አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትንግርት


#ክፍል_ሃምሳ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ታዲዬስ የፅዮንን ቀኝ እጇን እንደጨበጠ በቀስታ ደረጃውን ይዟት እየወጣ 1ኛ ፎቅ ላይ ወደተከራየው መኝታ ክፍሉ ወሰዳት….፡፡

‹‹የሚያምር ክፍል ነው >>አለችው ወደ ውስጥ መግባቷን ካረጋገጠች በኃላ::

‹‹የእኔ አይደለም የባለ ሆቴሎቹ ነው፡፡››

‹‹አውቃለሁ....ሁለት አልጋ ያለው ክፍል መከራየትህን ወድጄልሀለሁ.››

‹‹.ተሳስተሸል ....ባለ አንድ አልጋ ነው››አላት እየሳቀባት፡፡

‹‹አታይም ብለህ ትሸውደኛለህ እንዴ?››

‹‹ግን እንዴት ልታውቂ ቻልሽ..?ቅድም ነግሬሻለሁ ማለት ነው?››

‹‹አልነገርከኝም…ግን ክፍሉ በጣም ሰፊ ነው ... በዚህ ስፋት ደግሞ አንድ አልጋ ብቻ አይዘረጋም፡፡››

‹‹ስፋትን በሽታ መለየት ትችያለሽ ማለት ነው?››

‹‹ኖኖ.. በጆሮዬ ነው::››

‹‹አድናቂሽ ነኝ፡፡››

‹‹አመሰግናለሁ››አለችው እየፈገገች፡፡

‹‹እንደቆምሽ እኮ ነሽ ....ቁጭ በይ እንጂ››በዳበሳ ወደ አልጋው ተጠጋችና ጠርዝ ላይ ተቀመጠች፡፡

‹‹የምትፈልጊው ነገር አለ ወይስ እንተኛ?››

‹‹ኧረ ምንም አልፈልግም እንተኛ ....እኩለ ለሊት እኮ ሆኗል....ለሁለተኛ ቀን ካንተ ጋር ለመተኛት በጣም ጓጉቼያለሁ፡፡››

‹‹ተይ እንደባለፈው ዝም ብሎኝ እየተቃጠለ ይተኛል ብለሽ አስበሽ ከሆነ ካሁኑ ላስጠንቅቅሽ፡፡››

‹‹ባክህ አታደርገውም …እንደዛ ሰክረህ ያልተሳሳትክ ዛሬ በሰላሙ? >>

‹‹ስካር እኮ ማሳበቢያ ነች..እኔ ሰው ይሄንን ስህተት የሰራውት ሰክሬ ነው፣ከሰው የተደባደብኩት ሰክሬ ነው፣እንትናን የደፈርኩት ሰክሬ ስለነበር ነው፣ካለ ኮንደም የወጣውለት ሰክሬ ነው..ወዘተ ሲባል አያሳምነኝም፡፡ያ ሰው መጀመሪያውኑ ለእነዛ ነገሮች የተመቻቸ ስነ- ልቦና ያለው ሰው ቢሆን እንጂ በመጠጥ ብቻ ለወንጀል የሚዳረግ ሰው መኖሩን እጠራጠራለሁ.. እርግጥ መጠጥ ሲበዛ ብርታት ይሰጠው ይሆናል እንጂ ለስህተት ማቅለያ በቂ ምክንያት ሆኖ አይታየኝም....የእውነት ሆኖ እንኳን ስካር ለዛን ያህል ተፅዕኖ የሚያጋልጠው ከሆነ.... ያ ሰው መጠጥ በዞረበት መዞር የለበትም የሚል አቋም አለኝ፡፡

‹‹ስለዚህ እኔ በራሴ እተማመናለሁ… ንክችም አላደርግሽ እያልከኝ ነው?››አለችው፡፡

‹‹አልወጣኝም..እኔ ያልኩት ምናልባት የማደርገው ከሆነ ቀድሞውኑም ለማድረግ
ዕቅድና ፍላጎት ስላለኝ እንጂ ስለጠጣሁና
lስላልጠጣሁ አይደለም እያልኩሽ ነው፡፡›› አላትና ከተቀመጠበት ተነስቶ በቁሙ ልብሱን ማወላለቅ
ጀመረ…ጨረሰ፡፡ወደ እሷ ቀረበና ከላይ የለበሰችውን ሻርፕ አንስቶ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠው፡፡ቀጥሎ የለበሳችውን ቲሸርት

ጠርዙን ይዞ ወደ ላይ ሳበው..በጭንቅላቷ

ተሞሽልቆ ሲወልቅ ሀር መሳይ ሉጫ ፀጉሯን ብትን ብሎ አየሩን ሞላው ..እጇን ይዞ አቆማት፤በዝምታ ቆመችለት፤የለበሰችውን
ሰማያዊ ጅንስ ሱሪ ለማውለቅ መጀመሪያ ቀበቶውን ፈታ፣ቀጥሎ ቁልፉን አላቀቀ፣ዚፑን ቁልቁል አንሸራተተው፣ከዛ ወደታች ጎተተው...ሮዝ ፓንት ላይዋ ላይ ቀረ ..ወደ ላይ ተመለሰና
ጡት ማስያዣዋንም አወለቀላት::

‹‹..አሁን ወደ አልጋው መሄድ እንችላለን?››አላት፡፡

<< በነካ እጅህ ጨርሰው እንጂ?››

‹‹ፓንቱንም..?››

‹‹አዎ ምነው አንተ አላወለቅክም እንዴ? ››ብላ እጇን ወደእሱ ስትዘረጋ ሳታስበው እንደ ብረት የተገተረ ለስላሳ እርቃን ብልቱ አፈፍ አደረገች፡፡

‹‹አንተ ምነው እንዲህ እንደ ሚሳዬል ተቀሰረ..እውነትም ዛሬ ጉዴ ፈልቷል፡፡›› ብላ ወደ
እሱ ልጥፍ አለችበትና ከንፈሯን ወደ ከንፈሩ አስጠግታ ትንፋሿን ለቀቀችበት..ታዲዬስም
ጭምቅ አድርጐ አቀፋትና ከንፈሮቿን ዋጣቸው... ያለማቋረጥ በረረረረረረጅሙ
ከንፈሯን እየመጠጠ እጆቹን ወደታች አወረደና በኃላ በኩል ፓንቷ ውስጥ ሰቅስቆ አስገብቶ

ከወንዝ ወዲህ ማዶ እና ከወንዝ ወዲያ ማዶ በትይዩ መስመር ጉብ ያሉ ተራሮች የሚመስሉትን መቀመጫዋን እስኪያማት
ጨመቃቸው.. የተጎረሰው ከንፈሯ ሳያግዳት አቃተተች... እሷም እጆቿን በጭንቅላቱ

በጀርባው እያሽከረከረች ትዳብሰውና ትታገለው
ጀመር…እንትኑ ግን እየወጋት ነው፤ደግሞ እንዴት
ነው ጥንካሬው….?አቤት መቀመጫዋን ጨመቅ
ለቀቅ መልሶ ደግሞ ጨመቅ ሲያደርግላት   የምታሰማው የደስታ መቃተት፤ፓንቷን ወደታች ሳበላት ልታግዘው እግሯን ወደ ላይ ሰቀለችለት ተራ በተራ ከእግሮቿ አሾልኮ አወጣውና እዛው ወለሉ ላይ ጣለው፡፡ እስከአሁን አልጋውን አልያዙም እደቆሙ ነው፡፡ወደራሱ በኃይል ሳባትና ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፤ሁለቱ የሚፈላለጉና የሚሳሳቡ ሸለቆና ጉብታ ሳይዋሀዱ ውጫዊ በሆነ ንክኪ ሲፋተጉ ጉብታው ላይ የበቀለው ችፍግ ያለ ደን ሸለቆ አካባቢ ያለውን ሜዳ ላይ አርፎ በሚያደርገው የፍትጊያ ንክኪ ፅዮንን ልዩ ስሜት ተሰማት… ስሜት ብቻ ሳይሆን ሸለቆውም በደስታ ምንጭ አፍልቆ አካባቢውን በፈሳሽ አረሰረሰው፡፡››

እንደምንም ከንፈሯን ከከንፈሩ አላቀቀችና‹የእኔ ጌታ በጣም ነው የማፈቅርህ ..በቃ አድርገው..

