#ሰበር ዜና
#የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበሩት የኢንጂነር ስመኘው በቀለን አሟሟት እና የሰኔ 16 የቦምብ ጥቃት ምርምራን በተመለከተ ሊሰጥ የነበረው ጋዜጣዊ #መግለጫ #ተሰረዘ።
#መግለጫ የተሰረዘው የፌደራል ጠቅላይ ዋና አቃቤ ህግ አቶ #ብርሃኑ ጸጋዬ አስቸኳይ ስራ ስላጋጠማቸው ነው ተብሏል።
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አንድ ባልደረባ ለዲ ደብሊው እንደተናገሩት ጠቅላይ አቃቤ ህጉ “አስቸኳይ ስራ ስላጋጠማቸው ወደ ሌላ ቦታ በመሄዳቸው መግለጫው ለሌላ ጊዜ ተላልፏል።” መግለጫው ለሌላ ጊዜ መተላለፉ ቢነገርም ቁርጥ ያለ ቀን ግን አልተነገረለትም።
#በዛሬው መግለጫ የኢንጂነር ስመኘው አሟሟት እና ከሰኔ አስራ ስድስቱ ቦምብ ፍንዳታ በተጨማሪ በሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ተገልጾ ነበር።
#ዛሬ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ሊሰጥ ታቅዶ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫው ጊዜ ሲዘዋወር የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። በነሐሴ 25 ቀን 2010 ዓ. ም. ይሰጣል ተብሎ የነበረው መግለጫ ወደ ዛሬ ጳጉሜ 1 መተላለፉ ይታወሳል።
ምንጭ ፦ DW
@YeneTube @Mycase27
#የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበሩት የኢንጂነር ስመኘው በቀለን አሟሟት እና የሰኔ 16 የቦምብ ጥቃት ምርምራን በተመለከተ ሊሰጥ የነበረው ጋዜጣዊ #መግለጫ #ተሰረዘ።
#መግለጫ የተሰረዘው የፌደራል ጠቅላይ ዋና አቃቤ ህግ አቶ #ብርሃኑ ጸጋዬ አስቸኳይ ስራ ስላጋጠማቸው ነው ተብሏል።
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አንድ ባልደረባ ለዲ ደብሊው እንደተናገሩት ጠቅላይ አቃቤ ህጉ “አስቸኳይ ስራ ስላጋጠማቸው ወደ ሌላ ቦታ በመሄዳቸው መግለጫው ለሌላ ጊዜ ተላልፏል።” መግለጫው ለሌላ ጊዜ መተላለፉ ቢነገርም ቁርጥ ያለ ቀን ግን አልተነገረለትም።
#በዛሬው መግለጫ የኢንጂነር ስመኘው አሟሟት እና ከሰኔ አስራ ስድስቱ ቦምብ ፍንዳታ በተጨማሪ በሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ተገልጾ ነበር።
#ዛሬ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ሊሰጥ ታቅዶ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫው ጊዜ ሲዘዋወር የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። በነሐሴ 25 ቀን 2010 ዓ. ም. ይሰጣል ተብሎ የነበረው መግለጫ ወደ ዛሬ ጳጉሜ 1 መተላለፉ ይታወሳል።
ምንጭ ፦ DW
@YeneTube @Mycase27
#የአርበኞች ግንቦት 7 አቀባበል ኮሚቴ አባል የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛ #ብርሃኑ ተክለያሬድን ጨምሮ በአዲስ አበባ እና በአዲስ አበባ ዙሪያ ሁከት #እንዲፈጠር ረድተዋል በሚል የተጠረጠሩ #ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ የጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮም ተፈቅዶለታል።
በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው ሰብዓዊ መብትን የሚጥስ አያያዝ እየተተገበረባቸው እንደ ሆነ ለፍርድቤቱ ተናግረዋል።
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ የሆኑት ሄኖክ አክሊሉ ደንበኞቻቸው በጨለማ እና ቀዝቃዛ ክፍል እንዲታሰሩ መደረጋቸውን፣ ከህገ-መንግስቱ በተፃራሪ ፍርድ ቤት የቀረቡት ከ48 ሰዓታት በኋላ መሆኑን እንዲሁም ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በተለይ «የአዕይምሮ ህመም አለበት» ተብሎ ከሚጠረጠር ሰው ጋር እንዲታሰር መደረጉ ለህይወቱ አስጊ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ማስረዳታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎች በተገቢው መንገድ እንዲያዙ ፖሊስን ማሳሰቡንም አክለው ነግረውናል።
ፖሊስ ተጠርጣሪዎች ሁከትን በማስተባበር እና በመፍጠር ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ ያሳያሉ ያላቸውን ሰነዶች እና የባንክ ደብተር እንዳሉት ሆኖም ተጨማሪ ማስረጃ ለማሰባሰብ ተጨማሪ ቀን ያስፈልገኛል በማለት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።
ብርሃኑ ተክለያሬድ ከዚህ ቀደም በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ በነበረው ተሳትፎ ፣ቆየት ብሎ ደግሞ «የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄን ሊቀላቀል ሞክሯል » በሚል ለእስር መዳረጉ አይዘነጋም።
📌ብርሃኑ በቅርቡ ከእስር ከተፈቱ የፖለቲካ እስረኞች መካከል አንዱ ነበር።
ምንጭ ፦ BBC
@yenetube @mycase27
ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ የጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮም ተፈቅዶለታል።
በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው ሰብዓዊ መብትን የሚጥስ አያያዝ እየተተገበረባቸው እንደ ሆነ ለፍርድቤቱ ተናግረዋል።
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ የሆኑት ሄኖክ አክሊሉ ደንበኞቻቸው በጨለማ እና ቀዝቃዛ ክፍል እንዲታሰሩ መደረጋቸውን፣ ከህገ-መንግስቱ በተፃራሪ ፍርድ ቤት የቀረቡት ከ48 ሰዓታት በኋላ መሆኑን እንዲሁም ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በተለይ «የአዕይምሮ ህመም አለበት» ተብሎ ከሚጠረጠር ሰው ጋር እንዲታሰር መደረጉ ለህይወቱ አስጊ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ማስረዳታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎች በተገቢው መንገድ እንዲያዙ ፖሊስን ማሳሰቡንም አክለው ነግረውናል።
ፖሊስ ተጠርጣሪዎች ሁከትን በማስተባበር እና በመፍጠር ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ ያሳያሉ ያላቸውን ሰነዶች እና የባንክ ደብተር እንዳሉት ሆኖም ተጨማሪ ማስረጃ ለማሰባሰብ ተጨማሪ ቀን ያስፈልገኛል በማለት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።
ብርሃኑ ተክለያሬድ ከዚህ ቀደም በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ በነበረው ተሳትፎ ፣ቆየት ብሎ ደግሞ «የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄን ሊቀላቀል ሞክሯል » በሚል ለእስር መዳረጉ አይዘነጋም።
📌ብርሃኑ በቅርቡ ከእስር ከተፈቱ የፖለቲካ እስረኞች መካከል አንዱ ነበር።
ምንጭ ፦ BBC
@yenetube @mycase27