አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የት_ነበርኩ?

ፍቅረኛዬን ጠበኩት። አልመጣም፡፡ ወደ መዝናኛው የሚገባውን ሰው ሁሉ አያለሁ። አንዲት ቀጭን ሴት ከአንድ ወጣት
ጋር ገባች።

ምን ብሎ እንዳስደሰታት እንጃ የኮቱን እጅጌ ወደታች ስትስበው ከአንገቱ ጎንበስ አለላትና፤ “የኔ ቆንጆ!” ብላ አንገቷን
አጠማዛ ከንፈሩ ላይ ሳመችው።

የአፍላነቴን ጊዜ አስታወስኩ። በጭለማ ሊያውም በአንሶላ ውስጥ ካልሆነ ባደባባይ ከንፈር ተስሞ አይታወቅም ነበር።የትውልዱ ለውጥ ገረመኝ፡፡

ክንዷን በወገቡ ዙሪያ ለማድረግ ሞክራለች፤ አልተሳካላትም፡፡የወገቡን ሩብ ያክል እንኳን አላቀፈችውም ልዩነታቸው ገረመኝ እሱ የተራራ ጉማጅ የሚያክል ግድንግድ፣ እሷ በመዳፍ ውስጥ
ያለች ትንሽ አሳ የመሰለች ደቃቃ፡፡ ፍቅር የሚባለውን ነገር አመሰገንኩት፤ መጠንን፣ ቀለምን እና ዘርን የማይመርጥ የማያዳላ
ክቡር ነገር፡፡

ልጅቱ ያለማቋረጥ ትስቃለች። ድምጿ ከቃጭል የቀጠነና ስቅጥጥ የሚያደርግ ነው፡፡ መድረክ ላይ ያለች ይመስል ለሰው ሁሉ እንዲሰማ አድርጋ እየተወራጨች ስታወራ በአካባቢዋ መደማመጥ
የሚፈልግ ሰው እንዳለ ልብ ያለች አትመስልም፡፡
እንደተቀመጡ አስተናጋጇ ወደነርሱ ቀረብ አለች ። “አንድ ቀይ ወጥና አንድ አልጫ!” ብላ ጮኸች። የቤቱን ሰው ሁሉ ያዘዘች ነው የምትመስለው።

ዐይኔም ጆሮዬም ቀልቤም እነሱው ላይ
የሚያስደስትም፣ የሚያስጠላም ነገር እኩል ቀልብ መሳቡ ሁልጊዜም
ይገርመኛል፡፡ ሴቲቱ ከመገልፈጧ የተነሳ ሳቅ ውድድር ላይ እያላች የደከማት ትመስላለች። የምታደርገው ነገር ሁሉ ወዝ የለውም።

ትኩረቴ ሁሉ ወደ ጥንዶቹ ሆኖና ልቤ ተንጠልጥሎ እጠብቀው የነበረውን ፍቅረኛዬን በጥቂቱም ቢሆን እንድረሳው
ምክንያት ሆኑኝ፡፡ በዚህ አመሰገንኳቸው፡፡ ምክንያቱም ሁልጊዜ ፍቅረኛዬን ስጠብቅ ልቤ በአፍንጫዬ እስክትወጣ ድረስ ትዘላለች።አንድ ቀን እሱን በጉጉት ስጠብቅ ልቤ ፍርጥ እንዳትል እሰጋለሁ።

ሳቋን አቋርጣ፣ “አይገርምክም ሆድዬ፣ ወደኔ ሲቀርብ እኮ አላየሁትም። ሆዷን ደግፋና አጎንብሳ እንባዋ እስኪንጠባጠብ ድረስ ሳቀች።

"ያጋጠመሽ እኮ እንደዚህ የሚያስቅ አልመሰለኝም"
“ሆድየ እንዴት ላብ በላብ እንደሆንኩ እኮ አትጠይቀኝ ታዲያ ይሄ አያስቅም በናትክ"
“ቀርቦ ያደረገውን ብቻ ንገሪኝ የኔ ውድ..ሃ...ሃ...ሃ" ሳቀ፡፡ሳቁ ጎርናና ነው።

