመረው፡፡ ለአንድ ሳምንት ቤት ለቤት እየዞርን ብር አሰባሰብን፤ ጎረቤቱ ሁሉ ደስ እያለው ካሰብነው በላይ ብር አዋጣ፡፡ እንደውም
አንዳንዶቹ ለራሳቸው ጉዳይ ገዝተውት ከተረፋቸው ማገርና ኣውራጅ እየቀነሱ ውሰዱ
አሉን ፡ ግርማቸው የሰፈራችን እናፂ ስራውን በነፃ ሊሰራ ቃል ገባልን ደግሞ ለማማ ብር ልቀበል እንዴ!?” ብሎ ::
በሳምንቱ እማማን ለማስደነቅ በማሰብ ሳንነግራቸው ቤታቸውን ለማደስ ወሰንንና አልፎ
አልፎ እንደምናደርገው አንድ ሁለት
👍1
ሴቶች በጧት ሰፈራችን ወዳለው መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን እንዲወስዷቸው አደረግን፤አንዳንዴ እንደዛ እናደርግ ነበር ቤተክርስቲያን እንወስዳቸውና እዛው ሲጸበሉና ጸሎት ሊያደርሱ ውለው ማታ እንመልሳቸዋለን፤ የዛን ቀንም እማማ እዛው ዋሉ እኛም ተባብረን የቤታቸውን ጣራ ከማደስ አልፎ ምን የመሰለ ነጭ የ ማዳበሪያ ኮርኒስ ሰራንላቸው፡፡ ቤቱን አጸዳድተን ደጅ ፀሐይ ላይ የዋለ አልጋቸውን አስገባብተን ካነጠፍን በኋላ የሰፈር ሴቶች ቡና አፍልተው በድምቀት እማማን ተቀበልናቸው፤ እማማ እቤት እንደገቡና አልጋቸው ላይ እንዳረፉ ወደጣራው ባለማመን እየተመለከቱ፣ ዓይኔ ነው… ወይስ ያችን ሽንቁር ደፍናችኋታል!?” ብለው ጠየቁ። አጠያየቃቸው
ከደስታም ይሁን ምስጋና ይልቅ ወደ ቅሬታ ያመዘነ ነበር፡፡የተደረገውን ሁሉ አንድ በአንድ ነገር ናቸው፡፡ ቀጥሞና ሲያዳምጡን ቆዩና ዓይናቸውን ነጩ ኮርኒስ ላይ ሲያንከራትቱ ቆይተው ፊታቸው ቅጭም እንዳለ፣ “ደህና!” አሉ: ከዚች ቃል ውጭ ምንም አልተናገሩም፤ በዛው እንቅልፍ ወሰዳቸው። መቼም ሰው የፈለገ ለነፍሱ ቢሰራ በጎ ስራው ምስጋና መሻቱ አይቀርምና በዚህ የእማማ ዝምታ ቅሬታ ተሰምቶኝ ነበር፡፡ጓደኞቸም እንደዛው፡፡
በቀጣዩ ቀን ጧት አንድ የሰፈራችን ልጅ ሲሮጥ እቤት መጣና እማማ እያለቀሱ የሰፈሩ
ሰው ሁሉ ተሰብስቦ እያባበላቸው ነው አለኝ፡፡
ምነው አመማቸው እንዴ?”
እንጃ! ለምን የጣራውን ሽንቁር ዴፈናችሁብኝ? ብለው ነው እሉ ደነገጥኩ::
ምን ? ከምርህ ነው?” አልኩት እየቀለደ መስሎኝ ነበር::
ከምሬ ነው! እንደዛ አሉ እየተባለ ነው።
ተየይዘን እማማ ቤት ስንደርስ የሰፈሩ ሰው ቤቱን ሞልቶ እማማ ይጮኻሉ፣
✨ነገ ያልቃል✨
#UNMUTE #UNMUTE # UNMUTE
አሁንም #UNMUTE👇 ሰምታችኋል።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ከደስታም ይሁን ምስጋና ይልቅ ወደ ቅሬታ ያመዘነ ነበር፡፡የተደረገውን ሁሉ አንድ በአንድ ነገር ናቸው፡፡ ቀጥሞና ሲያዳምጡን ቆዩና ዓይናቸውን ነጩ ኮርኒስ ላይ ሲያንከራትቱ ቆይተው ፊታቸው ቅጭም እንዳለ፣ “ደህና!” አሉ: ከዚች ቃል ውጭ ምንም አልተናገሩም፤ በዛው እንቅልፍ ወሰዳቸው። መቼም ሰው የፈለገ ለነፍሱ ቢሰራ በጎ ስራው ምስጋና መሻቱ አይቀርምና በዚህ የእማማ ዝምታ ቅሬታ ተሰምቶኝ ነበር፡፡ጓደኞቸም እንደዛው፡፡
በቀጣዩ ቀን ጧት አንድ የሰፈራችን ልጅ ሲሮጥ እቤት መጣና እማማ እያለቀሱ የሰፈሩ
ሰው ሁሉ ተሰብስቦ እያባበላቸው ነው አለኝ፡፡
ምነው አመማቸው እንዴ?”
እንጃ! ለምን የጣራውን ሽንቁር ዴፈናችሁብኝ? ብለው ነው እሉ ደነገጥኩ::
ምን ? ከምርህ ነው?” አልኩት እየቀለደ መስሎኝ ነበር::
ከምሬ ነው! እንደዛ አሉ እየተባለ ነው።
ተየይዘን እማማ ቤት ስንደርስ የሰፈሩ ሰው ቤቱን ሞልቶ እማማ ይጮኻሉ፣
✨ነገ ያልቃል✨
#UNMUTE #UNMUTE # UNMUTE
አሁንም #UNMUTE👇 ሰምታችኋል።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ከዕለታት_ስምንት_ቀን (የሳምንት ፍቅር)
ከዕለታት አንድ ቀን፡-
እኔና ልጅቷ - ገና እንደተያየን
(ተዋደድን መሰል)
በጥቅሻ ተግባብተን - ስልክ ተቀያየርን፤
ከዕለታት ሁለት ቀን
ተቀጣጠርንና - ስልክ ተደዋውለን
ሻይ ቡና ልንል - ካፌ ውስጥ ተገኘን፤
ከዕለታት ሶስት ቀን
(እንደተገናኘን)
ብዙ ሳናወራ - ትንፋሽ ተቀያየርን
አንሶላ ተጋፈፍን፡፡
ከዕለታት አራት ቀን
ከዕለታት አምስት ቀን
ከዕለታት ስድስት ቀን
እየተጠራራን
ትንሽ እያወራን
ብዙ ፍቅር ሰራን፡፡
ከዕለታት ሰባት ቀን
(አንሶላ ውስጥ ሆነን)
“አንተ ማነህ?” አለች -
አንቺስ ማነሽ?” አልኳት
እሷን ነገረችኝ -
እኔንም ነገርኳት፤
ከዕለታት ስምንት ቀን
እኔም አልጠራኋት - እሷም አልደወለች
በሰባት ቀን ውሎ - ፍቅራችን አለቀች፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን፡-
እኔና ልጅቷ - ገና እንደተያየን
(ተዋደድን መሰል)
በጥቅሻ ተግባብተን - ስልክ ተቀያየርን፤
ከዕለታት ሁለት ቀን
ተቀጣጠርንና - ስልክ ተደዋውለን
ሻይ ቡና ልንል - ካፌ ውስጥ ተገኘን፤
ከዕለታት ሶስት ቀን
(እንደተገናኘን)
ብዙ ሳናወራ - ትንፋሽ ተቀያየርን
አንሶላ ተጋፈፍን፡፡
ከዕለታት አራት ቀን
ከዕለታት አምስት ቀን
ከዕለታት ስድስት ቀን
እየተጠራራን
ትንሽ እያወራን
ብዙ ፍቅር ሰራን፡፡
ከዕለታት ሰባት ቀን
(አንሶላ ውስጥ ሆነን)
“አንተ ማነህ?” አለች -
አንቺስ ማነሽ?” አልኳት
እሷን ነገረችኝ -
እኔንም ነገርኳት፤
ከዕለታት ስምንት ቀን
እኔም አልጠራኋት - እሷም አልደወለች
በሰባት ቀን ውሎ - ፍቅራችን አለቀች፡፡
#የዛሬ_ዘመን_ሰው
የዛሬ ዘመን ሰው ከድሮው ይቄላል
እራሱ እየዘራ - ራሱ ይነቅላል፡፡
የዛሬ ዘመን ሰው :-
የሰው ሰው ሳይፈልግ - ልክ እንደ ትላንቱ
ራሱ የወለደውን - አምጦ ካንጀቱ፣
በፌስታል ጠቅልሎ - ምንም ሳይፀየፍ
ከሔሮድስ ብሷል - ልጆች በመጨፍጨፍ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
የዛሬ ዘመን ሰው ከድሮው ይቄላል
እራሱ እየዘራ - ራሱ ይነቅላል፡፡
የዛሬ ዘመን ሰው :-
የሰው ሰው ሳይፈልግ - ልክ እንደ ትላንቱ
ራሱ የወለደውን - አምጦ ካንጀቱ፣
በፌስታል ጠቅልሎ - ምንም ሳይፀየፍ
ከሔሮድስ ብሷል - ልጆች በመጨፍጨፍ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
#የድንጋይ_ዘመን
በዚህ ድንጋይ ዘመን :-
መኪናችን ድንጋይ
ሹፌራችን ድንጋይ
ረዳቱ ድንጋይ
ተሳፋሪው ድንጋይ
ታኳችንም ድንጋይ ...
በሆነበት ጊዜ - ከጠፋ አሳቢ አካል
ድንጋይ በድንጋይ ላይ - ቢነሳ ይደንቃል!!??
በዚህ ድንጋይ ዘመን :-
መኪናችን ድንጋይ
ሹፌራችን ድንጋይ
ረዳቱ ድንጋይ
ተሳፋሪው ድንጋይ
ታኳችንም ድንጋይ ...
በሆነበት ጊዜ - ከጠፋ አሳቢ አካል
ድንጋይ በድንጋይ ላይ - ቢነሳ ይደንቃል!!??
👍1
#የእንባ_ቀብድ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እራገማለሁ አዎ! ተራግሜ ነው የምሞተው… ጨረሬን የነበረችበት መልሱ… ሕግ ታውቁ እነደሁ በህግ ፈጣሪን ትፈሩ እንደሆን በፈጠራችሁ ብያለሁ ጨሬን መልሱ አለዛ እራገማለሁ አዎ ተራግሜ ነው የምሞተው… እንዲሁ ተገንዤ የምሄድ እንዳይመስላችሁ ከነዘር ማንዘራችሁ የሚያጠፋ ርግማን ተራግሜ ነው የምሞተው
ጨረሬን የነበረችበት መልሱ!
አነጋገራቸው ሁሉ የሚያስፈራራ ነበር፡፡ ያች ገራገርና ፈግታ የማይለያቸው ሴትዮ ፊታቸው በቁጣ አስፈሪ ሆኖ ነበር፡፡ በዛ ላይ በየመሀሉ “ወዮዯዮ ጨረሬን” ብለው ይጮሃሉ ፡፡ከዘጠኝ ዓመት በፊት ለጥምቀት ሲዘፍኑ ካልሆነ፣ ከዛ ወዲህ እንዲህ ሲጮሁ አይቻቸው አላውቅም፡፡ የሰፈሩ ሰው ግራ ገብቶት እርስ በርስ ይተያያል ። ልክ እኔ ስደርስ ቤት ውስጥ የነበረው ሰው በሙሉ ዙሮ አየኝ፡፡ አስተያየታቸው አንተው ቤት እናድስ ብለህ ያመጣችውን ጣጣ አንተው እንደምታደርግ አድርግ የሚል ነበር ፡፡ ባወጣ ባወርድ የስራሁት ስህተት ኤልገባህ አለኝ፡፡ ምንድነው ጥፋቴ? የአንዲት አልጋ ላይ የዋሉ አቅመ ደካማ ቤት የተሸነቋቆረ አሮጌ ጣራ ሰፈሩን አስተባብሬ ማሳደሴ ማስመረቁ ቢቀር እንዴት ድፍን መንደር ያስረግማል …?