‹‹እርግጠኛ ነሽ?››አላት ይሄን ሁሉ መንገድ ከተጓዙ በኃላ እርግጠኛ ነሽ ብሎ መጠየቁ ለራሱም እየገረመው….፡፡

ከስር ሰቅስቆ ተሸከማትና አልጋው ላይ ዘረራት ..….ተከትሎ እግሮቿ መካከል ገባ...የጠነከረ ጉብታውን ሸለቆዋ ውስጥ ለመጨመር በራፍ አካባቢ ሲያሽከረክረው‹‹የእኔ ጌታ ፈራሁ..ታውቃለህ የመጀመሪያዬ እኮ ነው... ያ..መ..ኝ ይሆን?››ጠየቀችው፡፡

‹‹‹አይዞሽ አያምሽም ቀስ ብዬ…. አስታምሜ ነው፡፡››

‹‹እሺ እንደፈ..ለግክ...ግን የሀያ ስምንት አመት ድንግል ሴት በዚህ ዘመን አጋጥሞህ ያውቃል?››

‹‹እኔ አጋጥሞኝ አያውቅም.. ፡፡››እያለ በድርጊቱ ገፋበት፡፡
…እንደጠረጠረው ግን እየሆነለት አይደለም... በፊት ሲገምት ከንባብም ባገኘው መረጃ መሰረት ዕድሜ ከፍ እያለ ሲሄድ ድንግልና በራሱ ይወገዳል ወይም በጣም የመሳሳቱ ዕድል ሰፊ ነው የሚል ነበር..የፅዮን ግን ድፍን ነው..ቢለው ቢለው ከክርክሩ አልፎ ሊገባለት አልቻለም…፡፡

‹‹የእኔ ጌታ አመመኝ››አለችው ፅዬን ፡፡

‹‹እኔንም እያመመኝ ነው...ሳልላጥ አልቀረሁም... ሲወራ እንደሰማሁት ሊያቅተኝ ነው መሰለኝ፡፡››

‹‹ኧረ አያቅትህም የእኔ ጀግና ...ሰውነቴን ጨምድጄብህ ይሆናል... ይሄው ብላ እግሮቿን እስከ መጨረሻው በረጋግዳለት ዘና ለማለት ሙከራ አደረገች..እሱም በአዲስ መልኩ ወደ ውስጠቷ ለመጥለቅ እየተዘጋጀ ሳለ የመኝታ ቤቱ በራ ተንኳኳ..እንቅስቃሴውን አቋርጦ በገረሜታ አዳመጠ‹‹..በዚህ ለሊት ማነው የሚያንኳኳው?››

መንኳኳቱ ጠንከር እያለ መጣ‹‹ ...የእኔ ጌታ ተነስ ክፈት፡፡››

‹‹በዚህ ሰዓት ማን ነው..?ይቅርታ አጣርቼ ልምጣ፡፡››ብሏት ከጭኗ መካከል ወጣና ኮመዲኖው ላይ ያለውን ፎጣ አንስቶ በማገልደም ወደ በራፉ ሄዶ ከውስጥ የተሰካውን ቁልፍ አሽከርክሮ ከፈተና << ማነው?››ብሎ እይታውን ወደ ውጭ ሲወረውር ርብቃን ተገትራ አያት፡፡

በራፉን ሳያስብ ሙሉ በሙሉ በረገደውና ‹‹እንዴ !!ምን ሆንሽ..?ምን ተፈጠረ?›› ብሎ ወደ ውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘጋው፡፡

‹‹አይዞህ ምንም አልሆንኩም ..መጀመሪያ የከፈትከውን ጭን ዝጋና እናወራለን ››አለችው አይኖቿን የፅዮን እርቃን ገላ ላይ ሰክታ፡፡

ተንደርድሮ ሄደና ከላይ ዕርቃኗን የተዘረጋጋችውን ፅዬንን አልጋ ልብሱን በአንድ በኩል ገለጠና አለበሳት…እሷም ተቃውሞም ሆነ ድጋፍ ሳታሰማ ባለችበት ሁኔታ በዝምታ ያለምንም እንቅስቃሴ እንዳደረጋት ሆነችለት፡፡
👍798
#ትንግርት


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


የዶ/ርን ስልክ እንደዘጋ ርብቃ ጋር ነው የደወለው<<መቼስ እሁድ ስለሆነ ቤት ትኖሪያለሽ ብዬ ነው?››

‹‹አዎ ቤት ነኝ ..እየመጣህ ነው እንዴ?››

‹‹አዎ ፈልጌሽ ነበር?››

<<ና አለውልህ››አለችው፡፡ ስልኩን ዘጋውና ታክሲ ውስጥ ገባ፡፡

ሲደርስ ቆንጆ ቁርስ ሰርታ ጠበቀችው፤ በጣም የገረመው ያገኛት በህልሙ የመጣችበት ጊዜ የለበሰችውን ቀሚስ ለብሳ ነበር ፡፡

ከቁርስ በኃላ

‹‹አረፍ እንበል እንዴ? >> አለችው በአገጯ ወደ መኝታ ቤቷ እየጠቆመችው….፡፡

‹‹አይ እስቲ መጀመሪያ እዚሁ ሳሎን ሆነን እንነጋገር።

<<እንነጋገር?>>

‹‹አዎ ምነው?››

‹‹እኔ እንጃ እኔና አንተ እንነጋገር ብለን ተነጋግረን አናውቅም ብዬ ነዋ ..እኔ እንነጋገር ሲሉኝ ይጨንቀኛል...፡፡ የሆነ ችግር..የሆነ የተበላሸ ነገር ያለ መስሎ ነው የሚሰማኝ…ይገርምሀል እናትና አባቴ ሁል ጊዜ እንነጋገር እንዳሉና በጠረጴዛ ዙሪያ እንደተቀመጡ ነው... ግን አንድም ቀን በመግባባት አጠናቀውት አያውቁም...እና ቃሉ ያስጠላኛል፡፡››

‹‹እና ካልፈለግሽ ልተወው?››

‹‹አይደለም ..ዝም ብለህ በፊት እንደምታደርገው ቀለል አድርገህ በጨዋታ መልክ አውራኝ ነው ያልኩህ››

‹‹እሺ›› አለ ፈገግ ብሎ‹‹…ባለፈው አንድ ጨዋታ በስልክ ጀምሬልሽ ነበር….ስለ እኔ እና ስለ ፅዮን››

‹‹አስታወስኩት….፡፡››

‹‹እንድንጋባ ትፈልጋለች፡፡››

‹‹በጣም አፍቅራሀለች ማለት ነው ?አደራ ግን እዳትጎዳት... አንተ በጣም ምርጥ ጓደኛ መሆን እንደምትችል እኔ ምስክር ነኝ ..ለእሷ ደግሞ ምርጥ ባል ለመሆን ሞክር፡፡››

