‹‹ስራ አግኝቻለሁ እርዳታ አልፈልግም››
እናት ይህን ሲሰሙ ተገረሙ: ‹‹አሜሪካ ውስጥ? እንዴት››
ማርጋሬት ስለናንሲ ሌኔሃን ልትነግራቸው አትፈልግም:፡ ስራ የምትሰጣት ናንሲ መሆንዋን ካወቁ ከእሷ ጋር ተነጋግረው ሁሉንም ነገር
ያበላሹባታል፡ ‹‹ሁሉም ነገር አልቋል›› አለች በደፈናው፡፡
‹‹ምንድነው ያገኘሽው ስራ?›› እናት ጠየቁ፡፡
‹‹በጫማ ፋብሪካ ውስጥ የሽያጭ ረዳትነት››
‹‹ወይ አምላኬ! አበድሽ ይህን አይነት ስራ የምትሰሪው?››
ማርጋሬት በንዴት ከንፈሯን ነከሰች፡፡ ለምንድነው እናቷ ስራ እንዲህ የሚንቁት? ‹‹እኔ አላበድኩም እንደውም በዚህ አስተሳሰቤ እኮራለሁ›› አለች ማርጋሬት፡
‹‹ፋብሪካው የት ነው የሚገኘው?››
‹‹ፋብሪካ ውስጥ እንደሆነ አትሰሪም፤ በቃ!›› ሲሉ አባት ለመጀመሪያ
ጊዜ ተናገሩ፡
‹‹በሽያጭ ክፍል ውስጥ ነው የምሰራው፧ ፋብሪካ ውስጥ አይደለም፡፡
ደግሞም ቦስተን ውስጥ ስለሆነ ችግር የለም›› አለች ማርጋሬት፡
‹‹ያ ከሆነ ጥሩ ነው›› አሉ እናት፡ ‹‹የምትኖሪው ግን ስታንፎርድ ነው
እንጂ ቦስተን ውስጥ አይደለም››
‹‹አይሆንም እማ ቦስተን ነው የምኖረው፡፡ ትቼያችሁ ወደ ቦስተን ልሄድ መሆኑን እወቁት ነው የምለው፡፡ እዚያ ቤት ተከራይቼ ነው
የምኖረው››
‹‹ይሄ የማይሆን ነው›› አሉ እናት፡፡
ማርጋሬት በንዴት ተንጨረጨረች
አታጣጥዪ እማ›› አለች ከጣራ በላይ እየጮኸች፡፡ እሷ ስትጮህ እናቷ ስለደነገጡ ጸጸት ተሰማት፡ ‹‹በኔ ዕድሜ ወጣት ሴቶች የሚያደርጉትን ነው እኔ የማደርገው›› ስትል አከለች ቀስ ብላ።
አዎ በአንቺ ዕድሜ ያሉ ወጣቶች እንዲህ ነው የሚያደርጉት፡ እንዳንቺ ያሉ የጌታ ልጆች ግን አይሞክሩትም›› አሉ እናት፡፡
‹‹ታዲያ እኔ ከሌሎቹ በምን እለያለሁ?››
ብሳምንት አምስት ዶላር እየተከፈለሽ ለምትሰሪው ስራ አባትሽ መቶ
ዶላር የሚከፍልበት ምክንያት የለም››
‹‹አባባ ለቤት ኪራይ እንዲከፍልልኝ አልፈልግም››
‹‹ታዲያ የት ልትኖሪ ነው?››
‹‹ኪራይ ቤት ውስጥ አልኩሽ እኮ እማ››
‹‹የድሆች መኖሪያ ውስጥ! ግን ምን ታተርፊያለሽ?››
‹‹ወደ አገሬ መመለሻ ገንዘብ እስኪሞላልኝ ድረስ ገንዘብ አስቀምጣለሁ፡፡
ከዚያም ጦሩን እቀላቀላለሁ›› አለች ማርጋሬት፡
‹‹ስለምትናገሪው ምንም የምታውቂው ነገር የለም›› አሉ አባት፡፡
ማርጋሬት ንዴት ጠቅ አደረጋትና ‹‹ምንድነው የማላውቀው ነገር
አባባ?›› ስትል ጠየቀች:
እናት ጣልቃ ገቡና ‹‹አዎ የምታውቂው ነገር የለም›› አሉ፡
ማርጋት የእናቷን ንግግር አቋረጠችና ‹‹ቢሮ ውስጥ መላላክ፣ ቡና ማፍላትና ስልክ ማገናኘት አያቅተኝም፡፡ አንድ ክፍል ውስጥ እንደምኖር፣
መጸዳጃ ቤት ከሌሎች ጋር በጋራ እንደምጠቀም አውቃለሁ ደሃ መሆን
ባልፈልግም ነጻ ሆኜ መኖር ግን ያስደስተኛል›› አለች፡፡
‹‹ምንም የምታውቂው ነገር እኮ የለም›› አሉ አባት በንቀት ‹‹ነጻነት?
አንቺ? ከማጎሪያ እንደተለቀቀች ጥንቸል ነው የምትሆኚው ልጅት! ዕድሜሽን ሙሉ ተሞላቀሽ ስላደግሽ ብልሹ ልጅ ሆነሻል፡ ትምህርት እንኳን
አልተማርሽም›› አሉ፡፡ አባቷ በመጨረሻ የተናገሩት ነገር እንዴት ወደ ኋላ
እንዳስቀራት ስላስታወሳት በንዴት ‹‹እኔ መማር እፈልግ ነበር አንተ ነህ
ከትምህርቴ አስቀርተህ እንደዚህ መሀይም ያደርግኸኝ›› አለች፡፡
‹‹ልብስሽ እየታጠበልሽ፣ ምግብሽ እየተዘጋጀልሽ፣ የምትሄጅበት ቦታ
ሁሉ ሾፌር እያመላለሰሽ፣ ሌላው ቢቀር ከቤት እንዳትወጪ ሲባል የጎረቤት
ልጆች እየመጡ እያጫወቱሽ ነው ያደግሽው፡፡ ይሄ ሁሉ እንዴት እንደሚደረግልሽ እንኳን ሳታውቂ ነው ያደግሽው፡ አንድ ዳቦ ስንት
እንደሚያወጣ እንኳን ሳታውቂ ብቻዬን ልኖር ነው ትችያለሽ›› አሉ አባት
ምርር ብለው፡፡
‹‹ብቻዬን ስኖር ይህን ሁሉ በሂደት ማወቅ እችላለሁ››
‹‹ፓንትሽን እንኳን ማጠብ አትችይም፡፡ በአውቶብስ ተሳፍረሽ አታውቂም፡፡ አንድ ቤት ውስጥ ለብቻሽ ተኝተሽ አታውቂም፡፡ የመቀስቀሻ ሰዓት እንዴት እንደሚሞላ፣ ወጥመድ እንዴት እንደሚጠመድ፣ሰሃን
ማጠብ፣ እንቁላል መጥበስ አታውቂም››
‹‹ታዲያ ይሄ የማን ጥፋት ነው? ይሄን ሁሉ እንዳላውቅ ያደረግኸኝ አንት አይደለህም ወይ?›› አለች ማርጋሬት እያለቀሰች፡
አባት ፊታቸውን እንዳቀጨሙ ‹‹ቢሮ ውስጥስ ምን ልትጠቅሚ
ትችያለሽ? ሻይ ማፍላት እንኳን አታውቂ፤ ከጧቱ ሶስት ሰዓት እስከ አስር
ሰዓት ድረስ ቆመሽ መስራት አትችይ ይግረምሽና ሳምንት እንኳን
አትቆይም፧ ጥለሽው ትወጫለሽ፡፡››
ማርጋሬት ሲያስጨንቃት የነበረውን ነገር አባቷ ሲነግሯት ሆዷ በብስጭት ታመሰ፡፡ አባቷ ያሉት እውነት መሆኑን ስታስበው ፍርሃት
ፍርሃት አላት፡ ብቻዋን መኖር ሳያስጨንቃት አልቀረም: አንድ ስህተት
ሰርታ ወይም መስራት አቅቷት ከስራዋ ልትባረር ትችላለች፡፡ አባቷ በምሬት
የተናገሩት ነገር ወደፊት ሊሆን እንደሚችል ሳትገምት አልቀረችም:
የወደፊት ራዕይዋን የሚንድባት መሰላት፡፡
እምባዋን በጉንጮቿ
እየተንዥቀዥቀ አነባች፡:
አባቷ ጣታቸውን እያወዛወዙና ከጣራ በላይ እየጮሁ ‹‹ቦስተን ከተማ
እንደ ኦክሰንፎርድ መንደር እንዳይመስልሽ፡፡ እዚያ ብትነሺ ብትፈርጪ
የሚረዳሽ የለም፡ በዘረቢሶች ልትመረዢ ትቺያለሽ፡፡ ይሁዳውያን ቤት
በረንዳ አዳሪ ኔግሮዎች አስገድደው ይደፍሩሻል፡፡ ጦሩን እቀላቀላለሁ ላልሺው.›› ሲሉ አቋረጠቻቸውና፣
‹‹በሺህ የሚቆጠሩ እንደኔ ያሉ ወጣት ሴቶች ጦሩን ተቀላቅለዋል›› አለች ማርጋሬት እምባ በተናነቀው ድምጽ።
‹‹ታዲያ እነሱ አንዳንቺ ያሉ ሴቶች አይደሉም፡፡ እነሱ ጠንካራ ሴቶች ናቸው፡፡ እነሱ በጧት ተነስተው የጉልበት ስራ መስራት የሚችሉ ናቸው እንጂ እንዳንቺ ተሞላቀው ያደጉ ልፍስፍሶች አይደሉም፡፡ እግዜር አያድርገውና አንድ ችግር ቢደርስብሽ ዋጋ የለሽም›› አሉ አባት፡
ማርጋሬት ባለፈው ከቤት ጠፍታ የሄደች ጊዜ እንዴት እግሯ እንደተሳሰረ፣ ምን ያህል እንደፈራችና አቅመቢስ እንደነበረች ስታስታውስ በእፍረት ትሸማቀቃለች፡፡ በአንድ በኩል አባቷ እውነታቸውን ነው፡፡
አባቷ ጣታቸውን ወደ እሷ እየቀሰሩ ዓይናቸው ተጎልጉሎ የወጣ
እስኪመስል ድረስ አፍጥጠው ‹‹በቢሮ ስራውም ሆነ በጦሩ ውስጥ ሳምንት እንኳን ከቆየሽ ከምላሴ ጠጉር ይነቀል፤ ልፍስፍስ ነሽ›› አሉና በተናገሩት
ረክተው ቁጭ አሉ፡
ከዚያም ሄሪ ከየት መጣ ሳይባል ‹‹ይበቃል!›› ሲል ተሰማ፡ ይሄ የእሷና
የአባቷ ጉዳይ ቢሆንም ፍቅረኛው ስትሰደብ አላስችለው ብሎ ከጎኗ ሊቆም ደረሰላት፡፡ ሄሪ አጠገቧ መጥቶ ቁጭ አለና መሃረቡን አውጥቶ በእምባ
የረጠቡ ጉንጮቿን አበሰላት፡
አባትም ‹‹አንተ ወጠጤ · ›› ብለው ለመናገር ያሰቡትን ተናግረው ሳይጨርሱ ሄሪ ከመቀመጫው ተነሳና ‹‹እኔ ሴት ወይም ልጅ አይደለሁም፧ ከዚህ በኋላ ቢሰድቡኝ በቡጢ ነው የማንገጫግጮት›› አላቸው፡
አባት በዚህ ጊዜ አደብ ገዙ፡:
ሄሪ ተመልሶ ማርጋሬት ጎን ቁጭ አለ፡፡
ማርጋሬት ብትደናደድም በሆዷ ድል እንዳደረገች ይሰማታል፡፡ ትታቸው
እንደምትሄድ ነግራቸዋለች፡ ምንም እንኳን ቢቆጧትም፣ ቢያፌዙባትም፣
ቢያስለቅሷትም ከአቋሟ ንቅንቅ አላደረጓትም፡፡ ለመሄድ ቆርጣለች፡፡
እናት ይህን ሲሰሙ ተገረሙ: ‹‹አሜሪካ ውስጥ? እንዴት››
ማርጋሬት ስለናንሲ ሌኔሃን ልትነግራቸው አትፈልግም:፡ ስራ የምትሰጣት ናንሲ መሆንዋን ካወቁ ከእሷ ጋር ተነጋግረው ሁሉንም ነገር
ያበላሹባታል፡ ‹‹ሁሉም ነገር አልቋል›› አለች በደፈናው፡፡
‹‹ምንድነው ያገኘሽው ስራ?›› እናት ጠየቁ፡፡
‹‹በጫማ ፋብሪካ ውስጥ የሽያጭ ረዳትነት››
‹‹ወይ አምላኬ! አበድሽ ይህን አይነት ስራ የምትሰሪው?››
ማርጋሬት በንዴት ከንፈሯን ነከሰች፡፡ ለምንድነው እናቷ ስራ እንዲህ የሚንቁት? ‹‹እኔ አላበድኩም እንደውም በዚህ አስተሳሰቤ እኮራለሁ›› አለች ማርጋሬት፡
‹‹ፋብሪካው የት ነው የሚገኘው?››
‹‹ፋብሪካ ውስጥ እንደሆነ አትሰሪም፤ በቃ!›› ሲሉ አባት ለመጀመሪያ
ጊዜ ተናገሩ፡
‹‹በሽያጭ ክፍል ውስጥ ነው የምሰራው፧ ፋብሪካ ውስጥ አይደለም፡፡
ደግሞም ቦስተን ውስጥ ስለሆነ ችግር የለም›› አለች ማርጋሬት፡
‹‹ያ ከሆነ ጥሩ ነው›› አሉ እናት፡ ‹‹የምትኖሪው ግን ስታንፎርድ ነው
እንጂ ቦስተን ውስጥ አይደለም››
‹‹አይሆንም እማ ቦስተን ነው የምኖረው፡፡ ትቼያችሁ ወደ ቦስተን ልሄድ መሆኑን እወቁት ነው የምለው፡፡ እዚያ ቤት ተከራይቼ ነው
የምኖረው››
‹‹ይሄ የማይሆን ነው›› አሉ እናት፡፡
ማርጋሬት በንዴት ተንጨረጨረች
አታጣጥዪ እማ›› አለች ከጣራ በላይ እየጮኸች፡፡ እሷ ስትጮህ እናቷ ስለደነገጡ ጸጸት ተሰማት፡ ‹‹በኔ ዕድሜ ወጣት ሴቶች የሚያደርጉትን ነው እኔ የማደርገው›› ስትል አከለች ቀስ ብላ።
አዎ በአንቺ ዕድሜ ያሉ ወጣቶች እንዲህ ነው የሚያደርጉት፡ እንዳንቺ ያሉ የጌታ ልጆች ግን አይሞክሩትም›› አሉ እናት፡፡
‹‹ታዲያ እኔ ከሌሎቹ በምን እለያለሁ?››
ብሳምንት አምስት ዶላር እየተከፈለሽ ለምትሰሪው ስራ አባትሽ መቶ
ዶላር የሚከፍልበት ምክንያት የለም››
‹‹አባባ ለቤት ኪራይ እንዲከፍልልኝ አልፈልግም››
‹‹ታዲያ የት ልትኖሪ ነው?››
‹‹ኪራይ ቤት ውስጥ አልኩሽ እኮ እማ››
‹‹የድሆች መኖሪያ ውስጥ! ግን ምን ታተርፊያለሽ?››
‹‹ወደ አገሬ መመለሻ ገንዘብ እስኪሞላልኝ ድረስ ገንዘብ አስቀምጣለሁ፡፡
ከዚያም ጦሩን እቀላቀላለሁ›› አለች ማርጋሬት፡
‹‹ስለምትናገሪው ምንም የምታውቂው ነገር የለም›› አሉ አባት፡፡
ማርጋሬት ንዴት ጠቅ አደረጋትና ‹‹ምንድነው የማላውቀው ነገር
አባባ?›› ስትል ጠየቀች:
እናት ጣልቃ ገቡና ‹‹አዎ የምታውቂው ነገር የለም›› አሉ፡
ማርጋት የእናቷን ንግግር አቋረጠችና ‹‹ቢሮ ውስጥ መላላክ፣ ቡና ማፍላትና ስልክ ማገናኘት አያቅተኝም፡፡ አንድ ክፍል ውስጥ እንደምኖር፣
መጸዳጃ ቤት ከሌሎች ጋር በጋራ እንደምጠቀም አውቃለሁ ደሃ መሆን
ባልፈልግም ነጻ ሆኜ መኖር ግን ያስደስተኛል›› አለች፡፡
‹‹ምንም የምታውቂው ነገር እኮ የለም›› አሉ አባት በንቀት ‹‹ነጻነት?
አንቺ? ከማጎሪያ እንደተለቀቀች ጥንቸል ነው የምትሆኚው ልጅት! ዕድሜሽን ሙሉ ተሞላቀሽ ስላደግሽ ብልሹ ልጅ ሆነሻል፡ ትምህርት እንኳን
አልተማርሽም›› አሉ፡፡ አባቷ በመጨረሻ የተናገሩት ነገር እንዴት ወደ ኋላ
እንዳስቀራት ስላስታወሳት በንዴት ‹‹እኔ መማር እፈልግ ነበር አንተ ነህ
ከትምህርቴ አስቀርተህ እንደዚህ መሀይም ያደርግኸኝ›› አለች፡፡
‹‹ልብስሽ እየታጠበልሽ፣ ምግብሽ እየተዘጋጀልሽ፣ የምትሄጅበት ቦታ
ሁሉ ሾፌር እያመላለሰሽ፣ ሌላው ቢቀር ከቤት እንዳትወጪ ሲባል የጎረቤት
ልጆች እየመጡ እያጫወቱሽ ነው ያደግሽው፡፡ ይሄ ሁሉ እንዴት እንደሚደረግልሽ እንኳን ሳታውቂ ነው ያደግሽው፡ አንድ ዳቦ ስንት
እንደሚያወጣ እንኳን ሳታውቂ ብቻዬን ልኖር ነው ትችያለሽ›› አሉ አባት
ምርር ብለው፡፡
‹‹ብቻዬን ስኖር ይህን ሁሉ በሂደት ማወቅ እችላለሁ››
‹‹ፓንትሽን እንኳን ማጠብ አትችይም፡፡ በአውቶብስ ተሳፍረሽ አታውቂም፡፡ አንድ ቤት ውስጥ ለብቻሽ ተኝተሽ አታውቂም፡፡ የመቀስቀሻ ሰዓት እንዴት እንደሚሞላ፣ ወጥመድ እንዴት እንደሚጠመድ፣ሰሃን
ማጠብ፣ እንቁላል መጥበስ አታውቂም››
‹‹ታዲያ ይሄ የማን ጥፋት ነው? ይሄን ሁሉ እንዳላውቅ ያደረግኸኝ አንት አይደለህም ወይ?›› አለች ማርጋሬት እያለቀሰች፡
አባት ፊታቸውን እንዳቀጨሙ ‹‹ቢሮ ውስጥስ ምን ልትጠቅሚ
ትችያለሽ? ሻይ ማፍላት እንኳን አታውቂ፤ ከጧቱ ሶስት ሰዓት እስከ አስር
ሰዓት ድረስ ቆመሽ መስራት አትችይ ይግረምሽና ሳምንት እንኳን
አትቆይም፧ ጥለሽው ትወጫለሽ፡፡››
ማርጋሬት ሲያስጨንቃት የነበረውን ነገር አባቷ ሲነግሯት ሆዷ በብስጭት ታመሰ፡፡ አባቷ ያሉት እውነት መሆኑን ስታስበው ፍርሃት
ፍርሃት አላት፡ ብቻዋን መኖር ሳያስጨንቃት አልቀረም: አንድ ስህተት
ሰርታ ወይም መስራት አቅቷት ከስራዋ ልትባረር ትችላለች፡፡ አባቷ በምሬት
የተናገሩት ነገር ወደፊት ሊሆን እንደሚችል ሳትገምት አልቀረችም:
የወደፊት ራዕይዋን የሚንድባት መሰላት፡፡
እምባዋን በጉንጮቿ
እየተንዥቀዥቀ አነባች፡:
አባቷ ጣታቸውን እያወዛወዙና ከጣራ በላይ እየጮሁ ‹‹ቦስተን ከተማ
እንደ ኦክሰንፎርድ መንደር እንዳይመስልሽ፡፡ እዚያ ብትነሺ ብትፈርጪ
የሚረዳሽ የለም፡ በዘረቢሶች ልትመረዢ ትቺያለሽ፡፡ ይሁዳውያን ቤት
በረንዳ አዳሪ ኔግሮዎች አስገድደው ይደፍሩሻል፡፡ ጦሩን እቀላቀላለሁ ላልሺው.›› ሲሉ አቋረጠቻቸውና፣
‹‹በሺህ የሚቆጠሩ እንደኔ ያሉ ወጣት ሴቶች ጦሩን ተቀላቅለዋል›› አለች ማርጋሬት እምባ በተናነቀው ድምጽ።
‹‹ታዲያ እነሱ አንዳንቺ ያሉ ሴቶች አይደሉም፡፡ እነሱ ጠንካራ ሴቶች ናቸው፡፡ እነሱ በጧት ተነስተው የጉልበት ስራ መስራት የሚችሉ ናቸው እንጂ እንዳንቺ ተሞላቀው ያደጉ ልፍስፍሶች አይደሉም፡፡ እግዜር አያድርገውና አንድ ችግር ቢደርስብሽ ዋጋ የለሽም›› አሉ አባት፡
ማርጋሬት ባለፈው ከቤት ጠፍታ የሄደች ጊዜ እንዴት እግሯ እንደተሳሰረ፣ ምን ያህል እንደፈራችና አቅመቢስ እንደነበረች ስታስታውስ በእፍረት ትሸማቀቃለች፡፡ በአንድ በኩል አባቷ እውነታቸውን ነው፡፡
አባቷ ጣታቸውን ወደ እሷ እየቀሰሩ ዓይናቸው ተጎልጉሎ የወጣ
እስኪመስል ድረስ አፍጥጠው ‹‹በቢሮ ስራውም ሆነ በጦሩ ውስጥ ሳምንት እንኳን ከቆየሽ ከምላሴ ጠጉር ይነቀል፤ ልፍስፍስ ነሽ›› አሉና በተናገሩት
ረክተው ቁጭ አሉ፡
ከዚያም ሄሪ ከየት መጣ ሳይባል ‹‹ይበቃል!›› ሲል ተሰማ፡ ይሄ የእሷና
የአባቷ ጉዳይ ቢሆንም ፍቅረኛው ስትሰደብ አላስችለው ብሎ ከጎኗ ሊቆም ደረሰላት፡፡ ሄሪ አጠገቧ መጥቶ ቁጭ አለና መሃረቡን አውጥቶ በእምባ
የረጠቡ ጉንጮቿን አበሰላት፡
አባትም ‹‹አንተ ወጠጤ · ›› ብለው ለመናገር ያሰቡትን ተናግረው ሳይጨርሱ ሄሪ ከመቀመጫው ተነሳና ‹‹እኔ ሴት ወይም ልጅ አይደለሁም፧ ከዚህ በኋላ ቢሰድቡኝ በቡጢ ነው የማንገጫግጮት›› አላቸው፡
አባት በዚህ ጊዜ አደብ ገዙ፡:
ሄሪ ተመልሶ ማርጋሬት ጎን ቁጭ አለ፡፡
ማርጋሬት ብትደናደድም በሆዷ ድል እንዳደረገች ይሰማታል፡፡ ትታቸው
እንደምትሄድ ነግራቸዋለች፡ ምንም እንኳን ቢቆጧትም፣ ቢያፌዙባትም፣
ቢያስለቅሷትም ከአቋሟ ንቅንቅ አላደረጓትም፡፡ ለመሄድ ቆርጣለች፡፡
👍15
ይህም ሆኖ ጥርጣሬ ውስጥ ሳይከቷት አልቀረም፡፡ ምናልባትም
በመጨረሻው ሰዓት ላይ ያሰበችውን እንዳታደርግ ሽባ ሊያደርጋት የሚችል
ሽብር ሳይለቁባት አልቀረም፡፡ ለረጅም ሰዓት ያወረዱባት የስድብ ውርጅብኝና ፌዝ በራሷ መቆም እንደማትችል አድርጋ እንድትገምት አድርጓታል፡በህይወቷ በድፍረት ያደረገችው አንድም ነገር የለም፡ ታዲያ አሁን ታደርገው ይሆን? አዎ አደርገዋለሁ አለች በሆዷ እኔ ልፍስፍስ አይደለሁም፧ አለመሆኔንም በተግባር አሳያለሁ፡፡›
አባቷ ተስፋ ለማስቆረጥ ብዙ ቢጥሩም አልተሳካላቸውም፡ ነገር ግን
ጉዳዩን እንዳልተዉት እርግጥ ሆኗል፡ ወደ ሄሪ ፊቷን አዞረች፡፡ በአባቷ ፊት
ላይ የበቀል ስሜት ይነበባል፡፡ ኤልሳቤት ትዕዛዛቸውን ጥሳ ጥላቸው
ስለሄደች ልጅነቷን ክደዋል፡፡
ከዚህ በኋላ ቤተሰብ አለኝ ብላ መመለስ አትችልም፡
ለማርጋሬትስ ምን አስበውላታል?
✨ይቀጥላል✨
በመጨረሻው ሰዓት ላይ ያሰበችውን እንዳታደርግ ሽባ ሊያደርጋት የሚችል
ሽብር ሳይለቁባት አልቀረም፡፡ ለረጅም ሰዓት ያወረዱባት የስድብ ውርጅብኝና ፌዝ በራሷ መቆም እንደማትችል አድርጋ እንድትገምት አድርጓታል፡በህይወቷ በድፍረት ያደረገችው አንድም ነገር የለም፡ ታዲያ አሁን ታደርገው ይሆን? አዎ አደርገዋለሁ አለች በሆዷ እኔ ልፍስፍስ አይደለሁም፧ አለመሆኔንም በተግባር አሳያለሁ፡፡›
አባቷ ተስፋ ለማስቆረጥ ብዙ ቢጥሩም አልተሳካላቸውም፡ ነገር ግን
ጉዳዩን እንዳልተዉት እርግጥ ሆኗል፡ ወደ ሄሪ ፊቷን አዞረች፡፡ በአባቷ ፊት
ላይ የበቀል ስሜት ይነበባል፡፡ ኤልሳቤት ትዕዛዛቸውን ጥሳ ጥላቸው
ስለሄደች ልጅነቷን ክደዋል፡፡
ከዚህ በኋላ ቤተሰብ አለኝ ብላ መመለስ አትችልም፡
ለማርጋሬትስ ምን አስበውላታል?
✨ይቀጥላል✨
👍10
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ሰባት (37) «ማሪዮን» አለ። አየችው ፤ አቤት እንደማለት ። «ማሪዮን ያለፈው ኣልፏል ። ላሁኑ ሁለቱ የሚገናኙበትን መንገድ ቀይሺ ። የሚቻልሽን ሞክሪ ። ከዚያ በኋላ የሁለቱ ጉዳይ ነው። አንቺ ምንም ማድረግ አትችይም ። እኔና አንቺ ብዙ እድሜ አልትረፈንም ። ያችኮ ያለችዋን የተቻለንን ያህል እንድንደሰትባት እፈልጋለሁ እንጋባ ። አንድ ላይ እንኑር ፤ በሰላም ። እኔም እስከ ዛሬ የናፈቅሁት ፣ አንቺም ሠራሁት በምትይው ሀጢአት እስከ ዛሬ የተቀጣሽው በቂ ነው ። እኛም'ኮ በደስታ የመኖር ድርሻ አለን» አለ ጆርጅ ። ‹‹ድርሻው ይሁን ፣ ግን እኔ የመደሰት መብት ያለኝ ይመሰልሀል ጆርጅ ?» አለች ማሪዮን ቅዝዝ ብላ ፤ ከልቧ። ይህን ስትል ቅዝዝ እንዳለች ቁልቁል ሲያያት ገና ለግላጋ ወጣት ሆና ታየችው ፤ ለጆርጅ ኮሎዌ ። «በደንብ ነዋ |» አላት «የመኖር መብትሽን ማን ሊነሳሽ ፍቅሬ ?» ከዚያም ፀፀቷን ሁሉ እንድትረሳ ፤ ሀጢአት የምትለው ነገር ከንቱ ሀሳብ መሆኑንና ለወደፊቱ የሚቻለውን ካደረገች በኋላ ደስታቸውን እየተላበሱ በሰላም መኖር እንዳለባቸው ደግሞ ነገራት። ቀጥሎም… «ላሁኑ ግን ማረፍ አለብሽ ለጥ በቃ ። ለእንደዚህ ያለው በሽታ መድሐኒቱ እረፍት ነው። እሺ ?» አለ ወደ ላይ እያየችው ፍንድቅ ብላ ሳቀችና «ጆርጅ ኮሎዌ እወድሀለሁ» አለችው፡፡ «መውደድሽ ደግ ሆነ ። ምክንያቱም ወደድሽም ጠላሽ አንችኑ ማግባቴ አይቀርም ነበር ። የመጣው ቢመጣ። ገባሽ?»
«አዎና» ሁለቱም በደስታ ግለው በፈገግታ ይንቦገቦጉ ጀመር።
አንድ ነርስ በሩን ቀስ ብላ ከፍታ ሀኪሙ ለማሪዮን በደንብ መተኛት እንዳለባት መግለፃቸውንና ሌሊቱ እየተገባደደ መሆኑን እስክትነግራቸው ሁሉንም ረስተው በፍቅር ተተብትበው አንድ ላይ ቆዩ ። ጆርጅ ኮሎዌ እንደወጣ ማሪዮን ሂልያርድ ወደ ኒው ዮርክ ስልክ ደወለች… ከሳንፍራንሲስኮ ማለት ነው ። ጊዜው (ኒውዮርክ ውስጥ) አነጋጉ ላይ ቢሆንም ማይክል ስልኩን ቶሎ አላነሳውም ። ጠበቀች ፤ ማሪዮን። «ሃሎ?» አለ ፤እንቅልፍ የተጫጫነው የማይክል ድምፅ «የኔ ሸጋ ፤እኔ ነኝ » አለች ማሪዮን። «እማዬ ነሽ ? ደህና ነሽ ? ተሻለሽ? » ጥያቄውን አዥጎደጎደው። «ደህና ነኝ ። አይዞህ አትስጋ ። ይልቅስ አንድ ነገር ልነግርህ ስለፈለኩ ነው የደወልኩልህ »
« ገባኝ ። ጆርጅ ነግሮኛል » አለ እያዛጋ «እንዴት ነው እሺታ ወይስ እምቢታ?»
«እምቢታ የለም ። ሁሉንም ተቀብያለሁ » አለች ። «አሁን የጠራሁህ ለሌላ ጉዳይ ነበር» አለች ። መልስ አልሰጣትም ። ትንሽ እንደማጉረምረም ብቻ አለ ። «ስለዚያች ልጅ ጉዳይ» አለች ማሪዮን ። «የቷ ልጅ?» ማይክ እየተደናገረ ጠየቀ ። «ፎቶግራፍ አንሺዋ... ማይክል ገና አልነቃህም”ንዴ
«ገባኝ። እሺ።ምን ትሁን!»
«ታስፈልገናለች»
«ያን ያህል››
«በጣም ። ሆኖም እንደምታውቀው እንግዲህ እኔ የጆርጅ ሰው ነኝ። ልጀቷን ማደኑ ያንተ ሥራ መሆኑ ነው»
«ትቀልጃለሽ እማዬ ? እኔ ያለብኝን የሥራ ውጥረት እያወቅሺው ። ቤን ይከታተል የሷን ጉዳይ»
‹‹ቤንንማ አፍንጫህን ላስ አለችውኮ ። ይልቅ ስማ ። ልጅቷ ዘመናዊ ከመሆኗም በላይ የታረመችና በእውቀቷም የምትተማመን ሰው ናት ። ከማንም ኩታራ ጋር ለመነጋገር የምትፈቅድ አይመስለኝም… ከተቀጣሪዎች ጋር ማለቴ ነው»
«ገባኝ ። ግን የመቀመጫ እሾህ መስላ ነው ለኔ የታየችኝ››
«እሷ ሳትሆን አንተ ነህ እንዲያ የሆንክብኝ ። በምን መንገድ ልታግባባት እንደምትሞክር አላውቅም ። በሆነው ፣ በመሰለህ ሁሉ ብትቀርባት ደንታዬ አይደለም ። ግን እንፈልጋታለን። ለኔ ስትልም ቢሆን ይህን ነገር ዳር እንድታደርገው እፈልጋለሁ››
«የለም ፤ የለም ዛሬ ደህና አይደለሽም ። ጊዜ እንደሌለኝ እያወቅሽ እንዲህ ስትይ» አለ። «ይልቅ ይህን ጉዳይ ብቻ አንቺ ጨርሺ በቃ።»
«አላደርገውም ማይክ ፤ ደግሞ ይህን ጉዳይ አልፈፅምም የምትል ከሆነ ገና እኮ ነው ፤ሥራውን አልለቀኩምኮ !››
«ይህን ካላደረግክ አንደኛ ሥራዬን አልለቅም ፤ እዚያው እቢሮዬ ውስጥ እሞታለሁ ። ሁለተኛ…»
«በቃ በቃ!» አለ ማይክል አቋርጧት «እንዳልሽው ይሆናል »
«ልባርግ ! ቀልድ አይደለም ። ቃል ፤ ቃል ነው ። ቃልህን ከሻርክ ቃሌን እሽራለሁ ።»
« አረ በእግዜር |! እሺ አልኩሽኮ አሁን ትተኛለሽ ወይስ ?»
«እተኛለሁ ግን ይኸ ጉዳይ ነገ ዛሬ እንደሌለው እወቅ ። ገባህ?»
«ገባኝ ስሟን ማን ነበር ያልሺኝ ››
‹‹ሜሪ አዳምሰን»
«ሜሪ አዳምሰን ። በቃ ከነገ ጀምሮ የማገኝበትን መንገድ እፈልጋለሁ»
«ደግ... እግዜር ያክብርህ የኔ ቆንጆ»
«ደህና ደሪ የኔ አሮጊት ።... ቆይ... ቆይ እንኳን ለፍጥምጥሙ አበቃን ። ወሬውን ላናፍሰው ? ሙሽራው ማን እንደሆነ ልናገር ?»
«ምን ይጠየቃል ? ከጆርጅ የተሻለ ማንን ላገኝ ? አላፍርበትም» ሁለቱም ዘጉ ።
ማይክልንና ሜሪን ካገናኘች ፤ሁለቱ ተዋውቀው አንድ ነገር ከመሰረቱ አእምሮዋ ሰላም ያገኛል ። ማይክ የሠራችውን ሁሉ ሲሰማ ምን ይላት ? ሆኖም ፍቅሩን የማግኘቱ ደስታ ለሷ የሚኖረውን ጥላቻ ሊቀንሰው ይችላል። በኋላ ተፀፅታ የሠራችውን ሲያይ ይቅር ይላታል ። እንቅልፍ እያንሸራተተ……
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ሰባት (37) «ማሪዮን» አለ። አየችው ፤ አቤት እንደማለት ። «ማሪዮን ያለፈው ኣልፏል ። ላሁኑ ሁለቱ የሚገናኙበትን መንገድ ቀይሺ ። የሚቻልሽን ሞክሪ ። ከዚያ በኋላ የሁለቱ ጉዳይ ነው። አንቺ ምንም ማድረግ አትችይም ። እኔና አንቺ ብዙ እድሜ አልትረፈንም ። ያችኮ ያለችዋን የተቻለንን ያህል እንድንደሰትባት እፈልጋለሁ እንጋባ ። አንድ ላይ እንኑር ፤ በሰላም ። እኔም እስከ ዛሬ የናፈቅሁት ፣ አንቺም ሠራሁት በምትይው ሀጢአት እስከ ዛሬ የተቀጣሽው በቂ ነው ። እኛም'ኮ በደስታ የመኖር ድርሻ አለን» አለ ጆርጅ ። ‹‹ድርሻው ይሁን ፣ ግን እኔ የመደሰት መብት ያለኝ ይመሰልሀል ጆርጅ ?» አለች ማሪዮን ቅዝዝ ብላ ፤ ከልቧ። ይህን ስትል ቅዝዝ እንዳለች ቁልቁል ሲያያት ገና ለግላጋ ወጣት ሆና ታየችው ፤ ለጆርጅ ኮሎዌ ። «በደንብ ነዋ |» አላት «የመኖር መብትሽን ማን ሊነሳሽ ፍቅሬ ?» ከዚያም ፀፀቷን ሁሉ እንድትረሳ ፤ ሀጢአት የምትለው ነገር ከንቱ ሀሳብ መሆኑንና ለወደፊቱ የሚቻለውን ካደረገች በኋላ ደስታቸውን እየተላበሱ በሰላም መኖር እንዳለባቸው ደግሞ ነገራት። ቀጥሎም… «ላሁኑ ግን ማረፍ አለብሽ ለጥ በቃ ። ለእንደዚህ ያለው በሽታ መድሐኒቱ እረፍት ነው። እሺ ?» አለ ወደ ላይ እያየችው ፍንድቅ ብላ ሳቀችና «ጆርጅ ኮሎዌ እወድሀለሁ» አለችው፡፡ «መውደድሽ ደግ ሆነ ። ምክንያቱም ወደድሽም ጠላሽ አንችኑ ማግባቴ አይቀርም ነበር ። የመጣው ቢመጣ። ገባሽ?»
