#ሰው_ከቀየው_እንጂ፣
ወጥቼ ከቀሳው
ለጊዜው ታግየ
ሞትን ድል ብነሳው
መኖር አሸነፈኝ
ቤቴ ተደፍቶብኝ፣ ሁለት ወር አለፈኝ።
ተፈጥሮየ ከዳኝ፣ ፈሊጡን ቀየረ
አካሌ ሸፈተ፣ አዲስ ወግ ተማረ
ገላየ በቁሙ፣ ሳር ማብቀል ጀመረ።
እንዳልቆይ መታከት፣ እንዳልወጣ ሽብር
ሳይደከመኝ ተኝቼ
እንቅልፍ አንገቴ ላይ፣ ቀንበሩን ሳይሰብር
ካልጋ ተነስቼ
እየተደናገርሁ
እየተደናበርሁ
በምሳ ሰአቴ፣ ራት እየጋገርሁ
ኑሮ እንደ ሳር ጉንጉን፣ እያደናቀፈኝ
ሁለት ወር አለፈኝ!
ዛሬ ኮበለለ
ትላንትናን ቀድሞት፣ ባምባላይ ፈረሱ
ቀኔና ሌሊቴም፣ ሰልፍ እያፈረሱ
ይተራመሳሉ
ይርመሰመሳሉ
አርባም እድሜ ሆና
ያችን ለማሳጠር
ነፋስ በሰው ሲያድም፣ ከሞት ሲመሳጠር
ወዴትስ ይኬዳል
ሰው ከቀየው እንጂ፣ካለም ይሰደዳል?"
ወጥቼ ከቀሳው
ለጊዜው ታግየ
ሞትን ድል ብነሳው
መኖር አሸነፈኝ
ቤቴ ተደፍቶብኝ፣ ሁለት ወር አለፈኝ።
ተፈጥሮየ ከዳኝ፣ ፈሊጡን ቀየረ
አካሌ ሸፈተ፣ አዲስ ወግ ተማረ
ገላየ በቁሙ፣ ሳር ማብቀል ጀመረ።
እንዳልቆይ መታከት፣ እንዳልወጣ ሽብር
ሳይደከመኝ ተኝቼ
እንቅልፍ አንገቴ ላይ፣ ቀንበሩን ሳይሰብር
ካልጋ ተነስቼ
እየተደናገርሁ
እየተደናበርሁ
በምሳ ሰአቴ፣ ራት እየጋገርሁ
ኑሮ እንደ ሳር ጉንጉን፣ እያደናቀፈኝ
ሁለት ወር አለፈኝ!
ዛሬ ኮበለለ
ትላንትናን ቀድሞት፣ ባምባላይ ፈረሱ
ቀኔና ሌሊቴም፣ ሰልፍ እያፈረሱ
ይተራመሳሉ
ይርመሰመሳሉ
አርባም እድሜ ሆና
ያችን ለማሳጠር
ነፋስ በሰው ሲያድም፣ ከሞት ሲመሳጠር
ወዴትስ ይኬዳል
ሰው ከቀየው እንጂ፣ካለም ይሰደዳል?"