‹‹እሞክራለሁ….ከዛ በፊት ግን አንቺ ብታገቢኝ ምን አለበት ብዬ ልጠይቅሽ ነበር የመጣሁት››

<<እኔ....? ጋብቻ>>

‹‹አዎ ጋብቻ...ካፈቀርሺኝ ማለቴ ነው?››

‹‹ስለማፈቅርህማ ነው የማላገባህ..አየህ ታዲ እኔ ስላንተ ምንም አይነት ቆሻሻ ትዝታ እንዲኖረኝ አልፈልግም..7 አመት ሙሉ ህይወቴን በፍቅር አጣፍጠህልኛል...አንተን በማግኘቴ በጣም እጅግ በጣም እድለኛ ሰው ነኝ... ወደ ጋብቻ ¶ይዤህ ገብቼ የሆነ ነገር ታስቀይመኝና ይሄንን ስለአንተ ስገነባ የኖርኩትን የፍቅር ሀውልቴን ታፈርስብኛለህ ብዬ እሰጋለሁ.. ስለዚህ ይቅርብኝ፡፡››

‹‹በቃ የመጨረሻ ውሳኔሽ ይሄ ነው?››

‹‹አዎ ከዚህ በፊት አንተን ለማግባት ሁለት ሶስት ጊዜ አስቤ ነበር፤ቀድሜ ሁሉ ልጅ ልወልድልህ ፈልጌም ነበር፤ከዛ እንድታገባኝ ማለት ነው››

<<ሎጅ?>>

‹‹አዎ ልጅ ልወልድልህ ....ከዛ ላገባህ፡፡››

‹‹እና ሀሳብሽን ለምን ቀየርሽ?››

‹‹ተረጋግቼ ሳስበው የጅል ሴት ዘዴ ሆኖ አገኘሁት..አይህ ወንድ ልጅ እንዲያገባህ የተሳሳትክ መስለህ ማርገዝ ትክክለኛ ዘዴ አይደለም ፡፡ምን አልባት አፍሮ፣ይሉኝታ ይዞት፣አዘኔታ አንጀቱን አላውሶት..ወይም ለልጁ ካለው ፍቅር አንፃር በሁኔታዎች አስገዳጅነት ወደ ጋብቻ ተስማምቶ ሊገባ ይችል ይሆናል..ነገር ግን ቆየት ብሎ ጋብቻው ችግር ላይ መውደቁ አይቀርም፤አይደለም በሆነ ሰበብ አስገዳጅነት ይቅርና በፍፁማዊ ፍቀር እና በሙሉ ፍላጐት የገቡበት ጋብቻ እንኳን አስተማማኝ አይደለም፡፡››

«እና?»

‹‹እናማ ሀሳቤን ሰረዝኩ፡፡››

‹‹ለእኔ ልጅ የመውለዱን?››

‹‹....ኧረ አንተን ማግባቱንም ጭምር፡፡››

‹‹አሁን ግን እኮ ልጅ አርግዘሽልኛል፡፡››

‹‹የምን ልጅ?››

‹‹ልጅ ነዋ... እርጉዝ ነሽ፡፡››

‹‹አንተ እኮ ምላስህ ጥቁር ነው..በእናትህ አታሟርትብኝ፡፡››

‹‹ማሟረት አይደለም.. የእውነቴን ነው…፡፡አሁን የለበስሽውን ቀሚስ ለብሰሽ በህልሜ መጥተሸ ነበር..ለዚህ ነው በጥዋት ወደአንቺ የመጣሁት፡፡››

‹‹ይሄንን ቀሚስ አታውቀውም እኮ ከሶስት ቀን በፊት ነው የገዛሁት..በዚህ ሶስት ቀናት ውስጥ ደግሞ ካንተ ጋር አልተገናኘሁም፡፡››

‹‹እኔም የገረመኝ እሱ ነው..ጥምዝ የወርቅ ሀብል በፍቅር አጠለቅሺልኝ.. ስሜቴ እንደሚተረጉምልኝ ከሆነ ልጅ ሳታረግዢልኝ አልቀረሺም፡፡ >>

‹‹እንዴ ሀብል አጠለቅኩልህ ማለት እሺ እንዳልከው ልጅ ይሁን ..ከፅዬን እንደሆነስ ..? የግድ እኔ ስላጠለቅኩልህ ከእኔ ነው ማለት ይቻላል?››

‹‹አይ ከፅዮን ጋር መዋሀድ እንደማንችል አይቼያለሁ..በዛ ላይ ሀብሉ ሁለት ተመሳሳይ አንድ ላይ የተጠቀለለ ነበር ...አንዱን እራስሽ አንገት ላይ ስታጠልቂ አንዱን እኔ አንገት ላይ ነው ያደረግሽው፡፡››

‹‹ጥሩ ህልም ነው ፤ግን አንድ የዘነጋሀው ነገር ቢኖር እኔ በየሶስት ወሩ ሳላሰልስ የወሊድ መከላከያ መርፌ እንየተወጋው መሆኔን ነው፡፡››

‹‹አውቃለሁ.... ያ ማለት ግን ላለማርገዝሽ መቶ ፐርሰንት ማስተማመኛ ነው ማለት አይደለም..እዚህ ሰፈር በቅርብ ክሊኒክ አለ?››

‹‹አዎ ምነው ጠየቅከኝ?››

‹‹ተነሽ ሄደን ቼክ እናድርግ?››

‹‹ምኑን?››

‹‹ማርገዝ አለማርገዝሽን >>

‹‹የምርህን ነው እንዴ?›› አለችው በፍራቻም በመጠራጠርም ጭምር.. ምክንያቱም ከዚህ በፊት ታዲዬስ ተመሳሳይ ከህልም የመነጩ ትንቢቶችን ነግሯት እሱ እንዳለው ተግባራዊ ሲሆኑ ደጋግማ ታዝባለች፡፡

‹‹ተነሽ እንጂ፡፡››ትንሽ ካቅማማች በኃላ ተስማምታ ተነሳች.... ተያይዘው ወጡ፡፡

ከአንድ ሰአት በኃላ..ወደቤት ተመልሰው ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡

‹‹..ጭራሽ የሶስት ወር እርጉዝ?››በንዴት ተንጨረጨረች፡፡

‹‹ርብቃ አይዞኝ ተረጋጊ እንጂ፡፡››

‹‹እንዴት ልረጋጋ..?እኔ ገና ለገና ስራና ገንዘብ ስላለኝ ብቻ አባት የሌለው ልጅ መውለድ አልፈልገውም፡፡>>

‹‹ምን ማለት ነው? አባቱ እኮ አለሁ... እኔ ነኝ::››

‹‹አንተማ የሌላ ሰው ባል ልትሆን ነው››

‹‹እርሺው ..እኔ እንኳን ልጅ ኖሮኝ ቀድሞውንም ያንቺን ፍላጐት ላክብር ብዬ ነው እንጂ የማፈቅረው ማግባትም የምፈልገው አንቺን ብቻ ነው››...አፍጥጣ በአድናቆት አየችውና‹‹ፅዮንስ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አስረዳታለዋ››

‹‹ምን ብለህ …?ሞራሏ እኮ ሊነካ ይችላል?››

‹‹ጋብቻ የሰው ሞራል ለመገንባት ወይም ለይሉኝታ ሲባል የሚገባበት አይደለም፡፡››

‹‹ቢሆንም እኔ እንጃ ምን ማለት እንዳለብኝ እንኳን ማወቅ አልቻልኩም››

‹‹አባት የመሆን ብቃቴ ተጠራጥረሽ ነው አይደል፡፡››

አይ እሱን እንኮን ፍፁም ልጠራጠር አልችልም..ያንተን አባት የመሆን ብቃት ከተጠራጠርኩማ እኔ የአለም ትልቋ ደደብ ነኝ ማለት ነው..አንተ እኮ የአለም ምርጥ አባትነት ብትወዳደር እንደምታሸንፍ አውቃው››

‹‹እና ምንድነው ችግሩ››

ችግሩማ ምንም እንኳን በአባትነትህ ቅንጣት ጥርጣሬ ባይኖረኝም በባልነትህ ግን እኔ እንጃ..አንተ የትዳር ሰው ይወጣሀል ብዬ ማሰብ ይከብደኛል፡፡

ይቀጥላል

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።

#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍7616😱3🔥2🥰2👎1
#ትንግርት


#ክፍል_ሃምሳ_ሁለት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


..ውበት ማለት ከአይን ሌንስ ሞልቶ የሚተርፍ ውስጥን በደስታ ስሜት የሚያጥለቀልቅ በቀለማት ህብር የደመቀ ምስል ነው፡፡.

