#ድምጽ_አልባ_ጩኸት
ባይሆንማ ኖሮ ድምጽ አልባ ጩኸት
ለአዕምሮ ቃል ማውጫ ቢኖር አንደበት
ከምድር የሚሰማው የሰዎች ብሶት
ጫጫታና ረብሻ እግዜር ሆኖበት
መልስ ባልሰጠ ነበር መስማት አቅቶት፡፡
ባይሆንማ ኖሮ ድምጽ አልባ ጩኸት
ለአዕምሮ ቃል ማውጫ ቢኖር አንደበት
ከምድር የሚሰማው የሰዎች ብሶት
ጫጫታና ረብሻ እግዜር ሆኖበት
መልስ ባልሰጠ ነበር መስማት አቅቶት፡፡
#ፀደይን_በመስኮት
ክረምቱ ሲወጣ
ርጥብ ዳሱን ነቅሎ
አዳሜ
ከተሜ
ጃንጥላውን ሰቅሎ
ካቦርታውን ጥሎ።
አዳም ከሄዋኑ
(ድስት ከነክዳኑ)
ላጤውም ለብቻው
ወንዱ ደረት ሊያሳይ
በባሕር ዳርቻው
ሴቱም እንደልቡ፣ ቂጡን እየጣለ
በሙቅ አሸዋ ላይ
እየተንጋለለ
ቅብጠት ድርያ ሲያምረው
ማጭድ ታጥቆ ገባ
ሁሉን የማይምረው
ፊት ያለውን ሁሉ
በብረት መዳፉ፣ የሚያጠናግረው።
እምቢልታ ተነፋ
ደወል ተደወለ
ያልታደለው ጠፋ
ቀሪው እቤት ዋለ
ሰው ቤቱ መሸገ
መስኮት እንደጋሻ፣ እየወለወለ።
በየአደባባዩ
እዩኝ እዩኝ ባዩ
እንዳልተጀነነ
ሰው ለመኖር ብሎ፣ ከኑሮ መነነ!
እኔም እንዳገሬው፣ ለነፍሴ ብሳሳ
ለብሻት ሰነበትኩ፣ ቤቴን እንደገሳ።
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
ክረምቱ ሲወጣ
ርጥብ ዳሱን ነቅሎ
አዳሜ
ከተሜ
ጃንጥላውን ሰቅሎ
ካቦርታውን ጥሎ።
አዳም ከሄዋኑ
(ድስት ከነክዳኑ)
ላጤውም ለብቻው
ወንዱ ደረት ሊያሳይ
በባሕር ዳርቻው
ሴቱም እንደልቡ፣ ቂጡን እየጣለ
በሙቅ አሸዋ ላይ
እየተንጋለለ
ቅብጠት ድርያ ሲያምረው
ማጭድ ታጥቆ ገባ
ሁሉን የማይምረው
ፊት ያለውን ሁሉ
በብረት መዳፉ፣ የሚያጠናግረው።
እምቢልታ ተነፋ
ደወል ተደወለ
ያልታደለው ጠፋ
ቀሪው እቤት ዋለ
ሰው ቤቱ መሸገ
መስኮት እንደጋሻ፣ እየወለወለ።
በየአደባባዩ
እዩኝ እዩኝ ባዩ
እንዳልተጀነነ
ሰው ለመኖር ብሎ፣ ከኑሮ መነነ!
እኔም እንዳገሬው፣ ለነፍሴ ብሳሳ
ለብሻት ሰነበትኩ፣ ቤቴን እንደገሳ።
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
መሆናቸውን ብታውቅም እስከመጨረሻው ይከፉብኛል ብላ
አላሰበችም ነበርና በጊዜው ላፈቀረችው ሰው ቤተሰቧን ማጣቷ የሚገባው የመሰላት መስዋዕትነት ነበር። ሁሉም ሰላም እና ውብ ነበር። እየቆየ የባሏ ባህሪ መቀየር ጀመረ:: እሷ መርማሪ ፖሊስ
መሆኗን ተከትሎ ቤቷ ብጥብጥ ወረሰው።ዘግይቶ ሲገባት በብዙ
ህገወጥ ንግዶች ላይ እጁ እንዳለበት ጠረጠረች፡፡ ቢሆንም በቂ መረጃ የላትም
ቢሆንም ታፈቅረዋለች፡፡ቢሆንም ካለ እርሱ አንካሳ ናትና በየእለቱ እንደምትበረታባቸው ወንጀለኞች መረጃ
ለማግኘት አልታተረችም።በዚህ ትርምስ ውስጥ አርሴማ መጣች፡፡በመጀመሪያ የአርሴማ መወለድ ነገሮችን ያበረደ
መሰለ። ውጪ ማደሩን ተወ። መደብደቡን አቆመ።ድጋሚ የምታልመው ጥሩ ትዳር ኖራት። አርሴማ እያደገች ጤነኛ
አለመሆኗን ሲያውቅ ከበፊቱ በባሰ ከፋ፡፡
"እሺ እኔ ምን ማድረግ ነበረብኝ? እኔ እግዚአብሄር ነኝ? ልጄ ጤነኛ ብትሆን እኔስ ደስተኛ አልነበርኩም? ምን ማድረግ እችል ነበር?" አለችኝ ቀና ብላ፡፡
አርሴማ ከፍ ስትል ጭራሽ ከቤቱም ወጣ፡፡ በሁለት ሳምንት አንዴ (ትናንት እንዳደረገው) አርብ ከሰዓት መጥቶ አርሴማን ቤተሰቦቹጋ ይዟት ይሄዳል። ለልጁ የሚያስፈልገውን እሱም ሆነ
ቤተሰቡ ከማድረግ ቦዝነው አያውቁም፡፡ እሷን ከወንድ ጋር ታየሽ፣ ለልጄ መልካም አርአያ እየሆንሽ አይደለም እያለ
መቆጣጠሩን አለፍ ሲልም ትላንት እንዳደረገው መደብደቡን ቀጠለ። ምንም ማድረግ እንዳትችል አርሴማ አበሰረቻት። አርሴማ አባቷን ስታይ ፈንጠዝያ የሚቀሙት አይደለም። እሱ ሄዶ
ከትምህርት ቤት ያመጣት ቀን ስትጫወት ታመሻለች።
ልጄ ጤነኛ ብትሆን እና እንደ ጤነኛ ልጅ በሌላ የምትደሰት ብትሆን እሺ!
እንዴት አንድ የሳቋን ምክንያት
አሁንም ድረስ፡፡ ከእርሱ ጋር የነበራትን ህይወት ከመመለስ ልንጠቃት? ታውቃለህ? ሲደበድበኝ እያየች
አትጠላውም፡፡ አትፈራውም፡፡ እስሩ ገብታ ነው የምትሄደው።አለች ጥልቅ መከፋት ባለው ድምፅ፡፡
ለዓመታት እንዲመለስላት የምትችለውን ስታደርግ ኖራለች።አሁንም ድረስ።ከእርሱ ጋር የነበራትን ህይወት ከመመለስ ውጪ ሌላ አማራጭ አታስብም።
"ዛሬ ወደ ቤት የምትመለሺበት ምክንያት የለሽም።አብረን እንዋል!! ማታ እራት ልጋብዝሽ!" አልኳት ካለችበት ድብርት
እንድትወጣ፡፡ አልመለሰችልኝም፡፡ ቀና ብላ እያየችኝ "የእናትህን ጉዳይ ዛሬ እንድናጣራ አስቤ ነበር፡፡" አለችኝ ድምፅዋ ውስጥ ደስ የማይል ጥርጣሬ አደመጥኩ። አመነታሁ። ለማወቅ ጉጉት
አድሮብኛል። ለዛሬ ግን ከዚህ በላይ አሳዛኝ ነገር ለመስማት ዝግጁ አልነበርኩም።
"ነገ እናድርገው።ነገ ጠዋት። አሁን ምንም መስማት አልፈልግም። አሁን ስትስቂ ማየት ብቻ ነው የምፈልገው::"
አልኳት:: በምንቸገረኝ ትከሻዋን ሰበቀች። የገጠማትን ረስታ ከኔጋር መሆኗን ብቻ እንድታጣጥም ስጣጣር ዋልኩኝ። ቁርስ
ሰርቼ አበላኋት:: ተመልሰን ተኛን። ማታ ስላልተኛሁ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ስነቃ አጠገቤ ሳጣት ጮኬ ተጣራሁ።ምሳ እየሰራች ነበር፡፡ ገብቷታል:ፈ። ሆዷን ይዛ ሳቀችብኝ፡፡ መቃም እንደምፈልግ
ስነግራት ቡና እንደምታፈላልኝ ነገረችኝ፡፡ በየመሃሉ ጭልጥ ትልብኛለች።ሊመሻሽ ገደማ ወጥተን ቀሚስ እና ጫማ
ገዛሁላት፡፡ ለእራት ልንወጣ ቀሚሷን ላብሳ ተኳኩላ ብቅ አለች።ዝም አልኳት።
"አላማረብኝም? እ?" አለችኝ፡፡
"ምንም ተጨማሪ ነገር ሳትጠቀሚ እኮ ውብ ነሽ!" መለስኩላት።
እሱ ግን ሳልኳኳል አስጠላዋለሁ።" አለችኝ ከንፈሯን ወደ አንድ ጎን አጣማ (ቁሌታም ሴት ይወዳል ብላኝ ነበር ጠዋት ስታወራኝ። የወሲብ ፊልሞች ላይ እንደሚታዩት ሴቶች እንድትለብስለት እና የእነርሱን እንቅስቃሴ እንድትኮርጅለት
( እንደሚያደርጋት አክላልኝ ነበር፡፡)
"አሁን ለእኔ ብለሽ ነው የተቀባሽው? ለእኔ ብለሽ ከሆነ አጥፊው
ምክንያቱም እንደዛ ቆንጅዬ ነሽ! ለራስሽ ብለሽ ካደረግሽው ተይው::" ስላት አመነታች፡፡ ከዛም አጠፋችው።
እራት እየበላን እሷ ወይን እኔ ቢራ እየጠጣን እንዲህ ከወጣች
ዓመታት መቆጠራቸውን ከእንባዋ እየታገለች ነገረችኝ። ሁለት ብርጭቆ እንደጠጣች ሞቅ አላት።
"ታውቃለህ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም። ትክክል መሆኑንም እንጃ!" አለችኝ እቤት እንደገባን፡፡
"ምኑ?"
"የሚሰማኝ ስሜት"
"ምንድነው የሚሰማሽ?" ከአፏ የሚወጣው ዓረፍተ ነገር ምንም ቢሆን እኔ ጆሮጋ ሲደርስ “ላንተ ፍቅር የሚል ቢሆን እየተመኘሁ።
“በደለኝነት፣ ኀጢአተኝነት፣ ጥፋተኝነት፣ ከዳተኝነት፣ ክምር ወቀሳ!” ጭንቅላቷን ይዛ ጫማዋን እያንቋቋች ተረማመደች።
ልቤን ሲበርደው ታወቀኝ፡፡
“ለምን? በምን ምክንያት?” የራሴ የማይመስል ድምፅ ነው ያወጣሁት፡፡ እግሬም የዛለብኝ መሰለኝ እና ተቀመጥኩ።
"ታውቃለህ? ድሮ ድሮ የዛሬ ስምንት ዓመት በድብቅ ፍቅር እንደጀመርን አንድ ቀን ከሰፈር አርቆ ይዞኝ ሄደ፡፡ ሁለታችንም
ህይወት እንደምናያቸው የፍቅር ፊልሞች መጨረሻቸው ግጥምጥም ግጥምጥም ብሎ በደስታ ለዘለዓለም ኖሩ የሚሆን
የሚመስለን ወቅት ነበር፡፡ (የወቅቱን ስሜት በትዝታ ልጓም ጎትታ እንደመቦረቅ እያለች) የሆነ ህንድ ፊልም ላይ እንዳየው
የእኔንም የሱንም የግራ እጅ የቀለበት ጣታችንን ጫፍ በምላጭ ቆርጠን አደማነው።ያስቃል አይደል? የሆነ የጅል ቀልድ ነገር ይመስላል? ግን አያስቅም እሺ! የሁለታችንንም የደሙ ጣቶች
አጋጥመን ቃል ገባልኝ፡፡ ቃል ገባሁለት።እሱ የገባልኝን ቃል
የኖረው ሁለት ዓመታት ብቻ ነው:: እኔ እያንዳንዷ ቃሌን ለመጠበቅ ስምንት ዓመታቴ ተቀርጥፈው ተስሉ፡፡ ለሱ ብዬ
ሁሉንም ተውኩ፡፡ ለማንም ወንድ ልቤንም አካሌንም አስደፍሬ
አላውቅም። እስከ ህይወቴ ፍፃሜ በልቤ ከርሱ ሌላ ላይነግስ ምዬለታለኋ? ምን እንደሚሰማኝ ታውቃለህ? ደሙ በደሜ
ውስጥ ያለ (ትኩረቴን ላለማጣቷ እያረጋገጠች) እውነታው
ባይገጣጠምም እኔ ግን እዛው የዛሬ ስምንት ዓመት ላይ ነኝ።"ማውራቷን አቋርጣ ማልቀስ ጀመረች።ሞቅታውም እያገዛት መሆኑ ገብቶኛል።
"ታውቃለህ አይገባህም! እኔን ስትሆን ብቻ ነው የሚገባህ!" አለችኝ፡፡ ፀጥ ብዬ እየሰማኋት ሀሳቤን ከማቡካት ውጪ ምርጫ አልሰጠችኝም።እውነቷን ነው:: አንዳንዴ ከምክንያታዊነት የሚልቅ ስሜት እንዳለ አሰብኩ። በቦታው ስትገኝ ብቻ የሚገባህ! ሲስማህ ብቻ የምታውቀው። እሷ ዓለሟ ትዳሯ ነው። ዓለም ቤቷ ነው። ዓለሟ ልጇ ናት:: ዓለምን እንደማሸነፍ የላቀ ምን ሀሴት አለ? ምንስ ስኬት ይኖራል? ትዳሯን እንደገና ማሸነፍ
እንደገና በሱ ልብ መንገስ፣ ለልጇ የምትወደውን አባቷን መመለስ፣ ዓለሟን የራሷ ማድረግ ነው ምኞትና ልፋቷ!