“አይገርምም? መጀመሪያ የባሱን መደገፊያ በሁለት እጄ ይዤው ነበር፡፡ ከኋላዬ ክንዶቼን እንቅ አድርጎ ሲይዝ ተሰምቶኛል።
እኔ ደግሞ በቃ የሚይዘው ነገር ያጣ ነው የመሰለኝ፡፡”
“ብቻ አንቺ ላይ ሊንጠላጠል ፈልጎ እንዳይሆን?"
“ሞዛዛ!” አለችና በጥፊ አቃጠለችው፡፡ ዱላውን የለመደው ይመስላል። ምንም አልመሰለውም፡፡ ጥፊው ይደገም ይመስላል ፊቱን ቀበር እንደማድረግ ብሎ አድፍጦ ማዳመጡን ቀጠለ፡፡
“ፍቅር ካለ ለካስ ዱላም ይጣፍጣል?” አልኩ በሆዴ። አሁን በመዝናኛው ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ ጨዋታውን አቋርጦ እሷን
የሚያዳምጥ ይመስላል፡፡

“እላዬ ላይ ልጥፍ ሲል እኔ ደግሞ ያልተመቸው መስሎኝ ሳፈገፍግ የበለጠ ልጥፍ አለብኝ፡፡”
“ይለጥፍብሽ አንዳች! አልኩኝ በሆዴ፡፡
“እኔ የምለው... እና ሲለጠፍብሽ ዝም አልሽ?” አለ እሱም
እንደርሷ ባይሆንም ይጮኸል።

“እኔማ መጀመሪያ አልገባኝም፡፡ በኋላ ግን አንድ ነገር ከኋላዬ ሲላወስ የሰማሁ መሰለኝ፡፡ ገረመኝና እንዲህ ከወደታች የሚንቀሳቀስ ነገር ምን ሊኖር ይችላል ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚንቀሳቀሰው ነገር
የሚቧጥጠኝ መሰለኝ”
"እስኪቧጥጥሽ ድረስ አንቺ ምን ትሰሪያለሽ?" አለና የቤቱን ሰው ሁሉ በጨረፍታ መልከት አድርጎ አጎነበሰ።

“ኧረ በጣም ትገርማለክ ታዲያ ምን ላድርገው? ወደፊት ለማፈግፈግ ሙከራ አደረኩኝ ግን ምንም መላወሻ አልነበረም::"
የእጇ መወራጨት እየጨመረ ነው፡፡
“አንቺ ግን ይሄ ለወንድ ይነገራል? መንገር ያለብሽና መንገር የሌለብሽን ለይተሸ አታውቂም?”

“ኧረ ባክክ! አሁን ይህን የመሰለ ታሪክ ሳልነግርክ ልቅር?” ሳቋ ከበፊቱ ጨምሯል። የተቀመጠችበትን ወንበር በተደጋጋሚ በመቁነጥነጥ ናጠችው፡፡
እንደልቤ መዞር አልቻልኩም፡፡ግን እዚያው ሆኜ ሳልንቀሳቀስ በምንክ ነው የምትወጋኝ?ምናለ ከኋላዬ ዞር ብትልልኝ አልኩት ።አረ ምንም መውጊያ የለኝም አለ እዛው እኔ ላይ እንደተለጠፈ። ሲያዩት ትልቅ ሰው ይመስላል። ደሞ ሊያውም የገጠር ሰው። ሽቅብ ሽቅብ እየተነፈሰ “እንዴት ብዬ ልላዎስ እሜትዬ ከኋላዬ ጠፍንገው ይዘውኝ አለ፡፡ ይህን
እየተነጋገርን እኮ የሚላወሰው ነገር ቀጥሏል!እ...ህህህህ! አለች። አሁን አሁን የሆነ ይመስል እንደመዘግነን እያላትና ከወደትከሻዋ በኩል ወደላይ ሳብ ብላ አንገቷን እየሰበቀች፡፡

ከዚያም “የሚጠጣ ነገር አላዘዝክልኝም
አለችና አጨበጨበች፡፡ አንድ ሰው ብቻ ያጨበጨበ አይመስልም፡፡ አራት
እጅ ነው እንዴ ያላት? እጆቿን አየሁ። ከእንቁላል መጠን ከሚያንስ
መዳፍዋ ያን ያህል ድምጽ ይወጣል ብሎ የሚወራረድ ማንም የለም፡፡

