YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.86K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#update ቡራዩ

#በቡራዩ ተከስቶ ከነበረው ችግር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት 630 ወጣቶች 322 #ተፈቱ

ከዚህ ቀደም በቡረዩ ተከስቶ ከነበረው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት 630 ወጣቶች ከተከሰተው ችግር ጋር ግንኙነት ያሌላቸው መሆኑ በምርመራ የተረጋገጠ 322 ወጣቶች ስልጠና ወስደው ተለቀቁ፡፡

የቡራዩ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት የምርመራ አስተባባሪ ኮማንደር በቃና ሚደግሳ እንደገለጹት፣ 322 #ወጣቶች በቡራዩና በአዳማ ስልጠና ከወሰዱ በኋላ ነው የተለቀቁት፡፡

የተቀሩት 308 ለተፈጸመው #ወንጀል ተጠርጣሪ በመሆናቸው ጉዳያቸውን በፍርድ ቤት እየተከታተሉ መሆናቸውን ኮማንደር #በቃና ገልጸዋል፡፡

በቡራዩ ተከስቶ በነበረው የጸጥታ ችግር በንብረትና በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት መድረሱ ይታወሳል፡፡

ምንጭ:- የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽ ቢሮ
@yenetube @mycase27
#update ሜቴክ

#የዓለም ገነት ቆርቆሮ ፋብሪካ እና በግንባታ ላይ ያለው ፎር ፖይንት #ሸራተን ሆቴል ባለቤት አቶ #ዓለም ፍፁም ገብረስላሴ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ግለሰቡ ራቤራ የተባለን በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኝ ሆቴልን #እጅግ በተጋነነ ዋጋ 128 ሚሊየን ብር #ከሜቴክ የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ጋር የነበራቸውን ጥሩ ግንኙነት በመጠቀም በመሸጥ ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

በተጨማሪም ሆቴሉ #በባንክ ተይዞና እዳ እያለበት የባንክ እዳውን ገዢው ሜቴክ እንዲሸፍን ተደርጎ እንደተሸጠም ነው የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የገለፀው።

የግለሰቡ የሀብት ምንጭ ህብረተሰቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ #መቆየቱ አይዘነጋም።

ሰሞኑን መንግስት በተለይም በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ውስጥ ከተፈፀመ የሙስና #ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ይታወቃል።

እነዚህም ተጠርጣሪዎች እስከ ትናንት ድረስ ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው መታየት ጀምሯል።
ምንጭ ፦ FBC
@yenetube @mycase27