• ነግሪያለሁ እስተነገ ጨረሬን የነበረችበት ካልመለሳችሁ ውርድ ከራሴ ጨረሬን ነው የምፈልግ የእናት ጉርብትና ይቅርብኝ እህል ውሃችሁም ይቅርብኝ አልፈልግም
ርሃብ እንደሆነ ለምጀዋለሁ፥ ምን ያረገኛል …. ጨረሬን ብቻ ቦታዋ መልሱ፡፡ የሰፈር ልጆታ ጋር ተጠቃቅሰን ወጣንና ምን እንደምናደርግ መመካከር ጀመርን፡፡ ነገሩ እንግዳ ስለሆነብን
እንዳንዶቹ ትንሽ አእሞሯቸው ተቃውሶ ይሆናል 'ጠበል' እንውሰዳቸው አሉ አንዳንዶቹ ደግሞ እስቲ ይተኙና ነገ ጧት ምናልባት ይረሱት ይሆናል አሉ። ወደ እማማ ቤት ሰንመለስ ጩኸው ጩኸው እንቅልፍ ሸለብ አድርጓቸው ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን እማማ የወሰዱላቸውን ቁርስ አልበላም አሉ፡፡ እናቴ ሲጨንቃት በምሬት
ማትገባበት የሌለ ልጅ ምናለ አርፈህ ብትቀመጥ? ብላኝ እቤታቸው ሄደች፡፡ፈታቸውን አዞሩባት፡፡ ይሄን ነገር ስሰማ የምወዳቸውን ያህል በእማማ ተበሳጨሁ፡፡ ቀጥ ብዬ እናፂው ግርማቸው ቤት ሄድኩ፤ ከቤት ሊወጣ ሲል ነበር የደረስኩሰት፡፡ ገና ሲያየኝ እየሳቀ ደሞ የማንን ቤት ሥራ ልትለኝ ነው?” አለ።
አረ እባክህ ግራ የገባው ነገር ገጥሞናል”
“ምነው? እቤት ሰላም አይደሉም እንዴ!?”
አይ እቤት አይደለም …” ብዬ የሆነውን ሁሉ ነገርኩት። እንዲሁ ሽንቁሩ መደፈኑ ደስ
እንዳላላቸው ሲያዳምጠኝ ቆይቶ በሳቅ ፍርስ አለ!
ኧረ አያስቅም ግርማቸው! ሴትዮዋኮ እራገማለሁ እያሉ ነው።
እራገማለሁ …. ግርማቸው በጉዴ ወጣሁ !ያንን ሰሌን የመሰለ ጣሪያ ጥቀርሻውን አራግፈን ባደሰን ነው የምትረግመን? እና ምን ይሁን ነው አሁን?” ብሎ በእማማ ተቆጣ።
“ምናልባት ድፍንፍን ሲል ጨልሞባቸው ከሆነ የሆነ ሽንቁር ነገር ብትሰራላቸው "
“ምናሻኝ .ና እንሂድ ወንፊት ነው የማስመስልላት! “ ብሎ ወደ ቤቱ ገባና የአናጺ እቃውን ይዞ ተመለሰ ፡ ሆሆ ሃያ ዓመት አናጺ ሁኜ ስሰራ ጣራዩን ብሳልኝ ብሎ የመጣ ሰው ገጥሞኝም አያውቅ” እያለ ነበር በግርምት እማማ ቤት ስንደርስ ትክ ብለው አዩኝና እብራም አንተ ነህ አሉ ያስዴፈንከው አሉኝ፡ ወቀሳቸው ያስፈራ ነበር፡፡
ድንገት ሂጀ አልጋቸው ስር ተንበረከኩና እጃቸውን በሁለት እጄ ያዝኳቸው መዳፎቻቸው ከፉኛ ይቀዘቅዙ ነበር፡፡ እማማ ይቅርታ አድርጉልኝ እኔ ክረምት ሲመጣ አልጋዎት ላይ ዝናብ እንዳያፈስ አሰቤ ነው አሁን ግርማቸውን ጠርቸዋለሁ መልሶ እንደነበረ ይበሳልዎታል” አልኳቸው እማማ ድንገት እንደትንታ ቡፍ ብለው ሳቁና ትከሻቸው እየተንቀጠቀጠና እያሳሉ ከትከት ብለው ሳቁ፤ በውስጤ ይች ሴትዮ አዕምሯቸው ተናግቷል በቃ ብዬ አሰብኩ፡፡
እይ !አብርሃም ልታስበሳ አናጢ ይዘህ መጣህ…?”
“ምን ላድርግ? ተጨነቅንኮ እማማ!”
ግዴለም ተወው እሱንም ሥራ እታስፈታው …ግዴለም!” አሉ፡፡ ግርማቸው ተሰናብቶ
ከሄደ በኋላ አንዲት ዱካ ስቤ እማማ እልጋ አጠገብ ቁጭ አልኩ ። እማማ በጀርባቸው
እንደተኙ ወደ ኮርኒሱ አፍጥጠው ዝም ብለዋል፡፡ዝምታው ያስፈራ ነበር፡፡ ምን እንደምል፣ ምን እንደማደርግ ግራ ገብቶኝ እጄን ሳፍተለትል ድንገት ከሩቅ የሚሰማ በሚመስል ድምፅ
“ያች ጨረር ብለው ጀመሩ “ያች ቀጭን ጨረር …ጌታ የተቀበረበት መቃብር ውስጥ እንደተከሰቱት መልእክት ለኔ የምስራች ነበርች… መቼስ ያየህ እንሆነ አባቴ ከፉ ነበሩ. የከፉ ከፉ ነጋ ጠባ እናታችንን መቀጥቀጥ ነው ፣መስከር ነው …የትም ከርመው መምጣት ነው እንዲሁ በየመጠጥ ቤቱ ሲጣሉ በሚወዱት የመጠጥ ቤት አምባጓሮ ሞቱ፡፡ በኋላ እናታችን እርሻም ከስቡም ብቻዋን አልሆን ሲላት፣ አንዱን ከወደ ቆላ
የመጣ ባለጌ ሰው ነው ብላ አገባች፡፡ መቼስ ለመከራ ሲፈጥር አይለቅህ … የባሰ ነውረኛ ሁኖ ቁጭ አለ፡፡ ገና አንድ ፍሬ ልጅ ነኝ፣ እንጃ ይችን የዘውዲቱን ልጅ ባክል ነው (የጎረቤታችን ዘውዲቱ ልጅ ገና ዘጠኝ አመቷ ነው) ሰው ዞር ካለ ሳልፍም
ሳገድምም መጎንተል ነው ጭራሽ አንድ ቀን የላሞቹ በረት ስገባ ተከትሎ አነቀኝ የለበስኳትን ጥብቆዬን ሊያወልቅ ሲታገል ኡኡ…! ብዬ ስጮህበት እዛው እበቱ ላይ አንከባሎኝ ወጥቶ ሄደ፡፡ በገዛ ቤቴ ፈራሁ፤ የእናቴን ቀሚስ የሙጢኝ ብዬ በሄደችበት መከተል ሆነ፡፡ እሷ ሰው አግኝታ ሙታ ሂጅ አባትሽ ጋ ተጫዎች” ትለኛለች ..
በኋላ በሰበብ አስባቡ መግረፍ ሆነ ስራው ያመታቱ ያጨካከኑ ደሞ ተወው አታንሳው፡፡ የላሞቹ በረት የገባሁ እንደሆን ተከትሎ ከተፍ ነው፡፡ ወደ ጓሮ ለሽንት ዞር ያልኩ እንደሆነ እንደ ጥላ መከተል ነው፡፡ እንደው ነብሴ ተጨነቀች ፡፡ እናቴን አልነግር እንዲህ እንዳሁኑ ዘመን ልጅን ማን ይሰማል!? ገና ዘልዬ ሳልጠግብ ኑሮዬ ካሁን አሁን
መጣብኝ አነቀኝ ጭንቀት ሆነ፡፡ ገጠር ሽውታውም ኩፍኝም እያጣንም መቸም፣ አሞኝ
ጋደም ያልኩ እንደሆነ እናቴ ወጣ ካለች አትሂጅብኝ ለቅሶ ነው እየተንቀጠቀጥኩ
ተከትያት ደጅ ለደጅ ነው፡፡ ከመድኃኒያለምና ከሷ ሌላ ማን አለኝ? ታናናሽ እህቶቼና የሰፈሩ ውሪ ሁሉ ፈሪ ናት ከናቷ ቀሚስ ሥር አትወጣም” እያሉ መሳቂያ መዘበቻ አረጉኝ፡፡ ሲያመጣው ልክ የለው ይሄን ሆንኩ ሳትል እናታችን በሶስት ቀን በሽታ
ሞተችብን፡፡ ከሞቷም ካሟሟቷም በላይ ነብሴ መግቢያዋ መደበቂያዋ ጨነቃት እንዲህ እንዳይመስልህ የናቴ ልጅ ሐዘንተኛው እንኳን እግሩ ከቤት ሳይወጣ ቋንጣ እንዳየች ድመት ዓይኑ እኔ ላይ ነው፡፡
ሐዘኑም ምኑም ሲያበቃ ጎረቤት ቤት እየሄድኩ ብደበቅ አንጠልጥለው እያመጡ እቤቴ! እንዲቹ እንቅልፍ በዓይኔ ሳይዞር አድርና ቀን ወደእርሻው ሲሄድልኝ ቢመለሰ እንኳ ተኝቸ እንዳያገኘኝ እየፈራሁ… ከዚህ እንደጋሽ አለሙ ቤት የሚሆን ማሳው ውስጥ የተሰራ የእህል መክተቻ ጎተራ አለ… አርጅቶ እህል አይዝም እንዲሁ ቁሟል …ትልቅ ነው ያየህ እንደሆነ፣ ክዳኑን ገርበብ አርጌ እገባና መልሼ ከድኜ እዛው እተኛለሁ፡፡አሥር ጊዜ
እየመጣ ወንድሞቼን የት ሄደች? ሲል ይሰማኛል፣እንጃ ይሉታል፤ እየዛታ ይመለሳል፡፡
ድምጼን አጥፍቸ ዝም! ታዲያ በዛ ጨለማ የጭቃ ጎተራ ውስጥ ታፍኜ ለገመድ ማስገቢያ በተበሳው የጎተራው ሽንቁር በኩል የምትገባ ጨር ነበረች ከሰማይ ጀምሮ የተደበኩስት ጎተራ ድረስ ልትፈልገኝ የመጣች የእናቴ ነብስ ነው የምትመሰለኝ፡፡ ጨረሯ ፊቴ ላይ ስታረፍ እምባዬን የምታብስልኝ፡ የግዜር ጣት … በእጆቼ ስጫወትባት፣ እንደሰው በሹከሹክታ ሳወጋት እውላለሁ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እራገማለሁ አዎ! ተራግሜ ነው የምሞተው… ጨረሬን የነበረችበት መልሱ… ሕግ ታውቁ እነደሁ በህግ ፈጣሪን ትፈሩ እንደሆን በፈጠራችሁ ብያለሁ ጨሬን መልሱ አለዛ እራገማለሁ አዎ ተራግሜ ነው የምሞተው… እንዲሁ ተገንዤ የምሄድ እንዳይመስላችሁ ከነዘር ማንዘራችሁ የሚያጠፋ ርግማን ተራግሜ ነው የምሞተው
ጨረሬን የነበረችበት መልሱ!
አነጋገራቸው ሁሉ የሚያስፈራራ ነበር፡፡ ያች ገራገርና ፈግታ የማይለያቸው ሴትዮ ፊታቸው በቁጣ አስፈሪ ሆኖ ነበር፡፡ በዛ ላይ በየመሀሉ “ወዮዯዮ ጨረሬን” ብለው ይጮሃሉ ፡፡ከዘጠኝ ዓመት በፊት ለጥምቀት ሲዘፍኑ ካልሆነ፣ ከዛ ወዲህ እንዲህ ሲጮሁ አይቻቸው አላውቅም፡፡ የሰፈሩ ሰው ግራ ገብቶት እርስ በርስ ይተያያል ። ልክ እኔ ስደርስ ቤት ውስጥ የነበረው ሰው በሙሉ ዙሮ አየኝ፡፡ አስተያየታቸው አንተው ቤት እናድስ ብለህ ያመጣችውን ጣጣ አንተው እንደምታደርግ አድርግ የሚል ነበር ፡፡ ባወጣ ባወርድ የስራሁት ስህተት ኤልገባህ አለኝ፡፡ ምንድነው ጥፋቴ? የአንዲት አልጋ ላይ የዋሉ አቅመ ደካማ ቤት የተሸነቋቆረ አሮጌ ጣራ ሰፈሩን አስተባብሬ ማሳደሴ ማስመረቁ ቢቀር እንዴት ድፍን መንደር ያስረግማል …?