«አዎና» ሁለቱም በደስታ ግለው በፈገግታ ይንቦገቦጉ ጀመር።
አንድ ነርስ በሩን ቀስ ብላ ከፍታ ሀኪሙ ለማሪዮን በደንብ መተኛት እንዳለባት መግለፃቸውንና ሌሊቱ እየተገባደደ መሆኑን እስክትነግራቸው ሁሉንም ረስተው በፍቅር ተተብትበው አንድ ላይ ቆዩ ። ጆርጅ ኮሎዌ እንደወጣ ማሪዮን ሂልያርድ ወደ ኒው ዮርክ ስልክ ደወለች… ከሳንፍራንሲስኮ ማለት ነው ። ጊዜው (ኒውዮርክ ውስጥ) አነጋጉ ላይ ቢሆንም ማይክል ስልኩን ቶሎ አላነሳውም ። ጠበቀች ፤ ማሪዮን። «ሃሎ?» አለ ፤እንቅልፍ የተጫጫነው የማይክል ድምፅ «የኔ ሸጋ ፤እኔ ነኝ » አለች ማሪዮን። «እማዬ ነሽ ? ደህና ነሽ ? ተሻለሽ? » ጥያቄውን አዥጎደጎደው። «ደህና ነኝ ። አይዞህ አትስጋ ። ይልቅስ አንድ ነገር ልነግርህ ስለፈለኩ ነው የደወልኩልህ »
« ገባኝ ። ጆርጅ ነግሮኛል » አለ እያዛጋ «እንዴት ነው እሺታ ወይስ እምቢታ?»
«እምቢታ የለም ። ሁሉንም ተቀብያለሁ » አለች ። «አሁን የጠራሁህ ለሌላ ጉዳይ ነበር» አለች ። መልስ አልሰጣትም ። ትንሽ እንደማጉረምረም ብቻ አለ ። «ስለዚያች ልጅ ጉዳይ» አለች ማሪዮን ። «የቷ ልጅ?» ማይክ እየተደናገረ ጠየቀ ። «ፎቶግራፍ አንሺዋ... ማይክል ገና አልነቃህም”ንዴ
«ገባኝ። እሺ።ምን ትሁን!»
«ታስፈልገናለች»
«ያን ያህል››
«በጣም ። ሆኖም እንደምታውቀው እንግዲህ እኔ የጆርጅ ሰው ነኝ። ልጀቷን ማደኑ ያንተ ሥራ መሆኑ ነው»
«ትቀልጃለሽ እማዬ ? እኔ ያለብኝን የሥራ ውጥረት እያወቅሺው ። ቤን ይከታተል የሷን ጉዳይ»
‹‹ቤንንማ አፍንጫህን ላስ አለችውኮ ። ይልቅ ስማ ። ልጅቷ ዘመናዊ ከመሆኗም በላይ የታረመችና በእውቀቷም የምትተማመን ሰው ናት ። ከማንም ኩታራ ጋር ለመነጋገር የምትፈቅድ አይመስለኝም… ከተቀጣሪዎች ጋር ማለቴ ነው»
«ገባኝ ። ግን የመቀመጫ እሾህ መስላ ነው ለኔ የታየችኝ››
«እሷ ሳትሆን አንተ ነህ እንዲያ የሆንክብኝ ። በምን መንገድ ልታግባባት እንደምትሞክር አላውቅም ። በሆነው ፣ በመሰለህ ሁሉ ብትቀርባት ደንታዬ አይደለም ። ግን እንፈልጋታለን። ለኔ ስትልም ቢሆን ይህን ነገር ዳር እንድታደርገው እፈልጋለሁ››
«የለም ፤ የለም ዛሬ ደህና አይደለሽም ። ጊዜ እንደሌለኝ እያወቅሽ እንዲህ ስትይ» አለ። «ይልቅ ይህን ጉዳይ ብቻ አንቺ ጨርሺ በቃ።»
«አላደርገውም ማይክ ፤ ደግሞ ይህን ጉዳይ አልፈፅምም የምትል ከሆነ ገና እኮ ነው ፤ሥራውን አልለቀኩምኮ !››
«ይህን ካላደረግክ አንደኛ ሥራዬን አልለቅም ፤ እዚያው እቢሮዬ ውስጥ እሞታለሁ ። ሁለተኛ…»
«በቃ በቃ!» አለ ማይክል አቋርጧት «እንዳልሽው ይሆናል »
«ልባርግ ! ቀልድ አይደለም ። ቃል ፤ ቃል ነው ። ቃልህን ከሻርክ ቃሌን እሽራለሁ ።»
« አረ በእግዜር |! እሺ አልኩሽኮ አሁን ትተኛለሽ ወይስ ?»
«እተኛለሁ ግን ይኸ ጉዳይ ነገ ዛሬ እንደሌለው እወቅ ። ገባህ?»
«ገባኝ ስሟን ማን ነበር ያልሺኝ ››
‹‹ሜሪ አዳምሰን»
«ሜሪ አዳምሰን ። በቃ ከነገ ጀምሮ የማገኝበትን መንገድ እፈልጋለሁ»
«ደግ... እግዜር ያክብርህ የኔ ቆንጆ»
«ደህና ደሪ የኔ አሮጊት ።... ቆይ... ቆይ እንኳን ለፍጥምጥሙ አበቃን ። ወሬውን ላናፍሰው ? ሙሽራው ማን እንደሆነ ልናገር ?»
«ምን ይጠየቃል ? ከጆርጅ የተሻለ ማንን ላገኝ ? አላፍርበትም» ሁለቱም ዘጉ ።
ማይክልንና ሜሪን ካገናኘች ፤ሁለቱ ተዋውቀው አንድ ነገር ከመሰረቱ አእምሮዋ ሰላም ያገኛል ። ማይክ የሠራችውን ሁሉ ሲሰማ ምን ይላት ? ሆኖም ፍቅሩን የማግኘቱ ደስታ ለሷ የሚኖረውን ጥላቻ ሊቀንሰው ይችላል። በኋላ ተፀፅታ የሠራችውን ሲያይ ይቅር ይላታል ። እንቅልፍ እያንሸራተተ……
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
❤14👍11
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ስምንት (38) ጆርጅ ኮሎዌ በፍቅር ሲስማት ለስላሳው ሙዚቃ እንደገና ጀመረ ። የሠርጉ ሥነ ሥርዓት የተከናወነው በማሪዮን ሂልያርድ ቤት ሲሆን እሷም ለዚሁ የሠርጓ ቀን ሶስት ሙዚቀኞች ቀጥራ ነበር ። ለሠርጉ የታደሙት አንድ ሰባ የሚሆኑ ሰዎች ሲሆኑ ፤ የምግብ ቤቱ ክፍልም እንደ የዳንስ አዳራሽ ሆኖ ተዘጋጅቷል ። የቡፌ ግብዣው የሚከናወነው ደግሞ በዚሁ መኖሪያ ቤተ መፃሕፍት ውስጥ ነው ። ዝግጅቱ የተከናወነ ፤ቀኑም ተስማሚ ነበር። የየካቲት የመጨረሻው ቀን ። ይህ ቀን ጥርት ያለ ፤ ነፋሻና ሳንካ አልባ የሆነ የኒውዮርክ ቀን ሆኗል ። ማሪዮን ሳንፍራንሲስኮ የደረሰባትን ነገር እንደመርሳት ያለች ይመስላል ። ደሟ ግጥም ብሎ ሞልቷል ። ጆርጅ በደስታ ፈነድቋል፡፡
ጋዜጠኞችም በዚሁ ሠርግ ላይ ተገኝተዋል ። ታይም የተባለው ታዋቂ መጽሔት ፎቶ አንሺ ማይክልንና ማሪዮንን ፤ ባሏ ጆርጅን ፎቶ አነሳቸው። ማሪዮን በባለቤቷና በልጅዋ ታጅባ ነበር የተነሳችው ። ማይክል ሂልያርድ እናቱን ዳረ ። ማሪዮን ሂልያርድ ካሁን ጀምሮ ፤ ማሪዮን ኮሎዊ ትባላለች ፤ የጆርጅ ኮሎዌ ባለቤት ። ማይክል ሂልያርድ ከዚህ ጊዜ ጄምሮ የኮተር ሂልያርድ ባለቤት ነው ። የአንድ ግዙፍ ድርጅት (የኮተር ሂልያርድን ያክል ግዙፍ ድርጅት) ፕሬዚዳንት መሆን ! ለማይክል የተሰማው ስሜት . . . ሆኖም ይህም ስሜት ቢሰማውም . . . ይህን ስሜቱን ደግሞ ማይክል ሊደብቅ አይሻም ። ፕሬዚዳንት ፣ በዚህ እድሜው ባለቤት ! በማግስቱ ታይም የተባለው በመላው ዓለም የሚሰራጭ መጽሔት የማይክልን ፎቶ በሽፋኑ ይዞ ወጣ ። ድንቅ ተባል ። በዚህ እድሜ የኮተር ሂልያርድ ፕሬዚዳንት !. . የማሪዮንና የጆርጅ ኮሎዌ ሠርግ እለት የዛ ለት ማይክል ወደእናቱ ቀረብ ብሎ፣ «ሚስዝ ኮሎዌ ! » አለ አዲሱን የጋብቻ ስሟን እየተጠቀመና ለቀሰስተኛው ዳንስ እየጋበዛት ። «አዲሱን ስም እናክብረው ጋብቻውን እናክብረው» አለ ። አዲሱን ስም እናክብረው ሲል ናንሲ ትዝ አለችው ። እንዳለው ሆነ ። አከበሩት ፤ ጆርጅና ማሪዮን ኩሎዌ በጋብቻ ተሳሰሩ ። ሁለቱም ለረጅም ጊዜ ተሰቃይተዋል ። ደስ ይበላቸው ፤ ደስታ ይገባቸዋል ። ደስታ ያስፈልጋቸዋል ። ጋብቻቸውን ምክንያት በማድረግ ወደ አውሮፓ ሔደው ሽርሽር ይላሉ። ደስ ይሰኛሉ ። « በጣም ቆንጆ ነህ የኔ ሸጋ » አለች ማሪዮን ፡ ማይክልን በፍቅር እየተመለከተች ። «ያንቺን አላየሽ ። አሸብርቀሻል ፤ ተውበሻል » አለ ማይክ ከልቡ። «ቤቱ ሳይቀር እንደ አዲስ ያበራል ፤ አምሯል » እለ ። «በጣም አሸብርቋል አደል ? » አለች ማሪዮን ። ማይክ ከልቡ ተደስቶ ማሪዮንን ተመለከታት ። እናቱ ነችኮ። ይህቺ ሙሽሪት እናቱ ነች ። ሙሽራ ትመስላለች ፤ የእውነት ሁኔታዋ ሁሉ የሙሽራ . . . የልጃገረድ ሙሽራ ሆኖ ታየው ። «ሚስተር ሂልያርድ » የሚል ድምዕ ቀሰቀሰው ። « ማይክል ሂልያርድ በጣም ደስ ያለህ ትመስላለህ ዛሬ » ዌንዲ ነበረች ። ሲያያት እንደወትሮው አላፈረም ። ዓይኑ አልሸሻትም ። ይህ ቀርቷል። ዛሬ ቤን አቭሪና ዌንዲ ሊጋቡ ተጫጭተዋል ። የማጫ ቀለበቷ (ዕንቁ ያለበት ቀለበቷ ) እቀለበት ጣቷ ላይ ያበራል ። ሊጋቡ ወስነዋል ። ማይክል ሂልያርድም ዋና ሚዜ ሆኖ ተመርጧል ። ተስማምቷልም ።
«ደስ አትልም?» አለ ማይክ እናቱን ለዌንዲ እያሳያት ዌንዲ አንገቷን በአዎንታ ነቅንቃ በደስታ ፈገግ አሰች ። ደስ ብሎት ስላየችው ደስ እላት ። እንዲህ ደስ የሚለው መስሏት አያውቅም ። ብቻ ነገሩ ሁሉ አይገባትም ። ገባት አልገባት ደሞ ደንታዋ አይደለም ። ለሷ እንደሆነ ቤን አለላት ። የቤንን ያህል በፍቅር ደስ ያሰኛት ወንድ የለም ። «እንቺም በሚቀጥለው በጋ እንዲህ ቆንጆ ሆነሽ ማየት አለብኝ ። ሙሽራ ቁንጅት ሲል የሠራ አከላቴ በደስታ ይሞላል » አለ ማይክል ዊንዲን በደስታ እያየ ። ደስ አላት ። ዛሬ ጓደኛዋ ነው። ትወደዋለች ። አትመኘውም ለጓደኛ የሚገባውን ሁሉ ግን ትመኝለታለች ። «አሀ የኛ ጀግና ፤ የሰው እጮኛ ለማማገጥ ነዋ ?» ቤን አቭሪ ነበር እንዲህ ያለው ። ቤን ሶስት መለኪያ ሻምፓኝ ይዞ ነበር የመጣው ። «በሉ ተቀመጡ። ይኸው ! ሁለት መለኪያ የናንተ ነው አንሱና ጠጡ» አለ ቤን በደስታ ፈክቶ ። ቀጥሎም ፣ «በነገራችን ላይ ማይክ ምን እንደሚሻለኝ እንጃ እንጂ ፍቅር ይዞኛል ፤ ከማሪዮን ጋር » አለ ። «ቀለጥክ… ዛሬ ጠዋት ላንድ ጎረምሳ ዳርኳት» አለ ማይክ ። ቤን ወይኔ በሚል ሁኔታ ጣትና ጣቱን አጩሆ ደንግጦ ቀረ። በዚህም ነገር ሶስቱም ከልባቸው ሳቁ። ሙዚቃው የተጀመረው ገና ስቀው ሳያበቁ ነበር ። በዚህ ጊዜ ማይክ « ሙዚቃው ጀመረ። መሔድና እናቴን ለዳንስ መጋበዝ አለብኝ ። ደንቡ እንደሚለው እኔና እሷ ዳንሱን እንከፍታለን ። ጆርጅ ይቅርታ ጠይቆ ይነጥቀኛል።» ይህን ብሎ ወደ ዳንሱ አዳራሽ ከገባ በኋላ ነበር እናቱን ባዲሱ የጋብቻ ስሟ ጠርቶ የጋበዛት ።
« ዛሬ በጣም ደስ ያለው ይመስላል » አለች ዌንዲ ማይክ እንደተለያቸው ። «እንዲህ አንዳንድ ቀን እንኳ ደስ ብሎት እንየው እንጂ » አለ ቤን ፊቱ በተመስጦ ተሞልቶ። ከዚያም ድንገት ተመስጦን ነጥቆ ወጥቶና ከልቡ ፈገግ ብሎ «አንቺም ዛሬ በጣም ደስ ብሎሻል » አላት «ደሞ እኔ መቼ ከፍቶኝ ያውቃል? ዕድሜ ላንተ እንጂ›› አለች ከልቧ ። ለጥቂት ጊዜ ፀጥታ ሆነ ። ከዚያ በኋላ « በነገራችን ላይ ፤ እጠይቅሀለሁ እያልኩ እየረሳሁት «ያችን ፍቶ ግራፍ አንሺ አነጋገርካት ወይስ እንዴት አደረግክ?» ስትል ጠየቀችው ፡፡ «አላነጋገርኳትም » አለ ቤን ራሱን በአሉታ እየነቀነቀ «ማይክ ሊያነጋግራት አስቧል » አልመስልሽ አላት « ማይክ ጊዜ አግኝቶ ? » አለች ጥያቄዋ መደነቅም ነበር ። «ጊዜ እንኳን የለውም ። ግን ማይክ ለሥራ ጊዜ ያጣል ብለሽ ነው እንደምንም ያብቃቃዋል ።. ለዚህም ለሌላ ሌላ ሺህ ጉዳይም በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ሳንፍራንሲስኮ ይሔዳል » አለ ቤን ። ፀጥታ ሆነ ። ዌንዲ ማሰብ ቀጠለች ።
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ስምንት (38) ጆርጅ ኮሎዌ በፍቅር ሲስማት ለስላሳው ሙዚቃ እንደገና ጀመረ ። የሠርጉ ሥነ ሥርዓት የተከናወነው በማሪዮን ሂልያርድ ቤት ሲሆን እሷም ለዚሁ የሠርጓ ቀን ሶስት ሙዚቀኞች ቀጥራ ነበር ። ለሠርጉ የታደሙት አንድ ሰባ የሚሆኑ ሰዎች ሲሆኑ ፤ የምግብ ቤቱ ክፍልም እንደ የዳንስ አዳራሽ ሆኖ ተዘጋጅቷል ። የቡፌ ግብዣው የሚከናወነው ደግሞ በዚሁ መኖሪያ ቤተ መፃሕፍት ውስጥ ነው ። ዝግጅቱ የተከናወነ ፤ቀኑም ተስማሚ ነበር። የየካቲት የመጨረሻው ቀን ። ይህ ቀን ጥርት ያለ ፤ ነፋሻና ሳንካ አልባ የሆነ የኒውዮርክ ቀን ሆኗል ። ማሪዮን ሳንፍራንሲስኮ የደረሰባትን ነገር እንደመርሳት ያለች ይመስላል ። ደሟ ግጥም ብሎ ሞልቷል ። ጆርጅ በደስታ ፈነድቋል፡፡
ጋዜጠኞችም በዚሁ ሠርግ ላይ ተገኝተዋል ። ታይም የተባለው ታዋቂ መጽሔት ፎቶ አንሺ ማይክልንና ማሪዮንን ፤ ባሏ ጆርጅን ፎቶ አነሳቸው። ማሪዮን በባለቤቷና በልጅዋ ታጅባ ነበር የተነሳችው ። ማይክል ሂልያርድ እናቱን ዳረ ። ማሪዮን ሂልያርድ ካሁን ጀምሮ ፤ ማሪዮን ኮሎዊ ትባላለች ፤ የጆርጅ ኮሎዌ ባለቤት ። ማይክል ሂልያርድ ከዚህ ጊዜ ጄምሮ የኮተር ሂልያርድ ባለቤት ነው ። የአንድ ግዙፍ ድርጅት (የኮተር ሂልያርድን ያክል ግዙፍ ድርጅት) ፕሬዚዳንት መሆን ! ለማይክል የተሰማው ስሜት . . . ሆኖም ይህም ስሜት ቢሰማውም . . . ይህን ስሜቱን ደግሞ ማይክል ሊደብቅ አይሻም ። ፕሬዚዳንት ፣ በዚህ እድሜው ባለቤት ! በማግስቱ ታይም የተባለው በመላው ዓለም የሚሰራጭ መጽሔት የማይክልን ፎቶ በሽፋኑ ይዞ ወጣ ። ድንቅ ተባል ። በዚህ እድሜ የኮተር ሂልያርድ ፕሬዚዳንት !. . የማሪዮንና የጆርጅ ኮሎዌ ሠርግ እለት የዛ ለት ማይክል ወደእናቱ ቀረብ ብሎ፣ «ሚስዝ ኮሎዌ ! » አለ አዲሱን የጋብቻ ስሟን እየተጠቀመና ለቀሰስተኛው ዳንስ እየጋበዛት ። «አዲሱን ስም እናክብረው ጋብቻውን እናክብረው» አለ ። አዲሱን ስም እናክብረው ሲል ናንሲ ትዝ አለችው ። እንዳለው ሆነ ። አከበሩት ፤ ጆርጅና ማሪዮን ኩሎዌ በጋብቻ ተሳሰሩ ። ሁለቱም ለረጅም ጊዜ ተሰቃይተዋል ። ደስ ይበላቸው ፤ ደስታ ይገባቸዋል ። ደስታ ያስፈልጋቸዋል ። ጋብቻቸውን ምክንያት በማድረግ ወደ አውሮፓ ሔደው ሽርሽር ይላሉ። ደስ ይሰኛሉ ። « በጣም ቆንጆ ነህ የኔ ሸጋ » አለች ማሪዮን ፡ ማይክልን በፍቅር እየተመለከተች ። «ያንቺን አላየሽ ። አሸብርቀሻል ፤ ተውበሻል » አለ ማይክ ከልቡ። «ቤቱ ሳይቀር እንደ አዲስ ያበራል ፤ አምሯል » እለ ። «በጣም አሸብርቋል አደል ? » አለች ማሪዮን ። ማይክ ከልቡ ተደስቶ ማሪዮንን ተመለከታት ። እናቱ ነችኮ። ይህቺ ሙሽሪት እናቱ ነች ። ሙሽራ ትመስላለች ፤ የእውነት ሁኔታዋ ሁሉ የሙሽራ . . . የልጃገረድ ሙሽራ ሆኖ ታየው ። «ሚስተር ሂልያርድ » የሚል ድምዕ ቀሰቀሰው ። « ማይክል ሂልያርድ በጣም ደስ ያለህ ትመስላለህ ዛሬ » ዌንዲ ነበረች ። ሲያያት እንደወትሮው አላፈረም ። ዓይኑ አልሸሻትም ። ይህ ቀርቷል። ዛሬ ቤን አቭሪና ዌንዲ ሊጋቡ ተጫጭተዋል ። የማጫ ቀለበቷ (ዕንቁ ያለበት ቀለበቷ ) እቀለበት ጣቷ ላይ ያበራል ። ሊጋቡ ወስነዋል ። ማይክል ሂልያርድም ዋና ሚዜ ሆኖ ተመርጧል ። ተስማምቷልም ።
«ደስ አትልም?» አለ ማይክ እናቱን ለዌንዲ እያሳያት ዌንዲ አንገቷን በአዎንታ ነቅንቃ በደስታ ፈገግ አሰች ። ደስ ብሎት ስላየችው ደስ እላት ። እንዲህ ደስ የሚለው መስሏት አያውቅም ። ብቻ ነገሩ ሁሉ አይገባትም ። ገባት አልገባት ደሞ ደንታዋ አይደለም ። ለሷ እንደሆነ ቤን አለላት ። የቤንን ያህል በፍቅር ደስ ያሰኛት ወንድ የለም ። «እንቺም በሚቀጥለው በጋ እንዲህ ቆንጆ ሆነሽ ማየት አለብኝ ። ሙሽራ ቁንጅት ሲል የሠራ አከላቴ በደስታ ይሞላል » አለ ማይክል ዊንዲን በደስታ እያየ ። ደስ አላት ። ዛሬ ጓደኛዋ ነው። ትወደዋለች ። አትመኘውም ለጓደኛ የሚገባውን ሁሉ ግን ትመኝለታለች ። «አሀ የኛ ጀግና ፤ የሰው እጮኛ ለማማገጥ ነዋ ?» ቤን አቭሪ ነበር እንዲህ ያለው ። ቤን ሶስት መለኪያ ሻምፓኝ ይዞ ነበር የመጣው ። «በሉ ተቀመጡ። ይኸው ! ሁለት መለኪያ የናንተ ነው አንሱና ጠጡ» አለ ቤን በደስታ ፈክቶ ። ቀጥሎም ፣ «በነገራችን ላይ ማይክ ምን እንደሚሻለኝ እንጃ እንጂ ፍቅር ይዞኛል ፤ ከማሪዮን ጋር » አለ ። «ቀለጥክ… ዛሬ ጠዋት ላንድ ጎረምሳ ዳርኳት» አለ ማይክ ። ቤን ወይኔ በሚል ሁኔታ ጣትና ጣቱን አጩሆ ደንግጦ ቀረ። በዚህም ነገር ሶስቱም ከልባቸው ሳቁ። ሙዚቃው የተጀመረው ገና ስቀው ሳያበቁ ነበር ። በዚህ ጊዜ ማይክ « ሙዚቃው ጀመረ። መሔድና እናቴን ለዳንስ መጋበዝ አለብኝ ። ደንቡ እንደሚለው እኔና እሷ ዳንሱን እንከፍታለን ። ጆርጅ ይቅርታ ጠይቆ ይነጥቀኛል።» ይህን ብሎ ወደ ዳንሱ አዳራሽ ከገባ በኋላ ነበር እናቱን ባዲሱ የጋብቻ ስሟ ጠርቶ የጋበዛት ።
« ዛሬ በጣም ደስ ያለው ይመስላል » አለች ዌንዲ ማይክ እንደተለያቸው ። «እንዲህ አንዳንድ ቀን እንኳ ደስ ብሎት እንየው እንጂ » አለ ቤን ፊቱ በተመስጦ ተሞልቶ። ከዚያም ድንገት ተመስጦን ነጥቆ ወጥቶና ከልቡ ፈገግ ብሎ «አንቺም ዛሬ በጣም ደስ ብሎሻል » አላት «ደሞ እኔ መቼ ከፍቶኝ ያውቃል? ዕድሜ ላንተ እንጂ›› አለች ከልቧ ። ለጥቂት ጊዜ ፀጥታ ሆነ ። ከዚያ በኋላ « በነገራችን ላይ ፤ እጠይቅሀለሁ እያልኩ እየረሳሁት «ያችን ፍቶ ግራፍ አንሺ አነጋገርካት ወይስ እንዴት አደረግክ?» ስትል ጠየቀችው ፡፡ «አላነጋገርኳትም » አለ ቤን ራሱን በአሉታ እየነቀነቀ «ማይክ ሊያነጋግራት አስቧል » አልመስልሽ አላት « ማይክ ጊዜ አግኝቶ ? » አለች ጥያቄዋ መደነቅም ነበር ። «ጊዜ እንኳን የለውም ። ግን ማይክ ለሥራ ጊዜ ያጣል ብለሽ ነው እንደምንም ያብቃቃዋል ።. ለዚህም ለሌላ ሌላ ሺህ ጉዳይም በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ሳንፍራንሲስኮ ይሔዳል » አለ ቤን ። ፀጥታ ሆነ ። ዌንዲ ማሰብ ቀጠለች ።
👍15
የለም ማይክ አላውቀውም ፤ ሁል ጊዜ አዲስ ነው ። ብቻም አይመስለኝም ። ማይክ ምን እንደሆነ የሚያውቀው ያለኔ ምናልባት ቤን ። ቤንም ቢሆን እንጃ ። ምናልባት ያውቀው ነበር ማለት ይቻላል ፤ በፊት ። ግን አሁንስ ያውቀዋል ? አረ በፊትስ ቢሆን ያውቀው ነበር ? አስቸጋሪ ነገር ነው። «መደነስ ትፈልጊያለሽ ? » አለ ቤን መለኪያውን እጠረጴዛው ላይ እያኖረና እያቀፋት ። «መፈለግ ነው ! » አለች ደስ እያላት ። ተያይዘው ወደ ዳንሱ አዳራሽ ገቡ ። ትንሽ እንደደነሰ… ቢያንስ ለነሱ ትንሽ የደነሱ ነው የመሰላቸው ማይክል በመካከቸው ሊገባ እየሞከረ ። ‹‹ተራ ይድረሰኝ እንጂ »
«እንዲህ ነኝና ፤ ምናለ ይደርስሀል …» አለ ቤን «ሰውየው ደህናም አይደለህ ? ለመሆኑ ከእናትህ ጋር ልትደሰት እልነበረም እንዴ ትተኸን የሔድከው ? »
« ጆርጅን ስታይ እኔን ፈንግጣኝ ሔደች » ሶስቱም ሳቁ ። «ደግ አደረገች። አዋቂ ይሉሀል እንዲሀ ነው» አለ ቤን እየሳቀ ። ቤንም ወለሉን አልለቀቀ ፤ ማይክልም አልተመለሰ ። ሶስቱም ባንድነት መደነስ ጀመሩ ። መንገላወድ ልበለው ? ይህ የተሰማት ዌንዲ በሳቅ መንከትከት ጀመረች ። ቤንና ማይክ ያን ያህል ሲደሰቱ ስታይ አደጋው ከመድረሱ በፊት የነበረው ሁኔታ በዓይነ ኅሊናዋ ታያት ። እንዲህ ነበር ማለት ነው የሚደሰቱት ስትል አሰበች ። ዛሬ ይህ በመመለሱ ደስ አላት ። መሳቅ ጀመረች። በመካከሉ ማይክ ቤንን በትያትራዊ ቁጣ እየተመለከተ «ስማ አቭሪ !ከዚህ ጥፋ ብያለሁ ጥፋ ። ከእጮኛህ ጋር ለብቻየ መደነስ እፈልጋለሁ ማለት ይግባህ » ሲል አስጠነቀቀው። «አልሔድም ፣ አይቻልም ብል ምን ሊመጣ !» አለ ቤን «ሶስታችንም ከዳንሱ ወለል ተጠርገን እንድንጣል ታዛለች እናቴ ። ያ ደሞ ጥሩ አይመስለኝም » በዚህ ሁኔታ ከቆዩ በኋላ !
« ስሙ » አለ ማይክ «ለምን ሔደን ኬክ አንበላም? » ተስማሙ ። ኬክ ወዳለበት ሲሔዱ ቤን አቭሪ የጫማውን ሶል አየት ካደረገ በኋላ ሳታየው ዌንዲን በአውራጣቱ እያሳየና አትሰማም አሉ በሚል ሁኔታና ትያትራዊ ሹክሹክታ ፣ «ዳንስ አትችልም ይቺ ሴት ። ጫማዬን ታያለህ ? » አለው። ማይክም «የኔንም ተመልከተው! » ሲል አጋነነ ። «የናንተን አሳያችሁ እኔ ደሞ ነገ በእግሬ መሔዴ እማይቀር ነው » አለች ዌንዲ በማኩረፍ ። በዚህ እየተሳሳቁ እኬኩ ዘንድ ደረሱ። ኬኩን አንስተው እየገመጡ ዳንሱን መመልከት ጀመሩ ። የተጠሩት ሀብታሞች ነበሩ ፤ሁሉም ። በሀብታም ጋለሞቶች አንገት ላይ የተንጠለጠሉት የእንቁና የሉል ጌጦች ያበራሉ። ልጃገረዶችም አበባ መስለዋል፡፡ «ትንሽ ቀደም ብሎ ይህን ባይ ኖሮ » አለ ቤን በውሸት የፀፀት ድምጽ ልጃገረዶቹን ኢያየ ። «እህሳ !» አለ ማይክ ቀልዱን እየተክተለ ።
«እሀህ ... ወደ መፀዳጃ ቤት ብቅ ብዬ የአፍንጫዬን ላብ በፑደር ላስተካክል አስቤ ነበር ። አሁን ግን እናንተ ሰዎች የምትታመኑ ሆናችሁ አልታያችሁኝም ። ይቅርብኝ » አለች ዌንዲ ። «አይ ለዚህስ አታስቢ ። እጠብቅልሻለሁ » አለ ቤን። «ምን ጊዜ ኖሮህ ጌታዬ ! አንተንም የሚጠብቅ በተገኘ ፤ እንኳን አንተ ሰው ልትጠብቅ » ቤን አቭሪ « ግድየለሽም » ብሎ ብርጭቆዋን ተቀብሎ እንደማባረር አደረጋት ። ዌንዲ ወደ ወይዛዝርት ክፍል ስትሔድ ። «ሴት ብሎ ዝም ናት ፤ አይደል ?» አለው ማይክን ። ማይክም አድናቆቱን ከልቡ ገለጸ ። ከዚህ ቀጥሎ ቤን ማይክን በደንብ እየተመለከተ «ሁሌ ሳስበው ምንኛ ታድያለሁ እላለሁ ። ማይክ ያኔ ስነግርህ አለመቆጣትህ…. ስለኔና ስለሷ የነገርኩህ እለት… » አለ። «ለምን እቆጣለሁ!?. . . ደሞም'ኮ አየህ እኔ ለእንደዚህ ዓይነቱ ነገር ጊዜ የለኝም »
« ለወደፊቱ ግን ጊዜ እንደሚኖርህ አልጠራጠርም››
‹‹ምናልባት። ሆኖም ለጊዜው እናንተ ፡ እናንተ ሂዱ፤አግቡ ተጋቡ። እኔ ልጄ ከባድ ሥራ ፤ ከባድ ኃላፊነት አለብኝ » ማይክ ይህን ያህል ቢልም ከዚህ በፊት ይህን የመሰለ ነገር እንደሚያስከፋው አልተከፋም ። ፈገግታ በፊቱ ላይ እንዳለ ነበር እንዲሁ ፈገግ እንዳለ መለኪያውን ተመለከተ ። ከዚያም ለጤናችን በሚል ቅኝት ብድግ አድርጐ «ለሁላችን ! » አለ ሁለቱም ግጥም አድርገው ጠጡ።
•••••••••••••••••••••••••
ማይክል የእጅ ሻንጣውን ጧ እድርጎ ሲዘጋ አውሮፕላኑ የሳንፍራንሲስኮ ማረፊያውን አስፋልት ያዘ ። በመንገድ ላይም እያለ አላረፈም ነበር ። በሳንፍራንሲስኮ ውስጥ በሚቆይበት ጊዜ ብዙ ስራ መስራት አለበት ። ብዙ ስብሰባዎች ይጠብቁታል ። የተለያዩ ሐኪሞችን ማነጋገር ፣ ጥያቄዎችን መመለስ ፡ የተለያዩ ስራዎችን መመልከት አርኪቴክቶችን ማነጋገር፤ ማደራጀት ፤ መመሪያ መስጠት ። በዚያ ላይ ደሞ... ያችን ፎቶ ግራፍ እንሺም ማነጋገር፤ ማግባባት ማለቂያ የለውም ። ሆኖም እንደምንም ይወጣዋል፤ ለምዶታል ። ወይ የምግብ ሳዓቱን በማሳለፍ ወይ የመኝታ ሰዓቱን በመቅነስ ወይም ሌላ። በቻ... ይወጣዋል ። ይህን እያሰበ በአንደኛ ደረጃ የበረራ ክፍል ከተቀመጠበት ወንበር በላይ ባለው ርብራብ ላይ ኣጥፎ ያስቅመጠውን ካፖርት ሲያወርድ ሆስቴስዋ አይኗን እንደጣለችበት ተገንዝቦ ፊት እልሰጣትም ። እንደሁልጊዜው ፀጥ ብሎ ወደ ውጭው በር አመራ። ሲያዩት እንዲህ አድርጎ ትቷቸው መሄዱንም እንደስራው ሁሉ ለምዶታል ። ሰዓቱን አየ ። ከቀትር በኋላ መሆኑን ትገነዘበ። አውሮፕላን ማረፊያው ድረስ መጥቶ የሚጠብቀው መኪና እንዳለ ያውቃል ። ምናልባትም ዛሬውኑ ስብሰባዎች ማካሄድ ይኖርበታል ። ነገ ጧት ቁርስ ላይም ስብሰባ አለው ። ከአንድ ሰዓት ጀምሮ ። የማይክል ሂልያርድ ሕይወት ይኸው ሆኗል ። ማይክል ሂልያርድ ሰለ ስራ እንጂ ስለሌላ ነገር አያስብም ። በርግጥ ያስባል ። ሰለእናቱ ያስባል ። ስለጆርጅ ኮሎዊ ያስባል ። ስለቤንና ስለዌንዲም ያስባል ። እናቱና ጆርጅ ግን የሉም ። ማጆርካ ውስጥ የሙሽርና ወቅት እያሳለፉ አለማቸውን ይቀጫሉ ። ቤንም በዌንዲ እቅፍ ውስጥ በሰላም ኒውዮርክ ውስጥ ይምነሽነሻል ። ሁሉም ተከባካቢ አላቸው። ስለነሱ መጨነቅ አያስፈልግም ። እሱንም ቢሆን የሳንፍራንሲስኮ ሕክምና ማእከል እያቀማጠለ ያኖረዋል ። ይሰራል ከዚህ የበለጠ ምን አለ ? ስራ ሰላም ነው ለማይክል ሂልያርድ ።
እንዳሰበው ሆነ። መኪና ይጠብቀዋል ። ትሳፍሮ ወደ ታላቁ ፌይርሞንት ሆቴል አመራ ። ተይዘዋል የተባሉች ሁለቱም ልዩ ክፍሎች በትክክል እንደተጠበቁ ሆነው እገኛቸው። ሁለቱም ክፍሎች የራሳቸው ሳሎንና መኝታ ያላቸው የትሟሉ ክፍሎች ሲሆኑ ለማይክል እንዱ ክፍል በቂ እንደሆነ ግልፅ ነው። ሁለተኛውን ልዩ ክፍል የተከራየው ሰስብሰባ ሲል ነበር ። ሲያስበው በሁለቱም ውስጥ ሰብሰባዎችን ማካሄድ እንደሚችልም ገሙተ፤ ባንዴ። እቃው ተራግፎ ክፍሉ ውስጥ ከገባ በኋላ ጣመኑ በሚገባ ሳይለቀው ስራ ጀመረ፡። ያን ለት የመጨረሻውን ጉዳይ ተነጋግሮ ሲጨርስ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር ። ሌላ ጉዳይ ሊጨምር አልቻለም። ደከመው፡ ራበው። ይበቃዋል ።
«እንዲህ ነኝና ፤ ምናለ ይደርስሀል …» አለ ቤን «ሰውየው ደህናም አይደለህ ? ለመሆኑ ከእናትህ ጋር ልትደሰት እልነበረም እንዴ ትተኸን የሔድከው ? »
« ጆርጅን ስታይ እኔን ፈንግጣኝ ሔደች » ሶስቱም ሳቁ ። «ደግ አደረገች። አዋቂ ይሉሀል እንዲሀ ነው» አለ ቤን እየሳቀ ። ቤንም ወለሉን አልለቀቀ ፤ ማይክልም አልተመለሰ ። ሶስቱም ባንድነት መደነስ ጀመሩ ። መንገላወድ ልበለው ? ይህ የተሰማት ዌንዲ በሳቅ መንከትከት ጀመረች ። ቤንና ማይክ ያን ያህል ሲደሰቱ ስታይ አደጋው ከመድረሱ በፊት የነበረው ሁኔታ በዓይነ ኅሊናዋ ታያት ። እንዲህ ነበር ማለት ነው የሚደሰቱት ስትል አሰበች ። ዛሬ ይህ በመመለሱ ደስ አላት ። መሳቅ ጀመረች። በመካከሉ ማይክ ቤንን በትያትራዊ ቁጣ እየተመለከተ «ስማ አቭሪ !ከዚህ ጥፋ ብያለሁ ጥፋ ። ከእጮኛህ ጋር ለብቻየ መደነስ እፈልጋለሁ ማለት ይግባህ » ሲል አስጠነቀቀው። «አልሔድም ፣ አይቻልም ብል ምን ሊመጣ !» አለ ቤን «ሶስታችንም ከዳንሱ ወለል ተጠርገን እንድንጣል ታዛለች እናቴ ። ያ ደሞ ጥሩ አይመስለኝም » በዚህ ሁኔታ ከቆዩ በኋላ !
