#አለሁላት…!
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እናቴ ሁልጊዜ ሁለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ ትለዋለች፣
“አብርሽዬ የሚያገባትን ሴት ሳታሳየኝ እንዳትገለኝ፡፡
አገባሁ !
እናቴ እለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ አለችው፣
“ምነው ይሄንንስ ከሚያሳየኝ በገደለኝ
ሀና ምንተስኖት ትባላለች የምኮራባት ሚስቴ፡፡ እወዳታለሁ፣ አፈቅራታለሁ፡፡ ክፉ ነገር በሰፈሯ
እንዲያልፍ አልፈልግም፡፡ ሀኒዬ የእኔ ጥሩ ሱስ፣ ካላየኋት ያዛጋኛል' ስል ሰዎች አያምኑኝም፤ ሀኒ
የእኔ ልብ፣ የጠላችው ጠላቴ ነው:: ይሄ አባማ የሚባል ሰውዬ በቴሌቪዥን ያደረገው ንግግር
አስጠላኝ ብትለኝ፣ ሲ አይ ኤን ሳልፈራ፣ ኤፍ.ቢ.አይን ከቁብም ሳልቆጥረው ኦሳማ ላይ የግድያ
ሙከራ ባደርግ ደስታዬ ነው:: እንቅ አድርጌ አይኑን አፍጥጦ፣ “ኧረ አብርሽ በእናትህ የዛሬን
ማረኝ..ሁለተኛ በየትኛውም ሚዲያ ከመቅረቤ በፊት ንግግሬን ለሀና ምንተስኖት ኣሳውቃታለሁ..
ካልፈቀደችልኝ ኣላደርጎውም” ቢለኝ አልምረውም፡፡ እማምላክን አልምረውም !!
ሀናዬ የነብሴ ፍራሽ…ላያት ድሎቴ ናት። ሀና ካዘዘችኝ…አቤት ፍጥነቴ ገና ልትናገር ስትጀምር እኔ ሮጫለሁ፡፡ አልጋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዥን እያየች እኔ ቆንጆ ቡና እያፈላሁላት…የሆነ ነገር ብትፈልግል ልትናገር ስትጀምረው ነገሩን አምጥቼዋለሁ ፡፡ ለምን ትጨርሰዋለች.…ቃሏ ፍቅር
ነው..ፊደሎቾ እንደ ረሀብ ቀን እህል ያሳሱኛል፡፡
“አብርሽ " ስትለኝ በቦታህ!' እንዳሉት ሯጭ እዘጋጃለሁ፡፡ ወደ መሻቷ ተፈትልኮ በምድር
ላይ ያሉ ወንዶች ሁሉ የሚሰቶቻቸውን ፍላጎት ካሟሉበት ሰዓት የተሻለውን ለማስመዝገብ፡፡
"ድ." ብላ ስትጀምር ፈትለክ ብዬ ድስት…ድራፍት…ድንች ድልህ...ድፍድፍ (ከእማማ ፈጠኑ ቤት ድመት...ድንጋይ..ድራማ (ሲዲ) ይዤላት እያለከለኩ ከተፍ ስል፣ "ውይ አብርሽዬ…በቲቪ ድብ አይቼ ድቡን እየው ልልህ ነበር እኮ" ትለኛለች በፍቅር ዐይን እያየችኝ...!! አይከፋኝም ለምን እከፋለሁ፡፡ እንደገና ድብ ባየችና “ድ ብላ ስትጀምር፣ አሁን ባመጣኋቸው ነገሮች ላይ
ድብ ጨምሬ ባመጣሁላት..የእኔ ሀኒ መክሊት ብያታለሁ፡፡ እሷ ናት ቀኝም ግራም ጎኔ፡፡
ሀኒዬን እናቴ አትወዳትም፡፡ “አንዳች አስነክታው ነው ልጄን እቺ የሰው ጉድ” ትላታለች፡፡
አባቴ ገና ሲያያት የእናቱ፣ የአባቱ፣ የሁለት እህቶቹ ገዳይ ነው የምትመስለው አቤት ሲጠላት፡፡ በወሬ ወሬ “መንገድ ላይ አብረሃም እና... ሲሉት፣ "በቃ " ብሎ ይጮሀል።አብርሃም ካላችሁ አይበቃም….እናን ምን አመጣው?” ይላል፡፡ ያውቃል ማንም ጋር እንደማልታይ፤
ሀኒ ጋር ነኝ ቤት ውስጥ የምትበላውን እየሰራሁላት፡፡ ሀኒ ጋር ነኝ መንገድ ላይ ቦርሳዋን ይዤላት፤….ዣንጥላዋን ይዤላት ዕቃ ከገዛን አስቤዛም ቢሆን እኔ ይዣላት ሀኒ ጋር ነኝ የትም!!
ሀኒን እህቴ አትወዳትም፡፡ ከዘመናዊ ጓደኞቿ ጋር ሆና ከሩቅ ካየችኝ በሬ እንዳሯሯጠው ሰው መንገድ አሳብራ የጓደኞቿን እጅ እየጎተተች ትሸሻለች፡፡ “ወንድሜ በሬ አገባ” እያለች ነው የምታወራው አሉ!
ወንድሜ ሀናን አይወዳትም፡፡
"ለስንት ስንጠብቅህ እዚሂች አዚፋ ጋር ትወዘፋለህ” ይለኛል፡
&አዚፋ' ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ግዴለም ሀኒዬ 'አዚፋ ከሆነች፣ አዚፉ ይባረክ ! ስድብ ሰውን ካረከሰው፡ ሰው ስድቡን ስለምን አያከብረውም? ሀኒዬ አዚፉን አከበረች… እወዳታለሁ፡፡
ሀኒ ቆንጆ አይደለችም፡፡ የኔ ቆንጆ፣ ቆንጆ አይደለችም፡፡ "ኪንኪ ፀጉሯ ጠዋት ስትነሳ ያስፈራል”
ይላሉ፣ አዎ እውነት ነው፡፡ “አፍንጫዋ በአይኗና ቀላይኛው ከንፈሯ መካከል ያለ ሁለት የሽንቁር ነጥብ ነው እያሉ ያሟታል…እውነት ነው !!
ከንፈሯ ወጣ ወጣ ባሉ ጥርሶቿ (ገጣጣ ነው እነሱ የሚሉት) ከርስቱ ተገፍቷል፡፡ በዛ ላይ
ብትስቅ ዞሮ ማጅራቷ ላይ ይዘያየራል ይላሉ፡፡ አዎ እውነት ነው !!
የጣቶቿ መዶልዶም ከዘጠኝ ዓመቷ እስከ አስራ ዘጠኝ ዓመቷ 10000000000000000000
ኩንታል ገብስ ሳታቋርጥ የወቀጠች ያስመስላታል" ቢሉም (ተጋነነ እንጂ) እውነት ነው !!
“እግሯ ከየትኛውም ጫማ እንዲጣላ ተደርጎ ነው የተፈጠረው” ያሉትም አልዋሹም፡፡
lዚህ ሁሉ መናቅ፣ በዚህ ሁሉ መገፋት ተገፍታ እኔ የምባል ጥግ ላይ ደረሰች የሀኒ ዓለም
መጨረሻ፡፡የት ትሂድላቸው? አለሁላት ወንድሟ ነኝ:: ፍቅረኛዋ ነኝ፡፡ባሏም ነኝ!! አላፍርባትም፡፡
ኮራባታለሁ !! ሀኒዬ የኔ ናት:: ማነው እኔን አልፎ የሚዘልፉት ወንድ ?' የኤሌክትሪክ አጥሯ
ጠባቂ ውሻዋ ነኝ፡፡ ከእግሯ ስር የማልጠፋ::ባለቤቱ ያላከበረው አሞሌ፡ ወላ መልኩ ወላ
ዘመናዊነቱ አያስከብረውም፡፡ አንዱ የወረወራቸው አይደሉ ሌላኛው መኪና ላይ የሚኮፈሱት!
የተናቁ አሞሌዎች !! ሀኒዬን አከብራታለሁ !! እግዜር ያውቃል ልቤን !!
“ጥርስሽ አያምርም ቢሏት ከሳቅ ተጣላችላቸው፡፡ ሰው ፊት አትስቅም ሀኒ፡፡ የመጻፍ መብታችን፣የመሰለፍ መብታችን ተነካ የሚሉ የአገሬ ልጆች፣ የህኒዩን የመሳቅ መብት በአደባባይ ነጠነቁ፡፡እስካሁን ሻይ ቡና ለማላት ካፍቴሪያ መግባት ያስፈራታል፡፡ ራሷ ቤት ውስጥ ስትቀመጥ እንኳን እግሮቿን ሶፋ ስር ልትደብቅ ይከጅላታል፡፡ በመንገድ ዳር ዘለፋ መሳቀቅን ሸልመዋታል፡፡ ሰው ለሰላምታ ስትጨብጥ ትሳቀቃለች፡፡ የመዳፏን ሻካራነት በየጭብጡ የሚጮኸ አዋጅ አድርገው
ልቧ ውስጥ ተክለውባት፡፡
ሆኒዩን ቆንጆ ካልሆንሽ ሰው ከመሆን መንበር ተንኮታኩተሻል” ብለዋታልና ቆንጆዎች አምላክ
ይመስሏታል፡፡ የሴት ልጅ የክብር ጥጉ በየሆቴሉ ወንበር ተጎትቶላት መቀመጧ ነውን ? በአደባባይ
መታቀፍስ የፍቅር ኦሜጋ ሆኖ የታወጀው መቼ ነው ? እየተውረገረጉ የወንድ ጭብጨባ
ያደነቆራቸው ሀኒዬን ቃል ሳያወጡ በድርጊት ቀበሯት፡፡
አነሆ ለአንዲት ደሀ.ለአንዲት መልከ ጥፉ ደሀ ተልኬ የምታስተናግድበት ተራ ሻይ ቤት ተከሰትኩ፡ ያውም 'አዩኝ' ብሎ የሚቆሽሽ ነጭ ሸሚዝ ባማረ ጂንስ ሱሪ ለብሼ፣ ጥቁር መነፅሬን ሰክቼ እየተቆነንኩ በረንዳው ላይ ካሉት ወንበሮች በአንዱ ላይ ሰፈርኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ!” አለች ሀኒዬ እየተሸቆጠቆጠች፡፡ ሳያት ላማትብ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ እግዜር ሰውን
የት ድረስ ውብ እንደሚያደርግ አውቃለሁ፡፡ የት ድረስ መልከ ጥፉ አድርጎ እንደሚፈጥር እነሆ
የእጁን ውጤት ፊቴ አቁሞ አሳየኝ፡፡ “አቤት ችሎታው ምን ይሳነዋል!” አልኩ ::
ስራዬ በዛው ግድም ነበርና ደጋግሜ ሳያት ከቀን ወደቀን እየባሰ የሚሄድ ይሄ ጎደለው የማይባል ፍፁም የሆነ አስቀያሚነት እንዳሸከማት እየተገረምኩ ታዘብኩ፡፡ ግና የገረመኝ፣ “አቤት ስታስጠላ
እያልኩ ላያት መፈለጌ ደንበኛ ሆንኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ?"
"ቡና"
"ምን ላምጣልህ?"
“ቡና”
“ሰላም! ምን ላምጣልህ?”
“ቡና”
“ቡና ነው ዛሬም” (ፈገግ ለማለት እየሞከረች)
"አዎ" (በፈገግታ)
ከዛ ሳላዛት ቡና አመጣችልኝ…ቡና..ቡና….ቡና.…ሰላምታ ሀና ነው ስሟ፣ አንድ ቀን ጠየቅኳት…
ነገረችኝ፡፡ ስራ ከሌላት አጠገቤ ትመጣለች እናወራለን…እንዴት ደስ እንደምትል፡፡ ትልልቅ ጡቶቿን አልፎ ልቧ ይታያል ንጹህ ነው !
አንድ ቀን ከጎኔ የተቀመጡ ተስተናጋጆች "የሰው ጅብ” ሲሏት ጆሮዬ ጥልቅ አለ ያዘዝነው ዘገየብን ብለው !! በመሰደቧ ሳይሆን እኔ ፊት በመሰደቧ
በመሰደቧ የቅስሟ መስተዋት
ክፍት አፍ በወረወረው የዘለፉ ጠጠር ሲንኮታኮት ፊቷ ላይ እንዴት አንጀት የሚበላ መሳቀቅ አየሁ፡፡ ተሳዳቢዎቹ ጋር
የነበረች አንዲት ሴትም ላንቃዋ እስኪላቀቅ ሳቀች፡፡ አዘንኩ፡፡ ለምን አዘንኩ እኔንጃ !!
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እናቴ ሁልጊዜ ሁለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ ትለዋለች፣
“አብርሽዬ የሚያገባትን ሴት ሳታሳየኝ እንዳትገለኝ፡፡
አገባሁ !
እናቴ እለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ አለችው፣
“ምነው ይሄንንስ ከሚያሳየኝ በገደለኝ
ሀና ምንተስኖት ትባላለች የምኮራባት ሚስቴ፡፡ እወዳታለሁ፣ አፈቅራታለሁ፡፡ ክፉ ነገር በሰፈሯ
እንዲያልፍ አልፈልግም፡፡ ሀኒዬ የእኔ ጥሩ ሱስ፣ ካላየኋት ያዛጋኛል' ስል ሰዎች አያምኑኝም፤ ሀኒ
የእኔ ልብ፣ የጠላችው ጠላቴ ነው:: ይሄ አባማ የሚባል ሰውዬ በቴሌቪዥን ያደረገው ንግግር
አስጠላኝ ብትለኝ፣ ሲ አይ ኤን ሳልፈራ፣ ኤፍ.ቢ.አይን ከቁብም ሳልቆጥረው ኦሳማ ላይ የግድያ
ሙከራ ባደርግ ደስታዬ ነው:: እንቅ አድርጌ አይኑን አፍጥጦ፣ “ኧረ አብርሽ በእናትህ የዛሬን
ማረኝ..ሁለተኛ በየትኛውም ሚዲያ ከመቅረቤ በፊት ንግግሬን ለሀና ምንተስኖት ኣሳውቃታለሁ..
ካልፈቀደችልኝ ኣላደርጎውም” ቢለኝ አልምረውም፡፡ እማምላክን አልምረውም !!
ሀናዬ የነብሴ ፍራሽ…ላያት ድሎቴ ናት። ሀና ካዘዘችኝ…አቤት ፍጥነቴ ገና ልትናገር ስትጀምር እኔ ሮጫለሁ፡፡ አልጋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዥን እያየች እኔ ቆንጆ ቡና እያፈላሁላት…የሆነ ነገር ብትፈልግል ልትናገር ስትጀምረው ነገሩን አምጥቼዋለሁ ፡፡ ለምን ትጨርሰዋለች.…ቃሏ ፍቅር
ነው..ፊደሎቾ እንደ ረሀብ ቀን እህል ያሳሱኛል፡፡
“አብርሽ " ስትለኝ በቦታህ!' እንዳሉት ሯጭ እዘጋጃለሁ፡፡ ወደ መሻቷ ተፈትልኮ በምድር
ላይ ያሉ ወንዶች ሁሉ የሚሰቶቻቸውን ፍላጎት ካሟሉበት ሰዓት የተሻለውን ለማስመዝገብ፡፡
"ድ." ብላ ስትጀምር ፈትለክ ብዬ ድስት…ድራፍት…ድንች ድልህ...ድፍድፍ (ከእማማ ፈጠኑ ቤት ድመት...ድንጋይ..ድራማ (ሲዲ) ይዤላት እያለከለኩ ከተፍ ስል፣ "ውይ አብርሽዬ…በቲቪ ድብ አይቼ ድቡን እየው ልልህ ነበር እኮ" ትለኛለች በፍቅር ዐይን እያየችኝ...!! አይከፋኝም ለምን እከፋለሁ፡፡ እንደገና ድብ ባየችና “ድ ብላ ስትጀምር፣ አሁን ባመጣኋቸው ነገሮች ላይ
ድብ ጨምሬ ባመጣሁላት..የእኔ ሀኒ መክሊት ብያታለሁ፡፡ እሷ ናት ቀኝም ግራም ጎኔ፡፡
ሀኒዬን እናቴ አትወዳትም፡፡ “አንዳች አስነክታው ነው ልጄን እቺ የሰው ጉድ” ትላታለች፡፡
አባቴ ገና ሲያያት የእናቱ፣ የአባቱ፣ የሁለት እህቶቹ ገዳይ ነው የምትመስለው አቤት ሲጠላት፡፡ በወሬ ወሬ “መንገድ ላይ አብረሃም እና... ሲሉት፣ "በቃ " ብሎ ይጮሀል።አብርሃም ካላችሁ አይበቃም….እናን ምን አመጣው?” ይላል፡፡ ያውቃል ማንም ጋር እንደማልታይ፤
ሀኒ ጋር ነኝ ቤት ውስጥ የምትበላውን እየሰራሁላት፡፡ ሀኒ ጋር ነኝ መንገድ ላይ ቦርሳዋን ይዤላት፤….ዣንጥላዋን ይዤላት ዕቃ ከገዛን አስቤዛም ቢሆን እኔ ይዣላት ሀኒ ጋር ነኝ የትም!!
ሀኒን እህቴ አትወዳትም፡፡ ከዘመናዊ ጓደኞቿ ጋር ሆና ከሩቅ ካየችኝ በሬ እንዳሯሯጠው ሰው መንገድ አሳብራ የጓደኞቿን እጅ እየጎተተች ትሸሻለች፡፡ “ወንድሜ በሬ አገባ” እያለች ነው የምታወራው አሉ!
ወንድሜ ሀናን አይወዳትም፡፡
"ለስንት ስንጠብቅህ እዚሂች አዚፋ ጋር ትወዘፋለህ” ይለኛል፡
&አዚፋ' ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ግዴለም ሀኒዬ 'አዚፋ ከሆነች፣ አዚፉ ይባረክ ! ስድብ ሰውን ካረከሰው፡ ሰው ስድቡን ስለምን አያከብረውም? ሀኒዬ አዚፉን አከበረች… እወዳታለሁ፡፡
ሀኒ ቆንጆ አይደለችም፡፡ የኔ ቆንጆ፣ ቆንጆ አይደለችም፡፡ "ኪንኪ ፀጉሯ ጠዋት ስትነሳ ያስፈራል”
ይላሉ፣ አዎ እውነት ነው፡፡ “አፍንጫዋ በአይኗና ቀላይኛው ከንፈሯ መካከል ያለ ሁለት የሽንቁር ነጥብ ነው እያሉ ያሟታል…እውነት ነው !!
ከንፈሯ ወጣ ወጣ ባሉ ጥርሶቿ (ገጣጣ ነው እነሱ የሚሉት) ከርስቱ ተገፍቷል፡፡ በዛ ላይ
ብትስቅ ዞሮ ማጅራቷ ላይ ይዘያየራል ይላሉ፡፡ አዎ እውነት ነው !!
የጣቶቿ መዶልዶም ከዘጠኝ ዓመቷ እስከ አስራ ዘጠኝ ዓመቷ 10000000000000000000
ኩንታል ገብስ ሳታቋርጥ የወቀጠች ያስመስላታል" ቢሉም (ተጋነነ እንጂ) እውነት ነው !!
“እግሯ ከየትኛውም ጫማ እንዲጣላ ተደርጎ ነው የተፈጠረው” ያሉትም አልዋሹም፡፡
lዚህ ሁሉ መናቅ፣ በዚህ ሁሉ መገፋት ተገፍታ እኔ የምባል ጥግ ላይ ደረሰች የሀኒ ዓለም
መጨረሻ፡፡የት ትሂድላቸው? አለሁላት ወንድሟ ነኝ:: ፍቅረኛዋ ነኝ፡፡ባሏም ነኝ!! አላፍርባትም፡፡
ኮራባታለሁ !! ሀኒዬ የኔ ናት:: ማነው እኔን አልፎ የሚዘልፉት ወንድ ?' የኤሌክትሪክ አጥሯ
ጠባቂ ውሻዋ ነኝ፡፡ ከእግሯ ስር የማልጠፋ::ባለቤቱ ያላከበረው አሞሌ፡ ወላ መልኩ ወላ
ዘመናዊነቱ አያስከብረውም፡፡ አንዱ የወረወራቸው አይደሉ ሌላኛው መኪና ላይ የሚኮፈሱት!
የተናቁ አሞሌዎች !! ሀኒዬን አከብራታለሁ !! እግዜር ያውቃል ልቤን !!
“ጥርስሽ አያምርም ቢሏት ከሳቅ ተጣላችላቸው፡፡ ሰው ፊት አትስቅም ሀኒ፡፡ የመጻፍ መብታችን፣የመሰለፍ መብታችን ተነካ የሚሉ የአገሬ ልጆች፣ የህኒዩን የመሳቅ መብት በአደባባይ ነጠነቁ፡፡እስካሁን ሻይ ቡና ለማላት ካፍቴሪያ መግባት ያስፈራታል፡፡ ራሷ ቤት ውስጥ ስትቀመጥ እንኳን እግሮቿን ሶፋ ስር ልትደብቅ ይከጅላታል፡፡ በመንገድ ዳር ዘለፋ መሳቀቅን ሸልመዋታል፡፡ ሰው ለሰላምታ ስትጨብጥ ትሳቀቃለች፡፡ የመዳፏን ሻካራነት በየጭብጡ የሚጮኸ አዋጅ አድርገው
ልቧ ውስጥ ተክለውባት፡፡
ሆኒዩን ቆንጆ ካልሆንሽ ሰው ከመሆን መንበር ተንኮታኩተሻል” ብለዋታልና ቆንጆዎች አምላክ
ይመስሏታል፡፡ የሴት ልጅ የክብር ጥጉ በየሆቴሉ ወንበር ተጎትቶላት መቀመጧ ነውን ? በአደባባይ
መታቀፍስ የፍቅር ኦሜጋ ሆኖ የታወጀው መቼ ነው ? እየተውረገረጉ የወንድ ጭብጨባ
ያደነቆራቸው ሀኒዬን ቃል ሳያወጡ በድርጊት ቀበሯት፡፡
አነሆ ለአንዲት ደሀ.ለአንዲት መልከ ጥፉ ደሀ ተልኬ የምታስተናግድበት ተራ ሻይ ቤት ተከሰትኩ፡ ያውም 'አዩኝ' ብሎ የሚቆሽሽ ነጭ ሸሚዝ ባማረ ጂንስ ሱሪ ለብሼ፣ ጥቁር መነፅሬን ሰክቼ እየተቆነንኩ በረንዳው ላይ ካሉት ወንበሮች በአንዱ ላይ ሰፈርኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ!” አለች ሀኒዬ እየተሸቆጠቆጠች፡፡ ሳያት ላማትብ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ እግዜር ሰውን
የት ድረስ ውብ እንደሚያደርግ አውቃለሁ፡፡ የት ድረስ መልከ ጥፉ አድርጎ እንደሚፈጥር እነሆ
የእጁን ውጤት ፊቴ አቁሞ አሳየኝ፡፡ “አቤት ችሎታው ምን ይሳነዋል!” አልኩ ::
ስራዬ በዛው ግድም ነበርና ደጋግሜ ሳያት ከቀን ወደቀን እየባሰ የሚሄድ ይሄ ጎደለው የማይባል ፍፁም የሆነ አስቀያሚነት እንዳሸከማት እየተገረምኩ ታዘብኩ፡፡ ግና የገረመኝ፣ “አቤት ስታስጠላ
እያልኩ ላያት መፈለጌ ደንበኛ ሆንኩ፡፡
“ምን ልታዘዝ?"
"ቡና"
"ምን ላምጣልህ?"
“ቡና”
“ሰላም! ምን ላምጣልህ?”
“ቡና”
“ቡና ነው ዛሬም” (ፈገግ ለማለት እየሞከረች)
"አዎ" (በፈገግታ)
ከዛ ሳላዛት ቡና አመጣችልኝ…ቡና..ቡና….ቡና.…ሰላምታ ሀና ነው ስሟ፣ አንድ ቀን ጠየቅኳት…
ነገረችኝ፡፡ ስራ ከሌላት አጠገቤ ትመጣለች እናወራለን…እንዴት ደስ እንደምትል፡፡ ትልልቅ ጡቶቿን አልፎ ልቧ ይታያል ንጹህ ነው !
አንድ ቀን ከጎኔ የተቀመጡ ተስተናጋጆች "የሰው ጅብ” ሲሏት ጆሮዬ ጥልቅ አለ ያዘዝነው ዘገየብን ብለው !! በመሰደቧ ሳይሆን እኔ ፊት በመሰደቧ
በመሰደቧ የቅስሟ መስተዋት
ክፍት አፍ በወረወረው የዘለፉ ጠጠር ሲንኮታኮት ፊቷ ላይ እንዴት አንጀት የሚበላ መሳቀቅ አየሁ፡፡ ተሳዳቢዎቹ ጋር
የነበረች አንዲት ሴትም ላንቃዋ እስኪላቀቅ ሳቀች፡፡ አዘንኩ፡፡ ለምን አዘንኩ እኔንጃ !!
👍30😁4
የውበት ጥርሳቸውን ስለው ወንዱን ሊከረትፉት ከተማውን በቀን የወረሩት ሴቶች ያውም የጉም ጅቦት ላይ አፋቸውን ለአድናቆት ሲበረግዱ የሚውሉ ዘመናዊ ተብዬ ቅርፊት የከተማ ወንዶች፣አንዲት ደሀ ሚስኪን “የሰው ጅብ!” ብለው ተሳሳቁ፡፡ሰርታ በኖረች በጅብ አፋቸው ጅብ አሏት፡፡
በቀጣዩ ቀን አንገቷን ደፍታ፣ ምን ልታዘዝ?” አለችኝ በመከራ አንገቷን ብቅ ካደረገችበት
ግንኙነት በዘለፋ ኩርኩም ወደ ትንሽነት መልሰዋት ከ ሀ እስጀመሯት፡፡
"ስልክ እለሽ? አልኳት፣
"ቡና” የምል መስሏት ልትመለስ ካለች በኋላ ያልኩትን ባለማመን፣
"እ" አለችኝ
"ስልክ ቁጥርሽን ስጭኝ!"
“የድርጅቱኝ ነው?” ስትል ጠየቀችኝ፤
"ያችን የራስሽን!"
ዝም አለች:: ቆይታ…ቆይታ
"ዐ9…" አለች
"09 አልኳት ስልኬ ላይ እየፃፍኩ
"እ 09…" ፈራች፡፡ ማመን ከበዳት ፤ የኔ ሚስኪን! ጀግናው ወገኗ፣ ዘላፊ ወገኗ፣ ሃይማኖተኛ
ህዝቧ የገደላት…ሙት መቃብሯን ለመፈንቀል ሁሉም በየአፉ የወረወረባትን ድንጋይ፣ በአሽሙር
አካፋው በለበጣ መጋፊያው የመለሰባትን የቀብር አፈር መፈንቀል ከበዳት፡፡
“በዚህ ምልክት አድርጊልኝ እጠብቅሻለሁ' ብዬ ቁጥሬን ያመጣችው ደረሰኝ ላይ ፅፌ ሰጠኋት…
የሴት ክብር መሳም ነው ? መታቀፍ ነው ? ተስመው የተወረወሩ፣ ታቅፈው የተሸቀነጠሩ
ይናገሩ፣ ሴት ልጅ ያመነችው ወንድ፣ ጣላት፣ ተዋት! ከሚል አሽሙር ሲታደጋት፣ ያኔ ነው
ክብር ቦታዋ ላይ የምትቀመጠው: ሴት ልጅ ስታፈቅር እድሜዋን ነው ሸርፋ የምትሰጠው::
ሸራርፈው ሸራርፈው ሴቶቹን ከእድሜያቸውም ከውበታቸውም አጤልተው ገሸሽ ያሉ ወንዶች
ይስሙ! እኔ ሽቅርቅሩ ሀናን ወደድኳት፣ ወረተኛ አይደለሁም፡፡ ምንም ቢመጣ አልተዋትም፡፡
አዝኜ አይደለም፡፡ ሰማኋት፣ አይኔን ሳልወድ በግድ አስጨፈነችኝ፡፡
መንገድ ላይ ሀኒዬን በኩራት ሳቅፋት፣ የሚታቀፍ ጠፍቶ ይላሉ ሊታቀፉ ከየቤታቸው የወጡ እቅፍ ናፋቂዎች ሁሉ
ስስማት የሚያቅለሸልሻቸው አይናቸውን አዞሩ፡፡ ሀኒዩን አበድኩላት " ሆና ሴት ናት !! እግዜር
“ሴትነትን መደበቂያ ቢያጣ ባልረባ ስጋ ጠቅልሎ ያኖረባት የክብር መዝገብ፡፡ ወንዶች እግር
ላይ ሴትነትን ሲፈልጉ፡፡ ያማረ አፍንጫና ጥርስ ላይ ሴትነትን ሊያጠምዱ መንጠቆ ሲወረውሩ
እግዜር እንቁውን የት እንዳስቀመጠው ተመልከቱ፡፡
አገባታለሁ ሀናን “አገባታለሁ ያልኩ ቀን ሙሾ ባይነት ባይነት ወረደ፡፡ ሀና ራሷ ደነገጠች፡፡ከዛ በፊት እንዲሁ ከምቀር ፍቅር የሚባለውን ነገር ልሞከረው ቢያንስ ከትዝታው ጋር እኖራለው ብላ እንጂ፡ ያገባኛል ብላ በምን ጠርጥራ(በኋላ እንደነገረችኝ)፡፡
ተወራ በመንደሩ፣ አብርሀም ቡጡቃ ሻይ ቤት ያለችውን “ሆረር ሊያገባ ነው"
“እትቀልድ ባክ"
“ማርያምን?"
“ክርስቶስ ምስከሬ"
“ወላሂ”
“አበደ እንዴ?”መካሪ የለውም?
ተቀባበሉ ወሬውን
ለከብሩ…ለወጉ ለመዓረጉ፡ “ሀኒን ላገባት ነው ! ዳሩኝ!” አልኩ ቤተሰቦቼን፣
“አያገባም !!” አሉ፡፡
የራሳችሁ ጉዳይ! ብያቸው ከሀኒ ጋር አብረን መኖር ጀመርን፡፡ ወላ ቤተሰብ፣ ወላ ጓደኛ ድራሹ ጠፋ፡፡ ሀኒዬን ወደድኳት፡፡ ከዚህ ሁሉ አሰቃቂ መልከ ጥፉነት መሀል የተረፉት ጡቶቿ መስውሰውኝ በስሜት እንዳይሆን የወደድኳት ብዬ ጀማው ሲንጫጫ ፈራሁ…ኧረ ሀቂቃው ፍቅር ነው !!
አራት ዓመት አሳት በሆነ ፍቅር ኖሮን፣ ባሰብኝ ወደድኳት፡፡ ይሄው እርጉዝ ናት፤ ያውም የስምንት ወር፡፡ ሀኒ እኔ ጋር ትስቃለች፡፡ እኔ ጋር እግሯን አትደብቅም፡፡ በነበረው ግዝፈት ላይ እርግዝናና ያሳበጠው አስቀያሚ እግሯን ጉልበቴ ላይ አስቀምጬ ሳሽላት እንዴት ደስ እንደሚለኝ..
"አብርሽዬ"
"ያ እላታለሁ"
"እንትን ፈልጌ ነበር"
"ምን.." በቦታህ አብርሽ! ተዘጋጅ!
"ሰ" ሂድ ዲዲዲዲዲዲ ስጋ ስዕል (ከሰዓሊ ጓደኛዬ).ስስ ፒጃማ ስንግ ስራስር ነገር(ድንች፣
ቀይ ስር፣ ካሮት) ስእለት (ለማሪያም ሀኒ በሰላም ትገላገል ብዬ) እያለከለኩ ስመለስ፣ ውይ
አብርሽዬ……ስልኬን አቀብለኝ ለማለት ነበርኮ፧ ሮጥክብኝ…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…እኔ ፊት ስትስቅ
አትሳቀቅም ሀኒዬ !!
✨አለቀ✨
በቀጣዩ ቀን አንገቷን ደፍታ፣ ምን ልታዘዝ?” አለችኝ በመከራ አንገቷን ብቅ ካደረገችበት
ግንኙነት በዘለፋ ኩርኩም ወደ ትንሽነት መልሰዋት ከ ሀ እስጀመሯት፡፡
"ስልክ እለሽ? አልኳት፣
"ቡና” የምል መስሏት ልትመለስ ካለች በኋላ ያልኩትን ባለማመን፣
"እ" አለችኝ
"ስልክ ቁጥርሽን ስጭኝ!"
“የድርጅቱኝ ነው?” ስትል ጠየቀችኝ፤
"ያችን የራስሽን!"
ዝም አለች:: ቆይታ…ቆይታ
"ዐ9…" አለች
"09 አልኳት ስልኬ ላይ እየፃፍኩ
"እ 09…" ፈራች፡፡ ማመን ከበዳት ፤ የኔ ሚስኪን! ጀግናው ወገኗ፣ ዘላፊ ወገኗ፣ ሃይማኖተኛ
ህዝቧ የገደላት…ሙት መቃብሯን ለመፈንቀል ሁሉም በየአፉ የወረወረባትን ድንጋይ፣ በአሽሙር
አካፋው በለበጣ መጋፊያው የመለሰባትን የቀብር አፈር መፈንቀል ከበዳት፡፡
“በዚህ ምልክት አድርጊልኝ እጠብቅሻለሁ' ብዬ ቁጥሬን ያመጣችው ደረሰኝ ላይ ፅፌ ሰጠኋት…
የሴት ክብር መሳም ነው ? መታቀፍ ነው ? ተስመው የተወረወሩ፣ ታቅፈው የተሸቀነጠሩ
ይናገሩ፣ ሴት ልጅ ያመነችው ወንድ፣ ጣላት፣ ተዋት! ከሚል አሽሙር ሲታደጋት፣ ያኔ ነው
ክብር ቦታዋ ላይ የምትቀመጠው: ሴት ልጅ ስታፈቅር እድሜዋን ነው ሸርፋ የምትሰጠው::
ሸራርፈው ሸራርፈው ሴቶቹን ከእድሜያቸውም ከውበታቸውም አጤልተው ገሸሽ ያሉ ወንዶች
ይስሙ! እኔ ሽቅርቅሩ ሀናን ወደድኳት፣ ወረተኛ አይደለሁም፡፡ ምንም ቢመጣ አልተዋትም፡፡
አዝኜ አይደለም፡፡ ሰማኋት፣ አይኔን ሳልወድ በግድ አስጨፈነችኝ፡፡
መንገድ ላይ ሀኒዬን በኩራት ሳቅፋት፣ የሚታቀፍ ጠፍቶ ይላሉ ሊታቀፉ ከየቤታቸው የወጡ እቅፍ ናፋቂዎች ሁሉ
ስስማት የሚያቅለሸልሻቸው አይናቸውን አዞሩ፡፡ ሀኒዩን አበድኩላት " ሆና ሴት ናት !! እግዜር
“ሴትነትን መደበቂያ ቢያጣ ባልረባ ስጋ ጠቅልሎ ያኖረባት የክብር መዝገብ፡፡ ወንዶች እግር
ላይ ሴትነትን ሲፈልጉ፡፡ ያማረ አፍንጫና ጥርስ ላይ ሴትነትን ሊያጠምዱ መንጠቆ ሲወረውሩ
እግዜር እንቁውን የት እንዳስቀመጠው ተመልከቱ፡፡
አገባታለሁ ሀናን “አገባታለሁ ያልኩ ቀን ሙሾ ባይነት ባይነት ወረደ፡፡ ሀና ራሷ ደነገጠች፡፡ከዛ በፊት እንዲሁ ከምቀር ፍቅር የሚባለውን ነገር ልሞከረው ቢያንስ ከትዝታው ጋር እኖራለው ብላ እንጂ፡ ያገባኛል ብላ በምን ጠርጥራ(በኋላ እንደነገረችኝ)፡፡
ተወራ በመንደሩ፣ አብርሀም ቡጡቃ ሻይ ቤት ያለችውን “ሆረር ሊያገባ ነው"
“እትቀልድ ባክ"
“ማርያምን?"
“ክርስቶስ ምስከሬ"
“ወላሂ”
“አበደ እንዴ?”መካሪ የለውም?
ተቀባበሉ ወሬውን
ለከብሩ…ለወጉ ለመዓረጉ፡ “ሀኒን ላገባት ነው ! ዳሩኝ!” አልኩ ቤተሰቦቼን፣
“አያገባም !!” አሉ፡፡
የራሳችሁ ጉዳይ! ብያቸው ከሀኒ ጋር አብረን መኖር ጀመርን፡፡ ወላ ቤተሰብ፣ ወላ ጓደኛ ድራሹ ጠፋ፡፡ ሀኒዬን ወደድኳት፡፡ ከዚህ ሁሉ አሰቃቂ መልከ ጥፉነት መሀል የተረፉት ጡቶቿ መስውሰውኝ በስሜት እንዳይሆን የወደድኳት ብዬ ጀማው ሲንጫጫ ፈራሁ…ኧረ ሀቂቃው ፍቅር ነው !!
አራት ዓመት አሳት በሆነ ፍቅር ኖሮን፣ ባሰብኝ ወደድኳት፡፡ ይሄው እርጉዝ ናት፤ ያውም የስምንት ወር፡፡ ሀኒ እኔ ጋር ትስቃለች፡፡ እኔ ጋር እግሯን አትደብቅም፡፡ በነበረው ግዝፈት ላይ እርግዝናና ያሳበጠው አስቀያሚ እግሯን ጉልበቴ ላይ አስቀምጬ ሳሽላት እንዴት ደስ እንደሚለኝ..
"አብርሽዬ"
"ያ እላታለሁ"
"እንትን ፈልጌ ነበር"
"ምን.." በቦታህ አብርሽ! ተዘጋጅ!
"ሰ" ሂድ ዲዲዲዲዲዲ ስጋ ስዕል (ከሰዓሊ ጓደኛዬ).ስስ ፒጃማ ስንግ ስራስር ነገር(ድንች፣
ቀይ ስር፣ ካሮት) ስእለት (ለማሪያም ሀኒ በሰላም ትገላገል ብዬ) እያለከለኩ ስመለስ፣ ውይ
አብርሽዬ……ስልኬን አቀብለኝ ለማለት ነበርኮ፧ ሮጥክብኝ…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…እኔ ፊት ስትስቅ
አትሳቀቅም ሀኒዬ !!
✨አለቀ✨
👍47👏18❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ማሪየስ ፤ ሰማህ? አንተ ብሎ ባሮን እነዚያ ሽፍቶች ፤ ቀማኞች ፧ አታላዮች ፤ አታላዮች ፤ አታላዮች እውነተኛውን ንጉስ
ከድተው ቦናገርቴን የተከተሉ ፈሪዎች ፧ የፈሪ ፈሪዎች ናቸው:: ዋተርሉ ላይ ጠላቶችን ፈርተው የሸሹ ወርቦለች! ይኽ ነው እኔ የማውቀው::አባትህ ከነዚህ ዉስጥ ከሆነ አዝናለሁ አላውቀውም ብል ይሻላል
መሴይ ጊልኖርማንድ በቃላት ወናፍ ሲያራግቡት ማሪየስ በተራው ጨሰ፣ ተናደደ ፤ ቁጣው ገነፈለ፡፡ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡ የሚያደርገውን አጣ፤ የሚናገረውም ጠፋው፡፡ የአባቱ ስም ከፊቱ ተረገጠ፤ ተናቀ፡፡ በማን
በአያቱ፡፡ ታዲያ እንዴት ይበቀል? አያቱን መልሶ እንዳይሰድብ ያስነውራል::ዝም እንዳይልም አሳቡ ዘገነነው፡፡ በአንድ በኩል የአባቱ መቃብር በሌላ በኩል የአያቱ ሽበት ታየው፡፡ ነገሩ ሁሉ ስለተምታታበት ፈዝዞ ቀረ ።
ጥቂት ቆይቶ ቀና በማለት አያቱን አፍጥጦ አያቸው::
«በርበኖችና ትልቁ አሳማ ልዊ 18ኛ ይውደሙ» ሲል በታላቅ ቁጣና ጩኸት ተናገረ::
ንጉሡ ልዊ 18ኛ ከሞቱ አራት ዓመት አልፎአል:: ግን ለማሪየስ
ለውጥ አላመጣም::
ሽማግሌው በድንገት ፊታቸው በንዴት ብዛት ከፀጉራቸው ጀምሮ
ጠቆረ፡፡ ከዚያም ቃል ሳይናገሩ አንዴ ወደ መስኮት፧ አንዴ ወደ በሩ
በዝግታ ተራመዱ፡፡ ቀጥሉም እንዳረጀ በግ ድምብርብራቸው ወደ ወጣው ሴት ልጃቸው ዞር ብለው ፈገግ በማለት የሚቀጥለውን ተናገሩ፡:
«እንደ መሴይ ያለ ባሮን እንደ እኔ ያለ ቡርጓዥዋ ከአንድ ጣራ ስር
ለማኖር ያዳግታል፡፡» ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠና ቁጣቸው እንደነበልባል ከፊታቸው
ላይ እየሰራ ቀጥ ብለው ቆሙ:: እጃቸውን ወደ ማሪየስ ዘርግተው «ከዚህ ቤት ውጣልኝ» ሲሉ ጮሁ:: ማሪየስ ከቤቱ ወጣ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ለሴት ልጃቸው ሲናገሩ «ለዚህ ደም መጣጭ
በየስድስት ወር ስልሣ ፒስትልስ ትልኪለታለሽ፤ ለእኔ ግን ሁለተኛ ምንም ነገር እንዳታነሺ» ሲሉ አዘዙ፡፡
ነገሩ በጣም ስላሳዘናቸውና ስላናደዳቸው በሚቀጥሉት ሦስት ወራት የሚይዙትንና የሚጨብጡትን አሳጣቸው:: ሴት ልጃቸውን ሲያነጋግሩ እንኳን እጅግ ቀዝቀዝ ብለው ነበር፡፡
ማሪየስ ከቤቱ የወጣው ወደዚያ ቦታ ነው የምሄደው ሳይል ነበር
እነርሱም የት እንደሚሄድ አልጠየቁትም:: ጋሪ ተከራይቶ ዘልሉ ከገባ በኋሳ ጋሪው ወደ መራው ሄደ፡፡
ማሪየስ ምን ሊያደርግ ነው?
የእህቤሴ ጓደኞች
ማሪየስ ከቤቱ በወጣበት ጊዜ የለውጥ አየር ይነፍስ ነበር፡፡ ሰው ሁሉ ሳይታወቀው ንቅናቄ ውስጥ እየገባ አብዮተኛ ሆኖኣል፡፡ እያንዳንዱ ግለሰብ አንድ እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡ ንጉሣውያን ቤተሰብ እንኳን ሳይቀሩ በነገሩ ገቡ።ሰዎች ከጊዜ በኋላ ናፖሊዮንንና ነፃነትን እንደ አምላክ የማምለክ ስሜት አደረባቸው:: ሌሎች ደግሞ ዓለም ፍጹም እንድትሆን ተመኙ::
የዛሬው ምኞት ነገ ሥጋና ደም ለብሶ እሙን እንደሚሆን አመኑ፡፡
የአህቤሴ ጓደኞች እነማን ናቸው? አህቤሴ የተረገጡ፤ የተከፉና
የተረሱ ጭቁኖች ሲሆኑ እነዚህ ሰዎች በፖለቲካው እንቅስቃሴ ሳቢያ ብዙ ወዳጆች ያፈሩ ናቸው:: ጓደኞቻቸወም ከወደቁበት እንዲነሱ ከልብ ተመኙ:: ሰዎቹ ብዙ አልነበሩም:: ፓሪስ ከተማ ውስጥ ሃሌስና ኮርኒት ከተባሉ ሥፍራዎች በየጊዜው ከአንዲት አነስተኛ ቡና ቤት ውስጥ
ይሰበሰባሉ: ሥፍራው ወዛደሮች የሚኖሩበት አካባቢ ነው:: በዚያ አካባቢ ተማሪዎችም በብዛት ይገኛሉ፡፡ የአህቤሴ ጓደኞች የሚሰበሰቡበት ቡና ቤት
«ካፌ ሙሴን» ይባላል፡፡ ቡና ቤቱ ሰፊ ጓዳ ስለነበረው የአህቤቴ ጓደኞች ከዚያ ክፍል ውስጥ ይሰበሰባሉ:: ክፍሉ ከዋናው መጠጫ ክፍል ትንሽ ራቅ
ያለ ነበር፡፡ በጓሮ በኩል ወደ ውጭ የሚያስወጣ በር አለው::
ጓደኛሞቹ ከዚያች ክፍል ውስጥ ይጠጣሉ፤ ሲጃራ ያጨሳሉ:፧
ይጫወታሉ፤ የፖለቲካ ወሬ ያወራሉ:: የማያነሱት ነጥብ የለም፡ከክፍለ ግድግዳ ላይ የበፊቱን የፈረንሳይ ሪፑብሊክ ካርታ ሰቅለዋል።
የዚህ ቡድን አባሎች አብዛኞቹ ተማሪዎች ሲሆኑ ጥቂት ወዛደሮችም ነበሩበት፡፡ ጥቂት ቀንደኛ መሪዎች አሉዋቸው:: ከመሪዎቹ መካከል ኔንጀልራስ የተባለው የሀብታም ልጅ ቀንደኛ መሪ ሲሆን ደስ የሚልና
መልከ መልካም ወጣት ነው:: ደግሞም በጣም አዋቂ ከመሆኑም በላይ ወኔው ለጉድ ነው:: ከቀንደኛው መሪ ከኢንጆልራስ ጎን የተሰለፉ ሌሎችም ረዳት መሪዎች አሉ::
አንዳንዶቹ በፖለቲካው ሌሎቹ ደግሞ በሰው ልጅ ፍቅር የሰከሩ ናቸው:: አንዳንዶቹ ‹‹ጭቁኖችን ነፃ እናወጣለን ብለው የተነሱ ሲሆኑ ሌሎች ደግሞ «አገራችን ውስጥ አድልዎ የተለየው ትክክለኛ ፍርድ እንዲሰፍን ጽኑ እምነታችን ነው» የሚሉ ናቸው::
ሆኖም በመካከላቸው አንድ ተጠራጣሪ ሰው ነበር፡፡ ታዲያ የሕዝቦችና የግለሰብ መብት፧ የፈረንሳይ አብዮት ፧ ሪፑብሊክ ፧ ዲሞክራሲ ፧ ለሰው ሥልጣኔ፤ ሃይማኖት፧ መሻሻልና የመሳሰሉት ቃላት ለእርሱ ትርጉም የላቸውም:: እነዚህን ቃላት በሰማ ቁጥር ይስቃል:: ታዲያ ከነዚህ የተለየ ዓላማ ካላቸው ሰዎች መካከል ይህ ሰው እንዴት ሊደባለቅ ቻለ?