• ነግሪያለሁ እስተነገ ጨረሬን የነበረችበት ካልመለሳችሁ ውርድ ከራሴ ጨረሬን ነው የምፈልግ የእናት ጉርብትና ይቅርብኝ እህል ውሃችሁም ይቅርብኝ አልፈልግም
ርሃብ እንደሆነ ለምጀዋለሁ፥ ምን ያረገኛል …. ጨረሬን ብቻ ቦታዋ መልሱ፡፡ የሰፈር ልጆታ ጋር ተጠቃቅሰን ወጣንና ምን እንደምናደርግ መመካከር ጀመርን፡፡ ነገሩ እንግዳ ስለሆነብን
እንዳንዶቹ ትንሽ አእሞሯቸው ተቃውሶ ይሆናል 'ጠበል' እንውሰዳቸው አሉ አንዳንዶቹ ደግሞ እስቲ ይተኙና ነገ ጧት ምናልባት ይረሱት ይሆናል አሉ። ወደ እማማ ቤት ሰንመለስ ጩኸው ጩኸው እንቅልፍ ሸለብ አድርጓቸው ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን እማማ የወሰዱላቸውን ቁርስ አልበላም አሉ፡፡ እናቴ ሲጨንቃት በምሬት
ማትገባበት የሌለ ልጅ ምናለ አርፈህ ብትቀመጥ? ብላኝ እቤታቸው ሄደች፡፡ፈታቸውን አዞሩባት፡፡ ይሄን ነገር ስሰማ የምወዳቸውን ያህል በእማማ ተበሳጨሁ፡፡ ቀጥ ብዬ እናፂው ግርማቸው ቤት ሄድኩ፤ ከቤት ሊወጣ ሲል ነበር የደረስኩሰት፡፡ ገና ሲያየኝ እየሳቀ ደሞ የማንን ቤት ሥራ ልትለኝ ነው?” አለ።
አረ እባክህ ግራ የገባው ነገር ገጥሞናል”
“ምነው? እቤት ሰላም አይደሉም እንዴ!?”
አይ እቤት አይደለም …” ብዬ የሆነውን ሁሉ ነገርኩት። እንዲሁ ሽንቁሩ መደፈኑ ደስ
እንዳላላቸው ሲያዳምጠኝ ቆይቶ በሳቅ ፍርስ አለ!
ኧረ አያስቅም ግርማቸው! ሴትዮዋኮ እራገማለሁ እያሉ ነው።
እራገማለሁ …. ግርማቸው በጉዴ ወጣሁ !ያንን ሰሌን የመሰለ ጣሪያ ጥቀርሻውን አራግፈን ባደሰን ነው የምትረግመን? እና ምን ይሁን ነው አሁን?” ብሎ በእማማ ተቆጣ።
“ምናልባት ድፍንፍን ሲል ጨልሞባቸው ከሆነ የሆነ ሽንቁር ነገር ብትሰራላቸው "
“ምናሻኝ .ና እንሂድ ወንፊት ነው የማስመስልላት! “ ብሎ ወደ ቤቱ ገባና የአናጺ እቃውን ይዞ ተመለሰ ፡ ሆሆ ሃያ ዓመት አናጺ ሁኜ ስሰራ ጣራዩን ብሳልኝ ብሎ የመጣ ሰው ገጥሞኝም አያውቅ” እያለ ነበር በግርምት እማማ ቤት ስንደርስ ትክ ብለው አዩኝና እብራም አንተ ነህ አሉ ያስዴፈንከው አሉኝ፡ ወቀሳቸው ያስፈራ ነበር፡፡
ድንገት ሂጀ አልጋቸው ስር ተንበረከኩና እጃቸውን በሁለት እጄ ያዝኳቸው መዳፎቻቸው ከፉኛ ይቀዘቅዙ ነበር፡፡ እማማ ይቅርታ አድርጉልኝ እኔ ክረምት ሲመጣ አልጋዎት ላይ ዝናብ እንዳያፈስ አሰቤ ነው አሁን ግርማቸውን ጠርቸዋለሁ መልሶ እንደነበረ ይበሳልዎታል” አልኳቸው እማማ ድንገት እንደትንታ ቡፍ ብለው ሳቁና ትከሻቸው እየተንቀጠቀጠና እያሳሉ ከትከት ብለው ሳቁ፤ በውስጤ ይች ሴትዮ አዕምሯቸው ተናግቷል በቃ ብዬ አሰብኩ፡፡
እይ !አብርሃም ልታስበሳ አናጢ ይዘህ መጣህ…?”
“ምን ላድርግ? ተጨነቅንኮ እማማ!”
ግዴለም ተወው እሱንም ሥራ እታስፈታው …ግዴለም!” አሉ፡፡ ግርማቸው ተሰናብቶ
ከሄደ በኋላ አንዲት ዱካ ስቤ እማማ እልጋ አጠገብ ቁጭ አልኩ ። እማማ በጀርባቸው
እንደተኙ ወደ ኮርኒሱ አፍጥጠው ዝም ብለዋል፡፡ዝምታው ያስፈራ ነበር፡፡ ምን እንደምል፣ ምን እንደማደርግ ግራ ገብቶኝ እጄን ሳፍተለትል ድንገት ከሩቅ የሚሰማ በሚመስል ድምፅ
“ያች ጨረር ብለው ጀመሩ “ያች ቀጭን ጨረር …ጌታ የተቀበረበት መቃብር ውስጥ እንደተከሰቱት መልእክት ለኔ የምስራች ነበርች… መቼስ ያየህ እንሆነ አባቴ ከፉ ነበሩ. የከፉ ከፉ ነጋ ጠባ እናታችንን መቀጥቀጥ ነው ፣መስከር ነው …የትም ከርመው መምጣት ነው እንዲሁ በየመጠጥ ቤቱ ሲጣሉ በሚወዱት የመጠጥ ቤት አምባጓሮ ሞቱ፡፡ በኋላ እናታችን እርሻም ከስቡም ብቻዋን አልሆን ሲላት፣ አንዱን ከወደ ቆላ
የመጣ ባለጌ ሰው ነው ብላ አገባች፡፡ መቼስ ለመከራ ሲፈጥር አይለቅህ … የባሰ ነውረኛ ሁኖ ቁጭ አለ፡፡ ገና አንድ ፍሬ ልጅ ነኝ፣ እንጃ ይችን የዘውዲቱን ልጅ ባክል ነው (የጎረቤታችን ዘውዲቱ ልጅ ገና ዘጠኝ አመቷ ነው) ሰው ዞር ካለ ሳልፍም
ሳገድምም መጎንተል ነው ጭራሽ አንድ ቀን የላሞቹ በረት ስገባ ተከትሎ አነቀኝ የለበስኳትን ጥብቆዬን ሊያወልቅ ሲታገል ኡኡ…! ብዬ ስጮህበት እዛው እበቱ ላይ አንከባሎኝ ወጥቶ ሄደ፡፡ በገዛ ቤቴ ፈራሁ፤ የእናቴን ቀሚስ የሙጢኝ ብዬ በሄደችበት መከተል ሆነ፡፡ እሷ ሰው አግኝታ ሙታ ሂጅ አባትሽ ጋ ተጫዎች” ትለኛለች ..
በኋላ በሰበብ አስባቡ መግረፍ ሆነ ስራው ያመታቱ ያጨካከኑ ደሞ ተወው አታንሳው፡፡ የላሞቹ በረት የገባሁ እንደሆን ተከትሎ ከተፍ ነው፡፡ ወደ ጓሮ ለሽንት ዞር ያልኩ እንደሆነ እንደ ጥላ መከተል ነው፡፡ እንደው ነብሴ ተጨነቀች ፡፡ እናቴን አልነግር እንዲህ እንዳሁኑ ዘመን ልጅን ማን ይሰማል!? ገና ዘልዬ ሳልጠግብ ኑሮዬ ካሁን አሁን
መጣብኝ አነቀኝ ጭንቀት ሆነ፡፡ ገጠር ሽውታውም ኩፍኝም እያጣንም መቸም፣ አሞኝ
ጋደም ያልኩ እንደሆነ እናቴ ወጣ ካለች አትሂጅብኝ ለቅሶ ነው እየተንቀጠቀጥኩ
ተከትያት ደጅ ለደጅ ነው፡፡ ከመድኃኒያለምና ከሷ ሌላ ማን አለኝ? ታናናሽ እህቶቼና የሰፈሩ ውሪ ሁሉ ፈሪ ናት ከናቷ ቀሚስ ሥር አትወጣም” እያሉ መሳቂያ መዘበቻ አረጉኝ፡፡ ሲያመጣው ልክ የለው ይሄን ሆንኩ ሳትል እናታችን በሶስት ቀን በሽታ
ሞተችብን፡፡ ከሞቷም ካሟሟቷም በላይ ነብሴ መግቢያዋ መደበቂያዋ ጨነቃት እንዲህ እንዳይመስልህ የናቴ ልጅ ሐዘንተኛው እንኳን እግሩ ከቤት ሳይወጣ ቋንጣ እንዳየች ድመት ዓይኑ እኔ ላይ ነው፡፡
ሐዘኑም ምኑም ሲያበቃ ጎረቤት ቤት እየሄድኩ ብደበቅ አንጠልጥለው እያመጡ እቤቴ! እንዲቹ እንቅልፍ በዓይኔ ሳይዞር አድርና ቀን ወደእርሻው ሲሄድልኝ ቢመለሰ እንኳ ተኝቸ እንዳያገኘኝ እየፈራሁ… ከዚህ እንደጋሽ አለሙ ቤት የሚሆን ማሳው ውስጥ የተሰራ የእህል መክተቻ ጎተራ አለ… አርጅቶ እህል አይዝም እንዲሁ ቁሟል …ትልቅ ነው ያየህ እንደሆነ፣ ክዳኑን ገርበብ አርጌ እገባና መልሼ ከድኜ እዛው እተኛለሁ፡፡አሥር ጊዜ
እየመጣ ወንድሞቼን የት ሄደች? ሲል ይሰማኛል፣እንጃ ይሉታል፤ እየዛታ ይመለሳል፡፡
ድምጼን አጥፍቸ ዝም! ታዲያ በዛ ጨለማ የጭቃ ጎተራ ውስጥ ታፍኜ ለገመድ ማስገቢያ በተበሳው የጎተራው ሽንቁር በኩል የምትገባ ጨር ነበረች ከሰማይ ጀምሮ የተደበኩስት ጎተራ ድረስ ልትፈልገኝ የመጣች የእናቴ ነብስ ነው የምትመሰለኝ፡፡ ጨረሯ ፊቴ ላይ ስታረፍ እምባዬን የምታብስልኝ፡ የግዜር ጣት … በእጆቼ ስጫወትባት፣ እንደሰው በሹከሹክታ ሳወጋት እውላለሁ፡፡
👍1😁1
ጠሃይ ስትጠልቅ ጨረሯ ስትጠፋ ያ ክፉ ሰውዬ አረቄውን ተግቶ እየደነፋ ይመጣል፡፡ ጨረሯ ማታ የምትጠፋው ያንን ከፉ ሸሽታ
ይመስለኝ ነበር፡፡ ማንም ሳያየኝ ከጎተራዬ እወጣና እየተንቀጠቀጥኩ ገብቸ እንዱ ጥግ
ኩርምት ብዬ ካሁን አሁን መጣብኝ እያልኩ እንዳፈጠጥኩ አነጋለሁ፤ነገም ያው! ቶሎ
ነግቶልኝ ለወንድምና እህቶቸ የሚቀምሱትን ቂጣም ሆነ እንፍሮ አሰናድቼ፤ እኔም ሸንብራ
ቢጤ ቆልቼ ቋጥርና ማንም ሳያየኝ ወደዛ አሮጌ ጎተራ ገብቼ ሸንብራዬን እየቆረጠምኩ
እዛች ጨረር ጋር ብሶቴን በልጅ ነብሴ እንሾካሾኩ እውላለሁ፡ ጨለማ ለኔ ጭንቀት ነው ጀንበር ዞር ካለች ንብሴ' ትጨነቃለች እማማ ዝም ብለው ቆዩ ረዥም ዝምታ ታዲያ አንድ ሌሊት እዛቹ ጎጆ ጥግ ኵርምት እንዳልኩ …ኮቴ ሰማሁ በጨለማው ሊያቀኝ እያደባ ኑሯል፡፡ እንደው እንደፌንጣ ዘልዬ በጨለማው እንዴትም እንደከፈትኩት እንጃ በሩን በረገድኩና ልወጣ ስል ጥብቆዬን ቢያንቀኝ
ተተርትሮ እጁ ላይ ቀረ፣ ምናምኒት ሳልደርብ መለመላዬን በደረቀ ሌሊት ኡኡታዬን እያቀለጥኩ በረርኩ… ወደጎተራዬ ዘልየ ገብቸ ድምፄን አጠፉሁ፡፡ መቼስ ጨለማውን ያየ እንደሆን ዓይን ቢወጉት እይታይም … ሊምረኝ መሰለህ? የታባቷ ገባች?” እያለ መርዝ እንደቀመሰ ውሻ ማሳው ውስጥ ተቅበዘዘ ወደ ጎተራው ሲቀርብ ቅጠሉ
ሊንኮሸኮሽ ይሰማኛል እስካሁንም በበር የሰው ኮቴ ስሰማ እጨነቃለሁ፡፡ እራቁቴን ነኝ፣