ዶ/ር ሶፊያ እና ትንግርት ኮንትኔንታል ሆቴል ምሳ በልተው ከጨረሱ በኃላ መጠጥ እየተጎነጩ ጨዋታ ይዘዋል፡፡

‹‹እሺ ትንግርቴ ህይወት እንዴት ነው?››

ጠየቀቻት፡፡

‹‹እንደምታይው ነው፡፡››

‹‹ላገባ እኮ ነው ..ነግሬሻለሁ አይደል?››

‹‹አላስተዋወቅሽኝም እንጂ ነግረሺኛል፡፡››

‹‹አስቤ ነበር ግን ወደ አሜሪካ በረረ ..ያው ጣጣውን ጨርሶ አንደኛውኑ ከ15 ቀን በኃላ ወደ ሀገር ቤት ይመጣል ...ሊያገባኝ ፡፡የዛኔ አስተዋውቅሻለሁ፡፡››

‹‹ቆንጆ ነው?››ትንግርት ጠየቀቻት፡፡:

‹‹ያንቺን ያህል አያምርም እንጂ ቆንጆስ ቆንጆ ነው፡፡››እንዲህ ስትላት የትንግርት ፊቷ ቀላ፡፡

‹‹የሆንሽ ብሽቅ ነገር እኮ ነሽ...ሰውን መተንኮስ መቼም አታቆሚም፡፡››

እውነተኛ ስሜቴን እኮ ነው እየነገርኩሽ ያለሁት..ውበት ማለት ከአይን ሌንስ ሞልቶ የሚተርፍ ውስጥን በደስታ ስሜት የሚያጥለቀልቅ በቀለማት ህብር የደመቀ ምስል ነው፡፡..እንደዛ የሚሰማኝ ደግሞ አንቺን ሳይ ብቻ
ነው፡፡››

‹‹ታድዬ፡፡››አለቻት በማሾፍ፤ቀጠለች‹‹ግን ሁሌ አንድ ነገር ጠይቅሻለሁ እያልኩ ሳገኝሽ እረሳዋለሁ፡፡›››

‹‹ምንድነው አሁን ጠይቂኛ?››

‹‹ሀዋሳ ከመገናኘታችን በፊት ለስድስት ወራት ያህል በሚሴጅ ታጨናንቂኝ የነበርሽው አንቺ ነበርሽ አይደል?››

‹‹አዎ እኔ ነኝ...ማን መስሎሽ ነበር?››

‹‹እኔ እንጃ.... ብቻ ከድሮ የሽርሙጥና ህይወት ካፈራዋቸው ደንበኞቼ መሀከል የፍቅር ግርሻ ናላውን ያዞረው አንዱ ጀግና መስሎኝ ነበር፡፡››

‹‹ትንግርቴ..በእኔ ተረብሸሽ የማትፈልጊው ህይወት ውስጥ ተሰንቅረሽ ሶስት የባከኑ ዓመታት በማሳለፍሽ ግን በጣም አዝናለሁ፡፡››

‹‹የባከኑ አልሻቸው..እነዛ አመታት ፍፁም የባከኑ የሚባሉ አልነበሩም ...የህይወት ልምዶች ያገኘሁባቸው እና ስብዕናዬን የሞረድኩባቸው ዓመታት ነበሩ፤ያን ስል መከራ አልነበረውም፡፡...ስቃይ
አልተቀበልኩበትም፣አልተሰደብኩበትም፣አልተደ በደብኩበትም ፣አልተዋረድኩበትም ማለቴ አይደለም ግን ከተሰቃየሁት ስቃይ ይልቅ ያተረፍኩት በጎ ነገር ሚዛን ይደፋል እያልኩሽ ነው፡፡››

‹‹ግን በመሀል ህይወት አስጠልታሽ ማለቴ ተስፋ ቆርጠሸ አታውቅም?›› ትንግርት እየፈገገች‹‹ታስቂያለሽ..አንድ በጣም የምወዳት አማረች የምትባል ጓደኛዬ አንድ የሚያምር ንግግር ትናገር ነበር …ምን እንደምትል ታውቂያለሽ

<<ተስፋ የሌለው ሰው ተስፋ አይቆርጥም››ምን ለማለት እንደፈለገች መጀመሪያ አይገባኝም ነበር... በኃላ ግን ከገዛ ህይወቴ ጋር አቆራኝቼ ሳሰላሰለው ተገለፀልኝ…፡፡ እኔ ከዛች ከተለያየንበት ደቂቃ ጀመሮ ተስፋ ሚባል ነገር ከውስጤ ወድሞ ባዶ ንብ የሌለበት ቀፎ ሆኜ ነበር፡፡ሶስቱን አመት ሙሉ ያለምንም ተስፋ ነበር የኖርኩት..ለዛም ነው ያልተቸገርኩት…ምንም አጣለሁ ብዬ የምጨነቅለት፡፡..እዚህ ቦታ መድረስ አለብኝ ብዬ የምጥርበት..ይሄንን ነገር ማግኘት አለብኝ ብዬ የምጓጓለት ነገር አልነበረኝም፡፡››

‹‹ያሳዝናል...ትንግርቴ፡፡››

‹‹አትዘኚ...በህይወት ዝቅታ ወይም ከፍታ ላይ በአጋጣሚ ትንጠለጠያለሽ፡፡ከከፍታው
በምታገኚው ምቾት ተጠምደሽ ወይም ከዝቅታው ውስጥ በሚያጋጥምሽ መከራ ተደቁሰሽ አልባሌ ሰው ሆነሽ እንዳትቀሪ ግን የራስሽ ጥንካሬ ይወስነዋል፡፡ከፍታውም ሆነ ዝቅታው የራሱ የሆነ አውንታዊ አና አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፡፡አሉታዊ ጎኑን ተቋቁመን ጠቃሚውን ነገር መቅሰም የእኛ ፋንታ ነው፡፡››ትንግርት እንዲህ ስትናገር ዶ/ር ሶፊያ እንባዋን እያንጣባጠበች ነበር፡፡