ይህ ሰው ተጠራጣሪ ቢሆንም የራሰ እምነት ነበረው:: እምነቱ
በኢንጂልራስ ላይ ነው:: ኢንጂልራስን ይወደዋል፣ ያደንቀዋል፣ ያምንበታል::
ለዚህ ነው በዓላማ አንድ ከነበሩና እንደ ቤተሰብ ከሚተያዩ ሰዎች መካከል ሊገባ የቻለው:: ኢንጆልራስ ይህን ተጠራጣሪ በፍልስፍና ወይም በነበረው
የተለየ አሳብ ሳይሆን በጠባዩ ነው የገዛው፡፡
አንድ ቀን ከሰዓት በኋላ፤ ሕይወት በአጋጣሚ የተሞላች ናትና፧
አንድ ነገር በአጋጣሚ ይሆናል፡፡ ከፈረንሳይ አብዮት ጠንሳሾች መካከል አንዱ ከካፌ ሙሴን በራፍ ግድግዳ ተደግፎ ቆሞአል:: እርሱ ከዚያ እንደቆመ ጋሪ በዚያ በኩል ያልፋል፡፡ ይህ ሌግል የተባለ ወጣት ጋሪውን ሲመለከተው
በጣም ዝግ ብሎ ስለሚሄድ አንድ ነገር እንደሚፈልግ ጠረጠረ:: አነስተኛ ሻንጣ የያዘ ሰው ጋሪው ላይ ከነጂው ጎን ቁጭ ብሎአል፡፡ ሻንጣው ላይ ማሪየስ ፓንትመርሲ የሚል ጽሑፍ በጉልህ ተጽፎበት ስለነበር ሌግል ጽሑፉን ያነባል::
ማሪየስ ፓንትመርሲ የሚለው ስም በጣም ማረከው:: ጋሪው ከአጠገቡ ሲደርስ «መሴይ ማሪየስ ፓንትመርሲ» ሲል ተጣራ:: ጋሪው ቆመ:: ጋሪው
ላይ የነበረውና በአሳብ መጥቆ ሄዶ የነበረው ወጣት ቀና አለ፡፡
«ምን ነበር?» ሲል ጠየቀ፡፡
«መሴይ ማሪየስ ፓንትመርሲ ማለት አንተ ነህ?»
«ነኝ፡፡»
«ስፈልግህ ነበር፡፡»
«እንዴት ሊሆን ይችላል? አታውቀኝ፤ አላውቅህ» ሲል ማሪየስ ጠየቀው
«ትናንት ትምህርት ቤት አልመጣህም፡፡»
«ላልመጣ እችላለሁ::»
««በርግጥ አልመጣህም::
‹‹ተማሪ ነህ አንተም?»
«አዎን፧ እንዳንተው ተማሪ ነኝ:: ከትናንት ወዲያ ልክ ወደ ክፍል
ልገባ ስል፧ አለ አይደል አንዳንዴ አስተማሪዎች ሦስት ጊዜ ስምህን ሲጠሩ አቤት ካላልክ ይሠርዙሃል፡፡ ስልሣ ፍራንክ ቀለጠች ማለት ነው::»
ማሪየስ ዝም ብሎ ይሰማል:: ሌግል ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«ብሎንዳው የሚባለው አስተማሪ ነበር ስም የሚጠራው፡፡ አስተማሪውን ታውቀዋለህ አይደል? ያ እንኳን ቀፋፊና ግትር አፍንጫ ያለው! የቀረ ተማሪ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ማሪየስ ፤ ሰማህ? አንተ ብሎ ባሮን እነዚያ ሽፍቶች ፤ ቀማኞች ፧ አታላዮች ፤ አታላዮች ፤ አታላዮች እውነተኛውን ንጉስ
ከድተው ቦናገርቴን የተከተሉ ፈሪዎች ፧ የፈሪ ፈሪዎች ናቸው:: ዋተርሉ ላይ ጠላቶችን ፈርተው የሸሹ ወርቦለች! ይኽ ነው እኔ የማውቀው::አባትህ ከነዚህ ዉስጥ ከሆነ አዝናለሁ አላውቀውም ብል ይሻላል
መሴይ ጊልኖርማንድ በቃላት ወናፍ ሲያራግቡት ማሪየስ በተራው ጨሰ፣ ተናደደ ፤ ቁጣው ገነፈለ፡፡ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡ የሚያደርገውን አጣ፤ የሚናገረውም ጠፋው፡፡ የአባቱ ስም ከፊቱ ተረገጠ፤ ተናቀ፡፡ በማን
በአያቱ፡፡ ታዲያ እንዴት ይበቀል? አያቱን መልሶ እንዳይሰድብ ያስነውራል::ዝም እንዳይልም አሳቡ ዘገነነው፡፡ በአንድ በኩል የአባቱ መቃብር በሌላ በኩል የአያቱ ሽበት ታየው፡፡ ነገሩ ሁሉ ስለተምታታበት ፈዝዞ ቀረ ።
ጥቂት ቆይቶ ቀና በማለት አያቱን አፍጥጦ አያቸው::
«በርበኖችና ትልቁ አሳማ ልዊ 18ኛ ይውደሙ» ሲል በታላቅ ቁጣና ጩኸት ተናገረ::
ንጉሡ ልዊ 18ኛ ከሞቱ አራት ዓመት አልፎአል:: ግን ለማሪየስ
ለውጥ አላመጣም::
ሽማግሌው በድንገት ፊታቸው በንዴት ብዛት ከፀጉራቸው ጀምሮ
ጠቆረ፡፡ ከዚያም ቃል ሳይናገሩ አንዴ ወደ መስኮት፧ አንዴ ወደ በሩ
በዝግታ ተራመዱ፡፡ ቀጥሉም እንዳረጀ በግ ድምብርብራቸው ወደ ወጣው ሴት ልጃቸው ዞር ብለው ፈገግ በማለት የሚቀጥለውን ተናገሩ፡:
«እንደ መሴይ ያለ ባሮን እንደ እኔ ያለ ቡርጓዥዋ ከአንድ ጣራ ስር
ለማኖር ያዳግታል፡፡» ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠና ቁጣቸው እንደነበልባል ከፊታቸው
ላይ እየሰራ ቀጥ ብለው ቆሙ:: እጃቸውን ወደ ማሪየስ ዘርግተው «ከዚህ ቤት ውጣልኝ» ሲሉ ጮሁ:: ማሪየስ ከቤቱ ወጣ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ለሴት ልጃቸው ሲናገሩ «ለዚህ ደም መጣጭ
በየስድስት ወር ስልሣ ፒስትልስ ትልኪለታለሽ፤ ለእኔ ግን ሁለተኛ ምንም ነገር እንዳታነሺ» ሲሉ አዘዙ፡፡
ነገሩ በጣም ስላሳዘናቸውና ስላናደዳቸው በሚቀጥሉት ሦስት ወራት የሚይዙትንና የሚጨብጡትን አሳጣቸው:: ሴት ልጃቸውን ሲያነጋግሩ እንኳን እጅግ ቀዝቀዝ ብለው ነበር፡፡
ማሪየስ ከቤቱ የወጣው ወደዚያ ቦታ ነው የምሄደው ሳይል ነበር
እነርሱም የት እንደሚሄድ አልጠየቁትም:: ጋሪ ተከራይቶ ዘልሉ ከገባ በኋሳ ጋሪው ወደ መራው ሄደ፡፡
ማሪየስ ምን ሊያደርግ ነው?
የእህቤሴ ጓደኞች
ማሪየስ ከቤቱ በወጣበት ጊዜ የለውጥ አየር ይነፍስ ነበር፡፡ ሰው ሁሉ ሳይታወቀው ንቅናቄ ውስጥ እየገባ አብዮተኛ ሆኖኣል፡፡ እያንዳንዱ ግለሰብ አንድ እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡ ንጉሣውያን ቤተሰብ እንኳን ሳይቀሩ በነገሩ ገቡ።ሰዎች ከጊዜ በኋላ ናፖሊዮንንና ነፃነትን እንደ አምላክ የማምለክ ስሜት አደረባቸው:: ሌሎች ደግሞ ዓለም ፍጹም እንድትሆን ተመኙ::
የዛሬው ምኞት ነገ ሥጋና ደም ለብሶ እሙን እንደሚሆን አመኑ፡፡
የአህቤሴ ጓደኞች እነማን ናቸው? አህቤሴ የተረገጡ፤ የተከፉና
የተረሱ ጭቁኖች ሲሆኑ እነዚህ ሰዎች በፖለቲካው እንቅስቃሴ ሳቢያ ብዙ ወዳጆች ያፈሩ ናቸው:: ጓደኞቻቸወም ከወደቁበት እንዲነሱ ከልብ ተመኙ:: ሰዎቹ ብዙ አልነበሩም:: ፓሪስ ከተማ ውስጥ ሃሌስና ኮርኒት ከተባሉ ሥፍራዎች በየጊዜው ከአንዲት አነስተኛ ቡና ቤት ውስጥ
ይሰበሰባሉ: ሥፍራው ወዛደሮች የሚኖሩበት አካባቢ ነው:: በዚያ አካባቢ ተማሪዎችም በብዛት ይገኛሉ፡፡ የአህቤሴ ጓደኞች የሚሰበሰቡበት ቡና ቤት
«ካፌ ሙሴን» ይባላል፡፡ ቡና ቤቱ ሰፊ ጓዳ ስለነበረው የአህቤቴ ጓደኞች ከዚያ ክፍል ውስጥ ይሰበሰባሉ:: ክፍሉ ከዋናው መጠጫ ክፍል ትንሽ ራቅ
ያለ ነበር፡፡ በጓሮ በኩል ወደ ውጭ የሚያስወጣ በር አለው::
ጓደኛሞቹ ከዚያች ክፍል ውስጥ ይጠጣሉ፤ ሲጃራ ያጨሳሉ:፧
ይጫወታሉ፤ የፖለቲካ ወሬ ያወራሉ:: የማያነሱት ነጥብ የለም፡ከክፍለ ግድግዳ ላይ የበፊቱን የፈረንሳይ ሪፑብሊክ ካርታ ሰቅለዋል።
የዚህ ቡድን አባሎች አብዛኞቹ ተማሪዎች ሲሆኑ ጥቂት ወዛደሮችም ነበሩበት፡፡ ጥቂት ቀንደኛ መሪዎች አሉዋቸው:: ከመሪዎቹ መካከል ኔንጀልራስ የተባለው የሀብታም ልጅ ቀንደኛ መሪ ሲሆን ደስ የሚልና
መልከ መልካም ወጣት ነው:: ደግሞም በጣም አዋቂ ከመሆኑም በላይ ወኔው ለጉድ ነው:: ከቀንደኛው መሪ ከኢንጆልራስ ጎን የተሰለፉ ሌሎችም ረዳት መሪዎች አሉ::
አንዳንዶቹ በፖለቲካው ሌሎቹ ደግሞ በሰው ልጅ ፍቅር የሰከሩ ናቸው:: አንዳንዶቹ ‹‹ጭቁኖችን ነፃ እናወጣለን ብለው የተነሱ ሲሆኑ ሌሎች ደግሞ «አገራችን ውስጥ አድልዎ የተለየው ትክክለኛ ፍርድ እንዲሰፍን ጽኑ እምነታችን ነው» የሚሉ ናቸው::
ሆኖም በመካከላቸው አንድ ተጠራጣሪ ሰው ነበር፡፡ ታዲያ የሕዝቦችና የግለሰብ መብት፧ የፈረንሳይ አብዮት ፧ ሪፑብሊክ ፧ ዲሞክራሲ ፧ ለሰው ሥልጣኔ፤ ሃይማኖት፧ መሻሻልና የመሳሰሉት ቃላት ለእርሱ ትርጉም የላቸውም:: እነዚህን ቃላት በሰማ ቁጥር ይስቃል:: ታዲያ ከነዚህ የተለየ ዓላማ ካላቸው ሰዎች መካከል ይህ ሰው እንዴት ሊደባለቅ ቻለ?
ይህ ሰው ተጠራጣሪ ቢሆንም የራሰ እምነት ነበረው:: እምነቱ
በኢንጂልራስ ላይ ነው:: ኢንጂልራስን ይወደዋል፣ ያደንቀዋል፣ ያምንበታል::
ለዚህ ነው በዓላማ አንድ ከነበሩና እንደ ቤተሰብ ከሚተያዩ ሰዎች መካከል ሊገባ የቻለው:: ኢንጆልራስ ይህን ተጠራጣሪ በፍልስፍና ወይም በነበረው
የተለየ አሳብ ሳይሆን በጠባዩ ነው የገዛው፡፡
አንድ ቀን ከሰዓት በኋላ፤ ሕይወት በአጋጣሚ የተሞላች ናትና፧
አንድ ነገር በአጋጣሚ ይሆናል፡፡ ከፈረንሳይ አብዮት ጠንሳሾች መካከል አንዱ ከካፌ ሙሴን በራፍ ግድግዳ ተደግፎ ቆሞአል:: እርሱ ከዚያ እንደቆመ ጋሪ በዚያ በኩል ያልፋል፡፡ ይህ ሌግል የተባለ ወጣት ጋሪውን ሲመለከተው
በጣም ዝግ ብሎ ስለሚሄድ አንድ ነገር እንደሚፈልግ ጠረጠረ:: አነስተኛ ሻንጣ የያዘ ሰው ጋሪው ላይ ከነጂው ጎን ቁጭ ብሎአል፡፡ ሻንጣው ላይ ማሪየስ ፓንትመርሲ የሚል ጽሑፍ በጉልህ ተጽፎበት ስለነበር ሌግል ጽሑፉን ያነባል::
ማሪየስ ፓንትመርሲ የሚለው ስም በጣም ማረከው:: ጋሪው ከአጠገቡ ሲደርስ «መሴይ ማሪየስ ፓንትመርሲ» ሲል ተጣራ:: ጋሪው ቆመ:: ጋሪው
ላይ የነበረውና በአሳብ መጥቆ ሄዶ የነበረው ወጣት ቀና አለ፡፡
«ምን ነበር?» ሲል ጠየቀ፡፡
«መሴይ ማሪየስ ፓንትመርሲ ማለት አንተ ነህ?»
«ነኝ፡፡»
«ስፈልግህ ነበር፡፡»
«እንዴት ሊሆን ይችላል? አታውቀኝ፤ አላውቅህ» ሲል ማሪየስ ጠየቀው
«ትናንት ትምህርት ቤት አልመጣህም፡፡»
«ላልመጣ እችላለሁ::»
««በርግጥ አልመጣህም::
‹‹ተማሪ ነህ አንተም?»
«አዎን፧ እንዳንተው ተማሪ ነኝ:: ከትናንት ወዲያ ልክ ወደ ክፍል
ልገባ ስል፧ አለ አይደል አንዳንዴ አስተማሪዎች ሦስት ጊዜ ስምህን ሲጠሩ አቤት ካላልክ ይሠርዙሃል፡፡ ስልሣ ፍራንክ ቀለጠች ማለት ነው::»
ማሪየስ ዝም ብሎ ይሰማል:: ሌግል ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«ብሎንዳው የሚባለው አስተማሪ ነበር ስም የሚጠራው፡፡ አስተማሪውን ታውቀዋለህ አይደል? ያ እንኳን ቀፋፊና ግትር አፍንጫ ያለው! የቀረ ተማሪ
👍18
የመዘገበ እንደሆነ ደስታው አይጣል ነው:: ስም ሲጠራ ሁሉም አቤት ስላለ በጣም ተከፋ:: ብሉንዳው ዛሬ የሚቀጡት ሰው ስላላገኙ አዘኑ የኔ ፍቅር አልኩ በልቤ፡፡ በድንገት ወዲያው ማሪየስ ፓንትመርሲ ሲል ይጣራል፡፡ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንደገና ማሪየስ ፓንትመርሲ ሲል
ተጣራ፡ ብዕሩን አነሳ፡፡ ተቅማጥ ያዘኝ:: ስሙ ጎበዝ፤ ይህን ተማሪ እናድነው፧ ሞት ለብሉንዳው አልኩኝ በልቤ፡፡ ብዕሩን እንዳነሣ ለሦስተኛ ጊዜ ማሪየስ
ፓትመርሲ ሲል ተጣራ:: እኔ እንዳቀረቀርኩ 'አቤት' ስል መለስኩለት:: ስምህ ከመሰረዙ ዳነ፡፡›
" ጌታው..!» አላ ማሪየስ::
«ጌታማ ነበርኩ» ሲል ሌግል መለሰ::
«አልገባኝም» አለ ማሪየስ፡፡
ሌግል ወሬውን ቀጠለ፡፡
ስሜ ሌግል ይባላል፡፡»
«ሌግል፧ ደስ የሚል ስም ነው» አለ ማሪየስ፡፡
«አቤት ብዬ ስመልስ አስተማሪው ነብር መስሉ ቀና ብሎ ያየኛል፡፡
አንተ ፓንትመርሲ ከሆንክ እንግዲያው ሌግል አይደለህም' ሲል ስሜን ከዝርዝሩ ውስጥ ፋቀው፡፡»
«በጣም አዝናለሁ» ሲል ማሪየስ ጣልቃ ገባ፡፡ ሌግል ከት ብሎ ሳቀ::
«እኔ እንደሆነ ደስ ነው ያለኝ:: አንተ ከገባህበት የሕግ ትምህርት ልገባ
ገና ትምህርቱን ልጀምረው ስል ይህ አጋጣሚ አዳነኝ:: ስለዚህ በዚህ ስለዚህ በዚህ አጋጣሚ አንተን ላመሰግን እንጂ! ለመሆኑ የት ነው የምትኖረው?»
“ከጋሪው ላይ» አለ ማሪየስ እንደማፌዝ ብሎ::
የቱጃርነት ምልክት ነዋ!» ሲል ሌግል መለሰ:: «እንኳን ደስ ያለህ::
በአመት ወደ ዘጠኝ ሺህ ፍራንክ ነው ለባለጋሪው የምትከፍለው?»
ልክ ሌግል ይህን ሲናገር ጓደኛው ኩርፌይራ፡ ከቡና ቤቱ ብቅ አለ::
ማርያስ የመገረም ፈገግታ አሳዬ
ካጋሪው ሳልወርድ ለሁለት ሰዓት ያህል ተንቀዋልያለሁ:: አሁን
ግን ቢበቃኝ ይሻላል:: የት እንደምሄድ ግን አላውቅም ብል ለወጣቶች አዲስ ነገር አይሆንም::»
«አይዞህ» አለ ኩርፌይራክ፣ «ከእኔ ቤት ልንሄድ እንችላለን::
ያን እለት ወደ ማታ ኩርፌይራክ ከሚያርፍበት ሆቴል ማሪየስ |
አብሮ ሄደ፡፡
በጥቂት ቀናት ውስጥ ማሪየስና ኩርፌይራክ በጣም ተቀራረቡ::
በወጣትነት ዘመን ወዳጅ ማፍራት ቀላል ነው:: ማሪየስ ጓደኛው ኩርፌይራክ እስካለ ድረስ ደስ እያለው በነፃነት ይኖራል:: እንደፈለገው ነፃ ሆኖ መኖር ና?
ለእርሱ አዲስ ነገር ነበር፡፡ ኩርፌይራክ ጥያቄ በማብዛት አይነተርከውም፡ እነርሱ በደረሱበት የወጣትነት እድሜ ንትርክ እንደሚጠላ ኩርፌይራክ
ጠንቅቆ ያውቃል፡፡
ኩርፌይራክ ማሪየስን ወደ ካፌ ሙሴን ይዞት ሄደ:: ከዚያም ፈገግ
እያለ ወደ ጆሮው ጠጋ ብሎ «የንቅናቄው አባል እንድትሆን የመግቢያ ፈቃድ እሰጥሃለሁ» ሲል አንሾካሾከለት:: የእህቤሴ ጓደኞች ከሚሰበሰቡበት ክፍል ወሰደው:: ከሌሉች አባሎች ጋር «ተማሪ ነው»ሲል አስተዋወቀው።
ለምን ተማሪ ነው ብሎ እንዳስተዋወቀው ማሪየስ አልገባውም::
የማሪየስ አስተዳደግ የብቸኝነት ሲሆን እንዲህ ዓይነቱን ግርግር
አልለመደውም:: ወጣቶች በብዛት ተሰባስበው እርስ በእርስ ሲፋጩና በአንድ ላይ ሲወያዩ ለእርሱ አዲስ ነገር ነው:: አንዳንድ ተስፈንጣሪዎች በነገር
ስለሚነካኩ በመጠኑም ቢሆን ይደናገረዋል:: እነዚያ ወጣቶች ሁሉ በነፃነት እንደዚያ ሲወያዩ ገረመው:: አንዳንዴም ከመገረም አልፎ ይደነቃል፡፡ እነዚያ ወጣቶች በአስተሳሰብ በተለይም በፖለቲካ ጉዳይ መጥቀው ሄደዋል።
ወጣቶቹ ስለፍልስፍናና፧ ስለሥነጽሑፍ፤ ስለታሪክ፤ ስለሃይማኖት፧ ስለሥነ ጥበብና ስለመሳሰሉት ነገሮች ሲወያዩ አልፎ ኣልፎ መከታተል ይሳነዋል።
የአያቱን አስተሳሰብ ጥሎ የአባቱን በተከተለ ጊዜ ሁለተኛ የአሳብ ግጭት የሚደርስበት አልመሰለውም ነበር፡፡ ግን ባይናገረውም እንደዚያ አልሆነም፡፡ ቀደም ሲል የነበረው ማንኛውም አመለካከት ቀስ እያለ ይለወጥ ጀመረ፡፡
አንዳንዴም አሳብ እርስ በእርስ እየተጋጨበት ከግራ ወደ ቀኝ ያወዛውዘዋል፡፡ይህም እስከ መሰቃየት አደረሰው::
ወጣቶቹ የሚፈሩት ወይም በነፃነት የማይወያዩበት ነገር አልነበረም፡፡
እነርሱ የሚወያዩበት ነገር እርሱን በጣም ያስፈራዋል:: ስለንጉሱና
ስለናፖሊዎን እያነሱ በነፃ ይወያያሉ።
ማሪየስ ከዉይይቱ፡ ወስጥ ገብቶ አሳብ የሰጠ እንደሆነ ራሱ
ይገርመዋል:: አንድ ቀን ማታ የእህቤሴ ጓደኞች በሙሉ መጥተው ስብሰባ ይካሄዳል፡፡ ትልቁ መብራት ስለበራ ክፍሉ ወለል ብሏል፡፡ አርእስት እየቀያየሩ
ይወያያሉ፡፡ ውይይቱ ሲካሄድ ብዙ አይንጫጩም:: ስለዋተርሉ ጦርነትና ስለ ለናፖልዮን ወሬ ሲነሣ ማሪየስ ሳያስበው በድንገት ብድግ ብሎ ንግግር ይጀምራል
«እኔ አዲስ መጤ ነኝ፣ ሆኖም እስካሁን በሰማሁት በጣም ነው
የገረማችሁኝ:: የት ነው የምናመራው? እኛ ማን ነን? እናንተ ለመሆኑ እነማን ናችሁ? ወጣቶች መስላችሁኝ ነበር፡፡ ታዲያ ወኔያችሁን ምን ሰለበው?
ናፖሊዮንን ካላደነቃችዉ ማንን ልታደንቁ ነው? ከእርሱስ ይበልጥ መሪ ማንን ነው የምትፈልጉት? ያንን ትልቅ ሰው ካልወደዳችሁ ከእርሱ የተሻለ ማንን ልታመጡ ነው? ጓደኞቼ ስለእውነት ተናገሩ፡፡ ከእርሱ ይበልጥ ለሕዝብ የቆመ መሪ ከየት ሊመጣ ነው! ትልቅ መንግሥትና ታላቅ ጦር መፍጠር፤ እንደ ኣእዋፍ ሠራዊቱን በየተራራው ለማስራጨት፤ ከባድ
ክፍለ ጦር ለማሠማራት፤ ለማጥቃት፧ ለማርበድበድ ፤ አውሮጳ ውስጥ ተከብሮ ለመኖር፧ በታሪክ አምድ ከፍተኛ ሥፍራ ለማግኘት፤ ዓለምን አንዴ ሳይሆን ሁለቴ ለማሸነፍ ከእርሱ ይበልጥ ታላቅ ሰው ማን አለ? ከዚህስ ይበልጥ የከበረ ነገር ምን ይገኛል?»
«ነፃ መሆን» አለ ከስብሰባው ተሳታፊ አንዱ፡፡ ማሪየስን ለጥ ብሎ እጅ ነሳው። «ነፃ መሆን» በማለት የተጠቀሱት ቃላት አጥንቱን ሰርስረው ነው የገቡት ቀና ቢል መልስ የሰጠው ሰው ከነበረበት የለም:: አንድ ሰው ቶሎ
ቶሎ እያለ ሲዘፍን ተሰማ:: ዘፈኑ ስለጁለየስ ቄሣር የተዘፈነ ነበር:: ማሪየስ ውድ እናቴ» እያለ አዜመ:: ኤንጀልራስ ከኋላ መጥቶ ትከሻውን መታ መታ አደረገው።
«ወንድም፤ ውድ እናት ማለት እኮ ሪፑብሊክ ናት» አለው::
ማሪየስ ከሁለት እምነት መካከል ይወጠራል:: የጥንቱን ጨርሶ
ከሕሊናው አላስወጣም፤ አዲሱም ከልቡ ውስጥ ሥር አልሰደደም:: የትኛውን ያጠንክር? ከሁለት አንድ መምረጥ ቀላል አይደለም:: ለመወሰን ትክክለኛውን መንገድ የሚያሳይ መብራት ያሻል፡፡
ማሪየስ ለመቀጠል፤ ወደፊት ለመራመድ፤ ለማሰብ፤ ለመመራመር ሁኔታው ያስገድደዋል:: ወደፊት በሄደ ቁጥር አባቱን የቀረበ ይመስለዋል:
ከአባቱ እምነት ለመራቅ ደግሞ አይፈልግም:: ከአያቱም ሆነ ከጓደኞቹ ጋር በአሳብ ተራርቋል፡፡ ወደ ካፌ ሙሴን መሄዱን አቆመ::
በሕይወት፧ ለማሰላሰል የማይፈልጉትን ነገር ከጭንቅላት አውጥቶ ለመጣል ያዳግታል፡፡ ይህም በመሆኑ ሁለት ተቃራኒ አሳቦች ከሕሊናው ሊወጡ አልቻሉም:: አንድ ቀን ጠዋት የሚኖርበት ሆቴል ጠባቂ ከክፍሉ . ይገባሉ::
«መሴይ ከርፌይራክ ለአንተም ኃላፊ ነው?»
«አዎን»
«ግን ገንዘብ ያስፈልገኝ ነበር!»
«ኩርፌይራክ እንዲያነጋግረኝ ይንገሩት» አለ ማሪየስ፡፡
ኩርፌይራክ መጣ፧ የሆቴሉ ጠባቂ ከክፍሉ ወጣ፡፡ ማሪየስ በዓለም
ላይ የእኔ ነው የሚለው ዘመድ ወዳጅ እንደሌለው ለኩርፌይራክ ቀደም ብሎ ለመንገር ፈልጎ እንደነበር ገለጸለት::
«ታዲያ ምን ይሻልሃል?» ሲል ከርፌይራክ ጠየቀ::
ተጣራ፡ ብዕሩን አነሳ፡፡ ተቅማጥ ያዘኝ:: ስሙ ጎበዝ፤ ይህን ተማሪ እናድነው፧ ሞት ለብሉንዳው አልኩኝ በልቤ፡፡ ብዕሩን እንዳነሣ ለሦስተኛ ጊዜ ማሪየስ
ፓትመርሲ ሲል ተጣራ:: እኔ እንዳቀረቀርኩ 'አቤት' ስል መለስኩለት:: ስምህ ከመሰረዙ ዳነ፡፡›
" ጌታው..!» አላ ማሪየስ::
«ጌታማ ነበርኩ» ሲል ሌግል መለሰ::
«አልገባኝም» አለ ማሪየስ፡፡
ሌግል ወሬውን ቀጠለ፡፡
ስሜ ሌግል ይባላል፡፡»
«ሌግል፧ ደስ የሚል ስም ነው» አለ ማሪየስ፡፡
«አቤት ብዬ ስመልስ አስተማሪው ነብር መስሉ ቀና ብሎ ያየኛል፡፡
አንተ ፓንትመርሲ ከሆንክ እንግዲያው ሌግል አይደለህም' ሲል ስሜን ከዝርዝሩ ውስጥ ፋቀው፡፡»
«በጣም አዝናለሁ» ሲል ማሪየስ ጣልቃ ገባ፡፡ ሌግል ከት ብሎ ሳቀ::
«እኔ እንደሆነ ደስ ነው ያለኝ:: አንተ ከገባህበት የሕግ ትምህርት ልገባ
ገና ትምህርቱን ልጀምረው ስል ይህ አጋጣሚ አዳነኝ:: ስለዚህ በዚህ ስለዚህ በዚህ አጋጣሚ አንተን ላመሰግን እንጂ! ለመሆኑ የት ነው የምትኖረው?»
“ከጋሪው ላይ» አለ ማሪየስ እንደማፌዝ ብሎ::
የቱጃርነት ምልክት ነዋ!» ሲል ሌግል መለሰ:: «እንኳን ደስ ያለህ::
በአመት ወደ ዘጠኝ ሺህ ፍራንክ ነው ለባለጋሪው የምትከፍለው?»
ልክ ሌግል ይህን ሲናገር ጓደኛው ኩርፌይራ፡ ከቡና ቤቱ ብቅ አለ::
ማርያስ የመገረም ፈገግታ አሳዬ
ካጋሪው ሳልወርድ ለሁለት ሰዓት ያህል ተንቀዋልያለሁ:: አሁን
ግን ቢበቃኝ ይሻላል:: የት እንደምሄድ ግን አላውቅም ብል ለወጣቶች አዲስ ነገር አይሆንም::»
«አይዞህ» አለ ኩርፌይራክ፣ «ከእኔ ቤት ልንሄድ እንችላለን::
ያን እለት ወደ ማታ ኩርፌይራክ ከሚያርፍበት ሆቴል ማሪየስ |
አብሮ ሄደ፡፡
በጥቂት ቀናት ውስጥ ማሪየስና ኩርፌይራክ በጣም ተቀራረቡ::
በወጣትነት ዘመን ወዳጅ ማፍራት ቀላል ነው:: ማሪየስ ጓደኛው ኩርፌይራክ እስካለ ድረስ ደስ እያለው በነፃነት ይኖራል:: እንደፈለገው ነፃ ሆኖ መኖር ና?
ለእርሱ አዲስ ነገር ነበር፡፡ ኩርፌይራክ ጥያቄ በማብዛት አይነተርከውም፡ እነርሱ በደረሱበት የወጣትነት እድሜ ንትርክ እንደሚጠላ ኩርፌይራክ
ጠንቅቆ ያውቃል፡፡
ኩርፌይራክ ማሪየስን ወደ ካፌ ሙሴን ይዞት ሄደ:: ከዚያም ፈገግ
እያለ ወደ ጆሮው ጠጋ ብሎ «የንቅናቄው አባል እንድትሆን የመግቢያ ፈቃድ እሰጥሃለሁ» ሲል አንሾካሾከለት:: የእህቤሴ ጓደኞች ከሚሰበሰቡበት ክፍል ወሰደው:: ከሌሉች አባሎች ጋር «ተማሪ ነው»ሲል አስተዋወቀው።
ለምን ተማሪ ነው ብሎ እንዳስተዋወቀው ማሪየስ አልገባውም::
የማሪየስ አስተዳደግ የብቸኝነት ሲሆን እንዲህ ዓይነቱን ግርግር
አልለመደውም:: ወጣቶች በብዛት ተሰባስበው እርስ በእርስ ሲፋጩና በአንድ ላይ ሲወያዩ ለእርሱ አዲስ ነገር ነው:: አንዳንድ ተስፈንጣሪዎች በነገር
ስለሚነካኩ በመጠኑም ቢሆን ይደናገረዋል:: እነዚያ ወጣቶች ሁሉ በነፃነት እንደዚያ ሲወያዩ ገረመው:: አንዳንዴም ከመገረም አልፎ ይደነቃል፡፡ እነዚያ ወጣቶች በአስተሳሰብ በተለይም በፖለቲካ ጉዳይ መጥቀው ሄደዋል።
ወጣቶቹ ስለፍልስፍናና፧ ስለሥነጽሑፍ፤ ስለታሪክ፤ ስለሃይማኖት፧ ስለሥነ ጥበብና ስለመሳሰሉት ነገሮች ሲወያዩ አልፎ ኣልፎ መከታተል ይሳነዋል።
የአያቱን አስተሳሰብ ጥሎ የአባቱን በተከተለ ጊዜ ሁለተኛ የአሳብ ግጭት የሚደርስበት አልመሰለውም ነበር፡፡ ግን ባይናገረውም እንደዚያ አልሆነም፡፡ ቀደም ሲል የነበረው ማንኛውም አመለካከት ቀስ እያለ ይለወጥ ጀመረ፡፡
አንዳንዴም አሳብ እርስ በእርስ እየተጋጨበት ከግራ ወደ ቀኝ ያወዛውዘዋል፡፡ይህም እስከ መሰቃየት አደረሰው::
ወጣቶቹ የሚፈሩት ወይም በነፃነት የማይወያዩበት ነገር አልነበረም፡፡
እነርሱ የሚወያዩበት ነገር እርሱን በጣም ያስፈራዋል:: ስለንጉሱና
ስለናፖሊዎን እያነሱ በነፃ ይወያያሉ።
ማሪየስ ከዉይይቱ፡ ወስጥ ገብቶ አሳብ የሰጠ እንደሆነ ራሱ
ይገርመዋል:: አንድ ቀን ማታ የእህቤሴ ጓደኞች በሙሉ መጥተው ስብሰባ ይካሄዳል፡፡ ትልቁ መብራት ስለበራ ክፍሉ ወለል ብሏል፡፡ አርእስት እየቀያየሩ
ይወያያሉ፡፡ ውይይቱ ሲካሄድ ብዙ አይንጫጩም:: ስለዋተርሉ ጦርነትና ስለ ለናፖልዮን ወሬ ሲነሣ ማሪየስ ሳያስበው በድንገት ብድግ ብሎ ንግግር ይጀምራል
«እኔ አዲስ መጤ ነኝ፣ ሆኖም እስካሁን በሰማሁት በጣም ነው
የገረማችሁኝ:: የት ነው የምናመራው? እኛ ማን ነን? እናንተ ለመሆኑ እነማን ናችሁ? ወጣቶች መስላችሁኝ ነበር፡፡ ታዲያ ወኔያችሁን ምን ሰለበው?
ናፖሊዮንን ካላደነቃችዉ ማንን ልታደንቁ ነው? ከእርሱስ ይበልጥ መሪ ማንን ነው የምትፈልጉት? ያንን ትልቅ ሰው ካልወደዳችሁ ከእርሱ የተሻለ ማንን ልታመጡ ነው? ጓደኞቼ ስለእውነት ተናገሩ፡፡ ከእርሱ ይበልጥ ለሕዝብ የቆመ መሪ ከየት ሊመጣ ነው! ትልቅ መንግሥትና ታላቅ ጦር መፍጠር፤ እንደ ኣእዋፍ ሠራዊቱን በየተራራው ለማስራጨት፤ ከባድ
ክፍለ ጦር ለማሠማራት፤ ለማጥቃት፧ ለማርበድበድ ፤ አውሮጳ ውስጥ ተከብሮ ለመኖር፧ በታሪክ አምድ ከፍተኛ ሥፍራ ለማግኘት፤ ዓለምን አንዴ ሳይሆን ሁለቴ ለማሸነፍ ከእርሱ ይበልጥ ታላቅ ሰው ማን አለ? ከዚህስ ይበልጥ የከበረ ነገር ምን ይገኛል?»
«ነፃ መሆን» አለ ከስብሰባው ተሳታፊ አንዱ፡፡ ማሪየስን ለጥ ብሎ እጅ ነሳው። «ነፃ መሆን» በማለት የተጠቀሱት ቃላት አጥንቱን ሰርስረው ነው የገቡት ቀና ቢል መልስ የሰጠው ሰው ከነበረበት የለም:: አንድ ሰው ቶሎ
ቶሎ እያለ ሲዘፍን ተሰማ:: ዘፈኑ ስለጁለየስ ቄሣር የተዘፈነ ነበር:: ማሪየስ ውድ እናቴ» እያለ አዜመ:: ኤንጀልራስ ከኋላ መጥቶ ትከሻውን መታ መታ አደረገው።
«ወንድም፤ ውድ እናት ማለት እኮ ሪፑብሊክ ናት» አለው::
ማሪየስ ከሁለት እምነት መካከል ይወጠራል:: የጥንቱን ጨርሶ
ከሕሊናው አላስወጣም፤ አዲሱም ከልቡ ውስጥ ሥር አልሰደደም:: የትኛውን ያጠንክር? ከሁለት አንድ መምረጥ ቀላል አይደለም:: ለመወሰን ትክክለኛውን መንገድ የሚያሳይ መብራት ያሻል፡፡
ማሪየስ ለመቀጠል፤ ወደፊት ለመራመድ፤ ለማሰብ፤ ለመመራመር ሁኔታው ያስገድደዋል:: ወደፊት በሄደ ቁጥር አባቱን የቀረበ ይመስለዋል:
ከአባቱ እምነት ለመራቅ ደግሞ አይፈልግም:: ከአያቱም ሆነ ከጓደኞቹ ጋር በአሳብ ተራርቋል፡፡ ወደ ካፌ ሙሴን መሄዱን አቆመ::
በሕይወት፧ ለማሰላሰል የማይፈልጉትን ነገር ከጭንቅላት አውጥቶ ለመጣል ያዳግታል፡፡ ይህም በመሆኑ ሁለት ተቃራኒ አሳቦች ከሕሊናው ሊወጡ አልቻሉም:: አንድ ቀን ጠዋት የሚኖርበት ሆቴል ጠባቂ ከክፍሉ . ይገባሉ::
«መሴይ ከርፌይራክ ለአንተም ኃላፊ ነው?»
«አዎን»
«ግን ገንዘብ ያስፈልገኝ ነበር!»
«ኩርፌይራክ እንዲያነጋግረኝ ይንገሩት» አለ ማሪየስ፡፡
ኩርፌይራክ መጣ፧ የሆቴሉ ጠባቂ ከክፍሉ ወጣ፡፡ ማሪየስ በዓለም
ላይ የእኔ ነው የሚለው ዘመድ ወዳጅ እንደሌለው ለኩርፌይራክ ቀደም ብሎ ለመንገር ፈልጎ እንደነበር ገለጸለት::
«ታዲያ ምን ይሻልሃል?» ሲል ከርፌይራክ ጠየቀ::
👍13❤1
«እኔ እንጃ!» ሲል ማሪየስ መለሰ፡፡
የማሪየስ አክስት የልብ ክፋት ስለሌላት ማሪየስ እንዴት ሆኖ ይኖር ይሆን ብላ በማጠያየቅ የት እንዳረፈ ትደርስበታለች፡፡ አንድ ቀን ማሪየስ ከትምህርት ቤት ሲመለስ አክስቱ የጻፈችለትን ደብዳቤ ያገኛል፡፡ ከደብዳቤው ጋር ስድስት መቶ ፍራንክ በፖስታ ታሽጎ ተሰጠው:: ማሪየስ ገንዘቡን
መልሶ ለአክስቱ ላከላት:: ከገንዘቡ ጋር ለመተዳደሪያ የሚሆን ገንዘብ ራሱ ለማፍራት መቻሉን በመግለጽ ትህትና የተሞላበት ደብዳቤ ጻፈላት፡፡ በዚያን ጊዜ ኪሱ ውስጥ የነበረው ገንዘብ ግን ሦስት ፍራንክ ብቻ ነበር፡፡
ገንዘቡን ለመመለሱ አክስቱ ለአያቱ አልነገረቻቸውም፡፡ አያቱ ቀደም ሲል ስለእርሱ ሁለተኛ እንዳታነሳብኝ ስላለ የማሪየስን ወሬ ማንሳት አልፈለገችም:: ማሪየስ እዳው ስለበዛበት ሆቴል ቤቱን ለቅቆ ወጣ፡፡....
💫ይቀጥላል💫
የማሪየስ አክስት የልብ ክፋት ስለሌላት ማሪየስ እንዴት ሆኖ ይኖር ይሆን ብላ በማጠያየቅ የት እንዳረፈ ትደርስበታለች፡፡ አንድ ቀን ማሪየስ ከትምህርት ቤት ሲመለስ አክስቱ የጻፈችለትን ደብዳቤ ያገኛል፡፡ ከደብዳቤው ጋር ስድስት መቶ ፍራንክ በፖስታ ታሽጎ ተሰጠው:: ማሪየስ ገንዘቡን
መልሶ ለአክስቱ ላከላት:: ከገንዘቡ ጋር ለመተዳደሪያ የሚሆን ገንዘብ ራሱ ለማፍራት መቻሉን በመግለጽ ትህትና የተሞላበት ደብዳቤ ጻፈላት፡፡ በዚያን ጊዜ ኪሱ ውስጥ የነበረው ገንዘብ ግን ሦስት ፍራንክ ብቻ ነበር፡፡
ገንዘቡን ለመመለሱ አክስቱ ለአያቱ አልነገረቻቸውም፡፡ አያቱ ቀደም ሲል ስለእርሱ ሁለተኛ እንዳታነሳብኝ ስላለ የማሪየስን ወሬ ማንሳት አልፈለገችም:: ማሪየስ እዳው ስለበዛበት ሆቴል ቤቱን ለቅቆ ወጣ፡፡....
💫ይቀጥላል💫
👍15🥰1
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ቦምብ እንዲኖረኝ እፈልግ ነበር!! እንደ እጅ ስልኬ በፈለግኩበት ሰዓት ቁልፎቹን የምጫነው…
የራሴ፣ የግሌ ቦምብ፡፡ ቦምብ ሲባል ግን ይሄ ሰባት ሰው አቁስሎ፣ ሁለት ሰው ገደለ መስተዋት ሰባበረ ግድግዳ ደረመስ የሚባለው ዓይነት ቦንብ ሳይሆን በጅምላ ፊቱን ያጠቆረብንን፣ በጅምላ
የበደለንን፣ በጅምላ የገፋንን ሕዝብ በጅምላ ድራሹን የሚያጠፉ ኒውክሌር ቦምብ።
ቡምምምምምምምምምም ሰፈራችንን የዶግ አመድ አዲሳባን ከነስሟ ድራሿን የሚያጠፋ..
ወይ አዲስ አበበ አወይ ሸገር ሆይ
ከተማ እንደጤዛ እልም ይላል ወይ
እየተባለ እስኪዘፈን ወላ ሙሾ እስኪወርድ ድረስ በቃ አዲስ አበባን ባዶ የሚያደርግ .እንጦጦን
ሳይቀር ከስሩ ነቅሎ ህንድ ውቅያኖስ የሚጥል አዲሳባ የምትባል ከተማ እዚህ ነበረች፡፡ ምክንያቱ ባልታወቀ ፍንዳታ ጠፋች” እንዲሉ ባለታሪኮች፤ ምከንያት ነጋሪ ባለታሪክ አይተርፍማ፡፡
ኒውክሌር ቦምብ እንዲኖረኝ እፈልግ ነበር፡፡ ሰዎች 'የግል ቤትና መኪና ቢኖረን ብለው
እንደሚመኙት ቦምብ ቢኖረኝ እያልኩ እመኝ ነበር፡፡ እዚሀ መሐል አዲስ አበባ ሲፈነዳ ንዝረቱ የሩሲያን የበረዶ ግግር የሚሰነጣጥቅ ካናዳ ሊታጨድ የደረሰውን የስንዴ አዝመራ
የሚያረግፍ ኒውክሌር ቦምብ፡፡
ይሄ የተመኘሁት ቦምብ ቢኖረኝ ለመጥፎ ነገር አልጠቀምበትም፡፡ እንደ ቤት ዕቃ እንደ ፍሪጅ
ቁምሳጥን በቀጥታ ወስጄ አቶ ቀሰመ ወርቅ ቤት ውስጥ መሐሉ ላይ አስቀምጠውና እንዲፈነዳ
ቁልፉን እጫነዋለሁ፡፡ ቡምምምምምምምምም ከእኛ ሰፈር ጀምሮ አፈር ነሽ ድንጋይ፣ ዛፍ ነሽ ተራራ ነሽ እየጠራረገ...ወደታች ወደ ሜክሲኮ ሕንፃውን ሁሉ አመድ እያደረገ መንገዱን ሁሉ
እየገለባበጠ ይወርድና ወደ ጦር ኃይሎች (አቶ ቀለመወርቅ እዛ ወንድም አላቸው ..ከዛ ወደ
አየር ጤና፣ ዓለም ባንክ (አዲስ ቤት እያስገነቡ ነው ተበሏል ዓለም ባንክ አካሳቢ)
በዚህ በኩል ደግሞ ከመስቀል አደባባይ አድርጎ ካዛንችስ ነሽ ሀያ ሁለት፣ መገናኛ፣ መሪ ሲኤምሲ እየጠራረገ በኮተቤ በኩል ሲቪል ሰርቪስ (እዛ የአቶ ቀለመወርቅ ትልቁ ልጃቸው ይማራል ይሄ ደነዝ ተምሮ ላይገባው የመንግሥት እህል ይፈጃል ! ፍንዳታው ወደ ቦሌ፣ ኢምፔርያል ገርጅም መሄድ አለበት በቃ !! ማነው የሚከለክለኝ የፈለግኩትን ማሰብ መብቴ ነው ማንም ሰው በሀሳሱ ቀአንድ ጀምበር ዓለምን ማጥፋት ይችላል እንኳን ይህቺን ቢጢቃ
ካላቅሟ የምትንጠራራ በውራጅ የምትንደላቀቅ አዲስ አበባን ቀርቶ፡፡
አዲስ አበባ አቅፋ ደብቃ ጠጅ እያጠጣች ጮማ አያስቆረጠች አንቱ ብላ ባኖረችው፣ ቀለመወርቅ
በሚባል ሰው በላ ጭራቅ ሽማግሌ ምክንያት አሸብር የሚባል ቂሙን የማይረሳ ጠላት አፍርታለች፡፡
እኔ ነኝ አሸብር፡፡ አዲስ አበባ አዲስነቷን ሳትወድ ተነጥቃ
'አዲስ ፍራሽ' ትሆናታለች የታባቷ !!