« ስሙ » አለ ማይክ «ለምን ሔደን ኬክ አንበላም? » ተስማሙ ። ኬክ ወዳለበት ሲሔዱ ቤን አቭሪ የጫማውን ሶል አየት ካደረገ በኋላ ሳታየው ዌንዲን በአውራጣቱ እያሳየና አትሰማም አሉ በሚል ሁኔታና ትያትራዊ ሹክሹክታ ፣ «ዳንስ አትችልም ይቺ ሴት ። ጫማዬን ታያለህ ? » አለው። ማይክም «የኔንም ተመልከተው! » ሲል አጋነነ ። «የናንተን አሳያችሁ እኔ ደሞ ነገ በእግሬ መሔዴ እማይቀር ነው » አለች ዌንዲ በማኩረፍ ። በዚህ እየተሳሳቁ እኬኩ ዘንድ ደረሱ። ኬኩን አንስተው እየገመጡ ዳንሱን መመልከት ጀመሩ ። የተጠሩት ሀብታሞች ነበሩ ፤ሁሉም ። በሀብታም ጋለሞቶች አንገት ላይ የተንጠለጠሉት የእንቁና የሉል ጌጦች ያበራሉ። ልጃገረዶችም አበባ መስለዋል፡፡ «ትንሽ ቀደም ብሎ ይህን ባይ ኖሮ » አለ ቤን በውሸት የፀፀት ድምጽ ልጃገረዶቹን ኢያየ ። «እህሳ !» አለ ማይክ ቀልዱን እየተክተለ ።
«እሀህ ... ወደ መፀዳጃ ቤት ብቅ ብዬ የአፍንጫዬን ላብ በፑደር ላስተካክል አስቤ ነበር ። አሁን ግን እናንተ ሰዎች የምትታመኑ ሆናችሁ አልታያችሁኝም ። ይቅርብኝ » አለች ዌንዲ ። «አይ ለዚህስ አታስቢ ። እጠብቅልሻለሁ » አለ ቤን። «ምን ጊዜ ኖሮህ ጌታዬ ! አንተንም የሚጠብቅ በተገኘ ፤ እንኳን አንተ ሰው ልትጠብቅ » ቤን አቭሪ « ግድየለሽም » ብሎ ብርጭቆዋን ተቀብሎ እንደማባረር አደረጋት ። ዌንዲ ወደ ወይዛዝርት ክፍል ስትሔድ ። «ሴት ብሎ ዝም ናት ፤ አይደል ?» አለው ማይክን ። ማይክም አድናቆቱን ከልቡ ገለጸ ። ከዚህ ቀጥሎ ቤን ማይክን በደንብ እየተመለከተ «ሁሌ ሳስበው ምንኛ ታድያለሁ እላለሁ ። ማይክ ያኔ ስነግርህ አለመቆጣትህ…. ስለኔና ስለሷ የነገርኩህ እለት… » አለ። «ለምን እቆጣለሁ!?. . . ደሞም'ኮ አየህ እኔ ለእንደዚህ ዓይነቱ ነገር ጊዜ የለኝም »
« ለወደፊቱ ግን ጊዜ እንደሚኖርህ አልጠራጠርም››
‹‹ምናልባት። ሆኖም ለጊዜው እናንተ ፡ እናንተ ሂዱ፤አግቡ ተጋቡ። እኔ ልጄ ከባድ ሥራ ፤ ከባድ ኃላፊነት አለብኝ » ማይክ ይህን ያህል ቢልም ከዚህ በፊት ይህን የመሰለ ነገር እንደሚያስከፋው አልተከፋም ። ፈገግታ በፊቱ ላይ እንዳለ ነበር እንዲሁ ፈገግ እንዳለ መለኪያውን ተመለከተ ። ከዚያም ለጤናችን በሚል ቅኝት ብድግ አድርጐ «ለሁላችን ! » አለ ሁለቱም ግጥም አድርገው ጠጡ።
•••••••••••••••••••••••••
ማይክል የእጅ ሻንጣውን ጧ እድርጎ ሲዘጋ አውሮፕላኑ የሳንፍራንሲስኮ ማረፊያውን አስፋልት ያዘ ። በመንገድ ላይም እያለ አላረፈም ነበር ። በሳንፍራንሲስኮ ውስጥ በሚቆይበት ጊዜ ብዙ ስራ መስራት አለበት ። ብዙ ስብሰባዎች ይጠብቁታል ። የተለያዩ ሐኪሞችን ማነጋገር ፣ ጥያቄዎችን መመለስ ፡ የተለያዩ ስራዎችን መመልከት አርኪቴክቶችን ማነጋገር፤ ማደራጀት ፤ መመሪያ መስጠት ። በዚያ ላይ ደሞ... ያችን ፎቶ ግራፍ እንሺም ማነጋገር፤ ማግባባት ማለቂያ የለውም ። ሆኖም እንደምንም ይወጣዋል፤ ለምዶታል ። ወይ የምግብ ሳዓቱን በማሳለፍ ወይ የመኝታ ሰዓቱን በመቅነስ ወይም ሌላ። በቻ... ይወጣዋል ። ይህን እያሰበ በአንደኛ ደረጃ የበረራ ክፍል ከተቀመጠበት ወንበር በላይ ባለው ርብራብ ላይ ኣጥፎ ያስቅመጠውን ካፖርት ሲያወርድ ሆስቴስዋ አይኗን እንደጣለችበት ተገንዝቦ ፊት እልሰጣትም ። እንደሁልጊዜው ፀጥ ብሎ ወደ ውጭው በር አመራ። ሲያዩት እንዲህ አድርጎ ትቷቸው መሄዱንም እንደስራው ሁሉ ለምዶታል ። ሰዓቱን አየ ። ከቀትር በኋላ መሆኑን ትገነዘበ። አውሮፕላን ማረፊያው ድረስ መጥቶ የሚጠብቀው መኪና እንዳለ ያውቃል ። ምናልባትም ዛሬውኑ ስብሰባዎች ማካሄድ ይኖርበታል ። ነገ ጧት ቁርስ ላይም ስብሰባ አለው ። ከአንድ ሰዓት ጀምሮ ። የማይክል ሂልያርድ ሕይወት ይኸው ሆኗል ። ማይክል ሂልያርድ ሰለ ስራ እንጂ ስለሌላ ነገር አያስብም ። በርግጥ ያስባል ። ሰለእናቱ ያስባል ። ስለጆርጅ ኮሎዊ ያስባል ። ስለቤንና ስለዌንዲም ያስባል ። እናቱና ጆርጅ ግን የሉም ። ማጆርካ ውስጥ የሙሽርና ወቅት እያሳለፉ አለማቸውን ይቀጫሉ ። ቤንም በዌንዲ እቅፍ ውስጥ በሰላም ኒውዮርክ ውስጥ ይምነሽነሻል ። ሁሉም ተከባካቢ አላቸው። ስለነሱ መጨነቅ አያስፈልግም ። እሱንም ቢሆን የሳንፍራንሲስኮ ሕክምና ማእከል እያቀማጠለ ያኖረዋል ። ይሰራል ከዚህ የበለጠ ምን አለ ? ስራ ሰላም ነው ለማይክል ሂልያርድ ።
እንዳሰበው ሆነ። መኪና ይጠብቀዋል ። ትሳፍሮ ወደ ታላቁ ፌይርሞንት ሆቴል አመራ ። ተይዘዋል የተባሉች ሁለቱም ልዩ ክፍሎች በትክክል እንደተጠበቁ ሆነው እገኛቸው። ሁለቱም ክፍሎች የራሳቸው ሳሎንና መኝታ ያላቸው የትሟሉ ክፍሎች ሲሆኑ ለማይክል እንዱ ክፍል በቂ እንደሆነ ግልፅ ነው። ሁለተኛውን ልዩ ክፍል የተከራየው ሰስብሰባ ሲል ነበር ። ሲያስበው በሁለቱም ውስጥ ሰብሰባዎችን ማካሄድ እንደሚችልም ገሙተ፤ ባንዴ። እቃው ተራግፎ ክፍሉ ውስጥ ከገባ በኋላ ጣመኑ በሚገባ ሳይለቀው ስራ ጀመረ፡። ያን ለት የመጨረሻውን ጉዳይ ተነጋግሮ ሲጨርስ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር ። ሌላ ጉዳይ ሊጨምር አልቻለም። ደከመው፡ ራበው። ይበቃዋል ።
👍15
እዚያው እክፍሉ ውስጥ እንዳለ ስልክ ደውሎ ብስቴካ እንዲያመጡለት እዘዘ ። ብስቴካው እሰኪመጣለት አልጋው ላይ ተንጋሎ እግሩን ቡና ማቅረቢያው ጠረጴዛ ላይ ዘርግቶ ትዘረረ ። ወዲያው «አነጋገርካት ?!» የሚል ድምዕ የሰማ መሰለው። በርግጥ ድምጹን ሰምቶታል ። ግን ግዙፍ ድምፅ አልነበረም ። ድምጹን የሰማው በሀሳቡ ነበር ። ድምጹም የእናቱ ድምፅ ነበር ። ያን ያህል ጉልህ ሆኖ በመሰማቱ ገረመው ። ቀና አለ ። ክፍሉ ከሰዎች ጋር በነበረበች ጊዜ በተጨሰው የሲጋራ ጭሰና በዊስኪ ሽታ ታፍኗል። እንዲያም እለ በሀሳቡ ፤ የምበላውን ነገር እስኢያመጡልኝ ልደውልላት ። እኔንም እንዳልተኛ ይረዳኛል ።
ደወለ ።
«ሄሎ» አለች ሶስት እራቴ ስልኩ ከጮኸ በኋላ ። «እንደምን አመሸሸ ሚሰ አዳምስን። ማይክል ሂልያርድ እባላለሁ» አለ ። ባለችበት ላይ ደንዝዛ ቀረች ። ልትጮህ ቃጣት…..
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
ደወለ ።
«ሄሎ» አለች ሶስት እራቴ ስልኩ ከጮኸ በኋላ ። «እንደምን አመሸሸ ሚሰ አዳምስን። ማይክል ሂልያርድ እባላለሁ» አለ ። ባለችበት ላይ ደንዝዛ ቀረች ። ልትጮህ ቃጣት…..
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍15
‹‹የተሰባበሩ ነፍሶች››
ምዕራፍ አንድ
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
////
ከለሊቱ 8.15 ሞባይሏ ተንጣረረ… በግማሽ መንቃት ተንጠራርታ አጠፋችውና ወደእንቅልፏ ተመለሠች።ከ3 ደቂቃ ብኃላ የቤቷን መደበኛ ስልክ አንቃጨለ...ድምፁ እየሠመጠችበት ካለ የእንቅልፍ ማዕበል ዳግመኛ መንጭቆ አወጣት :: እያጎረመረመች ተነሳችና በዳበሳ መብራቱን አበራችው።እና መቆም በተሳናቸው እግሮቾ እየተንገዳገደች ስልኩ ወዳለበት ቦታ ሄደችና እጀታውን አንስታ ጆሮዋ ላይ ለጠፈች።
‹‹ሄሎ...ማን ል...በል?"
"ዶ/ር አምልጪ...ሊ...ገድ..ሉሽ ...እየ...መጡ ..ነው" ጭል ጭል እያለች ልጥፋ አልጥፋ በማለት ከንፋስ ጋር ትግል እንደገጠመች ቁራጭ ሻማ ለህይወቱ የሚታገል የተቆራረጠ እና እጅጉን የተዳከመ የወንድ ድምፅ..ማንነቱን ወዲያው አወቀችው፡፡
"ኤልያስ..?"
"እባ...ክሽ ፍጠ..ኚ"
‹‹ኤልያስ አንተ ደህና ነህ..?ጎድተውሀል እንዴ?"መልስ ሳይሆን የእቃ መንጓጓትና ድምፅ ነው የተሠማት ..ያንን ተከትሎ ከውጭ ተንጋግቶ የሚገባ ሚመስል የእግር ኮቴ፤ ጩኸትና ጫጫታ ጆሮዋ ላይ ለጥፋ በያዘችው ስልክ ውስጥ እየተሰማት ነው፡፡
‹‹አባዬ ..ምንድነው…?….ቶሎ በሉ አንብላንስ ጋር ደውሉ…››ብዙ ብዙ ድምፅ እየተደራረበ ወደ ጆሮዋ ይገባል፡፡
‹‹ሄሎ ኤልያስ...ሄሎ አናግረኝ…ሌላ ሰው አለ..ባካችሁ አነጋግሩኝ"
ስልኩ አልተዘጋም…ረዘም ላለ ደቂቃ ብትታገስም የሚያናግራት ሰውም አላገኘችም፡፡ ተስፋ ቆርጣ ስልኩን ዘጋችው..የእንቅልፍ ስሜት ተሟጦ ከውስጧ በኖ ስለጠፋ ፍፅም ንቁ ሆናለች።ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው።
"ምንድነው የተፈጠረው?"….ቢጃማዋን አውልቃ ሌላ ልብስ እየለበሰች መልስ የማታገኝላቸውን ጥያቄዎችን እየጠየቀች ነው።
"ግድያን ምን አመጣው? "
የሆነ የመንጎጎት ድምፅ ከውጭ የሠማች መሠላት "ቀስ ብላ ወደመስኮት ተጠጋችና መጋረጃውን በጥቂቱ ገለጥ አድርጋ አይኖቾን ወደውጭ አጨነቆረች።ምንም የሚታያት የተለየ ነገር የለም።
"ውይ ከፍራቻዬ የተነሳ በሀሳቤ የፈጠርኩት ነገር ነው"አለችና ዝግጅቷን ቀጠለች..በለበሰችው ልብስ ላይ ረዘም ያለ ብኒ ቀለም ያለው ባለኮፍያ ኮፓርት ደረበች...ኮመዲኖዎን ከፈተችና ውስጡ የነበረውን ብር በማውጣት ወደ ቦርሳዎ ከተተች።መታወቂያ እና ፓስፓርቷን፤ ኤት.ኤም ካርዶን መረጃ የምታከማችበትን 64 ጂቢ ፍላሽ ያዘችና እቤቷን ወደኃላም ሳታይ ግቢዎንም ለቃ ወጣች።
የተረገመ አጋጣሚ መኪናዋ ግቢዋ ውስጥ የለችም፡፡ የተወሰነ ያልተለመደ ድምጽ ስላሰማቻት ማታ ወደቤት ስትገባ ነበር ደንበኞቾ የሆኑ ጋራዥ ጋር ጎራ ብላ ለጥዋት እንዲያደርሱላት ጥላላቸው በኮንትራት ታኪሲ ወደቤቷ የገባችው…..ስለዚህ አሁን ያላት ምርጫ በእግር ማምለጥ ነው፡፡
ከቤቷ የውጨኛው በር 20 ሜትር ሳትርቅ ከሩቅ እየቀረበ የሚመጣ የመኪና ድምፅ ሰማች፡፡ በደመነፍስ ቅፅበታዊ ውሳኔ ወሰነች...፡፡ዘላ ከመንገድ ወጣችና በጨለማ የተጋረደ መሸሸጊያ በመፈለግ እራሷን አጣጥፍ በመወሸቅ የሚሆነውን ለማየት እይታዋን ወደመንገድ አስተካከለች ።አልተሳሳተችም አንድ የቀብር አስፈፃሚዎች ድርጅት ንብረት የምትመስል ጥቁር ጨለማ ሚኒባስ እየተክለፈለፈች መጣችና ከእሷ ቤት በራፍ ጋር ስትደርስ ቀጥ ብላ ቆመች። ወዲያው የኃላው በራፍ ተንሸራቶ ተከፈተና ሶስት የሆሊውድ አክሽን ፊልም ላይ የሚተውኑ ሚመስሉ የተወጣጠሩ ወጠምሻ ሰዎች ድብ ድብ እያሉ ወረድ።.
"እኚ ሁሉ ለአንድ ሴት ?"ስትል በውስጧ ጠየቀች
"አሁን በዚህ ሰውነታቸው ይሄን በአደገኛ ሽቦ የታጠረ ግዙፍ ግንብ አጥር እንዴት አድርገው ዘለው ሊገቡ ነው?›› እያለች ስታሰላስል ይግረምሽ ብለው ቀጥታ እንደቤቱ አባወራ ወደበራፍ ተጉዘው በተዝናና ሁኔታ ቁልፍ ከኪሳቸው አውጥተው በመክፈት ወደውስጥ ሲገብ ባለማመን ተመለከተች።ይሄ እንዴት ሆነ የቤቷ ቁልፍ እሷና ፕሮፌሰሩ ጋር ነበር ያለው፡፡ከዛን በላይ በዛ አካባቢ መቆየት እራስን ለአደጋ ማጋለጥ ነው ብላ ስላመነች ሚኒባሱ ውስጥ የቀረው ሹፌር እንዳያያት ተጠንቅቃ ከተወሸቀችበት ወጥታ ጥግ ጥጉን እየታከከች ከሰፈሯ ርቃ ወጣች።
አሁን ካለችበት መኖሪያ ቤቷ ከሚገኝበት ወሎ ሰፈር ወደብዙ አቅጣጫ ሚወስዱ መንገዶች አሉ..ወደቦሌ መሄድ ትችላለች….በአቋራጭ ወደላንቻ መሄድ ትችላለች..እሷ ግን የያዘችው ወደጎተራ የሚመራውን መስመር ነው….…ጎተራ ማሳለጫው ጋር ስትደርስ ለተወሰነ ደቂቃ ቆመችና ለሰከንድ አሰላሰለች …ከፊት ለፊቷ ሌላ ሶስት ምርጫ አጋጠማት ፡፡ወደግራዋ ታጥፋ ወደ ሳሪስ መሄድ ወደ ቀኞ ታጥፋ ወደ ላንቻና ስቴዲዬም መጎዝ ወይም የፊት ለፊቱን አስፓልት ይዛ ወደቄራ መሸምጠጥ….
ያለምንም ደጋፊ ምክንያት የፊት ለፊቱን መርጣ ጉዞዋን ቀጠለች…...አስር ደቂቃ ከተጓዘች ቡኃላ ከሰፈሯ በጣም መራቋንና አዳኞቾም በቀላሉ ሊያገኞት በሚችሉባት አቅጣጫና ስፍራ ላይ አለመሆኗን ስትረዳ እራሷን ገታ ተረጋግታ ማሰብ ጀመረች ፡፡
‹‹ከኃላ ከሚያሳድደኝ ሞት ሳመልጥ ፊት ለፊቴ ያልታሰበበት ሞት እንዳይገጥመኝ"አለችና ዙሪያዎን አማተረች….…ከጭፈራ ቤቶች የሚወጣ ድምፅ እንኳን አይሰማትም ወይም ከመሸታ ቤት ወጥቶ ወደቤቱ እየተወለጋገደ ሚሄድ ሰካራም በስፍራው አይታይም……ብቻ የተወሰኑ መቶ ሜትሮች ወደፊት ጠጋ ብሎ የቄራው አጥር አካባቢ የሚልከሰከሱ የተወሰኑ ውሾች ይታዬታል..በተረፈ አካባቢው ፍፅም ጭር ብሏል... መስቀለኛ መንገድ ላይ ነው ያለችው… ከፊት ለፊቷ በአንድ ሜትር ርቀት የትራፊክ መብራት አለ……ትንሽ ሳብ ብሎ ወደሚታየው የባስ ፌርማታ አመራችና ጥጎን ይዛ ቁጭ አለች።
‹‹ቀጥታ ፖሊስ ጣቢያ ሄጄ ላመልክት?›› የሚል ሀሳብ መጣላት፡፡ግን ነገሩ ፖሊስ ጆሮ አንዴ ከገባ ወደኃላ የሚመለስ ነገር አይኖርም…ሄዶ ሄዶ ወንጀሉ በግለሰቦች ደረጃ ታጥሮ አይቀርም ወደ ሆስፒታላቸውም መዛመቱ አይቀርም…ያ ሆስፒታል ደግሞ የእሷም ሀብት ነው……ጠቅላላ ልፋቷንና ህልሞን ያዘለ ተቋም ነው….የእሱ መውደም እሷንም ቀጥታ ያወድማታል….ይሄንን ሁሉ በታትና አሰበችና ‹‹የነገሩን ጭራ በደንብ ሳልይዝ ለጊዜውም ቢሆን ፖሊስ ጋ አልሄድም ››ብላ ሀሳቧን ሰረዘችው፡፡
‹‹እሺ ሌላ ምን ማድረግ እችላለሁ..?››በቀጣይ እራሷን የጠየቀችው ጥያቄ ነው፡፡አሁን ምን ላድርግ..?ማን ጋር ልደውል?ስትል ፕሮፌሰሩ ወደ አእምሮዋ መጣ፡፡
…እዚህ ጉዳይ ላይ ፕሮፌሰሩ አለበት?"ስትል ህሊናን አዙሮ የሚደፋ ጥያቄ እራሷን ጠየቀች።
ኘሮፌሰር ማለት የስራ ባለደረባዋ ነው...ፕሮፌሰር ማለት የረጅም ጊዜ የቅርብ ጓደኛዋ ነው...ፕሮፌሰር ማለት የሶስት አመት ፍቅረኛዋ ነው...ኘሮፌሰር ማለት ከአራት ወራት ብኃላ ልታገባው ሽር ጉድ ያለችለት ያለ የወደፊት ባሏ እና የልጇቾ አባት ለመሆን ጫፍ ላይ ያለ ሰው ነው....
ፕሮፌሰር ብዙ የውጭና የሀገር ውስጥ ዪኒቨርሲቲዎች ለሁለት አስር አመታት ያስተማረ በአለም አቀፍ የምርምር ጆርናሎች አያሌ የጥናት ስራዎቹን ያሳተመ የአደባባይ ምሁር ነው.....በዚህ ላይ ሀገሪቱ ከለቻቸው ከአንድ እጣት ከማይበልጡ የልብ ቀዶ ህክምና ሀኪሞች አንዱ ነው፡፡ታዲያ እንዴት ነው ይሄ ሰው የእሷን የትሙት በቃ ውሳኔ ከሌሎች ገዳይና ማጅራት መቺዎቾ ጋር በማበር ሊፈርም የሚችለው?እሷ ስለሆነች አይደለም ሌላ ማንስ ቢሆን እንዴት እንዲህ ያደርጋል? ይሄ ሰው እኮ ለእንስሳት ነፍስ ሁሉ አንጀቱ ከመንሰፍሰፍ የተነሳ ቬጂቴሪያል የሆነ ሰው ነው?..ምንም ሊዋጥላት አልቻለም፡፡
ምዕራፍ አንድ
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
////
ከለሊቱ 8.15 ሞባይሏ ተንጣረረ… በግማሽ መንቃት ተንጠራርታ አጠፋችውና ወደእንቅልፏ ተመለሠች።ከ3 ደቂቃ ብኃላ የቤቷን መደበኛ ስልክ አንቃጨለ...ድምፁ እየሠመጠችበት ካለ የእንቅልፍ ማዕበል ዳግመኛ መንጭቆ አወጣት :: እያጎረመረመች ተነሳችና በዳበሳ መብራቱን አበራችው።እና መቆም በተሳናቸው እግሮቾ እየተንገዳገደች ስልኩ ወዳለበት ቦታ ሄደችና እጀታውን አንስታ ጆሮዋ ላይ ለጠፈች።
‹‹ሄሎ...ማን ል...በል?"
"ዶ/ር አምልጪ...ሊ...ገድ..ሉሽ ...እየ...መጡ ..ነው" ጭል ጭል እያለች ልጥፋ አልጥፋ በማለት ከንፋስ ጋር ትግል እንደገጠመች ቁራጭ ሻማ ለህይወቱ የሚታገል የተቆራረጠ እና እጅጉን የተዳከመ የወንድ ድምፅ..ማንነቱን ወዲያው አወቀችው፡፡
"ኤልያስ..?"
"እባ...ክሽ ፍጠ..ኚ"
‹‹ኤልያስ አንተ ደህና ነህ..?ጎድተውሀል እንዴ?"መልስ ሳይሆን የእቃ መንጓጓትና ድምፅ ነው የተሠማት ..ያንን ተከትሎ ከውጭ ተንጋግቶ የሚገባ ሚመስል የእግር ኮቴ፤ ጩኸትና ጫጫታ ጆሮዋ ላይ ለጥፋ በያዘችው ስልክ ውስጥ እየተሰማት ነው፡፡
‹‹አባዬ ..ምንድነው…?….ቶሎ በሉ አንብላንስ ጋር ደውሉ…››ብዙ ብዙ ድምፅ እየተደራረበ ወደ ጆሮዋ ይገባል፡፡
‹‹ሄሎ ኤልያስ...ሄሎ አናግረኝ…ሌላ ሰው አለ..ባካችሁ አነጋግሩኝ"
ስልኩ አልተዘጋም…ረዘም ላለ ደቂቃ ብትታገስም የሚያናግራት ሰውም አላገኘችም፡፡ ተስፋ ቆርጣ ስልኩን ዘጋችው..የእንቅልፍ ስሜት ተሟጦ ከውስጧ በኖ ስለጠፋ ፍፅም ንቁ ሆናለች።ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው።
"ምንድነው የተፈጠረው?"….ቢጃማዋን አውልቃ ሌላ ልብስ እየለበሰች መልስ የማታገኝላቸውን ጥያቄዎችን እየጠየቀች ነው።
"ግድያን ምን አመጣው? "
የሆነ የመንጎጎት ድምፅ ከውጭ የሠማች መሠላት "ቀስ ብላ ወደመስኮት ተጠጋችና መጋረጃውን በጥቂቱ ገለጥ አድርጋ አይኖቾን ወደውጭ አጨነቆረች።ምንም የሚታያት የተለየ ነገር የለም።
"ውይ ከፍራቻዬ የተነሳ በሀሳቤ የፈጠርኩት ነገር ነው"አለችና ዝግጅቷን ቀጠለች..በለበሰችው ልብስ ላይ ረዘም ያለ ብኒ ቀለም ያለው ባለኮፍያ ኮፓርት ደረበች...ኮመዲኖዎን ከፈተችና ውስጡ የነበረውን ብር በማውጣት ወደ ቦርሳዎ ከተተች።መታወቂያ እና ፓስፓርቷን፤ ኤት.ኤም ካርዶን መረጃ የምታከማችበትን 64 ጂቢ ፍላሽ ያዘችና እቤቷን ወደኃላም ሳታይ ግቢዎንም ለቃ ወጣች።
የተረገመ አጋጣሚ መኪናዋ ግቢዋ ውስጥ የለችም፡፡ የተወሰነ ያልተለመደ ድምጽ ስላሰማቻት ማታ ወደቤት ስትገባ ነበር ደንበኞቾ የሆኑ ጋራዥ ጋር ጎራ ብላ ለጥዋት እንዲያደርሱላት ጥላላቸው በኮንትራት ታኪሲ ወደቤቷ የገባችው…..ስለዚህ አሁን ያላት ምርጫ በእግር ማምለጥ ነው፡፡
ከቤቷ የውጨኛው በር 20 ሜትር ሳትርቅ ከሩቅ እየቀረበ የሚመጣ የመኪና ድምፅ ሰማች፡፡ በደመነፍስ ቅፅበታዊ ውሳኔ ወሰነች...፡፡ዘላ ከመንገድ ወጣችና በጨለማ የተጋረደ መሸሸጊያ በመፈለግ እራሷን አጣጥፍ በመወሸቅ የሚሆነውን ለማየት እይታዋን ወደመንገድ አስተካከለች ።አልተሳሳተችም አንድ የቀብር አስፈፃሚዎች ድርጅት ንብረት የምትመስል ጥቁር ጨለማ ሚኒባስ እየተክለፈለፈች መጣችና ከእሷ ቤት በራፍ ጋር ስትደርስ ቀጥ ብላ ቆመች። ወዲያው የኃላው በራፍ ተንሸራቶ ተከፈተና ሶስት የሆሊውድ አክሽን ፊልም ላይ የሚተውኑ ሚመስሉ የተወጣጠሩ ወጠምሻ ሰዎች ድብ ድብ እያሉ ወረድ።.
"እኚ ሁሉ ለአንድ ሴት ?"ስትል በውስጧ ጠየቀች
"አሁን በዚህ ሰውነታቸው ይሄን በአደገኛ ሽቦ የታጠረ ግዙፍ ግንብ አጥር እንዴት አድርገው ዘለው ሊገቡ ነው?›› እያለች ስታሰላስል ይግረምሽ ብለው ቀጥታ እንደቤቱ አባወራ ወደበራፍ ተጉዘው በተዝናና ሁኔታ ቁልፍ ከኪሳቸው አውጥተው በመክፈት ወደውስጥ ሲገብ ባለማመን ተመለከተች።ይሄ እንዴት ሆነ የቤቷ ቁልፍ እሷና ፕሮፌሰሩ ጋር ነበር ያለው፡፡ከዛን በላይ በዛ አካባቢ መቆየት እራስን ለአደጋ ማጋለጥ ነው ብላ ስላመነች ሚኒባሱ ውስጥ የቀረው ሹፌር እንዳያያት ተጠንቅቃ ከተወሸቀችበት ወጥታ ጥግ ጥጉን እየታከከች ከሰፈሯ ርቃ ወጣች።
አሁን ካለችበት መኖሪያ ቤቷ ከሚገኝበት ወሎ ሰፈር ወደብዙ አቅጣጫ ሚወስዱ መንገዶች አሉ..ወደቦሌ መሄድ ትችላለች….በአቋራጭ ወደላንቻ መሄድ ትችላለች..እሷ ግን የያዘችው ወደጎተራ የሚመራውን መስመር ነው….…ጎተራ ማሳለጫው ጋር ስትደርስ ለተወሰነ ደቂቃ ቆመችና ለሰከንድ አሰላሰለች …ከፊት ለፊቷ ሌላ ሶስት ምርጫ አጋጠማት ፡፡ወደግራዋ ታጥፋ ወደ ሳሪስ መሄድ ወደ ቀኞ ታጥፋ ወደ ላንቻና ስቴዲዬም መጎዝ ወይም የፊት ለፊቱን አስፓልት ይዛ ወደቄራ መሸምጠጥ….
ያለምንም ደጋፊ ምክንያት የፊት ለፊቱን መርጣ ጉዞዋን ቀጠለች…...አስር ደቂቃ ከተጓዘች ቡኃላ ከሰፈሯ በጣም መራቋንና አዳኞቾም በቀላሉ ሊያገኞት በሚችሉባት አቅጣጫና ስፍራ ላይ አለመሆኗን ስትረዳ እራሷን ገታ ተረጋግታ ማሰብ ጀመረች ፡፡
‹‹ከኃላ ከሚያሳድደኝ ሞት ሳመልጥ ፊት ለፊቴ ያልታሰበበት ሞት እንዳይገጥመኝ"አለችና ዙሪያዎን አማተረች….…ከጭፈራ ቤቶች የሚወጣ ድምፅ እንኳን አይሰማትም ወይም ከመሸታ ቤት ወጥቶ ወደቤቱ እየተወለጋገደ ሚሄድ ሰካራም በስፍራው አይታይም……ብቻ የተወሰኑ መቶ ሜትሮች ወደፊት ጠጋ ብሎ የቄራው አጥር አካባቢ የሚልከሰከሱ የተወሰኑ ውሾች ይታዬታል..በተረፈ አካባቢው ፍፅም ጭር ብሏል... መስቀለኛ መንገድ ላይ ነው ያለችው… ከፊት ለፊቷ በአንድ ሜትር ርቀት የትራፊክ መብራት አለ……ትንሽ ሳብ ብሎ ወደሚታየው የባስ ፌርማታ አመራችና ጥጎን ይዛ ቁጭ አለች።
‹‹ቀጥታ ፖሊስ ጣቢያ ሄጄ ላመልክት?›› የሚል ሀሳብ መጣላት፡፡ግን ነገሩ ፖሊስ ጆሮ አንዴ ከገባ ወደኃላ የሚመለስ ነገር አይኖርም…ሄዶ ሄዶ ወንጀሉ በግለሰቦች ደረጃ ታጥሮ አይቀርም ወደ ሆስፒታላቸውም መዛመቱ አይቀርም…ያ ሆስፒታል ደግሞ የእሷም ሀብት ነው……ጠቅላላ ልፋቷንና ህልሞን ያዘለ ተቋም ነው….የእሱ መውደም እሷንም ቀጥታ ያወድማታል….ይሄንን ሁሉ በታትና አሰበችና ‹‹የነገሩን ጭራ በደንብ ሳልይዝ ለጊዜውም ቢሆን ፖሊስ ጋ አልሄድም ››ብላ ሀሳቧን ሰረዘችው፡፡
‹‹እሺ ሌላ ምን ማድረግ እችላለሁ..?››በቀጣይ እራሷን የጠየቀችው ጥያቄ ነው፡፡አሁን ምን ላድርግ..?ማን ጋር ልደውል?ስትል ፕሮፌሰሩ ወደ አእምሮዋ መጣ፡፡
…እዚህ ጉዳይ ላይ ፕሮፌሰሩ አለበት?"ስትል ህሊናን አዙሮ የሚደፋ ጥያቄ እራሷን ጠየቀች።
ኘሮፌሰር ማለት የስራ ባለደረባዋ ነው...ፕሮፌሰር ማለት የረጅም ጊዜ የቅርብ ጓደኛዋ ነው...ፕሮፌሰር ማለት የሶስት አመት ፍቅረኛዋ ነው...ኘሮፌሰር ማለት ከአራት ወራት ብኃላ ልታገባው ሽር ጉድ ያለችለት ያለ የወደፊት ባሏ እና የልጇቾ አባት ለመሆን ጫፍ ላይ ያለ ሰው ነው....
ፕሮፌሰር ብዙ የውጭና የሀገር ውስጥ ዪኒቨርሲቲዎች ለሁለት አስር አመታት ያስተማረ በአለም አቀፍ የምርምር ጆርናሎች አያሌ የጥናት ስራዎቹን ያሳተመ የአደባባይ ምሁር ነው.....በዚህ ላይ ሀገሪቱ ከለቻቸው ከአንድ እጣት ከማይበልጡ የልብ ቀዶ ህክምና ሀኪሞች አንዱ ነው፡፡ታዲያ እንዴት ነው ይሄ ሰው የእሷን የትሙት በቃ ውሳኔ ከሌሎች ገዳይና ማጅራት መቺዎቾ ጋር በማበር ሊፈርም የሚችለው?እሷ ስለሆነች አይደለም ሌላ ማንስ ቢሆን እንዴት እንዲህ ያደርጋል? ይሄ ሰው እኮ ለእንስሳት ነፍስ ሁሉ አንጀቱ ከመንሰፍሰፍ የተነሳ ቬጂቴሪያል የሆነ ሰው ነው?..ምንም ሊዋጥላት አልቻለም፡፡
👍28❤1
‹‹አዎ ኤሊያስን ያጠቁትም እሷን ለማስወገድ እቤቷ ድረስ የሚገድላት ሰው የላኩት ሌሎች የኮሚቴ አባላት ናቸው ፡፡በተለይ ሼክ ጠሀ እና አቶ ከፍያለው?አዎ እነሱ ናቸው ወንጀላቸውን ለማዳፈን ከፕሮፌሰሩ ጀርባ ገዳይ እስኮድ ያሰማሩት"ስትል ድምዳሜ ላይ ደረሰች።
"ግን የቤቴን መክፈቻ ቁልፍ ፕሮፌሰሩ ብቻ ነው ያለው እሱ ካልሰጣቸው ማን ሊሰጣቸው ይችላል?››አስጠሊታ ስሜት የሚያጭር ጥያቄ በምናቧ ተሠነቀበረ..ነው ወይስ ትናንት አባቴ ሞቶል ብሎ ድንገት ስራውን ጥሎ ወደክፍለሀገር የሄደው የቤቷ ዘበኛ ስራ ይሆን
."አዎ ወይ ዘበኛውን በብር ኃይል አታለውት እንዲተባበራቸው አድርገዋል…ወይ ደግሞ ከፕሮፈሰሩ ቁልፉን ሰርቀውት ይሆናል...አዎ እንደዛ ነው የሚሆነው"እርግጠኛ ሆነች።
ስልኳን አነሳችና ደወለችለት ፡፡ዘጠኝ ሰዓት እየተቃረበ ነው፡፡በሁለት ጥሪ ተነሳ፡፡
"ፕሮፌሰር እንዴት ነህ?"