ብርዱ ተወው ፍርሐቱ ያንዘፈዝፈኛል… ኋላ በዱላው ጎተራውን መታ መታ ሲያደረገው
ይኼ የከረመ አቧረው እንደ ዝናብ ወረደብኝ… እሳልኩ… አቶ መናጢ! ነይ አትወጭም
እያለ ክዳኑን ሊከፍት ሲጀምር … ጎረቤቶች እሪታን ሰምተው ኡሮ እየተጯጯሁ ሲመጡ ሰማሁ በዛ በለሊት ጨለማ ውስጥ በዛች የጎተራ ሸቁር… ከሰዎቹ ላምባዲና የመጣች ቀጭን ጨረር ራቁት ገላዬ ላይ ስታርፍ እንደ 'ጠሐይ የሞቀችኝ መሰለኝ
አቤት ደስታዋ አቤት! አቤት! አቤት! …አተረፉኝ፤ እሱንም በነጭ ለባሽ እያዳፉ ወደ ወሰዱበት እንጃ ልጆቹንም ወደ አክሰታቸን ዘንዳ ላኩን እዛው አደግን:ፍርሐቱ ግን ዛሬም ድረስ በርጋጊ አርጎኝ ቀረ! ቅጠል በተንኮሻኮሽ፣በበር የሚያልፍ ኮቴ በሰማሁ ቁጥር ብርክ ይይዘኛል እፈራለሁ ዘመኔ ያለቀው በፍርሐት ነው፡፡
ኑሮዬ እንደው መባከን ነው፤ እምብዛም ደስታ የለው… ከልጅነት እስከ እውቀት የሳኩባቸው፤ በደስታም የተጎበኘሁባቸው፣ ብርሃን ያየሁባቸው ቀናት ብቻ ነበሩ፡፡ ያ የሰባ ሰባት ርሃብ ስንቱን እንደ ቅጠል ያረገፈው መርገምት ማለፉን ያበሰረኝ
መንግሥትና ራዲዮኑ አይደለም፤ ብርሃን ነው ልጄ ብርሃን፡፡ ለሰው ብናገረው ውነት አይመስልም፡፡ ሰማዩ ሲደረቀበት የጥር ወር ፣ያለኝን አሟጥጫ ወዴት አባቴ ልሰደድ? እያልኩ ውጭ ላይ ከተፈጨበት ዓመት የሆነው የድንጋይ ወፍጮ ላይ ተቀምጨ ሳለቅስ ነበር፡፡ ጥር አሥር በአሥራ አንድ ማታ እንደ ነገ ብርሃነ ጥምቀቱ ሊከበር በዋዜማው ምሽት በዛ ኮከብ እንኳን በማይታይበት ጥቁር ሰማይ እንደ ፈትል ከር የቀጠነ ብርሃን ሰማዩን ለሁለት ሲከፍለው ደንግጬ በረገኩ፡፡ ያንን ሰማዩ ላይ ተዘርግቶ የጠፋ የብርሃን ዘንግ እንደገና አየዋለሁ ብዬ ባንጋጥጥ አልደገመውም ….በመነጋታው ምድሩ ላይ ጠፍቶ የኖረ ዝናብ ዶፍ ሆኖ ወረደ ከዝናቡም፣ ዝናቡ ካበቀለው ቡቃያም ይልቅ ያ የብርሃን ፀዳል ዓይኔ ላይ ዛሬም አለ .. ጥምቀት በመጣ ቁጥር ሰማዩ በብርሃን የተሞላ ይመስለኛል… የሕይዎቴን ትንሽ የምስራች እንዳቅሜ ልዘክር…አልጋ እስክይዝ ለጥምቀት ቀርቼ አላውቅም ነበር፡፡
ባልም እንደ አውሬ እያስፈራኝ ስሸሽ፣ ዘርም ሳላፈራ ኖርኩ አልከፋኝም! ቤቴን የምትሞላ ያች ጨረር የግዜር እጅ ነበረች … የግዜር ጣት !እዚህ ቤት ስንት ዓመቴ …?
ወደ ሃያ ዓመት ኖርኩ፤ ማስጠገን አቅቶኝ መሰለህ ልጄ? ዘጠኝ ዓመት ሙሉ አልጋ ላይ ስውል…የምትዳስሰኝ የግዜር ጣት እንዳትታጠፍ ብዬ.ያች ጨረሬን! ወስዳችኋት፡፡ ጨለማው እየቀረበ ነው፤የሰው እጅ በሰራት ብርሃን የማይገፈፍ ጨለማ እየመጣ ነው… ታውቆኛል ከእንግዲህ ብርሃን የለም፤ ተላመጅው ሲለኝ ነው መቃብሬን…?
እንቅልፍ ሸለብ አደረጋቸው…ብርድ ልብሳቸውን ደርቤላቸው ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ ከዛ ቀን በኋላ እማማ ማንንም አላናገሩም፤ በሳምንቱ ትላንት፣ ልክ ፀሐይ ስትጠልቅ እማማ ይችን ዓለም በሞት ተሰናበቱ !
✨ጨረስኩ✨
#UNMTE እያደረጋቹ አስተያየትም እየሰጣቹ ከቀን ቀን ቤቱም እየሳሳ ነው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባይገባኝም የተመቻቹ #Share እያደረጋቹ አንድ ሰው እስኪቀር እንቀጥላለን😔
ይመስለኝ ነበር፡፡ ማንም ሳያየኝ ከጎተራዬ እወጣና እየተንቀጠቀጥኩ ገብቸ እንዱ ጥግ
ኩርምት ብዬ ካሁን አሁን መጣብኝ እያልኩ እንዳፈጠጥኩ አነጋለሁ፤ነገም ያው! ቶሎ
ነግቶልኝ ለወንድምና እህቶቸ የሚቀምሱትን ቂጣም ሆነ እንፍሮ አሰናድቼ፤ እኔም ሸንብራ
ቢጤ ቆልቼ ቋጥርና ማንም ሳያየኝ ወደዛ አሮጌ ጎተራ ገብቼ ሸንብራዬን እየቆረጠምኩ
እዛች ጨረር ጋር ብሶቴን በልጅ ነብሴ እንሾካሾኩ እውላለሁ፡ ጨለማ ለኔ ጭንቀት ነው ጀንበር ዞር ካለች ንብሴ' ትጨነቃለች እማማ ዝም ብለው ቆዩ ረዥም ዝምታ ታዲያ አንድ ሌሊት እዛቹ ጎጆ ጥግ ኵርምት እንዳልኩ …ኮቴ ሰማሁ በጨለማው ሊያቀኝ እያደባ ኑሯል፡፡ እንደው እንደፌንጣ ዘልዬ በጨለማው እንዴትም እንደከፈትኩት እንጃ በሩን በረገድኩና ልወጣ ስል ጥብቆዬን ቢያንቀኝ
ተተርትሮ እጁ ላይ ቀረ፣ ምናምኒት ሳልደርብ መለመላዬን በደረቀ ሌሊት ኡኡታዬን እያቀለጥኩ በረርኩ… ወደጎተራዬ ዘልየ ገብቸ ድምፄን አጠፉሁ፡፡ መቼስ ጨለማውን ያየ እንደሆን ዓይን ቢወጉት እይታይም … ሊምረኝ መሰለህ? የታባቷ ገባች?” እያለ መርዝ እንደቀመሰ ውሻ ማሳው ውስጥ ተቅበዘዘ ወደ ጎተራው ሲቀርብ ቅጠሉ
ሊንኮሸኮሽ ይሰማኛል እስካሁንም በበር የሰው ኮቴ ስሰማ እጨነቃለሁ፡፡ እራቁቴን ነኝ፣
ብርዱ ተወው ፍርሐቱ ያንዘፈዝፈኛል… ኋላ በዱላው ጎተራውን መታ መታ ሲያደረገው
ይኼ የከረመ አቧረው እንደ ዝናብ ወረደብኝ… እሳልኩ… አቶ መናጢ! ነይ አትወጭም
እያለ ክዳኑን ሊከፍት ሲጀምር … ጎረቤቶች እሪታን ሰምተው ኡሮ እየተጯጯሁ ሲመጡ ሰማሁ በዛ በለሊት ጨለማ ውስጥ በዛች የጎተራ ሸቁር… ከሰዎቹ ላምባዲና የመጣች ቀጭን ጨረር ራቁት ገላዬ ላይ ስታርፍ እንደ 'ጠሐይ የሞቀችኝ መሰለኝ
አቤት ደስታዋ አቤት! አቤት! አቤት! …አተረፉኝ፤ እሱንም በነጭ ለባሽ እያዳፉ ወደ ወሰዱበት እንጃ ልጆቹንም ወደ አክሰታቸን ዘንዳ ላኩን እዛው አደግን:ፍርሐቱ ግን ዛሬም ድረስ በርጋጊ አርጎኝ ቀረ! ቅጠል በተንኮሻኮሽ፣በበር የሚያልፍ ኮቴ በሰማሁ ቁጥር ብርክ ይይዘኛል እፈራለሁ ዘመኔ ያለቀው በፍርሐት ነው፡፡
ኑሮዬ እንደው መባከን ነው፤ እምብዛም ደስታ የለው… ከልጅነት እስከ እውቀት የሳኩባቸው፤ በደስታም የተጎበኘሁባቸው፣ ብርሃን ያየሁባቸው ቀናት ብቻ ነበሩ፡፡ ያ የሰባ ሰባት ርሃብ ስንቱን እንደ ቅጠል ያረገፈው መርገምት ማለፉን ያበሰረኝ
መንግሥትና ራዲዮኑ አይደለም፤ ብርሃን ነው ልጄ ብርሃን፡፡ ለሰው ብናገረው ውነት አይመስልም፡፡ ሰማዩ ሲደረቀበት የጥር ወር ፣ያለኝን አሟጥጫ ወዴት አባቴ ልሰደድ? እያልኩ ውጭ ላይ ከተፈጨበት ዓመት የሆነው የድንጋይ ወፍጮ ላይ ተቀምጨ ሳለቅስ ነበር፡፡ ጥር አሥር በአሥራ አንድ ማታ እንደ ነገ ብርሃነ ጥምቀቱ ሊከበር በዋዜማው ምሽት በዛ ኮከብ እንኳን በማይታይበት ጥቁር ሰማይ እንደ ፈትል ከር የቀጠነ ብርሃን ሰማዩን ለሁለት ሲከፍለው ደንግጬ በረገኩ፡፡ ያንን ሰማዩ ላይ ተዘርግቶ የጠፋ የብርሃን ዘንግ እንደገና አየዋለሁ ብዬ ባንጋጥጥ አልደገመውም ….በመነጋታው ምድሩ ላይ ጠፍቶ የኖረ ዝናብ ዶፍ ሆኖ ወረደ ከዝናቡም፣ ዝናቡ ካበቀለው ቡቃያም ይልቅ ያ የብርሃን ፀዳል ዓይኔ ላይ ዛሬም አለ .. ጥምቀት በመጣ ቁጥር ሰማዩ በብርሃን የተሞላ ይመስለኛል… የሕይዎቴን ትንሽ የምስራች እንዳቅሜ ልዘክር…አልጋ እስክይዝ ለጥምቀት ቀርቼ አላውቅም ነበር፡፡
ባልም እንደ አውሬ እያስፈራኝ ስሸሽ፣ ዘርም ሳላፈራ ኖርኩ አልከፋኝም! ቤቴን የምትሞላ ያች ጨረር የግዜር እጅ ነበረች … የግዜር ጣት !እዚህ ቤት ስንት ዓመቴ …?
ወደ ሃያ ዓመት ኖርኩ፤ ማስጠገን አቅቶኝ መሰለህ ልጄ? ዘጠኝ ዓመት ሙሉ አልጋ ላይ ስውል…የምትዳስሰኝ የግዜር ጣት እንዳትታጠፍ ብዬ.ያች ጨረሬን! ወስዳችኋት፡፡ ጨለማው እየቀረበ ነው፤የሰው እጅ በሰራት ብርሃን የማይገፈፍ ጨለማ እየመጣ ነው… ታውቆኛል ከእንግዲህ ብርሃን የለም፤ ተላመጅው ሲለኝ ነው መቃብሬን…?
እንቅልፍ ሸለብ አደረጋቸው…ብርድ ልብሳቸውን ደርቤላቸው ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ ከዛ ቀን በኋላ እማማ ማንንም አላናገሩም፤ በሳምንቱ ትላንት፣ ልክ ፀሐይ ስትጠልቅ እማማ ይችን ዓለም በሞት ተሰናበቱ !
✨ጨረስኩ✨
#UNMTE እያደረጋቹ አስተያየትም እየሰጣቹ ከቀን ቀን ቤቱም እየሳሳ ነው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባይገባኝም የተመቻቹ #Share እያደረጋቹ አንድ ሰው እስኪቀር እንቀጥላለን😔
👍2
#ሰው_መሆን_ምንድን_ነው???