ሲመስለኝ ያልተረዳችው ነገር አብዛኛው ወንድ ወደድኩሽ ሲል ሊያስመስል ይችላል፡፡ ጠላሁሽ ካለ በቃ ማለቱ እንደሆነ አልገባትም። አርሴማን ሊወስድ ሲመጣ እግረ መንገዱን አብሯት መተኛቱ ከፍቅር ጋር ተዳቅሎባታል። የነሳትን ክብር ጋርዶባታል ፍቅሩን ያልጨረሰ እየመሰላት ልትጨምርለት ትዳክራለች።
“አንዳንዴ እንዲጠላኝ ያደረገው ፖሊስ መሆኔ ነው ብዬ አስብና ራሴን እወቅሳለሁ፡፡ ምናለ እሱ እንደሚፈልገው የቤት እመቤት ብሆን? እላለሁ! ልጄ በየቀኑ የምታየው አባት ይኖራት ነበር::"
ለንፅፅር የምታቀርበው ነገር ሲኖርህ ነው የተሻለ እና የባስ ብለህ ደረጃ የምታወጣው። እሷ ከእርሱ ውጪ የምታውቀው የላትም፡፡በምን ንፅፅር የምትለውጠው ህይወት የተሻለ መሆኑን
ትመዝናለች?
"ታውቃለህ አንዳንዴ እርግፍ አድርጌ ትቼው ቤተሰቦቼን ሄጄ ይቅርታ ልለምናቸው አስቤ አውቃለሁ፡፡ ያሳፍራል አይደል? እሉ ይበልጥብኛል ባልከው ሰው ተክደህ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
መሆናቸውን ብታውቅም እስከመጨረሻው ይከፉብኛል ብላ
አላሰበችም ነበርና በጊዜው ላፈቀረችው ሰው ቤተሰቧን ማጣቷ የሚገባው የመሰላት መስዋዕትነት ነበር። ሁሉም ሰላም እና ውብ ነበር። እየቆየ የባሏ ባህሪ መቀየር ጀመረ:: እሷ መርማሪ ፖሊስ
መሆኗን ተከትሎ ቤቷ ብጥብጥ ወረሰው።ዘግይቶ ሲገባት በብዙ
ህገወጥ ንግዶች ላይ እጁ እንዳለበት ጠረጠረች፡፡ ቢሆንም በቂ መረጃ የላትም
ቢሆንም ታፈቅረዋለች፡፡ቢሆንም ካለ እርሱ አንካሳ ናትና በየእለቱ እንደምትበረታባቸው ወንጀለኞች መረጃ
ለማግኘት አልታተረችም።በዚህ ትርምስ ውስጥ አርሴማ መጣች፡፡በመጀመሪያ የአርሴማ መወለድ ነገሮችን ያበረደ
መሰለ። ውጪ ማደሩን ተወ። መደብደቡን አቆመ።ድጋሚ የምታልመው ጥሩ ትዳር ኖራት። አርሴማ እያደገች ጤነኛ
አለመሆኗን ሲያውቅ ከበፊቱ በባሰ ከፋ፡፡
"እሺ እኔ ምን ማድረግ ነበረብኝ? እኔ እግዚአብሄር ነኝ? ልጄ ጤነኛ ብትሆን እኔስ ደስተኛ አልነበርኩም? ምን ማድረግ እችል ነበር?" አለችኝ ቀና ብላ፡፡
አርሴማ ከፍ ስትል ጭራሽ ከቤቱም ወጣ፡፡ በሁለት ሳምንት አንዴ (ትናንት እንዳደረገው) አርብ ከሰዓት መጥቶ አርሴማን ቤተሰቦቹጋ ይዟት ይሄዳል። ለልጁ የሚያስፈልገውን እሱም ሆነ
ቤተሰቡ ከማድረግ ቦዝነው አያውቁም፡፡ እሷን ከወንድ ጋር ታየሽ፣ ለልጄ መልካም አርአያ እየሆንሽ አይደለም እያለ
መቆጣጠሩን አለፍ ሲልም ትላንት እንዳደረገው መደብደቡን ቀጠለ። ምንም ማድረግ እንዳትችል አርሴማ አበሰረቻት። አርሴማ አባቷን ስታይ ፈንጠዝያ የሚቀሙት አይደለም። እሱ ሄዶ
ከትምህርት ቤት ያመጣት ቀን ስትጫወት ታመሻለች።
ልጄ ጤነኛ ብትሆን እና እንደ ጤነኛ ልጅ በሌላ የምትደሰት ብትሆን እሺ!
እንዴት አንድ የሳቋን ምክንያት
አሁንም ድረስ፡፡ ከእርሱ ጋር የነበራትን ህይወት ከመመለስ ልንጠቃት? ታውቃለህ? ሲደበድበኝ እያየች
አትጠላውም፡፡ አትፈራውም፡፡ እስሩ ገብታ ነው የምትሄደው።አለች ጥልቅ መከፋት ባለው ድምፅ፡፡
ለዓመታት እንዲመለስላት የምትችለውን ስታደርግ ኖራለች።አሁንም ድረስ።ከእርሱ ጋር የነበራትን ህይወት ከመመለስ ውጪ ሌላ አማራጭ አታስብም።
"ዛሬ ወደ ቤት የምትመለሺበት ምክንያት የለሽም።አብረን እንዋል!! ማታ እራት ልጋብዝሽ!" አልኳት ካለችበት ድብርት
እንድትወጣ፡፡ አልመለሰችልኝም፡፡ ቀና ብላ እያየችኝ "የእናትህን ጉዳይ ዛሬ እንድናጣራ አስቤ ነበር፡፡" አለችኝ ድምፅዋ ውስጥ ደስ የማይል ጥርጣሬ አደመጥኩ። አመነታሁ። ለማወቅ ጉጉት
አድሮብኛል። ለዛሬ ግን ከዚህ በላይ አሳዛኝ ነገር ለመስማት ዝግጁ አልነበርኩም።
"ነገ እናድርገው።ነገ ጠዋት። አሁን ምንም መስማት አልፈልግም። አሁን ስትስቂ ማየት ብቻ ነው የምፈልገው::"
አልኳት:: በምንቸገረኝ ትከሻዋን ሰበቀች። የገጠማትን ረስታ ከኔጋር መሆኗን ብቻ እንድታጣጥም ስጣጣር ዋልኩኝ። ቁርስ
ሰርቼ አበላኋት:: ተመልሰን ተኛን። ማታ ስላልተኛሁ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ስነቃ አጠገቤ ሳጣት ጮኬ ተጣራሁ።ምሳ እየሰራች ነበር፡፡ ገብቷታል:ፈ። ሆዷን ይዛ ሳቀችብኝ፡፡ መቃም እንደምፈልግ
ስነግራት ቡና እንደምታፈላልኝ ነገረችኝ፡፡ በየመሃሉ ጭልጥ ትልብኛለች።ሊመሻሽ ገደማ ወጥተን ቀሚስ እና ጫማ
ገዛሁላት፡፡ ለእራት ልንወጣ ቀሚሷን ላብሳ ተኳኩላ ብቅ አለች።ዝም አልኳት።
"አላማረብኝም? እ?" አለችኝ፡፡
"ምንም ተጨማሪ ነገር ሳትጠቀሚ እኮ ውብ ነሽ!" መለስኩላት።
እሱ ግን ሳልኳኳል አስጠላዋለሁ።" አለችኝ ከንፈሯን ወደ አንድ ጎን አጣማ (ቁሌታም ሴት ይወዳል ብላኝ ነበር ጠዋት ስታወራኝ። የወሲብ ፊልሞች ላይ እንደሚታዩት ሴቶች እንድትለብስለት እና የእነርሱን እንቅስቃሴ እንድትኮርጅለት
( እንደሚያደርጋት አክላልኝ ነበር፡፡)
"አሁን ለእኔ ብለሽ ነው የተቀባሽው? ለእኔ ብለሽ ከሆነ አጥፊው
ምክንያቱም እንደዛ ቆንጅዬ ነሽ! ለራስሽ ብለሽ ካደረግሽው ተይው::" ስላት አመነታች፡፡ ከዛም አጠፋችው።
እራት እየበላን እሷ ወይን እኔ ቢራ እየጠጣን እንዲህ ከወጣች
ዓመታት መቆጠራቸውን ከእንባዋ እየታገለች ነገረችኝ። ሁለት ብርጭቆ እንደጠጣች ሞቅ አላት።
"ታውቃለህ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም። ትክክል መሆኑንም እንጃ!" አለችኝ እቤት እንደገባን፡፡
"ምኑ?"
"የሚሰማኝ ስሜት"
"ምንድነው የሚሰማሽ?" ከአፏ የሚወጣው ዓረፍተ ነገር ምንም ቢሆን እኔ ጆሮጋ ሲደርስ “ላንተ ፍቅር የሚል ቢሆን እየተመኘሁ።
“በደለኝነት፣ ኀጢአተኝነት፣ ጥፋተኝነት፣ ከዳተኝነት፣ ክምር ወቀሳ!” ጭንቅላቷን ይዛ ጫማዋን እያንቋቋች ተረማመደች።
ልቤን ሲበርደው ታወቀኝ፡፡
“ለምን? በምን ምክንያት?” የራሴ የማይመስል ድምፅ ነው ያወጣሁት፡፡ እግሬም የዛለብኝ መሰለኝ እና ተቀመጥኩ።
"ታውቃለህ? ድሮ ድሮ የዛሬ ስምንት ዓመት በድብቅ ፍቅር እንደጀመርን አንድ ቀን ከሰፈር አርቆ ይዞኝ ሄደ፡፡ ሁለታችንም
ህይወት እንደምናያቸው የፍቅር ፊልሞች መጨረሻቸው ግጥምጥም ግጥምጥም ብሎ በደስታ ለዘለዓለም ኖሩ የሚሆን
የሚመስለን ወቅት ነበር፡፡ (የወቅቱን ስሜት በትዝታ ልጓም ጎትታ እንደመቦረቅ እያለች) የሆነ ህንድ ፊልም ላይ እንዳየው
የእኔንም የሱንም የግራ እጅ የቀለበት ጣታችንን ጫፍ በምላጭ ቆርጠን አደማነው።ያስቃል አይደል? የሆነ የጅል ቀልድ ነገር ይመስላል? ግን አያስቅም እሺ! የሁለታችንንም የደሙ ጣቶች
አጋጥመን ቃል ገባልኝ፡፡ ቃል ገባሁለት።እሱ የገባልኝን ቃል
የኖረው ሁለት ዓመታት ብቻ ነው:: እኔ እያንዳንዷ ቃሌን ለመጠበቅ ስምንት ዓመታቴ ተቀርጥፈው ተስሉ፡፡ ለሱ ብዬ
ሁሉንም ተውኩ፡፡ ለማንም ወንድ ልቤንም አካሌንም አስደፍሬ
አላውቅም። እስከ ህይወቴ ፍፃሜ በልቤ ከርሱ ሌላ ላይነግስ ምዬለታለኋ? ምን እንደሚሰማኝ ታውቃለህ? ደሙ በደሜ
ውስጥ ያለ (ትኩረቴን ላለማጣቷ እያረጋገጠች) እውነታው
ባይገጣጠምም እኔ ግን እዛው የዛሬ ስምንት ዓመት ላይ ነኝ።"ማውራቷን አቋርጣ ማልቀስ ጀመረች።ሞቅታውም እያገዛት መሆኑ ገብቶኛል።
"ታውቃለህ አይገባህም! እኔን ስትሆን ብቻ ነው የሚገባህ!" አለችኝ፡፡ ፀጥ ብዬ እየሰማኋት ሀሳቤን ከማቡካት ውጪ ምርጫ አልሰጠችኝም።እውነቷን ነው:: አንዳንዴ ከምክንያታዊነት የሚልቅ ስሜት እንዳለ አሰብኩ። በቦታው ስትገኝ ብቻ የሚገባህ! ሲስማህ ብቻ የምታውቀው። እሷ ዓለሟ ትዳሯ ነው። ዓለም ቤቷ ነው። ዓለሟ ልጇ ናት:: ዓለምን እንደማሸነፍ የላቀ ምን ሀሴት አለ? ምንስ ስኬት ይኖራል? ትዳሯን እንደገና ማሸነፍ
እንደገና በሱ ልብ መንገስ፣ ለልጇ የምትወደውን አባቷን መመለስ፣ ዓለሟን የራሷ ማድረግ ነው ምኞትና ልፋቷ!