መብቴ ነው በሀሳቤ ሕንፃዎቿን የፍርስራሽ ክምር ማድረግ ታሪክ ማድረግ፡፡ “እዚህ ላይ እኮ
ቀልበት መንገድ ነበር” እያለ ድሮ የሚያውቃት እስኪያዝንላት(ለወሬ ነጋሪ የሚተርፍ ካለ) አመድ ማድረግ ይህቺን አመዳም፣ የሰው ፊት እያየች የምታዳላን ወረተኛ ከተማ ንፋስ ያየው ዱቄት ማድረግ፡፡ ደግሞ ከሷም ብሶ አዱ ገነት…ኡኡቴ!!
እንዲህ እያልኩ ሳስብ ነፍሴ ትረካለች ውስጤ ይረጋጋል፡፡ አዲስ አበባን የተበቀልኳት
ይመስለኛል….ደስ ይለኛለ:: በቁጣ የጋላ ሰውነቴ ይቀዘቅዛል። አዕምሮዬም ተረጋግቶ ወደ
ማሰቡ ይመለሳል፤ አበቦች አበባ ሊመስሉኝ ይጀምራሉ፡፡ አይኔም በጎ በጎውን ማየት ይጀምራል፣
ውርውር የሚለውን ሰው እና መኪና ቆንጆዎቹን ሴቶች፣ ባጠቃላይ ሕዝቡን ማየት እጀምራለሁ…ግን ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፣ አልወዳቸውም፡፡
ጥላቻ የዘወትር ጸሎቴ ነው፡፡ የጥፋት ምኞት አባታችን ሆይ የዕለት ድጋሜ !! ምነው “በደፈናው ጥላቻ የሚል የእርጎ ዝንብ ሲንጋጋም አዲስ አበባን ከነሕዝቧ አልወዳትም፡፡ ደግሞ “አዲስ አዱዬ…እዱ ገነት” እያሉ ይመፃደቁላታል፡፡ ኡኡቴ አዱ ሲኦል !! የአፍሪካ ዋና ጀሀነም፣ የሰይጣን ንብረት መሰብሰቢያቸውን !!
አልወዳትም አዲሰ አበባን፡፡ አልወደውም ሕዝቡን፡፡ እንዲህ ነበር የማስበው ሁልጊዜም፡፡ ጧት
የአዲስ አበባ ቅዳሴ ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ሲናኝ መስጊዶቿ በአዛን የማለዳ አየሯን ሲሞሉት፣
እናንተ ከፉ ሕዝቦች ደግሞ ነጋላችሁ፡ ለክፉት ተነሱ' የሚሉ ይመስለኝ ነበር፡፡ ማታ ሕዝቡ
በየበረንዳው ተኮልኩሎ ድራፍቱን ሲገለብጥ፣ ቢራውን ሲያጋባ ውስጡ የተከለውን ክፋት
እንዳይደርቅበት ውኃ የሚያጠጣ ይመስለኝ ነበር፡፡ ሕዝቡ ራሱ ስለራሱ ደግነት፣ ስለራሱ ቸርነት፣
ስለራሱ እንግዳ ተቀባይነትና አማኝነት ለራሱ ሲያወራ ይገርመኛል፡፡ ለእኔ የአዲስ አበባ ህዝብ ብዙ አይደለም፤ አንድ አምሳል አንድ አካል ያለው ቀለመወርቅ' የሚባል አንድ ሰው ነው !!
አሸብር ነው ስሜ ዶክተር አሽብር በአምላክ 'በአምላክ' አባቴ አይደለም፣ አያቴም አይደለም
ማን እንደሆነ አላውቅም...እናቴም አታውቅም፡፡ ልክ ለእኔ አሸብር የሚል ሰም እንደወጣልኝ
“አባት' ለሚለውም ቃል በአምላክ የሚል ስም ወጣለት፡፡ የእኔን ስም ያወጣችው ብዙ ላሞች ያሏት ክፋትን እንደ ላም የምታረባ እና ባወራች ቁጥር ከንፈሯን በአውራ ጣቷና በአመልካች ጣቷ በቄንጥ የምትጠርግ ክፉ ባልቴት ነበረች፡፡የአባቴን ስም ያወጣችልኝ ግን እናቴ ናት፡፡ እናቴ አፀደ ! አቲዬ ነው የምላት (በዚህች ምድር ላይ ስሟ ላይ ዩ፥ ጨምሬ እቆላምጬ የምጠራት ብቸኛ ሰው እኔ ልጇ አሸብር ብቻ ነበርኩ፡፡)ደ
አንደኛ ከፍል እስከመዘገብ የአባት ስም አልነበረኝም፡፡ ልክ ትምህርት ቤት አቲዬ ወስዳኝ ስመዝነብ
ጉጉት የመሰለው መዝጋቢ እናቴን እያጣደፈ ጠየቃት፡፡ ድሪቶ ቀሚሷ በዓይኑ ቀፎት እያመናጨቀ
የእኔን ስም ጠየቃት፡፡ የንቀት አስተያየቱን፣ እናቴን ዝቅ የሚያደርግ የፊቱን ገፅታ አይቼዋለሁ በዚያው ድሪቶ ቀሚስ ስር በፍርሃት ተከልዬ.አይቼዋለሁ ቅንድብና ቅንድቡ እስኪነካኩ ሲጠጋጉ እናቴ ላይ ሲኮሳተር፡፡ ለራሷ ኑሮ የገላመጣት እናቴን ሲገላምጣት አይቼዋለሁ፡፡
አቲዩ አስመዝግባኝ ከፊቱ ዞር ስትል ፊቱን ጨፍግጎ መጥፎ ጠረን እንደሚያባርር ሰው ግራ እጁ አየሩን እያራገበ ሲያባርር አይቼዋለሁ፡፡ በእርግጥ አቲዩ እማማ የብርጓል ቤት እንኩሮ እያነኮረች ነበር፡፡ “ምዝገባው ዛሬ ነው የሚያልቀው“ ሲሏት ነው ብድግ ብላ ሳትለቃለቅ የመጣችው፡፡ ቢሆንስ ልክ ቆሻሻ እንደሸተተው ሰው ፊት እንዲያየው አድርጎ እጁን ያራግባል ? የእማማ የብርጓል ቁጥር አንድ የጠላ ደንበኛ እንዳልሆነ ሁሉ፣ አሻሮ ሸተተኝ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል ? ነብር አየው !! እንኳን ይህቺን አይቼ እንዲሁም ጥላቻ ጥላቻ ይለኛል፡፡ ያንን የውሻ ልጅ አስተማሪ እንደ ጠመድኩት
ጡረታ ወጣ !! ደግሞኮ አያፍርም መንገድ ላይ ሲያገኘኝ “የእኔ ተማሪ ነው!" እያለ በኩራት ያወራል።
“ስም ” አላት አቲዬን።
“የእኔን ነው ” አለች እየፈራች። ፈሪ ነበረች እናቴ፡፡ ፈሪው የአዲስ አበባ ሕዝብ እንደያቅሙ ደሀ ማስፈራራትን ተክኖበታል፡፡ በትእቢት ማከላፈቱ፣ በክፋት፣ በስድብና ዘለፋው እናቴን ፈሪ
በርጋጊ እድርጓታል፡፡
፡
፡
#አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ቦምብ እንዲኖረኝ እፈልግ ነበር!! እንደ እጅ ስልኬ በፈለግኩበት ሰዓት ቁልፎቹን የምጫነው…
የራሴ፣ የግሌ ቦምብ፡፡ ቦምብ ሲባል ግን ይሄ ሰባት ሰው አቁስሎ፣ ሁለት ሰው ገደለ መስተዋት ሰባበረ ግድግዳ ደረመስ የሚባለው ዓይነት ቦንብ ሳይሆን በጅምላ ፊቱን ያጠቆረብንን፣ በጅምላ
የበደለንን፣ በጅምላ የገፋንን ሕዝብ በጅምላ ድራሹን የሚያጠፉ ኒውክሌር ቦምብ።
ቡምምምምምምምምምም ሰፈራችንን የዶግ አመድ አዲሳባን ከነስሟ ድራሿን የሚያጠፋ..
ወይ አዲስ አበበ አወይ ሸገር ሆይ
ከተማ እንደጤዛ እልም ይላል ወይ
እየተባለ እስኪዘፈን ወላ ሙሾ እስኪወርድ ድረስ በቃ አዲስ አበባን ባዶ የሚያደርግ .እንጦጦን
ሳይቀር ከስሩ ነቅሎ ህንድ ውቅያኖስ የሚጥል አዲሳባ የምትባል ከተማ እዚህ ነበረች፡፡ ምክንያቱ ባልታወቀ ፍንዳታ ጠፋች” እንዲሉ ባለታሪኮች፤ ምከንያት ነጋሪ ባለታሪክ አይተርፍማ፡፡
ኒውክሌር ቦምብ እንዲኖረኝ እፈልግ ነበር፡፡ ሰዎች 'የግል ቤትና መኪና ቢኖረን ብለው
እንደሚመኙት ቦምብ ቢኖረኝ እያልኩ እመኝ ነበር፡፡ እዚሀ መሐል አዲስ አበባ ሲፈነዳ ንዝረቱ የሩሲያን የበረዶ ግግር የሚሰነጣጥቅ ካናዳ ሊታጨድ የደረሰውን የስንዴ አዝመራ
የሚያረግፍ ኒውክሌር ቦምብ፡፡
ይሄ የተመኘሁት ቦምብ ቢኖረኝ ለመጥፎ ነገር አልጠቀምበትም፡፡ እንደ ቤት ዕቃ እንደ ፍሪጅ
ቁምሳጥን በቀጥታ ወስጄ አቶ ቀሰመ ወርቅ ቤት ውስጥ መሐሉ ላይ አስቀምጠውና እንዲፈነዳ
ቁልፉን እጫነዋለሁ፡፡ ቡምምምምምምምምም ከእኛ ሰፈር ጀምሮ አፈር ነሽ ድንጋይ፣ ዛፍ ነሽ ተራራ ነሽ እየጠራረገ...ወደታች ወደ ሜክሲኮ ሕንፃውን ሁሉ አመድ እያደረገ መንገዱን ሁሉ
እየገለባበጠ ይወርድና ወደ ጦር ኃይሎች (አቶ ቀለመወርቅ እዛ ወንድም አላቸው ..ከዛ ወደ
አየር ጤና፣ ዓለም ባንክ (አዲስ ቤት እያስገነቡ ነው ተበሏል ዓለም ባንክ አካሳቢ)
በዚህ በኩል ደግሞ ከመስቀል አደባባይ አድርጎ ካዛንችስ ነሽ ሀያ ሁለት፣ መገናኛ፣ መሪ ሲኤምሲ እየጠራረገ በኮተቤ በኩል ሲቪል ሰርቪስ (እዛ የአቶ ቀለመወርቅ ትልቁ ልጃቸው ይማራል ይሄ ደነዝ ተምሮ ላይገባው የመንግሥት እህል ይፈጃል ! ፍንዳታው ወደ ቦሌ፣ ኢምፔርያል ገርጅም መሄድ አለበት በቃ !! ማነው የሚከለክለኝ የፈለግኩትን ማሰብ መብቴ ነው ማንም ሰው በሀሳሱ ቀአንድ ጀምበር ዓለምን ማጥፋት ይችላል እንኳን ይህቺን ቢጢቃ
ካላቅሟ የምትንጠራራ በውራጅ የምትንደላቀቅ አዲስ አበባን ቀርቶ፡፡
አዲስ አበባ አቅፋ ደብቃ ጠጅ እያጠጣች ጮማ አያስቆረጠች አንቱ ብላ ባኖረችው፣ ቀለመወርቅ
በሚባል ሰው በላ ጭራቅ ሽማግሌ ምክንያት አሸብር የሚባል ቂሙን የማይረሳ ጠላት አፍርታለች፡፡
እኔ ነኝ አሸብር፡፡ አዲስ አበባ አዲስነቷን ሳትወድ ተነጥቃ
'አዲስ ፍራሽ' ትሆናታለች የታባቷ !!
መብቴ ነው በሀሳቤ ሕንፃዎቿን የፍርስራሽ ክምር ማድረግ ታሪክ ማድረግ፡፡ “እዚህ ላይ እኮ
ቀልበት መንገድ ነበር” እያለ ድሮ የሚያውቃት እስኪያዝንላት(ለወሬ ነጋሪ የሚተርፍ ካለ) አመድ ማድረግ ይህቺን አመዳም፣ የሰው ፊት እያየች የምታዳላን ወረተኛ ከተማ ንፋስ ያየው ዱቄት ማድረግ፡፡ ደግሞ ከሷም ብሶ አዱ ገነት…ኡኡቴ!!
እንዲህ እያልኩ ሳስብ ነፍሴ ትረካለች ውስጤ ይረጋጋል፡፡ አዲስ አበባን የተበቀልኳት
ይመስለኛል….ደስ ይለኛለ:: በቁጣ የጋላ ሰውነቴ ይቀዘቅዛል። አዕምሮዬም ተረጋግቶ ወደ
ማሰቡ ይመለሳል፤ አበቦች አበባ ሊመስሉኝ ይጀምራሉ፡፡ አይኔም በጎ በጎውን ማየት ይጀምራል፣
ውርውር የሚለውን ሰው እና መኪና ቆንጆዎቹን ሴቶች፣ ባጠቃላይ ሕዝቡን ማየት እጀምራለሁ…ግን ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፣ አልወዳቸውም፡፡
ጥላቻ የዘወትር ጸሎቴ ነው፡፡ የጥፋት ምኞት አባታችን ሆይ የዕለት ድጋሜ !! ምነው “በደፈናው ጥላቻ የሚል የእርጎ ዝንብ ሲንጋጋም አዲስ አበባን ከነሕዝቧ አልወዳትም፡፡ ደግሞ “አዲስ አዱዬ…እዱ ገነት” እያሉ ይመፃደቁላታል፡፡ ኡኡቴ አዱ ሲኦል !! የአፍሪካ ዋና ጀሀነም፣ የሰይጣን ንብረት መሰብሰቢያቸውን !!
አልወዳትም አዲሰ አበባን፡፡ አልወደውም ሕዝቡን፡፡ እንዲህ ነበር የማስበው ሁልጊዜም፡፡ ጧት
የአዲስ አበባ ቅዳሴ ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ሲናኝ መስጊዶቿ በአዛን የማለዳ አየሯን ሲሞሉት፣
እናንተ ከፉ ሕዝቦች ደግሞ ነጋላችሁ፡ ለክፉት ተነሱ' የሚሉ ይመስለኝ ነበር፡፡ ማታ ሕዝቡ
በየበረንዳው ተኮልኩሎ ድራፍቱን ሲገለብጥ፣ ቢራውን ሲያጋባ ውስጡ የተከለውን ክፋት
እንዳይደርቅበት ውኃ የሚያጠጣ ይመስለኝ ነበር፡፡ ሕዝቡ ራሱ ስለራሱ ደግነት፣ ስለራሱ ቸርነት፣
ስለራሱ እንግዳ ተቀባይነትና አማኝነት ለራሱ ሲያወራ ይገርመኛል፡፡ ለእኔ የአዲስ አበባ ህዝብ ብዙ አይደለም፤ አንድ አምሳል አንድ አካል ያለው ቀለመወርቅ' የሚባል አንድ ሰው ነው !!
አሸብር ነው ስሜ ዶክተር አሽብር በአምላክ 'በአምላክ' አባቴ አይደለም፣ አያቴም አይደለም
ማን እንደሆነ አላውቅም...እናቴም አታውቅም፡፡ ልክ ለእኔ አሸብር የሚል ሰም እንደወጣልኝ
“አባት' ለሚለውም ቃል በአምላክ የሚል ስም ወጣለት፡፡ የእኔን ስም ያወጣችው ብዙ ላሞች ያሏት ክፋትን እንደ ላም የምታረባ እና ባወራች ቁጥር ከንፈሯን በአውራ ጣቷና በአመልካች ጣቷ በቄንጥ የምትጠርግ ክፉ ባልቴት ነበረች፡፡የአባቴን ስም ያወጣችልኝ ግን እናቴ ናት፡፡ እናቴ አፀደ ! አቲዬ ነው የምላት (በዚህች ምድር ላይ ስሟ ላይ ዩ፥ ጨምሬ እቆላምጬ የምጠራት ብቸኛ ሰው እኔ ልጇ አሸብር ብቻ ነበርኩ፡፡)ደ
አንደኛ ከፍል እስከመዘገብ የአባት ስም አልነበረኝም፡፡ ልክ ትምህርት ቤት አቲዬ ወስዳኝ ስመዝነብ
ጉጉት የመሰለው መዝጋቢ እናቴን እያጣደፈ ጠየቃት፡፡ ድሪቶ ቀሚሷ በዓይኑ ቀፎት እያመናጨቀ
የእኔን ስም ጠየቃት፡፡ የንቀት አስተያየቱን፣ እናቴን ዝቅ የሚያደርግ የፊቱን ገፅታ አይቼዋለሁ በዚያው ድሪቶ ቀሚስ ስር በፍርሃት ተከልዬ.አይቼዋለሁ ቅንድብና ቅንድቡ እስኪነካኩ ሲጠጋጉ እናቴ ላይ ሲኮሳተር፡፡ ለራሷ ኑሮ የገላመጣት እናቴን ሲገላምጣት አይቼዋለሁ፡፡
አቲዩ አስመዝግባኝ ከፊቱ ዞር ስትል ፊቱን ጨፍግጎ መጥፎ ጠረን እንደሚያባርር ሰው ግራ እጁ አየሩን እያራገበ ሲያባርር አይቼዋለሁ፡፡ በእርግጥ አቲዩ እማማ የብርጓል ቤት እንኩሮ እያነኮረች ነበር፡፡ “ምዝገባው ዛሬ ነው የሚያልቀው“ ሲሏት ነው ብድግ ብላ ሳትለቃለቅ የመጣችው፡፡ ቢሆንስ ልክ ቆሻሻ እንደሸተተው ሰው ፊት እንዲያየው አድርጎ እጁን ያራግባል ? የእማማ የብርጓል ቁጥር አንድ የጠላ ደንበኛ እንዳልሆነ ሁሉ፣ አሻሮ ሸተተኝ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል ? ነብር አየው !! እንኳን ይህቺን አይቼ እንዲሁም ጥላቻ ጥላቻ ይለኛል፡፡ ያንን የውሻ ልጅ አስተማሪ እንደ ጠመድኩት
ጡረታ ወጣ !! ደግሞኮ አያፍርም መንገድ ላይ ሲያገኘኝ “የእኔ ተማሪ ነው!" እያለ በኩራት ያወራል።
“ስም ” አላት አቲዬን።
“የእኔን ነው ” አለች እየፈራች። ፈሪ ነበረች እናቴ፡፡ ፈሪው የአዲስ አበባ ሕዝብ እንደያቅሙ ደሀ ማስፈራራትን ተክኖበታል፡፡ በትእቢት ማከላፈቱ፣ በክፋት፣ በስድብና ዘለፋው እናቴን ፈሪ
በርጋጊ እድርጓታል፡፡
👍36👏1
"አንቺ ነሽ አንደኛ ክፍል የምትመዘገቢው ?” አላት፡፡ አጠገባችን ያሉት ሁሉ ሳቁለት፡፡ አቲዬ ተሳቀቀች፡፡ ሰውነቷ ሽምቅቅ ሊል ቍሚሷን አንቄ ተሰምቶኛል፤ የመሸማቀቋ ንዝረት እንደ ታላቅ
የመሬት ርዕደት ለእኔ ለልጇ ተሰምቶኛል። የሰዎቹ ሳቅ በፍርሀት ሲያንቀጠቅጣት ተሰምቶኛል፡
የአንድን ታዳጊ የፍቅር ሕንፃ የሚያፈርስ የመሬት መንቀጥቀጥ እናት የምትባል ሚስኪን ምድር
ላይ ሲነሳ በሳቅ የሚያጅቡ ጅሎች ዙሪያችንን እያሳዘኑ ነበር ፡፡
"የልጅሽን ስም ንገሪኝ ሴትዮ!” አላት ከከበበው ሰው የተበረከተለትን ሳቅ ካጣጣመ በኋላ፡፡
የእሱ….አ..ሸብር….አሸብር ነው ስሙ" አለች ራሴን እያሻሸት፡፡
"የአባት ስም ?”
"ያባት” ብላ ዝም አለች፡፡ አባቴን መንደርተኛው ሁሉ ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፡ ወኔ ቢኖረው ሁሉም በኀብረት እንደ መፈክር በአንድ ላይ የአባቴን ስም ሊጠራው ይችል ነበር፡፡ ግን እንደማያውቅ ሁሉ የአቲዩን አፍ በጉጉት ይመለከት ጀመረ፡፡
"የአባቱ ስም ማነው”
“ቀ" መጨረስ አልቻለችም ቀለመወርቅ!” ልትል ፈልጋ እንደነበር የገባኝ ካደግኩ በኋላ ነው፤ የዛሬዋ ደግሞ የጉድ ናት የልጇም አባት የሚጠፋት...” ብሎ እንደገና እንዲስቁለት ሰዎቹን
አየ፡፡ ያልደመቀ ሳቅ ሳቁለት፡፡ “በይ ወደዛ ሁኝ ስታስታውሺ ትመለሻለሽ ተረኛ ቀጥል!” አለ
እስክሪብቶውን እያወናጨፈ፡፡ እናቴ ከእንቅልፉ እንደባነነ ሰው፣ 'በአምላክ…በአምላክ ነው ያባቱ ስም አለች፡፡ ጎረቤቱ እርስ በእርሱ ትያያ፣ እንሾካሾከ፡፡ መዝጋቢው ራሱን ግራና ቀኝ በብስጨት እያወዛወዘ መዘገበኝ፡፡ ራስ የሚያስወዘውዝ ስንት ጉዳይ እያለ፣ አቲዬ የእኔንኔ አባት
ስም እፈአሰበች ብሎ ይሄን በአድሉዎ የተሞላ ራሱን ይንጣል፡፡ ብዙ ሰዎች አንድን ነገር በቀላሉ
ስለሚያግኙት ማንም ሰው በቀላሉ የሚያገኘው ይመስላቸዋል፤ ለምሳሌ አባት !
ከምዝገባ ስንመለስ አቲዬን ጠየቅኳት፣ "አባቴ ማነው?”፡፡ ደንግጣ አየችኝና አጥብቃ በያዘችኝ እጇ ወደ መንገዱ ዳር ሳብ አደረገችኝ፡፡ ከሩቅ የሚመጣ እኛ ካለንበት ነገም የሚደርስ የማይመስል የጭነት መኪና እንዳይገጨኝ፡፡ አቲዬ መኪና መንገድ ላይ ስሄድ መኪናው በእካል ባይደርስ እንኳን ድምፁ የሚገጨኝ ነው የሚመስላት፡፡ ትሳሳልኛለች
!!አባትህማ በአምላክ ነው….አምላክ” አለችኝ፡፡ አነጋገሯ የገጠር ተፅእኖ ይጫነዋል፡፡ በአምላከ የሚለው ስም ለራሷም ሳይገርማት አልቀረም ::
“የት ነው ያለው?"
"ሁሉም ቦታ"
የታለ ? ብዬ ዞር ዞር አልኩ፡፡
አይታይም ..እሉ ግን እኔና አንተን ያየናል፡ ችግር ካጋጠመን ከየት መጣ ሳይባል ከተፍ ይላል”
"ከተፍ"
"አዎ ከተፍ ድንገት” አለችኝ አቲዬ እልህ በተሞላበት ድምፅ:: እንዲህ ስትለኝ አባቴ ፖሊስ መሰለኝ፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ሲያወሩ "ፖሊስ ከትፍ ብሎ” ሊሉ እሰማ ነበር፡፡....
”አቲዬ!”
“ወይዩ!”
"አባቴ ልክ እንደ እግዚያቢር ነው?
“አዎ ቁርጥ እንደ እግዚያብሄር፡፡" በአባቴ ዝና ትንሽ ልቤ ይሞላል፡፡
“አቲዩ!"
“ወይ” ትንሽ ያሰላቸኋት ትመስላለች፡፡
“ከእግዚያብሔርና ከአባቴ ማን ይበልጣል ?”
እኩኩል ናቸው እኩል ትለኛለች።..
✨አላለቀም✨
የመሬት ርዕደት ለእኔ ለልጇ ተሰምቶኛል። የሰዎቹ ሳቅ በፍርሀት ሲያንቀጠቅጣት ተሰምቶኛል፡
የአንድን ታዳጊ የፍቅር ሕንፃ የሚያፈርስ የመሬት መንቀጥቀጥ እናት የምትባል ሚስኪን ምድር
ላይ ሲነሳ በሳቅ የሚያጅቡ ጅሎች ዙሪያችንን እያሳዘኑ ነበር ፡፡
"የልጅሽን ስም ንገሪኝ ሴትዮ!” አላት ከከበበው ሰው የተበረከተለትን ሳቅ ካጣጣመ በኋላ፡፡
የእሱ….አ..ሸብር….አሸብር ነው ስሙ" አለች ራሴን እያሻሸት፡፡
"የአባት ስም ?”
"ያባት” ብላ ዝም አለች፡፡ አባቴን መንደርተኛው ሁሉ ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፡ ወኔ ቢኖረው ሁሉም በኀብረት እንደ መፈክር በአንድ ላይ የአባቴን ስም ሊጠራው ይችል ነበር፡፡ ግን እንደማያውቅ ሁሉ የአቲዩን አፍ በጉጉት ይመለከት ጀመረ፡፡
"የአባቱ ስም ማነው”
“ቀ" መጨረስ አልቻለችም ቀለመወርቅ!” ልትል ፈልጋ እንደነበር የገባኝ ካደግኩ በኋላ ነው፤ የዛሬዋ ደግሞ የጉድ ናት የልጇም አባት የሚጠፋት...” ብሎ እንደገና እንዲስቁለት ሰዎቹን
አየ፡፡ ያልደመቀ ሳቅ ሳቁለት፡፡ “በይ ወደዛ ሁኝ ስታስታውሺ ትመለሻለሽ ተረኛ ቀጥል!” አለ
እስክሪብቶውን እያወናጨፈ፡፡ እናቴ ከእንቅልፉ እንደባነነ ሰው፣ 'በአምላክ…በአምላክ ነው ያባቱ ስም አለች፡፡ ጎረቤቱ እርስ በእርሱ ትያያ፣ እንሾካሾከ፡፡ መዝጋቢው ራሱን ግራና ቀኝ በብስጨት እያወዛወዘ መዘገበኝ፡፡ ራስ የሚያስወዘውዝ ስንት ጉዳይ እያለ፣ አቲዬ የእኔንኔ አባት
ስም እፈአሰበች ብሎ ይሄን በአድሉዎ የተሞላ ራሱን ይንጣል፡፡ ብዙ ሰዎች አንድን ነገር በቀላሉ
ስለሚያግኙት ማንም ሰው በቀላሉ የሚያገኘው ይመስላቸዋል፤ ለምሳሌ አባት !
ከምዝገባ ስንመለስ አቲዬን ጠየቅኳት፣ "አባቴ ማነው?”፡፡ ደንግጣ አየችኝና አጥብቃ በያዘችኝ እጇ ወደ መንገዱ ዳር ሳብ አደረገችኝ፡፡ ከሩቅ የሚመጣ እኛ ካለንበት ነገም የሚደርስ የማይመስል የጭነት መኪና እንዳይገጨኝ፡፡ አቲዬ መኪና መንገድ ላይ ስሄድ መኪናው በእካል ባይደርስ እንኳን ድምፁ የሚገጨኝ ነው የሚመስላት፡፡ ትሳሳልኛለች
!!አባትህማ በአምላክ ነው….አምላክ” አለችኝ፡፡ አነጋገሯ የገጠር ተፅእኖ ይጫነዋል፡፡ በአምላከ የሚለው ስም ለራሷም ሳይገርማት አልቀረም ::
“የት ነው ያለው?"
"ሁሉም ቦታ"
የታለ ? ብዬ ዞር ዞር አልኩ፡፡
አይታይም ..እሉ ግን እኔና አንተን ያየናል፡ ችግር ካጋጠመን ከየት መጣ ሳይባል ከተፍ ይላል”
"ከተፍ"
"አዎ ከተፍ ድንገት” አለችኝ አቲዬ እልህ በተሞላበት ድምፅ:: እንዲህ ስትለኝ አባቴ ፖሊስ መሰለኝ፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ሲያወሩ "ፖሊስ ከትፍ ብሎ” ሊሉ እሰማ ነበር፡፡....
”አቲዬ!”
“ወይዩ!”
"አባቴ ልክ እንደ እግዚያቢር ነው?
“አዎ ቁርጥ እንደ እግዚያብሄር፡፡" በአባቴ ዝና ትንሽ ልቤ ይሞላል፡፡
“አቲዩ!"
“ወይ” ትንሽ ያሰላቸኋት ትመስላለች፡፡
“ከእግዚያብሔርና ከአባቴ ማን ይበልጣል ?”
እኩኩል ናቸው እኩል ትለኛለች።..
✨አላለቀም✨
👍37😁9
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ሕይወት ለማሪየስ እየከበደች ሄደች:: ልብሶቹን ሽጦ እስከመብላት የሚያደርስ ችግር ገጠመው:: ችግሩ በጣም የጠናውና ጦም ውሎ ማደር
የመጣው የሚሸጠው ንብረት ሲያልቅበት ነበር፡፡ ደረቅ ዳቦ ጠፍቶ በባዶ ሆዱ ሲተኛ፧ ጠኔ እንቅልፍ አላስወስድ ብሎ ቁልጭ ብለው ሲያነጉ፤ መብራት ጠፍቶ በጨለማ ሲተራመሱ፧ ማንደጃ ላይ እንጨት ወይም ከሰል ጠፍቶ ብርድ ሲያንቀጠቅጥ፤ ያለሥራ ሌት ተቀን ሲቀመጡ፧ የወደፊት
ተስፋ ሲጨልም፧ ሱሪ ከቂጥ ላይ ሲቀደድ፧ በጭቅቅት የደለበና ቀዳዳ ያለበት ቆብ ሲያጠልቁ፤ የቤት ኪራይ ስላልከፈሉ በር ከውጭ ሲዘጋ፣ በዚሁ ሳቢያ ጎረቤት ሲሳለቅ፤ ሀፍረት አንገት ሲያስደፋ፤ ሰው ሁሉ እንደለማኝ ሲቆጥር፤ የሚያዝን ቢገኝ 'ምስኪን' እያለ ሲጠራ፤ ምሬት፧
ብስጭትና ንዴት ራስ ሲያዞር ነው የኑሮ ጉድ ፧ የኑሮ መከራ የሚታየውና እነ ምንዱባን መጡ የሚባለው::
ማሪየስ ይህ ዓይነት ሁኔታ ሲገጥም ምን እንደሚኮን ከደረሰበት አጋጣሚ ትምህርት ቀሰመ:: አንገት ከመድፋት በስተቀር ሌላ ምርጫ
እንደሌለው አወቀ፡፡ ሆኖም የሚያሳዝነው የዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲገጥም ሰው በተፈጥሮው የሚመኛቸው እንደክብርና ፍቅር የመሳሰሉትን ነገሮች ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን በስውር ሕሊናው ልብሱ ስለተቀዳደደና ስላደፈ ሰዎች
የሚያሾፉበት፤ ድሃ በመሆኑ ሰዎች የሚሳለቁበት ይመስለዋል፡፡ ማሪየስ በወጣትነት ዘመኑ ከዚህ ዓይነት ፈተና ውስጥ በመውደቁ ያደረገው ቦት ጫማ ማለቅና መቆሸሽ ዓይኑን ዘቅዘቅ አድርጎ ያያል፡፡ በአጠቃላይ ያለበትን
ሁናቴ ያጤናል:: ፈተናው ደካሞች ስማቸው የሚጠፋበት ፤ ብርቱዎች በህፍረት ማቅ ተንነው የሚጠፉበት መሆኑን ይገነዘባል፡፡
በፈተና ጊዜ ከፈተናው ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ሳይታወቅ ብዙ ጠቃሚ ነገር ይሠራል:: ጉልህ ሆኖ የማይታይ ጉብዝና ይከሰታል፡፡
ሕይወት፤ መጥፎ አጋጣሚ ብቸኝነት መረሳት ድህነትና ሌሎችም የኑሮ ጦር ሜዳዎች ሲሆኑ እያንዳንዳቸው የተሰወሩ ጀግናዎች ናቸው::አንዳንዴም ከእውነተኛው የጦር ሜዳ ጀግና የላቁ ይሆናሉ::
በችግር አለንጋ ተፈትነው የሚወጡ ጀግኖች ጥቂቶች ናቸው::ሆኖም ለጀግንነታቸው ድንበር የለውም:: መከፋት ግላዊ ክብርን እንደሚንከባከብ ሁሉ መጥፎ አጋጣሚም ጡት አጥብቶ ያሳድገዋል፡፡ ‹‹ችግር ብልሃትን ይፈጥራል» ይባል የለ፡፡
ማሪየስ ያሳለፈው ሕይወት ከዚህ የራቀ አልነበረም፡፡ ቤቱን ራሱ ነበር የሚወለውለው:: ቀለቡን በብር ሳይሆን በሳንቲም ነበር የሚገዛው::ቀለቡን ለመግዛት ሴቶች እንጂ ወንዶች ከማይሄዱበት ሲሄድ ሰውነቱ
እየተሸማቀቀ ነበር:: ጨለማን ተገን በማድረግ ነበር ብዙውን ሥራ የሚሠራው:: በሣንቲም የገዛውን አነስተኛ ቀለብ ራሱ እየቀቀለ ለሦስትና ለአራት ቀን ነበር ቆጥቦ የሚበላው::
አያቱ ባዘዙት መሠረት አክስቱ በየወሩ ብር ብትልክለትም
ገንዘቡን ሳያመነታ ይመልስላታል፡፡ ሲመልስላት አልቸገረኝም እያለ ነበር የሚጽፍላት::
ማሪየስ የአባቱን ሀዘን አልጨረሰም:: አሁንም ቢሆን በአንድ ወቅት ትቶት የነበረውን ጥቁር ጨርቅ ልብሱ ላይ አድርጎአል፡፡ ግን የነበረው ልብስ ሁሉ እያለቀ በመሄዱ ጥቁር ጨርቅ የሚለጥፍበትም ኮት አለቀ:: የሚቀይረው ሌላ ኮት የለውም:: ሱሪዎቹም ተቀዳደዱ:: ጓደኛው ኩርፌይሪክ እስካሁን የዋለለት ውለታ አንሶ ጨርሶ መራቆቱን ስላየ አሮጌ
ኮቱን ሰጠው::
ማሪየስ ትምህርቱን ጨርሶ የሕግ ባለሙያ በሆነ ጊዜ ለአያቱ ይህን
በመግለጽ ደብዳቤ ጻፈላቸው:: አያቱ እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ደብዳቤውን አነበቡት፡፡ ከዚያም ቀዳድደው ከመሬት ጣሉት፡፡ ከሁለት ወይም ከሦስት ወር
ቀን በኋላ አያቱ ክፍላቸው ውስጥ ብቻቸውን ሲነጋገሩ አክስቱ ይሰማሉ:: ሽማግሌው ነገር ሲገባቸው የሚያደርጉት ልምድ ነው:: «ቂል ሰው ባትሆን ኖሮ አንድ ሰው ባንድ ጊዜ ባሮንና የሕግ ባለሙያ ሊሆን እንደማይችል ታውቅ ነበር» ብለው ሲናገሩ ነው የሰማቻቸው::
ችግር እንደ ማንኛውም የመጥፎ ነገር ውጤት በዝግታ አንድ ዓይነት
ቅርፅ አውጥቶ ይለምዱታል:: ከዚያም ቁሞ ለመሄድ የሚያስችል የኑሮ ፈር ይቀድዳል:: ለዚህ ነው ብዙ ችግረኞች ኑሮን ኖርን የሚሉት፧ ቆሞ መሄድ መኖር ከሆነ:: በዚህ ዓይነት ነበር የማሪየስ ፓንትመርሲም ኑሮ
የተመሠረተው::
ማሪየስ ለመኖር ባደረገው ጥረት ከጨለማ ወደ ጭላንጭል ለመሸጋገር ችሎ በዓመት ወደ ሰባት መቶ ፍራንክ ማግኘት ቻለ፡፡
የጀርመንኛና እንግሊዘኛ ቋንቋን አጠና፡፡ ኩርፌይራክ ከመጽሐፍ አሳታሚ ድርጅቶች ጋር ስላስተዋውቀውና ቀን ከሌሊት ሳይል የትርጉም ሥራ ስለሠራ ነበር ያንን ሰባት መቶ ፍራንክ ለማግኘት የቻለው፡፡ ይህ ገንዘብ ቆሞ ለመሄድ የሚያስችል ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ከዚያ የተሻለ ነኑሮ
የሚያኖር ነበር።
በዓመት ለቤት ኪራይ ሰላሣ ፍራንክ፣ በየወሩ ሦስት ፍራንክ ክፍሉን ለሚያጸዱለት ሴት ይከፍላል፡፡ ከዚህችም ገንዘብ እንደነገሩ ቁርስ ይሠሩለታል፡፡ በዓመት ወደ ሦስት መቶ ስልሣ አምስት ፍራንክ ለአንዲት )
እራት ለሚያዘጋጁለት ሴት ይሰጣል፡፡ ለልብሱና ለሌሎች ልዩ ልዩ ወጪዎች ወደ ሁለት መቶ ሃምሣ ፍራንክ ገደማ ያወጣል:: በዚህ ዓይነት ማንኛውንም ወጪ ችሎ በዓመት ወደ ሃምሣ ፍራንክ ይተርፈዋል:: ይህም ሀብታም የሚያሰኝ ነበር፡፡ እስከናካቴው እስከ አስር ፍራንክ የሚደርስ ገንዘብ ለጓደኞቹ ያበድራል:: አንድ ሰሞን ጓደኛው ኩርፌይራክ ስልሣ ፍራንክ ተበድሮታል።
ማሪየስ ሁለት ዓይነት ልብሶች ነበሩት፤ አንድ የዘወትር ሌላው
የክት፡፡ ሁለቱም ልብሶች ቀለማቸው ጥቁር ነበር፡፡ ሦስት ሸሚዞች ነበሩት:: አንዱን ሲለብሰው ሌላውን ለመቀየሪያ መሳቢያ ውስጥ ያስቀምጠዋል፡፡
ሶስተኛውን ለአጣቢ ይሰጣል፡፡ ቶሎ ያለቀው በአዲስ ይተካዋል፡፡
ሆኖም ብዙውን ጊዜ ሸሚዞቹ ቀዳዳ ስለማያጡ ያንን ለመደበቅ ኮቱን እስከ አንገቱ ነበር የሚቆልፈው::
ማሪየስ ለዚህ ማዕረግ የበቃው ከብዙ ዓመታት ስቃይና መከራ በኋላ ነበር በስንት ትግል፤ በስንት መከራና ስቃይ የታለፉ ዘመናት ፤ ከድንጋይ የከበዱ ዓመታት! ማሪየስ ግን ለአንድ ቀን እንኳን በዚህ ችግር አልተፈታም፤
ተጋተረው እንጂ እጁን አልሰጠም፤ ከዚህ ችግር ለመላቀቅ ብድር ከመበደር በስተቀር ያልፈጸመው ተግባር፧ ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም፡፡ የሰው
እዳ አምስት ሣንቲም አልነበረበትም፡፡ ቢያሻው ጦሙን ውሎ ጦሙን ያድራል እንጂ ሰው አያስቸግርም፤ ብድር አይጠይቅም:: ብድር የባርነት
መጀመሪያ መሆኑን ያውቃል፡፡ ባርነት እኮ በገንዘብ መሸጥ ብቻ አይደለም::አበዳሪ ከጌታ የከፋ መሆኑን ያምናል፡፡
ጌታ አንተነትህን ነው የሚገዛው:: አበዳሪ ግን አንተን ብቻ ሳይሆን
የሚገዛው ክብርህንም ጭምር ስለሆነ ከሰው ፊት ያስጨንቅሃል፤ ነፍስህንም ያሳድዳታል፡፡ ለዚህ ነበር ማሪየስ እዳ ከመግባት ለብዙ ቀናት በተከታታይ
ጦም ማደሩን የመረጠው:: ካልተጠነቀቅን፤ የሕይወትን አስቸጋሪ ዘመን ካላሳለፍን ሥጋችን ብቻ ሳይሆን ነፍሳችንም ጭምር የባለሀብቶች ባርያ ትሆናለች፡፡ ለዚህ ነበር ማሪየስ ክብሩን በቅናት ዓይን እያየ የጠበቃት::ለዚህ ነበር በዓይነ ህሊና ወደኋላ ተመልሶ ሲያዩት የሚያጸጽት ሥራ ለመስራት ያልደፈረው።
ከደረሰበት የኑሮ ፈተና አዲስ ኃይል ፤ አዲስ ጉልበት ለማግኘት
ተጣጣረ እንጂ አልተማረረም:: የዚህ ዓይነት እምነት ካለን ነፍሳችን ሥጋችንን ትገፋፋለች:: ወፍ እኮ የራስዋን ጎጆ ቀይሳና ተንከባክባ ነው የምትኖረው።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ሕይወት ለማሪየስ እየከበደች ሄደች:: ልብሶቹን ሽጦ እስከመብላት የሚያደርስ ችግር ገጠመው:: ችግሩ በጣም የጠናውና ጦም ውሎ ማደር
የመጣው የሚሸጠው ንብረት ሲያልቅበት ነበር፡፡ ደረቅ ዳቦ ጠፍቶ በባዶ ሆዱ ሲተኛ፧ ጠኔ እንቅልፍ አላስወስድ ብሎ ቁልጭ ብለው ሲያነጉ፤ መብራት ጠፍቶ በጨለማ ሲተራመሱ፧ ማንደጃ ላይ እንጨት ወይም ከሰል ጠፍቶ ብርድ ሲያንቀጠቅጥ፤ ያለሥራ ሌት ተቀን ሲቀመጡ፧ የወደፊት
ተስፋ ሲጨልም፧ ሱሪ ከቂጥ ላይ ሲቀደድ፧ በጭቅቅት የደለበና ቀዳዳ ያለበት ቆብ ሲያጠልቁ፤ የቤት ኪራይ ስላልከፈሉ በር ከውጭ ሲዘጋ፣ በዚሁ ሳቢያ ጎረቤት ሲሳለቅ፤ ሀፍረት አንገት ሲያስደፋ፤ ሰው ሁሉ እንደለማኝ ሲቆጥር፤ የሚያዝን ቢገኝ 'ምስኪን' እያለ ሲጠራ፤ ምሬት፧
ብስጭትና ንዴት ራስ ሲያዞር ነው የኑሮ ጉድ ፧ የኑሮ መከራ የሚታየውና እነ ምንዱባን መጡ የሚባለው::
ማሪየስ ይህ ዓይነት ሁኔታ ሲገጥም ምን እንደሚኮን ከደረሰበት አጋጣሚ ትምህርት ቀሰመ:: አንገት ከመድፋት በስተቀር ሌላ ምርጫ
እንደሌለው አወቀ፡፡ ሆኖም የሚያሳዝነው የዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲገጥም ሰው በተፈጥሮው የሚመኛቸው እንደክብርና ፍቅር የመሳሰሉትን ነገሮች ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን በስውር ሕሊናው ልብሱ ስለተቀዳደደና ስላደፈ ሰዎች
የሚያሾፉበት፤ ድሃ በመሆኑ ሰዎች የሚሳለቁበት ይመስለዋል፡፡ ማሪየስ በወጣትነት ዘመኑ ከዚህ ዓይነት ፈተና ውስጥ በመውደቁ ያደረገው ቦት ጫማ ማለቅና መቆሸሽ ዓይኑን ዘቅዘቅ አድርጎ ያያል፡፡ በአጠቃላይ ያለበትን
ሁናቴ ያጤናል:: ፈተናው ደካሞች ስማቸው የሚጠፋበት ፤ ብርቱዎች በህፍረት ማቅ ተንነው የሚጠፉበት መሆኑን ይገነዘባል፡፡
በፈተና ጊዜ ከፈተናው ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ሳይታወቅ ብዙ ጠቃሚ ነገር ይሠራል:: ጉልህ ሆኖ የማይታይ ጉብዝና ይከሰታል፡፡
ሕይወት፤ መጥፎ አጋጣሚ ብቸኝነት መረሳት ድህነትና ሌሎችም የኑሮ ጦር ሜዳዎች ሲሆኑ እያንዳንዳቸው የተሰወሩ ጀግናዎች ናቸው::አንዳንዴም ከእውነተኛው የጦር ሜዳ ጀግና የላቁ ይሆናሉ::
በችግር አለንጋ ተፈትነው የሚወጡ ጀግኖች ጥቂቶች ናቸው::ሆኖም ለጀግንነታቸው ድንበር የለውም:: መከፋት ግላዊ ክብርን እንደሚንከባከብ ሁሉ መጥፎ አጋጣሚም ጡት አጥብቶ ያሳድገዋል፡፡ ‹‹ችግር ብልሃትን ይፈጥራል» ይባል የለ፡፡
ማሪየስ ያሳለፈው ሕይወት ከዚህ የራቀ አልነበረም፡፡ ቤቱን ራሱ ነበር የሚወለውለው:: ቀለቡን በብር ሳይሆን በሳንቲም ነበር የሚገዛው::ቀለቡን ለመግዛት ሴቶች እንጂ ወንዶች ከማይሄዱበት ሲሄድ ሰውነቱ
እየተሸማቀቀ ነበር:: ጨለማን ተገን በማድረግ ነበር ብዙውን ሥራ የሚሠራው:: በሣንቲም የገዛውን አነስተኛ ቀለብ ራሱ እየቀቀለ ለሦስትና ለአራት ቀን ነበር ቆጥቦ የሚበላው::
አያቱ ባዘዙት መሠረት አክስቱ በየወሩ ብር ብትልክለትም
ገንዘቡን ሳያመነታ ይመልስላታል፡፡ ሲመልስላት አልቸገረኝም እያለ ነበር የሚጽፍላት::