"ደህና ነኝ …ምነው ደህና አይደለሽም እንዴ?"
‹‹ሰላም ነኝ››
‹‹የት ነሽ?"
"እንዴት የት ነሽ እቤቴ ነኛ"ኮስተር ብላ መለሰችለት፡፡
‹‹እቤት የት..ማለቴ እንዴት...?"የሚርገበገብ የተሰባሀረ እና ድንብርብሩ የወጣ ድምፅ
"እንዴት ማለት..?."
"ማለቴ በዚህ ሰአት በሰላም ልትደውይልኝ አትችይም ብዬ ነው ፡፡ሰዓቱን አይተሽዋል...?ምነው አመመሽ እንዴ?"
ልንገረው አልንገረው ...አለበት ?የለበትም ? ከፍተኛ ሙግት ከራሷ ጋር ገጠመች፡፡
"አረ አናግሪኝ...ካልሆነ ልምጣ እንዴ?"
"የት"
"እንዴት የት? እቤቴ ነኝ አላልሺኝም እንዴ?"
"አይ እቤት አይደለሁም..."
"አረ ግራ አታጋቢኝ ?የሆንሺውን ነገር ነገሪኝ"
‹‹መቼስ ያን የሚያህል ሰውዬ በዚህ መጠን አያስመስልም››አለችና እውነቱን መናገር ጀመረ…
‹‹የሆኑ ሰዎች ሊያጠቁኝ እቤቴ ድረስ መጥተው ነበር...››
"በፈጣሪ ሊያጠቁኝ ማለት ?›› ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
"ግን የቤቴን መክፈቻ ቁልፍ ፕሮፌሰሩ ብቻ ነው ያለው እሱ ካልሰጣቸው ማን ሊሰጣቸው ይችላል?››አስጠሊታ ስሜት የሚያጭር ጥያቄ በምናቧ ተሠነቀበረ..ነው ወይስ ትናንት አባቴ ሞቶል ብሎ ድንገት ስራውን ጥሎ ወደክፍለሀገር የሄደው የቤቷ ዘበኛ ስራ ይሆን
."አዎ ወይ ዘበኛውን በብር ኃይል አታለውት እንዲተባበራቸው አድርገዋል…ወይ ደግሞ ከፕሮፈሰሩ ቁልፉን ሰርቀውት ይሆናል...አዎ እንደዛ ነው የሚሆነው"እርግጠኛ ሆነች።
ስልኳን አነሳችና ደወለችለት ፡፡ዘጠኝ ሰዓት እየተቃረበ ነው፡፡በሁለት ጥሪ ተነሳ፡፡
"ፕሮፌሰር እንዴት ነህ?"
"ደህና ነኝ …ምነው ደህና አይደለሽም እንዴ?"
‹‹ሰላም ነኝ››
‹‹የት ነሽ?"
"እንዴት የት ነሽ እቤቴ ነኛ"ኮስተር ብላ መለሰችለት፡፡
‹‹እቤት የት..ማለቴ እንዴት...?"የሚርገበገብ የተሰባሀረ እና ድንብርብሩ የወጣ ድምፅ
"እንዴት ማለት..?."
"ማለቴ በዚህ ሰአት በሰላም ልትደውይልኝ አትችይም ብዬ ነው ፡፡ሰዓቱን አይተሽዋል...?ምነው አመመሽ እንዴ?"
ልንገረው አልንገረው ...አለበት ?የለበትም ? ከፍተኛ ሙግት ከራሷ ጋር ገጠመች፡፡
"አረ አናግሪኝ...ካልሆነ ልምጣ እንዴ?"
"የት"
"እንዴት የት? እቤቴ ነኝ አላልሺኝም እንዴ?"
"አይ እቤት አይደለሁም..."
"አረ ግራ አታጋቢኝ ?የሆንሺውን ነገር ነገሪኝ"
‹‹መቼስ ያን የሚያህል ሰውዬ በዚህ መጠን አያስመስልም››አለችና እውነቱን መናገር ጀመረ…
‹‹የሆኑ ሰዎች ሊያጠቁኝ እቤቴ ድረስ መጥተው ነበር...››
"በፈጣሪ ሊያጠቁኝ ማለት ?›› ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍18
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ሆራ ጨርቆሉ ማዝ ሆኖ ደም፣ ወተት፣ ሥጋና ማር እየተቀለበ፣ ከሰልና ቅቤ ተቀላቅሎ ፊቱንና የተላጨውን ራሱን
ተቀብቶ፣ ከሚዜው ጋር ውሎው ጫካ ነው። ከሎ የወገኖቹን ባህላዊ
የጋብቻ ሥነ ሥርዓት ለመጀመር ምክንያቱ አንድ ነበር ፍቅር። ሥነ ሥርዓቱን እያሟላ ሲመጣ ግን፣ አዲስ ስሜት አእምሮው ማፍለቅ ጀመረ።
ወገኖቹ የሆኑት ሐመሮች በአንድ ወቅት ከማኅበረሰባቸው
አግልለውት ነበር" ያውም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ፣ እንዲሞት ተደርጎ ተጥሏል። ከሚወዳቸው ወላጆቹና እኅት ወንድሞቹ፣ ከሚያፈቅረው የፍየልና ጥጃ ጥበቃው፣ ከቦረቀበትና ከተጫወተበት ማራኪ
የሐመር ምድር ተጎትቶ ተወስዶ፣ በጦር ተወግቶ፣ ወደ ገደልም ተገፍቶ፣ የሞትን ጽዋ ጕድጓድ ውስጥ እንዲቀምስ ተደርጎ ነበር።
የሕፃንና የወጣትነት አእምሮው ይህን የደረሰበትን መራራ ጽዋ
ጠንጥኖ በገዛ አእምሮው የዛን ጊዜውን መሪ ተዋናይ ሲያስታውሰው አፉን ደም ደም ይለዋልI ልሳኑ ይዘጋበታል ሕይወቱ የላሸቀ፣ የተበላሸ እንቍላል ሆኖ ባለመጥቀሙ ተሽቀንጥሮ የተወረወረ
ይመስለዋል።
የዛኔው የቍስል ስሜት ምልክት ጥሎ ካለፈ ዓመታት ቢቈጠሩም
ሁሌም አጋጣሚውን ባስታወሰ ቍጥር ሥቃዩ ይጀምረዋል" ሞት
ጒሮሮው ላይ ቆሞ ስለታም ሰይፉን ጕሮሮው ውስጥ ሊቀረቅርበት ሲመጣ ይታየውና ይባባል፤ መሸሻ፣ መደበቂያ፣ ማምለጫ መንገድ ያጣል። ከራስ ሕሊና የሚፈጠር አስፈሪ ነገር በምን አንቀጽ
ይከሰሳል! ምን ዓይነት ጠንካራ በር ያግደዋል?
«እኮ ለምን? ምን ባደረኳቸው በእንቦቀቅላነቴ ወቅት ልሸከመው
የማልችለውን ሞትና ፍርሃት አሸከሙኝ ምን ባደረኳቸው ከእናት ጉያ ነጥለው፣ አብሬአቸው ከምዘላቸው ጓደኞቼ ለይተው ለመከራ
ዳረጉኝ?» ባለፈው ሕይወቱ ከሎ ሆራ ራሱን በራሱ እየጠየቀ መልስ ያጣበት ጉዳይ ነው" ለብዙ ዓመታት የዕለት ተዕለት ትዕይንት ሆኖ የሚቀርበውን የቆየ ትዝታ ባስታወሰ ቍጥር የመጨረሻውን ረድፍ
ይዘው የሚደረደሩት ጥያቄዎች ከላይ የተዘረዘሩት ሲሆኑ መልሳቸው ግን ሰው ወይንም መዝገበ ቃላት ሳይመልሰው እስከ ዛሬ አብረውት ዘልቀዋል"
ከሎ ሆራ በሕይወቱ ሙሉ ያምንበት የነበረው አሁን ግን እንደ አጉም እየበነነ አልጨበጥልህ ይለው ጀምሯል" ወደ ወገኖቹ ብቻ
ሳይሆን ወደ ሐመር ምድር ለመመለስ አልሞም አያውቅም። የኖረው
እነሱን ሲረግምና ሲሸሽ ነው። አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንደ ጨረሰ በአገር አቀፍ የመሠረተ ትምህርት ዘመቻውም ወቅት፣ ከዘመቻው መቅረት ወይንም መለወጥ አልቻልህ ብሎት እንጂ እግሩንም
ለማንሣት አያስብም ነበር" የዛኔም ቢሆን ደግሞ፣ «ጌታዋን የተማመነች በግ...» እንዲሉ፣ መንግሥትን ተማምኖ እንጂ እንኳን የከፍተኛ ትምህርት ዕድሉ ሌላው ሁሉ ነገር ቢቀር ወደ ሐመር
ተመልሶ ለመምጣት አያስብም። በቆይታውም አይጥና ድመት ሆነው
ቆዩ እንጂ አልተቀራረቡም።
አሁን ግን ከሎ ሆራ አይጡም ድመቱም እሱ እንደሆነ በመቁጠር ወደ ቤቱና ወደ ባለቤቶቹ መመለስ ይከጃጅለዋል"
ከሎ ሆራ በእርግጥ አሁን ያለው ሐመር ነው" ሐመሮች በተለይም ዘመዶቹ ባዩት ቍጥር ይሳሱለታል" ወላጅ እናቱ ልክ እንደ ልጅነቱ እጆቹን እያፍተለተሉ እንባቸውን ያፈሱለታል ያላቸውንና
ቤት ያፈራውን ጎጆው ድረስ ተሸከመው ያመጡለታል፤ ከብት ለመዝለል በየዘመዶቹ ቤት ሲዞር እንደ ብርቅ ስመው አስተናግደውታል ከብት በሚዘለልበትም ወቅት ዘመዶቹ ዝግጅቱን በማሟላትና በለምለም ቅጠል መልካም ዕድልን በመመኘት አብረውት
ተጨንቀዋል ልጃገረድ ዘመዶቹም የዝምናድ ምልክት የሆነውን
ግርፋት በወኔና በፍላጎት ተገርፈውለታል።
ከሎ ሆራ ይህን ሁሉ ካመዛዘነ በኋላ ለዘመናት በአእምሮው ተቀብረው
የኖሩትን ጥያቄዎች ከመቃብራቸው እያወጣ መጣል ጀምሯል እናቱ እንደ ብርቅዬ ልጃቸው፣ ወንድምና እኅቶቹ እንደ
ተወዳጅ ወንድማቸው አድርገው ይቈጥሩታል“ ታዲያ ማንን ይጥላ?
ለሥቃዩ ሁሉ ተጠያቂው ማን ሊሆን? ለምንስ እንዲሞት አድርገው
ጣሉት?
ከሎ ሆራ አእምሮው ለጥያቄዎቹ መልስ አገኘ" ለመጣል ያበቃው ባህል ነው። እሱን ለመጉዳት፣ ከእናቱ ጉያ ለመነጠል የደፈሩት የአገር ሽማግሎች አንኳን ለሱ ከሜዳ ተነሥተው hፉ አላሰቡም”
የሐመር ሕዝብ ባህሉን አክባሪ፣ ካለ ዘመናዊ ሕግና ደምብ በባህላዊ ደምቦችና ሥርዓቶች የሚመራ፣ ተፋቅሮና ተዛዝኖ የሚኖር
ማኅበረሰብ ነው። ማንንም የማያገል፣ ባህሉን ከመከተል ዝንፍ
የማይል ሕዝብ መሆኑን አረጋግጧል። «ታዲያ ወገኖቼ በእኔ ላይ
ብቻ ልዩ ቅጣት አልፈጸሙብኝማ። ባህላዊው ደንብ መሟላት
ነበረበትና ተገደልኩ፤ ከሙትነት ተነሥቼ ስመጣ ግን ተቀበሉኝ" አሁን የተቀበሉኝ ስለ ተማርሁ፣ ከእነሱ የተለየ ሕይወት ስላየሁ አይደለም ባህሉ ስለሚፈቅድ ብቻ ነው ታዲያ ባህል ባመጣው ጦስ ወገኖቼን መጥላት አለብኝ?» ጨርቆሌ ማዝ ተብሎ ጫካ ለጫካ
የሚዞረው ከሎ ሆራ ዕድሜ ልኩን አእምሮውን ሰንገው ይዘው ያስጨንቁት የነበሩትን ጥያቄዎች መመለስ ጀመረ።
።።።።።።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣
ሰው ራሱን ማስተማር የሚችል ታላቅ ፍጡር ነው" በተለይም ታታሪ ሰዎች ከአምላክ የተሰጠውን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ
እየተጣጣሩ ናቸው። እየተሳካላቸውም ነው
በምርምር እንደ እብድ ያልለፈለፈ ፈላስፋ፣ ቀንና ሌሊት በምርምርና በሙከራ እልሁን ያልጨረሰ ሳይንቲስት፣ እንደ
ሚፈጥራቸው ገጸባሕርያት ስቅስቅ ብሎ ያላዘነ አሊያም በደስታ ያልተፍነከነከ ደራሲ፣ የሚሥለውን ሥዕል የተዋጣ ለማድረግ
ረቂቁን የተፈጥሮ ምሥጢር ለማወቅ በመጣጣር ያልዳከረ ሠዓሊ
l ሊኖር አይችልም" ካለም ከነሆድ አምላኩ ወገን የሆነ አስመሳይ መሆኑ ነው"
ካርለት የሐመር ሴቶችን ሕይወትና ማኅበራዊ ተሳትፎ የምታጠና
ወጣት አንትሮፖሎጂስት ናት ያለችበት ዘመን ሳይንስና ተክኖሎጂ የመጠቀበት፣ የሰው ልጆች በአዲስ ግኝቶች የሚንበሸበሹበት ወቅት ነው„
«እንደ ዱሮው ዘመን ይህን ይህን ማድረግ ያስቸግራል የሚል አዳማጭም ሆነ ተመልካች አያገኝም" መሆን አለበት ብዬ ብዙ
ሞከርኩኝ ፈተናና ሥቃይም ገጠመኝ፤ በመጨረሻ ግን ተሳካልኝ ሲባል አድናቆታዊው ጭብጨባ መቅለጡን አውቃለሁ። የሰው ልጅ በውኃ ውስጥ በባቡር መጓዝ በቻለበት፣ ሕዋ ላይ ከተማ በከተመበት፣አይጥና ድመት አብረው እንዲጫወቱ በተደረገበት ወቅት እኔስ
ሰውነቴ ቢቈስል፣ የአእምሮ ጭንቀት ቢደርስብኝ፣ ብገረፍ፣ ባል ባገባ ምኑ አዲስ ነገር ነው። ከዚህስ የቀለለ የዓላማ መሥዋዕትነት ምን
ሊኖር ይችላል?» ካርለት መኝታዋ ላይ ተጋድማ የምታስበው ነበር
ካርለት ለአንድ ወር ያክል በከብት ዝላይ ወቅት የተገረፈችው ቁስል አሠቃያት ጫማ የለመደውን እግሯንም እንቅፋቱና እሾሁ
እየተተካካ አንሰፈሰፋት" እየቆየ ሲመጣ ግን ይህ ሁሉ ሥቃይ እየታገሠ፣ ቍስሉም እየደረቀ፣ እግሯም እየደነደነ መጣ ካርለት በቃን በማይሉት ማስታወሻዎቿ የየዕለት ገጠመኞቿን
እያሰፈረች፣ በካሜራዋ እይታዋን እያጠናከረች፣ በድንኳኗ አካባቢ
አገገመች ካርለት አልፈርድ ልብሶቿን በሻንጣዋ ቆልፋ፣ ቆዳዋን በመልበስ፣ በባዶ እግሯ በጨሌና አንባር አጊጣ ስትወጣ ብዙ አዲስ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ሆራ ጨርቆሉ ማዝ ሆኖ ደም፣ ወተት፣ ሥጋና ማር እየተቀለበ፣ ከሰልና ቅቤ ተቀላቅሎ ፊቱንና የተላጨውን ራሱን
ተቀብቶ፣ ከሚዜው ጋር ውሎው ጫካ ነው። ከሎ የወገኖቹን ባህላዊ
የጋብቻ ሥነ ሥርዓት ለመጀመር ምክንያቱ አንድ ነበር ፍቅር። ሥነ ሥርዓቱን እያሟላ ሲመጣ ግን፣ አዲስ ስሜት አእምሮው ማፍለቅ ጀመረ።
ወገኖቹ የሆኑት ሐመሮች በአንድ ወቅት ከማኅበረሰባቸው
አግልለውት ነበር" ያውም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ፣ እንዲሞት ተደርጎ ተጥሏል። ከሚወዳቸው ወላጆቹና እኅት ወንድሞቹ፣ ከሚያፈቅረው የፍየልና ጥጃ ጥበቃው፣ ከቦረቀበትና ከተጫወተበት ማራኪ
የሐመር ምድር ተጎትቶ ተወስዶ፣ በጦር ተወግቶ፣ ወደ ገደልም ተገፍቶ፣ የሞትን ጽዋ ጕድጓድ ውስጥ እንዲቀምስ ተደርጎ ነበር።
የሕፃንና የወጣትነት አእምሮው ይህን የደረሰበትን መራራ ጽዋ
ጠንጥኖ በገዛ አእምሮው የዛን ጊዜውን መሪ ተዋናይ ሲያስታውሰው አፉን ደም ደም ይለዋልI ልሳኑ ይዘጋበታል ሕይወቱ የላሸቀ፣ የተበላሸ እንቍላል ሆኖ ባለመጥቀሙ ተሽቀንጥሮ የተወረወረ
ይመስለዋል።
የዛኔው የቍስል ስሜት ምልክት ጥሎ ካለፈ ዓመታት ቢቈጠሩም
ሁሌም አጋጣሚውን ባስታወሰ ቍጥር ሥቃዩ ይጀምረዋል" ሞት
ጒሮሮው ላይ ቆሞ ስለታም ሰይፉን ጕሮሮው ውስጥ ሊቀረቅርበት ሲመጣ ይታየውና ይባባል፤ መሸሻ፣ መደበቂያ፣ ማምለጫ መንገድ ያጣል። ከራስ ሕሊና የሚፈጠር አስፈሪ ነገር በምን አንቀጽ
ይከሰሳል! ምን ዓይነት ጠንካራ በር ያግደዋል?
«እኮ ለምን? ምን ባደረኳቸው በእንቦቀቅላነቴ ወቅት ልሸከመው
የማልችለውን ሞትና ፍርሃት አሸከሙኝ ምን ባደረኳቸው ከእናት ጉያ ነጥለው፣ አብሬአቸው ከምዘላቸው ጓደኞቼ ለይተው ለመከራ
ዳረጉኝ?» ባለፈው ሕይወቱ ከሎ ሆራ ራሱን በራሱ እየጠየቀ መልስ ያጣበት ጉዳይ ነው" ለብዙ ዓመታት የዕለት ተዕለት ትዕይንት ሆኖ የሚቀርበውን የቆየ ትዝታ ባስታወሰ ቍጥር የመጨረሻውን ረድፍ
ይዘው የሚደረደሩት ጥያቄዎች ከላይ የተዘረዘሩት ሲሆኑ መልሳቸው ግን ሰው ወይንም መዝገበ ቃላት ሳይመልሰው እስከ ዛሬ አብረውት ዘልቀዋል"
ከሎ ሆራ በሕይወቱ ሙሉ ያምንበት የነበረው አሁን ግን እንደ አጉም እየበነነ አልጨበጥልህ ይለው ጀምሯል" ወደ ወገኖቹ ብቻ
ሳይሆን ወደ ሐመር ምድር ለመመለስ አልሞም አያውቅም። የኖረው
እነሱን ሲረግምና ሲሸሽ ነው። አሥራ ሁለተኛ ክፍል እንደ ጨረሰ በአገር አቀፍ የመሠረተ ትምህርት ዘመቻውም ወቅት፣ ከዘመቻው መቅረት ወይንም መለወጥ አልቻልህ ብሎት እንጂ እግሩንም
ለማንሣት አያስብም ነበር" የዛኔም ቢሆን ደግሞ፣ «ጌታዋን የተማመነች በግ...» እንዲሉ፣ መንግሥትን ተማምኖ እንጂ እንኳን የከፍተኛ ትምህርት ዕድሉ ሌላው ሁሉ ነገር ቢቀር ወደ ሐመር
ተመልሶ ለመምጣት አያስብም። በቆይታውም አይጥና ድመት ሆነው
ቆዩ እንጂ አልተቀራረቡም።
አሁን ግን ከሎ ሆራ አይጡም ድመቱም እሱ እንደሆነ በመቁጠር ወደ ቤቱና ወደ ባለቤቶቹ መመለስ ይከጃጅለዋል"
ከሎ ሆራ በእርግጥ አሁን ያለው ሐመር ነው" ሐመሮች በተለይም ዘመዶቹ ባዩት ቍጥር ይሳሱለታል" ወላጅ እናቱ ልክ እንደ ልጅነቱ እጆቹን እያፍተለተሉ እንባቸውን ያፈሱለታል ያላቸውንና
ቤት ያፈራውን ጎጆው ድረስ ተሸከመው ያመጡለታል፤ ከብት ለመዝለል በየዘመዶቹ ቤት ሲዞር እንደ ብርቅ ስመው አስተናግደውታል ከብት በሚዘለልበትም ወቅት ዘመዶቹ ዝግጅቱን በማሟላትና በለምለም ቅጠል መልካም ዕድልን በመመኘት አብረውት
ተጨንቀዋል ልጃገረድ ዘመዶቹም የዝምናድ ምልክት የሆነውን
ግርፋት በወኔና በፍላጎት ተገርፈውለታል።
ከሎ ሆራ ይህን ሁሉ ካመዛዘነ በኋላ ለዘመናት በአእምሮው ተቀብረው
የኖሩትን ጥያቄዎች ከመቃብራቸው እያወጣ መጣል ጀምሯል እናቱ እንደ ብርቅዬ ልጃቸው፣ ወንድምና እኅቶቹ እንደ
ተወዳጅ ወንድማቸው አድርገው ይቈጥሩታል“ ታዲያ ማንን ይጥላ?
ለሥቃዩ ሁሉ ተጠያቂው ማን ሊሆን? ለምንስ እንዲሞት አድርገው
ጣሉት?
ከሎ ሆራ አእምሮው ለጥያቄዎቹ መልስ አገኘ" ለመጣል ያበቃው ባህል ነው። እሱን ለመጉዳት፣ ከእናቱ ጉያ ለመነጠል የደፈሩት የአገር ሽማግሎች አንኳን ለሱ ከሜዳ ተነሥተው hፉ አላሰቡም”
የሐመር ሕዝብ ባህሉን አክባሪ፣ ካለ ዘመናዊ ሕግና ደምብ በባህላዊ ደምቦችና ሥርዓቶች የሚመራ፣ ተፋቅሮና ተዛዝኖ የሚኖር
ማኅበረሰብ ነው። ማንንም የማያገል፣ ባህሉን ከመከተል ዝንፍ
የማይል ሕዝብ መሆኑን አረጋግጧል። «ታዲያ ወገኖቼ በእኔ ላይ
ብቻ ልዩ ቅጣት አልፈጸሙብኝማ። ባህላዊው ደንብ መሟላት
ነበረበትና ተገደልኩ፤ ከሙትነት ተነሥቼ ስመጣ ግን ተቀበሉኝ" አሁን የተቀበሉኝ ስለ ተማርሁ፣ ከእነሱ የተለየ ሕይወት ስላየሁ አይደለም ባህሉ ስለሚፈቅድ ብቻ ነው ታዲያ ባህል ባመጣው ጦስ ወገኖቼን መጥላት አለብኝ?» ጨርቆሌ ማዝ ተብሎ ጫካ ለጫካ
የሚዞረው ከሎ ሆራ ዕድሜ ልኩን አእምሮውን ሰንገው ይዘው ያስጨንቁት የነበሩትን ጥያቄዎች መመለስ ጀመረ።
።።።።።።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣
ሰው ራሱን ማስተማር የሚችል ታላቅ ፍጡር ነው" በተለይም ታታሪ ሰዎች ከአምላክ የተሰጠውን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ
እየተጣጣሩ ናቸው። እየተሳካላቸውም ነው
በምርምር እንደ እብድ ያልለፈለፈ ፈላስፋ፣ ቀንና ሌሊት በምርምርና በሙከራ እልሁን ያልጨረሰ ሳይንቲስት፣ እንደ
ሚፈጥራቸው ገጸባሕርያት ስቅስቅ ብሎ ያላዘነ አሊያም በደስታ ያልተፍነከነከ ደራሲ፣ የሚሥለውን ሥዕል የተዋጣ ለማድረግ
ረቂቁን የተፈጥሮ ምሥጢር ለማወቅ በመጣጣር ያልዳከረ ሠዓሊ
l ሊኖር አይችልም" ካለም ከነሆድ አምላኩ ወገን የሆነ አስመሳይ መሆኑ ነው"
ካርለት የሐመር ሴቶችን ሕይወትና ማኅበራዊ ተሳትፎ የምታጠና
ወጣት አንትሮፖሎጂስት ናት ያለችበት ዘመን ሳይንስና ተክኖሎጂ የመጠቀበት፣ የሰው ልጆች በአዲስ ግኝቶች የሚንበሸበሹበት ወቅት ነው„
«እንደ ዱሮው ዘመን ይህን ይህን ማድረግ ያስቸግራል የሚል አዳማጭም ሆነ ተመልካች አያገኝም" መሆን አለበት ብዬ ብዙ
ሞከርኩኝ ፈተናና ሥቃይም ገጠመኝ፤ በመጨረሻ ግን ተሳካልኝ ሲባል አድናቆታዊው ጭብጨባ መቅለጡን አውቃለሁ። የሰው ልጅ በውኃ ውስጥ በባቡር መጓዝ በቻለበት፣ ሕዋ ላይ ከተማ በከተመበት፣አይጥና ድመት አብረው እንዲጫወቱ በተደረገበት ወቅት እኔስ
ሰውነቴ ቢቈስል፣ የአእምሮ ጭንቀት ቢደርስብኝ፣ ብገረፍ፣ ባል ባገባ ምኑ አዲስ ነገር ነው። ከዚህስ የቀለለ የዓላማ መሥዋዕትነት ምን
ሊኖር ይችላል?» ካርለት መኝታዋ ላይ ተጋድማ የምታስበው ነበር
ካርለት ለአንድ ወር ያክል በከብት ዝላይ ወቅት የተገረፈችው ቁስል አሠቃያት ጫማ የለመደውን እግሯንም እንቅፋቱና እሾሁ
እየተተካካ አንሰፈሰፋት" እየቆየ ሲመጣ ግን ይህ ሁሉ ሥቃይ እየታገሠ፣ ቍስሉም እየደረቀ፣ እግሯም እየደነደነ መጣ ካርለት በቃን በማይሉት ማስታወሻዎቿ የየዕለት ገጠመኞቿን
እያሰፈረች፣ በካሜራዋ እይታዋን እያጠናከረች፣ በድንኳኗ አካባቢ
አገገመች ካርለት አልፈርድ ልብሶቿን በሻንጣዋ ቆልፋ፣ ቆዳዋን በመልበስ፣ በባዶ እግሯ በጨሌና አንባር አጊጣ ስትወጣ ብዙ አዲስ
👍22
ሁኔታ አጋጠማት። የሐመር ልጃገረዶችና ሴቶች ከልብ ቀረቧት ጐረምሶች ያሽኰረምሟት ጀመር። እነሱ የእኛ ናት፣ እሷ ደግሞ
የእነሱ ነኝ የሚል ስሜት ፈጠሩና ከልብ መቀራረብ ጀማመሩ"ለካርለት አዲሱ ቍልፍ በሩን ከፈተላት።
በተለይም ካርለት እንጨት ለመልቀም ወደ ጫካ ስትሄድ እንቅፋቱም፣ እሾሁም የለቀመችው እንጨት ክብደትም፣ ስቅስቅ
ብላ እስከማልቀስ ቢያደርሳትም ከልጃገረዶችና ካገቡ ሴቶች ጋር በኩንኩሮ፣ አጋም፣ ጨውሊንባ፣ እንኮይ፣ ሾላ፣ ዋንዛ ተሞላው ጬካ በሄደች ቍጥር የሚያወሩት፣ የሚዘፍኑት፣ ምሥጢራቸውን የሚያካፍሏት ሁሉ ማር ሆኖላታል ጣፋጭ!
«ባልሽን ትወጅዋለሽ?» ካርለት አንድ ጊዜ አንዷን ባለትዳር ነጠል ብለው እንጨት ሲለቅሙ ጠጋ ብላ ጠየቀቻት"
«ይእ!» በሣቅ እየተፍለቀለቀች ራሷን በአወንታ አወዛወዘች"
«...ይገርፍሻል?»
«ይእ!ባል ሆኖ እህ ላይገርፈኝ ነው!» በካርለት ጥያቄ እየተገረመች መለሰችላት"
«ለምንድነው የሚገርፍሽ?» ሌላው የካርለት ጥያቄ ነበር።
«ሳጠፋl በትክክል እንድሠራ፤ እሱ ካልመታኝማ አጠፋለሁu»
የታፈነ ሣቋን ለቀቀችው።
«ሲመታሽ አትጠይውም?»
«ይእ! ለምን? ወንድ ሆኖ ሴትን ካልምታት ታዲያ ስታጠፋ እያየ ዝም ሊል ነው?»
«ከባልሽ ወንድም ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ትፈጽሚያለሽ? »
«ይእ! ታዲያ ሊቀር ነው! ከባለቤቴ ታናሽ ወንድም ጋር።» ሣቋ ቀደማት።
ይህንና ይህን መሰሉን ውይይት ካርለት ከባለትዳር ሴቶች ጋር ባደረገች ቍጥር መልሳቸው ተመሳሳይ ይሆንባታል" ካርለት ከልጃገረዶች ጋር ስትጨዋወት ደግሞ ለየት ያሉ ነገሮችን ትሰማለች።
«ዕድሜሽ ስንት ነው?» ካርለት ልጃገረዷን ጠየቀቻት
«ይእ!» በአሉታ አንገቷን ግራና ቀኝ አወዛወዘችላት።
«እጮኛ አለሽ?»
«እ!» በአወንታ አንገቷን ላይና ታች አወዛወዘች
«እጮኛሽን ታውቂዋለሽ?» ካርለት ጠየቀቻት።
«እ!» ልጃገረዷ የካርለት ጥያቄ ግር አላት።
«ከእጮኛሽ ጋር ተገናኝታችሁ ታውቃላችሁ?» ልጃገረዷ በአሉታ አንገቷን ወዘወዘች።
«ከወንድ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ጀምረሻል?»
«ይእ! ያማ ይጠየቃል፤ በደንብ ነዋ» በሣቅ ፍርስ አለች።ተጠያቂዋ ልጃገረድ" ልጃገረዷ በካርለት የሞኛሞኝ ጥያቄ ስትሥቅ
ውላ ብታድርም አይወጣላትም። ሆኖም ካርለትን ባለማወቋ ብቻ
ስሜቷን ካለገደብ ለቃ ልታሳቅቃት አልፈለገችም።
«ግንኙነት ስታደርጊ እንዴት ነው?» ካርለት ጥያቄዋን
ቀጠለች" ልጅቷ ያን ግዜስ ሣቋን ልትቈጣጠር ተስኗት ከርቀት ያሉ ጓደኞቿ እስኪደነግጡ ድረስ በሣቅ ተፍለቀለቀችና የፍየል ቆዳዋን ከኋላ በኩል ለዐመል ያህል ከፍ አድርጋ፣ ጎንበስ በማለት ያደራረግ
ስልቷን አሳየቻት።
«እስh አሁን ከስንት ወንድ ጋር ቀበጥሽ?» ቍጥር አለማወቋን ካርለት ዘነጋች።
«ይእብዙ ነዋ!» መለሰች ልጃገረዷ።
«ካገባችና ካላገባች ልጃገረድ የየትኛውን ኑሮ ትወጃለሽ?»
«ሁለቱም ጥሩ ነው" ልጃገረድነት እንደ ልብ ለመጫወትና ከጐረምሳ ጋር ለመዳራት፤ ባል ማግባትም ልጅ ስለሚወለድ ደስ
ይላል» ብላ መለሰች ልጃገረዷ።
ካርለት፣ ልጃገረዶች ሆኑ ያገቡ ሴቶች በባህላቸው የሚረኩI ባህላቸውን የሚያከብሩና የሚወዱ ሆነው አገኘቻቸው። ካለሐፍረትና መሳቀቅ ከልባቸው የቀረቧት ሴቶች ከጓደኛ የሚደብቁት ምሥጢር የሚባል ነገር እንደሌላቸውም በተግባር አረጋገጡላት።
ካርለት እንደ ክልሉ ኗሪ ሕዝብ ባህል ራሷን ለማኖር በገባችው የራስ በራስ እምነት መሠረት ቆዳ እንደ መልበሱ፣ በባዶ እግር እንደ
መሄዱ፣ እንጨት እንደ መልቀሙ ሁሉ ለማረስም ሞካከረች"ስለዚህ እርፍን የሚጨብጡ የእጇ ጣቶችና መዳፏ ለስላሳና ገና
ያልገበረ በመሆኑ፣ መላጡ ወደ እጇ ተሸጋገረ" በዚያ ላይ ከብቶች ወዲያና ወዲህ ሲያላጓት አቅመ ቢስ በመሆኗ መውደቅ፣ መነሣት
ቀጠለች።
ያም ሆኖ ግን፣ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እጆቿ ጠነከሩl የአካል ጥንካሬዋም ዳበረ። ሌላው ያስቸገራት ልምድ ደግሞ ላሞችን ማለቡ ነበር" በሐመር ባህል የምታርስ፣ ከብት የምታልብ ልጃገረዷ ናት"ካርለትም መጀመሪያ ማለብ ስትሞክር መልኳና ወዟ አዲስ የሆነባቸው ከብቶች አላስጠጋሽ አሏት" ይባስ ብለውም በቀንዳቸው
ይደስቋት ጀመር።
አንድ ጊዜ እንዲያውም የጎን አጥንቷን አንዷ ላም ወግታት ለሁለት ሳምንት ያህል ውጋት እያጣደፋት ታማ ቆየች" ሲሻላት
ደግሞ ሙከራዋን እንደ ምንም ቀጥላ ከብቶችን በመላመድ ላሞችን
ማለብ ጀመረች።
💫ይቀጥላል💫
የእነሱ ነኝ የሚል ስሜት ፈጠሩና ከልብ መቀራረብ ጀማመሩ"ለካርለት አዲሱ ቍልፍ በሩን ከፈተላት።
በተለይም ካርለት እንጨት ለመልቀም ወደ ጫካ ስትሄድ እንቅፋቱም፣ እሾሁም የለቀመችው እንጨት ክብደትም፣ ስቅስቅ
ብላ እስከማልቀስ ቢያደርሳትም ከልጃገረዶችና ካገቡ ሴቶች ጋር በኩንኩሮ፣ አጋም፣ ጨውሊንባ፣ እንኮይ፣ ሾላ፣ ዋንዛ ተሞላው ጬካ በሄደች ቍጥር የሚያወሩት፣ የሚዘፍኑት፣ ምሥጢራቸውን የሚያካፍሏት ሁሉ ማር ሆኖላታል ጣፋጭ!
«ባልሽን ትወጅዋለሽ?» ካርለት አንድ ጊዜ አንዷን ባለትዳር ነጠል ብለው እንጨት ሲለቅሙ ጠጋ ብላ ጠየቀቻት"
«ይእ!» በሣቅ እየተፍለቀለቀች ራሷን በአወንታ አወዛወዘች"
«...ይገርፍሻል?»
«ይእ!ባል ሆኖ እህ ላይገርፈኝ ነው!» በካርለት ጥያቄ እየተገረመች መለሰችላት"
«ለምንድነው የሚገርፍሽ?» ሌላው የካርለት ጥያቄ ነበር።
«ሳጠፋl በትክክል እንድሠራ፤ እሱ ካልመታኝማ አጠፋለሁu»
የታፈነ ሣቋን ለቀቀችው።
«ሲመታሽ አትጠይውም?»
«ይእ! ለምን? ወንድ ሆኖ ሴትን ካልምታት ታዲያ ስታጠፋ እያየ ዝም ሊል ነው?»