ሲመስለኝ ያልተረዳችው ነገር አብዛኛው ወንድ ወደድኩሽ ሲል ሊያስመስል ይችላል፡፡ ጠላሁሽ ካለ በቃ ማለቱ እንደሆነ አልገባትም። አርሴማን ሊወስድ ሲመጣ እግረ መንገዱን አብሯት መተኛቱ ከፍቅር ጋር ተዳቅሎባታል። የነሳትን ክብር ጋርዶባታል ፍቅሩን ያልጨረሰ እየመሰላት ልትጨምርለት ትዳክራለች።
“አንዳንዴ እንዲጠላኝ ያደረገው ፖሊስ መሆኔ ነው ብዬ አስብና ራሴን እወቅሳለሁ፡፡ ምናለ እሱ እንደሚፈልገው የቤት እመቤት ብሆን? እላለሁ! ልጄ በየቀኑ የምታየው አባት ይኖራት ነበር::"
ለንፅፅር የምታቀርበው ነገር ሲኖርህ ነው የተሻለ እና የባስ ብለህ ደረጃ የምታወጣው። እሷ ከእርሱ ውጪ የምታውቀው የላትም፡፡በምን ንፅፅር የምትለውጠው ህይወት የተሻለ መሆኑን
ትመዝናለች?
"ታውቃለህ አንዳንዴ እርግፍ አድርጌ ትቼው ቤተሰቦቼን ሄጄ ይቅርታ ልለምናቸው አስቤ አውቃለሁ፡፡ ያሳፍራል አይደል? እሉ ይበልጥብኛል ባልከው ሰው ተክደህ
👍2🥰1😁1
በሚያነክስ ልብ
መመለስ? ለነገሩ አሁን እረፍዷል፡፡ ስምንት ዓመት ዘግይቻለሁ።ግን ምን የሚሉኝ ይመስልሃል? ዘመድ አዝማድ እየተጠቋቆመ ቅስሜን የሚያደቀው አይመስልህም?" እሷ ታወራለች እኔ
የምሰማውን ላጣጥም በሀሳብ እዛቁላለሁ፡፡
ሰው እንኳን ወድቀህ ተመቻችተህለት ክርስቶስ ሰው ሆኖ ቢመጣ በመኮነን የተቀባበለው ፍጡር ነው:: ምንም የሰራኸው ኀጢኣት ባይኖር በእናትህ በደል አንተን ይፈጅሃል፡፡ ለድርጊት
ፈሪ የሆኑ ሰዎች ማድረግ የሚችሉት የሰውን ውድቀትና ጥፋት መንቀስ ብቻ ነዋ፡፡ ስምሪት ሰው የራሱ ጉዳይ የማለት አቅም ያላት ሴት እንዳይደለች አውቃለሁ፡፡ ቤተሰቦቿን በተመለከተ
አንድ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ ጊዜው በትክክል
መቼ መሆኑን ባላውቅም።በሞቅታ ስለምታወራ ከመስማት ውጪ አፌን አላላቀኩም...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
መመለስ? ለነገሩ አሁን እረፍዷል፡፡ ስምንት ዓመት ዘግይቻለሁ።ግን ምን የሚሉኝ ይመስልሃል? ዘመድ አዝማድ እየተጠቋቆመ ቅስሜን የሚያደቀው አይመስልህም?" እሷ ታወራለች እኔ
የምሰማውን ላጣጥም በሀሳብ እዛቁላለሁ፡፡
ሰው እንኳን ወድቀህ ተመቻችተህለት ክርስቶስ ሰው ሆኖ ቢመጣ በመኮነን የተቀባበለው ፍጡር ነው:: ምንም የሰራኸው ኀጢኣት ባይኖር በእናትህ በደል አንተን ይፈጅሃል፡፡ ለድርጊት
ፈሪ የሆኑ ሰዎች ማድረግ የሚችሉት የሰውን ውድቀትና ጥፋት መንቀስ ብቻ ነዋ፡፡ ስምሪት ሰው የራሱ ጉዳይ የማለት አቅም ያላት ሴት እንዳይደለች አውቃለሁ፡፡ ቤተሰቦቿን በተመለከተ
አንድ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ ጊዜው በትክክል
መቼ መሆኑን ባላውቅም።በሞቅታ ስለምታወራ ከመስማት ውጪ አፌን አላላቀኩም...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#በእቅፍሽ_ውስጥ_ያለው_ሰላም
በደጃፌ
ያዱኛ ጅረት ይፈስሳል
ሲዘረጋ መዳፌ
አልማዝ አፍሶ ይመለሳል።
ድህነትን አልቀድስም፣ ሀብታም መሆን አልጠላም
ግና ገንዘብ ኪስን እንጂ፣ የልብን ክፍተት አይሞላም
ከሁሉም ግን የሚልቀው፣ እቅፍሽ ውስጥ ያለው ሰላም።
በጉልምስና ዘመኔ፣ ወደ ልጅነት ተዛውሬ
የወይን ፅዋየን ወርውሬ
እልፍ ጡቶችን ብጠባ
ካንዲት ሽንቁር ተመዝዤ፣ ሌላይቱ ውስጥ ብገባ
ብለዋውጥ ማህደር
ብቀያይር ሰገባ
ምን አገኘሁ? ምን አተረፍሁ? ምን ፈየድኩኝ? ምኔ ረባ?
ሥጋ በሥጋ ቢሞረድ፣ የደነዘ ነፍስ አይሰላም
ከሁሉም ግን የሚልቀው፣ እቅፍሽ ውስጥ ያለው ሰላም።
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
በደጃፌ
ያዱኛ ጅረት ይፈስሳል
ሲዘረጋ መዳፌ
አልማዝ አፍሶ ይመለሳል።
ድህነትን አልቀድስም፣ ሀብታም መሆን አልጠላም
ግና ገንዘብ ኪስን እንጂ፣ የልብን ክፍተት አይሞላም
ከሁሉም ግን የሚልቀው፣ እቅፍሽ ውስጥ ያለው ሰላም።
በጉልምስና ዘመኔ፣ ወደ ልጅነት ተዛውሬ
የወይን ፅዋየን ወርውሬ
እልፍ ጡቶችን ብጠባ
ካንዲት ሽንቁር ተመዝዤ፣ ሌላይቱ ውስጥ ብገባ
ብለዋውጥ ማህደር
ብቀያይር ሰገባ
ምን አገኘሁ? ምን አተረፍሁ? ምን ፈየድኩኝ? ምኔ ረባ?
ሥጋ በሥጋ ቢሞረድ፣ የደነዘ ነፍስ አይሰላም
ከሁሉም ግን የሚልቀው፣ እቅፍሽ ውስጥ ያለው ሰላም።
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
👍2
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
አንድ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ ጊዜው በትክክል
መቼ መሆኑን ባላውቅም። በሞቅታ ስለምታወራ ከመስማት ውጪ አፌን አላላቀኩም።
"ታውቃለህ ለሷ ብለህ ምንም ለመስዋት የተዘጋጀህላት ህፃን ልጅህ ምርጫ ቢሰጣት እሱን እንደምትመርጥ ማወቅ
የሚጠዘጥዝ ቁስል ስሜት እንደሚሰጥ? አታውቅም!! ህፃን ናት በሷ እኮ አልፈርድም፡፡ የሚሰማኝን ፍርሃትና ህመም ግን ልታውቀው አትችልም። ስታድግ አባቷን መርጣ ብትሄድስ? ለእርሷ ብዬ የከፈልኩላት ሁሉ ባይገባትስ? አባቷን ስላሳጣኋት ብትወቅሰኝስ? ለነገሩ አንተ የምትሳሳለት ሰው ኖሮህ አያውቅም::" አለችኝ።
ኖሮኝ አያውቅም፡፡ እስከገባኝ ድረስ በአንዲት ክስተት ስለእርሷ
የተገለጠልኝ ስስት ግን የሶስት ዓመት ጥርቅም እንጂ የዛች ቅፅበት ብቻ አልነበረም። ሶስት ዓመት ሙሉ በእያንደንዷ የስራ ቀን የቀኑን መንጋት ያህል ስምሪት የተለመደ ክስተቴ ነበረች፡፡
ቡና አብሪያት ስጠጣ፣ ስትናደድ ጉንጫ ሲቀላ ደስ ስለሚለኝ ሳበሳጫት፣ ለማንም የማላወራውን ስሜቴን ሳወራት፣ እሷ
እንደማውቃቸው ሴቶች አልነበረችም:: አሁን ያን ላስረዳት አልሞከርኩም፡፡ ከብዙ ወሬዋ እና ከ'ታውቃለህ? አታውቅም!በኋላ አልጋው ላይ ተጋድማ ማውራቷን ቀጠለች፡፡ እያወራች እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡ አልቀሰቀስኳትም አጠገቧ ተጋደምኩ።
"እናትህ ማገገሚያ ነው ያሉት::" አለችኝ ጠዋት ቀድማኝ ተነስታ ያበሰለችውን ቁርስ እየበላን፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ቀጥላ
በምትጠቀማቸው ሱሶች ምክንያት መግባቷን አከለችልኝ።ደነገጥኩ? አዘንኩ? ላያት እፈልጋለሁ? ስሜቴ ድብልቅልቅ አለ፡፡
ከስምሪት ጋር ከነጋ ከተወሰኑ ቃላት በላይ አልተነጋገርንም። ልቤን ከብዶኛል፡፡ ምንም የማውራት ፍላጎት የለኝም።ብዙ ዝም ካልኩ በኋላ የረባ ቃላት ሳንለዋወጥ ያለዚያ ቀን መኖሩን ወደማላውቀው የግል ማገገሚያ ሆስፒታል ደረስን፡፡ ሳያት ምን እንደምላት አላውቅም። ባታውቀኝስ ? ጭንቅላቷ የተቃወሰ
ቢሆንስ? እንደልጅነቴ ዞር በል ብላ ብትሰድበኝስ? ቆምኩ።የተዘጋጀሁ አልመስል አለኝ፡፡ ስምሪት ገብቷታል፡፡ እየደጋገመች እጄን ትጨምቀኛለች፡፡ እሷም ተጨንቃለች፡፡ አልጋው ላይ
ተጋድማ ሳያት ልጨብጣት? ልቀፋት? ፈገግ ልበል? ላልቅስ?የትኛው ላለሁበት ቦታና ስሜት እንደሚመጥን አላወቅኩትም።ስታየኝ ከአልጋዋ ወርዳ ማምለጥ ብትችል ፈልጋ ነበር፡፡
የለበሰችው ስስ የአልጋ ልብስ ውስጥ ተሸጎጠች፡፡ ስምሪት ቀድማ ሄዳ አቀፈቻት፡፡ ምንም ሳልናገር አጠገቧ ሄጄ ተቀመጥኩ፡፡ሳላገኛት በፊት ብዙ ጥያቄዎች ብትመልስልኝ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ከእድሜዋ በላይ አርጅታለች። ሰውነቷ ተጎሳቁሏል፡፡ ማለት የቻልኩት ዝም ብቻ ነው።
"ትልቅ ሰው ሆነሃል!" አለችኝ ፊቷን ከኔ አዙራ:: እያለቀሰች እንደሆነ አውቃለሁ። ላባብላት እፈልጋለሁ ግን አላደርገውም። ሳላስበው እጇን ያዝኳት። መልሼ ወዲያውኑ ለቀቅኳት፡፡
የቱንም ያህል ብትጠላኝ አልፈርድብህም። ይገባሃል::" አለችኝ
ፊቷን ደብቃኝ፡፡
“አልጠላሽም:: ባታወሪኝ እንኳን ትንሽ ደቂቃ አጠገብሽ ልሁን፡፡"አልኳት:: ድምፅ አውጥታ እያለቀሰች ፊቷን ወደእኔ መለሰች።ስምሪት አብራት ታነባለች፡፡ የማደርገው ጠፋኝ፡፡
“እያስጨነቅሽኝ ነው። እባክሽ አታልቅሺ፡፡” አልኳት አቅፌ ባባብላት ደስ ይለኛል። የሚሰማኝ ግን እሩቅነት ነው፡፡ እጄን ሰድጄ መለስኩት።በዝምታ ብዙ ካወራን በኋላ ተነሳሁ።
"መጥቼ አይሻለሁ::" አልኳት። ብርግግ ብላ ተቀመጠች፡፡ አንድ እርምጃ ጀርባዬን ሰጥቻት እንደተራመድኩ።
"ባቢሾ?" ብላ ጠራችኝ፡፡ የቤት ስሜ ነበር፡፡ አጠራሯ የፈለገችው ነገር ኖሮ ልትጠይቀኝ የፈራች ይመስላል። ምን ቸግሯት ይሆን ብዬ እያሰብኩ ተጠግቻት "ምነው?" አልኳት፡፡