ማሪየስ የአባቱን ሀዘን አልጨረሰም:: አሁንም ቢሆን በአንድ ወቅት ትቶት የነበረውን ጥቁር ጨርቅ ልብሱ ላይ አድርጎአል፡፡ ግን የነበረው ልብስ ሁሉ እያለቀ በመሄዱ ጥቁር ጨርቅ የሚለጥፍበትም ኮት አለቀ:: የሚቀይረው ሌላ ኮት የለውም:: ሱሪዎቹም ተቀዳደዱ:: ጓደኛው ኩርፌይሪክ እስካሁን የዋለለት ውለታ አንሶ ጨርሶ መራቆቱን ስላየ አሮጌ
ኮቱን ሰጠው::
ማሪየስ ትምህርቱን ጨርሶ የሕግ ባለሙያ በሆነ ጊዜ ለአያቱ ይህን
በመግለጽ ደብዳቤ ጻፈላቸው:: አያቱ እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ደብዳቤውን አነበቡት፡፡ ከዚያም ቀዳድደው ከመሬት ጣሉት፡፡ ከሁለት ወይም ከሦስት ወር
ቀን በኋላ አያቱ ክፍላቸው ውስጥ ብቻቸውን ሲነጋገሩ አክስቱ ይሰማሉ:: ሽማግሌው ነገር ሲገባቸው የሚያደርጉት ልምድ ነው:: «ቂል ሰው ባትሆን ኖሮ አንድ ሰው ባንድ ጊዜ ባሮንና የሕግ ባለሙያ ሊሆን እንደማይችል ታውቅ ነበር» ብለው ሲናገሩ ነው የሰማቻቸው::
ችግር እንደ ማንኛውም የመጥፎ ነገር ውጤት በዝግታ አንድ ዓይነት
ቅርፅ አውጥቶ ይለምዱታል:: ከዚያም ቁሞ ለመሄድ የሚያስችል የኑሮ ፈር ይቀድዳል:: ለዚህ ነው ብዙ ችግረኞች ኑሮን ኖርን የሚሉት፧ ቆሞ መሄድ መኖር ከሆነ:: በዚህ ዓይነት ነበር የማሪየስ ፓንትመርሲም ኑሮ
የተመሠረተው::
ማሪየስ ለመኖር ባደረገው ጥረት ከጨለማ ወደ ጭላንጭል ለመሸጋገር ችሎ በዓመት ወደ ሰባት መቶ ፍራንክ ማግኘት ቻለ፡፡
የጀርመንኛና እንግሊዘኛ ቋንቋን አጠና፡፡ ኩርፌይራክ ከመጽሐፍ አሳታሚ ድርጅቶች ጋር ስላስተዋውቀውና ቀን ከሌሊት ሳይል የትርጉም ሥራ ስለሠራ ነበር ያንን ሰባት መቶ ፍራንክ ለማግኘት የቻለው፡፡ ይህ ገንዘብ ቆሞ ለመሄድ የሚያስችል ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ከዚያ የተሻለ ነኑሮ
የሚያኖር ነበር።
በዓመት ለቤት ኪራይ ሰላሣ ፍራንክ፣ በየወሩ ሦስት ፍራንክ ክፍሉን ለሚያጸዱለት ሴት ይከፍላል፡፡ ከዚህችም ገንዘብ እንደነገሩ ቁርስ ይሠሩለታል፡፡ በዓመት ወደ ሦስት መቶ ስልሣ አምስት ፍራንክ ለአንዲት )
እራት ለሚያዘጋጁለት ሴት ይሰጣል፡፡ ለልብሱና ለሌሎች ልዩ ልዩ ወጪዎች ወደ ሁለት መቶ ሃምሣ ፍራንክ ገደማ ያወጣል:: በዚህ ዓይነት ማንኛውንም ወጪ ችሎ በዓመት ወደ ሃምሣ ፍራንክ ይተርፈዋል:: ይህም ሀብታም የሚያሰኝ ነበር፡፡ እስከናካቴው እስከ አስር ፍራንክ የሚደርስ ገንዘብ ለጓደኞቹ ያበድራል:: አንድ ሰሞን ጓደኛው ኩርፌይራክ ስልሣ ፍራንክ ተበድሮታል።
ማሪየስ ሁለት ዓይነት ልብሶች ነበሩት፤ አንድ የዘወትር ሌላው
የክት፡፡ ሁለቱም ልብሶች ቀለማቸው ጥቁር ነበር፡፡ ሦስት ሸሚዞች ነበሩት:: አንዱን ሲለብሰው ሌላውን ለመቀየሪያ መሳቢያ ውስጥ ያስቀምጠዋል፡፡
ሶስተኛውን ለአጣቢ ይሰጣል፡፡ ቶሎ ያለቀው በአዲስ ይተካዋል፡፡
ሆኖም ብዙውን ጊዜ ሸሚዞቹ ቀዳዳ ስለማያጡ ያንን ለመደበቅ ኮቱን እስከ አንገቱ ነበር የሚቆልፈው::
ማሪየስ ለዚህ ማዕረግ የበቃው ከብዙ ዓመታት ስቃይና መከራ በኋላ ነበር በስንት ትግል፤ በስንት መከራና ስቃይ የታለፉ ዘመናት ፤ ከድንጋይ የከበዱ ዓመታት! ማሪየስ ግን ለአንድ ቀን እንኳን በዚህ ችግር አልተፈታም፤
ተጋተረው እንጂ እጁን አልሰጠም፤ ከዚህ ችግር ለመላቀቅ ብድር ከመበደር በስተቀር ያልፈጸመው ተግባር፧ ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም፡፡ የሰው
እዳ አምስት ሣንቲም አልነበረበትም፡፡ ቢያሻው ጦሙን ውሎ ጦሙን ያድራል እንጂ ሰው አያስቸግርም፤ ብድር አይጠይቅም:: ብድር የባርነት
መጀመሪያ መሆኑን ያውቃል፡፡ ባርነት እኮ በገንዘብ መሸጥ ብቻ አይደለም::አበዳሪ ከጌታ የከፋ መሆኑን ያምናል፡፡
ጌታ አንተነትህን ነው የሚገዛው:: አበዳሪ ግን አንተን ብቻ ሳይሆን
የሚገዛው ክብርህንም ጭምር ስለሆነ ከሰው ፊት ያስጨንቅሃል፤ ነፍስህንም ያሳድዳታል፡፡ ለዚህ ነበር ማሪየስ እዳ ከመግባት ለብዙ ቀናት በተከታታይ
ጦም ማደሩን የመረጠው:: ካልተጠነቀቅን፤ የሕይወትን አስቸጋሪ ዘመን ካላሳለፍን ሥጋችን ብቻ ሳይሆን ነፍሳችንም ጭምር የባለሀብቶች ባርያ ትሆናለች፡፡ ለዚህ ነበር ማሪየስ ክብሩን በቅናት ዓይን እያየ የጠበቃት::ለዚህ ነበር በዓይነ ህሊና ወደኋላ ተመልሶ ሲያዩት የሚያጸጽት ሥራ ለመስራት ያልደፈረው።
ከደረሰበት የኑሮ ፈተና አዲስ ኃይል ፤ አዲስ ጉልበት ለማግኘት
ተጣጣረ እንጂ አልተማረረም:: የዚህ ዓይነት እምነት ካለን ነፍሳችን ሥጋችንን ትገፋፋለች:: ወፍ እኮ የራስዋን ጎጆ ቀይሳና ተንከባክባ ነው የምትኖረው።
👍18
ማሪየስ ሃያ ዓመት ሞላው:: የአያቱን ቤት ለቅቆ ከወጣ ሶስት
ዓመት አለፈ፡፡ ሁለቱም ወገን እጃቸውን ሳይሰጡ በእምነታቸው
ጸንተውና ለእርቅ ሳያጎበድዱ ነበር ዓመታቱ ያለፉት፡፡ አልተፈላለጉም፤ ለመጣላት ምን አፈላለጋቸው
እንደ እውነቱ ከህን ፧ ማሪየስ ስለአያቱ በነበረው አመለካከት ተሳስቷል በእርሱ አመለካክት አያቱ፡ መሳይ ጊልኖርማንድ ጨርሰው አይወዱትም
«ይህ ጠናዛ ሽማግሌ፣ አንዳንዴ እኔን ሲያይ ፊቱን ፈካ የሚያደርገው እወድሃለሁ ብሎ የሚምለውና የሚገዘተው በውሸት ነው» ይላል:: አዝህ ላይ እጅግ ተሳስቷል፡፡ ልጁን የማይወድ አባት ሊኖር ይችላል፡፡ የልጅ ልጁን የማያደንትቅና የማይወድ አያት ግን የለም:: መሴይ ጊልኖርማን
ማሪየስን እንደ አምላክ ነበር የሚያመልኩት:: ልባቸው በእርሱ ፍቅር ተሞልቷል፡፡ ማሪየስ ከቤት ወጥቶ በሄደ ጊዜ ቤቱ ወና፤ ልባቸው ባዶ ቀፎ ሆኖ ቀርቷል፡፡ ከቤታቸው ወጥቶ እንደሄደ ማንም ሰው ስለዚህ ልጅ
እንዳያነሳብኝ» ብለው የሰጡት ትእዛዝ መከበር አስቆጫቸው:: በመጀመሪ ይህ የቦናፖርቴ ተከታይ፤ ይህ ሽብር ፈጣሪ፤ ይህ ረባሽ ሲቸግረው ተመልሶ
ይመጣል» የሚል እምነት ነበራቸው:: ግን ሣምንታት፤ ወራት፧ ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ «ደም መጣጩ ልጅ» ባለመመለሱ መሴይ ጊልኖርማን ተስፋ ቆረጡ፡፡ «ከማባረር ሌላ እርምጃ በወሰድሁ» ሲሉ ተጸጸቱ። ያ ውሳኔ እንደገና የሚፈጸም ቢሆን አሁን አደርገው ነበር?» ሲሉ ራሳቸውን
ጠየቁ፡፡ ክብራቸው «አዎን» ብሎ ሲመልስ የሽማግሌ ጭንቅላታቸው ግን «የለም» በማለት ከወዲያ ወዲህ ተነቃነቀ፡፡
ልጁን በጣም ናፈቁት::
ሽማግሌዎች ፀሐይ ብርሃንን እንደሚሹ ሁላ! የልጆቻቸውንም ፍቅር ይፈልጋሉ፡፡ ፍቅራቸው ያሞቃቸዋል፡፡ መሴይ
ጊልኖርማንድ ብርቱ ሰው ቢሆኑም የማሪየስ ከቤታቸው መጥፋት አንድ ዓያነት ድክመት አሳደረባቸው:: ሆኖም ይህን ወሮበላ» ለመፈለግ አንድ
እርምጃ እንኳን ወደ ፊት አልተራመዱም:: ነገር ግን በጣም ተሰቃዩ ያስቡታል ግን አይፈልጉተም፡፡ ይመኙታል ግን ሊያዩት አይፈልጉም፡፡ ያ ሳቁ፤ ፈገግታው፧ ጨዋታው ፧ ትህትና ከፊታቸው ድቅን ይላል:: «ወይ ጉድ! አሁንስ በመጣና የፈለገውን ባደረግሁት» ይላሉ በልባቸው:: ሳይመጣ ሲቀር ሰውነታቸው ይዝላል።
አክስቱስ! እርስዋማ ለፍቅር ብዙም የማትጨነቅ ሴት ነበረች፡፡
ለእርስዋ ማሪየስ ማለት በጭላንጭል የሚታይ ብርሃን ነው:: እርሱን አሰላስለ በመጨነቅ ከድመት ጋር መጫወት ትመርጣለችካ.ጋትን ትመርጣለች:: የአያቱ የጊልኖርማድል የምሥጢር ስቃይ ያባባሰው ስለማሪየስ ሁለተኛ እንዳታነሣ የስጥዋት ትእዛዝ ነበር፡፡ ድንገት ከውጭ የመጣ ሰው ከማሪየስ አክስት ፊት «ያ ልጅዎ ምን በላው? የት ነው ያለው? ምን ይሠራል?» ተብላ የተጠየቀች እንደሆነ የኛ ባሮንማ የነገር ቀዳዳ ሲያገኝ የሕግ ሰው ነውና
እርሱን እየጠቀመ ነዋ ያለው» ስትል ትመልሳለች::
ሽማግሌው በጸጸት ሲነዱ ማሪየስ ግን የሕሊና እረፍት አግኝቶ ደስ
ብሎት ነበር የሚኖረው:: ያሳለፈው የመከራና የፈተና ዘመን የወደፊት
ህይወቱን ሞረደለት፡፡ ብረት በእሳት ይፈተናል እንዲሉ ማሪየስም በችግር ተፈትኖ ፈተናውን አለፈ፡፡ በልጅነት የሚደርስ ችግርና ድኅነት የወደፊት ኑሮን የማሻሻልና ታግሎ የመወጣት ዝንባሌን አሳድሮ በሕይወት ዘመን የልብ አሸናፊነትን ያጎናጽፋል። ድኅነት ያልጨበጡትን ለመጨበጥ ጉጉት ይፈጠርና ሐሞተ ቆራጥ ያደርጋል፡፡ ይህም ከጥሩ ደረጃ ያደርሳል፡፡
የሀብታም ልጅ አእምሮ ተደስቶ ለመኖር ይፈልግና በልጅነት ዘመኑ
ባዶ አእምሮው በፈረስ ግልቢያ፧ በአደን፣ ሲጃራ በማብነን፧ በዳንኪራ፤ ግብር በማግባት ፣ በፍቶተ ሥጋና በመሳሰሉት ይጠመዳል:: ሌላ የሚመኘው
ነገር አይኖርም:: የድሃ ልጅ ግን የእለት እንጀራውን ለማግኘት መሥራት አለበት:: የእለት እንጀራውን ካገኘ ያቺን ይበላል:: በዚህም ይደሰታል፡፡ ዓመታት ከተፈጥሮ ጋር የቅርብ ግንኙነት ስላለው ያንን ያደንቃል:: በሰዎች መካከል ስለሚሰቃይ የሰዎች ስቃይ ያስጨንቀዋል:: በላቡና በወዙ የሚበላውን ዳቦ በማፍራቱ ታግሎ መውጣትና የትልቅነት ስሜት ያድርበታል:: የስቃይ ብዛት ከሚፈጥረው ራስን የመቻል ፍላጐት ከመጨነቅ ወደ ማሰብ፣ ከማሰብ ችግሩ ደግሞ ራስን የመውደድ ስሜት ስለሚያሳድርበትና ለራሱም
ወደ መፈላሰፍ ስለሚያሸጋግረው የማወቅና የመማር ስሜት ይቀረጽበታል፡፡
ችግሩ ደሞ ራስን የመውደድ ስሜት ስለሚያሳድርበት
ለራሱም ስለሚያዝን የበለጠ ነገር ለማግኘት ይጥራል:: ይህም ችግር ከጫንቃው ሲወርድለት ራሱን እየረሳ ለተቸገረ ሁሉ ማዘን ይጀምራል፡፡ መንፈሳቸውን
ላቀነና ሕይወትን በፀጋ ለተቀበሉ ተፈጥሮ ደስታ እንደሚለግሳቸው
ለተደፈኑ ነፍሳትም ደስታ ይነሳቸዋል:: የአሳብና የእውቀት ሀብታም የሆኑት ለ።ጥሬ ገንዘብ ሀብታሞች ያዝናሉ:: የአሳብ ባለፀጋ ጥላቻን ከልቡ ሲፍቅ
የተስፋ ብርሃን ሕሊናውን ሰንጥቆ ይገባል:: ታዲያ ይህን ጊዜ ይከፋዋል ወይስ አይከፋውም?
የወጣትነት ስቃይ እውነተኛ ስቃይ አይባልም:: አንድ ወጣት የገንዘብ
ድሃ ሊሆን ይችላል፤ ግን ጤናው ፤ ጉልበቱ ፣ ፈጣን እርምጃው፣ የሚያበሩ ዓይኖቹ፤ የሚያሞቀው ደሙ፧ ወለላ ከንፈሩ፤ ከወተት የነጡ ጥርሶቹ ፤ ንጹህ ትንፋሹ ሁሉ የሚያስቀኑ በመሆናቸው የጨረጨሰ ንጉሥ ይቀናበታል::
ይህም በመሆነ ነው ማሪየስ በየቀኑ ጠዋት ጠዋት ሳይታክተው የእለት እንጀራውን ፍለጋ የወጣው:: በእጆቹና በአእምሮው ተጠቅሞ ለእለት እንጀራው ሲሠራ ጀርባው እየበረታና እየጠነከረ አእምሮው በአሳብ እየተሞላ
ሄደ:: ሥራውን ሲጨርስ መመራመሩን ቀጥሎ እግሩ ለእንቅፋት፤ ለእሾህ አንዳንዴም ለጭቃ መጋለጡንና አእምሮው ግን በብርሃን መከበቡን አመነ።
መንፈሰ-ቆራጥ፧ ረጋ ያለ ጭምት ወጣት ከመሆኑም በላይ በጣም ጨዋ፧ሀብታሞች የሌላቸውንና ነፃነት ያጎናጸፈውን ጤነኛ ጉልበትንና ጨዋነትን ያስገኘለት ምርምርን ስለሰጠው ጠዋት ማታ ፈጣሪውን አመሰገነ።
ማሪየስ ሁለት ጓደኞች ነበሩት፡: እነርሱም ወጣቱ ኩርፌይራክና
ሽማግሌው ማብዩፍ ናቸው።
ሽማግሌውን በይበልጥ ያቀርቡታል፡፡ ለዚህም ምክንያት ነበረው:: ማብዩፍ የማሪየስን አባት የሚያውቁና የሚወዱ ሰው
ናቸው:: በአጋጣሚ ነው አባቱ ስለቆመለት ዓላማና እርሱም ማን እንደነበር መሴይ ማብዩፍ ያጫወቱት::
መሴይ ማብዩፍ ፖለቲካ ብዘም አይወዱም:: የእርሳቸው ፖለቲካ ስለተክልና ስለመጻሕፍት ያላቸው ፍቅር ነው:: በዓለም ላይ ብዙ በሚደነቁ እንደ ዛፎች ማደግ፤ እንደ ኣበባ መፈንዳት እንደ ሳር መለምለምና እንደ ጽጌረዳ ማማር በመሳሰሉ ነገሮች ላይ ጊዜ እንደማጥፋት ሰዎች ስለሕዝባዊ ወይም ስለንጉሣዊ አገዛዝ፤ ስለሪፑብሊክ፤ ስለሕጋዊ አልጋ ወራሽና ስለመሳሰሉት ነገሮች በመጨቃጨቅ ጊዜ ማጥፋታቸው ይገርማቸዋል።እኚህ ሰው ሰዎችን ሲያፈቅሩ ሁካታቸውን ይጠላሉ:: ሰዎች ቤተክርስቲያን ውስጥ ስለማይነጫጩና ከዚያ ሥፍራ የመንፈስ እረፍት ስለሚገኝ ወደዚያ አካባቢ መሄድን ያዘወትራሉ:: ራሳቸውን የሚያስተዳድሩት ከአንዲት ከደረሱት መጽሐፍ ሽያጭ በሚገኝ ገቢ ሲሆን በዓመት እስከ ሁለት ሺህ ፍራንክ ያገኛሉ:: በጣም የሚያቀርቡት ወዳጅ መጽሐፍ ሲሆን መሴይ ማብዩፍ ምርጥ
ምርጥ መጻሕፍትን መሰብሰብ ይወዳሉ፡፡
እኚህ ሰው ከእርሳቸው በየዋህነት የማይተናነሱ የሴት ሠራተኛ
ነበርዋቸው:: ሴትዮዋ በየሳምንቱ እሑድ ከቤተክርስቲያን መልስ ጊዜያቸውን የሚያጠፉት በየጊዜው እየገዙ ያጠራቀሙትን ልብስ በመቀጠርና በማገላበጥ
ነበር:: እኚህ ሴት ማንበብ ስለሚችሉ አልፎ አልፎ የመሴይ ማብዩፍን መጻሕፍት ያነብባሉ፡፡
ዓመት አለፈ፡፡ ሁለቱም ወገን እጃቸውን ሳይሰጡ በእምነታቸው
ጸንተውና ለእርቅ ሳያጎበድዱ ነበር ዓመታቱ ያለፉት፡፡ አልተፈላለጉም፤ ለመጣላት ምን አፈላለጋቸው
እንደ እውነቱ ከህን ፧ ማሪየስ ስለአያቱ በነበረው አመለካከት ተሳስቷል በእርሱ አመለካክት አያቱ፡ መሳይ ጊልኖርማንድ ጨርሰው አይወዱትም
«ይህ ጠናዛ ሽማግሌ፣ አንዳንዴ እኔን ሲያይ ፊቱን ፈካ የሚያደርገው እወድሃለሁ ብሎ የሚምለውና የሚገዘተው በውሸት ነው» ይላል:: አዝህ ላይ እጅግ ተሳስቷል፡፡ ልጁን የማይወድ አባት ሊኖር ይችላል፡፡ የልጅ ልጁን የማያደንትቅና የማይወድ አያት ግን የለም:: መሴይ ጊልኖርማን
ማሪየስን እንደ አምላክ ነበር የሚያመልኩት:: ልባቸው በእርሱ ፍቅር ተሞልቷል፡፡ ማሪየስ ከቤት ወጥቶ በሄደ ጊዜ ቤቱ ወና፤ ልባቸው ባዶ ቀፎ ሆኖ ቀርቷል፡፡ ከቤታቸው ወጥቶ እንደሄደ ማንም ሰው ስለዚህ ልጅ
እንዳያነሳብኝ» ብለው የሰጡት ትእዛዝ መከበር አስቆጫቸው:: በመጀመሪ ይህ የቦናፖርቴ ተከታይ፤ ይህ ሽብር ፈጣሪ፤ ይህ ረባሽ ሲቸግረው ተመልሶ
ይመጣል» የሚል እምነት ነበራቸው:: ግን ሣምንታት፤ ወራት፧ ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ «ደም መጣጩ ልጅ» ባለመመለሱ መሴይ ጊልኖርማን ተስፋ ቆረጡ፡፡ «ከማባረር ሌላ እርምጃ በወሰድሁ» ሲሉ ተጸጸቱ። ያ ውሳኔ እንደገና የሚፈጸም ቢሆን አሁን አደርገው ነበር?» ሲሉ ራሳቸውን
ጠየቁ፡፡ ክብራቸው «አዎን» ብሎ ሲመልስ የሽማግሌ ጭንቅላታቸው ግን «የለም» በማለት ከወዲያ ወዲህ ተነቃነቀ፡፡
ልጁን በጣም ናፈቁት::
ሽማግሌዎች ፀሐይ ብርሃንን እንደሚሹ ሁላ! የልጆቻቸውንም ፍቅር ይፈልጋሉ፡፡ ፍቅራቸው ያሞቃቸዋል፡፡ መሴይ
ጊልኖርማንድ ብርቱ ሰው ቢሆኑም የማሪየስ ከቤታቸው መጥፋት አንድ ዓያነት ድክመት አሳደረባቸው:: ሆኖም ይህን ወሮበላ» ለመፈለግ አንድ
እርምጃ እንኳን ወደ ፊት አልተራመዱም:: ነገር ግን በጣም ተሰቃዩ ያስቡታል ግን አይፈልጉተም፡፡ ይመኙታል ግን ሊያዩት አይፈልጉም፡፡ ያ ሳቁ፤ ፈገግታው፧ ጨዋታው ፧ ትህትና ከፊታቸው ድቅን ይላል:: «ወይ ጉድ! አሁንስ በመጣና የፈለገውን ባደረግሁት» ይላሉ በልባቸው:: ሳይመጣ ሲቀር ሰውነታቸው ይዝላል።
አክስቱስ! እርስዋማ ለፍቅር ብዙም የማትጨነቅ ሴት ነበረች፡፡
ለእርስዋ ማሪየስ ማለት በጭላንጭል የሚታይ ብርሃን ነው:: እርሱን አሰላስለ በመጨነቅ ከድመት ጋር መጫወት ትመርጣለችካ.ጋትን ትመርጣለች:: የአያቱ የጊልኖርማድል የምሥጢር ስቃይ ያባባሰው ስለማሪየስ ሁለተኛ እንዳታነሣ የስጥዋት ትእዛዝ ነበር፡፡ ድንገት ከውጭ የመጣ ሰው ከማሪየስ አክስት ፊት «ያ ልጅዎ ምን በላው? የት ነው ያለው? ምን ይሠራል?» ተብላ የተጠየቀች እንደሆነ የኛ ባሮንማ የነገር ቀዳዳ ሲያገኝ የሕግ ሰው ነውና
እርሱን እየጠቀመ ነዋ ያለው» ስትል ትመልሳለች::
ሽማግሌው በጸጸት ሲነዱ ማሪየስ ግን የሕሊና እረፍት አግኝቶ ደስ
ብሎት ነበር የሚኖረው:: ያሳለፈው የመከራና የፈተና ዘመን የወደፊት
ህይወቱን ሞረደለት፡፡ ብረት በእሳት ይፈተናል እንዲሉ ማሪየስም በችግር ተፈትኖ ፈተናውን አለፈ፡፡ በልጅነት የሚደርስ ችግርና ድኅነት የወደፊት ኑሮን የማሻሻልና ታግሎ የመወጣት ዝንባሌን አሳድሮ በሕይወት ዘመን የልብ አሸናፊነትን ያጎናጽፋል። ድኅነት ያልጨበጡትን ለመጨበጥ ጉጉት ይፈጠርና ሐሞተ ቆራጥ ያደርጋል፡፡ ይህም ከጥሩ ደረጃ ያደርሳል፡፡
የሀብታም ልጅ አእምሮ ተደስቶ ለመኖር ይፈልግና በልጅነት ዘመኑ
ባዶ አእምሮው በፈረስ ግልቢያ፧ በአደን፣ ሲጃራ በማብነን፧ በዳንኪራ፤ ግብር በማግባት ፣ በፍቶተ ሥጋና በመሳሰሉት ይጠመዳል:: ሌላ የሚመኘው
ነገር አይኖርም:: የድሃ ልጅ ግን የእለት እንጀራውን ለማግኘት መሥራት አለበት:: የእለት እንጀራውን ካገኘ ያቺን ይበላል:: በዚህም ይደሰታል፡፡ ዓመታት ከተፈጥሮ ጋር የቅርብ ግንኙነት ስላለው ያንን ያደንቃል:: በሰዎች መካከል ስለሚሰቃይ የሰዎች ስቃይ ያስጨንቀዋል:: በላቡና በወዙ የሚበላውን ዳቦ በማፍራቱ ታግሎ መውጣትና የትልቅነት ስሜት ያድርበታል:: የስቃይ ብዛት ከሚፈጥረው ራስን የመቻል ፍላጐት ከመጨነቅ ወደ ማሰብ፣ ከማሰብ ችግሩ ደግሞ ራስን የመውደድ ስሜት ስለሚያሳድርበትና ለራሱም
ወደ መፈላሰፍ ስለሚያሸጋግረው የማወቅና የመማር ስሜት ይቀረጽበታል፡፡
ችግሩ ደሞ ራስን የመውደድ ስሜት ስለሚያሳድርበት
ለራሱም ስለሚያዝን የበለጠ ነገር ለማግኘት ይጥራል:: ይህም ችግር ከጫንቃው ሲወርድለት ራሱን እየረሳ ለተቸገረ ሁሉ ማዘን ይጀምራል፡፡ መንፈሳቸውን
ላቀነና ሕይወትን በፀጋ ለተቀበሉ ተፈጥሮ ደስታ እንደሚለግሳቸው
ለተደፈኑ ነፍሳትም ደስታ ይነሳቸዋል:: የአሳብና የእውቀት ሀብታም የሆኑት ለ።ጥሬ ገንዘብ ሀብታሞች ያዝናሉ:: የአሳብ ባለፀጋ ጥላቻን ከልቡ ሲፍቅ
የተስፋ ብርሃን ሕሊናውን ሰንጥቆ ይገባል:: ታዲያ ይህን ጊዜ ይከፋዋል ወይስ አይከፋውም?
የወጣትነት ስቃይ እውነተኛ ስቃይ አይባልም:: አንድ ወጣት የገንዘብ
ድሃ ሊሆን ይችላል፤ ግን ጤናው ፤ ጉልበቱ ፣ ፈጣን እርምጃው፣ የሚያበሩ ዓይኖቹ፤ የሚያሞቀው ደሙ፧ ወለላ ከንፈሩ፤ ከወተት የነጡ ጥርሶቹ ፤ ንጹህ ትንፋሹ ሁሉ የሚያስቀኑ በመሆናቸው የጨረጨሰ ንጉሥ ይቀናበታል::
ይህም በመሆነ ነው ማሪየስ በየቀኑ ጠዋት ጠዋት ሳይታክተው የእለት እንጀራውን ፍለጋ የወጣው:: በእጆቹና በአእምሮው ተጠቅሞ ለእለት እንጀራው ሲሠራ ጀርባው እየበረታና እየጠነከረ አእምሮው በአሳብ እየተሞላ
ሄደ:: ሥራውን ሲጨርስ መመራመሩን ቀጥሎ እግሩ ለእንቅፋት፤ ለእሾህ አንዳንዴም ለጭቃ መጋለጡንና አእምሮው ግን በብርሃን መከበቡን አመነ።
መንፈሰ-ቆራጥ፧ ረጋ ያለ ጭምት ወጣት ከመሆኑም በላይ በጣም ጨዋ፧ሀብታሞች የሌላቸውንና ነፃነት ያጎናጸፈውን ጤነኛ ጉልበትንና ጨዋነትን ያስገኘለት ምርምርን ስለሰጠው ጠዋት ማታ ፈጣሪውን አመሰገነ።
ማሪየስ ሁለት ጓደኞች ነበሩት፡: እነርሱም ወጣቱ ኩርፌይራክና
ሽማግሌው ማብዩፍ ናቸው።
ሽማግሌውን በይበልጥ ያቀርቡታል፡፡ ለዚህም ምክንያት ነበረው:: ማብዩፍ የማሪየስን አባት የሚያውቁና የሚወዱ ሰው
ናቸው:: በአጋጣሚ ነው አባቱ ስለቆመለት ዓላማና እርሱም ማን እንደነበር መሴይ ማብዩፍ ያጫወቱት::
መሴይ ማብዩፍ ፖለቲካ ብዘም አይወዱም:: የእርሳቸው ፖለቲካ ስለተክልና ስለመጻሕፍት ያላቸው ፍቅር ነው:: በዓለም ላይ ብዙ በሚደነቁ እንደ ዛፎች ማደግ፤ እንደ ኣበባ መፈንዳት እንደ ሳር መለምለምና እንደ ጽጌረዳ ማማር በመሳሰሉ ነገሮች ላይ ጊዜ እንደማጥፋት ሰዎች ስለሕዝባዊ ወይም ስለንጉሣዊ አገዛዝ፤ ስለሪፑብሊክ፤ ስለሕጋዊ አልጋ ወራሽና ስለመሳሰሉት ነገሮች በመጨቃጨቅ ጊዜ ማጥፋታቸው ይገርማቸዋል።እኚህ ሰው ሰዎችን ሲያፈቅሩ ሁካታቸውን ይጠላሉ:: ሰዎች ቤተክርስቲያን ውስጥ ስለማይነጫጩና ከዚያ ሥፍራ የመንፈስ እረፍት ስለሚገኝ ወደዚያ አካባቢ መሄድን ያዘወትራሉ:: ራሳቸውን የሚያስተዳድሩት ከአንዲት ከደረሱት መጽሐፍ ሽያጭ በሚገኝ ገቢ ሲሆን በዓመት እስከ ሁለት ሺህ ፍራንክ ያገኛሉ:: በጣም የሚያቀርቡት ወዳጅ መጽሐፍ ሲሆን መሴይ ማብዩፍ ምርጥ
ምርጥ መጻሕፍትን መሰብሰብ ይወዳሉ፡፡
እኚህ ሰው ከእርሳቸው በየዋህነት የማይተናነሱ የሴት ሠራተኛ
ነበርዋቸው:: ሴትዮዋ በየሳምንቱ እሑድ ከቤተክርስቲያን መልስ ጊዜያቸውን የሚያጠፉት በየጊዜው እየገዙ ያጠራቀሙትን ልብስ በመቀጠርና በማገላበጥ
ነበር:: እኚህ ሴት ማንበብ ስለሚችሉ አልፎ አልፎ የመሴይ ማብዩፍን መጻሕፍት ያነብባሉ፡፡
👍12🥰1
በ1830 ዓ.ም. ገደማ የመሴይ ማብዩፍ ወንድም ይሞታለ፡፡ ወዲያው አከታትሉ መሴይ ማብዩፍ ላይ ሌላ መጥፎ አጋጣሚ ይደርሳል። በወንድማቸውና በራሳቸው ስም በአደራ የተቀመጠወ አሥር ሺህ ፍራንክ በእሳቸው ሳይሆን በሌላ ስው ስህተት የተነሣ ይጠፋል:: ስለአበቦች የጻፉትም መጽሐፍ ገበያ ያሽቆለቁላል:: በሐምሌ ወር በተጀመረው ንቅናቄ ምክንያት
ነበር የመጽሐፍ ገበያ ያሽቆለቆለው:: መሴይ ማብዩና አንድ መጽሐፍ እንኳን ሳይሸጡ ሳምንታት አለፉ፡፡ በመጨረሻም ከጻፉት መጽሐፍ የተወስነውን በቅናሽ ዋጋ ሸጠው ቀደም ሲል ይሠሩት የነበረውን ሥራ ትተው ከግቢው ወጡ:: ከተማ ውስጥ እጅግ አነስተኛ በሆነ ገንዘብ ትንሽ
ቤት ተከራይተው ሲኖሩ ከቤታቸው እንዲመጡ የተፈቀደላቸው ማሪየስና አንዲት የመጽሐፍ ቤት ባለቤት ብቻ ነበሩ:: ሠራተኛቸውን ይዘው ነው የሄዱት፡፡
ማሪየስ በእግር መንሸራሸር በጣም ይወዳል:: አንዳንድ ቀን አበቦች ካሉብት አንዳንድ ቀን ደግሞ ዝም ብላ ከአውራ ጎዳናው ላይ ከወዲህ ወዲያ ይላል በመንገድ የሚያልፉ ተጓዦች አተኩረው ያዩታል፡፡ አንዳንዶቹ
አዘውትረው ስለሚያዩት ‹‹ምነው ገና በለጋነቱ አሳብ አበዛ» እያለ
ያዝኑለታል::
ማሪየስ ብዙ ጊዜ ያስብ የነበረው ስለኑሮው ነበር እንጂ ለንቅናቄው
የነበረው ስሜት ስለቀዛቅዞ ብዙም አያስጨንቀውም፡፡ ለኑሮ የነበረውን
ፍልስፍና አልለወጡም፡፡ ሆኖም ፍልስፍናው ወደ ሀዘኔታ እየተለወጠበት ነበር። እምነቱ ሁሉ ያተኮረው ስለሰዎች ደኅንነት ሆነ:: ይህም እምነቱ ሀገሩን በይበልጥ አስወደደው:: አገሩን ወደደ ስንል ደግሞ ለሕዝቡ በጣም ተቆረቆረ ማለታችን ነው:: በተለይ ደግሞ ለሴቶች በጣም ያዝናል፡፡
አንድ ቀን ሠራተኛው ‹‹ጎረቤቶቻችን እኮ ከቤታቸው ሊባረሩ ነው» ትለዋለች:: እርሱ አብዛኛው ጊዜውን የሚያጠፋው ከቤት ውጭ ስለነበር በአካባቢው ማን እንዳለ አያውቅም:: እነማን እንደሆነ ባያውቅም በምን ምክንያት» ብሎ ይጠይቃል፡፡
«የቤት ኪራይ መክፈል ስለአቃታቸው!» ስንት ይሆን ያለባቸው?»
«ሃያ ፍራንክ»
"
ማሪየስ ለመጠባበቂያ እንዲሆን ከቤት ያስቀመጠው ሰላሣ ፍራንክ
ነበረው።
«ይኸው ሃያ አምስት ፍራንክ፡፡ ሃያውን ለቤት ኪራይ ክፈይላቸው::
አምስቱንም ደግሞ ኣንዳንድ ቀዳዳ ቢደፍንላቸወ ስጫቸው:: እኔ እንደሰጠኋቸው ግን አትንገሪያቸው::....
💫ይቀጥላል💫
ነበር የመጽሐፍ ገበያ ያሽቆለቆለው:: መሴይ ማብዩና አንድ መጽሐፍ እንኳን ሳይሸጡ ሳምንታት አለፉ፡፡ በመጨረሻም ከጻፉት መጽሐፍ የተወስነውን በቅናሽ ዋጋ ሸጠው ቀደም ሲል ይሠሩት የነበረውን ሥራ ትተው ከግቢው ወጡ:: ከተማ ውስጥ እጅግ አነስተኛ በሆነ ገንዘብ ትንሽ
ቤት ተከራይተው ሲኖሩ ከቤታቸው እንዲመጡ የተፈቀደላቸው ማሪየስና አንዲት የመጽሐፍ ቤት ባለቤት ብቻ ነበሩ:: ሠራተኛቸውን ይዘው ነው የሄዱት፡፡
ማሪየስ በእግር መንሸራሸር በጣም ይወዳል:: አንዳንድ ቀን አበቦች ካሉብት አንዳንድ ቀን ደግሞ ዝም ብላ ከአውራ ጎዳናው ላይ ከወዲህ ወዲያ ይላል በመንገድ የሚያልፉ ተጓዦች አተኩረው ያዩታል፡፡ አንዳንዶቹ
አዘውትረው ስለሚያዩት ‹‹ምነው ገና በለጋነቱ አሳብ አበዛ» እያለ
ያዝኑለታል::
ማሪየስ ብዙ ጊዜ ያስብ የነበረው ስለኑሮው ነበር እንጂ ለንቅናቄው
የነበረው ስሜት ስለቀዛቅዞ ብዙም አያስጨንቀውም፡፡ ለኑሮ የነበረውን
ፍልስፍና አልለወጡም፡፡ ሆኖም ፍልስፍናው ወደ ሀዘኔታ እየተለወጠበት ነበር። እምነቱ ሁሉ ያተኮረው ስለሰዎች ደኅንነት ሆነ:: ይህም እምነቱ ሀገሩን በይበልጥ አስወደደው:: አገሩን ወደደ ስንል ደግሞ ለሕዝቡ በጣም ተቆረቆረ ማለታችን ነው:: በተለይ ደግሞ ለሴቶች በጣም ያዝናል፡፡
አንድ ቀን ሠራተኛው ‹‹ጎረቤቶቻችን እኮ ከቤታቸው ሊባረሩ ነው» ትለዋለች:: እርሱ አብዛኛው ጊዜውን የሚያጠፋው ከቤት ውጭ ስለነበር በአካባቢው ማን እንዳለ አያውቅም:: እነማን እንደሆነ ባያውቅም በምን ምክንያት» ብሎ ይጠይቃል፡፡
«የቤት ኪራይ መክፈል ስለአቃታቸው!» ስንት ይሆን ያለባቸው?»
«ሃያ ፍራንክ»
"
ማሪየስ ለመጠባበቂያ እንዲሆን ከቤት ያስቀመጠው ሰላሣ ፍራንክ
ነበረው።
«ይኸው ሃያ አምስት ፍራንክ፡፡ ሃያውን ለቤት ኪራይ ክፈይላቸው::
አምስቱንም ደግሞ ኣንዳንድ ቀዳዳ ቢደፍንላቸወ ስጫቸው:: እኔ እንደሰጠኋቸው ግን አትንገሪያቸው::....
💫ይቀጥላል💫
👍17
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#ሁለት
....አሸብር ብላ ስም ያወጣችልኝ ከቤታችን በላይ ብዙ ላም የምታረባ ቅሌታም ባልቴት ናት፡፡ ሰው ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ ከአቲዬም ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡ እኔ ልወለድ አቲዬ ምጥ የተያዘች ቀን የዚህች አቃጣሪ ባልቴት የአሜሪካ ላም ያልታወቀ ነገር በልታ ሆዷ
ተቆንዝሮና አረፋ ደፍቃ እየጓጎረች ነበር አሉ።
የመንደሩ ሰው ከእኔ እናት ምጥ ይልቅ የዚህች የመንደራችን ሀብታም ላም ነፍስ አስጨንቆት
አዋላጇ አልማዝ ሳትቀር ወደዛው ሂደው ነበርና አቲዩ ብቻዋን እኔን ተገላገለች፡፡ ወለደችኝ!!
የቀን ሥራ ያጠነከራት ብርቱ ሴት ባትሆን ኖሮ ሟች ነበረች፡፡ ብቻዋን ወለደችኝ !!"
አንድ የእንስሳት ሀኪም ተጠርቶ የአቃጣሪዋን ዘርፈ ላም ሆድ እስክሪብቶ በሚመስል ነገር
ወግቶ ሲያስተነፍስላትና ላሟ መጓጎሯን ስታቆም መንደርተኛው እልልታውን አቀለጠው!
እልልልልልልልልልል… አቲዬ እልልታውን ከሩቅ ሰምታለች፡፡ በዚህ መሀል አዋላጇ፡ “በሞትኩት ያቺ ሚስኪን ምን ደርሳ ይሆን?” ብላ ወደ ቤታችን ተጣደፈች። አቲዬን የተፈለቀ ወርቅ የመሰለ ወንድ ልጅ አቅፋ አገኘቻት፡፡ ያ የተፈለቀቀ ወርቅ እኔ ነበርኩ ያውም ገና በእሳት ሊፈተን የተዘጋጀ ወርቅ፡፡
ዘርፌ የሚሏት ሀብታም ባለላም የላሟን ደኅንነት ሊጠይቃት ቤቷ ሲጎርፍ የዋለውን ቅቤ አንጓች
ሁሉ ስታስተናግድ ውላ ወደ ማታ አስር እንጀራና ክክ ወጥ ይዛ ቤታችን መጣችና መንደርተኛው
በእኔ ላም በተሸበረበት ቀን ተወልዷልና አሸብር ብዬዋለሁ” አለች፡፡ አሸብር ሆኜ ቀረሁ!! ነገ አድጌ ብረብሽ! ስምን መልዓክ ያወጣዋል የሚል ሒሳብ 'መልዓክ ነኝ ልትል፡፡ እች…ስድብ የማይገልፃት…!ለ 'አንቱታ' የደረሰች ሴትዮ ናት፣ 'አንች የምላት ባትስማኝም ስንቃት ደስ ስለሚለኝ ነው፡፡
እንግዲህ አሸብር የተባልኩት አንዲት ተራ አጋሰስ..የአሜሪካ ላም ባጋበሰችው ፈስታል ታምማ
መንደርተኛውን ባሸበረችበት ቀን በመወለዴ ነው በቃ ! ደግሞ ምኔም የማያሸብር እንደወም
ቅጠል ሲንኮሻኮሽ እቲዬ አሮጌ ቀሚስ ስር የምደበቅ ፈሪ ነበርኩ ስሜን ያወጣው መልዓክ
አይደለም ዘርፌ የምትባል ቀንዳም ሰይጣን ናት!!
እኔኮ ሚያበሳጨኝ.…የዛን ጊዜ ዘመኑ ስላልሰለጠነ ነው ብዪ ውስጤ ከተመረዘበት ጥላቻ
እንዳይሽር፣ ዛሬም ድረስ ጎረቤቶቻችን ስለዛ ጊዜ ሲያወሩ ፊታቸው የተቀመጠችውን አቲዬን….ብቻዋን መውለዷን ከቁምነገር ሳይቆጥሩት ማለፋቸው ሳይበቃ፣ ከሞተች የቆየችውን የአሜሪካ ላም ደግነት፣ ባልዲ ሙሉ መታለብ ፌስታል በልታ ስታቃስት አንጀታቸው መንሰፍሰፉን
እየተቀባበሉ ማውራታቸው ነው፡፡ ደግሞ የሚንሰፈሰፍ አንጀት እንዳለው ሰው፡፡ጎማ አንጀት ሁሉ!!
አቤት ስጠላቸው! ልቤ ተሸንቁሮ የቋጠረው ፍቅር ፈሶ ያለቀበት ይመስል የተረፈኝ አፅናፍ
የለሽ ጥላቻ ብቻ ነው፡፡ ማንንም አልወድም ሁሉንም እጠላለሁ ! ዘርፌ መልዓክ ብትሆን ጥሩ ነበር
ስሜን እንድሆን፤ ይሄን ከመሬት ተነስቶ የሚሸበርና የሚያሸብር አውራና ምንዝር ጎረቤት ሁሉ እንዳሸብረው !! ወይ ነዶ ለሞላ ቦንብ ምናለ አንዲት ኒውክሌር ቦምብ ብትኖረኝ !! ለክፉ ነገር አልጠቀምባትም፣ ቀለመወርቅ ግቢ እወስድና …
አቲዩ ከገጠር ወደ አዲስ አበባ ስትገባ ገና 14 ዓመት እንኳን አሳምሮ አልሞላትም ነበር፡፡ ገጠር
የሚኖሩ ቤተሰቦቿ ምናምኒት የሌላቸው ያጡ የነጡ ድሆች ስለነበሩ በልጅነቷ ነው ልፋት
ዕጣ ፋንታዋ የሆነው ገጠር ስልችት አላት፡፡ ባል አልነበረም የስደቷ መነሻ፡፡ ያላቻ ጋብቻ
ምንትስ ብላ አልነሳረም ወደ ከተማ መኮብለሏ፡፡ የከተማ ሰው ከድህነት የሚያላቅቅ ዓመድሽን
የሚያራግፍ ደግ ነው ብለዋት እንጂ ባል ሽሽት አልነበረም፡፡
ከተሜው ያላቻ ጋብቻ እያለ የሚወተተው ሲያስመስል እኮ ነው፡፡ ለሀብት፥ በዘር፣ በእምነት
አቻ በማሳደድ ሱስ ስለተለከፈ፣ የመከፋፈልና የማግለል ንቅዘቱ ነው የሚያስለፈልፈው፡፡ ተራራ
ተሻግሮ የሚጮኸው ከተሜ ስንት የነቀዘ ባህል፣ የገማ ዓመል ጉያ ውስጥ ሸጕጧል። አሱን ብሎ የመብት ተከራካሪ፣ እሱን ብሎ ታዳጊ፡፡ ምን በወጣሽ ካለ እድሜሽ ማግባት እያለ
የገጠሯን ሴት በአዞ እንባ ሙሾ የሚያስወርድ ከተሜ በየጓዳው ከከፉ ባል ይከፋል፡፡
የልጅነት እግሮቿ ወደ አዲስ አበባ መሯት። ዘርፌ የምትባል ባለ ብዙ ላም ሴት የደሀ መንደር ከእኔ ወዲያ ሀብታም ላሳር' የምትል ክብረ ቢስ ባልቴት ላይ ሰዎች አምጥተው ጣሏት፡፡ ሴትዮዋ
ብዙ የአሜሪካ ላሞች ስለነበሯት አቲዬን በሰራተኝነት ቀጠረቻት፡፡
ገጠር ትታው የመጣችው አዛባ መዛቅና ላም ማላብ እዚህም መሀል አዲሳባ ጠበቃት፡፡ ሰው
እየመሰለው ይሮጣል እንጂ እጣ ፋንታውን በመሽሽ አያመልጠውም፡፡ እልፍ ሲሉ እልፍ ይገኛል ብሂል ጋር ስንተላለፍ እጣ ፉንታችንም አብሮን እያለፈ ከፊታችን ይጠብቁናል፡፡ እንዲያ ነው አቲዩን የገጠማት፣ ከእርሻ ላም ወደ አሜሪካ ላም!! አዲሳባ ራሷ የአሜሪካ ላም ናት፡፡ ብዙ
ላበላት ብዙ የምትታለብ፡፡ አላቢም ታላቢም ግፍ የሞላባት፣ ውጪዋ አብረቅራቂ ቀለም የተቀባ ሰፊ በረት !!