«ከባልሽ ወንድም ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ትፈጽሚያለሽ? »
«ይእ! ታዲያ ሊቀር ነው! ከባለቤቴ ታናሽ ወንድም ጋር።» ሣቋ ቀደማት።
ይህንና ይህን መሰሉን ውይይት ካርለት ከባለትዳር ሴቶች ጋር ባደረገች ቍጥር መልሳቸው ተመሳሳይ ይሆንባታል" ካርለት ከልጃገረዶች ጋር ስትጨዋወት ደግሞ ለየት ያሉ ነገሮችን ትሰማለች።
«ዕድሜሽ ስንት ነው?» ካርለት ልጃገረዷን ጠየቀቻት
«ይእ!» በአሉታ አንገቷን ግራና ቀኝ አወዛወዘችላት።
«እጮኛ አለሽ?»
«እ!» በአወንታ አንገቷን ላይና ታች አወዛወዘች
«እጮኛሽን ታውቂዋለሽ?» ካርለት ጠየቀቻት።
«እ!» ልጃገረዷ የካርለት ጥያቄ ግር አላት።
«ከእጮኛሽ ጋር ተገናኝታችሁ ታውቃላችሁ?» ልጃገረዷ በአሉታ አንገቷን ወዘወዘች።
«ከወንድ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ጀምረሻል?»
«ይእ! ያማ ይጠየቃል፤ በደንብ ነዋ» በሣቅ ፍርስ አለች።ተጠያቂዋ ልጃገረድ" ልጃገረዷ በካርለት የሞኛሞኝ ጥያቄ ስትሥቅ
ውላ ብታድርም አይወጣላትም። ሆኖም ካርለትን ባለማወቋ ብቻ
ስሜቷን ካለገደብ ለቃ ልታሳቅቃት አልፈለገችም።
«ግንኙነት ስታደርጊ እንዴት ነው?» ካርለት ጥያቄዋን
ቀጠለች" ልጅቷ ያን ግዜስ ሣቋን ልትቈጣጠር ተስኗት ከርቀት ያሉ ጓደኞቿ እስኪደነግጡ ድረስ በሣቅ ተፍለቀለቀችና የፍየል ቆዳዋን ከኋላ በኩል ለዐመል ያህል ከፍ አድርጋ፣ ጎንበስ በማለት ያደራረግ
ስልቷን አሳየቻት።
«እስh አሁን ከስንት ወንድ ጋር ቀበጥሽ?» ቍጥር አለማወቋን ካርለት ዘነጋች።
«ይእብዙ ነዋ!» መለሰች ልጃገረዷ።
«ካገባችና ካላገባች ልጃገረድ የየትኛውን ኑሮ ትወጃለሽ?»
«ሁለቱም ጥሩ ነው" ልጃገረድነት እንደ ልብ ለመጫወትና ከጐረምሳ ጋር ለመዳራት፤ ባል ማግባትም ልጅ ስለሚወለድ ደስ
ይላል» ብላ መለሰች ልጃገረዷ።
ካርለት፣ ልጃገረዶች ሆኑ ያገቡ ሴቶች በባህላቸው የሚረኩI ባህላቸውን የሚያከብሩና የሚወዱ ሆነው አገኘቻቸው። ካለሐፍረትና መሳቀቅ ከልባቸው የቀረቧት ሴቶች ከጓደኛ የሚደብቁት ምሥጢር የሚባል ነገር እንደሌላቸውም በተግባር አረጋገጡላት።
ካርለት እንደ ክልሉ ኗሪ ሕዝብ ባህል ራሷን ለማኖር በገባችው የራስ በራስ እምነት መሠረት ቆዳ እንደ መልበሱ፣ በባዶ እግር እንደ
መሄዱ፣ እንጨት እንደ መልቀሙ ሁሉ ለማረስም ሞካከረች"ስለዚህ እርፍን የሚጨብጡ የእጇ ጣቶችና መዳፏ ለስላሳና ገና
ያልገበረ በመሆኑ፣ መላጡ ወደ እጇ ተሸጋገረ" በዚያ ላይ ከብቶች ወዲያና ወዲህ ሲያላጓት አቅመ ቢስ በመሆኗ መውደቅ፣ መነሣት
ቀጠለች።
ያም ሆኖ ግን፣ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እጆቿ ጠነከሩl የአካል ጥንካሬዋም ዳበረ። ሌላው ያስቸገራት ልምድ ደግሞ ላሞችን ማለቡ ነበር" በሐመር ባህል የምታርስ፣ ከብት የምታልብ ልጃገረዷ ናት"ካርለትም መጀመሪያ ማለብ ስትሞክር መልኳና ወዟ አዲስ የሆነባቸው ከብቶች አላስጠጋሽ አሏት" ይባስ ብለውም በቀንዳቸው
ይደስቋት ጀመር።
አንድ ጊዜ እንዲያውም የጎን አጥንቷን አንዷ ላም ወግታት ለሁለት ሳምንት ያህል ውጋት እያጣደፋት ታማ ቆየች" ሲሻላት
ደግሞ ሙከራዋን እንደ ምንም ቀጥላ ከብቶችን በመላመድ ላሞችን
ማለብ ጀመረች።
💫ይቀጥላል💫
👍19❤3
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ዳያና ላቭሴይ እውነተኛ ፍቅር በአጭር ጊዜ እንደማይለቅ በሃዘን
አስታወሰች፡፡ መርቪን በፍቅሯ የተነደፈ ጊዜ የጠየቀችውን ነገር ሁሉ
በፍጥነት ለማድረግ ደስተኛ ነበር፡፡ አንድ ነገር ከፈለገች በመኪና በመሄድ ያመጣላት ነበር፡፡ ሲኒማ አምሮኛል ካለች ከስራውም ቀርቶም ቢሆን ይዟት ይገባ ነበር፡፡ ከባሰም ለጉብኝት ፓሪስ ይወስዳት ነበር፡ የፈለገችው ሻርፕ እስኪገኝ ድረስ በማንቼስተር ሱቆች እግሩ እስኪቀጥን እየዞረ ሲያስስ ቢውል አይደክመውም፡፡ ቴአትር ቤት ገብተው በመሃል ደበረኝ ካለችው ሳይጨርሱ ቢወጡ ቅር አይለውም፡፡ ታዲያ ይሄ ታዛዥነት ከተጋቡ በኋላ ቀስ በቀስእንደ ጉም በኖ ጠፋ፡፡ ከዚያ በኋላ የጠየቀችውን ባይነሳትም ያደርግ የነበረው
ግን በዳተኝነት ነበር፡፡ ግድ የለም ልታገስ ብሎ እንጂ እንደ በፊቱ በፍቅር
ማድረጉን እየተወ መጣ፡፡ በመጨረሻ እንደውም ትዕግስት እያጣ ሲመጣ
ሚስቱን ጭራሹን ‹‹ዞር በይ›› ማለት አመጣ፡፡
ታዲያ ማርክም እንዲህ ሊያደርገኝ ይችላል የሚል ፍርሃት አጫረባት፡
ማርክ እንግሊዝ አገር በቆየበት ጊዜ ባሪያዋ ሆኖ ነው የስነበተው
በጠፉ በሁለተኛው ቀን ተጣልተው መኝታ ለይተውነበር፡ ሆኖም እኩለ
ሌሊት ላይ እውጭ ያለው ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ አይሮፕላኑን እንዳልተገራ
ፈረስ ሲያሰግረው ዳያና በጣም ፈራችና ዓይኗን በጨው አጥባና ክብሯን ሽጣ ወደ ማርክ መኝታ ሄደች፡፡ እንደዚያም ሆኖ ውጤቱ አላማረም፡፡ በኋላ ወደ እኔ ይመጣል ብላ ብትጠብቅም እሱም ኩራት ልቡን ነፍቶት ሳይመጣ
በመቅረቱ በንዴት ኤሌክትሪክ ልትጨብጥ ምንም አልቀራትም:
ዛሬ ጧት ምንም አልተነጋገሩም ማለት ይቻላል፡፡ ጧት ከእንቅልፏ
የነቃችው አይሮፕላኑ ቦትውድ ሲያርፍ ሲሆን ከአልጋዋ ስትነሳ ማርክ
ወጥቶ መሄዱን አወቀች፡፡ ጧት ቁርስ ላይ መሳ ለመሳ ተቀምጠው በሃሳብ
ተውጠው ምግባቸውን ሲቆነጣጥሩ ነበር፡፡
ዳያናን መርቪን ከናንሲ ጋር የሙሽሮች ክፍልን ተጋርተው ማደራቸው
ለምን እንደዚህ እንዳናደዳት አልገባትም፡ ማርክ በዚህ ረገድ ቢያግዛት
በወደደች። በተቃራኒ አሁንም መርቪንን ትወጂዋለሽ እንዴ?ሲል
ጠይቋታል፡፡ ትዳሯንና ቤት ንብረቷን ትታ ከእሱ ጋር መኮብለሏን እያወቀ
ማርክ እንዲህ ማለቱ አናዷታል፡፡
ዙሪያዋን ስትመለከት በቀኝዋ የተቀመጡት ልዕልት ላቪኒያና ሉሉ ቤል
የቆጡን የባጡን ያወራሉ፡፡ ሁለቱም አይሮፕላኑ ሲወዛወዝ ስላደረ እንቅልፍ
ባይናቸው ሳይዞር ስለነጋባቸው ተዳክመዋል፡፡ በግራ በኩል የኤፍ.ቢ.አዩ ሰው ኦሊስ ፊልድና እስረኛው ፍራንኪ ጎርዲኖ በጸጥታ ምግባቸውን ይበላሉ።
የጎርዲኖ እግር በእግረ ሙቅ ከመቀመጫው ጋር ተጠፍሯል፡ሁሉም
በድካም የዛሉና ነጭናጫ ሆነዋል፡፡ እንዲህ ያለ አለቅጥ የረዘመ ሌሊት
ገጥሟቸው አያውቅም፡፡
አስተናጋጁ ዴቪ ቁርስ የተበላባቸውን ሰሃኖችና ቁሳቁሶች እየሰበሰበ
ነው፡፡ ልዕልት ላቪኒያ ‹‹እንቁላሉ አልበሰለም ሞርቶዴላው ደግሞ በጣም
ሙክክ ብሏል›› በማለት ስሞታ ያሰማሉ፡ ዴቪ ቡና ቢያመጣም ዳያና
አልጠጣችም::
ማርክን ሰረቅ አድርጋ አይታ ፈገግ ስትል እሱም በፈገግታ ተቀበላት
‹‹ከነጋ አንዴ እንኳን አላናገርከኝም›› አለችው፡፡
‹‹ምክንያቱም ከኔ ይልቅ ለመርቪን ልብሽ መጥፋቱን ስላወቅሁ ነው›
ወዲያው ጸጸት ገባት፡፡ መቅናቱ ትክክል ነው፡ ‹‹ይቅር በለኝ ማርክዬ›
አለች ‹‹ልቤ ያለው ካንተጋ ብቻ ነው እውነቴን ነው››
እጁን ሰዶ እጇን ያዝ አደረገና ‹‹እውነትሽን ነው?››
‹‹እውነቴን ነው፡፡ ትናንት ምን እንደነካኝ አላውቅም››
‹‹እሺ›› አለ ማርክ፡፡
ሁለቱም አፍቃሪዎቿ አፍጥጠውባታል፡፡ አንድ ውሳኔ ላይ መድረስ
እንዳለባት አውቃለች፡ ከመርቪን ጋር ብቻዋን ብትነጋገር ማርክን
አስከፋዋለሁ ብላ ገምታለች፡፡ አሁን መርቪንን ትቼ ከማርክ ጋር ነው
ያለሁት ስለዚህ ማርክን ነው መደገፍ ያለብኝ ስትል አሰበች፡፡
ልቧ ከበሮ እየደለቀ ‹‹ማርክ ፊት የማታናግረኝ ከሆነ ልሰማው አልፈልግም›› አለችው፡:
መርቪን ደንገጥ አለና ‹‹እሺ›› አለ በብስጭት፡፡ ወዲያው ራሱን አረጋጋና ‹‹ከዚህ በፊት ያልሺኝን ተገንዝቤያለሁ፤ምን ያህል ቀዝቃዛ እንደነበርኩ አንቺም ምን ያህል ብቸኝነት ይሰማሽ እንደነበር…›› ንግግሩንቆም አደረገ፤ ዳያና ምንም መልስ አልሰጠችም፡፡ ይቅርታ ማለት ወይም መጸጸትን መግለጽ የመርቪን ባህሪ አይደለም፡፡ ምን ሊል ነው?› አለች ዳያና በሆዷ።
‹‹እስካሁን ላደረግሁት ሁሉ ይቅር በይኝ›› አለ መርቪን፡ ዳያና የመርቪን አባባል ቢገርማትም እውነቱን መናገሩን አውቃለች፡ ‹ይህ ሁሉ ለውጥ ከየት መጣ?›
መርቪን ቀጠለና ‹‹የተዋወቅን ሰሞን አንቺን ለማስደሰት ጥረት አደርግ
ነበር፡፡ እንዲከፋሽ አልፈልግም ነበር፡፡ አሁን ኑሮሽን ጨለማ ማድረጌ
ተሰምቶኛል፡ ደስታ ማግኘት መብትሽ ነው፡፡ የሰው ሁሉ ዓይን ማረፊያ እንደሆንሽ አውቃለሁ፡››
ዳያና ይህን ስትሰማ እምባዋ በዓይኗ ሞላ፡፡ የወንዶችን ዓይን መሳቧ
እውነት ነው፡፡
‹‹አንቺን ማሳዘኔ ሀጢያት ነው›› አለ መርቪን፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ አንቺን ለማስደሰት እጥራለሁ፡››
ከዚህ በኋላ ጥሩ እሆናለሁ› ማለቱ ፍርሃት ለቀቀባት፡ ወደ ቤቷ እንድትመለስ ይፈልጋል ማለት ነው፡፡ እሷ ግን እንዲጠይቃት እንኳን
አትፈልግም፡፡ ‹‹ወደ አንተ ተመልሼ አልመጣም›› አለች ዳያና፡
‹‹ከማርክ ጋር ደስተኛ ህይወት የምትኖሪ ይመስልሻል?››
ዳያና ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች፡፡
‹‹ያስብልኛል ብለሽ ታምኛለሽ?››
‹‹አዎ ያስብልኛል››
ማርክ ጣልቃ ገባና ‹‹እኔን እንደ እቃ ቆጥራችሁ ስለኔ ትናገራላችሁ? አለ፡፡
ዳያና የማርክን እጅ ለቀም አድርጋ ያዘችና ‹‹እንዋደዳለን›› አለችው:
‹‹አይ!›› አለ መርቪን፡፡ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ፊቱ ላይ የለበጣ ፈገግታ
ተነበበ ‹‹ትዋደዳላችሁ›› አለ፡፡
መርቪን የተለሳለሰ መሰለ፡፡ ይሄ የእሱ ባህሪ አይደለም፡፡
ወይዘሮ ሌኔሃን ሄደህ ከሚስትህ ጋር ተነጋገር አለችህ እንዴ?›› አለች ዳያና ተጠራጥራ።
አላለችም፡፡ ሆኖም ልናገር እንደምችል ታውቃለች››
‹‹ታዲያ ፈጠን ብለህ ተናገረውና ይውጣልህ›› አለ ማርክ፡፡
መርቪን ማርክን ገላመጠውና ‹ጎረምሳው አንተን እዚህ ነገር ውስጥ
የሚያገባህ ነገር የለም፤ ዳያና እኮ አሁንም ባለቤቴ ናት›› አለ፡፡
ማርክ ፍቅረኛውን ለማገዝ ‹‹ተው እባክህ! ከዚህ በኋላ ከእጅህ ወጥታለች፤ ደግሞ ጎረምሳው አትበለኝ ሽ
ሽሜ›› አለው መርቪንን፡፡
‹‹መርቪን እዚህ አምባጓሮ ማንሳት አትችልም የምትለው ካለህ
አውጣና ተናገረው፤ አለበለዚያ አንድ ዓይነት ኃይል ያለህ አታስመስል››
አለችው ዳያና፡፡
‹‹ደህና፧ ነገሩ እንዲህ ነው›› ትንፋሹን ዋጥ አደረገና ‹‹መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ፤ ወደ ቤትሽ እንድትመለሺ ስጠይቅሽ ‹ምን ሲደረግ ብለሻል፧ ይሄ ሰው እኔ ማድረግ የማልችለውን አድርጎ ከሆነና ከእሱ ጋር
መኖር ደስታ የሚሰጥሽ ከሆነ መልካም እድል ይግጠማችሁ፡፡ መልካሙን
እመኝላችኋለሁ ይሄው ነው›› አለ፡፡ ከዚያም ጸጥታ ነገሰ፡
ማርክ ሊናገር ሲል ዳያና አቋረጠችውና ‹‹አንተ የተረገምክ እምነተ ቢስ
የሆንክ ሰው!›› አለች ‹‹እንዴት ያለኸው ደፋር ነህ!›› አለችና ምራቋን ጢቅ
አደረገች፡፡
መርቪን አባባሏ ግራ አጋባውና ‹‹ምነው?›› አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ዳያና ላቭሴይ እውነተኛ ፍቅር በአጭር ጊዜ እንደማይለቅ በሃዘን
አስታወሰች፡፡ መርቪን በፍቅሯ የተነደፈ ጊዜ የጠየቀችውን ነገር ሁሉ
በፍጥነት ለማድረግ ደስተኛ ነበር፡፡ አንድ ነገር ከፈለገች በመኪና በመሄድ ያመጣላት ነበር፡፡ ሲኒማ አምሮኛል ካለች ከስራውም ቀርቶም ቢሆን ይዟት ይገባ ነበር፡፡ ከባሰም ለጉብኝት ፓሪስ ይወስዳት ነበር፡ የፈለገችው ሻርፕ እስኪገኝ ድረስ በማንቼስተር ሱቆች እግሩ እስኪቀጥን እየዞረ ሲያስስ ቢውል አይደክመውም፡፡ ቴአትር ቤት ገብተው በመሃል ደበረኝ ካለችው ሳይጨርሱ ቢወጡ ቅር አይለውም፡፡ ታዲያ ይሄ ታዛዥነት ከተጋቡ በኋላ ቀስ በቀስእንደ ጉም በኖ ጠፋ፡፡ ከዚያ በኋላ የጠየቀችውን ባይነሳትም ያደርግ የነበረው
ግን በዳተኝነት ነበር፡፡ ግድ የለም ልታገስ ብሎ እንጂ እንደ በፊቱ በፍቅር
ማድረጉን እየተወ መጣ፡፡ በመጨረሻ እንደውም ትዕግስት እያጣ ሲመጣ
ሚስቱን ጭራሹን ‹‹ዞር በይ›› ማለት አመጣ፡፡
ታዲያ ማርክም እንዲህ ሊያደርገኝ ይችላል የሚል ፍርሃት አጫረባት፡
ማርክ እንግሊዝ አገር በቆየበት ጊዜ ባሪያዋ ሆኖ ነው የስነበተው
በጠፉ በሁለተኛው ቀን ተጣልተው መኝታ ለይተውነበር፡ ሆኖም እኩለ
ሌሊት ላይ እውጭ ያለው ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ አይሮፕላኑን እንዳልተገራ
ፈረስ ሲያሰግረው ዳያና በጣም ፈራችና ዓይኗን በጨው አጥባና ክብሯን ሽጣ ወደ ማርክ መኝታ ሄደች፡፡ እንደዚያም ሆኖ ውጤቱ አላማረም፡፡ በኋላ ወደ እኔ ይመጣል ብላ ብትጠብቅም እሱም ኩራት ልቡን ነፍቶት ሳይመጣ
በመቅረቱ በንዴት ኤሌክትሪክ ልትጨብጥ ምንም አልቀራትም:
ዛሬ ጧት ምንም አልተነጋገሩም ማለት ይቻላል፡፡ ጧት ከእንቅልፏ
የነቃችው አይሮፕላኑ ቦትውድ ሲያርፍ ሲሆን ከአልጋዋ ስትነሳ ማርክ
ወጥቶ መሄዱን አወቀች፡፡ ጧት ቁርስ ላይ መሳ ለመሳ ተቀምጠው በሃሳብ
ተውጠው ምግባቸውን ሲቆነጣጥሩ ነበር፡፡
ዳያናን መርቪን ከናንሲ ጋር የሙሽሮች ክፍልን ተጋርተው ማደራቸው
ለምን እንደዚህ እንዳናደዳት አልገባትም፡ ማርክ በዚህ ረገድ ቢያግዛት
በወደደች። በተቃራኒ አሁንም መርቪንን ትወጂዋለሽ እንዴ?ሲል
ጠይቋታል፡፡ ትዳሯንና ቤት ንብረቷን ትታ ከእሱ ጋር መኮብለሏን እያወቀ
ማርክ እንዲህ ማለቱ አናዷታል፡፡
ዙሪያዋን ስትመለከት በቀኝዋ የተቀመጡት ልዕልት ላቪኒያና ሉሉ ቤል
የቆጡን የባጡን ያወራሉ፡፡ ሁለቱም አይሮፕላኑ ሲወዛወዝ ስላደረ እንቅልፍ
ባይናቸው ሳይዞር ስለነጋባቸው ተዳክመዋል፡፡ በግራ በኩል የኤፍ.ቢ.አዩ ሰው ኦሊስ ፊልድና እስረኛው ፍራንኪ ጎርዲኖ በጸጥታ ምግባቸውን ይበላሉ።
የጎርዲኖ እግር በእግረ ሙቅ ከመቀመጫው ጋር ተጠፍሯል፡ሁሉም
በድካም የዛሉና ነጭናጫ ሆነዋል፡፡ እንዲህ ያለ አለቅጥ የረዘመ ሌሊት
ገጥሟቸው አያውቅም፡፡
አስተናጋጁ ዴቪ ቁርስ የተበላባቸውን ሰሃኖችና ቁሳቁሶች እየሰበሰበ
ነው፡፡ ልዕልት ላቪኒያ ‹‹እንቁላሉ አልበሰለም ሞርቶዴላው ደግሞ በጣም
ሙክክ ብሏል›› በማለት ስሞታ ያሰማሉ፡ ዴቪ ቡና ቢያመጣም ዳያና
አልጠጣችም::
ማርክን ሰረቅ አድርጋ አይታ ፈገግ ስትል እሱም በፈገግታ ተቀበላት
‹‹ከነጋ አንዴ እንኳን አላናገርከኝም›› አለችው፡፡
‹‹ምክንያቱም ከኔ ይልቅ ለመርቪን ልብሽ መጥፋቱን ስላወቅሁ ነው›
ወዲያው ጸጸት ገባት፡፡ መቅናቱ ትክክል ነው፡ ‹‹ይቅር በለኝ ማርክዬ›
አለች ‹‹ልቤ ያለው ካንተጋ ብቻ ነው እውነቴን ነው››
እጁን ሰዶ እጇን ያዝ አደረገና ‹‹እውነትሽን ነው?››
‹‹እውነቴን ነው፡፡ ትናንት ምን እንደነካኝ አላውቅም››
‹‹እሺ›› አለ ማርክ፡፡
ሁለቱም አፍቃሪዎቿ አፍጥጠውባታል፡፡ አንድ ውሳኔ ላይ መድረስ
እንዳለባት አውቃለች፡ ከመርቪን ጋር ብቻዋን ብትነጋገር ማርክን
አስከፋዋለሁ ብላ ገምታለች፡፡ አሁን መርቪንን ትቼ ከማርክ ጋር ነው
ያለሁት ስለዚህ ማርክን ነው መደገፍ ያለብኝ ስትል አሰበች፡፡
ልቧ ከበሮ እየደለቀ ‹‹ማርክ ፊት የማታናግረኝ ከሆነ ልሰማው አልፈልግም›› አለችው፡:
መርቪን ደንገጥ አለና ‹‹እሺ›› አለ በብስጭት፡፡ ወዲያው ራሱን አረጋጋና ‹‹ከዚህ በፊት ያልሺኝን ተገንዝቤያለሁ፤ምን ያህል ቀዝቃዛ እንደነበርኩ አንቺም ምን ያህል ብቸኝነት ይሰማሽ እንደነበር…›› ንግግሩንቆም አደረገ፤ ዳያና ምንም መልስ አልሰጠችም፡፡ ይቅርታ ማለት ወይም መጸጸትን መግለጽ የመርቪን ባህሪ አይደለም፡፡ ምን ሊል ነው?› አለች ዳያና በሆዷ።
‹‹እስካሁን ላደረግሁት ሁሉ ይቅር በይኝ›› አለ መርቪን፡ ዳያና የመርቪን አባባል ቢገርማትም እውነቱን መናገሩን አውቃለች፡ ‹ይህ ሁሉ ለውጥ ከየት መጣ?›
መርቪን ቀጠለና ‹‹የተዋወቅን ሰሞን አንቺን ለማስደሰት ጥረት አደርግ
ነበር፡፡ እንዲከፋሽ አልፈልግም ነበር፡፡ አሁን ኑሮሽን ጨለማ ማድረጌ
ተሰምቶኛል፡ ደስታ ማግኘት መብትሽ ነው፡፡ የሰው ሁሉ ዓይን ማረፊያ እንደሆንሽ አውቃለሁ፡››
ዳያና ይህን ስትሰማ እምባዋ በዓይኗ ሞላ፡፡ የወንዶችን ዓይን መሳቧ
እውነት ነው፡፡
‹‹አንቺን ማሳዘኔ ሀጢያት ነው›› አለ መርቪን፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ አንቺን ለማስደሰት እጥራለሁ፡››
ከዚህ በኋላ ጥሩ እሆናለሁ› ማለቱ ፍርሃት ለቀቀባት፡ ወደ ቤቷ እንድትመለስ ይፈልጋል ማለት ነው፡፡ እሷ ግን እንዲጠይቃት እንኳን
አትፈልግም፡፡ ‹‹ወደ አንተ ተመልሼ አልመጣም›› አለች ዳያና፡
‹‹ከማርክ ጋር ደስተኛ ህይወት የምትኖሪ ይመስልሻል?››
ዳያና ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች፡፡
‹‹ያስብልኛል ብለሽ ታምኛለሽ?››
‹‹አዎ ያስብልኛል››
ማርክ ጣልቃ ገባና ‹‹እኔን እንደ እቃ ቆጥራችሁ ስለኔ ትናገራላችሁ? አለ፡፡
ዳያና የማርክን እጅ ለቀም አድርጋ ያዘችና ‹‹እንዋደዳለን›› አለችው:
‹‹አይ!›› አለ መርቪን፡፡ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ፊቱ ላይ የለበጣ ፈገግታ
ተነበበ ‹‹ትዋደዳላችሁ›› አለ፡፡
መርቪን የተለሳለሰ መሰለ፡፡ ይሄ የእሱ ባህሪ አይደለም፡፡
ወይዘሮ ሌኔሃን ሄደህ ከሚስትህ ጋር ተነጋገር አለችህ እንዴ?›› አለች ዳያና ተጠራጥራ።
አላለችም፡፡ ሆኖም ልናገር እንደምችል ታውቃለች››
‹‹ታዲያ ፈጠን ብለህ ተናገረውና ይውጣልህ›› አለ ማርክ፡፡
መርቪን ማርክን ገላመጠውና ‹ጎረምሳው አንተን እዚህ ነገር ውስጥ
የሚያገባህ ነገር የለም፤ ዳያና እኮ አሁንም ባለቤቴ ናት›› አለ፡፡
ማርክ ፍቅረኛውን ለማገዝ ‹‹ተው እባክህ! ከዚህ በኋላ ከእጅህ ወጥታለች፤ ደግሞ ጎረምሳው አትበለኝ ሽ
ሽሜ›› አለው መርቪንን፡፡
‹‹መርቪን እዚህ አምባጓሮ ማንሳት አትችልም የምትለው ካለህ
አውጣና ተናገረው፤ አለበለዚያ አንድ ዓይነት ኃይል ያለህ አታስመስል››
አለችው ዳያና፡፡
‹‹ደህና፧ ነገሩ እንዲህ ነው›› ትንፋሹን ዋጥ አደረገና ‹‹መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ፤ ወደ ቤትሽ እንድትመለሺ ስጠይቅሽ ‹ምን ሲደረግ ብለሻል፧ ይሄ ሰው እኔ ማድረግ የማልችለውን አድርጎ ከሆነና ከእሱ ጋር
መኖር ደስታ የሚሰጥሽ ከሆነ መልካም እድል ይግጠማችሁ፡፡ መልካሙን
እመኝላችኋለሁ ይሄው ነው›› አለ፡፡ ከዚያም ጸጥታ ነገሰ፡
ማርክ ሊናገር ሲል ዳያና አቋረጠችውና ‹‹አንተ የተረገምክ እምነተ ቢስ
የሆንክ ሰው!›› አለች ‹‹እንዴት ያለኸው ደፋር ነህ!›› አለችና ምራቋን ጢቅ
አደረገች፡፡
መርቪን አባባሏ ግራ አጋባውና ‹‹ምነው?›› አላት፡፡
👍22❤3🥰1
‹‹መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ እያልክ የማይረባ ነገር ለምን
እንደምትናገር አልገባኝም፡፡ መርቪን ላቭሴይ አንድን ነገር የምትተወው
የማትፈልገው ሲሆን እንደሆነ አሳምሬ አውቃለሁ›› ሰው ሁሉ ጆሮውን ቀስሮ የሚያዳምጥ መሆኑ ግድም አልሰጣትም፡፡ ‹‹ምን እንደፈለክ አውቃለሁ፡፡ ትናንት ማታ ከዚያች ጋለሞታ ጋር የልብህን ስታደርስ ነው
ያደርከው አይደለም?››
‹‹አይደለም››
‹‹አይደለም?!›› አለችና አፍጣ አየችው፡፡ እውነቱን እየተናገረ መሆኑን ገምታለች አለዚያም በጣም ተቀራርባችኋል አይደለም? ልብህን ወስዳዋለች እሷም ወዳሃለች አሁን እኔን አትፈልገኝም፧ እውነት
አይደለም? እመን!››
‹‹ምንም የማምነው ነገር የለም››
‹‹እምነተ ቢስ ስለሆንክ ነዋ፡፡ እኔ አውቄብሃለሁ፤ አይሮፕላኑ ውስጥ
ያለው ሰው ሁሉ የሚጠረጥረውም ይህንኑ ነው፡፡ መርቪን በጣም
አዝኜብሃለሁ፡ ሃሞተ ኮስታራ ትመስለኝ ነበር፡፡››
ሃሞተ ኮስታራ! ይህ ቃል ጠቅ አደረገው::
‹‹እውነቴን ነው እንደፈለግሁ መሆን እንደምችል አሳዛኝ ወሬ ፈጥረህ ታወራለህ፡፡ በጣም ተለሳልሰሃል፤ እኔ ጣቱን የሚጠባ ህጻን አይደለሁም ልታታልለኝ አትችልም›› አለች፡፡
‹‹ደህና›› አለ መርቪን ‹‹ሰላማዊ ድርድር እንድናደርግ ብጠይቅሽ
አልተቀበልሽም፤ እንደፈለግሽ ሁኚ›› አለና ተነሳ ‹‹አነጋገርሽን የሰማ ሰው ከውሽማዬ ጋር አገር ጥዬ የምጠፋው እኔ እመስለዋለሁ›› ወደበሩ አመራና
ተ‹‹ስትጋቡ አሳውቂኝ›› አለና ሄደ፡፡
‹‹ደህና!›› አለች ዳያና ደሟ እየተንተከተከ፡፡ አካባቢውን ስትቃኝ ልዕልት ላቪኒያ ገልመጥ አደረጓት፤ ሉሉ ቤል ፈገግ አለች፤ ኦሊስ ፊልድ አባባሏን
ባለመውደድ ሲኮሳተር ፍራንክ ጎርዲኖ ደግሞ ወንድ ነሽ ሲል አደነቃት፡
በመጨረሻም የመርቪንን ሁኔታና በንዴት መገንፈል አይቶ ‹ማርክ ምን
ይል ይሆን› ብላ ስትመለከተው ጥርስ በጥርስ ሆኗል፡፡ እሷም የእሱ ሳቅ ተጋብቶባት ትስቃለች፡፡
‹ምንድነው የሚያስቅህ? አለችው እየሳቀች
‹‹ልክ ልኩን ነው የነገርሽው›› አለ ‹‹ኮርቼብሻለሁ፤ ደስም ብሎኛል።
‹‹ለምን ተደሰትክ?››
‹‹በህይወትሽ መርቪንን ስትጋተሪው የመጀመሪያሽ ነው?››
‹‹ሳይሆን አይቀርም››
‹‹ከዚህ በኋላ አትፈሪውም አይደል?››
‹‹አልፈራውም››
‹‹አትወጂውም ማለት እኮ ነው ይሄ››
‹‹ይሆን?›› አለች ሃሳብ ገብቷት፡፡ ለብዙ ጊዜ መርቪንን አልወደውም
ብላ ስታስብ ነበር፧ አሁን ግን ልቧ የሚነግራት ሌላ ነው ባለፉት ወራት
ከሱ እየተደበቀች ስትማግጥ እንኳን ለእሱ ያላት ፍቅር እንዳለ መሆኑን
አውቃለች፡፡ ትታው ሄዳ እንኳን ልቧ ከእሱ ጋር ነው፤ አሁን ደግሞ አይሮፕላን ውስጥ ጸጸት ጠቅ እያደረገ ሲያስቸግራት እግሩ ላይ ውደቂ ውደቂ ይላታል፡ ይህም ሆኖ ወደ እሱ መመለስ የማይታሰብ ነው፡፡
ማርክም ‹‹ከዚያች ጋለሞታ ሴትዮ ጋር ቢሄድ ምንድነው የሚሰማሽ?»ሲል ጠየቃት
«ግድ የለኝም» አለች ወዲያውኑ ‹‹አንተ ልክ ብለሃል፡ ከዚህ በኋላ
ወደ ኋላ መመለስ የለም፡፡››
✨ይቀጥላል✨
እንደምትናገር አልገባኝም፡፡ መርቪን ላቭሴይ አንድን ነገር የምትተወው
የማትፈልገው ሲሆን እንደሆነ አሳምሬ አውቃለሁ›› ሰው ሁሉ ጆሮውን ቀስሮ የሚያዳምጥ መሆኑ ግድም አልሰጣትም፡፡ ‹‹ምን እንደፈለክ አውቃለሁ፡፡ ትናንት ማታ ከዚያች ጋለሞታ ጋር የልብህን ስታደርስ ነው
ያደርከው አይደለም?››
‹‹አይደለም››
‹‹አይደለም?!›› አለችና አፍጣ አየችው፡፡ እውነቱን እየተናገረ መሆኑን ገምታለች አለዚያም በጣም ተቀራርባችኋል አይደለም? ልብህን ወስዳዋለች እሷም ወዳሃለች አሁን እኔን አትፈልገኝም፧ እውነት
አይደለም? እመን!››
‹‹ምንም የማምነው ነገር የለም››
‹‹እምነተ ቢስ ስለሆንክ ነዋ፡፡ እኔ አውቄብሃለሁ፤ አይሮፕላኑ ውስጥ
ያለው ሰው ሁሉ የሚጠረጥረውም ይህንኑ ነው፡፡ መርቪን በጣም
አዝኜብሃለሁ፡ ሃሞተ ኮስታራ ትመስለኝ ነበር፡፡››
ሃሞተ ኮስታራ! ይህ ቃል ጠቅ አደረገው::
‹‹እውነቴን ነው እንደፈለግሁ መሆን እንደምችል አሳዛኝ ወሬ ፈጥረህ ታወራለህ፡፡ በጣም ተለሳልሰሃል፤ እኔ ጣቱን የሚጠባ ህጻን አይደለሁም ልታታልለኝ አትችልም›› አለች፡፡
‹‹ደህና›› አለ መርቪን ‹‹ሰላማዊ ድርድር እንድናደርግ ብጠይቅሽ
አልተቀበልሽም፤ እንደፈለግሽ ሁኚ›› አለና ተነሳ ‹‹አነጋገርሽን የሰማ ሰው ከውሽማዬ ጋር አገር ጥዬ የምጠፋው እኔ እመስለዋለሁ›› ወደበሩ አመራና
ተ‹‹ስትጋቡ አሳውቂኝ›› አለና ሄደ፡፡
‹‹ደህና!›› አለች ዳያና ደሟ እየተንተከተከ፡፡ አካባቢውን ስትቃኝ ልዕልት ላቪኒያ ገልመጥ አደረጓት፤ ሉሉ ቤል ፈገግ አለች፤ ኦሊስ ፊልድ አባባሏን
ባለመውደድ ሲኮሳተር ፍራንክ ጎርዲኖ ደግሞ ወንድ ነሽ ሲል አደነቃት፡
በመጨረሻም የመርቪንን ሁኔታና በንዴት መገንፈል አይቶ ‹ማርክ ምን
ይል ይሆን› ብላ ስትመለከተው ጥርስ በጥርስ ሆኗል፡፡ እሷም የእሱ ሳቅ ተጋብቶባት ትስቃለች፡፡
‹ምንድነው የሚያስቅህ? አለችው እየሳቀች
‹‹ልክ ልኩን ነው የነገርሽው›› አለ ‹‹ኮርቼብሻለሁ፤ ደስም ብሎኛል።
‹‹ለምን ተደሰትክ?››
‹‹በህይወትሽ መርቪንን ስትጋተሪው የመጀመሪያሽ ነው?››
‹‹ሳይሆን አይቀርም››
‹‹ከዚህ በኋላ አትፈሪውም አይደል?››
‹‹አልፈራውም››
‹‹አትወጂውም ማለት እኮ ነው ይሄ››
‹‹ይሆን?›› አለች ሃሳብ ገብቷት፡፡ ለብዙ ጊዜ መርቪንን አልወደውም
ብላ ስታስብ ነበር፧ አሁን ግን ልቧ የሚነግራት ሌላ ነው ባለፉት ወራት
ከሱ እየተደበቀች ስትማግጥ እንኳን ለእሱ ያላት ፍቅር እንዳለ መሆኑን
አውቃለች፡፡ ትታው ሄዳ እንኳን ልቧ ከእሱ ጋር ነው፤ አሁን ደግሞ አይሮፕላን ውስጥ ጸጸት ጠቅ እያደረገ ሲያስቸግራት እግሩ ላይ ውደቂ ውደቂ ይላታል፡ ይህም ሆኖ ወደ እሱ መመለስ የማይታሰብ ነው፡፡
ማርክም ‹‹ከዚያች ጋለሞታ ሴትዮ ጋር ቢሄድ ምንድነው የሚሰማሽ?»ሲል ጠየቃት
«ግድ የለኝም» አለች ወዲያውኑ ‹‹አንተ ልክ ብለሃል፡ ከዚህ በኋላ
ወደ ኋላ መመለስ የለም፡፡››
✨ይቀጥላል✨
👍17
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ዘጠኝ (39) «ሄሎ» አለች ሶስት እራቴ ስልኩ ከጮኸ በኋላ ። «እንደምን አመሸሸ ሚሰ አዳምስን። ማይክል ሂልያርድ እባላለሁ» አለ ። ባለችበት ላይ ደንዝዛ ቀረች ። ልትጮህ ቃጣት…..