..እናልሽ ቆንጅቴ
የሆነ ዕለት ማታ
ገና አይኗ ያልበራ - የውሻ ቡችላ
ከእናቷ ተነጥቃ - መንገድ ዳር ተጥላ፣
ያውም በክረምቱ
ያውም በምሽቱ፣
እናቴን፣
ሙቀቴን፣
ህይወቴን እያለች
ቱቦ ስር ተኝታ - ታለቃቅሳለች፡፡
ምናልባት ሌሊቱን
ዝናብ ከዘነበ - ጎርፉ ይወስዳታል
ጎርፍ ካልወሰዳት
ራቱን ፍለጋ የወጣ ቀበሮ - ራት ያደርጋታል፡፡
ይህንን ስታይ - መኖር ይገርምሻል
ህይወት ግን ምንድን ነች?- ያፈላስፍሻል፡፡
ደግሞ በሌላ ቀን
አያቴ 'ሚሆኑ - እድሜ ጠገብ ባልቴት
በጠራራ ፀሐይ - ጥላ በሌለበት፣
ከአካላቸው ሚገዝፍ - የእንጨት ክምር አዝለው
ገዢ ይመኛሉ - ገንዘብ ተስፋ አድርገው፡፡
አንዲት ወጣት መጥታ - እየተቻኮለች
እንጨቱን ለመግዛት - ባልቴቷን ጠየቀች፤
“ስንት ነው?” ጠየቀች ወጣቷ
“ሃያ ብር” መለሱ አሮጊቷ፣
“ቀንሱልኝ ማዘር?”
“አስራ ስምንት አርጊው”
“አስራ አምስት ልውሰደው?”
“አላነሰም ልጄ?”
“ይህንም ማደርገው- ከምዞር ብዬ ነው!”
“በ...ይ እሽ ውሰጅው”::
ይታይሽ እንግዲህ
ሌሊቱን በሙሉ - የተጓዙበትን
መቼም ላይቃኑ - የጎበጡበትን፣
ከአራዊት ጋር ታግለው - ያመጡትን እንጨት
በአንድ ቢራ ዋጋ - አስራ አምስት ብር ሽጡት፡፡
አስራ አምስት ብር ብቻ!!!
አየሽ ያቺ ወጣት የ'ሷ ድካም እንጅ የባልቴቷ ኑሮ
አላስጨነቃትም
የምታወጣቸው አምስት ብሮች እንጅ - የአሮጊቷ ድካም
አላሳሰባትም፡፡
ይህንን ስታይ እንባ ያስወጣሻል
“መተዛዘን የታል?” ግራ ያጋባሻል፡፡
ትላንትና ደግሞ
በአንድ ቴሌቪዥን - ሰበር ዜና አይቼ
ሲያስታውከኝ አደርኩ - ከእንቅልፍ ተፋትቼ፤
ምን አየሁ መሰለሽ :-
አንድ የሰዎች ቡድን - ሰዎችን አግቶ
ሁሉንም በአንድ ላይ - ጠባብ ቤት ውስጥ ዘግቶ፣
እንደ በቆሎ እሸት - እያንከባለለ
ከነህይወታቸው - በእሳት አቃጠለ፡፡
በስመ አ..........ብ!!!
ይህንን ስታይ ህይወት ያስጠላሻል
የሰው ልጅ ምንድን ነው?' ያወዛግብሻል::
ታዲያ ግን አለሜ፤
ስንቱን ጉድ አይቼ፣
ስንቱን ጉድ ሰምቼ፣
በብዙ ቆስዬ፣
በብዙ ነድጄ፣
ነድጄ
ነድጄ........
አንቺን እንዳገኘሁ
ያስከፋኝን ሁሉ በአንዴ ረሳውና-
«ይህች ዓለም ጣፋጭ ነች - ቆንጆ ነች!› እላለሁ፡፡
እውነቴን ነው ምልሽ
አንቺን እንዳገኘሁ፡-
ባገባኋትና - አይኔን በአይኔ አይቼ
እስከፍፃሜየ - በኖርኩ ተደስቼ!
እያልኩ አመኛለሁ፡፡
ታዲያ ይህ ምኞቴ - ለኔም ይገርመኛል
'ሰው መሆን ምንድን ነው?” - ውስጤ ይጠይቀኛል፡፡
ምስኪኗን ቡችላ - በቆፈኑ ክረምት - ቱቦ ስር የጣሏት
ደካማዋን ባልቴት - ከእንጨት አሳንስው - ጣል ጣል ያረጓት፣
ስውን ሚያህል ፍጡር- ከነህይወታቸው - በእሳት ያጋዩዋቸው
እውነት ሰዎች ናቸው?
እኔ ራሴስ ብሆን?
ይህን ሁሉ ህመም - እያየሁ ያስቻለኝ
በምችለው መጠን - ርዳታ ፈላጊን - መርዳት የተሳነኝ
ጭራሽ ከአንቺ ጋራ - ሁሉን ረስቼ - መቦረቅ የሚያምረኝ
እውን እኔ ሰው ነኝ ??
ልጠይቅሽ እስኪ፡-
የምስኪኗን ጩኸት፣
የባልቴቷን ብሶት፣
የንፁሃንን ሞት፣
የሰውን ልጅ እክል፣
የምድርን ምስቅልቅል፣
አንቺ ካስረሳሺኝ
ጠቀምሽኝ?
ጎዳሽኝ?
ገደልሽኝ?
አዳንሽኝ?
መልስ እፈልጋለሁ
ሰው መሆን ምንድን ነው???
🔘መሉቀን ሰለሞን🔘
..እናልሽ ቆንጅቴ
የሆነ ዕለት ማታ
ገና አይኗ ያልበራ - የውሻ ቡችላ
ከእናቷ ተነጥቃ - መንገድ ዳር ተጥላ፣
ያውም በክረምቱ
ያውም በምሽቱ፣
እናቴን፣
ሙቀቴን፣
ህይወቴን እያለች
ቱቦ ስር ተኝታ - ታለቃቅሳለች፡፡
ምናልባት ሌሊቱን
ዝናብ ከዘነበ - ጎርፉ ይወስዳታል
ጎርፍ ካልወሰዳት
ራቱን ፍለጋ የወጣ ቀበሮ - ራት ያደርጋታል፡፡
ይህንን ስታይ - መኖር ይገርምሻል
ህይወት ግን ምንድን ነች?- ያፈላስፍሻል፡፡
ደግሞ በሌላ ቀን
አያቴ 'ሚሆኑ - እድሜ ጠገብ ባልቴት
በጠራራ ፀሐይ - ጥላ በሌለበት፣
ከአካላቸው ሚገዝፍ - የእንጨት ክምር አዝለው
ገዢ ይመኛሉ - ገንዘብ ተስፋ አድርገው፡፡
አንዲት ወጣት መጥታ - እየተቻኮለች
እንጨቱን ለመግዛት - ባልቴቷን ጠየቀች፤
“ስንት ነው?” ጠየቀች ወጣቷ
“ሃያ ብር” መለሱ አሮጊቷ፣
“ቀንሱልኝ ማዘር?”
“አስራ ስምንት አርጊው”
“አስራ አምስት ልውሰደው?”
“አላነሰም ልጄ?”
“ይህንም ማደርገው- ከምዞር ብዬ ነው!”
“በ...ይ እሽ ውሰጅው”::
ይታይሽ እንግዲህ
ሌሊቱን በሙሉ - የተጓዙበትን
መቼም ላይቃኑ - የጎበጡበትን፣
ከአራዊት ጋር ታግለው - ያመጡትን እንጨት
በአንድ ቢራ ዋጋ - አስራ አምስት ብር ሽጡት፡፡
አስራ አምስት ብር ብቻ!!!
አየሽ ያቺ ወጣት የ'ሷ ድካም እንጅ የባልቴቷ ኑሮ
አላስጨነቃትም
የምታወጣቸው አምስት ብሮች እንጅ - የአሮጊቷ ድካም
አላሳሰባትም፡፡
ይህንን ስታይ እንባ ያስወጣሻል
“መተዛዘን የታል?” ግራ ያጋባሻል፡፡
ትላንትና ደግሞ
በአንድ ቴሌቪዥን - ሰበር ዜና አይቼ
ሲያስታውከኝ አደርኩ - ከእንቅልፍ ተፋትቼ፤
ምን አየሁ መሰለሽ :-
አንድ የሰዎች ቡድን - ሰዎችን አግቶ
ሁሉንም በአንድ ላይ - ጠባብ ቤት ውስጥ ዘግቶ፣
እንደ በቆሎ እሸት - እያንከባለለ
ከነህይወታቸው - በእሳት አቃጠለ፡፡
በስመ አ..........ብ!!!
ይህንን ስታይ ህይወት ያስጠላሻል
የሰው ልጅ ምንድን ነው?' ያወዛግብሻል::
ታዲያ ግን አለሜ፤
ስንቱን ጉድ አይቼ፣
ስንቱን ጉድ ሰምቼ፣
በብዙ ቆስዬ፣
በብዙ ነድጄ፣
ነድጄ
ነድጄ........
አንቺን እንዳገኘሁ
ያስከፋኝን ሁሉ በአንዴ ረሳውና-
«ይህች ዓለም ጣፋጭ ነች - ቆንጆ ነች!› እላለሁ፡፡
እውነቴን ነው ምልሽ
አንቺን እንዳገኘሁ፡-
ባገባኋትና - አይኔን በአይኔ አይቼ
እስከፍፃሜየ - በኖርኩ ተደስቼ!
እያልኩ አመኛለሁ፡፡
ታዲያ ይህ ምኞቴ - ለኔም ይገርመኛል
'ሰው መሆን ምንድን ነው?” - ውስጤ ይጠይቀኛል፡፡
ምስኪኗን ቡችላ - በቆፈኑ ክረምት - ቱቦ ስር የጣሏት
ደካማዋን ባልቴት - ከእንጨት አሳንስው - ጣል ጣል ያረጓት፣
ስውን ሚያህል ፍጡር- ከነህይወታቸው - በእሳት ያጋዩዋቸው
እውነት ሰዎች ናቸው?
እኔ ራሴስ ብሆን?
ይህን ሁሉ ህመም - እያየሁ ያስቻለኝ
በምችለው መጠን - ርዳታ ፈላጊን - መርዳት የተሳነኝ
ጭራሽ ከአንቺ ጋራ - ሁሉን ረስቼ - መቦረቅ የሚያምረኝ
እውን እኔ ሰው ነኝ ??
ልጠይቅሽ እስኪ፡-
የምስኪኗን ጩኸት፣
የባልቴቷን ብሶት፣
የንፁሃንን ሞት፣
የሰውን ልጅ እክል፣
የምድርን ምስቅልቅል፣
አንቺ ካስረሳሺኝ
ጠቀምሽኝ?
ጎዳሽኝ?
ገደልሽኝ?
አዳንሽኝ?
መልስ እፈልጋለሁ
ሰው መሆን ምንድን ነው???
🔘መሉቀን ሰለሞን🔘
#አላምንም
ጓደኞቼ ቢያውቁ
እኔ እንደምወድሽ፣
አንቺ እንደማትጠይኝ
ግን እንደማትሆኚኝ
ላንቺ መንሰፍሰፌን
እንድተው መክነፌን፣
ሊያስረዱኝ ፈልገው
አዋዝተው ቀባብተው፡-
“ስማ የኛ ችኮ!
እሷ ማለት እኮ
አንተን ትወዳለች
ሌላም ትወዳለች
ሌላም ትወዳለች
ሌ ላ ም ትወዳለች........
ስለማትኖር ታምና
አትሆንህምና
ትቅርብህ!!” ቢሉኝም
ሰው ምቀኛ ነው - ሰዎችን አላምንም፡፡
(አቤት ሰው! አቤት ሰ.......ው
የሷን ወሬ ለኔ - መቶ ሚያላልሰው
ምን እንዳደርግ ነው?
ምንም ሳላኮርፋት
ምናለ ብወዳት
ምናለ ባፈቅራት?)
ነገሩን አልኩ እንጅ
ከሰዎች አብልጦ አይኔም ጠቁሞኛል
ስራሽን ነግሮኛል፡፡
ቢሆንም
ቢሆንም
“መጣሁ ጠብቅ” ብለሽ
ቶሎ ልትመለሽ፣
ልብሽ ከኔ ርቆ
ከሌላ ተዋውቆ፣
ሆነሽ የእምነት ደሐ - የፍቅር መሃይም
ባይኔ በብረቱ - ስትሳሚ ባይም፣
አይኔ ምቀኛ ነው - አይኔንም አላምንም፡፡
(አይኔን መች አጣሁት፡-
ሴቶችን ሁሉ - በአንች እያስመሰለ
የሌሎችን ኃጢያት - ለአንቺ እያሸከመ፣
ሌላው በተሳመ - በአንቺ እያላከከ
መጥፎ ምስል ልኮ - ልቤን እያወከ......
