በ#ሐረር ከተማ እየተስተዋለ ያለው የመጠጥ ውሃ እጦት #የህግ የበላይነት #ባለመከበሩ ምክንያት መሆኑን የሐረሪ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ቢሮ ሀላፊ አቶ ተወልደ አብዶሽ ገለጹ፡፡
ሀላፊው በሰጡት መግለጫ በኤረር ወረዳ ቂሌ አካባቢ ላይ የሚገኘው ውሃ ማሰራጫ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መቋረጡን የገለጹ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች #ከ2 አመት በፊት የተከፈለን ካሳ #በቂ አይደለም በማለት አገልግሎቱን በማቋረጣቸው ነው።
በሀሮማያ የሚገኘው የውሃ ማሰራጫም ከአገልግሎት ውጭ ሆኗል። ከመቋረጡ ቀደም ብሎ ለስራ ዕድል ፈጠራ የሚውል 10 #ሚሊየን ብር በ5 ቀናት ውስጥ ይከፈለን የሚል ደብዳቤ በሀሮማያ ኢፈባቴ ቀበሌ 01 ሊቀመንበር በኩል እንደደረሳቸው ሀላፊው ገልጸዋል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
ሀላፊው በሰጡት መግለጫ በኤረር ወረዳ ቂሌ አካባቢ ላይ የሚገኘው ውሃ ማሰራጫ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መቋረጡን የገለጹ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች #ከ2 አመት በፊት የተከፈለን ካሳ #በቂ አይደለም በማለት አገልግሎቱን በማቋረጣቸው ነው።
በሀሮማያ የሚገኘው የውሃ ማሰራጫም ከአገልግሎት ውጭ ሆኗል። ከመቋረጡ ቀደም ብሎ ለስራ ዕድል ፈጠራ የሚውል 10 #ሚሊየን ብር በ5 ቀናት ውስጥ ይከፈለን የሚል ደብዳቤ በሀሮማያ ኢፈባቴ ቀበሌ 01 ሊቀመንበር በኩል እንደደረሳቸው ሀላፊው ገልጸዋል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
#የህግ ባለሙያዋ ብርቱካን ሚደቅሳ አዲስ አበባ #ገቡ፡፡
ዛሬ ጧት አዲስ አበባ የገቡት ወ/ሪት #ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሰባት ዓመት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ነው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት፡፡
ከዚህ በፊት በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ለእስር ተዳርገው ነበር፡፡
አሁንም ለፍትህ መስፈን የበኩላቸውን እንደሚወጡ #ገልፀዋል ፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ፣ ከዩናይትድ ስቴትሱ ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል ።
ወ/ሪት #ብርቱካን በፌደራል ፍርድ ቤት ዳኛ፣በሕግ ባለሞያና ጠበቃ፣ የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መስራች የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል ።
ከ97 ምርጫ በኋላ ሁለት ጊዜ የፖለቲካ እስረኛ ሆነዋል ።
ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ላደረጉት አስተዋጽኦም ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘታቸውን የዘገበው ኢቢሲ ነው ።
ምንጭ ፦ኢቢሲ
@yenetube @mycase27
ዛሬ ጧት አዲስ አበባ የገቡት ወ/ሪት #ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሰባት ዓመት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ነው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት፡፡
ከዚህ በፊት በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ለእስር ተዳርገው ነበር፡፡
አሁንም ለፍትህ መስፈን የበኩላቸውን እንደሚወጡ #ገልፀዋል ፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ፣ ከዩናይትድ ስቴትሱ ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል ።
ወ/ሪት #ብርቱካን በፌደራል ፍርድ ቤት ዳኛ፣በሕግ ባለሞያና ጠበቃ፣ የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መስራች የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል ።
ከ97 ምርጫ በኋላ ሁለት ጊዜ የፖለቲካ እስረኛ ሆነዋል ።
ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ላደረጉት አስተዋጽኦም ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘታቸውን የዘገበው ኢቢሲ ነው ።
ምንጭ ፦ኢቢሲ
@yenetube @mycase27