። ሆኖም እንደምንም ብላ ተቆጣጠረቸው ። ትንፋሽዋንም ዋጥ አደረገች ። ይህን ሁሉ ካደረገች በኋላ «ነው? ሳንፍራንሲስኮ መጥተሃል ማለት ነው" አለች፡፡ ይህን የተናገረችው በመጠኑ በሚቆራረጥና በጎረና ድምፅ ነበር ። ያን ድምፅ የሰማው ማይክል የተቆጣች መሰለው ። ምን አስቆጣት ? አለ በሀሳቡ ። ምናልባት በሌላ ነገር ትበሳጭታ ይሆናል ። ወይም እቤቷ ሲደውሉላት አትወድ ይሆናል ። ብቻ የሰው ጠባይ ብዙ ነው ። ያም ሆነ ያ ማይክል ደንታው አይደልም ። «አዎ። ሳንፍራንሲስኮ ነው ያለሁት ። እና ተገናኝቶን አንዳንድ ነገር ብንወያይ ብዬ ነበር» አለ ማይክ «የለም የለም ። ምንም የምንነጋገረው ነገር የለም ። ለእናትህ ግልጹን የተናገርኩ መስሎኝ ነበርኮ» አለች። አልቅሺ አላት። ሰውነቷ በመላ ተንቀጠቀጠ ፤ የስልኩን እጀታ እንደያዘች ። «አልነገረችኝም ። ምናልባትም ረስታው ይሆናል» አለ ። የሱም ድምፅ እንደ እሷ ድምዕ ሙጥረት ይሰማበት ጀመረ። «ካንች ጋር እንደተለያያችው ቅለል ያለ የልብ ድካም በሽታ ስለተነሳባት ከህመሙ በኋላ ረሰታው ይሆናል ፣ ያው ልትረጂው እንደምትችይ…››
‹‹አመሣት ?» አለችና ዝም አለች « ግን ወዲያው… «አሁንስ እንዴት ነው ተሻላት?» ስትል ጠየቀች። «አሁን ደህና ናት ። ከዚያም አልፎ ባለፈው ሳምንት ባል አግብታ አሁን ማጆርካ ውስጥ ትገኛለች» አለ ማይክ ። አንድ ነገር መጥቶ እጉሮሮዋ ላይ ተሰነቅረ ። ውሻ! የኔን ሕይወት ብልሽትሽቱን አውጥታ ስታበቃ እሷ ተሰርጋ ትምነሽነሽ እንጂ ! እለች ፤ በሀሳቧ ። ጥርሷን ማንቀራጨጭም አማራት ። ስልኩን እጆሮው ላይ ድርግም ማድረግም አሰኛት። «ይህ እንኳ ከቁም ነገራችን ውጭ ነው» ኣለ የማይክል ድምዕ «እና መቼ እንገናኝ ትያለሽ ? »
«አንችልም ብዬ ነገርኩህኮ » ይህን ያለችው በፍጥነት ነበር ፤እንትፍ ያለችበትን ያህል ። ጉዳዩ አስደንግጦት ወይም አስገርሞት ኣይኑን ገርበብ አደረገ ግን ብዙም አልተጨነቀም ። ጉልበት አልነበረውም፤ ደክሞት ነበረና ። «እሺ ይሁን፤ተሸነፍኩ ። ላሁኑ ማለቴ ነው። ምናልባት ሀሳብሽን ከቆየርሽ ፌይርሞንት ሆቴል ነኝ። ደውይልኝ»
«አልደውልም»
«ደግ»
«ደህና ደር፤ ሚስተር ሂልያርድ»
«ደህና ደሪ፤ ሜሪ አዳምሰን» እንዴት ባንዴ ነገሩን ቁርጥ አደረገው! ደሞም ፈፅሞ ማይክልን የመሰለ ነገር የለውም! የደከመ፤ ሁሉ ነገር ገደል ይግባ ብሎ የተወ ይመስላል ። በነዚህ ሁለት ዓመታት ውስጥ ምን ደርሶበት ይሆን? ምን አጋጥሞት ይሆን? ስልኩን ከዘጋች በኋላ ለረጂም ጊዜ ስለማይክል ብዙ ጥያቄዎች ጠየቶች። ስለማይክል ባያሌው ኣሰበች።
•••••••••••••••••••••••••
«ውዴ ዛሬ በጣም ፀጥ ብለሻል። ቅር የተሰኘሽበት ነገር አለ ?› አለ ፒተር ግሬግሰን ምሳ የሚበሉበትን ጠረጴዛ አሻግሮ እያየ ። ሜሪ ምንም አልሆንኩም በሚል መንገድ ራሷን ነቅንቃ ወይን የተቀዳበትን መለኪያ እያሽከረከረች «ምንም አልሆንኩም» አለች «ምንም አልሆንኩም ። ቅር ያለኝ ነገርም የለም ። እያሰብኩ ነው… ስለምጀምረው አዲስ ስራ። አዲስ ፕሮጀክት ሳስብ ሁሌም እንዲህ ያደርገኛል ። ከአእምሮዬ ማውጣት አልችልም » ይህን ያለችው ስታብል ነበር ።ይህን ደግሞ እሷም ታውቅዋለቸ፤ ፒተርም ያውቀዋል ። ነገሩ ሌላ ነበር። ከትናንት በስቲያ ምሽት ማይክል ከደወለ ጊዜ ጀምሮ ናንሲ ዛሬን መኖር አልቻለችም ወደ ትናንት እየተጠለፈች ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት የሆነውን ሁሉ ታሰባለች ። የምታስበው ሁሉ የመጨረሻዋን ቀን ነበር።... ቢስክሌቶቻቸውን ሲነዱ፤ ወደ ባዛሩ ሲገቡ ፎቶ ግራፍ ሲነሱ ካንዲ ፍሎስ ስትልስ… ሰማያዊዎቹን መቁጠሪያዎች በባህሩ ዳርቻ ላይ ስትቀብራቸው፡፤ የገቡት ቃል... ያን ለት ማታ የለበሰችው ቀሚስ፤ማይክልን ልታገባ ስትወጣ እና .. እና በመጨረሻ የማይክል እናት ድምፅ . . እሷ በፋሻ ትደግልላ ያነጋገረቻት ።
ይኸ ሁሉ ልክ እንደፊልም ባይኗ ላይ ጎልቶ ይታያት ነበር። ስንቴ ሌላ ነገር ልታስብ ሞከረች ግን አልቻለችም ። ከዚህ ሀሳብ ልታመልጥ ከቶ አልቻለችም ። «ውዴ ግን. .ግን . . ደህና ነሽ?» አለ ፒተር በመጨነቅ ። «ምን ትሆናለች ብለህ ነው? አይዞህ አትጨነቅ ። ደህና ነኝ በእውነት ደህና ነኝ ። ይቅርታ ዛሬ መቼም አሰጨነቅኩህ ። ምናልባትም ደክሞኝ ይሆናል ፤ በቃ» አለች ሆኖም አላመናትም ። አይቷላ የተጠናወተው የሚመስል ገፅታዋን ። የተከፋ ፈቷን ፤ በዓይኖቹዋ መካከል የተቋጠረ ግንባሩዋን አይቷል ። «ከፌ ጋር በቅርብ ተገናኝታችሁ ነበር?» አለ ፒተር። «አልተገናኘንም ። አንድ ቀን ምሳ እጋብዛታለሁ እያልኩ አልቻልኩም። ኤግዚብሽኑ ከተከፈተ ወዲህ ስራ በዛ» አለች ። ኤግዚብሽኑን ሰታነሳ ውለታውን በሚነግር ድምፅ ነበር የተናገረችው ፈገግ ብላ ። ከዚያም አከታትላ «ምን! እንደምታየው ከፎቶ ግራፍ ማጠቢያ ክፍል ወጥቼ አላውቅም» አለች። «እንዲህ በጓደኝነት ማለቴ ሳይሆን እንደሐኪም አነጋግራሽ ታውቃለች ወይ? ማለቴ ነበር» ኣለ ። «እንዲያውም ። አልነገርኩህም እንዴ ከገና በአል በፊት ያን ጉዳይ ጨረሰን ብዬ?»
«ግን እኮ ማን እንደሆነ ውሣኔውን የሰጠው አልነገርሽኝም ። አንቺ ትሆኝ ፤እሷ »
«የወሰንኩት እኔ ነኝ ። ግን ስነግራት አልተቃወመችም »። አለች
ፒተር የአእምሮ ሕክምና እንደሚያስፈልጋት በመጠቆሙ ናንሲ ትንሽ ቅር አላት ። ስለዚህም ሕክምናው እንደማያስፈልጋት በተዘዋዋሪ እንዲህ ስትል ልትነግረው ሞከረች ። «ፒተር ምንም የመረበሽ ስሜት የለብኝም ። ድካም ብቻ ነው። ደሞ እሱ ይለቀኛል »
«ይሆናል ። ግን ልቤ ይጠራጠራል ምክንያቱም አየሽ እፊትሽ ላይ የሆነ ነገር ይታየኛል ። . . . ማለት ከሁለት ዓመት በፈት የነበረው ነገር የሆነው ሁሉ እየመጣ የሚያስጨንቅሽ ይመስለኛል » ይህን ሲል እየተጨነቀና ሁኔታዋን እያጤነ ነበር ። ሰምታው ሽምቅቅ ስትል ሲያይ ደነገጠ ። ራሱን ጠላ ። «የምን ያለፈ ነገር?» አለች ሜሪ « የማይረባ ነገር አታምጣ››
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ
ምዕራፍ ሰላሳ ዘጠኝ (39) «ሄሎ» አለች ሶስት እራቴ ስልኩ ከጮኸ በኋላ ። «እንደምን አመሸሸ ሚሰ አዳምስን። ማይክል ሂልያርድ እባላለሁ» አለ ። ባለችበት ላይ ደንዝዛ ቀረች ። ልትጮህ ቃጣት…..
። ሆኖም እንደምንም ብላ ተቆጣጠረቸው ። ትንፋሽዋንም ዋጥ አደረገች ። ይህን ሁሉ ካደረገች በኋላ «ነው? ሳንፍራንሲስኮ መጥተሃል ማለት ነው" አለች፡፡ ይህን የተናገረችው በመጠኑ በሚቆራረጥና በጎረና ድምፅ ነበር ። ያን ድምፅ የሰማው ማይክል የተቆጣች መሰለው ። ምን አስቆጣት ? አለ በሀሳቡ ። ምናልባት በሌላ ነገር ትበሳጭታ ይሆናል ። ወይም እቤቷ ሲደውሉላት አትወድ ይሆናል ። ብቻ የሰው ጠባይ ብዙ ነው ። ያም ሆነ ያ ማይክል ደንታው አይደልም ። «አዎ። ሳንፍራንሲስኮ ነው ያለሁት ። እና ተገናኝቶን አንዳንድ ነገር ብንወያይ ብዬ ነበር» አለ ማይክ «የለም የለም ። ምንም የምንነጋገረው ነገር የለም ። ለእናትህ ግልጹን የተናገርኩ መስሎኝ ነበርኮ» አለች። አልቅሺ አላት። ሰውነቷ በመላ ተንቀጠቀጠ ፤ የስልኩን እጀታ እንደያዘች ። «አልነገረችኝም ። ምናልባትም ረስታው ይሆናል» አለ ። የሱም ድምፅ እንደ እሷ ድምዕ ሙጥረት ይሰማበት ጀመረ። «ካንች ጋር እንደተለያያችው ቅለል ያለ የልብ ድካም በሽታ ስለተነሳባት ከህመሙ በኋላ ረሰታው ይሆናል ፣ ያው ልትረጂው እንደምትችይ…››
‹‹አመሣት ?» አለችና ዝም አለች « ግን ወዲያው… «አሁንስ እንዴት ነው ተሻላት?» ስትል ጠየቀች። «አሁን ደህና ናት ። ከዚያም አልፎ ባለፈው ሳምንት ባል አግብታ አሁን ማጆርካ ውስጥ ትገኛለች» አለ ማይክ ። አንድ ነገር መጥቶ እጉሮሮዋ ላይ ተሰነቅረ ። ውሻ! የኔን ሕይወት ብልሽትሽቱን አውጥታ ስታበቃ እሷ ተሰርጋ ትምነሽነሽ እንጂ ! እለች ፤ በሀሳቧ ። ጥርሷን ማንቀራጨጭም አማራት ። ስልኩን እጆሮው ላይ ድርግም ማድረግም አሰኛት። «ይህ እንኳ ከቁም ነገራችን ውጭ ነው» ኣለ የማይክል ድምዕ «እና መቼ እንገናኝ ትያለሽ ? »
«አንችልም ብዬ ነገርኩህኮ » ይህን ያለችው በፍጥነት ነበር ፤እንትፍ ያለችበትን ያህል ። ጉዳዩ አስደንግጦት ወይም አስገርሞት ኣይኑን ገርበብ አደረገ ግን ብዙም አልተጨነቀም ። ጉልበት አልነበረውም፤ ደክሞት ነበረና ። «እሺ ይሁን፤ተሸነፍኩ ። ላሁኑ ማለቴ ነው። ምናልባት ሀሳብሽን ከቆየርሽ ፌይርሞንት ሆቴል ነኝ። ደውይልኝ»
«አልደውልም»
«ደግ»
«ደህና ደር፤ ሚስተር ሂልያርድ»
«ደህና ደሪ፤ ሜሪ አዳምሰን» እንዴት ባንዴ ነገሩን ቁርጥ አደረገው! ደሞም ፈፅሞ ማይክልን የመሰለ ነገር የለውም! የደከመ፤ ሁሉ ነገር ገደል ይግባ ብሎ የተወ ይመስላል ። በነዚህ ሁለት ዓመታት ውስጥ ምን ደርሶበት ይሆን? ምን አጋጥሞት ይሆን? ስልኩን ከዘጋች በኋላ ለረጂም ጊዜ ስለማይክል ብዙ ጥያቄዎች ጠየቶች። ስለማይክል ባያሌው ኣሰበች።
•••••••••••••••••••••••••
«ውዴ ዛሬ በጣም ፀጥ ብለሻል። ቅር የተሰኘሽበት ነገር አለ ?› አለ ፒተር ግሬግሰን ምሳ የሚበሉበትን ጠረጴዛ አሻግሮ እያየ ። ሜሪ ምንም አልሆንኩም በሚል መንገድ ራሷን ነቅንቃ ወይን የተቀዳበትን መለኪያ እያሽከረከረች «ምንም አልሆንኩም» አለች «ምንም አልሆንኩም ። ቅር ያለኝ ነገርም የለም ። እያሰብኩ ነው… ስለምጀምረው አዲስ ስራ። አዲስ ፕሮጀክት ሳስብ ሁሌም እንዲህ ያደርገኛል ። ከአእምሮዬ ማውጣት አልችልም » ይህን ያለችው ስታብል ነበር ።ይህን ደግሞ እሷም ታውቅዋለቸ፤ ፒተርም ያውቀዋል ። ነገሩ ሌላ ነበር። ከትናንት በስቲያ ምሽት ማይክል ከደወለ ጊዜ ጀምሮ ናንሲ ዛሬን መኖር አልቻለችም ወደ ትናንት እየተጠለፈች ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት የሆነውን ሁሉ ታሰባለች ። የምታስበው ሁሉ የመጨረሻዋን ቀን ነበር።... ቢስክሌቶቻቸውን ሲነዱ፤ ወደ ባዛሩ ሲገቡ ፎቶ ግራፍ ሲነሱ ካንዲ ፍሎስ ስትልስ… ሰማያዊዎቹን መቁጠሪያዎች በባህሩ ዳርቻ ላይ ስትቀብራቸው፡፤ የገቡት ቃል... ያን ለት ማታ የለበሰችው ቀሚስ፤ማይክልን ልታገባ ስትወጣ እና .. እና በመጨረሻ የማይክል እናት ድምፅ . . እሷ በፋሻ ትደግልላ ያነጋገረቻት ።
ይኸ ሁሉ ልክ እንደፊልም ባይኗ ላይ ጎልቶ ይታያት ነበር። ስንቴ ሌላ ነገር ልታስብ ሞከረች ግን አልቻለችም ። ከዚህ ሀሳብ ልታመልጥ ከቶ አልቻለችም ። «ውዴ ግን. .ግን . . ደህና ነሽ?» አለ ፒተር በመጨነቅ ። «ምን ትሆናለች ብለህ ነው? አይዞህ አትጨነቅ ። ደህና ነኝ በእውነት ደህና ነኝ ። ይቅርታ ዛሬ መቼም አሰጨነቅኩህ ። ምናልባትም ደክሞኝ ይሆናል ፤ በቃ» አለች ሆኖም አላመናትም ። አይቷላ የተጠናወተው የሚመስል ገፅታዋን ። የተከፋ ፈቷን ፤ በዓይኖቹዋ መካከል የተቋጠረ ግንባሩዋን አይቷል ። «ከፌ ጋር በቅርብ ተገናኝታችሁ ነበር?» አለ ፒተር። «አልተገናኘንም ። አንድ ቀን ምሳ እጋብዛታለሁ እያልኩ አልቻልኩም። ኤግዚብሽኑ ከተከፈተ ወዲህ ስራ በዛ» አለች ። ኤግዚብሽኑን ሰታነሳ ውለታውን በሚነግር ድምፅ ነበር የተናገረችው ፈገግ ብላ ። ከዚያም አከታትላ «ምን! እንደምታየው ከፎቶ ግራፍ ማጠቢያ ክፍል ወጥቼ አላውቅም» አለች። «እንዲህ በጓደኝነት ማለቴ ሳይሆን እንደሐኪም አነጋግራሽ ታውቃለች ወይ? ማለቴ ነበር» ኣለ ። «እንዲያውም ። አልነገርኩህም እንዴ ከገና በአል በፊት ያን ጉዳይ ጨረሰን ብዬ?»
«ግን እኮ ማን እንደሆነ ውሣኔውን የሰጠው አልነገርሽኝም ። አንቺ ትሆኝ ፤እሷ »
«የወሰንኩት እኔ ነኝ ። ግን ስነግራት አልተቃወመችም »። አለች
ፒተር የአእምሮ ሕክምና እንደሚያስፈልጋት በመጠቆሙ ናንሲ ትንሽ ቅር አላት ። ስለዚህም ሕክምናው እንደማያስፈልጋት በተዘዋዋሪ እንዲህ ስትል ልትነግረው ሞከረች ። «ፒተር ምንም የመረበሽ ስሜት የለብኝም ። ድካም ብቻ ነው። ደሞ እሱ ይለቀኛል »
«ይሆናል ። ግን ልቤ ይጠራጠራል ምክንያቱም አየሽ እፊትሽ ላይ የሆነ ነገር ይታየኛል ። . . . ማለት ከሁለት ዓመት በፈት የነበረው ነገር የሆነው ሁሉ እየመጣ የሚያስጨንቅሽ ይመስለኛል » ይህን ሲል እየተጨነቀና ሁኔታዋን እያጤነ ነበር ። ሰምታው ሽምቅቅ ስትል ሲያይ ደነገጠ ። ራሱን ጠላ ። «የምን ያለፈ ነገር?» አለች ሜሪ « የማይረባ ነገር አታምጣ››
👍17
«ያ ሆነ ማለት እኮ አእምሮሽኮ ትክክል አይደለም ማለት አይደለም። ያለ ነው። ምክንያቱም እንዲህ አይነቱ ነገር ቶሎ አይለቅም ። ቁስሉ እንዲህ በቀላሉ አይሽርም ። እስከ አስር ዓመት እስከ ሃያ አመት የሚሰቃዩ ሰዎች አሉ ፤ አደጋ ከደረሰባቸው በኋላ። ውስጥሽ ሁሌም ያስታውሳል ። ሀሳቡን አዘውትረሽ ገሸሽ ካላደረግሽው አይለቅሽም »
«አድርጌዋለሁ ፤ ለቆኛልም»
«እሱን እንግዲህ በሚገባ እምታውቂው አንቺ ነሽ ። ሆኖም አትዘናጊለት። ልትደብቂው አትሞክሪ ። ያ ከሆነ በትንሽ በትንሹ ውስጥ ለውስጥ ይጎዳሽና ሕይወትሽን ይሰነክለዋል። ችሎታሽንም ውሱን አድርጎ ያስቀረዋል ። እኔ እንኳ ይህን ያህል መናገርም እያስፈልገኝም ። ግን አንቺ መጠንቀቅ ይኖርብሻል ። ከፌ አሊሰን ጋር ያለውን ግንኙነትም ለተወሰነ ጊዜ ብትቀጥይው የሚበጅ ይመስለኛል» ይህን ሁሉ ሲል ጉዳዩ እንዳስጨነቀው ይታወቅበት ነበር ። ይህን ብሎም ትክዝ አለ ። «ከፌ ጋር መቀጠሉ እንኳ አያስፈልገኝም» አለች ሜሪ።
ይህን ካለች በኋላ መልስ ሊሰጣት አልፈለገም ። መከራከር የለበትም ። ዝም ብሎ እጅዋን ይዞ ተይው እንደማለት ያህል መታ መታ አደረገው። ጉዳዩን ስላነሳና ስለረበሻት ግን ይቅርታ አልጠየቅም ። ሁኔታዋ ሁሉ ነገሩ አሳሳቢ እንደሆነ በግልፅ እንዲያይ አድርጎአታል ። በዚህ ሁኔታ ትንሽ እንደቆዩ «እሺ እንግዲህ። አሁን ብንሄድ ምን ይመስልሻል?» አለ ። ይህን ሲል ከልቡ ፈገግ እያለ ነበረና አፀፋውን ልትመልስለት ሞከረች። ግን አልቻለችም ። ልታምንለት አትፈልግም እንጂ ግምቱ ልክ እንደሆነ ገብቷታል ። ዋሽታዋለችና ፈገግታው እንቢ አላት። ከምግብ ቤቱ እንደወጡ ፤ «ቤት ላድርስሽ? ሲል ጠየቃት ። «አያስፈልግም ፤ ወደ ኤግዚብሽኑ አዳራሽ ጎራ ብዬ ጃክን ላነጋግረው አስቤአለሁ። የምናዘጋጃቸው ነገሮች አሉ» አለች። «ደግ» አለ ፒተር። እጁን እትከሻዋ ላይ ጣል ኦድርጎ ወደ ፀደዩ የፀሐይ ብር ገቡ። ጧት መሬቱን ሸፍኖ የነበረው ጉም በኖ ጠፍቶ ቀኑ ብሩህ ሆኗል ። የምግብ ቤቱ የቆሙ መኪናዎች አስተናባሪ የፒተርን ጥቁር አውቶሞቢል ነድቶ እመንገዱ አስገብቶ ሲያቆማት ፒተር የእንግዳ መቀመጫውን ጋቢና በር ለናንሲ ከፈተላት ። ገብታ ተቀመጠች ከዚያም በወዲያኛው በር ዞሮ እነጂው መቀመጫ ወንበር ላይ ተቀምጦ መሪውን ሲይዝ ቀሚሷን እያስተካከለች ፈገግ አለች። በሀሳብ ተውጣ ። ምን ያህል እንደሚያስብላት፤ የቱን ያህል እንደሚጨነቅላት ይገባታል ። ሆኖም ለምን እንደሚያፈቅራት አይገባትም ። ትጠራጠራለች። ለምን ? ትላለች። ስለፈጠረኝ ፍቅሩን ለፍጡሩ ሊሰጥ የሚገባው ዓይነት ፍቅር ይሆን ? ወይስ ፊት ስለምነሳው አላገኛትም ብሎ ስለሚያስብ ? እንጃ ። ሆኖም ሁልጊዜም መንገድ እምትዘጋ እሷ ናት ። ይህ ሀሳብ ስላለባት ይሆናል… ነፃ አትሆንም፤ ከፒተር ጋር ስትሆን። እሱ ግን ደግ ነው። ሁሉ ነገር ነው። ጥሩ ሰው አይደለሁም ማለት ነው የሚል ሃሳብ መጣባት ። ግን እንዴት ነፃ ትሁን? ፍርሃት አልባ ሁለተኛ አደጋ እንደሚደርስባት የሚያሳስብ ነገር አለባት ። ባለፈው የደረሰባት አደጋ ጥሎት ያለፈ ጠባሳ ቢኖር ነው። ምናልባትም ፌ አሊሰንን (የአእምሮ ሕክምና ጠቢቧን) ማነጋገር ሊኖርባት ይሆናል….»
«ዛሬ ዝምታ በዝምታ ሆነሻል፤ የኔ ፍቅር ። አሁንም ያንኑ አዲስ ፕሮጀክት እያሰብሽ ነው?» አለ ፒተር ሃሳቧን እያናጠባት። እራሷን በአዎንታ ነቅንቃ የእፍረት ፈገግታ ፈገግ እንዳለች እማጅራቱ አካባቢ በለሆሳስ ዳሰስ አደረገችው። እና ፤ «ግን ለምንድነው ይህን ያሀል እምትጨነቀው » ስትል ጠየቀችው።
«ምክንያቱም ሜሪ አንች ለኔ ወደር የሌለሽ ልዩ ፍጡር ስለሆንሽ ነው» አላት «እና ደግሞ ይህን የምልሽ ከልቤ መሆኑን ብታውቂልኝ ደስ ይለኝ ነበር» ግን ለምን? ይህን ያህል ለምን ? ምናልባት ፊቴን በፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ሲያክም ያቺን የሚወዳትን ሴት አስመስሎ ሰርቶኝ ይሆን እንዴ? እሷን እየመሰልኩት ይሆን እንዴ? ዝም ብሎ ሀሳብ ነበር ።
ሀሳቧን ፀጥ ለማድረግ ፤ አእምሮዋን ለማሳረፍ ወደ ኋላ ተለጥጣ ራሷን እሶፋው ላይ ጥላ አይኗን ከደነች። ሆኖም በዚያ ሁኔታ ብዙ አልቆየችም ። የጥይት መሰሏን መኪና መሪ አንድ መታጠፊያ ላይ ሲያዞረው አይኗን በግድ ገለጠች። አይኗን ገልጣ ስትመለከት፤ አንድ መናጢ ቀይ ጃጉዋር ኦቶሞቢል በሷ በኩል ከፊት ለፊት እየተፈተለከ ሲመጣ አየች። ጃጉዋሩ መንገዱን ለቆ ካሉበት አውቶሞቢል ፊት ለፊት እንዲመጣ ያደረገው እንድ እመንገዱ ዳር የቆመ የጭነት መኪና ነበር ፤ መንገዱን ስለያዘበትና ያንን ደርቦ ለማለፍ ሲሞክር ። ይህ ጃጓር ፍጥነቱንም አልቀነሰም ። መንገዱን ስቶ ፊት ለፊት መጣ። ፈረፋንጎውና የፒተር መኪና ፈረፋንጎ የተሳሳሙ እስኪመስል ድረስ ቀርቦ ታያት ። ያበደው የጃጓር ነጂ ፊት ለፊት ሲመጣ ፒተር እንደምንም ብሎ መንገዱን ለቀቀለትና ቀይ መብራት ጥሶ ወደፊት ተፈተለከ ። ጃጓሩን ተደንቆ ዞሮ አየው ሜሪ ግን የለችም ። ባለችበት ላይ ደርቃ ቀርታለች። የጨው አመድ ሆናለች። እፊት ለፊት ያለውን የእቃ ማስቀሙጫ መድራ ይዛ፤ አይኗ ፈጥጦ፡፤ የሰራ አካላቷ እየራደ ፤ ጥርሷ እየተንገጫገጨ አእምሮዋ ከዚህ በፊት እደረሰ አንድ አሰፈሪ ነገር ላይ ተተክሎ በጠቅላላ ጠፍታለች ።
የሜሪን ሁኔታ ያየው ፒተር ምን እንደታሰባት ፤ አሁን እምን ውስጥ እንዳለች ለማጤን ጊዜ አልፈጀበትም ። ስለዚህም የመንገዱን ዳር ካስያዘ በኋላ መኪናውን አቁሞ ሜሪን ንፋስ እንዲነካት ከመኪናው ሊያወጣት ሲይዛት ድርቅ ብላለች። ጎተት ሲያደርጋት በድንገት መኪናውን በጩኸት ሞላችው ። ከነፍስ ጠሊቅ ፍርሃት ወጥቶ ሀይለኛ ጩኽት ሆነ ። ዝም ለማሰኘት ማቀፍ ፤ መወዝወዝ፤ ጥብቅ አድርጎ መያዝ. . . ይህን ሁሉ ማድረግ ነበረበት ። ይህን ሁሉ አድርጎም በቶሎ ዝም አላለችም ። «ዝም በይ.. በቃ ዝም በይ… የለም እኮ አለፈ ። የለም ውሽት ነው። ያ ሁለተኛ አይደገምም ። እሰይ የኔመቤት ። በቃ በቃ ዝም በይ….
ይህን ሁሉ ብሎ ዝም አሰኛት ። ይህን ለማድረግ ግን ግማሽ ሰዓት ያህል ወሰደበት ። ቀስ እያለች ፀጥ አለች። ከዚያም ጉልበቷ ሁሉ ተሟጥጦ ተዝለፈለፈች። አቅሏን ግን አልሳተችም ። ቀስ ኢያለ እየደባበሰ አረጋጋት ። ይልቁንም ፊቷ ምንም እንዳልሆነ እንድ ትረዳ እጅዋን አንስቶ ፊቷን እየዳሰሳት «ይኸው ደህና ነሽ እኮ ! ምንም አልሆንሽም እኮ!
«አድርጌዋለሁ ፤ ለቆኛልም»
«እሱን እንግዲህ በሚገባ እምታውቂው አንቺ ነሽ ። ሆኖም አትዘናጊለት። ልትደብቂው አትሞክሪ ። ያ ከሆነ በትንሽ በትንሹ ውስጥ ለውስጥ ይጎዳሽና ሕይወትሽን ይሰነክለዋል። ችሎታሽንም ውሱን አድርጎ ያስቀረዋል ። እኔ እንኳ ይህን ያህል መናገርም እያስፈልገኝም ። ግን አንቺ መጠንቀቅ ይኖርብሻል ። ከፌ አሊሰን ጋር ያለውን ግንኙነትም ለተወሰነ ጊዜ ብትቀጥይው የሚበጅ ይመስለኛል» ይህን ሁሉ ሲል ጉዳዩ እንዳስጨነቀው ይታወቅበት ነበር ። ይህን ብሎም ትክዝ አለ ። «ከፌ ጋር መቀጠሉ እንኳ አያስፈልገኝም» አለች ሜሪ።
ይህን ካለች በኋላ መልስ ሊሰጣት አልፈለገም ። መከራከር የለበትም ። ዝም ብሎ እጅዋን ይዞ ተይው እንደማለት ያህል መታ መታ አደረገው። ጉዳዩን ስላነሳና ስለረበሻት ግን ይቅርታ አልጠየቅም ። ሁኔታዋ ሁሉ ነገሩ አሳሳቢ እንደሆነ በግልፅ እንዲያይ አድርጎአታል ። በዚህ ሁኔታ ትንሽ እንደቆዩ «እሺ እንግዲህ። አሁን ብንሄድ ምን ይመስልሻል?» አለ ። ይህን ሲል ከልቡ ፈገግ እያለ ነበረና አፀፋውን ልትመልስለት ሞከረች። ግን አልቻለችም ። ልታምንለት አትፈልግም እንጂ ግምቱ ልክ እንደሆነ ገብቷታል ። ዋሽታዋለችና ፈገግታው እንቢ አላት። ከምግብ ቤቱ እንደወጡ ፤ «ቤት ላድርስሽ? ሲል ጠየቃት ። «አያስፈልግም ፤ ወደ ኤግዚብሽኑ አዳራሽ ጎራ ብዬ ጃክን ላነጋግረው አስቤአለሁ። የምናዘጋጃቸው ነገሮች አሉ» አለች። «ደግ» አለ ፒተር። እጁን እትከሻዋ ላይ ጣል ኦድርጎ ወደ ፀደዩ የፀሐይ ብር ገቡ። ጧት መሬቱን ሸፍኖ የነበረው ጉም በኖ ጠፍቶ ቀኑ ብሩህ ሆኗል ። የምግብ ቤቱ የቆሙ መኪናዎች አስተናባሪ የፒተርን ጥቁር አውቶሞቢል ነድቶ እመንገዱ አስገብቶ ሲያቆማት ፒተር የእንግዳ መቀመጫውን ጋቢና በር ለናንሲ ከፈተላት ። ገብታ ተቀመጠች ከዚያም በወዲያኛው በር ዞሮ እነጂው መቀመጫ ወንበር ላይ ተቀምጦ መሪውን ሲይዝ ቀሚሷን እያስተካከለች ፈገግ አለች። በሀሳብ ተውጣ ። ምን ያህል እንደሚያስብላት፤ የቱን ያህል እንደሚጨነቅላት ይገባታል ። ሆኖም ለምን እንደሚያፈቅራት አይገባትም ። ትጠራጠራለች። ለምን ? ትላለች። ስለፈጠረኝ ፍቅሩን ለፍጡሩ ሊሰጥ የሚገባው ዓይነት ፍቅር ይሆን ? ወይስ ፊት ስለምነሳው አላገኛትም ብሎ ስለሚያስብ ? እንጃ ። ሆኖም ሁልጊዜም መንገድ እምትዘጋ እሷ ናት ። ይህ ሀሳብ ስላለባት ይሆናል… ነፃ አትሆንም፤ ከፒተር ጋር ስትሆን። እሱ ግን ደግ ነው። ሁሉ ነገር ነው። ጥሩ ሰው አይደለሁም ማለት ነው የሚል ሃሳብ መጣባት ። ግን እንዴት ነፃ ትሁን? ፍርሃት አልባ ሁለተኛ አደጋ እንደሚደርስባት የሚያሳስብ ነገር አለባት ። ባለፈው የደረሰባት አደጋ ጥሎት ያለፈ ጠባሳ ቢኖር ነው። ምናልባትም ፌ አሊሰንን (የአእምሮ ሕክምና ጠቢቧን) ማነጋገር ሊኖርባት ይሆናል….»
