YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ባለፉት ሁለት #ሳምንት ባልሞላ ጊዜ በአድስ አበባ ውስጥ በተፈጠሩ ግጭቶች ወደ #28 ሰዎች መሞታቸዉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሜጀር ጄነራል #ደግፌ በዲ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ #ገልፀዋል

ከነዚህ ዉስጥ በፀጥታ ኃይሉ የሞቱት #ሰባት ሲሆኑ ቀሪዎቹ በድንጋይ ተደብድበው እና #በስለት ተወግተው እንደሞቱም አክለውበታል።

ሰልፍ በተካሄደ ጊዜም ወደ ሕገወጥ ተግባራት የገቡ 1, 204 ሰዎችን በቁጥጥር ሥር አድርገው ለሕንፀት ወደ ጦላይ እስር ቤት እንደተወሰዱም ኮሚሽነሩ ገልፀዋል

ከተያዙት ዉስጥ ምንም አይነት የአዲስ አበባ መታወቂያ የሌላቸዉ እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።

📌ታሳሪዎችን አስመልክቶ ሰሞኑን በማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃን «የሚናፈሱ» ያሏቸውን ጉዳዮች እዉነት አይደሉም ሲሉም አጣጥለዋል።

©DW
@yenetube @mycase27
#update አዲስ አበባ
በአዲስ አበባ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል በመጠጥ ሀይል ተገፋፍቶ በፈፀመው ጥቃት የሁለት #ባልደረቦቹን ህይወት አጠፋ
:
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ #ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል #በመጠጥ ሀይል ተገፋፍቶ በባልደረቦቹ ላይ ጥቃት መፈፀሙ ተነግሯል።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ የፌደራል ፖሊስ አባሉ በባልደረቦቹ ላይ በፈፀመው ጥቃትም ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት #ህይወት አልፏል።

ፖሊስ ጥቃቱን ለማስቆም በወሰደው እርምጃም ጥቃቱን የፈፀመው የፌደራል ፖሊስ አባል ህይወቱ ማለፉን ኮሚሽነር #ጀነራል ዘይኑ ጀማል አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅም በስፍራው ተስተጓጉሎ የነበረው የትራፊክ እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች ወደ መደበኛ ሁኔታቸው መመለሳቸውን #ገልፀዋል
ምንጭ ፦ኤፍ ቢ ሲ
@yenetube @mycase27
#የህግ ባለሙያዋ ብርቱካን ሚደቅሳ አዲስ አበባ #ገቡ፡፡

ዛሬ ጧት አዲስ አበባ የገቡት ወ/ሪት #ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሰባት ዓመት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ነው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት፡፡

ከዚህ በፊት በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ለእስር ተዳርገው ነበር፡፡
አሁንም ለፍትህ መስፈን የበኩላቸውን እንደሚወጡ #ገልፀዋል ፡፡

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ፣ ከዩናይትድ ስቴትሱ ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል ።

ወ/ሪት #ብርቱካን በፌደራል ፍርድ ቤት ዳኛ፣በሕግ ባለሞያና ጠበቃ፣ የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መስራች የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል ።
ከ97 ምርጫ በኋላ ሁለት ጊዜ የፖለቲካ እስረኛ ሆነዋል ።

ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ላደረጉት አስተዋጽኦም ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘታቸውን የዘገበው ኢቢሲ ነው ።
ምንጭ ፦ኢቢሲ
@yenetube @mycase27