አንዳንድ የአሜሪካ ላሞች ከሰው ልጆች የበለጠ ክብር ይሰጣቸዋል፡፡ የአሜሪካ ላም ስለሆኑ ወይም፣ ላም ብቻ ስለሆኑ አይደለም ወትት ስለሚታለቡ፡፡ ስጋቸው ስለሚበላና ሌላ የምትታለብ ላም የሚታረድ በሬ ስለሚወልዱ፡፡ ይሄ የዓለማችን የደነዘ የምጣኔ ሀብት ቀመር ነው
የበለጠ የሚታለበውን የበለጠ ተንከባከበው !! ይልኻል በአደባባይ በከራቫት በታነቀ ተወካዩ፡፡ በተወካዩ መሪነት የስግብግብነትና የከፋት ኪራላይሶ የሚደግም አህዛብ ከተሜ ይባላል፡፡
አገር ይሁን ሰው ምንም ከሌለው ምናምቴ ነው፡፡ ይገፋል ይረገጣል፡፡ ለጠብታ ነዳጅ አንድ
አገር ሰው ቢፈጅ ዓለም ጭጭ የሚለው ለፅድቅ የሚሆንን መንገድ በግፍ ለመቀየስ ነው ካለወጉ !!ሰብዓዊነት ገደል ይግባ! ብለው ሰው መሆንህን ሊክዱ የሚዳዳቸው ሁሉ፣ በዕድልም ይሁን በችሎታህ አምልጠህ ሰው ስትሆንባቸው ገደል ያስገቧትን ሰብዓዊነት ጎትተው የሚያወጡባትን
ገመድ እንድትሰጣቸው ፊትህ ቁመው ጅራታቸውን ይቆላሉ፡፡ ደግነቱ ጭራቅ ለጭራቅ እስኪበላላ አይጨካከንም የጭራቅ ሕግ አለ፣ የጭራቅ መሀላ በየወንዙ የሚማማሉት ዓይነት፡፡ እንደ አተዬ አይነት ሚስኪን ልፋት የፈጠራት እንደ አህያ ያሻቸውን የሚጭኑባት ፍጥረት የሚማማሉበት ወንዝ ዳር ከተገኘች፣ አደፈረሽብን ከማለት አይመለሱም
እንደሰው ባልቆጠሯት እናቴ ጉልበት ሰው የሆኑ ብዙዎች ሰው ብቻ እንዳልሆኑ፣ ይልቅ በጣም
ሰው እንደሆኑ ሲሰማቸው (ከጣት ጣት ይበላለጣል የሚል ተረት ሁሉ አላቸው፡፡) የአትዬ ወጣት ሰውነት ላይ አይናቸውን ያቁለጨልጩ ጀመረ፡፡ ቀለመወርቅ የሚባል ካፖርትና ክብ ኮፍያ የማይለየው ባለ ትልቅ ቤትና ባለ መኪና ሰው ነበር። እሱስ አሁንም አለ፣ እኔ ውስጥ ከሞተ ቆየ እንጂ ! በውስጤ ሚሊየን ጊዜ ገድየው፣ ሚሊየን ጊዜ ተነስቷል የክፉ ሰው ነፍስ ጣር ይበዛበታል፡፡
ሁሉም ሰው ጋሽ ቀለሙ ነው የሚለው እና ይሄ ካፖርታም ቤታም እና መኪናም አጋሰስ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#ሁለት
....አሸብር ብላ ስም ያወጣችልኝ ከቤታችን በላይ ብዙ ላም የምታረባ ቅሌታም ባልቴት ናት፡፡ ሰው ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ ከአቲዬም ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡ እኔ ልወለድ አቲዬ ምጥ የተያዘች ቀን የዚህች አቃጣሪ ባልቴት የአሜሪካ ላም ያልታወቀ ነገር በልታ ሆዷ
ተቆንዝሮና አረፋ ደፍቃ እየጓጎረች ነበር አሉ።
የመንደሩ ሰው ከእኔ እናት ምጥ ይልቅ የዚህች የመንደራችን ሀብታም ላም ነፍስ አስጨንቆት
አዋላጇ አልማዝ ሳትቀር ወደዛው ሂደው ነበርና አቲዩ ብቻዋን እኔን ተገላገለች፡፡ ወለደችኝ!!
የቀን ሥራ ያጠነከራት ብርቱ ሴት ባትሆን ኖሮ ሟች ነበረች፡፡ ብቻዋን ወለደችኝ !!"
አንድ የእንስሳት ሀኪም ተጠርቶ የአቃጣሪዋን ዘርፈ ላም ሆድ እስክሪብቶ በሚመስል ነገር
ወግቶ ሲያስተነፍስላትና ላሟ መጓጎሯን ስታቆም መንደርተኛው እልልታውን አቀለጠው!
እልልልልልልልልልል… አቲዬ እልልታውን ከሩቅ ሰምታለች፡፡ በዚህ መሀል አዋላጇ፡ “በሞትኩት ያቺ ሚስኪን ምን ደርሳ ይሆን?” ብላ ወደ ቤታችን ተጣደፈች። አቲዬን የተፈለቀ ወርቅ የመሰለ ወንድ ልጅ አቅፋ አገኘቻት፡፡ ያ የተፈለቀቀ ወርቅ እኔ ነበርኩ ያውም ገና በእሳት ሊፈተን የተዘጋጀ ወርቅ፡፡
ዘርፌ የሚሏት ሀብታም ባለላም የላሟን ደኅንነት ሊጠይቃት ቤቷ ሲጎርፍ የዋለውን ቅቤ አንጓች
ሁሉ ስታስተናግድ ውላ ወደ ማታ አስር እንጀራና ክክ ወጥ ይዛ ቤታችን መጣችና መንደርተኛው
በእኔ ላም በተሸበረበት ቀን ተወልዷልና አሸብር ብዬዋለሁ” አለች፡፡ አሸብር ሆኜ ቀረሁ!! ነገ አድጌ ብረብሽ! ስምን መልዓክ ያወጣዋል የሚል ሒሳብ 'መልዓክ ነኝ ልትል፡፡ እች…ስድብ የማይገልፃት…!ለ 'አንቱታ' የደረሰች ሴትዮ ናት፣ 'አንች የምላት ባትስማኝም ስንቃት ደስ ስለሚለኝ ነው፡፡
እንግዲህ አሸብር የተባልኩት አንዲት ተራ አጋሰስ..የአሜሪካ ላም ባጋበሰችው ፈስታል ታምማ
መንደርተኛውን ባሸበረችበት ቀን በመወለዴ ነው በቃ ! ደግሞ ምኔም የማያሸብር እንደወም
ቅጠል ሲንኮሻኮሽ እቲዬ አሮጌ ቀሚስ ስር የምደበቅ ፈሪ ነበርኩ ስሜን ያወጣው መልዓክ
አይደለም ዘርፌ የምትባል ቀንዳም ሰይጣን ናት!!
እኔኮ ሚያበሳጨኝ.…የዛን ጊዜ ዘመኑ ስላልሰለጠነ ነው ብዪ ውስጤ ከተመረዘበት ጥላቻ
እንዳይሽር፣ ዛሬም ድረስ ጎረቤቶቻችን ስለዛ ጊዜ ሲያወሩ ፊታቸው የተቀመጠችውን አቲዬን….ብቻዋን መውለዷን ከቁምነገር ሳይቆጥሩት ማለፋቸው ሳይበቃ፣ ከሞተች የቆየችውን የአሜሪካ ላም ደግነት፣ ባልዲ ሙሉ መታለብ ፌስታል በልታ ስታቃስት አንጀታቸው መንሰፍሰፉን
እየተቀባበሉ ማውራታቸው ነው፡፡ ደግሞ የሚንሰፈሰፍ አንጀት እንዳለው ሰው፡፡ጎማ አንጀት ሁሉ!!
አቤት ስጠላቸው! ልቤ ተሸንቁሮ የቋጠረው ፍቅር ፈሶ ያለቀበት ይመስል የተረፈኝ አፅናፍ
የለሽ ጥላቻ ብቻ ነው፡፡ ማንንም አልወድም ሁሉንም እጠላለሁ ! ዘርፌ መልዓክ ብትሆን ጥሩ ነበር
ስሜን እንድሆን፤ ይሄን ከመሬት ተነስቶ የሚሸበርና የሚያሸብር አውራና ምንዝር ጎረቤት ሁሉ እንዳሸብረው !! ወይ ነዶ ለሞላ ቦንብ ምናለ አንዲት ኒውክሌር ቦምብ ብትኖረኝ !! ለክፉ ነገር አልጠቀምባትም፣ ቀለመወርቅ ግቢ እወስድና …
አቲዩ ከገጠር ወደ አዲስ አበባ ስትገባ ገና 14 ዓመት እንኳን አሳምሮ አልሞላትም ነበር፡፡ ገጠር
የሚኖሩ ቤተሰቦቿ ምናምኒት የሌላቸው ያጡ የነጡ ድሆች ስለነበሩ በልጅነቷ ነው ልፋት
ዕጣ ፋንታዋ የሆነው ገጠር ስልችት አላት፡፡ ባል አልነበረም የስደቷ መነሻ፡፡ ያላቻ ጋብቻ
ምንትስ ብላ አልነሳረም ወደ ከተማ መኮብለሏ፡፡ የከተማ ሰው ከድህነት የሚያላቅቅ ዓመድሽን
የሚያራግፍ ደግ ነው ብለዋት እንጂ ባል ሽሽት አልነበረም፡፡
ከተሜው ያላቻ ጋብቻ እያለ የሚወተተው ሲያስመስል እኮ ነው፡፡ ለሀብት፥ በዘር፣ በእምነት
አቻ በማሳደድ ሱስ ስለተለከፈ፣ የመከፋፈልና የማግለል ንቅዘቱ ነው የሚያስለፈልፈው፡፡ ተራራ
ተሻግሮ የሚጮኸው ከተሜ ስንት የነቀዘ ባህል፣ የገማ ዓመል ጉያ ውስጥ ሸጕጧል። አሱን ብሎ የመብት ተከራካሪ፣ እሱን ብሎ ታዳጊ፡፡ ምን በወጣሽ ካለ እድሜሽ ማግባት እያለ
የገጠሯን ሴት በአዞ እንባ ሙሾ የሚያስወርድ ከተሜ በየጓዳው ከከፉ ባል ይከፋል፡፡
የልጅነት እግሮቿ ወደ አዲስ አበባ መሯት። ዘርፌ የምትባል ባለ ብዙ ላም ሴት የደሀ መንደር ከእኔ ወዲያ ሀብታም ላሳር' የምትል ክብረ ቢስ ባልቴት ላይ ሰዎች አምጥተው ጣሏት፡፡ ሴትዮዋ
ብዙ የአሜሪካ ላሞች ስለነበሯት አቲዬን በሰራተኝነት ቀጠረቻት፡፡
ገጠር ትታው የመጣችው አዛባ መዛቅና ላም ማላብ እዚህም መሀል አዲሳባ ጠበቃት፡፡ ሰው
እየመሰለው ይሮጣል እንጂ እጣ ፋንታውን በመሽሽ አያመልጠውም፡፡ እልፍ ሲሉ እልፍ ይገኛል ብሂል ጋር ስንተላለፍ እጣ ፉንታችንም አብሮን እያለፈ ከፊታችን ይጠብቁናል፡፡ እንዲያ ነው አቲዩን የገጠማት፣ ከእርሻ ላም ወደ አሜሪካ ላም!! አዲሳባ ራሷ የአሜሪካ ላም ናት፡፡ ብዙ
ላበላት ብዙ የምትታለብ፡፡ አላቢም ታላቢም ግፍ የሞላባት፣ ውጪዋ አብረቅራቂ ቀለም የተቀባ ሰፊ በረት !!
አንዳንድ የአሜሪካ ላሞች ከሰው ልጆች የበለጠ ክብር ይሰጣቸዋል፡፡ የአሜሪካ ላም ስለሆኑ ወይም፣ ላም ብቻ ስለሆኑ አይደለም ወትት ስለሚታለቡ፡፡ ስጋቸው ስለሚበላና ሌላ የምትታለብ ላም የሚታረድ በሬ ስለሚወልዱ፡፡ ይሄ የዓለማችን የደነዘ የምጣኔ ሀብት ቀመር ነው
የበለጠ የሚታለበውን የበለጠ ተንከባከበው !! ይልኻል በአደባባይ በከራቫት በታነቀ ተወካዩ፡፡ በተወካዩ መሪነት የስግብግብነትና የከፋት ኪራላይሶ የሚደግም አህዛብ ከተሜ ይባላል፡፡
አገር ይሁን ሰው ምንም ከሌለው ምናምቴ ነው፡፡ ይገፋል ይረገጣል፡፡ ለጠብታ ነዳጅ አንድ
አገር ሰው ቢፈጅ ዓለም ጭጭ የሚለው ለፅድቅ የሚሆንን መንገድ በግፍ ለመቀየስ ነው ካለወጉ !!ሰብዓዊነት ገደል ይግባ! ብለው ሰው መሆንህን ሊክዱ የሚዳዳቸው ሁሉ፣ በዕድልም ይሁን በችሎታህ አምልጠህ ሰው ስትሆንባቸው ገደል ያስገቧትን ሰብዓዊነት ጎትተው የሚያወጡባትን
ገመድ እንድትሰጣቸው ፊትህ ቁመው ጅራታቸውን ይቆላሉ፡፡ ደግነቱ ጭራቅ ለጭራቅ እስኪበላላ አይጨካከንም የጭራቅ ሕግ አለ፣ የጭራቅ መሀላ በየወንዙ የሚማማሉት ዓይነት፡፡ እንደ አተዬ አይነት ሚስኪን ልፋት የፈጠራት እንደ አህያ ያሻቸውን የሚጭኑባት ፍጥረት የሚማማሉበት ወንዝ ዳር ከተገኘች፣ አደፈረሽብን ከማለት አይመለሱም
እንደሰው ባልቆጠሯት እናቴ ጉልበት ሰው የሆኑ ብዙዎች ሰው ብቻ እንዳልሆኑ፣ ይልቅ በጣም
ሰው እንደሆኑ ሲሰማቸው (ከጣት ጣት ይበላለጣል የሚል ተረት ሁሉ አላቸው፡፡) የአትዬ ወጣት ሰውነት ላይ አይናቸውን ያቁለጨልጩ ጀመረ፡፡ ቀለመወርቅ የሚባል ካፖርትና ክብ ኮፍያ የማይለየው ባለ ትልቅ ቤትና ባለ መኪና ሰው ነበር። እሱስ አሁንም አለ፣ እኔ ውስጥ ከሞተ ቆየ እንጂ ! በውስጤ ሚሊየን ጊዜ ገድየው፣ ሚሊየን ጊዜ ተነስቷል የክፉ ሰው ነፍስ ጣር ይበዛበታል፡፡
ሁሉም ሰው ጋሽ ቀለሙ ነው የሚለው እና ይሄ ካፖርታም ቤታም እና መኪናም አጋሰስ
👍27❤3
በእናቴ ቁንጅናና ወጣትነት ቋመጠ፡፡ ትልልቅ ልጆች አሉት፡፡ ሚስቱ ጋር ተፋትቷል (ባይፋታ
ነበር የሚገርመው)፡፡ ይሄ የአምሳ ምናምን ዓመት ሰው አንዲት ፍሬ ልጅ ሊያጠምድ ዘርፌ የምትባል አቃጣሪ ያረጀች አሮጌ መረብ ሰፈሩ ላይ ወረወረ፡፡ “ዘርፍዬ እንዴት ያለችውን ልጅ አመጣሻት ደሞ! » ሲል ይታየኛል በዓይነ ህሊናዬ፡፡
አቲዬ የምትባል ሚስኪን አሳ የህይወትን ዋና ልትለማመድ ስትፍገመገም መረቡ ውስጥ ገባች፤ዘርፌ የምትባል ቁራጭ የአሳማ ስጋ የከፋት መንጠቆ ላይ ተሰክታ አቲዬን አታለለቻት፡፡
"አፀደ!”
"እመት እትዬ"
"ኤዲያ እንደ ባላገር እመት!' አትበይ፣ አቤት! ነው የሚባል፡፡ ነይ እስቲ ለጋሽ ቀለሙ ወተት
አድርሽለት!” አለች ዘርፌ፡፡
"እሽ!” ብላ የወተት ጠርሙሱን እንስታ ልትሄድ መንገድ ጀመረች - የእኔ ታዛዥ አቲዬ፡፡ ባልቴቷ ተቆጣች::
ነይ ወዲህ የምን መንካተት ነው እቴ..ማንም መደዴ ቤት የምትሄድ መሰላት እንዴ…እንዲህ ተንኳተሽ ትልቅ ሰው ቤት ...ምኗ ገልቱ ነሽ አንችዬ..በይ ፊትሽን ታጠቢ እግርሽንም እዛ ድንጋይ ላይ ፈትገሽ ታጠቢው።
አቲዬ ሰውነቷ ነክቶት የማያውቀውን ልብስ፣ እግሯ ተጫምቶት የማያውቀውን ጫማ ከእመቤቷ ተቸራት፡፡ በደስታ ሰከረች፡፡ ስለከተሜ ሰዎች ቸርነት የሰማችው ቃል ስጋ ለብሶ ፊቷ ሲገተር አየችው:: አበባ መሰለች፡፡ ድሮም አበባ ነበርች !! እንኳን ያኔ አሁንም ውብ ናት የእኔ እናት !!
በዚህ ዓይነት ቀለሙ ለሚባለው ውሻ ወተት አደረሰች፡፡ደጋገመችው፡፡ ስትመላለስ ቆየች፡፡
የቀለመወርቅ ቤት ቤተመቅደስ መሰላት፣ ካልታጠቡ የማይረግጡት፡፡ አንድ ሌላ ቀን ዘርፌ አቲዬን ጠራቻት፡፡
"አፀደ”
"እመ...አቤት እትዩ!” (እመት አትበይ የባላገር ነው' ተብላለቻ፡፡)
ጋሽ ቀለሙ አመም አድርጎታል፡፡ ቤት ሰውም የለ፣ ሂጂ እስቲ እህል ውሃ ስሪለት፡፡ እኛ እያለን
በረሀብ አይሞት መቸስ ጡር ነው፡፡”
"ምን አገኛቸው?!” አለች አቲዬ የኔ የዋህ በእባቦች ጨዋታ መሃል ንፁህ ልቧን በአደራ እያስቀመጠች፣
"ምን እንደነካው እሱኑ ጠይቂው፣ እኔ መች ሞልቶልኝ እየሁት ብለሽ” አለች ዘርፌ፡፡
አቲዬ ወደ አቶ ቀለሙ ሄደች፣ ዋለች፣ አደረች፡፡ ልታስታምም ሄዳ እድሜ ልኳን ህሊናዋ ውስጥ የሚመረቅዝ በሽታ ይዛ ተመለሰች: አቲዬ ከዛን ቀን ጀምሮ ቅስሟ ተሰበረ፡ ፈገግታዋ ጠፋ፡
አንገቷን ደፋች፡፡ ቀለመወርቅ ይሉት መዥገር ግን ወጣትነቷን የመጠጠው ይመስል አማረበት
አረማመዱ ሳይቀር እንደወጣት ሆነ፡፡ ግዴላችሁም እድሜም እንደገንዘብ ይነጠቃል፡፡ ይሄ
ሰው የእናቴን እድሜ በግፍ ነጥቋታል፡፡
አቲዬ በዚህ ልክ የሌለው መከፋት፥ መግለጫ አልባ በሆነ ቅስም መሰበር ውስጥ እንዳለች :
“አፀደ!” አለች አሰሪዋ ዘርፌ፡፡
አቲዩ "አቤት!" አላለችም፣ ዝም ብላ አቃጣሪዋ ፊት ሄዳ ቆመች፡፡ እመትን በስልጣኔ ስም "አቤትን'
ከክብሯ ጋር ቀምተዋት ምኑን አቤት ትበል…፡፡ ዘርፌ ትእዛዟን እንዲህ ስትል ጀመረች፣
“ጋሸ ቀለሙ ሴት ሂጃና…"
“አልሄድም !" አለች እንባ ተናንቋት፡፡
“ምናልሽ እንች እከከከከከ ጭቅቅትሽን ሳላቅቅልሽ እንዲህ አፍሽን ሞልተሽ ትሰድቢኝ " ባልቴቷ በያዘችው የኒኬል ሰሀን አቲዬን ፊቷ ላይ ደረገመቻትና፣ እች ደነዝ እጄን አሳመመችኝ አለች
ሰሀኑ የስሚንቶው ወለል ላይ ወድቆ ተቅጨለጨለ፡፡ አቲዩ በቀኝ እጇ ሰሀኑ ያረፈበትን ፊቷን
ሸፍና፣ አግሯ እንደመራት ወደ መኪና መንገዱ በረረች፡፡ ትንሽ እንደሄደች እዚሁ አሁን ትልቁ ዳቦ
ቤት የተሰራበት ቦታ ላይ አንዲት ኪዮስክ ነበረች፣ አንዳንዴ እቲዬ እየተላከች እቃ የምትገዛባት
ባለቤቷ የአቲዬን ወጣትነት ስታይ ሁሌ ምራቋን የምትውጥ (ለሰራተኝነት)…ጠራቻት፡፡
"አፀደ.አንችን እኮ ነው!”
ዝም፡፡
“ምን ሆነሻል ?
ዝም…እርምጃዋን ቀንሳ እየቆመች፡፡
“አንችን እኮ ነው!”
ዝም፡፡
“እንዴ ደግሞ ፊትሽ ምን ጉድ ነው? እረ ጉዴ፣ ምንድነው ይሄ ሁሉ ደም?"
አቲዬ ደነገጠች፡፡ እጇን ከፊቷ ላይ እንስታ ተመለከተችው፣ በደም ተሸፍኖ ነበር፡፡
አሁን ያፈነችው እንባ ፈነዳ፡፡ ከልጅነቷ ጀምሮ ውስጧ የተጠራቀመው ጩኸት እና እዬዬ፣
መንደሩን የሚያሸብር ዋይታ ሆነ፡፡ መንደርተኛው ተሰበሰቡ፡፡
ምንድን ነው?
እንዴ እትዩ ዘርፈ ሰራተኛ አይደለችም እንዴ ምን አገኛት?”
ማናባቱ ነው የዘርፍዬን ልጅ እንዲህ ያደረጋት? ..ዘርፌ ዘርፍዬ…ወይዘሮ ዘርፌ እሜቴ ዘርፌ የዘርፌ ሰራተኛ
ሰው በመሆኗ ሳይሆን፣ በዘርፌ ንብረትነቷ መንደሩ ዘራፍ አለ፡፡
አኮ ማናባቱ ነው የነካት?
ተናገሪ ማነው የመታሽ?”
ዘርፌ ራሷ !
ዝም ሰፈሩ !! ዝምምምምምምምምምምምምምምምምምምምምምምም!!
ምን ኣጥፍተሽ ነው" አሏት አቲዩን፡፡
እሷም ዝም !
ታስታውቃለች ተንኮለኛ፡፡ ዝም ያለችው ጥፋቷ ቢሆን ነው።"
አንዲች ዘርፌ.የሴት ወንድ መች መጨማለቅ ትወድና..አንድ ነገር ስታደርጊ አግኝታሽ ነው::”
መንደርተኛው ዘባረቅ፡፡ ይሄ ዘባራቂ ሁሉ…፡፡ ይሄ ጉዳይ ከሆነ ስንትና ስንት ዓመቱ ሰፈሩ ግን አሁንም ዘባራቂ ነው !! ባለ ኪዮስኳ ብቻ ለአቲዬ አገዘች፡፡ “የሚመታ ይምታት፣ ምንስ
ብታደርግ እንዲህ ደም በደም እስከትሆን ትመታታለች፡፡ እች ጥጋበኛ ባልቴት፣ ምነው እች
ሴትዮ በመቁረቢያ እድሜዋ እግሯን አንስታ ፏለለች” አለች በብስጭት፡፡
ባለ ኪዮስኳና ዘርፌ ፀበኞች ነበሩ፡፡ ሁለቱም በመንደሩ ውስጥ የተሰሚነት የክብር ጉዳይ
ያጋጫቸዋል፡፡ አቲዬ ባለኪዮስኳ ጋር ሰራተኛ ሆና ቀረች፡፡ እጣ ፋንታን በመሸሽ አያመልጡትም ::
ይህች ሴት የምትደገፈው ሁሉ እሾህ፡ የምትረግጠው ሁሉ አረንቋ ይሆንባት ዘንድ ድፍን አዲስ አበባን ማነው በአሜኬላ የሞላባት? የእኔ ከርታታ ኩንታል ሙሉ የምስር ክክ፡ ሱቅ ሙሉ
ባልትና ማዘጋጀት፣ የሚሸጥ እንጀራ መጠፍጠፍ ነበር የጠበቃት፡፡ ልብሷ ሰውነቷ ላይ ተበጣጥቆ ፀጉሯ ላይዋ ላይ ጀልቶ ብልጣ ብልጧ ባለኪዮስክ ጉልበቷን እንደ ምስጥ መጠጠቻት፡፡
ደም መጣጭ የደሀ ክብር መጣጭ ! መንደር ሙሉ መዥገር ! እቺ ሚሊየን አዲስአበቤ፣
አምራና ተውባ በየመንገዱ ሰበር ሰካ የምትል ወይዛዝርት፣ የሚንጎማለል ሸበላ ሁሉ፣ 'የሰው
ላብ ገንዘቤ ውስጥ የለም ብለህ ማል ቢባል እግሬ አውጭኝ በሚል ሯጭ መንገዱ በተሞላ
ታላቁ የሽሽት ሩጫ !!
✨አላለቀም✨
ነበር የሚገርመው)፡፡ ይሄ የአምሳ ምናምን ዓመት ሰው አንዲት ፍሬ ልጅ ሊያጠምድ ዘርፌ የምትባል አቃጣሪ ያረጀች አሮጌ መረብ ሰፈሩ ላይ ወረወረ፡፡ “ዘርፍዬ እንዴት ያለችውን ልጅ አመጣሻት ደሞ! » ሲል ይታየኛል በዓይነ ህሊናዬ፡፡
አቲዬ የምትባል ሚስኪን አሳ የህይወትን ዋና ልትለማመድ ስትፍገመገም መረቡ ውስጥ ገባች፤ዘርፌ የምትባል ቁራጭ የአሳማ ስጋ የከፋት መንጠቆ ላይ ተሰክታ አቲዬን አታለለቻት፡፡
"አፀደ!”
"እመት እትዬ"
"ኤዲያ እንደ ባላገር እመት!' አትበይ፣ አቤት! ነው የሚባል፡፡ ነይ እስቲ ለጋሽ ቀለሙ ወተት
አድርሽለት!” አለች ዘርፌ፡፡
"እሽ!” ብላ የወተት ጠርሙሱን እንስታ ልትሄድ መንገድ ጀመረች - የእኔ ታዛዥ አቲዬ፡፡ ባልቴቷ ተቆጣች::
ነይ ወዲህ የምን መንካተት ነው እቴ..ማንም መደዴ ቤት የምትሄድ መሰላት እንዴ…እንዲህ ተንኳተሽ ትልቅ ሰው ቤት ...ምኗ ገልቱ ነሽ አንችዬ..በይ ፊትሽን ታጠቢ እግርሽንም እዛ ድንጋይ ላይ ፈትገሽ ታጠቢው።
አቲዬ ሰውነቷ ነክቶት የማያውቀውን ልብስ፣ እግሯ ተጫምቶት የማያውቀውን ጫማ ከእመቤቷ ተቸራት፡፡ በደስታ ሰከረች፡፡ ስለከተሜ ሰዎች ቸርነት የሰማችው ቃል ስጋ ለብሶ ፊቷ ሲገተር አየችው:: አበባ መሰለች፡፡ ድሮም አበባ ነበርች !! እንኳን ያኔ አሁንም ውብ ናት የእኔ እናት !!
በዚህ ዓይነት ቀለሙ ለሚባለው ውሻ ወተት አደረሰች፡፡ደጋገመችው፡፡ ስትመላለስ ቆየች፡፡
የቀለመወርቅ ቤት ቤተመቅደስ መሰላት፣ ካልታጠቡ የማይረግጡት፡፡ አንድ ሌላ ቀን ዘርፌ አቲዬን ጠራቻት፡፡
"አፀደ”
"እመ...አቤት እትዩ!” (እመት አትበይ የባላገር ነው' ተብላለቻ፡፡)
ጋሽ ቀለሙ አመም አድርጎታል፡፡ ቤት ሰውም የለ፣ ሂጂ እስቲ እህል ውሃ ስሪለት፡፡ እኛ እያለን
በረሀብ አይሞት መቸስ ጡር ነው፡፡”
"ምን አገኛቸው?!” አለች አቲዬ የኔ የዋህ በእባቦች ጨዋታ መሃል ንፁህ ልቧን በአደራ እያስቀመጠች፣
"ምን እንደነካው እሱኑ ጠይቂው፣ እኔ መች ሞልቶልኝ እየሁት ብለሽ” አለች ዘርፌ፡፡
አቲዬ ወደ አቶ ቀለሙ ሄደች፣ ዋለች፣ አደረች፡፡ ልታስታምም ሄዳ እድሜ ልኳን ህሊናዋ ውስጥ የሚመረቅዝ በሽታ ይዛ ተመለሰች: አቲዬ ከዛን ቀን ጀምሮ ቅስሟ ተሰበረ፡ ፈገግታዋ ጠፋ፡
አንገቷን ደፋች፡፡ ቀለመወርቅ ይሉት መዥገር ግን ወጣትነቷን የመጠጠው ይመስል አማረበት
አረማመዱ ሳይቀር እንደወጣት ሆነ፡፡ ግዴላችሁም እድሜም እንደገንዘብ ይነጠቃል፡፡ ይሄ
ሰው የእናቴን እድሜ በግፍ ነጥቋታል፡፡
አቲዬ በዚህ ልክ የሌለው መከፋት፥ መግለጫ አልባ በሆነ ቅስም መሰበር ውስጥ እንዳለች :
“አፀደ!” አለች አሰሪዋ ዘርፌ፡፡
አቲዩ "አቤት!" አላለችም፣ ዝም ብላ አቃጣሪዋ ፊት ሄዳ ቆመች፡፡ እመትን በስልጣኔ ስም "አቤትን'
ከክብሯ ጋር ቀምተዋት ምኑን አቤት ትበል…፡፡ ዘርፌ ትእዛዟን እንዲህ ስትል ጀመረች፣
“ጋሸ ቀለሙ ሴት ሂጃና…"
“አልሄድም !" አለች እንባ ተናንቋት፡፡
“ምናልሽ እንች እከከከከከ ጭቅቅትሽን ሳላቅቅልሽ እንዲህ አፍሽን ሞልተሽ ትሰድቢኝ " ባልቴቷ በያዘችው የኒኬል ሰሀን አቲዬን ፊቷ ላይ ደረገመቻትና፣ እች ደነዝ እጄን አሳመመችኝ አለች
ሰሀኑ የስሚንቶው ወለል ላይ ወድቆ ተቅጨለጨለ፡፡ አቲዩ በቀኝ እጇ ሰሀኑ ያረፈበትን ፊቷን
ሸፍና፣ አግሯ እንደመራት ወደ መኪና መንገዱ በረረች፡፡ ትንሽ እንደሄደች እዚሁ አሁን ትልቁ ዳቦ
ቤት የተሰራበት ቦታ ላይ አንዲት ኪዮስክ ነበረች፣ አንዳንዴ እቲዬ እየተላከች እቃ የምትገዛባት
ባለቤቷ የአቲዬን ወጣትነት ስታይ ሁሌ ምራቋን የምትውጥ (ለሰራተኝነት)…ጠራቻት፡፡
"አፀደ.አንችን እኮ ነው!”
ዝም፡፡
“ምን ሆነሻል ?
ዝም…እርምጃዋን ቀንሳ እየቆመች፡፡
“አንችን እኮ ነው!”
ዝም፡፡
“እንዴ ደግሞ ፊትሽ ምን ጉድ ነው? እረ ጉዴ፣ ምንድነው ይሄ ሁሉ ደም?"
አቲዬ ደነገጠች፡፡ እጇን ከፊቷ ላይ እንስታ ተመለከተችው፣ በደም ተሸፍኖ ነበር፡፡
አሁን ያፈነችው እንባ ፈነዳ፡፡ ከልጅነቷ ጀምሮ ውስጧ የተጠራቀመው ጩኸት እና እዬዬ፣
መንደሩን የሚያሸብር ዋይታ ሆነ፡፡ መንደርተኛው ተሰበሰቡ፡፡
ምንድን ነው?
እንዴ እትዩ ዘርፈ ሰራተኛ አይደለችም እንዴ ምን አገኛት?”
ማናባቱ ነው የዘርፍዬን ልጅ እንዲህ ያደረጋት? ..ዘርፌ ዘርፍዬ…ወይዘሮ ዘርፌ እሜቴ ዘርፌ የዘርፌ ሰራተኛ
ሰው በመሆኗ ሳይሆን፣ በዘርፌ ንብረትነቷ መንደሩ ዘራፍ አለ፡፡
አኮ ማናባቱ ነው የነካት?
ተናገሪ ማነው የመታሽ?”
ዘርፌ ራሷ !
ዝም ሰፈሩ !! ዝምምምምምምምምምምምምምምምምምምምምምምም!!
ምን ኣጥፍተሽ ነው" አሏት አቲዩን፡፡
እሷም ዝም !
ታስታውቃለች ተንኮለኛ፡፡ ዝም ያለችው ጥፋቷ ቢሆን ነው።"
አንዲች ዘርፌ.የሴት ወንድ መች መጨማለቅ ትወድና..አንድ ነገር ስታደርጊ አግኝታሽ ነው::”
መንደርተኛው ዘባረቅ፡፡ ይሄ ዘባራቂ ሁሉ…፡፡ ይሄ ጉዳይ ከሆነ ስንትና ስንት ዓመቱ ሰፈሩ ግን አሁንም ዘባራቂ ነው !! ባለ ኪዮስኳ ብቻ ለአቲዬ አገዘች፡፡ “የሚመታ ይምታት፣ ምንስ
ብታደርግ እንዲህ ደም በደም እስከትሆን ትመታታለች፡፡ እች ጥጋበኛ ባልቴት፣ ምነው እች
ሴትዮ በመቁረቢያ እድሜዋ እግሯን አንስታ ፏለለች” አለች በብስጭት፡፡
ባለ ኪዮስኳና ዘርፌ ፀበኞች ነበሩ፡፡ ሁለቱም በመንደሩ ውስጥ የተሰሚነት የክብር ጉዳይ
ያጋጫቸዋል፡፡ አቲዬ ባለኪዮስኳ ጋር ሰራተኛ ሆና ቀረች፡፡ እጣ ፋንታን በመሸሽ አያመልጡትም ::
ይህች ሴት የምትደገፈው ሁሉ እሾህ፡ የምትረግጠው ሁሉ አረንቋ ይሆንባት ዘንድ ድፍን አዲስ አበባን ማነው በአሜኬላ የሞላባት? የእኔ ከርታታ ኩንታል ሙሉ የምስር ክክ፡ ሱቅ ሙሉ
ባልትና ማዘጋጀት፣ የሚሸጥ እንጀራ መጠፍጠፍ ነበር የጠበቃት፡፡ ልብሷ ሰውነቷ ላይ ተበጣጥቆ ፀጉሯ ላይዋ ላይ ጀልቶ ብልጣ ብልጧ ባለኪዮስክ ጉልበቷን እንደ ምስጥ መጠጠቻት፡፡
ደም መጣጭ የደሀ ክብር መጣጭ ! መንደር ሙሉ መዥገር ! እቺ ሚሊየን አዲስአበቤ፣
አምራና ተውባ በየመንገዱ ሰበር ሰካ የምትል ወይዛዝርት፣ የሚንጎማለል ሸበላ ሁሉ፣ 'የሰው
ላብ ገንዘቤ ውስጥ የለም ብለህ ማል ቢባል እግሬ አውጭኝ በሚል ሯጭ መንገዱ በተሞላ
ታላቁ የሽሽት ሩጫ !!
✨አላለቀም✨
👍31👏4
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የሁለት ከዋክብት መቀራረብ
አሁን እንግዲህ ማሪየስ አድጎ የሚያስቀና መልከ መልካም ወጣት ሆኖአል፡፡ አፍንጫው ስልክክ ብሉ ከቁመቱ ዘለግ ያለና በሩቁ የሴቶች ዓይን የሚስብ ጎረምሳ ነው፡፡ ረጋ ብሎ ሲራመድ የዋህነቱ ከፊቱ ይነበባል፡፡ ጭምትና አሳቢ ከመሆኑም በላይ ለአዋቂነቱ ወደር የለውም
ማሪየስ አንደበቱ የሚጣፍጥ፣ ከንፈሩ ወለላ፣ ጥርሱ ከወተት የነጣ ፈገግታው ውሃ የሚያደርግ ስለሆነ አሟልቶ የሰጠው ወጣት ነው::
ድኅነት አኮማትሮት የተቀዳደደ ልብስ ይለብስ በነበረበት ጊዜ እንኳ ልጃገረዶች በአጠገቡ ሲያልፉ ሰርቀው እንደሚያዩት ያውቃል፡፡ እርሱ ግን አቀርቅሮ በመሄድ ይሸሻቸዋል፡፡ የለበሰው ልብስ እያዩ የሚሳለቁበት እንጂ
በውበቱ ተስበው እንደሆነ አይገነዘብም ነበር፡፡ እውነታው ግን በውበቱ በቁመናው ተማርከው ነበር የሚያፈጥጡበት::
ከሚያፈጥጡበት ሴቶች መካከል ሁለቱን ግን አይሸሽም፡፡ እነርሱ
ባለጢማምዋ አሮጊት ሠራተኛውና አንዲት መንገድ የሚያያት ልጅ ናቸው ከአንድ ዓመት በፊት ጀምሮ ዘወትር ለሽርሽር በወጣ ቁጥር የሚያያት
አንዲት ልጅ ነበረች፡፡ በየቀኑ በአንድ በተወሰነ መንገድ ሲያልፍ አንድ ጠና ያለ ስልሣ ዓመት ገደማ የሚሆነው ሽማግሌና አንዲት ልጅ ዘወትር ከአንድ ቦታ ጎን ለጎን ቁጭ ብለው ያያቸዋል፡፡ ሰውዬው ኮስተር ያለና ጡረታ የወጣ ወታደር ይመስላል:: ሀዘን ከፊቱ ላይ ይነበባል:: እርሱን ደፍሮ
ለማናገር ያስፈራል::
አብራው የምትቀመጠዋን ልጅ ማሪየስ በመጀመሪያ ያያት እለት
አሥራ ሦስት ወይም አሥራ አራት ዓመት ቢሆናት ነው ብሎ ገምቷል
በመጀመሪያ ሲያያት ይህን ያህል መልክዋ የሚስብ አልመሰለውም ነበር በኋላ ስታድግ ግን በጣም ቆንጆ ሆነችበት:: ልብስዋ የገዳም ተማሪ ዩኒፎርም ነው። ሽማግሌውና ልጅትዋ ጎን ለጎን ቁጭ ብለው ለተመለከተ አባትና ልጅ ለመሆናቸው አያጠራጥርም።
ማሪየስ በአጠገባቸው ሲያልፍ ሁለትና ሦስት ቀን ድረስ እነዚ ሰዎች ምንድን ናቸው ብሎ ራሱን ከመጠየቅ ሌላ ብዙ አልተጨነቀበትም እነርሱ ግን እንዲያውም ያዩት አይመስልም:: ሁለቱ ሲገናኙ የራሳቸው
ጨዋታ ይጫወታሉ እንጂ ለአለፈና ለአገደመ ደንታ አልነበራቸውም ልጅትዋ እየሳቀች ሳታቋርጥ ለረጅም ጊዜ ታወራላች:: ሽማግሌው
በመጠኑ ነው የሚያወራው አስተያየቱ አባት ለልጁ ያለውን ፍቅር ያመለክታል፡:
በዚያ መንገድ በየቀኑ መጓዝ እንደልምድ አድርጎ ወስዶታል፡፡ በየቀኑ በዚያ ሲያልፍ ደግሞ እነዚያን አባትና ልጅ ከተወሰነ ቦታ ተቀምጠው ያያቸዋል፡፡ ማሪየስ በመንገዱ አንድ ጊዜ ብቻ ማለፍ ሳይሆን በቀን አምስት ወይም ስድስት ጊዜም የሚያልፍበት ቀን አለ፡፡ እንግዲህ ሰዎቹን በየቀኑ
አምስት ወይም ስድስት ጊዜ ያያቸዋል ማለት ነው:: ግን ሁለቱም ወገን ሰላምታ አይለዋወጡም፡፡ እርግጥ ነው ሁለቱ ሰዎች በየቀኑ በተወሰነ
ሰዓት ከዚያች ከተወሰነች ሥፍራ ስለሚቀመጡ የማሪየስን ብቻ ሳይሆን የሌሎችም ከዚያ ሥፍራ አየር ለመቀበል የሚወጡ ተማሪዎች ዓይን መማረካቸው አልቀረም፡፡ ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ኩርፌይራክም ይገኛል:: ማሪየስ በልጅትዋ ስለተሳበና ዘወትር የምትለብሰው ልብስ ጥቁር ስለነበር «ወት/ጥቁር»፣ አባትየው ደግሞ ብዙውን ጊዜ ነጭ ልብስ ስለሚለብስ
«ክቡር ነጭ» የሚል ስም አወጣላቸው:: ስሞቹ እየተለመዱ ስለሄዱ ተማሪዎች በዚያ ባለፉ ቁጥር «ክቡር ነጭና ወት/ ጥቁር ሥፍራ ሥፍራቸውን ይዘዋል» እያሉ ይፎትቷቸዋል፡፡
እኛም ለአገላለጽ ስለሚያመች ስለታሪካቸው ስንናገር በዚሁ ስም
እንጠራቸዋለን፡፡ ማሪየስ በየቀኑ ለአንድ ዓመት ሙሉ ሲያያቸው ክቡር ነጭን ይወዳል:: ወ/ት ጥቁርን ግን እስከዚህም አላፈቀራትም፤ ግን አይጠላትም::
በሁለተኛው ዓመት ማሪየስ ለራሱ እንኳን ግልጽ ባልሆነ ምክንያት
በዚያ መንገድ ለስድስት ወር መንሸራሸሩን ያቆማል፡፡ ከስድስት ወር በኋላ አንድ ቀን በዚያ ያልፋል:: አየሩ ጥሩ ስለነበር ማሪየስ ደስ ብሎት ነበር
የሚራመደው:: ከዚያች ከተወሰነች ሥፍራ ሲደርስ አባትና ልጅ አሁንም ከዚያች ከተወሰነች ሥፍራ ተቀምጠው ይጫወታሉ፡፡
ሲቀርባቸው በሰውዬው ላይ ምንም ለውጥ አላየም:: ልጅትዋ ግን በጣም ተለውጣለች:: በጣም ቆንጆ ሆና ታየችው:: በአጠገባቸው ሲያልፍ
አቀርቅራ ስለነበር ዓይኖችዋን ለማየት አልቻለም::
በመጀመሪያ የልጅትዋ ታላቅ እህት እንጂ እርስዋ አልመሰለችውም::
ግን እየተመላለሰ ሲያያት ራስዋ መሆንዋን አረጋገጠ፡፡ በስድስት ወር ጊዜ እጅግ ውስጥ ትልቅ ሴት መሰለች:: የደረሰችበት እድሜ እንደ አበባ የምትፈነዳበትና
አምራና ደምቃ የምትታይበት ነበር፡፡ በድንገት የጽጌረዳ አበባ መሰለች::የትናንትናዋ የዋህ ሕፃን የዛሬዋ አደገኛ ሴት ሆነች::
ቁመትዋ ብቻ አልነበረም ያደገው መልኳም ጭምር ነበር የተለወጠው:: በዝናብ ወራት ዛፎች ብዙ ቅርንጫፎችን እ
አብቅለው በመስከረምና በጥቅምት ወራት በአበቦች ቅርንጫፎቻቸውን እንደሚያጌጡ
ሁሉ ልጅትዋም በአለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በመልክ አበባ አጌጠች፥ ተዋበች::
ጥቁር ልብስዋን አውልቃ ከቀለምዋ ጋር የሚሄድ ያሸበረቀ ልብ ለበሰች:: በአጠገብዋ ሲያልፉ የምትቀባው ሽቶ ያውዳል፤ የልጅነት ጠረንዋ ልብ ይሰነጥቃል::
በሁለተኛው ቀን ማሪየስ በአጠገብዋ ሲያልፍ ቀና ብላ አየችው::የተለየ ስሜት አልሰጣትም:: ማሪየስ ሌላ ነገር እያሰበ መንገዱን ቀጠለ። አራት ወይም አምስት ጊዜ እየተመላለሰ በልጅትዋ አጠገብ አለፈ።
እንደለመደው ለመንሸራሸር ነበር እንጂ ዞር ብሎ እንኳን አላያትም፡፡
በሚቀጥሉት ቀናት የሽርሽር ሰዓቱን ጠብቆ በዚያ አለፈ፡፡ ግን ወደ እነዚያ ሁለት ሰዎች ብዙም አልዞረም:: ልጅትዋ መለዋወጥዋንና ቆንጆ
መሆንዋን ካረጋገጠ በኋላ ከወጥመድዋ እንዳይገባ ቸለል ማለቱን መረጠ።የሚያልፈው ግን እርስዋ ከምትቀመጥበት መቀመጫ በጣም ቀርቦ ነበር፡፡
በጣም ደስ የሚል ቀን ነው:: ማሪየስ ልቡን ገልጦ የተፈጥሮ ውበት ራሱን አበርክቷል፡፡ የተፈጥሮ ውበት መላ ሕሊናውን ስለያዘበት ሌላ ነገር
ከጭንቅላቱ ውስጥ ሊገባ አልቻለም:: የተፈጥሮን ውበት እያሰላሰለ በተለመደው ሥፍራ ሲያልፍ የልጅትዋና የእርሱ ዓይን ግጥም አሉ፡፡ዓይንዋ ውስጥ ምን አለ? ማሪየስ እንዲነግረን ብንጠይቀው እንኳን ሊነግረን
አይችልም:: ልብን የሚሰልብ ነገር አለው:: ግን ዓይንነቱ ያው ዓይን ነው።
ሆኖም አንድ አይነት እንግዳ የሆነ ብልጭታ አለው።
ዓይንዋን መለስ አደረገችው:: እርሱም መንገዱን ቀጠለ፡፡
ዓይንዋን ሲያየው ያ የምናውቀው ገራገሩ የልጅ ዓይን አልነበረም፡፡
ምሥጢራዊ ጥልቀት ነበረው:: ገለጥ አድርጋ ወዲያው ነው የመለሰችው፡፡
እያንዳንድዋ ወጣት ልጃገረድ የዚህ የተለየ አስተያየት የምታይበት ጊዜ አላት:: በዚያች ሰዓት ከዓይንዋ ለሚገባ ወዮለት!