«ዛሬ ዝምታ በዝምታ ሆነሻል፤ የኔ ፍቅር ። አሁንም ያንኑ አዲስ ፕሮጀክት እያሰብሽ ነው?» አለ ፒተር ሃሳቧን እያናጠባት። እራሷን በአዎንታ ነቅንቃ የእፍረት ፈገግታ ፈገግ እንዳለች እማጅራቱ አካባቢ በለሆሳስ ዳሰስ አደረገችው። እና ፤ «ግን ለምንድነው ይህን ያሀል እምትጨነቀው » ስትል ጠየቀችው።
«ምክንያቱም ሜሪ አንች ለኔ ወደር የሌለሽ ልዩ ፍጡር ስለሆንሽ ነው» አላት «እና ደግሞ ይህን የምልሽ ከልቤ መሆኑን ብታውቂልኝ ደስ ይለኝ ነበር» ግን ለምን? ይህን ያህል ለምን ? ምናልባት ፊቴን በፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ሲያክም ያቺን የሚወዳትን ሴት አስመስሎ ሰርቶኝ ይሆን እንዴ? እሷን እየመሰልኩት ይሆን እንዴ? ዝም ብሎ ሀሳብ ነበር ።
ሀሳቧን ፀጥ ለማድረግ ፤ አእምሮዋን ለማሳረፍ ወደ ኋላ ተለጥጣ ራሷን እሶፋው ላይ ጥላ አይኗን ከደነች። ሆኖም በዚያ ሁኔታ ብዙ አልቆየችም ። የጥይት መሰሏን መኪና መሪ አንድ መታጠፊያ ላይ ሲያዞረው አይኗን በግድ ገለጠች። አይኗን ገልጣ ስትመለከት፤ አንድ መናጢ ቀይ ጃጉዋር ኦቶሞቢል በሷ በኩል ከፊት ለፊት እየተፈተለከ ሲመጣ አየች። ጃጉዋሩ መንገዱን ለቆ ካሉበት አውቶሞቢል ፊት ለፊት እንዲመጣ ያደረገው እንድ እመንገዱ ዳር የቆመ የጭነት መኪና ነበር ፤ መንገዱን ስለያዘበትና ያንን ደርቦ ለማለፍ ሲሞክር ። ይህ ጃጓር ፍጥነቱንም አልቀነሰም ። መንገዱን ስቶ ፊት ለፊት መጣ። ፈረፋንጎውና የፒተር መኪና ፈረፋንጎ የተሳሳሙ እስኪመስል ድረስ ቀርቦ ታያት ። ያበደው የጃጓር ነጂ ፊት ለፊት ሲመጣ ፒተር እንደምንም ብሎ መንገዱን ለቀቀለትና ቀይ መብራት ጥሶ ወደፊት ተፈተለከ ። ጃጓሩን ተደንቆ ዞሮ አየው ሜሪ ግን የለችም ። ባለችበት ላይ ደርቃ ቀርታለች። የጨው አመድ ሆናለች። እፊት ለፊት ያለውን የእቃ ማስቀሙጫ መድራ ይዛ፤ አይኗ ፈጥጦ፡፤ የሰራ አካላቷ እየራደ ፤ ጥርሷ እየተንገጫገጨ አእምሮዋ ከዚህ በፊት እደረሰ አንድ አሰፈሪ ነገር ላይ ተተክሎ በጠቅላላ ጠፍታለች ።
የሜሪን ሁኔታ ያየው ፒተር ምን እንደታሰባት ፤ አሁን እምን ውስጥ እንዳለች ለማጤን ጊዜ አልፈጀበትም ። ስለዚህም የመንገዱን ዳር ካስያዘ በኋላ መኪናውን አቁሞ ሜሪን ንፋስ እንዲነካት ከመኪናው ሊያወጣት ሲይዛት ድርቅ ብላለች። ጎተት ሲያደርጋት በድንገት መኪናውን በጩኸት ሞላችው ። ከነፍስ ጠሊቅ ፍርሃት ወጥቶ ሀይለኛ ጩኽት ሆነ ። ዝም ለማሰኘት ማቀፍ ፤ መወዝወዝ፤ ጥብቅ አድርጎ መያዝ. . . ይህን ሁሉ ማድረግ ነበረበት ። ይህን ሁሉ አድርጎም በቶሎ ዝም አላለችም ። «ዝም በይ.. በቃ ዝም በይ… የለም እኮ አለፈ ። የለም ውሽት ነው። ያ ሁለተኛ አይደገምም ። እሰይ የኔመቤት ። በቃ በቃ ዝም በይ….
ይህን ሁሉ ብሎ ዝም አሰኛት ። ይህን ለማድረግ ግን ግማሽ ሰዓት ያህል ወሰደበት ። ቀስ እያለች ፀጥ አለች። ከዚያም ጉልበቷ ሁሉ ተሟጥጦ ተዝለፈለፈች። አቅሏን ግን አልሳተችም ። ቀስ ኢያለ እየደባበሰ አረጋጋት ። ይልቁንም ፊቷ ምንም እንዳልሆነ እንድ ትረዳ እጅዋን አንስቶ ፊቷን እየዳሰሳት «ይኸው ደህና ነሽ እኮ ! ምንም አልሆንሽም እኮ!
👍12
አየሽው!» አላት ። ፒተር ባየውና በሆነው ነገር ሁሉ እጅግ ተረበሸ ። የገመተው ነገር እውነት እንደሆነ በሚገባ ተገነዘበ። በጣም መለስ ስትል ለስለስ ባለ፤ ግን ውሣኔ ባጠነክረው ድምፅ ‹‹የለም የለም፣ የፌ አሊሰንን ሕክምና መከታተል አለብሽ የገመትሽውን ያህል ቁስሉ አልዳነም ። ቆርጠሽ ካልተጋፈጥሽው ደሞ ሊድን አይችልም» አለ። አይኗን ክድና አዳመጠችው ግን እንዴት አድርጋ ትጋፈጠው? ምን ብላ ትጋፈጠው? ብትጋፈጠውስ የሚድነው ነገር ምንድነው ያለፈው ነገር ማለት ማይክ ማለትእኮ ነው ። ለማይክ ያላትን ፍቅር ደግሞ ምንስ ብላ እንዴትስ አድርጋ ልትረሳው ትችላለች? ማይክ ስልክ እንደደወለላት፣ ድምጹን ስትሰማ እቅፍ አድርጋ ልትስመው ምን ያህል እንደጓጓች እንዴት አድርጋ ትንገረው ለፒተር ? ቢያቅፋት የተመኘችውን ፣ማይክን ያለመችውን ምን ጉልበት አግኝታ ብታስረዳው ይገባዋል ?
ይቀጥላል...... ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
ይቀጥላል...... ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
❤9👍3
‹‹የተሰባበሩ ነፍሶች››
ምዕራፍ- ሁለት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
///
"በፈጣሪ ሊያጠቁኝ ማለት ?››
‹‹ምን አልባት ሊገድሉኝ…››
"እንዴ ምን ለማለት ነው? እነማን ናቸው...?
"ለጊዜው ማንነታቸውን እርግጠኛ ሆኜ መናገር አልችልም..ግን ደግሞ የእኛው ሰዎች ይመስሉኛል"
"ታዲያ እንዴት አመለጥሻቸው።"
"እድሜ ለኤልያስ ቀድመው እሱ ጋር ነበር የሄድት… ደውሎ ወደእኔ እየመጡ እንደሆነ አስጠነቀቀኝ።››
"እንዴት ?አልሞተም ማለት ነው?"
"እኔ እንጃ ….ውስጤ በጣም እየፈራ ነው… አምልጪ እያለኝ ነው ስልኩ የተቋረጠው ፡፡ምን አልባት እራሱን ስቶ መሠለኝ"
"እሺ አሁን የት ነሽ ?መጥቼ ልውሰድሽ"
ያለችበትን ስፍራ ነገረችው፡፡
‹‹በ10 ደቂቃ ውስጥ መጣሁ›› ብሎ ስልኩን ዘጋው።እሷም ነገሮችን መልሶ ወደማመንዠግ ተመለሰች።የሆነ የማታውቀው ስሜት ይረብሻት ጀመር፡፡ ስሜቷ ድፍርስርስ ከማለቱም በላይ ትከሻዎን እየከበዳት ነው።
ከተቀመጠችበት ቦታ ድንገት ተነሳች።መንገድን ተሻገረችና ተቃራኒውን አቅጣጫ ያዘች፡፡ በጨርቆስ አቅጣጫ ወደውስጥ የምትታጠፍ ቀጭን መንገድ ታጠፈችና የሆነች የዘበኛ ቤት ጀርባ ካለች ጠፍጣፋ ድንጋይ ጋር ዝርፍጥ ብላ ቁጭ አለች።
እሷ ከተቀመጠችበት ሀያ ሜትር በማይበልጥ ርቀት ላይ አንድ ሰፊ በረንዳ ባለው ቤት ከአስር በላይ የጎዳና ልጆች በተተረማመሰ አቅጣጫ የተተረማመሠ አለባበስ ለብሰው ተኝተዎል።በግራ በኩል ሁለት ከፊት ለፊት አንድ በአጠቃላይ ሶስት ውሾች ልጆቹ እግር ስር ተወትፈው ተኝተዋል። ከእነዚህ ህጻናት ጓደኞች የነበሩ ስንቶች እሷ ባለቤት በሆነችበት ሆስፒታል ባለቤቶች ትዕዛዝ ተፍነው ልክ ሱማሌ ተራ ገብቶ ታርዶ ለመለዋወጫ እንደሚበታተን መኪና የእነሱም ሆድ እቃ ተቀዶ ለሞላላቸውና ለደላቸው ሀብታሞች አካል መለዋወጫ ሆኖ ይሆን? .ዝግንን አላት……ከምድር ሌላ ጥግ የተሠራ ፊልም የመሠለ ትዕይንት በምናቦ እያመላለሰች ከፊት ለፊቷ እያየች ካለቻቸው ልጆች የነገ እጣ ፋንታ ጋር በማገናኘት እያሰላሰለች ተመስጣ ሳለ ስልኳ ጠራ… አነሳችው ፡፡ድምፅን በውስጧ ውጣ በሰለለ ድምፅ"ሄሎ"አለች፡፡
"ሄሎ እየደረስኩ ነው…. እዛው ነሽ?"
"አዎ የነገርኩህ ቦታ ነኝ ...ከሰላም ፋርማሲ ጎን ካለው የባስ ፌርማታ ቁጭ ብያለሁ...ቶሎ በል…. ብርድ ሊገድለኝ ነው።"
"ከዛ እንዳትንቀሳቀሺ ሁለት ደቂቃ ብቻ ስጪኝ"ስልኩ ተዘጋ፡፡
የሠጠችው ቅድም ተቀምጣ የነበረበትን ከአለችበት ተሻግሮ የሚገኘውን ስፍራ ነው።የዘበኛ ቤቱን ከለላ ለቃ ሳትወጣ እንገቷን አስግጋ አይኖቾን ከማዶ ተከለች።ለምን እንደዛ ማድረግ እንደፈለገች ለእሷም አልገባትም።ግን ድንገት ሀገር ሰላም ብላ ፤መንግስት አለ ብላ፤ አምላኳን አመስግና በተኛችበት ውድቅት ለሊት የህይወት ፍፃሜዎ ሊሆን ከጫፍ ደርሷ ነበር ፡፡ስለዚህ አይደለም ሌላ ሰው የራሷንም ጥላ ብትጠራጠር ማን ይፈርድባታል?"
"እንዴ..እንዴ...""እያየች ያለውን ነገር ከመደንገጧ የተነሳ በእጇ ይዛው የነበረ ቦርሳ ተንሸራቶ መሬት ላይ ወደቀባት...ቅድም ነፍሷን ሊነጥቋት እቤቷ መጥተው የነበሩ ወጠምሾቾ ከነጥቁር መኪናቸው ከመንገድ ወዲያ ማዶ እሷን ፍለጋ ከወዲህ ወዲያ እየተወነጨፍ ይሹለከለካሉ። ባለችበት እራሷን ኩርምትምት አደረገችና ተቀመጠች።እንደምንም አቅሟን አጠንክራ የወደቀባትን ቦርሳ እጇን ሰደደችና አነሳው፡፡ ውስጡ ያለውን ሞባይሎን አወጣችና ሙሉ በሙሉ አጠፋችው፡፡ መልሳ ወደቦርሳው ከተተች።
እንደምንም እራሷን አደፋፍራ አንገቷን አሰገገችና ማዶ የሚካሄደውን ትእይንት ማየቷን ቀጠለች …አንድ ሚኒባሷን እየተሽከረከረ በመወራጨት ስልክ ያወራል...ሌሎቹ በፍለጋቸው ተስፍ ቆርጠው ወደ ሚኒባስ ተመልሰው ገብተዋል..ብዙም ሳይቆይ ያኛውም የሚያወራውን ስልክ በማጠናቀቅ ከሹፌሩ በተቃራኒ ገቢናውን ከፍቶ ገባና መኪናወ ትንቀሳቀሰች…በአንድ ለሊት ሁለተኛ ጊዜ ነፍሷን በተአምር አተረፈች ፡፡
የመኪናዋን መሄድ ከተመለከተች ብኃላ በተሸጎጠችበት ቦታ ሆና ደቂቃዎችን አሳለፈች...ያጋጠማት ድብእዳ የማሰብ ብቃቷን የሚፈታተን ሆኖ ነው ያገኘችው...አሁን ማን ጋር ደውላ እርዳታ ለመጠየቅ እንደምትችል ወይንም ማን ቤት ሄዳ መጠለል እንደምትችል መወሰን አልቻለችም። የምትሄድባቸው ሰዎች ከአሳዳጆቾ ጋር ግንኙነት ይኑራቸው ወይም እዛ ስትሄድ አድፍጠው ጠብቀው ይድፋት መተማመን አልቻለችም።ድንገት አንድ ሰው ትዝ አላት ...ተመላላሽ ሰራተኛዋ ጥሩነሽ...የእሷን ቤት ታውቀዋለች ::አሁን ካለችበት 20 ደቂቃ አይርቅም ..በእርግጠኝነት አንደኛ እሷ ጋር ትሄዳለች ብሎ ማንም አያስብም፤ቢያስብ እንኳን እንዲህ በቀላሉ የቤቷን አድራሻ ማግኘት አይችሉም ስትል አሰበች።ወሰነች።
ከተቀመጠችበት ልትነሳ ስትመቻች ጎኗ ላይ የሆነ ጠጣር ነገር ቆረቆራት ::ዞር ስትል ፊቱን በከፊል የሸፈነ ከሲኦል ድንገት ወደታች የተወረወረ የሚመስል ወጠምሻ ሰው ጎኗ ተንበርክኮ አብረቅራቂ ጩቤ ጎኖ ላይ ሰድሮ ሊከመርባት በሚመሰል ሁኔታ ተጠግቷታል።ትንፋሹ ፊቷ ላይ ሲበተን የሚያቅለሸልሽ ስሜት ተሰማት..የሲጋራ፤የጫትና የኦልኮል ድብልቅ ሽታ ነው በአፍና በአፍንጫዋ ያለ ፍቃዶ ወደውስጦ የገባው፡፡
"በፈጣሪ...ምንድነው እሱ..?."ተናገረች፡፡
"ዝም በይ.."የሰከረ መሆኑ የሚያስታውቅ ሻካራ ድምፅ፡፡
"እሺ"እሷ ሳትፈቅድ አንደበቷ ቃላት ያወጣ ይመስል እጇን አፎ ላይ ከደነች
‹‹በዚህ ውድቅት ለሊት በዚህ ቦታ ምን አባሽ ነው ምትሰሪው?››
‹‹ከገዳዬቼ እየሸሸው››መለሰችለት
‹‹ከባለሚኒባሾቹ ነው?››
<‹አዎ››
የከተማዋ ቁጥር አንድ ቅጥር ነፍሰ ገዳዬች እንዲህ የሚያሳድዱሽ የትኛውን ፈርጣማ ባለሀብትን ወይም ባለስልጣንን ብታበሳጪ ነው…..?››ሰውዬ ስለገዳይና አስገዳዬች ብዙ የሚያውቅ ይመስላል፡፡
‹‹እኔ አስቤ ያባሳጨሁት ሰው የለም..ባክህ የምትፈልገው ቦረሳዬ ውስጥ አለ..እኔን ልቀቀኝ ልሂድበት››ለመጀመሪያ ጊዜ እንባዋ በጉንጮቾ ዝርግፍ ብሎ ወረደ… እያሳለፈችው ያለውን ከዚህ በላይ ልትቋቋመው የምትችለው መስሎ አልተሰማትም…..ነፍሷንም ለማተርፍ መንፈራገጡ ብዙም ውጤት ያለው መስሎ አልተሰማትም…ከአንዱ ሞት አምልጣ ሌላው የሞት መዳፍ ላይ እየወደቀች እራሷን እያገኘችው ነው …
‹‹.ሂዱ ሁላችሁም በከተማው ተሰማሩ ተሳክቶለት እሷን ያመጣ ሽልማት አለው›› ተብለው መላአከ ሞቶች ጠቅላላ እሷን ለማደን በከተማው ውስጥ በሁሉም አቅጣጫ የተሰማሩ መስሎ ነው የተሰማት..ከአንዱ ሾልካ ስታመልጥ ሌላው ከፊት ለፊቷ ይጠብቃታል፡፡
‹‹እኔ ብለቅሽ እኮ እነሱ ያገኙሻል››
‹‹የእድሌን እሞክራለሁ››
‹‹አይ እኔ የእድሌን ብሞክር አይሻልም ..?ስልካቸው አለኝ….ደውዬላቸው ስንት እንደምትወጪ እጠይቃቸዋለሁ?››
እስከአሁን ከደነገጠችው በላይ ደነገጠች….‹‹አረ በፈጣሪ ……የሠው ነፍስ ከየትኛውም ገንዘብ በላይ እኮ ነው?››
‹‹አረ ባክሽ….አሁን እዛ ፊትለፊትሽ የተረፈረፉት የጎዳና ልጆች ነፍስ ከገንዘብ በላይ ነው..?በእውነት እንደእዛ ነው የምታስቢው ..?ነው ወይስ አንዳንድ እንደአንቺ ለየት ያለ በወርቅ የተንቆጠቆጠ ና በእንቁ ያጌጠ ነፍስ ሲሆን ነው በገንዘብ ሊትተመን የማይችለው…?በይ አሁን ባዶ ዲስኩርሽን ለራስሽ አቆይውና ይሄን ጩቤ እዚህ ለስላሳ አንጀትሽ ውስጥ ሳልሽጠው ቀስ ብለሽ ተነሺ..››
ምዕራፍ- ሁለት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
///
"በፈጣሪ ሊያጠቁኝ ማለት ?››
‹‹ምን አልባት ሊገድሉኝ…››
"እንዴ ምን ለማለት ነው? እነማን ናቸው...?
"ለጊዜው ማንነታቸውን እርግጠኛ ሆኜ መናገር አልችልም..ግን ደግሞ የእኛው ሰዎች ይመስሉኛል"
"ታዲያ እንዴት አመለጥሻቸው።"
"እድሜ ለኤልያስ ቀድመው እሱ ጋር ነበር የሄድት… ደውሎ ወደእኔ እየመጡ እንደሆነ አስጠነቀቀኝ።››
"እንዴት ?አልሞተም ማለት ነው?"
"እኔ እንጃ ….ውስጤ በጣም እየፈራ ነው… አምልጪ እያለኝ ነው ስልኩ የተቋረጠው ፡፡ምን አልባት እራሱን ስቶ መሠለኝ"
"እሺ አሁን የት ነሽ ?መጥቼ ልውሰድሽ"
ያለችበትን ስፍራ ነገረችው፡፡
‹‹በ10 ደቂቃ ውስጥ መጣሁ›› ብሎ ስልኩን ዘጋው።እሷም ነገሮችን መልሶ ወደማመንዠግ ተመለሰች።የሆነ የማታውቀው ስሜት ይረብሻት ጀመር፡፡ ስሜቷ ድፍርስርስ ከማለቱም በላይ ትከሻዎን እየከበዳት ነው።
ከተቀመጠችበት ቦታ ድንገት ተነሳች።መንገድን ተሻገረችና ተቃራኒውን አቅጣጫ ያዘች፡፡ በጨርቆስ አቅጣጫ ወደውስጥ የምትታጠፍ ቀጭን መንገድ ታጠፈችና የሆነች የዘበኛ ቤት ጀርባ ካለች ጠፍጣፋ ድንጋይ ጋር ዝርፍጥ ብላ ቁጭ አለች።
እሷ ከተቀመጠችበት ሀያ ሜትር በማይበልጥ ርቀት ላይ አንድ ሰፊ በረንዳ ባለው ቤት ከአስር በላይ የጎዳና ልጆች በተተረማመሰ አቅጣጫ የተተረማመሠ አለባበስ ለብሰው ተኝተዎል።በግራ በኩል ሁለት ከፊት ለፊት አንድ በአጠቃላይ ሶስት ውሾች ልጆቹ እግር ስር ተወትፈው ተኝተዋል። ከእነዚህ ህጻናት ጓደኞች የነበሩ ስንቶች እሷ ባለቤት በሆነችበት ሆስፒታል ባለቤቶች ትዕዛዝ ተፍነው ልክ ሱማሌ ተራ ገብቶ ታርዶ ለመለዋወጫ እንደሚበታተን መኪና የእነሱም ሆድ እቃ ተቀዶ ለሞላላቸውና ለደላቸው ሀብታሞች አካል መለዋወጫ ሆኖ ይሆን? .ዝግንን አላት……ከምድር ሌላ ጥግ የተሠራ ፊልም የመሠለ ትዕይንት በምናቦ እያመላለሰች ከፊት ለፊቷ እያየች ካለቻቸው ልጆች የነገ እጣ ፋንታ ጋር በማገናኘት እያሰላሰለች ተመስጣ ሳለ ስልኳ ጠራ… አነሳችው ፡፡ድምፅን በውስጧ ውጣ በሰለለ ድምፅ"ሄሎ"አለች፡፡
"ሄሎ እየደረስኩ ነው…. እዛው ነሽ?"
"አዎ የነገርኩህ ቦታ ነኝ ...ከሰላም ፋርማሲ ጎን ካለው የባስ ፌርማታ ቁጭ ብያለሁ...ቶሎ በል…. ብርድ ሊገድለኝ ነው።"
"ከዛ እንዳትንቀሳቀሺ ሁለት ደቂቃ ብቻ ስጪኝ"ስልኩ ተዘጋ፡፡
የሠጠችው ቅድም ተቀምጣ የነበረበትን ከአለችበት ተሻግሮ የሚገኘውን ስፍራ ነው።የዘበኛ ቤቱን ከለላ ለቃ ሳትወጣ እንገቷን አስግጋ አይኖቾን ከማዶ ተከለች።ለምን እንደዛ ማድረግ እንደፈለገች ለእሷም አልገባትም።ግን ድንገት ሀገር ሰላም ብላ ፤መንግስት አለ ብላ፤ አምላኳን አመስግና በተኛችበት ውድቅት ለሊት የህይወት ፍፃሜዎ ሊሆን ከጫፍ ደርሷ ነበር ፡፡ስለዚህ አይደለም ሌላ ሰው የራሷንም ጥላ ብትጠራጠር ማን ይፈርድባታል?"
"እንዴ..እንዴ...""እያየች ያለውን ነገር ከመደንገጧ የተነሳ በእጇ ይዛው የነበረ ቦርሳ ተንሸራቶ መሬት ላይ ወደቀባት...ቅድም ነፍሷን ሊነጥቋት እቤቷ መጥተው የነበሩ ወጠምሾቾ ከነጥቁር መኪናቸው ከመንገድ ወዲያ ማዶ እሷን ፍለጋ ከወዲህ ወዲያ እየተወነጨፍ ይሹለከለካሉ። ባለችበት እራሷን ኩርምትምት አደረገችና ተቀመጠች።እንደምንም አቅሟን አጠንክራ የወደቀባትን ቦርሳ እጇን ሰደደችና አነሳው፡፡ ውስጡ ያለውን ሞባይሎን አወጣችና ሙሉ በሙሉ አጠፋችው፡፡ መልሳ ወደቦርሳው ከተተች።
እንደምንም እራሷን አደፋፍራ አንገቷን አሰገገችና ማዶ የሚካሄደውን ትእይንት ማየቷን ቀጠለች …አንድ ሚኒባሷን እየተሽከረከረ በመወራጨት ስልክ ያወራል...ሌሎቹ በፍለጋቸው ተስፍ ቆርጠው ወደ ሚኒባስ ተመልሰው ገብተዋል..ብዙም ሳይቆይ ያኛውም የሚያወራውን ስልክ በማጠናቀቅ ከሹፌሩ በተቃራኒ ገቢናውን ከፍቶ ገባና መኪናወ ትንቀሳቀሰች…በአንድ ለሊት ሁለተኛ ጊዜ ነፍሷን በተአምር አተረፈች ፡፡
የመኪናዋን መሄድ ከተመለከተች ብኃላ በተሸጎጠችበት ቦታ ሆና ደቂቃዎችን አሳለፈች...ያጋጠማት ድብእዳ የማሰብ ብቃቷን የሚፈታተን ሆኖ ነው ያገኘችው...አሁን ማን ጋር ደውላ እርዳታ ለመጠየቅ እንደምትችል ወይንም ማን ቤት ሄዳ መጠለል እንደምትችል መወሰን አልቻለችም። የምትሄድባቸው ሰዎች ከአሳዳጆቾ ጋር ግንኙነት ይኑራቸው ወይም እዛ ስትሄድ አድፍጠው ጠብቀው ይድፋት መተማመን አልቻለችም።ድንገት አንድ ሰው ትዝ አላት ...ተመላላሽ ሰራተኛዋ ጥሩነሽ...የእሷን ቤት ታውቀዋለች ::አሁን ካለችበት 20 ደቂቃ አይርቅም ..በእርግጠኝነት አንደኛ እሷ ጋር ትሄዳለች ብሎ ማንም አያስብም፤ቢያስብ እንኳን እንዲህ በቀላሉ የቤቷን አድራሻ ማግኘት አይችሉም ስትል አሰበች።ወሰነች።
ከተቀመጠችበት ልትነሳ ስትመቻች ጎኗ ላይ የሆነ ጠጣር ነገር ቆረቆራት ::ዞር ስትል ፊቱን በከፊል የሸፈነ ከሲኦል ድንገት ወደታች የተወረወረ የሚመስል ወጠምሻ ሰው ጎኗ ተንበርክኮ አብረቅራቂ ጩቤ ጎኖ ላይ ሰድሮ ሊከመርባት በሚመሰል ሁኔታ ተጠግቷታል።ትንፋሹ ፊቷ ላይ ሲበተን የሚያቅለሸልሽ ስሜት ተሰማት..የሲጋራ፤የጫትና የኦልኮል ድብልቅ ሽታ ነው በአፍና በአፍንጫዋ ያለ ፍቃዶ ወደውስጦ የገባው፡፡
"በፈጣሪ...ምንድነው እሱ..?."ተናገረች፡፡
"ዝም በይ.."የሰከረ መሆኑ የሚያስታውቅ ሻካራ ድምፅ፡፡
"እሺ"እሷ ሳትፈቅድ አንደበቷ ቃላት ያወጣ ይመስል እጇን አፎ ላይ ከደነች
‹‹በዚህ ውድቅት ለሊት በዚህ ቦታ ምን አባሽ ነው ምትሰሪው?››
‹‹ከገዳዬቼ እየሸሸው››መለሰችለት
‹‹ከባለሚኒባሾቹ ነው?››
<‹አዎ››
የከተማዋ ቁጥር አንድ ቅጥር ነፍሰ ገዳዬች እንዲህ የሚያሳድዱሽ የትኛውን ፈርጣማ ባለሀብትን ወይም ባለስልጣንን ብታበሳጪ ነው…..?››ሰውዬ ስለገዳይና አስገዳዬች ብዙ የሚያውቅ ይመስላል፡፡
‹‹እኔ አስቤ ያባሳጨሁት ሰው የለም..ባክህ የምትፈልገው ቦረሳዬ ውስጥ አለ..እኔን ልቀቀኝ ልሂድበት››ለመጀመሪያ ጊዜ እንባዋ በጉንጮቾ ዝርግፍ ብሎ ወረደ… እያሳለፈችው ያለውን ከዚህ በላይ ልትቋቋመው የምትችለው መስሎ አልተሰማትም…..ነፍሷንም ለማተርፍ መንፈራገጡ ብዙም ውጤት ያለው መስሎ አልተሰማትም…ከአንዱ ሞት አምልጣ ሌላው የሞት መዳፍ ላይ እየወደቀች እራሷን እያገኘችው ነው …
‹‹.ሂዱ ሁላችሁም በከተማው ተሰማሩ ተሳክቶለት እሷን ያመጣ ሽልማት አለው›› ተብለው መላአከ ሞቶች ጠቅላላ እሷን ለማደን በከተማው ውስጥ በሁሉም አቅጣጫ የተሰማሩ መስሎ ነው የተሰማት..ከአንዱ ሾልካ ስታመልጥ ሌላው ከፊት ለፊቷ ይጠብቃታል፡፡
‹‹እኔ ብለቅሽ እኮ እነሱ ያገኙሻል››
‹‹የእድሌን እሞክራለሁ››
‹‹አይ እኔ የእድሌን ብሞክር አይሻልም ..?ስልካቸው አለኝ….ደውዬላቸው ስንት እንደምትወጪ እጠይቃቸዋለሁ?››
እስከአሁን ከደነገጠችው በላይ ደነገጠች….‹‹አረ በፈጣሪ ……የሠው ነፍስ ከየትኛውም ገንዘብ በላይ እኮ ነው?››
‹‹አረ ባክሽ….አሁን እዛ ፊትለፊትሽ የተረፈረፉት የጎዳና ልጆች ነፍስ ከገንዘብ በላይ ነው..?በእውነት እንደእዛ ነው የምታስቢው ..?ነው ወይስ አንዳንድ እንደአንቺ ለየት ያለ በወርቅ የተንቆጠቆጠ ና በእንቁ ያጌጠ ነፍስ ሲሆን ነው በገንዘብ ሊትተመን የማይችለው…?በይ አሁን ባዶ ዲስኩርሽን ለራስሽ አቆይውና ይሄን ጩቤ እዚህ ለስላሳ አንጀትሽ ውስጥ ሳልሽጠው ቀስ ብለሽ ተነሺ..››
👍19❤1
በለሰለሰ አንደበቷ ለምና አንጀቱን አራራለሁ ብላ ጭራሽ የሚያበሳጨውን ነገር ተናግራው አስቆጣችው….ምርጫ አልነበራትም፡፡ የሚንቀጠቀጡ እግሮቾን እንደምንም አበርትታ ቆመች….ጩቤ የያዘ እጆችን እንደቀሰረ ቦርሳ በያዘ ሌላ እጁ ትከሻዋን ደርቦ ጨመደደና እየጎተተ ጨለማ ውስጥ ሁለት ሰው በመከራ በምታሳልፍ ቀጭን መንገድ ውስጥ ይዞት ገባ….ተስፋ በመቁርጥ ያለምንም መወራጨትና ትግል እንዳላት ሆና ተከተለችው…ደግነቱ ቡዙም ሳይጓዙ አንድ የቆርቆሮ በራፍ ጋር ስደርሱ ገፋ አድርጎ ከፈተና እሷን ቀድሞ ገፍትሮ አስገባት፡፡ ከኃላ ተከትሏት ገባ፡፡
የቆርቆሮውን በራ መልሶ ዘጋውና እየጎተተ በመዳዳ ወዳሉት ሶስት ክፍል ሰርቢስ ቤቶች ይዞት ሄደ፡፡ በቀኝ በኩል ጥግ ላይ ያለውን ክፍል ደረሱ.. ቁልፍ ከኪሱ አውጥቶ ይከፍታል ብላ ስትጠብቅ ዝም ብሎ በራፉን ሲገፋው ወለል ብሎ ተከፈተ..ገፍትሮ ወደውስጥ አስገባትና ተከትሎት ገብቶ መልሶ ዘጋው…..በዳበሳ መብራቱን ሲያበራው ጨለማው ተገፈፈና በክፍሉ ደማቅ ብርሀን ሞላ…ዝም ብሎ ገፍቶ ሲከፍተው ውስጥ ሰው ያለ መስሏት ነበር…ከገቡ ቡኃላ ዙሪያ ገባዋን ስታይ ግን ጠባብ እና በጣም ንጽህ አራት በአምስት ስፋት ያለት ክፍል ባዶ ነች፡፡ከአንድ ጥግ ያልተተኛበት ሮዝ ቀለም ያለው ባለዘርፍ አልጋ ልብስ የለበሰ ባለሜትር ከሀያ አልጋ ይታያል……ከአልጋው ጎን ባለ ኮመዲኖ ግዙፍ ጂፓስ አለ….ትንሽ እራቅ ብሎ ግድግዳ ላይ ተለጥፈ የተሰቀለ አርባ ምናምን ኢንች ቴሊቪዝን ይታያል…ከስር ሌሎች መጠናቸው አነስ የሚሉ ሁለት ቴሌቪዥኖች አሉ… መሀከል ላይ ባለ ጠረጵዛ ቁጥራቸው ቢያንስ 10 የሚሆኑ የተለያየ መጠን ያላቸው ስልኮች እና ታብሌቶች ተዘርግፈው ይታያሉ….
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
የቆርቆሮውን በራ መልሶ ዘጋውና እየጎተተ በመዳዳ ወዳሉት ሶስት ክፍል ሰርቢስ ቤቶች ይዞት ሄደ፡፡ በቀኝ በኩል ጥግ ላይ ያለውን ክፍል ደረሱ.. ቁልፍ ከኪሱ አውጥቶ ይከፍታል ብላ ስትጠብቅ ዝም ብሎ በራፉን ሲገፋው ወለል ብሎ ተከፈተ..ገፍትሮ ወደውስጥ አስገባትና ተከትሎት ገብቶ መልሶ ዘጋው…..በዳበሳ መብራቱን ሲያበራው ጨለማው ተገፈፈና በክፍሉ ደማቅ ብርሀን ሞላ…ዝም ብሎ ገፍቶ ሲከፍተው ውስጥ ሰው ያለ መስሏት ነበር…ከገቡ ቡኃላ ዙሪያ ገባዋን ስታይ ግን ጠባብ እና በጣም ንጽህ አራት በአምስት ስፋት ያለት ክፍል ባዶ ነች፡፡ከአንድ ጥግ ያልተተኛበት ሮዝ ቀለም ያለው ባለዘርፍ አልጋ ልብስ የለበሰ ባለሜትር ከሀያ አልጋ ይታያል……ከአልጋው ጎን ባለ ኮመዲኖ ግዙፍ ጂፓስ አለ….ትንሽ እራቅ ብሎ ግድግዳ ላይ ተለጥፈ የተሰቀለ አርባ ምናምን ኢንች ቴሊቪዝን ይታያል…ከስር ሌሎች መጠናቸው አነስ የሚሉ ሁለት ቴሌቪዥኖች አሉ… መሀከል ላይ ባለ ጠረጵዛ ቁጥራቸው ቢያንስ 10 የሚሆኑ የተለያየ መጠን ያላቸው ስልኮች እና ታብሌቶች ተዘርግፈው ይታያሉ….