‹‹ቢሆንም ትንግርቴ ይህ ላንቺ ፍፁም የሚገባ ህይወት አልነበረም፡፡››

‹‹ላንቺም እኮ ብር ከፍሎ ሰውን ማስገደል የሚገባሽ ህይወት አልነበረም፤ አሜሪካ ሄዶ ለስድስት ወር በአዕምሮ ህመም ማገገሚያ ሆስፒታል ውስጥ ታግቶ መኖር፤የማትፈልጊያቸውን ኪኒኖች እየጎመዘዘሽ መቃም፤በድንዛዜና በብዥታ ቀናቶችን መግፋት ላንቺም የሚገባ አልነበረም፤አየሽ ሶፊ ‹ተፈጥሮን በቁጥጥራችን ስር እናደርጋለን› የሚባለው በትክክል የሚሰራው በሶሰሻሎስቶች የመፈክር ባነር ላይ በቲዬሪ ደረጃ ብቻ ነው፡፡…እንደውም
በተቃራኒው ተፈጥሮ ነች እኛን ባብዛኛው የምትቆጣጠረን…የህይወት መስመርሽን አንቺ በፈለግሽው መንገድ ብቻ ማስኬድ አይቻልሽም፡፡ቤተሰብ ወደዚህ ይጎትትሻል፣ጓደኞችሽ ወደዛ ይስቡሻል፣ሀገርሽ ወደ ላይ ታወጣሻለች፣ያላሰብሻቸው አጋጣሚዎች ወደታች ያወርዱሻል፣ስለዚህ የሆነው ሁሉ ሆኗል፤በመሆኑም ደግሞ ለበጎነው ብለን መቀበልና ወደፊት መጓዝ ብቻ ነው የሚበጀን፡፡››

‹‹ለበጎ ነው ስትይ?››

‹‹በምንም ምክንያት ሆነ በምንም አንቺ ጥለሽኝ መሄድሽ በጊዜው ፈተናው ከባድ ቢሆንም በስተመጨረሻ ያመጣው ውጤት ዛሬ ህይወታችን እንዲህ ኖርማል እንዲሆን ስላደረገ ውጤቱ ጥሩ ሆኗል ማለቴ ነው፡፡››

‹‹ግን እኮ ሁለታችንም የምንፈልገው ያንን ኖርማል ያልሆነውን ህይወት ነበር፡፡››

‹‹ቢሆንም ዘላቂ ውጤቱ መልካም አይሆንም ነበር…ማህበረሰብ እንዴት ነበር የሚያሰቃየን...?
መቼ ነው የምታገቡት..?ኧረ ቆማችሁ ቀራችሁ፤ በዛ ላይ የልጅ መውለድ ጉዳይ አለ...


✂️✂️✂️?????????✂️✂️✂️

‹‹...እሱን እኮ ነው የምልሽ ...አደገኛ የሆኑ ውስብስብ የማህበራዊ ህይወት ቀውስ የሚያመጡብን ችግሮች ውስጥ መግባታችን አይቀርም ነበር፡፡››

‹‹ያልሻቸው ነገሮች እንደሚከሰቱ አውቃለሁ ... ቢሆንም ግን ምርጫ ቢቀርብልኝ አንቺን
ከማጣት ያንን ፈተና መጋፈጥን እመርጥ ነበር፡፡››

‹‹ይሆናል…ግን አሁን ሁሉም አልፏል ...መሆን ያለበት ሁሉ አሁን እንደሆነው ሆኗል... በመሆኑም ትክክል ነው፡፡››

‹‹እንዳልሽ ይሁን .…እሺ ግን ሳገባ ሚዜ ትሆኚኛለሽ››ዶክተር ነች ተናጋሪዋ፡፡

‹‹በሰርግ ነው እንዴ የምታገቢው?››

‹‹እስከአሁን አልወሰንኩም…. ግን አንድ ሃያ ሰው ጠርቼ የእራት ግብዣም ቢሆን ማድረጌ ይቀራል?››

‹‹ታዲያ ያገባች ሴት እኮ ሚዜ አትሆንም፡፡››

«ለምን?»

‹‹ባህላችን ነዋ...መነሻ ሀሳቡን ባላውቅም ምክንያቱን ስገምት ግን ያላገባች ሴት ሚዜ ስትሆን እግረ መንገዷን የራሷን አዳም የምታገኝበትን ዕድል እንድታመቻች ታስቦ የተቀየሰ ስውር ዘዴ ይመስለኛል፡፡››

‹‹አንቺ ...ትንታኔሽ አሳማኝ ይመስላል..በቃ እንደዛ ከሆነ ሌሎቹን ሁለት ሚዜዎች ያላገቡ እንዲሆኑ አደርጋለሁ ያንቺ ግን የግድ ነው፡፡››ተሳሳቁ፡፡

‹‹ካልሽ ምንቸገረኝ..የእኔን ልጅም ክርስትና ታነሺያለሽ፡፡››

‹‹እንዴ!!! አረገዝሽ እንዴ?››

‹‹አዎ 1 ወር ከ15 ቀን ሆነኝ፡፡››

‹‹ኦ!!! ፈጣሪ የእኔ ቆንጆ እንኳን ደስ አለሽ፡፡›››ከመቀመጫዋ በመነሳት ተጠምጥማባት እያገላበጠች ሳመቻት እና ወደ መቀመጫዋ ተመለሰች፡፡

‹‹ክርስትና ግን ስትይ ..ሁሴን ኦርቶዶክስ ሆነ እንዴ?››

‹‹ኧረ አልሆነም፡፡››

<<እና>>

‹‹ምን እና አለው ..ያው እሱም ሀይማኖት የለሽ እንደሆነ የእኔ ሀይማኖት ደግሞ አለየለትም፡፡››

‹‹ግን በኑሮችሁ ምንም ችግር አልፈጠረባችሁም?››

‹‹ያው እስከ አሁን በፍቅር ጥላ ስር ስለሆንን ችግር አልፈጠረብንም… በሚያስማማን እየተስማማን በልዩነታችን ደግሞ እንደልዩነታችን እየኖርን ነው፡፡ፍቅር እኮ ሁሉንም ክፍተቶችሽን ይደፍንልሻል...ፍቅር ሲሸረሸር ነው ሜዳ ሁሉ ገደል፣ነጩ ሁሉ ጥቁር፣ንግግሩ ሁሉ ጭቅጭቅ መስሎ ሚታይሽ፡፡››
👍7611😁2😢2👎1
#ትንግርት


#ክፍል_ሃምሳ_አራት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


..ከአንዱ ለምኖ ለአንዱ በመስጠት ብልጽግናን ማምጣት አይቻለም::

ለታዲዬስ ፣ትንግርት፣ሁሴን፣ዶ/ር ሶፊያ፣ፎዚያ እና ኤልያስ ዛሬ ልዩ ቀን ነች፡፡ለስድስት ወር የለፉበትን ...እንቅልፍ አጥተው ገንዘባቸውንም ዕውቀታቸውንም ያፈሰሱበት የድርጅታቸው የመጀመሪያ ፍሬ እነሱም የሚያዩበት ለማህበረሰቡም የሚያስተዋውቁበት ቀን ነው፡፡

ዝግጅቱ በሸራተን አዲስ የሚካሄድ ሲሆን የህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር ዲኤታ፣የተለያዩ ሀይማኖት አባቶች፣የኤንባሲ ሰዎች፣ታዋቂ ሙዚቀኞች፣የፊልም አክተሮች፣አትሌቶች፣ነጋዴዎች፣
ለዚህ ድርጅት ከምስረታው እሰከአሁን ከፍተኛ እገዛ ካደረጉት ከየተለያዩ የፌስ ቡክ ግሩፖች የተወከሉ ወጣቶች፣ከተለያዩ ሚዲያዎች የተሰበሰቡ ጋዜጠኞች እና ካሜራ ማኖች..አዳራሹን
ሞልተውታል፡፡

የዛሬው ዝግጅት ዓለማ በዋናነት ሁለት ሲሆን ሌላም አንድ ንዑስ ዝግጅት አለ፡፡መድረኩን የሚመራው ጋዜጠኛ ሁሴን ነው..ማይኩን ይዞ ወደ መድረክ ወጣና ጉሮሮውን ሞርዶ ንግግሩን
ጀመረ::