ሊያጣላኝ መሆኑን - አይኔን መች አጣሁት
አላምነውም ተውኩት፡፡)
እውነቱን ልንገርሽ ?
ስላንቺ ከሆነ
ጆሮየን አላምንም፣
አይኔንም አላምንም፣
ሰውንም አላምንም
ማንንም አላምንም፣
አላምንም፡፡
አላምንም።
አውነትን መጨፍለቅ - ከፍቅርሽ አይከብድም።
🔘ሙሉቀን ሰለሞን🔘
ጓደኞቼ ቢያውቁ
እኔ እንደምወድሽ፣
አንቺ እንደማትጠይኝ
ግን እንደማትሆኚኝ
ላንቺ መንሰፍሰፌን
እንድተው መክነፌን፣
ሊያስረዱኝ ፈልገው
አዋዝተው ቀባብተው፡-
“ስማ የኛ ችኮ!
እሷ ማለት እኮ
አንተን ትወዳለች
ሌላም ትወዳለች
ሌላም ትወዳለች
ሌ ላ ም ትወዳለች........
ስለማትኖር ታምና
አትሆንህምና
ትቅርብህ!!” ቢሉኝም
ሰው ምቀኛ ነው - ሰዎችን አላምንም፡፡
(አቤት ሰው! አቤት ሰ.......ው
የሷን ወሬ ለኔ - መቶ ሚያላልሰው
ምን እንዳደርግ ነው?
ምንም ሳላኮርፋት
ምናለ ብወዳት
ምናለ ባፈቅራት?)
ነገሩን አልኩ እንጅ
ከሰዎች አብልጦ አይኔም ጠቁሞኛል
ስራሽን ነግሮኛል፡፡
ቢሆንም
ቢሆንም
“መጣሁ ጠብቅ” ብለሽ
ቶሎ ልትመለሽ፣
ልብሽ ከኔ ርቆ
ከሌላ ተዋውቆ፣
ሆነሽ የእምነት ደሐ - የፍቅር መሃይም
ባይኔ በብረቱ - ስትሳሚ ባይም፣
አይኔ ምቀኛ ነው - አይኔንም አላምንም፡፡
(አይኔን መች አጣሁት፡-
ሴቶችን ሁሉ - በአንች እያስመሰለ
የሌሎችን ኃጢያት - ለአንቺ እያሸከመ፣
ሌላው በተሳመ - በአንቺ እያላከከ
መጥፎ ምስል ልኮ - ልቤን እያወከ......
ሊያጣላኝ መሆኑን - አይኔን መች አጣሁት
አላምነውም ተውኩት፡፡)
እውነቱን ልንገርሽ ?
ስላንቺ ከሆነ
ጆሮየን አላምንም፣
አይኔንም አላምንም፣
ሰውንም አላምንም
ማንንም አላምንም፣
አላምንም፡፡
አላምንም።
አውነትን መጨፍለቅ - ከፍቅርሽ አይከብድም።
🔘ሙሉቀን ሰለሞን🔘
#ምኗን_እንደወደድኩት?
አረማመዷ እንቅልፍ ነስቶኝ - ሌሊቱን ሙሉ እያለምኩት
ሐር መሳይ ጥቁር ጸጉሯ - ጠልፎ ሲጥለኝ እያየሁት
ምኗን እንደወደድኩት!?
እንደ በረዶ በነፁ - ጥርሶቿ እያሳሳችኝ
በአይኗ ጨረር እንዳልወጋ - አንገቴን እያስደፋችኝ
እንዴት ደስ እንዳለችኝ!?
አንገቷን ፣
የረዘመውን - ብስመው እንደሚያዞረኝ
ጡቶቿን፣
የሚዋጉትን - ብነካቸው እንደሚነዝረኝ
ገዳይ መሆኗን እያወኳት
እንዴት እንዳፈቀርኳት!?
ችቦ ማይሞላው ወገቧ - በልቶ ማያድር የመሰለ
ወ...ረ..ድ ሲሉ ዳሌዋ - ራስ ዳሽንን እያከለ
ምኗን እንደወደድኩት!?
ምኗን እንዳፈቀርኩት!???
አረማመዷ እንቅልፍ ነስቶኝ - ሌሊቱን ሙሉ እያለምኩት
ሐር መሳይ ጥቁር ጸጉሯ - ጠልፎ ሲጥለኝ እያየሁት
ምኗን እንደወደድኩት!?
እንደ በረዶ በነፁ - ጥርሶቿ እያሳሳችኝ
በአይኗ ጨረር እንዳልወጋ - አንገቴን እያስደፋችኝ
እንዴት ደስ እንዳለችኝ!?
አንገቷን ፣
የረዘመውን - ብስመው እንደሚያዞረኝ
ጡቶቿን፣
የሚዋጉትን - ብነካቸው እንደሚነዝረኝ
ገዳይ መሆኗን እያወኳት
እንዴት እንዳፈቀርኳት!?
ችቦ ማይሞላው ወገቧ - በልቶ ማያድር የመሰለ
ወ...ረ..ድ ሲሉ ዳሌዋ - ራስ ዳሽንን እያከለ
ምኗን እንደወደድኩት!?
ምኗን እንዳፈቀርኩት!???
#የከብቶች_አገር
አንዲት መንደር አለች - እጅጉን ጩኸታም
እረኛ የሌላት - ግን የከብቶች ሐብታም፡፡
ወጣ ገባ ምድሯ - በእንስሳት ተሞልቶ
አንድ የሚያደርጋቸው - 'ሚያግባባቸው ጠፍቶ፣
በሁሉም አቅጣጫ - በአራቱም ማዕዘን
ሲበረቱ ጩኸት - ሲደክሙ ማላዘን
እምቧ ...... ይላሉ ከብቶች
ያናፋሉ አህዮች !
ቢኺኺኺ
ሚያው
ውውውውው......
በጎች
ወሻዎች
በመንደሯ ያሉት የቤት እንስሳዎች ፣
በሚችሉት መጠን - በራሳቸው ዓለም
ሁሉም ይጮሃሉ - ማንም ዝም አላለም
በዚያች የከብት አገር
መጫ
ጮህ ብቻ እንጂ - መደማመጥ የለም!!
🔘መሉቀን ሰለሞን🔘
አንዲት መንደር አለች - እጅጉን ጩኸታም
እረኛ የሌላት - ግን የከብቶች ሐብታም፡፡
ወጣ ገባ ምድሯ - በእንስሳት ተሞልቶ
አንድ የሚያደርጋቸው - 'ሚያግባባቸው ጠፍቶ፣
በሁሉም አቅጣጫ - በአራቱም ማዕዘን
ሲበረቱ ጩኸት - ሲደክሙ ማላዘን
እምቧ ...... ይላሉ ከብቶች
ያናፋሉ አህዮች !
ቢኺኺኺ
ሚያው
ውውውውው......
በጎች
ወሻዎች
በመንደሯ ያሉት የቤት እንስሳዎች ፣
በሚችሉት መጠን - በራሳቸው ዓለም
ሁሉም ይጮሃሉ - ማንም ዝም አላለም
በዚያች የከብት አገር
መጫ
ጮህ ብቻ እንጂ - መደማመጥ የለም!!
🔘መሉቀን ሰለሞን🔘
#የት_ነበርኩ?
ፍቅረኛዬን ጠበኩት። አልመጣም፡፡ ወደ መዝናኛው የሚገባውን ሰው ሁሉ አያለሁ። አንዲት ቀጭን ሴት ከአንድ ወጣት
ጋር ገባች።
ምን ብሎ እንዳስደሰታት እንጃ የኮቱን እጅጌ ወደታች ስትስበው ከአንገቱ ጎንበስ አለላትና፤ “የኔ ቆንጆ!” ብላ አንገቷን
አጠማዛ ከንፈሩ ላይ ሳመችው።
የአፍላነቴን ጊዜ አስታወስኩ። በጭለማ ሊያውም በአንሶላ ውስጥ ካልሆነ ባደባባይ ከንፈር ተስሞ አይታወቅም ነበር።የትውልዱ ለውጥ ገረመኝ፡፡
ክንዷን በወገቡ ዙሪያ ለማድረግ ሞክራለች፤ አልተሳካላትም፡፡የወገቡን ሩብ ያክል እንኳን አላቀፈችውም ልዩነታቸው ገረመኝ እሱ የተራራ ጉማጅ የሚያክል ግድንግድ፣ እሷ በመዳፍ ውስጥ
ያለች ትንሽ አሳ የመሰለች ደቃቃ፡፡ ፍቅር የሚባለውን ነገር አመሰገንኩት፤ መጠንን፣ ቀለምን እና ዘርን የማይመርጥ የማያዳላ
ክቡር ነገር፡፡
ልጅቱ ያለማቋረጥ ትስቃለች። ድምጿ ከቃጭል የቀጠነና ስቅጥጥ የሚያደርግ ነው፡፡ መድረክ ላይ ያለች ይመስል ለሰው ሁሉ እንዲሰማ አድርጋ እየተወራጨች ስታወራ በአካባቢዋ መደማመጥ
የሚፈልግ ሰው እንዳለ ልብ ያለች አትመስልም፡፡
እንደተቀመጡ አስተናጋጇ ወደነርሱ ቀረብ አለች ። “አንድ ቀይ ወጥና አንድ አልጫ!” ብላ ጮኸች። የቤቱን ሰው ሁሉ ያዘዘች ነው የምትመስለው።
ዐይኔም ጆሮዬም ቀልቤም እነሱው ላይ
የሚያስደስትም፣ የሚያስጠላም ነገር እኩል ቀልብ መሳቡ ሁልጊዜም
ይገርመኛል፡፡ ሴቲቱ ከመገልፈጧ የተነሳ ሳቅ ውድድር ላይ እያላች የደከማት ትመስላለች። የምታደርገው ነገር ሁሉ ወዝ የለውም።
ትኩረቴ ሁሉ ወደ ጥንዶቹ ሆኖና ልቤ ተንጠልጥሎ እጠብቀው የነበረውን ፍቅረኛዬን በጥቂቱም ቢሆን እንድረሳው
ምክንያት ሆኑኝ፡፡ በዚህ አመሰገንኳቸው፡፡ ምክንያቱም ሁልጊዜ ፍቅረኛዬን ስጠብቅ ልቤ በአፍንጫዬ እስክትወጣ ድረስ ትዘላለች።አንድ ቀን እሱን በጉጉት ስጠብቅ ልቤ ፍርጥ እንዳትል እሰጋለሁ።
ሳቋን አቋርጣ፣ “አይገርምክም ሆድዬ፣ ወደኔ ሲቀርብ እኮ አላየሁትም። ሆዷን ደግፋና አጎንብሳ እንባዋ እስኪንጠባጠብ ድረስ ሳቀች።
"ያጋጠመሽ እኮ እንደዚህ የሚያስቅ አልመሰለኝም"
“ሆድየ እንዴት ላብ በላብ እንደሆንኩ እኮ አትጠይቀኝ ታዲያ ይሄ አያስቅም በናትክ"
“ቀርቦ ያደረገውን ብቻ ንገሪኝ የኔ ውድ..ሃ...ሃ...ሃ" ሳቀ፡፡ሳቁ ጎርናና ነው።
“አይገርምም? መጀመሪያ የባሱን መደገፊያ በሁለት እጄ ይዤው ነበር፡፡ ከኋላዬ ክንዶቼን እንቅ አድርጎ ሲይዝ ተሰምቶኛል።
እኔ ደግሞ በቃ የሚይዘው ነገር ያጣ ነው የመሰለኝ፡፡”
“ብቻ አንቺ ላይ ሊንጠላጠል ፈልጎ እንዳይሆን?"