በጣም እያመነታች እያየችኝ እጇን ወደ ፊቴ እያስጠጋች "አንዴ ልንካህ?" ስትለኝ ጭንቅላቴ በከባድ ነገር የተመታ መሰለኝ፡፡ ያ ስሜት ለዘመናት የያዝኩባትን ቂም የማጠብ አቅም ነበረው።ልጇን ለመንካት ያስፈቀደች እናት ህመም የእኔ እናት ህመም ብቻ ነው።ይሄ ስሜቷ ከጥላቻ ዋልታ ወደ ፍቅር አርያም
የማምጠቅ ምትሃት ነበረው። የዘረጋቻቸውን እጆቿን ሳምኩላት። እናትነት እንዲሰማት ማድረግ ተመኘሁ።
"ልጅሽ እኮ ነኝ! ብትቆነጥጪኝ እንኳን በኔ ላይ ስልጣን አለሽ!” አልኳት በእጁ አንገቴን ፀጉሬን ፊቴን ደባብሳኝ ስታበቃ በቀስታ እጇን ሰበሰበች። ከሆስፒታሉ እንደወጣሁ ብቻዬን መሆን ፈለግኩ፡፡ ስምሪትን ተሰናብቻት ማሰብ እስካቆም ጠጣሁ።በሚቀጥሉትን ቀናት የተለመደው ዓይነት ህይወት ቀጠልኩ።
አዲስ ነገር እናቴን እየሄድኩ አያታለሁ። አንዳንዴ ከስምሪት ጋር እንሄዳለን፡፡ ስላለፈው አናነሳም፡፡ ልጠይቃት የምፈልገው ብዙ ጥያቄ ቢኖርም አጠገቧ ስሆን ዝም ማለትን እመርጣለሁ።
ከስምሪት ጋር ልክ እንደበፊቱ ሆንን፡፡ ምንም እንዳልተፈጠረ፣ሳያት ምንም እንደማይሰማኝ፣ ስታረፍድ እንደማልንቆራጠጥ፡፡
አንድ ቀን ባሏ ሲመጣ ሳትኳኳል እንደጠበቀችው እና አስጠሊታ
መሆኗን ነግሯት ልጁን ይዞ እንደሄደ ነገረችኝ፡፡
በተደጋጋሚ ይሄን በማድረጓ አብረው መተኛት ማቆማቸውን ነገረችኝ፡፡ ከሳምንታት በኋላ እናቴ ከሱሷ ከማገገሟ በባሰ በጉበት በሽታ እየተሰቃየች ስለነበር ለከፍተኛ ህክምና ወደ ሌላ ሆስፒታል ተዛወረች።መታመሟን ስታውቅ ዘመዶቿጋ ስልክ ደወለች። እስከዛሬ መኖራቸውን እንኳን አስቤ ከማላውቃቸው
ቤተሰቦቼጋ ለመግባባት መሞከር ያልተለመደ ደባሪ ነገር አለው፡፡
የወንድ አያቴን፣ አጎቴንና አክስቴን ተራ በተራ እየመጡ ሲከርሙ ተዋወቅኳቸው። አክስቴ እዚሁ አዲስ አበባ መኖሯን
ማወቄ ገረመኝ፡፡ እንዴት አይጠያየቁም? አጎቴና አያቴ ከክፍለሃገር ነበር የመጡት: የገባኝ ነገር እናቴ ከቤተሰቦቿም ጋር ቢሆን የጠበቀ ግንኙነት ያላት አይመስለኝም:: ልጅ እንዳላት
እንኳን ያወቁኝ አሁን ነው። አልተገረምኩም እንኳን እነርሱ
አብሬያት ኖሬ የማውቀው ልጇ እንኳን ብዙ የማይፈታ እንቆቅልሽ እንዳላት አውቃለሁ፡፡
“አባትህ የምሰራበት የነበረ ሆቴል ያረፈ ቱሪስት ነበር። በጣም ጥሩ ሰው ነው። ፈረንሳዊ ነው:: የምትኖርበትን ቤት የገዛልኝ እሱ ነው።ሀገሩ ሚስትና ልጆች ስለነበሩት ተመልሶ ወደ ሀገሩ
ሄደ፡፡ አድራሻውን አላውቅም፡፡ ልጅ እንዳለው አያውቅም።አንተን ማርገዜን አልነገርኩትም።እሱ ባከበረኝ ልክ ማንም
ወንድ አክብሮኝ አያውቅም።እሱን ነው የምትመስለው::" አለችኝ ብቻዬን ሆስፒታል ያደርኩኝ የሆነ ቀን ማታ። ዝርዝር አድርጋ እንድትነግረኝ ልጠይቃት አስብና ማስታወስ የማትፈልገው
ታሪኳ ከሆነ ብዬ እየፈራሁ እተወዋለሁ። ማወቄ ለእኔ ከሚፈይደው ቁም ነገር ጋር ሳነፃፅረው ማስታወሷ የሚፈጥርባት
ህመም የሚያመዝን እየመሰለኝ አለማወቄን መረጥኩ። ይሄን
የነገረችኝ ጠዋት ለአክስቴና ከእናቴ ስር ለማይጠፋው የነፍስ አባቷ ቀኑን ለቅቄላቸው ወደ ስራ ልገባ እስኪመጡልኝ
እየጠበቅኳቸው ሳለ አንድ መልከ መልካም ወጣት ገራገር የመሰለች ሴት እጅ ጣቶች በጣቶቹ ቆልፎ ሆስፒታል መጣ። እናቴ ስታየው ግራ ተጋባች። የእርሱ ግድ የለሽነት እና የእናቴ
መቁነጥነጥ ሌላ የማላውቀው ታሪክ ክር ጫፍ መሆኑን ነገረኝ። አብራው የነበረችው ገራገር ሴት ወደ እናቴ ተቅለብልባ ሄዳ እየሳመቻት።
"እንዴት ነሽ ወለላ? መታመምሽን አባ ናቸው ትናንት የነገሩን?አሁን ተሻለሽ?" መልስ አትጠብቅም።ወዲያው ወደ ወጣቱ ዘወር ብላ "ና ሳማት እንጂ! ምን እዛጋ ይገትርሃል?" መልስ ሳይሰጣት በተገተረበት መቆሙን አይታ በዓይኗ ማባበልም ቁጣም የቀላቀለው ማጎረጥረጥ ታጉረጠርጣለች፡፡ ወንበር ላይ ያለ ንግግር ተቀመጠ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
አንድ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ይሰማኛል፡፡ ጊዜው በትክክል
መቼ መሆኑን ባላውቅም። በሞቅታ ስለምታወራ ከመስማት ውጪ አፌን አላላቀኩም።
"ታውቃለህ ለሷ ብለህ ምንም ለመስዋት የተዘጋጀህላት ህፃን ልጅህ ምርጫ ቢሰጣት እሱን እንደምትመርጥ ማወቅ
የሚጠዘጥዝ ቁስል ስሜት እንደሚሰጥ? አታውቅም!! ህፃን ናት በሷ እኮ አልፈርድም፡፡ የሚሰማኝን ፍርሃትና ህመም ግን ልታውቀው አትችልም። ስታድግ አባቷን መርጣ ብትሄድስ? ለእርሷ ብዬ የከፈልኩላት ሁሉ ባይገባትስ? አባቷን ስላሳጣኋት ብትወቅሰኝስ? ለነገሩ አንተ የምትሳሳለት ሰው ኖሮህ አያውቅም::" አለችኝ።
ኖሮኝ አያውቅም፡፡ እስከገባኝ ድረስ በአንዲት ክስተት ስለእርሷ
የተገለጠልኝ ስስት ግን የሶስት ዓመት ጥርቅም እንጂ የዛች ቅፅበት ብቻ አልነበረም። ሶስት ዓመት ሙሉ በእያንደንዷ የስራ ቀን የቀኑን መንጋት ያህል ስምሪት የተለመደ ክስተቴ ነበረች፡፡
ቡና አብሪያት ስጠጣ፣ ስትናደድ ጉንጫ ሲቀላ ደስ ስለሚለኝ ሳበሳጫት፣ ለማንም የማላወራውን ስሜቴን ሳወራት፣ እሷ
እንደማውቃቸው ሴቶች አልነበረችም:: አሁን ያን ላስረዳት አልሞከርኩም፡፡ ከብዙ ወሬዋ እና ከ'ታውቃለህ? አታውቅም!በኋላ አልጋው ላይ ተጋድማ ማውራቷን ቀጠለች፡፡ እያወራች እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡ አልቀሰቀስኳትም አጠገቧ ተጋደምኩ።
"እናትህ ማገገሚያ ነው ያሉት::" አለችኝ ጠዋት ቀድማኝ ተነስታ ያበሰለችውን ቁርስ እየበላን፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ቀጥላ
በምትጠቀማቸው ሱሶች ምክንያት መግባቷን አከለችልኝ።ደነገጥኩ? አዘንኩ? ላያት እፈልጋለሁ? ስሜቴ ድብልቅልቅ አለ፡፡
ከስምሪት ጋር ከነጋ ከተወሰኑ ቃላት በላይ አልተነጋገርንም። ልቤን ከብዶኛል፡፡ ምንም የማውራት ፍላጎት የለኝም።ብዙ ዝም ካልኩ በኋላ የረባ ቃላት ሳንለዋወጥ ያለዚያ ቀን መኖሩን ወደማላውቀው የግል ማገገሚያ ሆስፒታል ደረስን፡፡ ሳያት ምን እንደምላት አላውቅም። ባታውቀኝስ ? ጭንቅላቷ የተቃወሰ
ቢሆንስ? እንደልጅነቴ ዞር በል ብላ ብትሰድበኝስ? ቆምኩ።የተዘጋጀሁ አልመስል አለኝ፡፡ ስምሪት ገብቷታል፡፡ እየደጋገመች እጄን ትጨምቀኛለች፡፡ እሷም ተጨንቃለች፡፡ አልጋው ላይ
ተጋድማ ሳያት ልጨብጣት? ልቀፋት? ፈገግ ልበል? ላልቅስ?የትኛው ላለሁበት ቦታና ስሜት እንደሚመጥን አላወቅኩትም።ስታየኝ ከአልጋዋ ወርዳ ማምለጥ ብትችል ፈልጋ ነበር፡፡
የለበሰችው ስስ የአልጋ ልብስ ውስጥ ተሸጎጠች፡፡ ስምሪት ቀድማ ሄዳ አቀፈቻት፡፡ ምንም ሳልናገር አጠገቧ ሄጄ ተቀመጥኩ፡፡ሳላገኛት በፊት ብዙ ጥያቄዎች ብትመልስልኝ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ከእድሜዋ በላይ አርጅታለች። ሰውነቷ ተጎሳቁሏል፡፡ ማለት የቻልኩት ዝም ብቻ ነው።
"ትልቅ ሰው ሆነሃል!" አለችኝ ፊቷን ከኔ አዙራ:: እያለቀሰች እንደሆነ አውቃለሁ። ላባብላት እፈልጋለሁ ግን አላደርገውም። ሳላስበው እጇን ያዝኳት። መልሼ ወዲያውኑ ለቀቅኳት፡፡
የቱንም ያህል ብትጠላኝ አልፈርድብህም። ይገባሃል::" አለችኝ
ፊቷን ደብቃኝ፡፡
“አልጠላሽም:: ባታወሪኝ እንኳን ትንሽ ደቂቃ አጠገብሽ ልሁን፡፡"አልኳት:: ድምፅ አውጥታ እያለቀሰች ፊቷን ወደእኔ መለሰች።ስምሪት አብራት ታነባለች፡፡ የማደርገው ጠፋኝ፡፡
“እያስጨነቅሽኝ ነው። እባክሽ አታልቅሺ፡፡” አልኳት አቅፌ ባባብላት ደስ ይለኛል። የሚሰማኝ ግን እሩቅነት ነው፡፡ እጄን ሰድጄ መለስኩት።በዝምታ ብዙ ካወራን በኋላ ተነሳሁ።
"መጥቼ አይሻለሁ::" አልኳት። ብርግግ ብላ ተቀመጠች፡፡ አንድ እርምጃ ጀርባዬን ሰጥቻት እንደተራመድኩ።
"ባቢሾ?" ብላ ጠራችኝ፡፡ የቤት ስሜ ነበር፡፡ አጠራሯ የፈለገችው ነገር ኖሮ ልትጠይቀኝ የፈራች ይመስላል። ምን ቸግሯት ይሆን ብዬ እያሰብኩ ተጠግቻት "ምነው?" አልኳት፡፡
በጣም እያመነታች እያየችኝ እጇን ወደ ፊቴ እያስጠጋች "አንዴ ልንካህ?" ስትለኝ ጭንቅላቴ በከባድ ነገር የተመታ መሰለኝ፡፡ ያ ስሜት ለዘመናት የያዝኩባትን ቂም የማጠብ አቅም ነበረው።ልጇን ለመንካት ያስፈቀደች እናት ህመም የእኔ እናት ህመም ብቻ ነው።ይሄ ስሜቷ ከጥላቻ ዋልታ ወደ ፍቅር አርያም
የማምጠቅ ምትሃት ነበረው። የዘረጋቻቸውን እጆቿን ሳምኩላት። እናትነት እንዲሰማት ማድረግ ተመኘሁ።
"ልጅሽ እኮ ነኝ! ብትቆነጥጪኝ እንኳን በኔ ላይ ስልጣን አለሽ!” አልኳት በእጁ አንገቴን ፀጉሬን ፊቴን ደባብሳኝ ስታበቃ በቀስታ እጇን ሰበሰበች። ከሆስፒታሉ እንደወጣሁ ብቻዬን መሆን ፈለግኩ፡፡ ስምሪትን ተሰናብቻት ማሰብ እስካቆም ጠጣሁ።በሚቀጥሉትን ቀናት የተለመደው ዓይነት ህይወት ቀጠልኩ።