‹‹ክቡራን እና ክብሯት ጥሪያችንን ተቀብላችሁ እዚህ የተገኛችሁ ሁላችሁም እንዲሁም በየቤታችሁ ሆናችሁ ዝግጅቱን በቀጥታ በቴሌቨዥን ስርጭት እየተከታተላችሁ ያላችሁ በአጠቃላይ በድርጅታችን ስም ምስጋናችንን እያቀረብን እስከፍፃሜውም በፅሞና እንድትከታተሉን እየጠየቅን በቀጥታ ወደ ዝግጅቱ እንገባለን፡፡በቅድሚያ የድርጅታችን መሪ የሆኑት ዶ/ር ሶፍያ ፕሮግራሙን በንግግር እንዲከፍቱልን እንጠይቃለን… ዶ/ርን ወደ መድረክ ሸኙልን፡፡››ዶ/ር ሶፊያ በጭብጨባ ታጅባ ወደ መድረክ ወጣችና ማይኩን ከሁሴን ተቀብላ ንግግሯን ማሰማት ቀጠለች፡፡

‹‹ክቡራን እና ክቡራት የመንግስት ባለስልጣናት፣የሀይማኖት አባቶች፣ከተለያዩ የማህበራት ዘርፎችን በመወከል
የተገኛችሁ፣በየቤታችሁም በመሆን እየተከታተላችሁን ያላችሁ በአጠቃላይ..እንኳን ለዚህች ቀን አደረሰን አላለሁ፡፡

የዛሬው ፕሮግራማችን ሁለት ዓላማዎች አሉት፡፡ አንደኛው የወላጆች እና ልጆች የምረቃ በዓል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ለድርጅታችን የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ነው..እኔ አሁን አትኩሬ የተወሰነ ማብራሪያ ልሰጣችሁ የምፈልገው በመጀመሪያው ላይ ነው..ሁለተኛውን በተመለከተ አቶ ታዲዬስ ቆየት ብሎ ያብራራላችኋል፡፡

እንግዲህ እንደመነሻ ይሆነን ዘንድ የዛሬ አንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን አካባቢ በበጎ ፍቃደኝነት አሳዳጊ የሌላቸውን ህፃናትን እናሳድጋለን ብለው ከተመዘገቡ በብዙ ሺዋች ከሚቆጠሩ ባለቀና ልቦች መካከል ለጊዜው አቅማችንን መሰረት አድርገን 15ዐ ግለሰቦችንና በቡድን ከመጡት መካከል ደግሞ 5ዐ ዎቹን ወደ ስልጠና አስገብተን ነበር፡፡እንግዲህ በአንድ ወር ስልጠና ውስጥ በድርጅቱ ህግና የስልጠና ማኑዋል የተሰጣቸውን ስልጠና በመከታተል ከ15ዐ ዎቹ ግለሰቦች መካከል 43 በቡድን ሆነው ከመጡት መካከል ደግሞ 31 መስፈርቱን ማሟላት ስላልቻሉ ከይቅርታ ጋር እንደ ፍላጎታቸው ህፃናትን እንዲያሳድጉ ልንፈቅድላቸው አልቻልንም፡፡የተቀሩት እንግዲህ ብቁ ሆነው በመገኘታቸው እንሆ ዛሬ በእናንተ ፊት መርቀን ልጆቻቸውን በአደራ እናስረክባቸዋለን፡፡››

የደመቀ ጭብጨባ ከአዳራሹ...ቀጠለች ዶ/ር ‹‹ዛሬ አሁን ለነገርኳችሁ ወላጆች የምናስረክባቸውን ልጆችም ለ3 ወር በካምፕ በማስገባት ስልጠና ሰጥተናቸዋል፡፡ልዩነቱ ህፃናቱን አንዴ ወደ ማሰልጠኛ ካስገባናቸው:: የምንፈልገውን ብቃት እስክናገኝባቸው ድረስ የፈጀውን ያህል ይፍጅ እንለፋባቸዋለን፡፡ ልጆቹን ከበሸቀጠ የድህነት መንደር እንዲሁም በስነ- ምግባር እና በሞራል ከዘቀጠ ጎዳና ላይ ነው የምንሰበስባቸው፤አመላቸውን ማረቅ፣ ስነ- ልቦናቸውን መገንባት፣ጤንነታቸውን ማስተካከል፣ ተስጥኦቸውን ለይቶ ማወቅ፤ወዘተ እንደሀሳባችን እስክናሳካ 3 ወር ፈጀብንም ሶስት
አመት ተስፋ አንቆርጥባቸውም፡፡ የራሱ ጉዳይም ብለንም እርግጠኛ ባልሆንበት ሁኔታ ለአሳዳጊ ወላጅ አሳልፈን አንሰጣቸውም፡፡ይህ ነው ልዩ የሚያደርገን.. እንጂማ መአት በህፃናት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች እንዳሉ እናውቃለን...፡፡.››

ወላጅ ለመሆን ስልጠናውን ወስደው መስፈርቱን አላሟላችሁም ብለን ከመለስናቸው ውስጥ የተወሰኑት በጣም ተበሳጭተውብን ነበር፤ላሳድግ ባልኩ መልካም ልስራ ባልኩ እንዴት እከለከላለሁ?የሚል መከራከሪያ ሀሳብ
ነበራቸው፡፡ግን እኛም ያንን ስናደርግ እያዘንን ነው... እየገነባን ያለነው የወደፊቱን ትውልድ
ነው፡፡አንድ ሰው ገንዘብና ፍላጎት ስላለው ብቻ ዝግጁ የሆነ ስነልቦና እንዲሁም የወላጅ ባህሪ
ሳይኖረው ልጅን ያህል ነገር አሳድግ ብለን አንስተን አንሰጠውም..በፍፁም እንደዛ
አናደርግም፡፡በእኛ መአከል ሰልጥነው ልጅ የተረከቡ ሰዎች በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት
ከዚህ ከእኛ ጋር ለወሰዷቸው ልጆችም ብቻ ሳይሆን ከአብራካቸው ለወጡትም
ህፃናት፣ለዘመዶቻቸው ልጆች ፣ለጎረቤቶቻቸው ልጆችም ያገኙትን ዕውቀት እንዲጠቀሙበት
እንፈልጋለን፡፡አርአያ እንዲሆኑበት እንፈልጋለን፡፡ ለዛ ነው ማኑዋሉንም አዘጋጅትን ለእያንዳንዱ ያደልነው፡፡

‹‹ልጅ ማሳደግ ማብላትና ማጠጣት ብቻ ሳይሆን..የወደፊት የህይወት ዓላማቸውን፤ ተሰጥኦዋቸውን ከስር ከመሰረቱ እያጎለበቱ መንገድ ማስያዝን ይጠይቃል፡፡ ይሄንን ነው ጠቅላላ የሀገራችን ወላጆች ሊከተሉት የሚገባው መንገድ፡፡ ህብረተሰቡም እንደህብረተሰብ...መንግስትም እንደመንግስት የየራሳቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ እጠይቃለሁ፡፡ አመሰግናለሁ፡፡ አሁን ቀጥታ ወደ ምረቃ በዓሉ እንሄዳለን፤ ክብር የህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር ዲኤታ ለተመራቂ ወላጅ እና ህፃናት የምስክር ወረቀት ይሰጡልን ዘንድ እንጠይቃለን፡፡››