ገና ምንነትዋን የማታውቅ ነፍስ የመጀመሪያ እይታ ከጎሕ መቅደድ
ጋር ይመሳሰላል፡፡ ጎሕ ሲቀድ አንድ የማይታወቅና የሚያበራ ነገር ከእንቅልፉ ሚነቃበት ሰዓት ነው:: ጎሕ ሲቀድ ያልታሰበ ውበት፧ ያልታሰበ ድምቀት ያልተጠበቀ ነገር ያሳያል፡፡ እንዲሁም የፈነዳች አበባ የምትመስል ልጃገረድ እይታ ምንም ሳይታወቅ ካልታሰበ ወጥመድ ውስጥ ልብን አጥምዶና ያልታሰበ ጭንቀት ውስጥ ወዝፎ ካልተጠበቀ መንከራተት ያደርሳል:: ይህ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የሁለት ከዋክብት መቀራረብ
አሁን እንግዲህ ማሪየስ አድጎ የሚያስቀና መልከ መልካም ወጣት ሆኖአል፡፡ አፍንጫው ስልክክ ብሉ ከቁመቱ ዘለግ ያለና በሩቁ የሴቶች ዓይን የሚስብ ጎረምሳ ነው፡፡ ረጋ ብሎ ሲራመድ የዋህነቱ ከፊቱ ይነበባል፡፡ ጭምትና አሳቢ ከመሆኑም በላይ ለአዋቂነቱ ወደር የለውም
ማሪየስ አንደበቱ የሚጣፍጥ፣ ከንፈሩ ወለላ፣ ጥርሱ ከወተት የነጣ ፈገግታው ውሃ የሚያደርግ ስለሆነ አሟልቶ የሰጠው ወጣት ነው::
ድኅነት አኮማትሮት የተቀዳደደ ልብስ ይለብስ በነበረበት ጊዜ እንኳ ልጃገረዶች በአጠገቡ ሲያልፉ ሰርቀው እንደሚያዩት ያውቃል፡፡ እርሱ ግን አቀርቅሮ በመሄድ ይሸሻቸዋል፡፡ የለበሰው ልብስ እያዩ የሚሳለቁበት እንጂ
በውበቱ ተስበው እንደሆነ አይገነዘብም ነበር፡፡ እውነታው ግን በውበቱ በቁመናው ተማርከው ነበር የሚያፈጥጡበት::
ከሚያፈጥጡበት ሴቶች መካከል ሁለቱን ግን አይሸሽም፡፡ እነርሱ
ባለጢማምዋ አሮጊት ሠራተኛውና አንዲት መንገድ የሚያያት ልጅ ናቸው ከአንድ ዓመት በፊት ጀምሮ ዘወትር ለሽርሽር በወጣ ቁጥር የሚያያት
አንዲት ልጅ ነበረች፡፡ በየቀኑ በአንድ በተወሰነ መንገድ ሲያልፍ አንድ ጠና ያለ ስልሣ ዓመት ገደማ የሚሆነው ሽማግሌና አንዲት ልጅ ዘወትር ከአንድ ቦታ ጎን ለጎን ቁጭ ብለው ያያቸዋል፡፡ ሰውዬው ኮስተር ያለና ጡረታ የወጣ ወታደር ይመስላል:: ሀዘን ከፊቱ ላይ ይነበባል:: እርሱን ደፍሮ
ለማናገር ያስፈራል::
አብራው የምትቀመጠዋን ልጅ ማሪየስ በመጀመሪያ ያያት እለት
አሥራ ሦስት ወይም አሥራ አራት ዓመት ቢሆናት ነው ብሎ ገምቷል
በመጀመሪያ ሲያያት ይህን ያህል መልክዋ የሚስብ አልመሰለውም ነበር በኋላ ስታድግ ግን በጣም ቆንጆ ሆነችበት:: ልብስዋ የገዳም ተማሪ ዩኒፎርም ነው። ሽማግሌውና ልጅትዋ ጎን ለጎን ቁጭ ብለው ለተመለከተ አባትና ልጅ ለመሆናቸው አያጠራጥርም።
ማሪየስ በአጠገባቸው ሲያልፍ ሁለትና ሦስት ቀን ድረስ እነዚ ሰዎች ምንድን ናቸው ብሎ ራሱን ከመጠየቅ ሌላ ብዙ አልተጨነቀበትም እነርሱ ግን እንዲያውም ያዩት አይመስልም:: ሁለቱ ሲገናኙ የራሳቸው
ጨዋታ ይጫወታሉ እንጂ ለአለፈና ለአገደመ ደንታ አልነበራቸውም ልጅትዋ እየሳቀች ሳታቋርጥ ለረጅም ጊዜ ታወራላች:: ሽማግሌው
በመጠኑ ነው የሚያወራው አስተያየቱ አባት ለልጁ ያለውን ፍቅር ያመለክታል፡:
በዚያ መንገድ በየቀኑ መጓዝ እንደልምድ አድርጎ ወስዶታል፡፡ በየቀኑ በዚያ ሲያልፍ ደግሞ እነዚያን አባትና ልጅ ከተወሰነ ቦታ ተቀምጠው ያያቸዋል፡፡ ማሪየስ በመንገዱ አንድ ጊዜ ብቻ ማለፍ ሳይሆን በቀን አምስት ወይም ስድስት ጊዜም የሚያልፍበት ቀን አለ፡፡ እንግዲህ ሰዎቹን በየቀኑ
አምስት ወይም ስድስት ጊዜ ያያቸዋል ማለት ነው:: ግን ሁለቱም ወገን ሰላምታ አይለዋወጡም፡፡ እርግጥ ነው ሁለቱ ሰዎች በየቀኑ በተወሰነ
ሰዓት ከዚያች ከተወሰነች ሥፍራ ስለሚቀመጡ የማሪየስን ብቻ ሳይሆን የሌሎችም ከዚያ ሥፍራ አየር ለመቀበል የሚወጡ ተማሪዎች ዓይን መማረካቸው አልቀረም፡፡ ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ኩርፌይራክም ይገኛል:: ማሪየስ በልጅትዋ ስለተሳበና ዘወትር የምትለብሰው ልብስ ጥቁር ስለነበር «ወት/ጥቁር»፣ አባትየው ደግሞ ብዙውን ጊዜ ነጭ ልብስ ስለሚለብስ
«ክቡር ነጭ» የሚል ስም አወጣላቸው:: ስሞቹ እየተለመዱ ስለሄዱ ተማሪዎች በዚያ ባለፉ ቁጥር «ክቡር ነጭና ወት/ ጥቁር ሥፍራ ሥፍራቸውን ይዘዋል» እያሉ ይፎትቷቸዋል፡፡
እኛም ለአገላለጽ ስለሚያመች ስለታሪካቸው ስንናገር በዚሁ ስም
እንጠራቸዋለን፡፡ ማሪየስ በየቀኑ ለአንድ ዓመት ሙሉ ሲያያቸው ክቡር ነጭን ይወዳል:: ወ/ት ጥቁርን ግን እስከዚህም አላፈቀራትም፤ ግን አይጠላትም::
በሁለተኛው ዓመት ማሪየስ ለራሱ እንኳን ግልጽ ባልሆነ ምክንያት
በዚያ መንገድ ለስድስት ወር መንሸራሸሩን ያቆማል፡፡ ከስድስት ወር በኋላ አንድ ቀን በዚያ ያልፋል:: አየሩ ጥሩ ስለነበር ማሪየስ ደስ ብሎት ነበር
የሚራመደው:: ከዚያች ከተወሰነች ሥፍራ ሲደርስ አባትና ልጅ አሁንም ከዚያች ከተወሰነች ሥፍራ ተቀምጠው ይጫወታሉ፡፡
ሲቀርባቸው በሰውዬው ላይ ምንም ለውጥ አላየም:: ልጅትዋ ግን በጣም ተለውጣለች:: በጣም ቆንጆ ሆና ታየችው:: በአጠገባቸው ሲያልፍ
አቀርቅራ ስለነበር ዓይኖችዋን ለማየት አልቻለም::
በመጀመሪያ የልጅትዋ ታላቅ እህት እንጂ እርስዋ አልመሰለችውም::
ግን እየተመላለሰ ሲያያት ራስዋ መሆንዋን አረጋገጠ፡፡ በስድስት ወር ጊዜ እጅግ ውስጥ ትልቅ ሴት መሰለች:: የደረሰችበት እድሜ እንደ አበባ የምትፈነዳበትና
አምራና ደምቃ የምትታይበት ነበር፡፡ በድንገት የጽጌረዳ አበባ መሰለች::የትናንትናዋ የዋህ ሕፃን የዛሬዋ አደገኛ ሴት ሆነች::
ቁመትዋ ብቻ አልነበረም ያደገው መልኳም ጭምር ነበር የተለወጠው:: በዝናብ ወራት ዛፎች ብዙ ቅርንጫፎችን እ
አብቅለው በመስከረምና በጥቅምት ወራት በአበቦች ቅርንጫፎቻቸውን እንደሚያጌጡ
ሁሉ ልጅትዋም በአለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በመልክ አበባ አጌጠች፥ ተዋበች::
ጥቁር ልብስዋን አውልቃ ከቀለምዋ ጋር የሚሄድ ያሸበረቀ ልብ ለበሰች:: በአጠገብዋ ሲያልፉ የምትቀባው ሽቶ ያውዳል፤ የልጅነት ጠረንዋ ልብ ይሰነጥቃል::
በሁለተኛው ቀን ማሪየስ በአጠገብዋ ሲያልፍ ቀና ብላ አየችው::የተለየ ስሜት አልሰጣትም:: ማሪየስ ሌላ ነገር እያሰበ መንገዱን ቀጠለ። አራት ወይም አምስት ጊዜ እየተመላለሰ በልጅትዋ አጠገብ አለፈ።
እንደለመደው ለመንሸራሸር ነበር እንጂ ዞር ብሎ እንኳን አላያትም፡፡
በሚቀጥሉት ቀናት የሽርሽር ሰዓቱን ጠብቆ በዚያ አለፈ፡፡ ግን ወደ እነዚያ ሁለት ሰዎች ብዙም አልዞረም:: ልጅትዋ መለዋወጥዋንና ቆንጆ
መሆንዋን ካረጋገጠ በኋላ ከወጥመድዋ እንዳይገባ ቸለል ማለቱን መረጠ።የሚያልፈው ግን እርስዋ ከምትቀመጥበት መቀመጫ በጣም ቀርቦ ነበር፡፡
በጣም ደስ የሚል ቀን ነው:: ማሪየስ ልቡን ገልጦ የተፈጥሮ ውበት ራሱን አበርክቷል፡፡ የተፈጥሮ ውበት መላ ሕሊናውን ስለያዘበት ሌላ ነገር
ከጭንቅላቱ ውስጥ ሊገባ አልቻለም:: የተፈጥሮን ውበት እያሰላሰለ በተለመደው ሥፍራ ሲያልፍ የልጅትዋና የእርሱ ዓይን ግጥም አሉ፡፡ዓይንዋ ውስጥ ምን አለ? ማሪየስ እንዲነግረን ብንጠይቀው እንኳን ሊነግረን
አይችልም:: ልብን የሚሰልብ ነገር አለው:: ግን ዓይንነቱ ያው ዓይን ነው።
ሆኖም አንድ አይነት እንግዳ የሆነ ብልጭታ አለው።
ዓይንዋን መለስ አደረገችው:: እርሱም መንገዱን ቀጠለ፡፡
ዓይንዋን ሲያየው ያ የምናውቀው ገራገሩ የልጅ ዓይን አልነበረም፡፡
ምሥጢራዊ ጥልቀት ነበረው:: ገለጥ አድርጋ ወዲያው ነው የመለሰችው፡፡
እያንዳንድዋ ወጣት ልጃገረድ የዚህ የተለየ አስተያየት የምታይበት ጊዜ አላት:: በዚያች ሰዓት ከዓይንዋ ለሚገባ ወዮለት!
ገና ምንነትዋን የማታውቅ ነፍስ የመጀመሪያ እይታ ከጎሕ መቅደድ
ጋር ይመሳሰላል፡፡ ጎሕ ሲቀድ አንድ የማይታወቅና የሚያበራ ነገር ከእንቅልፉ ሚነቃበት ሰዓት ነው:: ጎሕ ሲቀድ ያልታሰበ ውበት፧ ያልታሰበ ድምቀት ያልተጠበቀ ነገር ያሳያል፡፡ እንዲሁም የፈነዳች አበባ የምትመስል ልጃገረድ እይታ ምንም ሳይታወቅ ካልታሰበ ወጥመድ ውስጥ ልብን አጥምዶና ያልታሰበ ጭንቀት ውስጥ ወዝፎ ካልተጠበቀ መንከራተት ያደርሳል:: ይህ
👍13😁2
ምትሃታዊ ኃይል ያለው ሳይወዱ በግድ ልብን ፈንቅሎ በመግባት እንደ ሽቶ ከሩቅ የሚጠራውና እንደ መርዝ ከቅርብ የሚያብሰለስለው ሕቅ ሕቅ፧ ያዝ
ለቀቅ፤ ሰፋ ጠበብ የሚያደርገውና ሳይታሰብ በድንገት አንቆ የሚይዘው ነገር ሰዎች ፍቅር ብለው ይጠሩታል፡፡ ይህ ፍቅር የሚሉት ነገር ማሪየስን
ጠለፈው::
ያን እለት ማታ ማሪየስ ወደ ቤት በተመለሰ ጊዜ የለበሰውን ልብስ
ወደ መስታወት ተመለከተው:: ግርማ ሞገስ የሌለውና በሰዎች ዘንድ ክብር ሊያጎናጽፍ የማይችል ልብስ መሆነን ለመጀመሪያ ጊዜ ተገነዘበ፡፡ ይህም ሞኝነት እንደሆነ አወቀ:: በሥራ ልብስ ሽርሽር መውጣት ስህተት መሆኑን
ደረሰበት:: ዘወትር የሚለብሰው የሥራ ልብስ የቀን ሠራተኛ እንዳስመሰለው አሁን ገና ገባው::
በሚቀጥለው ቀን ሽርሽር ከመሄዱ በፊት የክት ልብሱን ከቁም ሣጥን
አወጣ፡፡ አስተካክሎ ከለበሰና ፀጉሩን ጥሩ አድርጎ ካበጠረ በኋላ ወደ ሽርሽሩ ቦታ ሄደ:: ከሥፍራው እንደደረሰ ክቡር ነጭ እና ልጅትዋ ተቀምጠዋል፡፡
ኮቱን ቁልፍ ቆለፈ:: የተጨማደደ ካለ ቀጥ ብሎ እንዲዘረጋ ኮቱን ሳብ፤ሳብ፤ አሸት፧ አሸት አደረገው:: አባትና ልጅ ተቀምጠውበት ከነበረው ሥፍራ ደረሰ፡፡ ከሥፍራው እየተጠጋ ሲሄድ ከእርምጃው ዝግ እለ::
ለእርሱ እንኳን ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ሰዎቹ ከነበሩበት ሲደርስ ቀጥ ብሉ በመቆም ወደ አባትና ልጅ ፊቱን አዞረ:: በሌላ ቀን መንገዱን በመቀጠል
አልፎአቸው ነበር የሚሄደው:: የልጅትዋን ዓይን በመሳብ ትየው ወይም አትየው አይታወቅም:: ሆኖም ቀረም እርሱ ከአጠገብዋ ቀጥ ብሉ ራሱን ለትርኢት አቀረበ፡፡ ወደፊት ለመጓዝ ፈልጎ የስሜቱ ኃይል ጉልበቱን ስላፈሰሰበት መራመድ ተሳነው:: ልጅትዋ ሠርቃ ማየትዋን ተመለከተ::
በእርስዋ በኩል አፍጥጦ ማየቱን አልደፈረም:: ግን ሠረቅ አድርጎ
እንደተመለከተው ባለፈው ቀን የለበሰችውን ልብስ ለብሳ ከሽማግሌው ጋር ትጫወታለች፡፡ ወደፊት ጥቂት ተራምዶ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ እንደገና በቆንጆይቱ ልጅ አጠገብ አለፈ:: ልቡ በኃይል ይመታል:: ዞር ብሎ ሳያያትም
እርስዋ እንደምታየው አልተጠራጠረም:: አፍጥጣ የምታየው መሆኑን በእሳብ ሲያሰላስል የሆነ ነገር አደናቀፈው::
ሰዎቹ ከነበሩበት ጥቂት እልፍ እንዳለ ከድንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡
ከዚያ በፊት አልፎ ይሄዳል እንጂ ተቀምጦ አያውቅም:: ከሩብ ሰዓት በኋላ ተነስቶ እንደገና ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ሰውዬውም ሳያየኝ አይቀርም የሚል እምነት ስላደረበት እንደማፈር አለና ወደ መሬት አቀርቅሮ ነው መንገዱን
የቀጠለው:: ወደ ቤቱ ሄደ::
ያን እለት ማታ እራት መብላቱን ረስቶ ከክፍሉ ውስጥ እንደተጋደመ ሁለት ሰዓት ሆነ፡፡ ከዚያ በኋላ ሆቴል ቤት ፍለጋ ከመውጣት ደረቅ ዳቦ
መብላቱን ስለመረጠ ደረቅ ዳቦ ቆርጥሞ ልብሱን አውልቆ ከመስቀያ ላይ ከሰቀለ በኋላ ተኛ::
በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንት በየቀኑ ከሽርሽሩ ቦታ እየሄደ አባትና ልጅ ከሚቀመጡበት አካባቢ እየሄደ ምክንያቱን ሳያውቅ ከዚያ ይቀመጣል::ልጅትዋን ባያት ቁጥር በየቀኑ በይበልጥ የቆነጀች ይመስለዋል::
በሁለተኛው ሳምንት መጨረሻ ገደማ ያልተጠበቀ ነገር ይሆናል:: "ማሪየስ ከተለመደው ቦታ ቁጭ ብሎ መጽሐፍ ያነባል፡፡ ግን መጽሐፉን ይያዘው እንጂ እንደ እውነቱ ከሆነ አያነበውም ነበር፡፡ ለሁለት ሰዓት ቁጭ ብሎ ከመጽሐፉ ላይ ያፍጥጥ እንጂ አንድ ቅጠል እንኳን አልጨረሰም፡፡
ድንገት ቀና ሲል አንድ ነገር በማየቱ መላ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡ ልጅትዋ
የአባትዋን ክርን ይዛ ወደ እርሱ ስትመጣ ተመለከተ:: ማሪየስ ገልጦት የነበረውን መጽሐፍ አጠፈ፡፡ መልሶ ገለጠው:: ለማንበብ ሞከረ፣ መላ ሰውነቱ ተቅበጠበጠ፡፡ በቀጥታ ወደ እርሱ ነው የሚመጡት:: «ወይኔ ኮተት
ጉዴ» ሲል አሰበ፡፡ «ምን ሊሉኝ ነው::አባትና ልጅ ቀስ ብለው ነው የሚራመዱት:: ሺህ ዓመት መሰለው:: ግን ለጥቂት ሰኮንድ ነው የተጓዙት፡፡
«በአጠገቤ ሊያልፉ ነው? ወይስ ሊያናግሩኝ ነው? ካለፈችም እኮ ከቅርብ ሆና ታየኛለች» ሲል ማሪየስ ተጨነቀ:: መጽሐፉ ላይ እንዳተኮረ ኮቴ ስለሰማ መቃረባቸውን አወቀ፡፡ ሽማግሌው በቁጣ የሚያየው መሰለው።
እንዳቀረቀረ ጥቂት ቆየ:: ቀና ቢል ከአጠገቡ ናቸው:: ወጣትዋ በአጠገቡ አለፈች፡፡ ስታልፍ ትኩር ብላ አየችው:: ስታየው ተኮሳትራ ስለነበረ ልቡ እንደ ከበሮ መታ::
አንጎሎ በእሳት የተያያዘ መሰለው:: «በአጠገቤ አለፈች እኮ! ደግሞ እንዴት ብላ ነው የምታየኝ!» እርሱ ካሰባት ይበልጥ ቆንጆ መሰለችው። አይ ቁንጅና፧ ዘፋኞችን አፍ የሚያስከፍት፤ ደራሲያንን ብዕር የሚያስጨብጥ
ቁንጅና! የሰውን ብቻ ሳይሆን የመልአክትን ውበት ያጣመረ ቁንጅና! በቅዠት ዓለም የሚዋኝ እንጂ በእውን ሰው ሆኖ ሰው የሚያይ አልመሰለውም፡፡ ጫማው ላይ ትንሽ አዋራ ስላየና እርስዋም ከነአዋራው ስላየችው ተናደደ፡፡
በዓይኑ ተከተላት:: ከዓይኑ በተሰወረች ጊዜ ብድግ ብሉ ተነስቶ እንደ እብድ ከወዲያ ወዲህ ይቅበጠበጥ ጀመር፡: እንደወፈፌም ብቻውን ሳቀ፣
ጮክ እያለ ተናገረ:: በፍቅር መያዙን በአካባቢው የነበረ ሁሉ አወቀበት::
ከዚያችሥፍራ በየቀኑ ሲመላለስ አንድ ወር ሙሉ አለፈ፡፡ የመሄጃው
ሰአት ከደረሰ ወደዚያ ከመሄድ የሚያስቀረው ነገር ጠፋ፡፡ «አገልግሎት ማበርከት ሄደ» እያለ ኩርፌይራክ ይሸረድደው ጀመር፡፡ በሄደ ቁጥር ልጅትዋ ታየዋለች።
ቀስ በቀስ እየደፈረ በመምጣቱ አባትና ልጅ ከሚቀመጡበት እየተጠጋ መጣ፡፡ አባትየው እንዳያውቅበት የተቻለውን ሁሉ አደረገ፡፡ መቀመጫውን
ጀርባ እንዲሆን መረጠ፡፡ ከዛፎች ወይም ከዚያ ከሚገኝ ሐውልት
ጀርባ ሆኖ ለልጅትዋ በግልጽ እንዲታይና ከአባትዋ ግን እንዲሰወር የሚያስችል
ስፍራ መርጦ ነበር የሚቀመጠው፡፡ አንዳንድ ጊዜ መጽሐፍ በእጁ ይዞ ዛፍ በመደገፍ ከግማሽ ሰዓት በላይ እየቆመ ያያታል፤ እርስዋም እየሰረቀች
ታየዋለች:፡ አመለካከቱ የጤና አለመሆኑን ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ገብቷታል፡፡ የእርስዋም የዓይን ምላሽ ነገር እንዳለበት አውቋል፡፡
ማሪየስ እንደዚያ ሲመላለስ አባባ ሸበቶም ሳይገባው አልቀረም::
አሁን ክቡር ነጭ በማለት ፋንታ አባባ ሸበቶ እያለ ነው የሚጠራው::ማርየስ ይከተላቸው እንደሆነ ለማየት ዘወትር ከሚቀመጡበት ተነስተው
መላ ስፍራ ይቀይሩ ጀመር፡፡ ማሪየስ ፈተና የተሰጠው መሆኑን ባለመጠርጠር ስተት ይሠራል፡፡ አባባ ሸበቶ ሰዓት እየቀያየረ ይመጣ ጀመር፡፡ አንዳንድ
ልጅትዋን ይዞ አይመጣም:: ልጅትዋ አብራ ካልመጣች ማሪየስ ቶሎ ይሄዳል፡፡ ሌላው ስህተት!
ሦስተኛ ከባድ ስህተት ልጅትዋ የት እንደምትኖር ለማወቅ መፈለጉ
፡፡ አንድ ቀን ተከትሉአቸው ሄደ:: መኖሪያቸውን አየ፡፡ መኖሪያቸውን
ካየ ጀምሮ ከሽርሽሩ ቦታ እስኪሄዱ ድረስ ጠብቆ ኋላ ኋላቸው እየተከተለ ይሸኛቸው ጀመር፡፡ አንድ ቀን ማታ አንደ ልማዱ ከቤታቸው ድረስ ተከትሎ
የድፍረቱ ብዛት ዘበኛውን አነጋገረው::
«አሁን የገቡት ሽማግሌ የሚኖሩት አንደኛ ፎቅ ላይ ነው ፧ አይደል?»
“አይ ሦስተኛ ፎቅ ላይ ነው የሚኖሩት፡፡»
በሚቀጥለው ቀን አባባ ሸበቶና ልጅትዋ ከሽርሽሩ ቦታ ቶሎ ሄዱ።
ለቀቅ፤ ሰፋ ጠበብ የሚያደርገውና ሳይታሰብ በድንገት አንቆ የሚይዘው ነገር ሰዎች ፍቅር ብለው ይጠሩታል፡፡ ይህ ፍቅር የሚሉት ነገር ማሪየስን
ጠለፈው::
ያን እለት ማታ ማሪየስ ወደ ቤት በተመለሰ ጊዜ የለበሰውን ልብስ
ወደ መስታወት ተመለከተው:: ግርማ ሞገስ የሌለውና በሰዎች ዘንድ ክብር ሊያጎናጽፍ የማይችል ልብስ መሆነን ለመጀመሪያ ጊዜ ተገነዘበ፡፡ ይህም ሞኝነት እንደሆነ አወቀ:: በሥራ ልብስ ሽርሽር መውጣት ስህተት መሆኑን
ደረሰበት:: ዘወትር የሚለብሰው የሥራ ልብስ የቀን ሠራተኛ እንዳስመሰለው አሁን ገና ገባው::
በሚቀጥለው ቀን ሽርሽር ከመሄዱ በፊት የክት ልብሱን ከቁም ሣጥን
አወጣ፡፡ አስተካክሎ ከለበሰና ፀጉሩን ጥሩ አድርጎ ካበጠረ በኋላ ወደ ሽርሽሩ ቦታ ሄደ:: ከሥፍራው እንደደረሰ ክቡር ነጭ እና ልጅትዋ ተቀምጠዋል፡፡
ኮቱን ቁልፍ ቆለፈ:: የተጨማደደ ካለ ቀጥ ብሎ እንዲዘረጋ ኮቱን ሳብ፤ሳብ፤ አሸት፧ አሸት አደረገው:: አባትና ልጅ ተቀምጠውበት ከነበረው ሥፍራ ደረሰ፡፡ ከሥፍራው እየተጠጋ ሲሄድ ከእርምጃው ዝግ እለ::
ለእርሱ እንኳን ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ሰዎቹ ከነበሩበት ሲደርስ ቀጥ ብሉ በመቆም ወደ አባትና ልጅ ፊቱን አዞረ:: በሌላ ቀን መንገዱን በመቀጠል
አልፎአቸው ነበር የሚሄደው:: የልጅትዋን ዓይን በመሳብ ትየው ወይም አትየው አይታወቅም:: ሆኖም ቀረም እርሱ ከአጠገብዋ ቀጥ ብሉ ራሱን ለትርኢት አቀረበ፡፡ ወደፊት ለመጓዝ ፈልጎ የስሜቱ ኃይል ጉልበቱን ስላፈሰሰበት መራመድ ተሳነው:: ልጅትዋ ሠርቃ ማየትዋን ተመለከተ::
በእርስዋ በኩል አፍጥጦ ማየቱን አልደፈረም:: ግን ሠረቅ አድርጎ
እንደተመለከተው ባለፈው ቀን የለበሰችውን ልብስ ለብሳ ከሽማግሌው ጋር ትጫወታለች፡፡ ወደፊት ጥቂት ተራምዶ ወደኋላ ተመለሰ፡፡ እንደገና በቆንጆይቱ ልጅ አጠገብ አለፈ:: ልቡ በኃይል ይመታል:: ዞር ብሎ ሳያያትም
እርስዋ እንደምታየው አልተጠራጠረም:: አፍጥጣ የምታየው መሆኑን በእሳብ ሲያሰላስል የሆነ ነገር አደናቀፈው::
ሰዎቹ ከነበሩበት ጥቂት እልፍ እንዳለ ከድንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡
ከዚያ በፊት አልፎ ይሄዳል እንጂ ተቀምጦ አያውቅም:: ከሩብ ሰዓት በኋላ ተነስቶ እንደገና ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ሰውዬውም ሳያየኝ አይቀርም የሚል እምነት ስላደረበት እንደማፈር አለና ወደ መሬት አቀርቅሮ ነው መንገዱን
የቀጠለው:: ወደ ቤቱ ሄደ::
ያን እለት ማታ እራት መብላቱን ረስቶ ከክፍሉ ውስጥ እንደተጋደመ ሁለት ሰዓት ሆነ፡፡ ከዚያ በኋላ ሆቴል ቤት ፍለጋ ከመውጣት ደረቅ ዳቦ
መብላቱን ስለመረጠ ደረቅ ዳቦ ቆርጥሞ ልብሱን አውልቆ ከመስቀያ ላይ ከሰቀለ በኋላ ተኛ::
በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንት በየቀኑ ከሽርሽሩ ቦታ እየሄደ አባትና ልጅ ከሚቀመጡበት አካባቢ እየሄደ ምክንያቱን ሳያውቅ ከዚያ ይቀመጣል::ልጅትዋን ባያት ቁጥር በየቀኑ በይበልጥ የቆነጀች ይመስለዋል::
በሁለተኛው ሳምንት መጨረሻ ገደማ ያልተጠበቀ ነገር ይሆናል:: "ማሪየስ ከተለመደው ቦታ ቁጭ ብሎ መጽሐፍ ያነባል፡፡ ግን መጽሐፉን ይያዘው እንጂ እንደ እውነቱ ከሆነ አያነበውም ነበር፡፡ ለሁለት ሰዓት ቁጭ ብሎ ከመጽሐፉ ላይ ያፍጥጥ እንጂ አንድ ቅጠል እንኳን አልጨረሰም፡፡
ድንገት ቀና ሲል አንድ ነገር በማየቱ መላ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡ ልጅትዋ
የአባትዋን ክርን ይዛ ወደ እርሱ ስትመጣ ተመለከተ:: ማሪየስ ገልጦት የነበረውን መጽሐፍ አጠፈ፡፡ መልሶ ገለጠው:: ለማንበብ ሞከረ፣ መላ ሰውነቱ ተቅበጠበጠ፡፡ በቀጥታ ወደ እርሱ ነው የሚመጡት:: «ወይኔ ኮተት
ጉዴ» ሲል አሰበ፡፡ «ምን ሊሉኝ ነው::አባትና ልጅ ቀስ ብለው ነው የሚራመዱት:: ሺህ ዓመት መሰለው:: ግን ለጥቂት ሰኮንድ ነው የተጓዙት፡፡
«በአጠገቤ ሊያልፉ ነው? ወይስ ሊያናግሩኝ ነው? ካለፈችም እኮ ከቅርብ ሆና ታየኛለች» ሲል ማሪየስ ተጨነቀ:: መጽሐፉ ላይ እንዳተኮረ ኮቴ ስለሰማ መቃረባቸውን አወቀ፡፡ ሽማግሌው በቁጣ የሚያየው መሰለው።
እንዳቀረቀረ ጥቂት ቆየ:: ቀና ቢል ከአጠገቡ ናቸው:: ወጣትዋ በአጠገቡ አለፈች፡፡ ስታልፍ ትኩር ብላ አየችው:: ስታየው ተኮሳትራ ስለነበረ ልቡ እንደ ከበሮ መታ::
አንጎሎ በእሳት የተያያዘ መሰለው:: «በአጠገቤ አለፈች እኮ! ደግሞ እንዴት ብላ ነው የምታየኝ!» እርሱ ካሰባት ይበልጥ ቆንጆ መሰለችው። አይ ቁንጅና፧ ዘፋኞችን አፍ የሚያስከፍት፤ ደራሲያንን ብዕር የሚያስጨብጥ
ቁንጅና! የሰውን ብቻ ሳይሆን የመልአክትን ውበት ያጣመረ ቁንጅና! በቅዠት ዓለም የሚዋኝ እንጂ በእውን ሰው ሆኖ ሰው የሚያይ አልመሰለውም፡፡ ጫማው ላይ ትንሽ አዋራ ስላየና እርስዋም ከነአዋራው ስላየችው ተናደደ፡፡
በዓይኑ ተከተላት:: ከዓይኑ በተሰወረች ጊዜ ብድግ ብሉ ተነስቶ እንደ እብድ ከወዲያ ወዲህ ይቅበጠበጥ ጀመር፡: እንደወፈፌም ብቻውን ሳቀ፣
ጮክ እያለ ተናገረ:: በፍቅር መያዙን በአካባቢው የነበረ ሁሉ አወቀበት::
ከዚያችሥፍራ በየቀኑ ሲመላለስ አንድ ወር ሙሉ አለፈ፡፡ የመሄጃው
ሰአት ከደረሰ ወደዚያ ከመሄድ የሚያስቀረው ነገር ጠፋ፡፡ «አገልግሎት ማበርከት ሄደ» እያለ ኩርፌይራክ ይሸረድደው ጀመር፡፡ በሄደ ቁጥር ልጅትዋ ታየዋለች።
ቀስ በቀስ እየደፈረ በመምጣቱ አባትና ልጅ ከሚቀመጡበት እየተጠጋ መጣ፡፡ አባትየው እንዳያውቅበት የተቻለውን ሁሉ አደረገ፡፡ መቀመጫውን
ጀርባ እንዲሆን መረጠ፡፡ ከዛፎች ወይም ከዚያ ከሚገኝ ሐውልት
ጀርባ ሆኖ ለልጅትዋ በግልጽ እንዲታይና ከአባትዋ ግን እንዲሰወር የሚያስችል
ስፍራ መርጦ ነበር የሚቀመጠው፡፡ አንዳንድ ጊዜ መጽሐፍ በእጁ ይዞ ዛፍ በመደገፍ ከግማሽ ሰዓት በላይ እየቆመ ያያታል፤ እርስዋም እየሰረቀች
ታየዋለች:፡ አመለካከቱ የጤና አለመሆኑን ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ገብቷታል፡፡ የእርስዋም የዓይን ምላሽ ነገር እንዳለበት አውቋል፡፡
ማሪየስ እንደዚያ ሲመላለስ አባባ ሸበቶም ሳይገባው አልቀረም::
አሁን ክቡር ነጭ በማለት ፋንታ አባባ ሸበቶ እያለ ነው የሚጠራው::ማርየስ ይከተላቸው እንደሆነ ለማየት ዘወትር ከሚቀመጡበት ተነስተው
መላ ስፍራ ይቀይሩ ጀመር፡፡ ማሪየስ ፈተና የተሰጠው መሆኑን ባለመጠርጠር ስተት ይሠራል፡፡ አባባ ሸበቶ ሰዓት እየቀያየረ ይመጣ ጀመር፡፡ አንዳንድ
ልጅትዋን ይዞ አይመጣም:: ልጅትዋ አብራ ካልመጣች ማሪየስ ቶሎ ይሄዳል፡፡ ሌላው ስህተት!
ሦስተኛ ከባድ ስህተት ልጅትዋ የት እንደምትኖር ለማወቅ መፈለጉ
፡፡ አንድ ቀን ተከትሉአቸው ሄደ:: መኖሪያቸውን አየ፡፡ መኖሪያቸውን
ካየ ጀምሮ ከሽርሽሩ ቦታ እስኪሄዱ ድረስ ጠብቆ ኋላ ኋላቸው እየተከተለ ይሸኛቸው ጀመር፡፡ አንድ ቀን ማታ አንደ ልማዱ ከቤታቸው ድረስ ተከትሎ
የድፍረቱ ብዛት ዘበኛውን አነጋገረው::
«አሁን የገቡት ሽማግሌ የሚኖሩት አንደኛ ፎቅ ላይ ነው ፧ አይደል?»
“አይ ሦስተኛ ፎቅ ላይ ነው የሚኖሩት፡፡»
በሚቀጥለው ቀን አባባ ሸበቶና ልጅትዋ ከሽርሽሩ ቦታ ቶሎ ሄዱ።
👍17
እንደ ልማዱ ማሪየስ ተከተላቸው:: ከቤታቸው ከመግባታቸው በፊት አባባ ሸበቶ መለስ በማለት ማሪየስን አፍጥጦ አየው:: በሚቀጥለው ቀን ከሽርሽሩ
ቀሩ:: ማሪየስ እስኪጨልም ጠበቃቸው:: በጣም ሲመሽ ተነስቶ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሄደ:: ሦስተኛ ፎቅ ላይ መብራት አየ:: መብራቱ ሲጠፋ ከወዲያ ወዲህ ተንሸራሸረ:: መብራቱ ሲጠፋ ተነስቶ ወደ ቤቱ ሄደ በዚያ ዓይነት ድርጊት አንድ ሳምንት ሙሉ አሳለፈ::
በስምንተኛው ቀን ወደ ልጅትዋ ቤት ሲሄድ መብራት አልበራም::
«ለምን!» አለ ለራሱ፡፡ «እስካሁን መብራት አላበሩም ማለት ነው? ወይስ !
ምንድነው ነገሩ? ጊዜው ጨልሞአል፡፡» እስከ እኩለ ለሊት ጠበቀ፡፡ በመስኮት !
የሚታይ መብራት አልነበረም፡፡ በጣም አዝኖ ወደ ቤቱ ሄደ ::
በሚቀጥለው ቀን ጠዋት ከሰዎቹ ቤት ሄዶ በማንኳኳት ዘበኛውን
ኣፈአነጋገረው::
«ሦስተኛው ፎቅ ላይ የነበሩት ሰውዬስ?»
«ለቅቀዋል፡፡»
«ከመቼ ጀምሮ?» አለ ማሪየስ በዱላ እንደተመታ ሰው እየተንገዳገደ:
«ከትናንት::»
«የት ነው የገቡት ኣሁን?»
«እኔ እንጃ፡፡»
«አድራሻቸውን አልተዉማ?»
«አልተዉም::»
💫ይቀጥላል💫
ቀሩ:: ማሪየስ እስኪጨልም ጠበቃቸው:: በጣም ሲመሽ ተነስቶ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሄደ:: ሦስተኛ ፎቅ ላይ መብራት አየ:: መብራቱ ሲጠፋ ከወዲያ ወዲህ ተንሸራሸረ:: መብራቱ ሲጠፋ ተነስቶ ወደ ቤቱ ሄደ በዚያ ዓይነት ድርጊት አንድ ሳምንት ሙሉ አሳለፈ::
በስምንተኛው ቀን ወደ ልጅትዋ ቤት ሲሄድ መብራት አልበራም::
«ለምን!» አለ ለራሱ፡፡ «እስካሁን መብራት አላበሩም ማለት ነው? ወይስ !
ምንድነው ነገሩ? ጊዜው ጨልሞአል፡፡» እስከ እኩለ ለሊት ጠበቀ፡፡ በመስኮት !
የሚታይ መብራት አልነበረም፡፡ በጣም አዝኖ ወደ ቤቱ ሄደ ::
በሚቀጥለው ቀን ጠዋት ከሰዎቹ ቤት ሄዶ በማንኳኳት ዘበኛውን
ኣፈአነጋገረው::
«ሦስተኛው ፎቅ ላይ የነበሩት ሰውዬስ?»
«ለቅቀዋል፡፡»
«ከመቼ ጀምሮ?» አለ ማሪየስ በዱላ እንደተመታ ሰው እየተንገዳገደ:
«ከትናንት::»
«የት ነው የገቡት ኣሁን?»
«እኔ እንጃ፡፡»
«አድራሻቸውን አልተዉማ?»
«አልተዉም::»
💫ይቀጥላል💫
👍16❤4
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...አቲዩ ለስድስት ወር ከሰውነት ተራ እስከትወጣ ለባለኪዮስኳ ስትሰራ ከከረመች በኋላ ክረምት ገባ፡፡ ባላኪዮስካ አቲዬን በንስር ዓይን ስትከታተላት ነበር፡፡ ከእያንዳንዱ ቀን ጋር
እየተሽቀጓደመች ነበር፡፡ አንድ ማለዳ የአቲዬን ድሪቶ ልብሶች በፌስታል ቋጥራ ከድፍን ሃምሳ
ብር ጋር ሰጠቻትና፣ “በይ እግዜር ይከትልሽ!” ብላ ከቤቷ አስወጥታ ወረረቻት፡፡ የአቲዬ ሆድ ገፍቶ ነበር፡፡ የቀለመወርቅ ፅንስ ከውስጥ፣ የመንደሩ ሰው ከውጭ እየገፋ ሰው በሞላው አገር
እናቴን ምድረ በዳ ላይ አቆሟት፡፡
አቲዪ ስትፈጭ እና ስታነፍስ የዋለችው የምስር ክክ ብናኝ ፊቷና ፀጉሯ ላይ ተነስንሶ ነበር፡፡ ከስድስት ወር በፊት የነበረችው ልጅ እግር ቆንጆ ልጃገረድ ናት ቢባል ቀለሙ ራሱ አያምንም፡፡ መንገድ ዳር ቆመች፡፡ የክረምት ዝናብ ያካፋል፡፡ አንድ የመኪና ዕቃ መለዋወጫ ሱቅ በር ላይ ፍዝዝ ብላ ቆመች::ምንም እያየች ምንም ሰው፣ ምንም መኪና ምንም ቤት፡፡ ህይወት ዝም የምትልበት፣ አዕምሮ ዝም
የሚልበት፣ የሰው ልጅ ለሆነች ቅፅበት በቁሙ የሚሞትበት ቅፅበት አለ አይደል፡፡ አቲዬ በቁሟ ሞተች፡፡
አላዛርን ከሞት ያስነሳ ራሱም ከሞት የተነሳ ክርስቶስ አቲዬ! ብሎ ልክ እኔ እንደምጠራት
ጠራት፡፡ ዞር አለች ወደ ኋላዋ፡፡ ክርስቶስ ሳይሆን እንዲት ምቾት መድረሻ ያሳጣት ቆንጆ
ወጣት ነበረች … “ወደ ውስጥ ግቢ! ዝናብ መታሽ እኮ” አለቻት አቲዬን፡፡ ገና ሲያጉረመርም
እግሬ አውጭኝ ብሎ ሰው የሚሸሸው ዝናብ እንኳን፣ እንዳሻው ሰው ሳይ ይጨፍር ዘንድ ሰው በቁሙ የሚጠፋበት ቀን አለ፡፡ አቲዬ ጠፍታ ነበር፡፡
ወጣቷ ከፍ ያለ ወንበር ላይ ተቀምጣ እንፋሎቱ ወደ ላይ የሚመዘዝ ትኩስ ሻይ እየጠጣች ነበር፡፡
እቲዬ ወደ ውስተ ገባችና ኩርምት ብላ አንዱ ጥግ ቆመች፡፡ እንደ ቆመች ዝናቡ አባራ፡፡ ሰዉ
በያቅጣጫው ሩጫውን ጀመረ፡፡ አቲዪ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ የእርሷ ዝናብ አላባራም፣
መጠጊያ ላጣ ሰው የሕይወት ዶፍ አባርቶ አያውቅም፡፡ ሰው የፍቅር ዣንጥላ፣ የዝምድና ዣንጥላ፤
የጓደኝነት ዣንጥላ፣ የትዳር ዣንጥላ፣ የእውቀት ዣንጥላ፣ የስራ ዣንተላ፣ የተስፋ ዣንጥላ፣
የእምነት ዣንጥላ ይዞ ስለሚኖር እንጂ ከሕይወት ሰማይ ላይ ነፍስን የሚያበሰብስ መንፈስን
እንደ ወረቀት የሚያላሽቅ የብቸኝነት እና የተስፋ መቁረጥ ዝናብ አባርቶ አያውቅም፡፡
የአቲዬ ዝናብ አላባራም፡፡ ይሄን ሁኑ የነፍስ ዣንጥላ ጨካኝ ንፋስ ከእጇ ነጥቋታል፡፡ ንፋሱ
ቀሚሷን በግድ ገልቦ ውስጧ ቅዝቃዜ አስቀምጧል፡፡ ንፋሱ የሕይወት አቧራ አንስቶ ፊቷና
ፀጉሯን አልብሷል።ንፋሱ የተስፋ ጎጆዋን አፈራርሶ እዚህ አቁሟታል፡፡ አቲዬ የእኔ እናት
መሄጃ የላትም።
ቁልፎች ታንኳኩ፡፡ ቆንጆዋ ልጅ ጃኬቷን ደረበች፡፡ ውጭ የተደረደሩ እቃዎችን አስገባች፤ እናም ቁልፏን በሚያማምሩ ጣቶቿ እንዳንጠለጠሰች አቲዩን ግራ በመጋባት አየቻት፣ “
ውጪ!' ማለት ብልግና ነው፡፡ ቀድሞ ወጥቶ፣ ውጪ ጋር መቆም ግን ያው ውጪ ማለት ነው፡፡
አትዬ ዝናብ እስከያባራ ከተጠለለችበት ሱቅ በቀስታ እርምጃ ወጣችና በረንዳው ላይ ቆመች፤ባለሱቋ ቆንጆ ሴት ሱቋን ቆላለፈች፡፡ የአቲዩ ነገር ሳያሳዝናት አልቀረም፣ እ..ምን ሆነሽ ነው
እናትዬ?አለቻት፡፡ እቲዬ ዝም፡፡ ዓይኗ እንባ አቅርሮ ዝም…ወደ ሞቀ ቤቷ አልያም ወደ ቀጠራት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ያኮበኮበች ወጣት የአቲዬን የአርባ ቀን ዕጣ ከየት ጀምሮ ቢነገራት ይገባታል? አቲዪ ዝም አለች፡፡ አልለመደባትም እንዲህ ሆንኩ ብሎ ማውራት፣ አልለመደባትም ምሬት መዘብዘብ ልማዷ አይደለም።
ወጣቷ ጥቂት ብሮች ከቦርሳዋ አውጥታ ለአቲዬ ዘረጋችላትና “አይዞሽ! ይሄን ያዥ በቃ” አለቻት።
አተዬ ግን አማትባ ከተዘረጋው የወጣቷ እጅ በድንጋጤ አፈገፈገች፡፡ ልክ ጩቢ እንደተሳነዘረበት ሰው ነበር የበረገገችው፡፡ ለማኝ ልሆን?” ብላ በውስጧ አሰበች፡፡ እንባዋን እያዘራች ሽቅብ እግሯን ተከትላ ትጓዝ ጀመር፡፡
የትም የማያደርሱ የሚመስሉ እርምጃዎች አንዳንዴ አዕምሮ አስቦ ከሚደርስበት የተሻለ መፍትሄ ላይ ይደርሳሉ። ሰዎች የፈጣሪ መንገድ ይሏቸዋል፡፡ አቲዬ ዝም ብላ ብዙ ርቀት ተጓዘች። መታጠፊያ ስታገኝ እየታጠፈች፣ መንገድ ስታገኝ እየተሻገረች ዝም ብላ ወደፊት፡፡ ከዕጣ ፋንታዋ ትሸሽ ይመስል መንገዱ ባያልቅ ብላ ተመኘች፡፡ በቃ እስካዓለም ጥግ ዝም ብሎ ቀሪ እድሜዋን መጓዝ ::
ቀጥ ብላ ተመለከተች። ፀጥ ያለ ቤተከርስቲያን ከነታላቅ ጉልላቱ ፊት ፊቷ መንገዱን ተሻግሮ
ይታያል፡፡ የልብስ ፌስታሏን አንጠልጥላ አሮጌ ሃምሳ ብሯን በእጇ እንደጨበጠች፣ ዓለምን
መዳፉ የጨበጠ እግዚአብሔር ጋር የተፋጠጠች መሰላት፡፡
በዚህ ሁሉ በደል የዚህ ሁሉ ግፍና ስቃይ ጠንሳሽ እግዚኣብሔርን ፊትለፊት ያገኘችው መሰላት፡፡
እግዚአብሔር አይቷት ሳያፈገፍግ፣ የበደላት ሁሉ አሳፍሮት ሳይሸሽ በፊት ልትደርስበት መንገዱን
አቋርጣ ወደ ቤተክርስቲያኑ ገሰገሰች፡፡
እግዜር ፈርቷት እግሬ አውጭኝ የሚል መሰላት አቲዬ፡፡ መኪናዎች አምባረቁ፣ ሹፌሮች መኪናቸው መስኮት ብቅ ብለው ፀያፍ ስድብ ወረወሩባት። አንበሳ ጋር ልትፋለም ታላቁን ፈጣሪ 'በላ ልበልሃ' ልትለው በድፍረት የምትገሰግስ ጀግና በውሻዎች ጩኸት የምትበረግግ መስሏቸው።
አቲዬ ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ደረሰች፡፡ እግዜር ያኔ ለያት፡፡ ከሰማየ ሰማያት ዙፋኑ ላይ
እንደተቀመጠ ድምፅ ከወደ ምድር ሰማ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ” እያሉ በታላቅ ድምፅ የሚሰግዱና
የሚያሸበሽቡ እልፍ አእላፍ መላክትን “ዝም በሉ አንድ ለየት ያለ ድምፅ ከምድር ሰምቻለሁ” አለ፡፡
“ጌታ ሆይ ሞልቃቆች በስሱ እያማተቡ መኪናቸው ውስጥ ሆነው ሽው የሚሉት አይነት ድምፅ ይሆናል" አሉት መላዕክቱ፡፡
“አይደለም” አለ እግዚአብሔር፡፡
"የኮተታሞች የኮተት ጥያቄ ይሆናል" አሉት በምድራዊ ትርኪምርኪ የስጋ ጥያቄ የተማረሩት መላዕክት፡፡
"አይደለም አልኩ እኮ” አለ እግዚአብሔር በታላቅ ድምፅ፡፡
“ጌታ ሆይ! ምናልባት የሀብታሞች ከስኳር፣ ከደም ግፊት ከፈወስከኝ መጋረጃ ዣንጥላ የሚሉት
አይነት የተለመደው ስእለት ይሆን” ጠየቁ መላዕክቱ፡፡
ዝም አለ እግዚአብሐር !! ዝምታው አንዳች አስፈሪ ነገር አለው፡፡ በዝምታው ውስጥ ፅንፍ
የለሽ ሀዘንና ፍቅር ነበር።
ከልጅ ስጠኝ ንዝንዝ፣ ከስራ ስጠኝ ንትርክም የተለየ ድምፅ ነበር፡፡ ድምፄ ካማረልኝ ብላ
የምትዘምር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታላቅ ግርማ ሞገስ በእሳት ሰረገላ ደርሰህ ጠላቴን አፈር
ድሜ የምታስበላ የነገስታት ንጉስ፡፡ ከፀሐይ አስራ ዘጠኝ እጅ የምታበራ እያለች በተጠና
መንፈሳዊ ፉከራ መንፈሳዊ ዘራፍ የምታደነቁር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታሰበረ ልቧ በወጣ ማቃተት ዙፋኑን የነቃነቀችው እዚህ ግቢ የማትባል ሴት ናት፡፡ አንዲት ሴት በሩ ላይ ስትቆም፣
“ማነው የልብሴን ጫፍ በዕምነት የነካው” ብሏል እግዚአብሔር!