አዲስ ነገር እናቴን እየሄድኩ አያታለሁ። አንዳንዴ ከስምሪት ጋር እንሄዳለን፡፡ ስላለፈው አናነሳም፡፡ ልጠይቃት የምፈልገው ብዙ ጥያቄ ቢኖርም አጠገቧ ስሆን ዝም ማለትን እመርጣለሁ።
ከስምሪት ጋር ልክ እንደበፊቱ ሆንን፡፡ ምንም እንዳልተፈጠረ፣ሳያት ምንም እንደማይሰማኝ፣ ስታረፍድ እንደማልንቆራጠጥ፡፡
አንድ ቀን ባሏ ሲመጣ ሳትኳኳል እንደጠበቀችው እና አስጠሊታ
መሆኗን ነግሯት ልጁን ይዞ እንደሄደ ነገረችኝ፡፡
በተደጋጋሚ ይሄን በማድረጓ አብረው መተኛት ማቆማቸውን ነገረችኝ፡፡ ከሳምንታት በኋላ እናቴ ከሱሷ ከማገገሟ በባሰ በጉበት በሽታ እየተሰቃየች ስለነበር ለከፍተኛ ህክምና ወደ ሌላ ሆስፒታል ተዛወረች።መታመሟን ስታውቅ ዘመዶቿጋ ስልክ ደወለች። እስከዛሬ መኖራቸውን እንኳን አስቤ ከማላውቃቸው
ቤተሰቦቼጋ ለመግባባት መሞከር ያልተለመደ ደባሪ ነገር አለው፡፡
የወንድ አያቴን፣ አጎቴንና አክስቴን ተራ በተራ እየመጡ ሲከርሙ ተዋወቅኳቸው። አክስቴ እዚሁ አዲስ አበባ መኖሯን
ማወቄ ገረመኝ፡፡ እንዴት አይጠያየቁም? አጎቴና አያቴ ከክፍለሃገር ነበር የመጡት: የገባኝ ነገር እናቴ ከቤተሰቦቿም ጋር ቢሆን የጠበቀ ግንኙነት ያላት አይመስለኝም:: ልጅ እንዳላት
እንኳን ያወቁኝ አሁን ነው። አልተገረምኩም እንኳን እነርሱ
አብሬያት ኖሬ የማውቀው ልጇ እንኳን ብዙ የማይፈታ እንቆቅልሽ እንዳላት አውቃለሁ፡፡
“አባትህ የምሰራበት የነበረ ሆቴል ያረፈ ቱሪስት ነበር። በጣም ጥሩ ሰው ነው። ፈረንሳዊ ነው:: የምትኖርበትን ቤት የገዛልኝ እሱ ነው።ሀገሩ ሚስትና ልጆች ስለነበሩት ተመልሶ ወደ ሀገሩ
ሄደ፡፡ አድራሻውን አላውቅም፡፡ ልጅ እንዳለው አያውቅም።አንተን ማርገዜን አልነገርኩትም።እሱ ባከበረኝ ልክ ማንም
ወንድ አክብሮኝ አያውቅም።እሱን ነው የምትመስለው::" አለችኝ ብቻዬን ሆስፒታል ያደርኩኝ የሆነ ቀን ማታ። ዝርዝር አድርጋ እንድትነግረኝ ልጠይቃት አስብና ማስታወስ የማትፈልገው
ታሪኳ ከሆነ ብዬ እየፈራሁ እተወዋለሁ። ማወቄ ለእኔ ከሚፈይደው ቁም ነገር ጋር ሳነፃፅረው ማስታወሷ የሚፈጥርባት
ህመም የሚያመዝን እየመሰለኝ አለማወቄን መረጥኩ። ይሄን
የነገረችኝ ጠዋት ለአክስቴና ከእናቴ ስር ለማይጠፋው የነፍስ አባቷ ቀኑን ለቅቄላቸው ወደ ስራ ልገባ እስኪመጡልኝ
እየጠበቅኳቸው ሳለ አንድ መልከ መልካም ወጣት ገራገር የመሰለች ሴት እጅ ጣቶች በጣቶቹ ቆልፎ ሆስፒታል መጣ። እናቴ ስታየው ግራ ተጋባች። የእርሱ ግድ የለሽነት እና የእናቴ
መቁነጥነጥ ሌላ የማላውቀው ታሪክ ክር ጫፍ መሆኑን ነገረኝ። አብራው የነበረችው ገራገር ሴት ወደ እናቴ ተቅለብልባ ሄዳ እየሳመቻት።
"እንዴት ነሽ ወለላ? መታመምሽን አባ ናቸው ትናንት የነገሩን?አሁን ተሻለሽ?" መልስ አትጠብቅም።ወዲያው ወደ ወጣቱ ዘወር ብላ "ና ሳማት እንጂ! ምን እዛጋ ይገትርሃል?" መልስ ሳይሰጣት በተገተረበት መቆሙን አይታ በዓይኗ ማባበልም ቁጣም የቀላቀለው ማጎረጥረጥ ታጉረጠርጣለች፡፡ ወንበር ላይ ያለ ንግግር ተቀመጠ፡፡
👍4❤1
ወለላን እንደሚጠላት ያስታውቅበታል።
መፋጠጣቸው ግራ ያጋባኝ እኔ ራሴን አስተዋወቅኳቸው።
"ኪሩቤል እባላለሁ። የወለላ ልጅ ነኝ።" ከአፌ የወጣው ቃል እነሱ ጆሮ ጋር ሲደርስ ሌላ የሚያስደነግጥ ነገር እስኪመስለኝ ሁለቱም ደርቀው
እናቴ ምንም የወሬው አካል
እንዳልሆነች ሁላ ኮርኒሱ ላይ አፈጠጠች፡፡ ልጅቷ "ልጅ? ልጅ
ልጅ? ማለቴ የወለደችህ? ሲገርም::" እያለች ተራ በተራ ታየናለች። እንደመቅበጥበጥ ሲያደርጋት ከእድሜዋ በታች ህፃን ትመስላለች፡፡
"አዎን ልጂ ነኝ ምነው?" አልኳት።
"እሱ ወንድምህ ነው። ስህተት ይባላል፡፡ ማለቴ የወለላ ልጅ ነው።እኔ ረድኤት እባላለሁ:: ፍቅረኛዬ ነው::" ብላኝ ብዙ ጊዜ እንደምታውቀኝ ተንደርድራ አቀፈችኝ፡፡ ምን ማሰብ እንደነበረብኝ
ግራ ገባኝ:: በደመ-ነፍስ ጨበጥኩት። ስሙ ገርሞኛል።
እውነት ነው? ወንድሜ ነው?" አልኳት እናቴን፡፡ ምንም የገረመው የማይመስለውን ወንድሜን እያየሁት። አረጋገጠችልኝ፡፡ ለደቂቃዎች ዝም አልኩኝ፡፡ ማድረግ የፈለግኩት
እርሷን መውቀስ ነበር ወንድም እንዳለኝ ለምን እንደደበቀችኝ ግን አላደረኩትም።ሀያ ሁለት ዓመቱ ነው በስምንት ዓመቴ ጥላኝ የሄደች ጊዜ ሌላ ቤት መስርታ እንደ ነበር የእድሜው
ቁጥር ነገረኝ፡፡ ለወንድሜም ጥሩ እናት እንዳልነበረች ምንም ሳይናገር ገብቶኛል፡፡ ስልክ ተለዋውጠን ስለረፈደብኝ ወደ ስራ
ገባሁኝ፡፡ቀኑን ሙሉ እያሰብኩ የዋልኩት ስለእናቴ ተመዘው የማያልቁ ታሪኮች እና ልወጣ ስል ወንድሜ ስለጠየቀኝ ጥያቄ
ነበር።
"ደብዳቤዎች የምትፅፍላት አንተ ነበርክ?" ብሎኛል፡፡
ከስራ ስወጣ ስለወንድሜ እየነገርኳት ስምሪትን ልሸኛት እቤቷ ስንደርስ ባሏ አለመኖሯን አይቶ ሲመለስ ደረስን። ብዙ ስድብና ጥቂት ጥያቄ ቀላቅሎ አምባረቀ፡፡ ልትከላከል በማያስችላት ፍጥነት በጥፊ አላት።በምን ፍጥነት እንዳደረግኩት አላውቅም።በቡጤ ጉንጭና አገጩን አጎንኩት፡፡ ስምሪት መሃል መግባቷን ሲያይ ካልገደልኩት ብሎ ተወራጨ፡፡ እንደፈራ
ያስታውቅበታል።
ሴት የሚማታ ወንድ ከወንድ ጋር የመደባደብ ወኔ የለውም።ሽንታም!!" ካልኩት በኋላ ስምሪትን ያስከፋኋት ስለመሰለኝ አየኋት። ጥርሶቿ ባይስቁም ዓይኖቿ ሲስቁ አስተዋልኩ።ከብዙ
ድንፋታ በኋላ ሄደ። እቤቷ አስገብቻት ልሰናበታት ስል " ኪሩ ሳመኝ?" አለችኝ፡፡ ሰምቻታለሁ:: ዝም አልኳት።
"
ኪሩ?"
"ወዬ?" ስላት ጉንጯ ቀላ፡፡
አላስደገምኳትም። እየሳምኳት
አቋረጠችኝ፡፡
"ምነው?" አልኳት፡፡
"ቆይ የሚቀጥለውንም እኔ ካልጠየቅኩህ አታደርግም?" አለችኝ።
የመጀመሪያ ቀን ከወለሉ ላይ እንዳነሳኋት ተሸክሜ ክንዴ ላይ አቆየኋት፡፡ ከማውቃቸው ውብ ነገሮች ሁሉ የተለየች ድንቅ ፍጥረት ናት:: ወዲያው ስልኬ ጠራ። ከሆስፒታል ነበር፡፡ ምኑ
ነው ያልገባኝ? ጭራሽ ምንም አልገባኝም!! ይህቺ ሴትዮ እንቆቅልሼ ተቆለለሳ? እናቴ ሞታለች! ከመሞቷ ይብስ ለጆሮዬ አዲስ የሆነው ዜና እህትህ...... የሚለው ነበር። እህት አለኝ!
በአንድ ቀን ጠዋት እና ማታ የደበቀቻቸውን ወንድምና እህቴን
ዱብ ያደረገች እናት የኔ እናት ብቻ ናት!!
"ምን ሆነህ ነው? ምንድነው የሰማኸው?" ትለኛለች ስምሪት
በቆምኩበት መደንዘዜ አስደንግጧት።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
መፋጠጣቸው ግራ ያጋባኝ እኔ ራሴን አስተዋወቅኳቸው።
"ኪሩቤል እባላለሁ። የወለላ ልጅ ነኝ።" ከአፌ የወጣው ቃል እነሱ ጆሮ ጋር ሲደርስ ሌላ የሚያስደነግጥ ነገር እስኪመስለኝ ሁለቱም ደርቀው
እናቴ ምንም የወሬው አካል
እንዳልሆነች ሁላ ኮርኒሱ ላይ አፈጠጠች፡፡ ልጅቷ "ልጅ? ልጅ
ልጅ? ማለቴ የወለደችህ? ሲገርም::" እያለች ተራ በተራ ታየናለች። እንደመቅበጥበጥ ሲያደርጋት ከእድሜዋ በታች ህፃን ትመስላለች፡፡
"አዎን ልጂ ነኝ ምነው?" አልኳት።
"እሱ ወንድምህ ነው። ስህተት ይባላል፡፡ ማለቴ የወለላ ልጅ ነው።እኔ ረድኤት እባላለሁ:: ፍቅረኛዬ ነው::" ብላኝ ብዙ ጊዜ እንደምታውቀኝ ተንደርድራ አቀፈችኝ፡፡ ምን ማሰብ እንደነበረብኝ
ግራ ገባኝ:: በደመ-ነፍስ ጨበጥኩት። ስሙ ገርሞኛል።
እውነት ነው? ወንድሜ ነው?" አልኳት እናቴን፡፡ ምንም የገረመው የማይመስለውን ወንድሜን እያየሁት። አረጋገጠችልኝ፡፡ ለደቂቃዎች ዝም አልኩኝ፡፡ ማድረግ የፈለግኩት
እርሷን መውቀስ ነበር ወንድም እንዳለኝ ለምን እንደደበቀችኝ ግን አላደረኩትም።ሀያ ሁለት ዓመቱ ነው በስምንት ዓመቴ ጥላኝ የሄደች ጊዜ ሌላ ቤት መስርታ እንደ ነበር የእድሜው
ቁጥር ነገረኝ፡፡ ለወንድሜም ጥሩ እናት እንዳልነበረች ምንም ሳይናገር ገብቶኛል፡፡ ስልክ ተለዋውጠን ስለረፈደብኝ ወደ ስራ
ገባሁኝ፡፡ቀኑን ሙሉ እያሰብኩ የዋልኩት ስለእናቴ ተመዘው የማያልቁ ታሪኮች እና ልወጣ ስል ወንድሜ ስለጠየቀኝ ጥያቄ
ነበር።
"ደብዳቤዎች የምትፅፍላት አንተ ነበርክ?" ብሎኛል፡፡
ከስራ ስወጣ ስለወንድሜ እየነገርኳት ስምሪትን ልሸኛት እቤቷ ስንደርስ ባሏ አለመኖሯን አይቶ ሲመለስ ደረስን። ብዙ ስድብና ጥቂት ጥያቄ ቀላቅሎ አምባረቀ፡፡ ልትከላከል በማያስችላት ፍጥነት በጥፊ አላት።በምን ፍጥነት እንዳደረግኩት አላውቅም።በቡጤ ጉንጭና አገጩን አጎንኩት፡፡ ስምሪት መሃል መግባቷን ሲያይ ካልገደልኩት ብሎ ተወራጨ፡፡ እንደፈራ
ያስታውቅበታል።
ሴት የሚማታ ወንድ ከወንድ ጋር የመደባደብ ወኔ የለውም።ሽንታም!!" ካልኩት በኋላ ስምሪትን ያስከፋኋት ስለመሰለኝ አየኋት። ጥርሶቿ ባይስቁም ዓይኖቿ ሲስቁ አስተዋልኩ።ከብዙ
ድንፋታ በኋላ ሄደ። እቤቷ አስገብቻት ልሰናበታት ስል " ኪሩ ሳመኝ?" አለችኝ፡፡ ሰምቻታለሁ:: ዝም አልኳት።
"
ኪሩ?"