ሚንስቴሩ በሙሉ ሱፍ ሽክ ብለው በከረባት እንደታነቁ በተጀነነ እርምጃ ወደ መድረክ ወጥተው ከዶ/ር ጎን ቆሙ ፡፡ሁሴን የተመራቂዎቹን ስም ተራ በተራ ሲጠራ ወላጆቹ ከተረከቧቸው ህጻናት ጋር በመምጣት የምስክር
ወረቃታቸውን እየወሰዱ ወደ መቀመጫቸው ይመለሳሉ፡፡ ከነዚህ ተመራቂዎች ውስጥ..ሰሎሞንና የውብዳር አንድ ወንድ ልጅ(እነሱ የጠየቁት ሁለት ቢሆንም በታዲዬስ የሚመራው ቴክኒክ ብድን ግን በዚህ በአንዱ ልጅ ላይ የሚያሳዩት አፈፃፀም ታይቶ ከአመት በኃላ ሌላ ልጅ ሊጨመርላቸው ይችላል እንጂ አሁን ባለው ሁኔታ ከአንድ ልጅ በላይ አይፈቀድላችሁም በማለት ከለከሏቸው) ሌላው..ዶር ሶፊያና ከፕ/ዬሴፍ ጋር አንድ ሴት ልጅ፣ፎዚያ እና ኤልያስ አንድ ሴት ልጅ፣ፅዮን እና ዓላዛር ..ትንግርት እና ሁሴን አንድ ልጅ በመረከብ ከራሳቸው በመጀመር አርዓያነታቸውን አሳይተዋል፡፡

የምስክር ወረቀት የመስጠት ፕሮግራም ሲጠናቀቅ የክብር እንግዳውንና ዶ/ር ሶፊያ መድረኩን ለቀው ወደ መቀመጫቸው ሄዱ.... ሁሴን ቀጣዩን ፕሮግራም ማስተዋወቅ ጀመረ…፡፡

‹‹ክብሯን እንግዶች ወደ ቀጣዩ ፕሮግራማችን ከመሸጋገራችን በፊት የሙዚቃ እረፍት

እናደርጋለን..ድምፃዊ ሀሊማ እና ሄለን ወደ መድረክ፡፡››

በአካልም በየቤቱም እየተከታተሉ ያሉ አይኖቻቸውን ወደ መድረኩ ላኩ፡፡

የተባሉት ሙዚቀኞች ወደ መድረክ ሲመጡ ታዩ …ሀሊማ ጊታሯን ይዛ ወንበር ስባ ተቀመጠችና ማይኩን ወደ አፏ አስተካክላ አመቻቸች፡፡ሄለን ወደ ፒያኖው አመራች፡፡አብዛኛው ህዝብ አስታወሳቸው፡፡ ባለፈውም በቴሌቨዥን ቃለ መጠየቅ የተደረገላቸው ጊዜ ብቃታቸውን አሳይተዋል፤በአይድል ውድድርም እንደዛው…፡፡ ጀመሩ ሄለን ፒያኖውን ስታናግረው ሀሊማ ጊታሯን እየተጫወተች በድምጿም ታንቆረቁር ጀመር..
👍6413
#ትንግርት


#ክፍል_ሃምሳ_አምስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ሁሴን ተቀበለውና ቀጠለ <<ታዲዬስ ባለው ነገር ላይ ምንም አልጨምርም.. ቀጥታ ወደ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሙ ገብቼያለሁ፡፡እዚህም ያላችሁ በመላው ዓለም የምትገኙ አላማችንን የምትደግፉ በስልክም በኢሜልም ሆነ በተመቻችሁ ዘዴ ቃል መግባት ትችላላችሁ ... ከዛ በፊት ግን ይሄንን ዝግጅት የምንጀምረው፤በስጦታ ነው፡፡ስጦታውን የምትሰጠን ሰዓሊ ሰላም ነች.. ሰዓሊ ሰላም ወደ መድረክ…፡፡››

ሰላም ሸንከል ሸንከል እያለች ወደ መድረክ ስትወጣ ትንግርት ከኃላዋ 120 ሳ.ሜ በ 60 ሳ.ሜ ስፋት ባለው በሸራ ላይ የተሳለ ስዕል ይዛ ተከትላት ወጣች፡፡ስዕሉ ለህዝብ እይታ ቀረበ፡፡

<<እኛ ለእኛ›› የሚል ርዕስ አለው፡፡

አንድ ህፃን የተቦተራረፈ ልብስ እና የቆሸሸ ፊት ይዞ አስፓልት ዳር ከሚገኝ የቆሻሻ መጣያ ገንዳ
ጠርዝ ላይ ቂቢብ ብሎ በመውጣት ሞልቶ በመትረፍ አካባቢውን ሙሉ ከሸፈነው ቆሻሻ ላይ የተጣለ ምግብ ጎንበስ ብሎ የሚፈልግ ይመስላል፤አንደኛው እጁ ግን ወደ አስፓልቱ ተቀስሯል፤በተቀሰረው እጁ አቅጣጫ የቆመች የቤት መኪና ትታያለች፣ከመኪናዋ ውስጥ አንድ በተመሳሳይ ዕድሜ ላይ የሚገኝ የፀዳ ልብስ የለበሰና የተመቸው ህፃን በመስኮት ተንጠራርቶ መፅሀፍ እና ዳቦ ለጎስቆላው ልጅ ሊያቀብለው ሲንጠራራ ያሳያል፡፡

ሁሴን ቃላ መጠየቅ ሊያደርጋት ወደ ሰላም ተጠጋ

‹‹ስምሽን ብታስተዋውቂን?››

‹‹ሰላም እባላለሁ..ሰላም ታዲዬስ፡፡››

‹‹ሰላም እሺ ..…ለምንድነው ወደዚህ መድረክ የወጣሽው?››

‹‹ይሄንን ስዕል ለድርጅቱ በስጦታ ላማበረክት፡፡››

‹‹በጣም ጥሩ ነው ..ማነው የሳለው?››

<<እኔ ነኛ፡››

‹‹ለምን ርዕሱን ..እኛ ለእኛ አልሽው?››

‹‹ለእኛ ከእኛ ውጭ ማንም ስለሌለ ነዋ...ታዲዬስ አባት ባይሆነኝ እኔ ይሄኔ እዚህ

መድረክ ላይ ሳይሆን ሀዋሳ መንገድ ዳር ቁራሽ ዳቦ መግዣ ሳንቲም እየለመንኩ ነበር
ምታገኙኝ…..እባካችሁ የኢትዮጰያ ህዝቦች በጠቅላላ መጥናችሁ ውለዱ፤ልመና የሞራል
ነቀርሳ ነው ማንም ህፃን እንዲለምን አትፍቀዱ፤ጎዳናዎች ከቦታ ወደ ቦታ መተላለፊያዎች እንጂ ፈጽሞ የህጻናት መኖሪያዎች መሆን የለባቸውም፤ታዲ አባቴ ከዛ
የጎዳና ሰቆቃ አውጥተህ ሰው ስላደረግከኝ አመሰግንሀለው እሺ ... ደግሞ በጣም ነው
የምወድህ....ሁላችንም ልጆችህ
እንወድሀለን..ሁሉም የዓለም አባቶች እንደ አንተ እንዲሆኑ እንፈልጋለን..››ይሄን ስትናገር እንባዋን መግታት ስላልቻለች መድረኩ ጥላ ወረደች..አዳራሹን የሞላው ህዝብ ዓይኞች ሁሉ
በዕንባ ፈሳሽ ተሞሉ፡፡ሁሴን ከደቂቃዎች ዝምታ በኃላ መናገር
ጀመረ‹‹እሺ ሰላምን እንደሰማችኋት ይሄንን በነዛ
ትናንሽ እጆቿ የተሳለውን ድንቅ ስዕሏን በስጦታ አቅርባልናለች.. እናም ለጨረታ እናቀርበዋለን..፡፡
ሰላም ማለት የታዲዬስ ልጅ ነች..ቅድም ልዩ ጥኡመ ዜማ ለጆሮችን ያሰሙን ሀሊማ እና
ሄለንም የታዲዬስ ልጆች ናቸው፤ሚጡና ሙሴ
የሚባሉም ልጆች አሉት...በተለይ ሙሴ የልጅ ሳይንቲስት ነው…ስለሱ ሳስብ ምን እንደሚታሰበኝ ታውቃላችሁ ሰው ከሞተ በኋላ
ነፍሱ በሌላ ሰው አካል ሆና ዳግም ወደዚህ ምድር ትመጣለች የሚል እምነት የሚያራምዱ
ማህበረሰቦች አሉ ፤ያ እምነት እውነት ከሆነ የታዲዬስ ልጅ የሆነው ሙሴ የቶማስ ኤዲሰንን
ነፍስ ይዞ ለኢትዬጵያውያን ተስፋ ሊሆን የተፈጠረ ሳይሆን አይቀርም ብዬ እጠረጥራለሁ…. በአጠቃላይ ቅድም ታዲዬስ
የተናገረው ንግግር ለመናገር ብቻ ሳይሆን እሱ በተግባር ስለፈተነው ህጻናትን ከመሰረቱ ኮተኩተን ካሳደግናቸው ገና ከጥዋቱ ፍሬያቸው እንደምናይ ስላረጋገጠ ነው..፡፡