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍17
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ሆራ በጨርቆሌ ማዝነት በደንብ እየተቀለበ ከቆየ በኋላ ሚዜው ሰውነቱ እንደ ተመለሰ አረጋገጠ። ስለዚህ ከሎ ሆራና ሚዜው
ከተሪ (ዲክ ዲክ) ቆዳ የተተለተለ ቀበቶ መሳይና ኩርኩፋ ይዘው
በደንቡ መሠረት ጎይቲ አንተነህን በድብቅ ማሳደድ ጀመሩ።
ጎይቲ አንተነህ ከሎን አልወደደችውም እሷ ልቧ የጠፋባት ለዚያ ጀግና ለደልቲ ገልዲ ነው" መሬቱን በልበሙሉነት እየረገጠ
ሲንጐማለል፣ የሷንም ልብ እንደ ጠረማመሰው ሁሉ በፍቅር ታቃስታለች።
በኢቫንጋዲ ጭፈራ ወቅት አንዳንዴ መንደራቸው ብቅ ካለ ስሜት ቀስቃሽ የሆኑትን ሌሎቹን የዳንስ ምቶች ከሌሎች ጋር
ብትጨፍርም ጭንን በጭን የማግባቱ ጊዜ ቀድማ የምትጋብዘው እሱን ነው። ጭኑን በጭኗ ውስጥ ሲያስገባ የአእምሮዋን እንቅስቃሴ ያዛባና በቍጥጥሩ ስር ያደርጋታል" ከወገቧ ልጥጥ ብላ ወንድ ብልቱ ላይ ትለጠፍበታለች" በዚያ ወቅት ስሜት እንደ ቅቤ ይቀልጥና እሱም እሽት፣ እሷም አሽት፣ እሱም እሽት...ሲደራረጉ ይቆዩና
ሁለቱም ሲሸነፉ፣ ውጥረት ሲበዛባቸው ተያይዘው ወደ ጫካ፣ ወደ ልዩው የተፈጥሮ መኝታ ክፍል ጐራ ይላሉ“
ጫካው ውስጥ ወፎች፣ አራዊት፣ እባቦችና ሰዎችም ጭምር ፍቅራቸውን በነፃነት ይለዋወጣሉ ጫካ ውስጥ ትርዒት አቅራቢ እንጂ
ተመልካች አይኖርም። «ሁሉም ለየራሱ…» ብቻ መባባል ነው።
ጎይቲ አንተነህ ታዲያ ያ አራዊትን፣ ሰውን የገደለ ጀግና የፍቅርም ጀግና ሆኖ አግኝታዋለች" ጠምዘዝ አድርጎ በጠንካራ እጆቹ ወደ እሱ እያስጠጋ ትንፋሿ እስኪቋረጥ የሚስማትና እንደ ሕፃን ልጅ አቅፎ የሚያጫውታት ሁሉ ትዝታን ያልፈጠረባት እፎይታን ያልሰጣት ጊዜ የለም።
ከሎ ሆራ፣ ጎይቲ አንተነህን ባየ ቍጥር ከፍቅሩ ፅናት አንፃር ሰውነቱ እየተልፈሰፈሰ ቢርበተበትም ተፈቃሪዋ ግን ኵሩ ሆና ኵሩ ወንድ፣ ጅንን ጀግና፣ ስሙ የገነነ ወንድ ፈላጊ ነበረችና እሱ ለእሷ
ሲል ልብሱን አውልቆ ራቁቱን ቢሄድም፣ ሊያደርገው ያላሰበውን
እንዲያደርግ ፍቅሯ ቢያስገድደውም፣ እሷ ግን ለሱ ቁብ የማይሰማት
ሆነችበት"
የጎይቲ አንተነህ ልብ ያለው ደልቲ ገልዲ ላይ ሲሆን፣ የከሎ ሆራ ልብ የማለለው ደግሞ፣ ለጎይቲ አንተነህ ነው። ቢሆንም ከሎ
ሆራ እሷን የማግኘት ተስፋው አልጨለመበትም" እሱም ሆነ ሽያው
(ሚዜው) ከቀናቸው ጎይቲ አንተነህን ብቻዋን ሰከም ሰከም ስትል ሊያገኟት ይችላሉ።
አንድ ቀን በሬ ጠምዳ ስታርስ፣ አጥማጆቿ በርቀት ቍጥቋጦው ውስጥ ተደብቀው ሲከተሏት ዋሉ። መቼም እንደዚያን ቀን በከፊል የተመቻቸ ቀን ከዚህ በፊት አላጋጠማቸውም" በሬዎችን በጅራፍ ሸንቆጥ በማድረግ፣ ከወገቧ ወደ ጎንና ጎን ለጠጥ፣ ዳሌዎቿን ወጣ ገባ....እያደረገች ስለ ሐመር ጀግኖች፣ ስለ ከስኬ ወንዝ፣ ስለ በልጉ ታንጐራጕራለች። አጠገቧ የአጎቷ ልጅ ብቻ ነው ያለው፤ እሱ ዘወር ካለላቸው ፈጥነው ሊይዟትና የልባቸውን ሊያደርሱ ይችላሉ " እሱ እያለ ግን ምንም መሥራት አይችሉም ጎይቲ የተዘጋጀላትን ወጥመድ በጭራሽ አላወቀችም ዝም ብላ እርሻዋን ታርሳለች። አፍቃሪዋም፣ ከዘምባባው ዙሪያ ካለው ሰንበሌጥ ውስጥ ሆኖ በገዛ ምራቁ ይታነቃል።
አጥጆቿ፣ የኦጎቷን ልጅ ቦርጆ (አምላክ) ከዚያ አካባቢ ዘወር እንዲያደርገው ይመኛሉ" የአጎቷ ልጅ ደግሞ፣ ጎይቲ አንተነህ ልጃገረድ በመሆኗ ብቻዋን ትቷት ቢሄድ ሊደርስባት የሚችለውን
አጋጣሚ አሰበ" ኋላ እሱና ሌሎች ጐረምሳ ዘመዶቿ መጠበቅ ተስኗቸው ጀግንነት፣ ሀብት ከሌለው አንዱ ቢተናኮላት የሌሎች
ልጃገረዶች ማሽሟጠጥና በጓደኞቹ «ፈሪ» ተብሎ መናቁ፣ እሱንና ዘመዶቹን ስለሚያናድዳቸው ብቻዋን ትቷት ለመሄድ አልፈለገም።
ስለዚህ አዳኞች ታዳኟን በቍጥጥር ሥር እንዳያውሉ የአጎቷ ልጅ
«ጕሮሮ አጥንት» ሆኖባቸው ሳይሳካላቸው ቀረ።
በሌላ ቀናትም ውኃ ለመቅዳት ስትሄድ፣ ገበያ ስትመላለስ ትክለ
ቁመናዋን፣ ፈገግታዋን፣ የሚነጥረውን መቀመጫዋን ቀምሶ
ያልጠገበውና እያየ በመሳሳት ላይ ያለው የመንደሯ ጐረምሳ፣ እንደ
ሴት ውሻ ከቦ ስለሚከታተላት በድብቅ ለሚከታተሏት እንቅፋት
ሆኖባቸው ሰነበተ።
ከሎ ሆራ ከሚዜው ጋር ጫካ ለጫካ ሲዞርና ጎይቲ አንተነህን ሲከታተል ጕሮሮው ሲጮህበት ቢውልም፣ እየቆየ ግን መሰላቸት ጀመረ። ፊት ለፊት ሄዶ የደንቡን ለመፈጸም ያስብና ባህሉን ባለማክካበሩ የሚደርስበትን ውግዘትና ቅጣት እያሰበ፣ ሐሳቡን ከሕሊናው አውጥቶ ያሽቀነጥራል"
አንድ ቀን ግን፣ ጎይቲ አንተነህ ደንገዝገዝ ባለ ምሽት፣ ከቤቷ ወጥታ መንገዱን ስትነካው እነከሎ ተከተሏት" ከመንደሯ ዘወር
እንዳለች የመሮጥ ያህል እየተራመደች ወደፊት ገሰገሰች" ከሎ ሆራ፣
«የት እየሄደች ይሆን? ብቻዋን ካለፍርሃት እንዴት ትሄዳለች» በማለት ግራ ገባው ከወሮ ራቅ ብለው ካሉት መንደሮች ለመድረስ
ከመቻሏ በፊት ግን እነሱ ያቀዱትን ከመፈጸም የሚያግዳቸው የለም።
«አቤት ለስንት ጊዜ እንዳለፋን በግላጭ አገኘናት» ተባብለው
ከሎና ሚዜው ተቃቅፈው ደስታቸውን ተገላለጹና ፍጥነት ጨምረው
ለመያዝ ወደ ፊት ሽምጥ ሮጡ" እሷ ዘንድ ከመድረሳቸው በፊት ግን
ሁለቱም ሩጫቸውን ገትተው ቆሙ ከግራር ጥላው ሥር መሣሪያ የያዘና በርኮታው ላየ የተቀመጠ ሰው ያዩ መሰላቸው» አበሸቃቸው፣ ገረማቸውም፣ «ማን ይሆን?» ጠየቀ ከሎ፣ «እንጃ!» አለ ሚዜው። ስለዚህ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ወደ ቃጫው ተክል ገባ ብለው አደፈጡ። ጎይቲ አንተነህ ወደዚያ
ሰው እየቀረበች ስትሄድ እየተደነባበረች የሰካራም ጕዞ ጀመረች ሰውየው መጀመሪያ አላያትም ነበር። ዱካዋን ሲሰማ ግን
ከተቀመጠበት ፈንጠር ብሎ ተነሥቶ መሣሪያውን ሲደግን፣ ወደሱ
የምትገሰግሰው ጎይቲ አንተነህ ናት። መሣሪያውን አቃንቶ፣ እጁን ከፍቶ ጠበቃት፤ ያው እንደ ልማዱ እንደ ቀንድ የቆመው ጡቷን
ከሰውነቱ ስታሻሽለት፣ እሱም የኰራውን ዳሌዋን በሁለት እጁ ወደ
እሱ ይበልጥ እየሳበ፣ ትንፋሿ እስኪቈረጥ ድረስ ሳማት። እሷም ሆነ እሱ በተፈጠረው ሙቀት እንደ ቅቤ ቀለጡ።
ከሎ ሆራ፣ ይህን ትርዒት ራሱ እንደሚሠራ ሁሉ፣ እሱም ባለበት ደነዘዘ። ሰውነቱ ሁሉ ባለበት ሲወጣጠር ታወቀው። በእሱ ላይ የተለጠፈችበትና አቅፎ የሚስማት መሰለው። ዋና ተዋናይዎቹ ግን ወደ ዋናው እርካታ ጕዟቸው ለመሄድ አንዱ በሌላው ውስጥ ዘልቆ ሲገባ ከሎ ከሰመመኑ ነቃ። የሚወዳት ጎይቲ አንተነህ ከሱ ጋር
ሳይሆን ያለችው ከሌላ ሰው ጋር ነው። እሱ ያቀፈውና የሳመው ለካ ግንዱን ነው" እሱ ግንድ አቅፎ ሲስም፣ እሷ ሰው አቅፋ
ትቃበጣለች፣ «ዳሚት» አለ ከሎ፣ ሊቈጣጠረው በማይችለው ስሜት ተወጥሮ።
ከሎ ሆራ ሰውዬውን በደንብ ቢያስተውለውም ሊለየው
አልቻለም። ሚዜው ግን ነገረው፣ «አያ ደልቲ ገልዲ ነው» አለው።
"አዎ እሱ ነው ካለሱ እሷን እንዲህ የሚያደነባብራትና
ትንፋሿን የሚያሳጣት ወንድ የለም» በማለት፣ በእልህ ወደ ተዋጠ ሰሜት ውስጥ ገባ" ሚዜው ግን፣ ከርቀት የሚታየው ቅብጠት አፉን
አስከፍቶታል።
ፍቅረኛሞች የፍቅር ጥማቸውን ለማርካት እየደጋገሙ ሲጫወቱ ቆዩና ተለያዩ" ጎይቲ አንተነህ ወደ መንደሯ ስትመለስ ከኋላ የቀረባት ሰው እንዳለ ሁሉ ልቧ ተንጠልጥሎ አልፈጠነችም። መንደሯ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ሆራ በጨርቆሌ ማዝነት በደንብ እየተቀለበ ከቆየ በኋላ ሚዜው ሰውነቱ እንደ ተመለሰ አረጋገጠ። ስለዚህ ከሎ ሆራና ሚዜው
ከተሪ (ዲክ ዲክ) ቆዳ የተተለተለ ቀበቶ መሳይና ኩርኩፋ ይዘው
በደንቡ መሠረት ጎይቲ አንተነህን በድብቅ ማሳደድ ጀመሩ።
ጎይቲ አንተነህ ከሎን አልወደደችውም እሷ ልቧ የጠፋባት ለዚያ ጀግና ለደልቲ ገልዲ ነው" መሬቱን በልበሙሉነት እየረገጠ
ሲንጐማለል፣ የሷንም ልብ እንደ ጠረማመሰው ሁሉ በፍቅር ታቃስታለች።
በኢቫንጋዲ ጭፈራ ወቅት አንዳንዴ መንደራቸው ብቅ ካለ ስሜት ቀስቃሽ የሆኑትን ሌሎቹን የዳንስ ምቶች ከሌሎች ጋር
ብትጨፍርም ጭንን በጭን የማግባቱ ጊዜ ቀድማ የምትጋብዘው እሱን ነው። ጭኑን በጭኗ ውስጥ ሲያስገባ የአእምሮዋን እንቅስቃሴ ያዛባና በቍጥጥሩ ስር ያደርጋታል" ከወገቧ ልጥጥ ብላ ወንድ ብልቱ ላይ ትለጠፍበታለች" በዚያ ወቅት ስሜት እንደ ቅቤ ይቀልጥና እሱም እሽት፣ እሷም አሽት፣ እሱም እሽት...ሲደራረጉ ይቆዩና
ሁለቱም ሲሸነፉ፣ ውጥረት ሲበዛባቸው ተያይዘው ወደ ጫካ፣ ወደ ልዩው የተፈጥሮ መኝታ ክፍል ጐራ ይላሉ“
ጫካው ውስጥ ወፎች፣ አራዊት፣ እባቦችና ሰዎችም ጭምር ፍቅራቸውን በነፃነት ይለዋወጣሉ ጫካ ውስጥ ትርዒት አቅራቢ እንጂ
ተመልካች አይኖርም። «ሁሉም ለየራሱ…» ብቻ መባባል ነው።
ጎይቲ አንተነህ ታዲያ ያ አራዊትን፣ ሰውን የገደለ ጀግና የፍቅርም ጀግና ሆኖ አግኝታዋለች" ጠምዘዝ አድርጎ በጠንካራ እጆቹ ወደ እሱ እያስጠጋ ትንፋሿ እስኪቋረጥ የሚስማትና እንደ ሕፃን ልጅ አቅፎ የሚያጫውታት ሁሉ ትዝታን ያልፈጠረባት እፎይታን ያልሰጣት ጊዜ የለም።
ከሎ ሆራ፣ ጎይቲ አንተነህን ባየ ቍጥር ከፍቅሩ ፅናት አንፃር ሰውነቱ እየተልፈሰፈሰ ቢርበተበትም ተፈቃሪዋ ግን ኵሩ ሆና ኵሩ ወንድ፣ ጅንን ጀግና፣ ስሙ የገነነ ወንድ ፈላጊ ነበረችና እሱ ለእሷ
ሲል ልብሱን አውልቆ ራቁቱን ቢሄድም፣ ሊያደርገው ያላሰበውን
እንዲያደርግ ፍቅሯ ቢያስገድደውም፣ እሷ ግን ለሱ ቁብ የማይሰማት
ሆነችበት"
የጎይቲ አንተነህ ልብ ያለው ደልቲ ገልዲ ላይ ሲሆን፣ የከሎ ሆራ ልብ የማለለው ደግሞ፣ ለጎይቲ አንተነህ ነው። ቢሆንም ከሎ
ሆራ እሷን የማግኘት ተስፋው አልጨለመበትም" እሱም ሆነ ሽያው
(ሚዜው) ከቀናቸው ጎይቲ አንተነህን ብቻዋን ሰከም ሰከም ስትል ሊያገኟት ይችላሉ።
አንድ ቀን በሬ ጠምዳ ስታርስ፣ አጥማጆቿ በርቀት ቍጥቋጦው ውስጥ ተደብቀው ሲከተሏት ዋሉ። መቼም እንደዚያን ቀን በከፊል የተመቻቸ ቀን ከዚህ በፊት አላጋጠማቸውም" በሬዎችን በጅራፍ ሸንቆጥ በማድረግ፣ ከወገቧ ወደ ጎንና ጎን ለጠጥ፣ ዳሌዎቿን ወጣ ገባ....እያደረገች ስለ ሐመር ጀግኖች፣ ስለ ከስኬ ወንዝ፣ ስለ በልጉ ታንጐራጕራለች። አጠገቧ የአጎቷ ልጅ ብቻ ነው ያለው፤ እሱ ዘወር ካለላቸው ፈጥነው ሊይዟትና የልባቸውን ሊያደርሱ ይችላሉ " እሱ እያለ ግን ምንም መሥራት አይችሉም ጎይቲ የተዘጋጀላትን ወጥመድ በጭራሽ አላወቀችም ዝም ብላ እርሻዋን ታርሳለች። አፍቃሪዋም፣ ከዘምባባው ዙሪያ ካለው ሰንበሌጥ ውስጥ ሆኖ በገዛ ምራቁ ይታነቃል።
አጥጆቿ፣ የኦጎቷን ልጅ ቦርጆ (አምላክ) ከዚያ አካባቢ ዘወር እንዲያደርገው ይመኛሉ" የአጎቷ ልጅ ደግሞ፣ ጎይቲ አንተነህ ልጃገረድ በመሆኗ ብቻዋን ትቷት ቢሄድ ሊደርስባት የሚችለውን
አጋጣሚ አሰበ" ኋላ እሱና ሌሎች ጐረምሳ ዘመዶቿ መጠበቅ ተስኗቸው ጀግንነት፣ ሀብት ከሌለው አንዱ ቢተናኮላት የሌሎች
ልጃገረዶች ማሽሟጠጥና በጓደኞቹ «ፈሪ» ተብሎ መናቁ፣ እሱንና ዘመዶቹን ስለሚያናድዳቸው ብቻዋን ትቷት ለመሄድ አልፈለገም።
ስለዚህ አዳኞች ታዳኟን በቍጥጥር ሥር እንዳያውሉ የአጎቷ ልጅ
«ጕሮሮ አጥንት» ሆኖባቸው ሳይሳካላቸው ቀረ።
በሌላ ቀናትም ውኃ ለመቅዳት ስትሄድ፣ ገበያ ስትመላለስ ትክለ
ቁመናዋን፣ ፈገግታዋን፣ የሚነጥረውን መቀመጫዋን ቀምሶ
ያልጠገበውና እያየ በመሳሳት ላይ ያለው የመንደሯ ጐረምሳ፣ እንደ
ሴት ውሻ ከቦ ስለሚከታተላት በድብቅ ለሚከታተሏት እንቅፋት
ሆኖባቸው ሰነበተ።
ከሎ ሆራ ከሚዜው ጋር ጫካ ለጫካ ሲዞርና ጎይቲ አንተነህን ሲከታተል ጕሮሮው ሲጮህበት ቢውልም፣ እየቆየ ግን መሰላቸት ጀመረ። ፊት ለፊት ሄዶ የደንቡን ለመፈጸም ያስብና ባህሉን ባለማክካበሩ የሚደርስበትን ውግዘትና ቅጣት እያሰበ፣ ሐሳቡን ከሕሊናው አውጥቶ ያሽቀነጥራል"
አንድ ቀን ግን፣ ጎይቲ አንተነህ ደንገዝገዝ ባለ ምሽት፣ ከቤቷ ወጥታ መንገዱን ስትነካው እነከሎ ተከተሏት" ከመንደሯ ዘወር
እንዳለች የመሮጥ ያህል እየተራመደች ወደፊት ገሰገሰች" ከሎ ሆራ፣
«የት እየሄደች ይሆን? ብቻዋን ካለፍርሃት እንዴት ትሄዳለች» በማለት ግራ ገባው ከወሮ ራቅ ብለው ካሉት መንደሮች ለመድረስ
ከመቻሏ በፊት ግን እነሱ ያቀዱትን ከመፈጸም የሚያግዳቸው የለም።
«አቤት ለስንት ጊዜ እንዳለፋን በግላጭ አገኘናት» ተባብለው
ከሎና ሚዜው ተቃቅፈው ደስታቸውን ተገላለጹና ፍጥነት ጨምረው
ለመያዝ ወደ ፊት ሽምጥ ሮጡ" እሷ ዘንድ ከመድረሳቸው በፊት ግን
ሁለቱም ሩጫቸውን ገትተው ቆሙ ከግራር ጥላው ሥር መሣሪያ የያዘና በርኮታው ላየ የተቀመጠ ሰው ያዩ መሰላቸው» አበሸቃቸው፣ ገረማቸውም፣ «ማን ይሆን?» ጠየቀ ከሎ፣ «እንጃ!» አለ ሚዜው። ስለዚህ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ወደ ቃጫው ተክል ገባ ብለው አደፈጡ። ጎይቲ አንተነህ ወደዚያ
ሰው እየቀረበች ስትሄድ እየተደነባበረች የሰካራም ጕዞ ጀመረች ሰውየው መጀመሪያ አላያትም ነበር። ዱካዋን ሲሰማ ግን
ከተቀመጠበት ፈንጠር ብሎ ተነሥቶ መሣሪያውን ሲደግን፣ ወደሱ
የምትገሰግሰው ጎይቲ አንተነህ ናት። መሣሪያውን አቃንቶ፣ እጁን ከፍቶ ጠበቃት፤ ያው እንደ ልማዱ እንደ ቀንድ የቆመው ጡቷን
ከሰውነቱ ስታሻሽለት፣ እሱም የኰራውን ዳሌዋን በሁለት እጁ ወደ
እሱ ይበልጥ እየሳበ፣ ትንፋሿ እስኪቈረጥ ድረስ ሳማት። እሷም ሆነ እሱ በተፈጠረው ሙቀት እንደ ቅቤ ቀለጡ።
ከሎ ሆራ፣ ይህን ትርዒት ራሱ እንደሚሠራ ሁሉ፣ እሱም ባለበት ደነዘዘ። ሰውነቱ ሁሉ ባለበት ሲወጣጠር ታወቀው። በእሱ ላይ የተለጠፈችበትና አቅፎ የሚስማት መሰለው። ዋና ተዋናይዎቹ ግን ወደ ዋናው እርካታ ጕዟቸው ለመሄድ አንዱ በሌላው ውስጥ ዘልቆ ሲገባ ከሎ ከሰመመኑ ነቃ። የሚወዳት ጎይቲ አንተነህ ከሱ ጋር
ሳይሆን ያለችው ከሌላ ሰው ጋር ነው። እሱ ያቀፈውና የሳመው ለካ ግንዱን ነው" እሱ ግንድ አቅፎ ሲስም፣ እሷ ሰው አቅፋ
ትቃበጣለች፣ «ዳሚት» አለ ከሎ፣ ሊቈጣጠረው በማይችለው ስሜት ተወጥሮ።
ከሎ ሆራ ሰውዬውን በደንብ ቢያስተውለውም ሊለየው
አልቻለም። ሚዜው ግን ነገረው፣ «አያ ደልቲ ገልዲ ነው» አለው።
"አዎ እሱ ነው ካለሱ እሷን እንዲህ የሚያደነባብራትና
ትንፋሿን የሚያሳጣት ወንድ የለም» በማለት፣ በእልህ ወደ ተዋጠ ሰሜት ውስጥ ገባ" ሚዜው ግን፣ ከርቀት የሚታየው ቅብጠት አፉን
አስከፍቶታል።
ፍቅረኛሞች የፍቅር ጥማቸውን ለማርካት እየደጋገሙ ሲጫወቱ ቆዩና ተለያዩ" ጎይቲ አንተነህ ወደ መንደሯ ስትመለስ ከኋላ የቀረባት ሰው እንዳለ ሁሉ ልቧ ተንጠልጥሎ አልፈጠነችም። መንደሯ
👍22🥰2
ልትደርስ ስትል ግን አጥማጆቿ እንደ ጥንግ ተወርውረው ያዟት"
ከሎ ሆራ አቅፎ ይዞ፣ እየታገለችውም ቢሆን ኩርኩፋውን አጎረሳት
ሚዜውም የተሪውን ቀጭን ቁርበት ከፊት ለፊቷ አጋደመባት" በቃ
ቃልኪዳኑ ታሠረ
ከእንግዲህ ጎይቲ አንተነህ የእሱ እንጂ የሌላ አትሆንም ይህ ደግሞ ጎይቲ አንተነህን እልክ ውስጥ ጣላት ይሆናል ብላ ያላሰበችው ከተሜ መሳይ፣ ልፍስፍስ የሱ ሊያረጋት ነው"
እጇን እያወራጨች ጮኸች፤ አለቀሰች። የመንደሩ ሰው፣ ዘመዶቿ «አወይ ተደፈርን» እያሉ፣ መሣሪያቸውን እያቀባበሉ ደረሱላት" አባቷ አንተነህ ይመር ከሁሉም ቀድሞ እንደ ደረሰ ልጁን
ምን እንደ ሆነች አወቀ። ስለዚህ ምን ሆንሽ ማለት አላስፈለገውም" ከዚያ ይልቅ፣ «ማነው አንቺ ጉድ የሠራኝ?» ብሎ ጠየቃት" ጎይቲ አንተነህ ሳግ እየተናነቃት፣ «በቀደም…የጨርቅ ጎጆ ከኛ ፊት
ለፊት» ብላ ሳትጨርስ፣ አንተነህ ይመር በእፎይታ ተነፈሰ እንሂድ እንግደል የሚሉት ጐረምሶችም የአንተነህን መቀዝቀዝ ሲያዩ ልጓሙ ወደ ኋላ እንደ ተሳበ ፈረስ ባሉበት ተቅበጠበጡ።
ጎይቲ አንተነህ፣ አባቷና ዘመዶቿ እነዚያን ልፍስፍሶች ለምን ሳያራውጧቸው እንደ ቀሩ ግራ ገብቷት ጠላቻቸው፣ «ምነው ደልቲ
ገልዲ በኖረ ኖሮ፣ ይህን ሁሉ ቦቅቧቃ ልክ ያስገባልኝ ነበር። ወይኔ ወይኔ» እያለች ደረቷን እየደቃች፣ አምርራ አለቀሰች"ማንኛውም አባት በልጁ የወደፊት የሕይወት ዕጣ ማሰቡ የማይቀር በመሆኑ አንተነህ ይመርም ልጁ የወደፊት ዕድሏ ተስፋ
ያለው እንዲሆንላት በልቡ ተመኝቶላታል” በተለይም፣ እነካርለት ወደ ወሮ መንደር መጥተው ከእነሱ ጎጆ ፊት ለፊት ድንኳናቸውን ተክለው በነበረበት ወቅት በሕሊናው ውስጥ ተፈጥሮ የማያውቅ አዲስ ተስፋ ወደ ሕሊናው ገብቷል" ከሎ ሆራ፣ «ልጅህን ከሳጠኸኝ
አስተምራታለሁ,» እያለ አስጐምዥቶታል" አንተነህ ይመር ያ ሊበላ ያልደረሰውን ተስፋ በማሰቡ ብቻ ወስፋቱ ተልወስውሶ በአፉ ምራቅ ሞልቶበታል።
«ልጄ! አንዷ ልጄ ተምራ፣ እውነት ቀለም ለይታ ማየት ብችል ምን ይሰማኝ ይሆን? አይ የማያልቅብህ አምላክ! እኔ ለሷ የማውቀውን ስመኝላት አንተ በመለኮታዊ ኃይልህ የተሻለ መረጥክላት
ላንተ ከቶ ምን የሚሳንህ ነገር አለ! እኔን ከሞት አፋፍ መልሰህ፣ ከቅዱስ ሕዝቦችህ ጋር አገናኝተህ፣ ጤንነቴንና ሰላሜን ጠብቀህ ለዚህ
ያደረስከኝ አንሶ እውነት ልጄ ለቁም ነገር ልትበቃልኝ? ለዘመናት የተለየኋቸውን ዘመዶቼን ወረቀት ጥፋ ልታገናኘኝ? እፁብ ነገር!»
በማለት አንተነህ እጆቹን ወደ አምላኩ ዘርግቶ አማተበ"
ነገር ግን ይህን ባሰበበት አእምሮ ደግሞ አዲስ ተረኛ ሐሳብ እንደገና ይስተናገድበታል፣ «መቼም የልጄ ቤተሰብ ካርላ ነው
ስለዚህ ልጄ የምታገባው ከፀንጋዞች (ባዕዳን) ወገን ነው" ያለችኝ ልጅ አንድ እሷ ብቻ በመሆኗ የማገኘው ጥሎሽ በርከትከት ያለ ካልሆነ በረቴ ላይሞላ ነው፤ ከጓሮዬ ጋጥ የማሰማራው በግና ፍየል ላጣ ነው
ማሩስ ቢሆን መጥቀሙ ቀረ" ኧረ ስንቱ ወንድሜ! ይህን ሁሉ ካጣሁ
የሐመር ኑሮዬ አስጊ ሁኔታ ላይ መውደቁ ነው።» አንተነህ ይመር
ልጁ ጎይቲን እንደሱ ፍላጎትና የወደፊት ዕጣ ዕድል ለደህና ቤተሰብ
(ሀብቱ ለሚያስተማምን) ቢድራት እሷም ጠግባ ታድራለች እሱም በረቱን በከብት ይሞላል፤ ሁሌ የሚኘውንም ጥይት ገዝቶ በዝናሩ ላይ ሻጥ ሻጥ ያደርግበታል" ታዲያ ይህን ሁሉ እምነቱንና ፍላጎቱን
ሰቅሉ ሌላ መዓት ወርዶ፣ የፈራው ከደረሰ ምን ሊሆን ነው? ማንንስ ሊወቅስ ነው?
ይህ አቀበቱን የሚጎትት፣ ቁልቁለቱን እየገፋ የሚያሽከረክረው
ሐሳቡ እንቅልፍ ነሳው። እንዲያውም በሕይወቱ ሙሉ እንደዚህ የተጨነቀበትና እንደ አንዳንድ ነገረ ፈጅ መንገድ ለመንገድ የሚያወራበትን ምክንያት አላጣውም። ይህ ሁሉ ለልጁና ለራሱ ሲል ነው አንተነህ ይመር ልጁ የጩኸት ድምፅ እንዳሰማች ነፍሱ
በጭንቅላቱ የወጣች መስሎት ነበር። መልሷን ከሰማ በኋላ ግን ለልጁ
ኩርኩፋ ያጐረሳትና የተተለተለውን የተሪ ቆዳ ያጋደመላት ከሎ ሆራ
መሆኑን እንዳወቀ እንደ እንቦሳ እየዘለለ ሊቦርቅ አማረው እንደ አዕዋፍ ክንፍ እጆቹን እያርገበገበ መብረርም አሰኘው"
‹ደግሞም አስተምራታለሁ› ብሎ ቃል ገብቶለታል" በዓይነ ሕሊናው ልጁ ተምራ ትልቅ ሰው ስትሆን ታየው። ሐመር ዘመዶቹም
ቢሆኑ እንግዲህ ከሎ ሆራና ጎይቲ አንተነህ የፈለጋቸውን ቢሠሩና ያሻው አካባቢ ይዟት ቢሄድ በግል ንብረቱ ጠያቂ የለበትም። እንኳን
ባህላዊ ሥርዓቱን አሟላ፤ እንኳን እምነቱን ተከተለ፤ አንተነህ ይመር ይህን እንዳሰበ አሁንም አንድ ነገር አእምሮውን ቆንጠጥ አደረገው «ኮይታውስ (ጥሎሽስ) እንዴት ሊሆን ነው? ከብት የለው፤ መሣሪያ
የለው" ልብሱ ቢበዛ ለኔ ምኔ ነው? እዚህ ላይ ነገር ይበላሽ ይሆን?» እውነትም አንተነህ ይህን ባሰበ ቍጥር ጉንፋን ሊይዘው ማስነጠስ ጀመረው" ከሴት ልጁ ጋብቻ ኮይታ ካልተቀበለ ታዲያ ነገ ማን
ሊደርስለት ነው? በረቱ ባዶ፣ ዝናሩ ጥይት አልባ መሆኑ ቀረ ደንቡን መጣሱ መሆኑን ሲያስብም ሆዱን ባር ባር አለው።
💫ይቀጥላል💫
ከሎ ሆራ አቅፎ ይዞ፣ እየታገለችውም ቢሆን ኩርኩፋውን አጎረሳት
ሚዜውም የተሪውን ቀጭን ቁርበት ከፊት ለፊቷ አጋደመባት" በቃ
ቃልኪዳኑ ታሠረ
ከእንግዲህ ጎይቲ አንተነህ የእሱ እንጂ የሌላ አትሆንም ይህ ደግሞ ጎይቲ አንተነህን እልክ ውስጥ ጣላት ይሆናል ብላ ያላሰበችው ከተሜ መሳይ፣ ልፍስፍስ የሱ ሊያረጋት ነው"
እጇን እያወራጨች ጮኸች፤ አለቀሰች። የመንደሩ ሰው፣ ዘመዶቿ «አወይ ተደፈርን» እያሉ፣ መሣሪያቸውን እያቀባበሉ ደረሱላት" አባቷ አንተነህ ይመር ከሁሉም ቀድሞ እንደ ደረሰ ልጁን
ምን እንደ ሆነች አወቀ። ስለዚህ ምን ሆንሽ ማለት አላስፈለገውም" ከዚያ ይልቅ፣ «ማነው አንቺ ጉድ የሠራኝ?» ብሎ ጠየቃት" ጎይቲ አንተነህ ሳግ እየተናነቃት፣ «በቀደም…የጨርቅ ጎጆ ከኛ ፊት
ለፊት» ብላ ሳትጨርስ፣ አንተነህ ይመር በእፎይታ ተነፈሰ እንሂድ እንግደል የሚሉት ጐረምሶችም የአንተነህን መቀዝቀዝ ሲያዩ ልጓሙ ወደ ኋላ እንደ ተሳበ ፈረስ ባሉበት ተቅበጠበጡ።
ጎይቲ አንተነህ፣ አባቷና ዘመዶቿ እነዚያን ልፍስፍሶች ለምን ሳያራውጧቸው እንደ ቀሩ ግራ ገብቷት ጠላቻቸው፣ «ምነው ደልቲ
ገልዲ በኖረ ኖሮ፣ ይህን ሁሉ ቦቅቧቃ ልክ ያስገባልኝ ነበር። ወይኔ ወይኔ» እያለች ደረቷን እየደቃች፣ አምርራ አለቀሰች"ማንኛውም አባት በልጁ የወደፊት የሕይወት ዕጣ ማሰቡ የማይቀር በመሆኑ አንተነህ ይመርም ልጁ የወደፊት ዕድሏ ተስፋ
ያለው እንዲሆንላት በልቡ ተመኝቶላታል” በተለይም፣ እነካርለት ወደ ወሮ መንደር መጥተው ከእነሱ ጎጆ ፊት ለፊት ድንኳናቸውን ተክለው በነበረበት ወቅት በሕሊናው ውስጥ ተፈጥሮ የማያውቅ አዲስ ተስፋ ወደ ሕሊናው ገብቷል" ከሎ ሆራ፣ «ልጅህን ከሳጠኸኝ
አስተምራታለሁ,» እያለ አስጐምዥቶታል" አንተነህ ይመር ያ ሊበላ ያልደረሰውን ተስፋ በማሰቡ ብቻ ወስፋቱ ተልወስውሶ በአፉ ምራቅ ሞልቶበታል።
«ልጄ! አንዷ ልጄ ተምራ፣ እውነት ቀለም ለይታ ማየት ብችል ምን ይሰማኝ ይሆን? አይ የማያልቅብህ አምላክ! እኔ ለሷ የማውቀውን ስመኝላት አንተ በመለኮታዊ ኃይልህ የተሻለ መረጥክላት
ላንተ ከቶ ምን የሚሳንህ ነገር አለ! እኔን ከሞት አፋፍ መልሰህ፣ ከቅዱስ ሕዝቦችህ ጋር አገናኝተህ፣ ጤንነቴንና ሰላሜን ጠብቀህ ለዚህ
ያደረስከኝ አንሶ እውነት ልጄ ለቁም ነገር ልትበቃልኝ? ለዘመናት የተለየኋቸውን ዘመዶቼን ወረቀት ጥፋ ልታገናኘኝ? እፁብ ነገር!»
በማለት አንተነህ እጆቹን ወደ አምላኩ ዘርግቶ አማተበ"
ነገር ግን ይህን ባሰበበት አእምሮ ደግሞ አዲስ ተረኛ ሐሳብ እንደገና ይስተናገድበታል፣ «መቼም የልጄ ቤተሰብ ካርላ ነው
ስለዚህ ልጄ የምታገባው ከፀንጋዞች (ባዕዳን) ወገን ነው" ያለችኝ ልጅ አንድ እሷ ብቻ በመሆኗ የማገኘው ጥሎሽ በርከትከት ያለ ካልሆነ በረቴ ላይሞላ ነው፤ ከጓሮዬ ጋጥ የማሰማራው በግና ፍየል ላጣ ነው
ማሩስ ቢሆን መጥቀሙ ቀረ" ኧረ ስንቱ ወንድሜ! ይህን ሁሉ ካጣሁ
የሐመር ኑሮዬ አስጊ ሁኔታ ላይ መውደቁ ነው።» አንተነህ ይመር
ልጁ ጎይቲን እንደሱ ፍላጎትና የወደፊት ዕጣ ዕድል ለደህና ቤተሰብ
(ሀብቱ ለሚያስተማምን) ቢድራት እሷም ጠግባ ታድራለች እሱም በረቱን በከብት ይሞላል፤ ሁሌ የሚኘውንም ጥይት ገዝቶ በዝናሩ ላይ ሻጥ ሻጥ ያደርግበታል" ታዲያ ይህን ሁሉ እምነቱንና ፍላጎቱን
ሰቅሉ ሌላ መዓት ወርዶ፣ የፈራው ከደረሰ ምን ሊሆን ነው? ማንንስ ሊወቅስ ነው?
ይህ አቀበቱን የሚጎትት፣ ቁልቁለቱን እየገፋ የሚያሽከረክረው
ሐሳቡ እንቅልፍ ነሳው። እንዲያውም በሕይወቱ ሙሉ እንደዚህ የተጨነቀበትና እንደ አንዳንድ ነገረ ፈጅ መንገድ ለመንገድ የሚያወራበትን ምክንያት አላጣውም። ይህ ሁሉ ለልጁና ለራሱ ሲል ነው አንተነህ ይመር ልጁ የጩኸት ድምፅ እንዳሰማች ነፍሱ
በጭንቅላቱ የወጣች መስሎት ነበር። መልሷን ከሰማ በኋላ ግን ለልጁ
ኩርኩፋ ያጐረሳትና የተተለተለውን የተሪ ቆዳ ያጋደመላት ከሎ ሆራ
መሆኑን እንዳወቀ እንደ እንቦሳ እየዘለለ ሊቦርቅ አማረው እንደ አዕዋፍ ክንፍ እጆቹን እያርገበገበ መብረርም አሰኘው"
‹ደግሞም አስተምራታለሁ› ብሎ ቃል ገብቶለታል" በዓይነ ሕሊናው ልጁ ተምራ ትልቅ ሰው ስትሆን ታየው። ሐመር ዘመዶቹም
ቢሆኑ እንግዲህ ከሎ ሆራና ጎይቲ አንተነህ የፈለጋቸውን ቢሠሩና ያሻው አካባቢ ይዟት ቢሄድ በግል ንብረቱ ጠያቂ የለበትም። እንኳን
ባህላዊ ሥርዓቱን አሟላ፤ እንኳን እምነቱን ተከተለ፤ አንተነህ ይመር ይህን እንዳሰበ አሁንም አንድ ነገር አእምሮውን ቆንጠጥ አደረገው «ኮይታውስ (ጥሎሽስ) እንዴት ሊሆን ነው? ከብት የለው፤ መሣሪያ
የለው" ልብሱ ቢበዛ ለኔ ምኔ ነው? እዚህ ላይ ነገር ይበላሽ ይሆን?» እውነትም አንተነህ ይህን ባሰበ ቍጥር ጉንፋን ሊይዘው ማስነጠስ ጀመረው" ከሴት ልጁ ጋብቻ ኮይታ ካልተቀበለ ታዲያ ነገ ማን
ሊደርስለት ነው? በረቱ ባዶ፣ ዝናሩ ጥይት አልባ መሆኑ ቀረ ደንቡን መጣሱ መሆኑን ሲያስብም ሆዱን ባር ባር አለው።
💫ይቀጥላል💫
👍33