"ወዬ?" ስላት ጉንጯ ቀላ፡፡
አላስደገምኳትም። እየሳምኳት
አቋረጠችኝ፡፡
"ምነው?" አልኳት፡፡
"ቆይ የሚቀጥለውንም እኔ ካልጠየቅኩህ አታደርግም?" አለችኝ።
የመጀመሪያ ቀን ከወለሉ ላይ እንዳነሳኋት ተሸክሜ ክንዴ ላይ አቆየኋት፡፡ ከማውቃቸው ውብ ነገሮች ሁሉ የተለየች ድንቅ ፍጥረት ናት:: ወዲያው ስልኬ ጠራ። ከሆስፒታል ነበር፡፡ ምኑ
ነው ያልገባኝ? ጭራሽ ምንም አልገባኝም!! ይህቺ ሴትዮ እንቆቅልሼ ተቆለለሳ? እናቴ ሞታለች! ከመሞቷ ይብስ ለጆሮዬ አዲስ የሆነው ዜና እህትህ...... የሚለው ነበር። እህት አለኝ!
በአንድ ቀን ጠዋት እና ማታ የደበቀቻቸውን ወንድምና እህቴን
ዱብ ያደረገች እናት የኔ እናት ብቻ ናት!!
"ምን ሆነህ ነው? ምንድነው የሰማኸው?" ትለኛለች ስምሪት
በቆምኩበት መደንዘዜ አስደንግጧት።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
❤1👍1
#ሚሊዮን_ፀሐዮች_ሚሊዮን_ጨለሞች
ጨረቃ ብቅ አለት፣ ፀሐይ ስትከስም
ያው እንደ ወትሮ ነው
የምሽት የንጋት፣ ፈረቃው አይፈርስም!
የኔ ግን ይለያል
ልቦናየ ቢማስ
ሚሊዮን ፀሐዮች፣ ሚሊዮን ጨለሞች!
ሺ ሰማይ፣ ሺህ አድማስ
ተገልጦ ይታያል።
ስንቴ በጽልመቴ፣ ዙርያየን አዳፈንሁ
ስንቴ በጨረሬ፣ የምድርን ዐይን ወጋሁ
ባንድ ቀን ውስጥ ብቻ
ስንት ጊዜ መሽቼ፣ ስንት ጊዜ ነጋሁ!
ጨረቃ ብቅ አለት፣ ፀሐይ ስትከስም
ያው እንደ ወትሮ ነው
የምሽት የንጋት፣ ፈረቃው አይፈርስም!
የኔ ግን ይለያል
ልቦናየ ቢማስ
ሚሊዮን ፀሐዮች፣ ሚሊዮን ጨለሞች!
ሺ ሰማይ፣ ሺህ አድማስ
ተገልጦ ይታያል።
ስንቴ በጽልመቴ፣ ዙርያየን አዳፈንሁ
ስንቴ በጨረሬ፣ የምድርን ዐይን ወጋሁ
ባንድ ቀን ውስጥ ብቻ
ስንት ጊዜ መሽቼ፣ ስንት ጊዜ ነጋሁ!
#የመገፋት_ጣዕም
ነግጄ ሸቅጬ
ማትረፍ ባይሆንልኝ
ብርርርርርርርርርርር ...
ሳልል ቀርቼ
ከተስፋ ጋር ብገኝ
ከፊታቸው እንድገል .
ሲገፉኝ ሲገፉኝ
ሲገፉኝ ሲገፉኝ
ሲገፉኝ ሲገፉኝ
ካናት የሚቀቡት
ለጋ ቅቤ ሆንኩኝ።
ነግጄ ሸቅጬ
ማትረፍ ባይሆንልኝ
ብርርርርርርርርርርር ...
ሳልል ቀርቼ
ከተስፋ ጋር ብገኝ
ከፊታቸው እንድገል .
ሲገፉኝ ሲገፉኝ
ሲገፉኝ ሲገፉኝ
ሲገፉኝ ሲገፉኝ
ካናት የሚቀቡት
ለጋ ቅቤ ሆንኩኝ።
#ሰው_ከቀየው_እንጂ፣
ወጥቼ ከቀሳው
ለጊዜው ታግየ
ሞትን ድል ብነሳው
መኖር አሸነፈኝ
ቤቴ ተደፍቶብኝ፣ ሁለት ወር አለፈኝ።
ተፈጥሮየ ከዳኝ፣ ፈሊጡን ቀየረ
አካሌ ሸፈተ፣ አዲስ ወግ ተማረ
ገላየ በቁሙ፣ ሳር ማብቀል ጀመረ።
እንዳልቆይ መታከት፣ እንዳልወጣ ሽብር
ሳይደከመኝ ተኝቼ
እንቅልፍ አንገቴ ላይ፣ ቀንበሩን ሳይሰብር
ካልጋ ተነስቼ
እየተደናገርሁ
እየተደናበርሁ
በምሳ ሰአቴ፣ ራት እየጋገርሁ
ኑሮ እንደ ሳር ጉንጉን፣ እያደናቀፈኝ
ሁለት ወር አለፈኝ!
ዛሬ ኮበለለ
ትላንትናን ቀድሞት፣ ባምባላይ ፈረሱ
ቀኔና ሌሊቴም፣ ሰልፍ እያፈረሱ
ይተራመሳሉ
ይርመሰመሳሉ
አርባም እድሜ ሆና
ያችን ለማሳጠር
ነፋስ በሰው ሲያድም፣ ከሞት ሲመሳጠር
ወዴትስ ይኬዳል
ሰው ከቀየው እንጂ፣ካለም ይሰደዳል?"
ወጥቼ ከቀሳው
ለጊዜው ታግየ
ሞትን ድል ብነሳው
መኖር አሸነፈኝ
ቤቴ ተደፍቶብኝ፣ ሁለት ወር አለፈኝ።
ተፈጥሮየ ከዳኝ፣ ፈሊጡን ቀየረ
አካሌ ሸፈተ፣ አዲስ ወግ ተማረ
ገላየ በቁሙ፣ ሳር ማብቀል ጀመረ።
እንዳልቆይ መታከት፣ እንዳልወጣ ሽብር
ሳይደከመኝ ተኝቼ
እንቅልፍ አንገቴ ላይ፣ ቀንበሩን ሳይሰብር
ካልጋ ተነስቼ
እየተደናገርሁ
እየተደናበርሁ
በምሳ ሰአቴ፣ ራት እየጋገርሁ
ኑሮ እንደ ሳር ጉንጉን፣ እያደናቀፈኝ
ሁለት ወር አለፈኝ!
ዛሬ ኮበለለ
ትላንትናን ቀድሞት፣ ባምባላይ ፈረሱ
ቀኔና ሌሊቴም፣ ሰልፍ እያፈረሱ
ይተራመሳሉ
ይርመሰመሳሉ
አርባም እድሜ ሆና
ያችን ለማሳጠር
ነፋስ በሰው ሲያድም፣ ከሞት ሲመሳጠር
ወዴትስ ይኬዳል
ሰው ከቀየው እንጂ፣ካለም ይሰደዳል?"
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
---------------------------------------------------
ሁሉም የሕይወት ገፅ መጨረሻ ላይኖረው ይችላል ለህይወት መጨረሻ ብሎ ነገር የለም።የአንዱ ቀን መጨረሻ የሌላው ቀን መጀመርያ ነውና።የሰኞ ማለቅ የማክሰኞ መጀመር እንደሆነው የምድር መጠቅለል ለሰማያዊ ህይወት መጀመር እንደሚሆነው....ሌላ ፅንፍ ግን አለው።
=========================
"እናትሽ በጠና ታማለች፡፡ እባክሽ ልታይሽ ትፈልጋላች...ለአራተኛ ጊዜ የተላከልኝ መልዕክት ነው።
“እስካሁን አልሞተችም እንዴ? ለምን ታጓጓኛለች? አንዳችሁ እንኳን ምናለ ሞተች የሚል ብስራት ብታሰሙኝ?"
"በስመ አብ ወ ወልድ ወ መንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ!! (ገዳዳ መስቀል በሰራ እጁ እያማተበ) ምነው ልጄ? ምን የሚሉት ጭካኔ ነው? ደግም አይደል! እግዜርም አይወደው::" መልሴ
አንገሽግሾታል። ሀምሳ ዓመት የሚያልፈው ሰውዬ ነው።የወለደችኝ ሴትዮ የነፍስ አባቷ ነው።
"በናትህ ከቤቴ ውጣልኝ!!"
"ምነው ልጄ? እግዜር የሰጠኝን ሹመት ባታከብሪ በእድሜ አባትሽ አልሆንም?" የሚናገረው ቃል የለዘበ ይሁን እንጂ ቀይ
ወጥ የመሰለ ግለታም ዓይኑ እንደተጠየፈኝ ያሳብቅበታል።
እድሜውን ሳይሆን የለበሰውን የቤተ ክህነት ልብስ ባከብር ደስ ባለኝ ግን ለባሹ ልብሱን እንጂ ልብሱ ለባሹን እንዴት ሊያስከብረው ይችላል? ልብሱ ይሄን ከንቱ ሰውዬ እንዴት ክቡር
ሊያደርገው ይችላል? መሆን የነበረበት ልብሱ ተገፎ ለተከበረ ሰው መደረብ ነበር። ያኔ ልብሱም ለባሹም ይከበራሉ።
መጎናፀፊያ አካልን ይሸፍን ይሆናል፤ ምናልባትም የአካል እንከንን የነፍስ ሴሰኝነት ግን በልብስ አይሸፈንም፡፡ ዝቃጭ ምግባር ግን ለቅድስና ሌት ተቀን ለሚታገሉ ልበ ብርቱዎች በተዘጋጀ መደረቢያ አይከለልም። በሱ ቤት እኔ ከእናቴ ጋር የሚስራውን ብልግና አላውቅበትም። የናቴ ውሽማዋ ነው።
ይሄኔ በየመቅደሱ ሰው የዘራውን ያጭዳል' እያለ ይቦጠለቃል፡፡
ሴሰኝነትን እየዘራ መከበርን ለማጨድ ማጭድ ይስላል፡፡ ከንቱ!!
ይሄኔ ስንቶች ስንጥር ለምታክል በደላቸው ንስሃን ሽተው ከፊቱ
ሲመጡ ዋርካ የሚያክል ስድነቱን በብብቱ ሸሽጎ ልባቸው ለንስሃ
እንዲሰበር ዘክሯል። የዘቀጠ!
የእናቴን ጣር ላይ መሆን ሊነግሩኝ እንደመጡት ሶስቱ እሱም እየተፀየፈኝ ቤቴን ለቆ ወጣ፡፡ የመጀመሪያዋ የእናቴ ብቸኛ እህት ነበረች፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ብትኖርም ገጠር እያለሁ በልጅነቴ ለበዓላት ስትመጣ ነበር ያየኋት፡፡ ጠይቃኝም ጠይቄያትም የማንተዋወቅ አክስቴ ናት።
“ምን አገባኝ ታዲያ? ለምን ፍግም አትልም?" ስላት ብታንቀኝ ደስ ባላት።
"ጨካኝ! አረመኔ!" ብላኝ ወጣች። ሳስበው የኔ ዘመዶች ግን የሆነ
የዛገ የማሰቢያ ክፍል ሳይኖራቸው አይቀርም::እንደወለደችኝ ከነእሪታዬ ጥላኝ አሸሼ ገዳሜዋን ልትል ስትሄድ ዞራ ልታየኝ እንኳን የሚራራ አንጀት ያልነበራትን ሴትዮ ጨካኝ! አረመኔ
ያላሏት ዘመዶቼ በወተት ምትክ ክፋት፣ በእናት እቅፍ ፈንታ ጥላቻ፣ በልጅነት ቡረቃ ልዋጭ መገፋትን ሲግቱ ፍቅርና
ጥላቻን ካምታቱበት ልቤ ርህራሄ ይናፍቃሉ፡፡
ሁለተኛው የእናቴ ብቸኛ ወንድም ነበር፡፡ ታላቋ ነው። አጎቴ የቤታቸው አድባር!!