አቲዩ የእኔ ጀግና ማንንም ደጅ አልጠናቸም፡፡ በልብሷ መቆሸሽ ይናቋት እንጂ የእኔ እናት
ከአዲስ አበባ የሕዝብ ጎርፍ ቁራሽ አልለመነችም፡፡ ለማን ስሞታ እንደምትናገር አውቃለች፡፡
አጥሩን በድንጋይ ቢያጥር፣ ባማረ መኪና ቢንፈላሰሰ፣ ሴቱ በወርቅ ሽቆጠቆጥ..የአዲስ አበባ
ሰውና አቲዬ ልብ ለልብ ተነቃቅተዋል፡፡
አይታዋለች ሕዝቡን የህሊናውን ዓይን ጨፍና ጎዳና የፈሰሱትን የራሱን ጉዶች እንቁልልጭ እያለ
በየስጋ ቤቱ በረንዳ ላይ ጥሬ ስጋውን ሲያጋብስ፣ ቢራና ውስኪውን ሲገለብጥ አይታዋለች፡፡
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...አቲዩ ለስድስት ወር ከሰውነት ተራ እስከትወጣ ለባለኪዮስኳ ስትሰራ ከከረመች በኋላ ክረምት ገባ፡፡ ባላኪዮስካ አቲዬን በንስር ዓይን ስትከታተላት ነበር፡፡ ከእያንዳንዱ ቀን ጋር
እየተሽቀጓደመች ነበር፡፡ አንድ ማለዳ የአቲዬን ድሪቶ ልብሶች በፌስታል ቋጥራ ከድፍን ሃምሳ
ብር ጋር ሰጠቻትና፣ “በይ እግዜር ይከትልሽ!” ብላ ከቤቷ አስወጥታ ወረረቻት፡፡ የአቲዬ ሆድ ገፍቶ ነበር፡፡ የቀለመወርቅ ፅንስ ከውስጥ፣ የመንደሩ ሰው ከውጭ እየገፋ ሰው በሞላው አገር
እናቴን ምድረ በዳ ላይ አቆሟት፡፡
አቲዪ ስትፈጭ እና ስታነፍስ የዋለችው የምስር ክክ ብናኝ ፊቷና ፀጉሯ ላይ ተነስንሶ ነበር፡፡ ከስድስት ወር በፊት የነበረችው ልጅ እግር ቆንጆ ልጃገረድ ናት ቢባል ቀለሙ ራሱ አያምንም፡፡ መንገድ ዳር ቆመች፡፡ የክረምት ዝናብ ያካፋል፡፡ አንድ የመኪና ዕቃ መለዋወጫ ሱቅ በር ላይ ፍዝዝ ብላ ቆመች::ምንም እያየች ምንም ሰው፣ ምንም መኪና ምንም ቤት፡፡ ህይወት ዝም የምትልበት፣ አዕምሮ ዝም
የሚልበት፣ የሰው ልጅ ለሆነች ቅፅበት በቁሙ የሚሞትበት ቅፅበት አለ አይደል፡፡ አቲዬ በቁሟ ሞተች፡፡
አላዛርን ከሞት ያስነሳ ራሱም ከሞት የተነሳ ክርስቶስ አቲዬ! ብሎ ልክ እኔ እንደምጠራት
ጠራት፡፡ ዞር አለች ወደ ኋላዋ፡፡ ክርስቶስ ሳይሆን እንዲት ምቾት መድረሻ ያሳጣት ቆንጆ
ወጣት ነበረች … “ወደ ውስጥ ግቢ! ዝናብ መታሽ እኮ” አለቻት አቲዬን፡፡ ገና ሲያጉረመርም
እግሬ አውጭኝ ብሎ ሰው የሚሸሸው ዝናብ እንኳን፣ እንዳሻው ሰው ሳይ ይጨፍር ዘንድ ሰው በቁሙ የሚጠፋበት ቀን አለ፡፡ አቲዬ ጠፍታ ነበር፡፡
ወጣቷ ከፍ ያለ ወንበር ላይ ተቀምጣ እንፋሎቱ ወደ ላይ የሚመዘዝ ትኩስ ሻይ እየጠጣች ነበር፡፡
እቲዬ ወደ ውስተ ገባችና ኩርምት ብላ አንዱ ጥግ ቆመች፡፡ እንደ ቆመች ዝናቡ አባራ፡፡ ሰዉ
በያቅጣጫው ሩጫውን ጀመረ፡፡ አቲዪ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ የእርሷ ዝናብ አላባራም፣
መጠጊያ ላጣ ሰው የሕይወት ዶፍ አባርቶ አያውቅም፡፡ ሰው የፍቅር ዣንጥላ፣ የዝምድና ዣንጥላ፤
የጓደኝነት ዣንጥላ፣ የትዳር ዣንጥላ፣ የእውቀት ዣንጥላ፣ የስራ ዣንተላ፣ የተስፋ ዣንጥላ፣
የእምነት ዣንጥላ ይዞ ስለሚኖር እንጂ ከሕይወት ሰማይ ላይ ነፍስን የሚያበሰብስ መንፈስን
እንደ ወረቀት የሚያላሽቅ የብቸኝነት እና የተስፋ መቁረጥ ዝናብ አባርቶ አያውቅም፡፡
የአቲዬ ዝናብ አላባራም፡፡ ይሄን ሁኑ የነፍስ ዣንጥላ ጨካኝ ንፋስ ከእጇ ነጥቋታል፡፡ ንፋሱ
ቀሚሷን በግድ ገልቦ ውስጧ ቅዝቃዜ አስቀምጧል፡፡ ንፋሱ የሕይወት አቧራ አንስቶ ፊቷና
ፀጉሯን አልብሷል።ንፋሱ የተስፋ ጎጆዋን አፈራርሶ እዚህ አቁሟታል፡፡ አቲዬ የእኔ እናት
መሄጃ የላትም።
ቁልፎች ታንኳኩ፡፡ ቆንጆዋ ልጅ ጃኬቷን ደረበች፡፡ ውጭ የተደረደሩ እቃዎችን አስገባች፤ እናም ቁልፏን በሚያማምሩ ጣቶቿ እንዳንጠለጠሰች አቲዩን ግራ በመጋባት አየቻት፣ “
ውጪ!' ማለት ብልግና ነው፡፡ ቀድሞ ወጥቶ፣ ውጪ ጋር መቆም ግን ያው ውጪ ማለት ነው፡፡
አትዬ ዝናብ እስከያባራ ከተጠለለችበት ሱቅ በቀስታ እርምጃ ወጣችና በረንዳው ላይ ቆመች፤ባለሱቋ ቆንጆ ሴት ሱቋን ቆላለፈች፡፡ የአቲዩ ነገር ሳያሳዝናት አልቀረም፣ እ..ምን ሆነሽ ነው
እናትዬ?አለቻት፡፡ እቲዬ ዝም፡፡ ዓይኗ እንባ አቅርሮ ዝም…ወደ ሞቀ ቤቷ አልያም ወደ ቀጠራት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ያኮበኮበች ወጣት የአቲዬን የአርባ ቀን ዕጣ ከየት ጀምሮ ቢነገራት ይገባታል? አቲዪ ዝም አለች፡፡ አልለመደባትም እንዲህ ሆንኩ ብሎ ማውራት፣ አልለመደባትም ምሬት መዘብዘብ ልማዷ አይደለም።
ወጣቷ ጥቂት ብሮች ከቦርሳዋ አውጥታ ለአቲዬ ዘረጋችላትና “አይዞሽ! ይሄን ያዥ በቃ” አለቻት።
አተዬ ግን አማትባ ከተዘረጋው የወጣቷ እጅ በድንጋጤ አፈገፈገች፡፡ ልክ ጩቢ እንደተሳነዘረበት ሰው ነበር የበረገገችው፡፡ ለማኝ ልሆን?” ብላ በውስጧ አሰበች፡፡ እንባዋን እያዘራች ሽቅብ እግሯን ተከትላ ትጓዝ ጀመር፡፡
የትም የማያደርሱ የሚመስሉ እርምጃዎች አንዳንዴ አዕምሮ አስቦ ከሚደርስበት የተሻለ መፍትሄ ላይ ይደርሳሉ። ሰዎች የፈጣሪ መንገድ ይሏቸዋል፡፡ አቲዬ ዝም ብላ ብዙ ርቀት ተጓዘች። መታጠፊያ ስታገኝ እየታጠፈች፣ መንገድ ስታገኝ እየተሻገረች ዝም ብላ ወደፊት፡፡ ከዕጣ ፋንታዋ ትሸሽ ይመስል መንገዱ ባያልቅ ብላ ተመኘች፡፡ በቃ እስካዓለም ጥግ ዝም ብሎ ቀሪ እድሜዋን መጓዝ ::
ቀጥ ብላ ተመለከተች። ፀጥ ያለ ቤተከርስቲያን ከነታላቅ ጉልላቱ ፊት ፊቷ መንገዱን ተሻግሮ
ይታያል፡፡ የልብስ ፌስታሏን አንጠልጥላ አሮጌ ሃምሳ ብሯን በእጇ እንደጨበጠች፣ ዓለምን
መዳፉ የጨበጠ እግዚአብሔር ጋር የተፋጠጠች መሰላት፡፡
በዚህ ሁሉ በደል የዚህ ሁሉ ግፍና ስቃይ ጠንሳሽ እግዚኣብሔርን ፊትለፊት ያገኘችው መሰላት፡፡
እግዚአብሔር አይቷት ሳያፈገፍግ፣ የበደላት ሁሉ አሳፍሮት ሳይሸሽ በፊት ልትደርስበት መንገዱን
አቋርጣ ወደ ቤተክርስቲያኑ ገሰገሰች፡፡
እግዜር ፈርቷት እግሬ አውጭኝ የሚል መሰላት አቲዬ፡፡ መኪናዎች አምባረቁ፣ ሹፌሮች መኪናቸው መስኮት ብቅ ብለው ፀያፍ ስድብ ወረወሩባት። አንበሳ ጋር ልትፋለም ታላቁን ፈጣሪ 'በላ ልበልሃ' ልትለው በድፍረት የምትገሰግስ ጀግና በውሻዎች ጩኸት የምትበረግግ መስሏቸው።
አቲዬ ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ደረሰች፡፡ እግዜር ያኔ ለያት፡፡ ከሰማየ ሰማያት ዙፋኑ ላይ
እንደተቀመጠ ድምፅ ከወደ ምድር ሰማ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ” እያሉ በታላቅ ድምፅ የሚሰግዱና
የሚያሸበሽቡ እልፍ አእላፍ መላክትን “ዝም በሉ አንድ ለየት ያለ ድምፅ ከምድር ሰምቻለሁ” አለ፡፡
“ጌታ ሆይ ሞልቃቆች በስሱ እያማተቡ መኪናቸው ውስጥ ሆነው ሽው የሚሉት አይነት ድምፅ ይሆናል" አሉት መላዕክቱ፡፡
“አይደለም” አለ እግዚአብሔር፡፡
"የኮተታሞች የኮተት ጥያቄ ይሆናል" አሉት በምድራዊ ትርኪምርኪ የስጋ ጥያቄ የተማረሩት መላዕክት፡፡
"አይደለም አልኩ እኮ” አለ እግዚአብሔር በታላቅ ድምፅ፡፡
“ጌታ ሆይ! ምናልባት የሀብታሞች ከስኳር፣ ከደም ግፊት ከፈወስከኝ መጋረጃ ዣንጥላ የሚሉት
አይነት የተለመደው ስእለት ይሆን” ጠየቁ መላዕክቱ፡፡
ዝም አለ እግዚአብሐር !! ዝምታው አንዳች አስፈሪ ነገር አለው፡፡ በዝምታው ውስጥ ፅንፍ
የለሽ ሀዘንና ፍቅር ነበር።
ከልጅ ስጠኝ ንዝንዝ፣ ከስራ ስጠኝ ንትርክም የተለየ ድምፅ ነበር፡፡ ድምፄ ካማረልኝ ብላ
የምትዘምር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታላቅ ግርማ ሞገስ በእሳት ሰረገላ ደርሰህ ጠላቴን አፈር
ድሜ የምታስበላ የነገስታት ንጉስ፡፡ ከፀሐይ አስራ ዘጠኝ እጅ የምታበራ እያለች በተጠና
መንፈሳዊ ፉከራ መንፈሳዊ ዘራፍ የምታደነቁር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታሰበረ ልቧ በወጣ ማቃተት ዙፋኑን የነቃነቀችው እዚህ ግቢ የማትባል ሴት ናት፡፡ አንዲት ሴት በሩ ላይ ስትቆም፣
“ማነው የልብሴን ጫፍ በዕምነት የነካው” ብሏል እግዚአብሔር!
አቲዩ የእኔ ጀግና ማንንም ደጅ አልጠናቸም፡፡ በልብሷ መቆሸሽ ይናቋት እንጂ የእኔ እናት
ከአዲስ አበባ የሕዝብ ጎርፍ ቁራሽ አልለመነችም፡፡ ለማን ስሞታ እንደምትናገር አውቃለች፡፡
አጥሩን በድንጋይ ቢያጥር፣ ባማረ መኪና ቢንፈላሰሰ፣ ሴቱ በወርቅ ሽቆጠቆጥ..የአዲስ አበባ
ሰውና አቲዬ ልብ ለልብ ተነቃቅተዋል፡፡
አይታዋለች ሕዝቡን የህሊናውን ዓይን ጨፍና ጎዳና የፈሰሱትን የራሱን ጉዶች እንቁልልጭ እያለ
በየስጋ ቤቱ በረንዳ ላይ ጥሬ ስጋውን ሲያጋብስ፣ ቢራና ውስኪውን ሲገለብጥ አይታዋለች፡፡
👍27❤1👏1
በረሀብ የተቆራመቱ፣ ልብሳቸው ላያቸው ላይ ያላቀ ሚስኪን ሕፃናት በምቾት ብዛት ገና በሕፃንነታቸው የስጋ ክምር ከተሸከሙ ብጤዎቻቸው የሚሆኑ ሕፃናት የተረፋቸውን እንዲሰጧቸው
እጃቸውን በልመና ሲዘረጉ - አይታለች፡፡ የደህ ልጆች የሀብታም ልጆችን መኪና እየተከተሉ
ሲለምኑ አይታለች፡፡ የተረፈውን ሳንቲም በምፅዋት ስም ሲወረውር ደግ ይመሰላል ሕዝቡ
የደግነት ከበሮ እየደለቀ ደግነት ባህሌ ነው የሚለው ህዝብ !!
የልብስ ፌስታሏን ከጓኗ አስቀምጣ በግንባሯ ተደፍታ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ቃል አልተነፈስችም፤
ከስሩ ተነስታ ቀጥ ብላ ወደ ምፅዋት ማስቀመጫ ሳጥኑ ሂደችና ቀእጇ የጨበጠችውን ድፍን ሃምሳ ብር አጣጥፋ በጠባቧ የምጽዋት ሽቁር እስገብታ ፈቷን አዙራ እርምጃዋን ቀጠለች ባዶዋን !
እግዚአብሔር በምድር ላይ ከባዱን ብድር ጥላበት የሄደችውን ሴት እንዲህ አላት፡፡
ልጅሽ እልፍ እጥፍ ብድርሽን እከፍልሻለሁ፡፡ አቲዬ ምሀፀን ውስጥ በፅንሰቴ ከተገላበጥኩ፡
በቃ በዚህ ቀን መሆን አለበት እስከዛሬ ድረስ ትልቅና ውብ ቤተክርስቲያኖችን ሳይ በአትዬ ሃምሳ ብር የተገነቡ ነው የሚመስለኝ።
ቀና ስትል ፊት ለፊቷ ማንን እገኘች? አባ እስጢፋኖስን !! በተዓምር ማመን የዳዳኝ አቲዬ
ይህንን ስትነግረኝ ነው፡፡ አባ እስጢፋኖስ አቲዩን እያዩ፣ “አንቺ ዘርፌ ቤት የነበርሽው ልጅ
አይደለሽም እንዴ ?” አሉና ጠየቋት መነፅራችውን እያስተካከሉ፡፡ አባ እንኳን በዚህ ድንግዝግዝ አመሻሽ ቀርቶ በጠራራ ፀሐይ የቤተክርስቲያኑን ዋና በር የሚስቱ ፅኑ የዐይታ ችግር ያለባቸው አባት ነበሩ። አቲዬን ግን ተመለከቷት በመነፅራቸው ሳይሆን በእግዚፈር ዓይኖች !!
ያን ቀን አባ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ውስጥ አንዲት እናት መነኩሲት የሚኖሩባት የመቃብር ቤት አትዬን ወስደው አኖሯት፡፡ ሆዷ ውስጥ ወደዚች ምድር ሊቀላቀል የተዘጋጀ ፅንስ ከረገጠችው የቤቱ ወለል ስር ይህቺን ዓለም ጥግብ እስኪል ኖሮባት የተሰናበታት ሀብታም ሽማግሌ አፅም..
አትዬ መሐል ላይ፡፡....
✨አላለቀም✨
እጃቸውን በልመና ሲዘረጉ - አይታለች፡፡ የደህ ልጆች የሀብታም ልጆችን መኪና እየተከተሉ
ሲለምኑ አይታለች፡፡ የተረፈውን ሳንቲም በምፅዋት ስም ሲወረውር ደግ ይመሰላል ሕዝቡ
የደግነት ከበሮ እየደለቀ ደግነት ባህሌ ነው የሚለው ህዝብ !!
የልብስ ፌስታሏን ከጓኗ አስቀምጣ በግንባሯ ተደፍታ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ቃል አልተነፈስችም፤
ከስሩ ተነስታ ቀጥ ብላ ወደ ምፅዋት ማስቀመጫ ሳጥኑ ሂደችና ቀእጇ የጨበጠችውን ድፍን ሃምሳ ብር አጣጥፋ በጠባቧ የምጽዋት ሽቁር እስገብታ ፈቷን አዙራ እርምጃዋን ቀጠለች ባዶዋን !
እግዚአብሔር በምድር ላይ ከባዱን ብድር ጥላበት የሄደችውን ሴት እንዲህ አላት፡፡
ልጅሽ እልፍ እጥፍ ብድርሽን እከፍልሻለሁ፡፡ አቲዬ ምሀፀን ውስጥ በፅንሰቴ ከተገላበጥኩ፡
በቃ በዚህ ቀን መሆን አለበት እስከዛሬ ድረስ ትልቅና ውብ ቤተክርስቲያኖችን ሳይ በአትዬ ሃምሳ ብር የተገነቡ ነው የሚመስለኝ።
ቀና ስትል ፊት ለፊቷ ማንን እገኘች? አባ እስጢፋኖስን !! በተዓምር ማመን የዳዳኝ አቲዬ
ይህንን ስትነግረኝ ነው፡፡ አባ እስጢፋኖስ አቲዩን እያዩ፣ “አንቺ ዘርፌ ቤት የነበርሽው ልጅ
አይደለሽም እንዴ ?” አሉና ጠየቋት መነፅራችውን እያስተካከሉ፡፡ አባ እንኳን በዚህ ድንግዝግዝ አመሻሽ ቀርቶ በጠራራ ፀሐይ የቤተክርስቲያኑን ዋና በር የሚስቱ ፅኑ የዐይታ ችግር ያለባቸው አባት ነበሩ። አቲዬን ግን ተመለከቷት በመነፅራቸው ሳይሆን በእግዚፈር ዓይኖች !!
ያን ቀን አባ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ውስጥ አንዲት እናት መነኩሲት የሚኖሩባት የመቃብር ቤት አትዬን ወስደው አኖሯት፡፡ ሆዷ ውስጥ ወደዚች ምድር ሊቀላቀል የተዘጋጀ ፅንስ ከረገጠችው የቤቱ ወለል ስር ይህቺን ዓለም ጥግብ እስኪል ኖሮባት የተሰናበታት ሀብታም ሽማግሌ አፅም..
አትዬ መሐል ላይ፡፡....
✨አላለቀም✨
👍20❤2
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አደገኛው
የበጋው ወራት አልፎ ክረምት ገባ:: ግን አባባ ሸበቶም ሆነ ልጅቷ ድሮ ይመላለሱበት ከነበረው የሽርሽር ቦታ ብቅ አላሉም:: ማሪየስን ያስጨነቀውና ያጓጓው ያቸን ወለላ ፤ ያንን በውበት ያጌጠን ፊት ለማየት
ነበር፡፡ በቃኝ፤ ሰለቸኝ፧ ደከመኝ፤ ሳይል ጠዋት ማታ ፈለጋት:: ወጣ፧
ወረደ፤ ተንከራተተ፤ ግን አላገኛትም:: በዚህም የተነሳ ወትሮ ቆራጥ፧ ደፋር፧ ብልህ፣ አርቆ አስተዋይና የወደፊት ሕይወቱን በኩራትና በተስፉ ይመራ የነበረው ወጣት ከቤት እንደተባረረ ውሻ ዓላማቢስና ተንከራታች ሆነ፡፡ በአሳብ ባህር ሰጠመ:: የእርሱ ነገር በቃ ፤ አከተመ:: ሥራ አስጠላው፡ ቆሞ መሄድ ሰለቸው ፤ ብቸኝነት ሰውነቱን ወረረው:: ከፊቱ፡ ድቅን ብለው ይታዩ የነበሩት ብሩኅ ተስፋ፣ የኑሮ ግብና እውቀት እንደ ጭስ ተነኑበት፡ ዓለም የጨለመችና የተደፋችበት መሰለው:: አሁን የሚኖረው ቀደም ሲል ይኖርበት ከነበረው ቤት ውስጥ ነው::በዚያ አካባቢ ለነበረ ለማንም ደንታ አልነበረውም:: አንድ ጊዜ ተቸግረው የቤት ኪራይ የከፈለላቸው ጎረቤቱ፡ አሁንም አሉ:: ሌሎች ጎረቤቶቹ ግን
ቤት ለቅቀው ወደ ሌላ ሰፈር ሄደዋል፡፡ አንዳንዶቹም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል:: አንዳንዶቹም የቤት ኪራይ ለመክፈል ባለመቻላቸወ
ተባርረዋል::
እንድ ቀን በጠዋት ተነስቶ ቁርሱን በልቶ እንደጨረስ የነበረበት
ክፍል በር በዝግታ ይንኳኳል፡፡ የሚሰረቅ ንብረት ስላልነበረው ብዙውን ጊዜ የቤቱን በር አይቆልፍም፡፡ በሩን የሚቆልፈው ከበድ ያለ ሥራ ሲይዝ ብቻ ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ ወደ ውጭ ሲሄድ እንኳን በሩን ክፍት ትቶ ነበር
የሚሄደው::
በሩ እንደገና በዝግታ ተንኳኳ፡፡
«ይግቡ» አለ ማሪየስ፡፡
በሩ ተከፈተ::
«ይቅርታ ያድርጉልኝ፤ ጌታዬ!»
የሚያቃስትና የደከመ ድምፅ ነበር፡፡ በመጠጥ ኃይል ተዳክሞ በቅጡ መናገር የተሳነው የሽማግሌ ድምፅ ይመስላል፡፡ ማሪየስ ዞር ብሎ ሲያይ
አንዲት ወጣት ልጅ ከበሩ ቆማለች::
ወጣትዋ ገና ልጅ ናት:: የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደ ቡትቶ ስለነበር ስውነትዋ በብርድ ይንቀጠቀጣል፡፡ ሰውነትዋ ከመገርጣቱም በላይ አመድ
የለበሰች ይመስል ነጫጭባ ሆኖአል፡፡ ትንሽም አካልዋ የተሽፈነው ከወገብዋ
በታች ነው እንጂ ራቁትዋን ናት ማለት ይቻላል፡፡ በቀበቶ ፈንታ ቀሚስዋን የታጠቀችው በገመድ ነው:: ፀጉርዋንም ያሰረችው በቃጫ ገመድ ነው፡፡እጆችዋ በጭቃ ላቁጠዋል:: አንዳንድ ጥርሶችዋ የሉም:: ዓይኖችዋ ከመቦዘዝ አልፈው ፈዝዘዋል:: የአሥራ አምስት ዓመትዋ ወጣት የሃምሣ ዓመት አሮጊት መስላለች:: ታስጠላለች፤ ታሳዝናለች:: ማሪየስ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ በመገረም አያት:: በቅዠት ዓለም የምትታይ እንጂ በእውን ያለች አልመሰለውም።
የሚያሳዝነው አፈጣጠርዋ አስቀያሚ አልነበረም:: ተፈጥሮ የውበት ፀጋ አስታቅፎአታል:: በሕፃንነትዋ በጣም የምታምር፤ በጣም የተዋበች ልጅ እንደነበረች ታስታውቃለች:: የችግር ብዛት ውበትዋን ጨርሶ ሊያጠፋውና ሊያበላሸው አልቻለም:: ደመና በሰፈነበት እለት የፀሐይ ጨረር ለመታየት እንደሚታገልና ብልጭ ድርግም እንደሚል ሁሉ ውበትዋ
በማጣት ጨለማ ቢዋጥም መታየቱ አልቀረም::
«ምን ነበር፤ የእኔ እህት?» ሲል ማሪየስ ጠየቃት::
ልጅትዋ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደች ተናገረች::
«ይህን ማስታወሻ ስጭ ነው የተባልኩት መሴይ ማሪየስ::
ማሪየስ ብላ ነው በስሙ የጠራችው:: እንደምታውቀው ተገነዘበ፡፡
ግን ማን ናት ይህቺ ልጅ? የማሪየስን ስም እንዴት አወቀች?
«ግቢ» ብሎ ሳይጋብዛት ወደ ውስጥ ገባች፡፡ ያልተነጠፈውን አልጋና ከወለሉ ላይ የተበታተነውን ወረቀት አየች፡፡ ጫማ አላደረገችም ባዶ እግርዋን ናት፡፡ ጭንዋ አካባቢ ልብስዋ ስለተቀደደ ገላዋ ይታያል፡፡ ከጉልበትዋ ጀምሮ ልብስዋ በመቦጫጨቁና ፀጉርዋ በመቆሙ በጣም እንደበረዳት በጉልህ ይታያል፡፡
ደብዳቤውን ሰጠችው:: ማሪየስ ደብዳቤውን ከፍቶ አነበበው::
«ውድ ጎረቤትና የተወደድክ ወጣት..
በጣም እንደምታዝንልኝ ሰምቻለሁ፡፡ ባለፈው ጊዜ የስድስት ወር የቤት ኪራይ እንደከፈልክልኝ ደርሼበታለሁ:: የእኔ ልጅ እግዚአብሔር
ይባርክህ፡፡ ላለፉት ሁለት ቀናት እህል የሚባል ነገር በአፋችን እንዳልገባ ትልቅዋ ልጄ ትነግርሃለች:: ባለቤቴም ታምማለች፡፡ ከአሁን ቀደም ልብህ
እንደራራልኝ ሁሉ አሁንም እንደማትጨክንብኝ እተማመናለሁ፡፡ ስለዚህ
የተቻለህን እርዳን:: ልጄም የፈለገኸውን ሁሉ ትታዘዛለች፡፡»
ማሪየስ ተገርሞ የደብዳቤውን መልዕክት ሲያሳያት ልጅትዋ በድፍረት ክፍሉ ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትላላች:: ራቁትዋን መሆንዋን ብታውቅም
ስሜት አልሰጣትም:: ወንበሮችን አስተካክላ የወዳደቁትን ወረቀቶች አንስታ ከጠረጴዛ ላይ አኖረች::
«እህ መስታወትም አለህ!» አለች::
እንደ ማንጐራጉር ብላ ትዘፍን ጀመር:: ሆኖም በውስጥዋ የተዳፈነ ጭንቀትና ፍርሃት እንዳለባት እንጉርጉሮው ሳያሳጣት አልቀረም፡፡ ካላበዱ
በቀር ከሰው ቤት ገብቶ ባለቤት መሆን እንደሚያሳፍር የታወቀ ነው፡፡
ማሪየስ «ዝም ልበላት ወይስ ልናገራት» እያለ አሰላሰለ፡፡ ወደ መጽሐፍ መደርደሪያው ሄደች::
«እንዴ! ብዙ መጽሐፍ ነው ያለህ» አለች፡፡
ፊትዋ በራ ፧ ኩራት ኩራት አላት:: ማንኛውም ሰው አንድ የሚኩራራበት ነገር ካገኘ መንፈሱ ይረካል፤ ሞራሉ ይገነባል፡፡
«ማንበብ እችላለሁ ፤ እውነቴን ነው እችላለሁ» ስትል ተናገረች::
ቶሎ ብላ ተገልጦ የነበረውን መጽሐፍ አንስታ ማንበብ ጀመረች::ወዲያው ማንበቡን በመተው መጽሐፉን አስቀመጠች:: መንጎል አነሳች::
«መጻፍም እኮ እችላለሁ::»
ከቀለም ብልቃጥ አጠቀሰች:: ወደ ማሪየስ በመዞር «ለማየት
ትፈልጋለህ? መጻፍ እንደምችል ላሳይህ?» ስትል ጠየቀችው::
መልስ እንዲሰጣት ሳትጠብቅ ከጠረጴዛው ላይ ከነበረው ባዶ ወረቀት ላይ ጻፈች፡፡ ከዚያም ቀና ብላ ማሪየስን አየችው::
«በጣም ቆንጆ ልጅ እንደሆንክ ታውቃለህ?» ስትል ጠየቀችው::
እርስዋ ለምን ፈገግታ እንዳሳየችው እርሱ ደግሞ ለምን ፊቱ በቶሎ እንደቀላ በመገረም ሁለቱም በየበኩላቸው ያሰላስሉ ጀመር፡፡
ወደ ማሪየስ ተጠግታ እጅዋን ከትከሻው ላይ አሳረፈች:: ምነው
ሁልጊዜም ትዘጋኛለህ፡፡ እኔ እንደሆነ በደምብ አውቅሃለሁ፡፡ ደረጃ ላይ ዘወትር እንገናኛለን፡፡ እኔ አይሃለሁ ፤ አንተ ግን አታየኝም:: ፀጉርህ እንዲህ ተንጨባሮ ሳየው ደስ ይለኛል፡፡»
ስትናገር አንደበትዋን አለስልሳ ነው፡፡ ድምፅዋን ዝቅ አድርጋ በመናገርዋ ወይም በሌላ ምክንያት ይሁን አይታወቅም ከተናገረቻቸው ቃላት አንዳንዶቹ
ማሪየስ ጆሮ ውስጥ አልገቡም:: ማሪየስ ቀስ ብሎ ወደኋላ አፈገፈገ።በዚህ ጊዜ ወደ አንድ ሌላ ሰው እንድታደርስ የተጻፈውን ሌላ ማስታወሻ ገልጣ አሳየችው::
“ይኸው» አለች ፤ «ይህን ማስታወሻ መንገዱን አቋርጦ ከሚገኘው ቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚገኙ መነከሴ የምሰጠው ነው:: ምናልባት ከራሩልን ለቁርሳችን የሚሆን ምግብ ይሰጡናል::»
ይህን እንደተናገረች መሳቅ ጀመረች:: (ማሽላ እያረረ ይስቃል» ይባል የለ፡፡ ንግግርዋን ቀጠለች::
ዛሬ ቁርስ ብናገኝ ምን እንደሚባል ታውቃለህ? ከሁለት ቀን በኋላ
ቁርስ ቀመስን ይባላል:: ቁርስ ከተገኘ እንግዲህ ከትናንት ወዲያ ጀምሮ መብላት የነበረብንን ቁርስ፣ ምሳና እራት በላን ማለት ነው:: ከተገኘማ እሱንም በአንዴ መጠቅጠቅ ነው!»
ይህን ስትናገር ልጅትዋ ለምን እንደመጣች ታወሰው::
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አደገኛው
የበጋው ወራት አልፎ ክረምት ገባ:: ግን አባባ ሸበቶም ሆነ ልጅቷ ድሮ ይመላለሱበት ከነበረው የሽርሽር ቦታ ብቅ አላሉም:: ማሪየስን ያስጨነቀውና ያጓጓው ያቸን ወለላ ፤ ያንን በውበት ያጌጠን ፊት ለማየት
ነበር፡፡ በቃኝ፤ ሰለቸኝ፧ ደከመኝ፤ ሳይል ጠዋት ማታ ፈለጋት:: ወጣ፧
ወረደ፤ ተንከራተተ፤ ግን አላገኛትም:: በዚህም የተነሳ ወትሮ ቆራጥ፧ ደፋር፧ ብልህ፣ አርቆ አስተዋይና የወደፊት ሕይወቱን በኩራትና በተስፉ ይመራ የነበረው ወጣት ከቤት እንደተባረረ ውሻ ዓላማቢስና ተንከራታች ሆነ፡፡ በአሳብ ባህር ሰጠመ:: የእርሱ ነገር በቃ ፤ አከተመ:: ሥራ አስጠላው፡ ቆሞ መሄድ ሰለቸው ፤ ብቸኝነት ሰውነቱን ወረረው:: ከፊቱ፡ ድቅን ብለው ይታዩ የነበሩት ብሩኅ ተስፋ፣ የኑሮ ግብና እውቀት እንደ ጭስ ተነኑበት፡ ዓለም የጨለመችና የተደፋችበት መሰለው:: አሁን የሚኖረው ቀደም ሲል ይኖርበት ከነበረው ቤት ውስጥ ነው::በዚያ አካባቢ ለነበረ ለማንም ደንታ አልነበረውም:: አንድ ጊዜ ተቸግረው የቤት ኪራይ የከፈለላቸው ጎረቤቱ፡ አሁንም አሉ:: ሌሎች ጎረቤቶቹ ግን
ቤት ለቅቀው ወደ ሌላ ሰፈር ሄደዋል፡፡ አንዳንዶቹም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል:: አንዳንዶቹም የቤት ኪራይ ለመክፈል ባለመቻላቸወ
ተባርረዋል::
እንድ ቀን በጠዋት ተነስቶ ቁርሱን በልቶ እንደጨረስ የነበረበት
ክፍል በር በዝግታ ይንኳኳል፡፡ የሚሰረቅ ንብረት ስላልነበረው ብዙውን ጊዜ የቤቱን በር አይቆልፍም፡፡ በሩን የሚቆልፈው ከበድ ያለ ሥራ ሲይዝ ብቻ ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ ወደ ውጭ ሲሄድ እንኳን በሩን ክፍት ትቶ ነበር
የሚሄደው::
በሩ እንደገና በዝግታ ተንኳኳ፡፡
«ይግቡ» አለ ማሪየስ፡፡
በሩ ተከፈተ::
«ይቅርታ ያድርጉልኝ፤ ጌታዬ!»
የሚያቃስትና የደከመ ድምፅ ነበር፡፡ በመጠጥ ኃይል ተዳክሞ በቅጡ መናገር የተሳነው የሽማግሌ ድምፅ ይመስላል፡፡ ማሪየስ ዞር ብሎ ሲያይ
አንዲት ወጣት ልጅ ከበሩ ቆማለች::
ወጣትዋ ገና ልጅ ናት:: የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደ ቡትቶ ስለነበር ስውነትዋ በብርድ ይንቀጠቀጣል፡፡ ሰውነትዋ ከመገርጣቱም በላይ አመድ
የለበሰች ይመስል ነጫጭባ ሆኖአል፡፡ ትንሽም አካልዋ የተሽፈነው ከወገብዋ
በታች ነው እንጂ ራቁትዋን ናት ማለት ይቻላል፡፡ በቀበቶ ፈንታ ቀሚስዋን የታጠቀችው በገመድ ነው:: ፀጉርዋንም ያሰረችው በቃጫ ገመድ ነው፡፡እጆችዋ በጭቃ ላቁጠዋል:: አንዳንድ ጥርሶችዋ የሉም:: ዓይኖችዋ ከመቦዘዝ አልፈው ፈዝዘዋል:: የአሥራ አምስት ዓመትዋ ወጣት የሃምሣ ዓመት አሮጊት መስላለች:: ታስጠላለች፤ ታሳዝናለች:: ማሪየስ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ በመገረም አያት:: በቅዠት ዓለም የምትታይ እንጂ በእውን ያለች አልመሰለውም።
የሚያሳዝነው አፈጣጠርዋ አስቀያሚ አልነበረም:: ተፈጥሮ የውበት ፀጋ አስታቅፎአታል:: በሕፃንነትዋ በጣም የምታምር፤ በጣም የተዋበች ልጅ እንደነበረች ታስታውቃለች:: የችግር ብዛት ውበትዋን ጨርሶ ሊያጠፋውና ሊያበላሸው አልቻለም:: ደመና በሰፈነበት እለት የፀሐይ ጨረር ለመታየት እንደሚታገልና ብልጭ ድርግም እንደሚል ሁሉ ውበትዋ
በማጣት ጨለማ ቢዋጥም መታየቱ አልቀረም::
«ምን ነበር፤ የእኔ እህት?» ሲል ማሪየስ ጠየቃት::
ልጅትዋ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደች ተናገረች::
«ይህን ማስታወሻ ስጭ ነው የተባልኩት መሴይ ማሪየስ::
ማሪየስ ብላ ነው በስሙ የጠራችው:: እንደምታውቀው ተገነዘበ፡፡
ግን ማን ናት ይህቺ ልጅ? የማሪየስን ስም እንዴት አወቀች?
«ግቢ» ብሎ ሳይጋብዛት ወደ ውስጥ ገባች፡፡ ያልተነጠፈውን አልጋና ከወለሉ ላይ የተበታተነውን ወረቀት አየች፡፡ ጫማ አላደረገችም ባዶ እግርዋን ናት፡፡ ጭንዋ አካባቢ ልብስዋ ስለተቀደደ ገላዋ ይታያል፡፡ ከጉልበትዋ ጀምሮ ልብስዋ በመቦጫጨቁና ፀጉርዋ በመቆሙ በጣም እንደበረዳት በጉልህ ይታያል፡፡
ደብዳቤውን ሰጠችው:: ማሪየስ ደብዳቤውን ከፍቶ አነበበው::
«ውድ ጎረቤትና የተወደድክ ወጣት..
በጣም እንደምታዝንልኝ ሰምቻለሁ፡፡ ባለፈው ጊዜ የስድስት ወር የቤት ኪራይ እንደከፈልክልኝ ደርሼበታለሁ:: የእኔ ልጅ እግዚአብሔር
ይባርክህ፡፡ ላለፉት ሁለት ቀናት እህል የሚባል ነገር በአፋችን እንዳልገባ ትልቅዋ ልጄ ትነግርሃለች:: ባለቤቴም ታምማለች፡፡ ከአሁን ቀደም ልብህ
እንደራራልኝ ሁሉ አሁንም እንደማትጨክንብኝ እተማመናለሁ፡፡ ስለዚህ
የተቻለህን እርዳን:: ልጄም የፈለገኸውን ሁሉ ትታዘዛለች፡፡»
ማሪየስ ተገርሞ የደብዳቤውን መልዕክት ሲያሳያት ልጅትዋ በድፍረት ክፍሉ ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትላላች:: ራቁትዋን መሆንዋን ብታውቅም
ስሜት አልሰጣትም:: ወንበሮችን አስተካክላ የወዳደቁትን ወረቀቶች አንስታ ከጠረጴዛ ላይ አኖረች::
«እህ መስታወትም አለህ!» አለች::
እንደ ማንጐራጉር ብላ ትዘፍን ጀመር:: ሆኖም በውስጥዋ የተዳፈነ ጭንቀትና ፍርሃት እንዳለባት እንጉርጉሮው ሳያሳጣት አልቀረም፡፡ ካላበዱ
በቀር ከሰው ቤት ገብቶ ባለቤት መሆን እንደሚያሳፍር የታወቀ ነው፡፡
ማሪየስ «ዝም ልበላት ወይስ ልናገራት» እያለ አሰላሰለ፡፡ ወደ መጽሐፍ መደርደሪያው ሄደች::
«እንዴ! ብዙ መጽሐፍ ነው ያለህ» አለች፡፡
ፊትዋ በራ ፧ ኩራት ኩራት አላት:: ማንኛውም ሰው አንድ የሚኩራራበት ነገር ካገኘ መንፈሱ ይረካል፤ ሞራሉ ይገነባል፡፡
«ማንበብ እችላለሁ ፤ እውነቴን ነው እችላለሁ» ስትል ተናገረች::
ቶሎ ብላ ተገልጦ የነበረውን መጽሐፍ አንስታ ማንበብ ጀመረች::ወዲያው ማንበቡን በመተው መጽሐፉን አስቀመጠች:: መንጎል አነሳች::
«መጻፍም እኮ እችላለሁ::»
ከቀለም ብልቃጥ አጠቀሰች:: ወደ ማሪየስ በመዞር «ለማየት
ትፈልጋለህ? መጻፍ እንደምችል ላሳይህ?» ስትል ጠየቀችው::
መልስ እንዲሰጣት ሳትጠብቅ ከጠረጴዛው ላይ ከነበረው ባዶ ወረቀት ላይ ጻፈች፡፡ ከዚያም ቀና ብላ ማሪየስን አየችው::
«በጣም ቆንጆ ልጅ እንደሆንክ ታውቃለህ?» ስትል ጠየቀችው::
እርስዋ ለምን ፈገግታ እንዳሳየችው እርሱ ደግሞ ለምን ፊቱ በቶሎ እንደቀላ በመገረም ሁለቱም በየበኩላቸው ያሰላስሉ ጀመር፡፡
ወደ ማሪየስ ተጠግታ እጅዋን ከትከሻው ላይ አሳረፈች:: ምነው
ሁልጊዜም ትዘጋኛለህ፡፡ እኔ እንደሆነ በደምብ አውቅሃለሁ፡፡ ደረጃ ላይ ዘወትር እንገናኛለን፡፡ እኔ አይሃለሁ ፤ አንተ ግን አታየኝም:: ፀጉርህ እንዲህ ተንጨባሮ ሳየው ደስ ይለኛል፡፡»
ስትናገር አንደበትዋን አለስልሳ ነው፡፡ ድምፅዋን ዝቅ አድርጋ በመናገርዋ ወይም በሌላ ምክንያት ይሁን አይታወቅም ከተናገረቻቸው ቃላት አንዳንዶቹ
ማሪየስ ጆሮ ውስጥ አልገቡም:: ማሪየስ ቀስ ብሎ ወደኋላ አፈገፈገ።በዚህ ጊዜ ወደ አንድ ሌላ ሰው እንድታደርስ የተጻፈውን ሌላ ማስታወሻ ገልጣ አሳየችው::
“ይኸው» አለች ፤ «ይህን ማስታወሻ መንገዱን አቋርጦ ከሚገኘው ቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚገኙ መነከሴ የምሰጠው ነው:: ምናልባት ከራሩልን ለቁርሳችን የሚሆን ምግብ ይሰጡናል::»
ይህን እንደተናገረች መሳቅ ጀመረች:: (ማሽላ እያረረ ይስቃል» ይባል የለ፡፡ ንግግርዋን ቀጠለች::
ዛሬ ቁርስ ብናገኝ ምን እንደሚባል ታውቃለህ? ከሁለት ቀን በኋላ
ቁርስ ቀመስን ይባላል:: ቁርስ ከተገኘ እንግዲህ ከትናንት ወዲያ ጀምሮ መብላት የነበረብንን ቁርስ፣ ምሳና እራት በላን ማለት ነው:: ከተገኘማ እሱንም በአንዴ መጠቅጠቅ ነው!»