“ሞዛዛ!” አለችና በጥፊ አቃጠለችው፡፡ ዱላውን የለመደው ይመስላል። ምንም አልመሰለውም፡፡ ጥፊው ይደገም ይመስላል ፊቱን ቀበር እንደማድረግ ብሎ አድፍጦ ማዳመጡን ቀጠለ፡፡
“ፍቅር ካለ ለካስ ዱላም ይጣፍጣል?” አልኩ በሆዴ። አሁን በመዝናኛው ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ ጨዋታውን አቋርጦ እሷን
የሚያዳምጥ ይመስላል፡፡
“እላዬ ላይ ልጥፍ ሲል እኔ ደግሞ ያልተመቸው መስሎኝ ሳፈገፍግ የበለጠ ልጥፍ አለብኝ፡፡”
“ይለጥፍብሽ አንዳች! አልኩኝ በሆዴ፡፡
“እኔ የምለው... እና ሲለጠፍብሽ ዝም አልሽ?” አለ እሱም
እንደርሷ ባይሆንም ይጮኸል።
“እኔማ መጀመሪያ አልገባኝም፡፡ በኋላ ግን አንድ ነገር ከኋላዬ ሲላወስ የሰማሁ መሰለኝ፡፡ ገረመኝና እንዲህ ከወደታች የሚንቀሳቀስ ነገር ምን ሊኖር ይችላል ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚንቀሳቀሰው ነገር
የሚቧጥጠኝ መሰለኝ”
"እስኪቧጥጥሽ ድረስ አንቺ ምን ትሰሪያለሽ?" አለና የቤቱን ሰው ሁሉ በጨረፍታ መልከት አድርጎ አጎነበሰ።
“ኧረ በጣም ትገርማለክ ታዲያ ምን ላድርገው? ወደፊት ለማፈግፈግ ሙከራ አደረኩኝ ግን ምንም መላወሻ አልነበረም::"
የእጇ መወራጨት እየጨመረ ነው፡፡
“አንቺ ግን ይሄ ለወንድ ይነገራል? መንገር ያለብሽና መንገር የሌለብሽን ለይተሸ አታውቂም?”
“ኧረ ባክክ! አሁን ይህን የመሰለ ታሪክ ሳልነግርክ ልቅር?” ሳቋ ከበፊቱ ጨምሯል። የተቀመጠችበትን ወንበር በተደጋጋሚ በመቁነጥነጥ ናጠችው፡፡
እንደልቤ መዞር አልቻልኩም፡፡ግን እዚያው ሆኜ ሳልንቀሳቀስ በምንክ ነው የምትወጋኝ?ምናለ ከኋላዬ ዞር ብትልልኝ አልኩት ።አረ ምንም መውጊያ የለኝም አለ እዛው እኔ ላይ እንደተለጠፈ። ሲያዩት ትልቅ ሰው ይመስላል። ደሞ ሊያውም የገጠር ሰው። ሽቅብ ሽቅብ እየተነፈሰ “እንዴት ብዬ ልላዎስ እሜትዬ ከኋላዬ ጠፍንገው ይዘውኝ አለ፡፡ ይህን
እየተነጋገርን እኮ የሚላወሰው ነገር ቀጥሏል!እ...ህህህህ! አለች። አሁን አሁን የሆነ ይመስል እንደመዘግነን እያላትና ከወደትከሻዋ በኩል ወደላይ ሳብ ብላ አንገቷን እየሰበቀች፡፡
ከዚያም “የሚጠጣ ነገር አላዘዝክልኝም
አለችና አጨበጨበች፡፡ አንድ ሰው ብቻ ያጨበጨበ አይመስልም፡፡ አራት
እጅ ነው እንዴ ያላት? እጆቿን አየሁ። ከእንቁላል መጠን ከሚያንስ
መዳፍዋ ያን ያህል ድምጽ ይወጣል ብሎ የሚወራረድ ማንም የለም፡፡
በስርአት ማጣቷና ሁላችንንም በመረበሿ የተበሳጨን ብዙዎች ብንሆንም ጆሯችንን ግን እንዳያዳምጥ አልከለከልነውም፡፡
ቀጠለች ወሬዋን፡፡
“በጣም ያሳቀኝ ነገር ሰውየው ማግኔት ነገር ያጣበቀው ነው የሚመስለው፤ ቀስቀስም እኮ አይል አይገርምክም? ከዚያ በኋላ ነው የበለጠ የገረመኝ! እንደመንቀሳቀስ ስል...አልተስማማሽም እቱ? አርፈሽ ተቀመጭ፡፡ ምን ያወራጭሻል! አይለኝ መስለህ! እንዲነችና! አልኩና ልዞር ስል መዞር አቃተኝ።"
“ምን ትዞሪያለሽ ጠርንፎ ይዞሽ፡፡”
“አንተ ደግሞ...”
"የነገርሽኝን ነው ያልኩት።"
አነስ ያለ ጥፊ ደግማ ሰነዘረች።
“ኧረ እንኳን አብሬ ያልነበርኩኝ ሆሆሆ!...” አለ፡፡
“ደሞ አንቆ ይዞ ምናምኑን እያንቀሳቀሰብኝ አትንቀሳቀሽ ማለቱ አይገርምክም!”
'ወቸ ጉድ!ዛሬ ደሞ ምኑን ያሰማኛል አልኩና ማዳመጤን ቀጠልኩ። አልፎ አልፎ ወደበሩ አያለሁ፡፡ ጓደኛዬ የውሃ
ሽታ ሆኗል፡፡አስናጋጇ የሚበሉትን አቅርባ ተመለሰች፡፡
“ኧረ በናትክ አጉርሰኝ፣ ከመቼ ወዲክ ነው ብቻክን የምትወጥቀው? ነው ሰውየው አበሳጨክ?” መልስ አልሰጣትም፡፡
ወዲያው አንድ ሰው ሲገባ አየችውና፣
“ደናነክ?” አለችው ትከሻዋን እየሰበቀች፡፡
“እስክስ!” አልኩ አሁንም በውስጤ፡፡
“ምነው ጠፋክ?” አለችና በተለፋደደ ድምጽ፡፡ ፊቷን ወደ ጓደኛዋ መልሳ ወሬዋን ቀጠለች።
“ምን እንዳለ ታውቃለህ “እንደሱ አርፈሽ ተቀመጭ፡፡
የራበሽን ያህል ነው የማጠግብሽ፡፡' ሲለኝ በጣም ገረመኝ፡፡”
"የራበሽን ያክል?... ተርቤያለሁ ብለሽው ነበር እንዴ"
"ብሽቅ! በጥፊ እንዳልልህ!... ደሞኮ ወደ ጆሮዬ ዝቅ ብሎ ነው የሚንሾካሾከው! እህ....” አለች በድካም ስሜት፡፡
አፏ ውስጥ ያለውን ምግብ አላምጣ ከጨረሰች በኋላ፣ “ከዛ የሚላወሰው ነገር ኋላዬን ውጥር አድርጎ ሲይዘኝ ቀስ ብዬ እጄን ሰደድ አደረግኩ።”
“እጅሽን ሰደድሽ ልትይዢው? አንቺ ደፋር!” አላት፡፡
“አኸ ወደክ ነው ይዤውማ ነው፡፡”
“ማን ፈቅዶልሽ ነው የሰው እቃ ለመያዝ...”
“ኧረ ባክክ ጨምላቆ....” ብላ ሳትጨርስ፣
“ያጨምልቅሽ!” አለና ከንፈሯን ቆነጠጣት፡፡
“ኡህ ካልጠፋ ቦታ ከንፈሬ ላይ ትቆናጠጣለክ...እንዴ?”
“ቢመቸኝ ምንሽጋ እንደምቆነጥጥሽ ታውቂያለሽ?”
“ኧረ ባክክ! ምናምንክን ቆንጥጥ እሺ?”
እርግጠኛ ነኝ ጤነኛ አትመስልም፡፡ ሁለቱም ሲያዩዋቸዉ ከአማኑኤል አምልጠው የመጡ... ይመስላሉ።
“ባገኘው ኖሮ ማጅር ግንዱን ብዬ ጣቢያ እቀለብ ነበር!” አለ፡፡
“እንዴ ምን አደረገ?"
“ከዚህ በላይ ምን ያድረገኝ? የሰራው
ነው.…እንዴ አንቺ ተስማምተሽበታል እንዴ?"
"ግን መጨረሻውን ሳትሰማ ለምን እንዲክ ትሆናለክ?"
ፍቅረኛዬን ጠበኩት። አልመጣም፡፡ ወደ መዝናኛው የሚገባውን ሰው ሁሉ አያለሁ። አንዲት ቀጭን ሴት ከአንድ ወጣት
ጋር ገባች።
ምን ብሎ እንዳስደሰታት እንጃ የኮቱን እጅጌ ወደታች ስትስበው ከአንገቱ ጎንበስ አለላትና፤ “የኔ ቆንጆ!” ብላ አንገቷን
አጠማዛ ከንፈሩ ላይ ሳመችው።
የአፍላነቴን ጊዜ አስታወስኩ። በጭለማ ሊያውም በአንሶላ ውስጥ ካልሆነ ባደባባይ ከንፈር ተስሞ አይታወቅም ነበር።የትውልዱ ለውጥ ገረመኝ፡፡
ክንዷን በወገቡ ዙሪያ ለማድረግ ሞክራለች፤ አልተሳካላትም፡፡የወገቡን ሩብ ያክል እንኳን አላቀፈችውም ልዩነታቸው ገረመኝ እሱ የተራራ ጉማጅ የሚያክል ግድንግድ፣ እሷ በመዳፍ ውስጥ
ያለች ትንሽ አሳ የመሰለች ደቃቃ፡፡ ፍቅር የሚባለውን ነገር አመሰገንኩት፤ መጠንን፣ ቀለምን እና ዘርን የማይመርጥ የማያዳላ
ክቡር ነገር፡፡
ልጅቱ ያለማቋረጥ ትስቃለች። ድምጿ ከቃጭል የቀጠነና ስቅጥጥ የሚያደርግ ነው፡፡ መድረክ ላይ ያለች ይመስል ለሰው ሁሉ እንዲሰማ አድርጋ እየተወራጨች ስታወራ በአካባቢዋ መደማመጥ
የሚፈልግ ሰው እንዳለ ልብ ያለች አትመስልም፡፡
እንደተቀመጡ አስተናጋጇ ወደነርሱ ቀረብ አለች ። “አንድ ቀይ ወጥና አንድ አልጫ!” ብላ ጮኸች። የቤቱን ሰው ሁሉ ያዘዘች ነው የምትመስለው።
ዐይኔም ጆሮዬም ቀልቤም እነሱው ላይ
የሚያስደስትም፣ የሚያስጠላም ነገር እኩል ቀልብ መሳቡ ሁልጊዜም
ይገርመኛል፡፡ ሴቲቱ ከመገልፈጧ የተነሳ ሳቅ ውድድር ላይ እያላች የደከማት ትመስላለች። የምታደርገው ነገር ሁሉ ወዝ የለውም።
ትኩረቴ ሁሉ ወደ ጥንዶቹ ሆኖና ልቤ ተንጠልጥሎ እጠብቀው የነበረውን ፍቅረኛዬን በጥቂቱም ቢሆን እንድረሳው
ምክንያት ሆኑኝ፡፡ በዚህ አመሰገንኳቸው፡፡ ምክንያቱም ሁልጊዜ ፍቅረኛዬን ስጠብቅ ልቤ በአፍንጫዬ እስክትወጣ ድረስ ትዘላለች።አንድ ቀን እሱን በጉጉት ስጠብቅ ልቤ ፍርጥ እንዳትል እሰጋለሁ።
ሳቋን አቋርጣ፣ “አይገርምክም ሆድዬ፣ ወደኔ ሲቀርብ እኮ አላየሁትም። ሆዷን ደግፋና አጎንብሳ እንባዋ እስኪንጠባጠብ ድረስ ሳቀች።
"ያጋጠመሽ እኮ እንደዚህ የሚያስቅ አልመሰለኝም"
“ሆድየ እንዴት ላብ በላብ እንደሆንኩ እኮ አትጠይቀኝ ታዲያ ይሄ አያስቅም በናትክ"
“ቀርቦ ያደረገውን ብቻ ንገሪኝ የኔ ውድ..ሃ...ሃ...ሃ" ሳቀ፡፡ሳቁ ጎርናና ነው።
“አይገርምም? መጀመሪያ የባሱን መደገፊያ በሁለት እጄ ይዤው ነበር፡፡ ከኋላዬ ክንዶቼን እንቅ አድርጎ ሲይዝ ተሰምቶኛል።
እኔ ደግሞ በቃ የሚይዘው ነገር ያጣ ነው የመሰለኝ፡፡”
“ብቻ አንቺ ላይ ሊንጠላጠል ፈልጎ እንዳይሆን?"