"እንዴት እናትሽ መታመሟን ሰምተሽ ትቀሪያለሽ? ሞታም ቢሆን እኮ ይኸው ነው::" አለኝ በወቀሳ እፍረት የሚያሲዘኝ
መስሎት፡፡
“እሷ ብቻ ትሙት እንጂ ለሞቷ እንኳን አልዘገይም! ደስ እያለኝ መጥቼ እቀብራታለሁ።” ያልኩት አንቀጠቀጠው። ቅንጣት ርህራሄ እንደሌለኝ አስቦ ጥሎኝ ሄደ፡፡
ሶስተኛው አያቴ ነው:: የእናቴ አባት።
........…
"አባባ እኔን ለማናገር ሀገር አቋርጠህ መጥተህ ባላስቀይምህ ደስ
ይለኝ ነበር፡፡ እንዳደርገው እያስገደድከኝ ነው።እናቴ አንድ ሞት አይደለም አስር ሞት ብትሞት አልፀፀትም::" አልኩት::
"እናትሽ በህይወት ሳለች አግኝታሽ ገንዘብ ልትተውልሽ ትፈልጋለች። ካልደረስሽ ለሌላ ሰው ለማውረስ እያሰበች ነው።"
ብሉኝ ከፊቴ ላይ ስሜቴን መበርበር ጀመረ።
"ሃሃሃሃ ጥሩ ነዋ፡፡ በመኖሯ ማንንም ጠቅማ ማወቋን እኔንጃ በሞቷ እንኳን እስኪ ትጥቀም!" ስለው ደነገጠ፡፡
ንብረት ያሳሳታል ብሎ ማሰቡ ገርሞኛል፡፡ ምክንያቱም በኮልኮሌ ስብስብ ሀሴት የምቃርም ሴት አይደለሁም። የጮቤዬ ምንጭ ገንዘብ ቢሆን እንኳን ከዚህ በኋላ ምንም የገቢ ምንጭ ባይኖረኝ እድሜዬን ሙሉ ጮቤ እየረገጥኩ መኖር የምችልበት ሀብት ላለው ሀብታም የሸጠኝ እራሱ አያቴ ነው:: አያቴ ብቸኛው
በህይወቴ የተከሰተ ለጥሩ የተጠጋጋ ክስተት ነው።እናቴ ጥላኝ ስትሄድ የተቀበለኝ እሱ ነው:: ምንም እንኳን የልጁ ልጅ መሆኔን ሳያሳውቀኝ ባድግም፣ ምንም እንኳን ከሚያኖራቸው አገልጋዮች እንደ አንዷ ራሴን እየቆጠርኩ ስኖር
እንደልክ ሁሉ ቢያስችለውም፣ ምንም እንኳን እናቴ ማን እንደሆነች ሊነግረኝ ሳይፈልግ ባድግም፣ለጨለመ ልጅነቴ አንዱ ምክንያት ቢሆንም፣ ምንም እንኳን
በቅጡ ለማያውቀው ሀብታም ነጋዴ ቢሸጠኝም።ከብዙ ክፉ የኑሮዬ ገፅታዎች ውስጥ ደብዛዛው ክፉ እሱ ነው።
አልጋ ቢኖረኝ እንደ ፍጡር ለሊት ነበረኝ፡፡
ቅዠት ባይሆኑብኝ እንቅልፍ ነበረኝ፡፡
ቢያስተኙኝ ብዙ ህልም ነበረኝ።
ለሁሉም ርህራሄ አልባነቴን ብነግራቸውም ሁሉም የማይገባቸው ሀቅ ግን ሴትየዋን አልጠላትም በገፋችኝ ጥግ ወደርሷ የሚያስወነጭፈኝ ስበት አላት፡፡ የማስታውሰው ቅንጣቢ
የእናት የሚመስል ነገር አሳይታኝ አታውቅም፡፡ በክፋቷ ክምር ልጠላት እፍጨረጨራለሁ። ከንቱ መንፈራገጥ ብቻ ይሆንብኝና ለምትሰራው ቅጥ ያጣ ግፏ ምላሽ ከቀናት ንዴት በኋላ
በማልቆጣጠረው የእናት ፍቅር ጥም ሲቃጠል ራሴን አገኘዋለሁ።ብሽቅ እኔ! ልረሳት እመኛለሁ:: አልችልም።
ልጠላት አጥብቄ እፈልጋለሁ። አልችልም:: ልገላገላት እፈልጋለሁ። የሆነ ፍንትው ያለች ፀሃይ በደመቀችበት ማለዳ
ሞቷን የሚያበስረኝ መላዓክ በፈገግታ ታጅቦ "እነሆ እልልልልል የምትይበት ቀን መጥቶልሻል፡፡ እናትሽ በወዳጇ ሳጥናኤል እቅፍ ትገኛለች:: በክፋቷም በፍቅሯም የምትነጂበት ጊዜ አበቃ!" ቢለኝ ያ የተወለድኩበት ቀን የሚሆን ይመስለኛል። እናቴን መፈለግ ትቼ ራሴን የምፈልግ፡፡
በቁሟ አምርራ የምትጠላኝ እናቴ በሞቷ ዋዜማ ላይ ለንሰሃዋ መጫወቻ ጠጠር ልታደርገኝ ልታየኝ ትፈልጋለች፡፡ ኩነኔን
ፈርታ እንጂ እኔ አሳስቤያት አይደለም፡፡ ምናልባት ይቅርታ ልትጠይቀኝ እንኳን ከሆነ (አታደርገውም እንጂ!) ኀጢአቷን በኔ ይቅርታ ልትቀንስ እንጂ የሰበረችውን ልቤን ፍንክትካች ልትገጣጥም አስባ አይደለም፡፡
ከእያንዳንዱ ክፋት ጀርባ መሪር በደል አለ እያልኩ አስባለሁ።ጥያቄው የሚሆነው በደልን ይቅር ያለ በጎነት የለም ወይ? የሚለው ነው አንዳንዴ የወለደችኝን ሴት ሳስባት ለመራራነቷ ምክንያት እያበጀ በሚጃጃል ልቤ ልረዳት እሞክራለሁ።
ምክንያቷን ማወቅ እመኛለሁ። ከዛ ባዝንላት፣ ደሞ ያደረገችኝን
ሁሉ ብረሳላት፣ ደግሞም እድል ብሰጣት... በልፍስፍሱ እኔነቴ
ራሴን ለምወቅስበት መጠን ያህል ጊዜ ሞክሬያለሁ። አንድ እርምጃ ስጠጋት በመቶ ትሸሸኛለች፡፡ ይቅር ባልኳት እጥፍ
በደሏን ትከምርብኛለች፡፡ እንደቆሻሻ እየተፀየፈችኝ እንኳን እቅፏን እናፍቃለሁ። በሚያቆስል ምላሷ እየገሸለጠችኝ እንኳን
ፀጉሬን እየደባበሰች እንድታባብለኝ እቃዣለሁ። ራሴን ሳየው በርሷ የተለከፍኩ ይመስለኛል። የመኖር ትርጉም ቁልፌ በእሷ እናትነት ውስጥ ያለ ይመስለኛል፡፡ ሰውየው(የነፍስ አባቷ) ገስፀውኝ ከቤቴ ከወጡ ከሰዓታት በኋላም ይሄ ቄጤማ ማንነቴ ስለርሷ ማሰብ እንዳቆም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
---------------------------------------------------
ሁሉም የሕይወት ገፅ መጨረሻ ላይኖረው ይችላል ለህይወት መጨረሻ ብሎ ነገር የለም።የአንዱ ቀን መጨረሻ የሌላው ቀን መጀመርያ ነውና።የሰኞ ማለቅ የማክሰኞ መጀመር እንደሆነው የምድር መጠቅለል ለሰማያዊ ህይወት መጀመር እንደሚሆነው....ሌላ ፅንፍ ግን አለው።
=========================
"እናትሽ በጠና ታማለች፡፡ እባክሽ ልታይሽ ትፈልጋላች...ለአራተኛ ጊዜ የተላከልኝ መልዕክት ነው።
“እስካሁን አልሞተችም እንዴ? ለምን ታጓጓኛለች? አንዳችሁ እንኳን ምናለ ሞተች የሚል ብስራት ብታሰሙኝ?"
"በስመ አብ ወ ወልድ ወ መንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ!! (ገዳዳ መስቀል በሰራ እጁ እያማተበ) ምነው ልጄ? ምን የሚሉት ጭካኔ ነው? ደግም አይደል! እግዜርም አይወደው::" መልሴ
አንገሽግሾታል። ሀምሳ ዓመት የሚያልፈው ሰውዬ ነው።የወለደችኝ ሴትዮ የነፍስ አባቷ ነው።
"በናትህ ከቤቴ ውጣልኝ!!"
"ምነው ልጄ? እግዜር የሰጠኝን ሹመት ባታከብሪ በእድሜ አባትሽ አልሆንም?" የሚናገረው ቃል የለዘበ ይሁን እንጂ ቀይ
ወጥ የመሰለ ግለታም ዓይኑ እንደተጠየፈኝ ያሳብቅበታል።
እድሜውን ሳይሆን የለበሰውን የቤተ ክህነት ልብስ ባከብር ደስ ባለኝ ግን ለባሹ ልብሱን እንጂ ልብሱ ለባሹን እንዴት ሊያስከብረው ይችላል? ልብሱ ይሄን ከንቱ ሰውዬ እንዴት ክቡር
ሊያደርገው ይችላል? መሆን የነበረበት ልብሱ ተገፎ ለተከበረ ሰው መደረብ ነበር። ያኔ ልብሱም ለባሹም ይከበራሉ።
መጎናፀፊያ አካልን ይሸፍን ይሆናል፤ ምናልባትም የአካል እንከንን የነፍስ ሴሰኝነት ግን በልብስ አይሸፈንም፡፡ ዝቃጭ ምግባር ግን ለቅድስና ሌት ተቀን ለሚታገሉ ልበ ብርቱዎች በተዘጋጀ መደረቢያ አይከለልም። በሱ ቤት እኔ ከእናቴ ጋር የሚስራውን ብልግና አላውቅበትም። የናቴ ውሽማዋ ነው።
ይሄኔ በየመቅደሱ ሰው የዘራውን ያጭዳል' እያለ ይቦጠለቃል፡፡
ሴሰኝነትን እየዘራ መከበርን ለማጨድ ማጭድ ይስላል፡፡ ከንቱ!!
ይሄኔ ስንቶች ስንጥር ለምታክል በደላቸው ንስሃን ሽተው ከፊቱ
ሲመጡ ዋርካ የሚያክል ስድነቱን በብብቱ ሸሽጎ ልባቸው ለንስሃ
እንዲሰበር ዘክሯል። የዘቀጠ!
የእናቴን ጣር ላይ መሆን ሊነግሩኝ እንደመጡት ሶስቱ እሱም እየተፀየፈኝ ቤቴን ለቆ ወጣ፡፡ የመጀመሪያዋ የእናቴ ብቸኛ እህት ነበረች፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ብትኖርም ገጠር እያለሁ በልጅነቴ ለበዓላት ስትመጣ ነበር ያየኋት፡፡ ጠይቃኝም ጠይቄያትም የማንተዋወቅ አክስቴ ናት።
“ምን አገባኝ ታዲያ? ለምን ፍግም አትልም?" ስላት ብታንቀኝ ደስ ባላት።
"ጨካኝ! አረመኔ!" ብላኝ ወጣች። ሳስበው የኔ ዘመዶች ግን የሆነ
የዛገ የማሰቢያ ክፍል ሳይኖራቸው አይቀርም::እንደወለደችኝ ከነእሪታዬ ጥላኝ አሸሼ ገዳሜዋን ልትል ስትሄድ ዞራ ልታየኝ እንኳን የሚራራ አንጀት ያልነበራትን ሴትዮ ጨካኝ! አረመኔ
ያላሏት ዘመዶቼ በወተት ምትክ ክፋት፣ በእናት እቅፍ ፈንታ ጥላቻ፣ በልጅነት ቡረቃ ልዋጭ መገፋትን ሲግቱ ፍቅርና
ጥላቻን ካምታቱበት ልቤ ርህራሄ ይናፍቃሉ፡፡
ሁለተኛው የእናቴ ብቸኛ ወንድም ነበር፡፡ ታላቋ ነው። አጎቴ የቤታቸው አድባር!!