ይህን ስትናገር ልጅትዋ ለምን እንደመጣች ታወሰው::
👍13
ሰደርያው ኪስ ውስጥ ገባ፤ ምንም አልነበረም:: ልጅትዋ ግን ንግግርዋን ቀጠለች:: ስትናገር ማሪየስ ከአጠገብዋ መኖሩን ጨርሳ የረሳች ትመስላለች፡፡
አንዳንድ ቀን ማታ ማታ ወደ ውጭ እወጣለሁ:: አልፎ አልፎ በዚዬው እንደወጣሁ እቀራለሁ:: ባለፈው ዓመት አሁን ካለንበት ቤት
ከመግባታችን በፊት ከድልድይ ስር ነበር የምናድረው:: መቼም ብርዱ አይጣል ነው:: ትንሽዋ እህቴ እንዴት ይበርዳል ፤ አልበሱኝ እያለች ስትጮህ ነበር የምታድረው:: ታዲያ አንዳንድ ቀን በጣም ሰልቸት ሲለኝ ዝም ብዬ
በባዶ ሆዴ እዞር ነበር፡፡ ሁሉም ነገር ይምታታብኛል ፤ ይዞርብኛል::
የሚሆነውን ሁሉ አላውቅም:: ድምፅ ብቻ እሰማለሁ፡፡ አለ አይደል፧ ሆድ ባዶ ሲሆን የሚያደርገው ዓይነት::»
በመጨረሻ ዓይንዋ እየተንከራተተ አተኩራ አየችው::
ማሪየስ ኪሱን ሁሉ ሲበረብር አምስት ፍራንክና አሥራ ስድስት ሱስ አገኘ፡፡ የነበረው ገንዘብ ይኸው ነው:: «ለምሣ ይሆነኝ ነበር» ሲል አሰበ::
«ግን እኮ ነገ የሚሆነው አይታወቅም::ገንዘቡን አነሳና ለልጅትዋ ሰጣት.. ቶሎ ብላ ቆጠረችው::
«ተመስገን፧ ፀሐይዋ በራች» ስትል ተናገረች:: ከዚያም በማመስገን
ለጥ ብላ እጅ ነሳችው:: «እግዚአብሔር ይስጥልኝ» ብላ ወደ በሩ አመራች::
ከበሩ አጠገብ የሻገተ ዳቦ ወድቆ አየች:: ቶሎ ብላ አንስታ ቆረጠመችው::
«ጥሩ ነው፤ ግን እንደ ድንጋይ ደርቋል:: የተረፉት ጥርሶቼን ብቻ
እንዳያወልቅብኝ» እያለች ከክፍሉ ወጥታ ሄደች::
ለአምስት ዓመታት ማሪየስ በድኅነት፤ በብቸኝነትና በመከፋት ነው የኖረው:: እውነተኛ ችግር ማለት የቱ እንደሆነ ያወቀው ግን በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የወንድ ልጅ ስቃይ ያየ ሁሉ ስቃይና ችግር ማለት ምን እንደሆነ አውቃለሁ ብሎ ቢናገር ተሳስቷል፡፡ እውነተኛ ስቃይ፤ እውነተኛ መከራና
እውነተኛ ችግር የሚታየው በልጅነት ዘመን ደርሶ ሲታይ ስለሆነ እውነተኛ ችግር፣ ስቃይና መከራ ምን እንደሚመስል ያቺ መከረኛ ልጅ ለማሪዮስ
አሳየችው::
ማሪየስ ጎረቤቶቹ እንዴት እንደሚኖሩ እስከዚያን ጊዜ ድረስ ባለማየቱ ራሱን ወቀሰ፡፡ በአንድ ወቅት የቤት ኪራይ የከፈለላቸው ቅጽበታዊ ስሜት ገፋፍቶት ነበር፡፡ ለሰው የሚያዝን ሁሉ የሚያደርገው ነው:: ግን ማሪየስ
ከዚህ ልቆ መገኘት ነበረበት፡፡ ለምን ቢሉ እነዚህ ሰዎች ጋር የሚለያየው በአንድ ግድግዳ ስለሆነ ነው:: ከእርሱ ክፍል ቀጥሎ ያሉት ሰዎች ጦማቸውን
ውለው ጦማቸውን ያድራሉ፡፡ የቅርብ ጎረቤታቸው እርሱ ነው:: ሲተነፍስ እንኳን ይሰማቸዋል:: ሆኖም መኖር አለመኖራቸው እንኳን አልተገነዘበም::
በየእለቱ ድምፃቸውንና ኮቴያቸውን ቢያደምጥም እየሰማ አልሰማቸውም፤ እያሉ መኖራቸውን አላጤነም:: ቆሞ መሄድና መኖር ለየቅል ናቸው::
እርሱ በሌላ አሳብ ነበር የተያIlው:: የእርሱ ዓለም ከጎረቤቱ በጣም የተራራቀ ነው:: እርሱ በቅዠት ዓለም ሲንገዋለልና በፍቅር ዓለም ሲንሳፈፍ ጎረቤቱ በስቃይና በመከራ ዓለም መስመጣቸውን ልብ አላለም:: ከእነርሱ ቀጥሎ
ያለው ክፍል ምናልባት ለሰው የሚያዝን ሀብታም ቢገባበት ኖሮ ሰዎቹ ይረዱበት ነበር፡፡ ታዲያ ምን ይሆናል እርሱ መንገዱን ስለዘጋው ተስፋቸው በመነመነበት ፡፡ በርግጥ ሰዎቹ እድለቢስ፤ የአሳብ፤ የመንፈስና የገንዘብ ድሆች፤ክፉዎችና በሰዎች ዘንድ የተጠለ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህን ነው ምንዱባን ማለት የምድር ጎስቋላዎች ብለን የምንጠራቸው:: የማነው ጥፋቱ? የማይመለስ ጥያቄ! የተቸገረ በገጠመ ቁጥር የያዙትን ሁሉ መርጨት ይቻላል? አሁንም የማይመለስ ጥያቂ!
ማሪየስ ልጅትዋን ባየ ጊዜ ራሱን ከሚገባው በላይ ወቀሰ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የለየው ስስ ግድግዳ አተኩሮ ተመለከተው፤ መረመረው፡፡ ኮርኒሱ አጠገብ የሦስት ማዕዘን ቅርፅ ያለው ቀዳዳ አለ:: ጣራ ላይ ቢወጣ በዚያ
ቀዳዳ የጎረቤቱን ቤት ለማየት ይችላል፡፡ እስቲ ሰዎቹ ምን እንደሚመስሉ ባያቸውስ» ሲል አሰበ:: ወደ ቀዳዳው ተጠግቶ የጎረቤቶቹን ኑሮ በዓይኑ
ተመለከተ፡፡
ማሪየስ ራሱ ድሃ በመሆኑ የቤቱ እቃ እስከዚህም አልነበረም:: ቢሆንም ክፍሉ ንጹህ ነው:: ግን በቀዳዳ ያየው ዋሻ የከብት በረት እንጂ ሰው የሚኖርበት አይመስልም:: የመቆሸሹ፤ የወናነቱ፤ የመዝረክረኩና የማስጠላቱ መጠን እንዲህ ነው ብሎ ለመግለጽ ያዳግታል፡፡ የተሰባበሩ ሁለት የቀርከ
ወንበሮች፤ ቆሻሻ ያለበትና አንድ እግሩ የተሰበረ ጠረጴዛና የተሸራረፉ ሁለት ወይም ሦስት ሳህኖች ከክፍሉ ውስጥ ነበሩ:: ጥቀርሻ የመሰለ የሻይ
ማፍያ ጀበናና መጥበሻም ነበራቸው:: በመስኮትና በቀዳዳ ከሚገባ ብርሃን በስተቀር ሌላ መብራት የላቸውም:: መጋረጃቸው የሸረሪት ድር ነው:: እብድ እንደቦጫጨቀው ልብስ ወይም ድመት እንደቧጠጠው ፊት የቤቱ
ግድግዳዎች ተሰነጣጥቀዋል:: የማሪየስ ክፍል ወለል ሸክላ የተነጠፈ ሲሆን የእነዚህ ሰዎች ወለል ግን አዋራ የለበሰ ነው:: ከምድጃ ጭስ መውጣቱ ይታያል።
ከጠረጴዛው አጠገብ እንደ አሞራ አንገቱ የሳሳና እንደግመል ወገቡ
የጎበጠ ሽማግሌ ከወለል ላይ ተቀምጧል:: ሰውዬው የተቀዳደደ የሴት ሽሚዝ ለብሶ የተጣጣፈ ሱሪ ታጥቋል:: የእግሩ ጣቶች ካደረገው አሮጌ ቦት ጫማ ሾልከው በመውጣታቸው ከሩቅ ይታያሉ፡፡ ፒፓ ካፉ ላይ ሰክቶ
ይታያል፡፡
ያጨሳል፡፡ ከቤት ውስጥ ዳቦ ይጥፋ እንጂ ትምባሆ ኣ
ከልጠፋም:: ሰውዬው
እየጮኸ ሲናገር ማሪየስ ሰማው::
«ከሞትን በኋላ እንኳን ሁላችንም እኩል ነን ብሎ ማሰብ ሞኝነት
ነው:: ትልቅ ሰው ሲሞት የሚታጀበው በሠረገላ ነው:: ድሃ ሲሞት ቀባሪ እንኳን የሚያገኘው በግድ ነው:: የመቃብር ቦታም ቢሆን በምርጫ ነው የሚወሰነው:: ድሃ ከወንዙ ተረተር ወይም ከረግረጉ ላይ ሲቀበር ሀብታሙ ከአፋፉ ከደረቁ ቦታ ላይ ነው የሚቀበረው::»
አንዲት አርባ ወይም መቶ ዓመት ይሁናት የማታስታውቅ ሴት
ምራቅዋን ከእሳት ማንደጃው ላይ ደጋግማ ትተፋለች፡፡ እንደ ሰውዬው ! እርስዋም የተቀዳደደ ሸሚዝና የተጣጣፈ ጉርድ ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ጉልበትዋን
አጣጥፋና ወገብዋን ሰብራ ብትቀመጥም ረጅም መሆንዋን ታስታውቃለች::አጠገብዋ አንዲት ቀጠን ያለች ልጅ ተቀምጣለች፡፡ ልጅትዋ ማጋነን ባይሆን
ራቁትዋን ናት ማለት ይቻላል፡፡ ይህቺ ልጅ ከቤቱ ውስጥ የነበሩት ሰዎች የሚያወሩትን ማዳመጥ ቀርቶ የምትሰማ ወይም ከነአካቴው በዚህ ዓለም
የመኖር ጉጉት ያላት አትመስልም:: ልጅትዋ ከማሪየስ ቤት የመጣችው ልጅ ታናሽ እህት መሆን አለባት:: አሥራ አንድ ወይም አሥራ ሁለት ዓመት ቢሆናት ነው::
ልጅቱ ሳትፈልግ በግድ የተወለደች ትመስላለች:: የልጅነትም ሆነ
የወጣትነት ዘመን ምን እንደሆነ አታውቅም:: በአሥራ አምስት ዓመትዋ የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ፤ በአሥራ ስድስት ዓመትዋ የሃያ ዓመት ሴት ሳትመስል አትቀርም:: የዛሬዋ ትንሽ ልጅ የነገዋ አሮጊት ናት::
ማሪየስ ከዚያ ተንጠልጥሉ ለጥቂት ጊዜ ያንን ወና ቤት ቃኘው። ቅል የለው ማሰሮ፤ ወና ባዶ ቤት! ከመቃብር ቤት ይበልጥ ያስፈራል። ሰውዬው ዝም ብሎአል፡፡ ሴትዮዋም ቃል አትተነፍስም፡፡ ልጅትዋ መናገር
ቀርቶ የምትተነፍስ እንኳን አትመስልም፡፡
ሰውዬው ቆይቶ ቆይቶ «ተልካሻ፤ ሁሉም ነገር ተልካሻ ነው» ሲል
አጉረመረመ፡፡
አንዳንድ ቀን ማታ ማታ ወደ ውጭ እወጣለሁ:: አልፎ አልፎ በዚዬው እንደወጣሁ እቀራለሁ:: ባለፈው ዓመት አሁን ካለንበት ቤት
ከመግባታችን በፊት ከድልድይ ስር ነበር የምናድረው:: መቼም ብርዱ አይጣል ነው:: ትንሽዋ እህቴ እንዴት ይበርዳል ፤ አልበሱኝ እያለች ስትጮህ ነበር የምታድረው:: ታዲያ አንዳንድ ቀን በጣም ሰልቸት ሲለኝ ዝም ብዬ
በባዶ ሆዴ እዞር ነበር፡፡ ሁሉም ነገር ይምታታብኛል ፤ ይዞርብኛል::
የሚሆነውን ሁሉ አላውቅም:: ድምፅ ብቻ እሰማለሁ፡፡ አለ አይደል፧ ሆድ ባዶ ሲሆን የሚያደርገው ዓይነት::»
በመጨረሻ ዓይንዋ እየተንከራተተ አተኩራ አየችው::
ማሪየስ ኪሱን ሁሉ ሲበረብር አምስት ፍራንክና አሥራ ስድስት ሱስ አገኘ፡፡ የነበረው ገንዘብ ይኸው ነው:: «ለምሣ ይሆነኝ ነበር» ሲል አሰበ::
«ግን እኮ ነገ የሚሆነው አይታወቅም::ገንዘቡን አነሳና ለልጅትዋ ሰጣት.. ቶሎ ብላ ቆጠረችው::
«ተመስገን፧ ፀሐይዋ በራች» ስትል ተናገረች:: ከዚያም በማመስገን
ለጥ ብላ እጅ ነሳችው:: «እግዚአብሔር ይስጥልኝ» ብላ ወደ በሩ አመራች::
ከበሩ አጠገብ የሻገተ ዳቦ ወድቆ አየች:: ቶሎ ብላ አንስታ ቆረጠመችው::
«ጥሩ ነው፤ ግን እንደ ድንጋይ ደርቋል:: የተረፉት ጥርሶቼን ብቻ
እንዳያወልቅብኝ» እያለች ከክፍሉ ወጥታ ሄደች::
ለአምስት ዓመታት ማሪየስ በድኅነት፤ በብቸኝነትና በመከፋት ነው የኖረው:: እውነተኛ ችግር ማለት የቱ እንደሆነ ያወቀው ግን በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የወንድ ልጅ ስቃይ ያየ ሁሉ ስቃይና ችግር ማለት ምን እንደሆነ አውቃለሁ ብሎ ቢናገር ተሳስቷል፡፡ እውነተኛ ስቃይ፤ እውነተኛ መከራና
እውነተኛ ችግር የሚታየው በልጅነት ዘመን ደርሶ ሲታይ ስለሆነ እውነተኛ ችግር፣ ስቃይና መከራ ምን እንደሚመስል ያቺ መከረኛ ልጅ ለማሪዮስ
አሳየችው::
ማሪየስ ጎረቤቶቹ እንዴት እንደሚኖሩ እስከዚያን ጊዜ ድረስ ባለማየቱ ራሱን ወቀሰ፡፡ በአንድ ወቅት የቤት ኪራይ የከፈለላቸው ቅጽበታዊ ስሜት ገፋፍቶት ነበር፡፡ ለሰው የሚያዝን ሁሉ የሚያደርገው ነው:: ግን ማሪየስ
ከዚህ ልቆ መገኘት ነበረበት፡፡ ለምን ቢሉ እነዚህ ሰዎች ጋር የሚለያየው በአንድ ግድግዳ ስለሆነ ነው:: ከእርሱ ክፍል ቀጥሎ ያሉት ሰዎች ጦማቸውን
ውለው ጦማቸውን ያድራሉ፡፡ የቅርብ ጎረቤታቸው እርሱ ነው:: ሲተነፍስ እንኳን ይሰማቸዋል:: ሆኖም መኖር አለመኖራቸው እንኳን አልተገነዘበም::
በየእለቱ ድምፃቸውንና ኮቴያቸውን ቢያደምጥም እየሰማ አልሰማቸውም፤ እያሉ መኖራቸውን አላጤነም:: ቆሞ መሄድና መኖር ለየቅል ናቸው::
እርሱ በሌላ አሳብ ነበር የተያIlው:: የእርሱ ዓለም ከጎረቤቱ በጣም የተራራቀ ነው:: እርሱ በቅዠት ዓለም ሲንገዋለልና በፍቅር ዓለም ሲንሳፈፍ ጎረቤቱ በስቃይና በመከራ ዓለም መስመጣቸውን ልብ አላለም:: ከእነርሱ ቀጥሎ
ያለው ክፍል ምናልባት ለሰው የሚያዝን ሀብታም ቢገባበት ኖሮ ሰዎቹ ይረዱበት ነበር፡፡ ታዲያ ምን ይሆናል እርሱ መንገዱን ስለዘጋው ተስፋቸው በመነመነበት ፡፡ በርግጥ ሰዎቹ እድለቢስ፤ የአሳብ፤ የመንፈስና የገንዘብ ድሆች፤ክፉዎችና በሰዎች ዘንድ የተጠለ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህን ነው ምንዱባን ማለት የምድር ጎስቋላዎች ብለን የምንጠራቸው:: የማነው ጥፋቱ? የማይመለስ ጥያቄ! የተቸገረ በገጠመ ቁጥር የያዙትን ሁሉ መርጨት ይቻላል? አሁንም የማይመለስ ጥያቂ!
ማሪየስ ልጅትዋን ባየ ጊዜ ራሱን ከሚገባው በላይ ወቀሰ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የለየው ስስ ግድግዳ አተኩሮ ተመለከተው፤ መረመረው፡፡ ኮርኒሱ አጠገብ የሦስት ማዕዘን ቅርፅ ያለው ቀዳዳ አለ:: ጣራ ላይ ቢወጣ በዚያ
ቀዳዳ የጎረቤቱን ቤት ለማየት ይችላል፡፡ እስቲ ሰዎቹ ምን እንደሚመስሉ ባያቸውስ» ሲል አሰበ:: ወደ ቀዳዳው ተጠግቶ የጎረቤቶቹን ኑሮ በዓይኑ
ተመለከተ፡፡
ማሪየስ ራሱ ድሃ በመሆኑ የቤቱ እቃ እስከዚህም አልነበረም:: ቢሆንም ክፍሉ ንጹህ ነው:: ግን በቀዳዳ ያየው ዋሻ የከብት በረት እንጂ ሰው የሚኖርበት አይመስልም:: የመቆሸሹ፤ የወናነቱ፤ የመዝረክረኩና የማስጠላቱ መጠን እንዲህ ነው ብሎ ለመግለጽ ያዳግታል፡፡ የተሰባበሩ ሁለት የቀርከ
ወንበሮች፤ ቆሻሻ ያለበትና አንድ እግሩ የተሰበረ ጠረጴዛና የተሸራረፉ ሁለት ወይም ሦስት ሳህኖች ከክፍሉ ውስጥ ነበሩ:: ጥቀርሻ የመሰለ የሻይ
ማፍያ ጀበናና መጥበሻም ነበራቸው:: በመስኮትና በቀዳዳ ከሚገባ ብርሃን በስተቀር ሌላ መብራት የላቸውም:: መጋረጃቸው የሸረሪት ድር ነው:: እብድ እንደቦጫጨቀው ልብስ ወይም ድመት እንደቧጠጠው ፊት የቤቱ
ግድግዳዎች ተሰነጣጥቀዋል:: የማሪየስ ክፍል ወለል ሸክላ የተነጠፈ ሲሆን የእነዚህ ሰዎች ወለል ግን አዋራ የለበሰ ነው:: ከምድጃ ጭስ መውጣቱ ይታያል።
ከጠረጴዛው አጠገብ እንደ አሞራ አንገቱ የሳሳና እንደግመል ወገቡ
የጎበጠ ሽማግሌ ከወለል ላይ ተቀምጧል:: ሰውዬው የተቀዳደደ የሴት ሽሚዝ ለብሶ የተጣጣፈ ሱሪ ታጥቋል:: የእግሩ ጣቶች ካደረገው አሮጌ ቦት ጫማ ሾልከው በመውጣታቸው ከሩቅ ይታያሉ፡፡ ፒፓ ካፉ ላይ ሰክቶ
ይታያል፡፡
ያጨሳል፡፡ ከቤት ውስጥ ዳቦ ይጥፋ እንጂ ትምባሆ ኣ
ከልጠፋም:: ሰውዬው
እየጮኸ ሲናገር ማሪየስ ሰማው::
«ከሞትን በኋላ እንኳን ሁላችንም እኩል ነን ብሎ ማሰብ ሞኝነት
ነው:: ትልቅ ሰው ሲሞት የሚታጀበው በሠረገላ ነው:: ድሃ ሲሞት ቀባሪ እንኳን የሚያገኘው በግድ ነው:: የመቃብር ቦታም ቢሆን በምርጫ ነው የሚወሰነው:: ድሃ ከወንዙ ተረተር ወይም ከረግረጉ ላይ ሲቀበር ሀብታሙ ከአፋፉ ከደረቁ ቦታ ላይ ነው የሚቀበረው::»
አንዲት አርባ ወይም መቶ ዓመት ይሁናት የማታስታውቅ ሴት
ምራቅዋን ከእሳት ማንደጃው ላይ ደጋግማ ትተፋለች፡፡ እንደ ሰውዬው ! እርስዋም የተቀዳደደ ሸሚዝና የተጣጣፈ ጉርድ ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ጉልበትዋን
አጣጥፋና ወገብዋን ሰብራ ብትቀመጥም ረጅም መሆንዋን ታስታውቃለች::አጠገብዋ አንዲት ቀጠን ያለች ልጅ ተቀምጣለች፡፡ ልጅትዋ ማጋነን ባይሆን
ራቁትዋን ናት ማለት ይቻላል፡፡ ይህቺ ልጅ ከቤቱ ውስጥ የነበሩት ሰዎች የሚያወሩትን ማዳመጥ ቀርቶ የምትሰማ ወይም ከነአካቴው በዚህ ዓለም
የመኖር ጉጉት ያላት አትመስልም:: ልጅትዋ ከማሪየስ ቤት የመጣችው ልጅ ታናሽ እህት መሆን አለባት:: አሥራ አንድ ወይም አሥራ ሁለት ዓመት ቢሆናት ነው::
ልጅቱ ሳትፈልግ በግድ የተወለደች ትመስላለች:: የልጅነትም ሆነ
የወጣትነት ዘመን ምን እንደሆነ አታውቅም:: በአሥራ አምስት ዓመትዋ የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ፤ በአሥራ ስድስት ዓመትዋ የሃያ ዓመት ሴት ሳትመስል አትቀርም:: የዛሬዋ ትንሽ ልጅ የነገዋ አሮጊት ናት::
ማሪየስ ከዚያ ተንጠልጥሉ ለጥቂት ጊዜ ያንን ወና ቤት ቃኘው። ቅል የለው ማሰሮ፤ ወና ባዶ ቤት! ከመቃብር ቤት ይበልጥ ያስፈራል። ሰውዬው ዝም ብሎአል፡፡ ሴትዮዋም ቃል አትተነፍስም፡፡ ልጅትዋ መናገር
ቀርቶ የምትተነፍስ እንኳን አትመስልም፡፡
ሰውዬው ቆይቶ ቆይቶ «ተልካሻ፤ ሁሉም ነገር ተልካሻ ነው» ሲል
አጉረመረመ፡፡
👍15
ማሪየስ ባየው ነገር በጣም ተሳቅቆ ከነበረበት ሊወርደው ሲል ድምፅ በመስማቱ ከዚያው እንዲቆይ ይገደዳል፡፡ ሰዎቹ የነበሩበት ክፍል በር በችኮላ ይከፈታል፡፡ ትልቅዋ ልጅ ብቅ አለች:: በጭቃ የተለወሰ የወንድ 1
ጫማ አጥልቃለች:: ከአንድ ሰዓት በፊት ከማሪየስ ቤት ስትመጣ
ያልለበሰችውን የሌሊት ልብስ መሳይ ነገር ደርባለች:: ምናልባት ከማሪየስ ቤት ስትመጣ ለማሳዘን ብላ የደረበችውን ልብስ ከአጥር ውጭ አስቀመጣው ስትመለስ ለብሳው ይሆናል፡፡ በሩን በኃይል በርግዳ ከገባች በኋላ በኃይል
ወርውራ ዘጋችው:: ትንፋሽዋን ለመሰብሰብ ቆም አለች:: ከክፍሉ ውስጥ ስትገባ ትንፋሽ አጥሮአት በኃይል ነበር የምትተነፍሰው፡፡ ከዚያም የደስታ የእፎይታ አይታወቅም «እየመጣ ነው» ስትል ጮኸች፡፡
አባትየው ቀና ብሎ ተመለከታት፡፡ እናትየዋ ፊትዋን አዞረች፡፡ ትንሽዋ
ልጅ ነቅነቅ አላለችም::
«ማነው እሱ?» ኣባትየው ጠየቀ::
«ሰውዬው!»
«ለነፍሱ ያደረው?»
«አዎን»
«ደጉ ሰውዬ ነው?»
«አዎን»
«እውነትዋን ነው እንዴ? እየመጣ ነው?»
«በጋሪ እየመጡ ነው፡፡»
አባትየው ተነሳ፡፡
«እርግጠኛ ነሽ፤ እየመጣ ነው? ብቻ ይህቺን ወስላታ ማን ያምናል
ይህን ጊዜ ኣድራሻው ጠፍቶባት ይሆናል፡፡»
አባትየው ይህን ሲናገር በራቸው በዝግታ ተንኳኳ፡፡ ሰውዬው ሮጦ
ሄዶ በሩን ከፈተ፡፡ እየደጋገመ በማጎንበስ እጅ ነሳ፡፡
«ይግቡ ጌታዬ፤ ይግቡ:: እመቤት ገባ በይ እንጂ፤ ቤት ለእንግዳ፤
ግቡ! ግቡ» ሲል ቀባጠረ፡፡
አንድ ጠና ያለ ሰውና አንዲት ወጣት ከክፍሉ ውስጥ ገቡ:: ማሪየስ ከነበረበት እያየ ነው:: ምን ዓይነት ስሜት እንደተሰማው ለመግለጽ ያዳግታል፡፡
«እስዋው ናት፡፡»
ከፍቅር ወጥመድ ገብቶ የወጣ ብቻ ነው «እስዋው ናት» ማለት ምን ዓይነት ስሜት እንደሚያሳድር ሊገባው የሚችለው::
በእርግጥ እስዋው ነበረች:: በድንገት ዓይኑን የጋረደው ደመና መሰል ስድስት ወር መላ የጠፋችበት የጨለማ ኮከብ፤ በድንገት ብቅ አለች:: ያ ነገር ስላጨለመው በግልጽ ሊያያት አልቻለም:: ያቺ የዓይኑ ተስፋ ፤ ያቺ
እረፍት የነሳው ዓይን፤ ቅንድብ፤ አፍ፤ ከዓይኑ የተሰወረ ውበት ከፊቱ ድቅን ሲል ሕልም እንጂ እውን አልመሰለውም:: ያቺ ቆንጆ የመጣችው ያንን በረት የመሰለ ቤት ልታይ ነው።
የማሪየስ ሰውነት ተንሰፈሰፈ:: ምን! አሁን እርስዋ ናት ማለት ነው!
የልቡ ዓመታት እይታውን ጋረደበት:: ስቅስቅ ብሉ ሊያለቅስ ፈለገ፡፡ እንዴት? ከብዙ ቀን ፍለጋ በኋላ በድንገት እንደገና ስላገኛት! ወይስ ጠፍቶ የነበረውን ነፍሱ እንደገና ስላገኘ! የምን ማልቀስ አይገባም::
ብዙም አልተለወጠችም:: ትንሽ ግን ገርጥታለች:: ፊትዋ ባደረገችው ሰፊ ቆብ፤ የሰውነትዋ ቅርፅ በለበሰችው ካፖርት በመጠኑ ተሸፍኖአል፡፡
አብሮአት ያለው ሰው «አባባ ሸበቶ» ነው::
ወደ ውስጥ ራመድ በማለት በእጅዋ ይዛው የነበረወን አንድ
የተጠቀለለ ነገር ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች::
ትልቅዋ ልጅ ወደ ኋላ ሸሸት ካለች በኋላ ኮዜት ያጠለቀችውን ሰፊ
ባርኔጣ፤ የሐር ቀሚስና የደስ ደስ ያለው ፊት በቅናት ዓይን ተመለከተች::
አባባ ሸበቶ በሩህሩህ ዓይን እያየ ሰውዬውን አነጋገረው::
«ከዚህ ከተጠቀለለው ፓኮ ውስጥ ጥቂት አዳዲስ ልብሶችና
ብርድልብሶች ስላሉ ተጠቀሙበት::»
«ምስጋናችን በጣም የላቀ ነው:: ውለታዎ በጣም ከባድ ነው» አለች
ትልቅዋ ልጅ ለጥ ብላ እጅ እየነሳች:: ልጅትዋ ይህን ስትናገር አባትዋ ወደ ልጅቱ ጆሮ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ «አላልኩሽም? እቃ ብቻ! ገንዘብ የለም፡፡ ሁሉም ያው ናቸው» አላት:: አባባ ሸበቶና ኮዜት የቤቱ ሁኔታ አስገርሞአቸው
ጣራና ግድግዳውን ሲያዩ ሰውዬው ምንድነው የሚለው ብለው ስላልተጨነቁ፤ አልሰሙትም:::
ልጅትዋ ሁለቱን እንግዶች በአድናቆት ማየትዋን ቀጠለች:: እየተናገረች እንኳን ሰውዬውንና ልጅትዋን ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር እየቃኘት ነበር፡፡ ባልተቤቱ በድንገት ከመሬቱ ላይ ተጋድማ ወደነበረችው ወደ ሚስቱ
ፈጠን ብሎ ሄደ:: ድምፁን ዝቅ አድርጎ «ይህን ሰው ተመልከቺው» ሲል ተናገረ፡፡ ከዚያም ወደ አባባ ሸበቶ ሄዶ የሚከተለውን ተናገረ፡፡
«አዬ ጌታዬ! እንደሚመለከቱት ገላዬን የሸፈንኩት በባለቤቴ ሸሚዝ ! ነው:: እርሱም ቢሆን የተቀዳደደ ነው:: ሸሚዝ ባይኖር የታጠቁት ሱሪ ገመናዬን ባልሸፈነ ነበር፡፡ ጊዜው ደግሞ ክረምት ነው:: በልብስ እጦት ምክንያት ብርዱ ስለሚያስፈራ ከቤት አልወጣም:: ጌታዬ ፤ ነገ ምን እንደሚሆን ያውቃሉ? ነገ የካቲት 4 ቀን ነው:: (በአውሮጳ
ወርሃ የካቲት ክረምት ነው)፡፡ ቤቱ ያከራዩኝ ሰው እስከዚህ ቀን ዋዜማ ድረስ የቤቱን ኪራይ ;
ልከፍል ከዚህ ቤት እንደሚያስወጣኝ የመጨረሻ ቃሉን ሰጥቶኛል፡፡ ዛሬ ማታ መሆኑ ነው መሰለኝ! እንግዲህ ነገ ጠዋት ገመምተኛዋ ባለቤቴ ፧ሁለቱ
ልጆቼና እኔው ራሴ ከዚህ ቤት እንባረራለን ማለት ነው:: ከበረንዳ
በስተቀር ሌላ መጠጊያ የለንም:: በዚህ ብርድ ፧ በዚህ ቅዝቃዜ ያለልብስ በረንዳ ማደር ማለት ምን እንደሆነ ጌታዬ የሚያውቁት ነው:: ዝናብ ይዘንባል ፧ ወጨፎ አለ፡፡ አይጣል ነው ብቻ! ጌታዬ የስድስት ወር የቤት ኪራይ አለብኝ:: የተጠራቀመብኝ ውዝፍ ስልሣ ፍራንክ ነው::»
ግን ሰውዬው ውሸቱን ነበር፡፡ ማሪየስ የሁለት ወር የቤት ኪራይ
ስለከፈለለት ያለበት ውዝፍ ኪራይ የስድስት ወር አይሞላም:: አባባ ሸበቶ ከኪሱ አምስት ፍራንክ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ በተናቸው::
ዦንድሬ ማለት ሰውዬው ወደ ትልቅዋ ልጅ ዞር ብሉ «ይኼ
በሽቲያም! አምስት ፍራንክ ምን እንዳደርገው ነው የሚጥልልኝ?» ሲል በሹክሹክታ ተናገረ::
ወዲያው አባባ ሸበቶ ካፖርቱን አውልቆ ካጣጠፈው በኋላ ከወንበር ድጋፍ ላይ አስቀመጠው::
«በአሥራ ሁለት ሰዓት እመለሳለሁ» ካለ በኋላ «ያኔ ስመለስ ስልሣውን ፍራንክ አመጣልሃለሁ» ሲል ተናገረ::
«ባለውለታዎ ነኝ፤ በጣም ደግ ሰው ነዎት» ሲል ዦንድሬ እየጮኸ
መለሰ፡፡
የትልቅዋ ልጅ ዓይን ከካፖርቱ ላይ አረፈ፡፡
«ጌታዬ፤ ካፖርትዎን ረስተዋል!» ስትል አስታወሰች፡፡
ሚስተር ዣንድሬ ልጅትዋን ክፉኛ በዓይኑ ገሰፃት፡፡
አባባ ሸበቶ ወደ ልጅትዋ ዞር በማለት በፈገግታ መለሰላት፡፡
«ረስቼ አይደለም፤ ሆን ብዬ ነው ያስቀመጥኩት::»
“ጌታዬ» አለ ዦንድሬ ፤ በጣም ለተቸገረ ያዝናሉ ማለት ነው ፤
ከማመስገን በስተቀር ውለታዎን መክፈል አይቻልም:: እስከበሩ እንድሸኝዎት ቢፈቀድልኝ፡፡»
«ከወጣህ» አለ አባባ ሸበቶ፣ ‹‹ካፖርቱን ልበሰው በጣም ይበርዳል::»
ሚስተር ዣንድሬ በድጋሚ እስኪነገረው አልጠበቀም ፧ ቶሉ ብሎ ካፖርቱን ለበሰው:: ሁለቱ እንግዶችና ሚስተር ዦንድሬ ተያይዘው ወጡ፡፡
ሚስተር ዦንድሬ ቀደም ቀደም አለ፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
ጫማ አጥልቃለች:: ከአንድ ሰዓት በፊት ከማሪየስ ቤት ስትመጣ
ያልለበሰችውን የሌሊት ልብስ መሳይ ነገር ደርባለች:: ምናልባት ከማሪየስ ቤት ስትመጣ ለማሳዘን ብላ የደረበችውን ልብስ ከአጥር ውጭ አስቀመጣው ስትመለስ ለብሳው ይሆናል፡፡ በሩን በኃይል በርግዳ ከገባች በኋላ በኃይል
ወርውራ ዘጋችው:: ትንፋሽዋን ለመሰብሰብ ቆም አለች:: ከክፍሉ ውስጥ ስትገባ ትንፋሽ አጥሮአት በኃይል ነበር የምትተነፍሰው፡፡ ከዚያም የደስታ የእፎይታ አይታወቅም «እየመጣ ነው» ስትል ጮኸች፡፡
አባትየው ቀና ብሎ ተመለከታት፡፡ እናትየዋ ፊትዋን አዞረች፡፡ ትንሽዋ
ልጅ ነቅነቅ አላለችም::
«ማነው እሱ?» ኣባትየው ጠየቀ::
«ሰውዬው!»
«ለነፍሱ ያደረው?»
«አዎን»
«ደጉ ሰውዬ ነው?»
«አዎን»
«እውነትዋን ነው እንዴ? እየመጣ ነው?»
«በጋሪ እየመጡ ነው፡፡»
አባትየው ተነሳ፡፡
«እርግጠኛ ነሽ፤ እየመጣ ነው? ብቻ ይህቺን ወስላታ ማን ያምናል
ይህን ጊዜ ኣድራሻው ጠፍቶባት ይሆናል፡፡»
አባትየው ይህን ሲናገር በራቸው በዝግታ ተንኳኳ፡፡ ሰውዬው ሮጦ
ሄዶ በሩን ከፈተ፡፡ እየደጋገመ በማጎንበስ እጅ ነሳ፡፡
«ይግቡ ጌታዬ፤ ይግቡ:: እመቤት ገባ በይ እንጂ፤ ቤት ለእንግዳ፤
ግቡ! ግቡ» ሲል ቀባጠረ፡፡
አንድ ጠና ያለ ሰውና አንዲት ወጣት ከክፍሉ ውስጥ ገቡ:: ማሪየስ ከነበረበት እያየ ነው:: ምን ዓይነት ስሜት እንደተሰማው ለመግለጽ ያዳግታል፡፡
«እስዋው ናት፡፡»
ከፍቅር ወጥመድ ገብቶ የወጣ ብቻ ነው «እስዋው ናት» ማለት ምን ዓይነት ስሜት እንደሚያሳድር ሊገባው የሚችለው::
በእርግጥ እስዋው ነበረች:: በድንገት ዓይኑን የጋረደው ደመና መሰል ስድስት ወር መላ የጠፋችበት የጨለማ ኮከብ፤ በድንገት ብቅ አለች:: ያ ነገር ስላጨለመው በግልጽ ሊያያት አልቻለም:: ያቺ የዓይኑ ተስፋ ፤ ያቺ
እረፍት የነሳው ዓይን፤ ቅንድብ፤ አፍ፤ ከዓይኑ የተሰወረ ውበት ከፊቱ ድቅን ሲል ሕልም እንጂ እውን አልመሰለውም:: ያቺ ቆንጆ የመጣችው ያንን በረት የመሰለ ቤት ልታይ ነው።
የማሪየስ ሰውነት ተንሰፈሰፈ:: ምን! አሁን እርስዋ ናት ማለት ነው!
የልቡ ዓመታት እይታውን ጋረደበት:: ስቅስቅ ብሉ ሊያለቅስ ፈለገ፡፡ እንዴት? ከብዙ ቀን ፍለጋ በኋላ በድንገት እንደገና ስላገኛት! ወይስ ጠፍቶ የነበረውን ነፍሱ እንደገና ስላገኘ! የምን ማልቀስ አይገባም::
ብዙም አልተለወጠችም:: ትንሽ ግን ገርጥታለች:: ፊትዋ ባደረገችው ሰፊ ቆብ፤ የሰውነትዋ ቅርፅ በለበሰችው ካፖርት በመጠኑ ተሸፍኖአል፡፡
አብሮአት ያለው ሰው «አባባ ሸበቶ» ነው::
ወደ ውስጥ ራመድ በማለት በእጅዋ ይዛው የነበረወን አንድ
የተጠቀለለ ነገር ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች::
ትልቅዋ ልጅ ወደ ኋላ ሸሸት ካለች በኋላ ኮዜት ያጠለቀችውን ሰፊ
ባርኔጣ፤ የሐር ቀሚስና የደስ ደስ ያለው ፊት በቅናት ዓይን ተመለከተች::
አባባ ሸበቶ በሩህሩህ ዓይን እያየ ሰውዬውን አነጋገረው::
«ከዚህ ከተጠቀለለው ፓኮ ውስጥ ጥቂት አዳዲስ ልብሶችና
ብርድልብሶች ስላሉ ተጠቀሙበት::»
«ምስጋናችን በጣም የላቀ ነው:: ውለታዎ በጣም ከባድ ነው» አለች
ትልቅዋ ልጅ ለጥ ብላ እጅ እየነሳች:: ልጅትዋ ይህን ስትናገር አባትዋ ወደ ልጅቱ ጆሮ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ «አላልኩሽም? እቃ ብቻ! ገንዘብ የለም፡፡ ሁሉም ያው ናቸው» አላት:: አባባ ሸበቶና ኮዜት የቤቱ ሁኔታ አስገርሞአቸው
ጣራና ግድግዳውን ሲያዩ ሰውዬው ምንድነው የሚለው ብለው ስላልተጨነቁ፤ አልሰሙትም:::
ልጅትዋ ሁለቱን እንግዶች በአድናቆት ማየትዋን ቀጠለች:: እየተናገረች እንኳን ሰውዬውንና ልጅትዋን ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር እየቃኘት ነበር፡፡ ባልተቤቱ በድንገት ከመሬቱ ላይ ተጋድማ ወደነበረችው ወደ ሚስቱ
ፈጠን ብሎ ሄደ:: ድምፁን ዝቅ አድርጎ «ይህን ሰው ተመልከቺው» ሲል ተናገረ፡፡ ከዚያም ወደ አባባ ሸበቶ ሄዶ የሚከተለውን ተናገረ፡፡
«አዬ ጌታዬ! እንደሚመለከቱት ገላዬን የሸፈንኩት በባለቤቴ ሸሚዝ ! ነው:: እርሱም ቢሆን የተቀዳደደ ነው:: ሸሚዝ ባይኖር የታጠቁት ሱሪ ገመናዬን ባልሸፈነ ነበር፡፡ ጊዜው ደግሞ ክረምት ነው:: በልብስ እጦት ምክንያት ብርዱ ስለሚያስፈራ ከቤት አልወጣም:: ጌታዬ ፤ ነገ ምን እንደሚሆን ያውቃሉ? ነገ የካቲት 4 ቀን ነው:: (በአውሮጳ
ወርሃ የካቲት ክረምት ነው)፡፡ ቤቱ ያከራዩኝ ሰው እስከዚህ ቀን ዋዜማ ድረስ የቤቱን ኪራይ ;
ልከፍል ከዚህ ቤት እንደሚያስወጣኝ የመጨረሻ ቃሉን ሰጥቶኛል፡፡ ዛሬ ማታ መሆኑ ነው መሰለኝ! እንግዲህ ነገ ጠዋት ገመምተኛዋ ባለቤቴ ፧ሁለቱ
ልጆቼና እኔው ራሴ ከዚህ ቤት እንባረራለን ማለት ነው:: ከበረንዳ
በስተቀር ሌላ መጠጊያ የለንም:: በዚህ ብርድ ፧ በዚህ ቅዝቃዜ ያለልብስ በረንዳ ማደር ማለት ምን እንደሆነ ጌታዬ የሚያውቁት ነው:: ዝናብ ይዘንባል ፧ ወጨፎ አለ፡፡ አይጣል ነው ብቻ! ጌታዬ የስድስት ወር የቤት ኪራይ አለብኝ:: የተጠራቀመብኝ ውዝፍ ስልሣ ፍራንክ ነው::»
ግን ሰውዬው ውሸቱን ነበር፡፡ ማሪየስ የሁለት ወር የቤት ኪራይ
ስለከፈለለት ያለበት ውዝፍ ኪራይ የስድስት ወር አይሞላም:: አባባ ሸበቶ ከኪሱ አምስት ፍራንክ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ በተናቸው::
ዦንድሬ ማለት ሰውዬው ወደ ትልቅዋ ልጅ ዞር ብሉ «ይኼ
በሽቲያም! አምስት ፍራንክ ምን እንዳደርገው ነው የሚጥልልኝ?» ሲል በሹክሹክታ ተናገረ::
ወዲያው አባባ ሸበቶ ካፖርቱን አውልቆ ካጣጠፈው በኋላ ከወንበር ድጋፍ ላይ አስቀመጠው::
«በአሥራ ሁለት ሰዓት እመለሳለሁ» ካለ በኋላ «ያኔ ስመለስ ስልሣውን ፍራንክ አመጣልሃለሁ» ሲል ተናገረ::
«ባለውለታዎ ነኝ፤ በጣም ደግ ሰው ነዎት» ሲል ዦንድሬ እየጮኸ
መለሰ፡፡
የትልቅዋ ልጅ ዓይን ከካፖርቱ ላይ አረፈ፡፡
«ጌታዬ፤ ካፖርትዎን ረስተዋል!» ስትል አስታወሰች፡፡
ሚስተር ዣንድሬ ልጅትዋን ክፉኛ በዓይኑ ገሰፃት፡፡
አባባ ሸበቶ ወደ ልጅትዋ ዞር በማለት በፈገግታ መለሰላት፡፡
«ረስቼ አይደለም፤ ሆን ብዬ ነው ያስቀመጥኩት::»
“ጌታዬ» አለ ዦንድሬ ፤ በጣም ለተቸገረ ያዝናሉ ማለት ነው ፤
ከማመስገን በስተቀር ውለታዎን መክፈል አይቻልም:: እስከበሩ እንድሸኝዎት ቢፈቀድልኝ፡፡»
«ከወጣህ» አለ አባባ ሸበቶ፣ ‹‹ካፖርቱን ልበሰው በጣም ይበርዳል::»
ሚስተር ዣንድሬ በድጋሚ እስኪነገረው አልጠበቀም ፧ ቶሉ ብሎ ካፖርቱን ለበሰው:: ሁለቱ እንግዶችና ሚስተር ዦንድሬ ተያይዘው ወጡ፡፡
ሚስተር ዦንድሬ ቀደም ቀደም አለ፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
👍27