አሁን ወደ ሰላም ሥዕል ጨረታ እንግባ..በነገራችን ላይ ከዚህ ፕሮግራም በኋላ የሰላምን ሌሎች ድንቅ ስዕሎችን ማየት ከፈለጋች በሚቀጥለው ክፍል ጎራ በሉ..(ይሄንን ሲናገር በየቤታቸው ሆነው ዝግጅቱን በቴሌቨዠን ለሚከታተሉት ካሜራው የሰላም ስዕል ወደ ሚገኙበት ክፍል በማዞር ማስቃኘት ጀመረ ..13 የሚሆኑ የተለያየ ርዕስ እና መጠን ያላቸው ስዕሎች በግድግዳው ላይ ተሰባጥረው ለዕይታ ምቹ ሆነው ተሰቅለው አሳየ፡፡

ሰላም ለድርጅቱ በስጦታ ያበረከተችው ስዕል ከሸራተን ሆቴል አልወጣም..በሼኩ ትዕዛዝ ይመስላል በ1ዐዐ ሺ ብር መነሻ የተጀመረውን ጫረታ ፉክክር ዝግጅቱ ላይ ታድመው የነበሩት የሜድሮኩ ስራ አስኪያጅ በሁለት ሚሊዬን ብር እዛው አስቀሩት..ድርጅቶችም ግለሰቦችም ያቅማቸውን ወረወሩ..አጠቃላይ ቃል የተገባውና እጅ በእጅ የተሰጠው በድምሩ 25 ሚሊዬን ብር ሆነ፡፡

ሁሴን ፕሮግራሙን ወደ ሶስተኛው ዝግጅት ሊያሸጋግር ፈለገ‹‹ቅድሚያ ግን ሄለን እና ሀሊማ ወደ መድረክ ዳግም እንዲወጡ አደረገ...የቴዲ አፍሮን ላምባዲና ነው ያቀረቡት፤ ልክ እንዳጠናቀቁ ሁለተኛውን ሙዚቃ ሊቀጥሉ ሲሉ ትንግርት በምልክት አስቆመቻቸው እና ወደ መድረክ ወጣች ፡

‹‹ይቅርታ ለየት ያለ ዜና በስልክ ስለደረሰኝ ነው ወደ መድረክ የወጣሁት..ቴዲ አፍሮ ከሄለን እና ሀሊማ ጋር አዲስ አበባ ላይ አንድ ኮንሰርት በማዘጋጀት ገቢውን ለድርጅቱ እንዲሚያስገባ ነግሮናል.. ለጊዜው 1ዐዐ ሺ ብርም በአካውንታችን ዛሬውኑ እንደሚያስገባ አብስሮናል፤እንግዲህ እዚህ ዝግጅት ላይ የታደሙ ድምጻዊያኖቻችን እና ኮሜዲያኖችም ቅድም እንደሰማችሁት አንድ ኮንሰርት እንደሚያዘጋጁልን ቃል ገብተው ነበር..ይሄ ሁለተኛ ኮንሰርት መሆኑ ነው፡፡እናመስግናለን ››ብላ ወረደች፡

..በዚህ ዜና በጣም የፈነጠዙት ሀሊማ እና ሄለን ናቸው ፤ከሚወዱትና ከሚያደንቁት ለእነሱ እንደ ህልም ከሆነው ቴዲ አፍሮ ጋር በአንድ መድረክ ሊሰሩ ነው..በደስታ በተጥለቀለቀው ስሜታቸው የሚቀጥለውን ሙዚቃ መጫወት ጀመሩ.. የሰርግ ዘፈን ነው‹‹..ሙሽራዬ ሙሽራዬ ... የወይን አበባዬ››ሙዚቃውን ተከትሎ ከጀርባ ካለው በር ወደ መድረክ ሲወጣ የታየው ታዲዬስ ነው፡፡ ቅድም ከለበሰው ልብስ በተለየ አለባበስ ሙሉ ሱፍ ለብሶ ቀኝ እግሩን አስቀድሞ ታየ.. ከኃላው ነጭ የተንዘረፈፈ ቬሎ የለበሰች ወጣት ተከትላዋላች... ርብቃ ነኝ..፡፡እጅ ለእጅ ተቆላልፈው በዝግታ እርምጃ ሙሉ በሙሉ ወደ መድረኩ ወጡ…ጥጉን ይዘው እንደተጣበቁ ቆሙ፡፡

ሙዚቃው እንደቀጠለ ነው..ሌሎች ጥንዶች በተመሳሳይ ሁኔታ በተመሳሳይ አለባበስ ወጡ ዶ/ር ሶፊያ እና ፕ/ዬሴፍ ናቸው፡፡ ከነ ታዲዬስ ጎን ቆሙ..አሁንም ሌላ ጥንዶች ተከተሉ ፎዚያና ኤልያስ(የእነ ኤልያስ ጋብቻ ልዩነታቸውን በምን ሁኔታ ፈተው ወይም ለመፍታት ተስማምተው ለዚህ ጥምረት እንደበቁ ለጊዜው ከጥንዶቹ በስተቀር ማንም የሚያውቅ ሰው የለም) ህዝብ ከፍተኛ መደመም ወስጥ ገብቷል..በመጨረሻ ጥንድ ሆነው የወጡት የነ ሀሊማ የሙዚቃ አስተማሪዋ አይነ ስውሯ ፅዬን እና የሰላም የስዕል አስተማሪው ዓልዓዛር ናቸው፡፡ሙዚቃው አልቆ ተቋረጠ..ከዛ አምስቱም የታዲዬስ ልጆች ከያሉበት ወደመድረክ ወጡና ታዲዬስን እና አዲሷን እናታቸውን ርብቃን ከበው ቆሙ..በተመሳሳይ ሌሎች ጥንዶችም ዛሬ ለማሳዳግ የተረከቧቸው ልጆች ወደ መድረክ ወጥተው በእያንዳንዱ ጥንዶቹ መካከል በፈገግታ ቆሙ..ህዝቡ በደስታ እና በዕልልታ አዳራሹን አደበላለቀው፡፡

ሁሴን ወደ መድረኩ ወጣና መናገር ጀመረ….
👍7715🤔2👎1