“ሞዛዛ!” አለችና በጥፊ አቃጠለችው፡፡ ዱላውን የለመደው ይመስላል። ምንም አልመሰለውም፡፡ ጥፊው ይደገም ይመስላል ፊቱን ቀበር እንደማድረግ ብሎ አድፍጦ ማዳመጡን ቀጠለ፡፡
“ፍቅር ካለ ለካስ ዱላም ይጣፍጣል?” አልኩ በሆዴ። አሁን በመዝናኛው ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ ጨዋታውን አቋርጦ እሷን
የሚያዳምጥ ይመስላል፡፡
“እላዬ ላይ ልጥፍ ሲል እኔ ደግሞ ያልተመቸው መስሎኝ ሳፈገፍግ የበለጠ ልጥፍ አለብኝ፡፡”
“ይለጥፍብሽ አንዳች! አልኩኝ በሆዴ፡፡
“እኔ የምለው... እና ሲለጠፍብሽ ዝም አልሽ?” አለ እሱም
እንደርሷ ባይሆንም ይጮኸል።
“እኔማ መጀመሪያ አልገባኝም፡፡ በኋላ ግን አንድ ነገር ከኋላዬ ሲላወስ የሰማሁ መሰለኝ፡፡ ገረመኝና እንዲህ ከወደታች የሚንቀሳቀስ ነገር ምን ሊኖር ይችላል ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚንቀሳቀሰው ነገር
የሚቧጥጠኝ መሰለኝ”
"እስኪቧጥጥሽ ድረስ አንቺ ምን ትሰሪያለሽ?" አለና የቤቱን ሰው ሁሉ በጨረፍታ መልከት አድርጎ አጎነበሰ።
“ኧረ በጣም ትገርማለክ ታዲያ ምን ላድርገው? ወደፊት ለማፈግፈግ ሙከራ አደረኩኝ ግን ምንም መላወሻ አልነበረም::"
የእጇ መወራጨት እየጨመረ ነው፡፡
“አንቺ ግን ይሄ ለወንድ ይነገራል? መንገር ያለብሽና መንገር የሌለብሽን ለይተሸ አታውቂም?”
“ኧረ ባክክ! አሁን ይህን የመሰለ ታሪክ ሳልነግርክ ልቅር?” ሳቋ ከበፊቱ ጨምሯል። የተቀመጠችበትን ወንበር በተደጋጋሚ በመቁነጥነጥ ናጠችው፡፡
እንደልቤ መዞር አልቻልኩም፡፡ግን እዚያው ሆኜ ሳልንቀሳቀስ በምንክ ነው የምትወጋኝ?ምናለ ከኋላዬ ዞር ብትልልኝ አልኩት ።አረ ምንም መውጊያ የለኝም አለ እዛው እኔ ላይ እንደተለጠፈ። ሲያዩት ትልቅ ሰው ይመስላል። ደሞ ሊያውም የገጠር ሰው። ሽቅብ ሽቅብ እየተነፈሰ “እንዴት ብዬ ልላዎስ እሜትዬ ከኋላዬ ጠፍንገው ይዘውኝ አለ፡፡ ይህን
እየተነጋገርን እኮ የሚላወሰው ነገር ቀጥሏል!እ...ህህህህ! አለች። አሁን አሁን የሆነ ይመስል እንደመዘግነን እያላትና ከወደትከሻዋ በኩል ወደላይ ሳብ ብላ አንገቷን እየሰበቀች፡፡
ከዚያም “የሚጠጣ ነገር አላዘዝክልኝም
አለችና አጨበጨበች፡፡ አንድ ሰው ብቻ ያጨበጨበ አይመስልም፡፡ አራት
እጅ ነው እንዴ ያላት? እጆቿን አየሁ። ከእንቁላል መጠን ከሚያንስ
መዳፍዋ ያን ያህል ድምጽ ይወጣል ብሎ የሚወራረድ ማንም የለም፡፡
በስርአት ማጣቷና ሁላችንንም በመረበሿ የተበሳጨን ብዙዎች ብንሆንም ጆሯችንን ግን እንዳያዳምጥ አልከለከልነውም፡፡
ቀጠለች ወሬዋን፡፡
“በጣም ያሳቀኝ ነገር ሰውየው ማግኔት ነገር ያጣበቀው ነው የሚመስለው፤ ቀስቀስም እኮ አይል አይገርምክም? ከዚያ በኋላ ነው የበለጠ የገረመኝ! እንደመንቀሳቀስ ስል...አልተስማማሽም እቱ? አርፈሽ ተቀመጭ፡፡ ምን ያወራጭሻል! አይለኝ መስለህ! እንዲነችና! አልኩና ልዞር ስል መዞር አቃተኝ።"
“ምን ትዞሪያለሽ ጠርንፎ ይዞሽ፡፡”
“አንተ ደግሞ...”
"የነገርሽኝን ነው ያልኩት።"
አነስ ያለ ጥፊ ደግማ ሰነዘረች።
“ኧረ እንኳን አብሬ ያልነበርኩኝ ሆሆሆ!...” አለ፡፡
“ደሞ አንቆ ይዞ ምናምኑን እያንቀሳቀሰብኝ አትንቀሳቀሽ ማለቱ አይገርምክም!”
'ወቸ ጉድ!ዛሬ ደሞ ምኑን ያሰማኛል አልኩና ማዳመጤን ቀጠልኩ። አልፎ አልፎ ወደበሩ አያለሁ፡፡ ጓደኛዬ የውሃ
ሽታ ሆኗል፡፡አስናጋጇ የሚበሉትን አቅርባ ተመለሰች፡፡
“ኧረ በናትክ አጉርሰኝ፣ ከመቼ ወዲክ ነው ብቻክን የምትወጥቀው? ነው ሰውየው አበሳጨክ?” መልስ አልሰጣትም፡፡
ወዲያው አንድ ሰው ሲገባ አየችውና፣
“ደናነክ?” አለችው ትከሻዋን እየሰበቀች፡፡
“እስክስ!” አልኩ አሁንም በውስጤ፡፡
“ምነው ጠፋክ?” አለችና በተለፋደደ ድምጽ፡፡ ፊቷን ወደ ጓደኛዋ መልሳ ወሬዋን ቀጠለች።
“ምን እንዳለ ታውቃለህ “እንደሱ አርፈሽ ተቀመጭ፡፡
የራበሽን ያህል ነው የማጠግብሽ፡፡' ሲለኝ በጣም ገረመኝ፡፡”
"የራበሽን ያክል?... ተርቤያለሁ ብለሽው ነበር እንዴ"
"ብሽቅ! በጥፊ እንዳልልህ!... ደሞኮ ወደ ጆሮዬ ዝቅ ብሎ ነው የሚንሾካሾከው! እህ....” አለች በድካም ስሜት፡፡
አፏ ውስጥ ያለውን ምግብ አላምጣ ከጨረሰች በኋላ፣ “ከዛ የሚላወሰው ነገር ኋላዬን ውጥር አድርጎ ሲይዘኝ ቀስ ብዬ እጄን ሰደድ አደረግኩ።”
“እጅሽን ሰደድሽ ልትይዢው? አንቺ ደፋር!” አላት፡፡
“አኸ ወደክ ነው ይዤውማ ነው፡፡”
“ማን ፈቅዶልሽ ነው የሰው እቃ ለመያዝ...”
“ኧረ ባክክ ጨምላቆ....” ብላ ሳትጨርስ፣
“ያጨምልቅሽ!” አለና ከንፈሯን ቆነጠጣት፡፡
“ኡህ ካልጠፋ ቦታ ከንፈሬ ላይ ትቆናጠጣለክ...እንዴ?”
“ቢመቸኝ ምንሽጋ እንደምቆነጥጥሽ ታውቂያለሽ?”
“ኧረ ባክክ! ምናምንክን ቆንጥጥ እሺ?”
እርግጠኛ ነኝ ጤነኛ አትመስልም፡፡ ሁለቱም ሲያዩዋቸዉ ከአማኑኤል አምልጠው የመጡ... ይመስላሉ።
“ባገኘው ኖሮ ማጅር ግንዱን ብዬ ጣቢያ እቀለብ ነበር!” አለ፡፡
“እንዴ ምን አደረገ?"
“ከዚህ በላይ ምን ያድረገኝ? የሰራው
ነው.…እንዴ አንቺ ተስማምተሽበታል እንዴ?"
"ግን መጨረሻውን ሳትሰማ ለምን እንዲክ ትሆናለክ?"
👍3❤1
"መጨረሻውማ የበለጠ የሚያናድድ እንደሆነ ነው...”
ደርሳ ምን እንዳስኮረፋት ሳይታወቅ አኮረፈች።
"በናትሽ መጨረሻውን ንገሪኝ አላት እየተለማመጠ፡፡ ኩርፊያዋን ትታ፣
“እህ እየነገርኩክ! በቃ መላወሱን አቁሞ እየገፋኝ ሲመጣ
እጄን እንደምንም አሾልኬ ተጠማዘዝኩና በእጄ ያለ የሌለ ሐይሌን
አሰባስቤ ጭምቅ ሳረገው ሚያው! ብሎ...” ሁለቱም ሳቁ፡፡ በእርግጥም የምታወራው ከጀርባዋ የነበረው ሰውዬ
በማዳበሪያ ይዞት ስለነበረው ትንሽ ድመት ነበር። እኛም ሳናስበው ሳቅን ::
“አይ ድመቱ! አይ ድመቱ! ለካ በፊስታል ይዞት ትንፋሽ አጥሮት ነው!” አለችና ቀስ ብላ ዙሪያዋን ቃኘች፤ እንደምናዳምጣት
እርግጠኛ ነበረች፡፡
💫አለቋል ደሞ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ደርሳ ምን እንዳስኮረፋት ሳይታወቅ አኮረፈች።
"በናትሽ መጨረሻውን ንገሪኝ አላት እየተለማመጠ፡፡ ኩርፊያዋን ትታ፣
“እህ እየነገርኩክ! በቃ መላወሱን አቁሞ እየገፋኝ ሲመጣ
እጄን እንደምንም አሾልኬ ተጠማዘዝኩና በእጄ ያለ የሌለ ሐይሌን
አሰባስቤ ጭምቅ ሳረገው ሚያው! ብሎ...” ሁለቱም ሳቁ፡፡ በእርግጥም የምታወራው ከጀርባዋ የነበረው ሰውዬ
በማዳበሪያ ይዞት ስለነበረው ትንሽ ድመት ነበር። እኛም ሳናስበው ሳቅን ::
“አይ ድመቱ! አይ ድመቱ! ለካ በፊስታል ይዞት ትንፋሽ አጥሮት ነው!” አለችና ቀስ ብላ ዙሪያዋን ቃኘች፤ እንደምናዳምጣት
እርግጠኛ ነበረች፡፡
💫አለቋል ደሞ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#የወንበር_ፍቅር
ቀይ ነኝ - አምራለሁ
ለውበቴ ደግሞ እጨናነቃለሁ ፤
ውበቴን ሳጎላ - ውበቴን ሳሳምር
የቀለም ምርጫየ
ጥቁር::
ፀጉሬን እንደ ቱ ፓክ- ልጭት አደርግና
ጥቁር ኮፍያየን
ጥቁር ካናቴራ
ጥቁር ጂንስ ሱሪ
ጥቁር ጫማ ሳደርግ
ፓ!
ቅላቴ ይጎላል
ውበቴ ይደምቃል፡፡
ግን ግን
አያርግብኝና!
አ ያ ር ግ ብ ኝ ና!
በጣም የምወዳት
ቅድመ አያቴ ብትሞት፣
ሃዘኔን ላስታውስ
ምንድን ነው የምለብስ?
ጥቁር ልብስ???
🔘በሙሉቀን🔘
ቀይ ነኝ - አምራለሁ
ለውበቴ ደግሞ እጨናነቃለሁ ፤
ውበቴን ሳጎላ - ውበቴን ሳሳምር
የቀለም ምርጫየ
ጥቁር::
ፀጉሬን እንደ ቱ ፓክ- ልጭት አደርግና
ጥቁር ኮፍያየን
ጥቁር ካናቴራ
ጥቁር ጂንስ ሱሪ
ጥቁር ጫማ ሳደርግ
ፓ!
ቅላቴ ይጎላል
ውበቴ ይደምቃል፡፡
ግን ግን
አያርግብኝና!
አ ያ ር ግ ብ ኝ ና!
በጣም የምወዳት
ቅድመ አያቴ ብትሞት፣
ሃዘኔን ላስታውስ
ምንድን ነው የምለብስ?
ጥቁር ልብስ???
🔘በሙሉቀን🔘
#የኖህ_ዘመን_ቁጣ
በጠራዉ ሰማይ ላይ ደመና መጣና
ያ ብርሐን ድንገት ጭጋግ ለበሰና
ሰማይ አለቀሰ፤
ሰውም አለቀሰ፤
ዛፉም አለቀሰ፤
ወነንዙም አለቀሰ፤
ፍጥረት አለቀሰ፤
የሐዘን ዶፍ ከላይ በምድር ፈሰሰ።
ዘሩን ብቻ አይጎዳም ዳር የለውም ጭራሽ
መዘዙ ብዙ ነው የሰው ልጅ ሲበላሽ።
በጠራዉ ሰማይ ላይ ደመና መጣና
ያ ብርሐን ድንገት ጭጋግ ለበሰና
ሰማይ አለቀሰ፤
ሰውም አለቀሰ፤
ዛፉም አለቀሰ፤
ወነንዙም አለቀሰ፤
ፍጥረት አለቀሰ፤
የሐዘን ዶፍ ከላይ በምድር ፈሰሰ።
ዘሩን ብቻ አይጎዳም ዳር የለውም ጭራሽ
መዘዙ ብዙ ነው የሰው ልጅ ሲበላሽ።