በስርአት ማጣቷና ሁላችንንም በመረበሿ የተበሳጨን ብዙዎች ብንሆንም ጆሯችንን ግን እንዳያዳምጥ አልከለከልነውም፡፡
ቀጠለች ወሬዋን፡፡
“በጣም ያሳቀኝ ነገር ሰውየው ማግኔት ነገር ያጣበቀው ነው የሚመስለው፤ ቀስቀስም እኮ አይል አይገርምክም? ከዚያ በኋላ ነው የበለጠ የገረመኝ! እንደመንቀሳቀስ ስል...አልተስማማሽም እቱ? አርፈሽ ተቀመጭ፡፡ ምን ያወራጭሻል! አይለኝ መስለህ! እንዲነችና! አልኩና ልዞር ስል መዞር አቃተኝ።"
“ምን ትዞሪያለሽ ጠርንፎ ይዞሽ፡፡”
“አንተ ደግሞ...”
"የነገርሽኝን ነው ያልኩት።"
አነስ ያለ ጥፊ ደግማ ሰነዘረች።
“ኧረ እንኳን አብሬ ያልነበርኩኝ ሆሆሆ!...” አለ፡፡
“ደሞ አንቆ ይዞ ምናምኑን እያንቀሳቀሰብኝ አትንቀሳቀሽ ማለቱ አይገርምክም!”
'ወቸ ጉድ!ዛሬ ደሞ ምኑን ያሰማኛል አልኩና ማዳመጤን ቀጠልኩ። አልፎ አልፎ ወደበሩ አያለሁ፡፡ ጓደኛዬ የውሃ
ሽታ ሆኗል፡፡አስናጋጇ የሚበሉትን አቅርባ ተመለሰች፡፡
“ኧረ በናትክ አጉርሰኝ፣ ከመቼ ወዲክ ነው ብቻክን የምትወጥቀው? ነው ሰውየው አበሳጨክ?” መልስ አልሰጣትም፡፡
ወዲያው አንድ ሰው ሲገባ አየችውና፣

“ደናነክ?” አለችው ትከሻዋን እየሰበቀች፡፡
“እስክስ!” አልኩ አሁንም በውስጤ፡፡
“ምነው ጠፋክ?” አለችና በተለፋደደ ድምጽ፡፡ ፊቷን ወደ ጓደኛዋ መልሳ ወሬዋን ቀጠለች።
“ምን እንዳለ ታውቃለህ “እንደሱ አርፈሽ ተቀመጭ፡፡
የራበሽን ያህል ነው የማጠግብሽ፡፡' ሲለኝ በጣም ገረመኝ፡፡”
"የራበሽን ያክል?... ተርቤያለሁ ብለሽው ነበር እንዴ"
"ብሽቅ! በጥፊ እንዳልልህ!... ደሞኮ ወደ ጆሮዬ ዝቅ ብሎ ነው የሚንሾካሾከው! እህ....” አለች በድካም ስሜት፡፡
አፏ ውስጥ ያለውን ምግብ አላምጣ ከጨረሰች በኋላ፣ “ከዛ የሚላወሰው ነገር ኋላዬን ውጥር አድርጎ ሲይዘኝ ቀስ ብዬ እጄን ሰደድ አደረግኩ።”
“እጅሽን ሰደድሽ ልትይዢው? አንቺ ደፋር!” አላት፡፡
“አኸ ወደክ ነው ይዤውማ ነው፡፡”
“ማን ፈቅዶልሽ ነው የሰው እቃ ለመያዝ...”
“ኧረ ባክክ ጨምላቆ....” ብላ ሳትጨርስ፣
“ያጨምልቅሽ!” አለና ከንፈሯን ቆነጠጣት፡፡
“ኡህ ካልጠፋ ቦታ ከንፈሬ ላይ ትቆናጠጣለክ...እንዴ?”
“ቢመቸኝ ምንሽጋ እንደምቆነጥጥሽ ታውቂያለሽ?”
“ኧረ ባክክ! ምናምንክን ቆንጥጥ እሺ?”
እርግጠኛ ነኝ ጤነኛ አትመስልም፡፡ ሁለቱም ሲያዩዋቸዉ ከአማኑኤል አምልጠው የመጡ... ይመስላሉ።

“ባገኘው ኖሮ ማጅር ግንዱን ብዬ ጣቢያ እቀለብ ነበር!” አለ፡፡
“እንዴ ምን አደረገ?"
“ከዚህ በላይ ምን ያድረገኝ? የሰራው
ነው.…እንዴ አንቺ ተስማምተሽበታል እንዴ?"
"ግን መጨረሻውን ሳትሰማ ለምን እንዲክ ትሆናለክ?"
👍31