"እንዴት እናትሽ መታመሟን ሰምተሽ ትቀሪያለሽ? ሞታም ቢሆን እኮ ይኸው ነው::" አለኝ በወቀሳ እፍረት የሚያሲዘኝ
መስሎት፡፡
“እሷ ብቻ ትሙት እንጂ ለሞቷ እንኳን አልዘገይም! ደስ እያለኝ መጥቼ እቀብራታለሁ።” ያልኩት አንቀጠቀጠው። ቅንጣት ርህራሄ እንደሌለኝ አስቦ ጥሎኝ ሄደ፡፡
ሶስተኛው አያቴ ነው:: የእናቴ አባት።
........…
"አባባ እኔን ለማናገር ሀገር አቋርጠህ መጥተህ ባላስቀይምህ ደስ
ይለኝ ነበር፡፡ እንዳደርገው እያስገደድከኝ ነው።እናቴ አንድ ሞት አይደለም አስር ሞት ብትሞት አልፀፀትም::" አልኩት::
"እናትሽ በህይወት ሳለች አግኝታሽ ገንዘብ ልትተውልሽ ትፈልጋለች። ካልደረስሽ ለሌላ ሰው ለማውረስ እያሰበች ነው።"
ብሉኝ ከፊቴ ላይ ስሜቴን መበርበር ጀመረ።
"ሃሃሃሃ ጥሩ ነዋ፡፡ በመኖሯ ማንንም ጠቅማ ማወቋን እኔንጃ በሞቷ እንኳን እስኪ ትጥቀም!" ስለው ደነገጠ፡፡
ንብረት ያሳሳታል ብሎ ማሰቡ ገርሞኛል፡፡ ምክንያቱም በኮልኮሌ ስብስብ ሀሴት የምቃርም ሴት አይደለሁም። የጮቤዬ ምንጭ ገንዘብ ቢሆን እንኳን ከዚህ በኋላ ምንም የገቢ ምንጭ ባይኖረኝ እድሜዬን ሙሉ ጮቤ እየረገጥኩ መኖር የምችልበት ሀብት ላለው ሀብታም የሸጠኝ እራሱ አያቴ ነው:: አያቴ ብቸኛው
በህይወቴ የተከሰተ ለጥሩ የተጠጋጋ ክስተት ነው።እናቴ ጥላኝ ስትሄድ የተቀበለኝ እሱ ነው:: ምንም እንኳን የልጁ ልጅ መሆኔን ሳያሳውቀኝ ባድግም፣ ምንም እንኳን ከሚያኖራቸው አገልጋዮች እንደ አንዷ ራሴን እየቆጠርኩ ስኖር
እንደልክ ሁሉ ቢያስችለውም፣ ምንም እንኳን እናቴ ማን እንደሆነች ሊነግረኝ ሳይፈልግ ባድግም፣ለጨለመ ልጅነቴ አንዱ ምክንያት ቢሆንም፣ ምንም እንኳን
በቅጡ ለማያውቀው ሀብታም ነጋዴ ቢሸጠኝም።ከብዙ ክፉ የኑሮዬ ገፅታዎች ውስጥ ደብዛዛው ክፉ እሱ ነው።
አልጋ ቢኖረኝ እንደ ፍጡር ለሊት ነበረኝ፡፡
ቅዠት ባይሆኑብኝ እንቅልፍ ነበረኝ፡፡
ቢያስተኙኝ ብዙ ህልም ነበረኝ።
ለሁሉም ርህራሄ አልባነቴን ብነግራቸውም ሁሉም የማይገባቸው ሀቅ ግን ሴትየዋን አልጠላትም በገፋችኝ ጥግ ወደርሷ የሚያስወነጭፈኝ ስበት አላት፡፡ የማስታውሰው ቅንጣቢ
የእናት የሚመስል ነገር አሳይታኝ አታውቅም፡፡ በክፋቷ ክምር ልጠላት እፍጨረጨራለሁ። ከንቱ መንፈራገጥ ብቻ ይሆንብኝና ለምትሰራው ቅጥ ያጣ ግፏ ምላሽ ከቀናት ንዴት በኋላ
በማልቆጣጠረው የእናት ፍቅር ጥም ሲቃጠል ራሴን አገኘዋለሁ።ብሽቅ እኔ! ልረሳት እመኛለሁ:: አልችልም።
ልጠላት አጥብቄ እፈልጋለሁ። አልችልም:: ልገላገላት እፈልጋለሁ። የሆነ ፍንትው ያለች ፀሃይ በደመቀችበት ማለዳ
ሞቷን የሚያበስረኝ መላዓክ በፈገግታ ታጅቦ "እነሆ እልልልልል የምትይበት ቀን መጥቶልሻል፡፡ እናትሽ በወዳጇ ሳጥናኤል እቅፍ ትገኛለች:: በክፋቷም በፍቅሯም የምትነጂበት ጊዜ አበቃ!" ቢለኝ ያ የተወለድኩበት ቀን የሚሆን ይመስለኛል። እናቴን መፈለግ ትቼ ራሴን የምፈልግ፡፡
በቁሟ አምርራ የምትጠላኝ እናቴ በሞቷ ዋዜማ ላይ ለንሰሃዋ መጫወቻ ጠጠር ልታደርገኝ ልታየኝ ትፈልጋለች፡፡ ኩነኔን
ፈርታ እንጂ እኔ አሳስቤያት አይደለም፡፡ ምናልባት ይቅርታ ልትጠይቀኝ እንኳን ከሆነ (አታደርገውም እንጂ!) ኀጢአቷን በኔ ይቅርታ ልትቀንስ እንጂ የሰበረችውን ልቤን ፍንክትካች ልትገጣጥም አስባ አይደለም፡፡
ከእያንዳንዱ ክፋት ጀርባ መሪር በደል አለ እያልኩ አስባለሁ።ጥያቄው የሚሆነው በደልን ይቅር ያለ በጎነት የለም ወይ? የሚለው ነው አንዳንዴ የወለደችኝን ሴት ሳስባት ለመራራነቷ ምክንያት እያበጀ በሚጃጃል ልቤ ልረዳት እሞክራለሁ።
ምክንያቷን ማወቅ እመኛለሁ። ከዛ ባዝንላት፣ ደሞ ያደረገችኝን
ሁሉ ብረሳላት፣ ደግሞም እድል ብሰጣት... በልፍስፍሱ እኔነቴ
ራሴን ለምወቅስበት መጠን ያህል ጊዜ ሞክሬያለሁ። አንድ እርምጃ ስጠጋት በመቶ ትሸሸኛለች፡፡ ይቅር ባልኳት እጥፍ
በደሏን ትከምርብኛለች፡፡ እንደቆሻሻ እየተፀየፈችኝ እንኳን እቅፏን እናፍቃለሁ። በሚያቆስል ምላሷ እየገሸለጠችኝ እንኳን
ፀጉሬን እየደባበሰች እንድታባብለኝ እቃዣለሁ። ራሴን ሳየው በርሷ የተለከፍኩ ይመስለኛል። የመኖር ትርጉም ቁልፌ በእሷ እናትነት ውስጥ ያለ ይመስለኛል፡፡ ሰውየው(የነፍስ አባቷ) ገስፀውኝ ከቤቴ ከወጡ ከሰዓታት በኋላም ይሄ ቄጤማ ማንነቴ ስለርሷ ማሰብ እንዳቆም
👍4
አልፈቀደልኝም። ምናልባት በፈጣሪ እጅ
ተይዛ ጥያቄዎቼን ትመልስልኝ ይሆን? ከዓመታት በፊት የነበራት ድንዳኔ ቀልጦ ይሆን? በሚዋልል ሀሳቤ እየበገንኩም
ቢሆን ተኛች የተባለበት ሆስፒታል መጓዝ ጀመርኩ፡፡
የጭካኔ መርዟ ሰውነቴን ሁሉ እንደሚመዘምዘው እያወቅኩ
የተኛችበት ክፍል ደረስኩ፡፡ አጠገቧ የነበሩት ዘመዶቿ ዘመዶቿ መሰሉኝ! ከነፍስ አባቷና ከአክስቴ ውጪ
አላውቃቸውም፡፡ ምናልባትም ጓደኞቿ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሲያዩኝ አውሬ እንዳየ ታዳኝ መፈርጠጥ ቃጣቸው።ለሰላምታ እንኳን እጃቸውን ሳይዘረጉልኝ ክፍሉን ለቀው ወጡ። ስለእኔ ምን ብትላቸው ነው ሰው እንዳልሆነ ፍጡር የሚያዩኝ? እያልኩ አስባለሁ፡፡ አምጣ የወለደቻት እናቷ የምትፀየፋትን ልጅ ከሌላ
ጠፈር እንደመጣች ፍጡር ማየታቸው ተጨማሪ ማብራሪያ እንደማያስፈልገው አስብኩና ቅር አልተሰኘሁባቸውም። እኔና
እሷ ብቻ ተፋጠጥን። ፊቷ ጎረባብጦ እና አመዳም ሆኖ አህያ የፈነጨበት ሜዳ መስሏል። አጥንቷ ፊቷ ላይ ገጧል፡፡ ስትንቀሳቀስ በሰቀቀን ነው።
"እንዴት ነሽ?" ያልኳት የመሆኗ አኳኋን ግድ ሰጥቶኝ አልነበረም፡፡ ባትመልስልኝም ያለችበት ሁኔታ በግልፅ ይታያል።
"አልሞትኩም::" ያለችኝ መሞቷ እንደሚያፍነከንከኝ ሁሉ እርግጠኛ በመሆን ጥርሷን ነክሳ ነው:: በፍፁም ዓይኔን በሙሉ ዓይኗ አታይም።
"ምን ልትነግሪኝ ነው ልታገኚኝ የፈለግሽው? የሚጠቅም ነገር
መሆን አለበት::" በምትሰጠኝ መልስ ላለመብሸቅ ራሴን እያስናዳሁ መልሱን ጠበቅኩ።
"አልሰጠሽኝም እያልሽ የምትወቅሽኝን የእናትነት ፍቅር ማሳያ ከሆነሽ ብዬ ያለኝን ገንዘብ ልሰጥሽ ነው::" አለችኝ፡፡
አንቺ የሰይጣን ታላቅ እህት ከዚህ ሁሉ ኮልኮሌሽ ይልቅ አንድ የፍቅር ቃል፣ አንድ የይቅርታ ቃል፣ አንድ መሳም፣ የአንዴ
የእናት እቅፍ..አንዳቸው ብቻ እንኳ ልኬት በሌለው መጠን እንደሚበልጡ መገንዘብ የሚችል ልብ የለሽም ልላት ነበር ያሰብኩት።ዳሩ እሷ አጥፍቻለሁ ብላ ይቅርታ ከምትጠይቅ፣ተፀፅቻለሁ ብላ ከምታቅፈኝ፣ ናፍቀሽኛል ብላ ከምትስመኝ ሲኦል ሰባት እጥፍ ቢነድ ወደ እሳቱ ዓይኗን ጨፍና መወርወር
ትመርጣለች።
ከልብሽ የእናትነት ፍቅርሽ እንዲገባኝ ትፈልጊያለሽ?"
አይገባሽም እንጂ!" ስትናገር አለማፈሯ እኔን ያሳፍረኛል፡፡ እናት ሆና የምታውቅ ይመስል።
"እኔ ገንዘብሽን አልፈልገውም ለምትፈልጊው ሰው ስጪዉ ለኔ ግን ለጥያቄዎቼ መልስ ስጪኝ....
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
ተይዛ ጥያቄዎቼን ትመልስልኝ ይሆን? ከዓመታት በፊት የነበራት ድንዳኔ ቀልጦ ይሆን? በሚዋልል ሀሳቤ እየበገንኩም
ቢሆን ተኛች የተባለበት ሆስፒታል መጓዝ ጀመርኩ፡፡
የጭካኔ መርዟ ሰውነቴን ሁሉ እንደሚመዘምዘው እያወቅኩ
የተኛችበት ክፍል ደረስኩ፡፡ አጠገቧ የነበሩት ዘመዶቿ ዘመዶቿ መሰሉኝ! ከነፍስ አባቷና ከአክስቴ ውጪ
አላውቃቸውም፡፡ ምናልባትም ጓደኞቿ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሲያዩኝ አውሬ እንዳየ ታዳኝ መፈርጠጥ ቃጣቸው።ለሰላምታ እንኳን እጃቸውን ሳይዘረጉልኝ ክፍሉን ለቀው ወጡ። ስለእኔ ምን ብትላቸው ነው ሰው እንዳልሆነ ፍጡር የሚያዩኝ? እያልኩ አስባለሁ፡፡ አምጣ የወለደቻት እናቷ የምትፀየፋትን ልጅ ከሌላ
ጠፈር እንደመጣች ፍጡር ማየታቸው ተጨማሪ ማብራሪያ እንደማያስፈልገው አስብኩና ቅር አልተሰኘሁባቸውም። እኔና
እሷ ብቻ ተፋጠጥን። ፊቷ ጎረባብጦ እና አመዳም ሆኖ አህያ የፈነጨበት ሜዳ መስሏል። አጥንቷ ፊቷ ላይ ገጧል፡፡ ስትንቀሳቀስ በሰቀቀን ነው።
"እንዴት ነሽ?" ያልኳት የመሆኗ አኳኋን ግድ ሰጥቶኝ አልነበረም፡፡ ባትመልስልኝም ያለችበት ሁኔታ በግልፅ ይታያል።
"አልሞትኩም::" ያለችኝ መሞቷ እንደሚያፍነከንከኝ ሁሉ እርግጠኛ በመሆን ጥርሷን ነክሳ ነው:: በፍፁም ዓይኔን በሙሉ ዓይኗ አታይም።
"ምን ልትነግሪኝ ነው ልታገኚኝ የፈለግሽው? የሚጠቅም ነገር
መሆን አለበት::" በምትሰጠኝ መልስ ላለመብሸቅ ራሴን እያስናዳሁ መልሱን ጠበቅኩ።
"አልሰጠሽኝም እያልሽ የምትወቅሽኝን የእናትነት ፍቅር ማሳያ ከሆነሽ ብዬ ያለኝን ገንዘብ ልሰጥሽ ነው::" አለችኝ፡፡
አንቺ የሰይጣን ታላቅ እህት ከዚህ ሁሉ ኮልኮሌሽ ይልቅ አንድ የፍቅር ቃል፣ አንድ የይቅርታ ቃል፣ አንድ መሳም፣ የአንዴ
የእናት እቅፍ..አንዳቸው ብቻ እንኳ ልኬት በሌለው መጠን እንደሚበልጡ መገንዘብ የሚችል ልብ የለሽም ልላት ነበር ያሰብኩት።ዳሩ እሷ አጥፍቻለሁ ብላ ይቅርታ ከምትጠይቅ፣ተፀፅቻለሁ ብላ ከምታቅፈኝ፣ ናፍቀሽኛል ብላ ከምትስመኝ ሲኦል ሰባት እጥፍ ቢነድ ወደ እሳቱ ዓይኗን ጨፍና መወርወር
ትመርጣለች።
ከልብሽ የእናትነት ፍቅርሽ እንዲገባኝ ትፈልጊያለሽ?"
አይገባሽም እንጂ!" ስትናገር አለማፈሯ እኔን ያሳፍረኛል፡፡ እናት ሆና የምታውቅ ይመስል።
"እኔ ገንዘብሽን አልፈልገውም ለምትፈልጊው ሰው ስጪዉ ለኔ ግን ለጥያቄዎቼ መልስ ስጪኝ....
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#አንድነት_ማለት
አንድ አካል ማለት
አንድ አምሳል ማለት
እንደ ጎፈርና ሰው ..
ከማርትሬዛ አካል ተጣብቀው እንዳሉት
በድንን መጋራት
አይደለም አንድነት
አንድ አካል ማለት
አንድ አምሳል ማለት
እንደ ሃገሬ ተክል እንደ አክሱም ሃውልት
አካልን ለማቅረብ ለመጓዝ ቢያቅት
በአይን ውሃ ተያይቶ ካለ መግባባት
ይህ ነው አንድነት፡፡
አንድ አካል ማለት
አንድ አምሳል ማለት
እንደ ጎፈርና ሰው ..
ከማርትሬዛ አካል ተጣብቀው እንዳሉት
በድንን መጋራት
አይደለም አንድነት
አንድ አካል ማለት
አንድ አምሳል ማለት
እንደ ሃገሬ ተክል እንደ አክሱም ሃውልት
አካልን ለማቅረብ ለመጓዝ ቢያቅት
በአይን ውሃ ተያይቶ ካለ መግባባት
ይህ ነው አንድነት፡፡